Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ፓ መምህሩሃ ሰውዬው መንግሥቱ ለማ አነጋገራቸው ቅኔ አስተያያቸው ቅኔ አካሄዳቸው ቅኔ አኗኗራቸው ቅኔ ነበር። አብዬ ከመኝታ ቤት የመጡት ቆዬት ብለው ነው። እንደዘቢብ የሚጣፍጥ ጨዋታቸውን ከመጀመራቸው በፊት ምን ይምጣላችሁ። በዚህ ብቻም ሳይሆን ንፁህ ቢራ ሳይበዛ መውደዳቸውን ጊገዜና ቦታ ባያንስ ምሳሌ መጠቃቀስ ይቻል ነበር። እሺ አንድ ልጨምር። ምከሩት ፈተና እንዳይወድቅ ትንሸ ውሃ ሳይደፍር አይቀርም ያሉት ሌላው ትዝታዬ ነው። አብዬ የእምነታቸው ጥንካሬ የእውነታቸው ፍልስፍና አይበገሬነት ሲታይ በጥልቅ የቀሰሙት የቤተክህነቱና የዘመናዊው የላቀ ትምህርት በውስጣቸው ተዋህደው ከመኖር ይልቅ እኔ ልቅደም ጦርነት የሚገጥሙባቸው ነው የሚመስለኝ። ስለማይዋሹም ሕይወታቸው በግጭት የተሞሳ ነው። አንድ ፔኒ የአንድ ሽልንግ ኛ ክፍልፋይ ነው። ሠርጀሪ ቃሉ የእንግሊዝኛ ሲሆን ትርጉሙ ሁለት ነው። በኦክስፈርድ የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃሳት መሰረት አንደኛው ቀዶ ህክምና የሚባለውን የህክምና ተግባር የሚያመለክት ሲሆን ሁለተኛው የህክምና ዶክተሮች ህመምተኞችን እየተቀበሉ የሚያስተናግዱበትና የሚያነጋግሩበት ክፍል መጠሪያ ነው። ጀዝዊት በካቶሊክ እምነት ውስጥ ካሉት እጅግ በርካታ ዘርፎች መካከል አንዱ ነው። በአገራችን የታሪክ ሰነዶች ውስጥ ኢየሱሳውያን በመባል ነው የሚታወቁት። ስቲንከር የእንግሊዝ ቃል ነው። ዋቤ መፅሐፍት ውስጥ እንደሚጨመሩ ተስፋ በማድረግ ነው።
ፅ አሣግሣታሚው ክፍል አንድ ግለ ታሪክ መንደርደሪያ በባህል ሚኒስትሩ አስተያየት ዕድሜዬ ለጡረታ የደረሰ መሆኑን ባለመዘንጋት ሰው ሃምሣ ዓመት ከሆነው በኋላ አንድ አይነት ግለ ታሪክን የያዘልከከር የሆነ ፅሑፍ ለተከታዩ ትውልድ ማቆየት እንዳለበት በመገንዘብ አንድ ጥሩ ደብተር ገዛሁ። ሰው ። አባታችን ለወይዘሮ ፍሥሐ ማረፊያ እንዲሆናቸው የሰጡዋቸው ቤት በዚያን ጊዜ በጣሊያኖች ላይ ሽፍቶ የፊታውራሪ በዕደ ወታደር ለሆነው ለታላቄ ታላቅ ወንድሜ ለጋሼ ልሳን ተሰርቶለት የነበረውን ሁለት ክፍል የቆርቆሮ ቤት ነበር። በዚህ ሁኔታ ጥቂት ጊዜ ቆይተው አንድ ቀን ለገበያ ወደ አደሬ ግንብ ሲወርዱ የገዛ አሽከራቸውን ትተው እኔን ተከተለኝ ብለው በእግራችን አብረን ወረድን። ጧት ከሰዓት ወደማታ አንድ አንድ ሰዓት። በፊት ጊዜ እኔና ወንድሜ የሀበሻና የጣልያን ጦር አዛች ሆነን ሠራዊታችንን አሰልፈን አንድ ሳምንት ሙሉ ከተዋጋን በኋላ የኔ የሀበሻው ወገን ድል መሆኑን በሰሙ ጊዜ አባታችን የተቆጡት አጓጉል ሟርት ነው ብለው ነበር። የሥነ ድርሰት ዝንባሌዬ ግን ለጊዜው ባላውቀውም አንድ ታላቅ እርምጃ ያደረገው ጣልያን ሊወጣ ሲቃረብ እቅሄ ትምህርት ቤት ስገባ ነው። አባታችን ቅኔ ተማሪ ቤት ግባ ሲሉት ግን ሊገባ አልፈለገም። አንድ ቀን እንደለመድኩት ልቀዳ ሄጄ አንድ እኔ እማላውቃቸው ግን የሚያውቁኝ ሴት ወይዘሮ ውሀ ሊቀዱ መጥተው እዚያ ግጥም አልን። ብዙ ጊዜ ከዚያ ቀዳሁ። የተላከ ከመንግሥቱ ለማ ይድረስ ለክቡር አባቴ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ ታሪክ። ከዚህ የተነሣ አባቴ በቁጣ እብድ ሆነው በመጫኛ አንድ ቀን ጧት ጠበጠቡኝ። አሉኝ ወዲያው አንድ ጉባኤ ቃና ዘረፉ። ምነው ዛሬ ቅኔ ትምህርት የለም እንዴ። ሽማግሌ መቼ እሳቸው አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ ታሪክ ናቸው። ቅኔ ተቀኝቼ ደብተራ መንግሥቱ ተብዬ ጥቂት እንዳገለገልኩ አንድ ቀን ከታላቄ ታላቅ ከጋሼ ገብረ ክርስቶስ የተፃፈ ደብዳቤ ለአባታችን ከተፃፈው ጋር ለኔም መጥቶልኝ ኖሮ አባታችን ጠርተው ሰጡኝ። በዚያን ጊዜ ሙሴ አንቶን ጆንሰን በኬንያ ያስተምሯቸው የነበሩትን የኢትዮጵያ ስደተኞች ልጆች ሰብስበው ወደ ሐረር ተመልሰው የስደተኞች ትምህርት ቤት የሚባለውን ተማሪቤት አቋቁመው ነበር። ታዲያ ነገሩ በዚህ ላይ ቆሞ ሳለ አንድ ቀን በድንገት የፈረንጅ ትምህርት ለመማር ቆርጨ ተነሣሁ። መሀል ቤት የለም። ዋናው ነገር እዚህ ተማሪ ቤት ያልተለመደ ነገር ጅምናስቲክ የተባለ ትምህርት ማስተማሩ ነው። እንዲሁ አንተ መንግሥቱ ለማ ነህና የአለቃ ለማ ልጅ ነህ እንዲሁ ለምን የተማሪቤቱን ሕግ አክብረህ እንዲሁ ለምን አትማርም አሉ ሙሴ አንቶን በዚያ በስብከተ ወንጌል በለዘበ አማርኛቸው። ነገ በአሥር ሰዓት በጅምናስቲኩ ጊዜ እንዲሁ አንተ እዚህ ና። ቢሆንም አንድ አጠር ያለ የግጥም ድርሰት በዚያች መጽሐፍ መጨረሻ ላይ መፃፍ እንዳለበት በብርቱ ይሰማቸው ነበርና ቢቸግራቸው ከቅኔ ተማሪ ቤት በቅርቡ ተመርቄ የወጣሁትን ወጣት ደብተራ የሊቁን ያለቃ ለማን ልጅ ግጥሙን ባንድ ሳምንት ውስጥ አሰናድቼ እንዳቀርብ አዘዙኝ። ይህን ሳወጣ ሳወርድ የታላቄ ታላቅ ጋሼ ገብረ ክርስቶስ በጣልያን ጊዜ አንድ የሚያስቅ አጭር ታሪክ በአማርኛ ግጥም ደርሶ ለጓደኞቹ እያነበበ በጣም ተደንቆበት ነበር። ወዲያው ግን አባቴ ለፈረንጅ ትምህርት የፈቀዱልኝ የስድስት ወር ጊዜ ማለቂያው ስለተቃረበ ከተማሪ ቤት መውጣቴ መሆኑን ለሙሴ አንቶን ሄጄ ነገርኳቸው። በስደተኞች ተማሪ ቤት አራት ፎርም የሚባል ክፍል አለ። በዚያን ጊዜ የኛ ትምህርት ቤት ስም ከ ስደተኞች ወደ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከኛ በኋላ መንግሥት ያቋቋመው ሁለተኛው ትምህርት ቤት በአባታቸው ስም የራስ መኮንን ትምህርት ቤት ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ይህ ሁኔታ ሊፈጠር የቻለው ማለትፖሦ ያባትየው የራስ መኮንን ትምህርት ቤት ከልጅየው ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትምህርት ቤት በመዝሙርና በሰልፍ ብልጫ ማሳየቱ ከአሰበ ተፈሪ በመጣ አንድ አስተማሪ ምክንያት ነበር። ቢቸግረኝ ጊዜ እሺ እምቢ ካሳችሁ አንዲት ግጥም ደሞ አሰማችኋለሁ ግን ይቺኛዋ የሃይማኖት ግጥም አይደለችም አልኩ ባይሆንም ግዴለም ደስ ይበላቸው አለኝ ገድሌ። እንግዲህ ተማሪ ቤት ሲዘጋ ዕረፍቱን ወደ ቤት ሄጄ አዲስ አበባ ከእናትና አባቴ ዘንድ ነው የምቀመጠው። በዚህ ጊዜ ነበር ትምህርት ቤት ለክረምት ሲዘጋ ለዕረፍት ወደ ቤት ሄጄ አንድ ቀን ከፒያሣ ስመለስ መንገድ ላይ ከባድ ዝናብ መትቶኝ በግራ ጎኔ ከደረቴ ላይ ጭምድድ አድርጎ የሚይዝ አልፎ አልፎም እንደ ውጋት መሳይ ጠቅጠቅ የሚያደርግ የብርድ በሽታ የያዘኝ። መንግሥቱ ለማ የሚባለው ተማሪ የታል። እኔም እሳቸው በጨዋታ በተረት መልክ የሚናገሩት ነገር እንዲያው በቁም ጨዋታ አለመሆኑ ሲያገላብጡት አንድ ሚስጢር አንድ አይነት ምክር አንድ አይነት ትምህርት እንደሚሰጥ ደህና አድርጌ አውቅ ነበርና ባወጣው ባወርደው ባገሳብጠው ለትምህርት ውጭ አገር ለመሄድ ልሠናበት ከመጣሁበት ጉዳይ ጋር ያለው ግንኘነት አልታይ አለኝ። አንድ ቀን ያኮረፍኩበትን ምክንያት ጠየቀችኝ። ሚስተር ለማ በክርክሩ ተረታ ሚስተር ለማ ብለው እየሣቁ አጨበጨቡ። ሚስተር ለማ ትስማማ የለም። ለዚህ የረዳኝ አንደኛ ድሮ በስደተኞች ትምህርት ቤት ከዚያም በኋላ በኮተቤ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሣለሁ የጻፍኳቸው ግጥሞች በሙሉ ልብ ወለድ ተረት መሆናቸው ነው። ቀጥል ሚስተር ለማ አለኝ። አራት ሚስት አራት ቻቻታ ድብልቅልቅ ሆነ እዚህ ሳይ ሽማግሌው በዳኛነቱ ሁኔታውን ለማረጋጋት ሞከረ እስቲ እባካችሁ ዝም በሉ ላንዳፍታ ሚስተር ለማ አራት ሚስት አለኝ ብሎ ሲናገር እኔ ራሴ አልሰማሁም። ሚስተር ለማ አንተ ገና ተማሪ ጀማሪ በመሆንህ ትዳርህ ስላልደረጀ አራት ሚስት ብቻ ነው ያለኝ ብለህ አስረድተኸናል። አንድ ቀን ብቻ። አንድ ቀን ምንድነች። አልኩት አንተ አንድ ሚስት አለህ። ስንነዳ ሳለ አንዱ ያልበቃው ሚስተር ለማ አለ። ሚስተር ለማ የሚባል አንድ አፍሪቃዊ ተማሪ ገና በልጅነቱ አራት ሚስት አለው። ሚስተር ለማ አሁን ባገሩ በሱ ስም ያሉት ሚስቶች አራት ብቻ ቢሆኑም ያገባው ግን አሰር ሚስት ነው። ግን ዚ ሀ ሰው አንድ ጥቁር እኔ መሆኔን አይቶ መለስ ብሎ ወደኔ መጣ። መቼም መላ ሆስፒታሉ በሙሉ እንደሚያውቀው ሚስተር ለማ ባገሩ አራት ሚስት አለው ግን ቢኖረውም በዚህ በእንግሊዝ አገር አንድ እንኳን ስለሌለው እንደሌሎቹ በሽተኞች የሚታዘንለት ሆኗል። ዶክተሩ ጥቂት ይጠብቅ ሚስተር ለማ አለና ሌላ ሌላ ሥራ ይዞ ሲትረከረክ ጥቂት ደቂቃዎች አሳለፈ። ሚስተር ለማ ከባድ ጥያቄ ነው በጣም ከባድ። አግኝተኸዋል ሚስተር ለማ። አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ ታሪክ ማለት ነው። ስለዚህ አለቃ ለማ ኃይሉ የታሪክ ልጅ ማለት ነው። ታዲያስ ሚስተር ለማ አለኝ በፈገግታ። ምን አልክ ሚስተር ለማ። ወዲያው ግን ፊቱን ወደኔ መለስ አደረገና ብቻ ሚስተር ለማ አንድ ያልገባኝ ነገር አለ እርግጥ ስለ አማልክቶችህና ስለ አራቱ ሚሜስቶችህ በሆስፒታሉ በሙሉ የገነነውን ዝናህን እኔም ሰምቻለሁ ብቻ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ሆነህ ሌላው ቢቀር ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ጥቂት እንኳን ሳታውቅ ሳትሰማ ትቀራለህ። ልክ ነህ ሚስተር ለማ። ሚስተር ለማ አይደለም። ሚስተር ለማ ገና በፊት ተናግሯል። እውነት በድቤ ነው ሚስተር ለማ። ይልቅ ሚስተር ለማ አለች ነርሷ አሁን ምን ማድረግ ይሻላል። አንድ ልዩ ጭብጨባ ለሚስተር ለማ ይደረግለት። መቼስ ያን ጊዜ በእንግሊዝ አገር የሚኖሩት አፍሪቃዊ ሆነ እስያዊ ሰው ጥቂት ብቻ ነበሩ። የመንግስቱ ለማ የእጅ ፅሁፍ ረቂቅ የወዳጆቻቸው ትውስታ ወደር የለሹ የሞራል ጀግና አቶ ሀብተአብ ባይሩ ለአርታኢው እንዳጫወቱት ከመንግስቱ ለማ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቅነው ኮተቤ ትምህርት ቤት ነው። ታዲያ እጁ ተይዞ ወደ አራተኛ ክፍለጦር በእስረኛነት ከገባ በኋላ አንድ ቀን ስንጨዋወት ይገርምዎታል ከሞት ያዳኑኝ አቶ መንግሥቱ ለማ ናቸው አለኝ። ለምሣሌ በዚያን ወቅት ደጋግሞ ከሚሰነዝራቸውና ከሚወዳቸው አባባሎች መካከል አንዱ በአብዮት ጊዜም እንኳን አንድ ሰው ቀልድ ዘህጠህሆ መፍጠር ይችላል የሚል ነበር። መንግስቱ ለማ ብእቦነህ አሻግሬ ቅኔን ትርጓሜንና ዜማን በጎንደር በሸዋ በጎጃም ተምረው በ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ሀዲስን ከ ጀምሮ በሐረር አደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ የሀዲንና የሃይማኖተ አበውን ትርጓሜ ያስተማሩ ሊቁ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደታሪክ እመት አበበች ይልማን ያገቡና ሰኔ ቀን ሐረር ሳይ አደሬ ጢቆ መንግሥቱ ለማ የመጨረሻ ልጅ ሆነው ይወለዳሌ። አለቃ ለማ የቀጨኔ መድሃኒዓለም አለቃ ሆነው ወደ አዲስ አበባ ሲዛወሩም አብረዋቸው መጥተው በኮተቤ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በትጋት ይማራሉሌ። የኛ ይሁን የኛ ዓመት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እያለን ነው የተለመደች የብቸኝነት ጓደኛቸውን ሁለት ቢራ ለመውሰድ አብዬ አንድ ዘወር ያለች ግሮሰሪ ጥግ ይዘው ሲጎነጩ ከመካከላችን አንድ የእሳቸው ተማሪ የሆነ አንድ ሁለት ሲል አምሽቶ ሞቅ እንዳለው ዘው ሲል ዓይን ለዓይን ይጋጠማሉ።