Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
እንዴት ደስ ብሎኞል ቀዬውን ትቼው በመምጣቴ ውድ ጓደኞዬ ሆይ የሰው ልብ ምንኛ አስገራሚ ነው። ይኸን ስሜት የማይጋራ ሰዉ ቢኖር በበጋ ወራት እስኪደክመው ድረስ ተጉዞ ከእንደዚህ ያለ ምንጭ ጥሙን ያላረካ ብቻ ነውን። የዚህ ዓለምን ደስታ አንድትገበይበት ከሰማይ የተሰጣት ባል አድርጎላታል ለሷም ሆነ ለሕፃናቱ ቀኝ እጅነቱን ታጤነዋለች ይሁንና ለቨርተርም ትልቅ ግምት ትሰጠ ዋለች ከመጀመሪያው ትውውቃቸው አንስቶ የመንፈሶቻቸው ሁባሬ የሰመረ ነበር። መቸም ይህን እንዳማታረገው ለማድረግ እንደማትፈቅደውም መገንዘቧ አልቀረም ውብና ንፁህ ተፈጥሮዋ ከማንኛውም ወጥመድ ሁሉ መውጫ ዘዴ ወዲያው ሲያገኝ ለዚህ ግን መፍትሔ በማጣቱ በሐዘን ወግቶ የደስታ ኢላማዋን አሳታት ልቧን ከበደው ራዕይዋም ደመነ አሥራ ሁለት ተኩል ላይ ቨርተር ደረጃውን እየወጣ ወደሷ ሲመጣ ሰማችው ስሟን ሲጠይቅ እሱ ለመሆኑ አልተጠራጠረችም ልቧ ጮቤ ይመታ ጀመር እንዳይገባ ቢከለከል በመረጠች ነበር በሩን ሲከፍት «ቃል ገብተህልኝ ነበር ። ከእንግዲህ ብቻሽኝ በሜዳ ለሜዳ ከንቱ ነው አተልፊ። አንቺ ድንቡልቦቃ ማንፊሽ የኔ ነገር ኦሮማይ። ለተ። ልጅሽም ወዳጅሽም አፍቃሪሽም ፍፃሜው እየተቃረበ ነው ለተ ወደርየለሽ ስሜት ነው። ቃሉ ምን ማለት ነው። ባዕድ ቃል ነውባዶ ቃል ከልብ ጠብ የማይል በድን መሆን ለተ። በጠ ባቡና በቀዝቃዛው መቃብር ውስጥ መከተት። ያኔ ሕዝብ በተሰበሰበበት ስፍራ እጅ ለእጅ ለመያያዝና ቃሳት ለመለዋወጥ ያቀተን ጊዜ። እና አበባ የላክሽልኝ ጊዜ። ማለፊያ እንግዲያው እራሴን እየቀጣሁት ነው ከዚች ቅጽበት ጀምሮ የኔ ነሽ የኔ ኦ ለተ። ልቤ ውስጥ ያለውን ሁሉ እተነፍስላቸዋለሁ ለእናትሽ ለአንቺ ምስል» ሰዓት ላይ አሽከሩን አልበርት ተመልሶ እንደሆን ጠየቀው አሽከሩም ፈረሱ ሲያልፍ ስላየው ተመልሶአል አለው በዚህን ጊዜ ባልተደፈነ ኤንኮሎፕ ውስጥ ከትቶ ይህን መልእክት እንደያደርስሶት ሰጠው «እባክህ ወደጉዞስለምሔድ ሽጉጥህን አውሰኝ ደህና ሁን ከሠላምታ ጋር ለተ ያን ለሊት ችንሽ እንቅልፍ ነው የተኛች። ወይስ የጥንቱ ሠላሟ ነፃነቷ የዋህነቷና በራሷ የነበራት መተማመን ከደረሰባት ሁኔታ ጋር ሲነፃፀር። ተራርቀው የነበሩበት ወቅት አሁን አሳዘኖት ያኔ አልታወቃትም በር ሰዎች እርስ በርስ መወያየት በየበኩሉ ልክ ነኝ እያለ ሲያስብ ነገሮች ይወሳሰቡና ውሉ ይጠፋባቸዋል ድሩ አንዴ ከጠፋ መልሶ ማግኘት ያዳግታል ቆሎ ተቀራርበው በደስተኝነት ተቀራርበውቢሆን ኖሮ በመሃከላቸው መተሳሰብና መፈቃቀርተትፈጥሮ ልባቸውም ተበራይቶ የወዳጃችን የቨርተርም ደህንነት በተጠበቀ ነበር ነገሩን ያባባሰው ሌላም ጉዳይ አለ ቨርተር ከደብዳቤዎቹ እንደምንረዳው ራሱን የማጥፋት ሃሳቡን ደብቆ አያውቅም አልበርትም ስለዚህ ጉዳይ ሞግቶ ታል ከለተም ጋር አልፎ ኣልፎ ተነጋግሮበታል ለአልበርት እንኳን ሃሳቡ ይቅርና ጥቆማውም እንኳን ጠሩ ነው። በዙሪያዬ ሁሉ ነሽእናም ያገኘሁትን ሁሉ እዳላኅሳለሁ አንቺ ነክተሽው ይሆናልና ብዬ ቅድስት ሆይ። የሕይወትሽን ሐሴ ትና ሠላም ለመመለስ የሚያስችል መሆኑን ካወቅሁት ለመሞት ወኔ አያጥረኝምፎ ግና ጥቂት ክቡር ሰዎች ብቻ ናቸው ባፈሰሱት ደምና በሕይወታቸው ሕልፈት ለወዳጆቻቸው አዲስ ሕይወትና የተሻለ ዕድል ለማስ ገኘት የተቻላቸው የለበስኩትን ልብስ እንደለበስኩ መቀበር ነው ፍሳጎቴ ለተ ነክተሽዋልስለዚህም ተባርኳል ይህን ጥያቄ ለአባትሽም አቅርቤሳቸዋለሁ ሬሳዬ ሣጥን ውስጥ ሲከተት ነፍሴ ታያችኋለች ኪሴ ውስጥ ማንም ሰው እጁን እንዳይከት ይህ ሃምራዊ ሪባን ለመጀመሪያ ጊዜ ከልጆቹ ጋር ሳይሽ አስረሽው የነበረው ነው።
ሸክሙን እንደተጫነ የሚያለከልከው ጭቁን ሰው እንኳን እንደብጤቱ ፍዳውን ተቀብሎ ሲጎዳኝ ሁሉም አንዱም ሳይቀር ለደቂቃም ቢሆን መኖሩን እንደሚመኝ ፍንትው ብሎ ስለሚታየው ፀጥ ከማለት በቀር ምንም ማድረግ አይችል ከዚያም ወደ ውስ ጠቱ በመጥለቅ የራሱን ዓለም ይፈጥርና ሰው በመሆኑ ይደሰታል እንዲህ እምቅምቅ ያለ ሰው ቢሆንም የነፃነት ጣፋጭ ቃና ማለት ከዚህ ወህኒ ዓለም ባሰኘው ጊዜ ለማምለጥ እንደሚችል ግንዛቤውን በልቡ ውስጥ እንደያዘ ይቆያል ግንቦት ከድሮም ጀምሮ የምፈልገውን መኖሪያ ዓይነት ታውቀዋለህ አንድ ደርባባ ሥፍራ መለስተኛ መጠ ጊያ ካገኘሁ ሌላ ብዙ አልሻም አሁንም ልክ ይህንኑ ዓይነት ነው ያገኘሁት ከከተማው የአንድ ሰዓት ጉዞ ያህል ርቆ የሚገኝ ቫህልሃይም የሚባል ቦታ አለ ባንድ ኮረብታ ላይ ቁልብጭ ብሎ የተቀመጠ ነው ከሳይ ሆነህ ወደ መን ደሩ የሚያመራውን የእግር መንገድ በዓይንህ ስትቃኘው ከሸለቆው ባሻገር ያለውን አይታ ሁሉ ታጠቃልለዋለህ አንዲት በሰው መውደድና በፈገግታ የተመሉ አሮጊት ሁቴለኛ የወይን ጠጅ ቢራና ቡና ይሸጣሉ ከሁሉም የሚልቁት ግን ቅጠላቸውን አንዣርገው የቤተስኪያኑን ቅጥር ግቢ የሚያጠሉት ሁለት የትሩንሳጎ ዛፎች ናቸው ከቤተስኪያኑ ዙሪያ የገበሬዎች መኖሪያዎች የጓሮ አትክልቶችና ጎተራዎች ይገኛሉ ይህን የመሰለ ምቹ ሥፍራ ለማግኘት ቀላል አልነበረም ከሆቴሉ ውስጥ ትንሹን ጠረጴዛዬንና ወንበሬን አስወጥቼ ተቀምጩሃ ቡናዬን እየጠጣሁ ሆመርዬን አጣጥማለሁ ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ ከቀትር በኋላ ከነዚሀ ትሩንጎ ዛፎች ሥር ስራመድ ሳለሁ ያጋጣሚ ሆኖ አንድም ዝር የሚል ነፍስ አልነበረም። አልበርት ። ስለ ዕድሜ ባለፀጋነታቸውስንቱ በወጣትነቱ እንደሚቀጠፍእሳቸው ገና የካርልስባድን ዘፈን እየዘፈኑ ለከርሞ እዚያ አንደሚሔዱና ካለፈው ካያቻቸው ጊዜ ደሞ ዛሬ እንዴት በጣም እንደተሻሻሉና እንዳማረባቸውባይኸን ጊዜ እኔም በበኩሌ ከባለቤታ ቸው ጋር ሰላምታ ተለዋወጥኩ ሽማግሌው ደስ ተሰኝ ተው ትንሽ ያዝ እያረጋቸው ታሪካቸውን መናገር ጀመሩ «አሮጌውን ዛፍ» አሉ ሽማግሌው «ማን እንደተከለው አናውቅም አንዱ አለቃ እገሌ ነበር ይላል ሌላው ደሞ ሌላ ስም ይጠራል ያኛው ልጅ እግሩ ዛፍ ግን እድሜው ከሚስቴ ጋራ እኩል ነው ጥቅምት ሲመጣ አምሳ ኣመቱ የባለቤቴ አባት ጧት ተክለውት የዚያኑ ለት ምሽት እሷ ተወለደች የደብር እልቅናውን የተካሁዋቸው እኔ ነኝዛፉን ምን ያህል እንደሚወዱት እንደነበር ልነግርህ አልችልም እኔም ያንኑ ያህል ነው የምወደው የዛሬ ሃያ ሰባት ዓመት የቆሎ ተማሪ እንዳለሁ ለመጀመሪያ ጊዜ ደብሩን እግሬ ሲረግጠው ያሁኗ ባለቤቴ ከዛፉ ሥር ግንድ ላይ ተቀምጣ ሹራብ ስትሠራ ነበር» ለተ ሴቷ ልጃቸው የት እንደሔደች ጠየቀቻቸው እሳቸውም ከሚስተር ሸሚድት ጋር ገበሬዎቹን ለመመ ልከት ወደ ጨፌው ሔዳለች ብለው መለሱላት ከዚያም ትረካቸውን ቀጠሉ አማቻቸውና ሴት ልጃቸው እንዴት እንደወደዱዋቸውና በመጀመሪያም ግምጃ ቤትነቱን በኋላም እልቅልናውን ትተውላቸው እንዲሠሩ እንዳደረጉዋቸው አጫወቱኝ በዚህን ጊዜ ልጅቱና ሚስተር ሸሚድት የጓሮውን አትክልት አቋር ጠው ተመለሱ ከለተም ጋር የጋለ ሰላምታ ተለዋ ወጡ ለኔ የደስ ደስ ያላት በጣም መልከመልካም ብሩኔት መስላ ታየችኝለተወሰነ ጊዜ ገጠር ወጣ ሲሉ ጥሩ የምታስተናግድ ዓይነት ልጅ ሚስተር ሽሚድት ፍቅረኛዋ መሆኑ ወዲያው ግልጽ ሆነ ጨዋ ሰው ነው ግን ዝምተኛ። ሰው ማለት ሕፃን ማለት ። ውድ ዊልሄልም ሊያጫት ያቀደው ሰው እኮ ነው እዚሁ ያለው። » «ለምን ይሆን። » ሲል ጮኸ አልበርት «ይኸን ያህል ወላፈንዲ አይምሰልህ» አልኩት ስመልስለት «አንድ በሽታ አካላችንን በጣም ሲያጠቃውና የመከላከያ አቅማችንን ሲያደክመው መልሰን ጤናችንን ለመገንባትና ኖርማል ሕይወታችንን ለመምራት ሲያቅተን ለሞት የሚያበቃ በሽታ ብለን እንጠራዋለን ይኸን አባባል ወዳጄ ሆይ እስቲ ስለመንፈስ እናድርገው አንድ አቅሙ የተወሰነ በእይታዎቹ የታጠረ በሃሳቡ የተወናበደ ሰው ለምሣሌ አንውሰድ ይኖር ይኖርና አንድ ቀን በግልፍት ትዕ ግሥቱን ያጣና ራሱን ከማውደም አዘቅት ይወድቃል ይኸን ያልታደለ ፍጡር አእምሮው የተስተካከለ ሰው አጢኖት ልምከርህ ቢለው ከንቱ ነው ልክ ጤናማ ሰው ለአንድ በሽተኛ አልጋው አጠገብ ቆሞ ከጤንነቱ ትንሽ ላካፍለው እንደሚል አይነት ነው ለአልበርት ይኸም አልተዋጠለት በቅርቡ ወንዝ ውስጥ ሰምጣ ስለተገኘችው ልጃገረድ ታሪክ አስታወስኩት «በቤተሰብ ክልል ውስጥ የዕለትና የሣምንት ተግባሯን እያከናወነች ያደገች ወጣት ነበረች በየሣምንቱ እሁድ እሁድ የክት ልብሷን ለብሳ ቤተስኪያን ከመሣምና ከጓደኞቿ ጋራ ሽርሸር ከመውጣት ሌላ የምተውቀው ደስታ አልነበራትም በየአውደ ዓመቱም ጭፈራ መሄድና አንዳንዴም ከጎረቤት ጋራ ስለሆነ ነገር ወይም አሉቧልታ መጨዋወት ነበር ሥራዋ ቀስ በቀስ እንደ ፍም የተዳፈነ ተፈጥሮዋ ውሰጧ የተቀበረ ፍላጎቷን ይቆሰቁሰው ጀመር የጎረምሶቹ ቁልምጫ አባባሰው ከዚየም የድሮ ባህርይዋን እየተወችው መጣች አንድ ቀን ለአንድ ወንድ የማታቀው ስሜትአድሮባት ልቧ ወደሱ እጅጉን ተሳበ ተስፋዋን ሁሉ ባሱ አደረገች ዙሪያ ዓለሙን ረስታ ከሱ በቀር ሌላ ኣልታያት አለ አልሰማት አለ ናፍቆቷ እሱና እሱ ብቻ ሆነ አድሮባት ልቧ ወደሱ እጅጉን ተሳበ። «ወዳጄ ሆይ ። ዊልሄልም ሆይ። ደህና ሁን። ይኸን ትዕይንት ቀደም ሲል በጻፈኩልህ ደብዳቤ የገለፅኩት ይመስለኛልረጃጅሞቹ የአርዘ ሊባኖስ ዛፎች ይከቡሃል የተቸመቸሙት ቁጥቋጦዎች ጐዳናውን ያጠሉታል በመጨረሻም የታጠ ረችው አደባባይ የብቸኛነት ልብሰቀላን ትለግስሃለች አንድ ዕለት በቀትር ፀሐይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባ ባይዋ ውስጥ ቆሜ የተሰማኝ የስጋት ስሜት አሁንም ይጎበኘኛል ይህ ቦታ ወደ ሐሴት ወይም ወደ ሕመም ትዕይንትነት እንደሚለወጥ ደመነፍሴ ያኔ በለሆሳስ ጠቁሞኛል ግማሽ ሰዓት ያህል ስለመሰነባበት ጣፋጭ ትካዜ ሳስብ ቆይቼ መለስ ስል ከወደቴራሱ ሲመጡ ሰማሁዋቸውና ልቀበላቸው ሮጥሁ እየተንቀጠቀጥሁ እጂን ያዝኩትና ሳምሁት ቴራሱ ላይ እንደደረስን በዛፍ ከተሸፈነው ኮረብታ ላይ ጨረቃዋ ብቅ አለች ስለ ማኔህማኔሁ እያወራን ሳይታወቀን ሀዘን ቀስቃጂ የበጋ ጎጆ ዘንድ ደረስን አልበርትም አኔም በጎኗ ተቀመጥን እኔ ግን ወዲያው ተነስቼ እቁነጠነጥ ጀመር አደብ አጣሁ ከአርዘሊባኖሶች ባሻገርና በቴራሱ ላይ የፈሰሰውን የጨረቃ ብርሃን ልብ እንድንለው ለተ አሳሰበችን ግርማ የተመላ ሌሊት ነበር ዙሪያችንን ጠልቆ የከበበው ድብዝዝ ማለትም ይበልጥ አግዝፎታል በዝምታ ከቆየን በኋላ እንዲህ ስትል ተናገረች «በጨረቃ ብርሃን በምጓዝበት ጊዜ በሞት የተለዩኝ የማፈቅራቸው ሰዎች ትዝታ የመሞትንና የትንቢቱን ምፅአት ስሜት ይቀሰቅስብኛል ከሞትን በኋላ ሕይወት ይኖረናል ቨርተር» አለችኝ በጥልቅ ስሜት ተመልታ «ግን እዚያ እንገናኝ ይሆን። ደህና ሁን አልበርት። በራዕዩ ሁሉን አቀፍ የሆነውና በሌሎች ችሎታና አቅም የግሉን እቅድ ለማስፈፀም ሥልጣንና ብልሃት ያለው ብቻ ነው ጥር ውድ ለተ ሆይ ውጪ በረዶ ቀላቅሎ ከሚጥለው ዶፍ ተጠልዬ ከምገኝበት ትንሽ የገጠር ሆቴል ማረፊያ ውስጥ ሆኘ እንድጽፍልሽ ተገደድሁ በዲ እስከነበርሁበት ጊዜ ድረስ በዚያ የችግር ጉሮኖ ከነዚያ ከማይጥሙኝ ባይተዋር ሰዎች ጋር ሆዬ ምንም ልቤ እንድጽፍልሽ ቢዳዳው ምንም ጊዜ አንዲት ፋታ እንኳን አላገኘሁም ነበርነፁ ታዲያ አሁን እዚህች ጎጆ ውስጥ ከሰው ተለይቼና ጭርር ብሎብኝ ከውጪ በረዶው ትንሺን መስኮት እየቀጠቀጠ ሳለ ሃሳቤ መጀመሪያ ወደ አንቺ ገሠገሠ ገና በሩን ስገባ ቅርፅሽ ፊቴ ድቅን አለብኝነ እና ትዝታሽም ቡርክትና ፈዋሽ ትዝታሽ። አልበርት አለ። ከናንተ ጋር እንዳለሁ ያስመስለኛል ውድ አልበርት ሆይ ያንተም ሥፍራ ካለበት ልብ ውስጥ አልተነቃነቀም በእርግጥም አኔ ሁለተኛውን ስፍራ እይዛለሁሀእዚያም እንድቆይ እልጋለሁመቆየትም አለብኝ እሷ የምትረሳኝ ከሆነ አብዳለሁአልበርት ሆይ ይኸን ማሰቡ እንኳን እንደ ገሃነም ይፈጀኛል አልበርት ደህና ሁን ደህና አንቺም የሰማይ መልአክ ለተብርሃን ደህና ሁፒደህና ። ሐምሌ ሀ የለም ደህና ነው። የልቡ ትርታ ከሷ የልብ ትርታ ጋር አይገጥምም እሽአንድ ከምንወደው መጽሐፍ ውስጥ አንድ ጥቅስ በምናነብበት ጊዜ እንኳ የኔ ትርታ ከሷ ትርታ ጋር አብረው ይደልቃሉ ሌላም መቶ ጊዜ ይሆናል ስለሌላ ሦስተኛ ሰው ስናወራ አስተያየታችን አንድ የሚሆነው ውድ ዊልሄልም ሆይ። ወዳጄ ሆይ። ለምን ያህል ጊዜ። » አለችኝ ውድ ቨርተር ። ታህሣስ ዊልሄልም ሆይ። የልቡ ስጋትም ቀሪ አእምሮአዊ ኃይሉን ቦረቦረውብርታቱንና ሩቅ አስተዋይነቱንም ሀዘን ጓዱ ሆነ መከፋቱ የማያቋርጥ ሆነ አንደ ሀዘኑ መጠን እንግዲህ የአልበርት ጓደኞች የሚሉት ይኸንን ነው ቨርተር ቀኑን ሙሉ ሲባክን ይውልና ምሽት ላይ ሔዶ ይዘረራል አልበርትን የመሰለ ዝምተኛና ልበንንፁህ ሰው ቨርተር ሊያጤን አኣልተቻለውም አልበርት ለብዙ ጊዜ ሲመኝ የነበረውን ደስታ አግኝቶ በማጣጣም ላይ ያለና ይህም ደስታ ፀንቶ እንዲቆይለት የሚጥር ታታሪ ሰው ነው አልበርት ይላሉ ጓደኞቹ ቨርተር ከሚያውቀው ከጥንቱ ጠባዩ አልተቀየረም ያው እንደቀድሞው አክብሮት የሚገባው ሰው ነው ከሁሉም አስበልጦ ለተን ያፈቅራ ታል ይኮራባታል እና ሌላውም ሰው ሁሉ ይኸን እንዲገነዘብለት ይፈልጋል ቅንጣትም ጥርጣሬ እንዳይፈጠርበት ቢጥር ይፈረድበታል እንዴ። ለሁሉም ከዚያን ጊዜ ወዲህ ቨርተርን አንስቶት አያውቅም አሷም ብታነሳለት ወይ ወሬ ይለውጣል ወይ መልስ አይሠጣትም የሰውየውን ነፍስ ለማዳን ያደረገው ጥረት ቡግ ብሎ እንደ ከሰመ ነበልባል ሆነበት ለቨርተር ከዚያ ወደ ፍፁም ሥሪአልባና የሕመም ስሜት ተቀየረበት ለም ስክርነት እንዲያውም ትጠራ ይሆናል መባሉን ሲሰማ የሚይዝ የሚጨብጠው ጠፋው በዚህን ጊዜ ደሞ አስረኛው ሁሉን ነገር መካድ ጀምሮ ነበር አሉ በሥራ ላይ በተሠማራበት ጊዜ ያጋጠመውን መጥፎ ነገር ሁሉ ካምባሳደሩ ጋር ያሳለፈውን አስፈሪ ወቅት በአጠቃላይ ሽንፈቱንና ውድቀቱን ሁሉ እያነሳ ያሰላስል ጀመር ሁሉም ነገር ተግባሩን በሚገባ ካለመከ ታተልና ካለማከናወን የመነጨ መሰለው ከተስፋው የተቆራረጠ ከየዕፅለቱ ጥሪና ተልአኮው የተለያየና ለሚነዘንዘው እሾቱ ብቻ የተጋለጠ ሆነ የዚያችን ተወዳጅ ፍጡር የአእምሮ ሠላም ቅር በሚያሰኝ ግንኙነት እየበከለ በዓላማ ቢስነትና በፋይዳ ቢስነት ወደ ድቀታዊ ፍፃሜው ተቃረበ የሃሳቡ ድብልቅልቅነት የሚያቃጥለው ፍቅሩ የማያቋርጠው ጥረቱና ግረቱ እንዲሁም የሕይወቱ ችክታ ከዚህ በታች በሚቀርቡት ጥቂት ቀሪ ጽሑፎች ፍንትው ብለው ይታያሉ ታህሣስ ውድ ዊልሄልም ሆይ ሁናቴዬ በክፉ ዛር እንደተያዙ ሰዎች ዓይነት ነው አንዳንዴ በመዳፉ ውስጥ ያገባኛል በምኞት ወይም በፍርሃት ቀለበት ውስጥ አይደለም በባይተዋር ውስጣዊ እንፋሎት እንጅ ጉሮሮዬን በሚተናነቅና ልቤን ሊሰነጥቀው በሚቃጣ እንፋሉት ውስጥ እንጅ ወዮው ለኔ። ውድ ጓዴ ሆይ። » «ለምን እኮ። የሌላ ሰው ነኝስለዚህ ለምን እኔን ብቻ። » በዚህ ወቅት የለተ ሃሳብ ያተኮረው በንድ ነገር ላይ ብቻ ነበር ከመጨረሻው ንግግራቸው በኋላ ከሱ ለመለየት የቱን ያህል እንደሚያስቸግራትና እሱም ከሷ መለየቱ ምን ያህል እንደሚያሳምመው ተሰምቷታል አልበርት ከነሱ ጋር በነበረበት ጊዜ ቨርተር ከገና ዋዜማ በፊት እንደማይመጣ ሲነገረው ሰምቷል ስለዚህ ለአንድ ሥራ ጉዳይ ባካባቢው ወደሚገኝ ባለሥልጣን ዘንድ አልበርት ሔዶ እዚያው አድሮአል ለተ ብቻዋን ተቀምጣ ስለምታፈቅራቸው ሰዎች ትተክዝ ነበር ከአንግዲህ ከአልበርት ጋር ለዝንተ ዓለም ተቆራኝታለች ጥሩ አድርጋ አውቀዋ ለች። ለተ። ለተ ኖ። አልበርት። በሩ ሲንጓጓ ነቅታ ለተ ክው ብላ ቀረችሱ አልበርትን ቀሰቀሰችውና ተነሱ አሽከርየው እያለቀሰ ያየውን ነገራቸው ለተ ጉልበቷ ከድቷት ባሏ እግር ስር ዘፍ አለች ኃኪሙ ደረሰ ምስኪኑ ቨርተር የመትረፍ ተስፋ እንደሌለው ተረዳ የልቡ ትርታ ይመታል ግን እጆቹ በድን ሆነዋል ከቀኝ ዓይኑ በላይ ጥይቷ ገብታ ጭንቅላቱን በጥርቀዋለች በተጨማሪም አንድ እጁ ላይ የደም ስሩ ተበጥቶ ደሙ ይፈሳል እስትንፋሱ ግን አለ የወንበሩ ዣዥርባ ደም ስለነካው የተኮሰው ተቀምጦ እንደነበር መገመት ይቻላል ከዚያም ወድቆ ወለሉ ላይ ተንፈራግጧል ኋላም መስኮቱ አጠገብ በጀርባው ተንጋልሏል ሙሉ ልብሱን ሰማያዊ ኮቱን ከነሠደሪያው ለብሷል ቦቱንም እንዳጠለቀ ነው የቤቱ ነዋሪ ጎረቤቱ የከተማው ሰው ሁሉ ሲተረማመስ አልበርት ገባ ቨርተርን አልጋው ላይ አድርገውታል ራሱንም በፋሻ አስረውታል ከፊቱ ላይ ደሙ ተሟጥጧል ምኑም አይነቃነቅም የማጓራት ድምፅ ከሳምባው ብቅ ጥልቅ ይላልበቅርቡ ሕልፈቱ ይጠ በቃል ከወይን ጠጁ ጠርሙስ አንድ ብርጭቆ ብቻ ነበር የጠ ጣለት «ረኢሚሊያ ጋሎቲ» የተሰኘው የሌሲንግ ተውኔት ተገልጦ በጠረጴዛው ላይ ነበረ ስለ አልበርት ክውታና ስለ ለተ ጭንቀት ምንም አልናገርም የለተ አባት ወሬውን እንደሰሙ ሮጠው ደረሱ ሟቹንም ሳሙትና እንባቸውን አፈሰሱ ትላልቆቹ ልጆቻቸውም ወዲያውኑ መጡ ዙሪያውንም እየከበቡትና እጆቹን እየሳሙት አለቀሱፎ ከሁሉም በላይ የሚያፈቅረው የሁሉም ታላቅ የሆነው ልጅ ሕይወቱ እስካለፈ ድረስ ጉንጩን እየሳመው ነበር ከዚያም በግድ አላቅቀውት ከክፍሉ አስወጡት እኩለ ቀን ላይ ሕይወቱ አለፈች የለተ አባት በመገኘታቸው ምንም ችግር አልተፈጠ ረም ከምሽቱ ሰዓት ሲሆን እመረጠበት ስፍራ አስወስደው አስቀበሩት ሽማግሌውና ልጆቻቸው ሬሳውን ተከተሉት አልበርት ግን አልቻለም ለተ ሕይወቷን ያሰጋታል ሲባል ነበር አጃቢዎቹ የመቃብር ቆፋሪዎቹ ብቻ ነበሩ ፍታትም አልነበረውም።