Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የነፃነት ዋጋ ስንት ነው.pdf


  • word cloud

የነፃነት ዋጋ ስንት ነው.pdf
  • Extraction Summary

የነፃነት ዋጋ ስንት ነው። የሚል ጥያቄ አስከተለ ለምርጫ ቅስቀሳ ማድረጊያ ነው። እንደማለት ነው ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ፋብሪካዎች ይቋቋማሉ ስለዚህ ሰዎች በቅድሚያ እንዴት ወደ ከተማ ያመጣው ወንድሙን እኔን የከተሜ ልጅ አንድሆን በማድረጉ ሁሌ አመሰግነዋለሁ አሁንም አጎቴ ቢፍቱ ነብስህን በገነት ያኑራት አለዋለሁ እኛ ቤት እንግዳ ሲመጣ ጠላ ወይ ጠጅ ይገዛል ባሩዳ ደንበል ከመጣ ግን ቢራ ይገዛ ነበር። ይለኝ ነበር ብርፃኩኑ ነጋን ማለቱ ነው ታዋቂ ሰዎችን አውቃለሁ ማለት የሰው ልጅ ባህሪ ነው በሚል ሁሌ እያሾፍን እናልፈዋለን አንድ ቀን አብረን ቃሊቲ ሄደን ያየሁት ግን ብርሃኑ እና አባቴ በኳስ ሜዳ ከብዙ ዓመት በፊት የተገናኙ ሳይሆን ልክ እንደ ቅርብ ጊዜ በጤና ቡድን ውስጥ ተሳታፊ ስለነበር ማቆሙን ያወቅሁት ይህንን ፅሁፍ ለማዘጋጀት ከጋዜጠኛው አቤል ጋር ሆነን ሳናግረው ነበር። ሲሉ በቁጣ ገነፈሉ የከፍተኛው ሊቀ መንበር አቶ ተክሉ ካሳ ግን ጉዳዩን አፅንኦት ሰጥቶ ከተመለከተ በኋላ መፍትሄ ፈንጣቂ ምልከታቸውን ረ አንካችሁ አሉ አንድ መሳሪያ ተሰጥቶት ግዳጁን ሲወጣ የነበረ ሰው ደህና አይደለሁም ጤናዬ ታውኳል ብሎ ያስገባውን ማመልከቻ በአጃችን ይዘን ጥያቄውን አንቀበልም የምንለው መሳሪያውን ወደማን አእንዲያዞረው አስበን ነው። ተብሎ ቤተሰብና ጎረቤት ተነቃንቆ ሲወጣ ክረምት አሳልፎ በበጋ ሚሰትና ልጁን ሊወስድ የመጣው አባቴ ነበር። ብዬ ዓይኔን ወደ ሌሎች የፈተና ወረቀት አላማትርም በአኛ ዕድሜ ወሳኙ የትምህርት ህይወት የነበረው የኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ማለፍና ያለማለፍ ላይ ነው በትምህርት ቤታችን ከሺ በላይ የኛ ተፈታኝ ተማሪ አለ በዚያን ጊዜ ሀኪም ለመሆን መግቢያው ሲሆን የእኔ ውጤት ግን ብቻ ሆነ የእኔም እቅድ አጎቴ አዳነ ገለቱ ሐኪም ይሆናል ብሎ ያለመው ሕልም ሕልም ብቻ ሆኖ ቀረ ዛሬ ሳስበው ግን አምላኬን ተመስገን እለዋለሁ ሐኪም መሆን ልፈልግ እንጂ ሐኪም ምንድን ነው። እንደ መውጫ ከ ምርጫ ፃንጎቨር ስላልወጣ በቅጡ የዚህ ዓይነት ምርጫ ውጤት ምን አንደምታ አንዳለው አልተረዳም ነበር።

  • Cosine Similarity

በሚል ለተነሱ ጥያቆዎች ማብራሪያ የቀረበ ነው ይህ ጉዳይ አሁንም ጊዜው ያልፍበታል ብዬ አላስብም ከምርጫው ውጤት በላ ብዙ ሰዎች ስለሂደቱ ይጠይቁኛል በተሟላም ባይሆን መልስ ስሰጥ ቆይቻለሁ አሁን ግን ለሁሉም በአኩል መልስ እንዲሆን በሚል በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ቦታ እንዲኖረው አድርጌያለሁ ብዙ ግምቶችን አና መላ ምቶችን ያስቀራል ብዬም አምናለሁ ከምርጫው በጊላ ሁሉም አንባቢ ሊረዳው እንደሚችለው ለብዙ መላ ምቶችና የሀገር ውስጥና የውጭ ሚዲያዎች ባቀረቡት የተለያዩ በጎና በጎ ያልሆነ አስተያየቶች መጋለጤ ይታወሳል በፍፁም ያልጠበኩት ስለነበር ለዚህ የሚሆን ዝግጅት አልነበረኝም በምርጫ ውድድር ወቅት ለተወካዮች ምክር ቤት እንደምመረጥ ምንም ጥርጥር ያልነበረኝ ቢሆንም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛ ተመራጭ እሆናለሁ ብዬ ግን አላሰብኩም በምክር ቤት የፓርቲዬ ብቸኛ ተወካይ ሆኝ በፓርላማ ዋነኛ ተናጋሪ እሆናለሁ የሚል ግምትም ሆነ የግል ዝግጅት አልነበረኝም በፓርቲው ውስጥ በነበረኝ ዛላፊነት በተለይም በጥናትና ምርምር ቡድን አባልነቴ ብዙ ማድረግ የምፈልግ የነበረው ምክር ቤት ለሚገቡ አባላት የሙያ ድጋፍ የሚሰጥ በከዘዘላከበሄዚ ውስጥ በንቃት ለመሳተፍ ነበር የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ለፓርቲዬ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ድምፃቸውን በአማራጭ ማቅረቢያ የታሪክ ክስተት ሆንኩና አረፍኩት ይህ የታሪክ አጋጣሚ ከተፈጠረ በኋላ ጉዳዩን በጥልቀት መርምሬ ከድምዳሜ የደረስኩበት ቁርጥ አቋም ግን ይህ ኃላፊነት ያልተዘጋጀሁበትም ቢሆን እንኳ ከአሁን በላ በቁርጠኝነት ፃላፊነቱን ለመወጣት ከመዘጋጀት ውጭ ብዙ የተሻለ አማራጭ እንደሌለኝ ነው ስለዚህ የ ምርጫን ተከትሉ የመጡ ጉዳዮችም ለአንባቢ ቢቀርቡ ጠቃሚና ቀድመን የተነሳንበትን የነፃነት አጀንዳ ያጠናክራሉ ብዬ ስላመንኩ በዚህ መጽሐፍ እንዲካተቱ ተደርገዋል የዚህ መፅሐፍ አንደ ክፍል የሆነውን ስለግል የፖለቲካ ምልከታዬ እንድፅፍ የገፋፋኝ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊና የዳንዲ የነጋሶመንገድ ፀሐፊ ዳንኤል ተፈራ ነው ልክ ነው የእኔ ሰብዕና ከአሁን በኋላ በፖለቲካ ውስጥ እስካለሁ ድረስ ከዚህ የተለየ ሊሆን አይችልም ስለዚህ ለደጋፊዎቸም ሆነ ለተቃዋሚዎቼ በቅጡ በመረጃ የተደገፈ አስተያየት እንዲሰጡና ከመሰለኝ እና ደስአለኝ አስተያየት እንዲወጡ የሚረዳቸው ስለሚሆን ጠቃሚነቱን አምፔበታለሁ ቢሆንም በዚህ ርዕስ ስር መግለፅ የምፈልገው የራሴን የፖለቲካ አስተሳሰብ ሲሆን በምንም ዓይነት አባል የሆንኩበትን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን አይወክልም አንድነት ፓርቲ ካለው አቋም ጋር የእኔ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተመሳሳይነት ቢኖረው አንድነትን እንደ ፓርቲ የመረጥኩበትን ምክንያት ያጠናክርልኛል ልዩነት ሲኖር ደግሞ ፓርቲው የማንንም ሙሉ ፍላጎት እንደማያሟላ ሁሉ ለአፄም እንዲሁ ነው የሚለውን ከማሳየት ውጭ ሌላ መልዕክት ሊኖረው አይችልም ከዚህ አንፃር አቶ መለስ ዜናዊ ከሞቱ በላ በፋና ሬዲዮ ከኢህአዴግ የተሻለ የፖለቲካ አስተሳሰቤን ሊያሳካልኝ የሚችል ፓርቲ የለም የሚለውን ቃላቸውን በተደጋጋሚ እንሰማው እንደነበረው ለእፄም አንድነት የፖለቲካ አስተሳሰቤን ለማሳካት የመረጥኩት ፓርቲ መሆኑን ማስገንዘብ የግድ ይላል አንድነት ውስጥ አባል የሆነ ሁሉ ግን አንድ ዓይነት የፖለቲካ አስተሳሰብ አለው ተብሎ አይገመትም ትክክልም አይደለም ፓርቲው ግን ለብዙዎች አማካይ የሆነ የፖለቲካ ምህዳር ፈጥሮ በጋራ መድረክነት ያገለግላል በሚለው ነው መስማማት ያለብን የማንኛውም ፓርቲ አባላት የሰዎች ስብስብ ስለሆነ የተለያየ አስተሳሰብ መኖሩ ተፈጥሯዊ መሆኑን መቀበል የግድ ይላል ለዚህም ነው ፓርቲዎች ውስጥም የመሪነት ቦታ የሚይዙ ሰዎች አማካይ ቦታ በመያዝና በመፍጠር በአብዛኛው አባላት ይሁንታ አግኝተው የመሪነት ቦታ የሚይዙት እንደ ኢህአዴግ ባሉ ሶሻሊስት ነክ ግራ ዘመም ፓርቲዎች ውስጥ ግን የፓርቲ አባላት በዲሞክራሲያዊ አግባብ የሚመረጡበት ሳይሆን በሶሻሊስቱ አባባል ድርጅታዊ ሥራ ወይም ደግሞ በሴራ ተንታኞች አባባል አንጋሾች ከበ በል« የሚሠሩበት ነው ድንገቴዎችም በአንጋሾቻቸው በኩል ብቅ የሚሉበት ነው በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ስለ ፖለቲካ አተያዬ ማቅረብ የፈለግሁት ከዕቅዴ ቀድም ብሎ በታሪክ አጋጣሚ በሀገራችን ፖለቲካ ዋነኛ ተሳታፊ ስለሆንኩ እና ይህንን ደግሞ ማሳየት ደጋፊዎቼም ሆኑ ተቃዋሚዎቼ በግልፅ አውቀውት ግልፅ በሆነ መንገድ መጫወት አለብን ብዬ ስለማምን ነው በአኔ አምነት ኢትዮጵያ ሀገራችን አሁን ላለችበት ኋላ ቀር ደረጃ መድረስ ዋናው ምክንያት በግልፅ ርዕዮት ዓለም የተቃኘ ዘመናዊ መንግሥት ያለመኖርና የመሪነት ስልጣን የያዙትም ግለሰቦች ቢሆኑነ በተለይ ላለፉት ዓመታት የማውቀውን ለማለት ነው ወጥ በሆነ ሀገራዊ ራዕይ ሳይሆን በድርጅት ጥቅምና በግለሰቦች ፍላጎት ላይ የተመሰረቱ ስለነበሩ ነው ቻም ፅሪጋራቻ። ይህ እንግዲህ በቅንጅት ውስጥ በፓርላማ ተመራጭነት እንዳልከሰት አንድ መሰናክል ሆነ መሰናክሉንም የሠሩት ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ ናቸው ከምርጫው ሳምንት ቀድሞ በሚያዝያ በግል ካነሳሁት ፎቶ እና ስታዲየም አካባቢ የነበረውን የደስታ ስሜት በቃላት ልገልፀው የምችል አልነበረም ምንም የማልደብቀው ግን በሚያዝያ ኢህአዴግ ጠርቶት በነበረው ስብሰባ የወጣው ህዝብ ስሜቴን ረብሾት ነበር ነገር ግን በሚያዚያ በምንችለው አቅም መቀስቀስ አለብን ብለን በጠዋት ጥሩንባ እየነፋን ከሰፈር ስንወጣ የፌዴራል ፖሊሶች ጋር ገና ከካምፕ እየወጡ ስለነበር በምልክት እናደርግ የነበረው የወንድማማችነት መንፈስ በጣም የሚያስደስት ነበር ሁሌም ይህ ስሜት አብርኝ ይኖራል ከዕጩነት ከወጣሁ በኋላ በምርጫ በፓርቲዬ የተሰጠኝ ምንም ተልዕኮ አልነበረም የእ ሥራ በመራጭነት መሳተፍ ብቻ ነበር ነገር ግን በሥራ አጋጣሚ በምርጫ ታዛቢነት የተሰማሩ ብዙ ሰዎች ስለማውቅና በተዘዋዋሪ ታዛቢነት የሚሠሩ የአውሮፓና የሲቪክ ማህበራት ታዛቢዎችን ስለማውቅ ሥራዬ ከዚህም ከዚያ የምሰማቸውን ቅሬታዎች ለነዚህ ሰዎች ማቀበል ነበር በዕለቱ ከተቀበልኳቸው ስልኮች የማልረሳው የዶክተር አለማየሁ አረዳን ስልክ ነው በመራጩ ተነሳሸነት በጣም ተመስጦ በቀጣይ በወረዳና አካባቢ ምርጫ በንቁ እንደሚሳተፍ በወረዳ ደረጃ እንደሚወዳደር ውጤት ማስመዝገብ የሚቻለው በዝቅተኛው ደረጃ እንደሆነ የነገረኝን ነው በኋላ ላይ በፓርቲ መሪነት በሚያዝ ስልጣን ምክር ቤት የገቡትንም ሰዎች የፖለቲካ አመራር በመስጠት መቆጣጠር እንደሚቻል ሲያስብ አና ሲያምን ነው የተለየ መስመር ይዞ ወደ ሴራ ውስጥ የገባው የሚል እምነት አድሮብኛል ሴራውን ወደፊት እናየዋለን በግንቦት ምርጫ ማግስት እንደተለመደው በጠዋት ቢሮ ልገባ ስፄድ በማልፍበት መስመር ሁሉ ቀበሌ በር ላይ የተለጠፉ የምርጫ ውጤት የሚመለከቱ ሰዎች ስብስብ ታዘብኩኝ በጠዋት ሻይ ከምጠጣበት ሳይ ኬክ ቤት ድንገት አንድ ጓደኛዬ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ ከሆነ ጓደኛው ጋር ሆኖ ደወለልኝና ቢሮ ሳልገባም ተገናኘን ስለ ምርጫው ሁኔታ አውርተን በደስታ መንፈስ ውስጥ ሆነን ምርጫ ጣቢያዎችን እየዞርን ማየት ጀመርን በዚያውም አዲስ አበባ ውስጥ የምናውቀውን ምርጫ ጣቢያ ሁሉ አካለልን ሶስታችንም እየወረድን አይተን ነበር የምንመለስው ማንም ለማንም የምርጫውን ውጤት በውክልና አይመለከትም የአዲስ አበባን ካረጋገጥን በኋላ ሁላችንም ወደምናውቀው የክልል ከተሞች እየደወልን ማረጋገጥ ሥራችን ሆነ አንዲሁ ስልክ መደዋወል እና ፈንጠዝያ ሆኖ ዋለ ከዚህ በኋላ የሆነውን ሁሉ በህልሜም ሆነ በዕውኔ አስቤው አላውቅም ነበር በኢትዮጵያ ታሪክ የተፈጠረን ፈጣን የዲሞክራሲ ባቡር እንዲህ ባለ አስቀያሚ ሁኔታ መስመሩን ስቶ መንገደኛውንም ተሳፋሪውንም ያጭዳል ብዬ አልገመትኩም ግንቦት ቀን ዓም ምሽት ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን የአስቸኳይ ጊዜ መግለጫ የሰማሁት እንደ ልማዴ ሀገር ሰላም ነው ብዬ የኢህአዴግ ሹመኛ ከሆነ የሰፈሬ ልጅ ጋር ነው ፅለቱ በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገር ለቆ መሰደድ የሚል ምኞት በአዕምሮዬ ብልጭ ያለበት ነበር ደግነቱ የስደት ስሜቱ ወዲያው ጠፋ ሀገር ለማን ተትቶ ይኬዳል በሚል ስሜት ተሸነፈ ሁልጊዜ ይህንን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሳስብ አቶ መለስ ደርግ በመስከረም ወር ዓም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ክልክል ነው የሚለው አዋጅ ነው ከሀገር ያስወጣን የሚሉትን ያስታውሰኛል ይህ መግለጫ ከዚያ አዋጅ ኮፒ ተደርጎ ወይም በአንድ ሰው የተዘጋጀ ነው የሚመስለኝ ወደድንም ጠላንም ይህ ከደርግ አዋጅ የተቀዳ መግለጫ የዲሞክራሲውን ባቡር በመገልበጥ ዋነኛው ነበር ከሰኔ አንድ ግርግር በኋላ በሰፈራችን አውቶብስ ተራ ሰባተኛ አካባቢ በቀድሞ ወረዳ ቀበሌ ቀበሌ ጽቤት ግቢ ውስጥ የሰፈረ የአግአዚ ጦር ነበር ከአንድ ወዳጄ ጋር በትውልድ ሰፈሬ አካባቢ አንደተለመደው አብረን አምሽተን ልሸኘው ወደ ሰባተኛ አየወረድን ሀገር ሰላም ነው ብለን ጦሩ ከሰፈረበት አጠገብ ልኳንዳ ቤቶች ጋ ስንደርስ ስጋ ይዢ ልግባ። ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው ፈተና ካለፉ በኋላ ቢጠየቅ የአብራሪዎቹን የብሔር ተዋፅኦ መረጃ ለማወቅ ይረዳል ልንል እንችላለን በብሔር ማንነት ፈተና መውደቅና ማለፍ እንደማይኖር ግን መተማመን ያስቸግራል ይህ መቼ እንደሚፈነዳ የማይታወቅ ቦንብ ለዚህች ሀገር ቀናኢ ነኝ የሚል ማንም አካል በአፋጣኝ እንዲያስወግድልን መታገል አለብን ካልሆነ ግን የማይታረም ስህተት ይፈፀማል የሚል ስጋት ሁልጊዜ አለኝ ምክር ቤት ከገባሁ በኋላ አንድ የፀደቀ አዋጅ አለ ምናልባት ይህ አዋጅ በሥራ ላይ ሲውል ይህ ብሔር ማን ነው ብሎ የሚጠይቅ መታወቂያ አሰጣጥ ከጨዋታ ይወጣል የዚያን ጊዜ ከተቀበሩት ፈንጂዎች አንዱ ከሸፈ ልንል እንችላለን እኔ እስከማውቀው ድረስ ኢዴሊ የመጨረሻ ስብሰባውን ያካፄደው ለቅንጅት መስራች ጉባዔ የሚላኩትን አባላት የመረጥን ፅለት ነው ይህ ስብሰባ ዘግይቼም ቢሆን አንደተረዳሁት በከፍተኛ ሴራ የተጎነጎነ ሰዎች የሚሉት እና የሚሆኑት የማይገጥምበት አንደነበረ ተመልክቻለሁ ይህ ስብሰባ ከመካፄዱ ምናልባትም አንድ ወር ቀደም ብሎ አንድ ስብሰባ ተጠርቶ በ ምርጫ የተገኘውን ውጤት የሚመጥን አመራር ያስፈልጋል በሚል ኢዴሊ የአመራር ምርጫ አካሂዶ እኔም በከፍተኛ ድምፅ የኢዴሊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሁጄ ተመረጥኩኝ በዚህም ምርጫ ውጤት መሰረት ዶክተር አለማየሁ አረዳ ወደፊት በመምጣት የፓርቲው ሊቀመንበር ሆኖ ተመረጠ ፓርቲውን በሊቀመንበርነት ይመራ የነበረው አቶ ቸኮል ጌታሁንም ቦታውን ለዶክተር አለማየሁ አረዳ ያለምንም ማንገራገር አስረከበ ማንገራገርን ምን አመጣው እንዳትሉኝ ወደፊት የተሰነቀለትን ቢያውቅ ምን ይል እንደነበር ማሰብ ተገቢ ይመስለኛል ወደ መጨረሻው ስብሰባ ስንመለስ በስብሰባው የነበረው ዋነኛ አጀንዳ አንድ ብቻ ነበር ፓርቲውን ወክለው ቅንጅት መስራች ጉባዔ ላይ የሚሳተፉ አባላትን መምረጥ ከዚህያም ተከትሎ የላዕላይ ምክር ቤት አባላት የሚሆኑ ወኪሎች እና የቅንጅት ሥራ አስፈፃሚ የሚሆኑ አምስት አባላት ምርጫ ነበር መሥራች ጉባዔ ላይ የሚሳተፉ አባላትን መምረጥ ብዙ ችግር አልፈጠረም አቅጣጫ ብቻ አስቀምጠን ስምምነት ላይ ተደረሰ የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እንዴት ይካሄድ በሚለው ላይ ሰፊ እና አድካሚ የሆነ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ሁለት ሀሳቦች ነጥረው ወጡ አንደኛው ባሉት ሰባት ሥራ አስፈፃሚዎች ላይ አምስት እንጨምርና አስራ ሁለት ይሁኑ አነርሱም ከመካከላቸው አምስት የቅንጅት ሰራ አስፈፃሚ የሚሆኑትን አባላት ይምረጡ የሚለው ሲሆን ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ ሁሉም እንደ አዲስ ይጠቆሙና አስራ ሁለት ሰው ከተጠቆሙት ውስጥ ይመረጥ የሚለው ነበር በእኔ እምነት ከወር በፊት ፓርቲውን እንዲመሩ በሙሉ ስምምነት የተመረጡ ሰዎችን እንደገና ማወዳደር ተገቢ ስላልመሰለኝ የመጀመሪያውን ሃሳብ ደግፌ ብዙ ተከራክሬአለሁ የሚገርመው ነገር የፅለቱን ስብሰባ ዶክተር አለማየሁ እኔ አንድመራው አደረገ ምክንያቱም ሰብሳቢነትን በዙር በማድረግ የአመራር ክህሎት ማዳበር አስፈላጊ ነው የሚል አመክንዮ በማቅረብ አና በቀጣይ ፓርቲውን ለመምራት ዝግጁ መሆን የሚል ነበር ይህ ደግሞ ቅዱስ ዛሣብ ነው ዶክተር አለማየሁ አኔ በምመራው ስብሰባ ከተሰብሳቢ ጋር ሆኖ ሁለተኛውን ፃሣብ በመደገፍ ሽንጡን ገትሮ ተከራከረ ይህ ደግሞ በተለይ የሴቶች ተሳትፎን ከመጨመርና ለክልሎችም ተገቢውን ውክልና በቅንጅቱ ውስጥ እንዲያገኙ በሚል አሳማኝ በሚመስል ፃሳብ አጀበው አንደ ሰብሳቢ በደንብ ዛሃሳብን ከማራመድ ለሌሎች አድል መስጠት እንደተጠበቀ ሆኖ ይህንን ለመገዳደር የሚያስችል ምንም በቂ ምክንያት ስላላገኘሁ በሰብሳቢነቴ ለሁለተኛው አማራጭ እጅ ሰጠሁ ቤቱንም በዛው መስመር እንዲሄድ አደረኩት በዚሁ መሰረት የፅጩክ ጥቆማ ተካሄፄደና የተደራጀ በሚመስል ሁኔታ ዕጩዎች ቀረቡ የሚስጥር ድምፅ አሰጣጥን መሰረት አድርጎ ምርጫ ተካሄደ በምርጫውም ውጤት መሰረት ቅንጅትን ከሚወክሉት አስራ ሁለት ሰዎች ውስጥ ግርማ ሠይፉ የሚባል ስም ማግኘት ሳይቻል ቀረ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ለአመራርነት የመረጡትን ሰው በቀጣይ ቅንጅት ውስጥ ተወካይ እንዳይሆን የሚደረግበትን ድምፅ አሰጣጥ አንባቢ ልብ ይበለው በአውነቱ በተገኘው ውጤት ምንም ቅር አልተሰኘሁም የተገኘውን ውጤት ለተሰብሳቢዎች አሳውቄ የተመረጡት አስራ ሁለቱ አባላት አምስት ለቅንጅት የሥራ አስፈጻሚ የሚሆኑትን ከውስጣቸው እንዲመርጡ ወስነን ከስብሰባ ወጣሁ በጣም ርቦኝ ስለነበር ብቻዬን ወደ ካዛንችስ አመራሁ ካዛንችስ ደንበኛዬ ግሮሰሪ ቤት ምግብ ስለማይሠራ ምሳዬን ከጎረቤት እንዲያስመጣልኝ አድርጌ በላሁ ቢራ እየጠጣሁ ከግሮሰሪው ባለቤት ጋር የጦፈ ወሬ ይዢ እያለ ስልኬ አንቃጩለ ስለሺ ጠና ነበር የደወለው ይህንን ሰውዬ አንድ አትለውም ወይ። መኢአድ ለሊቀመንበርነት ኢንጅነር ኃይሉን በሌሉበት ዕጩ አድርጎ በማስመረጥ ከመጀመሪያው ከውድድር ውጭ ሆኖ የሌሎቹን ዕድል ወሳኝ ሆነ ቀስተደመና ለሊቀመንበር ቦታ አሯሯጭ መድቦ ለተቀዳሚ ሊቀመንበርነት ቦታ ያልተገመተ ዕጩ ይዞ ቀረበ ብርቱካን ሚደቅሳን የተጠና በሚመስል የድምፅ አሰጣጥ ብርቱካን ሚደቅሳ ዕጩዎቹን እነ ልደቱን አሸነፈች ለምክትል ሊቀመንበርነት እንዲሁ ልደቱና ስለሺ ጠና ተወዳደሩ ልደቱ አሸነፈ አሸነፈ ማለት ይከብዳል የተመደበለት ቦታ ተሰጠው ቢባል አግባብ ነው ዶክተር አለማየሁ በእርግጠኝነት ፀሐፊ እንደሚሆን አምኖ ለመጨረሻ ጊዜ በዕጩነት ቀረበ ከዚህ ቀደም ለዋና ፀሐፊነት እንደማይወዳደር በግል አጫውቶኛል ምክንያቱም ዋና ፀሐፊነት የሙሉ ጊዜ ሥራ ስለሆነ አርሱ ሥራ ስለሚበዛበት እንደማይፈልገው በተደጋጋሚ ይነግረኝ ነበር እኛም የፓርቲ ምክትል ቢሆን ከሱ ችሎታ ጋር በጣም ጥሩ እንደሆነ በተለይ በፓርቲ አቅም ግንባታ ምክር ቤት ከተመረጡት የቅንጅት ሰዎች አቅም ውሱንነት አንፃር በጣም ጥሩ ሥራ አንደሚሠራ እንጫወት ነበር ነገር ግን ቸኮል በቅንጅት አመራር ውስጥ እንዳይኖር የተበተበው ተንኮል መነሻ ሆኖ በአጸፋው በዶክተር ብርፃነ በሙሉነህ እና ስለሺ የሴረኛነት ተንኮል ሲጎነጎን ነበር በወቅቱ በነበረው ደንብ ፓርቲው ዕጩ አድርጎ ያላቀረበው ሰው በሌሎች ዕጩ ሆኖ ቀርቦ መወዳደር ይችላል ይላል በሰላም ጊዜ ቢሆን አሯሯጭ እንደማለት ሊሆን ይችላል በዚህ መሰረት ለፀሐፊነት ከፓርቲ እራሱን ሲያቀርብ ሙሉነህ በግል በብርቱካን ነው የተጠቆመው ይባላል ተጠቁሞ ዕጩ ሆኖ ውድድር ተጀመረ ውጤቱም ከብርቱካን ሚደቅሳ ቀጥሎ ቅንጅት በፍፁም ያልተጠበቀ ዋና ፀሐፊ ይዞ ብቅ አለ ደጅ ሆነን ውጤቱን ስንጠብቅ ለነበርን ሰዎች ከሚጠበቁ አራት ሰዎች ሁለቱ ድንገቴዎች ሆነውብናል ምርጫው እንደተጠናቀቀ ስለሺ ደውሎ መርከቡ ቀጣይ ፕሮግራሞችን አቋርጦ እንደወጣ እና ስልክ እአንደማያነሳ ነገረኝ ደወልኩለት ስልኬን ሲያነሳ የት ነህገ ስለው ሌላ ቦታ ከሰው ጋር ቀጠሮ አለኝ አለ እግዜር ያሳያችሁ በዚህ ዓይነት ልዩ ቀን ሌላ ቦታ ፕሮግራም ምን የሚሉት እንደሆነ ገምቱ የሴራዎች አባት የሆነው ዶክተር አለማየሁ በሌሎች ሴራ ተጠልፎ ወደቀ መርከቡ ሰመጠ ስለዚህ በዶክተር ብርዛፃኑ በሙሉነህና ስለሺ አቀናባሪነት በተሠራ ሴራ ዶክተር አለማየሁ የፈለጋትን በቅንጅት ከፍተኛ የፖለቲካ ቦታ የማግኘት ምኞት ምናልባትም ከልደቱ ጋር ቁልፍ ቦታዎችን በጋራ ለመቆጣጠር እና ቅንጅቱን በተለየ አቅጣጫ ለመውሰድ ያወጡት ዕቅድ ሳይሳካ ቀረ ይህ የሴራ ትንተና ልክ ነው ብለን ከወሰድን ዶክተር አለማየሁ ልደቱን አሳት ላይ ጥዶት ማህተም አላደርግም እንዲል ማለት ነው በነገራችን ላይ ዶክተር አለማየሁ ልደቱን እንዲያግባባ በቅንጅት ተወክሎ ነበር አመሉን ያውቃል በሚልጋ ወይም ልደቱ በራሱ ምርጫ ለብቻው ቅንጅት ዕውን አንዳይሆን በታሪክ አሳፋሪ የሆነውን ተግባር ፈፀመ በራሱ እጅ የፖለቲካ ሞትን ለራሱ ደገሰ ከአሁን በኋላ በኢትዮጵያ ፖለቲካ አንዳይነሳ ሆኖ ራሱን ቀበረ ይህ በገንዘብ ሊተመን የማይችል የተአማኒነት ጉድለት ምናልባትም እንደልደቱ ላለ ወጣት ለነበረ ፖለቲከኛ አድሜ ከሰጠው የስቃይ ዘመኑ ረጀም ባይሆን ጥሩ ነው ለልጅ ልጁ የሚተርፍ ይሆናል ይህን እድፍ ሊያፀዳ የሚችል የማስተርስ ፕሮግራም በዓለም ላይ ያለ አይመስለኝም አሁን የተያያዘውም የሦስተኛ አማራጭ ማደናገሪያም የሚሠራ አይደለም በቅንጅት የምስረታ ቀን በፓርቲዎች ቅድመ ዝግጅት ያልተደረገበት ነገር ግን አጅግ አስፈላጊ በጠቅላላ ጉባዔ መከናወን ያለበት ጉዳይ ታወሰ ይኸውም የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ መምረጥ ነው ፅጩ እንዴት ይቅረብ ሲባል ሁሉም ድርጀቶች ዕጩ ያቅርቡ ተባለ ኢዴሊም በሙሉነህ ጠቋሚነት እኔን ማስመረጥ አንዳሰቡ ዶክተር ብርዛፃነ መጥቶ ከነገረኝ በኋላ በአጭሩ ኢንተርቪው አደረገኝና ተስማምተን ዕጩ እንድሆን ተባለ በዚያን ሰዓት መርከቡ ስላልነበር የኔን ዕጩ መሆን ለኔሲል አስፋው በከፍተኛ ደረጃ ተቃወመች። ፍና ያመፇፇሥታ ሥጳጣፇ ጴባው ዕጴላኃዴሃ መፇሥፖ ጋረ ዳዖታሥመጓያሩ መሥራፖ መቋ ቻ ይያፖሃ ዴፖም ይያ ጋረ መድሉት ገፅ በማለት ፓርላማ ለመግባትም አዲስ አበባን ለመረከብም ፈቃደኛ አልነበርንም ይላል ስለዚህ ከላይ በዘረዘርኳቸው አብይ ምክንያቶች የተነሳ ስለ ቅንጅት የግሌን ማለት ተሰማኝ የመጨረሻውን የጨመርኩት መድሎት የሚባለውን የአቶ ልደቱ አያሌውን መጽሐፍ አንብቤ ጥሩ ጥሩውን ጠቅሼ ለምሳሌ በህገመንግሥት ላይ የሚሰጣቸውን ትንተና ውሸት ያልኳቸውን እያነሳን ከጓደኞቼ ጋር ስንነጋገር አንድ ጓደኛዬ ወሬ አታብዛ አርሱ ፃፈ ልብ ካለህ በጽሑፍ መልስህን ስጥ ስላለኝ ጭምር ነው እንጂ ልደቱ አያሌውን አጀንዳ ማድረግ ፈልጌ አይደለም በዚህ አጋጣሚ ልነግራችሁ የምፈልገው በኢህአዴጎች መንደር ስለ ልደቱ አውርተው አይጠግቡም ለተቃዋሚ መስመር በጣም አስፈላጊ አንደሆነ እየደጋገሙ ያነሳሉ ዝም ብዬ ሳስበው ግን የሆነ ያላለቀ ፕሮጀክት ያለ ይመስለኛል ይህንን የሚያውቁት አንግዲህ ሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች ቢሆኑም እኛንም አይመለከተንም አይባልም ስለዚህ ነቃ ማለት የግድ ይላል ከላይ እንደገለጽኩት ቅንጅት ፓርላማ አልገባም አዲስ አበባንም አልረከብም በማለቱ በዚህች ሀገር የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ አሉታዊ አስተዋፅኦ አድርጓል የሚለው ድምዳሜ ትክክል አይደለም አላለሁ ይህም የሆነው አንዳንዶች ሳያውቁ በስህተት አንዳንዶቹ ደግሞ አውቀው በድፍረት የሚነዙት ፕሮፓጋንዳ ውጤት ነው ዛቁ ግን ቅንጅት የወሰነው ፓርላማ እንግባ አዲስ አበባንም እንረከብ የሚል ነው ይህ በቃለ ጉባዔ የተያዘና የተወሰነ ነው በግልባጩ ግን ኢህአዴግ ፓርላማ እንዳይገባ አጥር ያጠረበትና አዲስ አበባን አላስረክበም ያለበት መሆኑ ነው ይህንን ጉዳይ መረዳት የፈለገ ግማሽ ሙሉ እና ግማሽ ጎዶሎ ከዘ ከዘ በ ከሸ ፀበህቬ በሚለው ምልከታ መሆን አለበት ኢህአዴግ ይህንን በህዝቡ ዘንድ ለማስረጽ በስፋት የተጠቀመው በሞኖፖል በያዘው ሚዲያ አማካኝነት ነው ሚዲያን በሚመለከት አንድ ወዳጄ በግል የገጠመውን ታሪክ አጫውቶኛል ይህ ታሪክ ኢህአዴግ ሚዲያውን አንዴት እንደሚጠቀምበት ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ እንዲሁም ለሌላ ጊዜም ለንፅፅር የሚረዳ ስለመሰለኝ ላካፍላችሁ ወደድኩ ይህ ጓደኛዬ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ተዷሚ ነበር ማለትም በአንድ መሥሪያ ቤት ውስጥ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ብቻ ሳይሆን ከዋናው ሥራ አስኪያጅ በላይ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚታውቅ ነበር በምርጫ ሰሞን ከሀገር ውጭ ስለነበር በመራጭነትም ለመመዝገብ ባለመቻሉ የምርጫውን መሟሟቅ ሲመለከት በምርጫው በአንድ ወይም በሌላ መልኩ መሳተፍ ይኖርብኛል ብሎ ይወስናል የቀረው አማራጭ ምርጫውን በግል ታዛቢ ሆኖ መሳተፍ ነበር ከሌሎች መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶቸ ጋር ሆኖ በታዛቢነት እንዳይሳተፍ ያለበት ኃላፊነት ብዙ ምቾት አልሰጠውም እና በግል መታዘብ አለብኝ በሚል ውሣኔ ወደ ምርጫ ቦርድ ይሄድና ይህንኑ ፃሳቡን ያሳውቃል ፈቃድም እንዲሰጠው ይጠይቃል አዎንታዊ መልስ ሰጥተው ሌላ ጊዜ መጥቶ እንዲጠይቅ ቀጠሮ ይሰጡትና ይለያያሉ የቀጠሮ ቀን ከመድረሱ በፊት በግል መታዘብ ለምትፈልጉ ምዝገባ ማድረግ እንደምትችለ የሚል ማስታወቂያ ይሰማና በማስታወቂያው መሰረት ወደ ምርጫ ቦርድ ይሄዳል መዝግበውት አስራ አንድ ፎቶ እንዲያመጣ ይነግሩትና ይህንንም በአስቸኳይ ይፈጽማል ከዚያ በኋላ ቢጠብቅ ቢጠብቅ የታዛቢነት መታወቂያ የሚሰጠው ሰው ያጣል ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም ሆነ ቢቸግረው በዚያን ጊዜ ገለልተኛ ከምትመስለን አሁን በደንብ ከምናውቃት የውስጥ አርበኛ ከሆነችው ሚሚ ስብዛቱ ጋር በግል ስለሚግባቡ ዝርዝሩን ይነግራትና ጉዳዩን በሚዲያ ማስተላለፍ አችላለሁ ግን ካለሁበት ኃላፊነት ጋር ጥሩ ስላልሆነ እነዚህን ሰዎች አስኪ አነጋግሪያቸው ይላታል በደረሳት ጥቆማ መሰረትም ሚሚ ስብፃሃቱ ምርጫ ቦርድን አነጋግራ ሰፊ ዘገባ በቪኦኤ ሠርታ አስተላለፈች በተከታታይም በሬዲዮና በቴሌቪዥን በግል መታዘብ አንደሚቻል ማስታወቂያ ይነገር ጀመር በተግባር ግን አይቻልም ። ውይይቱ ለህዝብ በመከፈቱ የኢህአዴግ ሴረኞች መግቢያ ቀዳዳ አግኝተው ፓርላማ መግባት አይገባም የሚል አጀንዳ በስፋት አራምደዋል እነርሱ ብቻም አይደለም ከምር የህዝብ ድምፅ መከበር አለበት የሚሉ ደጋፊዎችም ፓርላማ መግባት ትክክል አይደለም ብለው ሞግተዋል በማይጠበቅ ሁኔታም ለደሞዝ ከሆነ እኛ አእንከፍላችኋለን እስከ ማለት የደረሱ ሰዎች ነበሩ በቅንጅቱ የተወከሉት የመድረክ መሪዎች ግን ሲያስተላለፉ የነበረው መልዕክት ን ውሳኔውን ፓርቲው እንደሚያደርግ ነገር ግን ውሳኔው ምንም ይሁን ምን ህዝቡ በፀጋ እንዲቀበለው የሚል ነበር ይህ አካፄድ ያልጣመው የኢህአዴግመንግሥት ግን ቀጣይ ህዝብን የማወያየት ዕቅዶችን አገደ እንደዚያም ሆኖ ቅንጅት ላዕላይ ምክር ቤት ታሪካዊ ውሳኔ ነው ያስተላለፈው የሚል ፅምነት አለኝ ወደ ፓርላማ አትግቡ ያለውን የህብረተሰብ ድምፅ ከግምት ውስጥ ያስገባና ኢህአዴግ ፓርላማ እንዲገቡ ከፈለገ ደግሞ ዕድል የሚሰጠው ነበር ኢህአዴግ ግን የዚህ ዓይነት ታሪካዊ ፅድሎችን የመጠቀም ባህል ስለሌለው አምባገነንቱን ይፋ ያደረገ ጨካኝ እርምጃ ተግባራዊ አደረገ የህዝብ ተመራጮችን ማሰርና ደጋፊዎችን በጠራራ ፀሐይ በአልሞ ተኳሾች መግደል ተያያበ የቅንጅት ላዕላይ ምክር ቤት ፓርላማ እንግባ የሚል ውሳኔ ነው የወሰነው ሲባል ምን ማለት አንደሆነ ግልፅ ላድርግ ይህ ውሳኔ ሲወሰን የተለያዩ ሃሳቦች ሲንሸራሸሩ ስለነበር ጉዳዮችን ነጥብ በነጥብ ለይቶ በማየት በመጨረሻ ውሳኔው የተወሰነው በሙሉ ድምፅ ነው ልደቱን ጨምሮ ማለት ነው ልደቱ ከየት አምጥቶ እኔ እንግባ ስል እነርሱ አክራሪ የቅንጅት አመራሮች አንግባ አሉ አንዳለ ግልፅ አይደለም ፓርላማ ለመግባት ግን ለኢህአዴግ የቀረቡለት ቀላል ጥያቄዎች የሚከተሉት ነበሩ በቅንፍ የተጨመሩት የህገመንግሥት አንቀፆች የእኔ ናቸው ነባ ገለልተኛና ጠንካራ የማስፈፀም ብቃት ያለው የምርጫ ቦርድ ህገመንግሥት አንቀፅ ነፃና ገለልተኛ ፍርድ ቤት ህገመንግሥት አንቀፅ የፖሊስ የደህንነትና የመከላከያ ሃፃሃይል ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት መራቅ ህገመንግሥት አንቀፅ ሰኔ ዓም የተገደሉ ኢትዮጵያዊያንን ጉዳይ የሚያጣራ ገለልተኛ ኮሚሽን እንዲቋቋም ግድያውን በፈፀሙ ላይም ህጋዊ እርምጃ አንዲወሰድ ፍትሐዊ የመንግሥት ሜዲያ አጠቃቀም እንዲኖር የግል ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ እንዲቋቋም ህገመንግሥት አንቀፅ ከግንቦት ሰባት በኋላ በተወካዮች ምክር ቤት አሠራርና የአዲስ አበባ መስተዳድርን በተመለከተ የወጡትን ህጎች ቀድሞ ወደነበሩበት መመለስ በፖለቲካ አመለካከታቸው የታሰሩ አባላትን መፍታት የታሸጉ ቢሮዎቻችንን መክፈት እንዲሁም በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ እየተካፄደ ያለው ማሳደድ እንዲቆም እነዚህን ጥያቄዎች በተግባር መዋላቸውን የሚከታተልና የሚያስፈፅም ነፃ ኮሚሽን ይቋቋም የሚሉት ናቸው የተጠየቁት ጥያቄዎች እነዚህ ናቸው እነዚህ ደግሞ በህገ መንግሥት ላይ ከዚህ በተሻለ ዝርዝር የተቀመጡ ነገር ግን ገዢው ፓርቲ ሊያከብራቸው ያልቻላቸው በተራ ቁጥር አራት የተጠቀሰው ደግሞ ተቃዋሚዎች ወንጀል ሠርተዋል ካለ ለራሱ ለመንግሥት መረጃ የሚያገኝበት ነበር ይህም ሆኖ በጥቅምት ከተፈፀመው ድጋሚ ጭፍጨፋ በላ የተቋቋመው ኮሚቴ የግድያውን ምክንያት እንዳያጣራ መንግሥት የወሰደውን እርምጃ ተመጣጣኝ ነው አይደለም የሚለው ብቻ እንዲያይ ተደረገ ከላይ የተዘረዘሩትን ነጥቦች መንግሥት ተቀብሎ የቅንጅት መሪዎች ፓርላማ እንዲገቡ ማድረግ ቀላል የሚባል ሥራ ነበር በተለይ ለህዝብ ክብር ሲባል የቀረቡ ከመሆናቸው አንፃር ፓርላማ አትግቡ ሲል የነበረውን የህብረተሰብ ክፍል ጥያቄ ለማስታመም ስለሆነ ፓርላማ እንዲገቡ ሳይሆን እስር ቤት ማስገባት በሚል በቂመኝነት ላይ ተመስርቶ የተነደፈን ስትራቴጂ ለመፈፀም የሚተጋ መንግሥትናፓርቲ ለካድሬዎቹ ቅንጅት ፓርላማ አልገባም አለ ብሎ ይነግራል ካድሬዎችም ይህንኑ ይደግማሉ ጉዳዩም ካለፈ በኋላ ለግል ግንዛቤ እንኳን እንዲሆናቸው በማለት ነገሩን በጥልቀት ከማየት ይልቅ ክሱን ወደማይመለከተው ቅንጅት ለማድረግ ይጥራሉ እነዚህ ታዲያ ምድባቸውን አውቀው በድፍረት ከሚያጠፉት ናቸው ማለት ይቻላል አቶ ልደቱ መድሎት በተባለው መጽሐፉ ቅንጅት ፓርላማ ቢገባ ጥሩ ነበር ብሎ እኔ እንግባ ብዬ ነበር የሚል መልዕክት ያስተላልፋል አቶ ልደቱ በ ምርጫ በተደረገ ክርክር ወቅትም ለህዝብ ይፋ በሚተላለፍ የቴሊቪዥን ፕሮግራም ፓርላማ አንግባ ብዬ እንቢ ተባልኩሲል በምላሹ ውሸት ነው አላልክም የቅንጅት ውሳኔ የተላለፈው በሙሉ ድምፅ ነው ብዬ መልስ ስሰጠው ይህ ውሸት ስለሆነ ይቆረጥ ብሎ ፃሳብ አቅርቦ አቶ በረከት በድጋሚ ለማላገጥ አድል አግኝቶ ነበር ይህ የሆነው ደግሞ አቶ ልደቱ አምስት ዓመት ምክር ቤት ለመቆየት ዕድል አግኝቶ ከአቶ በረከት ጋር በደንብ ተግባብተውም በነበረበት ጊዜ ጭምር ነው ከዚህም በተጨማሪ ጋዜጣ ላይ ፓርላማ የምገባው በቅንጅቱ ውሳኔ መሰረት ነው ብሎ መግለጫ ሲሰጥ ነበር አንጂ በግሌ የተለየ ዛሃሳብ ነበረኝ ብሎ አያውቅም ፓርላማ ለመግባት ምክንያት የሆነው ግን አቶ በረከት በመጽሐፉ ገፅ እንዳስቀመጠው ነው ፓሂጎማው ፖሦመረሙው ፅዎሥፇ ያፖፇመጋው ያሂሄ ድደዝሇ ወጋራፖውፇ ልዳጓፉ ፓርኗጎማ ዳያሜፅኃረፆና ያጎመጋያዖዎቅ መያታፖው። ፈራቢሮ ያነነፇቋናሳ ገፅ እና አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል በኪኢቲቪበሬዲዮ ታቅደው ለማሳሳት በሚቅርቡ መረጃዎች ቢሳሳት ችግር የለውም ሊባል ይችላል የተማረ የሚባለው ክፍል ግን እንደፈለገ የተሳሳተ መደምደሚያ መሥራቱ ግን አግባብ አይመስለኝም የተማረ የሚለው መጠሪያ የተጨመረሰለት የተነገረን ለመስማት ብቻ ሳይሆን ያሉትን መረጃዎች መርምሮ ለማየት የሚችል ነው በሚል ይመስለኛል የታሪክ ተመራማሪዎች በተለይ ቅንጅት ለአቅመ ፓርቲ ሳይበቃ ሳይቀናጅ መፍረስ ዋና ዋና ምክንያቶች በተለይም ደግሞ በቅንጅት ጊዜ የተወሰዱትን የሠላማዊ ትግል አካፄዶች ጠንካራና ደካማ ጎኖቹን በዝርዝር እንዲፈትሹት እጠይቃለሁ ይህ ሲሆን ከኢህአዴግም ሆነ ከቅንጅት ግንኙነት የሌላቸው ቢሆኑ ግንኙነት የለንም በሚል ሳይሆን የምር የሌላቸው ቢሆኑ ይመረጣል ለታሪካችን አጅግ ጠቃሚ ይሆናል የሚል እምነት አለኝ በግሌ ቅንጅት በወቅቱ በነበረው ነባራዊ ሁኔታ ኃላፊነት የሚሰማው ውሣኔ እንደወሰነ አምናለሁ ምንም ስህተት አልሰራም ልል ግን አልችልም አንድ አንድ ጉዳዮች ከኩነት በኋላ ሲታዩ እንዲህ ቢሆን ማለት ቀላል ሊሆን ይቻላል ለምሣሌ ቅንጅት ያስቀመጣቸውን ስምንት ነጥቦች ፓርላማ ገብተው ቢያነሷቸው ሊባል ይችላል ይህንን ግን ማነፃፀር የሚኖርብን በዚያን ጊዜ ከነበረው የህብረተሰቡ ድምፃችን ይከበር ከሚለው ስሜት ጋር መሆን ይኖርበታል አዲስ አበባን በተመለከተ ፓርላማ አልገባም አሉ ካሉ በላ በመጨረሻም ከንቲባ ሆኖ የተመረጠውን ዶክተር ብርፃዛኑን ካሰሩ በኋላ አንደ አሸንጉሊት የሚያሽከረክሯቸውን ሠዎች በተለይ እነ አየለ ጫሚሶን ይዞ አዲስ አበባን ለማስረከብና የአዲስ አበባን ህዝብ ሊቀጡት ወስነው ነበር በዚህ ጊዜ ከእስር ቤት ውጭ የሚገኙ የቅንጅት አባላት ይህ ሴራ እንዳይሳካ አድርገዋል እኔንም ጨምሮ ይህ ትክክለኛ ውሳኔ ነበር ስለ አዲስ አበባ መረከብ ዶክተር ብርፃኑ የነፃነት ጎህ ሲቀድ በሚለው ከቃሊቲ በፃፈው መጽሐፉ በደንብ አስቀምጦታል ይሀንን አንብቦ የቅንጅት ውሳኔ ምን አንደነበር መረዳት የባለቤቱ ይመስለኛል ለማጠቃለል ቅንጅት ፓርላማ አልገባም አዲስ አበባንም አልረከበም የሚል አቋም አልወሰደም ስለዚህ የቅንጅት አመራሮች አስር ቤት ከመግባት ፓርላማ ይሻላቸው ነበር የሚለው ምርጫ በኢህአዴግ የተወሰነ አንጂ በቅንጅት የተወሰነ ያለመሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ይህንን ውሳኔ በአቶ በረከት ሰምዖን የሁለት ምርጫዎች ወግ አንዲህ ተብሎ ተቀምጧል ያሬዴራል ፖፓርዓማ ውሰዕም ለሰሳያቻያ ድረሰ ለዳሰ ታፉረዕጎቻታሥ ዳጂ ለሐፍ ኑፖጎቻይሥ ሪነዳፅ ለፀፃጎ መረያሀ ማተ ጎቃ ዳድፖወዕ ጴሕፀፈፇድም አለ ገፅ ስለዚህ አዲስ አበባን ቅንጅት አንረከብም አለ ነው መልሱ ወይስ መንግሥትኢህአዴግ አላስረክብም አለ ነው የሚቀለው። ከ ምርጫ ዕጩነት እንዴት እንደወጣሁ ቀደም ብዬ አስረድቼ ነበር በአንድነት ምስረታም በፖለቲካ የሚኖረኝ ተሳትፎ በተወሰነ ደረጃ እንዲሆን ማድረግ ተገቢ ነው ብዬ አምጌ በግል ሥራዬ ላይ ትኩረት ሰጥቼ በመሥራት ላይ ነበርኩ ይህም ማለት ከፖለቲካ ፍልስፍናዬ ጋር በሚጣጣም መልኩ መንግሥት ቀጣሪ መሆን የለበትም ማለት በቂ ስላልሆነ በኤኮኖሚ ውስጥ ቀጣሪ ሆኝ መውጣት አለብኝ ብዬ በማመን የተለያዩ ሥራዎችን አቅጁ ለመሥራት እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ነበርኩ በፓርቲ ያለኝ ተሳትፎ በአንድነት ፓርቲ ከምክር ቤት አባልነት በተጨማሪ የጥናትና ምርምር ኮሚቴ አባል ነኝ ፃላፊነቴ በዚህ መስመር የሚሰጠኝን ተግባር ከማከናወን የዘለለ አልነበረም በአጋጣሚ ብርቱካን ሚደቅሳ በመታሰሯ ምክንያት የምክር ቤት ስብሰባ በተደጋጋሚ መደረግ ይጀምራል በዚህ መነሻ የፓርቲ አመራር ሽግሽግ ተደርጎ ኢር ግዛቸው ፓርቲውን መምራት በመጀመሩ የተነሳ በተፈጠረው መቀራረብ ከስብሰባ ስንወጣ ምሳ አየበላን ብዙ ጉዳይ አንስተን እንጫወት ነበር አንዱ ጉዳይ በ ፅጩ አቀራረብ የነበረው ችግር አሁንም ምርጫ የምንገባ ከሆነ ይህ ችግር መደገም እንደሌለበት ከመድረክም ጋር የተጀመረው የዕጩክ ማቅረብ ድርድር በፍፁም ጥራትን ለድርድር እንዳያቀርብ በዚህ መስፈርት ከሆነ ለመወዳደር ችግር እንደሌለብኝ ከዚህ ውጭ ከሆነ ማለትም በኮታ ከሆነ መግባት አንደማልፈልግ አወራው ነበር የመድረክ ፅጩ የማቅረብ ድርድር ተጀምሮ ከባድ ፈተና ላይ አንደሆንን መረጃ አለኝ በአንድነት በኩል ምርጫ የምንገባ ከሆነ ብለን ለምርጫ ውድድር በማኒፌስቶ ዝግጅትና በክርክር ለሚቀርቡ ሰዎች መረጃ ማሰባሰብና ድጋፍ መስጠት ሰፋ ያለ ዝግጅት አያደረግን ነበር ባልታሰበ ሁኔታ ኢር ግዛቸው ደውሎ ምርጫ መወዳደራችን ለህዝቡ ለማሳወቅ የአዲስ አበባ ዕጩ ላይ ስምምነት ስለተደረሰ እና አንድነት አብዛኛውን የአዲስ አበባ ዕጩዎች እንዲያቀርብ ስለተወሰነ በኛ በኩል ደግሞ አንተ ስላለህበት ሙሉ አድራሻህን ስጥኝ ብሎ በስልክ ነገረኝ ምንድነው የምትለው ብዬ ስከራከር ውሳኔ ነው ይለኝና በዚሁ ሳላስብበት ድንገት ዕጩ ሆንኩና አረፍኩት ቤት ገብቼ ባለቤቴን ዳር ዳር ስላት ምንም ስሜት አልሰጣትም በተጨማሪ ሌሎች የተወሰኑ ሰዎችን አማከርኩ ጥሩ ነበር ግን ብዙም ተስፋ የለውም በሚል የ ምርጫ መጥፎ ስሜት ባለቀቀው ስሜት ዛሳባቸውን አካፈሉኝ የሰማሁትን መረጃ ይዢ ከራሴ ጋር በቅጡ አሰብኩበትና ለመወዳደር ወሰንኩ ይኹን ጉዳይ በዳር ዳርታ የነገርኳት ባለቤቴን ከአሁን በኋላ የሚመጣው በጎም ሆነ ክፉ ውጤት በቀጥታ የሚመለከታቸው እርሷን እና ልጆቻችንን ስለሆነ በሥነ ሥርዓት ማስረዳት እንዳለብኝ በማመን ውሳኔዬን ነገርኳት ከመነሻው አራስ ነብር ሆነች በጥሞና ለማስረዳት ሞከርኩ ለመቀበል ዝግጁ አልነበረችም ውሳኔዬን አስረግጩ ነገርኳት ፖለቲካ ውስጥ ስሳተፍ ቀስ በቀስ ወደ ህዝብ ለመውጣት ነው አንጂ ሁልጊዜ ጓዳ ጓዳ ብቻ የሚሠራ እንዳልሆነ ለማስረዳት ሞከርኩ አርግጥ ነው ጊዜ ሰጥተን ብዙ መወያየት ያስፈልግ እንደነበር አረዳለሁ ይህ ያልሆነው ግን በኔ በኩል ባለው ውሱንነት ብቻ ሳይሆን ከፓርቲው በኩል ውሳኔው ድንገት የመጣ እንደሆነ በማስረዳት ብትችል ከጎኔ ቆማ እንድትደግፍ ካልሆነ ግን ባለማደናቀፍ እንድትተባበረኝ ከአደራ ጭምር ቁርጠኛ አቋሜን ነገርኳት በድጋሚ ራት እየበላን ሁኔታውን በተረጋጋና ቀልድ በተላበሰ መልኩ ለማስረዳት ሞከርኩ በቀጣይ ጥሩም ሆነ መጥፎ ልጆቻችን ላይ የራሱ ጫና ስለሚያመጣ የስነ ልቦና ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ምናልባትም ቃሊቲ መመላለስ ሊኖር እንደሚችል በቀልድ አድርጌ ውሳኔዬን ለማስጨበጥ ሞከርኩ በማስከተልም ለሌሎች በተለያየ ደረጃ ለሚመለከታችው መረጃ ሰጠሁ ጊዜው በጣም አጭር ከመሆኑ አንፃር ብዙም ሳንቆይ ወደ ምርጫ ዘመቻ ገባን አሸነፍን አንዴት አሸነፍን። ብሎ መገምገም ተገቢ ነው በወረዳ ስድስት ምርጫ ክልል የተደረገው የምርጫ ዘመቻ ዝግጅት እና አተገባበር ያመጣው ውጤት ምንም ይሁን ምን ግን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሔደውን የኢህአዴግ የተደራጀ ሕገ ወጥ የምርጫ እንቅስቃሴ የሚሸፍን አይደለም ነገር ግን ሕብረተሰቡን በተወሰነ ደረጃ በእቅድ እየተመራን ተጠናክረን ከደገፍነው በማንኛውም አስቸጋሪ ሁኔታም ቢሆን ለአማራጭ ሀይል ድምፅ ሊሰጠን ዝግጁ መሆኑን የሚያሳይ ነው በምርጫ ውጤት መበላሸት የኢህዴግ ከፍተኛ ድርሻ እንደተጠበቀ ሆኖ በፅጩዎችና በተወዳዳሪ ፓርቲዎች በኩል ምንም ክፍተት አልነበረብንም ማለት ግን በቀጣይ ከስህተቶቻችን ለመማር ዝግጅት እንደሌለን ነው የሚያሳየው በዚህ ምክንያት አንዳንድ ሰዎች በ ምርጫ የተሸነፍነው ስላልሠራን ነው ወደሚል አንደምታ እንዲፄድ እንደማይፈልጉት ሁሉ በ ምርጫ የተሸነፍነውም በኢህአዴግ አፈና ብቻ ነው ማለትም ተገቢ አይሆንም በወረዳ ዕጩ ተመራጭ ሆኝ ከተመደብኩ ጊዜ ጀምሮ ምርጫው እንዴት መከናወን እንዳለበት ዕቅድ የተዘጋጀ ሲሆን ይህ ፅቅድ በአዲስ አበባ ዕጩዎች ምቤት ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ዕቅድ ሲወጣ እንደግብዓት አገልግሏል ይህ ዕቅድ በዋናነት የያዛቸው ፍሬ ነገሮች « በምርጫ ክልል ቢሮ መክፈትና ማደራጀት « የሙሉ ገዜ የምርጫ ዘመቻ ኃላፊ መመደብ » ዕቅድን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ገንዘብ ማሰባሰብ የተጠና የመረጃ ማስተላለፊያ ዘዴዎችን መንደፍና የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ አንዲኖር ማድረግ ዋና ዋናዎቹ ናቸው በዕቅዱ መሰረትም ለመተግበር ጥረት ተደርጓል ስራው በዕቅድ ከተያዘው ጊዜና በጀት በላይ የጠየቀ ቢሆንም በምርጫ ክልሉ አማካይ ሊባል በሚችል ቦታ ቢሮ የተከፈተ ሲሆን ቢሮው ጉልህ በሆነ ሁኔታ እንዲታይ ማስታወቂያ ሰሌዳ እንዲለጠፍበት ለቢሮ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ኮምፒውተር ስልክ ፕሪንተሮች ፀሐፊየእንግዳ ማረፊያ ወዘተ እንዲሟሉ ተደርጓል ይህም በመደረጉ ፈራ ተባ ይሉ የነበሩ የአንድነትመድረክ ደጋፊዎች ያለፍርሃት እንዲጎበኙት ዕዱል የሰጣቸው ሲሆን በዘመቻ ሥራው የተጠመዱ የጽቤት ሠራተኞችን ሲያዩ ድፍረትና መነሳሳት ፈጥሮላቸዋል ወረዳ አና ቡራዩ አካባቢ ነዋሪ የሆነ ብዙ ደጋፊዎቻችን የመረጃ ማዕከል አድርገው ሲጠቀሙበት የነበረ ሲሆን በቀጥታ የስልክ መስመራችን ብዙ አበረታች መልዕክቶች ይደርሱን ነበር ለምርጫ ተብሉ በምርጫ ወረዳ በተወዳዳሪ ዕጩ ቢሮ ሲከፈት ይህ የመጀመሪያው ይመስለኛል ኢህአዴግም በመንግሥት ተቋማት በቀበሌ ጽቤቶች ይሠራል እንጂ በዚህ መልኩ ተደራጅቶ ሠርቶ አያውቅም የዶክተር አሸብርን ግን እርግጠኛ አይደለሁም ይህ በምርጫ ክልል በዕጩ ተወዳዳሪ የሚመራ ጽቤት መክፈት ለወደፊቱም በበጎ ተሞክሮ ተወስዶ ሊሠራበት የሚገባ ነው ከዚህ አንፃር ዋናው ፈታኝ የሚመስለው የፋይናንስ አቅም ቢመስልም ቁርጠኝነቱ ካለ ግን ከዚህ በላይ ማድረግ ይቻላል የሚል እምነት አለኝ ከዚህ ጋር ተያይዞ የተከናወነው የምርጫ ኃላፊ መመደብ ነበር የምርጫ ዘመቻ ኃላፊ ዋና ተግባር በምርጫ ክልሉ ሊፈጠሩ የሚችሉ ማናቸውም ጉዳዮችን ዕጩውን ወክለው ማከናወን ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ የተዘጋጀውን ዕቅድ ለመተግበር የዕውቀት የፍላጎትና የሥነልቦና ዝግጅት አስፈላጊ ሁኔታ ነበር በዚህ መሰረት በአጋጣሚ ይህንን ኃላፊነት የወሰደችው በጋዜጠኝነትና በኢንፎርሜሽን ሳይንስ ባለሙያ የሆነችው እህቴ ተግባራን በብቃት ለመወጣት ችላለች ብዬ አምናለሁ ይህንን ተግባር በተለይ ከምርጫ አስፈፃሚዎች ጋር የሚደረጉ ተከታታይ ግንኙነቶችን በኃላፊነት ለመሥራት በጣም ጠቃሚ ሆኖ ነው ያገኘሁት ለምሳሌ ምርጫ አስፈፃሚዎች በተደጋጋሚ ለተለያዩ ጉዳዮች ይጠሩን ነበር ሁለት ቀን ራሴ ብፄድም የኢህአዴጉ ተወካይ አልመጣም ነበር የክፍለ ከተማ ተወካይ አየመጣች ውይይት ይደረግ ነበር እኔም ከዚያ በኋላ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ቀርቼ በተወካዬ በኩል ጉዳዬን ማስፈፀም ጀመርኩ ይህ በራሱ በተወዳዳሪ በኩል የሚፈጥረው የስነ ልቦና ጫና ከፍተኛ እንደሆነ ለመረዳት ያስችላል በዚሁ አጋጣሚ በኔ ወረዳ ተወዳዳሪ የሆኑ የአንድ ፓርቲ ዕጩ እንዴት ነው ለማሸነፍ ነው የሚወዳደሩት ወይስ ለምን ጊዜና ገንዘብ ያባክናሉ። የንዴት መሆኑ ገባን የተከለከሉ በተባሉት ሁለት ቦታዎች ላይ የነበሩንን ሁለት ፖስተሮች ህግ ለማክበር ሲባል እንዲነሱ አደረግን ይሁን እንጂ በዚያው ቦታ ላይ የመኢአድ ፖስተር እና ከፊት ለፊቱ ደግሞ ኢህአዴግን ምረጡ የሚል ካርድ አስከ ምርጫ መጨረሻው ዕለት ነበር ቀደም ሲል በፖስተር ልጠፋ የመለጠፊያ ቁሳቁስ አጠቃቀም የመለጠፊያ ቦታ አመራረጥ ወዘተ ብዙ ልምድ ስለተቀሰመ በጥራት የተለጠፈና አስከ ምርጫ ፍፃሜ በአብዛኛው ግልፅ ሆኖ የነበረ ሲሆን ሁልጊዜ በየቀበሌው ያሉ ተጠሪዎቻችን አንድ ፖስተር ሲቀደድ መረጃ ስለሚሰጡን ወዲያው መልሰን በአጥፍ እንተካ ነበር ከፖስተሮች ቀጥሉ ለቤት ለቤት ቅስቀሳ የሚረዳ የበራሪ ወረቀት በበቂ ሁኔታ እንዲዘጋጁ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን ሰላሳ ሺ ኮፒ ለሰላሳ አራት ሺ የተመዘገበ መራጭ ለማሰራት ተወስኗል ስርጭቱ ታቅዶ የነበረው ለምርጫው ሳምንት ሲቀረው በሚደረግ የቤት ለቤት ቅስቀሳ ነበር ይሁን እንጂ በደጋፊዎች ጉትጎታ ከፖስተር ልጠፋው ጋር ተቀናጅቶ በተደረገ የቤት ለቤት ቅስቀሳ ራሴም በመኪና በመዞር ጭምር ከታቀደው ጊዜ ቀድሞ ለመራጩ እንዲደርስ ተደርጓል በዚህም መራጩ በቢል ቦርድና በፖስተር ጀምሮት የነበረውን ውይይት ቤቱ ድረስ በመጣለት በቀለም በታተመ በራሪ ወረቀት ውይይቱን አንዲቀጥል ዕድል ፈጠረለት ይህም ለምርጫው የቀረው አጭር ጊዜ ከመሆኑ አንፃር ተገቢ ብቻ ሳይሆን በጣም አስፈላጊም ነበር በዕቅዱ መሰረት ለምርጫ አንድ ሳምንት ሲቀረው የታቀደው የቤት ለቤት ቅስቀሳ ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮችን የያዘ ነበር ወደ ክልል በተደረገ ጉዞ ምክንያት ሊሳካ ባይችልም በተመረጡ ቦታዎች በግል ለመተግበር ሙከራ ተደርጓል ከዚህም መረዳት የቻልነው አብዛኛው ነዋሪ መረጃ እንዳለው ብዙ ደጋፊዎቻችን ካርድ አንደሌላቸው አናቶቻቸው በቡና ጠጡ እየተዋከቡ እንደነበረ ነው ለዚህም የተጠቀምነው ወጣቶች እየተዘዋወሩ እናቶቻቸውን እንዲያስተምሩና መሰረተ ቢስ የሆኑ ፍርዛቶችን እንዲያስወግዱ ነበር አንደ አማራጭም ከፈሩ ምርጫ ጣቢያ እንዲቀይሩ እንዳይመርጡ ነበር ከማስፈራሪያዎቹ ጥቂቶችቡ መድረክን ከመረጣችሁ ብጥብጥ ይነሳል በዚህ መነሻ ልጆቻችሁ እንደ ምርጫ ይሞታሉ ልጆቻችሁ ሥራ እንዲያገኙ ያለው ብቸኛ አማራጭ ኢህአዴግ ብቻ ነው ሀገር ለመምራት የሚያስችል ፕሮግራም የላቸውም እንኳን ሀገር ሊመሩ አርስ በርስም አይስማሙም ወዘተ ዋና ዋናዎቹ ናቸው የቤት ለቤት ቅስቀሳውን ለማገዝ ቢል ቦርድ በተሰቀለባቸው አራት ቦታዎች አቅራቢያ ለሙሉ ቀን የሙዚቃና የቅስቀሳ ፕሮግራም በተያያዥነት ለማድረግ ታቅዶ ነበር ይህም የታቀደው በምርጫው ቅስቀሳ ማጠናቀቂያ ቀን የነበረ ሲሆን የአንድነት ወጣቶች በዕለቱ በነበረው ከተማ አቀፍ የመኪና ላይ ቅስቀሳ ተስበው በፕሮግራም ተቀናጅተው መሥራት ባለመቻሉ በወረዳው ባሉ ደጋፊዎች ብቻ በሁለት ቦታ ለመተግበር ተገደድን አንዱ ቦታ ላይ ደግሞ መብራት አንዳናገኝ ተደረግን በዚህም መነሻ ወደሌላ የቅስቀሳ አማራጭ ቀይረናል ማለትም የተከራየነውን የሙዚቃ መሣሪያ በመኪና ላይ በመጫን ሰፈር ለሰፈር ቅስቀሳ አድርገናል በዕለቱ በነበረው የሙዚቃ ዝግጅት የተረዳነው ህብረተሰቡ ሙያ በልብ የሚልና ተሰብስቦ ዛሳቡን ለመግለፅ ፍርዛት እንዳለበት ሲሆን በርግጠኝነት ጥሩ ሥራ አንደሠራን ቤት ለቤት አየፄድን ማረጋገጥ ችለናል ይህንን አደባባይ ለማውጣት ግን ኢህአዴግ ከበተነው የፍርፃት ስሜት በላይ መሥራት እንዳለብን ተገንዝበናል በዚህ ዕለት በአዲስ አበባ ዕጩዎች ትብብርና በመድረክ በተለይም አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የማሳተሚያ ወጪ ድጋፍ የተዘጋጀው የእጅ ምልክት ያለበት በራሪ ወረቀት ከፍተኛ ድምቀት ነበር የሰጠው ይህ በራሪ ወረቀት ስለ አካል ጉዳተኞች ኤችአይቪኤድስ የመሳሰሉ ማህበራዊ መልዕክቶች ይዞ ስለነበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ይህ ፖለቲካ አይደለም ብሎ እንዳይሰራጭ ብሎ ነበር ኢንጂነር ግዛቸው ግን ዝም በሉት አኔን ያነጋግረኝ ብሎ እንዲሰራጭ ተደረገ በራሪ ወረቀት ላይ የስፈረውን መልዕክት ይዘትና የበራሪ ወረቀቱን ዓይነት አባሪ ላይ ይመልከቱ በመጨረሻው የምርጫ ቅስቀሳ ዕለት የመኪና ላይ ቅስቀሳው በዋነኛነት ትኩረቱን የድምፅ አሰጣጥ ላይ በማድረግ ከፍተኛ ሥራ የተሠራ ሲሆን በዚያ ሰሞን የኢህአዴግ የምርጫ ቀስቃሾች ምን ቢለፉ የሰዉን የልብ ፃሳብ ማወቅ ስለተቸገሩ ኢህአዴግን መምረጥ ካልፈለጋችሁ በንቧ ትይዩ የኤክስ ምልክት አድርጉ ሲሉ ነበርና የከረሙት መራጮች ከምርጫ ምልክት ፊት ለፊት የኤክስ ምልክት ማድረግ ያለመምረጥ ምልክት አንዳይመስላቸው ስናሳስብ ዋልን እንዲሁም ሌሎች ከሸገር ኤፍኤም የተወሰዱ የመብት ጥያቄን ከስሜት በወጣ መንገድ ለማስተላልፍ የተሠሩ መልዕክቶች ሲተላለፉ ውለዋል ከላይ የተዘረዘሩ ተግባራት ሲከናወኑ የቅስቀሳ ተሳታፊዎች ለዚሁ ዓላማ የታተመውን ደረጃውን የጠበቀ ቲሸርት እንዲለብሱ ተደርጓል ይህም ለደጋፊዎቻችን እንደ መለያና ሕጋዊ የምርጫ ቅስቀሳ ላይ መሆናቸውን እንደሚያሳይ ህብረተሰቡም በህብረት ሲንቀሳቀሱ ትኩረት እንዲሰጣቸው እንደሚያደርግ በማስገንዘብ ተግባራዊ ተደርጓል በርግጥም የሚታይ ውጤት ነበረው የታዛቢ ምልመላና አመዳደብ በምርጫ ዘመቻ እንቅስቃሴ የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ በከፍተኛ ጥንቃቄና ትኩረት የተሠራ ሲሆን ብዙ ይሰራሉ ተብለው የተጠበቁ ፈተናውን የወደቁበት ያልተጠበቁ ጀግንነት ያሳዩበትና በምርጫው ለመሳተፍ መወሰኔ ተገቢ ብቻ ሳይሆን አስፈላጊም የነበረ መሆኑን የተረዳሁበት ሌላው አጋጣሚ ነበር የተገኘው ውጤት በሙሉ ታዛቢዎች ለደቂቃ ቢዘናጉ ለሌብነት የተደራጀ ሌላ አካል ባለበት ውጤቱ የተለየ ይሆን ነበር ለታዛቢነት የተቀመጠው መስፈርት ቀላል ቢመስልም ለማለፍ የቻሉት ግን ጥቂቶች ናቸው ማንበብና መፃፍ ቃለ ጉባኤን በደንብ ለማንበብና መረዳት እጅግ አስፈላጊ የመጀመሪያ መስፈርት ነበር ከታዛቢ የሚጠበቀው በብዙ ቦታዎች የተለመደ ቢሆንም ከወረዳ አኳያ ያደረግናቸው የሚፈራ መታዘብ ስለማይችል በግልፅ ያለመፍራቱን መግለጽ በዚህ ምክንያት ሊመጣበት የሚችለውን ችግር ለመጋፈጥ የተዘጋጀ የሚል ነበር « በምርጫው ዕለት በተዘዋዋሪ ታዛቢዎች ተገቢው ድጋፍ የሚደረግ ሲሆን ታዛቢዎች ግን በራሳቸው ተነሳሽነት የሞራል የበላይነት ለማሳየት ሙሉ ልብስ ከነክራቫቱ ለወንዶች ሴቶችም ኮትና ቀሚስ በምረቃ ዓይነት እንዲለብሱ ተስማምተዋል በሙሉ ታዛቢዎች በደንብ ማንበብና መፃፍ የሚችሉ ቢሆንም ፊርማ በእስክሪብቶ ብቻ ሳይሆን በጣት አሻራቸውም ጭምር አንዲሆን አቋም ተይዚል የተለያዩ ማስታወሻዎችንና ነጥቦችን መያዣ እንዲሆን በግል የተዘጋጀ አንድ ዓይነት የማስታወሻ ደብተር ተሰጥቷቸው ነው ወደ ምርጫ ጣቢያ የገቡት ይህንንም በሙሉ በተግባር ፈጽመውታል የታዛቢ መለያ ካርድ ለሁሉም ታዛቢ ወደ ምርጫ ጣቢያ ሲሄዱ እንዲሰጥ የተደረገ ሲሆን እሁድ የምርጫው ዕለት ከለሊቱ ሁሉም ታዛቢ ተገናኝቶ በከፍተኛ ሞራል መልካም ዕድል ተባብሎ ነው የተለያየው « በመጨረሻም መነሻ ቦታው በጣም ቅርብ ከሆኑት ጥቂት ምርጫ ጣቢያዎች በቀር ሁሉም ታዛቢዎች ወደሚሰማሩበት ጣቢያ በተመደቡላቸው መኪኖች አማካኝነት ተወስደው ሁሉም በሠላም ወደ ጣቢያው መቀላቀላቸውን አረጋግጠናል የድምፅ ቆጠራው እስከ ምሽቱ ይጠናቀቃል በሚል ግምት ተሰባስበን የአራት ፕሮግራም የማድረግ ዕቅድ የነበረን ቢሆንም በየጣቢያው በነበረው የቆጠራ ልዩነቶች ምክንያት ታዛቢዎች አየተንጠባጠቡ በመምጣታቸው በተለያየንበት ሁኔታ ለመሰባሰብ አልቻልንም ቶሎ የጨረሱ መጥተው እራት እየበሉ የምርጫ ውጤት አስረክበው ወደማረፊያቸው ተመልሰዋል አንዳንዶች ከ ሰዓት በኋላ ቀጠራ አልቆ ቢወጡም በማግስቱ ሰኛ የሰኔ ፆም ይገባ ስለነበር አራት ሳይበሉ ፆም ይዘዋል ተዘዋዋሪ ታዛቢዎችና አብረዋቸው የዋሉ ሾፌሮች ሙሉውን ሌሊት ታዛቢዎችን ቆጠራ ሲጨርሱ ከያሉበት ሲሰበስቡ መኪና ላይ አድረዋል በዚህ ወረዳ የመጨረሻው ታዛቢ ከምርጫ ጣቢያ የወጣው ሰኞ ጠዋት ላይ ከ ሰዓታት ቆይታ በኋላ ነው በወረዳ ስድስት ለተመዘገው ውጤት ታዛቢዎች ከማንም በላይ ጀግኖች ነበሩ በዚሁ ምስጋናዬ በድጋሚ ይድረሳችሁ አላለሁ የምርጫ ጣቢያዎችን በአብዛኛው ቀደም ብለን የለየን ቢሆንም አደረጃጀታቸውን ለማወቅ ግን እስከ ግንቦት አልተቻለም ነበር ይሁን እንጂ ቅዳሜ ግንቦት ባደረግነው የተቀናጀ ክትትል ተጣብቀው የተሠሩ የምስጢር ድምፅ መስጫዎችን ለማለያየት ብልዛፃት የተሞላበት ጥረት አድርገናል በዚህ ሂደት ድምፅ መስጫው እንዲጣበቅ ከሚፈልጉት ተወዳዳሪዎች ጋር ፊት ለፊት ፍጥጫ ተፈጥሯል ያቀርቡ የነበረው ምክንያት ግን ወሳኝ የድምፅ አሰጣጥ ሄደት ላይ ሳይሆን ለአንድ ቀን ምን ችግር አለው የሚል ነበር በሌላ በኩል ተጣብቀው የተሠሩ ድምፅ መስጫዎችን በተመለከተ ያለውን ሁኔታ በሌሎች ምርጫ ጣቢያዎች ለመመልከት ስንሄድ ለምሳሌ እኔ እና ዶክተር ነጋሶ በቦሌ አካባቢ ደንበል ህንፃ ጀርባ ከሚገኝ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተን እንዲስተካከል ስንጠይቅ የምርጫ አስፈፃሚው የፈጠረው ሁካታ እና በቅድሚያ ለፕሮፓጋንዳ የተዘጋጁት የኢቲቪ ካሜራዎች የሚፈጥሩት ወከባ ኢህአዴግ በተዛባ የምርጫ አፈፃጸምና ሚዲያ ድጋፍ ለማሸነፍ መቁረጡን የሚያሳይ ነበር ይሁን እንጂ በሄደቱ ለህሊናቸው ያደሩ የምርጫ አስፈፃሚዎች መኖራቸውንና ለመስተካከል የሚችሉ ነገሮችን ለማስተካከል ዝግጁነት ያላቸውም እንዳሉ ተገንዝቤአለሁ ሁልጊዜም ያለምንም ርህራሄ መወገዝ ያለበትን የምርጫ ቦርድ ሳስብ በጣት የሚቆጠሩ ቢሆኑም ከህሊናቸው ጋር ያሉ ሰዎችን እንደምንጎዳ እየተሰማኝ ልቤ ይከፈላል በምርጫው ፅለት ቴሌቪዥን ስከታተል የተረዳሁትም በብዙ ምርጫ ጣቢያዎች የነበረው አደረጃጀት ትክክል እንዳልነበረ ነው ምዕራፍ ሃ ግንቦት ጊ እንዴት ነበር። ተብያለሁ እኔ ግን በህጉ መሰረት በቢርዬ ነበርኩኝ የምርጫው ሂደት በታዛቢ ምክንያት ችግር ላይ ሊወድቅ እንደሚችል አመላካች ነገር መታየት የጀመረው ከታዛቢ ስም ዝርዝር የማሳወቂያቀን በህግ የተቀመጠው መጠናቀቅ ጋር ተያይዞ ነበር በገጠር አንቀበልም አሉን የገቡትን አስፈራሯቸው ወዘተ የሚሉ ስሞታዎች መምጣት የጀመረው ቀደም ብሎ ሲሆን ከዚያ አንፃር ያለው ችግር በህጉ መሰረት የተቀመጠው ቀን በተለይ የምርጫ አስፈፃሚና ኢህአዴግ በቅጡ ባልተለዩበት ሁኔታ ለህገ ወጥ ሥራ ምቹ መሆኑ » የምንመድባቸው ታዛቢዎች ሁኔታው አስፈሪ መሆኑ ቢታወቅም አስፈራሩን ብለው ከመፍራት ያልተላቀቁ መሆናቸው ወዘተ ችግሩን አባብሶታል ይህም ሆኖ እሁድ ከጠዋቱ ጀምሮ ከምስራቅ ጎጃም ከፍቼ ከትግራይ የደረሱን መረጃዎች ተስፋ አስቆራጭ ነበሩ ፍቼ ወሮ አስናቀች ባልቻ በሚወዳደሩበት ምርጫ ጣቢያ ለጥንቃቄ ተብሎ ከአዲስ አበባ ከተማ ተመልምለው የፄዱ ታዛቢዎችን ጭነው የፄዱ ሁለት መኪኖች የፍሬን ቱቦ ተቆርጦ በማደሩ ታዛቢዎች በአግር ረዥም ርቀት እንዲጓዙ የተደረገ ሲሆን በእግር ሲጓዙ ንብረታቸውን ተዘርፈው ምርጫ ጣቢያ ሳይገቡ ቀርተዋል በአዲስ አበባ ኮተቤ ንፋስ ስልክ ወረዳ ታዛቢዎች የምርጫ ታዛቢነት ካርድ ከወሰዱ በኋላ ከግማሽ በላይ ታዛቢዎች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች ሳይሄዱ ቀርተዋል ምስራቅ ጎጃም ገና ምርጫው ከመጀመሩ በታዛቢነት የገቡ የነበሩ የምርጫ ጣቢያውን ጥለው መውጣታቸውን ደውለው ነገሩን ለዚህም ማስፈራሪያ ደርሷቸው እንደሆነ የስልክ መልዕክት ደርሶናል ትግራይ አቶ ስዬ አብርሃ በሚወዳደርበት ምርጫ ጣቢያ ታዛቢዎችን የጫነ መኪና ሾፌር ትፈለጋለህ ተብሎ ወደ ጣቢያ ተወስዶ ታዛቢዎች በሰዓቱ ምርጫ ጣቢያ እንዳይደርሱ ተደርጓል ወዘተ እነዚህ ድርጊቶች በምርጫው አጀማመር ላይ የሚፈጥሩት ጫና እንደተጠበቀ ሆኖ በተጓዳኝ አንድ ለአምስት የኢህአዴግ የጥርነፋ ስትራቴጂ ቀደም ተብሎ መረጃ ያለ ቢሆንም በግልፅ የመራጭን በምስጢር የመምረጥ መብትና በነፃነት ለመምረጥ የሚደረግን ሂደት በሚያደናቅፍ መልኩ ያወርዱታል ተብሎ አልተገመተም ነበር የአንድ ለአምስት አፈፃፀሙ እንዲህ ነበር ቀደም ሲል ኢህአዴግን እንመርጣለን ብለው እንዲፈርሙ የተደረጉ ሰዎች ባስፈረማቸው ሰው ታጅበው እስከ ምርጫ ጣቢያው በር ድረስ አድርሰው ውስጥ ያለው ታዛቢ ማን እንደሆነ ነግረዋቸው እንዲገቡ ይደረጋል ውስጥ ያለው ታዛቢም ማን ማን እንደተላከለት በስልክ ይነገረዋል የተላኩለትን ሰዎች ቢያውቃቸውም ባያውቃቸውም በተሰጠው ልዩ ምልክት መሰረት ብድግ ብሉ ሰላምታ ይሰጣቸዋል በገለፃ ወቅትም በተዛባ ገለፃ ምን መምረጥ አንዳለባቸው ይነገራቸዋል በአብዛኛው ተያይዘው በተሠሩ የምስጢር ድምፅ መስጫዎች እንዲገቡ ይደረጋል እዚህ ውስጥ ምንም ማድረግ ባይቻል እንኳ ቀደም ሲል የተፈጠረው እንቅስቃሴ የሚፈጥረውን የሥነ ልቦና ጫና ማስተዋል ተገቢ ነው በዚህ ላይ ፊልም ይቀረፃል አሻራ ይነሳል የሚሉ የተለያዩ ማስፈራሪያዎች ሲነዙ አንደነበር ማስታወስ ይገባል ሌላ መረሳት የሌለባቸው ሁለት ነጥቦችየኢህአዴግ የምርጫ ምልክት አንደኛ ቦታ ላይ መቀመጡና አምስት ያህል ፓርቲዎች በእጅ ምልክት እንዲወዳደሩ ፈቃድ መሰጠቱ የፈጠረው ውዥንብር ነው የአንድ ለአምስት ጥርነፋ በአዲስ አበባ ደረጃ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ የተጠናቀቀ ይመስላል በከሰዓቱ ክፍለ ጊዜ መታወቂያ የሌላቸው መራጮች በተከታታይ በመምጣት ግርግር ይፈጥሩ እንደነበር መረጃ ነበረን በኛ በኩል ካርድ ከያዙና ስማቸው በማህደሩ ላይ ካለ ይምረጡ የሚል ቀና መልስ እየሰጠን እየመረጡ መውጣት ችለዋል በመጨረሻ የተረዳነው ግን ምርጫ አስፈፃሚዎች ያልመረጡ ሰዎችን ስም ዝርዝር ውጭ ለሚገኙ የኢህአዴግ ወኪሎች በመግለፅ እነርሱ ካርድ አስይዘው የሚልኳቸው በተለያየ ጥቅም የተገዙ ሰዎች መሆናቸውን ነው ለዚህ ምሳሌ የሚሆኑ ማሳያዎች ዕድሜዋ ዓመት ያልሞላት ልጅ ኛ ክፍል ነኝ ብላ ስትከራከር የህዝብ ታዛቢ ልክ ነው ብሎ በመፍረዱ መርጣ ወጥታለች በዚህ አጋጣሚ የህዝብ ታዛቢ ተብዬዎችንም ታዘቡልኝ አንድ መራጭ የቤት ቁጥር ሲናገር የሌላ መራጭን ቁጥር ተናግሮ ግርግር ሲፈጠር በስህተት ነው ብለው ሰውየው ዝም አንዲል አስገድደው አስኪደዋል የዘገዩ መራጮች ሲመጡ በቦታቸው ላይ ተፈርሞበት ሲያገኙ በስህተት ነው በሚል በሌላ ቦታ እየፈረሙ ወጥተዋል ወዘተ በዚህ ምርጫ እንደ ተቋም ከፍተኛ የዝቅጠት ደረጃ ላይ ደርሶ የተገኘው የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ነው በሌላ ጊዜ የነበረው ተግባራቸው አንደተጠበቀ ሆኖ በምርጫው ዕለት የነበረውን ብቻ እንመልከት በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ መድረክ የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበል ዶር ነጋሶ ጊዳዳ ገለፁ ብሉሎ በተደጋጋሚ በማስወራት ከዚህ ቀን ቀደም ብሎ በደቡብ ክልል መድረክ ከምርጫው ወጥቷል ተብሎ የተወራውን የፈጠራ ወሬ ድጋፍ ሲሰጥ ዋለ በዚህ ረገድ ኃላፊነቱን የተወጣው ሸገር ኤፍኤም ብቻ ሲሆን ሌሎቹ ሜዲያዎች አቅደውና አስበው የሚሠሩት ጥፋት ስለነበር ለማረምም አልቻሉም ፈቃደኝነቱም አልነበረም በዚያው ዕለት አስከትለው ኢር ግዛቸው ሽፈራውን ምርጫው አንዴት ነው። ከሚለው ጀምሮ መግባት አለበት ለሠላማዊ ትግል በምክር ቤት ውስጥ የተቃውሞውን ወካይ ድምፅ ያሰማል እስከሚሉ ይዘልቃሉ እኔም ይህን ጽሑፍ አንብቤ እንዳልገባ የሚያደርገኝ ነገር ማግኘት ተቸግሬ ባለሁበት ሁኔታ የመድረክ አባል ድርጅቶች መነሻቸው ይህ ጽሑፍ ይሁን አይሁን ባላውቅም በተለይ ኢህአዴግ ሀገሪቱን በጉልበቱ ከተቆጣጠረ ጀምሮ ከምክር ቤት ደጅ ጠፍተው በማያውቁት በፕርፈሰር በየነ ጴጥሮስ ፊታውራሪነት ፓርላማ እንዳይገባ እገባለሁ ቢልም መድረክን አይወክልም የሚል ማስፈራሪያ ያዘለ ቅስቀሳ ተጀመረ ቀጥሎም ጉዳዩ የመድረክ አጀንዳ ሆነ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የማይመቸውን ጉዳይ ወደ ጫፍ እየገፋ ጠርዝ ላይ አቁሞ መደራደር አንዱ ስትራቴጂው እንደሆነ የተረዳሁት ዘግይቼ ነው በዚህ አጀንዳ ግን ጠርዝ ላይ አቁሞ ሊደራደር ቢሞክርም እኔ ያገኘሁት ጊዜ ብዙ ፃሳቦችን ለማሰባሰብ ጊዜ ይሰጠኝ ነበር በዚህ ጉዳይ አቋም ያልያዙ የነበሩ ሰዎችም ከኔ ጋር ስለጉዳዩ ለመወያየት ጊዜ ሰጥቷቸዋል ውጤቱም በተቃራኒው እርሱን ጠርዙ ላይ ማድረግ ነው የሆነው በወቅቱ የመድረኩ ስብሳቢ የነበረው ኢንጀነር ግዛቸው ሽፈራው ባይሆን ኖሮ ፕሮፌሰር በየነ ወይም ዶክተር መረራ ቢሆኑ ሌላ ውጤት ሊመጣ ይችላል ብሉ መገመት ብዙ ስህተት ሊሆን አይችልም አጀንዳ ሆኖ ከቀረበ በኋላ የመድረክ አባል ድርጅቶች ለሁለት ተከፈሉ ለውሳኔም እንዲረዳቸው ተወያይተው የደረሱበት መንገድ በግንባር አግኝተው ሊያነጋግሩኝ ከስምምነት ይደርሳሉ በዚሁ መሰረትም መግባት የለበትም የሚለው ቡድን በዶክተር መረራ ጉዲና ተወክሎ መግባት አለበት የሚለው በአቶ ገብሩ አስራት ተወክለው ከወቅቱ የመድረክ ሰብሳቢ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ጋር በመሆን አምስት ኪሎ ከሚገኘው ሙዚየም ውስጥ ካለ ሬስቶራንት ተገናኘን በእኔ በኩል የነበረኝ አስተያየት እንዲሁም ያቀረብኩት ጥያቄ ቀላል የሚባል ነበር በቅድሚያ አኔን በሚመለከት በተለይ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በሚዲያ የሚሰጠው አስተያየት በግል ሳያውቀኝ በመሆኑ በትዕግስት ብዙ ወዳጆቼ ከሚሰጡኝ ምክር ተነስቼ ጭምር ዝም እንዳልኩ ነገር ግን ከአሁን በኋላ ስለ አኔ መገመት እንዲያቆም ሌሉችም እንዲሁ በግል ስለማያውቁኝ ከግምት በመነሳት አስተያየት ከመስጠት እንዲቆጠቡ ምክሬን አስተላለፍኩ በሌላ በኩል ደገሞ በግሌ ፓርላማ ለመግባት ምንም የተለየ የግል ፍላጎት እንደሌለኝ ቢሆንም ግን ከስሌት ውጭ በስሜት ሳይታሰብበት በሚወሰን ውሳኔ የፖለቲካ ህይወቴን ሰዎች እንዲያበላሹት ዕድል እንደማልሰጥ ነገር ግን የዚህችን ሀገር ፖለቲካ የሚጎዳ ከሆነ ወይም ደግሞ አንድም ቢሆን ለተቃዋሚ ፖለቲካ ዕድገት ጥቅም ከተገኘበት ፓርላማ አንደማልገባ ይህንንም በተጨባጭ እንዲያስረዱኝ ጥያቄዬን አቀረብኩ ዶክተር መራራ በዝርዝር ያስረዳኝ ሲጠቃለል የአኔ ፓርላማ መግባት እኛ ምርጫው ተጭበርብሯል እያልን አንተ ፓርላማ ብትገባ ከኛ አቋም ጋር ይጣረሳል ፓርላማው ለሚያቋቁመው መንግሥት ዕውቅና እንደ መስጠት አንደሚቆጠር ከዚህ በፊትም በፓርላማ የተቃዋሚ ተወካይ ሆነው የሠሩ ግለሰቦች እንደተጠበቀው እንዳልሆኑ አዚህ ያለውን ዝርዝር በመተው ብቻህን ገብተህ ኃላፊነቱ ሊከብድህ ይችላል በሚሉ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ነበሩ እነዚህ ከላይ የተዘረዙትን ጉዳዮች በሶስተኛና አራተኛ ተራ ቁጥር ላይ ያሉትን ካልሆነ በስተቀር የመጀመሪያ ሁለቱን ከብዙ ሰዎች ጋር የተወያየሁበት ስለሆነ መልሱ ከባድ አልነበረምሪ ብዙዎቹ እንደሚያውቁት ፓርላማ አይግባ የሚለውን ፃሳብ የሚያቀነቅኑት ሰዎች በ ምርጫ ተጭበርብሯል በሚል የሰው ህይወት ጠፍቶ እያለ ፓርላማ የገቡ እና ይህን ተከትሎ ለተመሰረተው መንግሥት እውቅና የሰጡ ስለሆኑ የሞራል ጥያቄ ማንሳት በቂ ሊሆን ቢችልም እኔ ግን ይህን መንገድ ሳልመርጥ በአጠቃላይ የሚከተለውን ምላሽ ሰጠሁ ምርጫው ተጭበርብሯል ብለን የኔ መግባት ይህን ሊያፋልስ የሚችልበት ሁኔታ የለም ሌባ ቤት ገብቶ ቲቪ ሲሰርቅ ፍሪጅ ሳይሰረቅ ቤት ውስጥ ስለተገኘ ሌባ አልገባም ማለት እንደማይቻል አሄ ከታዛቢዎቼ ጋር ተናንቂ ያስመለጥኩትን ከሌሎቹ ጋር ደምሮ ማስወሰድ ተገቢ እንዳልሆነ ይህ ማለት ለሌባው ቲቪ ስለሰረቀ ፍሪጅ እንደመመረቅ ነው የሚቆጠረው ለመንግሥት ዕውቅና መስጠት ቨጠርሃህፐ የሚለውን በተመለከተ የዚህ ምርጫ ውጤት ካልተቀየረ ከሚመሰረተው መንግሥት ጋር ምንም ግንኙነት እንደማታደርጉ ካረጋገጣችሁልኝ ልቀበለው እንደምችል ዩኒቨርሲቲም እንደማያስተምሩና ደመወዝም እንደማይወስዱ ግብርም እንደማይከፍሉ ፍርድ ቤት ፖሊስ ጣቢያ ለምንም ጉዳይ አንደማይፄዱ ወዘተ በጭንቅላቴ እየተመላለሰ ቢሆንም እነዚህን ነጥቦች በዕለቱ ውይይቱ ወቅት አልተናገርኩትም ቢሆንም ግንኙነት ብዬ ሳስቀምጥላቸው እነዚህንም አንደሚጨምር አውቃለሁ ከሌሎች በግል በዚህ ጉዳይ ስንወያይ ግን አነሳው ነበር እና ነው እዚህ ጋ ያስገባሁት በዚህ ውይይትም ላይ በአነጋገር ጨዋ ለመሆን ነው ከዚህ በፊት በተቃዋሚ ተወክለው እንደተቃዋሚ ተጠሪ ማለት ነው ፓርላማ የነበሩት ሰዎች በአግባቡ ውክልናቸውን ያለመወጣቸው ጉዳይ እኔን እንደማይመለከተኝ አሳወቅኩ ለዚህ በአግባቡና በወቅቱ የአርምት ዕርምጃ መውሰድ ተገቢ እንደነበር ይህን ሳያደርጉ ቀርቶ አስታሞ አስታሞ አሁን ከጀርባ ማንሳት ተገቢነት እንደሚጎድለው አስረዳሁ በመጨረሻ የተነሳውን ነጥብ በተመለከተ ግን ተገቢና ትክክል እንደሆነ ነገርኳቸው አሁን ምክር ቤት ስገባ በድምፅ ብልጫ ለማሸነፍ እና ውሳኔ ለማስቀየር እንዳልሆነ እንደሚረዱት መቶም ሁለት መቶም ሆነን ብንገባ አብልጫ ድምፅ እስከሌለን ድረስ ይህ እንደማይሆን አብራራሁ ብዙ ወንበር ኖሮን ቢሆን ኖሮም አንድ የተቃዋሚ ተጠሪአስተባባሪ መመደብ የግድ ይል እንደነበረ ነገር ግን አሁን በተከሰተው ሁኔታ አንድ ሰው ለዝግጅትም ሆነ ዛሳቦችን በተቀነባበረ ሁኔታ ለማቅረብ ጊዜ እንደሚያስፈልገው በዚህ በኩል ክፍተት አለ በሚለው ላይ ሙሉ በሙሉ እንደምስማማ አስረዳሁ በችግሩ ላይ መስማማት ማለት ግን በመፍትሔው ላይ መስማማት እንዳልሆነ በደንብ አስረግጩ ገለፅኩ ለዚህ የቀረበው መፍትሔ ፓርላማ አለመግባት የሚለው ትክክል አንዳልሆነ አስረዳሁ በኔ በኩል ለዚህ መፍትሔ ብዬ የማስበው ሊደግፈኝ እና የመድረኩን አጀንዳ በደንብ ላራምድ እንድችል የሚረዳኝ የቴክኒክ ቡድን ማቋቋም አንደሆነ ግልፅ አደረኩኝ በአንድነት በኩል የዚህ ዓይነት ዝግጅት ያለ መሆኑን መድረክ ሰዎች በመጨመር ምናልባትም ሻዶ ካቢኔ እና ሻዶ ፓርላማ ስለሚባለው አስተሳሰብ ጭምር ዝግጀት እንዲያደርጉ አስረዳሁ በመጨረሻም ዶክተር መረራ ይህ አጀንዳ ተከራክረን የማሳመን ጉዳይ ሳይሆን የመርህ ጉዳይ ነው አለኝ በእንግሊዘኛ በ። ጽሑፉ እንዲህ በማለትም ይገልፀዋል የአመራር ብቃቱን ካላሻሻለ ኢህአዴግ መሆኑ ነው በምርጫ ተሸንፎ ለኪራይ ሰብሳቢዎች ስልጣኑን ማስረከቡ ተገቢና የማይቀር ሲሆን ይህንን ክስተት በፀረዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማስቀረት ቢሞከርም የማይቻል ይሆናል ይላል ኢህአዴግ ለመድብለ ፓርቲ ምንም ዓይነት ትንተና ይስጠው ለምሳሌ አንበሳን ስሙን አህያ ወይም ዶሮ ስላልነው አህያ ወይም ዶሮ አይሆንም በተቃዋሚ ጎራ ያለን ኢህአዴግ የሰጠውን ትርጉም ትተን ምናልባትም ገልብጠን በማንበብ የኢህአዴግ አመራሮች በዓለም ያለውን ሁኔታ በማገናዘብ የፓርቲው ዶሴ እንደሚለው ሳይሆን በዓለም እንደተረጋገጠው የተቃዋሚዎቹን አጀንዳ ጠቃሚ ነው ብለው ማመን ሲጀምሩ በኢህአዴግ ጽሑፍ ሲዘቅጡ በገቢር ግን በአስተሳሰብ ልዕልና ከአለም ጋር ሲቀላቀሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዕድል ያገኛሉ ይህ ደግሞ ሩቅ አይደለም ምልክቶች እየታዩም ጭምር ነው ብዙዎች እንደሚያስቡት የኢህአዴግ አቅጣጫ ለተቃዋሚ ብቻ በር የሚዘጋ አድርገው ነው የሚገምቱት እውነታው ግን ይህ አይደለም የኢህአዴግ ሰነድ በር መዝጋት የሚፈልገው በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ብቻ አይደለም በራሱ በኢህዴግ አባላትም ላይ ነው ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ መስመር ያለው ድርጅት በአንድ ሀገር አንድ ብቻ መሆን አለበት ማለት አይደለም የኢህአዴግ አይነት ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ሊኖር ይችላል የሊብራል ዲሞክራሲ ስር በሰደደበትና የበላይነቱን ባረጋገጠበት ሀገር በመሰረታዊ ባህርያት ሊብራል የሆኑ በርካታ ፓርቲዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ በተግባር ተረጋግጧል በተመሳሳይ መልኩ መሰረታዊ ይዞታቸው አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ሆኖ ከዚህ በመለስ ባሉ ጉዳዮች የሚለያዩ ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ ፓርቲዎች የመኖራቸው ዕድል ቢያንስ በንድፈ ፃዛሳብ ደረጃ ዝግ አይደለም ይልና በማስከተልም በአሁኑ ወቅት ግን ከኪራይ ሰብሳቢነት ጋር የሚደረገው ፍልሚያ ፈታኝ በመሆኑ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ አቅማችንን መበተን የሚመረጥና የሚደገፍ አይሆንም በሚል ያግደዋል በመርህ ልክ የሆነውን በተግባር ግን እንዳይኖር ያደርገዋል በአንድ ወቅት በአዲሰ ታይምስ መጽሔት ላይ ባወጣሁት ፅሁፍ የኢህአዴግ አባል የሆነ በተለይ ከፍተኛ አመራር የተለየ ፃሳብ አለኝ ብሎ ህገ መንግሰታዊ የመደራጀት መብቱን ተጠቅሞ ከኢህአዴግ መውጣት እንደማይችል ይልቁንም እዚህ ደረጃ ከደረስ ወይ ከሀገር መውጣት ወይም ጫት ላይ መቀመጥ ነው ያለው አማራጭ ብዬ ነበር የኢህአዴግን ኢዲሞክራሲያዊነት የተረዳ ለተቃዋሚዎቹ ብቻ ሳይሆን ለአባላቱም ያው እንደሆነ መረዳት አይቸግረውም ከዘወትር ኑሯችን እአና ከኢህአዴግ ኢዲሞክራሲያዊ ትንተና በመነሳት ለአባላቱ የዚህን ያህል የሆነ ፓርቲ ለእኛ ለኪራይ ስብሳቢዎቹ ምን የተመቸ ሁኔታ አንደምንጠብቅ ነው የማይገባው ነገር አሁን ያለው ፓርላማ አንድ ተቃዋሚ ፓርቲ የሚወክል አንድ ሰው ብቻ ያለበት ሲሆን በተለይ የክትትልና ግምገማ ሥራዎችን ከመሥራት አንፃር ህዝቡም ከገለልተኛ አካል መረጃ እንዳያገኝ ከመሆኑ በተጨማሪ ፈፃሚው አካል መንግሥትም በዚህ ደረጃ ተግቶ ለመሥራት የሚያስገድደው አካል አጥቷል ይህ የ በአፈና የተደረገ የምርጫ ውጤት ያመጣው የመድበለ ፓርቲ ስርዓት አንዳይኖር ያደረገው መሆኑ ነው ስለዚህ የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች እና አጋር ድርጅቶች የአስፈፃሚውን ግድፈት በመንቀስ ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን ለመደጋገፍ በሚል የሚደረግ የክትትልና ግምገማ ሥራ ነው በሥራ ላይ ያለው ለምሳሌ ሰባ አምስት ተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በምክር ቤት ቢኖሩና ቢያንስ አራትና አምስት አባላት በየቋሚ ኮሚቴ ቢደለደሉ እያንዳንዱ ፈፃሚ አካል ምን ያህል ተግቶ እንደሚሠራና ሪፖርቱም መረጃን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ፈፃሚው እንደሚጥር መገመት አያስቸግርም ኢህአዴግ ግን በዚህም ደረጃ የተዘጋጀ አይመስልም ከላይ እንዳስቀመጥኩት ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚፈልጋቸው በሚያደርጉት አንቅስቃሴ ምን ያህል ፀረዲሞክራሲና ምናልባትም ፀረህዝብ አንደሆኑ ለማሳየት እና መያዣና መጨበጫ የሌለውን አብዮታዊ ዲሞክራሲ ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ የሚለውን ንድፈ ፃሳብ ለመተግበር ብቻ ነው በሩሲያ ሶሻሊዝምን በሚመለከት የተነገረ አንድ ቀልድ እዚህ ጋ ትክክለኛ ቦታው ይመስለኛል አንድ ልጅ አባቱን አባባ ሶሻሊዝምን የፈለሰፈው ሳይንቲስት ነው ወይ። ቀሪዎቹም በጣም በተወሰኑ ከህዝብ ጋር በሚደረጉ ውይይቶች ማሻሻያዎች ሊደረግባቸውና የተለያዩ ወገኖች እንዲቀበሉት ማደረግ ይቻላል ስለዚህ ይህንን ህገመንግሥት ተቀብሎ ሥራ መሥራት ይቻላል ብዬ አምናለሁ በዚህ ሁኔታ በሀገር አቀፍ ደረጃ ብዙ ልዩነት አለ ብዬ አላምንም አኔም የተለየ ነገር ማቅረብ አልችልም ልዩነት አለን የምንላቸው አንድ አንዶቹን ኢህአዴግ ራሱ ቢያሻሽላቸው የሚወዳቸው ሁሉ ይመስለኛል ይሁን እንጂ ኢህአዴግ ህገመንግሥቱን እንደ ቅዱስ መጽሐፍ እንድናየው የራሱን አርቴፊሻል አጥር ሰርቷል አንዲሁም ኢዴፓ ሶስተኛ የሚለውን አማራጭ ለማሳየት በሌላኛው ጎን አንድ ሌላ ባለቤት የሌለው አጥር ሠርቶ አቅርቧል ኢዴፓ የሠራው አጥር ህገመንግሥቱ ተቀዶ መጣል አለበት የሚሉ አሉ የሚለው ሲሆን በዚህ ጉዳይ ህገመንግሥቱ ተቀዳዶ መጣል አለበት የሚል ፓርቲ በኢትዮጵያ ውስጥ የለም ወይም እኔ ስለመኖሩ አላውቅም ስለዚህ በተጨባጭ በሌለ ጉዳይ ላይ መነጋገር አስፈላጊ አይደለምሪ ኢህአዴግም ሆነ ኢዴፓ ያጠሩት አጥር ለራሳቸው እንዲመቻቸው ነው ስለዚህ የኢትዮጵያ ህገመንግሥት በዚህ ጉዳይ ብዙ ጊዜ የሚነሱት ፕሮፌሰር መስፍን ናቸው ይሄውም ህገመንግሥቱ የተፃፈበት ወረቀት ቀለም ያህል አንኳን ዋጋ አልተሰጠውም በማለት ያቀረቡትን ዛሃሳብ ይልቁን መሻሻል የሚገባው ክፍሎች እንዳሉት ሆኖ ረጅም ርቀት ሊያስኬደን አንደሚችል ጥርጥር የለኝም ስለዚህ ዝርዝሩን ከዚህ በታች በተለያየ ርዕስ አስተያየቴን ስገልፅ አንዳንዶቹን አነሳቸዋለው ህገመንግሥት መናድ የሚባል ነገር የኢህአዴግ ቅዥት ነው ማለት ነው ልክ አንደ ህገመንግሥቱ ሁሉ ኢትዮጵያ ፌዲራላዊ ስርዓት ይኑራት በሚል ነጥብ ላይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሀይሎች ልዩነት ሲደመጥ አልሰማም በፌዴራሊዝም ስርዓቱ ላይ ያለው ልዩነት በህገ መንግሥት አንቀፅ ላይ ዝቋኋታቻ ያሟዎፇሩም ሀሠ ያፉፈረ ጋያ ማጋኑኦ ዳሕና ፈቃድ ይ ዕመመሰረፇ ጎው የሚለው ላይ ነው ይህንን በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ህገመንግሥታዊ ፌዲራሊዝም በአተገባበር ግን ኢህአዴግም እራሱ ቢሆን ተግባራዊ ያላደረገው ነው ስለዚህ ጥያቄውና ክርክሩ ያለው ለኢትዮጵያ ህዝብ በሚጠቅም መልኩ ይስተካከል ነው ይህ ደግሞ ቋንቋ አንድ መስፈርት ሆኖ ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አንዲሁም ፖለቲካዊ ፋይዳ ያላቸውን መመዘኛዎች መጨመር አለበት ነው ለምሳሌ በምንም መመዘኛ የሀረሪን ልዩ የፌዴራል ክልል መሆን የሚያስረዳ መመዘኛ ያለ አይመስለኝም ህገመንግሥቱንም የሚደገፍ አይደለም ምናልባትም ኢትዮጵያ ውስጥ ምርጫ በህዝብ ይሁንታ እንደማይከናወን ጉልህ ማሳያ ሊሆን የሚችለው በሐረሪ የሚደረገው ሊከበር ይገባዋል ያሉትን ዋጋ ቢስ ነው አሉት እየተባለ ነው የሚተረጎመው ይህንን ይዞ አጥር ማጠር ተገቢ አይመስለኝም ፕሮፌስር መስፍን ደግሞ ፓርቲ አይደሉም አባል የነበሩበትም ፓርቲ እንዲህ ብሎ አቋም ይዞ አያውቅም ምርጫ ነው የህዝቡ ብዛት በተመለከተ በምርጫ ሁል ጊዜ ሀረሪ ብቻ ስልጣን የሚይዝበት የኦህዴድ ዕጩ ምክትል የሚሆንበት ተዓምር በምርጫ ነው የሚመጣው የሚል አስገራሚ ድራማ ነው ሀረሪ ከኢህአዴግ አጋርነት እራሱን ቢያገል ይህች በነፃ ያገኛትን ወንበሩን አንደሚቀማ ያውቀዋል የሀረር ነዋሪዎች የሚወክላቸው ሰው በክልላቸው ስለማይኖር ከክልሉ ውጭ የሚኖር ሀረሪ ነው የሚወክላችው ሐረርን ለሚያክል ከተማ ይህ በፌዴራሊዝም ስም የሚቀለድ ቀልድ ነው በ ዓም በተደረገው ቆጠራ የሐረር ክልል ነዋሪ ከ ሺ ብዙ የማይዘል ሲሆን የሀረሪ ብሔር ቁጥር ሺ ወይም ከመቶ ብቻ ነው አማራ ኦሮሞ ሶማሌ እና ትግራይ በተከታታይ እና ከመቶ ያለውን የህዝብ ስብጥር ሲይዙ ሌሎች ደግሞ በድምሩ ከመቶ ይሆናል በጎሳ ፖለቲካ በሚናጥበት ሀገር ሀረሪዎች በሆነ ተዓምር የክልል ፕሬዝዳንት ለመሆን የሚያስችላቸውን ድምፅ ያገኛሉ ምዕራፍ እአነ ኢትዮጵያዊ ብሔረተኝነት እና ዘውጌያዊነት በአብዛኛው የምንመለከተው ዘውጌ ብፄርተኛ የሆኑ ሰዎች ኢትዮጵያዊነትን በማንኛውም ጊዜ ካልተስማማቸው አውልቀው የሚጥሉት ዓይነት ነገር ነው የሚመስለው ኢትዮጵያዊነታቸው ሁልጊዜም ከብሔር ማንነታቸው ያንሳል ለዚህም ነው አንዳንድ ከፍተኛ የፖለቲካ ሰብዕና ላይ የደረሱ ናቸው የሚባሉ ሰዎች ጭምር በብሔር አጥር ስር ሆነው ለኔ ያልሆነች ኢትዮጵያ ብትበታተን ግድ የለኝም የሚሉት የተገኙበትን ብሔር ወርቅ ሲሉና ስለኢትዮጵያዊነት ሲጠየቁ ግን ከሸሚዝ ቁልፍ ጋር የሚያነፃፅሩትም ከዚህ መነሻ ነው በአነርሱ እይታ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር የጥቅም ምንጭ እንጂ ሌላ ምንም አይደለችም የሚል ነው ይህ ነው ጆን ኤፍ ኬኒዲ ለሀገሬ ምን ላድርግ እንጂ ምን አደረገችልኝ አትበል በሚል ካስቀመጠው መርህ ጋር የሚጋጭ ብዬ በመግቢያ ላይ እንዳሰፍረው ያስገደደኝ በኢትዮጵያ እጅግ ተጋነው ከሚቀርቡ የብሔር ጭቆናዎች በመነሳት አንዲሁም በቅርቡ በሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ተጋነው ከሚቀርቡ የብዙ ብሔርነት አንፃር እንዲህ ዓይነት ብዙህነት በሌላ ዓለም የሌለ እና ኢትዮጵያ ላይ ብቻ የተጫነ አዳ አንዳንዴ ደግሞ ለኢትዮጵያ ብቻ የተሰጠ የተለየ ፀጋ አድርጎ ማቅረብ በጣም የተለመደ እና አሳሳች ነገር እየሆነ ነው የመጣው በቅርቡ ነፃባነቷን ያገኘችው ደቡብ ሱዳን እንኳን የሚሆኑ የተለያየ ቋንቋ የሚናገሩ ጎሳዎች እንዳሏት ትናገራለች ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ በመባል የምትታወቅ ሀገር በዓለም ላይ ያለ ሁሉ የሰው ዘር ያለባት ሀገር ነች ማለት ይቻላል ነገር ግን እነዚህ ዝርያዎች ተሰብስበው የመደራጀት መብታቸውን ተጠቅመው ለኛ የማትሆን ከሆነ አሜሪካን የሚባል ነገር የለም ትፍረስ ሲሉ ተሰምቶ አይታወቅም ቢያንስ አሁን ባለው የዓለም የአድገት ሁኔታ አሜሪካዊነት የሚያስደስት የማንነት መገለጫ ነው እንጂ በፈለጉ ጊዜ ሊያፈርሱት የሚሹት ጊዚያዊ መጠለያ አይደለም ሕንድ ናይጄሪያ ወዘተ የብዙ ዓይነት ብሔሮች መኖሪያ ሀገር ናቸው ወደ ዝርዝር መግባት ሳያስፈልግ ኢትዮጵያ በብሔር ብሔረሰብ መኖሪያነት በዓለም የተለየች ሀገር አይደለችም ስለዚህ ኢትዮጵያዊነትም ጊዜያዊ መጠለያ አይደለም ካልተመቸ አፍርሰውት ወደሌላ ምሽግ የሚኬድበት ሁኔታም የለም ለኢትዮጵያ ብሔርተኝነት ቦታ መስጠት አሁን የሚጠበቅብን ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት ይመስለኛል በቅርቡ የተጀመሩ የባንዲራ ቀን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የመሳሰሉትን ብሔራዊ በዓላት ልናደርጋቸው እንችላለን ኢትዮጵያ ትቅደም ሲባል ትሣግሬነት ኦሮሞነት ዶርዜነት ጉራጌነት ወዘተ ይውደም ማለት ነው ብሎ ያስተማረን ማን እንደሆነ ባላውቅም ጥቁር ካልሆነ ነጭ ነው የሚለው አስፍቶ ማየት የተሳነው ፍልስፍና አንደሆነ እገነዘባለሁ በምድር ላይ ያሉ ቀለማት ሁሉ በነጭና ጥቁር መካከል እንዳሉ ያለመረዳት ዳፍንት ከለር ብላይንድነስ የተፀናወተን ፍጡሮች የሆንን ይመስለኛል የኢትዮጵያ ብሔረተኝነት ምንድነው። ከ ህቭቨክቪር ቢክር ዐ ከ ቓርሃ ቼዐር በበዐ ኩቧ ከ ዝ ዐ ከ በበዘዐፒሃ ከ ይከ ከ ሀ ፐከ ርህ በ ርዐቧጄዉሆርቧ ከ ርዕዐ ህይከ ምዕራፍ ንሰየመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታና ምርጫ በኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን ብዙህነታችን የሚጠይቀን አማራጭ የማቅረቢያ ስርዓት ነው በእኔ አምነት የአንድ እናት ልጆች እንኳን በአስተሳሰብ ሊለያዩ እንደሚችሉ አንድም ቀን ተጠራጥሬ አላውቅም ለዚህም ነው አንድ ቀን በህይወቴ በዘር ወይም በጎሳ በተደራጀ ፖለቲካ ውስጥ ለመሳተፍ አስቤ የማላውቀው ፖለቲካ አስተሳሰብ እንጂ በዘርና ደም ትስስር የሚተላለፍ ነገር አይደለም እንደ አጋጣሚ ሆኖ የሪፐብሊካን ልጆች ሪፐብሊካን ቢሆነ የዲሞክራት ልጆች ዲሞክራት ሊሆኑ ይችላሉ ይህ ግን በዘር ማንነት ሳይሆን በአቅራቢያቸው ያለው የፖለቲካ አመለካከት ተፅዕኖ ነው ሊሆን የሚችለው በኢትዮጵያ እንዲኖር የምፈልገው የፖለቲካ አደረጃጀት በአዋጅ አንዲሆን አይደለም በሂደት አንዲመጣ የምፈልገው በአስተሳሰብ የሚለያዩ ከአምስት የማይበልጡቢበልጡም ግድ የለም ህብረ ብሔር ፓርቲዎች ሀገር አንድትሆን ሲሆን አሁን ያሉት የብሔር ፓርቲዎች አየከሰሙ በተለየ አወቃቀር ግን ለስልጣን ከመወዳደር ደረጃ ዝቅ ብለው በተለያየ ምክንያት በመንግሥት ይሁን ወይም በማንኛውም የተደራጀ አካል በቡድኖች ላይ ብሔሮችን ጨምሮ የሚደርስን ጫና ለህዝብ እና ለገዢ ፓርቲ የሚያጋልጡ እንዲሁም ለህዝብ ተወካዮች ድምፃቸውን ማሰማት የሚችሉ ስብስቦች እንዲሆኑ ነው ከፖለቲካ ፓርቲነት ተግባር ይልቅ እንደ ሲቪል ማህበር ሚና አንዲኖራቸው ነው በተለይ ለስልጣን የሚወዳደሩ ፓርቲዎች የዚህ ዓይነት እኩይ አስተሳሰብ ማራመድ ሲጀምሩ የማጋለጥ ሥራ በመሥራት የህዝብ ድምፅ እንዳያገኙ ማድረግ የሚችሉበትን ስርዓት መዘርጋት ይኖርባቸዋል እነዚህ አሁን በብሔር የተደራጁ ፓርቲዎች ከፖለቲካ ፓርቲነት ይልቅ የሲቪል ማህበርነታቸው የበለጠ ጎልቶ መውጣት አለበት ብዬ አምናለሁ ሁልጊዜ በምርጫ ተስፋ መቁረጥ የማልፈልገው አንድ ቀን በምርጫ ስርዓት ውስጥ ከልቡ ጋር የሆነ የምርጫ ኃላፊ ይመጣና ለማንም ሳይወግን ምርጫ የሚካፄድበት ስርዓት ሊመሰረት ይችላል የሚል ተስፋ ስላለኝ ነው ይህ ደግሞ ዝም ብሉ የሚመጣ ሳይሆን በምርጫ ስርዓት ውስጥ የሚሳተፉት ዜጎች ኢትዮጵያዊያን ከመሆናቸው አንፃር እኛ የምንፈልገውን ምርጥ ምርጫ እነሱም ይፈልጉታል የሚል ፅምነት ስላለኝ ነው ይህ ደግሞ በአኔ ምርጫ ክልል የነበሩና በንዑስ ምርጫ ጣቢያ ምርጫ አስፈፃሚዎች በተግባር ሲያደርጉ ያየሁት ሀቅ ነው እስከ አሁን ይህንን ቦታ በታሪክ አጋጣሚ ያገኙ ሰዎች ይህንን ታሪክ ሊሠሩ አልቻሉም አሁንም ያሉት ይሠሩታል ብሎ ማመን ቢከብድም ተስፋ መቁረጥ ግን አስፈላጊ አይደለም ስለምርጫ ካነሳን በኢትዮጵያ ህገመንግሥት መሻሻል ከሚገባው ፍሬ ነገር አንዱ መሪን የመምረጥ ጉዳይ ነው ህገመንግሥቱ ውስጥ መስፈር ካለበት ቅም ነገር አንዱ ዜጎች በቀጥታ የሚመራቸውን ቡድን ፓርቲ ብቻ ሳይሆን መሪያቸውንም መምረጥ አለባቸው የሚል አቋም አለኝ አሁን በኢትዮጵያ ያለው የፓርላሜንታዊ ስርዓት ከሞላ ጎደል ለህዝብ ውክልና ለማረጋገጥ ጠቃሚ ነው የሚል ዕምነት አለኝ ይህንን ውክልና የበለጠ ጠንካራ ለማድረግ ግን ኢትዮጵያ መከተል የሚገባት አንድ ተጨማሪ ነገር መኖር አለበት ብዬ አምናለሁ ይሄውም ቀጥተኛ ለህዝብ ድምፅ ተገዥ የሆነ በህዝብ በቀጥታ የሚመረጥ ጠቅላይ ሚኒስትር ወይም ፕሬዝዳንት ያስፈልጋታል በኢትዮጵያ ባለው የብዙህነት ሁኔታ በጣም አስፈላጊ የሆነ ጉዳይም ነው ብዙ ሰዎች ይህንን አሠራር አነስተኛ ቁጥር ላላቸው ህዝቦች ስጋት አድርገው ነው የሚያዩት እርግጠኛ መሆን ባይቻልም አሁን በሥራ ላይ ያለውን ስርዓት የመራው ህወሓት ስልጣን ለመያዝ ያለው አማራጭ የዚህ ዓይነቱ ድርጅታዊ አሰራር መሆኑን ስላመነበት አና በዚያን ጊዜ የነበረውን የኦነግን ከፍተኛ ተቀባይነት በመስጋት አንደሆነ እገምታለሁ ይህንን የጎሳየብሔር አስተሳሰብ የሚመራው ህወፃት ግን ይህንን ማድረጉ ብዙም ላይገርም ይችላል ይህ ችግር ጉልህ ሆኖ የወጣው ግን በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሞት ምክንያት የተፈጠረው ቀጣይ ማን ይሁን። ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛ ለምሳሌ አንድ ከደራሼ እራሱን ለዚህ ቦታ እጩ ያደረገ ግለሰብ ከደራሼ ውጭ ያሉትን ብሔሮች የሚያንቋሸሸ ድርጊት ቢፈፅም ለቦታው የሚያስፈልገውን ድምጽ ያገኛል ብሎ ማሰብ ቅዝት ነው የኢህአዴግ መሪ የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ በተለያየ ጊዜ ባደረጓቸው ንግግሮች የኢትዮጵያ ህዝብን አስከፍተው ነበር ለምሳሌ ባንዲራ ጨርቅ ነው የአክሱም ሀውልት ለወላይታ ምነ ነው ወዘተ በዚህ ወቅት አቶ መለስ የኢትዮጵያ ህዝብ በቀጥታ ድምፅ የሚመርጥ ቢሆን ኖሮ ይህን የጠቅላይ ሚኒስትርነት ወንበር በፍፁም አያገኙትም ነበር ነገር ግን በድርጅታዊ አሠራር የሚደረግ ሹመት ስለሆነ ከኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎት ውጭ አርሳቸውም ለይስሙላ እንኳን ይቅርታ ሳይጠይቁ ይህንን ከፍተኛ ስልጣን እስከ ፅለት ሞታቸው ይዘውት ነበር አሁን አሁን ደግሞ አንዳንድ ሰዎች የፕሬዝዳንታዊ ወይም ከፊል ፓርላሜንታዊ ስርዓት ለፌዴራል ስርዓቱ አደጋ ይሆናል ማለት ጀምረዋል ይህ በምንም መልኩ በመረጃ የተደገፈ ካለመሆኑም በላይ አዲስ የመጡትን የነብራዚልን ተሞክሮ ያለማወቅ ነው ብራዚሎች አንደ እኛው ፓርላሜንተሪ ስርዓት መረጡ ነገር ግን መሪያቻውን በቀጥታ መምረጥ ተገቢ መስሎ ሲታያቸው ህገመንግሥታቸው ላይ ጥቂት ማሻሻያዎችን በማድረግ የብራዚል የሆነ ቅይጥ ስርዓት ዘረጉ ይህ ተሞክሮ ጠቃሚ ነው ብዬ አምናለሁ የአሜሪካ ስቴቶች ፕሬዝዳንት በጋራ ስለመረጡ የፌደራል ስርዓቱ የሚፈርስበት ምክንያት ተነግሮ አያውቅም እንዲያውም የፌዴራል አካል የሚሆኑት ክልሎችም መሪዎቻቸውን በቀጥታ የሚመርጡበት ስርዓት ጥቅም እንጂ ጉዳት የለውም የሚመራቸውን በቀጥታ መምረጥ አይጠሉም ይህ ካልሆነ ግን በብሔር የተደራጁ ድርጅቶች በጉልበት ወይም ደግሞ ውስጥ ለውስጥ በሚያደርጉት ስምምነት ኢትዮጵያ በዙር መመራት ሊኖርባት የግድ ይላል ያለበለዚያ ደግሞ በተደጋጋሚ የተመረጠ ቡድን ሀገሪቱን ተቆጣጠረው በሚል ሽኩቻው ይቀጥላል ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርኩት ይህ ቦታ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ክፍት ሆኖ በብቃት እና በኢትዮጵያ ህዝብ ይሁንታ መሆን ካልተቻለ ሌላኛው አማራጭ ሁሉም ብሔሮች አንድ አንድ ጊዜ አስኪደርሳቸው በአንድ ዙር አንድ ዙር በአምስት ዓመት ሆኖ ብቻ ይጠናቀቅ ከተባለ አንድ ጊዜ የመራ ብሔር ይህ ዙር የሚደርስው ከ ዓመት በኋላ መሆኑ ነው በሁለት ዙር ከሆነ ደግሞ ዓመት ሊያስፈልገው ነው አሁን ባለው የኢህአዴግ አሠራር አራቱ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በተራ ይያዙት ቢባል እና አሁን በቅርቡ ኢህአዴግ ለድርጅት መሪነት ያስቀመጠውን የሁለት ተርምዙር መሪነት ህግ ወደ መንግሥት ስልጣንም ካመጣው በቅረቡ በሞት ስልጣናቸውን ካጡት ጠቅላይ ሚኒሰትር በላ የትግራይ ብሔር ወደ ስልጣን ለመምጣት ዓመት ያስፈልገዋል የአቶ ኃይለማርያም ውክልና ከወላይታ ሌሎችንም የደቡብ ብሔሮች ያስደስታል ብሎ ማሰብ ልክ አይሆንም የአቶ ኃይለማርያም ከወላይታ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ጉራጌ ሲዳማን ወይም ሌላ ደቡብ የሚገኘውን ብሔርሕዝብ በቃ ኮታ ደርሶናል ብሎ ይመቸዋል ማለት ፌዝ ነው መስፈርቱ ይህ ከሆነ ማለቴ ነው ይህ በፍፁም ኢትዮጵያ የጋራ ሀገራችን ነች ብለን በብሔር ኮታ የስልጣን ድልድል የሚታሰብ ሊሆን አይችልም በዚህ ጉዳይ ኢህአዴግ ያለው አቋም ግልፅ አይደለም ይህን አጀንዳ ግልፅ አቋም ቢይዝበት የኢህአዴግ የብሔር ፖለቲካ ሣበር ተብሎ ሊያበቃለት መሆኑ ጥርጥር የለውም መፍትሔው ይህችን ሀገር በቅንነትና በብቃት ሊያገለግሉ የሚችሉ ግለሰቦችን መመደብ ነው በኢትዮጵያ ያለው ሁፄታ ደግሞ ለዚህ በጣም የተመቸ ነው ለምሳሌ አንድ የኢትዮጵያ መሪ ለመሆን የሚፈልግ በህዝብ ቁጥር ከፍተኛ የሆነው የኦሮሞ ተወላጅ ቢወዳደር ኅዯ ለኦሮሞ ህዝብ ብቻ የተሻለ ጥቅም የሚያመጣ ዛሳብ ይዞ ቢቀርብና በሌሎች ተቀባይነት ከሌለው ኢትዮጵያን የምታክል ትልቅ ሀገር ሊመራ አይችልም አንዲሁም የአማራ ተወላጅ በቁጥር ሁለተኛ መሆን ለስልጣን ቅርብ አያደርግም ኢትዮጵያን የምታክል ትልቅ ሀገር ለመምራት ትልቅ ራፅይ እና ለሁሉም ተመጣጣኝ ዕድል የሚሰጥ ኢትዮጵያዊ ፃሳብ መሆን ይኖርበታል የመራጩን ህዝብ ከሃምሳ በላይ ማግኘት ያልቻለ ማንም ሰው ይህችን ሀገር እንዲመራ ዕድል በጓዳ በር ማግኘት የለበትም ከሃምሳ በመቶ በላይ ለማግኘት ደግሞ የሌሎችን ድጋፍ በወሳኝነት ይፈልጋል በምሳሌ ላስረዳ በሀገራችን ያሉ ሁለቱ ትልቅ ብሔሮች ኦሮሞና አማራ ናቸው በብሔር ፖለቲካ ለስልጣን እንወዳደር ካሉ መወዳደር የሚችሉት እነርሱ ብቻ ናቸው ሌላው አጃቢ ነው ሊሆን የሚችለው ይህ ሲባል ደግሞ ሁሉም አማራ አማራ ዕጩ ይመርጣል ሁሉም ኦሮሞ ኦሮሞ ዕጩ ይመርጣል በሚል ልክ ያልሆነ ታላቢ ነው በኢትዮጵያ ከፍተኛውን የመንግሥት ስልጣን ለመያዝ በጣም አስፈላጊ የሚሆነው ለመሪነት የሚሆን ሰብዕና እና ጥንካሬ እንዲሁም አያንዳንዲን ምርጫ ጣቢያ ማዕከል ያደረገ የምረጡኝ ቅስቀሳ ለማድረግ የሚያስችል ጠንካራ ፓርቲ መኖር ነው ስለዚህ ለኢትዮጵያ መሪ ለመሆን እንደ ግለሰብም እንደ ተቋምም የፖለቲካ ፓርቲ ጠንካራ መሆን ያስፈልጋል አሁን እየተደረገ አንዳለው በጓዳ ብቅ እያሉ ሀገር እንመራለን ብሎ ጉብ ማለት መቅረት ይኖርበታል ህገመንግሥቱ በሂደት እስኪሻሻል ዜጎች መሪያቸውን በቀጥታ መምረጥ ባይችሉ እንኳን ፓርቲዎች ቢመረጡ ማንን መሪ አድርገው ሊመርጡ እንደወሰኑ ለህዝብ ይፋ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ለምሳሌ በሆነ ምክንያት የአድዋ ህዝብ አቶ መለስን ላለመምረጥ ቢወስን ፓርቲው ምን አማራጭ አለው። በዚያን ጊዜ አልባንያ ብድር የሚሰጣት አጥታ አንጂ ላለመበደር ፈልጋ አይመስለኝም ሌላ ጊዜ ደግሞ በምክር ቤት ነጭ ካፒታሊዝም ነው የምንከተለው ብለው ነበር አሁን ግን ፓርቲያቸው አብዮታዊ ዲሞክራሲ የሚባል ፍልስፍና ተከታይ ሆኗል እንከተለዋለን ያሉት ነጭ ካፒታሊዝም ሂዎ ሊብራሊዝም የከሰረ ተብሎ ተጥሏል በዓለም ላይ ቀኝ ዘመም አና ግራ ዘመም የሚባሉ አስተሳሰቦች አሉ ሊብራል አስተሳሰብ ኖሯቸው ግራ ዘመም የሚባሉት በአብዛኛው ሶሻል ዲሞክራቶች እንደ አሜሪካ ደግሞ ዲሞክራቶች ያሉት ሲሆኑ ቀኝ ዘመም የሚባሉት ደግሞ ኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ የሚመሩና በአሜሪካ ደግሞ ሪፐብሊካኖቹ ናቸው አነዚህ ሊብራል በሚባል ጎራ ውስጥ የሚሳተፉ ሆነው የነፃ ኤኮኖሚ ስርዓትን እንደ መርህ ይዘው የመንግሥትን ጣልቃ ገብነት ደረጃ በመጨመርና በመቀነስ የኤኮኖሚ ፖለቲካ የሚጫወቱ ሲሆን በምንም ዓይነት ግን የግለሰብን ንብረት ማፍራት መብት አደጋ ላይ የማይጥሉ እና ዜጎች አገሌ ቢመረጥ ንብረቴን እወረሳለሁ ብለው የሚሰጉበት ሁኔታ የለም ውድድራቸው የሚያተኩረው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ደህንነት እንዴት ይረጋገጥ በሚለው የፖለቲካ አቅጣጫ ላይ ነው ግራ ዘመሞች መንግሥት ኃላፊነት አለበት ብለው የመንግሥትን ሚና ሲያጎሉት ቀኝ ዘመሞች ሥራ መፍጠርን እናበረታታ ሥራ ሠርቶ መኖር ደግሞ የሰው ልጅ ግዴታ ነው ብለው ያምናሉ ያልሰራ አይብላ መርፃቸው ነው ይህ ማለት ግን በተለያየ ምክንያት መስራት ያልቻሉትን በውስን ደረጃ ድጋፍ አይደረግላቸው የሚል አመለካከት የላቸውም በግሌ የቀኝ ዘመም ፖለቲካ አራማጅ ነኝ አሜሪካ ሀገር ብኖር የምመርጠው ሪፐብለካኑን ነው ኢትዮጵያ ባለችበት ነባራዊ ሁኔታ ግን ምን ዓይነት ነው የሚያስፈልገን ብዬ ሳስብ የራሴ ዞጨጠልከ አተያይ ይኖረኛል ለዚህም ነው አንድነት ውስጥ አባል መሆን የቻልኩት በዓለም ላይ ነፃ የሚባል የኤኮኖሚ ስርዓት የለም አንዲሁም ነፃ ኤኮኖሚ የሚባል ከመጽሐፍ ላይ በዘለለ ያለበት ሀገር በዓለም ላይ የለም ኖሮም አያውቅም ይህን አስተሳሰብ የሚያራምዱ ሰዎች የሉም ማለት ግን አይደለም እንደዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች በትምህርት ተቋማት ለምርምር እንጂ ዝብርቅርቁ በወጣ የአንድ ሀገር ህዝብ ላይ መሪ ሊያደርጋቸው የሚችል አማካይ ቦታ የለም መሪ መሆን የሚፈልጉ ግን ጠርዝ በያዙ አስተሳሰቦች ሳይሆን አማካይ በሆነ አሰተሳሰብ ነው የሚመሩት በዚህ የኤኮኖሚ ፍልስፍና መርህ ውስጥ ማስተላለፍ የፈለግሁት ኢህአዴግና አባላቱ ኒዮ ሊብራል እያሉ የሚያላዝኑት የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና ዝቅተኛነትና የሚዲያ የብቻ ቁጥጥራቸውን ተጠቅመው አላስፈላጊ የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት እንጂ እኔም ሆንኩ አባል የሆነኩበት ፓርቲዬ በዓለም ላይ በተግባር ለሌለ ፍልስፍና ቦታ የሌለን መሆኑን ነው በኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ሲባል ግብርና እና ከግብርና ጋር የተያያዘው መሬት ወሳኝ ነገሮች ናቸው ኢህአዴግ የመሬት ጉዳይን ህገመንግሥታዊ ድንጋጌ በማድረግ መሬትን ከዋነኛ የኤኮኖሚ ግብዓትነት እንዲወጣ በማድረግ ለሙስና እና ለህገ ወጥ አሠራር አንዲውል መንገድ ከፍቷል የኢትዮጵያ ግብርና ከመሰረቱ መለወጥ ይኖርበታል ብዬ አምናለሁ ኢትዮጵያዊው አርሶ አደር በቅድሚያ ፍትሐዊ የሆነ የመሬት ድልድል እንዲኖረው ማድረግ የመንግሥት የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባር መሆን አለበት በማስከተልም አርሶ አደሩ ለያዘው መሬት ባለ ሙሉ መብት መሆን ይኖርበታል በይዞታው ያለውን መሬት ከድልድሉ እንዲሁም ድልድልን ተከትሎ ከሚኖር ጥቂት የእፎይታ ጊዜ በኋላ መሬቱን በውርስና በሽያጭ የማስተላለፍ መብት ይኖረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ አነስተኛ የግብርና መሬት ይዞታ በህግ እንዲወሰን በማድረግ መሬትን አየቆራረጡ መሸጥና ማውረስ ገደብ እንዲኖረው ማድረግ አስፈላጊ ነው የሚል እምነት አለኝ በማንኛውም ሁኔታ መሬት ለውጭ ሀገር ዜጋ አሳልፎ መሸጥ በህግ መከልከል የሚገባው ሲሆን በውጭ ሀገር ዜጎች በሊዝ የሚያዙ ቦታዎች ተገቢው የመንግሥት ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግባቸው መሆን ይኖርባቸዋል ለምሳሌ በሊዝ ስም በድንበር አካባቢ የሚሰጡ ከፍተኛ ስፋት ያላቸው የእርሻ ቦታዎች ኢትዮጵያ ጅቡቲን በሊዝ ሰጥታ በኋላ ከአጂ አንደወጣች ካለመገንዘብ አና በተለይ ከዓባይ ጋር ተያይዞ ካለን ስትራቴጂክ ይዞታ አንፃር ብዙ ጥንቃቄ ሊደረግ አንደሚገባ አምነቴ ነው በጋምቤላ አካባቢ በሊዝ ለውጭ ዜጎች የሚሰጡ ቦታዎች ሁሌም ያሳስቡኛል ከግብርና ጋር ተያይዞ የመሬትን ጉዳይ ካነሳን አይቀር አጠቃላይ ስለመሬት ፖሊሲ ያለኝ እምነት ኢትዮጵያ በዜጎች የሚያዙ የግል መኖሪያ የንግድ የእርሻ ቦታ ሊኖራቸው እንደሚገባ አምናለሁ ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ በማህበረሰብ ከሚያዙ ቦታዎች ውጭ ያሉት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚገኙ ቦታዎች ሁሉ የመንግሥት ይዞታዎች ሆነው መቆየት ይኖርባቸዋል የሜል አቋም ነው ያለኝ መንግሥት በተጨማሪ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ከፍሎ የሚይዛቸው ይዞታዎችም ሊኖሩት ይችላሉ በማህበረሰብ የተያዙ ቦታዎች በምንም ዓይነት የማህበረሰብ ይዞታነታቸው ሲያበቃ የመንግሥት ይዞታ ነው መሆን የሚኖርባቸው መንግሥት መሬት በቅድሚያ ወደ ግል በሊዝ ወይም በይዞታነት የሚዛወርበትን መስመር የሚጀምር መሆን ይኖርበታል የማህበረሰብ ይዞታዎች በአካባቢው ነዋሪዎች ወደ ግል ማዛወር ካስፈለገ የመሬት ድልድል ሥራ የሚሠራው መንግሥት መሆን ይኖርበታል ኢህአዴግ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምንም ያልያዙትን አቋም በፕሮግራማቸው ያላስቀመጡትን የመንግሥት ሚዲያ ተመቸኝ ብሎ መሬት ለመሸጥና ለመቸብቸብ ይፈልጋሉ እያለ የሚነዛው ፕሮፓጋንዳ መሰረት የሌለው እንደሆነም መገንዘብ ያስፈልጋል በተግባር በህገ መንግሥቱ መሬት የህዝብና የመንግሥት ነው የሚለው ድንጋጌ እየዋለ ያለው የመንግስት ጭሰኝነትን ለማረጋገጥ ብቻ ነው ከዚህም በላይ መንግሥት ለፖለቲካ ጥቅምና ምርጫ ለማሸነፍ እንደሚጠቀምበት በገዛፃድ እየታየ ያለ ሀቅ ነው በከተማ ነዋሪ የሆኑ የገጠር የእርሻ መሬት በመንግስት ይዞታ መሆን አለበት የሚለውን ሃሳብ ለሚደግፉ ሰዎች አንድ ጥያቄ ነው ሁሌ የምጠይቃቸው የቤታቸሁን የባለቤትነት ካርታ ቀበሌ ጽቤት ቢሆን ደስ ይላችቷል ወይ። የሚል ነው የፋና ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ ይህንን ጥያቄ ጠይቄው ለህዝብ ሳያስተላልፈው ቆርጦታል ግብርና ላይ ለውጥ ይኑር ሲባል ግን የከተማ ልማትም ትኩረት የሚሻ ነው ኢትዮጵያ ግልፅ የሆነ የከተማ ልማት ስትራቴጂ ሊኖራት ይገባል ከተሜነትን ማስፋፋት ማለት ቀድሞ በከተማ ፋብሪካ ከፍቶ ለዚያ ፋብሪካ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል ከገጠሩ በማምጣት የሚደረግ መዋቅራዊ ሽግግር አድርገው የሚወስዱት ብዙ ናቸው በአሁኑ ጊዜ መሆን ያለበትም የሚገባውም ፋብሪካዎች ሊገነቡ የሚችሉት በከተሞች የሚፈጠርን ፍላጎት መሰረት አድርጎ ነው ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ፋብሪካዎች ይቋቋማሉ ስለዚህ ሰዎች በቅድሚያ እንዴት ወደ ከተማ ይምጡ የሜለው ጥያቂ መመለስ አለበት በገጠር የሚኖሩ ዜጎች ግልጽ የሆነ የመሬት ባለቤትነት ሲረጋገጥ የገጠር ነዋሪ የሆኑ የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች አባወራዎችና እማወራዎችም መሬቱ መሸከም ከሚችለው በላይ ያሉ ልጆቻቸውን ወደ ከፍተኛ ትምህርት እንዲዘልቁ በማድረግ መንግሥት ደግሞ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ሥራዎችን በተመረጡ ከተማዎች በሚገባ እንዲሟላ በማድረግ በከተማ ለመምህራንና ተማሪዎች ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በፀጥታና ደህንነት ክፍሉን በማጠናከርና ዋስትና በመስጠት ለእነዚህ የሚሆኑ አገልግሎቶችን እንዲያስፋፉ በማድረግ ከተሜነትን በአገልግሎት ማስጀመር ይቻላል በአገልግሎት የተጀመረ ከተሜነት ለዚሁ ሲሉ ለተሰበሰቡ ዜጎች ምርት ማቅረብ አስፈላጊ ሲሆን ይህንን ለማሟላት የሚፈጠረውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ፋብሪካዎችና ኢንዱሰትሪዎች ያድጋሉ ፋብሪካ ከፍቶ የገጠሩን ህዝብ ጉልበቱን ለመሸጥ ሲል ይመጣል የሚለው አስተሳሰብ ጊዜ ያለፈበት ነው ለፋብሪካ የሚሆን ብቁ የሰው ኃይልና በፋብሪካ የሚመረተውን ምርት የሚጠቀም በሌለበት ፋብሪካ ይገነባል ማለት ቀልድ ነው የሚሆነው አሁን ሀገራችን ኢትዮጵያ በከተሜነት በአፍሪካ ደረጃ እንኳን አጅግ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ነው የምትገኘው ውስን ሀብትን በተደራጀ ሁፄታ በመጠቀም ከተሜነትን ማስፋፋት ሳይቻል ቀርቶ በየቀበሌው የመሰረተ ልማት ለማዳረስ የሚደረገው ርብርብ በፍፁም የማያዛልቅ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊያን ከሌላው የዓለም ህዝብ በተለየ ሁኔታ ለዝንት ዓለም በገጠር አንዲኖሩ በመንግሥት ፖሊስ ምክንያት ሊፈረድባቸው አይገባም ይህ አሁን ባለው ሁኔታ በሀገራችን ያሉት ትላልቅ ክልሎች ኦሮሚያ አማራ እና የደቡብ ኃላፊነት ነው ኦሮሚያ ያለ ዋና ከተማ አንዴ አዲስ አበባ ሌላ ጊዜ አዳማ እየተባለ አማራ በባሕር ዳር ደቡብ በአዋሳ ተወስነው ሊቀሩ አይችሉም አይገባምም ይህ አሁን ያለውን የፌዴራሊዝም አወቃቀር ለማሻሻልተጨማሪ ምክንያት ሆኖ ሊያገለግል ይችላል ከቋንቋ ውጭ ሌሎች ፌዴራል አወቃቀሮች ከግምት መግባት ይኖርባቸዋል የሚለውን አስተሳሰብ ማለት ነው በማህበራዊ ዘርፍ አጅግ በጣም ብዙ ድፃዛ ቤተሰብ ልጆቹን ማስተማር ባልተቻለበት ሁኔታ የማይከፍል ትምህርት አይማር ማለት ወደፊት ከፍሎ የሚማር ዜጋ ለማፍራት ራዕይ ማጣት ስለሆነ ወላጆች ማስተማር ግዴታቸው ቢሆንም መንግሥት በቀጣይ ከፍለው ማስተማር የሚችሉ ዜጎች ኃላፊነቱን አስኪወስዱ ድረስ ቀስ በቀስ አየቀነሰ የሚሄድ የትምህርት ድጋፍ መኖር አለበት ብዬ አምናለሁ ከዚህም አልፎ ለትምህርት ጥራት አስፈላጊውን ትኩረት መስጠት አንዲሁም ህፃናት የመማር መብት ያላቸው መሆኑ ከግንዛቤ አንዲገባና የሲቪል ተቋማት ይህን ጥራትና ተደራሽነቱን በመከታተል ከፍተኛ ሚና አላቸው ብዬ አምናለሁ ጤናን በተመለከተም ተመሳሳይ አቋም ነው ያለኝ መንግሥት በተለየ ድጎማ የሚያደርግላቸው የጤና ዘርፎች መኖራቸውን አደግፋለሁ ነገር ግን ዜጎች ለጤናቸው ተገቢውን ክትትል ማድረግና ጤናቸውን መጠበቅ ይኖርባቸዋል የመንግስት ሚና ዜጎች በግል ቁጥጥር ሊያደርጉ የማይችሉባቸውን ወረርሽኝ መከላከልና ከፍተኛ ደረጃ ያላቸው የጤና ምርምሮችን እና ስርፀትን መደገፍ መሆን ይኖርበታል የማህበረሰብ የጤና ኢንሹራንስ እንዲስፋፋ በመደገፍ እና በማበረታት የጤና ሽፋን በጥራት ለሁሉም እንዲዳረስ የሚያደርግ ዘላቂ ወጭ ቆጣቢ ስርዓት መገንባት አንደሚቻል አምናለሁ በአሁኑ ጊዜ እየተተገበረ ያለው የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኛ በሚል በአብዛኛው በውጭ መንግሥት እርዳታ ላይ ጥገኛ የሆነ የጤና ፖሊሲ ዘላቂነቱ አስተማማኝ አይደለም ምዕራፍ አነ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ከዓለም የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የተለየ ሌላ ፍልስፍና የሚጠይቅ አይደለም ሀገሮች ቅድሚያ ሰጥተው የሚመለከቱት የውጭ አጋሮቻቸውን መረጣ ላይ መሰረት በማድረግ ነው በዓለም ፖለቲካ ገዥው አሳብ ዘላቂ ጥቅም እንጂ ዘላቂ ወዳጅ የሚባል የለም የሚለው ቢሆንም አቅጣጫና ቦታ ቀይሮ መለወጥ በማይቻለው ከጎረቤት ሀገሮች ጋር ያለ ግንኙነት ይህ ፍልሰፍና አይሠራም ጎረቤትን መምረጥ አይቻልም ስለዚህ በዋነኝነት ለሰላምና ዕድገታችን ተባብረን መሥራት የግድ ይለናል ኢትዮጵያ የትኩረት አቅጣጫዋን ማድረግ ያለባት በጎረቤት ሀገራት ላይ ነው የሚል ጠንካራ ዕምነት አለኝ ከኤርትራ ጋር ያለንን ግንኙነት ብዙ ሰዎች ሊታረም የማይችል አድርገው ይወስዱታል መሆን የሌለበት ነገር ግን በታሪክ አጋጣሚ በተፈጠረ መለያየትና አርሱንም ተከትሎ በገባንበት እርባና ቢስ ጦርነት ብዙ ዋጋ ተከፍሉበታል አሁንም ቢሆን ግን በዘላቂነት ሁለቱ ሀገሮች በጠላትነት ለመተያየት አንድም በቂ ምክንያት የሌለ ሲሆን አብሮ ለመሆን ግን ከብዙ በላይ ምክንያቶች በአፍንጫችን ስር ናቸው ይህንን ለማድረግ እርስ በርስ መቀራረብና የጋራ ማንነታችን ላይ ከፕሮፓጋንዳ የዘለለ የመልካም ጉርብትና ሳይሆን የአብሮነት ፕሮጀክት ሊኖረን ይንገባል ከዚህ በፊት የነበሩትን ነገሮች በሆነ ባልሆነ ቁርሾ እያነሱ ለመነቋቆር ካልሆነ በስተቀር ያሳላፍናቸውን ክፉ ቀኖች ለትምህርት አንዳዋልነው አድርገን አቅልለን ልናየው ይገባልአንዳንድ ሰዎች ይህንን ፕሮጀክት የባህር በር ለማግኘት የሚደረግ የብልጣብልጥ መንገድ አድርገው ሊገምቱት ይችላሉ ጉዳዩ ግን ከባህር በር አከራይ ተከራይነት ዘሎ በሁለቱ ሀገራት የሚገኙትን ህዝቦች በነፃ የመዘዋወርና የመሥራት መብትን በከፍተኛ ደረጃ ማረጋገጥን ያለመ ነው ከኤርትራዊያን ጋር በዓለም ላይ በጋራ የምንጠቀማቸው ፊደሎች ያሉን ብቸኛ ሀገሮች ነን ኤርትራዊና ኢትዮጵያዊ ብለን አራሳችንን ካልለየን በስተቀር ማንም ሌላ ሶስተኛ ወገን በዚህ አንፃር ሊለየን አይችልም ይህ መመሳሰል ከሱማሌዎችም ጋር ያለ ቢሆንም በጎላ መልኩ ግን የሚታየው ከኤርትራዊያን ጋር ነው ጅቡቲ ያለ ኢትዮጵያ ሀገር ነች ለማለት አስቸጋሪ ነው ኢትዮጵያ በሆነ ምክንያት እነዚህን ወደቦች መጠቀም ብታቆም ምን እንደሚውጣቸው አይታወቅም እንደዚህም ሆኖ ግን ጅቡቲያውያን በኢትዮጵያ ለልማት አጋዥ እንዲሆኑ በርትቶ መሥራት ያስፈልጋል የኢትዮጵያና ጅቡቲ ፖለቲካ ዋና ሞተር መሆን ያለበት ከፈረንሳይ ጋር የሚኖረን ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ማጠንጠኛ መሆን ይኖርበታል ኢትዮጵያ አሁን እያቀረበችው ያለውን መሰረታዊ አቅርቦት በማሻሻል የጅቡቲ ዜጎች በኢትዮጵያ የትምህርት ዕድል የሚያገኙበትን እና ድሬዳዋን እና አካባቢዋን ተመራጭ ሀገራቸው እንዲያደርጉት መሥራት ይጠበቅብናል ኢትዮጵያዊያንም በጅቡቲ ረረ የኤኮኖሚ ትስስር ፈጣሪ እንዲሆኑ መንግሥት ቀጥተኛ ድጋፍ ማድረግ ይኖርበታል ሱማሊያ ኾንትላንድም ሆነ ሞቃዲሾ ያሉት በተለይ ደቡብ ሱማሊያ ከኬኒያ ጋርም ተመሳሳይ ሽርክና ቢፈጥሩ የሚያዋጣቸው ይመስላል ነገር ግን ከኢትዮጵያ ጋር ለሚኖራቸው ግንኙነት ብዙ ተሞክሮ ያላቸው ናቸው ሆኖም ግን ኢትዮጵያ ከእነዚህ ሶስት የሰሜን እና ምስራቅ አዋሳኝ ሀገሮች ጋር የምታደርገው ግንኙነት በኬኒያና በሱዳኖች በኩል በዝምታ የሚታይ ላይሆን ይችላል ነገር ግን እነዚህ ሀገሮች ተጠናክረው መውጣታቸው ለህዝቦቻቸው ያለውን ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት ለህዝቦቻቸው ጥቅም ሲሉ የሚወስዱት ቁርጠኛ አቋም መሆን ይኖርበታል የዚህ ማህበረሰብ ውህደት ደግሞ ለኢጋድ አባላት መጠናከር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ስለሆነ በአንድ ዓለማ የጋራ ጥቅም አንዲሁም መከላከያ ስር በመሆን ከአላስፈላጊ የአርስ በርስ ትንኮሳና ንትርክ ርቆ በጋራ አላማ ላይ የተመሰረተ የኤኮኖሚ ብሉም የፖለቲካ ማህበረሰብ ግንባታ ላይ መትጋት ይኖርብናል እነዚህ የምስራቅ አፍሪካ በተለይም የአፍሪካ ቀንድ ሀገሮች የሚፈጥሩት ሰላምና ከጦርነት ነባ የሆነ ቀጠና በራሱ ለልማታቸው ከፍተኛ ድጋፍ ይሆናል ለጦርነት ዝግጅት የሚያወጡት ወጪ ብቻ የህዝቦቻቸውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ሊያውሉት ይችላሉ ይህ ግን ቀላል እና በአጭር ጊዜ ሊደረስበት የሚችል ነው የሚል ዕምነት የለኝም ለዚህም ነው የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥተን ከላይ ጀምረን በኤኮኖሚ መተሳሰር እና ለጋራ ፕሮጀክት መትጋት አለብን የምለው ለዚህ ፕሮጀክት ዝግጅት በቅድሚያ የኢትዮኤርትራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ግንባር መመስረት ይኖርበታል ሁለቱም ሀገራት አንዱ የአንዱን ተቃዋሚ መደገፍ ማቆም ይኖርባቸዋል የዜጎች ነፃ ዝውውር መፈቀድ ይኖርበታል በአኔ ዕይታ ኢትዮጵያ ለሁሉም ጎረቤት ሀገሮች ቅድሚያ መስጠት ይኖርባታል በተለይ ኤርትራ ጀቡቲ እና ሱማሊያ የመሰሉት የሰሜንና ምስራቅ አጎራባች ሀገሮችን በጋራ በመሆን ልናሸንፋቸው የምንችላቸው ብዙ ጉዳዮች አሉን እነዚህን ጉዳዮች ለማጠናቀቅ ግን ኢትዮጵያ በግንባር ቀደምነት ከታሪካዊ ጠላትነት ፍልስፍና ወጥታ ለታሪካዊ አጋርነት መመሥረት መሥራት ይኖርባታል እነዚህ የሰሜንን እና ምስራቅ አጎራባች ሀገሮች ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ በመሥራት አንድ ሰጥተው ሁለት የሚያገኙበት መሆኑን ማስጨበጥ ሲሆን ለኢትዮጵያዊያን ደግሞ አነርሱ ሁለት ያገኙት ከኛ ተቀንሶ ሳይሆን አብረን በመሆናችን ከተገኘ ትርፍ መሆኑን አብረን ካልሆንን እኛም አንድ እነርሱም ሁለት አያገኙም የሚለውን ማስጨበጥ ይኖርብናል ረረ ምዕራፍ አህ አደናጋሪ የኢህአዴግ የፖለቲካ ቃላቶች ኢህአዴግ ህዝቡንም አባላቱንም የሚያደናግርበት የተለያዩ ቃላቶች ይዞ በየጊዜው ብቅ አንደሚል ይታወቃል በዚህ ምዕራፍ ለማየት የመረጥኳቸው ሁለት ሲሆኑ አነርሱም የዜሮ ድምር አስተሳሰብ እና ኪራይ ሰብሳቢነት የሚሉትን ነው እነዚህን የመረጥኳቸው አብዛኛውን ጊዜ ተቃዋሚዎችን ለመስደብም ስለሚጠቀሙባቸው ጭምር ነው ኢህአዴግ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የዜሮ ድምር አስተሳሰብ አራማጆች ናቸው ብሎ ይከሳል እንጂ በግልፅ በሚታይ ተግባሩና በንድፈ ዛሃሳብ ደረጃ ባስቀመጠው ጽሑፍ እያስረዳን ያለው በስልጣን ላይ ካልሆነ በስተቀር ኢህአዴግ የሚባል ፓርቲ እና አብዮታዊ ዲሞክራሲ የሚባል አስተሳሰብ እንደማይኖር እያረጋገጠልን ነው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስልጣን ላይ ባይኖሩም እንደ ተቃዋሚ መኖርና ሃሳብን ለህዝብ ማቅረብ አንደሚቻል ስልጣን መያዝና አለመያዝ ተለዋዋጭ እንደሆነ ከመርህ ባለፈ በተግባር እያሳዩት ያለ ነገር ነው ኢህአደግ ግን የሚለው ኪራይ ሰብሳቢዎች ካሽነፉ አብዮታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰብ ዘቀጠ ብሎ ነው የሚወስድው ስለዚህ ይህንን ግብ ለማሳካት ትግሉ የሞት ሽረት ነው ብሎ ነው የሚያስቀምጠው የዜሮ ድምር አስተሳሰብ የሚባለው በዋነኝነት የሚገለፀው አንድ ሰው ወይም ቡድን አንድ ነገር ማግኘት ካለበት ሌላኛው ሰው ወይም ቡድን በተመሳሳይ ማጣት ይኖርበታል አንደኛው ቡድን ያገኘው እና አንደኛው ቡድን ያጣው ሲደመር ውጤቱ ዜሮ ነው የሚሆነው ይህ በኤኮኖሚክስ ሚዛኑን የጠበቀ ፎሀዘህጠ ቪህከበ የሚባለው ዓይነት ነው የዜሮ ድምር አስተሳሰብ ማለት በሀገራችን ፈጣሪ ከየት ያመጣል ከአንዱ ወስዶ ላንዱ ይሰጣል በሚል የሚገለፀውን የሚወክል ነው ይህ አስተሳሰብ በመሰረቱ በስህተት የተሞላ ነው ለዚህ ነው ሰዎች ካልሰረቁና ካላጭበረበሩ የሚከብሩ የማይመስላቸው አሴት መጨመር የሚባለውን የትልቁን ኬክ ታሪክ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን ፈጣሪ ሳይቀማ የሚሰጥ መሆኑንም የዘነጉ ናቸው በእምነትም በመደበኛ አስተምህሮም ስህተት ነው ኢህአዴግ ከዚህ አንፃር ግልፅ የሆነ አስተሳሰብ አለው ብሎ ማሰብ ይቸግራል ካድሬዎቹም ሆኑ የበላይ አመራሮቹ ልክ እንደሌሎች ቃላቸውን እንደፈለጉ ባሻቸው ጊዜ የሚደነቅሩት ነገር ነው የሆነው ብዙ ጊዜም አንደስድብ ይጠቀሙበታል የዜሮ ድምር አስተሳሰብ በርጠ ከቫ በተለይ በድርድር ወቅት አንዱን አስጥሎ አንዱ አግኝቶ ለመውጣት የሚደረግ ጥረት ስለሚሆን ተገቢ አስተሳሰብ አይደለም ይህ ማለት ግን በሁሉም ጊዜ ትክክል አይደለም የሚባል እንዳልሆነ ማወቅ ይገባል ለምሳሌ የፓርላማ ወንበርን በተመለከተ ለምርጫ በሚደረግ ውድድር አንዱ ፓርቲ ወንበር ካገኘ አንዱ ማጣቱ የግድ ነው የምርጫ ውድድር ሲደረግ ሌላኛውን አሳጥቶ ራስ ለማግኘት የሚደረግ ጥረት በመሆኑ ክፋት የለውም ወንበሩ እስከ ሆነ ድረስ እና የወንበር ቁጥር ለውጥ ካልመጣ በፓርቲዎች መፃዛከል የሚደረግ ውድድር በዜሮ ድምር አስተሳሰብ የሚመራ ነው የሚሆነው አሁን ባለው ሁኔታ ከአንዳንድ የምክር ቤት አባላት ጋር ስነጋገር የፓርላማ ወንበራቸውን ለመድበለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ መልቀቅ አንደሚኖርባቸው አንዳንድ ሀገሮች በሚከተሉት የምርጫ ስርዓት እንዲህ ዓይነት ውጤት እንደማይፈቀድ ሲነገራቸው የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብ ነው ብለው ሌላ የቃላት ድሪቶ ከማምጣት የዘለለ መልስ የላቸውም ኬኩ ውስን በሆነበት የዜሮ ድምር ጨዋታ የግድና የተፈቀደ ጨዋታ ነው ከላይ ማብራራት እንደሞከርኩት የዜሮ ድምር ፖለቲካ በርጠፀ ፐከበ በተደራዳሪዎች መካከል በሚደረግ ድርድር መንፈስ አድርገን ብንወስደውና ኢህአዴግ አና ተቃዋሚዎች እንደ ተደራደሪ ስንመዝናቸው ለዜሮ ድምር ፖለቲካ ቅርብ ማን ነው። የሚለው ነው ኢህአዴግ ወደኋላ ሲመለከት የቀድሞ ገዢዎች ወደፊት ሲመለከት ደግሞ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ያላቸው ተቃዋሚዎች ናቸው ነው የሚለው እንዲሁም የቀድሞ ስርዓት ናፋቂዎችም ሊል ይችላል አሁን በሀገራችን በመስፋፋት ላይ ያለውን ኪራይ ሰብሰቢነት ጉቦ ወይም ሙስና በሀገራችን ታሪክ በየትኛውም ዘመን ታይቶ አይታወቅም ስለዚህ ይህ የኢህአዴግ ስርዓት ይህን ጉዳይ በኪራይ ሰብሳቢነት እንደ ስርዓት የዘረጋልን እራሱ ነው ተጠያቂውም እንዲሁ ኢህአዴግ ነው በአኔ እምነት የኪራይ ሰብሳቢነት ትርጉም ሲጠቃለል ስልጣንን መከታ ያደረገ ህገ ወጥነት ነው ይህ ድርጊት ኪራይ ሰብሳቢነት ተባለ ጉቦ ወይም ሙስና ለኔ ትርጉሙ ብዙም ለውጥ አያመጣም የህገ ወጥነት ምንጩ ደግሞ ቀላል ነው ከህጋዊ ስርዓት ያለ መስፈን ጋር ተያይዞ የጠፋው የተጠያቂነት ጉዳይ ነው በአንድ ሀገር ውስጥ ተጠያቂነት ያለው ስርዓት የመንግሥት አካል ከተዘረጋ እና ይህ በሚጓደልበት ጊዜ ስርዓት የሚያስይዝ የፍትህ ስርዓት ካለ ህገ ወጥነት ሊስፍን የሚችልበት ምንም መንገድ የለም ከዚህ በታች የምንመለከታቸው ኢህአዴግ የኪራይ ሰብሳቢነት ምንጭ ብሎ የለያቸውን ናቸው አነዚህን ተመልክታችሁ እነዚህ ጉዳዮች እንዴት ከተቃዋሚ ጋር ሊያያዙ አንባቢዎች ፍርድ ትሰጣላችሁ መሬት መሬትን በተለይ በከተማ ዋነኛ የኪራይ ሰብሳቢነት ምንጭ ነው ተብሉ ይታመናል በተግባርም የተመረጡ ሰዎች በተለየ ሁኔታ መሬት እንዲያገኙ እየተደረገ ከነፃ ገበያ መርህ ውጭ አንዲከብሩ ያደርጋል በገበያ ህግ ይመራ ሲባል ግን ኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ነው ይላል ለባለስልጣኖቹ መሬትን የማስተዳደር ስልጣን ያለ አግባብ የሰጠውና መሬት ዋነኛ የኤኮኖሚ አምድ መሆኑን አውቆ የዘነጋው የስርዓቱ ባለቤት የሆነው ኢህአዴግ ነው መሬት በመንግሥት የህዝብ ነው የሚለው ተቀባይነት የሌለው ስለሆነ እጅ ሆኖ ለፖለቲካ መጠቀሚያ እስከዋለ ድረስ መሬት የህገ ወጥ መክበሪያ መንገድ መሆን ይቆማል የሚል ዕምነት የለኝም ኪራይን በማደል ስም መንግሥት ሚናውና ለማሳደግና ቁጥጥሩን ለማጥበቅ መሬት የሚቸበችብ ስርዓት እስካለ ድረስ ዓይነቱን አየለዋወጠ ህገወጥነቱም ይቀጥላል ግብር መንግሥት ከዋና ዋና ስራዎቹ አንዱና ዋነኛው ግብር መሰብሰብ ሲሆን ይህንን ተግባሩን በፍትሃዊነት ያለአድሎ ለመወጣት የሚያስችለው ስርዓት ዘርግቶ በተግባር ማዋል ይኖርበታል በሀገራችን ይህ ሲሆን የማይታየው መንግሥት በተለያየ ምክንያት የህገ ወጥነት መስኮት ስለሚከፍት እና በዚህ ምክንያትም የተለያዩ ሰዎች በህገ ወጥነት ስለሚከብሩ ነው ይህንን የሚመለከት ዜጋም የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ በሚል የተሳሳተ መርህ ግብር መክፈልን አእንደሚያኮራ ተግባር ሳይሆን እንደሞኝነት መቁጠር ይጀምራል ግብር መንግሥት ያለ አድሎ የሚሰበስበው መሆኑ በመርህነት አጠያያቂ ባይሆንም መንግሥት ከዚህ ዘሎ ግብርን በፖለቲካ አቋማቸው ሰዎችን ፍዳ ማሳያ መሳሪያና አንዳንዴም ለከፍተኛ እስር የሚዳርግ የማጥቂያ መሳሪያ እየሆነ ነው የሚገኘው በአንድ ወይም በሌላ መንግሥት በከፈተው ህገ ወጥ መስኮት ተጠቃሚ የሆነ ነጋዴ መብቱን ለመጠየቅ አንገቱን ቀና ካደረገ መገኛው የት አንደሚሆን ይታወቃል ይህ ብቻ አይደለም ግብር በመክፈል ዙሪያ መንግሥት ራሱ ነጋዴ በመሆኑ ያለአድሎ ግብር ለመሰብሰብ ይቸገራል የመንግሥት ግዢግንባታዎችን ጨምሮ የመንግሥት ግዥዎችና ማንኛውም ዓይነት መንግሥት የሚያደርጋቸው ኮንትራቶችና ውሎች በነዓ ገበያ መርህ ሊገኝ በሚችል ተመጣጣኝ ዋጋና ጥራት ደረጃ የሚከናወኑ አይደሉም የመንግሥት ግዥን የሚፈፅሙ የመንግሥት ኃላፊዎችና አቅራቢዎች በሚያደርጉት ድርድር ከተገቢው ዋጋ በላይ ክፍያ እንዲፈፀምና ከሚፈለገው ጥራት በታች እንዲቀርብ በማደረግ ህገ ወጥ ተግባራት ይፈፀማሉ ይህ የሚሆነው መንግሥት የሞራል ልዕልናቸው የወረደ ሹሞቹን በስርዓቱ ውስጥ በመሰግሰግ አና ከዚህ ውጭ በውድድር የሚገኝ ምንም ዓይነት ሥራ እንዳይኖር በማድረግ ነው ለዚህ ደግሞ ተጠያቂው የመንግሥት ሌቦችን የሚያሰማራው እራሱ ኢህአዴግ ብቻ ነው የንግድ ስርዓቱ የንግድ ስርዓቱ በተለይ የጅምላ ንግድና ማከፋፈል ሥራው በነፃ ገበያ ስርዓት እንዲሆን የማያደርገው እና በጣት የሚቆጠሩ ከባለስልጣን ጋር ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ብቻ ዋና ዋና የገቢ ምርቶችን እንዲቆጣጠሩ በማድረግ ህገ ወጥ ጥቅም አንዲያጋብሱ ፅድል የሚፈጥረው መንግሥት ነው እነዚህን ችላ ብሎ የንግድ ስርዓቱን ፈር ለማስያዝ እያለ አንድ ጊዜ ዋጋ ትመና ሌላ ጊዜ ደግሞ ምስኪን ቸርቻሪ ነጋዴዎችን ማሰርሙያዩዬ ብሎ የያዘው መንግስት ነው የንግድ ስርዓቱ በገበያ ህግ በነፃነት ከተመራ መፍትሔ እንደሚሰጥ ዋነኛ ማሳያ በሀገራችን የነበረውን የሲሚኒቶ ፅጥረትና አሁን ያለበት ሁኔታ ነው ለነገሩ በእጥረት መዛል ቁጭ ብለው ህገ ወጥ ሀብት የሚያካብቱ አስካሉ ድረስ ችግሩ ይቀጥላል ከላይ የተመለከትናቸው በሙሉ ግን የሚመለከቱት አራሱ ኢህአዴግን ነው እንጂ ሌላ ሶስተኛ አካልን አይደለም የሌባ ዓይነ ደረቅ መልሶ ልብ አድርቅ እንደሚባለው ኢህአዴግ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ወይም በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ቅርበት የሌላቸውን በኪራይ ሰብሳቢነት ወይም በኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ይከሳል ለኢህአዴግ ከተቃዋሚ ፓርቲ በተጨማሪ ሚዲያው ሲቪክ ማህበራት ወዘተ ኪራይ ሰብሳቢዎች ናቸው አንዳንድ ጊዜ ከአንዳንድ የምክር ቤት አባላት ጋር መደበኛ ያልሆኑ ውይይቶችን ስናደረግ አናንተ እኮ ኪራይ ሰብሳቢዎች ናችሁ ይሉኛል አዎ እኛ ቤት እያከራየን አናንተ ግን ስልጣናችሁን መከታ አድርጋችሁ አላቸዋለሁ አቶ በረከት በሁለት ምርጫዎች ወግ መጽሐፋቸው ኪራይ ሰብሳቢ የሚሉትን ቅንጅትን አዲስ አበባን ተቆጣጥሮ የመሬት ዋጋን ዜሮ አገባዋለሁ ብሎ ነበር ይላሉ ይህ እንዴት ህገ ወጥ ጥቅምን እንደሚያስገኝ ባላውቅም መደናገሩ ግን ከላይ እስከ ታች መሆኑን ሊያሳይ ይችላል ዶክተር ብርሃኑ በአንድ በኩል ፓርላማ በመግባትና ባለመግባት ክርክር ውስጥ በአሯሯጭነት እየተሰለፈ በሌላ በኩል ደግሞ የመሬትን ዋጋ ዜሮ የሚያደርግበትን ውሉን ሳይስት ለከንቲባነት ተግቶ እየሠራ ነበር ይላል መቼም ዋጋ ዜሮ ተደርጎ ከዜሮ ከልክ ያለፈ ህገ ወጥ ጥቅም የሚገኝበትን የኪራይ ሰብሳቢነት ክስ የሚያውቀው ኢህአዴግ ብቻ ነው አንድ ጊዜ የአዲስ ነገርጋ ዜጣው መስፍን ተደናጊረ እያለ የአስመራና የአዲስ አበባ ገዥዎችን መደናገር በኤርትራውያን ዜማ እያለ በጽሑፉ ያስቃኘን ነበር አሁንም ተደናጊረ ካልሆነ በስተቀር አና ምስኪኖቹን ለማደናገር ካልሆነ የኪራይ ሰብሰቢነት ፖለቲካ ኤኮኖሚ ፍልስፍናውም ጦሱና መዘዙም ለኢህአዴግና የኢህአዴግ ብቻ ነው የሚሆነው ከተቃዋሚ ፓርቲ ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም ነገር ግን ኢህአዴግ ባስቀመጠው ፍች በየቦታው የሚደነቀረውን ሳይሆን ከላይ ባስቀመጥኩት መስመር ከሆነ ተቃዋሚዎች በጋራ እያንዳንዳችን በግል ልንንደው የሚገባ ህገወጥ ተግባር ነው ይህንን ህገ ወጥ ተግባር እደግፋለሁ የሚል ካለ ይህንኑ ይዞ ለምርጫ ለህዝብ ዳኝነት ማቅረብ ነው መቼም ህዝቡ አንደተለመደው በጉልበት ካለሆነ ደሙን የሚመጠውን መዥገር ይመርጣል ማለት ተገቢ አይደለም በመንግሥት ስልጣን እና ባለስልጣንን ተገን አድርጎ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ማጋበስ ላይ ያሉ ሰዎች መዥገር ካልሆኑ ምን ሊገልጻቸው ይችላል ጎበዝ። በቂ ዝግጅት ባለማድረጉ በሜዳው አራሱ ቤት ለቤት እየዞረ ባስመዘገባቸው መራጮች መድረክ ነጥብ አስቆጥሮ ወጥቷል በእኔ ምርጫ ጣቢያ የተመዘገበውን ውጤት በአባሪ ላይ መመልከት ጠቃሚ ነው የማህበራዊ ጥናት ባለሞያዎች ይህንን ውጤት ይዘው የመራጩን ህዝብ ስነልቦና የኢኮኖሚ አቅም አምነት ወዘተ ሊተነትነበት አንደሚችሉ አምነቴ ነው ከዚህ አንፃር የመነሻ ፃሣብ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ አሁን ባለው ሁኔታ ይህንን ሽንፈት ለመሸፈን የሚደረገው መፍጨርጨር መላላጥ እንጂ ያመጣው ፋይዳ የለም ኢህአዴግ ያለው አማራጭ ምርጫውን ጠቅልሎ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ሞዴል መውሰድና ፓርላማው በዓመት አንዴ ወይም ሁለቴ የሚሰባሰብ በማድረግ በፓርላማ የሰበሰባቸውን ካድሬዎች የልማት ሰራዊት ብሎ ወደመጡበት መመለስ ነው በዚህ ዓይነት የምርጫ ውጤት ተመሳሳይ ፃሳብ የሚያራምዱ ሰዎች ሰብሰቦ ደሞዝ መቁረጥ ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚያመዝነው ነገር ግን ከዚህ ትምህርት ወስዶ የመድብለ ፓርቲ ፖለቲካን ከምር ማድረግ አማራጭ ሳይሆን ግዴታ ነው አዚህ ጋ ምርጫው የህዝብ ውሳኔ ነው የሚለው ቀልድ መቆም ይኖርበታል በዚህ መጽሐፍ በግልፅ ለማሳየት እንደተሞከረው በኢትዮጵያ ምርጫ ፌዝ እንደሆነ ለማረጋገጥ የሐረሪን ምርጫና የምርጫ ውጤት መፈተሽ በቂ ነው ይህ ምርጫ ኢህአዴግ አንደሚያስበው የኢትዮጵያ ህዝብ በብሔሩ ነው የሚያስበው ቢባል አንኳን ፈተና ሊያልፍ አይችልም ኢትዮጵያ ነፃ እና ገለልተኛ ምርጫ የሚያስፈልጋት ወቅት በቅርቡ መምጣት ይኖርበታል ኢህአዴግም ትክክለኛውን የህዝብ ውሳኔ መስማት ከፈለገ ማድረግ ያለበት ቀላል ነገር ምርጫ ቦርድን ነፃ እና ገለልተኛ የሙያ መሥሪያ ቤት ማድረግ ነው እኛ ምርጫ ስንል እርስ በርሳችን ነው ካልተባለ በስተቀር አሁን ባለንበት የፍርዛት ድባብ ስር ሆነን ጥቂት በሚባሉ የፖለቲካ መሪዎች ሀገራችን ከገባችበት አጣብቂኝ ለማውጣት የሚያስችል ለውጥ ይመጣል የሚል ዕምነት የለኝም አሁን ያሉትም ቢሆኑ በአንድ ዘፈን ሁለት ዓይነት ዳንስ የሚደንሱ ናቸው ይህ ለውጥ እንዲመጣ እና ሀገራችን እና ህዝቧ በዓለም ላይ ያሉ ሀገሮች የሚያጣጥሙትን ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የምንመኝ ከሆነ ነፃነት ካማረን ቀድመን ማሸነፍ ያለብን ፍርፃትን ነው ብዬ አምናለሁ በፍርሃት ጥላ ስር ላለ ህዝብ አምባገነኖች ዲሞክራሲን በኮታ ቀበሌ አምጥተው ሊሰጡን ወይም በብሉ ቱዝ ሊያካፍሉን አይችሉም አምባገነኖች ፈሪዎች ስለሆኑ በጀግንነት ይህን ሊከውን የሚችል ፃሣብ ሊያመነጩ እንኳን አይቻላቸውም ስለዚህ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የተማረው ክፍል ዕጩ የፖለቲካ መሪ ይሆናል ብዬ ስለማምን ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት እንዳለበት ሊሰማው ይገባል ሁሉም የተማረ ሰው ፖለቲከኛ ይሁን የሚል ሀሳብ እንደሌለኝ መቼም ትረዱኛላችሁ ብዬ አምናለሁ ነገር ግን ለፖለቲካ ስልጣን ለሚተጉ ሰዎች በግልፅ የሙያና የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ የምርጫ ጉዳይ አይደለም ይህ ሳይሆን ቀርቶ ማንም ለሙከራ ገብቶ የሀገሪቱን ፖለቲካ ሲዘውር ይህች ሀገር አደጋ ላይ ብትወድቅ ተጠያቂው የሚችል መስሎት ፖለቲካውን ለመዘወር የገባው ሳይሆን የሚችለው እንዲገባ ኃላፊነታችንን ያልተወጣን እንዲሁም ኃላፊነቱን ለመወጣት ወደፊት ያልመጣ የተማረ የሚል ቅፅል ያገኙ ዜጋ ሁሉ ነው የሚሆነው ኢህአዴግ ስለትና እሳት ይዞ እያስፈራራን ይህ እንዴት ይሆናል ብሎ ወደጊላ ማለት የሚቻል አይመስለኝም ነፃነት በነፃ የሌለ መሆኑን ተረድቶ አሳቱንም ስለቱንም አንዴት አንደምናከሸፍ ማሰብ ያለብን እኛ ነፃነት ፈላጊዎች እንጂ ኢህአዴግ ሊሆን አይችልም በኢህአዴግ በኩል ህዝቡን ለማሰፈራራት የቀየሰው መንገድ ለጊዜው በደንብ ነው የተሳካለት ካለው አቅምና ድርጅት በላይ ተኝተን እንደሚያየን ፈጣሪ በሚያክል ግርማ ሞገስ እየፈራነው እንገኛለን ከፍርሃት መገላገያው መንገድ ግን አንድ ሚሊዮን ሰው ነፃነቱን ቢያውጅ አንድ ሚሊዮን ደህንነት ወይም ሰላይ ሊመደብለት አይችልም የነፃ ዜጎች መብዛት አማራጭ የለውም ከሚታቀዱልን ህገ ወጥ ወጥመዶች እራሳችንን በማንኛውም ሰዓት መጠበቅ ግብር ማጭበርበር መሬት በነዛ ሲቀርብልን ለምን ብለን መጠየቅ ወይም ከህጋዊ ስርዓት ውጭ ያለመጫወት ከመንግሥት ጋር እንዲሁም ከሌሎች ጋር የሚኖረንን ግብይት በህግና በህግ ብቻ ማድረግ ከማንኛውም አማላይ ግብይቶች ጋር ከተያያዙ ህገ ወጥ ድርጊቶች መጠበቅ ኢህአዴግ ብዙ ወንጀለኞች ለማሰር ይችል ይሆናል ነገር ግን ብዙ የፖለቲካ እስረኞች ማሰር መከራውን ነው የሚያበዛው ስለዚህ እስርን እንደማስፈራሪያ ያለመቀበል ከፍርፃት መገላገያ ዋና ዋናዎቹ መንገዶች ናቸው ብዬ አምናለሁ አመስግናለሁ ዋቢ መፅሐፍት በረከት ሰምኦን የሁለት ምርጫዎች ወግ ዓም ልደቱ አያሌው የአረም እርሻ ታህሳስ ዓም ፕሮግሬስ ማተሚያ ቤት ልደቱ አያሌው መድሎት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሦስተኛ አማራጭነት ሚናፕሮግሬስ ማተሚያ ቤት አንተነህ ሙሉጌታየሁለት ዓለም ሰዎች ንግድ ማተሚያ ድርጅት የዲሞክራሲ ሰርአት ግንባታ ትግልና አብዮታዊ ዴሞክራሲ መጋቢት ዓም ልማት ዴሞክራሲና አብዮታዊ ዴሞክራሲ ጥቅምት ዓም ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት ፅዕትም ዚበበፀየ አዩ ልበ ልከ አ ሼፎዐበር ዐሃርዐቬ ዞበበ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact