Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የታክስ ሥልጣን ክፍፍል ሥርዓት የተለየ ነው። በአሁኑ ጊዜ የፌዴራል መንግስት የጋራ የተባሉ ታክሶችን መጣሉና መሰብሰቡ ሕገመንግስታዊ ነው። የገቢውን መሰረት ታክስ ከፋዩ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከመድረሱ ባሉት ሰላሳ ቀናት ውሰጥ የሚፈለግበትን ታክስ ካልከፈለ ወይም ። ለግብር ይግባኝ ጉባዔ በሰጠው ውሳኔ ላይ ሕጉ በሚያዘው የጊዜ ገደብ ውስጥ ይግባኝ ካላቀረበ ወይም ።
ፍያጨፍክር ሀ ሸ ር በማለት ይገልጸዋል ትርጉሙም በጭሩታክስ ማለት መንግስት ለጠቅላላው ህብረተሰብ ጥቅም የሚያደርጋቸውን ወጪዎች ለመሸፈን እንዲችል ማንኛውም ታክስ ከፋይ በተለይ በግል የልዩ ጥቅም ጥያቄ ሳያነሳ መክፈል ያለበት በሕግ የተጣለ የግዴታ ክፍያ ነው ከዚህ ትርጉም መረዳት አንደሜቻለው ታክስ በሕግ የተጣለ ግዴታ ነው ይህ በመሆኑ ታክስ መክፈል በገዛ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን አስገዳጅነት ባህሪ ያለው ነው ታክስ እንዲከፈል ግዴታ አለመወጣት የወንጀል ተጠያቂነት ያስከትላል ታክስ የሚጣለው በመንግስት ነው ማንም ሰው ታክስ የመጣል መብት የለውም የመንግስት ብቻ ነው ታክስ የመጣልና መሰብሰብ ህጋዊ መብት ያለው ታክስ የሚከፈለው በታክስ ከፋይ ነው ታክስ ከፋዩ የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ሊሆን ይችላል ታክስ የሚጣለውና የሚሰበሰበው ለጠቅላላው ሕብረተሰብ ጥቅም ነው ስለዚህ መንግስት በሚያወጣው ወጪ ተጠቃሚ የሚሆነው ታክስ ከፋዩ ብቻ ሳይሆን ታክስ ከፋይ ያልሆነውም ሊሆን ይችላል ታክስ ከፋዩም ለከፈለው ታክስ ከመንግስት በቀጥታ በግሉ ልዩ ጥቅም የመጠየቅ መብት የለውም ማለትም በሚከፈለው ታክስ እና መንግስት በሚሰጠው አገልግሎት መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት የለም ስለዚህ አንድ ሰው ታክስ የሚከፍለው ከመንግስት ቀጥተኛ እና እኩል የሆነ ጥቅም ስለሚያገኝ ሳይሆን መንግስት ለሚያከናውናቸው ተግባሮች እገዛ የማድረግ ግዴታ ጭምር ስላለበት ነው አላማ መንግስት ታክስን የሚጥለውና የሚሰበስበው የተለያዩ አላማዎች ለማስፈፀም ነው ጥቂቶቹም ገቢን ለመፍጠር መንግስት ለጠቅላላው ሕብረተሰብ ጥቅም የሚያደርጋቸውን ወጪዎች ለመሸፈን የሚያስችለው ገቢ ያስፈልገዋል ለዚህ ደግሞ አንዱ የገቢ ምንጭ ታክስ ነው የታክስ ዋና አላማም የመንግስት ገቢን መፍጠር ነው የገቢ እና የሐብት ልዩነትን መቀነስ በሐብታምና በደሀ መካካል ያለውን ልዩነትን ለማጥበብ ብዙ መንግስታት አየጨመረ የሚሔደው የታክስ ሥርዓት ዐርሀፌ ኪ ሃጪ ተግባራዊ ያደርጋሉ በዚህ አይነቱ የታክስ ሥርዓት ውስጥ ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙ ሰዎች ከፍ ያለ ታክስ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ መካካለኛ ገቢ የሚያገኙት ደግሞ ዝቅ ያለ ታክስ ይከፍላሉ ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኙ ሰዎች ደግሞ ከታክስ መክፈል ነፃ ሊደረጉ ይችላሉ ከፍተኛ ገቢና መካካለኛ ገቢ ከሚያገኙ ሰዎች የተሰበሰበውን ታክስ መንግስት ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኙ ሰዎች ወይም ምንም ገቢ የሌላቸው ወይም ሥራ አጦችን ለመደጎም ያውለዋል ኢኮኖሚን ለማረጋጋት መንግስት ታክስን ኢኮኖሚን ለማረጋጋት አላማ ሊጠቀምበት ይችላል መንግስት ታክስን በመጠቀም የዋጋ ግሽበት እና የኢኮኖሚ መቀዝቀዝን ለመቆጣጠር ሊጠቀምበት ይችላል ይሔንንም አውን የሚያደርገው እንደ ሁኔታው የታክስ ማስከፈያ መጠን « በመጨመር ወይም በመቀነስ ወይም አዲስ ታክስ በመጣል ወይም የተወሰኑ ታክሶችን በማንሳት ሊሆን ይችላል ጎጂ ወይም መሰረታዊ ያልሆኑ ምርቶችና ፍጆታ መቀነስ በሕብረተሰቡ ጤና ላይ ችግር የሚያስከትሉ ምርቶች ወይም መሰረታዊ ያልሆኑ ምርቶቾ ፍጆታ ለመቀነስ መንግስት ታክስን አንዱ መሳሪያ አድርጎ ሊጠቀም ይችላል ይሔንንም ብዙን ጊዜ ተግባራዊ የሚያደርገው በተመረጡ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ታክስ በመጫን ነው ለዚህ አላማ የሚጣለው የታክስ አይነተ አክሳይስ ታክስ የሚባለው ነው በሕብረተሰቡ ጤና ላይ ችግር የሚያስከትሉ ምርቶች ወይም መሰረታዊ ያልሆኑ ምርቶቾ ላይ ከፍተኛ ታክስ መጣል ዋጋቸው እንዲጨምር ስለሚያደረግ አብዛኛው ሰው እነዚህን ምርቶች ከመግዛት ሊቆጠብ ይቻላል የሚል እምነት አለ ። ውጪ ንግድ ለማበረታታት መንግስት ውጪ ንግድን ለማበረታታት ወደ ውጪ የሚላኩ እቃዎችን ወይም ምርቶች ከታክስ ነፃ ሊያደርጋቸው ይችላል ይህ ደግሞ ምርቶች በውጭ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል መዋቅር የታክስ መዋቅር ማለት በአንድ ሀገር ውስጥ የሚጣሉ እና የሚሰበሰቡ የታክስ ዓይነቶች ማለት ነው በሀገሮች መካከል ባለው የኢኮኖሚ ፖለቲካ እና ማህበራዊ ልዩነቶች የተነሳ ሀገሮች የተለያዩ የታክስ መዋቅር አሏቸው ይህ ማለት ግን ምንም ዓይነት ተመሳሳይነት የላቸውም ማለት አይደለም ለምሳሌ የገቢ ታክስ ኤክሳይዝ ታክስተጨማሪ እሴት ታክስ እና የጉምሩክ ቀረጥ በብዙ ሀገሮች የሚጣሉ እና የሚሰበሰቡ የታክስ አይነቶች ናቸው ብዙ ፀሐፊዎች የታክስ አይነቶችን በተለያየ መደብ ይከፋፍላሉ በተለይ ታክሶችን ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ብሎ መከፋፈል የተለመደ ነው ታክሶችን ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ብሎ ለመከፋፈል እንደ መሰረት ሆኖ የሚያገለግለው ታክሱን የመክፈል የመጀመሪያው ሸክም አና የመጨረሻው ሸክም ማን ላይ ያርፋል ለሚለው ጥያቄ የሚሰጠው መልስ ነው ይሔንኑ በመተራስ ዳልተን የተባለ ጸሐፊ ቀጥተኛ ታክሶችን ክ ኢከርከ ፍኳክከፎሃ ኘ ከዕ ህዌፍ ዐቧ ህሆኪዐዕቢ ክፍኘ ኗ ብሯ ፎርቪ ጺፎ ከከዕ ጸኡ ዝሆከሮኪ ርዉ ቧ እፍ ክቨሬጪ ክፎ በማለት ባአጭሩ ይገልጻቸዋል ከዚህ ትርጉም ቀጥተኛ ታክሶችን በተመለከተ ታክስ የመክፈል የመጀመሪያው ሆነ የመጨረሻው ሸክም የሚያርፈው በአንድ ሰው ላይ መሆኑን መረዳት ይቻላል በሌላ አባባል ታክሱ የመክፈል ሸክም ወደ ሌሎች ሰዎች አይሻገርም ወይም በሌሎች ሰዎች ላይ አያርፍም ማለት ነው ታክሱ የሚከፈለው በቀጥታ ታክስ በተጣለበት ሰው ነው ከቀጥተኛ ተክሶች ውስጥ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ላይ የሚጣል ታክስ የንግድ ሥራ ትርፍ ግብር ከቤት ኪራይ በሚገኝ ገቢ ላይ የሚጣል ታክስ በወለድ ላይ የሚከፈል ገቢ ታክስ የንብረት ታክስ የአርሻ ገቢ ታክስ የውርስ ታክስ የስጦታ ታክስን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል በሌላ በኩል ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶችን በተመለከተ ታክሶቹን የመክፈል የመጀመሪያው እና የመጨረሻው ሸክም የሚያርፈው በአንድ ሰው ላይ ሳይሆን በተለያዩ ሰዎች ላይ ነው በዚህ መሰረት ታክሱን የመክፈል የመጀመሪያው ሸክም የሚወድቀው አግባብ ባለው ህግ ውስጥ ታክስ ከፋይ ተብሎ በተጠቀሰው ታክስ ከፋይ ላይ ሲሆን የመጨረሻው ሸክም የሚወድቀው ደግሞ በሸማቹ ላይ ነው ይህም ማለት አግባብ ባለው ህግ ውስጥ ታክስ ከፋይ ተብሎ የተጠቀሰው ሰው የከፈለውን ታክስ በዋጋ መልክ የታክስ ሸክሙን ወደ ሸማቹ እንዲሻገር ያደርጋል ማለት ነው ቀጥተኛ ካልሆኑ ታክሶች ውስጥ የሽያጭ ታክስ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስኤክሳይዝ ታክስ የጉምሩክ ቀረጥን በምሳሌነት መጥቀስ ይችላል ሌሎች ፀሐፊዎች የታክስ አይነቶችን የገቢ ታክስ የንብረት ታክስ እና የርጧቬቨ ታክስ ብለው ይከፋፍላሉ ይሔም ክፍፍል የታክስ መሰረትን መሰረት ያደረገ ነው የታክስ መሰረት ከ ማለት ታክሱ የሚጣልበት ነገር ማለት ነው ማንኛውም ታክስ የታክስ መሰረት አለው የታክስ መሰረት ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ የንግድ ሥራ ትርፍ ገቢ አንድ ሰው እቃ ወይም አገልግሎት ለመግዛት የሚያወጣው ገንዘብ በውርስ የተገኘ ሀብት መጠን ወዘተ ሊሆን ይችላል በሌላ በኩል የንብረት እና የርዕሃታክሶች የምንላቸው ደግሞ ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶችን ተብለው ከላይ የተጠቀሱ የታክስ አይነቶችን የሚመለከቱ ናቸው ሐገሮች እንደ ሐገራቸው ሁኔታ የታክስ አይነቶችን በተለያዩ መንገድ ሊከፋፍሉ ይችላሉ የታክስ ሥልጣን ክፍፍል በፌዴራል ሥረዓት የታክስ ሥልጣን ምንነት የታክስ ሥልጣን በተለያዩ መንገዶች ሊገለጽ ይችላል ለምሳሌ ርዐጾ የተባለ ፀሓፊ የታክስ ሥልጣንን ቭ ል ከ ሃ ይዐሆፀያ ዕ ዐ ርዐፀር ርዐበስገይአህ ዕያ ዐ ዐከ ይያዐጓይፀ ድ ር ያነፀ በስቋህቨል ዕያ ፀቭርዐ ፀጸዌፀስርበስፍኗ ያማዘያፖ ጋሳጸመሳ። ዕ ዐሃር እ ር ይፀ ዮሃ ከፍ ፀርህፀሃፀ ዐህበፀ ዕ ሃፀ ዕር ይሃ ከፀ ርዐሠፎ በማለት የታክስ ሥልጣን የሕግ አውጪው የመንግሥት አካል ብቻ መሆኑን በአጭሩ አስቀምጦታል በኢፌድሪ ህገመንግስት የፌዴራል መንግሥት ህግ አውጪው አካል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የክልሎች ዳግም የክልል ምቤቶች በመሆኑ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፌዴራል መንግሥት በተመለከተው ገቢ ምንጭ ክልል የክልል ምቤቶች ዳግም ለክልሎች በተመለከተው ገቢ ምንጭ ክልል ታክስ የመጣል ሥልጣን አሏቸው አንቀጽ ህግ አስፈፃሚው እና ህግ ተርጓሚው አካል ግን ታክስ የመጣል ሥልጣን የላቸውም የታክስ ሥልጣን ገፅታዎች የታክስ ሥልጣን ሶስት ገፅታዎች አሉት አንደኛው የሕግ ማውጣት ነው ይህ የታክስ ሥልጣን ገጽታ መሰረታዊ ሕጎችን በመደንገግ ታክስን መጣል የሚመለከት ነው ይህ የታክስ ሥልጣን ገጽታ የበለጠ ለመረዳት ከታክስ ጋር በተያያዘ መጣል በ የሚለው ቃል ትርገሙን ማየት ጠቀሜታ አለው ብላክስ ሎው ዲኪሺነሪ መጣል በ የሚለውን ቃል ከ ኛ ብክበር በር ዐ ከከ ከር ዐ በከ ር የቧርኪኳ በዐቧከበጀ ከ ከ ከ በህበ ከበ በ ህሀዝ ር ዐ በማለት ይፈተዋል ታክስ መጣል ህግ ማውጣት ተግባር መሆኑንና ይህም ተግባር ታክስ እንዲጣል መወሰን የታክሱን አላማ አንዲሁም ታክስ የሚጣልበትን ነገር እና ማስከፈያውን መጠን መወሰንን የሚመለከት መሆኑን ከዚህ ትርጉም መረዳት ይቻላል ሁለተኛው ገፅታ ታክስ መሰብሰብ ነው ይህ የታክስ ሥልጣን ገፅታ የተጣሉትን ታክሶች የታክስ ህጉን በማስፈጸም የመሰብሰብ ሥልጣንን የሚመለከት ነው ሶስተኛው ገፅታ መጠቀም ነው ይህ የታክስ ሥልጣን ገፅታ የተሰበስበው የታክስ ገቢ መጠቀምን ወይም ከታክሱ ከሚገኘው ገቢ ተጠቃሚ የመሆን መብትን የሚመለከት ነው በብዙ ሐገሮች የታክስ ሥልጣን ይዘት እነዚህን ሶስት ገጽታዎች የያዘ ነው ከዚህ አንፃር ሲታይ ሕግ አውጪው አካል ታክስን በተመለከተ ሰፊ ሥልጣን ያለው መሆኑን መረዳት ይችላል ሕግ አውጪው ከታክስ ጋር ተያያዥነት ባላቸው የተለያዩ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ የመወሰን ሥልጣን አለው ከእነዚህ ውስጥ አንዱ አንድ የተወሰነ የታክስ መጣል አለበት ወይስ የለበትም በሚለው ላይ ውሳኔ መስጠት ነው ሕግ አውጪው ሥልጣን በዚህ ላይ ብቻ የተገደበ ሳይሆን የሚጣለው የታክስ አይነት ማስከፈያው መጠን አተማመን ዘዴን መክፈያ ጊዜ አሰባሰብ መንገድና አፈፃፀሙ ምን ወይም እንዴት መሆን አለበት እስከ መወሰን የሚሔድ ነው መርሆች በፌዴራል ሥረዓት የታክስ ሥልጣን ክፍፍል በምን መርህ ላይ መመስረት አለበት ለሚለው ጥያቄ ወጥ የሆነ መልስ የለም የታክስ ሥልጣን ክፍፍሉም እንደ ሐገሩ ተጨባጭ ሁኔታ ይለያያል ሆኖም ግን ያሉት ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው በአብዛኛዎቹ የፊዚካል ፌዴራሊዝም ፀሐፊዎች ዘንድ በተወሰኑ መርሆች ላይ ከሞላ ጉደል መግባባት አለ ለማለት ይቻላል እነዚህ መግባባት የተደረሰባቸው መርሆች በይበልጥ አሰተዳደራዊ አመቺነት እና ቅልጥፍናን መሰረት ያደረጉ ናቸው ከእነዚህ መርሆች ውስጥ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው ኢኮኖሚን ለማረጋጋት የሚረዱ ታክሶች በፌዴራል ሥርዓት የሐገሪቱን አጠቃላይ ኢኮኖሚ የመቆጣጠር ሥልጣን የፌዴራል መንግስት ነው ይህ ስልጣን የፌዴራል መንግስት የተሰጠ በመሆኑ ኢኮኖሚን ለማረጋጋት ሚና ያላቸው ታክሶች ለማከላዊ መንግስት መሆን አለባቸው ያ ፀዕዐኬር ፀክህ ርፀክጺቧ ይሄም ማእከላዊ መንግስት ወይም ፌዴራል መንግስት በሕገ መንግስቱ ከሚኖረው ሐላፊነትና ተግባር ጋር የተያያዘ ነው በዚህ መርህ መሰረት የኩባንያ እና ተጨማሪ እሴት ታክሶችን የመጣል ሥልጣን ለፌዴራል መንግስት የግል ገቢ ታክስ እና የችርቻሮ የሽያጭ ታክስ ደግሞ ለክልሎች መሆን ይኖርባቸዋል ገቢን ለማመጣጠን አመቺ የሆኑ ታክሶች መንግስት በሐገሪቱ ዜጎች መካከል ፍታሐዊ የሆነ የገቢ ክፍፍል እንዲኖር የማደረግ ሐላፊነት አለበት በፌዴራል ሥርዓት ደግሞ ይህ ሐላፊነት በተለይ የፌዴራል መንግስቱ ነው ስለዚህ በዚህ መርህ መሰረት ገቢን ለማመጣጠን የሚረዱ ታክሶችን የመጣል ሥልጣን ለፌዴራሉ መንግስት መስጠት እንዳለባቸው ነው ቹ መሰረታቸው ቋሚ የሆኑ ታክሶች መሰረታቸው ቋሚ የሆኑ ታክሶች ለክልል መንግስት መተው አለባቸው ዚክ ዐቨ ከሀ ለዚህ ደግሞ የመሬት ታክስን መጥቀስ ይቻላል በሌላ በኩል የታክስ መሰረታቸው ክልል ዘለል የሆኑ የታክስ መሰረቶች ለፌዴራል መንግስት መስጠት ይኖርባቸዋል የታክስ መሰረታቸው ሥርጭት በሁሉም ቦታ እኩል ያልሆኑ ታክሶች የታክስ መሰረታቸው ሥርጭት በሁሉም ቦታ እኩል ያልሆኑ ታክሶች ለፌዴራል መንግስት መስጠት አለባቸው ክህዝቄ ሃሬኘ ክኪቪቬዩሃ ክፍከሆፎዉዉ ቪክኳ ኪዕህ ርፍፎቧቤቪኋፍፎሷ ይህ መርህ ይበልጥ የሚመለከተው የተፈጥሮ ሀብትን ነው የተፈጥሮ ሀብት በሁሉም ክልሎች በእኩል መጠን አይገኝም ይህ ደግሞ በክልል መንግስታት መካከል ከፍተኛ የኢኮኖሚ ልዩነት እንዲኖር ያዳርጋል ከፍታዊነት አንጻር ሲታይ ከተፈጥሮ ሀብት ከሚገኘው ጥቅም ተጠቃሚ መሆን ያለበት የተፈጥሮ ሀብቱ የሚገኝበት ክልል ብቻ ሳይሆን ሁሉም የፌደሬሽኑ አባላት መሆን ይኖርባቸዋል ለዚህ ደግሞ ያለው አማራጭ የተፈጥሮ ሀብትን በተመለከተ የታክስ ሥልጣኑ ለክልል መንግስት ሳይሆን ለፌዴራል መንግስት መስጠት ነው የፌዴራል መንግስትም ከተፈጥሮ ሐብቱ የሚሰበሰበውን የታክስ ገቢ ሁሉም ክልል ተጠቃሚ እንዲሆን የማድረግ ሐላፊነት አለበት በሌላ በኩል የተፈጥሮ ሐብቱ በሚገኝበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች የተፈጥሮ ሐብቱን በተመለከተ የይገባናል ስሜት ሊኖራቸው ይችላል የተፈጥሮ ሐብት የይገባናል ጥያቄ ፖለቲካዊ ይዘትም ሊኖረው ይችላል ይሄን ተንተርሶ የሚነሳው ጥያቄ የፌዴራል ሥርዓቱን ሕልውና ሊፈታተን ይችላል ከዚህ የተነሳ የተለያዩ ፌደሬሽኖች ከተፈጥሮ ሐብት የሚያገኘውን የታክስ ገቢ ክፍፍል በተመለከተ የተለያዩ አማራጮች ወስዳዋል ለምሳሌ በቀድሟ ሩሲያ ፌደሬሽን ከተፈጥሮ ሐብት የሚገኘውን የታክስ ገቢ የተፈጥሮ ሐብቱ ለሚገኝበት ክልል በማካፈል ችግሩን ለመፍታት ተሞክሯራል በአጭሩ ከተፈጥሮ ሐብት በሚገኘው ገቢ ላይ የትኛው የመንግስት እርከን ታክስ ሥልጣን ሊኖረው ይገባል የሚለው ጥያቄ አስተዳደራዊ አመቺነት እና ቅልጥፍናን ብቻ መሰረት አድርጎ የሚወሰን አይደለም የተፈጥሮ ሐብትን በተመለከተ የታክስ ሥልጣን ክፍፍሉ ለሐገሪቱ ኢኮኖሚ የሚኖረውን ጠቀሜታ በፌዴራል ሥረዓቱ ሕልውና ላይ ያለውን ተጽአኖ እና የተፈጥሮ ሐብቱ ባለበት አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎችን ስሜትና ፍላጎት ከግምት ውስጥ ማስገባትን የሚጠይቅ ነው የአገልግሎት ታክሶችን እና ክፍያዎችን የአገልግሎት ታክሶች እና ክፍያዎች የመጣልና የመሰበሰብ ሥልጣን ለሁለቱም የመንግስት እርከኖች ሊሰጥ ይችላል ኬ ርከኡ ጠከ ጸጳዌሯዐጅ። ፎሃ ፈፍፍቧ ሇፎ በአጠቃላይ በፌዴራል ሥረዓት የታክስ ሥልጣን ክፍፍል አንደ ሁኔታው አሰተዳደራዊ አመቺነት ቅልጥፍናን የታክስ ክልላዊ ወይም ብሔራዊ ባህሪ የታክሱ ምንጭ ባለቤትነት እና ሌሎች ነጥቦችን ከግምት ውስጥ ማስገባትን የሚጠይቅ ነው ለማለት ይቻላል ዘዴዎች ሽከ በንድፈ ሐሳብ ደረጃ ሶስት አይነት ሕገመንግሥታዊ የታክስ ሥልጣን ክፍፍል ዘዴዎች አሉ አንደኛው ሁሉንም የታክስ ሥልጣን ለፌዴራል መንግሥት መስጠት ነው ሕግመንግሥቱ ሁሉንም የታክስ ሥልጣን ለፌዴራል መንግሥት የሚሰጥ ከሆነ የክልል መንግሥታት ሙሉ በሙሉ በፌዴራል መንግሥት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ ይህ አማራጭ በፌዴራል ሥረዓት ሥልጣንና ኃላፊነት ያልተማከለ መሆን አለበት የሚለው መርህ የሚጋፋ በመሆኑ ብዙም ተቀባይነት ያለው አይደለም ሁለተኛው የአንደኛው ዘዴ ተቃራኒ ሲሆን ይህም ሁሉንም የታክስ ሥልጣን ለክልል መንግሥታት የሚሰጥ ነው በዚህ ዘዴ መሰረት ሕገመንግሥቱ ሁሉንም የታክስ ሥልጣን ለክልል መንግሥታት የሚሰጥ ከሆነ ክልሎች የገቢያቸውን የተወሰነ መጠን ወደ ፌዴራል መንግሥት ወደ ላይ እንዲያዞሩርዕዌሆ ሇኪሀ ከክኳ የሚጠይቅ ነው ይህ አማራጭ ዘዴ የፌዴራል መንግሥቱ በታክስ ፖሊሲ ማከናወን የሚገባውን ተግባሮች ማለትም የገቢ ክፍፍል በክ ከኢ ኢኮኖሚ ማረጋጋትና እና የታክስ ማዋሐድን እንዳያከናውን ስለሚያደርገው ተቀባይነቱ አምብዛም አይደለም በተጨማሪም በክልሎች መካከል የኢኮኖሚ ልዩነት ባለ ጊዜ የክልል መንግሥታት በፌዴራል መንግሥቱ ውስጥ ከመሳተፍ ወደ ኃላ እንዲሉ ሊያደርጋቸው ይችላል ሶስተኛው ዘዴ የታክስ ሥልጣኑን በሁለቱ የመንግሥት እርከኖች መካካል የሚከፋፈል ነው ይህ በአብዛኛው የፌዴራል ሥርዓት ተከታይ ሐገሮች ሕገመንግሥት ተቀባይነት ያገኘ የታክስ ሥልጣን ክፍፍል ዘዴ ነው የታክስ ሥልጣንን በሁለቱ የመንግስት እርከኖች መካከል እንዲከፋፈል የሚያደርገው ዘዴ በስሩ ሶስት ንዑስ ክፍሎች አሉት አንደኛው ብቸኛ የታክስ ሥልጣን ነው ሕገመንግስቱ የተወሰነ የታክስ ምንጮች ለፌዴራልና ለክልል መንግሥታት ብቻ ለብቻ ለያይቶ ሊሰጥ ይችላል የፌዴራል መንግሥት ወይም የክልል መንግሥታት በተለያዩ ነገሮች የንግድ ሥራዎች ወይም ሰዎች ላይ ራሱን የቻለ የታክስ ሥልጣን ያላቸው ከሆነ ይሔ ብቻኛ የታክስ ሥልጣን ይባላል ብቸኛ የታክስ ሥልጣን አጠቃላይ የህግ ማውጣት ሥልጣን ክፍፍልን ሊከተል ይችላል ይህም በመርህ ደረጃ እያንዳንዱ የመንግሥት እርከን በራሱ ህገ ማውጣት ሥልጣን ክልል ውስጥ በሚወድቁ የገቢ ምንጭ መሰረቶች ላይ ማንኛውንም አይነት ታክሶችን ሊጥል ይችላል ሁለተኛው የጋራ የታክስ ሥልጣን ርኪርፌጩ ቼህ ር ኳእ ነው ሕገመንግሥቱ ሁለቱም የመንግሥት እርከኖች የተወሰነ የታክስ አይነቶች ወይም ሁሉንም የታክስ አይነቶች በተመለከተ ሕግ ማውጣት መሰብሰብና የሚሰበሰበውን ገቢ የመጠቀም ሥልጣን ሊሰጣቸው ይችላል የፌዴራል መንግሥት እና የክልል መንግሥት በተመሳሳይ የንግድ እንቅስቃሴዎች ወይም የተወሰነ ነገር ላይ ታክስ የመጣል አኩል ሕገመንግስታዊ ሥልጣን ያላቸው ከሆነ የታክስ ሥልጣኑ የጋራ ነው ለማለት ይቻላል በመርህ ደረጃ እያንዳንዱ የመንግሥት እርከን የታክስ ሥልጣኑን ራሱን ችሎ ተግባራዊ የማድረግ መብት አለው ነገር ግን የፌዴራል ሥረዓት ተከታይ ሐገሮች ሕገመንግስት የተለያዩ የጋራ ታክስ ሥልጣን ይደነግጋሉ ለምሳሌ የጋራ የታክስ ሥልጣን የካናዳ የአሜሪካና የሕንድ ሕገመንግስት አይነተኛ ባህሪ ነው በካናዳ ሕገመንግሥት የክልል መንግሥታት የታክስ ሥልጣን ቀጥተኛ በሆኑ ታክሶች ላይ ብቻ ነው በሌላ በኩል የፌዴራል መንግሥት ታክስን በመጠቀም ማንኛውንም ገቢ መፍጠር አንደሚችል ሥልጣን ተሰጥቶታል ስለዚህ ቀጥታኛ ታክሶችን በተመለከተ የፌዴራል መንግሥትና የክልል መንግሥታት የጋራ የታክስ ሥልጣን አሏቸው ማለት ነው ከሌሎች ፌደሬሽኖች ጋር ሲነፃፀር የአሜሪካ ህገመንግሥት ሰፊ የጋራ ታክስ ሥልጣን ይደነገጋል ለምሳሌ በሕገመንግስቱ ሁለቱም የመንግሥት እርከኖች በግለሰብ እና በኩባኒያ ኮሮፕሮቲ ገቢ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ጩ እና ኤክሲይዝ ታክስን በሞተር ዘይት አልኮል እና የትንባሆ ምርቶች ላይ የታክስ ሥልጣን አሏቸው በሕገመንግሥቱ እኩል የታክስ ሥልጣን መሰጠቱ የታክስ መደራረብን እና የፌዴራል እና የክልል ታክስ ሕጎች መቃረንን ይፈጥራል የፌዴራል ሕግ በላይነት ይህን ችግር ይፈታዋል በሕንድ የገቢ ታክስ የውርስ ታክስ ኤክሳይዝ ታክስ በማስታወቂያ ላይ የሚጣል ታክስና የንብረት ታክስ የጋራ ታክስ ናቸው የአንዳንድ ፌዴሬሽን ሕገመንግሥት የፌዴራል መንግሥት የክልል መንግሥታትን የጋራ ታክስ ሥልጣን እንዲቋረጥ ማድረግ የሚችልበትን ሁኔታ ይደነግጋል ለምሳሌ የጀርመን ህገመንግሥት መጥቀስ ይቻላል በጀርመን የሁለቱ የመንግስት እርከኖች የጋራ ነው በተባሉ ጉዳዮች ለይ በጋራ ሕግ ማውጣት ሥልጣን አሏቸው ሆኖም ግን የፌዴራል መንግስት በሕገመንግስቱ የጋራ ሥልጣን ነው በተባሉ ጉዳዮች ላይ ሕግ የሚያወጣው ሕግ ማውጣቱ ብሔራዊ ፋይዳ ካለውና በሙሉ በሐገሪቱ እኩል የሆነ የኑሮ ሁኔታንና ኢኮኖሚ አንድነትን ለመፍጠር አስፈላጊ ሲሆን ነው በሌላ በኩል የጋራ ተብለው በተሰጡ ጉዳዮችን በተመለከተ ክልሎች በበ የህግ ማውጣት የሚችሉት በጉዳዮች ላይ የፌዴራል መንግስት ቀድሞ ሕግ ካለወጣ ወይም እስኪያወጣ ብቻ ነው ይህ በመሆኑ የጀርመን ህገመንግስት ሁለቱም የመንግስት እርከኖች ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ ላይ በአንድ ጊዜ በጋራ ሕግ የማውጣት ሥልጣንን ተግባራዊ እንዲሆን የሚፈቅድ አይደለም ስለዚህ በጀርመን ሕገመንግስት የጋራ ሥልጣን ለየት ያለ ትርጉም ያለው መሆኑን መረዳት ይቻላል ሶስተኛው የታክስ ሥልጣን ክፍፍል ዘዴ ከፌ ሯሸ ርያ ኪ ነው ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው የታክስ ሥልጣን ሶስት ገፅታዎች አሉት እነሱም ሕግ ማውጣት መሰብሰብ አና ገቢውን መጠቀም ናቸው እነዚህን የታክስ ሥልጣን ገፅታዎች በሁለቱ የመንግስት አርከኖች መካከል የሚከፋፍሉ ሐገሮች አሉ ሕገመንግስቱ በመርህ ደረጃ አንድ የተወሰነ ታክስን በተመለከተ የታክስን የመጣል ሥልጣን ለፌዴራል መንግሥት ሰጥቶ ከታክሱ የሚሰበሰበውን ገቢ የተወሰነውን ወይም ሙሉ በሙሉ የክልሉች እንዲሆን ሊደነግግ ይችላል በዚህ መሰረት አንዱ የመንግስት እርከን የታክስ ህግን ያወጣል ሌላው ደግሞ የተጣለውን ታክስ በመሰብሰብ ሕጉን ያስተዳድራልአሁንም ሌላው ከታክስ የሚገኘውን ገቢ ተጠቃሚ ሊሆን ይችላል ለምሳሌ የሕንድ ህገመንግሥት የፌዴራል መንግሥት የቴንብር ቀረጦችንና በመድሓኒቶች ላይ ኤክሳይዝ ታክሶችን የመጣል ሥልጣን አለው ከእነዚህ የሚገኘው ገቢ የመሰብሰብ ሥልጣን ደግሞ ለክልል መንግስታት የተሰጠ ነው በተመሳሳይ የፌዴራል መንግሥት የሸያጭ ታክስን ሕግ ማውጣትና የታክሱን የመሰብሰብ ሥልጣን አለው ነገር ግን ከእነዚህ ታክሶች የሚገኘውን የተጣራ ገቢ የክልሎች ነው ይህ የተጣራ ገቢም ህግ አውጪው በሚያወጣው የክፍፍል ቀመር መሰረት በክልሎች መካከል እንዲከፋፈል ይደረጋል በጀርመን ሕገመንግሥትም ውስጥም ከ ተደንግጓል በጀርመን ሕገመንግት መሰረት ከገቢ ታክስ ኮሮፕሬሽን ታክስና ከተርን ኦቨር ታክስ የሚገኘው ገቢ የሁለቱም መንግስት ነው በዚሁ መሰረት ሁለቱም መንግሥት እርከኖች ከገቢ ታክስና ኮሮፕሬሽን ታክስ አኩል ድርሻ ያላቸው ሲሆን ከተርን ኦቨር ታክስ የሚገኘው ገቢ የሚከፋፈልበትን ቀመርም ተደንግጓል በአጠቃላይ የፌዴራል መርህ አላማ እያንዳንዱ የመንግሥት እርከን ተለይቶ የተሰጠውን ሥልጣንና ተግባር ራሱን ችሎ እንዲያከናውን የወጪ ፍላጎቱን ለማሟላት የሚያስችለው የፋይናስ አቅም አንዲኖረው ማድረግ ነው ሆኖም ግን በተግባር የክልሎች የገቢ ምንጭና የወጪ ፍላጎትን ማመጣጠን አዳጋች እንደሆነ በዘርፉ ጻሐፊዎች ብዙ የተባለበት ጉዳይ ነው ፌዴሬሽኖች ይህን ችግር የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ለመፍታት ይሞክራሉ የመወያያ ጥያቄዎች የታክስ ህግ አላማ እና በኢፌድሪ ህግመንግስት የተደነገገው የመልማት መብት መካከል ያለው ግንኙነት እንዴት ይገለጻል። የታክስ ሥልጣን ክፍፍል በኢፌዴሪ ሕገመንግስት የታክስ ሥልጣን ክፍፍል በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት ዘርዘር ባለ መልኩ ተደንግጓል ሕገመንግሥቱ የታክስ ሥልጣንን በሶስት መደቦች ከፋፍሏል እነሱም የፌዴራል መንግስት የታክስ ብቸኛ ሥልጣን የክልል መንግሥታት ብቸኛ የታክስ ሥልጣን እና የፌዴራልና የክልል መንግሥታት የጋራ የታክስ ስልጣን ናቸው እነዚህንም የፌዴራልና የክልል መንግስታት ብቸኛ የታክስ ሥልጣን እና የፌዴራልና ክልል መንግስታት የጋራ ታክስ ሥልጣን በማለት ሁለት ቦታ ከፍሎ ማየት ይቻላል የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ብቸኛ የታክስ ሥልጣን በኢፌድሪ ሕገመንግሥት የፌዴራል መንግሥት ለፌዴራሉ መንግሥት በተሰጡ የገቢ ምንጮች ክልል ግብርና ቀረጥ መጣልና መሰበሰብ እንደሚችል ተደንግጓል አንቀፅ በተመሳሳይ ሁኔታ የክልል መንግሥታትም በተሰጣቸው የገቢ ምንጮች ክልል ግብርና ቀረጥ መጣልና መሰብሰብ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል አንቀፅ ስለዚህ ሁለቱም የመንግሥት እርከኖች በተሰጣቸው የታክስ ክልል ህግ ማውጣትና ታክስ የመስተዳደር ሥልጣን አሏቸው ማለት ነው በተጨማሪም ከየራሳቸው የታክስ ምንጭ የሚያገኙትን ገቢ የመጠቀም መብት አሏቸው የኢፌዴሪ ሕግ መንግሥት የፌዴራል መንግሥት ታክስና ግብር ሥልጣን እና ክልል መስተዳድሮች የታክስና የግብር ሥልጣን በሚል ርእስ ብቸኛ የታክስ ሥልጣን ዘርዝራል የታክስ ሥልጣን ክፍፍሉ በአጠቃላይ ግብር ከፋዮች ምደባ ወይም የገቢ ምንጭን መሰረት ያደረገ ነው በሌላ አገላለጽ የእያንዳንዱ የመንግስት እርከን ብቸኛ የታክስ ሥልጣን መሰረት የታክስ መሰረት ሳይሆን የታክስ ምንጭ ነው ይህ በመሆኑ በህገመንግስቱ የተደነገገው የታክስ ሥልጣን ክፍፍል ሥርዓት ሁለቱም የመንግስት እርከኖች በተመሳሳይ ገቢ ወይም ታራንዛክሽን ላይ በአንድ ጊዜ ታክስ እንዲጥሉ የሚፈቅድ አይደለም በህገመንግሥቱ በሁለቱ የመንግሥት እርከኖች መካከል እንዲከፋፈሉ የተደረጉ የታክስ ገቢ ምንጮችየወጪና የገቢ ዕቃዎች ታክስና ክፍያዎችየገቢ ታክስየሽያጭና የእክሳይዝ ታክስ የንብረት ታክስ እና የአገልግሎት ክፍያዎች በማለት ከፋፍሎ ማየት ይቻላል አንቀፅ እና የወጪና የገቢ ዕቃዎች ታክሶችና ክፍያዎች በሁሉም ፌዴሬሽኖች ማለት ይቻላል የወጪና የገቢ ዕቃዎች ላይ የጉምሩክ ቀረጥ መጣል እና የመሰብሰብ የፌዴራል መንግሥት ብቸኛ ሥልጣን ነው የኢፌድሪ ህገመንግስትም ከዚህ የተለየ አይደለም በወጪና ገቢ እቃዎች ላይ የጉምሩክ ቀጥተኛ ታክስና ሌሎች ክፍዎች መጣልና መሰብሰብ የፌዴራል መንግሥት ብቸኛ ሥልጣን መሆኑ በሕገመንግስቱ ተመልክቷል አንቀጽ የገቢ ታክስ የገቢ ታክስን መጣልና መሰብሰብ ሥልጣን ለየትኛው የመንግሥት እርከን መስጠት አለበት ለሚለው ጥያቄ አንድ ወጥ የሆነ መልስ የለም አንዳንዶቹ የግል ገቢ ታክስን ሯፒ ክቧዕበ ለፌዴራል መንግሥት ሲሰጡ ሌሎች ደግሞ ለክልሎች ይሰጣሉ ለምሳሌ በጀርመን ሁለቱንም የመንግሥት እርከኖች የገቢ ታክስን በጋራ የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን አሏቸው በአሜሪካ ደግሞ የገቢ ታክስን መጣል እና መሰብሰብ ሥልጣን የክልል መንግሥታት ነው የኢፌድሪ ሕገመንግስት የገቢ ታክስን የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን ለፌዴራል መንግስት ብቻ ወይም ለክልል መንግስታት ብቻ አልሰጠም በሕገመንግስቱ የገቢ ታክስን የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን በሁለቱ የመንግስት እርከኖች መካከል እንዲከፋፈል ነው ያደረገው በዚሁ መሰረት የፌዴራል መንግሥት እና የክልል መንግሥታት በምን ዓይነት የታክስ ምንጮች ላይ የገቢ ታክስ መጣልና መሰብሰብ አንደሚችሉ ተለይቶ ተደንግጓል በመሆኑም ሁለቱም የመንግሥት እርከኖች ተለይተው በተሰጧቸው የገቢ ምንጮች ላይ የገቢ ታክስን የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን አሏቸው ማለት ነው የገቢ ታክስ የሚጣልባቸው የታክስ ምንጮች ውስጥ አንደኛው የግል የስራ ግብር ርበቧፎ ክቧ ፎዉሄበኬ ነው የግል የስራ ግብርን በተመለከተ ህገመንግሥቱ ታክስ ከፋዮችን በአምስት ከፍሏቸዋል እነሱም የፌዴራል መንግስት ተቀጣሪዎች የክልል መንግስታት ተቀጣሪዎችየመንግስት ልማት ድርጅት ተቀጣሪዎች የአለም አቀፍ ድርጅቶች ተቀጣሪዎችና የግል ተቀጣሪዎች ናቸው የፌዴራሉ መንግሥት ተቀጣሪዎች የፌዴራል መንግሥት የሆኑ የልማት ድርጅቶች ተቀጣሪዎች እና የአለም አቀፍ ድርጅቶች ተቀጣሪዎች ገቢ ላይ የፌዴራል መንግስት የስራ ግብር የመጣልና የመሰብሰብ ብቸኛ ሥልጣን አለው በተመሳሳይ ክልሎች የክልል መንግስታት የሆኑ የልማት ድርጅቶች ተቀጣሪዎችና በግል ተቀጣሪዎች ላይ የስራ ገቢ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ብቸኛ ሥልጣን አሏቸው ሁለተኛው የገቢ ታክስ የልማት ድርጅቶች የንግድ ትርፍ ግብር የሚመለከተ ነው በፌዴራል መንግሥት ባለቤትነት ስር በሆኑ የልማት ድርጅቶች ላይ የንግድ ትርፍ ግብር መጣልና መሰብሰብ የፌዴራል መንግሥት ብቸኛ ሥልጣን ነው የክልል መንግሥታት ባለቤትነት ስር በሆኑ የልማት ድርጅቶች ላይ የንግድ ትርፍ ግብር መጣልና መሰብሰብ ደግሞ የክልል መንግሥታት ብቸኛ ሥልጣን ነውየዚህ ታክስ ሥልጣን ክፍፍልም ባለቤትነት መሰረት ያደረገ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል ሶስተኛው በየክልሉ የሚገኙ ግለሰብ ነጋዴዎችን የሚመለከት ነው በየክልሉ የሚገኙ ግለሰብ ነጋዴዎችን በተመለከተ የክልል መንግሥታት የንግድ ትርፍ ግብር የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን አሏቸው አንቀጽ አራተኛው የአየርየባቡርየባህር ትራንስፖርት ገቢዎችን የሚመለከት ሲሆን በእነዚህ ስራዎች በሚገኘው ገቢዎች ላይ የፌዴራል መንግስት የገቢ ታክስ መጣልና የመሰብሰብ ብቸኛ ሥልጣን አለው በሌላ በኩል የክልል መንግሥታት ክልል ውስጥ በውዛፃ ላይ ከሚደረግ ትራንስፖርት በሚገኘው ገቢ ላይ የታክስ ስልጣን አሏቸው አምስተኛው የብሔራዊ ሉተሪ እና ሌሎች የአድል ሙከራ ገቢዎች ላይ የሚጣልና የሚሰበሰብ የገቢ ታክስ ነው ይህ የፌዴራል መንግስት ብቸኛ ሥልጣን ነው ስድስተኛው ቤቶችና ሌሎች ንብረቶች በማከራየት በሚገኘው ገቢ ላይ የሚጣል የገቢ ታክስ ነው ይህን በተመለከተ የፌዴራል መንግሥት ባለቤትነት ሥራ በሚገኙ ቤቶችና ሌሎች ንብረቶች ገቢ ላይ የፌዴራል መንግስት ታክስ የመጣልና የመሰበሰብ ብቸኛ ሥልጣን ያለው ሲሆን የክልል መንግስታት ደግሞ በግል ባለቤትነት ሥር ባሉ ቤቶችና ሌሎች ንብረቶች በሚገኝ ገቢ ላይ የገቢ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ብቸኛ ሥልጣን አሏቸው የዚህ ታክስ ሥልጣን ክፍፍልም ባለቤትነትን መሰረት ያደረገ መሆኑ መረዳት ይቻላል ሰባተኛው የእርሻ ሥራ ገቢ ታክስ ነው የአርሻ ሥራ ገቢ ታክስን በተመለከተ የክልል መንግስታት በግል በሚያርሱ እና በህብረት ሥራ ማህበራት በተደራጁ ገበሬዎች ላይ የእርሻ ሥራ ገቢ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ብቸኛ ሥልጣን አሏቸው ስምንተኛው ከአነስተኛ ማዕድን ሥራዎች የሚገኝ ገቢን የሚመለከት ነው በሕገመንግስቱ ከአነስተኛ ማዕድን ሥራዎች በሚገኘውን ገቢ ላይ የገቢ ታክስ የመሰበሰብ ሥልጣን የክልሎች ብቸኛ ሥልጣን ነው አንቀጽ የሸያጭ እና ኤክሳይዝ ታክሶች የሽያጭ እና ኤክሳይዝ ታክሶች በፌዴራልና በክልል መንግሥታት መካከል የተከፋፈለ ነው በፌዴራል መንግሥት ባለቤትነት ሥር በሆኑ የልማት ድርጅቶች ሽያጭ ምርቶች ወይም አገልግሎት በተመለከተ የፌዴራል መንግስት የሽያጭ ታክስ እና ኤክሳይዝ ታክስ የመጣል እና የመሰብሰብ ብቸኛ ሥልጣን ተሰጥቷል አንቀፅ ክለሎች ደግሞ በእነሱ ባለቤትነት ሥር ባሉ የልማት ድርጅቶች ላይ ተመሳሳይ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል አንቀፅ በተጨማሪም የክልል መንግስታት በክልላቸው ውስጥ በሚገኙ ግለሰብ ነጋዴዎችን ላይ የሽያጭ አና ኤክሳይዝ ታክስ የመጣልና የመሰበሰብ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል የንብረት ታክሶች ለታክስ አላማ ንብረቶች በተለያ መደቦች ሊመደቡ ይችላሉ በንብረት ላይ የሚጣል ታክስ የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ በመሬት እና በሕንፃ በአመታዊ የመሬት ዋጋ ታክስ ወይም መሬት ሲሸጥ የሚከፈል የመሬት ዝውውር ታክስ ሊጠቀሱ ይችላሉ የተፈጥሮ ሐብትን ፍለጋ በተመለከተ የሚጣሉ ልዩ ክፍያዎች ወይም ታክሶች ብዙን ጊዜ እንደ ንብረት ታክስ ይቆጠራሉ ለመኪናዎች ምዝገባ የሚከፈለው ክፍያ እንደ ንብረት ታክስ ሊቆጠር ይችላል በአንዳንድ ሐገሮች በሟች ንብረት ዋጋ ላይ የሚጣል የውርስ ታክስ ህፎከበልከር ከንብረት ታክስ ይመደባል በሐገራችን ከቤቶች ከመሬት ከደን እና ከማዕድን ሥራዎች ጋር በተያያዘ የሚጣሉና የሚሰበሰቡ ታክሶች እንደ ንብረት ታክስ የሚቆጠሩ ናቸው ከእነዚህ ውስጥ የክልል መንግስታት በእነሱ ባለቤትነት ሥር ባሉ ቤቶች የመሬት መጠቀሚያ ከደን የሚገኝ ሮያሊቲ አና በዝቅተኛ የማዕድን ሥራዎች ላይ የሮያሊቲ ክፍያዎችን መወሰንና መሰብሰብ ሥልጣን አሏቸው የአገልግሎት እና ሌሎች ክፍያዎች የኢፌድሪ ሕገመንግስት የፌዴራል እና የክልል መንግስት የታክስ ሥልጣን በሚደነግጉ አንቀጾች ስር የአገልግሎት ክፍያዎች እና የቴንብር ቀረጥ የመወሰንና የመሰብሰብ ሥልጣን የማን እንደሆነ በግልፅ ደንግጓል የአገልግሎት ክፍያዎች እና የቴንብር ቀረጥ አገልግሎቱ በሚሰጥበት ቦታ መሰብሰብ አለባቸው ይሔም ከአመቺነት አንፃር ነው ይህም ማለት አገልግሎቱን የሰጠው የፌዴራል መስሪያ ቤት ከሆነ የፌዴራል መንግስት ክፍያውን ይወሰናል ይሰበስባል በተመሳሳይ አገልግሎቱን የሰጠው የክልል መሥሪያ ቤት ከሆነ የክልል መንግስት ክፍያውን ይወስናል ይሰበስባል ማለት ነው በዚሁ መሰረት በሕገመንግስቱ የፌዴራል አንቀጽ አና የክልል መንግስታት አንቀጽ እያንዳንዳቸው ከሚሰጧቸው ፈቃዶችና አገልግሎቶች የሚመነጩ ክፍያዎችን የመወሰንና የመሰበሰብ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል እንዲሁም የፌዴራል የቴምብር ሽያጭ መጣል እና የመሰብሰብ ስልጣን ለፌዴራል መንግስት የተሰጠ ነው የጋራ የታክስ ሥልጣን ርከርህቨክከ። ይሪዕዕፀታ ዕድረጅዶቻ ዖሃሯድ ረፉ ይ ለና ባጎ ሰሰሶኖቻ ዖሥፖረፍ ድረሻ ይ ዘረና ዖጃዖያጭ ፖታጳዕ ዕጋጋራ ይፖጎታደፀይፅሪዕባታ ፅያሯሥፖኛ ዖማሪድሃ ሥሯዎሥቻ ያማናፖውም ሃፔፖርሷያምና ደጋሃ ሥራዎዎቻ ይ ያደ ረና ይሮዕሏጀ ፍደመቻ ዕጋራ ይፕላታ ይፅዕዕታ ከዚህ ድንጋጌ መረዳት እንደሚቻለው የጋራ የታክስ ሥልጣን ከሚመለከታቸው ታክሶች ውስጥ አንዱ በፌዴራል መንግስትና ክልሎች በጋራ የሚቋቋሙ የልማት ድርጅት ላይ የሚጣሉ ታክሶች ሲሆኑ ታክሶቹም የንግድ ትርፍ ግብር የሥራ ግብር የሽያጭና ኤክሳይዝ ታክስ ናቸው የልማት ድርጅቶቹም የፌዴራል ሥርዓቱ ከተመሰረተ በኃላ የፌዴራል መንግስት እና ክልሎች በጋራ የሚያቋቁሟቸው እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል በሌላ በኩል ከ ጀምሮ የመንግስት የኢኮኖሚ ፖሊሲ አቅጣጫ በነፃ ገበያ መርህ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት ከክልሎች ጋር አዲስ የጋራ ልማት ድርጅቶችን ከማቋቋም ይልቅ ነባር የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል እያዛወረ ይገኛል የፌዴራል ሥርዓቱ ከተመሰረተ በኋላ የፌዴራል መንግስት እና የክልሎች በጋራ ያቋቋሟቸው የልማት ድርጆቶች የሉም ስለዚህ በተግባር በሕገ መንግስቱ አንቀጽ መሰረት በፌዴራል መንግስት እና ክልሎች በጋራ የሚጣል እና የሚሰበሰብ ታክስ አለ ለማለት አይቻልም የጋራ ታክስ ሥልጣን የሚመለከታቸው ሁለተኛው የታክስ አይነቶች በድርጅቶች እና በባለአክስዮኖች የትርፍ ድርሻ ላይ የሚጣሉና የሚሰበሰቡ ሲሆነ የታክሶቹም ንግድ ትርፍ ግብርና የሸያጭ ታክስ ናቸውየንግድ ትርፍ እና የሽያጭ ታክስ የሚመለከታቸው ድርጅቶችም የአክስዮን ማህበር ከ ርሄጻዉሃ እና ሐላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርዐፇፎዖ እህጠቨዉጪ ርዐጠዌጸጻዉሃ መሆናቸው በህገመንግስት ጉባኤ ላይ የተደረገው ውይይት መረዳት ይቻላል ስለዚህ የጋራ የታክስ ሥልጣን በግለሰብ ነጋዴዎች ቼሄከሯ አና የሽርክና ማህበርን ከሯ የሚመለከት አይደለም ሶስተኛው የጋራ የታክስ ሥልጣን የተፈጥሮ ሀብትን የሚመለከት ነው በሕገመንግስቱ አንቀጽ መሰረት ከፍተኛ የማዕድን ሥራዎች አና ማናቸውም ፔትሮሊየምና የጋዝ ሥራዎች ላይ የገቢ ግብር እና ሮያሊቲ ክፍያዎችን መጣልና መሰብሰብ የፌዴራል እና የክልሎች የጋራ ሥልጣን ነው ብዙ ፌዴሬሽኖች በተፈጥሮ ሀብት ላይ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን ለፌዴራል መንግስት ይሰጣሉ የኢፌድሪ ሕገመንግስት በተፈጥሮ ሀብት ላይ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ የፌዴራል መንግስት ብቸኛ ሥልጣን አድርጎ አልሰጠም ከጥቂት በስተቀሮች በስተቀር ይህ የታክስ ሥልጣን የጋራ ነው በሕገመንግስቱ አንቀጽ በግልጽ እንደተመለከተው በማናቸውም ፔትሮሊየምና የጋዝ ሥራዎች ላይ የገቢ ግብር እና የሮያሊቲ ክፍያዎች መጣልና መሰብሰብ የፌዴራል መንግስቱ እና የክልሎች የጋራ ሥልጣን ነው የማዕድን ስራዎችን በተመለከተ ግን የታክስ ሥልጣኑ በሁለት ቦታ የተከፈለ ነው አንደኛው የክልሎች ብቸኛ የታክስ ሥልጣን ሲሆን ሁለተኛው የጋራ የታክስ ሥልጣን ነው ክፍፍሉም የተመሰረተው በማዕድን ሥራዎቹ መጠን ላይ መሆኑ መገንዘብ ይቻላል በዚሁ መሰረት ሕገመንግስቱ የማዕድን ሥራዎችን ከፍተኛና ዝቅተኛ ብሎ ከፋፍሏል ቀደም ሲል እንዳየነው በዝቅተኛ የማዕድን ሥራዎች ላይ የሮያሊቲ ክፍያዎችን መወሰንና መሰብሰብ የክልሎች ብቸኛ ሥልጣን ነው የፌደራል እና የክልሎች የጋራ የታክስ ሥልጣን የሚመለከተው ከፍተኛ ማዕድን ሥራዎች ላይ የሚጣሉና የሚሰበሰቡ የገቢ ግብር እና የሮያሊቲ ክፍያዎችን ብቻ ነው ከፍተኛው እና ዝቅተኛው የማዕድን ሥራዎች ምን እንደሆኑ በአዋጁ ቁጥር እና ደንብ ቁጥር በዝርዝር ተመልክቷል በአጠቃላይ የተፈጥሮ ሀብት ላይ የሚጣሉና የሚሰበሰቡ ታክሶችን በተመለከተ የታክስ ሥልጣኑ ክፍፍል የተፈጥሮ ሀብት ባለቤትነት መብት የመንግስትና የሕዝብ ብቻ ነው የሚለውን የሕገመንግስቱን አንቀጽ መሰረት ያደረገ ነው ለማለት ይቻላል ስለዚህ በሕገመንግስቱ አንቀጽ እና የተጠቀሱትን ታክሶች የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን የጋራ በመሆኑ እነዚህን ታክሶች የፌዴራል መንግስት ብቻውን ወይም የክልል መንግስታት ብቻቸውን መጣልና መሰብሰብ አይችሉም ሌላው መታየት ያለበት ነጥብ የጋራ ታክስ ሥልጣን ገጽታዎች ናቸው የጋራ የታክስ ስልጣን ከሚደነግገው የህገመንግስቱ አንቀጽ መረዳት እንደሚቻለው የጋራ ታክስ ሥልጣን ሁለት ገጽታዎች አሉት እነሱም ታክሶችን መጣል እና መሰብሰብ ናቸው ማለትም የጋራ ታክስ ሥልጣን ገጽታ የሚጣለው እና የሚሰበስበውን የታክስ ገቢ መጠቀምንርርፎፅ ፔዕዝፍ ህኳ የክ ሯርፀጠ የሚያጠቃልል አይደለም በመሆኑም የፌዴራል መንግስትም ሆነ የክልል መንግስታት በጋራ ታክስ ሥልጣን መሰረት ከሚጣሉት እና ከሚሰበሰቡት ከታክሶች የሚገኘውን ገቢ የመወሰን ሥልጣን የላቸውም በጋራ ታክስ ሥልጣን መሰረት ከሚጣሉት እና ከሚሰበሰቡት ታክሶች በሚገኘው ገቢ ላይ የመወሰን ሥልጣን ያለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው ፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራል መንግስትና የክልሎች የጋራ የተባሉ ገቢዎች በሁለቱ የመንግስት እርከኖች መካካል የሚከፋፈልበትን ሁኔታ የመወሰን ሥልጣን በሕገመንግስቱ ተሰጥቶታል አንቀጽ በፌዴራል ሥርዓት የታክስ ገቢን በሁለቱ የመንግስት እርከኖች መካካል እንዲከፋፈል የማድረጉ ሥርዓት ዉክጨቬ ይባላል የታክስ ክፍፍሉ ሥርዓት እንደ ሐገሩ ይለያያል ለምሳሌ በሕንድ የፌዴራል መንግስቱ ታክሶችን ይጥላል ይሰበስባል ገቢው ግን ከክልል መንግስታት ጋር የሚከፋፈል ነው በኢፌድሪ ህገመንግስት የታክስ ክፍፍል ሥርዓቱ ከሕንድ የተለየ ነው የታክስ ክፍፍሉ ሥርዓት የሚመለከታቸው የታክስ ገቢዎች በአንዱ የመንግስት እርከን ብቻ የሚጣሉና የሚሰበሰቡ አይደሉም በመሆኑም ከኢፌድሪ ሕገመንግስት አንጻር የታክስ ገቢ ክፍፍል ማለት የጋራ ከተባሉ ታክሶች የሚያገኘውን ገቢ መከፋፈል ብቻ የሚመለከት ሳይሆን የጋራ የተባሉትን ታክሶችን በጋራ መጣልና መሰብሰብን የሚያጠቃልል ነው ለ ከጋራ ታክስ ሥልጣን ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮች የህገመንግስቱ አንቀጽ ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮችን ተፈፃሚ የሚያደርግ ነው እነዚህም የታክስ አጣጣል እና አሰባሰብ ናቸው ታክስ የመጣል ሥልጣንም በተወሰነ ገቢ ላይ ሊሰበሰብ የሚገባውን የታክስ መጠን መወሰን እና ታክስ ከፋዩ ላይ ግዴታን መጣልና የሚያመለክት መሆኑን ቀደም ሲል ተመልክተናል የጋራ የታክስ ሥልጣንን የሚደነገገው የህገመንግስቱ ድንጋጌ ሁለት መሰረታዊ ችግሮች አሉበት ለማለት ይቻላል አንደኛው ከመርህ አንፃር የሚታየው ነው የፌዴራሉ መንግስት ከእያንዳንዱ ክልል ጋር በየጊዜው በሚያደርገው ስምምነት የሚመሰረቱ ኩባኒያዎች በባህርያቸው ሥርጭታቸው በአንዱ ክልል የሚወሰን አይደለም በመሆኑም እያንደንዱ ኩባኒያ ከየክልሉ ጋር በሚያደርገው ስምምነት ቢመሰረት እንቅስቃሴያቸው በአንድ ክልል የተወሰነ ስለማይሆን በታክስ አያያዝ ክሬዬበፀ ረገድ በአኩልነት መታየት ስላለባቸው አንድ አገራዊ ታክስ መጣኔ ሊገዛቸው ይገባል በሌላ በኩል ኩባኒያዎችበነዳጅበጋዝና በማዕድን ስራ ላይ የተሰማሩትን ጨምሮ ከእያንዳንዱ ክልል ጋር በጋራ በሚወሰን መጣኔ ታክስ ይክፈሉ ቢባል የካፒታል ሥረጭት ችግር ከማስተከሉም በላይ የዚህ ዓይነቱ ኩባኒያዎች አገራዊ ባህርይ ያላቸው በመሆኑ በተወዳዳሪነታቸው ላይ ተፅዕኖ የሚያሳርፍ ይሆናል በመሆኑም በኩባኒያዎች ገቢ ላይ የተለያዩ የታክስ መጣኔ መወሰን ለኢኪኖሚ ምክንያት ትክክል አይሆንም በአንድ አቋም ላይ ያሉ ታክስ ከፋዮች በአንድ አይነት መጣኔ ታክስ መክፈላቸው የታክስን ገለልተኝነት ይጠብቃል ይህ ደግሞ ትክክለኛ የኢኮኖሚ አመራር ያሰርፃል የጋራ ታክስ ሥልጣን የሚደነግገው የህገመንግስቱ አንቀጽ ከእነዚህ መርሆች አንጻር ሲፈተሽ ችግር ያለበት ሆኖ እናገኘዋለን ሁለተኛው ከተግባር አንፃር ያለበት ችግር ነው የሕገመንግስቱ አንቀጽ ከተግባር አንፃርም መሰረታዊ ችግር ያለበት ነው ችግሩም በጋራ መጣልና እና መሰብሰብ ከሚለው ሐረግ የሚመነጭ ነው ቀደም ሲል እንደተመለከተው ከታክስ ጋር በተያያዘ መጣል ህሃ የሚለው ቃል በተወሰነ ገቢ ላይ ሊሰበሰብ የሚገባውን የታክስ መጠን መወሰን እና ታክስ ከፋዩ ላይ ግዴታ መጣልን የሚመለከት ነው የታክስ መጣኔ የሚወሰነው በአዋጅ ብቻ ነው አዋጁ ደግሞ የሚወጣው በሕግ አውጪው አካል ማለትም እንደአግባብነቱ በፌዴራል መንግስት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በክልል ምክር ቤቶች ስብሰባ ነው በሕግመንግስቱ አንቀጽ ሥር በተደነገገው መሰረት በጋራ ታክስ በሚጣልባቸው ገቢዎች ላይ የታክሱ መጣኔ ሊወሰን የሚችለው ከላይ እንደ ተጠቀሰው በአዋጅ ስለሚሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በክልል ምክር ቤቶች ስብሰባ ነው በሕገመንግስቱ አንቀጽ ስር በተደነገገው መሰረት በጋራ ታክስ በሚጣልባቸው ገቢዎች ላይ የታክሱ መጣኔ ሊወሰን የሚችለው በአዋጅ ስለሚሆን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና የእያንዳንዱ ክልል ምክር ቤት በየጊዜው የጋራ ስብሰባ በማድረግ ውሳኔ ማስተላለፍ ይኖርባቸዋል ይህ ደግሞ በተግባራዊ ችግሮች ምክንያት ተፈፃሚ ሊሆን የሚችል አይደለም የታክስ አሰባሰብ መታየት ያለበት ከመብት ወይም ከሥልጣን አንፃር ሳይሆን ከተግባር አመቺነት ነው በሕገመንግስቱ አንቀጽ መሰረት ታክሱ በጋራ ለመሰብሰብ አመቺ አይደለም ይህ አመቺ ሊሆን የሚችለው ታክሱን የመሰብሰብ ሥራ ለአንድ የመንግስት እርከን ከተሰጠ ብቻ ነው ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች የተነሳ በሕገመንግስቱ አንቀጽ ሥር የተደነገገው ተግባራዊ ሆኖ አያውቅም ድንጋጌውን ተግባራዊ እንዲሆን ለማድረግ ያለው ብቸኛው መፍትሔ ማሻሻል መሆኑ ታምናበት በ ዓም ማሻሻል ሥራ ተጀምሮ የማሻሻያ ረቂቁም ቀርቦ የህዝብ ተወካዮች ምር ቤት የማሻሻያ ረቂቁን መጋቢት ዓም በሰላሳ ስምንተኛው መደበኛ ስብሰባው በሙሉ ድምጽ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ደግሞ በሚያዝያ ዓም በሁለተኛው መደበኛ ጉባኤ ላይ በአንድ ድምጽ ፀድቋል በተጨማሪም ረቂቁ በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ሚያዝያ ፀድቋል ረቂቁ የማሻሻያው ሃሳቡም በሕገመንግስቱ አንቀጽ የተጠቀሱትን ታክሶች የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን የፌዴራል መንግስት እንዲሆን ነገር ግን ታክሱን የመሰብሰብ በተመለከተ የፌዴራል መንግስት ሥልጣኑን ለክልሎች በውክልና መስጠት እንደሚቻል የሚገልፅ ነው ነገር ግን ይህ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ለውይይትና ውሳኔ ለመላው ሕዝብና ለክልል ምክር ቤቶች ቀርቦ መጽደቅ አለመጽደቁ የሚታወቅ ነገር የለም ማሻሻያው ግን በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ አለመውጣቱን በእርግጠኝነት ለመናገር ይቻላል ይህ እንዳለ ሆኖ በአሁኑ ጊዜ በተግባር በህገመንግስቱ አንቀጽ አና ስር የተጠቀሱት ታክሶች የሚጣሉትና የሚሰበሰቡት በፌዴራል መንግስት ነው የመወያያ ጥያቄዎች በኢፌድሪ ህገመንግስት ተለይተው በፌዴራል መንግስት ወይም በክልል መንግስታት እንዲጣሉ እና እንዲሰበሰቡ የተደረጉ ታክሶች በተመለከተ የታክስ ሥልጣን ክፍፍሉ መሰረት ምንድነው። ተለይተው ያልተሰጡ የታክስ ሥልጣኖች ሀል የኢፌዴሪ ህገመንግስት የታክስ ሥልጣንን ክፍፍልን በተመለከተ የገቢ ምንጮችን የመለያየት «ዌኳ ዐ ሇፀክ ህር ዘዴን የተከተለ ነው የታክስ አይነቶችና መሰረቶች ላይ በመመስረት ሕገመንግስቱ ለፌዴራልና ለክልል መንግስታት የታክስ ሥልጣን ብቸኛና የጋራ በማለት ለያይቶ ደንግጓል ቀጥሎ መታየት ያለበት ነጥብ አዲስ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን የማነው የሚለው ነው ብዙ ፌዴሬሽኖች አዲስ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን ለፌዴራሉ መንግስት ይሰጣሉ ለምሳሌ ሕንድና ብራዚልን መጥስ ይቻላል የሕንድ ሕገ መንግስት በጋራ ታክስ ሥልጣን ዝርዝር ወይም በክልል መንግስታት የታክስ ሥልጣን ዝርዝር ውስጥ ያልተጠቀሱ ታክሶች የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን የፌዴራል መንግስቱ ነው በሌላ በኩል አዲስ ታክስን የመጣልና ሥልጣን ለክልል መንግስታት የሚሰጡ ሐገሮችም አሉ ለምሳሌ አሜሪካን መጥቀስ ይቻላል በአሜሪካ በሕገመንግስቱ ለፌዴራል መንግስት በግልፅ ያልተሰጡ ሥልጣኖች የክልል መንግስታት በመሆኑ ክልል መንግስታት በህገመንግስቱ ተለይተው ያልተሰጡ ታክሶች ላይ ሥልጣን አሏቸው ተለይተው ያልተሰጡ የታክስ ሥልጣኖችን በተመለከተ የኢፌድሪ ሕገ መንግስት ከላይ ከተጠቀሱት ፌዴሬሽኖች ለየት ይላል ሕገመንግስቱ እንደ ሌሎች ፌዴሬሽኖች አዲስ ታክስን የመጣል ሥልጣን የፌዴራል መንግስት ወይም የክልል መንግስት ነው በማለት ቁርጥ ያለ መልስ ከመስጠት ይልቅ በሕገመንግስቱ ተለይተው የፌዴራል መንግስት ወይም የክልሎች ብቸኛ የታክስ ሥልጣን ወይም የጋራ ያልተባሉ ታክሶች ላይ እንዴት ውሳኔ እንደሚሰጥ ብቻ ይደነግጋል ይህን አስመልክቶ አንቀፅ እንደሚከተለው ይነበባል ዝማጂሂ ሕመጋዕሥ ፇፈልፀሦው ይሳሦሠፅው ታፖታዕና ፇረ ቦዖመጋሟሳ ሥጳኋማኖዎፇቻ ያሟመሰፅጎፖ ያፌዴሪሃ ምረ ይና ይእ ፇወጎሃዶቻ ምረ ይሥ ጋራ ዕ ያሥፅታታፖ ጎነፖሦኛ ድምሄ ይወፅናታ ከዚህ መረዳት እንደሚቻለው በህገመንግስቱ ተለይተው ያልተሰጡ ታክሶችን ወይም አዲስ ታክሶችን የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን በሁለቱ ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ የሚወሰን ነው ስለዚህ ሁለቱም የመንግስት እርከኖች በሕገመንግስቱ ውስጥ ተለይተው ከተሰጣቸው የታክስ አይነቶች ውጪ አዲስ ታክሶችን መጣልና መሰብሰብ አይችሉም በሕገመንግስቱ ውስጥ ያልተጠቀሱ ማንኛውም የታክስ አይነት መጣልና መሰብሰብ በቅድሚያ የሁለቱን ምክር ቤት ውሳኔ የሚጠይቅ ነው በዚሁ መሰረት ሁለቱም ምክር ቤቶች በጋራ በሚያደርጉት ስብሰባ አዲስ ታክሶችን የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን የፌዴራሉ መንግስት ብቸኛ ሥልጣን ወይም የክልሎች ብቸኛ ሥልጣን ወይም የጋራ እንዲሆን ሊወስኑ ይችላሉ ይህ ከሆነ ብቻ ነው የፌዴራል ወይም የክልል መንግሥታት የታክስ ሥልጣን ሊሰፋ የሚችለው በተግባርም በሕገመንግስቱ ተለይተው ያልተሰጡ የታክስ ሥልጣኖችን በተመለከተ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት በጋራ ባደረጉት ስብሰባ በተለያየ ጊዜ ውሳኔ ሰጥተዋል ለምሳሌ ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ተርን ኦቨር ታክስን መጥቀስ ይቻላል አነዚህ ታክሶች በህገመንግስቱ የፌዴራል መንግስት ወይም የክልል መንግስት ብቸኛ የታክስ ሥልጣን ወይም የጋራ የታክስ ሥልጣን ዝርዝር ውስጥ አልተጠቀሱም ህገመንግስቱ ከፀደቀ በኋላ ግን ሁለቱ ምቤቶች በጋራ ባደረጉት ስብሰባ አነዚህ ታክሶችን የመጣል አና የመሰብሰብ ሥልጣን የፌዴራል መንግስት እንዲሆን በመወሰናቸው ምክንያት የፌዴራል መንግስት በአሁኑ ጊዜ ይህን የታክስ ሥልጣን ተግባራዊ እያደረገ ነው የጋራ እንዲሆኑ የተወሰኑ የታክስ ሥልጣኖችም አሉ ለምሳሌ የድርጅቶች ኤክሳይስ ታክስ የፈጠራ መብትን በማከራየት የሚገኝ ገቢ ድርጅት መጥቀስ ይቻላል በተጨማሪም ሁለቱ ምክር ቤቶች በጋራ በሚያደርጉት ስብሰባ አዲስ ታክሶችን የመጣል ሥልጣን የማን መሆን አለበት ብቻ ሳይሆን በሚጣሉት ታክሶች ገቢ ክፍፍል ላይም ውሳኔ ይሰጣሉ ለምሳሌ ተጨማሪ አሴት ታክስ እና ተርን ኦቨር ታክስ በተመለከተ የገቢ ክፍፍሉ ግለሰቦች ነጋዴዎች የሚመለከት ከሆነ ፌዴራል መንግስት ክልል መንግስት ጻ ድርጅቶች ር ፌዴራል መንግስት ዐክልል የፌዴራል መንግስት የልማት ድርጅት ፌዴራል መንግስት ክልል እንዲሆን ተወስኗል የመወያያ ጥያቄዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስ የድርጅቶች ኤክሳይስ ታክስ እና የፈጠራ መብትን በማከራየት የሚገኝ ገቢ ድርጅት በተጨማሪ በሕገ መንግስቱ ለፌዴራል መንግስት ወይም ለክልል መንግስት ብቸኛ የታክስ ሥልጣን ወይም የጋራ ተብለው ያልተጠቀሱ ታክሶች ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ አንቀጽ መሰረት በማድረግ በክልል መንግስት ወይም በፌዴራል መንግስት የሚጣሉና የሚሰበሰቡ ሌሎች ታክሶችን ጥቀሱ የሕገመንግስቱ አንቀጽ ድንጋጌ መኖር ጥቅሙ ምንድነው። ክፍል ሁለት የታክስ መዋቅር በኢፌድሪ መንግሥት መግቢያ በዚህ ክፍል በኢፌዴሪ መንግሥት ያሉ የታክስ አይነቶችን በዝርዝር እንመለከታለን በኢፌዴሪ መንግሥት ከሚጣሉና ከሚሰበሰቡ የታክስ አይነቶች ውስጥ የገቢ ታክስ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስኤክሳይዝ ታክስ ሱር ታክስ የቴንብር ቀረጥ እና የጉምሩክ ቀረጥ ተጠቃሽ ናቸው በዚህ ክፍል የምንመለከተው የገቢ ታክስ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቭር ታክስ ኤክሳይዝ ታክስ እና የቴንብር ቀረጥን ብቻ ይሆናል በሌላ በኩል የገቢ ታክስ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቭር ታክስ ኤክሳይዝ ታክስ እና የቴንብር ቀረጥን የሚመሰከቱ ህጎች ሰፊ ይዘት ያላቸው በመሆኑነ በዚህ አጭር ፅሑፍ እነዚህን ታክሶች የሚመለከቱ ሕጎችን አጠቃላይ ይዘት ሙሉ በሙሉ ማቅረብ የሚቻል አይደለም ስለዚህ ፅሑፉ ወይም ትምህርቱ የሚያተኩረው በህጎቹ በታቀፉ የተወሰነ ነጥቦች ላይ ብቻ ይሆናል በተለይም ትምህርቱ የሚያተኩረው ስለታክሶቹ ምንነትአጣጣል የታክስ ከፋዮች ግዴታን እና የታክስ ግዴታን አለመወጣት የሚያስከትለውን ኃላፊነት ላይ ይሆናል በዚሁ መሰረት ይህ ክፍል አምስት ንዑስ ክፍሎች አሉት በመጀመሪያው ንዑስ ክፍል በቅድመ ኢፌዲሪ ያለውን የታክስ መዋቅር በአጭሩ ይዳሰሳል በሁለተኛው ንዑስ ክፍል በኢፌዲሪ ያለው የታክስ መዋቅር በሁለት መደብ ማለትም ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ተብለው ይቀርባሉ በንዑስ ክፍል ሶስት ደግሞ የቴምብር ቀረጥ ይቀርባል በንዑስ ክፍል አራት የታክስ ወንጀሎች በመጨረሻው ንዑስ ክፍል ደግሞ የታክስ ይርጋ ይቀርባል በዚሁ መሰረት ሰልጣኞች ይህን ክፍል ካጠናቀቁ በላ በኢፌዴሪ መንግስት የሚጣሉ እና የሚሰበሱ የታክስ አይነቶች ላይ የተወሰነ ግንዛቤ ይጨብጣሉ በኢፌድሪ መንግስት ያለውን የታክስ መዋቅር ከቀድመ ኢፌድሪ ካለው የታክስ መዋቅር ጋር ያነጻጽራሉ የገቢ ታክስ ምንነት አጣጣል ማስከፈያ መጠን መጣኔ በቂ ግንዛቤ ይኖራቸዋል የገቢ ታክስ አይነቶችን አንድ በአንድ ይለያሉ የገቢ ታክስ ከፋዮች ግዴታ ይዘረዝራሉ የገቢ ታክስ ግዴታ አለመወጣት የሚያስከትለውን ኃላፊነት ጠንቅቀው ያውቃሉ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የተርን ኦቨር ታክስ ምንነትአላማ አጣጣል ያስረዳሉ የተጨማሪ እሴት ታክስና የተርን ኦቨር ታክስ ከፋዮች ግዴታና ይተነትናሉ የተጨማሪ እሴት ታክስና የተርን ኦቨር ታክስ ግዴታአለመወጣት የሚያስከትለውን ኃላፊነት ጠንቅቀው ያውቃሉ የኤክሳይዝ ታክስ ምንነት አላማ የሚከፈልበት ሁኔታና የሚከፈልባቸው ዕቃዎች እና የአከፋፈል ሥርዓት ያስረዳሉ የኤክሳይዝ ታክስ ከፋዮች ግዴታ ያውታሉ የኤክሳይዝ ታክስ ግዴታን አለመወጣት የሚያስከትለው ሐላፊነት ይረዳሉ የቴምብር ቀረጥ ህጋዊ መሰረትና አፈፃፀም ይገነዘባሉ የቴምብር ቀረጥ ህግን መተላለፍ የሚያስከትለውን ውጤት ይገነዘባሉ በታክስ ላይ ስለሚሰሩ ወንጀሎች በቂ ግንዛቤ ይጨብጣሉ ታክስ የመክፈል ግዴታ በይርጋ የሚታገድበትን ሁኔታ ይረዳሉ የታክስ መዋቅር በቅድመ ኢፌድሪ በአጭሩ በሀገራችን ታክስ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለው ነው ታክስ ከመቼ ጀምሮ መጣልና መሰብሰብ እንደተጀመረ በትክክል ባይታወቅም ብዙ ፀሐፊዎች ታሪኩን ከመንግስት ምስረታ ጋር ያቆራኙታል በቅድመ ኢፌድሪ የነበረውን የታክስ መዋቅር ከሐይለስላሴ ዘመን በፊት በሐይለስላሴ ዘመን በደርግ ዘመን በሽግግር መንግስት ዘመን ብሎ ከፋፍሎ በአጭሩ ማየት ይቻላል በዚህ መሰረት ከሐይለስላሴ ዘመን በፊት ያለው የታክስ ሥርዓት ዘመናዊ አልነበረም ታክስ የሚከፈለው በአይነት ነበር የዚህ ዘመን ታክስ የእህል ምርቶች የቤት እንስሳዎችና የቤት እንስሳዎች ውጤት የበግ ፀጉር ቅቤ ወተት የሚመለከቱ ነበር በሐይለስላሴ ዘመን ደግሞ የታክስ ሥረዓቱ ቀደም ሲል ከነበረው የተሻለ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ዘመናዊ አልነበረም በዚህ ዘመን በርካታ የታክስ ህጎች የወጡ ሲሆን እነዚህ ህጎችም የ ህገመንግስትን መሰረት ያደረጉ ነበር በዚህ ዘመን ከነበሩት የታክስ አይነቶች ውስጥ የገቢ ታክስ የመሬት ታክስ የትምህርት የጤና የእርሻ የመንገድ የጨው የትንባሆ የአልኮልየከብትአስራት የጉምሩክ ቀረጥየቴንብር ቀረጥ በዋነኝነት የሚጠቀሱ ናቸው በደርግ ዘመን ቀደም ሲል ሥራ ላይ ከነበሩ ታክሶች ውስጥ የመሬት ታክስ የትምህርት ታክስ የጤና ታክስ የኪራይ ገቢ ታክስአስራትየተባሉት የታክስ አይነቶች እንዲሰረዙ ተደርገዋል በሌሎች ላይም የተለያዩ ማሻሻያዎች ተደርጎባቸዋል በዚህ ዘመን ሲጣሉና ሲሰበሰቡ ከነበሩ የታክስ አይነቶች ውስጥ የገቢ ታክስ የከተማ መሬት ኪራይ ታክስ የከተማ ቤት ኪራይ ታክስ የገጠር መሬት መጠቀሚያና ክፍያ ኤክሳይዝ ታክስ ታራዛክሽን ታክስ የሽያጭ ታክስ የጉምሩክ ቀረጥ እና የቴንብር ቀረጥ በዋነኝነት የሚጠቀሱ ናቸው በሽግግር መንግስት ዘመን በክልሎች መቋቋም ምክንያት መሰረታዊ የታክስ ፖሊሲ ለውጥ ተደርጓል የተለያዩ ታክሶች ላይ ታክስ መጣኔው እንዲሻሻል ተደርጓል ለምሳሌ ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ የሚጣል ታክስ የንግድ ትርፍ ሥራ ታክስን መጥቀስ ይቻላል የታክስ መሰረት እንዲሰፉ ተደርጓል ለዚህም አዳዲስ ታክሶችን ተጥለዋል ለምሳሌ የማዕድን ገቢየካፒታል ንብረቶች በማስተላለፍ በሚገኝ ጥቅም ላይ የሚጣል የገቢ ታክስን መጥቀስ ይቻላል ወደ ውጭ በሚላኩ እቃዎች ቡና ሌጦ እና ቆዳ አንሰሳ የዝሆን ጥርስ እና ሌሎች ላይ የተጣሉት ታክሶች ከቡና በስተቀር እንዲነሱ ተደርገዋል በኢፌድሪ ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች በአሁኑ ጊዜ በስራ ላይ ላሉት የታክስ አይነቶች ሕጋዊ መሰረት ሕገመንግስቱ ነው ሕገመንግስቱን መሰረት በማድረግም የተለያዩ የታክስ አዋጆች ወጥተዋል አዋጆችን በመንተራስ የተለያዩ ደንቦች ተደንግገዋል መመሪያዎችም ወጥተዋል በሕገመንግስቱ እና ን በእነዚህ ሕጎች መሰረት ሥራ ላይ ያሉ የታክስ አይነቶችን በዝርዝር ከማየታችን በፊት ታክስን በተመለከተ በኢፌድሪ ዘመን የተደረጉ አንዳንድ ለውጦችን ጠቅለል ባለ መልኩ ማየቱ ጠቃሚ ነው ከእነዚህ ለውጦች ውስጥ ጥቂቶቹም የታክስ ማስከፈያው መጠን መቀነስ ለምሳሌ ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ የሚጣለው የታክስ ማስከፈያ መጠን ከ ወደ እንዲቀነስ ተደርጓል የጉምሩክ ቀረጥም ማስከፈያ መጠን እንዲሁ ቀንሷል ወደ ውጪ በሚላክ ቡና ላይ የተጣለው ታክስ ተነስቷል የሸያጭ ታክስ በተጨማሪ አሴት ታክስ እንዲተካ ተደርጓል ታክስን ከተከፋይ ሒሳብ ላይ ገቢ የማድረግ ሥርዓት ከ« ህቨፎኳከ ተግባራዊ አንዲሆን ተደርጓል የታክስ ከፋዩ መለያ ቁርጥ ተግባራዊ እንዲሆን ተደርጓል የታክስ መሰብሰብ ሥልጣንም ለገቢ ሚኒስቴር የተሰጠ ሲሆን ታክስ አስገቢው ባለሥልጣንም ግዴታቸውን በማይወጡ ታክስ ከፋዮች ላይ የሚፈለገውን ታክስ በቀጥታ በህግ አስገድዶ ለመሰብሰብ የሚያስችለው ሥልጣን እንዲኖረው ተደርጓል ቀጥተኛ ታክስ የገቢ ታክስ በኢፌድሪ መንግስት ከቀጥተኛ ታክስ ጎራ የሚመደበው የታክስ አይነት የገቢ ታክስ ነው ለማንኛውም አይነት ታክስ የህግ መሰረቱ ህገመንግስቱ በመሆኑ የገቢ ታክስ መሰረትም የሔው ህገመንግስት ነው በአሁኑ ግዜ የገቢ ታክስ የሚጣለው አና የሚሰበሰበው ህገመንግስቱን መሰረት በማድረግ በወጡ ሁለት ሕጎች ነው እነሱም የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር አና የሚኒስትሮች ምክር ቤት የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር ናቸው እነዚህ ሕጎች የገቢ ታክስን በተመለከተ ለአርባ ዓመት ሲሰራበት የነበረውን የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር አና በየጊዜው የተደረጉትን ማሻሻያዎች የተኩ ናቸው የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር ሁለት ምዕራፍ ክፍሎች እና አንቀጾች ያሉት ሲሆን የመጀመሪያው ክፍል መሰረታዊ ድንጋጌዎችን የያዘ ሲሆን ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ሥነስረታዊ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው ቀጥለን የመጀመሪያው ክፍል ስር አጠቃላይ ድንጋጌዎች ተብለው ከተቀመጡት ውስጥ መታየት ያለባቸውን አንዳንድ ነጥቦች እንመለከታለን መጀመሪያ የገቢ ታክስ ምንነት ምንነት የገቢ ታክስ ምንነትን ለመረዳት በመጀመሪያ ገቢ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ማየቱ ጠቃሚ ይሆናል ገቢ ለሚለው ቃል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም የለም ብዙ ሙሑሮች ወይም ኤክስፐርቶች ቃሉን በተለያየ መንገድ ይጠቀሙበታል በመሆኑም ገቢ የሚለው ቃል እንደ አገባቡ የተለያየ ትርጉም ሊይዝ ይችላል ይሔን አንድ ፀሐፊፁ ከ ፎቭፔፍ ህህ ሀጧፌ ፎክ ርቪሃ በፎክቨሺቧ ከሬ ርብል ጀርቧ ከ ፔጸበ«ሯህ ዕር የከፎቪ ዕህዉ ጀሔል ዐ ሯፍርሺዕቧ ቧጪ ዕርዕክርፎበፍ ፎወፈ ዕ ዝሇክከከ ርዐክፍፎቧልወ ወዉ በ ከበ ርዕሃሃ በማለት ገቢ ለሚለው ቃል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም ላይ መድረስ እንዳልተቻለ በጥሩ ሁኔታ ገልጾታል ስለዚህ የተለያደ ሙሑሮችና ኤክስፐርቶች ገቢ ለሚለው ቃል የሚሰጡት ትርጉም ከተሰማሩበት ሞያ አንጻር የሚታይ ነው ለምሳሌ የኢኮኖሚስት እና የሕግ ባለሙያ ለገቢ የሚሰጡት ትርጉም አንድ ላይሆን ይችላል እንዲሁም ገቢ ለሚለው ቃሉ የሚሰጠው ትርጉም አንደ ሐገሩ ሁኔታ ሊለያይ ይችላል ይዘቱም እንዲሁ በታክስ ሕግ ውስጥ እንኳ ገቢ ለሚለው ቃል ተቀባይነት ያለው አንድ ወጥ ትርጉም ለማግኘት አይቻልም ሐገሮች የሔን ችግር ለመፍታት የመረጡት ዘዴ በታክስ ሕግ ውስጥ ገቢ ለሚለው ቃል ትርጉም መስጠትን ነው በእኛም ሐገርም የተወሰደው አማራጭ ይሄው ነው ለታክስ አላማ የገቢ ግብር አዋጅ ገቢ ለሚለው ቃል የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል «ገቢ» ማለት ማናቸውም የኢኮኖሚ ጥቅም ሲሆን በመደበኛነት የተገኘ ባይሆንም ከማናቸውም ምንጭ በጥሬ ገንዘብ ወይም አይነት በማናቸውም መልክ ለግብር ከፋዩ የተከፈለው በስሙ የተያዘለትን ወይም የተቀበለውን ጥቅም ሁሉ ይጨመራል አንቀጽ ከዚህ እንደምንረዳው ገቢ የሚከተሉትን ነጥቦችን የያዘ ነው አነሱም ። የገቢውን መሰረት ታክስ ከፋዩ ገቢው በስሙ የተያዘለት ወይም የተቀበለው ሊሆን ይችላል ታክስ ከፋዩ ገና ወደፊት ሊያገኝ የሚችለው ገቢ ለገቢ ታክስ አላማ ገቢ በሚለው ትርጉም የሚሸፈን አይደለም አንድ ሰው ከላይ የተጠቀሱትን አምስት ነጥቦች የሚያሟላ ገቢ ማግኘቱ ከተረጋገጠ የገቢ ግብር የመክፈል ሕጋዊ ግዴታ አለበትአንቀጽ ባጭሩ የገቢ ታክስ ማለት አንድ ሰው በሚያገኘው ገቢ ላይ የሚጣል እና የሚሰበሰብ ታክስ ነው ለማለት ይቻላል ታክስ ከፋዩም ማንኛውም ግለሰብ ድርጅት ወይም ማህበር ሊሆን ይችላል አንድ ታክስ ከፋይ የሆነ ሰው የሚያገኘው ገቢ ሁሉ ታክስ የሚከፈልበት ላይሆን ይችላል አንድ ታክስ ከፋይ መክፈል ያለበትን የታክስ መጠን ለመወሰን ጥቅል ወይም ያልተጣራ ገቢ አና ታክስ የሚከፈልበት ገቢን መለየት ያስፈልጋል ጥቅል ወይም ያልተጣራ ገቢ ማንኛውም ኢኮኖሚያዊ ጥቅምን የሚመለከት አንቀጽ ሲሆን ታክስ የሚከፈልበት ገቢ ማለት ደግሞ በገቢ ግብር አዋጅን በአዋጁ መሰረት በሚወጡት ደንቦች ማናቸውም ወጪ እና ሌሉች ተቀናሽ ሂሳቦች ከተቀነሱ በኋላ የሚቀረው የገቢ መጠን ነወ አንቀጽ በመሆኑም ግብር የሚከፈልበት ገቢ የሚወሰነው አግባብነት ባላቸው ሕጎች መሰረት ከጥቅል ገቢ መቀነስ ያለባቸው ወጪዎች እና ሌሎች ተቀናሽ ሂሳቦች ከተቀነሱ በላ ነው ለምሳሌ የገቢ ግብር አዋጅ የገቢ ግብር የማይከፈልባቸው ገቢዎች በሄእየገቢ ግብር ከሚከፈልበት ገቢ ውስጥ የማይካተቱ ርፎቪሟዌ እና ተቀናሽ ወጪዎችን ክ ሯሯ ይደነግጋል ስለዚህ የገቢ ግብር የሚከፈልበትን ገቢ ለመወሰን መጀመሪያ ከጥቅል ገቢ ላይ ግብር የማይከፈልባቸው ገቢዎች ወይም የገቢ ግብር ከሚከፈልበት ገቢ ውስጥ የማይካተቱ ወይም ተቀናሽ ወጪዎችን መቀነስ አለባቸው ማለት ነው በአጭሩ ታክስ የሚከፈልበት ገቢ ማለት የገቢ ግብር መጠንን ለማስላት መሰረት የሆነ የገቢ መጠን ነው ለማለት ይቻላል ተፈጻሚነት ወሰን የገቢ ህግ ተፈጻሚነት ወሰን ለመገንዘብ የገቢ ታክስን የመጣል ሥልጣንን ለመወሰን የሚረዱ መርሆችን ማየቱ ጠቃሚ ይሆናል የገቢ ታክስን የመጣል ሥልጣንን ለመወሰን የሚረዱ ሶስት መርሆች አሉ አንደኛው የግዛት ወይም የምንጭ መርህ ነው በዚህ መርህ መሰረት የገቢ ግብርን የመጣል ሥልጣን የሚወሰነው የገቢው መሰረት ምንጭ በማየት ነው የገቢ ሥልጣንን ለመወሰን የገቢው መሰረት ምንጭ በማድረግ ከሆነ አንድ ሰው በአንደ ሐገር ውስጥ ነዋሪ ባይሆንም የገቢ ግብር ሊጣልበት ይችላል ሁለተኛው የነዋሪነት መርህ ነው በዚህ መርህ መሰረት የገቢ ግብርን ለመጣል የሚታየው የገቢው ባለቤት መኖሪያ ነው ገቢውን ያገኘው ሰው ነዋሪነቱ በአንድ ሐገር ውስጥ ከሆነ ያ ሰው በሚያገኘውን ገቢ ላይ የሚኖርበት ሐገር መንግሥት የገቢ ግብር የመጣል ሥልጣን ይኖረዋል ሶስተኛው የዜግነት መርህ ነው በዚህ መርህ መሰረት የገቢ ግብር ሥልጣን ለመወሰን የሚታየው ገቢውን ያገኘው ሰው ዜግነት ነው በዚህ መርህ መሰረት የሐገሪቱ ዜግነት ያለው ሁሉ መኖሪያው የትም ሆነ የት እንዲሁም የገቢ ምንጭ የሚገኝበት ግዛት የትም ሆነ የት በሚያገኘው ገቢ ላይ ግብር መክፈል አለበት ሐገሮች የገቢ ግብርን ለመጣል አንዱን ወይም ሁሉንም መርሆች በማጣመር ተግባራዊ ሊያደርጉ ይችትላሉ ወደ ሐገራችን ስንለመለስ ኢትዮጵያ የተከተለችው የነዋሪነት መርህን ነው አንቀጽ በመሆኑም በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆነ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲሁም በኢትዮጵያ ውጭ ባገኘው ገቢ ላይ ነዋሪ ለሆነበት ለኢትዮጵያ መንግስት የገቢ ታክስ የመክፈል ግዴታ አለበት ስለዚህ ታክስ ከፋይ ነዋሪነቱ በኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ የገቢ ምንጩ ከኢትዮጵያ ውስጥ ወይም ውጭ መሆኑ ልዩነት አያመጣም ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ከኢትዮጵያ ውጪ ባገኘው ገቢ ላይ ገቢው ለተገኘበት አገር ግብር የከፈለ መሆኑ ሲረጋገጥ በውጭ አገር የተከፈለው ታክስ እንዲካካስለት መጠየቅ ይችላል አንቀጽ በሌላ በኩል አዋጁ በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆኑ ሰዎችን በተመለከተ ተፈፃሚ የሚሆነው ኢትዮጵያ ውስጥ ባገኙት ገቢ ላይ ብቻ እንደሆነ ይደነግጋል ለምሳሌ ዋና መሥሪያ ቤቱ አሜሪካ የሆነ ድርጅት በኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ሥራ የሚከናውን ከሆነ በድርጅቱ ላይ ታክስ የሚጣለው በኢትዮጵያ ውስጥ በሚያገኘው ገቢ ላይ ብቻ ይሆናል ድርጅቱ በዋናው መሥሪያ ቤቱ በሚያገኘው ትርፍ ላይ ታክስ ሊጣል አይችልም ምክንያቱም ድርጅቱ በኢትዮጵያ ነዋሪ ስላልሆነ ነው ስለዚህ አለም አቀፍ ታክስን በተመለከተ የታክስ ከፋዩ መኖሪያ ወይም የገቢ ምንጩ መሰረት በኢትዮሏጴያ ውስጥ መሆን አለበት ከታክስ ከፋዩ ዜግነት ግን ታክስን ለመጣል መሰረት ሆኖ አያገለግልም የመወያያ ጥያቄዎች አንድ ታክስ ከፋይ በኢትዮጵያ ነዋሪ ነው የሚባለው መቼ ነው። ቀጥተኛ ያልሆኑ ታክሶች በኢፌድሪ መንግስት ከሚጣሉ እና ከሚሰበሰቡ የታክስ አይነቶች ውስጥ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክሰ ኤክሳይስ ታክስ የጉምሩክ ቀረጥ እና ሱር ታክስ ቀጥተኛ ካልሆኑ የታክስ አይነቶች ጎራ የሚመደቡ ናቸው ከእነዚህ ውስጥ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስ እና ኤክሳይስ ታክስ ቀጥለው ይቀርባሉ መጀመሪያ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተጨማሪ እሴት ታክስ በልኸ ሀ ምንነት ተጨማሪ እሴት ታክስ ከሽያጭ ታክስ ጎራ የሚመደብ የታክስ አይነት ነው ልበ ከዕህፀ ተጨማሪ እሴት ታክስ ርሀህበህኪፎዝፔፎክዬ ርከ ዕቧ የከወ ሇ ክበሄ ባዉቧቧጴርበሬፀ ቧ ጺ ። ተጨማሪ እሴት ታክስ በአንድ ደረጃ ብቻ የሚከፈል ሳይሆን በአያንዳንዱ ደረጃ የሚከፈል ታክስ መሆኑን ከዚህ ምሳሌ በቀላሉ መረዳት ይቻላል ታክሱም በእያንዳንዱ ደረጃ ማለትም ከጥሬ አቃ አቅራቢ ጀምሮ እስከ ችርቻሮ ሻጩ የተከፋፈለ መሆኑን አንዲሁም በእያንዳንዱ ደረጃ ታክሱ የሚሰላው በእቃው አጠቃላይ ዋጋ ላይ ሳይሆን በተጨማሪ እሴቱ ወይም ዋጋ ላይ ብቻ መሆኑንም መረዳት ይቻላል ተጨማሪ አሴት ታክስ በብዙ ሐገሮች ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ውሎ አድሯል በእኛ ሀገር ግን ተግባራዊ መሆን የጀመረውም በቅርብ ጊዜ ነው ተጨማሪ እሴት ታክስ በሕገመንግስቱ አንቀጽ መሰረት በማደረግ በፌዴራል መንግሥት የሚጣል እና የሚሰበሰብ ታክስ ነው ከ በፊት በአዋጅ ቁጥር እንደተሻሻለው የሚጣልና የሚሰበሰብ የሽያጭ ታክስ ነበር ይህ ሽያጭ ታክስ በተጨማሪ እሴት ታክስ ተተክቷል ስለዚህ ተጨማሪ አሴት ታክስ ለሐገራችን ኢኮኖሚ አዲስ ነው ለማለት ይቻላል ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚመለከቱ ሁለት ሕጎች አሉ እነሱም የተጨማሪ አሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር አና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተጨማሪ እሴት ታክስ ደንብ ቁጥር ናቸው ሽያጭ ታክስን በተጨማሪ እሴት ታክስ መተካት ያስፈለገበት ምክንያት በአዋጁ መግቢያ ላይ በግልፅ ተመልክቷል አንዱ ምክንያት የሽያጭ ታክስ የሽያጭ እንቅስቃሴ በተከናወነ ቁጥር በሚፈጠረው ተጨማሪ እሴት ላይ ታክስ መሰብሰብ ስለማያስችል ነው ሽያጭ ታክስ የሚሰበሰበው ብዙን ጊዜ በጅምላ ሽያጭ ወይም በችርቻሮ ሽያጭ ደረጃ ነው ታክሱም የሚጣለው በዕቃው አጠቃላይ ዋጋ ላይ ነው የሽያጭ ታክስ ከአምራቹ እስከ ችርቻሮ ሻጩ ድረስ በሚካሔደው የንግድ ልውውጥ ውስጥ በአንድ ደረጃ ብቻ የሚጣል በመሆነ በየደረጃው በሚፈጠረው ተጨማሪ እሴት ዋጋ ላይ ታክስ መሰብሰብ አያስችልም ተጨማሪ እሴት ታክስ ግን የመክፈል ሐላፊነት በተለያዩ ደረጃዎች የተከፋፈለ በመሆኑ የሽያጭ እንቅስቃሴ በተከናወነ ቁጥር የሚፈጠረው ተጨማሪ እሴት ዋጋ ታክስን ለመሰብሰብ የሚያስችል ነው ይህ ምን ማለት እንደሆነ ከላይ የቀረበውን ምሳሌ ተመልከቱ ሁለተኛው ምክንያት አስተዳደራዊ አመቺነት ነው ተጨማሪ አሴት ታክስ መክፈል ግዴታ በተለያዩ ታክስ ከፋዮች መካከል የተከፋፈለ በመሆኑ ታክሱን ላለመክፈል የሚደረገው ጥረት አነስተኛ ነው በሬል ሇዝ በሌላ አገላለፅ የተጨማሪ አሴት ታክስ አሰባሰብ ሥረዓት ታክስ ከፋዩ ታክሱን ላለመክፈል የሚደረገውን ተግባር ለመቆጣጠር በቀላሉ የሚያስችል ነው ሶስተኛው ምክንያት ተጨማሪ እሴት ታክስ ቁጠባንና ኢንቨስትመትን የሚያበረታታ መሆኑ ነው ለዚህ መሰረቱ ተጨማሪ እሴት ታክስ በካፒታል አቃዎች ላይ የሚጣል ታክስ ስላልሆነ ነው ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚጣለው በፍጆታ እቃዎችና አገልግሉቶች ላይ ነው የካፒታል አቃዎችን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ውጪ ማድረጉ ቁጠባንና ኢንቪስትመትን ያበረታታል ለ የተጨማሪ እሴት ታክስ ቅድመ ሁኔታዎች በሀገራችን ዕቃ አቅርቦት ጩሄቨ ዐ ወይም አገልግሎት መስጠት ዐጠይእከኢ ያ ገጨ በተጨማሪ እሴት ታክስ ለመታቀፉ መሟለት ያለባቸው ሁኔታዎች የፅቃ አቅርቦት እናወይም አገልግሎት ተጨማሪ እሴት ታክስ የመክፈል ግዴታ ባለበት ሰው መከናወን አለበት ተጨማሪ እሴት ታክስ መክፈል ግዴታ በሌለበት ነጋዴ የተከናወነ የአቃ አቅርቦት በተጨማሪ እሴት ታክስ አይሸፈንም ለተጨማሪ እሴት ታክስ አላማ ታክሱን መክፈል ግዴታ ያለባቸው ። ሸማች ተርን ኦቨር ታክስ ኗ ብር አጠቃላይ ተርን ኦቨር ታክስ ብር ይሆናል ማለት ነው ከዚህ መረዳት እንደሚቻለው አንድ ፅቃ ከአንድ ጊዜ በላይ ታክስ የሚጣልበት መሆኑን ነው መ ነፃ የሆኑ ግብይቶች በተርን ኦቨር ታክስ አዋጅ መሠረት የሚከተሉት ግብይቶች ከታክስ ነፃ ናቸው ቢያንስ ሁለት ዓመት ያገለገለ መኖሪያ ቤት ሽያጭ እና የመኖሪያ ቤት ኪራይ የፋይናስ አገልግሎቶች በሃይማኖት ድርጅቶች የሚሰጡ የእምነት ወይም ከአምልኮት ጋር የሚገኛኙ አገልግሎቶች የሕክምና አገልግሎቶች እና በሐኪም የሚታዘዙ መድኃኒቶች በትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የማሰተማር አገልግሎቶች እንዲሁም ለሕፃናት የሚሰጡ አገልግሎቶች ለሰብዓዊ ዕርዳታ የሚውሉ ዕቃዎች አገልግሎቶች የኤሌክትርክ የኬሮሲን እና ውፃ አቅርቦት የትራንስፖርት አገልግሎቶች ማንኛውም የሥራ እንቅስቃሴ ለማከናወን ለሚሰጥ ፈቃድ ለመንግስት የሚፈጸም ክፍያ ከስልሳ በመቶ በላይ ሠራተኞቹ አካል ጉዳተኛች የሆኑበት አካል ጉዳተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ድርጅት የሚያቀርባቸው ዕቃዎችና አገልግሉሎቶች መፃሕፍት ሰ ግዴታዎች እና ግዴታዎችን አለመወጣት የሚያስከትለው ሐላፊነት የተርን ኦቨር ታክስ ከፋይ የተለያዩ ግዴታዎች አለበት አንዱ ግዴታ ታክሱን ማስታወቅና ታክሱን መክፈል ነው የተርን ኦቨር ታክስ ከፋይ የታክሱን ስሌት በትክክል በማከናወን የታክሱን ማስታወቂያ በሕጉ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ ለታክሱ ባለስልጣን በማቅረብ ታክሱን የመክፈል ግዴታ አለበት የሒሳብ ጊዜውም እንደ ግብር ከፋዮቹ ደረጃ ይለያያል አንቀጽ ታክሱ የማስታወቂያ ማቅረቢያ ጊዜውም እያንዳንዱ የሂሳብ ጊዜ በተጠናቀቀ በአንድ ወር መክፈል አለበት ስለዚህ ተርን ኦቨር ታክስ ታክስ ከፋዩ ራሱ ታክሱን በማሳወቅ የሚከፊል ነው ሁለተኛው የተርን ኦቨር ታክስ ከፋዩ ግዴታ ሒሳብ መዝገብ መያዝ ነው ቀደም ሲል በገቢ ግብር አዋጅ ውስጥ የሂሳብ መዝገብ መያዝ ግዴታ ያለባቸው ታክስ ከፋዮች ተመልክተናል በገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ መሠረት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የተጣለባቸው ታክስ ከፋዮች ለተርን ኦቨር ታክስ አወሳሰን እንዲያገለግል በገቢ ግብር አዋጅ የታዘዘውን የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ አለባቸው በዚህ መሰረት በገቢ ግብር አዋጅ መሰረት የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ተብለው የሚታወቁ አና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የመመዘገብ ግዴታ የሌለባቸው ታክስ ከፋዮች እንዲሁም የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች የሆኑ የተርን ኦቨር ታክስ ከፋዮች የሒሳብ መዝገብ መያዝ ግዴታ አለባቸው የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ግን የሒሳብ መዝገብ መያዝ ግዴታ የለባቸውም ሌላው የተርን ኦቨር ታክስ ከፋይ ግዴታ ለውጦችን ማስታወቅ ነው ረ አወሳሰን ተርን ኦቭር ታክስ በመረጃ ወይም በቁርጥ ሊወሰን ይችላል ከላይ እንደተመለከተው አንድ የተርን ኦቭር ታክስ ታክስ ከፋዩ ራሱ ታክሱን በማሳወቅ የሚከፈል የታክስ አይነት ነው በተርን ኦቨር ታክስ አወሳሰን ሲባል ሕጉ የተወሰኑ የተርን ኦቨር ታክስ ከፋዮች የሒሳብ መዝገብ እንዲይዙ ግዴታ ይጥላል የታክስ ባለስልጣኑም የታክስ ከፋዩ ያሳወቀው ታክስ ትክክል ለመሆኑ ለማረጋገጥ የታክስ ከፋዩን ሒሳብ መዛግብትና ሌሎች ሰነዶችን የመመርመር ሥልጣን አለው የታክስ ባለስልጣኑ በምርምራው ታክስ ከፋዩ ሊከፍል የሚገባውን ታክስ አሳንሶ ያስታወቀ መሆኑን ከደረሰበት ተጨማሪ የታክስ ውሳኔ ይሰጣል በመርህ ደረጃ የሒሳብ መዝብ መያዝ ግዴታ ያለባቸውን ታክስ ከፋዮች ታክስ የሚወስነው የሒሳብ መዛግብትና ሌሎች ደጋፊ ሰነዶችን መሰረት በማድረግ ነው ይህም የሚሆነው መዛግብቶቹና ደጋፊ ሰነዶቹ በታክስ ባለስልጣኑ ዘንድ ተቀባይነት ካገኙና ታክስ ከፋዩም እንዲያቀርባቸው ሲጠየቅ ካቀረባቸው ነው ነገር ግን መዛግብቶቹ እና ደጋፊ ሰነዶቹ በማንኛውም ምክንያት ተቀባይነት ካጡ ወይም ታክስ ከፋዩ እንዲቀርባቸው ሲጠየቅ ካላቀረባቸው ወይም የሒሳብ መዛግብትና ደጋፊ ሰነዶቹ ከሌሉ የታክስ ባለስልጣኑ ታክሱን ባለው መረጃ ወይም የዕቃውን ወይም የአገልግሎቱን የአገር ውስጥ ገበያ ዋጋ ዋጋው የማይታወቅ ከሆነ የተመሳሳዩን የገበያ ዋጋ መሰረት በማድረግ ለመወሰን ይችላል አንቀጽ ጋ በሌላ በኩል በገቢ ግብር አዋጅ መሰረት የዚሳብ መዝገብ የማይዙ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች የተርን ኦቨር ታክስ በቁርጥ የሚወሰን ነው የስሌቱ መሰረትም ለገቢ ግብር መሰረት የሆነው ጠቅላላ ገቢ ነው አንቀጽ የተርን ኦቨር ታክስ ሕግን መተላለፍ የፍትሐብሔር ተጠያቂነት ሊያስከትል ይችላል የተርን ኦቨር ታክስ ከፋይ የሆነ ሰው በአዋጅ የተጣለበትን ግዴታ ካልተወጣ አስተዳደራዊ መቀጮ ሊጣልበት ይችላል አስተዳደራዊ መቀጮ ሊያስጥሉ የሚችሉ ጥፋቶች ውስጥ ። የታክስ ይርጋ ቀደም ሲል እንዳየነው የገቢ ግብርተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስ አና ኤክሳይዝ ታክስ ታክስ ከፋዩ በሚያቀርበው ማስታወቂያና ሌሎች መረጃዎች መሰረት ሊወሰኑ ይችላሉ ሆኖም ግን ታክስ ከፋዩ በሚያቀርበው የታክስ ማስታወቂያ ወይም መረጃ መሰረት የሚከፈለው ታክስ የመጨረሻ አይደለም ታክስ አስገቢው ባለስልጣን በታክስ ከፋዩ ራሱ ተሰልቶ የቀረበውን ወይም የተከፈለውን ታክስ የማጣራት ሥልጣን አለው በማጣራቱም ሒደት ታክሱ ስህተት ወይም ያልተካተተ ገቢ ያለ መሆኑ የተረጋገጠ ከሆነ ባለስልጣኑ ያቀረበውን ታክስ ወይም ማስታወቂያ አስተካክሎ ታክሱን የመወሰን ሥልጠን አለው የተስተካከለው ወይም የተሻሻለው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያው ለታክስ ከፋዩ ሊደርሰው ይገባል ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ታክስ ከፋዩ ያቀረበውን የታክስ ማስታወቂያ ወይም የከፈለውን ታክስ እንደገና በማጣራት ውሳኔ መስጠት የሚችለው በምን ጊዜ ውስጥ ነው። ታክስ የታክስ ከፋዩን ሀብት በመያዝ የሚሰበሰቡትን ሁኔታ ይረዳሉ ይግባኝ ሥርዓት የገቢ ግብር ተጨማሪ አሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስ እና ኤክሳይዝ ታክስ የይግባኝ አቀራረብ ሥረዓት ተመሳሳይ መሆኑን ታክሶችን ከሚጥሉ ህጎች መረዳት ይቻላል በታክስ ባለስልጣኑ የሚሰጡ የታክስ ውሳኔዎች ሁሌም የመጨረሻ እንዳልሆኑ በህጎቹ ተመልክቷል ባለስልጣኑ በሰጠው ውሳኔ ቅሬታ የተሰማው ታክስ ከፋይ ቅሬታውን እንደሁኔታው ለአቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ ወይም ለግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ማቅረብ ይችላል አቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ የአቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ አባላት በታክስ ባለስልጣኑ ኃላፊ አቅራቢነት እንደ አግባብነቱ በገቢዎች ሚኒስትር ወይም አግባብ ባለው የክልል ባለስልጣን የሚሰየሙ ናቸው የአቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ በግብር ከፋዮች መቀጫ እንዲነሳ ወለድ ቀሪ እንዲደረግ ወይም የግብር ግዴታ እንዲሻሻል የሚቀርቡ ማመልከቻዎችን መመረመርና የውሳኔ የመስጠት ሥልጣን አለው ለዚህም ማናቸውንም የጽሑፍ ማስረጃዎች ወይም መረጃዎች የመሰብሰብ አንዲሁም ለማጣራት ማንኛውንም ሰው መጥራትና መጠየቅ ይችላል በተጨማሪም ኮሚቴው የግብር አስገቢው ባለስልጣን የሰጠው የግብር ውሳኔ ትክክለኛ የተሟላ እና ታክሱን የሚጥለውን አዋጅ ጠብቆ የተሰጠ መሆኑን የማረጋገጥ ሥልጣን አለው እንዲሁም ምስክር ወረቀት በመከልከል ወይም ንግድ ፈቃድ በመሰረዙ ግብር አስገቢው ባለስልጣን በሰጣቸው ምክንያቶች ቅር የተሰኘ ግብር ከፋይ ቅሬታውን ለአጣሪ ኮሚቴ ማቅረብ ይችላልየገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ አጣሪው ኮሚቴ ከግብር ከፋዮች የሚቀርበውን አቤቱታ ሊያይ የሚችለው ግብር ከፋዩ የግብር ውሳኔ ማስታወቂያ በደረሰዉ በአስር ቀናት ውስጥ አቤቱታውን ካቀረበ ነው የአጣሪው ኮሚቴ ውሳኔ ተፈፃሚነት የሚኖረው የውሳኔ ፃሳቡ በግብር አስገቢው ባለስልጣን ኃላፊ ከፀደቀ ነው የግብር አስገቢው ባለሥልጣን ኃላፊ ኮሚቴው ባቀረበው ሃሳብ ካልተስማማ ምክንያቱን በመግለጽ ጉዳዩ እንደገና እንዲታይ ለኮሚቴው ሊመልሰው ይችላል በመጨረሻም መቀጮውን ማንሳትን በተመለከተ ኮሚቴው የገቢዎች ሚሂስትር በሚያወጣው መመሪያ መሠረት በግብር ከፋዩ ላይ የተጣለው አስተዳደራዊ መቀጮ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲነሳ ማድረግ ይቻላል ግብር ይግባኝ ጉባኤ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የግብር ውሳኔ ላይ ይግባኝ የሚቀርበው ለግብር ይግባኝ ጉባኤ ነው ግብር አስገቢው ባለሥልጣን የሚሰጠው የግብር ውሳኔ ማለት የሚፈለገውን ፍሬ ግብር ብቻ ሳይሆን ግብር ከፋዩ ወይም ግብርን ከተከፋይ ሒሳብ ቀንሶ ገቢ የማድረግ ግዴታ ያለበት ሰው ግዴታውን ባለመወጣቱ የሚጣለውን አስተዳደራዊ መቀጮንም የሚጨምር ነው የግብር ይግባኝ ጉባኤዎች እንደ አስፈላጊነታቸው በፌዴራል ደረጃ የፌዴራል የግብር ይግባኝ ጉባኤ በእያንዳንዱ የክልል ዋና ከተማ የክልል የግብር ይግባኝ ጉባኤ በእያንዳንዱ የዞን ዋና ከተማ የዞን የግብር ይግባኝ ጉባዔና በእያንዳንዱ የወረዳ አስተዳደር ከተማ የወረዳ የግብር ይግባኝ ጉባኤ እንደሚቋቋሙ ተደንግጓል የፌዴራል የግብር ይግባኝ ጉባኤ ተጠሪነቱ ለፍትህ ሚኒስትር ሲሆን ሌሎቹ በየደረጃው ላሉት የስራ አስፈፃሚ አካላት ነው ግብር አስገቢው ባለስልጣን በሚሰጠው የግብር ውሳኔ ቅር የተሰኘ ግብር ክፋይ ለግብር ይግባኝ ጉባኤ ይግባኝ ለማቅረብ በሕጉ የተዘረዘሩትን ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላት ይጠበቅበታል አነዚህም ቅድመ ሁፄታዎች ሁለት ናቸው አንደኛው አካራካሪ የሆነውን የግብር መጠን አምሳ በመቶ ለግብር አስገቢው ባለስልጣን ማስያዝ ነው ሁለተኛው የይግባኝ ማቅረብያ ጊዜን የሚመለከት ሲሆን ግብር ከፋዩ የግብር ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው ወይም በአቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ በተሰጠ በሰላሳ ቀን ውስጥ ይግባኙን ማቅረብ አለበት እነዚህን ሁኔታዎች ያላሟላ ይግባኝ በይግባኝ ጉባኤ ተቀባይነት የለውም ይግባኙ የቀረበበት ቀን የሚባለውም ይግባኙ በቀጥታ ለይግባኝ ጉባኤው የቀረበ ከሆነ ይግባኝ በመዝገብ ቤት የተመዘገበበት ቀን ሲሆን ይግባኝ በሪኮማንዴ የተላከ ከሆነ ደግሞ በፖስታ ቤት ተመዘገበበት ቀን ይሆናል የታክስ ባለሥልጣን በሚሰጠው የታክስ ውሳኔ ላይ ይግባኝ ሊያቀርብ የሚችለው ታክስ ከፋዩ ወይም ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ታክስ ቀንሶ ገቢ የማድረግ ሐላፊነት ያለበት ሰው ሊሆን ይችላል የታክስ ባለስልጣኑ ለግብር ይግባኝ ጉባኤ ይግባኝ የሚልበት ሁኔታ አይኖርም ታክስ ከፋዩ የሚያቀርበው የይግባኝ ማመልከቻም የይግባኝ ፍሬ ነገር እና የይግባኝ ምክንያቶች የግብር ከፋዩን ስም አድራሻ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ኣባሪ ሰነዶችና ለግብር አስገቢው ባለሥልጣን መያዣ የተከፈለበት ደረሰኝ ፎቶ ኮፒ የያዘ መሆን አለበት ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ቢጎድል የይግባኝ ጉባኤው ይግባኝ ባይ የተባለውን ጉድለት እንዲያሟላ ይጠይቀዋል ይግባኝ ባይ በአምስት ቀኖች ውስጥ የተባለውን ጉድለት ማስተካከል አለበት ያላስተካከለ እንደሆነ የቀረበው የይግባኝ ማመልከቻ ወዲያውኑ ውድቅ ይሆናል የይግባኝ መስማት ሒደትም በተመለከተ ታክስ ከፋዩ የሚያቀርበው ይግባኝ ከማሰማቱ በፊት የይግባኙ ማመልከቻ ግልባጭ ለግብር አስገቢው ባለስልጣን ደርሶ መልስ እንድሰጥበት መደረግ አለበት ይግባኝ ባይ በሁለት የቀጠሮ ጊዜ ሳይገኝ የቀረ እንደሆነ ወይም ይግባኙን ካቀረበ በኃላ የመልስ መልስ ሳያቀርብ ቢቀር ወይም የግብር አስገቢው ባለስልጣን የይግባኝ ማመልከቻ ከደረሰው በኃላ በሁለት የቀጠሮ ጊዜዎች ሳይገኝ የቀረ እንደሆነ ወይም ለይግባኙ መልስ ሳይሰጥ ቢቀር ተከራካሪው ወገን በሌለበት ውሳኔ ይሰጣል ግብር ይግባኝ ጉባኤ የግብር አስገቢው ባለስልጣን ውሳኔ የውሳኔው ይዘት ምን መያዝ አንዳለበት በሕጉ ተመልክቷል ይግባኝ ሰሚ ጉባኤም የግብር ውሳኔ የማፅናት የመቀነስ ወይም የመሰረዝ ሥልጣን አለው ጉባኤው የፍሬ ነገር እና የሕግ ስህተት የማረም ሥልጣን አለው ማለት ነው ይግባኝ ሰሚ ፍቤት የይግባኝ ጉባኤ የሰጠው ውሰኔ በሕግ ረገድ ስህተት አለበት የሚል ወገን ይግባኙን ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ላለው ፍቤት የማቅረብ መብት አለው ሆኖም ግን ይግባኝ ባዩ ይግባኙን ለማቅረብ ሁለት ግዴታዎች ሟሟላት ይጠበቅበታል አንደኛው ጉባኤው ውሳኔ በተሰጠ ሰላሳ ቀን ውስጥ ይግባኙን ማቅረብ ነው ሁለተኛው ይግባኝ ጉባኤው የተወሰነበትን ሙሉ ግብር መክፈል ነው ይግባኝ የቀረበለት ፍቤቱም ያለው ሥልጣን በሕግ ረገድ የተወሰነውን ክርክር ብቻ ተመልክቶ ውሳኔ ከሰጠ በኃላ ጉዳዩን ወደ ጉባኤው መመለስ ነው ፍቤቱም በሚሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ተከራካሪ ወገን አሁንም በደረጃው ቀጥሎ ለሚገኘው ፍቤት ይግባኝ የማቅረብ መብት ተሰጥቶታል የይግባኝ ሰሚው ፍቤት የመጀመሪያው ፍቤት በይግባኝ ያየውን ጉዳይ ብቻ የሚያይ ነው ይግባኝ ባዩም ውሳኔው በተሰጠ ሰላሳ ቀን ውስጥ ይግባኙን ማቅረብ ይኖርበታል አዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ ከሌሎች የይግባኝ ሥርዓቶች በተለየ ሁኔታ ወደ መደበኛ ፍቤቶች ይግባኝ የቀረበ እንደሆነ ጉዳዩ በይግባኝ ሰሚው ፍቤት ቀርቦ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ አፈፃፀሙ የማይታገድ መሆኑ ነው በጉባኤው ውሳኔ መሰረት ታክሱ የሚከፈል ይሆናል ለዚህ ሕጉ ታክስ ከፋዩ የሰጠው ብቸኛ መፍትሔ ቢኖር የታክሱ ውሳኔ በመጨረሻው ይግባኝ ፍቤት የተሻሻለ ወይም የተለወጠ አንደሆነ ከሚገባው በላይ የተከፈለው እንዲመለስለት ማድረግ ነው ሌላው መታየት ያለበት ነጥብ ደግሞ የይግባኝ ሰሚው ፍቤት ሥልጣን ወሰን ነው ከግብር ይግባኝ ጉባኤ ላይ የሚቀርበውን ይግባኝ የሚያይ ፍቤት ሥልጣኑ የተገደበ ነው የፍቤቱ ሥልጣን በሕግ ረገድ ተፈፅሟል የተባለውን ስህተት በማቃናት ጉዳዩን ወደ ጉባኤው መላክ አንጂ በታክስ አወሳሰን የግምት ሥራ ውስጥ መግባት እንደሌለበት በአዋጆቹ ተመልክቷል ጥያቄው ታዲያ በሕግና በፍሬ ነገር ሥራ መሀል ያለውን የልዩነት መስመር እንዴት ማስመር ይቻላል የሚለው ነው ታክስን በተመለከተ ለፍቤት ከሚቀርቡት ይግባኞች መረዳት እንደሚቻለው በይግባኝ ቅሬታነት አዘውትረው የሚቀርቡት ታክስ የተጠየኩት በማይመለከተኝ ሥራ ነው የተተመነብኝን ገቢ ሰርቼ ያላገኘሁት ነው ያቀረብኩት የሂሳብ መዝገብ በአግባብ የተያዘ ሆኖ ሳለ የታክስ ባለስልጣኑ ባለመቀበል ታክሱን በግምት ወሰነብኝ ሊቀነሱ የሚገባቸው ሂሳቡች አልተቀነሱልኝም ታክሱ በይርጋ ታግዶ ሳለ መጠየቄ ያለአግባብ ነው ቁርጥ ግብር ከፋይ ስለሆንኩ የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የለብኝም ታክስ የተጠየኩበትን ሥራ አልሰራሁም ወይ ሥራውን አቋርጫለሁ የግብር ውሳኔ ማስታወቂያ በአግባቡ እንዲደረሰኝ አልተደረገም የተጣለብኝ መቀጫ አይመለከተኝም ወዘተ የሚሉ ናቸው ከእነዚህ ውስጥ የትኛው የሕግ የትኛው ደግሞ የፍሬ ነገር ጥያቄ ነው የሚለውን መመለስ አስቸጋሪና አንዳንዴም የሚያወዛግብ ሥራ ነው ቀደም ሲል በነበሩት ህጎች መሰረት ከተሰጡት ውሳኔዎች መረዳት እንደሚቻለው በአንዳንድ ፍቤቶች የፍሬ ነገር እንጂ የሕግ ስህተት አይደሉም ተብለው የተጣሉ ጉዳዮች በሌሎቹ ክርክር ሲካሔድባቸው ይታያሉ በሚቀርበው የታክስ ይግባኝ ክርክር ውስጥ የትኛው የሕግ ወይም ደግሞ የፍሬ ነገር ጥያቄ ነው ለሚለው ወሰን ማበጀት አዳጋች ቢሆንም የፍሬ ነገር ክርክር የአንድ ነገር መኖርና አለመኖር ጋር የተያያዘ ሲሆን የህግ ክርክር ደግሞ በሕግ ድንጋጌዎች አፈጻጸምና ትርጉም ጋር የተያያዘ ነው ለማለት ይቻላል ግራ ቀኙን የሚያከራክረው ነጥብ የአንድ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ከሆነ የዚህ አይነቱ የፍሬ ነገር ተከራካሪ ወገኖች በሚያቀርቡት የማስረጃ ክብደት የሚወስን ይሆናል ታክስ ከፋዩ ነጋዴ መሆን አለመሆኑ ታክስ ከፋዩ ትክክለኛ ስራ ፍቃድ ያለው መሆን አለመሆነ ታክስ ከፋዩ በተወሰነ ጊዜ የንግድ ሥራ ማከናወን አለማከናወነታክሱን ማሳወቅ አለማሳወቁ ታክሱን በጊዜ መክፈል አለመክፈሉ የሒሳብ መዝገብ መያዝ አለመያዙ እና የመሳሰሉት የፍሬ ነገር ክርክሮች ናቸው ለማለት ይቻላል እነዚህን ጭብጦች በማስረጃ ሊነጥሩ የሚችሉ ናቸው ለምሳሌ አንድ ታክስ ከፋይ የንግድ ሥራ ማከናወኑን የታክስ ባለስልጣኑ የተባለው ሰው ገቢ በሚያስገኝ ሥራ ላይ መሰማራቱን ማስረጃ ማቅረብ አለበት ይህ የሕግ ትርጉም አይጠይቅም በሌላ በኩል ገቢው የተገኛው ከመቀጠር ነው ወይስ ከንግድ የሚለው የሕግ ክርክር የሚያስነሳ ነው ስለዚህ የግብር ከፋዮች መብት ላለማጣበብ አያንዳንዱን ጉዳይ በጥልቀት መመርመር አስፈላጊ ይሆናል የመወያያ ጥያቄዎች የአቤቱታ አጣሪ ኮሚቴ ሥልጣን ምንድነው። የታክስ አሰባሰብ አፈፃፀም ታክስ በሕግ የሚጣል ግዴታ መሆኑንአንዲሁም ታክስ የመጣሉ ሥልጣን የሕግ አውጭው አካል ብቻ እንደሆነ ቀደም ሲል ተመልክቷል ሕግ አውጪው አካል ባለው ሥልጣን ታክስን መጣል ብቻ ሳይሆን የተጣለው ታክሱን ማን መሰብሰብ እንዳለበት እና እንዴት መሰብሰብ አንዳለበት መደንገግ ይጠበቅበታል ሕግ አውጪው አካል የተጣለው ታክስ የሚሰበስብበትን ሥረዓት የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በሚያወጣው ህግ ውስጥ ማካተት ወይም አሰባሰቡን የሚመለከቱ ስነ ስርዓታዊ ህጎች ወይም ደንቦችን ማውጣት ይኖርበታል ለዚህ አላማ የሚወጡ ህጎችም የሚጣለውን ታክስ መሰብሰብ የሚያስችሉ መሆን ይኖርባቸዋል በመሰረቱ ታክስ የሚጣለው እና የሚሰበሰበው ከአጠቃላይ ጥቅም በመሆኑ አንድ ታክስ ከፋይ ሕጉ በሚያዘው መሰረት ታክሱን በመክፈል የዜግነት ግዴታውን መወጣት ይጠበቅበታል ሆኖም ግን ሁሉም ይሔን ተገንዝቦ የታክስ ግዴታውን ይወጣል ማለት አይቻልም ስለዚህ ሕጉ በሚያዘው መሰረት ግዴታቸውን በማይወጡ ታክስ ከፋዮች ላይ የሚፈለገውን ታክስ በሕግ በማስገደድ መሰብሰብ የግድ ይላል በሐገራችን የገቢ ታክስተጨማሪ እሴት ታክስ ተርን ኦቨር ታክስ እና ኤክሳይዝ ታክስ በሚጥሉ አዋጆች ውስጥ አንድ ታክስ ከፋይ የታክስ ግዴታውን ባልተወጣ ጊዜ ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ታክሱን እንዴት በሕጉ አግባብ አስገድዶ መሰብሰብ እንዳለበት ተደንግጓል መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎችን ተመልክተዋል ሀ የመጨረሻና ተፈጻሚነት ያለው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ቀደም ሲል እንደተመለከተው የታክስ ባለስልጣኑ ታክሱን በሚወሰንበት ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያውን ለታክስ ከፋዩ ማድረስ ወይም መስጠት ይኖርበታል የታክስ ውሳኔው ማስታወቂያው የደረሰው ታክስ ከፋይም በህጉ የተለያዩ አማራጮች የተቀመጡለት በመሆኑ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያው ሁል ጊዜ የመጨረሻና ተፈፃሚነት ያለው ላይሆን ይችላል የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የመጨረሻና ተፈፃሚነት ያለው ሊሆን የሚችለው ። ይግባኝ ፍቤቱም የመጨረሻው ውሳኔ ከሰጠ ነው በዚህ ሁኔታ የመጨረሻና ተፈፃሚነት ያለው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ መሠረት የሚፈለግበትን ታክስ ያልከፈለ ታክስ ከፋይ ጥፋተኛ ነው ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ጥፋተኛ ከሆነው ታክስ ከፋይ ላይ የሚፈለገውን ታክስ አስገድዶ የመሰብሰብ ሥልጣን አለው ይህን ሥልጣኑን ተጠቅሞ ታክሱን አስገድዶ ለመሰብሰብ የሚችለው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያው የመጨረሻና ተፈፃሚነት ያለው ሲሆን ነው ታክሱም የሚሰበሰበው የታክስ ከፋዩን ሀብት በመያዝ ነው ለ የታክስ ከፋዩን ሀብት መያዝ የታክስ አስገቢውን ባለስልጣን ሥልጣን ታክስን በመወሰን ብቻ የተገደበ አይደለም ሥልጣኑ ታክስን ከመወሰን አንስቶ በታክስ ውሳኔን አስከ ማስፈፀም የሚሔድ ነው በዚሁ መሰረት የታክስ አስገቢው ባለስልጣን ጥፋተኛ በሆነው ታክስ ከፋዩ ላይ የሚፈለገውን ታክስ እና ታክሱን ለመሰብሰብ የወጣውን ወጪ የታክስ ከፋዩን ሀብት ቤርሯካ በመያዝ የማስፈፀም ሥልጣን ተሰጥቶታል ቀደም ሲል ሲሰራባቸው በነበሩት ህጎች አንድ ታክስ ከፋይ እንደ ታክስ ውሳኔው ካልፈጸመ ታክስ አስገቢው መስሪያ ቤት ፍርድ ቤት ሔዶ የአፈፃፀም መዝገብ መክፈት ይኖርበታል ታክስ አስገቢው መስሪያ ቤት በራሱ ታክሱን አስገድዶ የመሰብሰብ ሥልጣን አልነበረውም ማለት ነው በወቅቱ ሥራ ላይ የነበረው ሕግም የሚያዘው ይሄፄንኑ ነበር የአሁኑ ህግ የሚያዘው ግን ቀደም ሲል ከነበረው የተለየ ነው አሁን ሥራ ላይ ባለው ህግ ታክስ አስገቢው ባለስልጣን በአንድ ታክስ ከፋይ ላይ የሚፈልገውን ታክስ ለመሰበሰብ ፍቤት ሔዶ የሚከፈተው የአፈጻጸም መዝገብ የለም የታክስ ውሳኔውን የሚያስፈፅመው ራሱ ነው ከላይ እንደተጠቀሰው ታክስ አስገቢው ባለስልጣን የታክስ ውሳኔውን የሚያስፈፅመው የታክስ ከፋዩን ሀብት በመያዝ ነው ለታክስ አፈፃፀም አላማ መያዝ ማለት በማናቸውም መንገድ መያዝን እንዲሁም የታክስ ከፋዩ የሆነ ገንዘብ ወይም ንብረት በእጁ ከሚገኝ ሰው ታክስ መሰብሰብን እንደሚጨምር በህጉ ተመልክቷል በዚህ መሠረት ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ታክሱን ለመሰብሰብ የታክስ ከፋዩ በባንክ ቤት ያለውን ጥሬ ገንዘብ ወይም ከመቀጠር የሚያገኘው ገቢ ወይም የታክስ ከፋዩ የሚንቀሳቀስ ንብረት እንዲያዝ ማድረግ ይቻላል ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘው ታክስ ከፋዩ ከመቀጠር የሚያገኘው ገቢ ያለው ከሆነ ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ከተቀጣሪው ደመወዝ የመክፈል ኃላፊነት ላለበት ኃላፊ ማስታወቂያ በመስጠት እንዲያዝ ማድረግ ይቻላል ባልተከፈለ የታክስ ምክንያት ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ለመያዝ የታክስ አስገቢው ባለስልጣን በመጀመሪያ መፈፀም ያለበት ግዴታ አለ ይሔም ግዴታ ደመወዙን የመያዝ ሀሳብ እንዳለው አስቀድሞ ለታክስ ባለዕዳው በፅሑፍ ማስታወቅ ነው ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ይህን ማስታወቂያ ደመወዝ ከመያዙ ከሰላሳ ቀን በፊት ለታክስ ባለዕዳው እንዲደርሰው የማድረግ ግዴታ አለበት የታክስ ባለዕዳውን ደመወዝ መያዝ ውጤትም በታክስ ዕዳ ምክንያት ደመወዝ እንዲያዝ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ የታክስ ዕዳ ተከፍሎ እስከሚያልቅ ወይም የታክሱ ዕዳ በይርጋ ምክንያት ሊጠየቅ የማይቻል እስከሚሆንበት ጊዜ ድረስ የሚቀጥል ነው በሌላ በኩል በታክስ ዕዳ ምክንያት የማይያዙ ገቢዎች በአዋጆች ተጠቅሰዋል እነሱም በሰንጠረዥ ሆ ከግብር ነፃ ከተደረገው የገቢ መጠን ሳያልፍ ሰራተኛው የሚያገኘው ደመወዝ ወይም ማናቸውም በተወሰነ ጊዜ የሚገኝ ሌላ ገቢ እአና በማናቸውም የኢትዮጵያ ሕግ አንዳይከበሩ የተደረጉ ገቢዎች ናቸው ታክስ አስገቢው ባለስልጣን የታክስ ከፋዩን ንብረት ወይም ንብረቶች ለታክስ ዕዳ መክፈያ ለማዋል ንብረቱን ወይም ንብረቶቹን በመያዝ በሐራጅ ወይም በባለስልጣኑ በፈቀደ በማናቸውም ሌላ ዘዴ ለመሸጥ ይችላል ሐራጁም የሚደረገው ንብረቱ ከተያዘበት ቀን አንስቶ ከሚቆጠር አስር ቀናት ጊዜ በኋላ መሆን አለበት ሆኖም ግን ንብረቱ የሚበላሽ ከሆነ የንብረቱን ባህሪ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተገቢ መስሉ በታየው ጊዜ ሊሸጠው ይችላል እንዲሁም የታክስ አስገቢው ባለስልጣን በታክስ ዕዳ ምክንያት ንብረቱን የመያዝ ሀሳብ አንዳለው አስቀድሞ ለታክስ ባለዕዳው በጽሑፍ ማስታወቅ አለበት የጽሑፍ ማስታወቂያውም ንብረቱ ከመያዙ ከ ቀን በፊት ለታክስ ከፋዩ ሊደርሰው ይገባል ሆኖም ግን የታክስ አስገቢው ባለስልጣ የታክሱን አሰባሰብ የሚያዳናቅፍ ሁኔታ መኖሩን የተረዳ አንደሆነ የሰላሳ ቀን የጊዜ ገደብ ሳይጠበቅ ታክሱ ወዲያውኑ እንዲከፈል ለማደረግ ጥያቄ ካቀረበና ታክስ ከፋዩ ለመከፈል ፈቃደኛ ካለሆነ ንብረትን በመያዝ ታክስ የመሰብሰብ አፈፃፀም ሕጋዊ ይሆናል የንብረት መያዝ ውጤትም በሕጉ ተመልክቷል በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የተከበረ ወይም በአፈፃፀም ላይ ያለ ወይም በዋስትና የተያዘ ካለሆነ በስተቀር ማናቸውም በታክስ ምክንያት የተያዘ ንብረት በእጅ የሚገኝ ወይም ለታክስ ከፋዩ ማናቸውም ግዴታ ያለበት ሰው የታክስ አስገቢው ባለስልጣን ሲጠይቀው የያዘውን ሀብት የማስረከብ ወይም ያለበትን ግዴታ የመፈጸም ሐላፊነት አለበት ንብረቱን ለማሰረከብ ፈቃደኛ ሳይሆን ከቀረ ግን በተያዘው ንብረት መጠን በግል ተጠያቂ ይሆናል የተጠያቂነቱ ግን ከሚፈለገው የታክስ ዕዳ መጠን ማለፍ የለበትም በተጨማሪም ንብረቱን ለማስረከብ ፈቃደኛ ያልሆነው ያለበቂ ምክንያት ከሆነ የታክስ ዕዳ መጠን አምሳ ፐርሰንት በተጨማሪ የመክፈል ግዴታ አለበት በሌላ በኩል በይዞት ሥር ያለውን ንብረት አስረከበ ወይም ከታክስ ከፋዩ የሚፈለገውን ገንዘብ ለታክስ አስገቢው ባለስልጣን በተጠየቀው መሰረት ገቢ ያደረገ ሰው ካስረከበው ንብረት ወይም ገቢ ካደረገው ገንዘብ ጋር በተያያዘ የግብር ግዴታውን ባልተወጣው ታክስ ካፋይ ወይም ማናቸውም ሌላ ሰው ከሚፈለግበት ዕዳ ወይም ካለበት ግዴታ ነባ እንደሚሆን ተመልክቷል ዋስትና የተሰጣቸው የሌሎች አበዳሪዎች የቅድሚያ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ታክስ ተከፋይ ከሚሆንበት ቀን አንስቶ ተከፍሉ እአስከአለቀበት ጊዜ ድረስ ታክስ የመክፈል ግዴታ ባለበት ሰው ሀብት ላይ የታክስ አስገቢው ባለስልጣን ከማናቸውም ሌሎች ዕዳዎች የቀደምትነት መብት አለው የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የታክስ አስገቢው ባለስልጣን የታክስ ዕዳ የሚፈለግበትን ሰው ሀብት በዋስትና ተይዞ እንዲቆይ ንብረቱን ለመዘገበው አካል የጽሑፍ ተዕዛዝ የሚሰጥ መሆኑን ለታክስ ከፋዩ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል ታክስ ከፋዩም ማስጠንቀቅያው በደረሰው ቀን ውስጥ ታክሱን ያልከፈለ እንደሆነ ታክስ አስገቢው ባለስልጣን ለመዘገበው ባለስልጣን የታክስ ከፋዩ ሀብት ባልተከፈለው የታክስ ዕዳ መጠን በዋስትና ተይዞ እንዲቆይ ትዕዛዝ ይሰጣል በዚህ መሰረት ትዕዛዝ ሲሰጥ መዝጋቢው ባለስልጣን ማናቸውንም ክፍያ ሳይጠይቅ ንብረቱን በዋስትና እንዲያዝ ሀሀ የደረሰውን ትዕዛዝ እንደማናቸውም በሀብቱ ላይ እንዳለ የመያዣ ሰነድ ይመዘግባል የዋስትናው ምዝገባ የሚፈለገውን ታክስ ለማስከፈል በማናቸውም መልክ በሕግ እንደተሰጠ መያዣ በ ወይም እንደማናቸውም ሌላ ዕዳ ወይም ክፍያ ሆኖ ይቆጠራል በመጨረሻም በታክስ ዕዳ ምክንያት የተያዘ ንብረት የተሸጠ እንደሆነ ከሽያጩ ከተገኘው ገንዘብ ውስጥ ታክስ ከፋዩ ከሚፈለግበት ዕዳ በላይ የሆነው ገንዘብ ለንብረቱ ባለቤት ይመለሳል የመወያያ ጥያቄዎች በኢትዮጵያ ሕግ እንዳይከበሩ የተደረጉ ገቢዎች ካሉ ጥቀሱ የታክስ አስገቢው ባለስልጣን ራሱ የሰጠውን ውሳኔ ራሱ የታክስ ከፋዩን ንብረት በመያዝ በሐራጅ እንዲሸጥ ማድረጉ ፍታዊ አይደለም ብለው ትችት የሚሰነዝሩ ሰዎች አሉ በዚህ ረገድ እናተ ምን ትላለችው።