Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
አንቀጽ ውሉን ስለመሰረዝ በዚህ ህግ መሰረት ከተከፈሉ በኋላ የሚተርፍ ገንዘብ ቢኖር ለባለዕዳው ወይም ባለዕዳው ማሕበር ሲሆን ለማህበርተኞቹ በድርሻቸው መጠን ተመላሽ ይደረጋል ርዕስ አምስት ስለ ኪሳራ ሂደት ተመልሶ እንዲንቀሳቀስ ፍርድ ቤቱን ለመጠየቅ ይችላል በዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ መሰረት የኪሳራውን ሄደት ለመዝጋት ወጪ የሆኑ ገንዘቦችን አስቀድሞ መክፈል አለበት አንቀጽ ንብረት አስተዳዳሪው አጅ ማስቀመጡን በማስረዳት የመክሰሩ ሂደት አንዲዘጋ ለፍርድ ቤቱ ሊያመለክት ይችላል።
በብ ልቪዐጠዩሃ ምዕራፍ አምስት ስለ ደላላ አንቀጽ ትርጉም ደላላ ማለት ንብረት እቃ ወይም አገልግሎት ለመግዛት ወይም ለመሸጥ የሚፈልጉ ሰዎችን የሚያገናኝ ሙያዊ እገዛ የሚያደርግ ሰዉ ወይም የንግድ ማኅበር ነው የድለላ ዓይነቶችና የእያንዳንዱ ዝርዝር ሁኔታ በህግ ሊወሰን ይችላል ደላላ የሚያዋውለው ውል አይነትና ምንነት ወይም የሚያገናኛቸው ሰዎች ማንነት ምንም ቢሆን ነጋዴ ይባላል ደላላ ሁለቱም ተስማሚዎች በውላቸው በግልጽ ያስቀመጡት ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር ሁለቱን ተስማሚዎች በመወከል እነሱን ተክቶ ገንዘብ ለመቀበልም ሆነ ማንኛውንም ወደ ተግባር የሚያስገባ እንቅስቃሴ ማድረግ የለበትም አንቀጽ ለማሳያ የተቀበለውን ናሙና የማስቀመጥ ግዴታ ደላላው ለማስማማት ሥራው እንዲረዳው የተቀበለውን ማንኛውንም ናሙና የስምምነቱ ሂደት ፍጻሜ እስከሚያገኝ ድረስ በአግባቡ ጠብቆ ማስቀመጥ ይኖርበታል አንቀጽ ለተዋዋዮች ስለ ማስታወቅ በለማድ የታወቀ ካልሆነ ወይም በስምምነት በተለየ ሁኔታ ካልተወሰነ በስተቀር ተዋዋዮቹ ውል ለመዋዋል ከተስማሙ በውሉ ሊያካትታቸው ያሰባቸውን የውል ቃሎችና ሁኔታዎች ደላላው ለተዋዋዮቹ ማሳወቅ አለበት በለማድ የታወቀ ካልሆነ ወይም በስምምነት በተለየ ሁኔታ ካልተወሰነ በስተቀር በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ መሰረት የተዘጋጀውን ውል ተዋዋዮች ካላጸደቁት በስተቀር በእነሱ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም አንቀጽ የስምምነት ሰነዱን ለተስማሚ ወገኖች ስለማስረከብ በደላላው አማካኝነት የተደረገው ስምምነት እንደተጠናቀቀ ደላላው ሳይዘገይ ወዲያውኑ የሁለቱም ተስማሚ ወገኖች ስም ወይም የንግድ ስም ስምምነቱ የተደረሰበት ቀን እና የስምምነቱን ይዘት በአጭሩ የያዘ የስምምነቱን ሰነድ አዘጋጅቶ የራሱ ስም ፊርማ እና ማህተምያለበት ለሁለቱም ተስማሚዎች ሊሰጣቸው ይገባል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተገለጸው የስምምነት ሰነድ ተፈጻሚነት የሚኖረው ሁለቱም ተስማሚዎች ሲያጸድቁት ነው አንቀጽ ስለ ደላላው ግዴታ እና ኃላፊነት ደላላዉ የሚያከናውነው የድለላ ስራ በህግ የተፈቀደ መሆኑን የማረጋገጥ ፃላፊነት አለበት ደላላው በተቻለ መጠን ትክክለኛና የተሟላ መረጃ ለተዋዋይ ወገን መስጠት ይኖርበታል ደላላው በየጊዜው ስላከናወናቸው ሥራዎች ድለላው በማን እና በማን መካከል ስምምነት አእንደተካሄፄደ የተደረሰበት ስምምነት ቀኑን አና ዓመተ ምህረቱን በሚያሳይ መልኩ መዝግቦ ማስቀመጥ የንግድ ሚስጥሮችን ጠብቆ የማቆየት በማንኛውም ጊዜ እነዚህ ሰነዶች ከተሰማሚዎች በአንዱ ወይም በሁለቱ ወይም ሕጋዊ ሥልጣን ባለው አካል ሲጠየቅ የማቅረብ እና የመስጠት ዛላፊነት እና ግዴታ አለበት ደላላዉ ስለሚያስማማዉ ጉዳይ ከሦስተኛ ወገን የተከፈለዉን ማንኛዉንም አበል ወይም ክፍያ ለሁለቱም ተስማሚ ወገኖች ማሳወቅ አለበት ለድለላ ስራ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ይጠየቃል ደላላው ወይም ደላሎች በተዋዋይ ወገኖች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ፃላፊ ይሆናል ደላላው በህግ ከተፈቀደው ውጪ የሚያከናውናቸው ተግባራት በህግ የሚያስጠይቁት ይሆናል አንቀጽ ስለደላላው አበል ደላላው ውሉን ካዋዋለ በኋላ ወሉ ቢፈጸምም ባይፈጸምም የአገልግሉት ክፍያ ሊከፈለው ይገባል የድለላ የአገልግሎት ክፍያ አገልግሎቱን በጠየቀው ወገን ይከፈላል የድለላውን አገልግሎት የጠየቁት ሁለቱም ወገኖች የሆኑ እንደሆነ አገልግሎት ክፍያው በሁለቱ ወገኖች በጋራ ወይም በአንደኛው ወገን እንዲከፈል ስምምነት ሊደረግ ይችላል በሁለቱም ተስማሚዎች በተደረገው ውል የደላላ የአገልግሎት ክፍያ አበል የሚያመለክት ድንጋጌ ከሌለ የደላላውን አበል የሚከፍለው የደላላውን ሥራ የጠየቀው ወገን ብቻ ነው ለደላላው የሚከፈለው የአበል መጠን በሁለቱም ተስማሚዎች እና ደላላው በሚያደርጉት ስምምነት ይወሰናል በስምምነት ካልተወሰነ በአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ ያለውን ልማድ በመውሰድ ሊወሰን ይችላል የዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ ቢኖርም ለደላላዉ የሚከፈለዉ አበል በህግ ሊወሰን ይችላል በህግ ያልተወሰነ ከሆነና ክፍያው ከፍተኛና ያልተመጣጠነ የሆነ እንደሆነ በፍርድ ቤት ሊወሰን ይችላል ምዕራፍ ስድስት ስለኮሚሽን ወኪል አንቀጽ የኮሚሽን ወኪል ትርጉምና አሰራር የኮሚሽን ወኪል ማለት ራሱን ችሎ የሞያ ተግባሩ አድርጎ ጥቅም ለማግኘት ወኪሉን በመወከል በራሱ ስም ሸቀጦችን ወይም የሚንቀሳቀሱ ንብረቶችን ወይም እነዚህን የመሳሰሉ ማናቸውንም ንብረቶችን በስሙ የሚገዛ ወይም የሚሸጥ ወይም ወኪሉን በመወከል በስሙ የመጓጓዣ ውል የሚዋዋል ሰው ወይም የንግድ ማኅበር ነው ባለኮሚሲዮኖች ባለኮሚሲዮን ስለአደረጋቸው ሰው ወይም የንግድ ማኅበር ሆነው በራሳቸውም ስም ስለሚያደርጉት የንግድ እንቅስቃሴ በሁሉቱም በኩል በግልጽ የተደነገገ ውል እስከሌለ ድረስ ሃላፊ ናቸው ባለኮሚሲዮኖች ባለኮሚሲዮን ካደረጋቸው ሰው ጋር ካደረጉት የዋጋ ስምምነት ውጪ ዋጋውን አሳንሰው ወይም አስበልጠው ሊገዙ ወይም ሊሸጡ አይችሉም ከዚህ በላይ የተደነገገው አንደተጠበቀ ሆኖ በዝቅተኛ ዋጋ ለሸጡትም ሆነ በከፍተኛ ዋጋ ለገዙት ልዩነቱን ባለኮሚሲዮን ላደረጋቸው ሰው ወይም የንግድ ማኅበር የመክፈል ግዴታ ይኖርባቸዋል የተደረገው ሽያጭ ወይም ግዥ ግን ሳይፈርስ ኮሚሲዮን ባደረጋቸው ሰው ላይ የሚጸና ይሆናል ተዋዋይ ወገኖች እና የውሉ አይነትና አላማ ምንም ቢሆን የኮሚሽን ወኪል ነጋዴ ነው አንቀጽ የፍትሐብሔር ሕግ ተፈጻሚነት በፍትሐብሔር ሕግ የኮሚስዮን ውልን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በኮሚሽን ወኪል ላይም ተፈፃሚነት ይኖራቸዋል አንቀጽ ስለአክስዮን ደላሎች በሌላ ሕግ በልዩ ሁኔታ ካልተደነገገ በቀር በአክሲዮን ገበያ የሚሠሩ ደላላዎች የኮሚሽን ወኪል ናቸው ርዕስ ሦስት ስለ ሒሳብ ምዕራፍ አንድ ሒሳብ መያዝ ግዴታ ስለ መሆኑ አንቀጽ ነጋዴዎችና የንግድ ሥራ ማኅበሮች ማንኛውም የንግድ ሥራ የሚሠራ ኢትዮጵያዊ ወይም የኢትዮጵያ ዜግነት የሌለው ነጋዴ ሰው ወይም የንግድ ማኅበር እንደሚሠራው የንግድ ሥራ ስፋትና ዓይነት በንግድ ሥራ ልምድና ደንብ መሠረት የሚያስፈልግ የሒሳብ መዝገቦችና ሰነዶች ሊኖሩት ይገባል ማንኛውም ሰው ይሁን የንግድ ማኅበር በዚህ የንግድ ሕግ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች አሟልቶ ነጋዴ የሚለውን እውቅና እስካገኘ ድረስ የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ አለበት ማንኛውም የውጭ ዜጋ በዚህ ንግድ ሕግ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች አሟልቶ የነጋዴ አውቅና አግኝቶ ነጋዴ እስከተባለ ድረስ የዛፃገሩ ሕግ የሒሳብ መዝገብ እንዲይዝ የሚያስገድደው ባይሆንም በዚህ ሕግ ግን የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ አለበት አንቀጽ ስለ አነስተኛ ንግድ ነጋዴዎች የአነስተኛ ንግድ ነጋዴዎች የሒሳብ መዝገብ ከመያዝ ነጻ ናቸው የአነስተኛ ንግድ ሥራ አሰራር እና የካፒታል መጠን በሕግ ይደነገጋል ምዕራፍ ሁለት መያዝ ስለሚገባቸው መዛግብቶች እና ሰነዶች አንቀጽ ንግዶችን ሰለመመዝገብ ማንኛውም ነጋዴ ስለሚነግደው ንግድ ዓይነትና ስለአነጋገዱም ሁኔታ አስተያየት ሳያደርግ በየዕለቱ ንግዱን የሚመዘግብበት የሒሳብ መዝገብ እአና የሒሳብ ማመዛዘኛ መዝገብ ሊኖረው ይገባል በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው ቢኖርም ማንኛውም ነጋዴ እንደየሥራው ባሕርይ እና አስፈላጊነት ሌሎች የሒሳብ መዛግብት ሊኖሩት ይችላል ከዚህ በላይ የተደነገገው የሒሳብ መዛግብት የመያዝ ግዴታ አንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ነጋዴ ስለሚያደርጋቸው ልውውጦች ስለሚልካቸው ወይም ሰለሚቀበላቸው ሰነዶች አስመልክቶ ቅጅዎች ሊኖሩት ይገባል በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው እንዳለ ሆኖ ማንኛውም ነጋዴ በየቀኑ መዝገብ ላይ ለግል ኑሮው የሚያወጣውን ወጪ መመዝገብ አለበት በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው ቢኖርም ግለሰባዊ ወጪዎች እንደ ድርጅቱ ወጪዎች በእለታዊ ሒሳብ መዝገብ ላይ በዝርዝር መስፈር የለበትም ማንኛውም ነጋዴ ቢያንስ በወር እንድ ጊዜ በንግድ ሒሳብ ያስገባውን የማመዛዘን እና የንግድ እንቅስቃሴዉን ዕለት በዕለት ለመቆጣጠር የሚያስችሉትን ሰነዶች ጠብቆ የማቆየት ግዴታ አለበት አንቀጽ ሰለ መዛግብቶች አያያዝ በዚህ ህግ አንቀፅ ሃዐ መሰረት መያዝ የሚገባቸው መዝገቦች የቅደም ተከተል ስርዓት በመጠበቅ እንዲሰራባቸውና አንዳችም ክፍት ቦታ ሳይተውባቸው ወይም አንዳችም መለዋወጥ ሳይደረግባቸው እንዲጠበቁ ማድረግ ይገባል በደንቦች መሰረት ስልጣን ከተሰጣቸው ሹሞች አንዱ ለነዚህ መዛግብት ተራ ቁጥር እየተሰጣቸው አጭር የፊርማ ምልክት ያደርግባቸዋል የመዛግብቶቹን የገጽ ብዛት በእያንዳንዱ መዝገብ መጨረሻ ገጽ ላይ ባለስልጣኑ ዘርዝሮ ይጽፋል ማንኛውም ነጋዴ በበጀት አመቱ መጨረሻ ላይ የየቀኑ የሂሳብ መዝገብ እና የማመዛዘኛ ሂሳብ መዝገብ ለመዝጋቢው አካል በማቅረብ በዓመቱ በሂሳብ መዝገብ ገቢ ለማድረግ የተጠቀመባቸውን ቁጥሮች ተከታታይነት እና ሕጋዊነት ሊያረጋግጥ ይገባል በአያንዳንዱ የሂሳብ መዝገብ ወይም የማመዛዘኛ ሂሳብ መዝገብ ገጽ ላይ ቁጥር ተሰጥቶት ካለቀ በኋላ የሂሳብ መዝገቡ የመጨረሻው ገጽ ላይ የተሰጠው ቁጥር በመዝጋቢው አካል ፊት ቀርቦ መረጋገጥ ይኖርበታል ነጋዴው ከስራ ባህሪው ወይም እንደአስፈላጊነቱ የሚይዛቸው ሌሎች የሂሳብ መዛግብት ቢኖሩትም በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ ለመዝገቦች የተሰጡትን ቁጥሮች መጠቀም የለበትም አንቀጽ የሒሳብ መዛግብትን በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች መመዝገብ ነጋዴዎች አጠቃላይ የሒሳብ እንቅስቃሴያቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች መመዝገብ ይችላሉ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ መሠረት የሚያዙት የሒሳብ መዛግብት ልክ በእጅ ጽሑፍ የሚያዙ የሒሳብ መዛግብት ወይም የማመዛዘኛ ሒሳብ መዝገብ ማሟላት የሚገባቸውን ወይም መያዝ ያለባቸውን ፎርማሊቲዎች ማካተት አለባቸው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደረገ ምዝገባ ልክ በጽሑፍ አንደተያዘ ምዝገባ ተቆጥሮ በማንኛውም ጊዜ ነጋዴው እንደ ማስረጃ ሊጠቀምበት ይችላል አንቀጽ የንግድ መዛግብት ተጠብቀው የሚቆዩበት የጊዜ ገደብ ማንኛውም ነጋዴ የሒሳብ መዛግብት አና ሰነዶች ሥልጣን በተሰጠው አካል ተረጋግጠው ሥራ ላይ ካዋሉበት ቀን ጀምሮ ወይም ሰነዶቹ ሥራ ላይ ከዋሉበት የመጀመሪያው ቀን ጀምሮ እስከ አሥር ዓመት ድረስ ጠብቆ የማኖር ግዴታ አለበት በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተገለጸው የቀን አቆጣጠር መዝገቡ ከተዘጋበት ቀን ጀምሮ ወይም ሰነዶቹ በነጋዴው እጅ ከገቡበት ወይም ለሌላ ሦስተኛ ወገን ከተላኩበት ጊዜ ጀምሮ ሊሆን ይችላል አንቀጽ መልዕክቶችን ስለመያዝ ነጋዴው በሥራው ምክንያት የደረሱት መልዕክቶች ዋናው ካልሆነ በቂ በሆነ ምክንያት ግልባጩን መዝግቦ አሥር ዓመት ድረስ ጠብቆ ማኖር አለበት ምዕራፍ ሦስት የሒሳብ መዝገቦችን ማስረጃ አድርጎ መጠቀም አንቀጽ የሒሳብ መዝገቦችን ማስረጃ ስለማድረግ ክርክሩ የተነሳው በነጋዴዎች ወይም በንግድ ማኅበሮች መካከል ከሆነ እና የክርክሩ ይዘትም በመካከላቸው ስላለው ወይም ስለነበረው ንግድ በተመለከተ ሲሆን ፍርድ ቤቱ የሒሳብ መዝገብን እንደማስረጃ ሊቀበለው ይችላል በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ መሠረት ፍርድ ቤቱ የሒሳብ መዛግብትን አንደ ማስረጃ መቀበል የሚችለው የሒሳብ መዛግብቱ የንግድ ሕጉ የሚያስቀምጠውን መስፈርት አሟልተው ሲገኙ ብቻ ነው አንቀጽ የሒሳብ መዛግብት በያዘው ነጋዴ ላይ ማስረጃ ስለመሆናችው የንግድ መዝገቦች በባለመዝገቡ ላይ እንደማስረጃ ሊቀርቡ ይችላሉ ባለመዝገቡ በመዝገቡ ለመጠቀም የሚፈልገው ሰው ለሚለው ቃል ተቃራኒ የሚሆኑትን ከፍሎ ለማስቀረት አይችልም ምዕራፍ አራት የሒሳብ አያያዝ ደንቦች አንቀጽ የቪህ ምዕራፍ ድንጋጌዎች አፈጻጸም ወሰን ነጋዴዎች የሆኑ ሰዎችና የንግድ ማኀበሮች በዚህ ምፅራፍ በተመለከቱት ቁጥሮችና በህግ በሚደነገገዉ የሒሳብ አያያዝ ደንብ ድንጋጌዎች መሠረት መሥራት አለባቸው በአንዳንድ ዓይነት ነጋዴዎችና የንግድ ማኀበሮች ላይ የተለዩ ደንቦች ሊወሰንላቸው ይችላል እነዚሁም ደንቦች በንግድ ሥራው ዐይነትና ከፍተኛነት መጠን በያይነቱ ለመሆን ይቸላሉ አንቀጽ የገንዘብ መግለጫ የማንኛዉም ነጋዴ መሠረታዊ የገንዘብ መግለጫዎች የሚከተሉትን መያዝ ይገባቸዋል ሀ የሒሳብ ማመዛዘኛ ለ የገቢ መግለጫ የገቢና ኪሳራ መግለጫ ሐ የዋና ገንዘብ መግለጫ መ የገንዘብ ፍሰት መግለጫ እና ሠ ስለሒሳብ መዝገብ አያያዝ ሥርዓቱ ያሉ ማስታወሻዎች የሒሳብ ማመዛዘኛዉ በአንድ በተወሰነ ቀን ያለዉን የሀብት የዕዳ እና የማመጣጠኛ ሒሳቦችን መያዝ አለበት የገቢ መግለጫዉ የትርፍ እና ኪሳራ መግለጫዉ በተወሰነዉ ጊዜ የነበረዉን የተሰበሰበ የገቢ የዋጋ እና የወጪ ሒሳቦችን መያዝ አለበት የዋና ገንዘብ መግለጫዉ በተወሰነዉ ጊዜ ዉስጥ የነበረዉን የዋና ገንዘብ እንቅስቃሴ በወቅቱ ከነበረዉ የመጨመር ወይም የመቀነስ ሁኔታ ጭምር መያዝ አለበት የገንዘብ ፍሰት መግለጫዉ በተወሰነዉ ጊዜ ዉስጥ የነበረዉን የተሰበሰበ እና የተከፈለ ገንዘብ መያዝ አለበት ከላይ የተገለጹት የእያንዳንዱ ዝርዝር በሒሳብ መዝገብ አያያዝና ኦዲት ሥርዓት ደንብ ይደነገጋል አንቀጽ አላቂ ለሚሆን ነገር የዋጋ መተኪያ የእርጅናና የወጭ መጠባበቂያ ገንዘቦች አላቂ ለሆነ ነገር የዋጋ መተኪያ ማለት የግድ በጊዜ ሂደት በሚያረጁ ግዙፍነት የሌላቸዉ ንብረቶች ላይ ለደረሰ ኪሳራ በሒሳብ መዝገብ አያያዝ የሚተመን ዋጋ ነዉ የአርጅና ድንጋጌዎች በቋሚ ንብረት ላይ እንደሚደርስ ለሚጠበቅ የዋጋ መቀነስ ታሳቢ የተደረጉ ይሆናሉ አላቂ ለሚሆን ነገር የዋጋ መተኪያ የእርጅናና የወጭ መጠባበቂያ ገንዘቦች የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በሒሳብ ማመዛዘኛ በእያንዳንዱ ሀብት ርዕፅስ ሥር ሊመላከቱ ይገባል አንቀጽ የማደራጃ ወጪዎች የማደራጃ ወጪዎች ማለት የንግድ ሥራው የሚከናወንበት የጥቅም ማስገኛ ቤቱ በተቋቋመ ጊዜ የሆነው ወጪ ወይም የጥቅም ማስገኛ የሥራ ማከናወኛ መሣሪያዎችን ለመግዛት ወጪ የሆነው ገንዘብ ሁሉ ነው የማደራጃ ወጪዎች በአጠቃላይ ተቀባይነት ባለዉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መርሆዎችና አግባብነት ባለዉ የገቢ ግብር ደንብ መሠረት አላቂ ለሆነ ነገር የዋጋ መተኪያ ሊደረግላቸዉ ይገባል አንቀጽ ዋና ገንዘብና የመጠባበቂያ ገንዘቦች ዋናው ገንዘብ ከባለቤቱ ወይም ከማኀበርተኞቹ በየድርሻው በገንዘብ ወይም በዐይነት ለጥቅም ማስገኛ የንግድ ቤቱ የተሰጠው መሠረታዊ ሀብቱ ነው ዝርዝሩ በሒሳብ መዝገብ አያያዝና ኦዲት ደንብ ይወሰናል በንግድ ቤቱ እጅ ከዋናው ገንዘብ ሳይቀላቀል ተቀማጭ የሆነ የትርፍ ክፍል ወይም ከዋናዉ ገንዘብ ተለይቶ የተቀመጠ ገንዘብ ሁሉ የመጠባበቂያ ገንዘብ ይባላል ዝርዝሩ በሒሳብ መዝገብ አያያዝና ኦዲት ደንብ ይወሰናል አንቀጽ ስለ አገማመት የማይነቀሳቀሱ ቋሚ ሀብቶች የሆኑት በሒሳብ ማመዛዘኛ ውስጥ በመሠረታዊ ዋጋቸው ይመዘገባሉ ወይም እንደገና ተገምተው እንደሆነ እንደገና በተገመቱበት ዋጋቸው ይመዘገባሉ በተቆዋጠሩበት ቀን ያሉት ሸቀጦች ዕቃዎች የዕቃ መጠቅለያዎችና የተከማቹ ፅቃዎች የሚገመቱት በሚያወጡት ዋጋ ልክ ነው ተንቀሳቃሽ ያልሆኑት ንብረቶች በሒሳብ ማመዛዘኛ ሒሳብ ክፍል በተገዙበት ዋጋ ይመዘገባሉ ቅንጣቢዎቹ ከፋብሪካ ሥራ የሚቀሩ ልቅምቃሚና ጥራጊዎቹ በሒሳብ ማጣሪያው ቀን ባለው ገበያ ዋጋ ይገመታሉ ወይም የገበያ ዋጋ ልክ ያልኖረ እንደሆነ ያወጣሉ ተብሎና በሚሰጣቸው ዋጋ ይገመታሉ በሒሳብ ማመዛዘኛ ሒሳብ ክፍል ተሠርቶ ያለቀላቸው ዕቃዎችና በመሠራት ላይ የሚገኙ ዕቃዎች በሒሳብ ማጣሪያው ቀን ባለው ዋጋቸው ይመዘገባሉ ፅቃው በተቄጠረበት ቀን ተከማችተው የሚገኙት ሸቀጦች በገሚስ የተሠሩት ዕቃዎች በሙሉ የተሠሩ ዕቃዎች የፅቃ መጠቅለያዎች እርግጠኛ ዋጋቸው ከወጣበት ቀን በታች የሆነ እንደሆነ ነጋዴው ወይም የንግድ ማኀበሩ ስለ ዋጋ ጉድለት መተኪያ የሚሆን ገንዘቦች ማደራጀት አለበት የነጋዴዉ ደንበኞች እና ሌሎች ግዙፍነት የሌላቸዉ ነገሮች አገማመት በአጠቃላይ ተቀባይነት ያለዉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መርሆዎችን የተከተለ ይሆናል ርዕስ አራት ስለንግድ መዝገብ ምዕራፍ አንድ ስለ ንግድ መዝገብ አቋቋም አንቀጽ መርህ በህግ በተለየ ሁኔታ ካልተወሰነ በስተቀር በኢትዮጵያ ውስጥ የንግድ ስራ ላይ የሚሰራ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ ዜጋ ወይም የንግድ ድርጅቶች በንግድ መዝገብ መመዝገብ አለበት ማንኛዉም ሰዉ በንግድ መዝገብ ላይ ሳይመዘገብ ማንኛዉም ዓይነት የንግድ ሥራ ፈቃድ ማግኘት አይችልም ማንኛዉም ሰዉ በንግድ መዝገብ የሚመዘገበዉ ዋና መሥሪያ ቤቱ በሚገኝበት ሥፍራ ነዉ ማንኛዉም ሰዉ በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ የንግድ ሥራዎችን ቢሠራ በንግድ መዝገብ የሚመዘገበዉ አንድ ጊዜ ብቻ ይሆናል በተለያዩ ሥፍራዎች ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት የሚከፍት ማንኛዉም ሰዉ ሥራ ከመጀመሩ በፊት የመጀመሪያ ምዝገባ በተመዘገበበት ቦታ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱን ማስመዝገብና ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ በሚገኝበት ሥፍራ ላለዉ መዝጋቢ መሥሪያ ቤት ወዲያዉኑ ማሳወቅ አለበት ማንኛዉም ሰዉ በንግድ መዝገብ ሲመዘገብ የድርጅቱን ስም ከሌላ ነጋዴ ጥቅም ጋር የማይጋጭ መሆኑን በማረጋገጥ በንግድ መዝገብ ዉስጥ ማስገባት አለበት አንቀጽ የንግድ ምዝገባ ስለማከናወን በማዕድን ዘርፍ የሚሠሩ የዉጭ ነጋዴዎች የፌደራል መንግሥት የልማት ድርጅቶች የንግድ አእንደራሴዎች የዉጭ አገር ነጋዴዎች በዓለም አቀፍ ጨረታ አሸናፊ ሆነዉ የሚገቡ የዉጭ አገር ነጋዴዎች ተቋቁሞ የሚገኝ የንግድ ድርጅትን ገዝቶ ባለበት ሁኔታ ንግድ ለማካፄድ የሚፈልግ የዉጭ አገር ነጋዴ በሌሎች ህጎች የንግድ ሥራ እንዲሠሩ የተፈቀደላቸዉ ማህበራት በፌደራል ደረጃ የሚቋቋሙ የዘርፍ ማህበራት እንዲሁም በሚኒስትሩ ታምኖበት የተፈቀደላቸዉ የንግድ ምክር ቤቶች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በፌደራል ደረጃ ንግድን በሚያስተዳድረዉ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ይመዘገባሉ በክልል መንግሥታት የሚቋቋሙ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች እና በተዋረድ በክልል የሚቋቋሙ የዘርፍ ማህበራት ንግድን በሚያስተዳድሩ የክልል አካላት ይመዘገባሉ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ፈቃድ በሚሰጥባቸዉ የንግድ መስክ መሠማራት የሚፈልግ ማንኛዉም ሰዉ በንግድ መዝገብ በመመዝገብ በቀጥታ ለሚኒስትሩ ማመልከት ይችላል ግለሰብ ነጋዴ ወይም የንግድ ማህበር በንግድ መዝገብ እንዳይመዘገብ በህግ መሠረት የቀረበ መቃወሚያ በንግድ መዝገብ ከመመዝገብ ያግደዋል አንቀጽ የንግድ ምዝገባ የሚጸናበት ሁኔታ ማንኛዉም የንግድ ምዝገባ የሚጸናዉ አመልካች በንግድ መዝገብ ከተመዘገበበት ዕለት ቀጥሉ ባለው የስራ ቀን ጀምሮ ነዉ ዝርዝሩ በህግ ይወሰናል አንቀጽ ስለንግድ ማህበራት ህጋዊ ሰዉነት የንግድ ማህበራት የህግ ሰዉነት የሚያገኙት በምዝገባ ይሆናል የንግድ ማህበራት ሲቋቋሙ በአገር አቀፍ ሥርጭት ባለዉ ጋዜጣ ለህዝብ ይፋ መደረግ አለባቸዉ አንቀጽ የምዝገባ መረጃዎችንና ሰነዶችን ስለማስተላለፍ አግባብ ያለው አካል በዚህ ህግ መሠረት የንግድ ምዝገባ እንዳከናወነ የምዝገባ መረጃዎችን ለማእከላዊ ምዝገባ የመረጃ ቋት ወዲያዉኑ ማስተላለፍ ይኖርበታል አንቀጽ ስለ መዝገቦች ዓይነትና የመመዝገብ ሥልጣን የዚህ ንግድ ህግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ስለሚቋቋሙ የንግድ መዝገቦች ዓይነት ምዝገባን ስለሚያከናውኑ አካላትና ስለሚኖራቸው ስልጣንና ተግባራት እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች በህግ ይወሰናል አንቀጽ መግለጫ ስለመስጠት በንግድ መዝገብ አማካኝነት የሚደረግ ማስታወቅ የሚፈፀመው ነጋዴው መዝገብ ለመያዝ ሥልጣን ባለው ኃላፊ ዘንድ ቀርቦ የሚሰጠውን መግለጫ መሠረት በማድረግ ይሆናል በንግድ መዝገቡ የተደረገውም ምዝገባ የፀና የሚሆነው ምዝገባው ከተደረገበት ዕለት ቀጥሎ ካለው የሥራ ቀን ጀምሮ ነው በንግድ ድርጅቶች የሚሰጡ መግለጫዎች ምዝገባን በተመለከተ የዚህ ሕግ ሁለተኛው መጽሐፍ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ ምዝገባን ስለማስታወቅ በንግድ ሚኒስቴር የሚመዘገቡ ወይም ከአንድ በላይ በሆኑ ክልሎች የሚካሔዱ የንግድ እንቅስቃሴዎችን የሚመለከቱ ዋና ወይም ተጨማሪ ምዝገባዎች የምዝገባ ለውጦችና ስረዛዎች ሁሉ ወዲያውኑ አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ታትመው እንዲወጡ መደረግ አለበት በአንድ ክልል ወይም ለፌደራል መንግሥቱ ተጠሪ በሆነ ከተሞች ብቻ የተወሰኑ የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚመለከቱ ጉዳዩች ማስታወቂያ በክልሉ ወይም በፌደራል መንግሥቱ ተጠሪ በሆነ ከተማ በሚታተም ጋዜጣ እንዲወጡ ይደረጋል የተወሰኑ ጉዳዩች ብቻ በጋዜጣ አንዲወጡ በሕግ ካልተደነገገ በስተቀር ማናቸውም በንግድ መዝገብ ውስጥ የገባ መረጃ በንዑስ ቁጥር መሰረት በጋዜጣ ታትሞ መውጣት ይኖርበታል አንቀጽ ስለፃላፊነት የንግድ ምዝገባን የሚያከናውን አካል ሰራተኞቹ ከምዝገባ ጋር በተያያዘ ለሚያደርሱት ጉዳት ተጠያቂ ይሆናሉ አንቀጽ የንግድ መዝገብ ለህዝብ ክፍት ስለመሆንና መረጃ የማግኘት መብት የንግድ ማህበራት መዝገብ ለህዝብ ክፍት መሆን ይኖርበታል ሦስተኛ ወገኖችም መዝገቡን መመልከት ይችላሉ ማንኛውም ሰው የተወሰነውን ክፍያ ከፍሎ በመዝገብ የገባውን መረጃ ለማየት ወይም ግልባጭ ወይም ከመዝገቡ አጭር የተውጣጣውን ቃል አንዲሰጠው ወይም የሚፈልገው ጉዳይ ያልተመዘገበ ከሆነም አለመመዝገቡን የሚያረጋግጥ የሕግ ማስረጃ እንዲሰጠው ሥልጣን ያለውን መዝጋቢ መጠየቅ ይችላል መዝጋቢው የተጠየቀውን አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለበት አንቀጽ በንግድ ሰነዶች ላይ ስለሚገለጽ ጉዳዩች ማንኛውም የተመዘገበ ነጋዴ ለንግድ ሥራዎች በሚጠቀምበት ደረሰኝ ደብዳቤ ወይም በሌላ በማንኛውም ሰነድ ላይ የተመዘገበበትን ቦታ እና የምዝገባ ቁጥሩን መግለጽ አለበት ምዕራፍ ሁለት በንግድ መዝገብ ስለሚገቡ ጉዳዮች ክፍል አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ በመዝገቡ ስለሚገቡ ጉዳዩች የንግድ መዝገብ ዋና ወይም ተያያዥ ወይም ማሟያ ምዝገባዎች ማናቸውም ዓይነት ለውጦችና የተሰረዙ ጉዳዩች የሚካተቱበት ነው አንቀጽ በመዝገብ የማስገባቱ ስነስርዓት መረጃዎች በመዝገብ የሚገቡት እንዲመዘገብ በሚጠይቀው ሰው በሚቀርብ የፅሁፍ መግለጫ መነሻነት ነው በመዝገብ የገባ መረጃ በአንቀፅ በተመለከተው ምክንያት ሊሰረዝ ይችላል አንቀጽ ስለመግለጫውትክክለኛነት መዝጋቢው ለምዝገባ የቀረበለትን መግለጫ የተሟላ መሆኑንና ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አለበት አንድ ሰው በነጋዴነት ለመመዝገብ ካመለከተ አመልካቹ ምዝገባ የተጠየቀበትን ንግድ ለማካፄድ የሚያስችለውን ህጋዊ መመዘኛዎች ያሟላ መሆኑን መዝጋቢው ማረጋገጥ አለበት መዝጋቢው ለመግለጫው በደጋፊነት የቀረቡለት የጽሑፍ ማስረጃዎች ከመግለጫው ጋር የሚጣጣሙ መሆኑን ማጣራት አለበት መዝጋቢው አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው ሌሎች ተጨማሪ ሰነዶችና መረጃዎች እንዲቀርቡለት አመልካቹን ሊጠይቅ ይችላል ክፍል ሁለት ስለምዝገባ አንቀጽ የተሸጠ ወይም የተከራየ የንግድ መደብር ምዝገባ አንድ የንግድ መደብር የተሸጠ ወይም የተከራየ እንደሆነ የቀድሞው ነጋዴ ከመዝገብ እስኪሰረዝ ድረስ ገዥው ወይም ተከራዩ ሊመዘገብ አይችልም አንቀጽ ስለመመዝገቢያ ቦታ ማንኛውም ሰው በንግድ መዝገብ የሚመዘገበው በንግድ መዝገብ ለመመዝገብ ስልጣን ባለው የፌደራል መንግስቱ አካል ወይም በፌደራል መንግስቱ የማይመዘገብ እንደሆነ ዋና መስሪያ ቤቱ ባለበት ስፍራ ይሆናል በዚህ ሕግ አንቀፅ ፋ መሠረት የንግድ ሚኒስቴር ፈቃድ ከሚሰጥባቸው የንግድ ሥራዎች በስተቀር ማንኛውም ሌላ የምዝገባ ማመልከቻውን የሚያቀርበው የንግድ ሥራውን በሚያዘጋጅበት ላለው መዝጋቢ ነው ማንኛውም ነጋዴ ዋና ምዝገባ ሊያደርግ የሚችለው በአንድ የምዝገባ ቦታ ብቻ ነው በአንድ መዝገብም ከአንድ በላይ በሆነ የመዝገብ ቁጥር ሊመዘገብ አይችልም አንቀጽ ስለምዝገባ በዚህ ህግ የተደነገጉት እንደተጠበቁ ሆነው ምዝገባን በተመለከተ ዝርዝሩ በህግ ይወሰናል አንቀጽ ስለመክሰር የሚሰጥ ፍርድ መክሰርን ወይም የማገገሚያ ስምምነትን በተመለከተ የሚሰጠውን ፍርድ ማስመዝገብን አግባብነት ያላቸው የዚህ ሕግ መጽሐፍ አምስት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ ክፍል ሶስት ከመዝገብ ስለመሰረዝ አንቀጽ መነገድን ስለመተው ማንኛውም የተመዘገበ ነጋዴ የንግድ ሥራውን በማንኛውም ምክንያት የተወ ወይም የንግድ መደብሩን ባከራየ ጊዜ በአንድ ወር ውስጥ ከመዝገብ እንዲሰረዝ ማመልከት አለበት በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው አንደተጠበቀ ሆኖ ነጋዴው የንግድ ስራውን የተወ ወይም ንግድ ለመነገድ አንደማይችል በህግ የተወሰነበት መሆኑን መዝጋቢው መስሪያ ቤት ባወቀ ጊዜ ወይም ነጋዴው ሀሰተኛ መረጃ ወይም ሰነድ አቅርቦ በመመዝገቡ ምክንያት ምዝገባው ሊሰረዝ ይችላል የንግድ ማህበራት ምዝገባ ስረዛ የሚጸናው የስረዛው ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ይሆናል ሌሎች የንግድ ምዝገባ ስረዛዎች ስረዛው በመዝገብ ከሰፈረበት ቀን ጀምሮ የጸኑ ይሆናል አንቀጽ የነጋዴው መሞት ማንኛውም ነጋዴ በሞተ በሁለት ወር ውስጥ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የሟች ሚስት ወይም ባል ወይም የሟች ወራሾቹ ምዝገባው እንዲሰረዝላቸው ማመልከት አለባቸው በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተጠቀሱት ባለመብቶች የንግዱን ሥራ በጋራ ባለቤትነት ማካሄድ የሚቀጥሉ ከሆነ አዲስ ምዝገባ እንዲደረግላቸው ማመልከት አለባቸው የጋራ ባለቤትነቱ ሲቀር ንግዱ የተላለፈለት ሰው በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ መሠረት የተደረገው ምዝገባ እንዲሰረዝለትና አዲስ ምዝገባ እንዲደረግለት ማመልከት አለበት አንቀጽ ምዝገባን በትዕዛዝ ስለመሰረዝ ማንኛውም ነጋዴ የንግዱን ሥራ ማቆሙን ወይም መነገድ ያልቻለ ለመሆኑ ውሳኔ መኖሩ በታወቀ ጊዜ የመዝጋቢው መሥሪያ ቤት የበላይ ኃላፊ ምዝገባው እንዲሰረዝ ይወስናል በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተሰጠውን ውሳኔ ራሱ ነጋዴው መዝጋቢውና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት እንዲያውቁት መደረግ አለበት አንቀጽ ምዝገባን ያለማሰረዝ የሚያስከትለው ውጤት ማንኛውም የንግድ መደብሩን ያስተላለፈ ወይምያከራየ ነጋዴ ምዝገባውንም አስከሚያሰርዝ ድረስ መደብሩ የተላለፈለት ሰው ወይም ተከራይ ለገባው ዕዳ በአንድነትና በነጠላ ኃላፊ ይሆናል አንቀጽ መመዝገብ ወይም አለመመዝገብ ስለሚያስከትለው ውጤት ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበበት በስተቀር ማንኛውም የተመዘገበ ነጋዴ ወይም የንግድ ድርጅት ነጋዴ ነው ተብሎ ይገመታል ማንኛውም የተመዘገበ ነጋዴ ወይም የንግድ ማህበር ነጋዴ ላለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ አይፈቀድለትም ነጋዴነት የሚያስከትለውንም ዛላፊነት ሁሉ ይቀበላል በዚህ ሕግ መሠረት መመዝገብ የሚገባው ሆኖ ሳይመዘገብ የቀረ ማንኛውም ሰው ለሶስተኛ ወገኖች ነጋዴ መስሎ መቅረብ የለበትም ከቀረበ ግን እንደ ነጋዴ ተቆጥሮ ኃላፊ ይሆናል የንግድ ድርጅቶችን በሚመለከት አግባብ ያላቸው የዚህ ሕግ የሁለተኛው መጽሐፍ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ በመዝገብ የገባ ጉዳይ ስለሚያስከትለው ውጤት ማንኛውም ሰው በንግድ መዝገብ እንዲገባ ያደረገውን ጉዳይ እንዲለወጥ ካላመለከተ በስተቀር የተመዘገበው ትክክል አይደለም ብሎ ማስረጃ ለማቅረብ አይፈቀድለትም ሦስተኛ ወገኞች በንግድ መዝገብ የተመዘገበ ፍሬ ነገር አላወቅንም ነበር ብለው ማስረጃ ማቅረብ አይፈቀድላቸውም አንቀጽ ሦስተኛ ወገኞች መብት ሊነኩ የማይችሉ ነጋዴዎችን የሚመለከቱ ጉዳዬች የሚከተሉት ጉዳዩች በንግድ መዝገብ ያልተመዘገቡ ቢሆንም ቅን ልቡና ያላቸውን የሦስተኛ ወገኖች መብት ሊነኩ አይችሉም የነጋዴው አካለ መጠን ያለመድረስ የነጋዴው ማግባት የነጋዴው የጋብቻ ውል የነጋዴው ጋብቻ መፍረስ የነጋዴው ችሎታ ማጣት በዚህ ሕግ ተጥር መሠረት የቀረበ መቃወሚያ የሥራ አስኪያጅ ሥልጣን አንድ ቅርንጫፍ ወይም ወኪል ጽሕፈት ቤት በማስተዳደር ብቻ የተወሰነ መሆኑ የሥራ አስኪያጅ መሻር አንቀጽ የሦስተኛ ወገኖች መብት ሊነኩ የማይችሉ የንግድ ድርጅቶችን የሚመለከቱ ጉዳዬች በንግድ መዝገቡ ባለመመዝገባቸው በሶስተኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሊሆኑ የማይችሉ የንግድ ማህበራትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ በዚህ ህግ ሁለተኛው መፅሀፍ የተመለከቱት ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ በህግ ስለሚወሰኑ ጉዳዮች የዚህ ህግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አሰጣጥን ስረዛን መልሶ ምዝገባና ሌሎች የሚመለከቱ ዝርዝር ጉዳዮች በህግ ይወሰናሉ ርዕስ አምስት ስለንግድ መደብር ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌ አንቀጽ ትርጓሜ የንግድ መደብር በዚህ ሕግ አንቀፅ በ ከተጠቀሱት የንግድ ሥራዎች አንዱን ለማካሄድ የተሰባሰበና የተደራጀ ማናቸውም ግዙፍነት የሌለው ተንቀሳቃሽ ንብረት ነው አንቀጽ ነጋዴና የንግድ መደብር ማንኛውም ነጋዴ የንግድ መደብር ሥራን ያካሄዚዳል የተለያየ የንግድ ሥራዎችን ለማከናወን እንዲቻል በርካታ የንግድ መደብሮች ሥራዎችን ሊያንቀሳቅስ ይችላል አንድን የንግድ መደብር በባለቤትነት በአላባ ተጠቃሚነት ወይም በተከራይነት ሊያካሂድ ይችላል አንደ ነጋዴ የሚቆጠረው የንግድ መደብሩን የሚያካሂደው ሰው ሲሆን ባለቤቱ ወይም አከራዩ ነጋዴ ሊባል አይችልም አንቀጽ ስለ ዋና የንግድ መደብርና ቅርንጫፎች ወይም ወኪል ጽህፈት ቤቶች አንድ የንግድ መደብር አንድ ዋና መደብር ብቻ ወይም ዋና የንግድ መደብርና ቅርንጫፍ ወይም ወኪል ጽህፈት ቤት ሊኖረው ይችላል የንግድ መደብር ሌሎች ግዙፍነት የሌላቸው ነገሮች በተለይም ዋናው የንግድ መደብር ሳይሆን አንድ ቅርንጫፍ ወይም ወኪል ጽህፈት ቤት የተሸጠ ወይም በኪራይ የተሰጠ እንደሆነ እንደ ንግድ መደብር መሸጥ ወይም መከራየት ይቆጠራል የዚሁ የንግድ መደብር ዋና መሥሪያ ቤት ገዥው ወይም ተከራዩ የሚያንቀሳቅሰው የቅርንጫፍ ወይም የወኪል ጽህፈት ቤት ሥራ በሚያከናውንበት ቦታ ይሆናል ምዕራፍ ሁለት የንግድ መደብር የሚይዛቸው ነገሮች ክፍል አንድ የንግድ መደብር አካላት አንቀጽ ስለነጋዴው መልካም ስምና ግዙፍነት ስለሌላቸው ነገሮች የንግድ መደብር በዋነኛነት የነጋዴውን መልካም ስም ይይዛል የንግድ መደብር ሌሎች ግዙፍነት የሌላቸው ነገሮች በተለይም ሀ የንግድ ስም ለ የንግድ ምልክትና ሌላ የንግድ ስራ የሚካሄድበት ልዩ መገለጫ ሐ የንግዱ ሥራ የሚከናወንበትን ቦታ የማከራየት መብት መ የፓተንት ወይም የቅጂና ተዛማች መብት ሠ ከነጋዴው ጋር ሳይሆን ከንግድ መደብሩ ጋር የተያያዙ ሌሎች ልዩ መብቶች ሊይዝ ይችላል አንቀጽ ግዙፍነት ስላላቸው ነገሮች የንግድ መደብር ግዙፍነት ያላቸው እንደ መሣሪያዎች ወይም ዕቃዎችና ሸቀጣ ሸቀጦች የመሳሰሉትን ነገሮች ሊይዝ ይችላል አንቀጽ ገንዘብ የመጠየቅ መብቶችና ዕዳዎች የንግድ መደብር የንግድ ሥራ የሚከናወንበትን ቦታ ከማከራየት መብት በስተቀር የነጋዴውን የገንዘብ መጠየቅ መብትና ዕዳን አይጨምርም የዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ ድንጋጌ ቢኖርም አግባብ ባለው ህግ የንግድ ድርጅቶች በሚተላለፉበት ጊዜ ሰራተኞች ስለሚኖራቸው መብት እንዲሁም በዚህ ሕግ አንቀጽ እና አንቀጽ የተደነገጉት እንደተጠበቁ ናቸው ሳሙኤል ግርማ የሕግ አማካሪና ጠበቃ ጠህ ቨፐበ ርበህዚበ። በ ልቪዐቦጠፍሃ ፆ«ሇሙጭ አንቀጽ ኩባንያው የሚፈርስባቸዉ ምክንያቶች በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከቱት ጠቅላላ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕዝብ ኩባንያ በሚከተሉት ምክንያቶች ይፈርሳል ሀ የአባላት ቁጥር በሕግ ከተፈቀደው ዝቅ ሲልና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሌላ አባል መተካት ባለመቻሉ ምክንያት ጥቅም አለኝ በሚል ሰው ጠያቂነት የንግድ ማህበር መዝጋቢው አካል ኩባንያው እንዲፈርስ ሲወስን ለ የአስተዳደር አካላት የሌሉት በመሆነ ምክንያት ጥቅም አለኝ በሚል ሰው ጠያቂነት የንግድ ማህበር መዝጋቢው አካል ኩባንያው እንዲፈርስ ሲወስን ሐ ኩባንያው የዋና ገንዘቡን ሶስት አራተኛ በኪሳራ ሲያጣ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሀ እና ለ ድንጋጌዎች ቢኖሩም የንግድ ማኀበር መዝጋቢው አካል አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የጊዜ ገደቡን ለተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ወይም ኩባንያው የአስተዳደር አካላትን አሟልቶ ሥራ እንዲቀጥል ሊፈቅድ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሐ እንደተመለከተው ኩባንያው የዋና ገንዘቡን ሶስት አራተኛ በኪሳራ ያጣ እንደሆነ የዳሬክተሮች ቦርድ የኩባንያውን መፍረስ ወይም መቀጠል የሚወስን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ መጥራት አለበት የዳይሬክተሮች ቦርድ የሚኖር ከሆነ የተቆጣጣሪ ቦርድ ወይም ኦዲተሮች ጠቅላላ ጉባኤ መጥራት ያልቻሉ እንደሆነ ጥቅም ባለው ሰው አመልካችነት ፍርድ ቤት ኩባንያው እንዲፈርስ ሊወስን ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተደነገገው መሠረት የንግድ ማኀበር መዝጋቢውን አካል ሳያስፈቅዱ ከስድስት ወራት በላ ባለአክሲዮኞች እያወቁ ኩባንያው ሥራውን እንዲቀጥል ያደረጉ ከሆነ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ኩባንያው ለሚገባው ማንኛውም ዕዳ በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ ይሆናሉ አንቀጽ የኩባንያውን መፍረስ ስለማስታወቅ በዚህ ሕግ መሠረት ኩባንያው እንዲፈርስ በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ወይም በፍርድ ቤት የተወሰነ እንደሆነ የመፍረሱ ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በ ቀናት ውስጥ ኩባንያው አንዲፈርስ ስለመወሰኑ ሰፊ ስርጭት ባለው ጋዜጣና በኩባንያው ድረ ገጽ በይፋ መገለጽ አለበት ማስታወቂያውም በመጣራት ላይ ያለ የሚል ሀረግ ተጨምሮበት የኩባንያውን ስም የዋና ገንዘቡን መጠን የፈረሰበትን ምክንያት የሒሳብ አጣሪውን ስምና አድራሻ አንዲሁም የስልጣን ወሰን መያዝ አለበት ኩባንያው እንዲፈርስ የተሰጠው ውሳኔ እና በውሳኔው መሠረት ሒሳብ አጣሪ መሾሙን የሚያመለክቱ ሰነዶች በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት መቀመጥ እንዲሁም በንግድ መዝገብ መመዝገብ አለባቸው አንቀጽ ሒሳብ አጣሪ ስለመሾምና ስለመሻር ሂሳብ አጣሪዎች በመመስረቻ ጽሑፍ ያልተሾሙ ከሆነ የኩባንያውን መፍረስ በወሰነው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ይሾማሉ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተደነገገው መሰረት ሒሳብ አጣሪዎች ያልተሾሙ ከሆነ በዳይሬክተሮች ቦርድ በተቆጣጣሪ ቦርድ በኦዲተሮች በባለአክሲዮኖች ወይም በገንዘብ ጠያቂዎች አቤቱታ አቅራቢነት በፍርድ ቤት ይሾማሉ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት የተሾሙ ሒሳብ አጣሪዎች በጠቅላላ ጉባኤው ሊሻሩ ይችላሉ እንዲሁም በማንኛወም አካል ቢሾሙ ሒሳብ አጣሪዎች በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተጠቀሱት ሰዎች አመልካችነት በበቂ ምክንያት ፍርድ ቤት ሊሽራቸው ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተደነገገው መሰረት ሒሳብ አጣሪዎችን የሻረው አካል አዲስ አጣሪዎችን መሾም አለበት አንቀጽ የሒሳብ አጣሪዎች ሥራ መልቀቅ የኩባንያው ሒሳብ አጣሪዎች ለሾማቸው አካል የሶስት ወራት የቅድሚያ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሥራቸውን መልቀቅ ይችላሉ አጣሪዎች የተሾሙት በጠቅላላ ጉባኤ ወይም በመመስረቻ ጽሑፍ ከሆነ ማስጠንቀቂያውን ለኩባንያው ቦርድ ማቅረብ አለባቸው ሂሳብ አጣሪዎች በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሰረት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጡ ሥራቸውን የለቀቁ እንደሆነ በዚህ ምክንያት በኩባንያው ላይ ለሚደርሰው ጉዳት በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ ይሆናሉ አንቀጽ ለሒሳብ አጣሪነት ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች ሒሳብ አጣሪ ሆኖ መሾም የሚችለው ቀጥሎ የተመለከቱትን መስፈርቶች የሚያሟላ ሰው ነው መልካም ስነምግባር ያለው የሒሳብ ማጣራት ሥራ ለማከናወን አስፈልጊ የሆነ ሙያ ያለው በንግድ ኩባንያ አደራጀነት ዳይሬክተርነት ሥራ አስኪያጅነት በተቆጣጣሪነት በኦዲተርነት ወይም በሌሎች የአመራር ኃላፊነቶች ላይ ተመድቦ ሲሰራ ከኃላፊነቱ ጋር በተያያዘ ወይም በማንኛውም ሁኔታ የዕምነት ማጉደል የስርቆትየውንብድና ወንጀል ወይም ለሂሳብ አጣሪነት ብቁ የማያደርግ ተመሳሳይ ወንጀል ፈፅሞ ጥፋተኛነቱ ያልተረጋገጠ አንቀጽ የሒሳብ አጣሪዎች የሥራ ዋጋ ሒሳብ አጣሪዎች ለሚሰጡት አገልግሉት የሥራ ዋጋ ይከፈላቸዋል የሥራ ዋጋ ክፍያው በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት በሚሾማቸው አካል ይወሰናል አንቀጽ ሒሳብ በሚጣራበት ጊዜ የኩባንያው ሕጋዊ ሰውነት ቀጣይነት ሒሳብ ማጣራቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ኩባንያው ከስያሜው ቀጥሎ በመጣራት ላይ ያለ የሚል ሐረግ ተጨምሮበት ሕጋዊ ሰውነቱን እና ስሙን እንደያዘ ይቀጥላል ሒሳብ በሚጣራበት ጊዜ የኩባንያው አስተዳደር አካላት ለማከናወን የሚችሉት ለማጣራቱ ሥራ አስፈላጊ የሆኑ እና ከአጣሪው ሥልጣን ውጭ የሆኑ ሥራዎችን ብቻ ነው አንቀጽ የከሰረ ኩባንያ ሂሳብ ስለሚጣራበት ሁኔታ የኩባንያው መክሰር በፍርድ ቤት የተወሰነ እንደሆነ ሒሳብ መጣራቱ ኪሳራን በሚመለከቱት የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ይፈጸማል የኩባንያው ዳይሬክተሮች ኩባንያውን ለመወከል ሥልጣን የሚኖራቸው ለሥራው አስፈልጊ በሆነ መጠን ብቻ ነው አንቀጽ የሒሳብ አጣሪዎች ግዴታና ኃላፊነት በሕግ ወይም በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር የሒሳብ አጣሪዎች ግዴታና ኃላፊነት የዳይሬክተሮች ቦርድ ዓይነት ይሆናል ሒሳብ አጣሪዎች የኩባንያውን ንብረቶችና የሒሳብ መዝገቦች ይረከባሉ የዳይሬክተሮች ቦርድ ከመጨረሻው የበጀት ዓመት ማብቂያ ሒሳብ መጣራቱ አስከተጀመረበት ጊዜ ያለውን የኩባንያው አስተዳደር የሚመለከት የሥራ ሪፖርት ለሒሳብ አጣሪዎች ያቀርባል ሒሳብ አጣሪዎችና የዳይሬክተሮች ቦርድ የኩባንያውን ሀብትና ዕዳዎች የያዘ ዝርዝር መዝገብ በጋራ አዘጋጅተው ይፈርማሉ ኩባንያው ያለው ገንዘብ ፅዳዎችን ለመክፈል በቂ ካልሆነ ሒሳብ አጣሪዎች ባለአክሲዮኖች ያልከፈሉት የአክሲዮን ድርሻ ካለ ማስከፈል ይኖርባቸዋል አንቀጽ የሒሳብ አጣሪዎች ሥልጣን እና ኃላፊነት በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ ወይም በሾማቸው ጉባኤ የተጣሉ ገደቦች ካሉ እንደተጠበቁ ሆኖ ሒሳብ አጣሪዎች የማጣራቱን ሥራን ለማከናውን ሙሉ የሆነ ሥልጣን ይኖራቸዋል በተለይም የኩባንያውን ሀብት ለመሸጥ በፍርድ ቤት ለመወከል ክርክር የሚያስነሱ ጉዳዮችን በስምምነት ወይም በግልግል ለመጨረስ የኩባንያውን ገንዘብ ለመሰብሰብ እና ዕዳዎችን ለመክፈል ይትላሉ ሒሳብ አጣሪዎች ቀደም ሲል የነበሩ ውሎችን ለማስፈጸም ካልሆነ ወይም የሒሳብ ማጣራቱ ሥራ ካላስገደደ በስተቀር አዲስ ሥራዎችን መጀመር አይችሉም ሒሳብ አጣሪዎች በሕግ በመመስረቻ ጽሑፍ ወይም በባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ከተሰጣቸው ስልጣን ውጭ በመስራታቸው በኩባንያው ወይም በሦስተኛ ወገኖች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት በአንድነትና በነጠላ ኃላፊ ይሆናሉ አንቀጽ ከዕዳ ክፍያ በፊት የንብረት ክፍፍል ማድረግ የተከለከለ ስለመሆኑ ሒሳብ አጣሪዎች የኩባንያውን ገንዘብ ጠያቂዎች ዕዳ ሳይከፍሉ ወይም ለክፍያ የሚያስፈልገው ገንዘብ በፍርድ ቤት ሳይቀመጥ የኩባንያውን ንብረት ለማከፋፈል አይችሉም አንቀጽ ገንዘብ ጠያቂዎችን ስለመጥራትና ክፍያ ስለመፈጸም ስማቸው በሒሳብ መዝገብ ውስጥ የተመለከተ ወይም በሌላ መንገድ ለሚታወቁ ገንዘብ ጠያቂዎች የኩባንያውን መፍረስ በተመዘገበ ደብዳቤ ወይም አስቀድሞ ስምምነት በተደረሰባቸው ሌሎች ዘዴዎች እንዲያውቁት እና የሚጠይቁትን ገንዘብ ሊያስረዱ የሚችሉ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ ይገለጽላቸዋል ሌሎች ገንዘብ ጠያቂዎች በመመስረቻ ጽሑፉ በተመለከተው አኳኋን የኩባንያውን መፍረስ ሰፊ አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ለሦስት ተከታታይ ወራት በወር አንድ ጊዜ እንዲሁም በኩባንያው ድረገጽ ማስታወቂያ በማውጣት እንዲያውቁት ይደረጋል ለኩባንያው ገንዘብ ጠያቂዎች የሚደረገው ክፍያ ሒሳብ አጣሪዎች ሥራቸውን በጀመሩበት ጊዜ ባዘጋጁት የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ መሠረት ይፈጸማል አንቀጽ የገንዘብ ጠያቂዎች መብት ጥበቃ የታወቁ የኩባንያው ገንዘብ ጠያቂዎች ጥያቄያቸውን ለሒሳብ አጣሪዎች ያላቀረቡ ከሆነ የሚከፈላቸው ገንዘብ መጠን በፍርድ ቤት ይቀመጣል ለገንዘብ ጠያቂዎች ተመጣጣኝ ዋስትና ካልተደረገላቸው ወይም ከኩባንያው የሚጠየቁ ግዴታዎች እስከሚፈጸሙ ድረስ የሀብት ክፍፍሉ ካልተላለፈ በስተቀር የመፈጸሚያ ጊዚያቸው ያልደረስ ወይም አከራካሪ የሆኑ ከኩባንያው የሚጠየቁ ግዴታዎችን ለመፈጸም የሚያስችል ተመጣጣኝ ገንዘብ በፍርድ ቤት መቀመጥ ይኖርበታል አንቀጽ የመጨረሻ የፃብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ ሒሳብ አጣሪዎች የኩባንያው ዕዳ ከተከፈለ በኋላ አጣሪዎች ከተረፈው ንብረት ላይ አያንዳንዱ አክሲዮን ከመቶኛ ምን ያህል ሊደርሰው አንደሚችል የሚያሳይ የመጨረሻ የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ ማዘጋጀት አለባቸው በመመስረቻ ጽሑፉ ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ሒሳብ አጣሪዎች የአክሲዮኖቹ ዋጋ ሙሉ በሙሉ መከፈላቸውንና ከአክሲዮኖቹ ጋር የተያያዙ ቀዳሚ መብቶችን ግምት ውስጥ በማስገባት በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ ላይ የተመለከተውን የድርሻ ክፍፍል ይወስናሉ ሒሳብ አጣሪዎች የፈረሙባቸው የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ እና የኦዲተሮች ሪፖርት አግባብ ባለው የመንግስት አካል መቀመጥ አለበት ማንኛውም ባለአክሲዮን የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተደነገገው መሠረት ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት ሦስት ወራት የመጨረሻው የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ ውድቅ እንዲደረግ ተቃውሞውን ለፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል ማመልከቻው የሚታየው የሶስት ወሩ ጊዜ ካለቀ በኋላ ሲሆን ብዙ ማመልከቻዎች ካሉም በአንድነት ይታያሉ ፍርድ ቤቱ በቀረቡት ጉዳዮች ላይ የሚሰጠው ውሳኔ በሌሎች ባለአከሲዮኖች ላይም ተፈጻሚ ይሆናል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ አቤቱታ ያልቀረበ አንደሆነ የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫው እንደጸደቀ ይቆጠራል አንቀጽ የሀብት ክፍፍሉን ስለማቆየት የኩባንያውን ተራፊ ንብረት ለባለአክሲዮኖች ለማከፋፈል የሚቻለው በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሥር የተመለከው ማስታወቂያ አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ለሦስተኛ ጊዜ ከወጣ ከክንድ ዓመት በጊላ ነው ሆኖም ገንዘብ ጠያቂዎች በክፍፍሉ የማይጎዱ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ ካመነ ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት ተራፊው ንብረት ለባለአክሲዮኖች እንዲከፋፈል ሊፈቅድ ይችላል አንቀጽ ያልተወሰደን ገንዘብ ስለማስቀመጥ አንድ ባለአክሲዮን ከተራፊው ንብረት ላይ የሚገባውን ድርሻ በዚህ ህግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የሀብትና ፅዳ ሒሳብ መግለጫ እና የኦዲተሮች ሪፖርት አግባብ ባለው የመንግስት አካል ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት ሦስት ወራት ውስጥ ያልወሰደ አንደሆነ ሒሳብ አጣሪዎች የባላክሲዮኑን ስም ወይም አክሲዮኖቹ ለአምጨው የሆኑ እንደሆነ የአክሲዮኖቹን ቁጥር በመግለጽ ገንዘቡን በልዩ ሒሳብ ባንክ ያስቀምጣሉ አንቀጽ ኩባንያውን ከንግድ መዝገብ ስለመሰረዝ የመጨረሻው የሀብትና ዕዳ ሒሳብ መግለጫ ከፀደቀ በኋላ ሒሳብ አጣሪዎች ኩባንያው ከንግድ መዝገብ እንዲሰረዝ ማድረግ ይኖርባቸዋል አንቀጽ የገንዘብ ጠያቂዎች መብት በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ኩባንያው ከንግድ መዝገብ ከተሰረዘ በኋላ የሚመጡ ገንዘብ ጠያቂዎች ባለአአክሲዮኖች ከተራፊው ንብረት በደረሳቸው መጠን እንዲከፍሏቸው መጠየቅ ይችላሉ ገንዘብ ጠያቂዎቹ ያልተከፈላቸው በአጣሪዎች ቸልተኝነት ከሆነ ከሂሳብ አጣሪዎች ላይ መብታቸውን መጠየቅ ይትላሉ አንቀጽ የኩባንያውን መዝገቦች ጠብቆ ስለመያዝ የፈረሰው ኩባንያ የሒሳብ መዛግብት ለ ዓመታት አግባብ ባለው የመንግስት አካል ተጠብቀው መቀመጥ አለባቸው ማንኛውም ሰው የሂሳብ መዝገቦችን ለመመርመር ይችሳላል ምዕራፍ አስር ስለድረገፅ አንቀጽ ድረገጽ ስለማቋቋም ኃላፊነቱ የተወሰነ የህዝብ ኩባንያ ድረ ገጽ ሊኖረው ይገባል አንቀጽ ድረገፅ ላይ ስለሚገለፁ ነገሮች የሚከተሉት መረጃዎች በወቅቱ ድረገፅ ላይ መውጣት ይኖርባቸዋል ሀ የኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍና ካሉም ማሻሻያዎቹ ለ ጠቅላላ ጉባኤውን የሚመለከቱ የስብሰባ ጥሪዎችና ተያያዥ መረጃዎች ሐ የኩባንያው የስራ አፈጻጸምና የፋይናንስ ሪፖርቶች የኦዲት ሪፖርቶች መ ሴሎች በዚህ ሕግ ወይም በመመስረቻ ጽሑፍ መሰረት በይፋ መገለጽ ያለባቸው መረጃዎች ሠ ለባለአክሲዮኖች ገንዘብ ጠያቂዎችና ባለድርሻ አካላት አስፈላጊ የሆነ ሌላ ማንኛውም መረጃ ድረገጹ የኤሌክትሮኒክ ጉባኤ ለማድረግና በኤሌክትሮኒክ መንገድ ድምጽ ለመስጠት የሚቻልበትን ሁኔታ ማካተት አለበት አንቀጽ መረጃዎች በድረገፁ ላይ ስለሚቆዩበት ጊዜ የሚከተሉት መረጃዎች በድረገጹ ላይ ከወጡበት ቀን ጀምሮ ሀ የስብሰባ ጥሪና ተያያዥ መረጃዎች ስብሰባው እስከሚጠናቀቅበት ፅለት ድረስ ለ የሂሳብ ሰነዶች ለአምስት አመታት ሐ ሌሎች መረጃዎች ለስድስት ወራት መቆየት አለባቸው ድሕረገጹ ለማንኛም ሰው ተደራሽ መሆን ይኖርበታል ኩባንያው የድረገፁን ደህንነት ለመጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል ርዕስ ሰባት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ ትርጓሜ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ማለት ዋና ገንዘቡ አስቀድሞ የተወሰነ በአክሲዮን የተከፋፈለና አክሲዮኑ ለህዝብ ክፍት ያልሆነ አንዲሁም ባለአክሲዮኖች ከከፈሉት መዋጮ በላይ ኃላፊ የማይሆኑበት የንግድ ማኀበር ነው የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ቁጥር ከአንድ እስከ ሰዎች ነው ኩባንያው የሚተላለፉ የግዴታ ወረቀቶችን ማውጣት አይችልም አንቀጽ የኩባንያው ዋና ገንዘብ የኩባንያው አነስተኛ ዋና ገንዘብ መጠን እና የአንዱ አክሲዮን ዋጋ እንደ ኩባንያው ዓላማ በየጊዜው እየታየ በደንብ ይወሰናል የሁሉም አክሲዮኖች ዋጋ እኩል መሆን አለበት አንቀጽ የኩባንያው ስም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የንግድ ዓላማውን የሚገልጽ ስም ይኖረዋል ከኩባንያው ስም ቀጥሎ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሚለው ሐረግ መጻፍ አለበት ሆኖም ኩባንያው አንድ ባለአክሲዮን ብቻ ያለው ከሆነ ከኩባንያው ስም ቀጥሎ ኃላፊነቱ የተወሰነ ባለአንድ ባለአክሲዮን የግል ኩባንያ የሚለው ሐረግ መጨመር አለበት አንቀፅ የባለ አክሲዮኖች ቁጥር ወደ አንድ ዝቅ ያለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የባለአክሲዮኖቹ ቁጥር ወደአንድ ዝቅ ካለ እና ሌላ ሰው በባለአክሲዮንነት ካላስገባ እና ቀሪው ባለአክሲዮን በብቸኝነት መቀጠል ከፈለገ የባለአክሲዮኖች ቁጥር ወደክንድ ዝቅ ካለበት ቀንጀምሮ በስድስት ወራት ውስጥ የመመስረቻ ፅሁፉን በማሻሻል ለመዝጋቢው አካል ማቅረብ ይኖርበታል ኩባንያው በብቸኛ ባለአክሲዮን ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ስሙ ኃላፊነቱ የተወሰነ ባለአንድ ባለአክሲዮን የግል ኩባንያ በሚል መሻሻል ይኖርበታል ምዕራፍ ሁለት የኩባንያው ምስረታ አንቀጽ ለኩባንያው ምስረታ የሚያስፈልጉ ጠቅላላ ሁኔታዎች ማንኛውም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሚመሠረተው ዋና ገንዘቡ በሙሉ ሲከፈል እና መመስረቻ ጽሑፉ በሕግ ሥልጣን በተሰጠው አካል ሲረጋገጥ ነው አንቀጽ የመመስረቻ ጽሑፉ ይዘት የኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ የሚከተሉትን መያዝ አለበት የባለአክሲዮኑን ወይም የባለአክሲዮኖችን ስም ዜግነትና አድራሻ የኩባንያውን ስም ዋና መስሪያ ቤትአእንዳሉም ቅርንጫፎቹን የኩባንያውን የንግድ ዓላማ የኩባንያውን ዋና ገንዘብ መጠን አና ይኸው በሙሉ የተከፈለ መሆኑን የሚያሳይ መግለጫ እያንዳንዱ ባለአክሲዮን የከፈለውን የገንዘብ መጠን በዓይነት የተከፈለ መዋጮ ካለ ግምቱን አያንዳንዱ ባለአክሲዮን የያዘውን የአክሲዮን ብዛት የትርፍ አከፋፈል ሥርዓት ዳይሬክተሮች ካሉት ብዛታቸውንና ሥልጣናቸውን የሥራ አስኪያጆችን ቁጥርና ሥልጣናቸውን አዲተሮች ካሉ ብዛታቸውን ኩባንያው የሚቆይበትን ጊዜ ኩባንያው የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የሚያስታውቅበትን መንገድና ጊዜ አንዲሁም በኩባንያው ሥራ አመራር በኩባንያውና በአባላት ወይም በአባላት መካከል ያለውን ግንኙነት የሚመለከቱ ጉዳዮችን ሌሎች በሕግ ወይም በባለአክሲዮኖች ስምምነት እንዲካተቱ የተወሰኑ ጉዳዮችን አ አንቀጽ የኩባንያው መዋጮ ከሙያ አገልግሎት በስተቀር ሌሎች በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከቱት የገንዘብና ሌሉች የዓይነት መዋጮዎች ኃላፊነቱ ለተወሰነ የግል ኩባንያም ተፈጻሚነት አላቸው አንቀጽ በዓይነት የተከፈለ መዋጮ ግምት ባለ አክሲዮን በዓይነት መዋጮ የከፈለ እንደሆነ የመመስረቻ ጽሑፉ የመዋጮውን ዓይነትና ዋጋሌሉሎች ባለአክሲዮኖች የተቀበሉበትን ዋጋ እና ከኩባንያው ዋና ገንዘብ ውስጥ በዓይነት ለከ የዓ በዓ ፈለው ባለአክሲዮን የተሰጠውን የአክሲዮን ድርሻ መጠን ማሳየት አለበት ይነት መዋጮ የሚገመትበት መንገድ በባለአክሲዮኖች ይወሰናል ይነት የተከፈለ መዋጮ በተከፈለበት ጊዜ ለተደረገው ግምት ባለአክሲዮኖቹ ሁሉ ለሦስተኛ ወገኖች በአንድነትና በተናጠል ኃላፊዎች ይሆናሉ በዓይነት የተከፈለ መዋጮ ግምት ከዋጋው በላይ ሆኖ ከተገኘ ያዋጣው ባለአክሲዮን በግምቱና በትክክለኛ ዋጋ መካከል ያለውን ልዩነት በጥሬ ገንዘብ መክፈል አለበት ከዋጋው በላይ ስለመገመቱ ባያውቁም እንኳ ባለአክሲዮኖች ለዚህ ገንዘብ መከፈል በአንድነትና በተናጠል ኃላፊዎች ይሆናሉ ምዕራፍ ሦስት ስለአክሲዮኖችና የባለአክሲዮኖች መብትና ግዴታ አንቀጽ የአክሲዮኖች ዓይነት ኩባንያው ማውጣት የሚችለው ስም የተመዘገበባቸው አክሲዮኖችን ብቻ ነው አንቀጽ በመያዣ ወይም በአላባ ስለሚሰጡ አክሲዮኖች ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር አክሲዮን በመያዣ ወይም በአላባ የተሰጠ አንደሆነ በኩባንያው ጉባኤዎች ድምፅ የመስጠት መብት የሚኖረው አክሲዮኑን በመያዣ ወይም በአላባ የሰጠው ሰው ብቻ ነው አንቀጽ የአክሲዮን ምስክር ወረቀት ስለሚይዛቸው ነገሮች አያንዳንዱ አክሲዮን የሚከተሉትን መያዝ አለበት የአክሲዮኑ መለያ ቁጥር ቅደም ተከተል ዓይነት አክሲዮኑ መደበኛ ወይም ልዩ መብት የሚሰጥ ስለመሆኑ ልዩ መብት የሚሰጥ ከሆነ የመብቱን ዓይነት ኩባንያው ቦርድ ካለው የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ከሌለው ደግሞ የሥራ አሲኪያጁን ፊርማ የኩባንያውን ስም ዋና መስሪያ ቤትና ኩባንያው የሚቆይበትን ጊዜ የኩባንያውን ዋና ገንዘብና አክሲዮኑ የወጣበትን ዋጋ መጠን የኩባንያው መመስረቻ ጽሑፉ የተፈረመበትን ቀን ኩባንያው በንግድ መዝገብ የተመዘገበበትን ቀንና ቦታ ሌሎች አስፈላጊ የሆነ መረጃዎችን አንቀጽ ስለአክሲዮኖች መዝገብ የኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት የሚከተሉትን የአክሲዮኖች ዝርዝር በአክሲዮን መዝገብ መያዝ አለበት ሀ የባለአክሲዮኖችን ስምና አድራሻ የእያንዳንዱን ባለአክሲዮን ድርሻ እና የአክሲኖችን መለያ ቁጥር ለ የሚደረግ የአክሲዮን ትልልፍ ሐ በእነዚህ ዝርዝሮች ላይ የተደረገውን ማንኛውም ማሻሻያ የኩባንያው ዳይሬክተሮች ቦርድ ካለ ሰብሳቢው ወይም ዳይሬክተር ከሌለ ደግሞ ስራ አስኪያጁ የአክሲዮን መዝገቡ የመጨረሻ ዝርዝር ከተቀመጠ ጀምሮ የተለወጠ ነገር የለም ብሉ ካላስታወቀ በስተቀር በየዓመቱ መጀመሪያ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሀ እና ለ የተመለከቱትን መረጃዎች የያዘ ዝርዝር በቦርዱ ሰብሳቢ ወይም ዳይሬክተር ከሌለ ደግሞ በሥራ አስኪያጁ አግባብ ላለው የመንግስት አካል መላክ አለበት ባለአክሲዮኖች መዝገቡን በነዓ መመልከት ወይም የመዝገቡን ግልባጭ መውሰድ ይችላሉ ኩባንያውም ጥያቄው በቀረበ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ግልባጩን ለጠያቂው መስጠት አለበት ማንኛውም ሦስተኛ ወገን መዝገቡን መመልከት ይችላል አንቀጽ አክሲዮኖችን ስለማስተላለፍ በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር አክሲዮኖች በባለአክሲዮኖች መካከል ያለገደብ ሊተላለፉ ይችላሉ በመመስረቻ ጽሑፉ ላይ የበለጠ የድምጽ ብልጫ ወይም ሙሉ ድምጽ እንደሚያስፈልግ ካልተወሰነ በስተቀር የኩባንያው አባል ላልሆኑ ሰዎች የሚደረገው የአክሲዮን ትልልፍ ተፈጻሚ የሚሆነው ከኩባንያው ዋና ገንዘብ ቢያንስ ሦስት አራተኛ ድርሻ ካላቸው ባለአክሲዮኖች የአብላጫውን የድምጽ ድጋፍ ሲያገኝ ነው ውሳኔውም በንግድ መዝገብ ላይ መመዝገብ አለበት ኩባንያው በመጣራት ላይ ቢሆንም የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንንቀጽ ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል የኩባንያው ባለአክሲዮን ያልሆነ ሰው የአንዱን ባለአክሲዮን ድርሻ በፍርድ አፈጻፀም ያገኘ አንደሆነ የኩባንያው ባለአክሲዮን ለመሆን በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሰረት የሌሎችን ባለአክሲዮኖች ድጋፍ ማግኘት አለበት የኩባንያው ባለአክሲዮኖች በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው ካልተስማሙ ከአባላት መካከል ለመግዛት ፍላጎት ላለው አባል በሸያጭ ያስተላልፋል ለመግዛት ፍላጎት ያለው ባለአክሲዮን ካልተገኘ ኩባንያው ለፍርድ ባለመብቱ የአክሲኖቹን ዋጋ ይከፍለዋል ዋና ገንዘቡም በዚህ ልክ እንዲቀንስ ይደረጋል የኩባንያው አክሲዮኖች ዝውውር በጽሑፍ መሆን አለበት ዝውውሩ በአክሲዮን መዝገብ ላይ ካልተመዘገበ በስተቀር በኩባንያውና በሦስተኛ ወገኖች መቃወሚያ ሊሆን አይችልም አንቀጽ አክሲዮኖችን በውርስ ስለማግኘት በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር አንድ ባለአክሲዮን ሲሞት ወራሾቹ ባለአክሲዮን ሊሆኑ ይችላሉ ሆኖም በባለአክሲዮንነት የማይቀጥሉ የሆነ እንደሆነ በመጨረሻው የንብረት ዝርዝር መዝገብ መሰረት የሟቹ የአክሲዮን ድርሻ እንዲከፈላቸዉ ይደረጋል አንቀጽ ተፈጻሚነት ስላላቸው ድንጋጌዎች በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ ድረስ የተመለከቱት ድንጋጌዎች ለዚህ ምዕራፍና እንደአግባብነታቸው ተፈጻሚነት አላቸው ምዕራፍ አራት የኩባንያው ሥራ አመራር አንቀጽ የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በዳይሬክተሮች ቦርድ እንዲመራ በመመስረቻ ጽሑፍ ሊወሰን ይችላል የዳይሬክተሮች ቦርድ የሚኖር ከሆነ የአባላቱ ቁጥር ከአንድ አስከ ሰባት ይሆናል በዚህ ሕግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕዝብ ኩባንያ የቦርድ አባላት ሹመት ስለሚገቡት ዋስትና መሻር የስራ ዘመን ውሳኔ አሰጣጥ ተጠያቂነት የአገልግሎት ክፍያ ስልጣንና ተግባር እና ሌሎች አግባብነት ያላቸው በዚህ ሕግ የአንቀጽ ንዑስ አንቀፅ ንዑስን አንቀፅ ድንጋጌዎች ለኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ዳይሬክተሮች ቦርድ እንደ አግባብነታቸው ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ ስለ ኩባንያው ሥራ አስኪያጅ ኩባንያው ባለአክሲዮን ወይም ባላክሲዮን ያልሆነ በጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ የሚሾም አንድ ወይም ከዚያ በላይ ሥራ አስኪያጅ ይኖረዋል ኩባንያው በዳይሬክተሮች ቦርድ እንዲተዳደር በመመስረቻ ጽሑፍ የተወሰነ አንደሆነ ሥራ አስኪያጁ የሚሾመው በቦርዱ ይሆናል ሥራ አስኪያጁ የቦርድ አባል ሊሆን አይችልም ሥራ አስኪያጁ የኩባንያው ተቀጣሪ ነው አንቀጽ የስራ አስኪያጁ ስልጣን ኩባንያው በቦርድ የሚተዳደር ከሆነ ስለስራ አስኪያጅ ሥልጣን በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ አንደ አግባብነቱ ተፈጻሚ ይሆናል ኩባንያው ቦርድ የሌለው ከሆነ ሥራስኪያጁ የኩባንያውን ዓላማ ለማሳካት በኩባንያው ስም ለመስራት ሙሉ ስልጣን ይኖረዋል በኩባንያው መመስረቻ ጽሑናፍ ላይ የሥራ አስኪያጁን ሥልጣን የሚገድቡ ተቃራኒ ስምምነቶች በባለአክሲዮኖችና በሥራ አስኪያጁ መካከል ካልሆነ በስተቀር ውጤት አይኖራቸውም አንቀጽ የስራ አስኪያጁ ተጠያቂነት ተቃራኒ ስምምነት ቢኖርም ሥራ አስኪያጁ በዚህ ሕግ ወይም በመመስረቻ ጽሑፍ የተመለከቱ ድንጋጌዎችን በመተላለፍ ለሚያደርሰው ጉዳት ለኩባንያው ለባለአክሲዮኖች እና ለሦስተኛ ወገኖች ኃላፊ ነው ሥራ አስኪያጆች ከአንድ በላይ በሆኑ ጊዜ ለፈጸሙት ጥፋት በአንድነትና በተናጠል ኃላፊዎች ይሆናሉ ኩባንያው ሲከስር ንብረቱ ዕዳውን ለመክፈል በቂ ሆኖ ያልተገኘ እንደሆነ በከሰረው ኩባንያ ንብረት ጠባቂ አመልካችነት ፍርድ ቤት የኩባንያው ስራ አስኪያጅ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲከፍል ለመወሰን ይችሳላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው በኩባንያው አስተደደር ውስጥ ባልተካፈሉ ባለአክሲዮኖች እንዲሁም ተገቢውን ጥንቃቄና ትጋት መፈፀማቸዉን ባስረዱ ስራ አስኪያጆች እና ባለአክሲዮኖች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም አንቀጽ ሥራ አስኪያጁን ስለመሻር ሥራ አስኪያጁ ሊሻር የሚችለው በሾመው አካል ነው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ቢኖርም በቂ ምክንያት አለ ብሎ ሲያምን ማንኛውም ባለአክሲዮን በሚያቀርበው ጥያቄ መሠረት ፍርድ ቤት ስራ አስኪያጁን ሊሽረው ይችላል በተሻረው ምትክ ሌላ ስራ አስኪያጅ እስኪሾም ድረስ ያለ ከሆነ እንደቅደም ተከተላቸዉ ሌላኛው ስራ አስኪያጅ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወይም የዳይሬክተሮች ቦርዱ ተክቶ ይሠራል አንቀጽ ስለኦዲተር የገንዘብ ዝውውራቸዉ ወይም የሂሳብ ሚዛናቸዉ አግባብ ባለው የመንግስት አካል ከሚወሰነው መጠን በላይ የሆነ ኃላፊነታቸዉ የተወሰነ የግል ኩባንያዎች ኦዲተር መሾም አለባቸዉ በቢህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ የተመለከቱ ድንጋጌዎች እንደ አስፈላጊነታቸው ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ኦዲተሮችን በሚመለከት ተፈጻሚነት አላቸው አንቀጽ ባለአንድ ባለአክሲዮን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ተሰያሚ ባለአንድ ባለአክሲዮን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በብቸኛው ባለአክሲዮን ሞትችሎታ ማጣት ወይም በሌላ ተመሳሳይ ምክንያት ክፍተት እንዳይፈጠር ህጋዊ ባለመብት ኩባንያውን እስከሚረከብ ድረስ ባለአክሲዮኑ የሚያከናውነውን ስራ የሚሰራ ሰው ባለ አክሲዮኑ መሰየም ይኖርበታል ባለአክሲዮኑ የሰየመበትን አና ተሰያሚው ፈቃዱን የገለፀበት የፅሁፍ ማስረጃ ከመመስረቻ ፅሁፉ ጋር ለመዝጋቢው አካል ኩባንያው ሲቋቋም መቅረብ ይኖርበታል ባለአክሲዮኑ ተሰያሚውን በማናቸውም ጊዜ መቀየር እንዲሁም ተሰያሚው ለባለአክሲዮኑ እና ለኩባንያው የሰላሳ ቀናት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ፈቃዱን ማንሳት ይችላል ተሰያሚው ስራውን ከጀመረ በኋላ በስራው ለመቀጠል ካልፈለገ ወይም ካልቻለ ራሱ ወይም ጥቅም ያለው ሰው በምትኩ ሌላ ሰው እንዲሰየም ለፍርድ ቤት ሊያመለክት ይችላል ተሰያሚው ስራ ላይ በሚቆይበት ጊዜ ለአገልግሎቱ ለስራ አስኪያጅ የሚከፈለውን ክፍያ ያህል ይከፈለዋል ተሰያሚው አንድ የኩባንያ ባለቤት ለኩባንያው እንደሚያደርገው አይነት በጥንቃቄ እና በትጋት መስራት አለበት ተሰያሚው ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ ሊሜደርሰው ጉዳት ተጠያቂ ነው አንቀጽ ተፈጻሚነት ያላቸው ድንጋጌዎች በዚህ ሕግ ከአንቀጽ ከ እስከ ከ አስከ እና ድንጋጌዎችች ለዳይሬክተሮች እንዲሁም ከአንቀጽ እስከ የተመለከቱ ድንጋጌዎች ለዳይሬክተሮች ለስራ አስኪያጅ እና ኦዲተሮች እንደ አግባብነታቸው ተፈፃሚነት አላቸው ምዕራፍ አምስት ስለኩባንያው ጉባኤዎች አንቀጽ የጉባኤ አይነች ባለአክሲዮኖች መደበኛ ወይም አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ይኖራቸዋል አንቀጽ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በየዓመቱ እያንዳንዱ የሒሳብ ዓመት ከተዘጋበት ቀን ጀምሮ ባሉት አራት ወራት ውስጥ ቢያንስ አንድ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ መደረግ አለበት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተወሰነው የአራት ወራት ጊዜ በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ ወይም አግባብ ባለው የመንግስት አካል ውሳኔ እስከ ስድስት ወራት ሊራዘም ይችላል የጉባኤው ጥሪ የዳይሬክተሮች ቦርድ ካለ በቦርዱ ቦርዱ ካልጠራ ወይም ቦርድ ከሌለው በስራ አስኪያጅ እነርሱ ካልጠሩ የሚኖር ከሆነ በኦዲተር መጠራት ይኖርበታል ከኩባንያው ዋና ገንዘብ ቢያንስ አስር በመቶ ድርሻ ባላቸው ባለአክሲዮኖች ጥያቄ ከቀረበለት በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀጽ የተጠቀሰው አግባብ ያለው አካል ተጨማሪ ጉባኤ መጥራት ይኖርበታል በዚህ አንቀጽ ኃላፊነት የተሰጣቸው አካላት ጉባኤውን ለመጥራት ካልቻሉ ወይም ፈቃደኛ ካልሆኑ በማንኛውም ባለአክሲዮን ጠያቂነት ፍርድ ቤት ጠቅላላ ጉባኤውን የሚጠራና የመወያያ አጀንዳ የሚያዘጋጅ ሰው ሊመርጥ ይችላል አንቀጽ ቃለ ጉባኤ የጉባኤዎች ቃለጉባኤ በጽሑፍ መዘጋጀትና በጉባኤው በተገኙ ባለአክሲዮኖች መፈረም አለበት የጉባኤዎቹ ቃለ ጉባኤ በተለይ ከዚህ በታች የተመለከቱትን ጉዳዮች መያዝ አለበት ሀ የጉባኤውን ጥሪ አደራረግ ለ የስብሰባውን ቦታና ቀን ሐ አጀንዳዎችን መ ቦርድ ካለ በጉባኤው የተገኙ የቦርድ አባላትን ስም ሠ በስብሰባው ላይ የተገኙ ባለአክሲዮኖች ብዛትና የምልዓተ ጉባኤውን ቁጥር ረ ለጉባኤው የቀረቡ ሰነዶች ሰ የውይይቱን አጭር ማጠቃለያ የተሰጡት ድምጾች ውጤት እና ቀ ጉባኤው ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች ኩባንያው አንድ አባል ብቻ ያለው በሚሆንበት ጊዜ አጀንዳውንና በአጀንዳው ላይ የሰጠውን ውሳኔ የያዘ ቃለ ጉባኤ በማዘጋጀትና በመፈረም በኩባንያው እንዲቀመጥ ማድረግ አለበት ምልዓተጉባኤው ባለመሟላቱ ምክንያት ጉባኤው ለመሰብሰብ ሳይችል የቀረ እንደሆነ የጉባኤው ሰብሳቢ ይኸው በቃለ ጉባኤ እንዲያዝ ያደርጋል አንቀጽ ያለጉባኤ የሚሰጡ ውሳኔዎች የዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ ቢኖርም የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ በተለየ ሁኔታ ካልወሰነ በስተቀር የጉባኤው መካሄድ በሕግ ወይም በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ መሰረት አስገዳጅ ባልሆነ ጊዜ የጉባኤ ጥሪ ሳይደረግ ለእያንዳንዱ ባለአክሲዮን የውሳኔ ሀሳቦችን ለመላክና በጽሑፍ ወይም በኤሌክትሮኒክ ዘዴ ድምፅ እንዲሰጥ ለማድረግ ይችላል አንቀጽ የባለአክሲዮኖች መብት በኩባንያው መመስረቻ ጽሑፍ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር ማንኛውም ባለአክሲዮን በራሱ ወይም በወኪል አማካኝነት በአካል ወይም በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ በጉባኤው ለመሳተፍ እና ድምጽ ለመስጠት ይችላል እያንዳንዱ ባለአክሲዮን በኩባንያው ውስጥ ባሉት አክሲዮኖች ልክ የድምፅ ብዛት ይኖረዋል አንቀጽ የመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ምልዓተ ጉባኤና አብላጫ ድምፅ ጉባኤ ለማካሄድ ከኩባንያው ዋና ገንዘብ ከግማሽ በላይ የያዙ ባለአክሲዮኖች በስብሰባው ላይ መገኘት አለባቸዉ በመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የሚተላለፉ ውሳኔዎች በጉባኤው ከተገኙት ባለአክሲዮኖች የአብላጫውን ድምፅ ማግኘት አለባቸው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተውን ምልዕተ ጉባኤ በመጀመሪያው ጉባኤ ማግኘት ያልተቻለ እንደሆነ ባለአክሲዮኖች በተመዘገበ ደብዳቤ ወይም በሌላ አመቺ የኤሌክትሮኒክስ ዘዴ በድጋሜ ይጠራሉ ውሳኔውም ባለአክሲዮኖች ከዋና ገንዘቡ ያላቸው ድርሻ ከግምት ውስጥ ሳይገባ በተገኙ አባላት አብላጫ ድምፅ ይተሳላፋል አንቀጽ የአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ምልዓተ ጉባኤና አብላጫ ድምፅ የኩባንያውን ዜግነት ለመለወጥ ወይም የነባር አክሲዮኖችን ዋጋ ከፍ ለማድረግ የሚተላለፍ ውሳኔ የሁሉንም ባለአክሲዮኖች ስምምነት ማግኘት አለበት ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር በመመስረቻ ጽሑፉ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ማሻሻያ ከኩባንያዉ ዋና ገንዘብ ሶስት አራተኛውን ድርሻ ባላቸው ባለአክሲዮኖች የአብላጫውን ድምፅ ድጋፍ ማግኘት አለበት በመመስረቻ ጽሑፉ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች የንግድ ማኅበራትን ለሚመዘግበው የመንግስት አካል መቅረብ አለባቸው አንቀጽ ተፈጻሚነት ያላቸው ድንጋጌዎች የዚህ ሕግ የአንቀጽ ንዑስ አንቀፅ ከንዑስ አንቀፅ እስከ እስከ አስከ እና ድንጋጌዎች አንደ አግባብነታቸው ለዚህ ምፅራፍ ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል ምዕራፍ ስድስት የኩባንያው ሒሳቦች አንቀጽ በሕግ የተወሰነ የመጠባበቂያ ገንዘብ የኩባንያው የመጠባበቂያ ገንዘብ የዋናው ገንዘብ አስር በመቶ እስከሚሆን ድረስ ከትርፉ ቢያንስ አምስት በመቶ በየዓመቱ በመጠባበቂያ ሂሳብ መቀመጥ አለበት አንቀጽ ሐሰተኛ የትርፍ ድርሻ ሐሰተኛ የሆነ የትርፍ ክፍያ የተቀበሉ ባለአክሲዮኖች እንዲመልሱ መጠየቅ ይቻላል ሐሰተኛ የሆነ የትርፍ ክፍያ አንዲመለስ የሚቀርብ ጥያቄ የተከፈለን ሐሰተኛ የትርፍ ክፍያ ክፍያው ከተፈጸመበት ቀን አንስቶ በአምስት አመታት ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል አንቀጽ ተፈጻሚነት ያላቸው ድንጋጌዎች ከአንቀጽ እስከ እና ከአንቀጽ እስከ የተዘረዘሩት የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች እንደ አግባብነታቸው ለዚህ ምዕራፍ ተፈጻሚ ይሆናሉ ምዕራፍ ሰባት የኩባንያው መፍረስና ሒሳብ መጣራት አንቀጽ የመፍረሻ ምክንያቶች በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከቱት ጠቅላላ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በሚከተሉት ምክንያቶች ሊፈርስ ይችላል ሀ አስፈላጊ የሆነ የኩባንያው የአስተዳደር አካል ባለመኖሩ በባለአክሲዮን ወይም በገንዘብ ጠያቂ አግባብ ላለው የመንግስት አካል ኩባንያው አንዲፈርስ ጥያቄ ሲቀርብ ለ ወራሾቹ ኩባንያው እንዲቀጥል ካልፈለጉ በስተቀር ኩባንያው አንድ አባል ብቻ ያለው ከሆነና ይህ አባል ሲሞት በመመስረቻ ጽሑፉ ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር የባለአክሲዮን በፍርድ ችሉታ ማጣት መክሰር ወይም ዕዳን መክፈል ያለመቻል ወይም ሞት ኩባንያውን አያፈርሰውም አንቀጽ የኩባንያው ዋና ገንዘብ ሶስት አራተኛ መጥፋት የኩባንያው ዋና ገንዘብ ሶስት አራተኛ በኪሳራ ሲጠፋ የዳይሬክተሮች ቦርድ ካለ ቦርዱ ወይም ከሌለ ስራ አስኪያጁ ስለ ኩባንያው መፍረስ አለመፍረስ በባለአክሲዮኖች እንዲወሰን ማድረግ አለበት የኩባንያው ሶስት አራተኛ ዋና ገንዘብ መጥፋት ከታወቀበት ጊዜ አንስቶ በ ቦሥሦስት ወራት ውስጥ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው ካልተፈፀመ ጥቅም ያለው ሰው ኩባንያው እንዲፈርስ ለፍርድ ቤት ማመልከት ይችላል አንቀጽ ተፈጻሚነት ያላቸው ድንጋጌዎች በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ የተዘረዘሩት ድንጋጌዎች እንደአግባብነታቸው የኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ መፍረስንና ሒሳብ መጣራትን በሚመለከት ተፈጻሚ ይሆናሉ ርዕስ ስምንት የንግድ ማኀበራት መለወጥ አንቀጽ ጠቅላላ ድንጋጌ አንድ የንግድ ማኀበር ወደሌላ ዓይነት የንግድ ማኀበር መለወጡ የመመስረቻ ጽሑፍ ከማሻሻል በስተቀር በመሰረቱ ሕጋዊ ሰውነት ያለው አዲስ ማኀበር መቋቋሙን አያስከትልም የአንድ ማኅበር መለወጥ እንደነገሩ ሁኔታ በአባላቱ ሙሉ ድምፅ በማኀበሩ መመስረቻ ጽሑፍ ወይም በዚህ ሕግ በተመለከተው አብላጫ ድምጽ ይወሰናል ማንኛውም የማኀበሩ አባል ያለፈቃዱ ግዴታው ከፍ እንዲል ወይም የአባልነት መብቱን በከፊል ወይም በሙሉ እንዲያጣ ማድረግ አይቻልም የማኀበሩ የመለወጥ ውሳኔም ሰፊ ስርጭት ባለው ጋዜጣ እና ማኀበሩ ድረገጽ ካለው በድረገጽ መውጣት አለበት የሶስተኛ ወገኖች መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ማኀበሩ ሲለወጥ የተለወጠበት ማኀበር ዓይነት የሚቋቋምበትን ሁኔታ የሚመለከቱ የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ በማኀበሩ መለወጥ ያልተስማሙ ባለአክሲዮኖች መብት የማኅበሩን መለወጥ ያልተቀበሉ ባለአክሲዮኖች በዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ መሰረት ድርሻቸውን ለማኀበሩ ሸጠው ከማኀበሩ መውጣት ይችላሉ አንቀጽ የገንዘብ ጠያቂዎች መብት የተለወጠው ማኀበር መብትና ግዴታ በንግድ መዝገብ ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ለአዲሱ ማኀበር ይተላለፋል አዲሱ ማኀበር እንደተመዘገበ ወዲያውኑ ከቀድሞው ማኀበር ገንዘብ ጠያቂዎች ማስረጃቸውን እንዲያቀርቡና ተቃራኒ ሀሳብ ካላቀረቡ አዲሱ ማኀበር ዕዳ ከፋያቸው መሆኑ ይገለጽላቸዋል ገንዘብ ጠያቂዎችን ለመጥራት በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ገንዘብ ጠያቂዎች ገንዘባቸው አስከሚከፈላቸዉ ወይም በቂ ዋስትና እስከሚሰጣቸዉ ድረስ ከማኀበሩ ሀብት ላይ ለአባላት ክፍያ አይፈጸምም ስራ አስኪያጆች ወይም እንደነገሩ ሁኔታው የኩባንያው ፀሐፊ የቀድሞው ማኀበር መለወጥ ሰፊ ስርጭት ባለው ጋዜጣ እንዲገለፅ እና በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተወሰነው ከተፈፀመ በኋላ የቀድሞው ማኀበር ከንግድ መዝገብ እንዲሰረዝ ማድረግ አላባቸዉ ስራ አስኪያጆች እና የኩባንያው ፀሐፊ በዚህ አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ እስከ የተደነገጉትን ድንጋጌዎች ለማስፈፀም በአንድነትና በነጠላ ኃላፊዎች ይሆናሉ አንቀጽ የአባላት ኃላፊነት የማጎኀኅበሩ ገንዘብ ጠያቂዎች የማኀበሩን መለወጥ የተቀበሉ መሆናቸው ካልተረጋገጠ በስተቀር ኃላፊነታቸዉ ያልተወሰነ አባላት የመለወጡ ውሳኔ በንግድ መዝገብ ከመመዝገቡ በፊት ማኀበሩ ለገባው ግዴታ ከነበረባቸዉ ኃላፊነት ነፃ አይሆኑም የማኅበሩ ገንዘብ ጠያቂዎች መለወጡን በተመለከተ ማኀበሩ ያሳለፈው ውሳኔ በተመዘገበ ደብዳቤ ወይም ባሳወቁት የኤሌክትሮኒክ ዘዴ ተልኮላቸው ከተላከበት ቀን አንስቶ ባሉት ቀናት ውስጥ ያለመቀበላቸውን በግልጽ በጽሑፍ ካላሳወቁ የማኀበሩን መለወጥ እንደተቀበሉ ይቆጠራል ርዕስ ዘጠኝ የንግድ ማህበራት መዛመድ መዋፃድና መከፋፈል ምእራፍ አንድ የኩባንያዎች መዛመድ አንቀጽ ትርጓሜ የሕግ ሰውነት ያላቸው ኩባንያዎች አንዱ ከሌላው አክሲዮን የገዛ ከሆነ ወይም እርስ በእርስ አክሲዮን የተገዛዙ ከሆነ ወይም በመካከላቸው የሆልዲንግና ተቀጥላ ግንኙነት ካለ ወይም የአንድ ቡድን ኩባንያ አባላት ከሆኑ የተዛመዱ ኩባንያዎች ይባላሉ አንቀጽ አንድ ኩባንያ ከሌላ ኩባንያ ስለሚኖረው አክሲዮን የአንድ ኩባንያ ዋና ገንዘብ አስር በመቶ ወይም ከዚያ በላይ የሆነው ድርሻ በሌላ ኩባንያ የተያዘ ከሆነ የመጀመሪያው ኩባንያ በሁለተኛው ኩባንያ ውስጥ አክሲዮኖች ሊኖሩት አይችልም ሁለት ኩባንያዎች አክሲዮኖቻቸውን የተገዛዙ ሆኖ አንዱ ኩባንያ ከሌላው ኩባንያ ዋና ገንዘብ ውስጥ አስር ከመቶ ወይም ከዚያ በላይ የገዛ ከሆነ ይዞታቸዉን ለኩባንያው መዝጋቢ አካል ማስታወቅ አለባቸው መዝጋቢው አካልም የተገዛዙትን በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተወሰነው መጠን እንዲቀንሱ ይጠይቃቸዋል ለመቀነስ የማይስማሙ ከሆነ ከመካከላቸው አነስተኛ ይዞታ ያለው ኩባንያ ይዞታውን እንዲሸጥ ያዛል አንዱ ኩባንያ በሌላው ኩባንያ ውስጥ ያለው ይዞታ እኩል የሆነ እንደሆነና አንደኛው ኩባንያ ይዞታውን ለሌላው ኩባንያ ለመሸጥ ያልተስማማ እንደሆነ እያንዳንዳቸው በሌላው ኩባንያ ውስጥ ያላቸው ድርሻ ከአስር ከመቶ በታች መቀነስ አለበት ኩባንያዎቹ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ወይም የተመለከተውን የፈፀሙ ለመሆናቸዉ ለመዝጋቢው አካል የጽሑፍ መግለጫ ማቅረብ አለባቸው አንቀጽ ትርጓሜ በዚህ ሕግ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር ቡድን ማለትሆልዲንግ ኩባንያንና የሆልዲንግ ኩባንያውን ተቀጥላኩባንያ ወይም ኩባንያዎችን የሚያቅፍ ነው ተቀጥላ ኩባንያ ማለት በቀጥታ ወይም በሌላ ተቀጥላ ኩባንያ በኩል በተዘዋዋሪ በሌላ ኩባንያ ቁጥጥር ሥር ያለኩባንያ ነው ቁጥጥር ማለት ሆልዲንግ ኩባንያ በቀጥታ ብቻውን ወይም ከሌሎች ባለአክስዮኖች ጋር በመሆን የፋይናንስየአሠራር እአና ሌሎች የተቀጥላ ኩባንያ ፖሊሲዎችን የመምራት ሥልጣን ነው በተቀጥላኩባንያ ላይ ቁጥጥር አለ የሚባለው ሆልዲንግ ኩባንያው ሀ በክርሱ ቁጥጥር ያለ መሆኑን በተለየ ሁኔታ በግልጽ ማስረዳት ካልተቻለ በስተቀርበተቀጥላ ኩባንያው ውስጥ ያሉ ከግማሽ በላይ ድምፅ የሚያሰጡ መብቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በባለቤትነት የተያዘ ለ በሌላ ኩባንያ ግማሽ ወይም ከግማሽ ያነሰ ድምፅ የመስጠትመብትኖሮትከሌሎች ባለአክሲዮኖች ጋር በተደረገ ስምምነት ከግማሽ በላይ የሆነውን ድምፅ የመስጠት መብትከያዘ ከተጎናጸፈ በመተዳደሪያ ደንብ ወይም በስምምነት የኩባንያውን የፋይናንስ የአሠራርና ሌሉች ፖሊሲዎችን ከተቆጣጠረየመቆጣጠርመብት ከያዘየኩባንያውን ንግድ የመቆጣጠር ሥልጣን ካለው የኩባንያውን ከፍተኛ አስፈጻሚ አካል አባላት መካከል አብዛኛውን አባለት የመሾምና የመሻር መብት ካለው ወይም በተግባር አብላጫውን የጠቅላላ ጉባዔዎችን ወይም ተመሳሳይ አካላትን ድምፅ ሲሠራበትና ንግዱን ሲቀጣጠር ነው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ለ እና መ ቁጥጥር አለ ተብሎ የሚገመተው የከፍተኛው አስፈጻሚ አካል አባላት በሌላ ኩባንያ ለሁለት ተከታታይ የበጀት ዓመታት ሲሰየሙ ነው ሌላው ኩባንያ መሰየሙን አድርጎታል የሚባለው በተጠቀሰው የበጀት ዓመት ከአር በመቶ በላይ ድምፅ የመስጠት መብት ሲኖረውና በኩባንያው ከእርሱ የበለጠ ድምጽ የመስጠት መብት ያለው ሌላ ባለአክሲዮን የሌለ ከሆነ ነው ን ሙሉ ለሙሉ በባለቤትነት የተያዘ ኩባንያ ማለት ከሆልዲንግ ኩባንያው በስተቀር በአርሱ ስም የሚሠሩ ሌሎች ባለአክሲዮኖች ወይም ሌሎች ማናቸውም ተቀጥላ ኩባንያዎች ወይም ሰዎች የሌሉበት ኩባንያ ነው አንቀጽ ተሳትፎን ስለ መተመን ለቁጥጥር ዓላማ በተግባር የሚሠራባቸውን ድምፅ የሚያሰጡ መብቶችን የያዙ አክሲዮኖችን የመሸጥ ወይም የመግዛት መብት ድምዕ ለሚያሰጡ መብቶች ቆጠራ የሚታሰቡ ይሆናሉ በተቀጥላ ኩባንያው በራሱ ወይም በተቀጥላ ኩባንያዎቹ ባለቤትነት ከተያዙ አክሲዮኖች ጋር የተያያዙ የተጣመሩ ድምፅ የሚያስጡ መብቶች በተቀጥላ ኩባንያ ውስጥ ያሉ ድምፅ የሚያስጡ መብቶች አቆጣጠር ተፈጻሚ አይሆነም አንቀጽ ቁጥጥርን የማስታወቅ ኃላፊነት የሆልዲንግ ኩባንያ የሥራ አመራር ቁጥጥሩ አንደተጀመረ ወዲያውኑ ለተቀጥላ ኩባንያው ማሳወቅ ይኖርበታል ተቀጥላ ኩባንያው እንዳወቀ ወደያውኑ በሌላ ኩባንያ ያሉትን አክሲኖችንና ድምፅ የሚያሰጡ መብቶችን ሳይዘገይ ለሆልዲንግ ኩባንያው ማሳወቅ ይኖርበታል አንቀጽ የሆልዲንግ ኩባንያው ለተቀጥላ ኩባንያው አመራርመመሪያትእዛዝ የመስጠትመብት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና የተመለከተው ልዩ ሁኔታ እነደተጠበቀ ሆኖ ሆልዲንግ ኩባንያ ለተቀጥላ ከባንያው መመሪያ የመስጠት መብትአለው በዚህ ሕግ አንቀጽ የተደነገጉት ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነውየተቀጥላ ኩባንያው የማኔጅመንት አካል በሆልዲንግ ኩባንያው የተሰጠውን መመሪያ ትእዛዝ ማክበር ይኖርበታል የሚከተሉት የማኔጅምንት አባላት በመመሪያውአ ይገደዱም ሀ በተለይ መተዳደሪያ ደንብን የባለአክሲዮኖችን ስምምነትን ወይም ማናቸውንም ሕግ ደንብ መሠረት በማድረግ በሆልዲንግ ኩባንያው ወይም ኩባንያውን በሚቆጣጠሩት ባለአክሲዮኖች ያልተሾሙ ዳይሬክተሮችና ሥራ አስኪያጆች ለ ከአባልነት ክፍያ ውጭ ከኩባንያው ወይም ከኩንባያው ጋር ትስስር ካለቸው ሰዎች ጋር ንብረት ወይም ገንዘብ ነክ ግንኙነት የሌላቸውዳ ሬክተሮች ሐ ካሉየ ሠራተኛ ተወካይ የሆኑዳ ይሬክተሮች ሙሉ ለሙሉ በሆልዲንግ ኩባንያ ባለቤትነት ያልተያዘ ተቀጥላ ኩባንያ አመራሩ በሆልዲንግ ኩባንያው የሚመራ መሆን ወይም አለመሆኑን ለመዝጋቢው አካል ማሳወቅ አለበት በተቃራኒው አንዲታወቅ ካልተደረገ በስተቀር ሙሉ ለሙሉ በሆልዲንግ ኩባንያ ባለቤትነት የተያዘ ተቀጥላ ኩባንያ ከኦልዲንግ ኩባንያው መመሪያ እንደሚቀበል ተደርጎ ስለሚገመት ሙሉ ለሙሉ በሆልዲንግ ኩባንያው መያዙን እንጂ መመሪያ የሚቀበል ወይም የማይቀበል መሆኑን ለመዝጋቢው አካል ማስታወቅ አይጠበቅበትም አንቀጽ በተቀጥላ ኩባንያ ደረጃ ስለሚኖር መረጃ የማግኘት መብት በተቀጥላ ኩባንያ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አግባብ ያለውን ሕግ የሚተላለፍ ወይም የሦስተኛ ሰዎችን መብት የሚነካ ካልሆነ በቀር የኩባንያ የቦርድ ዳይሬክተሮች ወይም ተመሳሳይ ደረጃ ያለው ተቋም ከተቀጥላ ኩባንያው ማናቸውንም መረጃዎች የማግኘት መብት አለው አንቀጽ የመረጃ መብት እና ልዩ መረጃ ስለመጠየቅ በቡድን የታቀፉ ሥር ያሉ ኩባንያዎችና የቡድኑ የቀድሞ አባል ኩባንያዎች መረጃዎች መረጃ የማግኘትና ልዩ ምርመራ እንዲደረግ የመጠየቅ መብት ላላቸው ክፍት ናቸው አንቀጽ በቡድን ውስጥ ስለሚኖር የንግድ ዕድሎች የተቀጥላ ኩባንያው ንሌሎች ዳይሬክተሮች ዳይሬክተሮች የሌሉ እንደሆነተቆጣጣሪ ያልሆኑ የኩባንያው ባለአክሲኖች ካልፈቀዱ በስተቀርተቀጥላ ኩባንያው ሙሉ ለሙሉ በሆልዲግ ኩባንያው ባለቤትነት ካልተያዘ ሆልዲንግ ኩባንያው በራሱ ወይም በሌላ ተቀጥላ ኩባንያው አማካይነት የኩባንያውን የንግድ ዕድሎችን አጋጣሚዎችን ሊጠቀምባቸው አይችልም አንቀጽ ልዩ ምርመራ አንዲደረግ የመጠየቅ መብት ስላላቸው ባለአክሲዮኖች በዚህ ሕግ አንቀጽ በተመለከቱት ሁኔታዎች የተቀጥላ ኩባንያ ባለአክሲኖች በሆልዲንግ ኩባንያው ላይ ልዩ ምርምራ እንዲደረግ መጠየቅ ይችላሉ አንቀጽ በሽያጭ የማስተላለፍ መብት የሆልዲንግ ኩባንያ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከዘጠና በመቶ በላይ የሆነውን አክሲኖችን ወይም ድምፅ የሚያሰጡ በመብቶችን በባለቤትነት ከያዘ ሌሉቹ ባለአክሲዮኖች ሆልዲንግ ኩባንያው አክሲዮናቸውን እንዲገዛቸው መጠየቅ ይችላሉ የተቀጥላ ኩባንያው ባለአክሲዮኖች ሆልዲንግ ኩባንያው ወይም በአርሱ የተወከለ የተሰየመ ሌላ ሰው አክሲዮናቸውን እንዲገዛቸው በፍርድቤት መጠየቅ ይችላሉ የመሸጫው የውል ቃሎችና ዋጋው የሚወሰንበት መመዘኛ አንዲሁም ዋጋውን በተመለከተ ስምምነት ላይ ካልተደረሰ ዋጋው በፍርድ ቤት በተሾመ ባለሙያ ሚወሰን መሆኑ በመጠየቂያው ሰነድ መገለጽ ይኖርበታል አንቀጽ ስለቡድን ጥቅሞች የተቀጥላ ኩባንያ የሥራ አመራር በተለይም በሆልዲንግ ኩባንያው በተሰጠ መመሪያ ከኩባንያው ተፃራሪ ተቃራኒ የሆነ ውሳኔ የወሰነ እንደሆነ የተጣለበትን እምነት እንዳልተወጣ የማያስቆጥረው ሀ ውሳኔው የቡድኑን አጠቃላይ ጥቅም የጠበቀ ከሆነ ለ የሥራ አመራሩ ኪሣራው ጉዳቱ ወይም የጥቅም መጓደሉ በቂ ነው ተብሎ በሚገመት ጊዜ ውሰጥ በጥቅምበትርፍ ወይም በተጠቃሚነት ይስተካከላል ይተካል ይለወጣል ብሎ በበቂ ሁኔታ ከገመተ እአና ጉዳቱየጥቅም መጓደሉ ወይም ተጠቃሚነቱ የኩባንያውን ቀጣይ ህልውና አደጋ ላይ የማይጥለው ከሆነ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ለ ሙሉ ለሙሉ በሆልዲንግ ኩባንያው ባለቤትነት በተያዘ ተቀጥላ ኩባንያ ላይተፈጻሚ አይሆንም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ያልተሟላ እንደሆነ ተቀጥላ ኩባንያው የሥራ አመራር የሆልዲንግ ኩባንያውን መመሪያዎች አልፈጽምም ማለት ላለመፈጸም ይችላል አንቀጽ የተሳሳተ ግብይት ለቡድኑ ጥቅም ተብሎ በሆልዲንግ ኩባንያው በተሰጡ መመሪያዎች የሚመራ ተቀጥላ ኩባንያ በራሱ ሀብት የኩባንያውን ንብረት ከመጣራት የሚያደነው መሆኑ ተስፋ የሚጣልበት ካልሆነሆልዲንግ ኩባንያው ሳይዘገይ በተቀጥላ ኩባንያው ላይ ሥር ነቀል የመዋቅር ለውጥ ማካፄድ ወይም የኩባንያው ንብረት እንዲጣራ ሂደቱን መጀመር ይኖርበታል ሆልዲንግ ኩባንያው የዚህን አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተላለፈ እንደሆነ ወይም የተቀጥላ ኩባንያውን ጥቅም በሚጎዳ መንገድ የመራው እንደሆነአደጋ ላይ ከመውደቁ በፊት ተቀጥላ ኩባንያው ላልከፈለውዕዳ ተጠያቂ ነው በዚህም ጊዜ ሆልዲንግ ኩባንያው አደጋውን የሚያውቅ ወይም ማወቅ የሚገባውእንደነበረ ተደርጎ ይገመታል ፍርድ ቤትም የገንዘብ ጠያቂዎችን አግባብነት ያለቸውን ዕዳዎች ያጣራል አንቀጽ የካሳ መብት ጥያቄውን ስለሚያቀርበው አካል በዚህ ህግ አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ መሠረት የሚቀርብ የካሣ መብት ጥያቄ የሚቀርበው በተቀጥላ ኩባንያው ሂሣብ አጣሪበአስተዳደሪ ወይም በንብረት ጠባቂ ብቻ ነው ፍርድ ቤት በራሱ አነሳሽነት የካሳ መብት ሊወስን የሚችል ስለመሆኑ ፍርድ ቤት በዚህ ህግ አንቀጥ መሰረት ለደረሰ ጉዳት ሆልዲን ኩባንያው ካሳ እንዲከፍል ጥያቄ ባይቀርብለትም እንኳን በራሱ አነሳሽነት የመብት ጥያቄውን ሊያንቀሳቅሰው ይችላል አንቀጽ ሆልዲንግ ኩባንያ ለተቀጥላ ኩባንያው ያለበት ኃላፊነት ሆልዲንግ ኩባንያ በተቀጥላው ኩባንያ ላይ ያለውን ሥልጣን ተቀጥላ ኩባንያውን ለኪሳራ በሚዳርግ ሁኔታ መጠቀም አይኖርበትም በተለይም ተቀጥላ ኩባንያው የሚከተሉትን እንዲፈጽም ሊያደርገው አይገባም ሀብቱን ወደሆልዲንግ ኩባንያው ወይም ለሌላ ወገን እንዲያስተላልፍ ወይም በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀንስ ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ትርፉን እንዲቀንስ ወይም ወደራሱ ወይም ለሌላ ወገን እንዲያስተላልፍ ለራሱ ወይም ለሌላ ኩባንያ ዕዳ ዋስ እንዲሆን ያለ በቂ ምክንያት እንቅስቃሴውን የሚጎዱ ውሳኔዎችን እንዲወስንወይም ህልውናውን አደጋ ላይ የሚጥል ክፍያ እንዲፈጽም አንቀጽ ሆልዲንግ ኩባንያ ለተቀጥላው ያለበት ተጠያቂነት ሆልዲንግ ኩባንያው ሀ ያለውን የመቆጣጠር ስልጣን በአግባቡ ባለመወጣት ወይም በዚህ ሕግ በአንቀጽ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች በመተላለፍ ወይም ማናቸውንም ህገወጥ ድርጊት በመፈጸም ተቀጥላ ኩባንያውን ለዕዳ እንዲዳረግ ወይም ጉዳት እንዲደርስበት ካደረገ ለ የተቀጥላ ኩባንያውን ትርፍ ወይም አዳ ወደራሱ ወይም ወደ ሌላ ኩባንያ የሚያዛውር ስምምነት ካለ ሐ ተቀጥላ ኩባንያው ያለበትን ፅዳ እንዳይከፍል የራሱን ወይም የተቀጥላውን ሀብት ከገንዘብ ጠያቂዎች እንዲሸሽ ካደረገ መ ተቀጥላ ኩባንያውን ያቋቋመው ያለበትን እዳ ወይም ወደፊት ይመጣል ብሎ የገመተውን አዳ ወደተቀጥላ ኩባንያው ለማስተላለፍ ከሆነኩባንያውን ያቋቋመው ለዚህ አላማ ከሆነ ለሚመጣው ኃላፊነት ተጠያቂ ይሆናል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ለ ሐ እና መ መሠረት ለሚመጣ አላፊነት ሆልዲንግና ተቀጥላ ኩባንያው በአንድነትና በተናጠል ኃላፊዎች ናቸው ምዕራፍ ሁለት የማኀበራት መዋፃድ እና መከፋፈል አንቀጽ የማኀበራት መዋሀድ አንድ የንግድ ማኀበር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ማኀበራትን በመጠቅለል ወይም ሁለትና ከዚያ በላይ የሆኑ ማኀበራት ተቀላቅለው አዲስ ማኀበር በመመስረት ሊዋሀዱ ይችላሉ ለመፍረስ በመጣራት ላይ ያለ ማኀበር የንብረት ክፍፍል ከመደረጉ በፊት ከሌላ ማኀበር ጋር ሊዋሀድ ይቸላል ውህደቱ በማንኛውም የንግድ ማኀበር መካከል ሊደረግ ይችላል አንቀጽ የማኀበራት መከፈል የንግድ ማኀበራት በሚከተሉት ሁለት መንገዶች ሊከፈሉ ይችላሉ የአንድ ማኀበር ሀብት ወደሁለት ወይም ከዚያ በላይ ወደ ሆኑ ክፍሎች ሲከፈልና በአያንዳንዱ የሀብት ክፍል መሰረት አዳዲስ ማኀበራት ሲመሰረቱ ወይም የተከፋፈለው የእያንዳንዱ የሃብት ክፍል ወደ ለነባር ማኀበራት ሲተላለፍ ወይም የአንድ ማኀበር የተወሰነ የሀብት ክፍል አዲስ ማኀበር ሲመሰረት ወይም ወደ ነባር ማኀበር ሲተላለፍ አንቀጽ የውህደት ወይም መከፈል ውሳኔ ኃ ውህደቱ ወይም መከፈሉ መመስረቻ ጽሑፍን ለማሻሻል ተፈጻሚ በሚሆኑ ድንጋጌዎች መሰረት በሚወሀዱት በእያንዳንዱ ማህበር ወይም በሚከፈለው ማኀበር መወሰን አለበት ሆኖም የሚዋሀደው ወይም የሚከፈለው ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕዝብ ኩባንያ ከሆነ የውህደት ወይም የመከፈለ ውሳኔው ያሉ እንደሆነ ልዩ መብት ባላቸው ባለአክሲዮኖች ልዩ ጉባኤ ወይም የግዴታ ወረቀት ባለቤቶች ጉባኤ መፅደቅ አለበት በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ውሳኔ ያልተስማማ የማጎኀበሩ አባል በዚህግ አንቀጽ መሰረት አክሲዮኑን ሽጦ ከማህበሩ የመውጣት መብት አለው አንቀጽ የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነት የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነት በሚዋሀዱት ወይም በሚከፈሉት ማኅበራት ተዘጋጅቶ እንደአግባቡ በእያንዳንዱ ማኀበር የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ወይም በስራ አስኪያጅ መፈረም አለበት የመዋሀድ ወይም የመከፈል ስምምነቱ መመስረቻ ጽሑፍን ለማሻሻል ተፈጻሚ በሚሆኑ በዚህ ሕግ ድንጋጌዎች መሰረት በእያንዳንዱ ማኀበር መጽደቅ አለበት ሆኖም ውህደቱ ወይም ክፍፍሉ በአባላቱ ላይ ተጨማሪ ግዴታ የሚያስከትል የሆነ እንደሆነ ስምምነቱ ሙሉ ድምጽ መጽደቅ አለበት የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነት እንደአግባቡ የሚከተሉትን መያዝ አለበት ህህ የሚዋሀዱትን ወይም የሚከፈሉትን ማኀበራት ዓይነት የንግድ ስምና የዋና መስሪያ ቤት አድራሻ ለ ውህደቱ ወይም መከፈሉ አዲስ ማኀበር የሚያስገኝ ከሆነ የማኀበሩን ዓይነት የንግድ ስምና የዋና መስሪያ ቤቱን አድራሻ ሐ የውህደቱ ወይም የመከፈሉ ምክንያትና ሁኔታ መ የእያንዳንዱን ማኀበር የፀደቀ ዓመታዊ የተጠቃለለ የሒሳብ ሪፖርት ሠ ወደጠቅላዩ ወይም አዲሱ ማኀበር የተዛወረውን ሀብት እና ዕዳ መግለጫ የሀብት ግምትና የአገማመቱ ሁኔታ ረ በውህደቱ ወይም በመከፈሉ የሚገኙ አክሲዮኖች ድርሻዎች ወይም መያዣዎች የሚተላለፉበትን ሁኔታና ተመን ትርፍ ማስገኘት የሚጀምሩበትን ጊዜ እና መብትን የሚመለከቱ ልዩ ሁኔታዎች ተግባራዊ መሆን የሚጀምሩበትን ጊዜ ሰ የጠጠቅላዩ ወይም የተከፋዩ ማኀበር ባለድርሻዎች በጠቅላዩ ወይም በአዲሱ ማኀበር ውስጥ የሚኖራቸውን ድርሻ እና መብት በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ባለመስማማታቸው ከማኀበሩ ለሚወጡ አባላት የሚሰጠውን የገንዘብ መጠን ቀ ተጠቅላዩ ወይም ተከፋዩ ማኀበር ያከናወናቸው ተግባራት በጠቅላዩ ወይም አዲስ በሚቋቋመው ማንገበር እንደተከናወኑ የሚቆጠርበትን ቀን በ ያልተወሰነ ኃላፊነት ያለባቸው ባለድርሻዎች ካሉ ስማቸውን ተ ከመደበኛ አክሲዮኖች የተለየ ጥቅምና ልዩ መብት የሚያስገኙ አክሲዮኖችን ለያዙ አባላት የተሰጠ መብትና ጥቅም መ ውህደቱ ወይም መከፈሉ የሚያስከትለውን ግዴታ እና ኃላፊነት እንዲሁም በገንዘብ ጠያቂዎች ላይ የሚኖረውን ተጽዕኖ ነ ለአባላት ወይም ለስራ አመራሮች ሊሰጥ የሚችለውን ልዩ ጥቅም እና ዝ ሌሎች አግባብነት ያላቸው መረጃዎችን አንቀጽ የውህደት ወይም መከፈል ሪፖርት በውህደቱ ወይም በመከፈሉ የሚሳተፉት ማኀበራት ለጉባኤ የሚቀርብ የውህደት ወይም የመከፈል ሪፖርት በጋራ ወይም በየግላቸው ማዘጋጀት አለባቸው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ሪፖርት የሚከተሉትን መያዝ አለበት ሀ የውህደቱን ወይም የመከፈሉን አላማና ውጤቱን ለ የውህደቱን ወይም መከፈሉን ስምምነት ሐ ለባለአክሲዮን የሚሰጠውን የአክሲዮን ዋጋ የሚሰላበት ተመንካለ የማስተካከያ ክፍያ አባላት በጠቅላዩ ወይም በአዲሱ ማኀበር ውስጥ የሚኖራቸውን ድርሻ መብት አና ግዴታ መ በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ባለመስማማታቸው ከማኀበሩ ለሚወጡ አባላት በጥሬ ገንዘብ የሚሰጠዉን ክፍያ ሠ በጠቅላዩ ማኀበር ዋና ገንዘብ ላይ የሚኖረውን ጭማሬ ረ እንደአግባብነቱ ውህደቱን በተመለከተ አግባብ ካለው አካል ፈቃድ የተሰጠው መሆኑን ሰ ውህደቱ ወይም መከፈሉ በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ተሳታፊ በሆኑ ማኀበራት ሰራተኞች ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ እና ሸሽ ሌሎች አግባብነት ያላቸው መረጃዎችን አንቀጽ ስምምነቱን ስለማሳወቅ የመዋሀድ ወይም የመከፈል ስምምነቱ ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት ሦስት ወራት ውስጥ በየወሩ ለአንድ ጊዜ አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ለህዝብ መገለፅ አለበት እንዲሁም ማስታወቂያው በሚዋሀደው ወይም በሚከፈለው ማኀበር ዋና መስሪያ ቤት መለጠፍ አለበት የሚዋሀደው ወይም የሚከፈለው ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕዝብ ኩባንያ ከሆነ በተጨማሪ ማስታወቂያው በኩባንያው ደረገጽ መውጣት አለበት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ለህዝብ የሚገለፀው ማስታወቂያ በዚህ ህግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሀሐሠ እና ሰ የተመለከቱትን መረጃዎች በአንቀጽ የተመለከተውን የገንዘብ ጠያቂዎች መብት እና በአንቀጽ የተመለከተውን የግዴታ ወረቀት ባለቤቶች መብት መያዝ አለበት በዚህ አንቀጽ ንዐስ አንቀጽ መሠረት የመጀመሪያው ማስታወቂያ ለሕዝህ ይፋ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ባሉት ሦስ ወራት ውስጥ ውህደቱ ወይም መከፈሉ አግባብ ላለው የመንግስት አካል ቀርቦ መጽደቅ ወይም አዲስ ማኀበር የሚቋቋም ከሆነ መመዝገብ አለበት አንቀጽ የውህደት ወይም የመከፈል ኦዲት የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነት እንደአግባብነቱ በዳይሬክተሮች ቦርድ ወይም በሚመለከታቸው ሌሎች አመራሮች የሚዘጋጀው የውህደት ወይም መከፈል ሪፖርት ዓመታዊ የተጠቃለለ ሂሳብ አና ሌሎች አስፈላጊ የውህደት ወይም መከፈል ሁኔታዎች ኦዲት መደረግ አለባቸው በውህደቱ ወይም መከፈሉ የሚሳተፉት ማህበራት በጋራ ኦዲተር ሊሾሙ ይችላሉ የኦዲተሮችን አሺሺም በተመለከተ የዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል በውህደቱ ወይም በመከፈሉ የሚሳተፉ ማኀበራት ለኦዲቱ አስፈላጊ የሆነ ሰነዶችንና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን ለኦዲተሮች ማቅረብ አለባቸው ኦዲተሮቹ የሚከተሉትን በመመርመር ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው ሀ በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ተካፋይ ለሆኑ ማኀበራት አባላት የተሰጡ አክሲዮኖች ዋጋ አይነትና ተመን ተመጣጣኝ ስለመሆኑ ለ የአተማመን ዘዴው ትክክለኛ ስለመሆኑ ሐ በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ባለመስማማታቸው ከማህበራቱ ለሚወጡ አባላት የሚሰጠው ክፍያ ተገቢ ስለመሆኑ መ በጠቅላዩ ማኀበር ዋና ገንዘብ ላይ የሚደረገው ጭማሪ በዚሁ ማኀበር ውስጥ ድርሻ የሚሰጣቸውን አባላት መብት የሚያስጠብቅ ስለመሆኑእና ሠ ሌሉች አግባብነት ያላቸውን ሁኔታዎች የንግድ ማኀበራት መዝጋቢው አካል ከኃላፊነቱ የተወሰነ የሕዝብ ኩባንያ በስተቀር ዓመታዊ የገንዘብ ዝውውራቸውን ወይም የሂሳብ ሚዛናቸውን መነሻ በማድረግ ከተወሰነው መጠን በታች የገንዘብ ዝውውር ወይም የሂሳብ ሚዛን ያላቸው ማኀበራት ከውህደት ወይም ከመከፈል ኦዲት ግዴታ ነጻ እንዲሆነ መወሰን ይችላል አንቀጽ ሰነዶችን የማግኘት መብት በውህደቱ ወይም በመከፈሉ ተሳታፊ የሆኑ ማኀበራት ለአባላት ለገንዘብ ጠያቂዎች አና ለሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የውህደት ወይም መከፈል ስምምነቱን የውህደት ወይም የመከፈል ሪፖርቱን የኦዲት ሪፖርቱን የተጠቃለለ የሂሳብ ሚዛን እና ሌሎች ለጉዳዩ አግባብነት ያላቸው መረጃዎችን በዋና መስሪያ ቤቱም ሆነ በቅርንጫፎቹ የውህደቱን ወይም የመከፈሉን ውሳኔ የሚያፀድቀው ጉባዔ ከሚደረግበት አንድ ወር በፊት ሊታይ በሚችልበት ቦታ ማስቀመጥ አለባቸው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተጠቀሱት ሰዎች የመረጃዎችን ቅጅ መውሰድ ይችላሉ አንቀጽ ውህደቱ ወይም መከፈሉ የሚፀናበት ጊዜ የማኀበራት ውህደት ወይም መከፈል የሚፀናው በውህደቱ ወይም በመከፈሉ አዲስ ማኀበር በሚቋቋምበት ጊዜ ውህደቱ ወይም መከፈሉ የሚጸናው አዲሱ ማንገበር በተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ይሆናል በሌሎች ሁኔታዎች ውህደቱ ወይም መከፈሉ የሚጸናው አግባብ ባለው የመንግስት አካል ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ ነው አንቀጽ የውህደትና እና የመከፈል ውጤት ውህደት ወይም መከፈል ኃ የሂፈሳብ መጣራት ሳያስፈልግ የጠፊው ማኀበር መፍረስን የውህደቱ ወይም መከፈሉ ተግባር በተጠናቀቀበት ጊዜ የነበረው የጠፊው ማኀበር ሀብትና ዕዳ ወደ ጠቅላዩ ወይም አዲስ ወደ ተመሰረተው ማኀበር መተላለፍን በውህደት ወይም መከፈል ስምምነት በተቀመጡ ሁኔታዎች መሰረት የጠፊው ማኀበር አባላት በጠቅላዩ ወይም አዲስ በተቋቋመው ማኀበር ውስጥ ድርሻ የማግኘት መብትን እና የተወሰነ ሃብቱ ተከፍሎ አዲስ ማኀበር የመሰረተው ወይም ወደ ሌላ ማኀበር ፃብቱን ያስተላለፈው ማኀበር አባላት አንደ ስምምነታቸው ሁኔታ ፃብቱን በከፈለው አዲስ በተመሠረተው ወይም ሣብቱ በተላለፈለት ማኀበር ውስጥ ድርሻ የማግኘት መብትን ያስከትላል አንቀጽ በውህደት ወይም መከፈል ጊዜ የአባላት መብት ጥበቃ የማኀበሩ አባላት በውህደት ወይም መከፈል ስምምነት በተቀመጡ ሁኔታዎች መሠረት በጠፊው ወይም በተከፈለው ማኀበር ውስጥ ከነበራቸው አኩል ወይም ተመጣጣኝ የሆነ ድርሻና መብት በጠቅላዩ ወይም አዲስ በተቋቋመው ማንበር ውስጥ ይኖራቸዋል ኃ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሠረት አባላት በጠፊው ወይም በተከፈለው ማኀበር ውስጥ ከነበራቸው ድርሻ ተመጣጣኝ ድርሻ መስጠት ባልተቻለ ጊዜ ከተሰጣቸው ድርሻ አስር በመቶ የማይበልጥ የማስተካከያ ክፍያ ሊያገኙ ይችላሉ በጠፊው ወይም በተከፈለው ማኀበር ውስጥ ድምጽ መስጠት የማያስችሉ አክሲዮኖችን ይዘው ለነበሩ ባለአክሲዮኖች በጠቅላዩ ወይም አዲስ በተመሰረተው ማገበር ውስጥ ተመሳሳይ ወይም አንድ ዓይነት ዋጋ ያላቸው አክሲዮኖች ሊሰጣቸው ይችላል በጠፊው ወይም በተከፈለው ማኀበር ውስጥ ትርፍ ብቻ የሚያስገኙ አክሲዮኖችን ይዞ ለነበረ ባለአክሲዮን ተመሳሳይ አክሲዮን መስጠት ወይም ማህበሩ የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነት በተፈረመበት ቀን በነበራቸው ዋጋ አክሲዮኖችን ከባለአክሲኑ ላይ መግዛት አለበት በተጠቅላዩ ወይም በተከፈለው ማኀበር ውስጥ ልዩ መብት የሚያስገኙ አክሲዮኖች ይዘው ለነበሩ አባላት እኩል ወይም ተመጣጣኝ መብት የሚሰጡ አክሲዮኖች መሰጠት አለበት አንቀጽ የገንዘብ ጠያቂዎች መብት ከሚዋሀደው ወይም ከሚከፈለው ማኀበር ላይ ገንዘብ ጠያቂዎች ገንዘብ የመጠየቅ መብታቸው የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነት ለሕዝብ ይፋ ከመገለጹ በፊት የመክፈያ ጊዜው የደረሰ ከሆነ ማስታወቂያው ለሕዝብ ይፋ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሦስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ውህደቱ ወይም መከፈሉ አንዳይፈጸም በፍርድ ቤት ለመቃወም ይችላሉ ፍርድ ቤቱ ገንዘብ ጠያቂዎች ውህደቱን ወይም መከፈሉን የፈቀዱ መሆኑን ወይም የሚጠይቁት ገንዘብ የተከፈላቸው መሆኑን ካረጋገጠ ተቃውሟቸውን ውድቅ ማድረግ አለበት ፍርድ ቤቱ የሚዋሀደው ወይም የሚከፈለው ማንበር ያለበትን ዕዳ ለገንዘብ ጠያቂዎች እንዲከፍል ወይም ለዕዳ መክፈያ የሚሆን በቂ ዋስትና እንዲያቀርብ በማዘዝ ተቃውሞውን ውድቅ በማድረግ የውህደት ወይም የመከፈል ስምምነቱ ሊያፀናው ይችላል አንቀጽ የግዴታ ሰነድ ያች መብት የሚዋሀደው ወይም የሚከፈለው ማኀበር የግዴታ ሰነድ ያፐች ጉባኤ ውህደቱን ወይም መከፈሉን ያላፀደቀው አንደሆነ ዕዳ ከፋይ የሆነው ማኀበር የውህደት ወይም መከፈል ስምምነት በማስታወቂያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ ይፋ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ ጥያቄ ከሚያቀርቡ የግዴታ ሰነድ ያች የፅዳ ሰነዶችን መልሶ መግዛት አለበት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ ተዋህደው ወይም ተከፍለው አዲስ ማገበር ለሚመሰርቱ ማገበራት የዕዳ ሰነድ ያገፐችም ተፈፃሚ ይሆናል ማኅበሩ የግዴታ ሰነድ ያፐች ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት የዕዳ ሰነዶቻቸውን ዋጋ የሚከፍል መሆኑን ያስታወቀ እንደሆነ የፅዳ ሰነድ ያፐች ጉባኤ ሳያስፈልግ የጠቅላዩ ወይም አዲስ የሚቋቋመው ማህበር ገንዘብ ጠያቂ ይሆናሉ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ጥያቄ ያላቀረበ የግዴታ ሰነድ ያዥ የጠቅላዩ ወይም የአዲሱ ማህበር ገንዘብ ጠያቂ ይሆናል አንቀጽ የገንዘብ ጠያቂዎችን እና የግዴታ ሰነድ ያዥችን መብት ስለማስታወቅ በንግድ መዝገብ ውስጥ የሚካተቱ ዝርዝሮች በአንቀጽ ለገንዘብ ጠያቂዎች እንዲሁም በዚህ ህግ አንቀጽ ለዕዳ ሰነድ ያፐች የተሰጡትን መብቶች በግልጽ ማመልከት አለባቸውርዕስ አስር በውጭ ሀገር ስለተቋቋመ ወይም በውጭ ሀገር ስለሚሰራ ማኀበር አንቀጽ በውጭ ሀገር ተቋቁሞ ዋና መስሪያ ቤቱ በኢትዮጵያ ስለሆነ ማኀበር የዚህ ሕግና አግባብ ያላቸው የሌሎች ሕጎች ድንጋጌዎች በውጭ ሀገር ተቋቁሞ ዋና መስሪያ ቤቱ ወይም የንግድ ስራ ቦታው በኢትዮጵያ በሆነ ማህበር ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ በውጭ ሀገር ተቋቁሞ በኢትዩጵያ ውስጥ ተቀጥላ ወይም ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ያለው ማኀበር በውጭ ሀገር ተቋቁሞ በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት ተቀጥላ ወይም ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ባለው ማኀበር ላይ የመመስረቻ ጽሑፍ ለመዝጋቢው አካል ስለማቅረብንና ማስታወቅን እና የሂሳብ ሚዛንን በማስታወቂያ ማውጣትን የሚመለከቱት የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች በተቀጥላ ወይም ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ ማኀበሩ በኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት የወከለውን ሰው ስም ማስታወቅና ፊርማው በንግድ መዝገብ እንዲቀመጥ ማድረግ አለበት ተቀጥላ ወይም ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ስራውን ስለሚያከናውንበት ሁኔታ እና ስለ ልዩ ሁኔታዎች የተደነገጉት ድንጋጌዎች በማኀበሩ ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ በዚህ ሕግ ከታወቀው የተለየ ቅርጽ ስላለው ማኀበር የማኀበሩን ውሳኔ በንግድ መዝገብ ስለማስገባት እና የዳይሬክተሮችን ኃላፊነት የሚመለከቱት ኃላፊነቱ የተወሰነ የሕዝብ ኩባንያ ድንጋጌዎች በዚህ ሕግ ከታወቀው የተለየ ዓይነት ቅርጽ ባለው የውጭ አገር ማኀበር ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ አንቀጽ ኃላፊነት በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች በመተላለፍ በማኀበሩ ስም የሰሩ ሰዎች ስለማኀበራቱ ግዴታ በጋራና በተናጠል አላፊ ይሆናሉ አንቀጽ በኢትዮጵያ ተቋቁሞ በውጭ አገር ስለሚሰራ ማህበር በኢትዮጵያ ተቋቁሞ በውጭ አገር በሚሰራ ማህበር ላይ የዚህ ህግ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ አንቀጽ የውጭ ሀገር ጥቅሞችን በውስጡ ስለያዘ ማኀበር የውጭ ሀገር ጥቅሞችን በውስጡ በያዘ ማኀበር ላይ ገደብ የሚጥሉ ወይም ልዩ ሁኔታ የሚያስቀምጡ ልዩ ድንጋጌዎች የተጠበቁ ይሆናሉ ሶስተኛ መጽፍ ስለማጓጓዝ ስራና ስለኢንሹራንስ ርዕስ አንድ ስለማጓጓዝ ስራ ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች ክፍል አንድ በሁሉም ማጓጓዣ ስራዎች ላይ ተፈፃሚ ስለሚሆኑ ድንጋጌዎች አንቀፅ የማጓጓዣ ውል የማጓጓዣ ውል ማለት አጓጓዥ የማጓጓዣ ዋጋ ተከፍሎት መንገደኞችን ጓዝን ወይም ዕቃን መነሻ ከሆነው መድረሻ እስከሆነው ስፍራ ለማድረስ የማጓጓዝ ግዴታ የገባበት ስምምነት ነው አንቀፅ ልዩ የክፍያ ስርዓት ልዩ የክፍያ ስርዓት ማለት በጥቅል ወይም በኪሎ ግራም የተወሰነውን የአጓጓዥ የኃላፊነት መጠን የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት አሠራርን መሠረት በማድረግ ገንዘቡ ከሚከፈልበት ሀገር ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የምንዛሬ ተመን ነው አንቀፅ አደገኛ ዕቃ አደገኛ ፅቃፓ ማለት በባህሪያቸው አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ናቸው ተብለው በሚመለከተው አካል የተመደቡ ተቀጣጣይ የሬዲዮ ሞገድ የሚያመነጩ በሰው ልጅ ጤንነት በአካል ወይም በአካባቢ ላይ አደጋ ወይም ጥፋት የሚያስከትሉ የንጥረ ነገር የፈሳሽ ወይም የጋዝ ባህሪ ያላቸው እአና የመሳሰሉ ዕቃዎች ማለት ነው አንቀፅ ዕቃ ቃቃ ገ ማለት ማንኛውም ንብረት ሲሆን በጠጣር በፈሳሽ ወይም በጋዝ መልክ የሚገኝ ጥሬ ዕቃ ምርት መሳሪያ ሸቀጥ ለገበያ የተዘጋጀ ሶፍት ዌር እንስሳ የተፈጥሮ ሀይል ውጤት ከከርስ ምድር ሀብት የተገኘ እና ሌሎች ተመሳሳይ ንብረቶች ያካትታል አንቀፅ ጓዝ ጫዝ ማለት መንገደኛው ራሱ በሻንጣ በካርቶን ወይም በሌላ ሁኔታ በእጁ የሚይዘው እና በአጓዓዙ ያልመዘገበ ወይም በተመሳሳይ ሁኔታ በአጓጓዣ ተመዝግቦበእሱ ኃላፊነትና አደራ ስር ሆኖ የሚጓጓዝነው አንቀፅ በባሕር ላይ ስለሚደረግ ማጓጓዝ ሰዎችን ጓዝን ወይም ዕቃን በባህር ላይ ማጓጓዝ ስራ በሚመለከት ከዚህ ህግ ተፈጻሚነት ውጪ ሆኖ የባሕር ህግ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ ክፍል ሁለት የማጓጓዝ ሥራ ሰነድ እና ውል ንኡስ ክፍል አንድ የማጓጓዣ ሰነድ አንቀፅ ማጓጓዣ ሰነድ የሚይዛቸው ዝርዝሮች ማንኛውም የመንገደኛ የማጓጓዣ ሰነድ ቀጥሎ የተመለከቱት ዝርዝሮች ሊይዝ ይገባል ሀ የተሰጠበትን ቀንና ቦታ ለ መነሻ እና መድረሻውን ቦታና ጊዜ ሐ መጓጓዣው ከመዳረሻው በፊት የሚያርፍ እንደሆነ እነዚህኑ ማረፊያ ቦታዎች መ የአጓጓኙን ስም እና አድራሻ ሠ የማጓጓዣውን ዓይነት ረየማጓጓዣ ክፍያ እና ተዛማጅ ክፍያዎች ማንኛውም የተመዘገበ የእጅ ጓዝ ሰነድ በዚህ አንቀቀፅ ንዑስ አንቀፅ ከተዘረዘሩት በተጨማሪ የእጅ ጓዙን ክብደት አና ጥቅል ብዛት የሚያመለክት መሆን አለበት ማንኛውም የዕቃ የማጓጓዣ ሰነድ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ ከተዘረዘሩት በተጨማሪ የሚከተሉትን ዝርዝሮች ሊይዝ ይገባል ሀ የላኪውን የተቀባይን ስም እና አድራሻ ለ ዕቃዎቹን ለማጓጓዝ የመነሻ ርክክብ የተደረገበት ቀንና ቦታ እንዲሁምበመድረሻ የማስረከቢያ ቦታ ሐ የዕቃውን አይነት ብዛት ወይም መጠን ክብደት ዕቃው የታሸገበትን ዘዴ መ በጥቅሉ ብዛት እና በጥቅሉ ላይ ያለውን ልዩ ምልክት ያለም እንደሆነ የተሰጠውን ቁጥር ወጦ አደገኛ የሆነ ዕቃ ካለ ስለ ዕቃው አስፈላጊውን ጠቅላላ መረጃ ፎ ከማጓጓዙ ሥራ ጋር የተያያዙ የማጓጓዣ ክፍያዎች ተጨማሪ ክፍያዎችና ሌሎች ውሉ ከተደረገበት ጊዜ እስከ ማስረከቢያ ጊዜ ድረስ የሚወጡ ወጪዎች እና ሰ የአጓጓዝ ስምምነት ማረጋገጫ ለጉምሩክ መብት ማስፈፀም እና ለሌሎች ሥነሥርዓቶች የሚጠየቁ ሰነዶች አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ጊዜ በአባሪነት መያያዛቸውን የሚያመላክት መሆን አለበት አንቀፅ የማጓጓዣ ሰነድ አገልግሎት የማጓጓዣ ሰነድ መኖር የማጓጓዝ ሥራ ውል መደረጉን ያረጋግጣል በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው ቢኖርም የማጓጓዣ ሰነድ አለመኖር ወይም ዋጋ የሌለው መሆን ወይም መጥፋት ወይም ከመደበኛው የተለዬ መሆን ወይም በትክክል አለመሞላት የማጓጓዣ ውል አልተፈጸመም አያሰኘውም ወይም ያለውን ዋጋ አያሳጣውም የማጓጓዣ ሰነድ መኖር ዕቃዎቹን አጓጓዥ ስለመቀበሉ የፅቃዎች ብዛት ወይም የጥቅሎችን ቁጥር በጥቅሎቹ ላይ ያለውን ልዩ ምልክቶችና መግለጫዎች ትክክለኛነት እንዲሁም የዕቃዎቹ ክብደት እና የዕቃዎቹን ውጫዊ ሁኔታ እና ስለአስተሻሸጋቸው ማስረጃ ነው አንቀፅ የኤሌክትሮኒክ ሰነዶች ተቀባይነት ለማጓጓዝ ስራ ተብለው የተዘጋጁ የኤሌክትሮኒክ ሰነዶች ተቀባይነት ባለው የኤሌክትሮኒክ መንገድ እስከተዘጋጁ ድርስ እነደጽሁፍ ሰነድ ተቀባይነት ይኖራቸዋል የኤሌክትሮኒክ ሰነዶች በተዋዋይ ወገኖች እንዲፈረሙ ወይም በምስክር እንዲረጋገጡ አይጠየቅም አንቀፅ የዕቃ ማጓጓዣ ሰነዶችን እንደሚተላለፍ ሰነድ መጠቀም በላኪውና አጓጓዙ ስምምነትሁሉም የዕቃ ማጓጓዣ ሰነዶች እንደሚተላለፍ ሰነድ ሆነው ሊዘጋጁ ይትላሉ አንቀፅ መንገደኛ የጉዞ ሰነድ እንዲይዝ ማስገደድ የሚቻል ስለመሆኑ አጓጓዥ መንገደኛው የማጓጓዣ ሰነድ ወይም የደንበኝነት ትኬት እንዲቀበል እና ጉዞው እስኪያልቅ ጠብቆ እንዲይዝ ሊያስታውቀው ይቸችላል አንቀፅ የዕቃ መላኪያ ሰነድ ስለመስጠት ላኪው የፅቃ መላኪያ ሰነድ አዘጋጅቶ አጓጓዝ እንዲቀበለው ሊጠይቅ ይችላል ይህ ባልሆነ ጊዜ አጓጓዥ ላኪውን የዕቃ መላኪያ ሰነድ አዘጋጅቶ እንዲሰጠው ሊጠይቀው ይችላል ላኪው እና አጓንዓጓ ከተስማሙ የማጓዓዣው ሰነድ አጓዓጓዣ በሚሰጠውና ላኪው ተገቢ የሆኑትን ጽሁፎች በሚያሰፍርበት እንደደረሰኝ ባሉ ሌሎች ሰነዶች ሊተካ ይችላል አንቀፅ የጉምሩክ ሰነዶች እና ሌሎች ሥነሥርዓቶች ላኪው ፅቃው ከመድረሱ በፊት መሟላት የሚገባቸው የጉምሩክ እና ለሌሎች ሥነ ሥርዓቶች አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን ከማጓጓዣ ሰነድ ጋር ማያያዝ ወይም ለአጓጓዝ መስጠት እና አጓጓዥ የጠየቀውን መረጃዎች ማቅረብ ይኖርበታል አጓጓዝ እነዚሁኑ ሰነዶችና መረጃዎች ትክክለኛነትም ሆነ የተሟሉ ስለመሆናቸው ለመመርመር ምንም ዓይነት ግዴታ የለበትም ላዚኪው በነዚህ ሰነዶችና መረጃዎች አለመኖር ያለመሟላት ወይም ግድፈት የተነሳ ለሚደርሰው ጉዳት በአዓጓዖ ጥፋት ወይም ቸልተኝነት ካልሆነ በስተቀር ለአጓጓ ኃላፊ ይሆናል ከማጓጓዣ ሰነድ ጋር የተያያዘ ወይም ለአጓጓዝ በእጁ የተሰጠው ሰነዶች መጥፋት ወይም ተገቢ ያልሆነ አጠቃቀም ምክንያት ለሚደርሰው ጉዳት አጓጓዝ ያለበት ኃላፊነት የውክልና ኃላፊነት ሲሆን ይህም ኃላፊነት አጓጓዝ ዕቃው በጠፋ ጊዜ ከሚከፍለው ካሳ ሊበልጥ አይችልም አንቀፅ የማጓጓዣ ሰነድ ፊርማ በዚህ ህግ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው ቢኖርም የአጓጓዥ እና የላኪው ፊርማ በእጅ በመዛፍ በጣት አሻራ ወይም ለዚሁ በተዘጋጀ መሳሪያ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ሊሆን ይችላል አንድ ሰው መፈረም የማይችል እንደሆነ አንደሁኔታው በጣት አሻራ ወይም ስልጣን ባለው አካል ፊት በመፍቀድ ሊሆን ይችላል አንቀፅ ትክክለኛ ያልሆነ እና ያልተሟላ የዕቃ ማጓጓዣ ሰነድ ላኪው ለአጓጓዓዝ በሰጠው እና በማጓጓዣ ሰነድ ላይ የተሞላው መረጃ ትክክለኛ ባለመሆኑ ወይም በበቂ ሁኔታ ያልተሟላ መግለጫ በመስጠቱ አጓጓዝ ለወጪ ቢዳረግ ወይም ኪሳራ እና ጉዳት ቢደርስበት ላኪው ሙሉ ኃላፊነት አለበት ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ በስተቀር አጓዓጓ። በ ልቪዐበዩሃ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ የኪሳራ ሂደት ትርጓሜ የኪሣራ ሂደት ማለት በባለዕዳውም ሆነ በዚህ መፅሃፍ ድንጋጌዎች መሠረት የኪሣራ ሒደትን ለማስጀመር መብት ባላቸው ሌሎች ሰዎች ጥያቄ አቅራቢነት የሚደረግ እንደጥያቄው አይነትና ሁኔታ የባለዕዳው ንግድ ወይም ዕዳ በአዲስ የሚደራጅበት ወይም የባለዕዳው መክሰር የሚታወጅበትና በግዴታ የሚደረግ የንብረት ሽያጭ የሚከናወንበት ሂደት ነው አንቀጽ አላማ የኪሳራ ሂደት አላማዎች የሚከተሉት ናቸው በገበያ ውስጥ መተማመንን በመፍጠር የኢኮኖሚ መረጋጋትና እድገት እንዲኖር ማድረግ ዕዳን ለማስመለስ በሚደረጉ የተናጠል እርምጃዎች ሀብት እንዳይባክን እና እንዲጠበቅ ማድረግ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መብታቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲያስከብሩበት ማስቻል በተመሳሳይ ሁኔታ ላይ በሚገኙ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መካከል ፍትሐዊነትን መጠበቅ የማገገሚያና የኪሳራ ሂደቱ ጊዜውን የጠበቀ ቀልጣፋ እና ገለልተኛ እንዲሆን ማድረግ ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች መብት አውቅና መስጠትና የመብት ጠያቂዎችን ደረጃ የሚመለከት ግልፅ ድንጋጌ ማስቀመጥ በጊዜያዊ የገንዘብ ችግር ምክንያት ዕዳ ከመክፈል ያቋረጡ ወይም ለማቋረጥ የተቃረቡ ነጋዴዎች እንደገና ተደራጅተው እንዲያገግሙ እድል መስጠት እና በኪሣራ ሂደት ውስጥ አልፈው ማገገም ያልቻሉትን ከንግዱ እንዲወጡ በማድረግ የአዲስ ጅማሬ ተስፋ መስጠት አንቀጽ የተፈጻሚነት ወሰን የዚህ መፅሃፍ ድንጋጌዎች የእሽሙር ማኅበራት ከሆኑት በስተቀር ነጋዴ በሆኑ ሌሎች ሰዎች ላይ ተፈፃሚዎች ይሆናሉ በሌላ ሕግ እንዲታይ ካልተደነገገ በስተቀር በሌሎች ሕጎች መሠረት የተቋቋሙና የሚገዙ ነጋዴዎች ላይ የዚህ መፅፃፍ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ በዚህ መጽሃፍ ድንጋጌዎች መሠረት የተጀመረ የኪሣራ ሂደት ከኢትዮጵያ ውጪ በሚገኙ የባለፅዳው ንብረቶች ላይም ተፈጻሚ ይሆናሉ አንቀጽ ሥልጣን ስላለው ፍርድ ቤት ፅዳን እንደገና ከማደራጀት አና ከመክሠር ጋር በተያያዘ የሚቀርብ አቤቱታ የሚታየው የነጋዴው ስራ በተቋቋመበት ነጋዴው ከአንድ በላይ የሆኑ የንግድ መደብሮች ያሉት እንደሆነ ዋናው የንግዱ ሥራ ወይም ዋናው መስሪያ ቤት ባለበት ቦታ ሥልጣን ባለው ፍርድ ቤት ይሆናል በውጪ ፃገር ባለ ፍርድ ቤት የተሰጠው የኪሳራ ውሳኔ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለ የባለዕዳው ንብረት ላይ ተፈጻሚ የሚሆነው ፍርድ ቤቱ አግባብነት ያለው ጥያቄና ማመልከቻ ሲቀርብለት ሀ የሃገሪቱን ሕጎች እና ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸውንና ያጸደቀቻቸውን ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች እና ሌሎች ልዩ ድንጋጌዎች በመከተል ወይም ለ ውሳኔው በተሰጠበት ሀገር በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የተሰጠ ፍርድ የሚፈጸም ከሆነ ወይም ወደፊት እንደሚፈጸም ማረጋገጫ የሚቀርብ ከሆነ በፃገሪቱ ሉዐላዊነት ደህንነት ህዝባዊና ማህበራዊ ጥቅሞች እንዲሁም በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ገንዘብ ጠያቂዎች መብትና ጥቅም ላይ ምንም ጉዳት የማይደርስ መሆኑን ያረጋገጠ እንደሆነ ነው የዓለምአቀፍ ስምምነቶች ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው የንግዱ ዋና መሥሪያ ቤት በውጪ አገር ያለ እና መክሠሩ በውጪ አገር ፍርድ ቤቶች የተወሰነ ቢሆንም መክሠሩ በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ሊታይ ይችላል አንቀጽ ስለ ክፍያ መቋረጥ ሁኔታዎች ለዚህ መጽዛፍ ዓላማ የክፍያ መቋረጥ ማለት የመክፈያ ጊዜያቸው የደረሱ ዕዳዎችን ወይም የመክፈያ ጊዜያቸው ያልደረሱ ዕዳዎችን ወደፊት ለመክፈል ያለመቻል ወይም ፅዳው ከሐብቱ በላይ ሲሆን ነው የባለዕዳውን የመክፈል ችሎታ ለመወሰን ፍርድ ቤቱ የሚከተሉትን ሁኔታዎች ይመረምራል ሀ የባለዕዳውን አጠቃላይ የሐብት መጠን ለ የባለዕዳውን አጠቃላይ የዕዳ መጠን ሐ የባለዕዳውን የገንዘብ ፍሰት መ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች የተናጠል መብት የማስከበር እንቅስቃሴ በንብረቱ ዋጋ አና በንግዱ ቀጣይነት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽዕኖ እና ሠ ተያያዥ የሆኑ የገበያና የገንዘብ ሁኔታዎችን ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከቱትን ጉዳዮች ለመመርመር ሀ ባለዕዳው በአቤቱታው ወይም በመልሱ ያያያዛቸውን የሒሳብ መግለጫዎች ለ እነዚህ በቂ ሆነው ካልተገኙ በግልጽ በለያቸው ጉዳዮች ላይ ቀዳሚ ምርመራ በማዘዝ በምርመራው የተገኙ ማስረጃዎችን ይመለከታል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የቀረበለትን አቤቱታና በአቤቱታው ላይ በባለዕዳው የተሰጠውን ምላሽ ከመረመረ በኋላ የነጋዴውን መክሠር የሚያረጋግጥ ውሳኔ ካልሰጠ በስተቀር አንድ ነጋዴ ዕዳውን መክፈል በማቋረጡ ብቻ አእንደከሰረ አይቀጠርም ርዕስ ሁለት ዕዳን እንደገና ማደራጀት ምዕራፍ አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ ዕዳን እንደገና ማደራጃት ትርጉምና አላማዉ ፅዳን እንደገና ማደራጀት ማለት ዕዳዉን መክፈል ያቋረጠ ወይም ሊያቋርጥ ያለ ባለዕዳ የኪሳራ ዉሳፄ ከተሰጠ ወይም ከመሰጠቱ በፊት በገንዘብ መብት ጠያቂዎች ድምጽ ብልጫ እና በፍርድ ቤት ዉሳኔ መሰረት ዕዳዉን አንደገና በማደራጀት ባለዕዳዉ የንግድ ስራዉን እያከናወነ አንዲቀጥል ወይም የንግድ ስራዉን እንደገና እንዲጀምር የሚያስችል ስርአት ነዉ ፅዳ እንደገና ተደራጅቷል የሚባለዉ በዚህ መጽሐፍ ድንጋጌዎች መሰረት የዕዳዉ መጠን አይነት እና የአከፋፈል ሁኔታዎች በሌላ የዕዳ ወይም የመብት አይነት መጠንና የአከፋፈል ሁኔታዎች በፍርድ ሲለወጡ ነዉ ዕዳ ከዚህ በታች ከተመለከቱት በአንዱ ወይም ከአንድ በላይ በሆኑት ጥምረት አንደገና ሊደራጅ ይችላል ሀ የመክፈያ ጊዜዉን በማራዘም ለ የዕዓዉን መጠን በመቀነስ ወይም በመጨመር ሐ ዕዳዉን እኩል የበለጠ ወይም ያነሰ ዋጋ ባለዉ ሌላ አይነት ዕዳ ወይም መብት ወይም ንብረት በመተካት መ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን የባለዕዳዉ ድርጅት ባለድርሻ በማድረግ ሠ የባለዕዳውን ንብረት በከፊልም ሆነ በሙሉ ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች በመተውወይም ረ በሌሎች ተመሳሳይ መንገዶች ነው ባለዕዳዉ ለተለያዩ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ያሉበት ዕዳዎች በተለያየ መልኩ እንደገና ሊደራጁ ይችላሉ ዕዳን በአዲስ የማደራጀት ሂደትና ዉጤት በርእስ ሁለት ባሉት ድንጋጌዎች መሰረት ይገዛል በአንድ ወይም ከዚህ በላይ ባሉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎችና ባለዕዳ መካከል በዚህ መጽሐፍ ድንጋጌዎች ዉጭ በዉል የሚደረግ ዕዳን በአዲስ የማደራጀት ስምምነት አግባብነት ባላቸዉ የዉል ሕግ ድንጋጌዎች ይገዛሉ አንቀጽ የዕዳ እንደገና መደራጀት ላይ የሚሰጥ ፍርድ ማስታወቂያ የዕዳ እንደገና መደራጀትን በማጽደቅ ወይም ውድቅ በማድረግ የተሰጠ ፍርድ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ያለውን አካፄድ በመከተል በማስታወቂያ መዉጣት አለበት አንቀጽ የዕዳ እንደገና መደራጀትን በተመለከተ በተሰጠ ፍርድ ላይ ይግባኝ ስለማለት የዕዳ እንደገና መደራጀትን በማጽደቅ ወይም ውድቅ በማድረግ በተሰጠ ፍርድ ላይ ባለዕዳዉ ወይም በዚህ ሕግ አንቀጽ መሰረት የተቃወሙት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ይግባኝ ሊሉ ይችላሉ ይግባኝ ሊቀርብ የሚቻልበት ጊዜም የፍርድ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ አስከ አስራ አምስት ቀን ድረስ ነዉ የይግባኙችንም ማመልከቻ እንደአግባብነቱ ባለዕዳዉ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው በክርክሩ ዉስጥ የሚገኙት ባለጉዳዮች ሁሉ እንዲያዉቁት መደረግ አለበት አንቀጽ በንግድ መዝገብ ስለመግባት ፅዳን እንደገና ለማደራጀት የቀረበ ሐሳብ የጸደቀበት ወይም ውድቅ የተደረገበት ፍርድ በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተደነገገዉ መሰረት አግባብ ያለው የፍርድ ቤት አካል በንግድ መዝገብ መግባቱን ማረጋገጥ አለበት አንቀጽ በባለዕዳዉ ላይ ስለሚደረግ ክልከላ አንደገና በተደረገው አደረጃጀት ወይም በፍርዱ ዉስጥ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በቀር ባለዕፅዳዉ እንደገና በተደረገው አደረጃጀት ዉስጥ የተካተቱትን በሙሉ እስኪፈጽም ድረስ የማይንቀሳቀስ ንብረቶቹን እንዳይሸጥ አንዳይለዉጥ ወይም እንዳያስይዝ ወይም የመያዣ መብት እንዳይሰጥና በጠቅላላዉም ለሥራዉ ዐይነት በሚያስፈልገዉ አኳጊን ካልሆነ በቀር ከንብረቱ እንዳይቀንስ የተከለከለ ነው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተዉን ክልከላ በመጣስ የተሠራ ማናቸዉም ሥራ እንደገና የተደረገው አደረጃጀት ከመጽደቁ በፊት የነበሩትን የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በሚመለከት ውጤት አይኖረውም አንቀጽ ዕዳን እንደገና የማደራጀትን አፈጻጸም ስለመቆጣጠር ዕዳን የማደራጀት ተቆጣጣሪው ዕዳዉ እንደገና እንዲደራጅ የቀረበዉን ሐሳብ በማጽደቅ የተሰጠዉን ውሳኔዬ አፈጻፀም በውሳኔው በተመለከተው ስነስርዓት መሰረት ይቆጣጠራል ዕዳን የማደራጀት ተቆጣጣሪው ገንዘብ ጠያቂን ሊጎዳ የሚችል ነገር ሲያጋጥመው ለፍርድ ቤቱ ማሳወቅ አለበት ተቃራኒ ድንጋጌ ቢኖርም ፍርድ ቤቱ ዕዳን የማደራጀት ተቆጣጣሪው በስራ ላይ በሚቆይበት ጊዜ ያወጣቸውን ወጪዎች እና የሚከፈለውን የአገልግሎት ክፍያ ይወስናል አንቀጽ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ዉጤት የንብረት መያዣ ያላቸዉና መያዣቸዉንም ያልለቀቁ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች አንዲሁም መብታቸዉን ያገኙት የፍርድ ቤቱ ሂደት ከተጀመረ በኋላ የሆኑ መያዣ የሌላቸዉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች እንደገና በተደረገው የፅዳ ማደራጀት አይገደዱም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው አንደተጠበቀ ሆኖ ዕዳዉ አንደገና የተደራጀበት ውሳኔ በዚህ መጽፃፍ ድንጋጌዎች መሰረት ከተሻረ ወይም ቀሪ ከሆነ አንደገና በተደረገው ማደራጀት መሰረት ሙሉ ለመሉ የተከፈላቸዉ ካልሆኑ በስተቀር የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ በቀደመዉ ማደራጀት መሰረት የነበራቸዉን ገንዘብ መጠየቅ ይችላሉ በቀደመዉ ማደራጀት መሰረት የገንዘብ ጥያቄ ሲቀርብ እንደገና በተደረገው ማደራጀት የተከፈላቸዉ ገንዘብ ግምት ዉስጥ ይገባል ምዕራፍ ሁለት ኪሳራ በፍርድ ቤት ከመታወጁ በፊት ዕዳን እንደገና ስለማደራጀት አንቀጽ ዕዳን እንደገና ለማደራጀት የሚቀርብ ጥያቄ አንድ ባለዕዳ ዕዳውን መክፈል ካቋረጠ ወይም ሊያቋርጥ ከደረሰ በዚህ መጽሐፍ ድንጋጌዎች መሰረት ኪሳራ ከመታዎጁ በፊት ባለዕዳው አራሱ ወይም ማንኛውም ገንዘብ ጠያቂ በዚህ ርአስ ድንጋጌዎች መሠረት ዕዳ እንደገና የማደራጀት ሂደት እንዲከፈትለት ስልጣን ላለዉ ፍርድ ቤት ማመልከት ይችላል የኪሳራ ሂደቱ ተጀምሮና ኪሳራው ከመታወጁ በፊት ባለዕዳዉ ዕዳዉ እንደገና እንዲደራጅ ጥያቄ ካቀረበ እናፍርድ ቤቱ ከፈቀደ በዚህ ርእስ ድንጋጌዎች መሰረት ይታያል አንቀጽ ስለ ጥያቄዉ አቀባበል ሁኔታዎች ዕዳን እንደገና የማደራጀት ጥያቄ ተቀባይነት እንዲያገኝ ባለዕዳዉ በሚያቀርበዉ ጽሑፍ ያሉበትን ዕዳዎች በሙሉ በመዘርዘር በምን መልኩ እንደገና እንደሚደራጁ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት ባለዕዳው ዕዳዉን መክፈል ያቋረጠ ወይም ሊያቋርጥ የደረሰ መሆኑን የሚያስረዱና በታወቁ የሂሳብ አዋቂዎች የተረጋገጡ መግለጫዎችን ማያያዝ አለበት ባለዕዳዉ ዕዳዎቹን መክፈል ያቋረጠበትን ወይም የሚያቋርጥበትን እና እንደገና ለማደራጀት የጠየቀበትን ምክንያቶች የሚያመለክት መግለጫና ማስረጃዎች ማቅረብ አለበት ፍርድ ቤቱ በመግለጫዎቹ ያልተካተቱ ጥያቄዎችን ዉድቅ ያደርጋል ወይም እንደ ነገሩ ሁኔታ ጉድለቶቹን ጠቅሶ ተሟልተዉ እንዲቀርቡ ያዛል አንቀጽ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ፍርድ ቤቱ ባለዕዳዉ ዕዳዉን መክፈል ማቋረጡን ወይም የሚያቋርጥ መሆኑን ካላመነበት ፅዳዉን እንደገና ለማደራጀት የቀረበዉን ጥያቄ ውድቅ ማድረግ አለበት ፍርድ ቤቱ ባለዕዳዉ ዕዳዉን መክፈል ማቋረጡን ወይም የሚያቋርጥ መሆኑን ቢቀበለውም ፅዳን እንደገና ለማደራጀት የቀረበውን ሐሳብ ዉድቅ ካደረገው የባለዕዳዉን መክሰር ያዉጃል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ እና መሰረት እንደገና የመደራጀት ጥያቄዉን ዉድቅ ካላደረገዉ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሂደትን ይጀምራል አንቀጽ የባለዕዳዉን መክሰር ማወጅ ባለዕዳዉ ንብረቱ ቢሸጥና ቢከፋፈል የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ሊያገኙ የሚችሉት ጥቅም ዕዳን አንደገና ከማደራጀት የተሻለ ከሆነ ዕዳዉን አንደገና በተደራጀዉ መልኩ የሚፈጽም ስለመሆኑ የሚያረጋግጡ የንብረት ወይም የሰዉ ዋስትናዎች በቂ ካልሆኑ ንብረት ደብቆ ወይም ዕዳዉን አጋኖ ከተገኘ እጅግ ቢያንስ ከሁለት ዓመት ወዲህ ወይም የንግዱን ሥራ ከጀመረ ሁለት ዓመት ያልሞላው ከሆነ ይህን ሥራ ከጀመረበት ጊዜ ወዲህ በንግድ መዝገብ ያልተመዘገበ ወይም የሒሳብ መዝገብ በሚገባ ያልያዘ ከሆነ ከኪሳራ ጋር በተያያዘ ያሉ የወንጀል ድንጋጌዎችን በመጣስ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ወይም በአለፉት አምስት አመታት መክሰሩ የታወጀበት ወይም ዕዳዉን በፍርድ ቤት እንደገና ያደራጀ ከሆነ ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን ዕዳን በአዲስ የማደራጀት ጥያቄ ዉድቅ ያደርገዋል አንቀጽ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሂደት ስለማስጀመር ፍርድ ቤቱ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሂደት እንዲጀመር ከወሰነ በዚሁ ውሳኔ ሀዕዳን እንደገና ማደራጀትን የሚቆጣጠርና የሚያቀላጥፍ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪ እንደአግባቡ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ይሰይማል ለ ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን አንስቶ ከ ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ዉስጥ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች እንዲሰበሰቡ ጥሪ ያደርግላቸዋል ውሳኔው በማስታወቂያ የሚወጣበትንና ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች የሚነገርበትንም ቀን ይወስናል ሐ ባለዕዳዉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹን ስም ዝርዝር ሞልቶ በቶሉ ለማቅረብ ያልቻለ መሆኑን በጥያቄዉ ዉስጥ ባስረዳ ጊዜ ፍርድ ቤቱ ባለዕዳው ዝርዝሩን ሞልቶ ከስምንት ቀን ባልበለጠ ጊዜ ዉስጥ እንዲያቀርብ ያዘዋል መ ባለዕዳው ለማደራጀቱ ሂደት ወጪ መሸፈኛ የሚሆን በቂ ገንዘብ ከስምንት ቀን ባልበለጠ ጊዜ ዉስጥ በፍርድ ቤቱ አንዲያስቀምጥ ያዘዋል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ ሐ ወይም መ የተሰጠ ትአዛዝ ያልተጠበቀ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ባለዕዳዉ መክሰሩን ያዉጃል አንቀጽ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪ ላይ በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ ያሉት ድንጋጌዎች ተፈጻሚዎች ይሆናሉ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪ በሰጣቸዉ ትእዛዞች ላይ በጉዳዩ ያገባኛል የሚል ማንኛውም ሰዉ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት መቃወሚያ ለማቅረብ ይችላል አንቀጽ ውሳኔውን ስለ ማስታወቅ ፅዳን እንደገና ለማደራጀት በቀረበው ጥያቄ ላይ የተሰጠዉ ውሳኔ በሚመለከተው የፍርድ ቤት ሐላፊ አማካይነት በፍርድ ቤቱ መግቢያ በር ላይ ይለጠፋል የማስታወቂያው ቅጂም ሕጋዊ ማስታወቂያን ለመቀበል በተፈቀደለት ጋዜጣ ይወጣል የሚመለከተው የፍርድ ቤት ሐላፊም በአንቀጽ ንኡስ አንቀጽ በተደነገገዉ መሠረት ውሳኔው በንግድ መዝገብ እንዲገባ ያደርጋል የዕዓ ማደራጀት ተቆጣጣሪውና የሚመለከተው የፍርድ ቤት ሐላፊ ፈርመዉበት በባለዕዳዉ የሒሳብ መዝገቦች ውሳኔ ስለመሰጠቱ ምልክት ካደረጉ በኋላ መዝገቦቹን ለባለዕዳዉ ይመልሱለታል አንቀጽ ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች የሚሰጥ ማስታወቂያ የዕዓ ማደራጀት ተቆጣጣሪው የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ የሚሰበሰቡበትን ቦታና ጊዜ ይወስናል በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ለ መሠረት ፍርድ ቤቱ በወሰነዉ ጊዜ ዉስጥ የሚመለከተው የፍርድ ቤት ሐላፊ እንዳስፈላጊነቱ በተመዘገበ ደብዳቤ በፋክስ ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚያስችል ማናቸውም ዘዴ ለአያንዳንዱ የገንዘብ መብት ጠያቂ ቀጥሉ የተዘረዘሩትን የያዘ ማስታወቂያ መላክ ይኖርበታል ሀ የባለዕዳዉን እና የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪውን ስም ለ ለገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ጥሪ የተደረገበት ውሳኔ የተሰጠበትን ቀን እና የስብሰባዉን ጊዜና ቦታእና ሐ ባለእዳዉ ያቀረባቸዉን ሐሳቦች በአጭሩ አንቀጽ ስለሰነድ ማስረጃዎች ማስታወቂያዎች በታዘዘው መሰረት መውጣታቸውን እና ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች መድረሳቸውን የሚያሳዩ የሰነድ ማስረጃዎች ከመዝገቡጋራ ተያይዘዉ መቀመጥ አለባቸዉ አንቀጽ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሄደትን የመጀመር ዉጤት ፍርድ ቤቱ በቀረበዉ ጥያቄ ላይ የመጨረሻ ፍርድ እስኪሰጥ ድረስዕዳን እንደገና የማደራጀት ሄደት ከተጀመረበት አንሥቶ የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት አስካለው ጊዜ መብቱን ያገኘ የገንዘብ መብት ጠያቂ የማስፈጸምን ሥርዐት ለመጀመር ወይም ለመቀጠል በባለዕዳዉ ንብረቶች ላይ የቀዳሚነትን መብት ለማግኘት ወይም በመያዣነት ለማስመዝገብ አይችልም የይርጋ ዘመን መቆጠር ክስ የመቀጠል መብት ማጣት ወይም የመብት መከልከል ሁሉ ይታገዳል የቀዳሚነት መብት የሌላቸዉ ተራ ዕዳዎች የመክፈያ ጊዜያቸው እንደደረሰ ይቆጠራል ሆኖም የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን በሚመለከት ወለዶች ከመታሰብ ይታገዳሉ ለግብር ተከፋይ የሚሆኑት ገንዘቦች የቀዳሚነት መብት ባይኖራቸዉም እንኳ በዚህ አንቀጽ የተመለከቱት ዉሳኔዎች አይፈጸሙባቸዉም አንቀጽ የባለዕዳዉን ንብረቶች ስለ ማስተዳደር ፅዳን አንደገና የማደራጀት ሂደት በሚከናወንበት ጊዜ ባለዕዳዉ በዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው ተቆጣጣሪነት ንብረቶቹን የማስተዳደር እና ንግዱን የመምራት ኃላፊነቱን እንደ ያዘ ይቆያል የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው እና ፍርድ ቤቱበማናቸውም ጊዜ የሂሳብ መዝገቦችንና ሰነዶችን መመርመር ይችላሉ አንቀጽ የባለዕዳዉ ድርጊቶች በገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ላይ መቃወሚያ ሰለ አለመሆናቸዉ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሂደት በሚከናወንበት ጊዜ ባለዕዳዉ የሚሰጣቸው ሥጦታዎችና ሌሎች ልገሳዎች ወይም የሚሰጣቸዉ ዋስትናዎች በገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ላይ መቃወሚያ ሊሆኑባቸዉ አይችሉም የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው ጥቅም የሚገኝበት መሆኑን በማገናዘብ በጽሑፍ ካልፈቀደለት በስተቀር ባለዕዳዉ በሐዋላ ወረቀት ወይም በተስፋ ሰነድ ቢሆንም እንኳ ብድር የገባባቸዉ ዉሎችያደረጋቸዉ ግልግሎች ወይም ስምምነቶች ለንግዱ ሥራ አስፈላጊ ሳይሆን ያደረገዉ የንብረት ማስተላለፍ ወይም የሚንቀሳቀስ እና የማይንቀሳቀስ የመያዣ መብት መፍቀድ ሁሉ በገንዘብ መብት ጠያቂዎች ላይ መቃወሚያ ሊሆኑባቸዉ አይችሉም አንቀጽ ዕዳን እንደገና በማደራጀት ሂደት ስለሚደረግ የኪሳራ መታዎጅ ባለዕዳዉ የዚህን ሕግ አንቀጽ እና ድንጋጌዎች ከተላለፈ ወይም ከንብረቱ የተወሰነውን ከደበቀ በማጭበርበር ከዝርዝር ውስጥ ሳያካትታቸው የቀሩ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ከነበሩ ዕዳዉን ከፍ አድርጎ ካሳየ ወይም በአጠቃላይ የማጭበርበር ድርጊት ፈጽሞ ከተገኘ በወንጀል የሚኖረው ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው በሚሰጠው ሐሳብ መሰረት የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው ጉዳዩን ለፍርድ ቤት ማሳወቅ አለበት ፍርድ ቤቱም የባለዕዳውን መክሰር ማወጅ አለበት አንቀጽ በዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው ስለሚዘጋጅ መግለጫ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው የባለዕዳዉን የንብረት ዝርዝር መዝገብ ያደራጃል የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹንና የባለዕዳዎቹን ዝርዝር ይመረምራል ስለ ንግዱ ሁኔታና ስለ ባለዕዳዉ ስነምግባር ዕዳን እንደገና ለማደራጀት ስለቀረበዉ ሐሳብ እና ለገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ስለቀረቡት ዋስትናዎች የሚያስረዳ ዝርዝር መግለጫ ያዘጋጃል መግለጫዉም የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ስብሰባ ከመደረጉ ቢያንስ ከአምስት ቀናት በፊት ለሚመለከተው የፍርድ ቤት ሐላፊ መሰጠት ይኖርበታል አንቀጽ ስለገንዘብ መብት ጠያቂዎች ስብሰባ የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ሰብሳቢ የዕዳ ማደራጀት ተቆጣጣሪው ነዉ ማንኛዉም የገንዘብ መብት ጠያቂ በራሱ ወይም ስልጣን ባለዉ እንደራሴ ወይም በወኪሉ አማካይነት በስብሰባዉ ሊሳተፍ ይችላል ባለዕዳዉ ራሱ መገኘት አለበት ሆኖም ከአቅም በላይ ምክንያት ካጋጠመው በተቆጣጣሪው ፈቃድ በእንደራሴ ወይም በወኪል ሊወከል ይችላል በዚህ ሕግ አንቀጽ መሰረት የቀረበዉ መግለጫ ከተነበበ በላ ባለዕዳዉ የመጨረሻ ሐሳቡን ያቀርባል አንቀጽ ዕዳን እንደገና ለማደራጀት የቀረበውን ሐሳብ ስለመመርመር ማንኛዉም የገንዘብ መብት ጠያቂ የቀረበዉን አሳብ የማይቀበልበትን ምክንያት ለመግለጽና በጣምራ በሚቀርቡት የገንዘብ መጠየቂያ መብቶች ላይ ክርክር ለማንሳት ይችላል ባለዕዳዉም በበኩሉ ምላሽ ለመስጠትና በሚቀርቡትም ዕዳዎች ላይ ክርክር ለማንሣት ይችላል የሚጠየቀቅባዉን ማስረጃዎች በሙሉ መስጠት አለበት ክርክሮቹ በአጭሩ በቃለጉባኤ ተመዝገበዉ ማስረጃዎችም ካሉ መያያዝ አለባቸዉ አንቀጽ የስብሰባዉን ጊዜ ስለ ማራዘም ስብሰባ በተጠራበት ቀን ጉዳዩን ለመቋጨት ያልተቻለ እንደሆነ በስብሰባው ለተገኙትም ሆነ ላልተገኙት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ጥሪ ሳይደረግ ስብሰባውን ወደቀጣዮቹ የስራ ቀናት በማስተላለፍ አስኪጠናቀቅ ድረስ ሳይቋረጥ እንዲቀጥል መደረግ አለበት አንቀጽ ክርክር የተነሣባቸዉን ዕዳዎች ለጊዜዉ ስለመቀበል የዕዓ ማደራጀት ተቆጣጣሪው ለድምጽ አሰጣጥና ለአብላጫ ድምጽ አቆጣጠር ብቻ ክርክር የተነሣባቸዉን ዕዳዎች በሙሉ ወይም በከፊል ሊቀበላቸዉ ይችላል ሆኖም በጊዜያዊነት መቀበሉ በዕዳዎቹ ላይ የሚሰጠዉን የመጨረሻ ዉሳኔ የሚነካ አይሆንም ተቀባይነት ያላገኙ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ተቀባይነት አግኝተው ቢሆን ኖሮ የድምፅ ብልጫዉን አቆጣጠር ሊለውጠው ይችል ከነበረ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ጥያቄዉ ለመጽደቅ በሚቀርብበት ፍርድ ቤት አቤቱታ ለማቅረብ ይችላሉ አንቀጽ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሐሳብን ለመቀበል ስለሚያስፈልገዉ የድምጽ ብልጫ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሐሳብ ተቀባይነት እንዲያገኝ የቀዳሚነት መብት ወይም የመያዣ መብት ከሌላቸዉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ቢያንስ ሁለት ሦሥተኛው በተገኙበት በአብላጫ ድምጽ መደገፍ አለበት በባለዕዳዉ ንብረቶች ላይ የመያዣ መብት ያላቸዉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መብታቸውን ካልተው በስተቀር ድምጽ መስጠት አይችሉም። አንቀጽ በውሳኔው ላይ ስለሚጠየቅ ይግባኝ የመክሠር ውሳኔ እንዲታወቅ ከተደረገበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ይግባኝ ማቅረብ ይቻላል ይግባኙም በተፋጠነ ሥነ ሥርዓት በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ ይወሰናል ውሣኔውም ወዲያውኑ ተፈጻሚ ይሆናል አንቀጽ መቃወሚያ ወይም ይግባኝ የማይቀርብባቸው ውሣኔዎች ከዚህ በታች ባሉት ውሣኔዎች ላይ መቃወሚያ ወይም ይግባኝ ሊቀርብባቸው አይችልም ህ የንብረት አስተዳዳሪውን ወይም ምትኩን ለመሾም ወይም ለመሻር የተሰጠ ውሳኔ ለ ነጻ ለመውጣት በቀረቡ ጥያቄዎች እንዲሁም ለዕዳ ከፋዩና ለቤተሰቡ ርዳታ ለማግኘት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ የተሰጠ ውሳኔ ሐ የሐብቱ አካል የሆኑ ንብረቶች ወይም ሸቀጦች እንዲሸጡ የሚፈቅድ ውሣኔ መ ንብረት አስተዳዳሪው በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በሰጠው ትዕዛዝ ላይ ለፍርድ ቤት በቀረበ አቤቱታ ላይ የተሰጠ ውሳኔ ሠ የንግዱ ሥራ እንዲቀጥል የሚፈቅድ ውሣኔ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መ የተመለከተው ጉዳይ በፍርድ ቤት በሚታይበት ጊዜ ንብረት አስተዳዳሪው ፍርድ ቤት መቅረብ አይችልም አንቀጽ የመክሰር ውሳኔን ስለማንሳት የከሰረ ባለዕዳ ውሣኔ በተሰጠበት ቀንና በተቃውሞ ወይም በይግባኝ ላይ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት ባሉት ቀናት መካከል ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች በመክፈል ዕዳን በማቻቻል ከእነርሱ ጋር ስምምነት በማድረግ ወይም በሌሎች መንገዶች መክፈልን ከማቋረጥ ሁኔታ የወጣ እንደሆነ የመክሰሩ ውሳኔ መነሳት አለበት በማናቸውም ሁኔታ ቢሆን የመክሰሩን ሥራ የሚያስፈጽሙት ሰዎች የፈጸሟቸው ሕጋዊ የሆኑ ሥራዎች ያስገጂቸው ውጤቶች እንደጸኑ ይቆያሉ ምዕራፍ ሁለት የኪሳራ ሂደቱን ስለሚያስፈጽሙ ሰዎች ክፍል አንድ ፍርድ ቤት አንቀጽ ስለ ፍርድ ቤቱ ሥልጣን የመክሰርን ውሣኔ የወሠነው ፍርድ ቤት የኪሳራ ሂደቱን በሙሉ ይቆጣጠራል ከኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ሥልጣን በላይ በሆኑት በማናቸውም ነገሮች ላይ ውሣኔ ይሰጣል የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው በሚሰጣቸው ትዕዛዞች ላይ የሚቀርቡ ይግባኞችን ያያል አንቀጽ ስለ ፍርድ ቤቱ የዳኝነት ሥልጣን በባለዕዳው ላይ የኪሳራ ውሳኔ ያስተላለፈው ፍርድ ቤት ከኪሳራ ጋር በተያያዘ በሚነሱ በማናቸውም የመብት ጥያቄዎች ላይ የዳኝነት ስልጣን ይኖረዋል በመደበኛ ፍርድ ቤት ወይም በሕግ ስልጣን በተሰጠው ሌላ አካል በመታየት ላይ ያለ ጉዳይ የኪሳራውን ጉዳይ በማየት ላይ ባለው ፍርድ ቤት ተጠቃሎ ይታያል ውሳኔ ያገኘ ጉዳይም ካለ አፈጻጸሙ ታግዶ ከኪሳራው ጉዳይ ጋር አብሮ ይታያል ክፍል ሁለት የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪ አንቀጽ ስለኪሰራ ሂደት ተቆጣጣሪው መሰየምና ስልጣን የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የኪሳራ ሂደቱን ለመቆጣጠርና ለማቀላጠፍ በፍርድ ቤት የሚሰየም ሰው ነው ተቆጣጣሪው ሀ ከኪሳራ ሂደቱ የሚመነጩና በፍርድ ቤቱ ስልጣን ስር የሚወድቁ ጥያቄዎችንና ክርክሮችን ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል ይህም በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ውስጥ ይጠቀሳል ለ አግባብነት ያላቸውን ባለሥልጣናት በመጠየቅ ወይም በራሱ ሥልጣን ከኪሳራው ጋር የተያያዙ ንብረቶችን ለመጠበቅ አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎችን ሁሉ ይወስዳል ሐ በሕግ የተደነገገ ሲሆን ወይም አስፈላጊ ሆኖ ያገኘው እንደሆነ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ ስብሰባ እንዲደረግ ጥሪ ያደርጋል መ ራሱ እንዲሰይም በሕግ በተለየ ካልተሰጠው በስተቀር ንብረት አስተዳዳሪው ለኪሳራው ሂደት አስፈላጊ የሆኑ ረዳቶችን እንዲሰይም ሊፈቅድለት ይችላል ሠ ንብረት አስተዳዳሪው በከሣሽነት ወይም በተከሳሽነት በፍርድ ቤት ቀርቦ እንዲከራከር በጽሁፍ ይፈቅድለታል አንቀጽ ስለኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ትእዛዝ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ትእዛዝ ወዲያውኑ በፍርድ ቤት መዝገብ መቀመጥ አለበት ስለመቀመጡም በተመዘገበ መልእክት ወይም ስለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚቻል ማናቸውም ሌላ ዘዴ ለባለጉዳዮቹ መገለጽ ይኖርበታል ተቆጣጣሪው በሰጠው ትእዛዝ ላይ ባለጉዳዮቹ ትእዛዙን እንዲያውቁት ከተደረገበት ቀን አንስቶ ባሉት አስር ቀናት ውስጥ መቃወሚያቸውን ለፍርድ ቤቱ ማቅረብ ይችላሉ ፍርድ ቤቱም በመጀመሪያው ቀጠሮ ውሳኔ መስጠት አለበት አንቀጽ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪውን ስለመተካት ፍርድ ቤቱ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪውን በማናቸውም ጊዜ በሌላ ሊተካው ይችላል ክፍል ሦሥት ንብረት አስተዳዳሪ አንቀጽ ስለ ንብረት አስተዳዳሪ መሰየም ፍርድ ቤቱ አግባብ ባለው አካል ከተዘጋጀ የንብረት አስተዳዳሪዎችና ተቁጣጣሪዎች መዝገብ ውስጥ ከተመዘገቡ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ኗሪ ከሆኑት መካከል ንብረት አስተዳዳሪውን ይሰይማል የሚሰየሙ ንብረት እሰተዳዳሪዎች ቁጥር እንደ ኪሣራው ሒደት ውስብስብነት እና እንደ ንብረቶቹ ብዛት በፍርድ ቤቱ ይወሰናል ከአንድ በላይ ንብረት አስተዳዳሪዎች የተሰየሙ እንደሆነ በአንድ ላይ ይሰራሉ ፍርድ ቤቱ እንደአስፈላጊነቱ ከመካከላቸው ለአንዱ ወይም ለብዙዎቹ ለብቻ የመሥራት መብትን መስጠት ይችላል እንዲህ በሆነ ጊዜ ይሔን ሥልጣን የተቀበሉ ንብረት አስተዳዳሪዎች ብቻ አላፊዎች ይሆናሉ የሚከተሉት ሰዎች በንብረት አስተዳዳሪነት ሊሰየሙ አይችሉም ሀ ከዚህ ቀደም በማጭበርበር መክሰር ወንጀል ወይም በሌላ ለንብረት አስተዳዳሪነት ብቁ በማያደርግ ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘና ያልተሰየመ ሰው ለ የሕዝባዊ መብቱን ለጊዜውም ቢሆን የሚከለከል የቅጣት ውሳኔ የተፈረደበት ሰው ሐ ባለዕዳው የንግድ ማህበር የሆነ እንደሆነ የማህበሩ ባለድርሻዎች ወይም የማህበሩን ስራ በበላይነት የሚመሩ ሰዎች መ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሐ ስር የተገለጸ ሰው የትዳር አጋር እና እስከ አራት ደረጃ ድረስ የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ያላቸው ሰዎች ሠ ባለዕዳው የተፈጥሮ ሰው በሆነ ጊዜ የባለዕዳው የትዳር አጋር እና እስከ ሁለተኛ ደረጃ ድረስ የሥጋ ወይም ጋብቻ ዝምድና ያላቸው ሰዎች እና ረ ከኪሣራው ላይ የገንዘብ መብት ጠያቂ የሆነ ሰው ሰ በንብረት አስተዳዳሪነት መስራቱ የጥቅም ግጭት ሊፈጥር የሚችልበት ማንኛውም ሰው ንብረት አስተዳዳሪው የባለዕዳውን ንብረት መግዛት አይችልም አንቀጽ ስለ ንብረት አስተዳዳሪው ሥልጣን ንብረት አስተዳዳሪው የከሠረውን ባለዕዳ ንብረት በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ስር ሆኖ የማስተዳደር ሐላፊነት አለበት ከሶስተኛ ወገኖች ጋር ለሚኖር ግንኙነት ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኅብረት እንደራሴ ነው ንብረት አስተዳዳሪው ሐላፊነቱን ለሌላ ሰው ማስተላለፍ አይችልም ሆኖም የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ከፈቀደለት ለአንዳንድ ሥራ በተለየ ሐላፊነቱን ለሌላ ሰው ማስተላለፍ ይችላል አንቀጽ ገንዘብ ስለማስቀመጥ በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የሚወሰኑት የአስተዳደር እና ሌሎች ወጪዎች ሁሉ ከተቀነሱ በኋላ ንብረት አስተዳዳሪው የሚቀበላቸው ገንዘቦች ሁሉ ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ ወዲያውኑ ተቀማጭ መሆን ይኖርባቼዋል ይኸውም ገንዘብ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ፈርሞ በሚሰጠው የመክፈያ ትዕዛዝ ካልሆነ በስተቀር ወጭ ሊሆን አይችልም በፍትሐብሔርና በወንጀል ሕግ የሚኖርበት ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ የዚህን አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ያልፈጸመ የንብረት አስተዳዳሪ ከሐላፊነቱ መነሳት ይኖርበታል አንቀጽ ንብረት አስተዳዳሪው በሠራው ሥራው ላይ አቤቱታ ስለማቅረብ ንብረት አስተዳዳሪው በሠራው ሥራ ላይ የከሠረው ሰው ወይም በጉዳዩ ያገባኛል የሚል ሌላ ማንኛውም ሰው ለኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው አቤቱታ ማቅረብ ይችላል የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪውም በሶስት ቀን ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል አንቀጽ ስለ ንብረት አስተዳዳሪው ከሐላፊነት መነሳት የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው በከሠረው ሰው ወይም በገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ በሚቀርብለት አቤቱታ ወይም በራሱ ተነሳሽነት ንብረት አስተዳዳሪ ከሐላፊነቱ እንዲነሳ ፍርድ ቤቱን መጠየቅ ይችላል ጸም የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው በከሰረው ሰው ወይም በገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ በቀረበለት አቤቱት ላይ በአምስት ቀናት ውስጥ ውሳኔ ያልሰጠ እንደሆነ አቤቱታ አቅራቢዎች ጥያቄያቸውን ለፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላሉ ፍርድ ቤቱም የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪውን መግለጫ የንብረት አስተዳዳሪውን ማብራሪያ እና እስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የዐቃቤሕግን አስተያየት መሰረት በማድረግ ይወስናል አንቀጽ ስለ ንብረት አስተዳዳሪው ሐላፊነት ንብረት አስተዳዳሪው ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ ሁሉ የመንግስት ስራን እንደሚያከናውን ሰራተኛ ይቆጠራል ንብረት አስተዳዳሪው ስራውን በጥንቃቄ ማከናዎንና አስፈላጊ ሲሆን በተገቢው ጥንቃቄ ስራውን ማከናዎኑን ማሳየት ይኖርበታል የፈጸመውን የአስተዳደር ሥራ ሁሉ በየቀኑ የሚመዘግብበት አስቀድሞ በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የተፈረመበት አንድ መዝገብ መያዝ አለበት የኪሳራ ሂደቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከሐላፊነቱ በተነሳ ንብረት አስተዳዳሪ ላይ የሚቀርብ የመብት ጥያቄ በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ፍቃድ እርሱን በተካው ንብረት አስተዳዳሪ መቅረብ ይኖርበታል በኪሣራው ሂደት ጊዜ ሥራውን የሚተው ንብረት አስተዳዳሪ በአንቀጽ እንደተደነገገው ስለሥራው አመራር መግለጫ መስጠት አለበት አንቀጽ የንብረት አስተዳዳሪው የሥራ ዋጋ የንብረት አስተዳዳሪውን ወጪዎችና የሥራ ዋጋ እንዲሁም የአከፋፈሉን ሁኔታ የሚወስነው የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ነው በቂ ምክንያት ከተገኘ ተቆጣጣሪው ለንብረት አስተዳዳሪው የቅድሚያ ክፍያ እንዲከፈለው ሊፈቅድ ይችላል የከሠረው ሰውና የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ተቆጣጣሪው በሰጠው ውሳኔ ላይ መቃወሚያቸውን ውሳኔው በደረሳቸው በስምንት ቀናት ውስጥ ለፍርድ ቤቱ ማቅረብ ይችላሉ በዚህ አንቀጽ ከተመለከቱት በስተቀር ለንብረት አስተዳዳሪው ሌላ ገንዘብ ሊከፈለው አይቻልም በወንጀልና በፍትሐብሔር የሚኖር ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ ይሕንን ክልከላ በመጣስ የተከፈሉ ገንዘቦች በሙሉ ተመላሽ መሆን አለባቸው ክፍል አራት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ አንቀጽ ስለኮሚቴው መቋቋም በዚህ ሕግ አንቀጽ እንደተደነገገው የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ዝርዝር አግባብ ባለው የፍርድ ቤት አካል ዘንድ ከተቀመጠበት ቀን አንስቶ ባሉት አሥር ቀናት ውስጥ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ መቋቋም አለበት የኪሳራ ሒደት ተቆጣጣሪው ጠቃሚ መሆኑን የገመተ እንደሆነ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ኮሚቴ እስከሚቋቋም ድረስ ጊዜያዊ ኮሚቴ እንዲቋቋም ማድረግ ይችላል የኪሳራ ሒደት ተቆጣጣሪው ከገንዘብ መብት ጠያቂዎች መካከል ሦስት ወይም አምስት አባላት መርጦ ኮሚቴውን ያቋቁማል ከአባላቱ መካከል የኮሚቴውን ሰብሳቢ ይሰይማል ይህንንም ለፍርድ ቤቱ በማቅረብ ያስጸድቃል ማንኛውም የኮሚቴ አባል በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው በሚቀርብ ሐሳብ መሰረት በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔ ካልሆነ በስተቀር ከሐላፊነቱ ሊነሳ አይችልም ሆኖም ተቆጣጣሪው ምትክ እንዲተካለት የጠየቀን አባል በሌላ አባል ሊተካ ይችላል ከባለዕዳው ጋር እስከ አራተኛ ደረጃ ድረስ የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ያለው ማንኛውም የገንዘብ መብት ጠያቂ የኮሚቴ አባል ለመሆን አይችልም አንቀጽ ስለኮሚቴው ተግባራት ሃሳቡን እንዲሰጥ ሕጉ የሚያስገድድበት ሁኔታ አንደተጠበቀ ሆኖ ፍርድ ቤቱ ወይም የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው ኮሚቴው ዛሳቡን አንዲሰጥ ሊጠየቅ ይችላል ኮሚቴው ውሳኔ የሚያስተላልፈው በድምጽ ብልጫ ይሆናል ኮሚቴው ባለዕዳው ያቀረበውን ሂሳብና ጉዳዩን በተመለከተ ያዘጋጀውን መግለጫ መመርመርና የንብረት አስተዳዳሪውን ሥራ መቆጣጠር አለበት ኮሚቴው በማናቸውም ጊዜ የኪሳራው ሂደት የሚገኝበትን ደረጃ እና ገቢ የሆኑትንና የተከፈሉትን ገንዘቦች ሂሳብ መግለጫ መጠየቅ ይችላልጹ ንብረት አስተዳዳሪውም በሕግ የተያዙ ጉዳዮችን በተመለከተ ከኮሚቴው ጋር መመካከር አለበት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ አባላት ለሚፈጽሙት ከባድ የሆነ ቸልተኝነት ብቻ ኃላፊዎች ይሆናሉ የኮሚቴው አባላት ለአገልግሎታቸው ዋጋ አይከፈላቸውም ሆኖም በንብረት አስተዳዳሪው ፊርማ ያወጧቸው ወጪዎች እንዲመለሱላቸው የመጠየቅ መብት አላቸው ምዕራፍ ሦስት ጊዜያዊና የመጠባበቂያ እርምጃዎች ክፍል አንድ የመጠባበቂያ እርምጃዎች አንቀጽ የባለዕዳውን መዝገቦች ስለመዝጋት በዚህ ሕግ አንቀጽ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ንብረት አስተዳዳሪው መዝገቦቹና ሒሳቦቹ ሲዘጉ ባለዕዳው እንዲገኝ ጥሪ ማድረግ ይኖርበታል ባለዕዳው በጥሪው መሰረት ያልቀረበ እንደሆነ በአርባ ስምንት ሰዓት ውስጥ እንዲቀርብና በእጁ መዛግብት ካሉም ይዞ እንዲቀርብ በተመዘገበ መልዕክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ እንዲጠራ ይደረጋል ባለዕዳው ለመቅረብ የማይችልበትን ምክንያት ያስረዳ እንደሆነ እና የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ምክንያቱ በቂ መሆኑን የተረዳ እንደሆነ ባለዕዳው ሌላ ሰው አንዲወክል ሊፈቅድለት ይችላል ባለዕዳው ራሱ ወይም በወኪል አማካኝነት ለመቅረብ ፈቃደኛ ሆኖ ካልተገኘ ባለዕዳው አንዲቀርብ ንብረት አስተዳዳሪው አስፈላጊው እንዲፈጸም ለዐቃቤ ሕግ ማስታወቅ አለበት አንቀጽ የባለዕዳውን መብቶች ስለመጠበቅ ንብረት አስተዳዳሪው ስራውን እንደጀመረ ባለዕዳው በራሱ ባለዕዳ ላይ ያለውን መብት ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ አለበት ከኪሳራ መታዎጅ በኋላ በጸደቀ ዕዳን እንደገና ማደራጀት ወይም ዚሳብ ማጣራት ባለፅዳው ያላስመዘገበውን በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን የመያዣ መብት ንብረት አስተዳዳሪው ማስመዝገብ አለበት ንብረት አስተዳዳሪው ንብረት አስተዳዳሪ መሆኑን አስረድቶ የመያዣ መብትን የሚያስመዘግበው በገንዘብ መብት ጠያቂዎች ሕብረት ስም ነው አንቀጽ በማይንቀሳቀሱ የባለዕዳው ንብረቶች ላይ የመያዣ መብትን ስለማስመዝገብ ንብረት አስተዳዳሪው የባለዕዳው በሆኑትና ወደፊትም በሚያገኛቸው የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ስም የመያዣ መብት ማስመዝገብ አለበት ኪሳራ ከታዎጀ በኋላ ዕዳን እንደገና በማደራጀት ሂደት የመጨረሻው ክፍያ ከተከፈለ በኋላ ወይም ዕዳ እንደገና ያልተደራጀ እንደሆነ የሂሣብ ማጣራቱ ሥራ ተጠናቆ ከተዘጋ በኋላ ባለዕዳው በሚያገኘው የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የመያዣ መብት አይመዘገብም አንቀጽ በንግዱ ላይ የመያዣ መብት ስለማስመዝገብ በዚህ ሕግ በሁለተኛው መጽሐፍ በአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ለ በተመለከተው መ መሰረት ሕጋዊ የሆኑትን የመያዣ መብቶች በባለዕዳው ንግድ ወይም ንግዶች ላይ ንብረት አስተዳዳሪው ማስመዝገብ አለበት በመዝገብ የሚገቡትም የሚከተሉት ናቸው ሀ የባለዕዳው ስምና አድራሻ ለ የባለዕዳው መክሰር የታወጀበት ቀን ሐ የባለዕዳውን መስሰር ያወጀው ፍርድ ቤት ስም መ የንግዱ አይነትና አድራሻ መ መያዣ የተደረገው የንግዱ ክፍል እና መያዣ የሆነ ቅርንጫፍ ወይም ወኪል ካለ አድራሻው በዚህ አንቀጽ መሠረት በሚደረግ ማንኛውም መያዣ ላይ በዚህ ህግ አንቀጽ እስከ ሉት ድንጋጌዎች ተፈጻሚዎች ይሆናሉ። አንቀጽ ንብረት መብት ወይም ገንዘብ እንዲመለስ የተሰጠ ውሳኔ ሰለ ሚኖረው ውጤት በዚህ ክፍል ድንጋጌዎች መሰረት ንብረት መብት ወይም ገንዘብ እንዲመልስ የተወሰነበት ሰው ከባለዕዳው የተቀበለውን ንብረት መብት ወይም ገንዘብ በተቀበለት ሁኔታ ለንብረት አስተዳዳሪው መመለስ አለበት ሆኖም ንብረቱን አራሱን መመለስ የማይቻል ሲሆን የንብረቱን ዋጋ ይመልሳል ንብረቱን ወይም መብቱን ለሦስተኛ ወገን አስተላልፎ እንደሆነ ንብረቱ እንዲመለስ በተወሰነበት ቀን የነበረውን የገበያ ዋጋ ይከፍላል ዋጋው ተቀንሶ የተላላፈን ንብረት ወይም መብት እንዲመልስ የተደረገ ሰው ለባለዕዳው የከፈለውን ዋጋ ወይም ንብረት ወይም መብት መልሶ የመውሰድ መብት ይኖረዋል የመክፈያ ጊዜአቸው ሳይደርስ ወይም ደርሶ የተከፈሉ ክፍያዎችን እንዲመልስ የተደረገ ሰው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ሕብረት አባል በመሆን እንደ ሌሎች የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ክፍያ የማግኘት መብት ይኖረዋል ክፍል አራት የባለዕዳውን ንብረቶች ስለማስተዳደር አንቀጽ ሰለ ንብረት አስተዳዳሪው ጠቅላላ ተግባር ንብረት አስተዳዳሪው የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪውን በማስፈቀድ በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሚበላሹትን ዋጋቸው የሚቀንሰውን ወይም ለማስቀመጥ ብዙ ወጪ የሚያስፈልጋቸውን ዕቃዎች ይሸጣል የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የሽያጩን ስርዓት እና ሁኔታዎች ይወስናል ለባለዕዳው ሊከፈሉ የሚገባቸውን ዕዳዎች ሰብስቦ ገቢ ያደርጋል የባለዕዳው ሐብት የሆኑትንና መመለስ የሚገባቸውን ንብረቶች ያስመልሳልይረከባል የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴን በማማከር እና በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ፍቃድ መሰረት የባለዕዳውን የንግድ ስራ ያካሂዳል አንቀጽ የንግድ ማሕበራት መዋጮዎች እንዲከፈሉ ስለ መጠየቅ እና ስለ ኀላፊነት የሚቀርብ ክስ በማናቸውም የንግድ ማህበር በማህበሩ የመመስረቻ ጽሁፍ ከተወሰነው ጊዜ በፊት ቢሆንም አንኳን ንብረት አስተዳዳሪው ያልተከፈሉ መዋጮዎች እንዲከፈሉ ለማስገደድ ይችላል በዚህ ሕግ አንቀጽ አና ፋ መሰረት በዳይቴክተሮች ላይ በኀላፊነት የሚቀርበውን ክስ ንብረት አስተዳዳሪው የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን ኮሚቴ በማማከር ያቀርባል አንቀጽ የባለዕዳውን ንግድ ስለ ማስቀጠል የሕዝብን ወይም የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን ጥቅም ለማስጠበቅ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ብቻ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪውን ሪፖርት እና የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን ኮሚቴ አስተያየት ከተቀበለ በኋላ ፍርድ ቤቱ ንብረት አስተዳዳሪው የንግድ ስራውን እንዲያካሂድ ሊፈቅድለት ይችላል ንብረት አስተዳዳሪው በአርሱ ምትክ የንግድ ስራውን የሚያካሂድለት ሌላ ሰው እንዲሰይም የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ሊፈቅድለት ይችላል ተተኪውም ንብረት አስተዳዳሪው ንግዱን ለማካፄድ ያሉት አስፈላጊ ስልጣኖች ሁሉ ይኖሩታል የንግዱ ስራ የቀጠለ እንደሆነ በንግዱ መቀጠል ምክንያት የገንዘብ መብት ጠያቂ የሆኑ ሰዎች ከሕብረቱ ላይ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ይሆናሉፎ የኪሳራው ሂደትም አይፈጸምባቸውም በሕብረቱ ውስጥ ከሚገኙ ሌሎች የገንዘብ መብት ጠያቂዎችም ቅድሚያ ይኖራቸዋል አንቀጽ የመያዣ ውሉችን ስለ ማድረግ ንብረት አስተዳዳሪው የንግዱ ስራ በመቀጠሉ ምክንያት ለተፈጠሩ ወይም ለሚፈጠሩ ግዴታዎች ዋስትና የሚሆን አዲስ መያዣ ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ላይ ሊያቋቁም ይችላል ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ላይ መያዣ ለማቋቋም ንብረት አስተዳዳሪው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴን ፈቃድ በቅድሚያ ማግኘት አለበትሹ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ ያልተስማማ እንደሆነ ንብረት አስተዳዳሪው ፍርድ ቤቱ የመያዣ ውሉን መቋቋም እንዲፈቅድ መጠየቅ ይችላል አንቀጽ ሌሎች ንብረቶችን ስለ መሸጥ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ባለዕዳውን ካዳመጠ በኋላ በዚህ ሕግ አንቀጽ ከተመለከቱት ውጭ ያሉ የንግድ እቃዎችን ወይም ሌሎች የሚንቀሳቀሱ ንብረቶችን ባለዕዳው በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ ተጠርቶ በተገኘበት ወይም ተጠርቶ ካልተገኘ በሌለበት ንብረት አስተዳዳሪው እንዲሸጥ ሊፈቅድለት ይችላል የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የሽያጩን ሁኔታ ይወስናል ከሽያጩ የሚገኘውም ገንዘብ ኪሳራው የሚመለከተው ንብረት አካል ይሆናል። ከዚህ የተረፈው ገንዘብ ኪሳራው የሚመለከተው ንብረት አካል ይሆናል አንቀጽ በመያዣ የተያዘ ንብረትን ስለ ማስለቀቅ ኃ በመያዣ የተሰጠ ንብረት ዋጋ ከዕዳው በልጦ ሲገኝ ንብረት አስተዳዳሪው ዕዳውን በመክፈል ወይም ለዕዳው ተመጣጣኝ የሆነ ሌላ መያዣ በመስጠት መያዣ የተደረገ ንብረት እንዲለቀቅ ማድረግ ይችላል ንብረቱን በመያዣ የያዘው የገንዘብ መብት ጠያቂ መያዣውን ለመልቀቅ ፍቃደኛ ሳይሆን የቀረ እንደሆነ ንብረት አስተዳዳሪው ለፍርድ ቤቱ ሊያመለክት ይችላል ፍርድ ቤቱም ንብረት አስተዳዳሪው መጀመሪያ ዕዳውን ለመክፈል ጥያቂ ባቀረበበት ቀን የነበረውን ዕዳ የገንዘብ መብት ጠያቂው እንዲቀበል እና መያዣው እንዲለቀቅ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል በተለዋጭ የቀረበው የመያዣ ንብረትም በቀድሞው መያዣ የተደገፈውን ዕዳ ሙሉ በሙሉ ለመሸፈን በቂ ሆኖ ካገኘው ገንዘብ ጠያቂው ተለዋጩን መያዣ እንዲቀበል ትእዛዝ ይሰጣል አንቀጽ ስምምነት እና ግልግል ስለ ማድረግ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹን ኮሚቴ በማማከርና የከሰረውን ባለዕዳ በማዳመጥ ወይም በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ ተጠርቶ ካልተገኘ በሌለበት ንብረት አስተዳዳሪው ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ላይ ያለን የመብት ጥያቄ በስምምነት ወይም በግልግል እንዲጨርስ ሊፈቅድለት ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ስምምነት ወይም ግልግል የተደረገበት ጉዳይ ዋጋው ያልተወሰነ ወይም ከንብረት አስተዳዳሪው ስልጣን በላይ ከሆነ ስምምነቱ ወይም ግልግሉ በፍርድ ቤቱ መጽደቅ አለበት ፍርድ ቤቱ ስምምነቱን ወይም ግልግሉን ከማጽደቁ በፊት የከሰረው ባለዕዳ መጽደቅ የለበትም የሚልበት በቂ ምክንያት ካለው ተቃውሞውን እንዲያቀርብ አድል መስጠት ይኖርበታል ተቃውሞው ተገቢ ሆኖ ካገኘው ወይም ስምምነቱ ወይም ግልግሉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን ጥቅም ይጎዳል ብሎ ካመነ ውድቅ ያደርገዋል አንቀጽ የንብረት አስተዳዳሪው ተጠያቂነት እና ይርጋ ንብረት አስተዳዳሪው የዚህን መጽሐፍ ድንጋጌዎች በመተላለፍ በፈጸማቸው ወይም ሳይፈጽም በቀራቸው ተግባራት በገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ወይም በባለዕዳው ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ኃላፊ ይሆናል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የሚቀርብ ክስ የኪሳራ ሂደቱ ከተዘጋበት ቀን ጀምሮ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል ክፍል አምስት ባለዕዳው የተዋዋላቸውንና ሙሉ በሙሉ ያልተፈጸሙ ውሎችን በተመለከተ አንቀጽ ባለዕዳው ስላልፈጸመው ውል በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር የባለዕዳው መክሰር ከታዎጀበት ቀን በፊት ባለዕዳው የተዋዋለው ውል ጸንቶ ይቆያል የመክሰር ውሳኔ ውሉን ወዲያውኑ ያቋርጠዋል የሚል የውል ቃል ተፈጻሚነት አይኖረውም ለኪሳራው ሂደት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ንብረት አስተዳዳሪው የኪሳራ ሄደት ተቆጣጣሪውን እና የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴን በማማከር የከሰረው ባለዕዳ የተዋዋለውን ውል አግባብ ባለው ሕግ መሰረት ለማቋረጥ ወይም ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ ይችላል አንቀጽ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ቅሬታ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ በንብረት አስተዳዳሪው ውሳኔ ያልተስማማ እንደሆነ ቅሬታውን ውሳኔው ከተወሰነበት ቀን አንስቶ በሰባት ቀናት ጊዜ ውስጥ ለፍርድ ቤቱ ማቅረብ ይችላል ፍርድ ቤቱ የንብረት አስተዳዳሪውን ውሳኔ ከኪሳራ ሂደቱ አላማዎች አንጻር በመመርመር ውሳኔ ይሰጣልፁ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል አንቀጽ የውሉ መቀጠል ወይም መቋረጥ ስለሚኖረው ውጤት ውሉ የቀጠለ እንደሆነ የዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል የዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ንብረት አስተዳዳሪው የውል መቋረጥ ውሳኔውን አስከሚያሳውቅበት ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ሌላኛው ተዋዋይ በውሉ መሰረት ላቀረባቸው ሸቀጦች ወይም አገልግሎቶች የሚከፈሉ ክፍያዎች ላይም ተፈጻሚ ይሆናል አንቀጽ ልዩ ሁኔታዎች የዚህ ሕግ አንቀጽ እና ድንጋጌዎች ቢኖሩም የሚከተሉት አግባብ ባላቸው ሕጎች መሰረት ተፈጻሚ ይሆናሉ የአሰሪና ሰራተኛ ውሎች የባንክ እና ኢንሹራንስ ውሉሎች ከመንግስት የአስተዳደር አካላት ጋር የተደረጉ የግዢ ውሎች በፋይናንስ በአክስዮን እና በምርት ገበያዎች ስርዓት መሰረት የተደረጉ ውሎች አንቀጽ የንግድ ቤት ኪራይ ውልን የሚመለከቱ ልዩ ድንጋጌዎች የዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ባለዕዳው የንግድ ስራውን በሚያካሂድበት የማይንቀሳቀስ ንብረት እንዲሁም የዚሁ ንብረት አካል የሆነ ለባለዕዳው እና ለቤተሰቡ መኖሪያነት የሚያገለግል ቤትን የሚመለከት የኪራይ ውል በተከራዩ ባለዕዳ መክሰር ብቻ አይፈርስም አከራዩ ለባለፅዳው ንግድ ስራ በሚያገለግል የሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን ልዩ የመያዣ መብት የሚገድብ ወይም ዋጋ የሚያሳጣ የንብረት አስተዳዳሪው ውሳኔን በመቃወም ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ማቅረብ ይችላል አንቀጽ የኪራይ ውል መቀጠል ወይም መተላለፍ ንብረት አስተዳዳሪው የኪራይ ውሉን ለቀረው የኪራይ ዘመን ለመቀጠል ወይም ለሌላ ሰው ለማከራየት የሚችለው ንብረት አስተዳዳሪው ወይም ከእርሱ የሚከራየው ሰው የቤቱን አገልግሎት አይነት የማይለውጥ የሆነ እንደሆነ ነውር ሆኖም የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው የቤቱን አገልግሉት አይነት እንዲለውጥ ሊፈቅድ ይችላል የኪራይ ውሉ እንዲቀጥል የተደረገ እንደሆነ ለአከራዩ ጊዜው የደረሰ ኪራይ ሁሉ ከተከፈለው እና ውሉ በተደረገበት ጊዜ የተሰጡት ዋስትናዎች የጸኑለት እንደሆነ ወይም አከፋፈሉ ከተቋረጠ በኋላ የተሰጡት ዋስትናዎች በቂ መሆናቸው የተገመተ እንደሆነ አከራዩ የወቅቱን እና የወደፊቱን ኪራይ እንዲከፈለው ለማስገደድ አይችልም ምዕራፍ አምስት የገንዘብ መብት ጥያቄዎችን ስለ ማቅረብ እና መመርመር ክፍል አንድ የአቀራረቡ እና የምርመራው ስርዓት አንቀጽ የገንዘብ መብት ማስረጃዎችን ስለ ማቅረብ የኪሳራ ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን አንስቶ ማንኛውም የገንዘብ መብት ጠያቂ የሚጠይቀውን የገንዘብ መጠንና ማስረጃወችን እራሱ ወይም በወኪሉ አማካይነት ለንብረት አስተዳዳሪው በአካል በተመዘገበ መልዕክት ወይም ለመድረሱ ማረጋጋጫ ሊቀርበት በሚችል ማናቸውም ዘዴ ሊያቀርብ ይችላል ንብረት አስተዳዳሪው በገንዘብ መብት ጠያቂዎች ለቀረቡለት ሰነዶች ማረጋገጫ ደረሰኝ መስጠትና የኪሳራ ሂደቱም ከተዘጋ በኋላ ሰነዶቹን መመለስ አለበት የኪሳራው ሂደት ከተዘጋ ከአንድ አመት በኋላ ለሰነዶቹ መመለስ ተጠያቂ አይሆንም አንቀጽ በአንድነት እና በነጠላ ኀላፊነት ያለባቸው ሽሪኮችን መክሰር ስለ ሚመለከት ጥያቄ ባለዕዳው ያልተወሰነ ኃላፊነት ያለበት የንግድ ማህበር የሆነ እንደሆነ በማህበሩ መክሰር ውስጥ የገንዘብ መብት ጥያቄአቸውን ያቀረቡ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በሚገባቸው ገንዘብ ልክ ያልተወሰነ ኃላፊነት ባለበት በእያንዳንዱ ሸሪክ መክሰር ውስጥ መብታቸው እንዲታወቅላቸው ጥያቄ እንዳቀረቡ ይቆጠራል አንቀጽ ማስረጃ ለማቅረብ ስለ ማይገደዱ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ማስረጃ ማቅረብ አይጠበቅባቸውም ሀ ያልተከፈለ ደሞዝ እና ከአሰሪና ሰራተኛ ውል የሚመነጩ ሌሎች ክፍያዎችን የሚጠይቁ የባለዕዳው ሰራተኞች ለ የግብር እና ታክስ ክፍያዎችን የሚጠይቁ የመንግስት አካላት ሐ ባለዕዳው ተዋውሎአቸው ንብረት አስተዳዳሪው እንዲቀጥሉ ባደረጋቸው ወይም ንብረት አስተዳዳሪው ራሱ በተዋዋላቸው ውሎች ምክንያት የገንዘብ መብት ጠያቂ የሆኑት ሰዎች ንብረት አስተዳዳሪው እነዚህን የገንዘብ መጠየቂያ መብቶች የባለፅዳውን የሂሳብ መዝገቦች የደሞዝ መክፈያ ፔይሮሎችን እና ሌሎች ተገቢነት ያላቸውን ሰነዶች በመመርመር ያረጋግጣል አንቀጽ ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች ስለሚሰጥ ማስታወቂያ ንብረት አስተዳዳሪው ስራውን አንደጀመረ ወዲያውኑ ለገንዘብ መብት ጠያቂዎች በዚህ ሕግ አንቀጽ በተደነገገው መሰረት ማስረጃዎቻቸውን እንዲያቀርቡ በማስታወቂያ ያሳውቃቸዋል ማስታወቂያው የባለዕዳውን እና የንብረት አስተዳዳሪውን ስምና አድራሻ የሚገልጽ ሆኖ ማስታወቂያ ለማውጣት በተፈቀደለት አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ላይ መውጣት አለበት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ማስረጃዎቻቸውን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሠላሣ ቀናት ውስጥ ማቅረብ አለባቸው አንቀጽ የክፍያ ጥያቄዎችን ስለ መመርመርና ማረጋገጥ ንብረት አስተዳዳሪው የቀረቡለትን የገንዘብ መብት ጥያቄዎችና ማስረጃዎችን መርምሮ የሚያረጋግጠው ተቋቁሞ እንደሆነ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ ወይም የኮሚቴው ወኪል እንዲሁም የከሰረው ባለዕዳ በተገኘበት ወይም በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ ተጠርቶ ካልተገኘ በሌለበት ይሆናል የተዘጋጀው የዕዳዎች ዝርዝር በኪሳራ ሄደት ተቆጣጣሪውም የተፈረመ መሆን ይኖርበታል ንብረት አስተዳዳሪው የቀረቡለት የገንዘብ መብት ጥያቄዎችን በሙሉ ወይም በከፊል ሊቀበል ወይም ውድቅ ሊያደርግ ይችላል የገንዘብ መጠናቸው ተለይቶ ያልታወቀ መፈጸማቸው በሁኔታ ወይም በግዴታ ላይ የተመሰረተ ዕዳዎችን ንብረት አስተዳዳሪው በጊዜአዊነት ሊቀበል ይችላል ንብረት አስተዳዳሪው ጥያቄ ያስነሳን የገንዘብ መብት መጠየቂያ ማስረጃን በተመለከተ ተጨማሪ ማስረጃ ወይም ማብራሪያ መቅረብ ያለበት መሆኑን ያመነ እንደሆነ ይህንኑ ከነምክንያቱ ለሚመለከተው የገንዘብ መብት ጠያቂ በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ ማሳወቅ አለበት የገንዘብ መብት ጠያቂውም ማስታወቂያው በደረሰው በስምንት ቀናት ውስጥ የተጠየቀውን ማስረጃ ወይም ማብራሪያ ማቅረብ አለበት አንቀጽ ተቀባይነት የሌላቸው ዕዳዎች ዓለምዓቀፍ ስምምነት እንደተጠበቀ ሆኖ ንብረት አስተዳዳሪው በውጭ አገር መንግስታት በተሰጡ የግብር የታክስ የገንዘብ ቅጣት ውሳኔዎች መሰረት የሚቀርቡ የገንዘብ መብት ጥያቄዎችን መቀበል አይኖርበትም አንቀጽ የዕዳዎችን ጊዜአዊ ዝርዝር ስለ ማስቀመጥ ምርመራው እንዳለቀ ንብረት አስተዳዳሪው ወዲያውኑ የአጠቃላይ ፅዳዎችን የተቀበላቸውና ውድቅ ያደረጋቸው ዕዳዎችን የሚያመለክት ዝርዝር የያዘ ሰነድ አዘጋጅቶ አግባብ ባለው የፍርድ ቤቱ አካል ያስቀምጣል በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ልዩ መብት አለን የሚሉትን የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ዝርዝር ለኪሳራ ሄደት ተቆጣጣሪው ማቅረብ ይኖርበታል ንብረት አስተዳዳሪው አንድን የገንዘብ መብት ጥያቄ በሙሉ ወይም በከፊል ውድቅ ያደረገ እንደሆነ በዝርዝሩ ውስጥ ምክንያቱን በግልጽ ማመልከት አለበት አንቀጽ የዝርዝሩን መቀመጥ ስለማስታወቅ ንብረት አስተዳዳሪው በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ዝርዝሩ አግባብ ባለው የፍርድ ቤቱ አካል መቀመጡን ለገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ ወዲያውኑ ያስታውቃል ንብረት አስተዳዳሪው ያልተቀበላቸውን ዕዳዎች ለሚመለከታቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ማናቸውም ዘዴ ወዲያውኑ ያስታውቃል አንቀጽ ስለአቤቱታዎች ዕዳው በሂሳብ ሚዛን ውስጥ የታየ ወይም ሰነዱ የተመረመረ የገንዘብ መብት ጠያቂ በአካል ወይም በወኪሉ አማካይነት ማስታወቂያው በጋጤጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስምንት ቀናት ውስጥ በቀረበው የዕዳዎች ዝርዝር ላይ ያለውን አቤቱታ አግባብ ላለው የፍርድ ቤት አካል ማቅረብ ይችላል በንብረት አስተዳዳሪው ውሳኔ ጥቅሙ ወይም መብቱ የሚነካ ባለዕዳ ሸሪክ ባለአክስዮኖን የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ኮሚቴ ዐቃቤ ህግ ወይም ሌላ ማንኛውም ሰው አቤቱታ የማቅረብ ተመሳሳይ መብት አለው አንቀጽ የዕዳዎች ዝርዝር መጻፍና መዘጋጀት ስለሚያበቃበት ጊዜ በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑሰ አንቀጽ የተደነገገው የጊዜ ገደብ እንዳበቃ ለፍርድ ቤት የቀረበ ማንኛውም አቤቱታ እንደተጠበቀ ሆኖ የዕዳዎች መጻፍ ይቆማል ንብረት አስተዳዳሪው የዕዳዎቹን የመጨረሻ ዝርዝር አዘጋጅቶ ለኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ያሳውቃል ዝርዝሩም አቤቱታ ያልቀረበባቸውን እአና ንብረት አስተዳዳሪው የተቀበላቸውን ፅዳዎች እንዲሁም የገንዘብ መብት ጠያቂውን ማንነት አና የታመነለትን የገንዘብ መጠን ማመልከት አለበት አንቀጽ ክርክር በቀረበባቸው ዕዳዎች ላይ ስለሚሰጥ ውሳኔ አግባብ ያለው የፍርድ ቤት አካል ክርክር በተነሳበት ዕዳ ባለጉዳይ የሆኑትን ጉዳዩ በፍርድ ቤት ከሚሰማበት ከአምስት ቀን አስቀድሞ በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ በማሳወቅ ከኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው መግለጫ ጋር ጉዳዩን ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል ፍርድ ቤቱም ባለ ጉዳዮቹን ከሰማ እና ተቃውሞውን ከመረመረ በላ የገንዘቡን ልክ በመወሰን የገንዘብ መብት ጠያቂው በኪሳራው ሂደት ለጊዜው እንዲገባ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል አግባብ ያለው የፍርድ ቤት አካል በተመዘገበ መልእክት ወይም ለመድረሱ ማረጋገጫ ሊቀርብበት በሚችል ሌላ ማናቸውም ዘዴ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ለሚመለከታቸው ባለጉዳዮች ትዕዛዙ በተሰጠ በሦሥት ቀናት ውስጥ ማሳወቅ አለበት በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ቅር የተሰኘ ሰው ትዕዛዙ በተሰጠ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ይግባኝ የመጠየቅ መብት አለው አንቀጽ የኪሳራ ሂደትን ስለ ማገድ እና መቃወሚያን ስለ ማለፍ ፅዳን በመቃወም ክርክር ከቀረበና ክርክሩም ሂደቱን የሚያዘገየው ከሆነ ፍርድ ቤቱ ስልጣን ያለው ሌላ ፍርድ ቤት በመቃወሚያው ላይ ውሳኔ እንከሚሰጥ ድረስ የኪሳራ ሂደቱ ታግዶ እንዲቆይ ወይም መቃወሚያው እንዲታለፍ ሊወስን ይችላል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያው እንዲታለፍ የወሰነ እንደሆነ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሰረት ንብረት አስተዳዳሪው ይህን ዕዳ በጊዜአዊነት እንዲቀበለው ሊፈቅድ ይችላል ፅዳው የወንጀል ክስ የሚያስከትል የሆነ እንደሆነ የመክሰሩን ጉዳይ የሚመለከተው ፍርድ ቤት የኪሳራው ሂደት እንዲቋረጥ ለማዘዝ ይችላል። አንቀጽ መክፈሉ ከመቋረጡ በፊት ከዕዳው ላይ ከፊሉን ስለ ተቀበለ የገንዘብ መብት ጠያቂ በከሰረው ሰውና በሌሎች የጋራ ተገዳጆች መካከል የአንድነት እና የነጠላ ዋስትና የተገባላቸው ሰነዶች የያዘ የገንዘብ መብት ጠያቂ ከሚጠይቀው ገንዘብ ከፊሉን መክፈሉ ከመቋረጡ በፊት የተቀበለ እንደሆነ በህብረቱ ውስጥ ገብቶ የሚታሰብለት ገንዘብ ከሚገባው ገንዘብ ላይ በከፊል የተቀበለው ተቀንሶ ነው ለሚቀረውም ገንዘብ በጋራ ተገዳጆቹ ወይም በዋሶቹ ላይ ያለውን መብቶች እንደያዘ ይቆያል በከፊል የከፈለ የጋራ ተገዳጅ ወይም ዋስ ስለ ባለዕዳው በከፈለው ገንዘብ መጠን ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ውስጥ ይገባል አንቀጽ በኪሳራ ሂደት በአንድነት እና በነጠላ ኃላፊነት ስላለባቸው ሸሪኮች ፍርድ ቤቱ በአንድነትና በነጠላ ኃላፊነት ያለባቸው ሸሪኮች ያሉበት ማሕበር እና የእነዚህ ሸሪኮች መክሰራቸውን በአንድ ውሳኔ ይወስናል የማሕበሩ እና የሸሪኮቹ ሐብት ተነጣጥለው ይታያሉ የኪሳራ ሂደቱም በተናጠል ይካሄዳል መክፈል ከሚገባው በላይ ስለ ከፈለው ገንዘብ የእያንዳንዱ ሸሪክ መክሰር በሌላው ማህበርተኛ መክሰር ላይ ክስ ለማቅረብ የተሰጠው መብት ሳይነካ ከማህበሩ ላይ የገንዘብ መብት ጠያቂ የሆነ ሰው ገንዘቡ በሙሉ አስኪከፈለው ድረስ በሚደረጉት ክፍያዎች ሁሉ ተካፋይ ለመሆን መብት አለው ከማህበርተኞቹ ላይ የግል ገንዘብ ጠያቂ የሆኑት ሰዎች በመብታቸው ሊሰሩበት የሚችሉት ባለዕዳ በሆናቸው ማህበርተኛ መክሰር ውስጥ ብቻ ነው እያንዳንዱ የገንዘብ መብት ጠያቂ ከእርሱ ጋር ተካፋይ የሆኑትን የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መብት ለመቃወም ይችላል ክፍል ሦስት የንግድ መደብር አካል ባልሆነ ተንቀሳቃሽ ንብረት ላይ የመያዣ ዋስትና ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መብት አንቀጽ የንብረት መያዣ ዋስትና ስላላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች የገንዘብ መብት ጥያቄአቸው በሚንቀሳቀስ ንብረት ዋስትና የተረጋገጠላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ለመረጃ አላማ ብቻ በንብረት ዝርዝር ውስጥ እንዲገቡ ይደረጋል ንብረት አስተዳዳሪው በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ፍቃድ ኪሳራው ለሚመለከተው ንብረት ጥቅም ሲል ዕዳውን በመክፈል በመያዣ የተሰጠውን ንብረት ለመቀበል ይችላል አንቀጽ ስለተሸሽጠ መያዣ በመያዣ የተያዘውን የሚንቀሳቀስ ንብረት ንብረት አስተዳዳሪው ዕዳውን በመክፈል ካልወሰደውና የገንዘብ መብት ጠያቂው ከፅዳው መጠን በሚበልጥ ዋጋ የሸጠው አንደሆነ ትርፉን ንብረት አስተዳዳሪው ይቀበላል የሸጠበት ዋጋ ከዕዳው መጠን ያነሰ ከሆነ የገንዘብ መብት ጠያቂው ለልዩነቱ ገንዘብ እንደ ተራ ገንዘብ ጠያቂ ሆኖ በኀብረቱ ውስጥ ይገባል የገንዘብ መብት ጠያቂው በመያዣ የያዘውን ንብረት ኪሳራው ወደሚመለከተው ንብረት በመመለስ ተራ ገንዘብ ጠያቂ ለመሆን ይችላል ንብረት አስተዳዳሪው ይህን ንብረት የመቀበል ግዴታ አለበት አንቀጽ አከራይ ስላለው ምርጫ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሰረት የኪራይ ውሉ የተቋረጠ እንደሆነ አከራዩ ኪሳራው ከመታዎጁ በፊት ላለው ሁለት ዓመት እና በተያዘው የኪራይ ዓመት ላልተከፈለው ኪራይ ከኪራይ ውሉ አፈጻጸም የሚነሱ የመብት ጥያቄዎችን እንዲሁም የድንገተኛ ጉዳት ካሳን በተመለከተ ልዩ መብት ይኖረዋል በተከራየው ቤት ውስጥ የነበሩት የንግድ ወይም የቤት አቃዎች የተወሰዱና የተሸጡ እንደሆነ አከራዩ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ስር ከተደነገገው በተጨማሪ ከተያዘው የኪራይ ዘመን መጨረሻ ጀምሮ ላለው አንድ አመት ላልተከፈለው ኪራይ ልዩ መብት ይኖረዋል አንቀጽ የተንቀሳቃሽ ንብረት ሻጭ በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ የሚንቀሳቀስ ንብረትን ለባለዕዳው የሸጠ ሰው በፍትሐብሔር ሕግ በተመለከተው መሰረት ለማይንቀሳቀስ ንብረት በመያዣ የተሰጠው ዋስትና ኪሳራውን በሚመለከተው ንብረት ላይ መቃወሚያ ሆኖ ሊቀርብ አይችልም የዚህን አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ የሚቃረን ማናቸውም ስምምነት ዋጋ አይኖረውም አንቀጽ በሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ የቀደምትነት መብት ላላቸው ገንዘብ መብት ጠያቂዎች ስለ መክፈል በዚህ ሕግ አንቀጽ የተደነገገው የፅዳዎች ዝርዝር የያዘ ሰነድ ውስጥ ለተመለከቱትና በሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ የቀደምትነት መብት ላላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው መጀመሪያ ከተሰበሰበው ገንዘብ እንዲከፈላቸው ይፈቅዳል በቀደምትነቱ ላይ ክርክር የተነሳ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ይወስናል ክፍል አራት በማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ የመያዣና ልዩ መብት ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች አንቀጽ ከሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዋጋ በፊት ስለ ተከፋፈለ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሸያጭ ዋጋ ከማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ ሙሉ ገንዘባቸውን ያልተቀበሉ የመያዣ ወይም ልዩ መብት ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በዚህ ሕግ አንቀጽ እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች መሰረት መብታቸው ተቀባይነት ያገኘ እንደሆነና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ ከሚንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ በፊት ወይም በተመሳሳይ ጊዜ የተከፋፈለ እንደሆነ ባልተከፈላቸው ገንዘብ መጠን ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረት ላይ ከሚከፈለው ገንዘብ ከተራ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ጋር ተካፋይ ይሆናሉ አንቀጽ ከማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዋጋ በፊት ስለ ተከፈለ የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ ከመከፋፈሉ በፊት ከሚንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ አንድ ወይም ከአንድ በላይ ክፍያዎች ተደርገው እንደሆነ በዚህ ሕግ አንቀጽ የተደነገጉት ልዩ ሁኔታዎች ካላጋጠሙ በስተቀር በአግባቡ ተቀባይነት ያገኙ ልዩ መብት ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በጠቅላላ መብታቸው መጠን በክፍያው ውስጥ ገብተው ይካፈላሉ አንቀጽ ዋስትና ከሌለው ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረት የተቀበሉትን ገንዘብ ስለ መቀነስ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ከተሸጡና የመያዣና ልዩ መብት ባላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መካከል ያለው ተራ ከተወሰነ በላ ከእነዚሁ መካከል ከማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ ለጠቅላላው የገንዘብ መብታቸው ተካፋይ ለመሆን የሚችሉት የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በመያዣቸው መሰረት ገንዘብ ለማግኘት የሚችሉት ዋስትና ከሌለው ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረት ውስጥ ያገኙት ገንዘብ ተቀናሽ ሆኖ ነው ተቀናሽ የሆነውም ገንዘብ መያዣ ባለው ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ውስጥ አይቀርም ዋስትና ወደሌለው ኪሳራው ወደሚመለከተው ንብረት ተመላሽ ሆኖ ይቆያል አንቀጽ የመያዣ መብት ላላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በከፊል ስለ መክፈል ከማይንቀሳቀስ ንብረት የሽያጭ ዋጋ በከፊል ለመከፈል ተራ የገቡ የመያዣ መብት ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን በተመለከተ የሚከተሉት ተፈጻሚ ይሆናሉ ከማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ዋጋ በከፊል ክፍያ ከተቀበሉ በኋላ በሚቀራቸው ገንዘብ መጠን ተራ በገቡበት ዋስትና ከሌለው ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረት ላይ ተካፋይ ይሆናሉ ቀደም ሲል በተደረገው ክፍፍል ውስጥ ከዚሁ ድርሻ በላይ የተቀበሉት ገንዘብ ተራ ከገቡበት መያዣ ካለው ክፍያቸው ላይ ተቀንሶ ዋስትና በሌለው ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ውስጥ ተይዞ ይቆያል ክፍል አምስት በንግዱ መደብር ላይ የመያዣ መብት ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች መብት አንቀጽ ከሌሎች የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዋጋ በፊት ስለ ተከፋፈለ የንግድ መደብር የሽያጭ ዋጋ የንግዱ መደብር ሽያጭ ዋጋ ከሌሎች ተንቀሳቃሽ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ በፊት ወይም በአንድነት ወይም በተመሳሳይ ጊዜ የተከፋፈለ እንደሆነ ከመደብሩ የሽያጭ ዋጋ ሙሉ ገንዘባቸውን ያልተቀበሉ የመያዣ ወይም ልዩ መብት ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በዚህ ሕግ አንቀጽ አና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች መሰረት መብታቸው ተቀባይነት አግኝቶ እንደሆነ ባልተከፈላቸው ገንዘብ መጠን ኪሳራው ለሚመለከተው ንብረት ከሚከፈለው ገንዘብ ውስጥ ከተራ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ጋር ተካፋይ ይሆናሉ አንቀጽ ከንግድ መደብሩ ሽያጭ ዋጋ በፊት ስለ ተከፋፈሉ የሌሎች ተንቀሳቃሽ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ በዚህ ሕግ አንቀጽ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ የንግዱ መደብር የሽያጭ ዋጋ ከመከፋፈሉ በፊት የሌሎች ተንቀሳቃሽ ንብረቶች የሽያጭ ዋጋ ተከፋፍሎ እንደሆነ መያዣ ያላቸውና መብታቸውም በአግባቡ ተቀባይነት ያገኘ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ከሚከፋፈለው ገንዘብ ላይ በሚጠይቁት ገንዘብ መጠን ተከፋይ ይሆናሉ አንቀጽ በመያዣ ካልተያዘው ንብረት የሽያጭ ዋጋ የተከፈለውን ስለ መቀነስ የንግድ መደብሩ ከተሸጠና የሽያጩም ገንዘብ የሚከፋፈልበት ሁኔታ ከተወሰነ በጊላ በመደብሩ ላይ ለገንዘባቸው በሙሉ መያዣ ያላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ገንዘባቸውን ከመደብሩ ሽያጭ ዋጋ ላይ የሚያገኙት በመያዣ ካልተያዘው ንብረት የሽያጭ ዋጋ ያገኙት ገንዘብ ተቀናሽ ከተደረገ በኋላ ነው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የተቀነሰው ገንዘብ ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረት ላይ የገንዘብ መብት ጠያቂ ለሆኑት ጥቅም መያዣ ወዳልሆነው ንብረት ተመላሽ ይሆናል አንቀጽ በንግድ መደብሩ ላይ የመያዣ መብት ላላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በከፊል ስለ መክፈል ከንግድ መደብሩ የሽያጭ ዋጋ ላይ የመያዣ መብት ኖሮአቸው በከፊል ብቻ የተከፈሉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን በተመለከተ የሚከተሉት ተፈጻሚ ይሆናሉ ዋስትና በሌለው ንብረት ውስጥ ያላቸው መብት የሚወሰነው ከንግዱ መደብር ዋጋ ላይ ከተከፈላቸው ዋጋ በላ በሚቀራቸው ገንዘብ መጠን ነው ቀደም ሲል በተደረገው ክፍፍል ውስጥ ከድርሻቸው በላይ የተከፈላቸው ገንዘብ ለመቀበል ተራ በገቡበት መያዣ ካለው ክፍያቸው ላይ ተቀንሶ ዋስትና ለሌለው ኪሳራው የሚመለከተው ንብረት ተመላሽ ሆኖ ይቆያል ክፍል ስድስት በመፋለም የመጠየቅ መብት አንቀጽ የንግድ ወረቀቶችን በመፋለም ስለ መጠየቅ ኪሳራው በታዎጀበት ቀን በባለዕዳው ይዞታ ውስጥ በአይነት የሚገኙትን የንግድ ወረቀቶች ወይም ሌሎች ያልተከፈለባቸው ሰነዶች መልሶ ለመውሰድ የሚቻለው የሰነዶቹ ባለቤት እነዚህን ወረቀቶች ወይም ሰነዶች ለከሰረው ባለዕዳ የሰጠው ዋጋቸውን ተቀብሎ እንዲያስቀምጥለት ብቻ የሆነ እንደሆነ ብቻ ነው እንዲሁም የሰነዱ ባለቤት የተወሰኑ ክፍያዎችን ባለዕዳው እንዲፈጽምለት የሰጠውን ገንዘብ መጠየቅ ይችላል አንቀጽ በአደራ የተቀመጠውን ወይም እንዲሸጥ የተሰጠውን ዕቃ መልሶ ስለመጠየቅ ለከሰረው ባለዕዳ በአደራ የተሰጡ የንግድ ዕቃዎች ወይም በባለቤቱ ስም ለመሸጥ የተቀበላቸውን ዕቃዎች በሙሉ ወይም በከፊል በአይነት የሚገኙ ከሆነ ባለቤቱ እንዲመለሱለት ለመጠየቅ ይችላል የእነዚሁ እቃዎች ዋጋ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲመለስ ለመጠየቅ የሚቻለው በጥሬ ገንዘብ ወይም ዋጋ ባለው ነገር ያልተከፈለ ወይም በባለዕዳውና በገዢው መካከል በተመላላሽ ሂሳብ ያልተቻቻለ የሆነ እንደሆነ ነው የንብረቱ ባለቤት በውላቸው መሰረት ለከሰረው ባለዕዳ መክፈል የነበረበትን ያልተከፈለ የአገልግሎት ክፍያ ለመጠየቅና ይህንኑ ለማስፈጸም ለከሰረው ባለዕዳ በህግ የተሰጠውን ልዩ የመያዣ መብት ንብረት አስተዳዳሪው ይጠቀምበታል አንቀጽ ኪሳራ ከመታዎጁ በፊት ሽያጫቸው የተሰረዘ ዕቃዎችን በመፋለም ስለ መጠየቅ በፍርድ ቤት ውሳኔ ወይም በውሉ ቃል መሰረት ኪሳራ ከመታዎጁ በፊት ሽያጫቸው የተሰረዘ ዕቃዎች በዐይነት ካሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመፋለም ለመጠየቅ ይቻላል የሽያጩ መሰረዝ በፍርድ ቤት የታዘዘው ወይም የጸደቀው ኪሳራ ከታዎጀ በላ ቢሆንም ገንዘቡ ያልተከፈለው ሻጭ ያቀረበው የመፋለም ጥያቄ ወይም ክስ ኪሳራው ከመታዎጁ በፊት ከሆነ ጥያቄውን ወይም ክሱን በከፊል ንብረት ላይም ቢሆን ለማቅረብ ይችላል አንቀጽ ባለሀብትነትን በማስጠበቅ የተሸጠ ተንቀሳቃሽ ንብረትን ስለ ማስመለስ ዋጋው እስኪከፈል ድረስ ባለሀብትነቱ ሳይተላለፍ ለባለዕዳው የተሸጠን የሚንቀሳቀስ ንብረት በመፋለም ለመውሰድ የሚቻለው የሽያጩ ውል ኪሳራው ከመታዎጁ በፊት በፍትሐብሔር ሕግ ባለሐብትነትን ለራስ ለማስጠበቅ ስለሚደረግ ሽያጭ ምዝገባን በሚደነግገው ሕግ መሰረት ተመዝግቦ አንደሆነ ብቻ ነው አንቀጽ በጉዞ ላይ ያሉ ለከሰረው ባለዕዳ የተላኩ ዕቃዎችን በመፋለም ስለ መጠየቅ ለከሰረው ባለዕዳ የተላኩ በጉዞ ላይ ያሉ ዕቃዎች በራሱ መጋዘን ውስጥ ወይም ስለርሱ በሚሸጠው የኮሚሺን ወኪል መጋዘን ውስጥ ያልገባ ከሆነ ላኪው በመፋለም ለመጠየቅ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው ቢኖርም ላኪው በፈረመው ሰነድ መሰረት ፅቃዎቹ ከመድረሳቸው በፊት ያለማጭበርበር በቅን ልቡና ለተዋዋለ ሁለተኛ ገዢ የተሸጡ እንደሆነ የመፋለሙ ጥያቄ ተቀባይነት አይኖረውም አንቀጽ ስለ መያዝ መብት ለከሰረው ባለዕዳ ያልተሰጡትን ወይም ለአርሱ ወይም ስለአርሱ ሆኖ ለሚሠራ ሦስተኛ ወገን ያልላካቸውን ዕቃዎች ሻጩ ለመያዝ ይችላል አንቀጽ ንብረት አስተዳዳሪው ዕቃዎችን እንዲያስረክቡት ለማስገደድ ስለ መቻሉ በዚህ ሕግ አንቀጽ እና የተመለከቱት ሁኔታዎች ባጋጠሙ ጊዜ በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ፍቃድ ንብረት አስተዳዳሪው ለሻጩ የተዋዋለበትን ዋጋ በመክፈል ሻጩ ዕቃዎቹን እንዲያስረክበው ለማስገደድ ይችላል ንብረት አስተዳዳሪው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ዕቃዎቹን እንዲያስረክበው ያልጠየቀው እንደሆነ ሻጩ ከዕቃዎቹ ዋጋ የተቀበለውንና ከከሰረው ባለዕዳ ለመጫኛ አና ለመጓጓዣ ለኮሚሲሽን ለኢንሹራንስ ወይም ለሌሎች ወጪዎች አስቀድሞ የወሰዳቸውንና እነዚህን ለመሳሰሉ ምክንያቶች የሚከፈሉትን ወጪዎች ኪሳራው ለሚመለከተው ንብረት ይመልሳል እነዚህንም ወጪዎች ራሱ ይከፍላል ሆኖም ሻጩ በውሉ አለመፈጸም ምክንያት ለሚደርስበት ጉዳት የጉዳት ካሳ ሊጠይቅ ይችላል አንቀጽ የመፋለም ጥያቄዎችን ስለ መቀበል የመፋለም ጥያቄዎችን በኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው ፍቃድ ንብረት አስተዳዳሪው ለመቀበልና ለማስተናገድ ይችላል ርዕስ አራት ኪሳራው የሚመለከተውን ንብረት በግዴታ ስለ ማጣራት እና ዕዳዎችን ስለ መክፈል ምዕራፍ አንድ ኪሳራው የሚመለከተውን ንብረት በግዴታ ስለ ማጣራት አንቀጽ የኪሳራው ንብረት በግዴታ ተጣርቶ እንዲሸጥ ስለመወሰን ኪሳራው ከታወጀ በኋላ ዕዳን እንደገና የማደራጀት ሐሳብ ያልቀረበ ወይም የቀረበው ሐሳብ ሳይጸድቅ የቀረ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ኪሳራው የሚመለከተው ንብረት በግዴታ ተጣርቶ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች እንደክፍያ ቅደም ተከተላቸው ክፍያ እንዲያገኙ ይወስናል አንቀጽ ለባለዕዳው ስለሚደረግ ድጋፍ ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረት ላይ ለከሰረው ባለዕዳ ወይም ለቤተሰቡ ድጋፍ ለመስጠት ይቻል እንደሆነ ለማወቅ ንብረት አስተዳዳሪው የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹን ኮሚቴ ያማክራል ኮሚቴው ሀሳቡን የተቀበለው እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ንብረት አስተዳዳሪው በሚያቀርበው መግለጫ መሰረት የድጋፉን መጠን ይወስናል አንቀጽ ስለ ንብረት ሽያጭ ንብረት አስተዳዳሪው በፍትሐብሔር ሥነሥርአት ሕግ ድንጋጌዎች መሰረት የባለዕዳውን የማይንቀሳቀሱ እና የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ይሸጣል። ሀ የባለዕዳው ንግድ እንዲቀጥል ተወስኖ እንደሆነ ንግዱን ለመቀጠልና ለማካሄድ የወጡ ወጪዎች ለ ንብረት አስተዳዳሪው በህግ ወይም በፍርድ ቤት የተሰጡትን ስልጣኖችና ተግባሮች ሲያከናውን በተፈጠሩ ግዴታዎች የወጡ ወጭዎች እና ሐ ባለዕዳው የተዋዋላቸው ውሎች እንዲቀጥሉ ተደርገው እንደሆነ ከእነዚህ ውሎች የሚመነጩ ግዴታዎችን ለመፈጸም የተከፈሉ ገንዘቦችና ወጪዎች አንቀጽ ከደረጃቸው ዝቅ የሚደረጉ የገንዘብ መብት ጥያቄዎች መብቶች ንብረት አስተዳዳሪው ሊያስፈርሳቸው ያልቻለውንና ከባለዕዳው ጋር በስጋ ወይም በጋብቻ አስከ አራተኛው ደረጃ ያሉትን ጨምሮ ግንኙነት ካላቸው የገንዘብ መብት ጠያቂዎች የሚመነጩ ዕዳዎችን ፍርድ ቤቱ በመያዣ ካልተጠበቁ የገንዘብ መጠየቂያ መብቶች በላ እንዲከፈሉ ሊወስን ይችላል ይህ ድንጋጌ በተለይ ያልተገባ ቅድሚያ ለማግኘት ወይም የሌሎች የገንዘብ መብት ጠያቂዎችን ጥቅም ለመጉዳት የተደረጉ ተግባሮች ተፈጽመው ሲገኙ ተፈጻሚ ይሆናል አንቀጽ የአከፋፈሉ መርህ የሚከፋፈለው አጠቃላይ ገንዘብ በተመሳሳይ የክፍያ ደረጃ ያሉ ሁሉንም ዕዳዎች ለመክፈል የማይበቃ እንደሆነ የገንዘብ መብት ጠያቂዎቹ በተረጋገጠላቸው የመብት ድርሻቸው መጠን ተመጣጣኝ ክፍያ ይቀበላሉ የሚከፋፈለው አጠቃላይ ገንዘብ ሁሉንም ዕዳዎች ለመክፈል የማይበቃ አንደሆነ ከፍ ባለው የክፍያ ደረጃ ላይ ያሉ ሁሉም የገንዘብ መብት ጠያቂዎች የተረጋገጠላቸውን ገንዘብ በሙሉ ሳይቀበሉ ዝቅ ብሎ ባለው የክፍያ ደረጃ ላይ ላሉ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ክፍያ አይፈጸምም አንቀጽ ክርክር ያለባቸውን የገንዘብ መብት ጥያቄዎች ድርሻ ጠብቆ ስለማቆየት በተቀባይነቱ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ያልተሰጠበትን ከገንዘብ መብት ጥያቄዎች ተያያዥነት ያለውን ድርሻ የንብረት አስተዳዳሪው ጠብቆ ያቆያል አንቀጽ ስለ አከፋፈሉ ሥርዓት ንብረት አስተዳዳሪው በዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ መሰረት ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ስም ስለኪሳራው ከከፈተው ሒሳብ ላይ የገንዘብ መብት ጥያቄው ተቀባይነት ላገኘው ለእያንዳንዱ ገንዘብ ጠያቂ የሚደርሰውን ክፍያ ይከፍለዋል የተከፈለው የገንዘብ መጠንም የገንዘብ መብት ጠያቂው ባቀረበው ሰነድ እና ንብረት አስተዳዳሪው በሚይዘው አጠቃላይ የዕዳዎች መዝገብ ላይ ይገለጻል አንቀጽ ለባለዕዳው ወይም ለባለድርሻዎች ስለሚመለስ ገንዘብ ከባለዕዳው የሚፈለጉት ዕዳዎች እና ወጪዎች በሙሉ በዚህ ህግ መሰረት ከተከፈሉ በኋላ የሚተርፍ ገንዘብ ቢኖር ለባለዕዳው ወይም ባለዕዳው ማሕበር ሲሆን ለማህበርተኞቹ በድርሻቸው መጠን ተመላሽ ይደረጋል ርዕስ አምስት ስለ ኪሳራ ሂደት መዘጋት አንቀጽ የኪሳራ ሂደት ስለ ሚዘጋባቸው ምክንያቶች የኪሳራውን ሂደት በስምምነት ስለመፈጸም በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ የተደነገጉት ድንጋጌዎች እንደ ተጠበቁ ሆነው የኪሳራው ሂደት በሚከተሉት ምክንያቶች ይዘጋል ከግዴታ ማጣራት የተገኘው ገንዘብ በሙሉ ሲከፋፋል በቂ ንብረት የሌለ እንደሆነ ወይም ኪሳራው ከሚመለከተው ንብረትየሚፈሰግ ቀሪ ዕዳ የሌለ እንደሆነ አንቀጽ በቂ ንብረት ባለመኖሩ ስለሚዘጋ የኪሳራ ሂደት በቂ ንብረት ባለመኖሩ ምክንያት የኪሳራውን ሂደት መቀጠል የማይቻል ከሆነ ፍርድ ቤቱ የኪሳራ ሂደት ተቆጣጣሪው በሚያቀርበው መግለጫ መሰረት ወይም በራሱ አነሳሽነት ሂደቱ እንዲዘጋ ለመወሰን ይችላል ፍርድ ቤቱ የኪሳራው ሂደት እንዲዘጋ የወሰነ እንደሆነ እያንዳንዱ የገንዘብ መብት ጠያቂ በግሉ ክስ ለማቅረብ ያለው መብት ወዲያው ይመለስለታል የከሰረው ባለ ዕዳም ንብረቶቹን ለማስተዳደር በእነርሱም ላይ ለማዘዝ የነበረውን መብት እንደለቀቀ ይቆያል እንዲሁም አዲስ የገባቸው ዕዳዎች ኪሳራው በሚመለከተው ንብረት ላይ መቃወሚያ ሊሆኑ አይችሉም ኪሳራው የሚመለከተው ንብረትም ከአዲሶቹ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች ጋር ተካፋይ አይሆንም አንቀጽ በቂ ንብረት ባለመኖሩ የተዘጋን የኪሳራ ሂደት መልሶ ስለ ማንቀሳቀስ ባለዕዳው ወይም ማንኛውም ጥቅም ያለው ሰው የኪሳራ ሂደቱን ለማስቀጠል የሚወጣውን ወጭ ለመሸፈን የሚበቃ ንብረት መኖሩን ካሳየ ወይም በንብረት አስተዳዳሪው እጅ በቂ ገንዘብ ካስቀመጠ በማናቸውም ጊዜ የተዘጋው የኪሳራ ሂደት ተመልሶ እንዲንቀሳቀስ ፍርድ ቤቱን ለመጠየቅ ይችላል በዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ መሰረት የኪሳራውን ሄደት ለመዝጋት ወጪ የሆኑ ገንዘቦችን አስቀድሞ መክፈል አለበት አንቀጽ ንብረት አስተዳዳሪው ከገንዘብ መብት ጠያቂዎች የተቀበላቸውን ሰነዶች በተመለከተ ስላለበት ኃላፊነት ንብረት አስተዳዳሪው ከገንዘብ መብት ጠያቂዎች የተቀበላቸውንና ለአቅራቢዎቹ ያልመለሳቸውን ሰነዶች በተመለከተ ኪሳራው ከታወጀበት ቀን ጀምሮ አምስት አመት ካለፈው በኋላ ተጠያቂ አይሆንም አንቀጽ ከባለዕዳው የሚፈለግ ቀሪ ዕዳ ባለመኖሩ ስለሚዘጋ የኪሳራ ሄደት ባለዕዳው ማስረጃቸውን ላቀረቡ የገንዘብ መብት ጠያቂዎች በሙሉ የጠየቁትን ገንዘብ አንዲሁም እስከዚያን ጊዜ ድረስ የመክሰሩን ሂደት ለማካሄድ የወጡትን ወጪዎችና የንብረት አስተዳዳሪውን የአገልግሎት ዋጋ መክፈሉን ወይም ለመክፈል አስፈላጊ የሆነውን ገንዘብ በንብረት አስተዳዳሪው አጅ ማስቀመጡን በማስረዳት የመክሰሩ ሂደት አንዲዘጋ ለፍርድ ቤቱ ሊያመለክት ይችላል።