Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የረጋ ሰው-1.pdf


  • word cloud

የረጋ ሰው-1.pdf
  • Extraction Summary

ስመሽ ተፈጥሮ ሁሉ ፀጥ ስል ፍቅር ከመኝታችሁ ይቀሰቅሳቹሃል አሁን ከሁሉም በላይ ፀጥታ ስሰፍን ልባችሁ ከተፍ ይላል አፍቃሪ ነፍስ በናፍቆት የምትሞተው ምሽት ላይ ነው ፀጥታ ፍቅር በውስጣችሁ እንድጎላ ያደርጋል ፍቅር ፀጥታ ነው አሳዎች በባህር ውስጥ ሰላም እንደልባቸው የምንወሳቀሱት ፀጥታ ስኖር ነው ትንሽየ የምጠራጠሩት ነገር ባህር ውስጥ ካለ መረበሽ ይጀምራሉ አዕምሮ ስመሽ የምሸነፈው በፅጥታ ሃያልነት ነው የሀይማኖት አባቶች ለረጅም ሰዓት ሰጥ ብሎ ይቀመጣሉ ፀጥታ ውስጥ ነው አንድ በጣም ተናጋሪ ይሆነ ሰውየ ነበር ይህ ሰው ሁሉንም ሰዎች ተናግሮ አናግሮ ማሸነፍ ይችላል በጣም ተከራካሪና ተነጋር አንደበተሪቱ ስለሆነ ሰዎችን በቀላሉ ያሸንፋል እናም ጋዜጠኛ ጠየቀው በምትኖሪበት አከባቢ ውስጥ ብዙ ሰው አሸንፈካል። ማንስ ነው አሸናፊ። ህያውና በድንስ ብወዳደሩስ በምን አይነት መስፈርት ነው የምወዳደሩት። አለም ወደ እንድ መንደር እየሄዴች ባለችበት ጊዜ እኛ እኮ እርስበርስ እየተገፋፋን ነው እውነታው ግን የምረባ ሃሳብ የትኛው ነው። እውነትስ ይህ አዕምሮ የእናንተ ነው። እውነታው ሁሌም ይህንን ጥያቄ ችላ ብላችሁ በማይረባ ሃሳብ እራሳችሁን ማጨናነቁ ነበር መሰረታዊ ጥያቄ መጠቀም ሳይሆን ለምንድ ነው የምጠቀመው ነው። ካለስ ምን ያህል ነው።

  • Cosine Similarity

ጫፍ መያዝ መሓል ያለውን አለመረዳት ነው አጠግብህ ያለውንም እንደጠላት ትቆጥራለህ በዘርህ መካከል ስትኖር ግን አጠገብህን ያለውን ጎሮቤትህን እንደውበት ትቆጥራለህ መሓል መኖር መረዳት ነው ከጫፍና ከከፍታ ውጭ ያለ ፍሴት ነው የተለያየው የሰው ቋንቋና ሀይማኖቱ እንጅ ፍጥረቱ አይደለም ሰው መነሻውን መገንዘብ ተስኖታል ምክንያቱም አንድ ነፍስና አንድልብ የያዘውን የራስህን አምሳያ አንተ የማትናገረውን ቋንቋ መናገር ስላልቻለ ብቻ የተለየ ፍጥረት አድርጎ ማስቡን ተምሮ ዶክተር ከሆነ ቦኋላ እንኳን ልቀይረው አልቻለውም ሰውና ባህር አንድ ነው ከአንደ ቦታ በፈልቁም አለምን ይዞራሉ አባይ ወንዝ ከኢትዮጵያ ብፈልቅም ብዙ የአፍርካ ሀገሮችን አቋርጦ ይሄዳል ሀገራችን ውስጥ እስካለ የሀገራችን አካል ነው ሱዳን ስደርስ የሱዳን አካል ነው ግብፅ ስደርስ የግብፅ አካል ነው እያለ ይቀጥላል ከኢትዮጵያ የተነሳው ውሃ ማንነቱን ሳይቀይር ሱዳን ይደርሳል ከዛን ወደ ግብፅ ያልፋል መነሻው የረጋ ሰው ቁቤ ነጥብ አንድ ነው አባይ ሱዳን ስለደረሰ ሱዳናዊ መሆን አይችልም ግብፅ ስለደረሰም ግብፃዊ መሆን አይችልም አባይ ውሃ ነው ሰውም እንደዛ ነው ኢትዮጵያዊ ስለተባልክ የተለየፍጥረት አይደለክም አሜርካዊም ስለተባልክ የተለየ ፍጥረት መሆን አትችልም ግብፃዊም ብትሆን ያው ነው አመራም ኦሮሞም ብትሆን ያውነህ የተለየ ፍጥረት አይደላችሁም ሰው ሰው ነው አንድ ኢትዮጵያዊ አሜርካ ብኖር ያው ነው ብቀይር ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን እንጅ ሰውነቱን አይቀይርም ፈረንሳያዊም ጀርመናዊም ብትሆን ለውጥ የለውም መነሻ ነጥባችን አንድ ነው ሰው ከምለው ሰው ይፈልቃል ዘርና ቋንቋ ሰው ላይ ያለ ገባር ወንዝ ነው ገባር ወንዝ ከዋናው ወንዝ ጋር ይደባለቃል እንጅ መነሻውን አይቀይርም ዘር ሀይማኖትና ቋንቋ ወደ ሰው ይደባለቃሉ እንጅ የሰውን መነሻ አይለውጡም አባይ ወንዝ ሱዳን ስደርስ ዋይት ነይል ገባር ብኖረውም አባይ አባይ ነው መነሻውን ነጥብ አያስጥልም አይቀይርም የጎሮበታችሁ ውበት በህይወት ሁሌንተና ውስጥ ያለ አብስትራክት መሳይ ስዕል ነው በሰከነ መንፈስ ካለያችሁ ውበቱ አይገባችሁም ህይወት ፊቷን የረጋ ሰው ቁቤ ባዞረችበት ወቅት የድረሱልኝ ጥርው ወደ ጆሮአችሁ አይገባም ምክንያቱም ሰባዊነትን በዘርና በጎሳ መካከል ገላችሁታልና ለብዙ ዘመን ቤቴክርስትያን ስለእምነት ስትሰብክ ኖራለች መሰጅድም እንደዛው ስለ መሃመድ ስስበኩ ኖሮዋል አንድም ጊዜ ስለሳባዊነት ለመስበክ አልደፈሩም ሳባዊነት የማይሰማው ሰው ላይ ስለእምነት ትምህርት ብሎ መድፋት ምንም ትርጉም የለውም ለዛ ነው ቤቴክርስትያን ስትቃጠል መስጅድ ለማቃጠል የምሮጡት መስጅድም ስቃጣል እንዳዛው ቤተክርስትያን ለማቃጠል የምሯሯጡት እምነታቸው ጎሮበትህ ስጎዳህ መልሰ ጉዳው በምል ሀሳብ ተመስርቶ የክርስትያንና የእስልምናን ከንቱ ስም ብቻ በህይወታቸው አንግቦ ከሳባዊነትና ከእምነቱ ነፃ ሆነው ያልፋሉ አጻፈታ ካለው እምነት ልሆን አይችልም በቀል ይሆናል ሰባዊነትን ያልተጎናፀፈ ሰው ርህራሄ በልቦናው አይኖርም እምነታችሁ ከሰው ሰባዊነት የተነሳ ይሁን ያኔ አምላክ በልባችሁ ያድራል በህይወታችሁ ውስጥ የረጋ ሰው ቁቤ በያዛችሁት ርህራሄያችሁ በኩል ልጆቹንና ጎሮበታችሁን ያናግራል የማይረቡ ሀሳቦችን በውስጣችሁ ባከማቻችሁ ጊዜ መንፈሳችሁን ታጨናንቃላችሁ በመንፈሳችሁ በኩል መፍሰስ ያለበትን ሀሳብ ለይታችሁ እስካል አወቃችሁም ድረስ የአንድት ሰከንድ ከንቱ ቃል ሀሳባችሁን መቆጣጠር አያቆምም ሰው እራሱን የምገነባው ሀሳቡ በመንፈሶቹ መካከል ሰላም ስያሰፍን ነው ከንቱ ሀሳቦች ግን ወደ አዕምሮዋችሁ በገቡ ማግስት መፍሰሻ መንገዶችን ይሸረሽራሉ በተባለሸው የህይወታችን ክፍል አዕምሮዋችንን ስንሞላና በእርባና ብስ ሀሳብ እራሳችንን ስናጨናንቅ መንፈሳችን ይረበሻል መንፈሳችን ስጨናነቅ ስሜታችን እንድ ሀምሌ ፀሐይ ይዋዥቃል ሰው ወጥ የሆነ መንፈስና ከመንፈስ ጋር የተስማማ ስሜት ከሌለው ወደ እብዴት ያመራል የተረጋጋ መንፈስ የስሜታችን መመላለሻ መንገድ ነው በተራጋጋ መንፈስ ውስጥ አንድት ወጥ የሆነች ነፍስ ለምስጋና ትቆማለች ከመንፈሱ ጋር ጥዋትና ማታ የምናበብ ሰው በአምላኩ ግዛት ውስጥ የሰላም አየር ስተነፍስ ይኖራል የረጋ ሰው ቁቤ አንድት አሮጊት እንድህ አለች አብጄ ነበር ያበድኩት ግን የማስበውን ካለማወቀ የመጣ ነገር ነው ብዙ ሰዎች ማሰባቸውን እንጅ ስለምን እንደምያስቡት እንኳን በቅጡ አያውቁትም ስለምን እንደምናስብና ውጤቱን ለይተን የማንናውቅ ከሆነ ሀሳባችን መልሶ የጭንቀት ስሜት ያሳድርብናል የጭንቀት ስሜቱም ሰው ልጅ በሩን እንድዘጋና ለብቻ ቁጭ ብሎ ስሜቱን በውስጡ እንድያግል እድሉን ይፈጥራል የጭንቀት ስሜቱም በእኛ ውስጥ እኛ ከንቃታችን እስከምንላቀቅ ድርስ ከእኛ ጋር ይኖራል በንቃታችሁ ስር ወጣችሁ ወደ እብደት ህይወት ከገባችሁ ቦኋላ የምታገኙትን ስጋት አልባ ህይወትና ነፃ የሀሳብ ሞገድ በንቃት እያላችሁ ለማግሄት ተለማመዱ አንድ ሰው አድስ ህይወት መንገድ ለመጀመር ጥበብ አያስፈልገውም የምያስፈልገው ነገር ብኖር ዝግጁ መሆንና የተረጋጋ ፀጥታ የሞላበትን የህይወት መንገድ በውስጡ ማስቀመጥ ነው ጥበብ የምፈሰው ዝግጁ በሆኑ ነፍሶች መካከል ነው በማይረባ ነገር ግን በሁሌንተናችሁ መካከል የእናንተ ስብእና መስሎ የተቀመጡትን ከንቱ ሀሳቦች ከውስጣችሁ የረጋ ሰው ቁቤ ነቅላችሁ አውጡ ሀሳባችሁ እንደ ህፃናት ሀሳብ ይሁን አንድ ነገር ላይ ረግቶ ጊዜ ወስዶ እንደቀመጥ አታድርጉት አንድ የማይረባ ሀሳብ በውስጣችሁ አኑራችሁ ስለሀሳሱ አብዝታችሁ ማሰብ ስትጀምሩ ለራሳችሁ ደስታና ሀሴት ጊዜ ታጣላችሁ ሁሌም አንድ ነገር በህይወታችሁ መካከል አኑሩ እኔ ዛሬ እየኖረኩ ነው የምለውን ሀሳብ በህይወታችሁ ያዙ በዚህም በኩል ደስታችሁ በአሁን የተከበበ ለከንቱ ሀሳቦች ጊዜ የማይሰጥ ይሆናል ይህም ስሆን በህይወታችሁ የተረጋጋና ፀጥተኛ ሰላም በውስጣችሁ ማሳደር ትችላላችሁ የረጋ ሰው ቁቤ የወደቁ ነገሮች አጎቴ እጄን ይዞኝ መንገድ እየሄድን ሳሌ ይዣት የነበረችሁ ሳንትም ከእጀ ወደቀች የወደቀችሁን ሳንትም ለማንሳት ጎንበስ ስል አጎተ የያዘውን እጀን ይዞ ጎቴተኝ አጎቴ ሳንትም ወድቆብኝ ነው ማንሳት አለብኝ አልኩት እርሱን ግን እጄን ይዞኝ ምንም መልስ ሳይሰጠኝ ሄዴ ሳንትሙን ባለማንሳተ እየተበሳጨው ተከተልኩት ትንሽም እንደተራመድን እንደህ አለኝ አንድ አንድ በህይወትህ ውስጥ የምወድቁትን ነገሮችን አታንሳቸው ምናልባት ቀድሞውኑ የተቀመጡበት ቦታ ላይመቻቸው ይችላልና ብዙዎች ከህይወታቸው የወደቀውን ነገር ለማንሳት ጎንበስ ባሉበት ቅስበት የደስታቸው አብሳር የሆነች ተወርዋሪ ኮከብ አልፋቸዋልች የወደቀውንም ለማንሳት ጎንበስ ያሉትም በወደቀው ነገር ስባት ተስበው እራሳቸው ወድቀዋል አንዳንዶች ደግሞ ነገሮችን ንቆ ጥለዋል ትንንሽ ውስጣቸው ተቀምጦ የምረብሽ ነገሮችን ከውስጣቸው ነቅለዋል ትንንሽ ናቸው ያሉት ነገሮች ትልልቁን የረጋ ሰው ቁቤ ጥለዋል ንቀት ትንሸ ለማኝ ብመስልም ስያድር ግን ክፉ ንጉስ ይሆናል ሌሎች ደግሞ አምሳሉ የሆነውን ሰው ስወድቅ ጥሎ አልፏል ንጉስ ባሪያዎችን መናቅ በጀመረ ጀንበር የዙፋኑ ወንበር መነቃነቅ ይጀምራል ባርያ በጉልበት የምትገዛው በአንድ ሀሳብ ሁነው የክፉ ንጉሳቸሁን የበደል ጅራፍ ማስብ እስካልቻሉ ነው የክፉ ንጉሳቼውን የጅራፍ ጭወት መስማት ከጀመሩ ግን ማመፅ ይጀምራሉ ሰው አንዱ ሌለኛው ውስጥ የምኖር የአምላክ ፍጥረት ነው እኔ ውስጥ ያለው ሰው አንተ ውስጥም አለ እኔ ከአንተ ጋር የተሳሰርኩት በዝምድና ብቻ አይምሰልህ ማየት በማንችለው የአምላክ እጅ በሆነው ፍቅር ነው በዛም ትስስራችን መንፈስህ ወደ እኔ የምገባው የአንተ የቀኝ እጅ ሆኖ ነው አንተን ስያምህ የምያመኝ እኔ ስደሰት የምትቦርቀው በማናየው ነገር የመተሳሰራችን ምስጢር ነው ጠላት የጠላቱን ሞት ስሰማ የምያዝነው ተቀናቃኝ ስላምያጣ ነው ይህም የትስስራቸው የጥላቻ ገመድ ነው የእኔ መንፈስ ላንተ ባለኝ አመለካከት መሓል ይኖራል የረጋ ሰው ቁቤ ባንተ ግዛት ውስጥ ፍቅር ለመዝራት ከመጣው አንተ ሪስትማሬት ሁኔኝ የሰብሉንም ፍሬ አብረን በፍቅር እንበላለን አኔ እሳት ሁጄ ወደ ግዛት ስመጣ አንተ ደግሞ ውሃ ሁኔኝ እሳት ይዥ የምመጣው እርስትህን ለማጥፋት ነው አንተ ግን ቀድሜህ አጥፋኝ በልብህ ውስጥ ባስቀመጥከኝ መጠን ወደ ግዛት እመጣለሁ የግዛትህን በር ክፊት በተውክልኝ ጊዜ ከአንተ ጋር አኖራለሁ የፊት ፈገግታክ ከትላንትናው አንድት የጤፍ ፍሬ በጎደለች ጊዜ ከግዛት እለቃለሁ በትዕቢት ወደ ግዛትህ አትጋብዘኝ የጊዛቶች መሶሶ በፍቅር እስካልታነፁፀ ድረስ የሃያልነትህ መለክያ አታድርገኝ እኔ ከንቱነኝ ከንቱነተን የምረሳው አንተ በውስጥ በምትሰጠኝ የፍቅር ግዛት ነው የግብዞች ግዛት ብረት በለበሱ ሎለዎቸ ይጠበቃል የብፁሃን ግዛት ግን በር የለውም በበራቼው በኩል የምታልፈውን የአምላክ የእጁ ጥበብ የሆነችሁን ትንኝ ወደ ቤታቸው ይጋብዛሌሉ የአንድ ፃድቅ ግዛት ለትንኝ ነፍስ ከግብስ ንጉስ ነፍስ በላይ ትራራለች እኔ የአምላክ ትንኝ ነኝና የግዛቶችህን በር አትዝጋብኝ የረጋ ሰው ቁቤ በእርጅናየም ወራት ማሬት ላይ የምንፏቀቅ ትልነኝና ሃያልነትህን ልታሳየኝ ብለህ አትርገጠኝ በረገጥከኝም ጊዜ ለመሬት ቅርብ የሆኑት አንደበቶቼ ብጮሁም ወደ አንተ አቤቱታየን ልያሰሙ አይችሉምና እራህን በደም አታጨማለቅ ይልቅ በለስላሳ እጆችህ የደረቁ እግሮቼን እጠብ እኔ ድግሞ ለአምላክ ቅርብ በሆኑ መንፈሰ እምርቅሃለሁ በጊዛቶቼ ውስጥ ያፈራዋቸውን ጥበብ አስተምርሃለሁ ከአምላከም ጋር ያለኝን የብኩርና ክብረን አወርስሃለሁ በእስትንፋሴም መካከል የሀዘኖችህን ቀን አበዛለሁ በሀዘኖችህም ቀን የአምላክን የጥበብ ስራዎች ታከናውናለህ በዘነች ነፍስህ ውስጥ የድሆችን እንባ ወደ አምላክ ታደርሳለህ ሰፍ ግዛት ባለው ልብህ መካከል አለም ርስት የከለከለቻቸውን ድሆች ሪስት ትሆናቸዋለህ አንተ በደሆችና በአምላክ መካከልም የቆምክ አለቃ ሳትሆን አገልጋይ ባርያ ነህ በልብህ መካከል እንደ ሁለንተናክ አኑራቸው ይህ የማናየው ያስተሳሰረን ፍቅር ነውኖ የረጋ ሰው ቁቤ መካፈል ሁሌት በገዳም ውስጥ የምኖሩ ብላቴናዎችን አንድ አባት አስጠረተው ብርቱካን ሰጧቼው ልጆቹም ብርቱካኑን ይዘው መንገድ ላይ እየተጫወቱ ስሄዱ ራባቸውና ብርቱካኑን መብላት ፈለጉ ይህን ጊዜ ብርቱካኑን የምያካፍልላቸው ሰው ስፈልጉ አንድ አባት መጡባቸው ልጆቹም ወደ እኔሱ በመቅረብ ብርቱካኑን እንድያካፍሉላቸው ለመኑ አባም ልጆቹን ከሰመሙ ቦኋላ አብራችሁ ብሉ ብለው አጠገባቼው አለፉ ብላቴናዎቹም ብርቱካኑን የምያካፍልላቸው ሰው ብያጡም እየተጫወቱ መንገዳቸውን ቀጠሉ ትንሽም እንደተራመዱ ሌላ አባት ይመጡባቸውና ብርቱካኑን እንድያካፉላለቸው ይጠይቃሉ አባም በአባትነት ፈገግታ ፈገግ ካሉ ቦኋላ አብራችሁ ብሉ ልጆቼ ብለው አጠገባቸው አለፉ ልጆቹም እኛ ይህንን ብርቱካን ብንካፈል አንዱ ለአንዱ ልያስበልጥ ይችላል ስለዚህ አንድ የምያካፍልልን ሰው የረጋ ሰው ቁቤ ያስፈልጋል ተባብለው ሌላ ሰው እየፈለጉ መንገዳቸውን ቀጠሉ ልጆቹም መንገዳቸው ላይ በጫወታ ታጅበው ስሄዱ አንድ አባት ዛፍ ስር ተቀምጦ አዩና ወደ እኔሱ ሂዴው ብርቱካን ተካፍሎ መብላት እንደፈለጉና የምያካፍላቸው ሰው እንዳጡ ደግሞ ሁለት አባት ጠይቀው አብራችሁ ብሉ እንደተባሉም ጭምር ነገሯቸው አባም እንድህ አሉ ብርቱካኑን አብራችሁ ብትበሉ እንጅ እዚህ በምንኖርበት አከባብ መካፈል የምባል ነገር የለም እዚህ ያለው ህይወት የአብሮነት ህይወት ነው ሁሉም ነፍሶች በአንድ ሀሳብ ለምስጋና የምቆሙበት ቦታ ነው የአንዱ ነፍስ ህመም ለሁሉም ነፍስ ይተርፋል የሌላው ነፍስ ፈሽታ ለቀሩት ደስታ ነው አንድ ዜማ በተመሳሳይ ጊዜ ከልባቸው የሚያፈልቁ ሰዎች ብቻ ይኖራሉ የአባቶችም እይታ ከተለያየ የህይወት ገፅ ብቀዳም በአንድት ቀጭን መንገድ የምፈስ ምንጭ ነው በዚህም ስፍራ ሁሉም ሰው የተፈጥሮ አየርን ወደ ውስጥ የምያስገባበት ቅስበት አንድ ነው ከዛም አለም ወደ እዚህ ስንሸጋገር የመከፋፈል ስሌት ከህይወታችን ክፍል ሰርዘን ነው እዚህ ያለው ህይወት የረጋ ሰው ቁቤ የአብሮነት የጋራ ህይወት ነው ከራስ አልፎ ለሌላው ወገን የሚቆም መልካም ተግባር ነው አለም ስለደስታ ስታስተምር ስጋችሁን ምሳሌ ወስዳ ነው እዚህ ግን ደስታን የምያስተምሩት አምላክ በነፍሳችን ውስጥ በብርሃን ገፆቹ ስያልፍ ነው በብርሃን ገፆቹም ፍቅርና ርህራሄ በውስጣችን ስያስቀምጥ የፍጥረትን ፀሎት በልባችን ወደ አምላክ እናቀርባለን አለም እርኩስና ቅዱስን ነገር መለየት ስለማትችል ሁሉንም ነገር የደስታ መንገድ ነው ብላ ታስተምራለች እዚህ ግን የደስታ መንገድ በምስራቅ በኩል ወደ ሰው ልጅ ህይወት ይፈሳል የሰው ልጅ በምስራቅ በኩል የምትፈሰውን ደስታ በምስጋና ይቀበላል በነፍስ መካከል የምትጸልየው ጸሎት በሀሴት ተሞልታ ወደ አምላኳ ትደርሳለች መካፋፈል እዛው ጥለን የመጣነው አስተምሮት ነው አሁን ያለን አስተምሮት አብሮነት የተሞላውና ፍቅር ይዞ ርህርሄን ያካተተ ትምህርት ነው ፍቅርን በህይወቱ ውስጥ የምያፈስ ሰው የርህራሄ መንፈስ ይበዘዋል ፍቅር ህይወታቻን ስሆን ርህራሄ ደግሞ ድርግታችን ነው ያን ጊዜ ነፍሳችን በአምላኳ አይን ውበት ይኖራታል የረጋ ሰው ቁቤ የተመረጠችና የተወደደች የምትሆነው በፍቀር ጎብኝታ በርህራሄ ስትሰጥ ነው እዚህም ውስጥ የዘርና ቋንቋ ልዩነት የለም አብሮነት ውስጣችን ስገባ ልዩነት ከውስጣችን ይተናል ከተሰበረ ልብ ውስጥ ፍቅር ስፋስ ከምያነቡ አይን ውስጥ እንባ ይፈሳል በተሰበርም መንፈስ ውስጥ ድንበርና መከፋፈል ይጠፋል ሰው ልቡ ተሰብሮ አይኑ ስያነባና መንፈሱ ስዋሃድ ሁሉንም ፍጥረት እንደቤቴሰብ አድርጎ ይቆጥራል ከተሰበሩ ልብና ከምያነባው አይን የምወጣው ህይወት የመስጠትን ጥበብ ትካናለች አንድ ክርስትያን ለተቸገሩት ድሆች በራራ ጊዜና እጁን በዘረጋላቸው ጊዜ ለአምላኩ ያበድራል መስጠት የአማኝ የሁል ጊዜ ድርግቱ ነው አሁን ግን የምሰጥ እጆች በስግብግብነት ተይዘው መዘርጋት እያቆሙ ነው መስጠትም እንደ ባህል በአመት አንድ ጊዜ የምከበሩ ባህሎች እየሆኑ መቷል ይህም ስግብግብ ሀሳቦች በህይወታችን ስርስሰዱ የምሆን ስሜት ነው መስጠት የአምላክ ቀኝ እጁ ሲሆን በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ስገኝ የምናደርገው ተግባር ነው የአምላክ ቀኝ የረጋ ሰው ቁቤ እጅ በህይወታችሁ እንድኖር ለግሱ መለገሳችሁም ሀሴት ነውና ያለህን ነገር ለድሆች ስትሰጥ አምላክ እጆችህን በበረከት ሞልቶ በሰጠው ቦታ ይክስሃል በመስጠት ጊዜ የምናገኘው ሀሴት የአምላካችን ቅስበታዊ የደስታ ስሜት ምላሽ ነው እናም ልጆቼ እዚህ ያሉ ሰዎች የጋራ ሁለንተና ስለምኖሩ መከፋፈል የምለው ቃል በዚህኛው ህይወታችን ውስጥ ትርጉም የለውም ቃሉንም ረስተናል የረጋ ሰው ቁቤ እንባ አንድ በደጃፈ ስታልፍ አንድት ዘለላ እንባ አስቀምጠሸ እለፍ ሙሉ ታርካችን ከእንባሽ እረዳለሁ የጎደለውን የታርካችንን ክፍል በእንባየ እሞላለሁ ውዴ የአንድ ሰው እንባ የግል ንብረት ነው የሁለት ሰው እንባ የጋራ ነው የሶስት ሰው እንባ ግን የሀገር ነው የአንድ ሀገር አሳዛኝ ታርክ በብዙ ሰዎች እንባ የተፀፈ ታርክ ነው የአንድ ሀገር የደስታ ታርክ ከሶስትና ከዛን በላይ ባሉት የሰዎች ሳቅ የተፃፈ ነው ፍቅሬ የእኔና ያንች እንባ ኩሬ ስሆን የሶስት ሰው እንባ ደግሞ ባህር ነው ገና ልጆች ወልደን ሌላ እንባ እስከምንጨምር ኩረያችን እንዳይደርቅ ከውስጣችን እናንባ በእንባችንም መካከል ገና ሀገር የምሆኑ የምናልባት ልጆች ይፈለፈላሌሉ በዛሬ እንባችን ውስጥ ነገ የሳቅ ዘመናችን ይታየኛል የጨለማ ዘመን በአንባ ካልሆነ በምንም አይነጋም ለነገው ፈሽታ ዘመናችን የዛሬው የእንባ ቀናቶች ድልድይ ናቸው እረፍት ከጭንቀት ቦኋላ ስመጣ ይበልጥ ትርጉም የረጋ ሰው ቁቤ ይኖረዋል ከመራራ ቆምጣጠ ቦኋላ የምሰጥሸ ጨው ከማር የበለጠ ይጣፈጣል አንድ ወዳጄ እንድህ አለኝ እኔ ፍቅሬን ሳገባ ደጉ አብርሃም አባቴ ነበር ደጓ ሳራም እናቴ ነበረች በሁለቱ ስመረቅ ኢየሱስ ምስክር ነበር ለዛ ቀን አምላክነቱን ከምስክር ጋር አዋህዶ ከጎነ ቆመ እንደዛማ ባይሆን ኑሮ እኔ እሷ በምድረ በዳ ሳገባ ሌላ ምስክር ማን ይኖረኝ ነበር ሳራንም እዛን ቀን ከአብራሃም ጋር እንድ ለዘመናት ምሳሌ ሆኖ የኖረ ፍቅር እንዴት ገነባችሁ ብየ ጠየኳት እሷም ሁሌም እሱን እንባዋ መካከል ደብቃ ይዛው እንደኖረች ነገረችን አብርሃምም እንደዛው በእንባዎቹ መካከል ሳራን አንግቦ እንደኖሬ አወጋኝ እንባ የፍቅር መመላለሻ መንገድ ነው የአንድ አፍቃር እንባ በአምላክ እግር ላይ ታርፋለች የአምላክም ዙፋን በፍቅር ከሰዎች በምፈስ እንባ የተገነባ ነው ሰው በእንባም የአምላክን ዙፋን ያንኳኳል የእውነታችንን ህይወት ከእኛ ጋር የምቆየው በእናባችን መካከል ፍቅርን ስንዘራ ነው ሰውም ያየውንና የሰማውን የአምላኩን እውነት በአይኖቹ በኩል እንባ እያፈሰሰ ይመሰክራል የረጋ ሰው ቁቤ እንባችን የቅድስና ዘመናችንን በውስጣችን የማኖር ጥበብ ነው በእንባችን በኩል አምላክን ስንጠራ ለእኛ ይበልጥ ይቀርባል የሰው ልጅ እንባ የአምላክ እግር ላይ ስፈስ የሰው ልጅ ደም የአምላክ ልብ ላይ ይፈሳል በልጆቹ እንባና ደም አምላክ እጅግ ይከፋል ሀዘኑም የሰውን ልጅ አጥንት ይሰብራል ከውስጣችን የምፈሰው እንባ የእውነታችን ፍሬ ነው ፍሬውም የአምላክ ማሳ ውስጥ የምዘራ እህል ነው በማሳው ውስጥ የምዘሩም ፍሬ በተለያየ ጊዜም ብዘራ ሁሉም በአንድ ጊዜ ይደርሳል ፍሬውም የማይበላለጥ እህል ያፈራል እህሉም በደረሰ ጊዜ በመላእክቶቹ ወደ አምላክ ጎተራ ይሰበሰባሉ ፍቅሬ የእንባችን ዘመን በአምላክ ለስላሳና ውብ እጆች እንድዳሰሱልን የእናበ ዘመንሽን ተግተሸ አንብ የሰው ልጅም ህይወት ልክ እንደሳንትም ሁሌት ገፅታዎች አሉት በዝህኛው ዘመን እንባ የዘራ ነፍስ በቀጣዩ ህይወት ደስታን ታጭዳለች ባየነው በዳሰስነውና በሰማነው እንባን ስናፈስ በማናየውና በንዳስሰው ደስታን እናጭዳለን የረጋ ሰው ቁቤ የደስታና የሀዘን ህይዎቶች በአንድ ነፍስ ውስጥ ያልፋሉ ሁሌት የተለያዩ ብመስሉም በአንድ ሳንትም ላይ ያሉ ሁሌት ጎንዮሽ ናቸው ህይወት በአንድ በፍቅር ጎን ያለ ሁሌት የደስታና የሀዘን ጎኖች ነው የፍቅር ጎን ሁሌቱንም የሰው ልጆች የደስታና የሀዘን መልክ አንድ ላይ የምይዝ ፀጋ ነው ፍቅሬ የሀዘናችን ጎን ስገለበጥ የደስታችን ጎን እናገኛለን የሁለቱም ጎኖች ህልውና ግን ፍቅር ነው የእኛም ህይወት የሀዘን ጎንን በእንባ ስያዘም የደስታ ጎንን በሳቅና በምስጋና ያዘማል እናም ፍቅሬ የትንሽዬ ቀናት ጥርቅም እንባ በዘላለም መካከል ፍፃሜ የሌለውን የዘላለም ደስታን በሰው ህይወት ውስጥ የመፍጠር ጥበብ ነው የረጋ ሰው ቁቤ ዝምታ ሁሌት ዝምታየ ከመካነ መቃብር በላይ ገስፎ ከታየሽ ፍቅሬ አትስግ በዝምታየ መካከል የአምላክን የሹክሹክታ ድምፅ እየሰማው ነው የአምላክን የሹክሹክታ ድምፅ መስማት የምችለው በዝምታው መካከል የሰከነ መንፈስ ከተፈጥሮ ሰላም ጋር አዋህዶ የያዘ ሰው ነው የአምላክም የሹክሹክታ ድምፅ ከአሌት ስር የተረገጠችን ትንኝ ያፅናናል የሹክሹክታው ድምፅ በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ውብ ዜማ የምሆኖው ጣዕም ባጣ ህይወት ውስጥ የእሱን የመፅናኛ ቃላቶች ስንሰማበት ነው ብዙዎች እርሱን ስከተሉት የነበሩ ብሆኑም እንድህ ተባብሎ ይጠያያቁም ነበር ማነው መሳርያ ሳይ ኖረው በቃላቱ ብቻ ውብ ዜማን ማፍለቅ የምችለው ይባባሉ ነበር ቃላቶቹ እጅና እግር አውጥተው በውስጠ ስሯሯጡ በዝምታየ መካከል ቁጭብየ ሰማለሁ ለስላሳ እግሮቹ አሌት ልብን ስረግጡ የእሱ ህመም ይሰማኛል በቃማኛ የረጋ ሰው ቁቤ ግርሳ የተወረሩት የልበ ጊዛቶችን ስያፀዳ በምምገው የሰላም አየር መካከል ችግሮቼን እተነፍሳለሁ የመንፈሰንም ጥማት ልቤ ላይ በምገነባው ማደሪያው እስትንፋሱን ስያወጣ ይታደሳል ሰው ከቃሉ እራሱን የምያንፀው በዝምታው ጊዜ ከራሱ ጋር ስታደሰ ነው ከአንደበቱም የምትወረወር አንድት ቃል ገምሱን ንጉስ ስታደርገው ገምሱን ደግሞ የንጉሱ ባርያ ታደረጋለች ሰው ከአንደቤቱ በወረወረው ቃሉ ጋር ትግል ይዞ ይኖራል ደካሞች ታግሎ ከቃላቼው በታች ሆኖ ስሸነፍ ሞኞች ደግሞ ከቃላቼዉ በላይ ነን ብሎ ስያስቡ ባዶ ሆነው ያልፋሉ ጥቅት ብልሆች ግን በቃላቸው በመገኘት በጥበብ ይኖራሉ ሰው ሰላሙን የምቀማው ከአንደበቱ በተወረወሩ ቃላት ነው ቃሉ ላይ ቆሞ እራሱን ስያንፅ ከቃሉ በታች ሆኖ ደግሞ እራሱን ያፈርሳል በቃሉ ስገኝ ግን ከመንፈሱ ጋር ይዋሃድና ከእውነት ጋር ከፍ ይላል የቃል መዘዝ ሴፍ ከምመዝ በፍት የምኖር ክፉ እርሾ ነው ሴፍ የክፋት ዳቦ ለመድፋት የምጠቅም የአሳት ማገዶ ነው የክፋት ቃላቶች ከተሸከመች አንደበት ይልቅ የረጋ ሰው ቁቤ ድዳ ጆሮ በአምላኳ ዘንድ ትፀድቃለች በክፋት የተሞላች ነፍስ የዝምታ ቀናቶች አይኖሯትም የምላሷ ክፉ ቃላት አለመወርወር እንደ ድዳ ትቆጥራለች ለክፉ ነፍስ የዝምታ ቀናት የፍርድ ቀኗ ነውና የዝምታ ቀናትን ትጠላለች የዝምታሽን ዘመን ከመንፈስሽ ጋር በመግጠም የሰላም አይር ወደ ህይወትሽ እንድ ገባ አድርጊ የሰላምሽ አየር ከአንች ጋር ለምኖረው መንፈስ ምግብ ነው ነፍስሽ ትመገበዋለች ስጋሽ ትታደሳለች በህይወትሽ መካከል የምፈሰው እስትንፋስሽ በደስታ በውጥስሽ ይመላለሳል ሰው እስትናፋሱን ስያዛባ መንፈሱ ሰላም አጥቶ ይረበሻል እስትንፋስሽን በልብሽ ላይ አድርጊ ያን ጊዜ ልብ ምትሽ እራሱን በፍቅር ያዛል እናም ፍቅሬ በውብ ነፍሴ መካከል የዝምታ ቀናቶቼን ዜማ በአምላክ ሸክሹክታ እየሰማው ነውና አትስግ በዝምታየ መካከል የነገህ ከእኛ አብራክ የምፈለፈሉትን ነፍሶች ለአምላክ አደራ እያልኩት ነውና አታስብ በእኛ መካከል የምቆሙ የመልካም መንፈሶች ባሌቤት እንድሆኑ እየለመንኩት ነውና አትረብሸኝ የረጋ ሰው ቁቤ ፍቅሬ በዝምታየ መካከል የአምላክ ሹክሹክታ የማዳምጠው ሺህ የክፋት ቃላት የምደመስስበት አንድት ከዳዊት ጠጠር በላይ የጠጠረች የማሸነፍያ ቃላት እንድሰጠኝ በትንሽየ ትዕግስት መሃል የሱን ፍፃሜ የሌለውን ቼርነት እየጠበኩ ነውና ዝምታየን አትፍሪ የአምላክ ስጦታ በአንድ የንግስ በኣል ላይ ሰዎች ስሌታቸውን እያስገቡ ነበር ስሌቶቹን ከምያስገቡት መካከል ውስጥ አንደኛው ተነሳና እንድህ አለ አምላከ ልመናየን ሰምቶኝ ከበሸታ ፈውሶኛልና ለክብሩ መገለጫ ስል አንድ ሺህ ብር አምጥቻለሁ እልል ብላችሁ አመስግኑልኝ አለ ምዕመናኑም ካሉበት በጭብጨባና በእልልታ አስተጋቡ ሁሌተኛውም ተነሳና የስሌቱን መንስዔ ተናገረ አምላኬ ችግሬን ተረድቶ ደርሶልኛል ልጄ ለብዙ ዘመናት ተምራ ያለስራ ቤት ውስጥ ተቀምጣ ነበር አሁን ግን ቸሩ መዳኒአለም ደርሶልኝ ልጄ ስራ አግኝታለች እኔም ለአምላኬ ስራ ለክብሩ መገለጫ ስል አንድ ጊደር የረጋ ሰው ቁቤ አምጥቻለሁ እልል ብላችሁ አመስግኑልኝ አለ ምዕመናኑም ከምስራቅ እስከ ምእራብ በጭብጨባ በእልልታ አስተጋቡ ሶስተኛው የስሌቱን ምክንያት መናገር ጀመር አምላከ በህይወተ በደስታ እንድኖርና እንደምኖርም ስለደረገኝ ደስ ብሎኝ አንድ በግ ለክብሩ መገለጫ ስል ይዢ መጥቻለሁ እኔን ደስ እንዳለኝ እናንተም ደስብላችሁ አመስግኑልኝ አለ ምዕመናኑ ከዚህም ከዛም በእልልታ መስጋናቸውን አቀረቡ እንደዝህ አይኔት የምስጋና አገልግሎት ብጠቀም ደስ ይለኛል ምክንያቱም ከበሽታ ስላዳነን ብቻ ቀን ጠብቀን ማመስገን የለብንም ለችግራችን ብቻ ስለደረሰልን ቀን ቆርጠን ማመስገን የለብን ባጠቃላይ ምስጋናችን ከሀዘንና ከችግር ጋር ብቻ የተያያዘ መሆን የለበትም አምላክ በቸርነቱ ደስተኛ ስላደረገንም ማመሰገን ይገባናል ደስታችን ራሱ የምስጋናና የአምልኮዋችን መነሻ ልሆነን ይገባል ደስተኛ ከሆነች ነፍስ የምትወጣው ምስጋና አምላኳ ፊት በብርሃን አክልል አግጣ በፈገግታ ታጅባ ትቆማለች የረጋ ሰው ቁቤ የህይወትን ሃያልነት ፈርቶ ለፍቅረንዋይ የተንበረከኩት እንደምወድሽ ለመፃፍ ብዬ ወረቀት ገለፅኩና ተውኩት ከዚህ በታች የምፅፈው ሀሳብ እንጅ ስሜት አይደለም ወረቀት ሀሳብ እንጅ ስሜት አይዝም ስሜት ከባሌበቱ ልብ ውስጥ ብቻ የምፍልቅ የእውነት ፅዋ ነው ወረቀት ላይ የምያልፍ ሀሳብ በድን ነው በባሌበቱ ልብ ውስጥ ያለ ስሜት ለዘለላም ህያው ነው ሀሳቦች ላለውና ገና ለምመጣ ትውልድ የምቃረም ፊደል እንጅ ምንም አይደሉም ስሜት ግን ሀይል ያለው ፍርሃትን የምያስወግድልን ድፍረትም ጭምር ነው ልፃፍስ ብል የነገ ቀናችንን ነው ወይስ ስላለፈው ፍቅራችንን ነው የምፅፈው ስላለፈ ከሆነ ትላንት ነው ስለምመጣው ከሆነ ምናልባት ነው ከህይወት እቅፍ ውስጥ ሆነሽ በነገህ ፍራቻ መተንፈስ ያልቻልሽሁን አለኝ ስለምትይው ህይወት ነው ዛሬ ላይ የምፅፈው የፍቅርን ነፃነት ሀያልነት ውበት እኮ ሰው በራሱ በፈጠረው የነገን ቀን ፍራቻ ከዛሬው ህይወቱ ላይ ፊቆታል ፍቅሬ ንገርኝ ስለመቸ ፍቅራችን ልፃፍ ትላንት ተቃቅፈን የረጋ ሰው ቁቤ የተለያየውን በድንሽን አቅፌ በድኔን አቅፈሽ ከንፈራችን ብቻ የተናበበውን የፍቅራኛሞች ፍቅር ከፍርሃት ነፃ የምትሆነው በምገናኙበት ቅስበት የአንድት እይታ ፈገግታ ብቻ ነው ከዛን ቦኋላ ያለው ወግና ፍቅራቸው የምሆነው ነገህ ህይወት የችግር የበላይነት ቀንበሯን ይዛ ወደ ነገ ቤታቸው የምትመጣበት ፍራቻ ይሆናል ማንስ ነው ነገን አሸንፎ ወደ ሌለኛው ነገ ለዘላለም ተሸጋገሬ አንድት ነገ ያሉት ቀን ዛሬ ትሆንን የነገን ነገ ለዘላለም ትቀማናለች በነገ ፍራቻ መካከል ማንም ዛሬን አላለፈም በዛሬ ህይወት ያለው ፍቅር መካከል ግን የነገን ፍርሃቻ ጥቅቶች አፍርሷል የነገህሀ ፍራቻ ፍቅሬ ዛሬያችንን የምገድል ሃያል ነው በያዙትና በምራመዱበት መንገድ ላይ ጨለማና ብርሃን እንቅፋትና ድሎት ሀዘንና ደስታ የግድ ይኖራሉ ህይወት ሁሉን ፍሬ ያዘለች ሙሉ ቀንነችና በቀኖቹም መካከል ያሉ የብርሃንና የጨለማ ቀኖች በአንድት የጋራ በሆነች የፍቅረኛሞች ፈገግታ ድል ይነሳሉ በአንድት እስትንፋስ መካከል ያለች ፍቅር መሰረቷ ከተያዘ የዘላለምን የህይወት መንገድ ታመለክታለች የፍቅር ሀያልነት የምገኘው በአንድት ቅስበታት በዘነችው የረጋ ሰው ቁቤ ነፍስ ላይ የምነሳው ወላፈን የልባችንን የብርሃን ወጋገን ስያገኝ ነው በልበችሁ ውስጥ ለዘላለለም የምቀመጠው በነፍሳችሁ በኩል የተላከ መልክት ብቻ ነው የቀረው በጊዜ ህዴት የምመጣና በራሱ ጊዜ የምጠፋ መሰረት የሌለው ጊዛዊ ስሜት ነው የብዙ ልባችን ጥረቅም የሆነው ትልቁ ልብ ሁሉንም ያስተሳሰረው በዛሬ ባለችሁ ከፍርሃት በፀዳችሁ ቀን ውስጥ ነው በራሱ ፈጥሮ በራሱ ፈርቶስ እስከመቸ የሰው ልጅ ተንበርክኮለት ይችላል ተያይዘን ወደ ከፍታው እንውጣና የአምላክን ሽክሹክታ እንስማ በፍራቻና በዛቻ ከምኖሩት ማህበረሰብ እንገለልና በተፈጥሮ መካከል ያለውን ነፃነት እንጎንጭ አለሜ ነፃነት በአንድ ሰው ወይም በአንድ የድርጅት የምመጣ ነገር አይደለም ነፃነት ከፍጥረት በላይ ከፍያለና ከአምላክ በታች ዝቅ ያለ በሰውና አምላክ መካከል ያለ ከፍታ ነው አምላክ ዝቅ ስል ፍጥረት ከፍ ስል የምገናኙበት ቦታ ነው የፍጥረትና የአምላክ ውይይት የሰውና የአምላክ ልብም እዛ ቦታ ላይ ነው የተሳሰረው በከፍታችን ውስጥ አምላካችን የማየት ጉጉታችን የምጨምረበትም ቦታ የረጋ ሰው ቁቤ ነው ማቼ ትመጣለህ ማቼስ እንመጣለን ልናይ ናፍቀናል ከዚህ ሁሌ ከምንገናኝበት ቦታ ይዘሄን ሂድና ለዘላለም አብሬን እንኑሩ የምባባሉበት ቦታ ነው በነፃነታችን ውስጥ የምመላለሰው እስትንፋስ ከእሱ ልብ ውስጥ የምነሳ ለፍጥረቱ የምሳሳበት ትርታ ነው ፍጥረት በእሱ እቅፍ ውስጥ የምንደዋለል የሁለንተናው አካል ነው ፍቅሩ በፍጥረት መካከል የምዘዋወር አየር ው ይቀርታው በማለዳ የምትወጣው የማለዳ ጮረነች ሀዘኖቹ የክረምት ዳመና ሲሆኑ እንባው ዳመና ከጠለለው ሰማይ የምወረድ ዝናብ ነው በረከቱ እንባው ከዘነበበት መሬት የምበቅሉ እህል ናቸው ፍቅሬ ነፃነታችን ይህ ነው ፍጥረትንና አምላክን ያስተሳሰረ በዚህም ከፍታ ውስጥ እንኖራለ የነዝ የስጦታው ምልክት የሆኑትን እምቦቆቅላሳ ልጆች እንወልዳለን የሰውን ዘር የማስቀጠል ፀጋውን እንዘራለን በምን ወልዳቸው ልብ ውስጥ ያለውን አምላክ ሰው የመሆን ጥበቡን እናስተምራለን በምናፍቁት ልቦቻችን ውስጥ እሱም ለዘላለም ፍቅርና ፀጋን ያበዛል የአምላክ እርምጃ በሰው እንቅስቃሰ ውስጥ ያለ ዱካ ነው እኛ በእስትንፈሳችን በተንቀሳቀስን ጊዜ የእሱን መኖር የረጋ ሰው ቁቤ እንረዳለን ምክንያቱም የምንቀሳቀሱ ፍጥረት ሁሉ የእሱ የመኖርና የመፍጠር ምልክቶች ናቸውና አምላክ በፍለጋ የምመጣ ሳይሆን በተዘጋጀና በምኖር ልብ ላይ ባለምስጋና ውስጥ የምገኝ የተፀነሰና የምወለድ የምስጋና ልጅ ነው በአካል ተገናኝተን ባንተቃቀፍም በምስጋና ውስጥ የመናፈቅ እቅፈን አደርሳለሁ በምስጋና ውስጥ የአብራክ ልጁ የመሆንና ተፈጥሮን የማፍቀር ፀጋዬን እነግረዋለሁ ከሁሉም በላይ የሆነው የእሱ ጥበብ መሆነን እመሰክራለሁ ዛሬን ያለስጋት እንድኖር ምስጋናን በእስትንፋሱ መካከል እወልዳለሁ በእኔና በአንች መካከል ያለውን ቀን የነገን ሃያልነት ፍራቻ ዛሬን አትግደይ በፍራቻሽ ውስጥ ከሁሉ በላይ ነው ያልሽው ፍቅር ይሞታልና የረጋ ሰው ቁቤ ሰላም የኩሬ ውሃ የንብ መንጋና ሰላም አንድ ናቼው የኩሬ ውሃ ስሰፍን ስረጋ ንፁ ውሃ ይሰጣቹነል ከፈለጋችሁ እንደመስታወትም እራሳችሁን ውስጡ ታያላችሁ ሰው ስረጋ ልክ እንደጠላ የኩሬ ውሃ ይሆናል እራሱን የምያየና የምያሳየው እራሱን ብቻ ነው ለገዛ ራሱ መስታወት ይሆናል ግን ኩሬ ውሃ በደፈረሰ ጊዜ ንፅህናው ይቆሽሻል ውበቱ ይጠፋና እድፍ ይሆናል አይደለም ሰው ለማሳየት እራሱን ማየት አይችልም ለመጠጥነት አይውልም ብንጣጠውም ፈዋሽነቱ ይጠፋና በሸታ ይፈጥራል የውሃው ንፅህና ያለው በረጋታው ውስጥ ነው የንብ መንጋ በሰላም ስኖር ታታሪ ነው ማሪን የምያክል ጣፋጭ ነገርን ለሰው ልጅ በመስረት ይሰጣል የማር ውጤት በሰላሙ ንብ ውስጥ ያለህዴት ነው ሰላማቸው እስከተጠበቀ ድረስ ንብ ጨዋና ትጉህ ሰራተኛ ናቸው ንቦች ጸብን በራሳቸው ጊዜ አያስነሱም በሌላ አካል ፀብ ይፈጠራል ወደ ፀብ የምገቡትም ፀብ ለማቀጣጠል ሳይሆን ፀቡን ለማረጋጋት ነው ለሰላም ዘብ ስቆሙ ለምከሰተው ውጅንብር ሁሉ ሃላፍነት ይወስዳሉ የረጋ ሰው ቁቤ ግን ንብ ከተቶነኮሰ ንብ ጨዋነቱ ይቀራና ተናዳፍ ይሆናሉ እርጋታቸው ወደ ሽብር ይቀየራል ሁሌም የሰላም ንቦች ወደ ወታደራዊ ጊዴታ ውስጥ ይገባሉ የሚከማቸው ማር ይቆምና ለህይወት ጉዳይ ሀይላቼውን ያውላሉ በሰላም እጦት የንቦቹ መስተጋብር ይቆማል በሰላሙ ኖረው ፍቅር ይጠፋና ጥላቻ ጥሪጣሬ ይሰፍናል ለስራ ታታሪነታቸውን ትቶ ወደ ሰላም ማስፈን ያዞራሉ ሰላም ስኖር እንደኩሬ ውሃና የንብ መንጋ ነው የረጋ ትውልድ ይፈጠራል ፍቅር ለሰው ልጅ መስተጋብሩን ያሰፍናል ውበት ይጎላና አንድነት ያብብል ከነካችሁት ግን ድፍሪስ ነው በሰላም ሀገር ከተወለደው ይልቅ ሰላም የናፈቃት ሀገር ውስጥ የተወለደ ብላቴና ስለሰላም ዋጋ ያውቃል ደቅቃው ተናዳፊ ነው ሰክነዱ ውጂንብር ነው እርጋታ ይጠፋና ደመነፍሳዊነት ይሰፍናል የምትኖሩለት ይረሳና እራሳችሁን ትጠራጠራላችሁ ከሰው ታንሱና እኔነት ይነግሳል ሀገር በልጆቿ ላይ ሴፍ ታነሳለች ሀገር እንደ ሀገር ሳይሆን እንደግለሰብ ፍላጎት ብቻ ትቆማለች እስትንፋስ ሽምያ ይሆናል ያቀፋችሁት ይዋጋል የሰማችሁት ይናከሳል ያጎረሳችሁት ይቧቀሳል ከሁሉም በላይ አሁን ነበር ይሆናል የረጋ ሰው ቁቤ ስድስት ልጆች የሞቱባት እናት ልጆቼ እየመጡ ነው ተዘጋጅቸ ልጠብቃቸው በጣም ቀጭን በሆነች መንገድ የእናታቸው እቅፍ ስለናፈቁ በቀጭኗ መንገድ ላይ በችግር እየተራመዱባት ነው ደጃፈን ያዘጋኝ የልጆቼ ጭወት ዛሬ መልሶ በልጆቼ የደስታ ስቃ ይከፈታል ጥቁር መጋረጃም በልጆቸ የብርሃን ልብስ አመድ ሆኖ ይጠፋል እናታቸውን በመናፈቅ ያሰለፉት ዘመን ዛሬ በእናታቸው የአይን ወሳፈን ብቻ የስቃይ ዘመናቸውን ይረሱታል ለዘመናት የተዘጋው የእናታቸው የፍቅር በር ዛሬ ዳግም ብለጆቼ ሳቅ በደስታ ታጅቦ ይከፈታል ለዘመናትም በእንባ የረጠበው የእናታቸውን ጉያ ዛሬ በልጆቼ የበረከት እጆች ይታበሳል ልበ ላይ ድር የሰራውን የልጆቼን ናፍቆትና በልጆች እጦት በሀዘን የተሞላውን ህይወተን አምላክ በልጆች ብዛት ደጃፈን ይሞላና የእርግማን ዘመኔን ያስረሳኛል ልጆቼ እየመጡ ነው ለመምጫቼውም ማንም ነጋርት አልነፋላቸውም ምክንያቱም የጦርነት አውድማ የፈጠረው ንጉስ ዳግም የሰላም ጥር ማበረከት የረጋ ሰው ቁቤ አይችልምና ሰላማችሁ ሰላሜ ነው ብለው ያላመነ ንጉስ የንግስና ዙፋኑን በህዝቦቹ እጅ ልረሳ አይቻለውም የልጆቸን ወደ እኔ መምጣት የሀገረው ህዝብ ባይፈልግም ልጆቼ ግን የእናታቸውን የተፈታ መቀናት ዳግም ለማሰር ወደ እናታቸው ቤት በሰልፍ እየፈሰሱ ነው ለአንድ ብላቴና እናቱን እንደመናፈቅ መንፈሱን የምያዝል ስቃይ የለም ለአንድ ልጅ አለም ስቃይ ባበዛበት ጊዜ ወደ ዘላለም ቤቱ ገብቶ ለማረፍ የምያስባት እናቱ ብቻ ናት የልጆቼንም የሰላም ሳቅ ደጃፈን ዘግቼ ለብቻየ ደግመ ሰማለሁ ዳግም የልጆቼን ትንሳኤ በተዘጋ ቤቴ ውስጥ ለብቻየ አከብራለሁ የሰላማቸው ሰላም አይደለም የስቃያቸውንም ጭወት ለማንም አላካፍለም ለብቻየ የምሰማው አምላከ በልጆቼ በኩል የምያሰማኝ የህይወተ ዜማ ነው ደግሜ ደጋግሜ እሰመዋለሁ አይሰለቸኝም ከነፍሰ እየፈለቀች ወደ ህይወት የምፈስ የልጆቼ ስቃ መንፈስ ነው መልካም ንጉስም የሌላት ህዝብ በልጆቼ ሳቅ ይቀናሉ መልካም ከሆኑት ልጆቼ ጋርም ያለኝ ህይወት ወደ ጦርነት አውድማ ልወረዊሩ ይፈልጋሉ እኔ ግን ልጆቼን በጉያዎቼ ደብቅያቸዋለሁ ማንም ቆፍሮ ልያገኝ አይችልም የረጋ ሰው ቁቤ በአንድ ክፉ ንጉስ ፍላጎት ሺ የሀገረው እናት ልጆቻቸውን ወደ ጦርነት አውድማ ልኮ በዶ ጭኖቻቸውን ታቅፎ ቀርተዋል አንድት እናትም በደከመች ጊዜ የተፈታ መቀነቷን የምያስርላት ልጀ ከአጠገቧ ስታአጣ የቤቷን መሶሶ ይዛ አምላኳን ዘለፈች እንድህም ብላ አምርራ አለቀሰች በሰጠሄኝ ልክ ቀምትሄኝ በቀማሄኝ ልክ ደግሞ ጠላትህን አበጀከው እውነት የሀገረው እናቶች ሁሉም ይጠሌሉነሃል ምን አይኔት ስግብግብ ነው አብዝቶ ሰቶ ተነስቶ ሁሉንም የምቀማው ለደስታ ጊዜስ ይቅር ለሀዘናችን ጊዜ ለመከራችን ሁሌት ፀጉር በምናበቅልበት ጊዜ እንኳን የምሆን እንዴት አንድ እናት ከደጃፏ ላይ የምስቅ አንድት ብላቴና ታጣለች እስከ መቼስ የእናት ጡት ተቀባይ አቶ የማሬት እንብርት ያርሳል ይህ በረከት ነው ወይስ እርግማን እኛኮ ሰተሀን ከነሳህን ወድ ነገሮች ተምታቱብን ለልጆቻችንም ያወረስነው ያንተ መልካምነት በልጆቻችን ህይወት ክፋት ሆኖ ስበቅል እናት የልጁን አይን መሸከም አቅቷት ያፈረው አይኖቿን የመሬት እንብርት ስር ደበቀችሁ እንዴትስ በሺህ ዘመን ትውልድ መካከል በመልካምነት ያለፈ አምላክ በእኛ ልጆች መካከል ክፉ ሆኖ ይበቅላል የረጋ ሰው ቁቤ በእሳት መካከል ለምትጣጣረው ነፍሳችን የበረከት ውሃ ጠፍቶት እንዴትስ እሳት ቶን ይጨምርባታል ልጆችም ያሙሃል እንድህ ብሎ የእናታችንንስ ጉያ ለምን እንደሰማይ ኳዋክብት ከእኛ ርቀው በናፍቆት ብቻ እንድናያቸው አደረገ የአንድ እናት መዓዛ የልጆቿ አፍንጫ ስር ነው ልያቅፋትም እጁን በዘረጋ ጊዜ መልሶ እራሱን የምያቅፍበትስ ጊዜ ለምን ረዘመ የልጆቿን የስኦል የስቃ ጭወት እናት በምድር ሆና ታዳምጣለች የእናት ጆሮ ለልጆቿ ከምንም ነገር የበለጠ ቅርብናትና የእናትም ልብ በልጅ ልብ ውስጥ የእናትነትን የፍቅር ስሜት ልጁን ለመውለድ በተጨነቀች ጊዜ የልጆ ልብ ውስጥ ረስታዋለች ስሜቱም የልጅና የእናት የፍቅር ገመድ ልጄን በህይወቱ እየተከተለ የእናቱ የናፍቆት ስሜት እየወጋው የህመም ዘመን ሆኖበታል አምላኬ ስለ እናት ብለህ ይህንን ዘመን እርሳው የልጆችንም ህይወት እንደገና ከእናታቸው ጋር ይዋሃድና የተነፋፈቁበትን ዘመን እንደ አድስ አስጀምራት በሰቆቃ ህይወት ላይ የተረሳው የእናትነት የሙሾ ዜማ በልጆቿ የደስታ ድምፅ ከህይወቷ ገጽ ላይ በትንላት የልጆቿንም መልካም ዘርን ለሀዘን ከለበሰችሁ ከፈኗ ላይ ሪጭና የሞት የረጋ ሰው ቁቤ መንፈስ ከህይወቷ ላይ ድባቅ ምታላት ይህ የልጆቿ ለእናታቸው የምለምኑት የዘውትር ፀሎት ነውና ለአንድትም እናት ረጅም የሆኑባትን የእንባዋ ጊዜ በአንድት የልጄ ፈገግታ የገነትን የደስታ በር ትሳለማለች አንድት ስድስት ልጆች የተጎዱባትን እናት ህመም ስትጠይቃት እርሷ ግን የአንዱን ልጃን ናፍቆት ብቻ በማውራት ዘመኗ ያልፋል የአምስቱን ልጆቿን የናፍቆት ዜማ ለመስማት አምስት የዘመን ህይወት እርሷን መጠበቅ ትገደዳለህ አፏን ከፍታ ካወራችልህም ይልቅ ከአይኗ የምፈሱ እንባዎች ይበልጥ እውነቱን ይነግሩሃል ልጆቿንም በመጠበቅ የህይወቷን ጊዜ የፈጀች እናት ስለ ህይወት ብትጠይቃት መጠበቅ የህይወቷን ሙሉ ታርክ የያዘ መፅሃፍ መሆኑን ትነግር ይሆናል ምናልባት በህይወቷ ያካበተችሁ ነገር የመጠበቅ ጥበብ ስለሆነ ከአንድ እናት ልጆቿን ከተቀማች የምወጣው የሀዘን እንጎርጎሮ ልክ እንደሷ ልጆቻውን ከተቀሙ እናቶች ልብ ላይ ስያርፍ የጋራ የሀዘን ዜማቸውን ከህይወታቸው ክፍል ያወጡታል የረጋ ሰው ቁቤ ስድስት ልጆቿንም ያጣችሁ እናት ድምጹዋን ከፍ አድርጋ እንድህ አለች እባካችሁ ልጆቼ ወደ እኔ የምመጡበት መንገድ ቀጭን ስለሆነ ቀማኛና ዘራፍ ስግብግባና ግብዞች መንገዱን ለቀቁት እንዴ እኔ ያሉት እናቶች ብቻ ወደ እልፍኝ ግቡና የልጆቻችሁን የናፍቆት እንባ ከልጆቼ አናት ላይ ታፈሳላችሁ የልጆቻችሁንም የናፍቆት ረሃብ በልጆቼ ልብ ውስጥ የልጆቻችሁን እጣፋንታ ትፈልጋላችሁ በልጆቻችሁ ጥበቃ የደረቀች ነፍሳችሁን የምርስ የናፍቆት እንባ በልጆቼ የነፍስ መልክት ውስጥም ታገኙ ይሆናል የረጋ ሰው ቁቤ ፈገግታችሁን ከሁለንተናችሁ እየፈለቀ በፊታችሁ በኩል ለሰው የምደረሰው ፈገግታችሁ እንደማለዳ ብርሃን ይሁን አንድት የብርሃን ጨረር በመስኮት በኩል ገብታ መኝታችን ላይ አርፋ ቃናችንን እንደምታሳምረው ሁሉ ለአንድ ሰው የምትሰጡት ፈገግታ ብርሃን ነው ሰው ከእንቅልፉ ተነስቶ የማለዳውን ብርሃን ለማየት እንደምጓጓው ወደ እናንተ ስመጣ ፈገግታችሁን ለማየት እንድጓጓ አድርጋችሁ ተቀበሉት ምናልባት ፊታቹ ላይ የምታይ መልካም ፈገግታ ህይወት ጀረባ ለሰጠችሁ ነፍስ መፅናኛ ይሆናታል ያልሳካ መንፈስ ለተጠናወተው ሰው አድስ የተስፋ መንገድ ፍንጭ ያመለክታል ፈገግታችሁ በጨለማ መንገድ በኩል ለጠላታችሁ ብርሃን ይሁን በመንገድ ላይ ቆሞ ድንጋይ ይዞ ለምጠብቃችሁ ጠላት ፈገግታችሁን አብሩለት ምናልባት ድንጋዩ ራሱ በፈገግታችሁ ዳቦ ይሆን ይሆናል ሰው በፈገግታው ብርሃን ጨለማውን ይደመስሳል በፈገግታውም በኩል አምላኩን ያናግራል የረጋ ሰው ቁቤ ፈገግታችሁን እንደ እንጀራችሁ አድርጋችሁ ያዙት እንደ ውሃችሁም አድርጋችሁ ጠጡት እንደ ሰላማችሁም በልባችሁ በመንፈሳችሁና በሀሳባችሁ አኑሩት በቻላችሁም ሀይል ለሰዎች ለግሱት በህይውታችሁ ትልቁ ሀብታችሁ ፈገግታችሁ ነው በአካለችሁ ሁለንተና መካከል ፈገግታችሁን አኑሩ ለሰው ልጅ ብቻ የምሰጥ ሀብታ አድርጋችሁ አትቁጠሩት ለፍጥረት ሁሉ የምተርፍ ነውና ይህን ሀብት ከሁሉም ጋር ተቋደሱት ፈገግታ ለሌላ አካል የምታበረክቱ የማይጨበጥ መልካም ስጦታ ነው የአንድ ሰው ነፍስ ፈገግ ስትል በፊታችሁ በኩል ለተፍጥሮ የደስተኝነታችሁን የምስራች የምታስተጋቡበት መንገድ ነው አባባ ይዞላችሁ ለመጣ ብቻ እውነተኛ የነፍሳችሁን ፈገግታ አታሳዩ ድንጋይ ተሸክሞ ለምጠብቃችሁም ጠላታችሁ ፈገግታችሁን ለግሱት የግብዞችን ነፍስ በፈገግታ ብቻ ማሸነፍ ትችላላችሁ ምክንያቱም የግብዝ ነፍስ ንፉግነች ፈገግ ማለትን አታውቅም ነገር ግን በፈገግታችሁ በኩል የግብዝነት ስሜታቸሁን ልታስጥሉም ትችላላችሁ የግብዝነት ስሜት በህይወታችን የረጋ ሰው ቁቤ የምያመጣው የፈገግታችን መጉደል ነው ፈገግታን ከፊታቸው የምያኖሩ ነፍሶች ሁሌም በመስጠት ህይወት ውስጥ ያሉ ናቸው ለፍጥረት ሁሉ ያለን ፍቅር በህይወታችን ስሞላ በፊታችን በኩል ብርሃን ሆኖ ይወጣል ፊጥረትን እንደቤታችሁ እንደገዛራሳችሁ አድርጋችሁ ውደዱ ያንጊዜም ውበቱ ይገለጥላችሃል የራሳችሁ የሆነው ንብረት ለባሌቤቱ ውብ ነው ይህም ስሜት ሰው ልጅ ለራሱ ካለው ፍቅር ጋር ስያነፃፅር በልቡ ያኖራል እናንተም ፍጥረትን ከራሳችሁ በኩል አድርጋችሁ ያዙት አንድት ጎጆዋን ለመቀለስ በጓሮዋችሁ ዛፊ ላይ ያረፈችን ወፍ ከቤታችሁ ላይ አንድት ሳር አንስታችሁ በፈገግታ ስጧት ያንጊዜም የተፈጥሮ ፍቅር ከአወጣችሁት ህግ በላይ መሆኑን ትረዳላችሁ ልትወልድ ብላ በደጃፋችሁ ለምትቆራጠጥ ውሻ የመውለጃ እርስት ስጧት ያን ጊዜ በርትታ ቤታችሁን መጠበቅን ለወለደች ብቹሎቿ ታስተምራለች ተፈጥሮ በሰው ነፍስ ርህራሄ ውስጥ ያለች ውበት ነች አፍቅሯት መስጠትን ታስተምራቹነለች የረጋ ሰው ቁቤ ለሌላው የምናሳየው የብርሃን ፈገግታ በተከፋ ሰው ነፍስ ውስጥ የመፅናኛ ቃል ትዘራለች ፈገግታ ሰውን ከሰው የምያገናኝ የፍቅር ድልድይ ነው በህይወታችሁ ለድልድዩ ቦታ ስጡ ለአንድ ሰው የምታሳየውን ፈገግታ ቤትህን ለምጠብቅልህም ውሻህ ሳታጎል አሳያት በዛን ጊዜም ውሻው የባለቤቱን መምጣት በተስፋ ይጠባበቃል እውነት እላችሃለሁ ሰው የፖሎትካ መጫወቻ የምሆነው ፈገግታውን በፖሎትከኛው ከተቀማ ቦኋላ ነው ፖሎትከኞች መጀመርያ አባል ስያፈሩ ከህይወቱ ውስጥ ፈገግታን ይሰርቃሉ ፈገግታውን የተሰረቀ ሰው ባዶነት ይገበዋል ከፍቅርም ሁለንተና የወጡ ፍጡራን ይሆናሉ ለዛም ነው ፖሎትከኞች አንድ ፅንፍ ይዞ ብቻ የምወጉት ፈገግታ የተፈጥሮ ሁለንተና ነው ፖሎትከኞች ይህንን ልረዱ አይችሉም ምክንያቱም ፈገግታ ከምታወራው ቋንቋ ከምታመልከው ዘር በላይ የሆነ የሰው ልጅ የመልካም መንፈስ መንገድ ነው በዛ መንገድ እውነት ብቻ ትንሸራሸራለች ሰው ልጅ ብቻ ያለቀለም ያለጎሳ ያለዘር ያለሀይማኖት አክራርነት ይንሸራሸርባታል የረጋ ሰው ቁቤ ፈገግታ ከሀይማኖት ፅዕንፈኛነትና ከዘር አክራርነት የፀዳ ከውስጣችን የምፈልቅ ንፁ የተፈጥሮ መንፈስ ነው በተፈጥሮ መሃልም ያለ እውነት ነው ይህንንም እውነት ከፖሎትካ ሀሳብና ተፅእኖ የፀዳ ብቻ ሊደርሳት ይችላል ለከንቱ ፖሎትካኞች የሠጣችሁ ጆሮ ለተፈጥሮ ስትሰጡ ብቻ በፈገግታ ቋንቋ ማውራት ትጀምራላችሁ እስከ ዛሬ ሰው ከአንድ ከፍቅር ማዕድ ላይ ከተለያየ ጎሳና ሀይማኖት ስበላ ምግቡን ጨርሶ አያውቅም ነገር ግን አንድ ፖሎትከኛ ማኣዱ ላይ ስፈጠር ብቻ ከፍቅር ማኣዱ ይጎላል እውነት እላችሃለሁ እስከ ዛሬ ፖሎትከኞች አለምን ስሸረሽሩ የኖሩት የሰውን ልጅ ፈገግታ ቀምቶ የራሳቸውን የራስወዳድነት ስሜትና አኔ ብቻ ብራሃን ነኝ የምለውን ስሜት በሰው ልጅ ውስጥ ጨምሮ ነው ፖሎትካ ምንም ማለት አይደለም በአንድ ሰው ሀሳብ ውስጥ ሺህ ሰው ማኖር ማለት ነው ሺህ ሰው በአንድ ሰው ሀሳብ ስነዳ የየራሱን የግል መንገዱን ይጥሳል ህይወት ውብ የምትሆነው ሰው ሁሉም በራሱ መንገድ በፈገግታ ታጅቦ ስኖራት ነው የረጋ ሰው ቁቤ ከፖሎትካ መንገድ ውጡ የፖሎትካ መንገድ አንድ ነው አባትን ያደረሰበት ቦታ ልጅንም ያደርሳል ፖሎትካችሁ ፍቅርን በህይወታችሁ የምያጎድል ከሆነ ህይወታችሁን መቃብር ያድርጓል ፖሎትካችሁ ደስታችሁን የምቀማና በሃዘን ውስጥ የምዘፈቃችሁ ከሆነ በድን ሆናቹሃል ፖሎትካችሁ በዘርና ከሀይማኖት ተዘፍቆ የእርስበርስ መስተጋብራችሁን ከቀማችሁ ገሏቹሃል ምክንቱም የአንዱን ዘር ሌላው ውበቱን ማየት ካልቻለ የአንዱን ሀይማኖት ሌለው ሀይማኖት ውብ መዝሙሩን መስማት ካልቻለና በየእኔ ይበልጣል ስሜት ብቻ ካሰራችሁ የማይንቀሳቀስ በድን ናችሁ ያምራል ብላችሁ የለበሳችሁት ልብስ ከተለያየ መልክ ካለው ነገር እንደተሳራ መገንዘብ ካልቻላችሁ ሰውነታችሁ ላይ ስያርፍ ያለውን ውበት ማየት አትችለም አሻንጉልት ላይ ብቻ ስሰቀል አይታችሁ ነው ማለት ነው የገዛችሁት ፖሎትከኞቻችሁን እናንተ ምሩ እንጅ እንደመሯችሁ አትፍቀዱላችሁ ልክ እንደምፈስ ውሃ ራስ ሁኑ በተደፋችሁ ጊዜ የራሳችሁን መንገድ ፈልጉ በመንገዳችሁም በሙሉ ነፃነትና ፍቅር በተሞላ ልብ ፈሰሱበት ፖሎትከኞቻችሁ በራሳቸው ሀሳብ ሳብያ ብቻ የረጋ ሰው ቁቤ ህዝቦችን ልፈጥሩ ይጥራሉ ይህም የህዝቡን ሰላምና ፍቅር የምያጎድል ከሆነ እርስበርስ ያላችሁን ፈገግታችሁን ይቀማቹሃል የፖሎትከኞች ሀሳብ በህዝቡ ሀሳብ እስካልተዋጠ ድረስ ሀገር ነፃነት ሳይሆን ህግ ብቻ እንዳወጣች ትኖራለች ነፃነታችሁ ከተፈጥሮ ጋር ቁርኝታችሁን የምያጠነክር መሆን አለበት ተፈጥሮ ልዩ ልዩ ስለሆነች ውብ ነች ይህንን ውበት የምታዩት ህይወታችሁ መካከል ፈገግታን እርስበርስ በፍቅር ስትለዋወጡ ነው ፖሎትከኞቻችሁ በመካከላችሁ ትልቅ ፈገግታችሁን የምከለክል ድንበር ከገነቡ እንደራሳቸው ሀሳብ ህዝቡን ያስገድዳሉ እናንተ በህይወታችሁ መካከል ያቆሙትን ድንበር አፍርሳችሁ መካከላችሁ ያለውን የራሳችሁ የሆነውን ፍቅርን አኑሩ አንድ ፖሎትከኛ የፍቅር ቃል የምወጣው ምናልባት የስልጣን ዘመኑ አልቆ ስልጣን ስለቅ ነው በማገልገል ላይ ብቻ የተመሰረተ ስልጣንና ግብዝነት የሌለው ፍቅራችሁ ግን ከልዩ ልዩ ተፈጥሮ ጋር ተዋህዶ ለዘላለም ከእናንተ ጋር ይኖራል ንቁ። የተለያየ ነገር ውቤት እንጅ ጥላቻን ፈጥሮብን መንፈሳችንን የምያሰቃይ መሆን የለበትም ባዶ እስክብሮቶ ቀለም እስካል ጨመራችሁ መጻፍ የረጋ ሰው ቁቤ እንደማይችል ሁሉ ባዶ ህይወትም ፍቅርን ካልጨመራችሁበት ፈገግታን ማፍለቅ አይችልም የተለያየ ዘርና ሀይማኖት የያዘውን መአዳችሁን በፍቅር ሙሉት ያንጊዜ በመካከላችሁ ፈገግታ ይነግሳል ሰለማችሁም ከነፍሳችሁ መካከል ይሰፍናል ዘርና ሀይማኖት የሌለውን የፈገግታችሁን ቋንቋ መናገር ትችላላችሁ በልባችሁ ውስጥ ፍቅር ብቻ የምሸከም ቦታ ያዙ በዛም ፍቅር ገና የምታውቁትና ወደ ፊት ይመጣል የምትሉት አድስ ፍጥረት ትወዱበታላችሁ ሁሌም ፍቅርና ተፈጥሮን በመውደድ ውስጥ ያለውን ስሜት በውስጣችሁ አኑሩ እርሱም የሰውን ልጅ እውነተኛ የአምላክ አምሳሉ ያደርገዋልና የረጋ ሰው ቁቤ የህይወት ፍሰት አሳ ባህርን አንደምያፈቅረው ሁሉ እናንተም ህይወትን አፍቅሯት የአሳ ህይወት ከባህር ውጭ ባዶ ነው የሰው ልጅ በገዛ ህይወቱ መካከል የራሱን አምሳያ ነፍስ በፍቅር ማኖር እስካልቻለ ድረስ ህይወትን በቅጡ ሳይረዳ ያልፋል የምትሰሩትን ነገር በፍቅር ካልወደዳችሁ ጊዜ ከማባከን ውጭ የልፋታችሁን ውጤት በደስታ አታፍሱትም በልባችሁ ያለውን ስሜት በህይወት በኩል ተግብራሻ አፍቅሩት ከራሳችሁ ጋር ያላችሁንም መስተጋብር በመልካሙ መንገድ ያዙት በህይወት ውስጥ ያላችሁትን መጥፎ እጣፋንታ እንደ መልካም እድል ተጠቀሙበት መልካም እድል ወደ እኛ የምመጣው እኛ በምናሳየው የተስፋ መንገድ ነው እናንተ ማንም ልረዳችሁ የማይችል እንቁ ፍጥረት ናችሁ ከተፈጥሮ ጋር ያላችሁን ውህደት ከገዛ ራሳችሁ ጀምሩት ከራሳችሁም ወደ ተፈጥሮ ፍሰሱ የህይወታችሁን መልካም ጎን ከህይወት ልምድ ትረዳላችሁ ጊ የረጋ ሰው ቁቤ ህይወት በእናንተ በኩል በፍቅር እንድፈስ በውስጣችሁ እራሳችሁን ለመበቀል ሸንቁራችሁ ያስቀመጣችሁትን አሉታዊ ስሜቶች አስወግዱት ያስሜት የእናንተን የሁለንተናችሁን ፍሰት ይገድባቹሃል ሰው በመልካሙ ሀሳብ ላይ የምገነባ ድንቅ ፍጡር ነው እውነት ውስጥ የምኖር የእውነት አካል ነው ህይወት በሰው ልጅ ፍሰት ውስጥ በተለያያ መንገድ ያለች እውነት የመግለጭያ መንገድነች እናንተ ስትኖሩ ህይወት ትኖራለች ህይወት ሰው ከተፈጥሮ ጋር ያለው የጥርቅም ጊዜ ነው ታርክ ደግሞ ሰው በህይወቱ ማካከል የምፈፅማቸው የድርግቶቹ ጥርቅም ነው አንድት የብርቱካን ዛፍ ላይ የተንጠለጠለች የብርቱካን ፍሬ ለውህዴት የምሆን ሁሉን ነገር በብርቱካን ዛፉ በኩል ታገኛለች ሰውም በህይወት ውስጥ ያለ የብርቱካን ፍሬ ነው የብርቱካኑም ፍሬ ከዛፉ በተቆረጠች ጊዜ እድገቷ እንደምቆመው ሁሉ እናንተም ከህይወት እንቅስቃሴ ውስጥ ስትቆሙ በድን ትሆናላችሁ ህይወትን ማቆም አይቻልም ያለው አማራጭ አብሮ መፍሰስ ነው በህይወት ፍሰት ውስጥ በደስታ ፈሰሱ ከህይወት ጋር ያለውን ትስስር በአሁን አድርጉት ነፍሳችሁ ከስጋት ነፃ ትሆናለች ስለነገና ስለምመጡ ዘመን ማሰብ እራስ ላይ የረጋ ሰው ቁቤ እዳ መጣል ነው ምን እንደሆነ በቅጡ ያልተረዱትን እዳ ተሸክሞ ባሪያ መሆን ነው የአሁኑ ህይወታችሁ መጨረሻ አሁን ነው በህይወት መኖራችሁንም የምታቁት አሁን ነው የአሁናችሁም ህይወት ሌላ ፍጥረት ያላችሁትን በመስጠት በርህራሄ የተሞላ ይሁን የህይወታችሁ መሃል ፍሰት ላይ የመልካምነት ፅዋ ለወዳጆቻችሁ እያስጎነጫችሁ ኑሩ ህይወት በፍጥረት መካከል ያለች ስርነች ሁሉንም አስተሳስራ ትይዛለች የስራችሁን ግንኙነት በፍቅርና በደስታ ገንቡት ያንጊዜ የህይወትን ጥልቅ ምስጢር ትረዳላችሁ በአዕምሯችሁ የምትይዙት ከንቱ ሀሳብና የስግብግብነት ስሜት የስሩን ህይወት ያቀጭጫሉ ሁሉም ስሮች አፈር ውስጥ እስካሉ አንዱ ከሌላው የምለይበት ነገር የለውም የሰው ነፍስ እስከ ተመሳሰለ ድረስ በቀለምና በዘር በጎሳና በሀይማኖት አትከፋፍሉ ነፍሳችን ከአንድ ቦታ የተቀዱ ናቼው በቤላቤቱ ህልውና ውስጥ ስናያት ግን በባሌበቱ ስብእና ትሳላለች እይታችሁን ሁሌም በያዛችሁት ነፍስና ሌላ አካል መካከል ያለውን ልዩነት አጥፍታችሁ እዩት የሰው ልዩነት ነፍሱ ሳይሆን አለምን ከተቀላቀለ ቦኋላ የያዘው እሴቶቹ መሆኑን ትረዳላችሁ ነፍሳችን የረጋ ሰው ቁቤ በአንድት ባህር እንደምኖሩ የአሳ ክምችት ነች ግኝታችን ከአንድ ቦታ ነው በልዩነታችሁ መካከል የያዛችሁት የበቀል ሀሳብ ከሀሳባችሁ ውስጥ አውጥታችሁ ጠላቴ ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ሰው ጋር በሀሳበችሁ እራት ተገባበዙ በሀሳባችሁ የያዛችሁትን ጠላትነት ክፍተት አግኝታችሁ ሳትፈፅሙት በፊት እርቅን በሀሳባችሁ አውርዱ አብራችሁም የሰላም መአድ ተቋደሱ በአንድ የጀንበር ጥላ ስር በፍቅር እንደምትኖሩ አስቡ እፅዋቶች በምያበረክቱት ንፋስ አብራችሁ እንደምትምጉና እስትንፋሳችሁን በውስጣችሁ እንደምትጠብቁ አስቡ በሀሳብ ውስጥ ካለው ጠላትህ ጋር ስትወዳጅ ያለምንም ፍራት በአካል ስታገኘው አቅፍ ትስመዋለህሀ የረጋ ሰው ቁቤ ከአብራኬ ከአብራኬ የወጣውን ስትሰጠኝ ሀሳቦችሁን ከሀሳብህ አድርግልኝ ፍቅሩን ከተፈጥሮ ውስጥ አኑርልኝ የእኔ ብየ እንደጠራው ከመንፈሱ ውስጥ የአባትን ድርሻየን በትለቁ ፃፍልኝ ልጅነቱን በአባትን ጭፍን የራስወዳድነት ስሜት እንዳልቀማው ማስተዋልን ከልበ አኑረው እንደልጅ አቅፈ በጉያ መካከል እንድደብቀው የልጅነት ዘመኑን በአባትነቴ የፍቅር ልብ ውስጥ አንፀው ልጅ ነውና እንደ እራሴ አኩያ አይቸው እንዳልፈርደው ለፍርድ የምቸኩለውን ህልናየን ግራ በእሱ የልጅነት ዘመን ውስጥ አባትነተን ማስተዋል ከማይችሉ ከናፍሩ ላይ አኑረው ደጋግመው አባዬ ይበለኝ የእኔን ጎልማሳነት ዘመን ከልጅነቱን ወዝ ጋር አድሰው አባትነቴን አንድረሳ እንደራሴ ጓደኛ እንዳየው እይታየን እየው እግር የምያነሳበት ጊዜ የመጀመርውን እርምጃ በአባቱ ልብ ላይ እንድሰርፍ የእግሮቹን ፋና በፊቴ አኑራቸው የአይኑን እንባዎች በህይወተ ውስጥ በፍቅር እንድፈሱ የአባትነት ግዴታየ ይሁን ልጀ ነውና የረጋ ሰው ቁቤ እስትንፋሱን በራሴ አምሳል ውስጥ ደብቅልኝ እኔ ብቻ ስከፋው ልስማው የራቡን ዘመናት በእኔ ክፉ እጣፋንታ ላይ ፃፍልኝ በአባቱ እቅፍ ውስጥ የራሃብ ስሜቱን እንደረሳ አድረገው በሰከነ የአባትኔት መርቃት ውስጥ የልጀን የደስታ ዘመናት አኑረው በምትፈሰው የህይወቱ ገፅ ላይም የአባቱን የመልካም ምኛት ብስራት ፃፍለት የልጄን የደስታ ስቃ የእኔ የሁልጊዜ ሳቄ አድርገው የህይወትን እውነት የምመረምሩ አይኖቹ ላይ ከፍቅርህ የተቀዳውን ጥበብ ግለፅለት ትግስት በተላበሱም ጥበብ ህይወቱን በፍቅር መስተጋብር መካከል የመስጠትን እውቀት በልቦናው አኑረው አምላኩን በምያመሰግኑ ነፍሱ ላይ የሰላም ዘመን ህይወቱን ባርክልኝ ከሁሉም ከሁሉም ግን በምጥ ወክት የሞተችሁን እናቱን በልጄ ሁለንተና ውስጥ በፍቅር አኑረው ይህም አባት ለልጁ ካለው የእስትንፋስ ዘመኑ የምበልጥለት የእናቱ የምንጊዜም ስጦታው ነውና የረጋ ሰው ቁቤ የልብ መልዕክት ጥዋት የምሰማው ማታም የምደግመውን የአምላክ ድምፅ በልበ ውስጥ አኑረያለሁ ቃሉ በህይወተ መካከል የምመላለሰው እኔ ከቃሉ በኋላ የተገነባውና ቃሉ የወለደኝ ስለሆንኩ ነው አምላክ ብዙ ሰውን የክብሩ መገለጫ አድርጎ አካላቸውን አጎሎ ፈጥሯል አይን እጅ እግርና የመሳሰሉትን አጉሏል እስከዛሬ ግን ከሰው ክፍሎቹ ውስጥ ልብን አጉሎ ፈጥሮ አያውቅም ምክንያቱም ልብ የአምላክ የዙፋኑ መቀመጫ ነውና ልባችን በህይወታችን ሂደት ውስጥ የአምላክ እርምጃ መነሻም ነው የአምላካችን ፍቅር በልባችን መካከል የሰፈነ የሰላም መንፈስና ስሜት ነው አምላክ ቤቴሰባዊነት የምያጠናክረው በልባችሁ ውስጥ አርፎ ነው በልበችሁ ውስጥ ያስቀመጣችሁትን በረካሽ ቃላቶች በአንደበታችሁ በኩል አታስወጡት በከንቱ ሀሳባችሁ ውስጥ አትግደሉት በልባችሁ መካከል በደስታ አኑሩትና ዘላለም በምታመሰግን ነፍሳችሁ ማካከል አፍስሱት የረጋ ሰው ቁቤ በልባችሁ የያዛችሁት የአምላካችሁ ፍቅር በፍጥረት መካከል ከእናንተ በስስት እይታችሁ ስወጣ በምዘረጉና በምያንከባክቡ እጆች መካከል ይፈፀማሉ ሀሳበችሁ እይታ ይኑረው ድርጋታችሁም ውጤትን ያነገበ ይሁን ሰው በምያስብ አዕምሮ ስያስብ በምሰሩ እጆች ይታደስና በያዘው ሀይል ስተገብር ህይወትን በጥበብ ይመራል በያዛችሁትም ቅንጣት ታክል እምነት መካከል የይቻላል መንፈስን ፈልጉ ፈልጋችሁም ባገኛችሁ ጊዜ የአይቻልምን መንፈስ ከህይወታችሁ ውስጥ ትገሉበታላችሁ የረጋ ሰው ቁቤ የተፈጥሮ ቋንቋ እንድት ለዘመናት በብቸኝነት የኖረች አሮግት ድግስ አዘጋጅታ በተሰበሰበው ህዝብ መካከል እንድህ አለች በጣም ተዋደን በፍቅር እንኖር ነበር እኔ በውስጥ ያኖርኩት የራሴም ሰው አድርገ አስበው ነበር በሁሉም የህይወተ ክንውን ውስጥ እሱን አኑረዋለሁ በራሳችን የወደ ፊት ህይወት ከእርሱ ጋር የራሳችንን የህይወት መንገድ እንድኖርም አልማለው አንድ ልብ ላይ አምሳክ ስፈርድ የራሱን ልብ እንደ ልቦች ስብስብ ይቆጥራል ምክንያቱም የአምላክ ልብ የሰው ልብ ስብስብ ነውና ሁሉንም የሰው ልብ በአንድ መንገድ ያስተሳሰረና ሁለንተናውን በውስጡ ያኖረም ነው የሰው ልብ ስታመም የአምላክ ልብ ላይ ይቆስላል ሰው በልቡ መካከል ትንሽ ኩሬ መሳይ የፍቅር ስሜት ስያኖር በአምላክ ልብ ውስጥ ባህር ይሆናል በፍቅሩ ህይወትን ስታሰሉ ውጤት አይኖረውም በፍቅር ግን ህይወትን ስትኖሩ ሀሴት ይሆናል የረጋ ሰው ቁቤ አንድ እንሆናለን ያልኩትን ልጅ አብረን በፍቅር እንደምንኖር ሳልም ሀሳቦቼ ሁሉ እውን ይሆናሉ ህልም ብቻ ውጤት ልሆን አይችልም ህልም ጥሬት የምጠይቅ የሀሳብ ውጤት ነው ሃሳባችሁ ላይ ሀያላችሁን አፍስሱ በፍቅር ደግሞ ተግብሩት ሁሉም እውን ይሆናል አንድ ወጣት ሁሌም ትልቅ ደረጃ እንደምደርስ ለራሱ ይናገር ነበር እኔ ነገህ ትልቅ ታዋቅ ሙዝቀኛ እሆናለሁ እያለ ለገኘው ሰው ሁሉ ያወራል ነገር ግን ይህ ልጅ ታዋቅ ሙዝቀኛ ሳይሆን ብዙ ዘመናት አለፉት ሰዎች ለራሳቸው የምያወሩትን ህልም በሀሳባቸው አስቀምጠው በልባቸው አፍቅሮና በሀይላቸው ለመተግባር ካልተጣጣሩ ውጤታማ ልሆኑ አይችለም ይህም ልጅ በሃሳቡ ብቻ ይዞ ታዋቅ ሙዚቀኛ ለመሆን ያልም ነበር ግን ይህ ልሆን አልቻለም ማድረግ የነበረበት ግን በሃሳቡ የያዘውን ሀሳብ ወደ ልቡ በፍቅር ማውረድ ነበርበት በሃይሉም እንድተገበር መንቀሳቀስ ነበረበት ይህን ማድረግ ሳይችል ስቀር ሃሳቡ ውስጥ ብቻ አስቀምጦት ሙዝቀኛ የመሆን ህልሙን ገደለ አንድ ገበሬ እህል ለመዝራት ሀሳብ ጉልበትና ስራውን የምወድበት ፍቅር ያስፈልጉታል ስራውን አስቦ ስራውን የረጋ ሰው ቁቤ አፍቅሮና ጉልበቱን አውጥቶ ካልሆነ ገበረው ምርታማ ልሆን አይችልም ሀሳባችሁን ወደ ፍቅር ፍቅራችሁን ደግሞ በሀይላችሁ በኩል አፍስሱት ያንጊዜ ያሰባችሁት ይሳካል ሃሳብ ብቻውን ምንም ነው ፍቅር ሃሳባችሁ የምታሳኩበት ማነቃቅያ ስሜት ሲሆን ሀይላችሁ መተግበሪያ ጉልበት ነው በሃሳባችሁ ብቻ ያለውን ህልማችሁን እራሱ እግር እንድያወጣ አትጠብቁ ሙሉ የእናንተን ጥሬትና ፍቅር ይጠይቃል ስራችሁን ሁሌም እንደ አድስ መንፈስ ቁጥሩት ገና ያላወቃችሁትና ልታውቁት የምያነሳሳችሁን ስሜት በውስጣችሁ ያዙ ሰዎች በመንገዳቸውና በህይወታቸው በመሰላቼት ብዛት ሁሌም ከፍቅር የምያወጣቸውን መንገድ እንደያዙ ነው የምትይዙት መንገድ ሁሌም አድስ ነው በረባ ባልረባ የምንሰላች ከሆነ እውነታኛ ስሜታችን በውስጣችን ይዋዥቃል መኖር የምንችለው በያዝ ነው ነገር ላይ መሆን አለበት በሃሳባችን ያለው ነገር ለማግኘት አመታትን ልፈጅ ይችላል በእጃችን ያለው ግን ከሀሳባችን የዘለሌ እውነትነት አለው በእውነቱ መንገድ ወደ ህይወታችሁ ፈሰሱ ያን ጊዜ የያዛችሁት ነገር ለምመጣው የደስታችሁ መንገድ ይሆናል የረጋ ሰው ቁቤ ነገሮች ወደ እናንተ እንደ ፈሱ ከፈለጋችሁ በህይወታችሁ ውስጥ ብዙ መንገዶችን ክፍት አድርጉ መንገድ የሌለው ደስታ መፍሰስ አይችልም መፍሰስ የምለው ቃል እራሱ መንገደ ነፃነት የምጠይቅ ነገር ነው ህይወት ልክ እንደ ሰፍ ጎዳና ነው ለመንሸራሸር ግን የሃሳባችሁ ከፍታና ዝቅተ ይወስናል መፍስስ በነፃነት ስሆን ህይወት በፍቅር ይሞላል ከሁሉም አክራርነት የፀዳ የራሱን እውነተኛ መንፈስ ያለው በነጻነት ይፈሳል ይችህ አለም በብዙ ተፈጥሮና በብዙ ፀጋ የበለፀገችናት ሰዎች ግን የፍጥረትን ፀጋ በራሳቸው ከንቱ ስሜት በማዞር አድስ ለምመጣው ትውልድ የተፈጥሮን ቋንቋ አበላሽቶ የራስ ወዳድነት ስሜታቸው የወለደውን አርትፍሻል ቋንቋ እያወረሱ ይገኛሌሉ አምላክ የተለያየ ፀጋዎች በቀለምና ቁመት በውፍረትና በቅጥነት በምድር የፈጠረው ውበት ለሰው ልጅ እንድሰጥ አስቦ ነው ሰዎች የራሳችሁን ከንቱ ስሜት ወደ ሰው ለማሰገባት ስሉ የተፈጥሮን ትክክለኛ ሁለንተና እያዛቡ ነው ይህም ከንቱ በውስጣችን ያስቀመጥ ነው ረካሽ ስሜት የወለደው ሀሳባችን ነው የዘመኑ ትውልድ ከፍብሎ የበረረ ብመስለውም ከራሱ ጋር እና ከተፈጥሮ ጋር ለየቅል እየነጎደ ነው ሰው ከተፈጥሮ መለያየት የረጋ ሰው ቁቤ ስጀምር ከግዛዊ ስሜቱ ጋር መቆራኘት ይጀምራል የተፈጥሮ ቋንቋ ብዙ ምስጥሮች ያሉትና የተለያዩ የሰው ልጅ እውነተኛ ጥበብን የያዘ ስሆን ይህንን ግን ሰው ካለመረዳቱ የተነሳ በገዛ ስሜቱ ተፈጥሮን ለማሽከርከር ስጥር ያለምንም ውጤት በትንሽየ የጥበብ ብልጭታ እራሱን እያታለለ ይኖራል ተፈጥሮ ጥበብን በሰከነ መንፈስ የምመረምርና ስሜት ያልወለደውን መሻት በውስጡ ያኖርን ብቻ እውነተኛ የጥበብ መንገድን ታስተምራለች አበቦች እንኳን በያዙት መአዛና ቀለም ሰውን ማዝናናት እንደምችሉ ሰው አውቃለሁ ብሎ ልያወራላችሁ ይችላል ነገር ግን አበባን ለመትከል ጓሮውን የምቆፍር ግን ጥቅት ነው ምክንያቱም ሰው የተፈጥሮን ቋንቋ አውቃለሁ ብሎ ስያወራ ብቻ እንደተረዳ አድርጎ ስያስብ ከድርግቱ እራሱን ያቅባል የተፈጥሮ ቋንቋ እኛ በተጠጋነውና ከተፈጥሮጋራም አብሬን በኖርን ጊዜ ልንረዳው የምንችለው ንፁ ያልተመረዘ ቋንቋ ነው አለም ብዙ ቋንቋዎችን አዛብታ ለትውልድ ስትሰብክ ኖራለች ለምሳሌ ቀይ አበባ ቀይ የሆኑ ልብሶችም ሆኑ ቀይ መክናና የተለያዩ ቀይ ነገሮች የፍቅር መገለጫ አድርገው ይቆጡሩና ለትውልድ ስያስተምሩ ኖረዋል የረጋ ሰው ቁቤ ነገር ግን ቀይ ነገሮች የፍቅር መግለጫ ነው ካሉ በእግርኳስ ላይ ቀይ ካርድ የተመለከተ ተጫዋች ዳኛውን ዘሎ መሳም ነበረበት በእግር ኳስ በትራፍክ ህጎችና በእስፖረቱ አለም ቀይ ካርድ የጥፋት ምልክት ነው ይህም ምን ያህል በትውልዱ መካከል የተፈጥሮን ቋንቋ እያዛቡ እንዳስተማሩ መገንዘብ አያቅትም ቫላንታየን ሁለተኛ ምሳሌ ልውሰድላችሁ ቫላንታየን ሰው ልጅ በሶስት መቶ ስልሳ አምስት ከንሁስ ቀናቶች መካከል የምያከብረው የፍቅር ቀን ነው ክፉ ሀሳቦች ወደ ሰው ስገቡ አንድ ትንሽ እውነትና ብዙ ብልጠቶችን ይዞ ነው በትንሽየ እውነት ሰውን ስያሳምኑ በብልጠታቸው ደግሞ ሰውን ያጃጅላሉ አንድ ቀን ብቻ የፍቅር ቀን በህይወቱ የምያቀብር ሰው ሶስት መቶ ስልሳ አራት ቀናቶችን በጦርነት ያሳልፈል ማለት ነው እውነት እላችሃለሁ ፍቅር ልክ እንደ እስትንፋሳችሁ ቁጠሩ ስትስቡትና ስታወጡት ብቻ እውነትን በውስጣችሁ የምትቆጣጠሩት ነገር ግን ክፉ ሀሳቦች ከሶስት መቶ ቀናት በላይ ውስጥ አንድ ቀን ብቻ ሰውን ለመሸወድ የፍቅር ቀን ስያስከብሩ የቀረውን ብዙ ቀን ግን በክፉ ድርግት ሰውን ስያጃጅል ይኖራል የረጋ ሰው ቁቤ ቫላንታይን ዴይ ሳስበው ሰጣን ለሰው ልጅ ያወጣው እቅድ ይመስለኛል እንደዛማ ካልሆነ ትክክለኛ አዕምሮ ያለው አንድት ቀን ብቻ በህይወቱ አመት ዙሮ በመጣ ቁጥር የፍቅር ቀን ብሎ አያከብርም የፍቅር ቀናችሁ ለህይወት ለመቆየት ወደ ውስጣችሁ በየሰከንዱ እንደምመላለስ እስትንፋሳችሁ ይሁን ፍቅር አብራችሁ በየከሰንዱ የምኖር ጸጋችሁ ነው ኢየሱስ ስያስተምር ከነበረውና ከወረወረው ቃላቶቹ ውስጥ ሁሌም ፍቅርና ርህራሄ ነበሩበት እናንተም በፍቅርና በርህራሄ መካከል እራሳችሁን አንፁ በፍቅር ተወልዳችሁ በርህራሄ እድጉ ከወደጆቻችሁም ጋር በፍቅር ተገናኝታችሁ በርህራሄ መካከል ተግባቡ በፈገግታ ደግሞ ስመሽ ተሸኛኙ በዚህም መንገድ የህይወታችሁን ትልቁ ጨረቃ ታያለችሁ ሰላማችሁ በፍቅርና በርህራሄ ስሞላ የአምላካችሁን የሹክሹክታ ድምፅ በህይወታችሁ መካከል ትሰማላችሁ በማስተዋላችሁም መካከል ለፍጥረት ሁሉና ለአድሱ ትውልድ መልክት አስቀምጣችሁ ማለፍ ትችላላችሁ ወደ ዋናው ሀሳብ ልመልሳችሁ እና በልቤ ያኖርኩትን ፍቅሬን አብሬው ለኖርኩት ጊዜ ሁሉን የህይወተን በሮች የረጋ ሰው ቁቤ በፍቅር ከፍቼ የፍጥረት የዝማሬ ድምፅ እሰማበት ነበር ዛሬም በአካል አጣገቤ ባይኖርም ቃላቶቹ በሃሳቦቼ መካከል እየተመላለሱ በፍቅር ይጎበኙኛል የምታፈቅሩት ሰው ከህይወታችሁ በአካል ላይኖር ይችል ይሆናል በሀሳባችሁና በህልማችሁ መካከል ግን ሁሌም በትዝታዎች አማካኝነት እንደጎበኛችሁ ይኖራሉ ፍቅር በሰው ውስጥ ያለነገር ስሆን ሀሳባችሁ ወደ ፍቅር ስሜት በነጎዱ መጠን ፍቅር በውስጣችሁ ይጨምራል የፍቅር ምግብ እኛ ከውስጣችን የምናመነጨው የፍቅር ስሜት ነው ለዛ ነው የምታፈቅሩትን ሰው ደጋግማችሁ በፍቅር ስሜት ባሰባችሁ ቁጥር ፍቅሩ በውስጣችሁ የምበዛው ፍቅር ውስጣችን ስያድር የምንወደውን ሰው በውስጣችን በሃሳብ ድጋም ስንወልደው ፍቅር በእኛ ውስጥ ሕያው ይሆናል ሶቅራጠስ ብሎ ነበር አምላክ ሁሌት አይን ሁሌት ጆሮ አንድ ልብ የሰጠን አንዱን ከአንዱ እንድን ለይበት ነው እኔ ግን እላችሃለሁ አምላክ ሁሌት አይን ሁሌት ጆሮ ነገር ግን አንድ ልብ የሰጠኝ በአንድ ከተማ አንድ ንጉስ ብቻ እንድኖር ፈልጎ ነው በአንድ ከተማ ውስጥ ማቼም የረጋ ሰው ቁቤ ሁሌት ንጉስ ተስማምቶ መኖር አይችሉም ህዝቦቹም በሁሌት ንጉሱን መገዛት አይፈልጉም የንጉሶቹም ምኞት ለየቅል ልሆን ስለምችል ግዴታ አንዱ ንጉስ አንዱን መብላት አለበት እናንተም በልባችሁ መካከል አንድን ንጉስ ብቻ ማኖር የምትችሉት ለዛ ነው አንድ ንጉስ ብቻ መሾም ስትችሉ ልባችሁ በአንድ የእውነት መንገድ መፍሰስ የምችለው መንፈስ ስሜታችሁንና መሻታችሁን ይዞ በፍቅር ከትልቁ ልብ ጋር ዝምድና መፍጠር ስችል ነው አንድት ክፉ ቀን ግን ፍቅሬን ቀማኝ ያችን ቀን እሱን ብትቀማኝም የህይወት ክፍሌነች ስለዝህም አልጠላት አልኮንናትም በአካል ነክቼ እንዳል ዳስሰው በአይኖቼ አይቼ እንዳልረካበት ያደረገችኝ ቀን የእውነቶቼን እውነት እንዳስብ አደረገችኝ እናም የነካውትንና የዳሰስኩትን በሃሳብ ብቻ እንዳኖር ተገደድኩኝ ፍቅሩ በልበ ስኖር በሃሳቦቼ መካከል በትዝታ መልክ ይቀመጣል ከፍ ብየ በልበ ያኖርኩትን በሀሳቦቼም መካከል በከፍታ አኖራለሁ በህይወተ መካከል እውነት ሆኖ የመጣውን በአውነትነቱ ተቀብያለሁ እውነት ስከማች ታርክ ስሆን ለሰምው የምናልባት ድርግት ልመስለው ይችላል በባሌበቱ ልብ ውስጥ ግን የአንድ ዘመን እውነት ነው የረጋ ሰው ቁቤ አውነት በህይወታችሁ በፍቅር ስበለፅግ ከተፈጥሮ ጋር ትግባባላችሁ ተፈጥሮ ጋርም ተስማምቶ በእውነት የኖር የአምላኩን የጥበብ እጆች ቀን በቀን እያየና እየተገረመ ይኖራል የፍቅር ስሜት በውስጣችን ያኖረ አምላክ በራሱ እቅፍ ውስጥ በፍቅር እንደምኖር ያን ጊዜ ትረዳላችሁ ከአምላክ ልብ ውስጥ የምትፈሰው አንድት ጠብታ ፍቅር በምድር ላይ ስታርፍ የተፈጥሮን ሁለንተና ፈጥራለች አለምም በአንድት የአምላክ የፍቅር ጠብታ መካከል የምትኖር የራሱ ፀጋ ናት በልበ አፍቅሬ በሀሳብ የማኖረውን ፍቅሬን በሞት ብነጠቅም በሁለንተናየ መካከል በእራሰ ስብእና በውስጤ አኖረዋለሁ በህይወት መካከል ሁሉም የፍቅር ክንውኖች ከፍቅር ናቸው አንድ ሰው አፍቅሮ እንደተጎዳ ልነግራችሁ ይችላል በዝህ ሰው ህይወት ውስጥ አለም አንድ የፍቅር መጥፎ ጎን ሹክ ብላበት ልሆን ይችላል እውነት እላችሃለሁ በፍቅር መካከል የጉዳት ድርግቶች እንዳለሁ ኢየሱስ እንኳን ስያስተምር ሰምቸው አላውቅም ኢየሱስ ካስተማሬው ትምህርት መካከልም በፍቅር ሰው ይጎዳል ያለበት ቦታም አንድም ቃል ከአፉ ወቶት አያውቅም አለም ግን የዝህን ተገላብጦሽ ታስተምራቹነለች የረጋ ሰው ቁቤ ሰዎችም አፍቅሮ እንደተጎዱ በብዛት ያወራሉ ፍቅር ግን በውስጣችን ተቀምጦ ሁለንተናችንን ሀሴት የምያደርግ መንፈስ እንጅ የጉዳት ውጤት አይደለም በፍቅር ህይወት ውስጡ ሁለንተናውንም የምቀርፅ ሰው እስትንፋሱንም በፍቅር ይምጋል የፍቅር ትረጉምም አዛብታችሁ የተረዳችሁና ከማፍቀርም እራሳችሁን የገደባችሁ ሰዎች አሁኑኑ የፍቅር መንፈስ ተላበሱና ወደ እውነተኛ ስሜታችሁ ፍሰሱ የልባችን ፀጋ ማፍቀር እስከ ሆነ ድርስ የልባችሁን መቅረዝ በፍቅር ብርሃን ሙሉት የልባችሁንም ግዛት በሀሴት አኑሩት ከሁሉም ከሁሉም ማፍቀር ያቆማችሁ የልባችሁ ባዶ አደራሽ ይዛችሁ በምድር የምትመላለሱበት ጊዜ ይብቃችሁ መኖር እስካለችሁ ድረስ አይናችሁን ለማየት ጆሮዋችሁን ለመስማት ልባችሁን ለማፍቅር እጃችሁን ደግሞ ጠላታችሁንም ጭምር ለማቀፍ ተጠቀሙት እያንድንዱ የአካለችሁ ክፍል ስራ ስጀምሩ ከውስጣችሁ በሸታ መንፈስ ይወጣና ህይወታችሁ ልክ ገና እንደተወለደ ህፃን ይሆናል ያንጊዜ ነገሮችን በትኩረት መመልከት ትጀምራላችሁ ከሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ትኩረት ስወጣ ባዶ ስሜት በቻ በውስጣቸው ይነግሳል ባዶ የረጋ ሰው ቁቤ ስሜት የምሞላና የምንቀሳቀስ ነፍስ በውስጡ ይፈልጋል እናም መላ አካላችሁን አንቀሳቅሱ ህይወት እራሷ በሀሴት መፍሰስ ትጀምራለች ከሁሉም ከሁሉም መሰላቼት በባዶ ስሜታችሁ በኩል የምመጣ በውስጣችሁ የምኖር እናንተን በጥገኝነት ተጠቅሞ ቀስ በቀስ የምገድላችሁ ስሜት መሳይ በሽታ ነውና እራሳችሁን ከመሰላቼት ስሜት ጠብቁ የመሳለች ስሜት የገባውም ነፍስ የዛሬዋን የደስታ ቀን ማጣጣም አትችልም በማጣታችሁም በኩል የምወለደውን የቅናት ስሜትም በህይወታችሁ ውስጥ ነቅላችሁ አውጡ የቅናት ስሜት ወዳጃችሁንም የምቀማችሁ ክፉ ሀሳብ የምጠነስሰው ስሜት ነው በጦርነት ላይ የዘመተ ብቻ ስለ ጉዳት ማውራት ይችላል ምክንያቱም ጦረነት የምቀሰቅስ ነፍስ ፍቅርን ከውስጡ ስደተኛ ያደረገ ሀሳብ ያለው ስለሆነ ጦርነትን እንደ መፍትሄ ይቆጥራል እርስበርስ ካለችሁ ፍቅር በላይ በልጦ ጦርነትን ያሰበች ነፍስ ውጤቱን በጉዳት ትገልፀዋለች ሴፍ ያነሳች እጅ በአንደበቷ በኩል ጉዳቱን ለትውልድ ብትሰብክም በልቧ ግን የጦርነትን ሽርፍራፍ ሀሳቦችን ዛሬም ድረስ እንደያዘችና ከውስጧ ማውጣት እንዳልቻለች ነው የረጋ ሰው ቁቤ አለምም ለጦረነት ያላት ቦታ ለፍቅር ብኖራት የተፈጥሮ በረከቶች በአንድ ሀብታም እጅ ላይ ብቻ ባልወደቀ ነበር የጦርነትም ሀሳብ ብዙ ግብዞች አበረከቶ የምስክኖችንም ጎሮሮ በሀብታም ደጃፍ ላይ ለምፅዋት አስከፈተ ጦርነት የአንድ ሌሊት ውጤት ስሆን ፍቅር ግን እየኖርከው እንኳን ፍፁም አድርገ ልትረዳው የማችለው ስሜት ነው የፍቅሬንም ቀብር በምድር ውስጥ ባኖረውም በልቤ ውስጥ ግን አብቦ ይኖራል አፈር ቆፍረን ከቀበርነው ይልቅ በልባች ውስጥ በፍቅር ያስቀመትነው ህያው ነው በህይወት ውስጥ ያኖርከው ህይወት በነፍስም ውስጥ ሆኖ ለፍቅር አምላክ ምስጋና ያቀርባል ከፍቅሬ መቃብር ላይ አፈሩን አንስቼ ወደ ቤተ ገባው ቤቴንም ጠረኩትና የመቃብሩን አፈር በቤቴ ውስጥ በተንኩት አሁን እርሱ እዚህም ከእኔ ጋር ይኖራል ከዚህ ቦኋላ ህይወተን በደስታ በሀሴት እመራለሁ ፍቅሬ በውስጤ እስካለ ድረስ የፍጥረትን ዜማ ከራሴ ህይወት ጋር አዋህጄ እሰማለሁ የሀዘንተኞችንም ሙሾ በፍቅሬ ነፍስ ውስጥ በፍቅር አወጣለሁ ምክንያቱም የረጋ ሰው ቁቤ የምመጣውንም የምሄደውንም በፍቅር መቀበልና በፈገግታ ተሞልቶ በፍቅር መሸኘትን ፍቅር አስተምሮኛልና ደጃፎቼ በመልካም ጠረን እንደአወዱ ናቸው ለምመጡት እንግዶቼም የፍቅር ሰላምታቸውን በመልካም መኣዛ በኩል ያደረሱልኛል ደስታየም የሁሉም ደስታ ነው ከፍጥረት ስለሆንኩኝ የፍጥረት እንብርት ነኝ በፍቅር የምኖርና በደስታ ፍጥሬተን በውስጤ የማስተናግድ ሰው ነኝ ይህ የእኔ እውነት ነው አካለም ነው እወደዋለሁ በእኔ ህይወት ውስጥ ያለ የፍቅሬ ውህደት የወለደው የተፈጥሮ ፀጋ ነው እናም አፈቅረዋለሁ ነገር ግን የሆነ ዘመን የተደረገ እውነት ለሰዎች ስታወሩላቸው እንደታርክ ይሰሟቹሃል በባሌበቱ ልብ ውስጥ የተቀመጠ የእውነቱ እርሾ ግን ለዘላለም ከታርክ የቀደመ እውነት ሆኖ ይኖራል አለች አንደ ብቻ ቀና ብላ ወደ ምስራቅ ተመልክታ የረጋ ሰው ቁቤ የጣላችሁት የቃል ቁልፍ አንድ ክፉ ንጉስ ነበር ንጉሱም በአምስት መቶ መትር ላይ በሹል የሰሩ ብረቶችን ያቆምና ባርያዎቹን እዛ ላይ በባዶ እግራቸው ሂደው ካሸነፉ አንድ እንስራ ሙሉ ወርቅ እሸልማለሁ በማለት ባሪያዎቹን ያወዳድራል ንጉስም ይህንን ድርግት እንደ መዝናኛ ይቆጥረዋል ባሪያዎቹ ይህንን ውድድር ብወዳደሩም አንድም ቀን ግን ማንም ሹል ብረቱ ላይ ሂዶ ጨርሶ አያቅም ምክንቱም በብዛት የቆመው ሹል ብሮቶቹ ላይ ሂዶ ሳይጨርሱ ይወድቃሉ በሹል ብረቱ ላይም ስወድቁ ህይወታቸው ታልፋለች ንጉሱ ግን ለዘመናት ብዚህ ድርግት እንደ ቲርዕት ቆጥሮ ስዝናናበት ኖሮዋል ባሪያዎቹ አሸንፎ የምያገኙትን ወርቅ ብቻ በማሰብ ለዘመናት ህይወታቸው አደጋ ላይ ጥለዋል ይህንን ድል አሸንፎ ወርቁን የተሸለመ ግን ማንም አልነበረም ገና ግማሽ እንኳን ሳይደርሱ ሹሉ ብረት እግራቼውን ይወጋና ብረቱ ላይ ይወድቃሉ ውጤት ያለሁ ህይወት ከፍ ብሎ በሰው እይታ ጎልቶ መታየት እንደሆነ ብዙዎች የረጋ ሰው ቁቤ ያምኑበታል ነገር ግን ይህ ነገሮችን በጥልቀት የማየታችን እይታ የጋረደ ነው ሰዎች ይህን ያህል ሞኝ ናቸው ገና ተሸልሞ ለምኖሩት የደስታ ህይወት ብሎ ህይወታቸውን ይሰዋሉ መኖር ዛሬ ያለውን ህይወት በመልካም እስትንፋስ መካከል በደስታ እየተነፈሱ መኖርን አልተረዱም ህይወታቼውን አደጋ ላይ የምጥሉትም በምናልባት ያለች የነገ ህይወት በማሰብ ዛሬን ያለምንም መልካም ህይወት ያልፋሉ ውጤት የሌለውን ድርግት አንዱ ስፈፅም ሌለኛው ማስተዋል ስላማይችል በዛው መንገድ ይሄድና አንድ አይነት ውጤት ላይ ይደርሳሉ አባቱ የሄደበት መንገድ ላይ ልጅ ብሄድበት መድረሻቸው አንድ ነው ህይወት በብዙ ምርጫ የተሞላች ነች ውጠቱም ከራሳችሁ ስሜት ጋር ስሆን እውነት ይኖረዋል አንድ በጣም የተቸገረ ሰው ሜቶ መቶ ብር ብጠይቅህና አንተ ያለሄው ብር ዘጠና ዘጠኝ ብር ብቻ ብሆን ብሩን ብትሰጠው ምናልባት ዘጠናዘጠኝ ብር ስለሰጠው ላያመሰግንህ ይችሳል ነገር ግን ለአስቀረሄው አንድት ብር እንደክፋት ቆጥሮ ይቀየምሃል የሰው ስሜት ሄሜትን እንደ ጣፋች የነፍስ መግብ አድርጋ ማሰብ የረጋ ሰው ቁቤ እስካላቆመች ድረስ የሰው ነፍስ ለእውነት አትቀርብ ከሀመተኛ አንደበት የምወጡ ምስጋናም በደመና ውስጥ ጉም ሆነው ይቀራሉ ሀመትን የምትወልድ አንደበት መሃን ቃላቶችን በህይወቷ ትፈጥራለች መልካም አንደበት ብቻ የህይወትን ፍሬ ቃል ለሰው ትዘራለች ሀሜት ከምታወራ አንደበት ይልቅ ድዳ አንደበት ለምሳጋና ስጣጣር የአምላክ የምስጋና ግዛቶች ይከፈታሉ በድዳ ልብ ውስጥ ያለውም የምስጋና ቃል በአምላክ ልብ ላይ በረከት ሆኖ ይዘንባል እውነት እላችሃለሁ የምታማው አንደበት የገሃነብ ደጆችን ቁልፍ በምላሷ ትቀርፃለች አንድ አባት በአስተምሮት ውስጥ እንደህ አሉ አምላክ በምድር ላይ ስጋ ለብሶ በህይወት ዘመናችን ይመጣብናል ስመጣብን አንድት ቁልፍ ሰቶን ያልፋል ቁልፉም የገነት በር መክፈቻ ቁልፍ ናት ግን ብዙ ሰዎች የቁልፏን ጥቅም ስለማያውቁት በወሰዱ ማግስት የት እንዳስቀመጡ ይረሳሉ ቁልፏንም ስጥሉ የገነት ተስፋቸው ያከትማል እኔሱ የመጣላቸው ምስጢር አምላክ ቁልፏን በሰጣቼው ማግስት አለም ተመሳሳይ ቁልፍ ቀረፃ መዘጋጀቷ ነው አለምም ቀስ በቀስ የረጋ ሰው ቁቤ የአምላክን የገነት ቁልፍ እያስጣለች እራሷ የቀረፀችሁን ታሳቅፋቸዋለች ሰዎችም ከዚህ የተነሳ ይታለሉና የገነት ቁልፍ በአለም ላይ ጥለውት ይሄዳሌሉ አምላክም ይህን የምያደርገው ለልጆቹ ካለው ፍቅር የተነሳ ነው የአምላኩን የቃል ቁልፍ የያዘ ብቻ በምድርና በሰማይ መካከል ያለውን የገነትን በር ያገኛል ከዚህም አመሳስላ አለም የሰጠችሁን ቁልፍ ሰዎች ይዞ ስሄዱ በዛ የተዘጋጀላቸውን የገነት በር አይከፍትላቸውም በእጃቸውም የያዙትን ቁልፍ ቤታቸውን ለመክፈት ስሞክሩና አግኝተው ስከፍቱት ገሃነብ ይሆንባቸዋል ሰው ቁልፍ በእጁ መያዙን እንጅ የምን ቤት እንደሆነ የምረዱት እዛደርሰው ከከፈቱት ቦኋላ ነው የገነት ቁልፍ አስተውላችሁ ካላስቀመጣችሁ ብዙ ተመሳሳይ ቁልፎችን አለም ታመርታለች እውነተኛውን ቁልፍ በነፍሳቹ መካከል ያዙት ለአፍታም የቃሉን ቁልፍ ከህይወታችሁ አታውጡ አንድት ቃሉን ባወጣችሁ ጊዜ አለም አስመሳይ ቁልፏን በውስጣችሁ ማኖር ትጀምራለች እውነተኛ የራሳችሁን ስሜት ለአፍታ እንዳትዘነጉት ምክንያቱም አለም ብዙ የመሻት ስሜቶችን በውስጣችሁ የረጋ ሰው ቁቤ ትዘራለችና ነቅታችሁ ጠብቁ ለጥቅት ደቅቃ በህይወቱ ያንቀላፋ የቁልፉን ቃል ይነጠቃል የቤታችሁን በር በቁልፋችሁ እንደምት ከፊቱ ሁሉ የነፍሳችሁንም የገና በር በቃሉ ትከፍታላችሁ የቃሉን ቁልፍ ከምንም በላይ በህይወታቸሁ መካከል አስቀምጡ በተቸገራችሁና በተደሰታችሁ የምስጋናችሁ ጊዜ አንዳይቋረጥ ምስጋናችሁ ስቋርጥ ቁልፉን ትዘነጋላችሁ ምስጋና የቁልፉ ማንጠልጠያ ገመድ ነውና ገመዱን በምስጋና ከውስጣችሁ አኑሩት የጎደሉ ቃላቶች የቁልፉ ፀርናቸውና ወደ ውስጣችሁ እንድገቡ አትፍቀዱ ለፍቅር በጎደለ ልባችንና ለምስጋና የማይታዘዝ ነፍስ የአምላክን ግዛት ጥላ የወጣች ባሪያነች ባርነትን የምሹ ስሜቶች በጎደሉ ቃላቶች በኩል በውስጣችን ይወለዳሉ ከዚህን በፊት በህይወታችሁ ለተከሰተ መጥፎ ነገር አንደ የተደረገ ታርክ ነው ለተከሰተው ነገር መንስኤ ለማጥናት ጊዛያችሁን አትፍጁ ይልቅ ስለ መፍትሄው አስቡ አንድ ለተከሰ ነገር መንስኤ ከድርግቱ በፊት ያለ ነገር ነው ነገር ግን ከድርግቱ ቦኋላ ላለው ነገር መፍትሄ ብቻ የችግሩ ቁልፍ ይሆናል የረጋ ሰው ቁቤ ሰዎች ችግራቸውን ይበልጥ የምያባብሱት ስለችግሩ ጠልቆ ስያስቡ ነው ችግር ከተከሰተ ቦኋላ ያለው መፍትኤ በውስጣችን ስለ መፍትኤ በጥልቀት ማሰላሰል ነው አዕምሮአችን እኛ ያጎረስነውን ነገር ላይ ተመስርቶ በማሰብ ይጠመዳል ከችግራችሁ ቦኋላ ስለ መፍትኤው ለዕምሮዋችሁ አጉርሱት በዚህም መንገድ ለችግሩ መፍትኤ ታገኛላችሁ መፍትኤውም የጣለችሁትን ወይም አለም የቀየረችባችሁን ቁልፍ መልሳችሁ አንሱት ከቁልፉ ጋር የእናንተ የፍቀር ነፍስ ተጥለዋልና መልሳችሁ በውስጣችሁ አኑሩ የመልካምነት ደጃፎች በጣላችሁ ቁልፍ ሳብያ ነፍሳችሁ ላይ አታዘጉ በፍቅር በተከፈተ ልብ ውስጥ ቁልፋችሁን አኑሩ ቁልፍ ራሱ በምድር ላይ የርሂራሄን በር ይከፍታል በዛም በኩል ሰው ለሰው ተፈጥሮም ለሰው ያለውን መስተጋብር ያጠነክራል ውስጣችሁን አንፁ በምላሳችሁ ላይ የምስጋና መዝሙር አዚሙ ቁልፉንም በውስጣችሁ አኑሩ በህይወት በኩል አልፋችሁም የገነትን በር ታገኛለችሁ ቁልፉም የራሱን በር ስያገኝ ወለል ብሎ ይከፈታል እዛም ውስጥ በፍቅር ለዘላለም ትኖራላችሁ አደራ ከዚህ ሁሉ በፊት ግን ቁልፉን በህይወታችሁ ውስጥ በፍቅር አኑሩት የረጋ ሰው ቁቤ የጥበብ በር አንድ አባት ልጁ ጥበብ እንድማረለት ፈለገና አንድ ጠቢብ ጋር ወሰደው ጠቢቡም ልጁን ተቀብሎ ጥበብ ማስተማር ከመጀመሩ በፊት ፊትለፊቱ ተቀምጦ የራሱን ዝምታ እንድስማ አዘዘው ልጁም ከጠቢቡ ፊት ለፊት ስቀመጥ ዋለና ማታ አባቱ ይዞት ወደ ቤት እየገባ ሳለ ዛሬ ምን እንደተማረ ጠየቀው ልጁም ዝምታህን ስማ ብሎኝ ቀኑን ሙሉ ዝማታዬን ለመስማት ጠቢቡ ፊት ለፊት ስቀመጥ እንደዋለ ነገረው በሁለተኛ ቀንም ልጁን አባቱ ጠቢቡ ጋር አመጣና ወደ ስራው ሄደ ዛሬም ጠቢቡ ቁጭ ብሎ ዝምታውን እንድሰማ አዘዘው ልጁም ጠቢቡ ፊት ለፊት በዝምታ ስቀመጥ ውሎ እንደትላንትና ማታ አባቱ መጣና ወሰደው አባቱ ዛሬም ደገሜና ምን ስማር እንደ ነበር ጠየቀው የረጋ ሰው ቁቤ ልጁም ዛሬም ቁጭ ብሎ ዝማታውን ብቻ ስሰማ እንደዋለ ነገረው አባትየውም እንዴት ዛሬም አንድ አይነት ድርግት ብቻ ያስደግመዋል እያለ ልጁን ይዞ ወደ ቤት ገባ ለሶስተኛ ጊዜም ልጁን ጠቢቡ ጋር አድርሶ አባትየው ወደ ስራው ሄደ ማታ ከስራ ቦታ መጣና ልጁን ይዞት ወደ ቤት እየገባ ሳለ እንደተለመደው ምን ስማር እንደዋሌ ጠየቀው ህፃኑ ዛሬም ተቀምጦ ዝምታውን ስሰማ እንደ ነበረ ነገርው አባትየው በድርግቱ ተበሳጨና በቃ ይህን ብቻ ነው ስትማር የምትውለው አለው አዎ ይህንን ነው ሳደርግ የምውለው አለና መለሰ አባትየውም በተደጋጋም ልጁን ብያመላልሰውም ጠቢቡ ግን ልጁን ዝምታውን ብቻ እንድሰማ ያስተምረው ነበር በዚህ ትምህርቱ ተስፋ ይቆርጥና ልጁን ጠቢቡ ጋር መውሰዱን ትቶ ቤት ውስጥ የተለያዩ መፅሐፍትና መጫወጫ ገስቶለት እዛው እንድማር አደረገው የረጋ ሰው ቁቤ ልጁም ቤት ውስጥ መፅሐፍት እያነበበ ሰነበተ ነገር ግን በሌለኛው ቀን አመሻሽ ላይ ልጁ ወደ ጠቢቡ ጋር እየሮጠ ሄደና እንድህ አለው አንድ ሀይል በዝምታየ መካከል መቶ ስወረኝና ስያናግረኝ ተሰማኝ ድምፅ አላወጣም በውስጤ ሀሴት ስያደረግ ግን ሰማሁኝ ዝምታየን መስማት ቻልኩኝ አለ ጠቢቡም ልጁን እንድህ አለው የጠቢብ የመጀመርያ ስራው ዝምታውን መስማት መቻሉ ነው የጥበብም የመጀመርያው መግብያ በር ዝምታ ነው የረጋ ሰው ቁቤ የመስጠት ጥበብ የስስት አይኖችሽ በላየ ላይ ይሁኑ ምናልባት የግብዝነት ስሜቴን በውስጤ ይገቱ ይሆናል ዘንግቼሽ እንዳልኖር የፍቅር መንፈስሽ ሁሌም ይጎብኙኝ አንች በእኔ ውስጥ የትላንትና ስብዕናዬን ያፈረስሽ አድሱ ማንነተነሽ የሴት ፍጥሬት ገና እንደ አድስ ከአንች በውስጤ ተፈጠረ ሁሌም ለሰው ያለን ስሜት አድስ ነው የምያረጅ መንፈስና ስሜት የለም ባለቤቱ ግን ከመንፈሱና ከስሜቱ በፊት በሀሳብ ያረጃል በሃሳብሽ ውስጥ ያለው አድስ ሀሳብ ነኝ በመንፈስሽ ውስጥም ያለሁት አድስ መንፈስ ነኝ አንች የአድስ ጥርቅሞቸ ስሜትነሽ የአድስም ህይወት የመንፈስ እርካታነሽ ህይወት የምትቀጥል ባህርነች ሁሉንም እንደየግል ማንነቱ ተሸክማ ትሄዳለች ህይወት የምትፈረደው በባለቤቱ ልብ ውስጥ ቦታ ስታጣና የስደተኝነት ስሜት ስነግስ ነው በህይወት ውስጥ የምፈስ የህይወት አካል ነው በህይወትም አካል ውስጥ ያለ ነፍስ ለህይወት ምስጋና ያቀርባል ህይወትም በለፋባት ሳይሆን ባመሰገናት ልክ የደስታ ግዛት ታወርሳለች የረጋ ሰው ቁቤ አንችን ህይወት የያዘችሽ አንድ አካል ብትሆኝም በራሴ ህይወት ውስጥ ሙሉ አለምነሽ ሰው በዚህ ሰፊ አለም ውስጥ የራሱን የብቻ አለም ይኖረዋል የብቻም አለሙ ከባለቤቱ ልብና አምሮ የተቀዳ በፍቅርና በሀሳብ የምትገነባ የባለቤቱ መደበቅያ ዋሻነች በዋሻ ውስጥ ባይተዋርነት የተሰማው ሰው የአለምን የደስታ ምስጢር አይረዳም በራሱ መደበቅያ ዋሻ ውስጥ ብርሃን ይዞ የወጣ ብቻ የዚህችን አለም ምስጢር ይረዳል በያዘውም የብርሃን ጥዋፍ የአለምን ጨለምተኝነት እየደመሰሰ ምስጢሮቹን ከህይወት ጥርስ ውስጥ ይፈለፍላል ምስጢሩም ከጥያቄ ሀሳባችን በስተጀርባ ያለው ፊለጋ ስሆን ፊለጋውም በህይወታችን ልምምድ የምናገኘው መልስ ነው ሀሳብ በጥያቄና በአድንቆት መካከል ያለ ድልድይ ነው አስባችሁ ትጠይቃላችሁ አይታችሁና አስባችሁም ትገረማላችሁ የምያይ አይን የምያስብ ጭንቅላት ስፈጥር የምያስብ አዕምሮ የምያደንቅ መንፈስ ትፈጥራለች በመገረም መንፈሳችሁ መካከል ውበት ስያጎላ ምስጢሩን የምፈልግ ስሜትም ትፈጥራለች ምስጢር ለመረዳት የምፈልግ ነፍስ በፊለጋ የተሞላች የረጋ ሰው ቁቤ ስሜት በውስጡ አምቃ የያዘችነች ፊለጋው ድርግት ስሆን የምገኘው የብርሃን ፍንጥቅ ውጤት ነው እውቀትን ለመፈለግ አዕመሮ ስነቃ ሀይሉን ያድሳል ፍቅርንም ለመሻት ልብ ስነቃ ፍቅር ውስጡ እንዳለና መስጠት ላይ የተመሰረተ እርካታን ከውስጡ ያፈልቃል ፍቅርም በውስጣችን የተከማቸ በሰጠን ቁጥር የማይቀንስ ሙሉ ጸጋ ነው ፀጋው ከውስጣችን ስፈልቅና ወደ ሌላ ሰው ህይወት ስገባ የደስቴኝነት ስሜት በጋራ እንቋደሳለን በሳቅና ለቅሶ ደስታና ሀዘን መካከል ያለው ልዩነት የባለቤቱ የምፈራረቅ ስሜት ብቻ ነው ሁሉም ስሜቶች በአንድ ሰው ህይወት ውስጥ የምመላለሱ ስሜቶች ናቸው ማብቅያ የሌለው ደስታችሁ ሀዘናችሁን ስያሸንፍ ከውስጣችሁ የምወጣው የድል ስሜታችሁ ነው ሀዘናችሁ የተሸነፈ ለት ደስታችሁ ያይላል ደስታችሁ የተሸነፍ ለት ሀዘናችሁ ያይላል ሰው የስሜቶች ጥርቅም እንጅ ምንም ነው ከስሜታችሁ ወታችሁ አንድት የከፍታችሁን እውነት ስታዩ ስሜታችሁ እናንተ ውስጥ የምያልፍ ነገር መሆኑን ትረዳላችሁ የአንድ ጊዜ ሀዘን ስያልፍ የሌላ ጊዜ ደስታ የረጋ ሰው ቁቤ ወደ ህይወታችሁ ይመጣል የስሜቶቹ መቀያየር አንድን ሰው ላይቀይር ይችላል ሰው ግን ስሜቶቹን መቀየር ይችላል ሀዘናችሁን በውስጣችሁ ባሳደራችሁ ጊዜ የደስታችሁ ስሜት ይቀጭጫል የደስታችሁም ስሜት በውስጣችሁ ስነድ የሀዘን ስሜታችሁን ያጠፋል ይህም ሰው በውስጡ የምይዘውና አብሮ የመኖሩ ምስጢር ናቸው ከዚህ ስሜቶቹ አንድት እርምጃ ከፍ ማለት ቢችል የራሱን ከፍታ ያገኛል ከፍታችን ከስሜታችን በላይ ያለ እውነተኛ የሰው ልጅ መንገድ ነው አምላክ ከስሜታችን ከፍ ብሌን እውነተኛውን መንገድ ስንጀምር ወደ እኛ ይቀርባል በዛም መንገድ ሰው አንድት እርምጃ ስራመድ አምላክ ሰባት እርምጃዎችን ወደ ሰው ይቀርባል በእውነትም መንገድ ፍርድ አይኖርም ፍቅር የመንገዱ ብርሃን ነው በዛም መንገድ መላ አካላችሁ ፀጥ ስል ልበችሁ ማወራት ይጀምራል በአንድት ከልባችሁ በምትወጣው ቃል መንገዳችሁ ወደ አምላክ ይቀርባል ነፍሳችሁም ስታመሰግን መንፈሳችሁ ከናፍሮቻችሁ ላይ አርፎ ይዘምራሉ በምስጋናችሁም መካከል የአምሳክ የብርሃን ገፆች ይኖራሉ የረጋ ሰው ቁቤ ልባችን አምላክ በአንድነት በእኛ ውስጥ የምያርፍ ግዛቱ ነው ግዛቱን በቆሸሸና በረከሰ ሀሳቦች አታርክሱ በሁለንተናችሁ መካከል የምመላለሰውን የአምላክን መንፈስ በቅን ልባችሁ ይጎበኛሌሉ የእውነት ዜማም በልባችሁ ፍልቀው በከንፍሮቻችሁ ድዳዎችን ያናግራሉ ያንጊዜ ድዳዎች ከቃላት በላይ የሆነውን ሰውን ልጅ እውነተኛ ሰሜት ይረዱታል ቅዱስናውንም በህይወታችሁ ውስጥ አኑሩ እርኩሶችን ታነፁበታላችሁ የብርሃን ገፆችንም በልቦናችሁ ውስጥ ያዙ አይነስውሮችን ትመሩበታላችሁ የእውነት መንገድ ጠፍቶባቸው በጨለማ ለምዳክሩ ወንድሞቻችሁ የብርሃን አይኖች ትሆናላችሁ ቃሉንም በህይወታችሁ ውስጥ ዝሩት የመልካምነት ቃል ለጎደላችሁን ሰዎች ትሞላላችሁ ማባያ አግኝተው እንጀራ ላጡ ወጎኖች የእንጀራ ቃል ያበጁበታል ፍቅሩንም በልባችሁ ውስጥ አሳድሩ ፍቅር ለራቆተው ታበድራላችሁ አምላክም ለልጆቹ በደረሳችሁና ፍቅሩን በለገሳችሁ እጥፍ ይለግሳችሃል አንድት ንፁ ውሃ ከወንዝ ቀድታ የምትመጣ እንስት ውሃውን እንጅ እንስራውን እንደማትሰጥህ ሁሉ የረጋ ሰው ቁቤ ፍቅራችሁን እንጅ ልባችሁን አትስጡ ልባችሁ ውስጣችሁ ያለው የአምላክ ማደርያ ነውና የአምላክም የምስጢር ቃሎች መኖርያ ነው ከሰው አካል ልብ ሰው ከአምላኩ ጋር ጉባዬ የምይዝበት ቦታም ነው መስጠት ያለባችሁ ስጡ ፍቅርን ከውስጡ እንደ ንፁ ውሃ አፍስሳችሁ ስጡ ልባችሁን ግን እንደ እንስራው ወደ ቤታችሁ ስደዱት እንግዳውም በመጣ ጊዜ ማደርያ እንዳያጣ ደጃፋችሁም የምያልፍ መልካም መአዛ የቤታችሁን ጣራ እንደምጎበኝ ሁሉ መልካም መኣዛችሁ የወዳጆቻችሁን ህይወት ይጎብኙ ምናልባት የተዘበራረቀው የወዳጃችሁ ህይወት በመአዛው ችግሮቹን ይረሳባት ይሆናል የነፍሱን እስትንፋስ በበሰበሱ ሀሳቦች የዘጉት ችግሮቹ በመልካም መአዛው ይከፈቱ ይሆናል የአንድት የአይናችሁ ቅስበት መልካም እይታ የተቸገረችን ነፍስ ፈገግ ታስብላለች አንድት መልካም ቃልም የተጨነቀችን ነፍስ ታፅናና ይሆናል መልካምነትን ከሁሉ የምበልጥ በምድር ላይ የምትንቀሳቀሱበት እስትንፋሳችሁ አድርጋችሁ ያዙ ለመስጠትም በዘረጋችሁ ጊዜ ሀሴት ወደ ህይወታችሁ ትፈሳለች ንፉግ ሀብታም ለማከማቼት እጁን ስዘረጋ የደሃዎች ጭወት የረጋ ሰው ቁቤ በአምላካቸው ላይ ትበረታለች የደሃው ጭወት ከባለፀጋው ህይወት አንፃር ስለምትታይ የአምላክን የፍቅር ዙፋን ትዘልፋለች የደሃው ነቀፈታ ንፉግ ሀብታም የፈጠረው የግብዝነት ስሜት ነውና ህይወታችሁ በመስጠት ላይ ባለው የምስጋና ቃልም ይሞላ ፍቅር የሞላት ልብ መስጠትን ስያስተምር ምስጋናን የሞላት ነፍስ በከናፍሮቻችን ላይ ዚማሬን ታሰማለች በመስጠት መካከል የምትመላለስ ነፍስ የደስታ ባህር ውስጥ ለዘለላም ትሰምጣለች እየሰጣችሁ በደስታ ባህር ውስጥ ስመጡ ህይወታችሁ ያን ጊዜ በአምላክ ቃሉ ውስጥ ታርፋለች የረጋ ሰው ቁቤ የምስራቅ ደጃፊ አንድ ቀን ጥዋት ጥዋፍ እያበራሁ ወደ ምስራቅ ስሄድ አንድ አባት መጡብኝና ልጀ ወደምስራቅ ደጃፍ ነዉ የምትሄደዉገ። በረጋ አዕምሯችሁ የአንድነትን ሀሳብ አመንጭታችሁ ከረጋ ልባችሁ ፍቅር አፍልቃችሁና ከረጋ ነፍሳችሁ ምስጋናን እየሰዋችሁ በደስታ የታጀበውን ህይወት ኑሩ የረጋ ሰው ቁቤ ጊዜና ዕድል አንድ እድል የምባል ነጭ ልብስ የለበሰ ሰውየ በጀርባው ላይ ስሳይ ተሸክሞ በተደጋጋም ከደጃቸ ላይ ቆሞ ይጠራኛል እኔ ግን ከውስጥ በኩል በራፈን ሸጉጨ ቤቴ ውስጥ ተቀምጫለሁ እድልም በተደጋጋም ሳይሰላች ስጠራኝ ቆይቶ ሳልከፍትለት ስቀር ተስፋ ቆርጦ ደጃፈን ጥሎ ስደት ስጀምር ደጃፈን ከፈትኩኝ ደጃፈን ከፍቸም ስመለከት እድል ጀርባውን ለእኔ ሰቶኝ ስሄድ ከጀርባው በኩል ለእኔ የመጣውን ስሳይ ይዞ ስመለስ አየውት ተከትየም ብጠራው ልሰማኝ ግን አልቻለም ሩጨም ልደርስበት አልቻልኩም ደግመም ጠራውት አሁንም ግን ምንም ድምፅን አልሰማም ወደ ዳጃፌ ተመልሸ በአይኔ ተከተልኩት እያየሁትም ጉም ውስጥ ገባ ወደ ቤቴም ገባውና የቤተንም በር ገነጠልኩት ቤቴንም ያለበር አስቀረውት ምናልባት ተመልሶ ይመጣ ይሆን ብዩ የረጋ ሰው ቁቤ መርሳት መጥላትን አላውቅም ልቤ ሰገነት ነው ደጃፈም ክፍት ነው ምናልባት ዶፊ ስዘንብ መጠለያ ያጣው ጠላቴ መቶ ያርፍበታል በዛች ቅስበትም በፍቅር ውስጥ የምኖር የክብርና የይቅርታን ታላቅና ታናሽነት ይረዳ ይሆናል በገዛ ሃሳብ ውስጥ የጠላትነት ስሜት የፈጠረው የአባቴ የሙት ልጅ የሆነው ወንድሜ በእኔ ውስጥ ያለውን የፍቅርን ዳርቻ ስረዳ የይቅርታ ጉዞ በምስራቅ በኩል ወደ አድስ ዓለማችን ይጀምራል የሳሳ የመሰለው የዚምድናችን ሀረግ ለዘመናት በመንፈሳችን ሀያልነት ተሳስሮም እንደኖረ ይገባውም ይሆናል ወንድሙን ለመግደል ቤቱን ዘግቶ በረቱ ውስጥ አስሮ የመጣውን በግ ለመግደል በሄዴ በውንድሙ ፍቅር ስሸነፍ አስሮ የመጣውን በግ ያርድና የተዘጋውን የወንድምነት የፍቅር በር በይቅርታ ይከፍታል በዚህ ሰፍ አለም ላይ ፀሐይ ብቻዋን ብርሃን ለምድር ታደርሳለች ልባችን በውስጣችን ብቻዋን ያለች ለአከላችን ፍቅርና ደም ታደርሳለች ሁለቱም በሰውና በተፈጥሮ ማካከል ያሉ የሁለንተናችን ማዕከል ናቸው የረጋ ሰው ቁቤ እናም በልቤ ውስጥ ያለው ያንተ ፍቅር ዘላለማዊ ነውና በይቅርታ ልብህ ተቀበለኝ የጠጠረ ልብ አምላክ አንድ ቀን መላዕክና ሰጣንን አንድ ላይ ጠራ ሁሌት ተራራ ጎን ለጎን ቆሞው ይታያያሉ ሁሌቱን ተራራ የምታገናኝ አንድት ቀጭን ክር በተራራው መካከል ተዘርግታ ትገኛለች ወደ መገንጣያው ተራራ እስከምወስዳቼው ድረስ ሁለቱም ወደ ተራራው ለመውጣት ግዴታ በቀጭኗ ክር ላይ ማለፍ ይገደዳሉ አምላክም ከተራራው ላይ ተራ በተራ ተሻግረው እሱ ካስቀመጠበት ቦታ ላይ ያስቀመጣቸውን አንድንድ ሰው እንድያመጡ አዘዛቸው ቀጭኗ ክር ሁለቱን በአንድ ላይ መሸከም ስለማትችል ከመላዕክቱና ከሠጣኑ ማን ቀድሞ በቀጭኗ ክር ተሻግሮ አንድ ሰዉ ይዞ እንደሚመጣ እድሉን ሰጣቸው ሰጣን ግን አኔ ቀድሜ ካል ሄድኩ ሞቼ አገኛለሁ አለ አምልክም ፈቀደለትና ለሰጣን የመጀመሪያ ዕድልን ሰጠው ሰጣኑም ቀጭን ክሩ ላይ ተሸግሮ ወደ ሌለኛው የረጋ ሰው ቁቤ ተራራ እንዳለፈ የተሻገረበትን ቀጭኑን ክር ቆረጠው መልዕክቱም ማዶ እንደቆመ ቀር አምላክም እንድህ አለው ማቼም ብሆን ሰጣን ማንነቱን መቀየር አይችልም ለዛም ነው ወደ መንግስቴ ሰማያት ወደ ሆነው ወደ ቤቱ መመለስ የማይቻለው የመሐን እንባ አንድ ቤቴሰብ እጅግ ያማሬ ኑሮ ይኖራሉ የመንደሩ ኗዋሪዎች በእኔስ የተደላደለ ኑሮ ይቀኑ ነበር አኗኗሯቸውም እጅግ የምያስገርም ነበር ሰዎች የሌሎችን ህይወት አይተው የምቀኑት አይናቸው ማየት እስከቻለ ድረስ ብቻ ነው አይናቼው ያየውን በመሻታቸው ውስጥ የእኔነት ስሜት ስያይል ህይወት የኑሮ ሀይል ስታጣ መሻት ትሆንባቼዋለች ሰዎቹ ግን አንድ ችግር ነበረባቸው ልጅ መውለድ አይችሉም ነበር የዘውትር ጸሎታቸውም ልጅ ፍለጋ ላይ ያዘወትራል አንድ መንገደኛ ቤታቸው መጣና እንድያሳድሩት ጠየቃቸው እኔሱም መልካም ሰዎች ስለነበሩ እግሩን አጥቦ አሳደሩት መንገደኛውም ጥዋት የረጋ ሰው ቁቤ ቤታቸው ያሳደሩትን ቤቴሰብ አመስግኖ ወጣና መንገዱን ስጀምር የሰፈሩ ሰዎች እንግዳውን ከቦት ስለቤቴሰቦችሁ ያማረ አኗኗር እንድነግራችሁ ለመኑት መንገደኛውም እውነት እውነት እላቹሃለሁ እንደዚህ አይኔት አዘንተኛ ቤቴሰብ አይቸ አላውቅም ፍሬያቸው በውስጣቸው የሞቴ የነገህን የብርሃን ጮራ መታቀፍ የማይችሉ ናቸውና እንባቸው እጅግ የበረታና የአምላክን ዙሃን ያጠበም ባሮችናቸው በማግኘታቸው ዙፋን ላይ የማጣትን ካባ የደረቡ ናቸውና አትቅኑባቸው ይልቅ እዘኑላቸው እናንተ ያቀፋችሁትን የሳማችሁትን መዓዳችሁ ላይ አብራችሁ የተሻማችሁትን እኔሱ ለማግኘት አልታደሉምና እቅፋቸው ንፋስ ከማቀፍ ውጭ ሌላ ነፍስ ያጣ የነገህ ምርኩዝ ያጡ የዛሬ ቀን ባለፀጋ ናቸው እኔሱ እናንተ በደጃችሁ ላይ ባሰማራችሁት ግለገሎች ስቀኑ እናንተ ግን በእኔሱ የጌጥ ቀናቸው ትቀናላችሁ ሁሌም ፍሬያቸውን በማየት በፍለጋ የተጠመዱ ስደተኞች ናቸው በእናንተ መካከል ያለረፈ ቤት እንጅ በውስጣቸው ያረፈ ልቦናና የተረጋጋ መንፈስ የሳቸውም የረጋ ሰው ቁቤ በህይወታቸው ውስጥ አምላካቸውን በፍሬያቸው መካከል ይፈልጋሉ የማግኘት ተስፋቸው ቀን በነጎደ ጊዜ ትመነምናለች እናንተ ስማችሁ የጠገባችሁትን እኔሱ ለማቀፍ ይመኛሉ ስለበዛባችሁ ስታማሩ እኔሱ ስለተነፈጉ ያመሰግናሉ በምስጋናቸውም ውስጥ ያለች እንባ ያልተፈታ የፍሬያቸው ምስጢርነች በእናንተ አይን ውብ ሆነው የታዩት በአምላክ አይን ማጣት ያመነመናቸው የነብጤ ናቸው በምናልባት ተስፋ ህይወትን የምገፉ ሀብታቸውም ወራሽ ያጠ ወፍዘራሽ ነው የፍሬ ፀጋ በውስጣቸው የለለ ስጋ ለባሽ መናኛ ህይወታቸው ምዕራፍ ያጣ የተበተነ ገለባ ነው አይናቸውን በአይናቸው ማየት ያልቻሉ ፍሬያቸው የተሰወረባቸው የእፎይታ ወንበር ያጡ በጨለማ መካከል እንቅፋት የበዛቸው በተስፋ ማጣት የምቧዚኑ መሸሸጊያ ያጡ ባርያ ናቸውና በጎጆዋችሁ ውስጥ አስጠልሏቸው ለመሳም ፈልጎ የደረቀው ከናፍሮቻቸውን ደቂቃችሁን ሰዳችሁ እንድስሟቸው ፍቀዱ ልጅ ማቀፍ የናፈቀው እቅፍ ምናልባት የነገን የማግኘት ተስፋን በማህፀኗ ውስጥ ያለመልም ይሆናል ሁሉ ተርፏቸው አይናቸውን ያጡ ባይተዋር ናቸው የሚባርክ የሚሰጥ አብሳርው መላዕክት ደጃፋቸውን አልረግጥ ያላቸው በመዘጋጀት እድሜያቸውን የረጋ ሰው ቁቤ የፈጁ በደጃፋቸው የምዋትረውን ብላቴና ለማየት መንገድ የምጠብቁ ናፍቆት ያሳሳቸው የስስት ልጆች ያጡ ናቸው የዘር ሀረጋቸው ማስቀጠል ያልቻሉ የሞት ቤቴሰብ ናቸውና ፀልዩላቸው አንድ ቀን በመጠበቅ ፋንታ ማግኘት የገባቼው ቀን ከሁሉም በላይ ለምስጋና የምታበራ ነፍስ ይኖራቸው ይሆናል አለና መንገደኛው መንገዱን ቀጠለ መንገደኛው ከከተማው የመውጫ ባር ላይ ደርሶ ወደ ኋላ ዞሮ ስያይ አንድት ነጭ እርግብ ወደ ቤቴሰቦቹ ቤት አቅጣጫ ስትበር ተመለከተ ቤቴሰቡም ከአመት ቦኋላ ወንድ ልጅ አገኙ በእንባቸው መካከል የተወለደው በጀንበራቸው መጥለቅያ ጊዜ ያገኙት ማርፍያ ብርሃናቸው ሆነ ከፍሬያችሁ መካከል የምወለዱት ሁሌቱ አንድ የመሆን ምስጢር ነውና የረጋ ሰው ቁቤ በለጋስ እጆች ልብ ሀሴት ያረጋል ህይወት የከበደችሁ አንድ ዳቦ መግዛት ያልቻሉ ላይ ሳይሆን መቶ ዳቦ መግዛት እየቻሉ አንድት ዳቦ መመፅወት ያልቻሉት ላይ ነው ተፈጥሮ በፀጋ መካከል አኑራ በጥም ያጠፋቻቸው ነፍስ ናቸውና በተራቡት ላይ የመታገስን ፅዋ ያበዛችሁ ሌላ የምሻገሩት የብርሃን በር በህይወት ውስጥ አቅፋ ስለያዘችላቸው ነው ዳቦ ከያዙ ንፉግ ሀብታም ይልቅ አፈር የዘገነች የደቂቅ እጅ የተባረከችነች የመስጠታችን መቅኔ ባሌን ላይ ሳይሆን በተረዳነውና በአዛኝ ልባችን ውስጥ ያለፀጋ ነው ሁሉን የያዘችሁ ህይወት በአንድ ትልቅ የመስጠት ስንሰለት ብታጣምሬን አለም ምነኛ ወብ ትሆነ ነበር ንፉጎች ብቻ ከዛ ሰንሰለት ለመውጣት ስሉ የዓለምንና የህይወትን ውብ ገፅታ አጠፉት የተራቤው ወንድምህን ስታዘው የህይወትን የባሪያ ዕጣፋንታ ሰጠሄው ባልበላ አንጀቷ እህትህን ስታስገድድ የህይወትን ስሜት አልባ መንገድ አሳየሃት ንፉጋም እጆች እየቀሙ ብኖሩም ምንም ሳይዙ ይህችን ዓለም ተሰናብቶ ይሄዳሉ የረጋ ሰው ቁቤ አንድ ንፉግ ሀብታም ብዙ ሀብትና ንብረት ስያከማች ከርሞ አንድ ጥዋት ላይ ባሪያው ይሞትበታል የሞተውን ባርያ እንድቀብሩት ለሎለዎቹና ለቀሩት ባሪያዎቹ ነግሮ ሰብስቧቸው ይዞ ወደ ማሳው ወርዶ ስቃኝ ውሎ ወደ ቤቱ እየገባ ሳሌ ከፈረሱ ላይ ወድቆ ይሞታል የባሪያውና የሀብታሙ ነፍስ ወደ አምላክ ፊት ቀረቡ የባሪያ ነፍስ ይበልጥ ስታበራ የንፉግ ሀብታም ነፍስ ይበልጥ ትደበዝዛለች ንፉጉ ሀብታምም የራሱን ነፍስ ስመለከት በንዴት አምላከ ይህ የእኔ ባሪያ ነበር የእኔ የምሰጠውን ቁራጭ ዳቦ እየበላ ነው የምኖረው እኔ እሱንና እሱን መሰሎች ብዙ የራብ ጊዜያቸውን አስታግሸያለሁ እኔ ብዙ ወርቅና የምያበሩ ዳይመንዶችም ነበሩኝ ወደ እዚህ እየመጣን ይህ ባሪያ ዘርፎኝ ይሆናል እንጅ እንዴዚህ የምያበራስ ነፍስ እሱ በምድር ሳሌስ አልነበረውም የእኔ ነፍስ ከሁሉም ባሪዎቼና ሎሌዎች ጥርቅም በላይ በምድር ሳለን ታበራ ነበረች አሁን ታድያ እንዴት እሱ ከእኔ በላይ ልያበራቻለ ብሎ አምላኩን ጠየቀ አምላክም እንደህ አለው ሁሉም ባሮችህ ለአንተ በምድር ለምያበራው ነፍስ ስሉ የራሳቸውን ክብሪ አንተ ከንፉግ የረጋ ሰው ቁቤ ስሜት የተረፈውን አንድት ዳቦ ስለምትሰጣቸው ስያበሩልህ ኖረዋል በምድር ላከማቼው ሳይሆን በምድር ለቤቴነ ነፍስ ቤቴ በክብር ብርሃን ትቀበላለች በምድር በጥማት ብዛት የተሰነጣጠቀን መሬት ማርካት አፈሩ ከድቶት የጎረጎዴን መሙላት የቤቴ የቅን ልቦች ስራ ነው ባሮችህ በአንተ ትዕዛዝ ሳይሰላችሁ አገልጎሎታቸውን ስያበረክቱልህ ኖሯል ማገልገል መንቀሳቀስ ነው የተንቀሳቀሰ ነፍስ ውስጥ የአምላክ ህይወት አለበት አምላክ በሰው ህይወት ውስጥ የምነቀሳቀስ ነፍስ እንጅ በማዘዝ ብቻ የምኖር አለቃ አይደለም ባሮቼም በማገልገል ስንቃቸውን ስያከማችሁ ኖረዋል ከስንቃቸውም መካከል ራስ የምሆነው በምድር ሳሌ ባሪያክ የሆነው ነፍስ ላይ አሁን የምታየው ብርሃን ነው አለው ለሁሉም ተፈጥሮ በመኖር መካከል የያዘችሁን በረከት አንዱ ንጉስ ስሆንባት የሌሎቹ እጣፋንታ ባሪነት ነው ንፉግነት ያመጣው ስልጣነ መሳይ የነገን ቀን የመፍራት ስሜት ነው በዛሬ ሌሊት በበረከት ያደረች ነፍስ የዘላለም ህልም ታልማለች በንፉግነት ያመሽች ግን ሌሊቱን በጥማት ስትቃጠል ታነጋለች በዛሬና ነገ መካከል ያለው ቀን ልዩነት የለውም በባሌቤቱ ነፍስ ውስጥ የረጋ ሰው ቁቤ ያለው መሻት ግን ቀኖቹን ይቀያራል ደህኔትን ማንም አይፈልገውም ደህኔትን መፊራት ግን ህማም ነው የጥበብ እይታ ከችግር ውስጥ ያለን የእረፍት መንገድ ታሳያለች ከመጣ ቦኋላ አብሮ ተስማምቶ መኖር ደግሞ ከመፈለግ የዘለለ ጥበብ ነው ማጣት ያሰቡትን ስሜት አላማሟላት እንጅ ሌላ ምንድ ነው አጥቶ ከምያዝኑና አግኝቶ ከምጠሙ ነፍሶች በላይ ማጣቱን በምስጋና ያበሰረ እሱ የህይወትን መንገድ ያገኛል ህይወት ያለምስጋና መድረሻም ይሆን መጣፈጫ የላትም ምስጋና ህያው ህይወት ውስጥ ያለ ስንቅ ነው የምፈልገውን ያጣ ደሃ ነው አግኝቶ የተጠማ ግን ረሃብተኛ ነው ማጣታችሁና ማግኘታችሁ በሀሳባችሁ ውስጥ ያስቀመጣችሁት እንቁ ነው ሌላ ምንም ልሆን አይችልም በሃሳብ ያለ እንቁ ያጡት ጊዜ ካገኙት አንድት ዳቦ በታች የረከሰ ከንቱ ነው የንጉስን ደጃፍ የምለማመጡት የነብጤ የንጉስን በረከት እስክበሉ ነው ህይወት የመኖርን ጥያቄ እስከምትጠይቅ ድረስ ሰው ማጣቱን ያስባል ህይወት ሁሌም እየጠየቀች ስለምትኖሩ ማግኘቱን ብያልሙት ይሻላል በአንድት የህይወት ጥያቄ ውስጥ እራሳቸውን የምቀያይሩ ብዙ የህይወት ጥያቄዎች አሉና የረጋ ሰው ቁቤ ከልባችሁ መካከል በማለዳ የምወጣው በረከት የቀኑ የፀሓይ ብስራት ነው ከህይወታችሁ ውስጥ ያለውም በረከት በእናንተ ውስጥ ያለና ከእናንተ ውስጥ የምወጣ ምንጭ ነው እሱን ተከተሉት ቀኖቹ የራሳቸውን የፀጋ መንገድ የያዙ ናቸው ቀናችሁ የመነሻችሁ ጅረት ነው ሀይላችሁንና አቅማችሁን ይዛችሁ በህይወት ሰልፍ ላይ ፍሰሱ የቀኖቻችሁ ጥርቅም ሳምንትና ወራት ተረፎም አመታትን ያስቆጥራሉ የደቅቃችሁ ሽርፊራፊ የሰውን ልጅ የመኖርን ጥበብ ይዛለች አንድ እብድ ነው ተብሎ መንደሩ የተፈረጀ ሰው ቀኑን ሙሉ ሳያቋርጥ በመሳቅ ያሳልፋል የመንደሬውም ሰው ሁሌ ጊዜውን በማያቋርጥ ሳቅ ስለምያሳልፍ እብድ በማለት ከማህበረሰቡ አግልሉታል አንድ ለመንደሩ እንግዳ የሆነ ሰው ለብቻ ተገሎ የምስቀውን ሰው ይመለከትና ለምን እንደዚህ በደስታ እንደምስቅ ይጠይቀዋል ሰውየውም እየሳቀ እንድህ አለው ለአንድት ደቂቃ ሳቄን ባቋርጥ እንግዳ የሆነ ስሜት ይገባል ሰዎች የምያቁት ህይወትን በመተንፈስ ብቻ ማስቀጠል እንደምችሉ ነው የረጋ ሰው ቁቤ ነፍስ ያለው ህይወት ግን በሳቅ ተሞልቶ ለዘላለም በሀሴት ይቀጥላል አለው ማጣታችሁን የህይወታችሁ ፍፃሜ አታድርጉት የስሜታችሁም መከፋት በውስጣችሁ አታኑሩ ህይወት ባህር ላይ እንዳለች መረከብ ነች ጥርት ብሎ በተንጣለለውም ባህር ላይ ትንሸራሸራለች በሀይለኛ ወጀብ ባህሩ ላይ በተነሳ ጊዜም አትቆምም ትጓዛለች መጓዛችሁ እውነት ውስጣችሁ እስካለች ድረስ አይቆምም መለማመድ ያለባችሁ ነገር በችግር ውስጥ እንድምትኖሩ እንጅ ችግር ውስጣችሁ እንዳለ አይደለም ሰው ስለሆናችሁ የተፈጥሮ አካል ስለሆናችሁ ብቻ ችግር ውስጥ ትኖራላችሁ እንጅ የተለየ ችግር እናንተ ውስጥ ልኖር አይችልም ችግር ወደ እናንተ ስመጣ አትደንግጡ ሰው መሆን ራሱ ለችግር መዘጋጀት ነው ተፈጥሮ ሁሉን ይዛ ተፈጥራለች ከፊታችን የኖሩባት አያት ቅድሜ አያታችን ተፈጥሮ አዛብተዋሉ እኛ ደግሞ ዛሬ ይበልጥ እያዛባን እንገኛለን ስለዚህ ችግር ስገጥማችሁ ከችግር በላይ ከፊብላችሁ ስለመብትሄ ማሰብ የተሻለ ጥበብ ነው የረጋ ሰው ቁቤ ህይወት በድሎት ብቻ የምታኖረን ገፅ የላትም በችግርና በመከራ ውስጥ እንደምታኖረን ጭምር በተለያየ መንገድ ታሳየናለች ጥቅት ችግሮች ብዙ የመፍትሄ ሀሳቦችን ታመጣለች አዳድስ ፈጠራዎች በችግር ምክንያት የተፈጠሩ ብሆኑም ዛሬ ግን የሰው ልጅ የስንፍና ምልክት እየሆኑ መተዋል ፈጠራዎቹ ችግሮቻችን ብቀሪፉልንም ስንፍናችንንም እንዳዘው ይጨምራሉ ሰው በህይወት ውስጥ ስንቀሳቀስ ብዙ የተፈጥሮ ሚስጥሮችን ይረዳል በእንቅስቃሴ ውስጥ ያለውም ህይወቱም ጥንካሬን ይላበሳል አንድ ሱቅ ሂዶ እቃ ስገዛ የነበረው ሰው ቤቱ ድረስ ስሜጣለት ሰዓቱን ልቆጥብ ይችላል ግን ተቀምጦ እቃዎቹን ማስመጣቱ ግን ህይወቱን ከእንቅስቃሴ ይገድበዋል አንድ ሰው የፈለገውን እቃ ቤቱ ድረስ እንድመጣለት በዛሬው ዘመን ማዘዝ ይችላል እንደዚህ አይኔት ስራዎች ለአካላታ ጎዶሎ ሰዎች እጅግ ተመራጭ ነው ጤናማ የሆነን ሰው ግን ከእንቅስቃሴ ይገድባል ስንፍናንም ይጨምራል በሽታዎች የምበረቱት ከእንቅስቃሴ እራሳቸውን ገድቦ መቀመጥ በምያበዙት ሰዎች ላይ ነው ዛሬ በአለም ዙርያ ከዚህ የተነሳ የረጋ ሰው ቁቤ አብዛኛው በሽተኞችን እስፖርት እንድሰሩ በህክምና ባላሙያዎች ይመከራሉ የቤታችሁን በር ላለመዝጋት ስሉ እንኳን ሪሞት ያስገጥሙበታል እኔዚህ ፈጠራዎች ሰውን ከእንቅስቃሴ ገድቦታል አንድቦታ መቀመጡም ድብሪት ፈጥሮበታል ህይወት ሁሌም በእንቅስቃሴ ውስጥ ያለችነች ሬሳ ብቻ አንድ ቦታ ያለድብሪት መቀመጥ ይችላል ህይወት የለውም በድን ነው ዛሬ ደግሞ ሰው ህይወት እያለው በስንፍናው ምክንያት በድን ሆኖ ቤት ውስጥ ተጎልቶ ተቀምጧል መንቀሳቀሳችን አዳድስ የታደሱ አየሮችን ወደ ውስጣችን የምናስገባና የምናስወጣበት መንገድ ነው የተቀመጠ ነገር ይረሳል አንድ ቦታ ተቀምጣችሁ እራሳችሁ ረስታቹሃል ተነስታችሁ ተንቀሳቀሱ እራሳችሁን አድሱ አንድ አንድ የሰውነት ክፍላችሁ እንቅስቃሴ ከማጣታቸው ብዛት ስራቸውን ረስተዋል አዳዲስ ቀን በውስጣችሁ የምፈጠሩት እናንተ የዛሬያችሁን ቀን አዲስ ብስራት ስታሰሙ ነው አንድት ቦታ መጎለታችሁ ሀሳባችሁ ወደ አላስፈላግ ቦታ ከመውሰድ ሌላ ምንም ጥቅም የለውም የረጋ ሰው ቁቤ ህያው እንደሆናችሁ በህይወት ሰልፍ ውስጥ እንደምትንቀሳቀሱ አስቡ ወደ ራሳችሁ ግቡና ለምን እና እንዴት እንዴምትኖሩ አስቡ ህይወት ለሁሉም እኩልነች የሰው ልጅ መከፋፈል ነው አንዱን ከፍና ዝቅ ያደረገው ከማርጀታችሁ ከመውደቃችሁ በፊት ሀሳባችሁ ወድቋል ጭንቅላታችሁ የሃሳባችሁ ማዕከል ነው ስታረጁ መጀመርያ ከወገባችሁ በላይ ያለው ጭንቅላታችሁ ያጎነብሳል ብዙ አዛውንት ያረጀ ሰው ማየት ትችላላችሁ አንደዛውም ዛፍ ስቆረጥ መጀመረያ የዛፉ ቅርንጫፍ ነው መሬት የምነካው ከመውደቃችሁ በፊት ሀሳባችሁ ወድቋል ሀሳባችሁ ቀና ስታደርጉ እናንተ እራሳችሁ ቀና ትላላችሁ እያደጋችሁ ያላችሁ ችግኝ ናችሁ ጫፋችሁ ስረገጥ እድገት ወደ ላይ ትታችሁ ወደ ስር አዙራችሁ ነው ጫፋችሁን ወደ ላይ አንሱና አቃኑ ህይወትን በማግኘት ሳይሆን በሞራል ስሆን ነው የምኖረው ሁሌት ልጆች መንገድ ላይ ስደባደቡ አገኘዋቸውና አገላግየ ለምን እንደምደባደቡ ጠየኳቸው የረጋ ሰው ቁቤ አንደኛው በጣም በጋለ ስሜት የደሃ ልጅ ብሎ ሰደበኝ አለኝ ልጁ እንባ ተናንቆታል ያለው ብቸኛው አማራጭ መደብደብ ብቻ ነው ምክንያቱም ደህነቱ አይደለም ልጁን ለድብድብ ያበቃው ደህኔቱም ፀሐይ የሞቀ ሀገር ያወቀ ጉዳይ ነው በሞራሉ መምጣቱ ልጁን ለፀብ ጋብዞታል ሰው ከያዘው ነገር ይልቅ በሞራል ነው የምኖረው ሁሌት እንቁላል ብቻ ለመሸጥ ገብያ የወጣችሁ እናቴ የምገዛት ሰው ባለ ብዙ መክና ነው ልብ በሉ በሞራል ነው ሁሌቱን እንቁላል ሽጣ ሽሮ ገስታ ወደ ቤት የምትመለሰው ምክንያቱም ሁሌቱ እንቁላል ለሰባቱ ልጆቿ እንደማይበቃ ታውቃለች እውነት እላችሃለሁ የብዙዎች ህይወት በሞራል ስለተኖረ ነው የዛሬዋን ቀን የምንኖራት የተወራረስ ነው ሌላ ነገር ምንም የለንም ሞራል ብቻ ተወራረሰናል ሰው በተረዳው መንገድ እንጅ ባለው ነገር ብቻ መኖር አይችልም መረዳት የህይወት የመጀመሪያ ክፍል ነው አንድት ዳቦ ለሰባት ሰው ብታካፊል ልዳረስ ይችላል ግን ሰዎቹ ጠግቦ አይበሉትም የደሃ እናት ማጀት የተረዳው ይህንን ነው ማዳረስን ስድስቱ ልጆቼ በልተዋሉ አንዱ ልጄ ይቅሪበት አትልም ምክንያቱም የረጋ ሰው ቁቤ የአንጀት ምዛን ለሁሉም እኩልን ነው ሁሉንም ይጠይቃል መልስም ይፈልጋል በህይወት ውስጥ ስቴት ያለ ነው አንደ መሳሳት የነገሮች ጅማሬ ነው ሁሌተኛ እሱኑኑ መልሶ መድገም ግን ያለምንቃት ስተት ያለማስተዋል ችግር ነው አንድ ያልተማረ ህፃን ሁሌም የታላቅ ወንድሙን መፃሐፍ ስከፍትና ስዕሎቹን ስመለከት መፅሐፉን ገልብጦ ነበር ታላቅ ወንድሙ ሁሌም ይህንን መፅሀፍ ስትከፍት አስተካክለ ግለጥ አትገልብጠው በማለት ይመክረው ነበር ይህ ብላቴና ግን አንድም ቀን መፅሐፉን ስከፊት ለማስተካከል ሞክሮ አያውቅም ብላቴናውም ትምህርት ቤት ገብቶ መፅሀፍ ስከፍት ገልብጦ ከፈተው የመጀመሪያ የመምህሯ ስራ ልጁን መገፀፅ ነበር ብሆንም ግን ልጁ በቀጣይ አሁንም መፅሐፉን እንደዛው መልሶ ከፈተው መምሁሯም ተበሳጭታ ልጁን ገረፈችሁ ወላጅም እንድጠራ አዘዘችሁ አባቱም ትምህርት ቤት ሂዶ የልጁን ችግር ተረድቶ ወደ ቤት ገባ ልጁም የምነገረውን ስህተት ተቀብሎ ያለምነቃት ያለማድረግ ችግር እንዳለበት ስረዳ ከሰል የረጋ ሰው ቁቤ አቀታጥሎ ልጁን አስከቻለ ድረስ እጁን ከሰሉ ላይ እንድያስቀምጥ አሰገደደው ልጁም እጁን ከሰሉ ላይ ትንሽ እናዳስቀመጠ አቃጠለውና እጁን በፍጥነት ከእሳቱ ላይ አነሳ አባትየውም ለምንድ ነው እሄ አንሳ ሳልልህ እጅህን ያነሳሄው አለው በቁጣ አባዬ አቃጠለኝ ስህቴት እየሰራክ ነው እጄ ብቃጠል አስ አለው በተደጋጋም የተሳሳታችሁት ነገር ከስህቴት አልፎ ልማድ ይሆንባቹሃል ቶሎ ብላችሁ ከስሀተታችሁ መንቃት ካልቻላችሁ ለልማድ ትጋለጣላችሁ ከስህቴታችሁ በብርሃን ፊጥነት ነው መንቃት የምጠበቀው በመጀመሪያ ጊዜ አንድት ስጋራ ማጨስ ስህቴት ልመስል ይችላል መጀመሪያ ያንን ድርግት ለፈፀመ አዕምሮ ስህቴት ነው ሁሌትና ሶስት ጊዜ ከደገማችሁ ግን ሱስ ይሆንና አዕምሯችሁም ስህቴትነቱን ይረሳል የመጀመሪያ ድርግት ደውል ነው እናንተ ንቅታችሁ ደውሉን እስካል ሰማችሁ ድረስ የደውሉን ጭወት ትለምዱትና ከቁብ መቁጠርን ታቆማላችሁ ለመጀመሪያ ጊዜ የወቀሳችሁ አዕምሮ ለሁለተኛ ጊዜ ስትደግሙት ልማድ አድርጎ ይቀበላል የረጋ ሰው ቁቤ ሰው መግደል ከሀሳብ የወረደ ልማድ የሆነባቸው ሰዎች አሉ መስረቅ ለአመታት ስጠላ የነበረ ብሆንም ስደረግ ግን ሱስ የሆነ በሽታ ነው ሌብነት ሀሳባችሁ ውስጥ ያለ እንጅ ልባችሁ ውስጥ ያለ ስሜት አይደለም አንድ ሌባ እየሰረቀ ለብኔቱን ለራሱ የማይናገረውና በሰዎችም ዘንድ ሌባ መባልን የማይፈልገው ልቡ ውስጥ ያለው የእውነቱ ነፃብራቅ ሌብነት ስላል ሆነ ነው የእውነታችሁ ነፃብራቅ ልባችሁ ውስጥ ነው ያለው ሌብነት ግን ከአዕምሯችሁ ውስጥ የፈለቀ አሉታዊ ሀሳብ ነው ሌብነት ስሜት አይደለም ሀሳብ ነው ሀሳብ ስተገበር ሰውየውን ሌባ ልያስብል ይችላል ምክንያቱም ማሰብ የአንድ ሰው ሀሳብ ነው መስረቅ ግን አደባባይ ላይ የወጣ የሰውየው የተወገዘ ድርግት ነው አንድ ታምራት የምባል ሰውየ ነበር የመንግስት ድርጅት ውስጥ ነው የምሰራው ይህ ሰውየ አማኝ ብሆን በጣም በሙስና ሀገር ምድሩን ያስቸገረ ሰው ነው ከሴኞ እስከ አርብ ባሉ ቀናት ውስጥ ሙስና ብበላም እሁድ ስደርስ ግን ወደ ቤቴክርስትያን ይሄዳል ይህ ሰው ሙሴኛ ነው ሙስና ግን ሃሳቡ ውስጥ የተቀመጠ አሉታዊ ሃሳብ ነበር እሁድ ወደ ቤቴመቅደስ መሄድን ምን አመጣው ልብ በሉ የአምላክ ፍቅር በልባችን ነው የረጋ ሰው ቁቤ የምያርፈው በልባችን ውስጥ የምኖር የእውነት ነፃብራቅ ነው ሰውየውንም እሁድ ስደርስ የምያስገድደው ይህው እውነት ነው ሙሰኝነት ሃሳብ ስሆን ፍቅር ስሜት ነው ይህ ሰውየ ቅዱስ ልሆን አይችልም እርኩስ ነው ረክሷል የረከሰው ግን የሙሰኝነት ሃሳቡ ነው ሃሳባችሁ ስያርክሳችሁ ልባችሁ ያነፃቹሃል ሀሳባችሁ ቆሻሻ ነው ልባችሁ ውስጥ ያለው ፍቅር ሳሙና ነው ሁሌም ያጠራቹሃል ሀሳባችሁ ውስጥ ያለውን ብታጡ ምንም ነው ሌላ ሀሳብ ስመጣ በእሱ ይተካል አንድ ሌባን ሌብኔቱን ተው ብትሉት ምንም አያሳስበውም መተው ይችላል ምክንያቱም ሌብነት ሀሳብ ነው ከሰውየው የምጠበቀው ሀሳቡን ብቻ መርሳት ነው አንድን አፍቃሪ ግን የሚታፈቅራትን ልጅ እርሳት ተዋት ማለት ከባድ ነው ምክንያቱም ማፍቀር ሀሳብ አይደለም ስሜት ነው በቀላሉ በመተው ይከብዳል ምናልባት እሷን ለመረሳት እስከዛሬ ያፈቀራትን ጊዜ ድጋም ለመርሳት ልወስድበት ይችላል የልባችሁን መጣት ይከብዳል ስሜቱ ህሜም ነው ከዚህ ህሜም ለመዳን የተሻለ ስሜትና ጊዜ ያስፈለገዋል ያፈቀረን ሰው ለመፈወስ ከጊዜ የተሻለ መዳኒት የለውም የረጋ ሰው ቁቤ የልባችሁን ስታጡ ህይወት የጨለመች ይመስላቹሃል ለሰፍው ሰማይ ፀሐይ የጋራ ብርሃን ስትለግስ ለእየግላችን ልባችን ፀሐይ ነች ለዛ ነው አፍቅሮ ያልተሳካላትን ሰው ሁለንተናው በቀናቶች መካከል የጨለመ የምመስለው በስሜቱ ቦታ ሀሳቦች ስለምተኩ ለረጅም ጊዜ ብቻቸውን ተቀምቶ ማሰብን ይመርጣለ ያጊዜ በጣም ከባድ ጊዜ ነው ምክንያቱም በልባችሁ የምታስቀምጡት የእውነትን ነፃብራቅ ነው የምወዱትን ሰው ለመርሳት ያፈቀሩበትን ሁሌትና ሶስት አሊያም እድሜ ልክ ጊዜ ልወስድባቼው ይችላል እውነት ጥሏችሁ እንድህ ሄድ አትፈቅዱም ሌብኔት ውሸት ስለሆነ በመሄዱ ትደሰታላችሁ እንጅ አታዝኑም መጥፎ ሀሳቦች አዕምሮን ተገን አድርጎ ስኖሩ እውነተኛ ስሜቶች ልብን ማደረያ አድርጎ ይኖራሉ እሌት በእሌት ከልባችሁ እየፈለቃችሁ ትኖራላችሁ ስለዚህም ሁሌም አድስ ናችሁ በአድስ የህይወት ጀንበር ሌላ አድስ ታርክ ለመስራት ማልዳችሁ ትነሳላችሁ ለዛማናት የተሸከማችሁት ታርክ የእናንተ ሀይል ጠፍሮ ከመያዝ ይልቅ ምንም አይጠቅማችሁም እሌት በእሌት ከልባችሁ ተወለዱ አዕምሯችሁን እናንተ አሰናዱት ሀሳቦቹን እናንተ ከልባችሁ መሻት አመንጭታችሁ አቃብሉት አዕምሮን ከፈቀዳቹሌት የልባችሁን ምዛን የረጋ ሰው ቁቤ ያዛባል አይን የተመለከተው ነገር መጀመሪያ ለአዕምሮ ይደረሳል በአይን በኩል የምደረሳችሁ ሁሉም ነገር የህይወታችሁን ሚዛን የምጠብቅ አይደለም በአይናችሁ የተመለከታችሁ ውበት ግን ቀጥጣ ወደ ልብ ይወርዳል ውቤት ሃሳብ አይደለም ስሜት ነው የህይወታችሁ ሚዛን በልባችሁ መካከል የኖረላችሁ ስትፈጠሩ ጀምሮ ነው ምናልባት ረስታችሁት ልሆን ይችላል በልባችን ውስጥ ያለው ሚዛን በፍቅር ዙፋን የምፈረድ ነው በፍቅር የተፈረደ ሰው ጠላት የለውም ምክንያቱም ፍቅር ሁለንተናን የያዘ የተፈጥሮ ግብ ነው ሀሳቦቻችሁ የምወለዱት የፍቅርን ሟዛን ለማዛባት ነው የምታፈቅሩበትን ለማሰብ ስለሚታባክኑ ለፍቅርና ለይቅሪታ የምሆን ጊዜ ይሻማቹሃል የመጀመሪያ ፍቅራችሁን አስቡት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር የያዘው ሰው ሁሉንም ጊዜውን ፍቅርን በማሰብ የምያፈቅራት ልጅ በማሰብ እሷ ላይ በመመሰጥ ብያጠፋ ደስ ይለዋል በደቅቃ ውስጥ በአንድ ርዕስ በተለያየ መንገድ የምያፈቅራትን ልጅ ያስባል ሀሳቦቹ በፍቅር ላይ ብመሰረትም በቅስበታት ውስጥ ደስታና ሀዘንን በስሜቱ ያስተናግዳል እሷን ይበልጥ ባሰበ ቁጥር ፍቅሯ ይጨምራል ምክንያቱም የምታስቡትን የምትሆኑት የረጋ ሰው ቁቤ በደጋገማችሁ ጊዜ ነው አዕምሮና ልብ አንድ ላይ የምሰሩት በፍቅር ጊዜ ነው ስታፈቅሩ አዕምሮ ማሰብ ስጀምር ከልብ መሻት ጋር ይናበባል በዛች ቅስበት ልብና አዕምሮ ያለምንም ቅድሜ ሁኔታ ይጣመራሉ የምታፈቅሩትን ሰው በአይን ስታዩት በቅስበት ሁሌት ነገር ይከሰታል አዕምሯችሁ ማየታችሁን ከእይታ እውነት መሆኑን ስቀበል ልባችሁ ወዲያው የደስታ አሊያም የፍራቻ ስሜት ይፈጥራል ይህን ስሜት በህይወቱ ውስጥ የያዘ ሰው ሪህራሄንና ይቅርታን ይላበሳል ፍቅር የይቅራታና የርህራሄ መንገድ ነው አብዝታችሁ በፈቀራችሁ ጊዜ ለስህቴት ትጋረጣላችሁ ባጠፋችሁም ጊዜ ይቅር ትላላችሁ ለበደላችሁትም ትራራላችሁ በፍቅር ውስጥም ብሆን ስህቴት አለ ስህቴቱም የፍቅር አካል ነው አንድ ፍቅረኛሞች ሁሌም ምግብ ተመግቦ ልጨርሱ አንድ ጉርሻ ስቀር የሴት ጓደኛውን አንድ ድርግት አስለምዷት ነበር ይህም ድርግት አንድት የቀረችሁ ጉርሻ ማሳረግያ ትባላለች የመጨረሻዋን መሳረግያ በማለት የምወዳትን ልጅ በማጉረስ መአዱን ያነሳሉ በተደጋጋም ይህን ነገር አድርጎ ካስለመዳት ቦኋላ አንድ ቀን ይህንን ድርግት ሳይፈፅም መአዱን ያነሳሌ ይህን ጊዜ ልጅቷ ትበሳጭና የረጋ ሰው ቁቤ ታኮራፋለች ይቅርታ ጠይቆ የህይወቱ ትልቁ ስህቴት እንደሆነም ነገራት እውነት በፍቅር ውስጥ ስህቴት ፍቅራችሁን የምታጠናክሩበት እንጅ ፍቅራችሁን የምታቋርጡበት ችግር ልሆን አይገባም በስሀቴታችሁ ውስጥ ፍቅራችሁ ልኖር ይገባል ከመሳሳታችሁ በስተጀርባ ያለው ይቅርታ የፍቅራችሁ ሞሶሶ ነው የርህራሄያችሁም ስሜት የመዋደዳችሁ ትሩፋት ነው አንድ ሚሜስቱን በጣም የምወዳት ሰው ሚስቱ የካንሰር ታማም ስለነበረች ሁሌም ከስራ መልስ መዳአኒት ገስቶ ይመጣ ነበር ጥዋት የምትውጠውን መዳአኒት አስተካክሉ በባሩ ወደ መስሪያ ቤት ይሄዳል ይህን ድርግቱን ለዘጠኝ አመት ሳይሰላች ካደረገ ቦኋላ አንድ ቀን ባቡር ተበላሽቶ ቤት ለመድረስ ሌላ ባቡር መጠበቅ ነበረበት ሌላ በተበላሸው ባቡር ቦታ የተቀየር ባቡር ዘግይቶ ስለነበር የደረሰው እሱ የተቀየረውን ባቡር ለመጠብቅ ትዕግስቱ አልነበረውም ስለዚህ በእግሩም መንገዱን ይጀምራል አንድ ሣአት ከሩብ በእግር ከተጓዘ ቦኋላ ቤት ስደረስ ባሌቤቱ ወረቀት በያዘችቤት ወንበር ላይ ተደፍታ ወድቃ አገኛት የረጋ ሰው ቁቤ በድንጋጤ ወረቀቱን ተቀብሎ ስመለከት እንድህ ይላል በህይወት ውስጥ ያለኝን ሰልፍ አቋርጫለሁ ሁሌም በሰልፉ መካከል ስትጓዝ አጠገብህ እንዳለሁ እአስበኝ ምክንያቱም ለአመታት ካስቸገርኩህ በላይ ይህ አይከብድምና ለአንድ አፍታ ዓለም በአንድነት ብተሳሰብ ፍቅር ይነግስ ነበር የሁሉም ሰው ስሜትና ፍላጎት ለአንድ አፍታም አንድ ላይ አይመጣም ሰው በአይን ብቻ ስለምተያይ ልዩነቱን ያስባል አንድ ቻይናዊና አሜርካዊ ልዩነት የላቸውም ኢንግለዛዊና ኢትዮጵያዊም ብሆን እንደዛው ድንበርና የተለያየ ቋንቋ ስለተናገራችሁ ብቻ ልዩነታችሁን አጉልታችሁ አትመለከቱ ሰው መሆን ብቻ አንድ አድርጎናል ሁሉም ነገር የራሱ ስብስብ አለው ሰው የምለው አንድ ላይ ሰብስቦናል ከተለያዩ ሀገራት የምፈልቁ ወንዞች እንኳን ስብስብ አላቼው ሸለቆ መፍሰሻቸው ስሆን መሰብሰብያቸው ቀይ ባህር አሊያም ውቅያኖስ ይሆናል ከሙሲልም ሀገር የምፈስ ወንዝ ከክርስቲያን ሀገር ከምፈስ ወንዝ ጋር ስገናኝ በፍቅር ይደባለቃሉ መገናኘታቸው ውሃ መሆናቸው ብቻ ከሁሉም ነገር ይልቃል ከመደባለቃቸው ቦኋላ ያለው ህይወትስ ለራሳቸውም ለሰው የረጋ ሰው ቁቤ ልጅም ፍፁም ልዩነት የለውም ናይል እና ኤፍራጠስ ብደባለቁ የትኛው ናይል የትኛው ኤፍራጠስ መሆኑ ለመለየት ይከብዳል መደባለቅ ሀይል ስሆናቸው ያገኙትን ጠራርጎ ይዞ ይሄዳሉ ልዩነቱ የተጓዙበት ሸለቆ ወይም መንገድ እንጅ የውሃው አይደለም የትኛውም ሀገር ላይ አንድ ሀይማኖትና አንድ ብሄር ብቻ ልኖር አይችልም ሀይማኖትና ብሔር የቡድን ነው ሀገር የጋራችንነች የተለያየ የቡድን ስብስብ ነው ሀገር ማለት እምነት ብቻ ነው የግል አንድ አማኝነኝ ባይ ይህንን ነገር ነው መረዳት ያልቻለው ፅንፈኛ ሀይማኖተኞች የመለያየታችንን ውበት ማጥፈት ይፈልጋሉ አንድ ቄስ ነበር የእሱ ልጅ ግን የእሱ እምነት ተከታይ መሆን ስላልፈለገ ሌላ ሀይማኖት ተከታይ ሆነ በዚህም ድርግት መዕምናኑ ቄሱ ላይ ተነሱ አንተ የእኛ ሀይማኖት መርና ተከታይ ሁኔ ልጅህ እንዴት ሌላ ሀይማኖት ተከታይ ይሆናል ይህ የአንተ ድመክት ነው ልጅህ የእኛ ሀይማኖት ተከታይ መሆን ነበረበት አሉት የረጋ ሰው ቁቤ ቄሱም አንድ ጥያቄ ጠየቃቸው ኢየሱስ በምድር ስመላለስ በነበረበት ጊዜ ማንን ነው በጉልበት አስገድዶ የእሱ ተከታይ ያደረገው። ማንም ልመልስ አልቻለም ሁሉም ዝም ብሎ ተበተነ ፍቅሩ እስካል ማርካችሁ ድረስ እሱን ልትከተሉ አትችሉም እምነት በግዴታ ውዴታ የምትቀበሉት ነገር አይደለም ፍቅር ብቻ ነው መስፈርቱ ማንስ ነው በጉልበት ተገዶ ሰው የምያፈቅሬው ፍቅር በነፃነት ውስጥ ያለ መልካም ስሜት ነው ሁሉም የአምላክ የእጁ ጥበብ እስከሆነ ድረስ የአንተን ሀይማኖት ብቻ ስለተከተለ ለይተ መውደድ አትችልም እሱን ለመውደድ ሰው መሆኑ ብቻ በቅ ነው ኢየሱስ ሁሉንም ይወድ ነበር የተከተሉትን ብቻ አላፈቀረም የትኛውም ፍጥረት አምላክ የተጠበበበት ጥበብ ነው ልዩነተታችን ውበት እንጅ የምንጠፋፋበት የምንገለማመጥበት ሀገር አያስፈጥረንም ለመውደዳችሁ ገደብና ደረጃ አታበጁ የምትወደው ብሔር ተወሳጅ ስለሆነ ከሆነ ለይተህ የምታፈቅረው ልብ ላይ ጫና እየፈጠርክ ነው ማለት ልባችሁ የምሰራውና የህይወታችሁን ፍሴት በሰላም የምመራው ጫና እስካል የረጋ ሰው ቁቤ ፈጠራችሁበት ነው ይህን ውዴድ ይህንን አትወዴድ የምትሉ ከሆነ ግን ውዝግብ ውስጥ ይገባል ለዛ ነው ብዙ ሰዎች በዘረኝነት ፍቅር ተለክፎ ውሳኔ ላይ የምዋዥቁት ምክንያቱም የምትወዱት በምክንያት ለይታችሁ ከሆነ መውደዳችሀ ልብ ላይ ያልደረሰ በሃሳብና በልብ መካከል ተንጠልጥሎ የቀረነው ዘረኛ የሆነ ሰው አቋዋም የለውም ምክንያቱም ዘረኛ ስትሆን ከሰው ልጅ አንድ ደረጃ ታንሳለህ ከህይወት ሁሌንተና አንድ ፅንፍ ብቻ ይዘህ ለመኖር ስለምሞክሩ የህይወታቸው ፍፃሜ እጅግ አሳዛኝ ይሆናል ለምሳሌ ሂትሌርን መውሰድ ትችላላችሁ ለአመታት የጀርመንን የበላይነት ለማስፋፋት ስጥር የኖር ብሆንም ለራሱ ርህራሄ ከማጣቱ የተነሳ እራሱን አጠፋ ዘረኛ የምሆን ሰው ፍቅር የለውም ዘረኛ የሆነ ሰው ፍቅሩ በደመና ውስጥ ነው የምኖረው ትንሽዬ ፀሐይ በወጣ ጊዜ ይጠፋል የዘረኞች ፍቅር ነፃነት ልሰጣችሁ አይችልም ምክንያቱም እራሱ ጥገኛ ነው የፍቅር ማማ ላይ መውጣት አይቻለውም በነጎረች ላይ በምክንያታዊነት የምኖር ጥገኛ ነው በአንድ ዕንፍ ላይ የተገደበ ነው ፍቅር ልትገድቡት የማትችሉት ሃያል ነው ሩዋንዳ የረጋ ሰው ቁቤ ውስጥ በጎሳ ተከፋፍሎ እርስበርስ ስጋደሉ ከሁሌቱ ጎሳ በፍቅር የተጣመሩ ፍቅረኛሞች ነበሩ እናትና አባታቸው እየተጋደሉ እኔሱ ግን ፍቅራቸውን ማቆም አልቻሉም ለዛ ነው ፍቅር ሁለንተና ነው የምለው ምንም ነገር ልያቆመው አይችልም ኢየሱስን ለማቆም ሞክሮ ነበሩ ግን አልቻሉም ምክንያቱም የሰው ልጅ በፍቅር ውስጥ ይኖራል እንጅ ልቆጣጠረው አይችልም አሳዎች በባህር ውስጥ ይኖራሉ ግን ባህሩን መቆጣጠር አይችለም በባህሩ ላይ ምንም የበላይነት የላቸውም ባህሩ ግን ለአሳ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የባህሩ አካላትም ሁለንተና ነው የፍቅር ከፍታ ላይ መውጣት የምትችሉት ነጻ ስትሆኑ ነው ነፃነት ከምንምና ከአሉታዊ በላይ የሆነ ነገር ነው ርህራሄና ይቅርታ የፍጡራን ነፍስ የተሸከመ የፍቅር አካል ናቸው ዘረኛ ስትሆኑ ፍቅርን ከውስጣችሁ ታጠፋላችሁ ምክንያቱም አንድ ሰው ሁሌቱንም ልሆኑ አይችልም የብዙ ዘረኞችና አንበገነን መሪዎች ፍፃሜ አሳዛኝ ነው ለአመታት ያለፍቅር ስለኖሩ የህዝባቸው እንባና መከራ አይታያቸውም ፍቅር ስኖራችሁ ብቻ ርህራሄን ትላበሳላችሁ አንባገነን መሪዎች ወንበር መልቀቅ የማይፈልጉት ለዚህ ነው ለአመታት አዕምሯቸውን ብቻ የረጋ ሰው ቁቤ ስጠቀሙ ኖሮዋል አእምሮ ለትዛዝና ለፍርድ እንጅ ምንም አይጠቅምም የራሳቸውን አንድት ስሜት ብቻ ይዞ ይኖራሉ እሱም ሁሌም የበላይ አካል መሆን ሁሉንም ነገር በሃይል መግዛት ሀይለኛነኝ በምል ህይወት ውስጥ ትህትና የለም ፍቅር ትሁት በሆነ ልብ ላይ ይበዛል ህይወት ልብንም ትፈልጋለች ፍቅር እርስበርስ ያስተሳሰረን ስውር የአዛነታ መንገድ ነው አንድ ሰው በወጣ በገባ ቁጥር ሚስቱንና ልጆቹን ያሸብራል ይገርፋል አንባገነን በሆነ አመራር ቤቱን ይመራል ሚሜስቱና ልጆቹ የእሱን ባህሪ ለምዶውታል ሁሌም መደብደብና መገረፍ ለሚስቱና ለልጆቹ የእሌት ተሌት ተግባር ነው ሰውየ እጅግ ታሞ አልጋ ላይ ይወድቃል መንቀሳቀስም ሆነ ከአልጋ መውረድ አልቻለም ይህን ጊዜ ሚስቱ ስትገረፍበት የነበረችሁን አለንጋ አምጥታ ከእኔ ልጆቿ ፊትለፊቱ ቁማ ምናልባት እኛን ከገረፍ ትድን ይሆናል ብላ ተማፀነችሁ ባሏ ግን ምንም ነገር መመለስ አልቻለም በድንጋጠ ከአልጋው ወድቆ ሞቴ ምክንያቱም ለአመታት ለቤቴሰቡ ስያበረክት የኖረው ይህን ብቻ ነበር ሚስቱና ልጆቹ ግን የአሱን መዳን በፍቅር ይጠባበቁ ነበር ለዛም ነው ታሞ የረጋ ሰው ቁቤ እንኳን ሳለ እራሳቸውን ዝቅ አድርጎ እንድገረፋቸው የሰጡት በፍቅርና በፍቅር እርስ በእርስ ተከባብራችሁ ኑሩ እውነት አላችሃለሁ ከፍቅር የበለጠ መዳኒት በሰው ህይወት ውስጥ የለም ፍቅር ያለና የምኖር ነው ከመምጣታቹ በፊት ነበር ከመጣቹ ቦኋላም አለ ከሞታቹሁም ቦኋላ ይኖራል ከሁሉም ታላላቆቹ የሞቱት ለፍቅር ነው የረጋ ሰው ቁቤ በፀጥታ ውስጥ ፍቅር ይጎላል ቀን በጫጫታ የተሞላ ነው ውሎዋችሁ በጫጫታ ስሞላ አዕምሯችሁ ስራ ላይ ይውሳል በጫጫታ ውስጥ አዕምሮ ብቻ ነው ተጠቃም ምክንያቱም አዕምሮ ጫጫታ ሁከታን ይፈልጋል በሁከታ ውስጥ ነው አዕምሮ ሰዎችን የምወስደው ወይንም ከራሳችሁ የምያሸሸው አዕምሮያችን እረፍት ስለማንሰጠው እረጋታን ጸጥታን አያውቅም እረፍታ አልባ ሩጫ የአዕምሮ ባህር ሆኗል ልባችን ደግሞ የአዕምሯችን ተገላብጦሽ ነው ልባችን ማታ በፀጥታ ውስጥ ነው ስራ የምጀምረው ልባችሁ ቀን ላይ ደም ከማሰራጨት በስተቀር ሌላ ፋይዳ የለውም የምታፈቅሩትን ሰው ከቀን ይልቅ ማታ ላይ ነው ይበልጥ የምታስቡት የምትፈልጉት ልባችሁ ማታ ላይ ነው ይበልጥ የምያፈቅረው ብዙ ዘፋኞች ማታ ላይ ፍቅር እንደምበረታባቸው ዘፍነዋል ማታ ምንተከስቶ ነው ፍቅር የበረታው ብላችሁ እራሳችሁን ጠይቃችሁ ታውቃላችሁ። ሰውየው አዎ አንድት ሴት ታሸንፍኛለች እሷም ሚስተነች ምንም ብናገር ሁሉንም ቃላቶቼን በዝምታዋ ውስጥ ትረሳዋለች አለ ዝምታችሁ ውስጥ መርሳት አለ ጸጥታ ሌላውን ዓለም መረሳት ነው ከራሳችሁ ጋር በፀጥታ ውስጥ ስተሆኑ ሌላውን አለም ትረሳላችሁ ምክንያቱም እራሳችሁንና ሌላውን አለም አንድ ላይ ማኖር አትችሉም ፀጥታ ወደ የረጋ ሰው ቁቤ ራሳችሁ መአከል የምወስዳችሁ መንገድ ነው በዝምታችሁ ውስጥ ያለው ሰላም ነው ልብ በሉ ተናጋሪው ሰውየ የተሸነፈው በሚስቱ ዝምታ ነው ለዛም ነው ልያገባት የቻለው እንደዛ ካልሆነማ እሷ ተናጋሪ ብትሆን ሁለቱም ያለመግባባት ደረጃ ላይ ይደረሱ ነበር አንድ በጣም ብዙ ሰቶች አግብቶ የፈታ ሰው ነበር ሴቶችን ባገባ ወራት ለፍቺ ፍርድ ቤት ይቀርባል ለፊቺ የምያቀርበው ምክንያት ሁሉም ሰቶች በጣም ጭቅጭቅ ይወዳሉ የምል ነበር ይህ ተልካሻ ምክንያት ለፊቺ ያበቃው ነበር እውነታው ግን ሴቶቹ ሳይሆኑ እሹ ነበር ጭቅጭቅ የምወደው ይድረጊት በጣም ስላሰለቼ ሌላ ሴት ላለማግባት ወስኖ ነበር ይህ ውሳኔው ግን ለብዙ ጊዜያት መቆየት አልቻለም ከሁለት አመታት ቦኋላ ሌላ ሴት ተዋውቆ ለትዳር በቃ ከሴቷ ጋርም ለብዙ አመታት በጋብቻ ውስጥ በሰላም መኖር ቻለ በዚህ የተገረመው ጓደኛው እንዴት ከዚህችኛዋ ጋር በሰላም ለመኖር እንደቻለ ሚስጥሩን ብትነግረኝ ብሎ ጠየቀው ምንም ምስጢር የለውም እውነታው እኔ እሳት ሁፔ ስሄድ እሷ ውሃ የመሆኗ ጉዳይ ብቻ ነው ቃላቶቼን ዋጋ የረጋ ሰው ቁቤ የምታሳጣቼው በፀጥታ ነው አንድ ዛፍ ላይ የተቀመጠችን ወፍ በጭወት አልያም የምትወረውሪባት ድንጋይ ካላስደነገጣት እራስህ ትገረማለህ መርጋት ከፍሪሃት በላይ መሆን ነው እገለዋለው የምትለው ሰው መልሶ ካቀፈህ እራስ ትሞታታለህ ሚስቴ በዝምታዋ ውስጥ የእኔን ከንቱ ቃላት በራሴ ውስጥ እንድገድል አደረገችኝ አለው ዝምታችሁ ከራሳችሁ ጋር ያላችሁትን ግንኙት የምታጠናክሩበት መንገድ ላይ አልፋችሁ በአከባቢያችሁም ጋር የምትዋሃዱበት ነው የምታፈቅሩትን ሰው ማሰብ ማሰላሰል በፀጥታ በኩል ትውውቅና ቀረበታን መፍጠር ነው በፀጥታችሁ ውስጥ የምከሰተውን ፍቅር አጥብቃችሁ ያዙት እሱነው ወደ ትክክለኛ ማንነታችሁ የምወስዳችሁ የአዕምሮ ሰላም የምሰጣችሁ በልባችሁ መካከል ያለው ሰላም የሠፈነበት ፀጥታ ነው በአዕምሮ ጭንቀት የተጠቃን ሰው ሳይካትሪስቶች የምያደረጉት ነገር ብኖር ፀጥታ የሰፈነበት ቦታ ላይ ለረጅም ሰዓት እንድቀመት ማዘዝ ወይም ማድረግ ነው ፀጥታና የአዕምሮ መረበሽን ምን አገናኘው ልትሉ የረጋ ሰው ቁቤ ትችላላችሁ እውነታው ግን ከአዕምሯችሁ መውጣት የምትችሉት ብቸኛው አማራጭ ፀጥታ ውስጥ በመግባት ነው ፀጥታ ከአዕምሯችሁ የምትወጡበት መንገድ ነው ከአዕምሯችሁ ወጣችሁ ማለት ወደ ልባችሁ ወረዳችሁ ማለት ነው አንድ ጊዜ አንድ ቤት በጉንዳን ተወረሬ ጉንዳን ወደ ቤታቸው ስገባ ሰዎችን ይጨንቃል እናም ያንን ጉንዳን ከቤታቼው ለማበረር ስሉ የጉንዳኑን መሰመር ይጠርጋሉ አልያም አመድ ይደፉበታል ጉንዳኑ አንደ ከመስመሩ ከወጣ ግን ቤት ውስጥ ይበተናል እናም ያጉንዳን ለረጅም ቀናት ከቤት ውስጥ ላይወጣ ይችላል ረዝራጁም ቢሆን ቤት ውስጥ ይቀራል አንድ አባት ግን ጉንዳን ወደ ቤታቼው ስገባ አመድ አይደፉም አይጠርጉምም ይልቅ ጉንዳኑን መንገድ ያሳዩት ነበር ከቤታቼው እንድወጣ መንገድ ያሳዩታል ልክ ጉንዳን በመስመር ወደ ቤታቼው ስገባ አባት ደግሞ የመውጫ መንገድ ያሳዩታል ሳይካትሪስቶችም እንደዛ ነው የምያደረጉት ጉንዳኑ በአዕምሯችሁ ውስጥ ተበትኗል አሁን እኔሱ ማድረግ ያለባቼው ነገር እናንተን ከአዕምሮ ማስወጣት ነው ያለውም አማራጭ ለብቻ የረጋ ሰው ቁቤ በፀጥታ ውስጥ መሆንን ነው በጸጥታ ከአዕምሯችሁ ስትወጡ ልባችሁ ማበብ ይጀምራል ልባችሁ በፀጥታ ውስጥ ነው ማበብ የምጀምረው ችግሩ አለም አዕምሮ ላይ ብቻ መስራቷ ልብ ያለውን ሰው መፍጠር አለመቻሉ ነው የሰው አዕምሮ አያብብም ግፋ ብል ያስባል ደስታችሁ ሰላማችሁ ያለው ልባችሁ ውስጥ ነው አዕምሮ የሁከት መንደር ነው አዕምሯችሁን ሁሌም ብሆን መሸሸ አለባችሁ አዕምሮ አንደማሰብ ከጀመሬ ሚዛናዊነትን አይጠብቅም ልባችሁ ነው ሚዛናዊነትን የምጠብቀው ልባችሁ የህይወት ስር ስሆን አዕምሯችሁ ጫፍ ነው ስራችሁን ስታንከባክቡ ብቻ ነው ጫፋችሁ የምፈካው ፈገግታችሁ በፊታችሁ በኩል ብታይም መነሻው ስሩ ግን ልባችሁ ነው ከአዕምሮ ምንም አይነት ደስታ ልመጣ አይችልም ብነሳም ጥቅት አዎንታዊ ብዙ አሉታዊ ሃሳብ ነው ከልባችሁ ነው መላ አካላችሁን የምያጥለቀልቀው ስሜት የምነሳው አሁን የባህሩን መነሻ ሳይሆን ጫፉን ነው አለም ይዛ ያለችሁ ኢየሱስ ግን መነሻውን ያዙ ስል ነበር ፍቅር መነሻ ነው ጫፍ አይደለም እናም መነሻውን ተንከባከቡት ጫፉ ራሱ ያብባል የረጋ ሰው ቁቤ ዘር ሀይማኖት ጎሳ ወዘተ ጫፍ ናቼው እኔ ግን እላችሃለሁ ከሁሉም መነሻ ምንጩ ይበልጣል ባህሩ ከደረቀ ጫፉ የለም ጫፉን ብቻ ማለምለም ስለምፈልጉ ነው አለም እንደዚህ ስቃይ የበዛባት መነሻውን ማንም አይፈልግም የትምፍጭው ዱቄቱን አምጭው አይደል ተረቱ ከዱቄቱ ይልቅ የምፈጨው እህል መነሻው ያስፈልጋል በረግጥ አድካም ነው መነሻውን መፈለግም ሆነ ማወቅ ብሆንም ግን ከማንም መጫወቻነት ያስጥላል ከራስ እስርቤትም ነፃ ያወጣል ማንም አለምን የምያውቃት ከተቀላቀለበት ጊዜ አንስቶ ነው ከዛ በፊት የነበረው ታርክ ነው ታርክ የሰማችሁት እንጅ የኖራችሁትን አይሆንም የሰው ልጅ ግን ከታርክ ጋርም ትግል ገጥሞ ይኖራል እንደኛ ሀገር ያሉ ህዝቦች ከታርክ ጋራ ያላቸው ቁረኝት በጣም በቀላል የምታይ አይደለም ስለእውነት ከሆነ ዛሬ ለምንኖሩት ህይወት ይልቅ ላለፈው ለገዛ አያት ቅድመ አያታችሁ ታርክ ይበልጥ ትጨነቃላችሁ የምገርመው አያታችን ኑሮውን ኑሮ ነበር የሞተው እኛ ግን የእሱን ታርክ ለመስቀል ስንል ታርክ አልባ ትውልድ ሁኔን እንቀራለን ታርክ ሌላምንም ነገር ማለት አይደለም የሆነ ዘመን የተደረገ ድርግት እንጅ የረጋ ሰው ቁቤ ጥፍራችሁ ስያድግ ትቆረጣላችሁ ከዛ ከቆረጣችሁ ቦኋላ ግን ጥፍሩን አትፈልጉትም ግን ማንኛውም ሰው ረጅም ጥፍር እንደነበረው ያውቃል የትኛውም ሰው ጥፍሩ ትንሸም ብትሆን ተቆርጦ ነበር ዋናው ነገር ጥፍሩ እንደነበረ መገንዘቡ እንጅ ቆርጦ ጥሎት ላለፈው ጥፍር መሞት አይደለም ጥፍሩ ከእናንተ ከተለየ ጊዜ በድን ነው ምክንያቱም ጥፍራችሁ መብቀሉን አያቆምም እናንቴም መቁረጡን አታቆሙም ታርክም እንደዛ ነው ትንሽም ትሆናለች እንጅ ሁሉም ታርክ አለው ዋናው ነገር ግን ባላችሁበት ቅስበት ታርክን መረዳት እንጅ ከታርክ ጋር መሟገት አልያም ለታርክ መኖር አይጠቅምም ለታርክ ከመኖር አለመዋለድ ይሻላል ምክንያቱም የራሳችሁን ታርክ የላችሁምና ውብ ታርክ እንዳለው የምያወራው ሳይሆን በተሰማራበት መስክ ላይ ውብ ታርክ የምያፅፍ ትውልድ መፍጠር ነው ከበድን ጋር ትግል ገትማችሁ ለምን ትኖራላችሁ ለምንስ የሞቴ ሰው መንፈስ በታርክ መልክ መቶ ያስጨንቃችሃል የዛሬ መቶ ሁሌት መቶ ከዛን በላይ ዓመት በፊት የተደረገ ታርክ የዛሬን ትውልድ ለምን ያስጨንቃል ለምን ለታርክ ባሪያ ትሆናላችሁ እናንተ አሁን ብቻ የምትኖሩ ህያው ናችሁ ከአሁን ውጭ ያለው የረጋ ሰው ቁቤ ቅስበት ወደ ፊት ምናልባት ነው እናንተስ ካላችሁበት ዘመን ውጭ ሌላ በምድር ላይ ተመልሳችሁ የምትኖሩበት ዘመን አላችሁ። ቀዳሚው ጥያቄ ይህ ነው የማይረቡ ሃሳቦችን በማፍለቅ አዕምሮ የሰውን ልጅ ያጠወልጋል አልያም ይገላል በአዕመሮ ምክንያት ካሉት ፈጥረታት ሁሉ የሰው ልጅ ብቻ ነው የምጎዳው እንስሳት አራዊት በአእመሮ ምክንያት ጉዳት ስደረስባቼው አይታዩም ምክንያቱም አያስቡም የሰው ልጅ የጎዳው ማሰቡ አይደለም ምን እንደምያስብና ማቼና የትቦታ ላይ የረጋ ሰው ቁቤ አዕምሮውን መጠቀም እንዳለበት ለይቶ አለማወቁ ነው በልቡ ምክንያት አንድም የተጎዳ ሰው የለም ማነው አፍቅሮ የተጎዳ መጎዳት የምለውስ ቃል እውነት የፍቅር ባህሪ ነው መጎዳትና መጉዳት የአዕምሮ ስራ ነው ልባችሁ ማፍቀር እስከቻለ ድረስ ብታፈቅሩ እንኳን ህይወት ውብ ትሆናለች አፍቃሪ ሰዎች ምድር ውብ ስያደረጉ ጨካኝ ሰዎች ውቧን አበባ ይቀጥፋሉ ሁሌት ሰዎችን ወደ አበባ ማሳ ብትወስዱ የተለያዬ ሁኔታ ውስጥ ይሆናሉ አንድኛው አበባውን በተመስጦ ስመለከት ሁሌተኛው አበባውን ቀጥፎ ለመውሰድ ይፈልጋል አፍቃሪ ሰዎች በአባበው ሁለንተና ስማረኩ እራስ ወዳድ የሆኑ ሰዎች አባበውን የግላቼው ማድረግ ይፈልጋሉ ማፍቀር ያለገደብ ስሆን ህይወት በሀሴት ትሞላለች ለማግኘት ብቻ የምታፈቅሩ ከሆን ፍቅራችሁ ገደብ ይኖረዋል ፍቅራችሁ እኔነት ላይ የተመሰረተ ይሆናል የምታፈቅሩትን ሰው ላለማግኘት ማፍቀር አለባችሁ ያኔ ነው ፍቅር ፊሴቱ ሳይቋረጥ የምፈሰው ፍቅርና ውሃ አንድናቼው ውሃ ከመሬት ስር ስፈልቅ ያለምንም ቅድሜ ሁኔታ ነው ማንም ይቅዳው ማንም ይጠቀምበት አሊያም ማንም አይቅዳው ማንም የረጋ ሰው ቁቤ አይጠቀምበትም ውሃው ከመሬት እንብርት ውስጥ ወደ ምድር መፍሴሱን አያቆምም ፍቅርም እንደዛ ነው መሆንም ያለበት ገደብ ልኖረው አይገባም መፍሴስ ብቻ ነው ባህሪው አፍቃሪያችሁን አገኛችሁ አላገኛችሁ መፍሰሱን ማቆም የለባችሁም ለማግኘት ብቻ የምታፈቅሩ ከሆነ ፍቅር ጥቅም ይሆናል ፍቅር ጥቅም አይደለም ጥቅም በቦታና በሁኔታ የተገደበ ነው ፍቅር ዘላለም ህያው ነው ፍቅርን ለራሳችሁ ነው ማኖር ያለባችሁ ለምታፈቅሩት ሰው መሆን የለበትም አንድ ባልና ሚስት ቁጭ ብሎ ስያወጉ ባል ውዴ እኔ ለአንች ስል ነው የምኖረው አለት እሷም ዝም ስትል ባልየው ምነው ውዴ አንችስ ለእኔ አትኖሪም ብሎ ጠየቃት ሚሰትየው ብልህ ነበረች ለአንተ አልኖርም ለራሴ ነው የምኖረው አለችሁ ባልየው ይህንን ስሰማ ተበሳጨ ምክንያቱም እሷም ለእሱ እንድትኖር ፈልጎ ነበር እውነታው ግን ከእሱ መልስ ይልቅ የእሷ መልስ ነበር ትክክል ውሃ ከመሬት እንብርት ስር ብፈልቅም ለእናንተ ብሎ አይደለም ለራሱ ብሎ ነው እናንተ እያገለገለ እንዳለ እንኳን ውሃ የረጋ ሰው ቁቤ አያቅም ውሃው የምፈሰው ለራሱ ስል ነው ፍቅርም እናንተ እስካላችሁ ነው የምፈልቀው ግዴታ የባልየው ፍቅር እንድያገኝ ሚስትየው ፍቅርን ለራሷ ማኖር ነበረባት እንደዛ ካልሆነ ባልዩ ፍቅርን ከሚስቱ ማግኘት አይችልም እናም ሚስትየውን የምያቆየው ከራሷ የምፈልቀው ፍቅር ነው ወደ ራሳችሁ ተመለሱ ወደ ልባችሁ ግቡ እራሳችሁን የምታገኙት ልባችሁ ውስጥ ነው አዕምሯችሁ እናንተ ማኖር አይችልም የዱር አራዊቶች ተሰብስቦ በፍቅር የምኖሩት አዕምሮ ስላላቸውና ስለምያስቡ አይደለም ልብ ስላላቼው ነው ፍቅር ስላኖሩ ነው ዛሬ ምድር በስቃይ በተሞላችበት ጊዜ ዝንጀሮዎች በፍቅር ተሰብስቦ እየኖሩ ነው ስቃይ የምመነጨው ከገዛ አዕምሯችሁ ውስጥ ነው እናም ዝንጀሮዎች ማሰብ ብችሉ ኖሮ ከሰው ልጅ የከፋ ስቃይ ይበዛባቸው ነበር ግን እውነታው ከሰው ልጅ ይልቅ ልባቼውን ስለምጠቀሙ በአንድነት ለመኖር በቅቷል የሰው ልጅ እውነታው ያለው ልቡ ውስጥ ነው የአዕምሮን ጥያቄ ሁሉንም መልሳችሁ አትችሉትም አዕምሮ አንድ ጥያቄ ጠይቆ መልስ ፍለጋ ስትወጡ ሌላ ዘጠና ዘጠኝ ጥያቄ አዘጋጅቶ ይጠብቃቹሃል ስለዚህ የረጋ ሰው ቁቤ አዕምሯችሁን እርሱት ወደ ልባችሁ ግቡና ልባችሁን አስታውሱ የትኛውም ትምህርት አዕምሮን ማስታወስ ነው ጭብጡ ሰዎች ለገዘ አዕምሯቸው ባሪያናቼው የትኛውም ተፅእኖ የምጀምረው ከአዕምሮ ነው የአፍርካ ትውልድ ዛሬ የተገዛው በአካል አይደለም በአዕምሮ ነው አባቱ ቅድሜ አያቶቹ ናቼው በአካል የተገዙት አሁን በአዕምሮ ነው ባሪያ የሆኑት ይህ ከሁሉም ይከፋል ነፃነታችሁ ያለው በአዕምሯችሁና በልባችሁ መካከል ባለው ሰላም ነው ሰላም የሁለቱን ሚዛን የምጠበቅ ነው የረጋ ሰው ያለው በሁለቱ መካከል ባለው ሰላም ውስጥ ነው አንዱ የአንዱ የበላይ ከሆነ ህይወት ባሪያ ታደርጋቹነለች እኔ ግን እላችሃለሁ ልባችሁን አስታውሱ አዕምሮ አያኖሪም ስቃይ ያበዛል ልባችሁ ነው በሰላም የምያኖረው ፍቅራችሁን በፀጥጣችሁ ውስጥ ፈልጉ አዕምሯችሁን አሳሪፉና ልባችሁን እንድሰራ ፍቀዱለት ልባችሁን ለዘመናት ኮንናቹሃል ፍቅር በምድር ላይ የለም ጠፋ ትላላችሁ ፍቅር አለ አልጠፋም አዕምሯችሁን ብቻ ስለምትጠቀሙ ፍቅርን ማኖር የረጋ ሰው ቁቤ አልቻላችሁም አዕምሮን ያለ እረፍት መጠቀም ልብን ያቀጭጫል አንድ ሴት ልጅ አባዬ ሰዎች እንዴት ያብዳሉ ስትል አባቷ ጠየቀች አባቷም ሁሌት ክሎ ብርቱካን ገስቶ ቤት እስክት ደሪስ ድረስ በግራ እጄ ብቻ እንድትሸከም አደረጓት ልጂቱም ትንሸ እንደተራመደች ግራ እጀ ዛለባትና ወደ ቀኝ እጂጁ ብርቱካኑን ማዘዋወር ፈለገች አባትዮ ግን ውል ነውና ወደ ቀኝ እጄ እንዳትቀይር አሰጠነቀቋዋት ትንሽ እንደተራመደች ፈስታሉን ለቀቀችሁ አባቷም ለምን ለቀሽው አሏት እሷም ከበደኛ እጄ ዛሌ ብላ መለሰች አባትዬውም እስከዛሬ ድረስ እኮ እራስሽን በአዕምሮሽን ውስጥ ብቻ ተሸክመሽ ትኖር ነበር እሱ ታዲያ ለምን አልከበደሽም አሏት የሰዎች እብደት ለዘመናት አንድን ችግር በአዕምሯቸው ውስጥ ተሸክሞ መዞር ነው አዕምሯችሁ መሸከም የረጋ ሰው ቁቤ ስያቅተው ልጅቷ ፈስታሉን እንደለቀቀችሁ ከቁጥጥር በላይ ይሆንና እራሱን ይለቃል ሁሉንም ነገር በአዕምሮ መቆጣጠር ስለምትሞክሩት አዕምሮ ከራሱ በላይ ስሆን ያለእናንተ ፍቃድ አራሱን ይለቃል እብዴት ከአቅም በላይ የአዕምሮ መዛል ውጤት ነው ለዘመናትም በአዕምሯ ውስጥ ብቻ ነበር እራሳችሁን ስትሸከሙ የነበረው ቀኝ እጅም ሆነ ልብ እንዳላችሁ ረስታቹሃል በአዕምሯቸው ውስጥ ብቻ የምኖሩ ሰዎች ፍቅር እንዳለ አያቁም አያምኑምም ምክንያቱም ተሳስተው ከአዕምሯቸው ስወጡ ልክ ህፃን ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በባዶ እግሯ መሬት እንደረገጠች ይሆናሉ ከአዕምሯቸው ወቶ ወደ ልባቸው ስገቡ ቶሎ ብሎ ወደ አዕምሯቸው ለመመለስ ጥሬት ያደረጋሉ ህፃናትም ለመጀመሪያ ጊዜ በባዶ እግራቸው መሬት ስረግጡ ቶሎ ብሎ ከመሬት ላይ እግራቸውን ያነሳሉ መሬት እንደ እናት ማህፀን ምቹ አይደለችም ትቆረቁራለች ከአዕምሮ ወደ ልብ ግን ተገላብጦሽ ነው ወደ ልባችሁ ስትገቡም ከእሳት ከውጥሬት ወደ እረፍት መግባት ያስደነግጣል ያለመዳችሁት ነገር ነው የማታቁት ምቾት ያስደነግጣቹሃል በጥሪጣረ ይሞላሉ ምክንያቱም አለም እረፍት እንደነሳቻቼው በአንደ ማሰብ የረጋ ሰው ቁቤ የማይሆን ነገር ነው አዕምሮ መጠራጠር ስለሆነ ቶሎ አያምኑም አለም ለማንም ምቹ አይደለችም ከዛ ይበልጥ የምጎዳው ግን ለራስ ምቹ አለመሆን ነው ለገዛ ራሳችሁ ምቹ ህይወት አለመፍጠር ነው ከራሳችሁ ጋር አለመሆን ነው አዕምሮ በራሳችሁ ላይ የሃሳብ ናዳ ካዘነበ ጭንቀት ከፈጠረባችሁ ታዲያ ለእናንተ ሰላም የሚሰጥ ማነው። ራዕያችሁ አለፍ አይደለም ዘላለማዊ ነው የአማኞች ራዕይ መንግስተ ሰማየት ለመውረስ ነው እናም አሁን የቆሙባት ቅስበት ወደ መንግስተ ሰማየት የምትወስድ መንገድ ነች ግን መንገዱን ስቀላቀሉ አይታዩም ይልቅ ስወጡ ነው የምታዩት ምክንያቱም ልባችሁ እንጅ አዕፅምሯችሁ ዘላለማዊ እንደሆነ አያምንም ሰው የገዛ የአዕምሮው ባሪያ ነው ዘመናዊ ትምህርት ሰዎች ከልባቼው ወደ አዕምሯቸው እንድሰደዱ ስያደረግ ከዘላለማዊነት ወደ ጊዜያዊነት እንደሸሹ አደረጋቼው እኔ አብርሃም ከጭንቅላት ይለቅ ልባቸውን ነው የተጠቀሙት እናም ሰውን ሁሉ በአንድነት ለማስተናገድ በቁ ልባችሁ ውስጥ ነው የሰው ልጅ አንድነት ያለው አለም ወደ ጭንቅላት ብቻ የምያደላ ትምህርት መስጠት ከጀመረች ወዲህ አለም እየተጠበበች መጣች ሀገራት እየተካፈሉ መጡ እዚህ የረጋ ሰው ቁቤ ጎሮበታችን ሱዳን ለሁለት ተካፍላ ሁሌት ሰመንና ደቡብ ሆኑ ኤርትራና ኢትዮጵያ የተካፈሉት ጭንቅላት ብቻ የሚያደልብ ትምህርት በተማሩ ሰዎች ነው አዕምሮ አንድነትን አያውቅም መከፋፈል ነው ስራው ዘላለማዊነት ያለው ልብ ውስጥ ነው ራዕይ በአዕምሮ ስታሰብ ጥሩ ነው ይበልጥ ወደ ልብ አንድነት ስወርድ ዘላለማዊነት ይኖረዋል የዛሬ አማኞች ከልብ ወደ አዕምሮ ሸሸተዋል አዕምሮ ያስባል ድርግት ግን የልብ ግፊት ይጠይቃል አንድ ሰው እንደተራበ ታስባላችሁ ለዛ ሰው የምትመጸውቱት ግን በልባችሁ ግፍት ነው ስሜቱ ይበልጥ ስሰማችሁ ትመፀውታላችሁ አዛነታ ሰባዊነት የጠፋው ሰዎች ከልባቼው ወደ አዕምሯቸው ስለተሰደዱ ነው አዕምሮ ውስጥ ሃሳብ እንጅ ድርጊት የለም የሁሉም ወንዞች መሰብሰብያ ባህር ነው ልባችሁ ነው ባህር ሰዎች ስመሽ የምሰበሰቡት ወደ ጎጆዋቸው ነው አካላችሁ ስመሽ የምሰበሰቡት ወደ ልባችሁ ነው አዕምሮ ማደስ አያቅም ነገሮችን ወደ ውጥረት መውሰድ ነው ሀገራችን በቀላሉ የምታዩ ተረቶች አሉ ግን በጣም ትልቅ መልዕክት የያዙ አባቴ ልጅ እያለው ሁሌም ስቾኩል የረጋ ሰው ቁቤ አንተ ልጅ ልብ ጊዛ ይለኝ ነበር ልብ ሰዎች እራሳቸውን የምያድሱበት ቦታ ነው ሳምሶን ከባዲ ሰው ነበር ወደ ልቡ ስገባ ግን እራሱን ማደስ ጀመሬ የገልላ ፍቅር ሳምሶንን ማደስ ጀምሮ ነበር በልባችሁ ውስጥ የማሸነፍና የመሸነፍ ደረጃ የለም አዕምሮ ውስጥ ነው ማሸነፍ ያለው እናም ሳምሶን ወደ ልብ ስወርድ መታደስ ስጀምር ሞት ቀደመው ምክንያቱም የሳምሶን ተቀናቃኞች አዕምሯቸው ውስጥ ነው ያሉት መሸናነፍና ከመሸነፍ ፉክክር ወቶ ወደ ሰፈነው ሰላም ስገባ ነው ፍፃመው የመጣው ሳምሶን እድለኛ ነው ከደረጃ ወቶ ወደ ሰፈነው አለም ወርዷል ወደ ልባችሁ ስትገቡ ጠላት የላችሁም አዕምሮ ውስጥ ስትኖሩ ነው ጠላት የምታፈሩት ጠላትነት ሃሳብ ስሆን ድርጊቱ የስሜት መገንፈል ነው በልባችሁ ውስጥ ስትኖሩ ትጠላላችሁ እንጅ አትጠሉም ኢየሱስ ሞሃመድ ቡዲሃ ይጠሉ ነበር እንጅ አልጠሊሉሌም በምድር ላይ እግዚብሔር ወዳጅ እንጅ ጠላት አልፈጠረም የተፈጠረው ፍጡር ትዕብት ነው እራሱን ለጠላትነት ያበቃው አዕምሮ ውስጥ አለመታዘዝ ስፈጠር ወደ ልብ ስወርድ ትዕቢት ይሆናል የረጋ ሰው ቁቤ እናም ልብ መግዛት ከውድድር መውጣት ነው ከራስ ጋር መዋሀድ ነው ወደ ራስ መመለስ ነው ስመሽ ወደ ቤታችሁ እንደምተሰበሰቡት ወደ ልባችሁ መመለስ መታደስ ነው አዕምሮ ሁሌም ውጥረት ያበዛል ሳያቋርጥ ያለእረፍት ሀይል ይጠቀማል አዕምሮ ሳይተኛ ለሶስት ቀን በተከታታይ ብሰራ ሰው እራሱን ይስታል እራሱን ባይስት እንኳን የምሰራውን ማገናዘብ ያቅተዋል ለሰው ልጅ ምሽትና ንጋት የተፈጠረው የቀንን ውጥረት በማታ እረፍት በእንቅልፍ እንድታደስ ነው የእንቅልፍ ትንሽ የለውም እራሳችሁን አሟቹ ለሰላሳ ደቅቃ ብትተኙ ስትነቁ አዕምሯችሁ ታድሶ ታገኛላቹ አዕምሮን ማሳረፍ እድሳት ነው ከአዕምሮ መውጣት ስትችሉ እረፍት ትለማመዳላችሁ የምጠቅማችሁን ሀይል የማይረባ ነገር በማሰብ እያባከናቹ ነው ማብራት ሀይል የምጠቅመው ስመሽ ነው ማብራት የጨለመን ለመግለፅ ነው ቀን ግን ማብራት ብታበሩ ለውበት ካልሆነ በስተቀር ፋይዳ የለውም ሀይላችሁን የምታውሉት ለጥቅም መሆን አለበት አዕምሯችሁን ስጨልም አብሩት ጨለማን የምገፍ የብርሃን ሃሳብ ያመነጭ ይሆናል ችግር በሌለበት አዕምሮን መጠቀም አዕምሯችሁ ላይ ጫና ከመፍጠር በስተቀር የረጋ ሰው ቁቤ ጥቅም የለውም ጮጋራችሁን የምያማችሁ ባዶ ስሆን ነው የምፈጨው ምግብ ስያጣ ነው ባዶ ጮጋራ እርስበርሱ ስለምፋተግ ህመም ይፈጥራል ባዶ ጭንቅላት ያለምክንያት የምትጠቀሙ ከሆነ አዕምሮን ማስጨነቅ ውጭ መፍቴሄ አያመጣም ምክንያቱም ችግር ስኖር መፍትሄ ለመፈለግ አዕምሮ ንቁ ይሆናል የአዕምሮ ምግብ ምክናታዊነት ነው ያለምክንያት አዕምሮን ማስገደድ ኢፍታዊ ነው ሀይል ማባከን ነው ለአዕምሮ የምታባክኑትን ሀይል ለልባችሁ አውሉት ለመታደስ ተጠቀሙት ለቁጥር የሚያዳግት የማይረባ ሃሳብ የምታስቡት በሀይል ነው አዕምሮ ስግል ነው ህመም የምያሰማው ኮምፕተር ጫና ስበዛበት ቢዚይ ይሆናል አዕምሮ ጫና ስበዛበት ራስምታት ይሆናል የሰዎች እንባ የምነሳው ከአዕምሮ አይደለም ከልብ ነው አዕምሮ ስነካ ብስጭት ከሰውነታችን ይነሳል ልብ ስነካ ነው እንባ የምናወጣው እንባ ትስስር ያለው ከልብ ጋር ነው ከስሜት ጋር ነው በሀዘን ተሞለታችሁ ስታለቅሱ ስሜት ነው በደስታ ተሞልታች ስትስቁ ከደስታ ብዛት እንባችሁ የምወርደው ከስሜት ነው እንባችሁ የስሜታችሁ መንገድ ነው የረጋ ሰው ቁቤ ወደ ልብ መግባት ከክፍፍል በላይ መሆን ነው ክፍፍል የምኖረው አዕምሮ የበላይ ሲሆን ነው ከአዕምሮ በላይ ስትሆኑ አንድ ትሆናላችሁ ራዕያችሁ ዘላለማዊ ስሆን ውስን አይሆንም የምያቆመው አይገኝም ጅረት ይሆናል ጅረት ለአንዲት ሰከንድ ሳይቆም ይፈሳል ራዕያችሁ እንደጅረት ዘላለማዊ መሆን ነው ራፅያቸውን እውነት ያደረጉ ሰዎች ታርካቸውን ስታነቡ ብዙን ጊዜ ወደ ልባቸው የወረዱ ናቼው በአዕምሯቸው ራዕይ አስቦ በልባቼው ግን የኖሩ ሰዎች ናቼው ለዛ ነው ራዕይ አሁን መፍለቅ ነው ያልኳችሁ አዕምሮ አሁንን ማሰብ ማሰላሰል ነው እረፍት የለውም ልብ ነው አሁንን የምኖረው እርፈት ያለው ልቡ ውስጥ ነው ውሃ ከመሬት ውስጥ መንገድ ስያገኝ ይፈልቃል መፍለቅ ከጀመረ አያቆምም ራዕይ አንደ ከአዕምሮ ሃሳብ ወደ ልብ ወርዶ መኖር ነው ሰዎች በምያፈቅሩበት ጊዜ ህይወትን መኖር ይጓጓሉ ቀን በቀን ይታደሳሌ ስለራሳቸው እረፍትና ውበት ይጨነቃሉ ስለምያፈቅሩት ብቻ አይምሰላችሁ የምጨነቁት ስለራሳቸውም አብዝቶ ይመሰጣሉ የረጋ ሰው ቁቤ አንድት ጓደኛዬ ወንድ ልጅ መስታወት ፊት መቆም ካበዛ አፍቅሯል ማለት ነው ትላለች እውነት ነው ወንዶች ስያፈቅሩ ለራሳቸው ውበት ይጨነቃሉ የተለያዩ የአለባበስ ስታየሎችን ለማድረግ ይሞክራሉ ከዚህን በፊት ያልሞከሩትን ነገር መሞከር ይጀምራሉ በዛ ውስጥ እድሳት ያደረጋሉ ይህ የመጣው ወደ ልብ መውረድ ስለጀመሩ ነው ኢድሳት ማሰብ የአዕምሮ ስራ ስሆን መተግበሩ ልብ ውስጥ ያለ ጉዳይ ነው ይበልጥ ወንዞች ገባር ስያገኙ ይጠነክራሉ እናም አዕምሮን በምያስፈልግ ብቻ ተጠቅማችሁ ወደ ልባችሁ ውስጥ መኖር ከጀመራችሁ ይበልጥ ራዕያችሁ እውን ይሆናል ራዕይ ማሰብ ሳይሆን መኖር ነው ራዕይ አሁን የምትጀምሩት የዛሬ ቤት ነው አሁን እየኖራችሁ ያለቅስበት ስሆን ዛሬ ጠቅላለ ጊዜ ነው ብርቱካን የምትበሉት ልጣጩን ሳይሆን ከልጣችሁ ውስጥ ያለውን ስጋ ነው እናም ራዕይ የምኖረው ዛሬ ሳይሆን ከዛሬ ውስጥ ያለ አሁንን ነው የረጋ ሰው ቁቤ መስማት የምትጀምሩት ከራሳችሁ ነው መስማት የምጀመረው ከራስ ነው አንድ ልጅ ልክ እንደተወለደ የምሰማው ነገር ብኖር የገዛ ጭወቱን ነው መልካም ከሆነው ከእናቱ ማዕፀን ውስጥ መንቀሳቀስ ስጀመር እንግዳ የሆነ ሁኔታዎች መከሰት ይጀምራሉ ይህንን እንግዳ የሆነ ክስተት ስለምስፈራው መጮው ይጀምራል መስማት የምጀመረውም ከዛ ጭወት ቦኋላ ነው የሰው ተፈጥሮ ከራሱ ነገሮችን ለመጀመር ታስቦ ነው አይን አላችሁ ታያላችሁ ለመጀመሪያ የምታዩት ግን እራሳችሁን አይደለም አከባቢያችሁን ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሰሙት ግን የገዛ የራሳችሁን ጭወት ነው በጆሮ የራሳችሁን ስታዳብሩ በእይታ ግን አከባቢያችሁን ታስተውላላችሁ ህፃናት እንደተወለዱ እራሳቸውን ማየት አይችለም እራሳችሁን ለማየት ብዙ ዕድሜ ልፈጅባችሁ ይችላል እራስህን በፅሞና ማየት በሰው ልጆች ላይ የምጀመረው ስጎረሙሱ ነው ለአቅሜ አዳም ስበቁ እራሳቸውን ማየት ይጀምራሉ ይህ እይታ ጥሩ ሆኖ ሳሌ እይታው ግን ከራስ ሳይሆን ከእኩዮቹ አንፃር እራሳቸውን ማየት የረጋ ሰው ቁቤ ይጀምራሉ ምክንያቱም አከባቢበው አንዱን ከአንዱ በማወዳደር ስለተጠመደ ልጆቹም የውድድር ሰላለባ ይሆናሉ ህፃናቶቹ ስለራሳቸው ነው ቀድመው የሚሰሙት እይታ ስለራስ ቀድማችሁ ከሰማችሁ ቦኋላ የምመጣ ነገር ነው ሚዛናቼው ያለው በልባቼው ሳይሆነ በእኩዮቻቸው አልፎም በወላጆቻቸው እጅ ውስጥ ነው አንድ ልጅ ቆንጆ እንደሆነ እራሱን ከማየቱ በፊት ቀድሞ ከወላጆቹ ይሰማል እራሳችንን የምናይበት የማዳበር ስልት ማህበረሰባችን የለውም ማህበረሰቡ እይታው ሁሌም ከራስ ወደ አከባቢ ያደላል የገዛ ልጆቻቸውን እንኳን ከምያዩ ይልቅ ደብቆ ያስቀመጡትን ወርቅና ብር በእየቀኑ ማየት የስደስታቸዋል እይታችሁ ግን መሆን ያለበት ከራሳችሁ ወደ ልባችሁ መሆን አለበት ከራሳችሁ በላይ በምድር ላይ ለራሳችሁ አስፈላጊው ነገር የለም በማየትና መስማት መካከል ያለው ልዩነት ይህ ነው መስማት ከራስ ስጀምር ህይወት ያብባል መስማት ስለራስ ማወቅ ነው ህጻናት እንደተወለዱ የምያለቅሱት ለዛ ነው ስለራሳቸው ማወቅ ስለምጀምሩ ነው ይህም ምቾት ይነሳቸዋል ያለምንም ትምህርት የምታደረጉት ነገር ማልቀስ ነው እናም ማልቀስን እንደመፍትሄ የረጋ ሰው ቁቤ ይወስዱታል ግን እያደጉ ስመጡ ማልቀሳቸው ከጥቅም ጋር ይያያዛል አንድ ህፃን ልጅ አሻንጉልቱን ስቀማ አሻንጉልቱን ለማስመለስ ግዴታ ማልቀስ ይጀምራል ይህን የምፈልገውን ነገር በማልቀስ ምግኘት እንደምቻል ልጁ ይረዳል ይህ ነገር ከሰዎች ጋር ያድግና ትልቅ ሆኖ የምፈልጉትን ስያጡ እንኳን እንባቸው ይቅድማቼዋል እራሳችሁን ከመስማት ስትጀምሩት የህይወት ፍሰት ከእናንተ ወደ አከባቢያችሁ ይሆናል ከአከባቢያችሁ ወደ እናንተ የምመጣው ነገር ጉዳቱ ያመዝናል ከራሳችሁ መስማት ስትጀምሩ ምን አይነት ሰው እንደሆናችሁ ትለያላችሁ እራስን መስማት ከምንም በላይ ከራሳችሁ ጋር ያላችሁትን ድርሻ ትልቁን ቦታ ይይዛል አንድ እናት ልጂ በትምህርት በጣም ዝቅጠኛ ውጤት አመጣባትና በጣም ተበሳሇታ ልጂን ስትገርፍ ደረስኩባትና ምን ሆነሽ ነው ልጁን የምትገርፊው።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact