Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convertir en PDF
  • Liste de lecture
  • Abrégé
  • Livre audio
  • Chercher
  • Télécharger
  • myzon
  • S'identifier
  • registre
English  አማርኛ  Français  العربية
Livre du jour

የጣሊያን ውዽቀት.pdf


  • word cloud

የጣሊያን ውዽቀት.pdf
  • Extraction Summary

ዐዐ«ፈሰዕነሀ ፖ ጄኔራል ናዚም ያለውን ሃይል ሁሉ አስተባብሮ እንደተለመደው አካባቢውን በፀረ ሰው እና በፀረ ተሽከርካሪ ፈንጅ አጥሮ የመጨረሻውን ፊልሚያ ለማድረግ ተዘጋጅቶ ይጠብቅ ነበር በመጨረሻም የጎንደር ከተማ ከተከበበች በኋላ ህዳር አስራ ቋ ቀን ሀወ ዓም ከጠዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ጦርነቱ ተጀመረ የእንግሊዝ እና የጠላት መድፎች ሰማይና ምድሩን ያናውጡት ጀመር የእንግሊዝ የጦር አውሮፕላኖች ከዳባት በመነሳት የናዚን የጦር ሰፈር በቦንብ ይቀጠቅጡት ጀመር ።

  • Cosine Similarity

በገዐዐ«ጸፈቋሰሪዕነሀ የጎንደር ጦርነት የአርበኞች ድል የፋሽስት ኢጣልያ የመጨረሻ ውድቀት ወራሪው የፋሽስት ጣሊያን ጦር በጀግኖች አርበኞች ተጋድሎና በእንግሊዝ ረዳትነት ሚያዝያ ቀን ቋጀሆ ዓም ድል ሆኖ አዲስ አበባን ከለቀቀ በኋላ የተቀረው የጠላት ጦር የምስራቅ አፍሪካ የኢጣሊያ ጦር የበላይ አዛዥ በሆነው በዱክ ዳዎስታ አመራር ስር ደሴ ላይ መሽጎ ሲጠባበቅ የቀረው ጦር እንዲሁ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ጦር አዛዥ በሆነው በጄኔራል ናዚ አመራር ጎንደር ላይ መሽጎ የሙሶሎኒን እርዳታ ይጠባበቅ ነበር ይሁንና ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በድል አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ አርበኛው እንደቀደመው ከእንግሊዝ ጦር ጋር በመተባበር የጠላትን ጦር እየደመሰሰ አዲስ አበባ በድል አንደገባ ሁሉ አሁንም በየፃገሩ መሽጎ የተቀመጠውን የጠላት ጦር ከእንግሊዝ ጦር ጋር በመተባበር እንዲደመስስ በሰጡት ትአዛዝ መሠረት በተለይም በደሴ እና በጎንደር መሽጎ የተቀመጠውን የዱክ ዳዎስታንና የጀነራል ናዚን ጦር እንዲደመስሱ ከግርማዊነታቸው የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተቀብለው ደጃዝማች ኃብተሥላሴ በላይነህ አርበኞቻቸውን ይዘው ወደ ይ ደጃዝማች ኃብተሥላሴ በላይነህ አባ ጉራች በመጀመሪያም እነ ደጃዝማች ኪዳነወልድን ፊታውራሪ ከበደ ካሣን አንዲሁም ሌሎች የጦር አለቆችን በማስከተል የዱክ ዳምስታን ጦር ለመደምሰስ ከሸዋ ተነስተው ወደ ደሴ ጉዚቸውን ቀጠሉ። ዐዐ«ፈሰዕነሀ ፖ ጄኔራል ናዚ ጎንደር ላይ አርባ ሺህ የሚገመተውን ሰራዊቱን ሰብስቦ የጎንደርን ዙርያ በከፍተኛ ፀረ ተሽከርካሪና እና ፀረ ሰው ፈንጂ በመድፍና በመትረየስ አጥሮ እንዲሁም በከፍተኛ ሜካናይዝድ ጦር ምሽጉን አጠናክሮ ሂትለር የተባበሩትን የጦር ቃል ኪዳን አባል ሃገራትን እያሸነፈ እንደሆነና በቅርቡም ለነርሱ አርዳታ እንደሚደርሳቸው የሓሰት ፕሮፕጋንዳ ለወታደሮቹ በመንዛት ጠንክረው እንዲዋጉ ያበረታታ ነበር ሙሶሎኒም የዱክ ዳዎስታን መማረክ እንደሰማ የምስራቅ አፍሪካ የኢጣሊያ ጦር የበላይ አዛዥ አድርጎ ሾመው የሚወስደውን ቁልቋል በር የተባለውን የጠላት ምሽግ ለማስለቀቅ የእንግሊዝ ወታደሮችና አርበኞች በመተባበር ጥቃት ሰነዝሩ ይሁንና ጥቃቱ በጥንቃቂ የተጠና ባለመሆኑ የእንግሊዝ ወታደሮችና አርበኞች በጠላት ዒላማ ውስጥ በመግባታቸው ከፍተኛ ዕልቂት ሆነ ብዙ ጀግኖች አርበኞችም ሰውነታቸው በፈንጅ እየተበጣጠሰ ወደቁ የእንግሊዝ የጦር አውሮፕላኖች ያደረጉትም የአየር ደብድባ ውጤት ባለማምጣቱ ጦሩ እንዲያፈገፍግ ተደርጎ ሌላ በቂ ዝግጅት ተደርጎ ከሳምንት በኋላ ጥቃት እንዲጀመር ተወሰነ የፋሽስት ኢጣሊያ ታንክ ጎንደር ላይ መሽገው ሲጠባበቁ በዚህ ጊዚያዊ ድል ከፍተኛ ደስታ የተሰማው ጄኔራል ናዚ እንደቀደመው ሁሉ በአውሮፕላን የፕሮፕጋንዳ ወረቀት በመበተን የማይደፈር መሆኑን ለማሳየት ጣረ በዚህ ጥቃት አለመሳካትና የወንድሞቻቸው ዕልቂት የተበሳጩት ደጃዝማች ኃብተሥላሴ እና ሌሎችም የጦር አዛፐች ለሚቀጥለው ጥቃት የራሳቸውን ዕቅድ በማውጣት ሲዘጋጁ ቁዩ ጥቃቱም እንደተባለው ካንድ ሳምንት በላ ህዳር ቀን ሀፀ ዓም ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ተጀመረ ከሁለቱም ወገን ቀዝቅዝ ያለ የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ ከቆየ በኋላ ከቀኑ አምስት ሰዓት ሲሆን የአንግሊዝ መድፎች ምሽጉን በሃይል በመደብደባቸው በዚህ ማህል ፋታ ያገኙት አርበኞች በድንገት ወደ ምሽጉ ክልል በመግባት የታጠረውን ሽቦ እየቆረጡ በተጠመደው ፈንጂ ላይ አንዱ ባንዱ ላይ አየተረማመዱ የእጅ ቦንባቸውን በመንቀል በደረታቸው እየተሳቡ ወደ ጠላት ምሽግ በመግባት ያርበደብዱት ጀመር ከዚያም ፍርቃ በር የተባለውን ምሽግ ተቆጣጥረው ግስጋሴያቸውን በመቀጠል የቁልቋል በር ምሽግን ተቆጣጠሩት የምሽሸጉንም መሰበር ያየው የኢጣሊያኑ ጦር አዛዥ ኮሎኔል አጎሊኒ ነጭ ባንዲራ በማውለብለብ እጅ በመስጠቱ ጦርነቱ ወደ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ተጠናቀቀ ለዚሁም ድል ጄኔራል ፎክስ ለደጃዝማች ኃብተሥላሴ ያለውን አድናቆት ገልፆላቸዋል ይሁን አንጂ ጄኔራል ዊልያም ፕላት ወደ ፃገሩ ተመልሶ ለእንግሊዝ መንግስት ስለጦርነቱ ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ስለ ኢትዮጵውያትኑ አርበኞች አንድም ያለው ነገር አልነበረም ይህንኑም ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ኢትዮጵያ እና የህይወቴ እርምጃ በተባለው መጽሃፋቸው « አርበኞቻችን ያገኙትን ድል ሁሉ እንግሊዞች የነሱ እንደሆነ አድርገው ይገልፁ ነበር »ብለው ፅፈውታል ከዚህ በኋላ ወደ ጎንደር ከተማ የሚወስደው በር ስለተከፈተ ሠራዊቱ ተጉዞ አዘዞ ሰፈረ ጄኔራል ናዚም ያለውን ሃይል ሁሉ አስተባብሮ እንደተለመደው አካባቢውን በፀረ ሰው እና በፀረ ተሽከርካሪ ፈንጅ አጥሮ የመጨረሻውን ፊልሚያ ለማድረግ ተዘጋጅቶ ይጠብቅ ነበር በመጨረሻም የጎንደር ከተማ በየአቅጣጫው ተከበበች በጠዳ በፈንጠር እና አዘዞ ደጃዝማች ኃብተሥላሴ በላይነህ ደጃዝማች ኪዳኔ ወመድህን ፊታውራሪ ከበደ ካሳ ፊታውራሪ ተሰማ ዕርገጤ እና ሌሎችም በእንግሊዝ ጦር በኩል ጄኔራል ቻርለስ ፎክስጄኔራል ዊሊያም ፕላት እና ሜጀር ዳግላስ በሰቀልት በልደታ ደጃዝማች በዛብህ በለው ደጃዝማች ካሣ መሸሻ ደጃዝማች ከበደ ወንድም አገኝ እና ሌሉችም በቁስቋም ደጃዝማች ብሬ ዘገየ ደጃዝማች ጀንበሩ ብሩደጃዝማች ጫኔ የመረጡ አና ሌሎችም በዚህ ሁኔታ የጎንደር ከተማ ከተከበበች በኋላ ህዳር አስራ ቋ ቀን ሀወ ዓም ከጠዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ጦርነቱ ተጀመረ የእንግሊዝ እና የጠላት መድፎች ሰማይና ምድሩን ያናውጡት ጀመር የእንግሊዝ የጦር አውሮፕላኖች ከዳባት በመነሳት የናዚን የጦር ሰፈር በቦንብ ይቀጠቅጡት ጀመር ። እንግሊዞችም በምሽጉ ውስጥ የሚገኘውን በጊዜው ለኢትዮጵያ ፃዛገር መከላከያ ማደራጃ ሊጠቅም ይችል የነበረን በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመተውን የጦር መሳሪያ ታንክመድፍ የጦር ተሽከርካሪ ወዘተ ወደ ኤርትራ አጓጓዙት በግራ በኩል የሚታዩት ደጃዝማች ኃብተሥላሴ በላይነህ ጎንደር የጄኔራል ናዚን ጦር ድል አድርገው አዘዞ ከእንግሊዝ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጸጳጄኔራል ፎክስ ጄኔራል ዊዝሮል ጄኔራል ጀምስ ፀሜጀር ዳግላስ ከወዳጃቸው ከካፒቴን ዴርክ ጋር የተነሱት ፎቶግራፍ ነው ከዚህ በኋላ ጄኔራል ፎክስ ለማስተዛዘኛ በሚመስል መልኩ አራት መቶ ሽህ ብር ለደጃዝማች ኃብተሥላሴ ሰጥቷቸው ላርበኞቻቸው አከፋፍለውታል ከዚህ በኋላ ልዑል አልጋ ወራሽ ጎንደር መጥተው ስለነበር አርሳቸውን ተቀብለው ከርሳቸው ጋር ከቆዩ በጊላ ከነሠራዊታቸው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰው የካቲት ቀን ዘቋወ ዓም በታላቅ ሰልፍና ሥነ ሥርዓት ስድስት ዓመት ከተለዩዋቸው ንጉሠ ነገሥታችው ፊት ቀርበው ቆርጠጥ ቆርጠጥ ጎርደድ ጎርደድ አንዳንዴም በርከክ እያሉ በጊዜው ባንዲራችን የተባለው ጋዜጣ እንደፃፈው ኃብቴ ኃብተ ሥላሴ ነብስ አሰናባች እንደ ሥላሴ የጠቅል አሽከር የንጉስ ተፈሪ ለሃይማኖቱ ተከራካሪ ጄኔራል ገዳይ ኒሻን ያሠረ ማጆር ማራኪ የተከበረ ያንተ አሽከር ያንተ ወታደር በዘመተበት የማያሳፍር ዘው ዘው ባይ ከጦሩ ማህል ጄኔራል ናዚ አቤት አቤት ሲል እያሉ ይህንንና ይህን የመሳሰለውን የፉከራ ቃል እየተናገሩ ከማይጨው ጀምረው እስካሁን ድረስ የሠሩትን ጀብዱ ሲቆጥሩ እንኳን ከዚህ በፊት ሥራ የሰራውን ቀርቶ ያልሰራውንም ዘራፍ ለገናው ለማለት ወኔውን ይቀሰቅሰው ነበር ፎቶግራፍ ነው ከዚህ በኋላ የማረኳቸውን ከባድና ቀላል መትረየሶች በማበርከት ያደረጓቸውን አግልግሎቶች ጠቅሰው «እፄ አገልጋይም እንኩዋን አይነዎን አይቼ ከፊትዎ ቀርቤ ድካሜንና ሙያዬን ተናገርኩ እንጂ እንግዲህ እኔ ይህንን አድል ካገኘሁ በኋላ አውነተኛ ባሪያዎ ነኝና ምንም አላሳስብም ብለው ቢናገሩ» ግርማዊ ጃንሆይ «ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ከመውደዱ የተነሣ እንግዲህ እናንተ ጌቶች ናችሁ እንጂ ባሮች አይደላችሁም አንዳላቸው ተወዳጅ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም ሥራህም በማንም አፍ የተመሰገነ ነው»ብለው ሞገሳዊ ቃል ሰጥተዋቸዋልረባንዲራችን ጋዜጣ ኛ ዓመት ቁጥር ወሀ የካቲት ቿቷ ቀን ሀቋ ዓም ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የካቲት ቀን ሀቋ የጀግኖች አርበኞቻቸውን ሰልፍና ፉከራ ሲመለከቱ ደጃዝማች ኃብተሥላሴ በላይነህ በመጋቢት ወር ሀ ዓም ማይጨው ላይ በተደረገው ታላቁ ጦርነት ከክብር ዘበኞች ጋደኞቻቸው ጋር ሆነው ከፍ ባለ ጀግንነት ከጠላት ጋር በመዋጋት አገራቸውንና ንጉሠ ነገሥታቸውን አገልግለዋል ከዚያም እንደተመለሱ በንጉሠ ነግሥታቸው መሪ ትዕዛዝ መሠረት የጦርነት ትግላቸውን በሰሜን ሸዋ በመቀጠል አምስት ዓመት ሙሉ በአርበኝነት የጦር መሪ በመሆን እጆግ ከፍ ባለ ጀግንነት ሌት ከቀን ያለ አንዳች አረፍት በየጦር ሜዳው የጠላትን ኃይል ያንበረከኩ ታላቅ ጀግና ነበሩ የገደሏቸውንም የጠላት መኮንኖች ለመጥቀስ ያህል በተቃጠሉ ጊዜ የጦር መሪ የነበሩት አርበኞች ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህና ፊታውራሪ ጂማ ሰንበቴ ነበሩ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Commentaires:


memezon

Options de téléchargement | Convertir en PDF | Livre du jour

© dirzon | Conditions d'utilisation | Intimité | Sur | Services | Contact