Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሀ በማያምኑ ሰዎች የሚገለጥ የዐማሌቅ አሠራር የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ በሆነው በወይን ጠጅ ሐት ባደረገ ጊዜ ንግሥት አስጢን አጅግ የተዋበች ስለነበረች ንጉሥ አርጤክስስ ለአለቆችና ለባለሥልጣናት ሊያሳያት ፈልጎ እርስዋ ግን እምቢ በማለትዋ ከንጉሥ ክብር የጎደለች ሆነች አስቴር ደግሞ በርግጥ አቋም አላት ሞገስንም አግኝታለች ነገር ግን የታላቁ የአምላካችን አሠራር ነውና ለእግዚአብሔር አሠራር ራሳችንን አጋልጠን መስጠት አለብን ባሁኑ ዘመን በብዙ ቦታዎች የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ በእረኝነት ሥልጣን ሥር በትክክል የማይሄድና ከተሰጠው ሥልጣን ዚት ክርስቲያንን ቅርጽ የሚያስይዝዋት አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች በሳይ ለመሆን የሚሞክር ከሆነ በሮሜ ያለውን ቃል በማንበብ ሁሉም የተስጠው የአገልግሎት ስጦታ እንዳለው ከተሰጠው የአገልግሎት ሥልጣን በላይ በትዕቢት እንዳያስብ በተሰጠው ሥልጣን ብቻ እንዲንቀሳቀስ ከቃሉ ላይ በደንብ አስረግጩ እነግረዋለሁ ከዚህ የተነሣ እኔ ባለሁበት ቤተ ክርስቲያን በሥርዓት እንድትመራ የሚያደርግ እረኛ ማነው።
»«»» ምዕራፍ ለመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የወርቁ በትር መዘርጋት የወርቁ በትር መዘርጋት በግብዣው ቦታ የሰይጣን ራስ መቀጥቀጥ የመላእክት ኣገልግሎት በመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የብልዕግና ምርኮ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት ሀ ጣዖትን የሚያመልኩ አገሮች ለ ሥልጣናቸውን የሚጠቀሙ አማኞች ያሉበት አገር ሐ ሥልጣናቸውን የማይጠቀሙ አማኞች ያሉበት አገር ምዕራፍ የቀለበቱ ማኅተም ለመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የቀለበቱ ማኅተም መመለስ የአመለካክት ተሐድሶን ማግኘት ሀ የዘንዶው ምንጭ ለ የጉድፍ መጣያ ስፍራ ሐ የንጉሙ ኩሬ መዋኛ መ የሸለቆው ቅጽር በር ምዕራፍ የቤተ ክርስቲያን በትንሳኤው ኃይል በታላቅ ክብር የበቀል ቅባት በቤተ ክርስቲያን መፍሰስ ሀ የሳምሶን ምሳሌነት ለ የሙሴ ምሳሌነት ሐ የበቀል ቅባት የሚፈስባቸው ሰዎች የመንፈስ ቅዱሰ እውነተኛ ቦታውን መያዝ ሀ የቤተ ክርሰቲያን በትንሳኤው ኃይል መመላለስ ለ የመንፈስ ቅዱሰና የቤተ ክርስቲያን መዘጋጀት ሐ የአምልኮ መታደስ የቤተ ክርሰቲያን መፈራት የብዙ ሰዎች መዳን በድል ላይ ድል መጨመማ የቤተ ክርስቲያን ወደ እምነት አንድነት መምጣት የቤተ ክርስቲያን መነጠቅ ሀ የፔሪም በዓል መነጠቅ ለ የማትነጠቅ ቤተ ክርስቲያን ማጠቃለያ መቅድም መጽሐፈ አስቴርን የፃፈው ሰው ማን እንደሆነ አይታወቅም ይሁን እንጂ የሜዶንና የፋርስን ሕግ ጠንቅቆ የሚያውቅ አይሁዳዊ እንደጻፈው ይታመናል መጽሐፉ በመርዶክዮስ ወይም በዕዝራ ተጽፎአል የሚልም ግምት አለ በመጽሐፉ ውስጥ አንድ ጊዜ እንኳን የእግዚአብሔር ስም አልተጠቀስም ይሁን እንጂ የአምላክ ተአምራታዊ እጆች አይሁዶችን ሲረዳ ጠላቶቻቸውን ሲደመስስ እንዲሁም ከአዘቅት ውስጥ ከፍ ሲያደርጋቸው ይታያል በመጽሐፉ ውስጥ ጐልተው የሚታዩት ባለ ታሪኮች መርዶክዮስና አስቴር ሲሆኑ ደካማ በሆኑት በእነዚህ አይሁዶች ሕይወት ውስጥ የተከናወነው ሁሉ የሚያንጸባርቀው እግዚአብ ሔርን ነው ሁለቱ በተአምር በመንግሥቱ አመራር ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን ሳይ ራሳቸውን ያገኙት ጾምን በማወጅና ራስን በማዋረድ ወቅት ሲያገፔ ደግሞ ጠሳቶቻቸውን እስከ መጨረሻ መስቀላቸው የመጽሐፉን መንፈሳዊ ይዘት ያመለከታል መርዶክዮስም ሆነ አስቴር ስውን የማይፈሩ ኑ እምነት ያላቸው ሰዎች ናቸው በመንፈሳዊ ዕድገታቸው በኩልም ቢሆን ቅደም ተከተላቸውን የሚያውቁ ሰዎች ነበሩ በተለይም አስቴር ወደ ንጉሥጮ ለመግባት ስትወስን በሕይወትዋ ቆርጣ ነበር የገባችው ጉዳይዋን ወዲያው ለንጉሥ አልተናገረችም ግን አመቺ ጊዜ ሰማግኘት ንጉሠን ለእራት ጋበዘችው መርዶክዮስም ቢሆን በሞት ፍርድ የሚያስቀጣ ቢሆንም እምቢ አሻፈረኝ ለሃማ አልስግድም ያለ ቆራጥ ነበር የእነዚህን ሁለት ባለታሪኮች እና ሌሎችንም የመጽሐፉን ክፍል ስንመለከት ኣሁን ላለችው የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ጥላ ናቸው መጽሐፍ ቅዱስ በሁለተኛ ጢሞቴዎስ ድረስ የአግዚአብሔር ስው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የአግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል ይሳል መጽሐፈ አለቴርን በመንፈስ ቅዱስ ዕርዳታ በማጥናት መጋቢ መኮንን ሞገስ ለመጨረሻው ዘመን የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ትምህርት አዘል የሆነ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የሚል መጽሐፉን ደርሶ አቅርቦልናል መጋቢ መኮንን ሞገስ በግብጽ አገር ካይሮ ከተማ ውስጥ ያለችው ማራናታ የኢትዮጵያውያን ቤተ ክርስቲያን ዋና መጋቢ ነው በዚያው ክፍለ ዓለም የተበተኑ ወገኖቻችንን በወንጌል በመድረስ በማሳደግና በአገልግሎት በማሠማራት በእግዚአብሔር መንግሥት ሥራ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ወንድም ነው የመጋቢ መኮንን ሞገስን መንፈሳዊ ብስለት መጽሐፉን ጠለቅ ብሳችሁ ስታነብቡት ትረዳሳችሁ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የተባለውን መጽሐፍ አንብቤ የግል አስተያየቴንና እርማትም እንድሰጥ በመጠየቄ በጣም ተደስቻለሁ ምክንያቱም እግዚአብሔር በተለያዩ ልጆቹ ውስጥ ያለውን ጸጋ እንዳይ ረድቶኛል ደራሲው መጋቢ መኮንን ከጌታ ዘንድ የተቀበለው የቃል መገለጥ በዘመናችንም ሳለች ቤተ ከርስቲያን መንፈስ ቅዱስ የሚናገረውን የአሳብ ጥልቀት ተመልክቼ ተደንቄአለሁ ቤተ ክርስቲያን ለመክበር ተጠርታለች ወደዚያ ሙላት ደግሞ የሚያደርሳት የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው በሐዋርያት እጅ የተገለጡት ተአምራትና ድንቅ ቅዱሳን መዳሕፍት ተለይተው ከተጠረዙ በኋላ አሁን አስፈላጊ ስሳልሆኑ ቀርተዋል የሚል ትምህርት አለ ይህ የስህተት ትምህርት ቤተ ክርስቲያንን ተአምራት ዓልባ ከማድረጉም በሳይ ፍልስፍናውን ለአማኞችዋ ታስተምራለች ለዚህ ነው ዛሬ ቤተ ክርስቲያን በሰይጣን ላይ ኃይል ያጣችው ጳውሎስ ለጢሞቲዎለ ሲጽፍለት የአምልኮት መልክ አሳቸው ኃይሉን ግን ክደዋል ከእነዚህ ደግሞ ራቅ ጢሞ ይለዋል እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ የተሞላች ቤተ ክርስቲያንን በዓለም ዙሪደ እያነሳሳ ነው በተለያየ የአገልግሎት ቅባት የተቀቡ አገልጋዮችን እያስነሳ ተሃድሶ በየአቅጣጫው በመካሄድ ላይ ይገኛል ይህ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን ወደ ቀድሞ ክብርዋና ኃይልዋ ተመልሳ ትታደሳለች ነቢዩ ሐጌ በምዕራፍ ላይ ከፊተኛው ይልቅ የዚህ የሁለተኛው ቤት ክብር ይበልጣል ይሳል ንግሥት አስቴር ከንጉሠ በተሰጣት ቅባትና ሽቱ አም ፈታና ተኳኩላ ንግሥት አስጢንን እንደተካቻት በመጨረሻው አለች አብተ ክርስቲያን ጌታ ሸላልሞ ለራሱ ያቀርባታል መ ሚያገለግሉዋት የተቀቡ ቅሪቶችዋ ወደ ሙላት የተወደዳችሁ አንባቢዎች የመጨረሻዋ ዘመ ን ቤተ ክርስቲያንን ከህ በኪ እ ግዚአበልር መሬለዊ ግሪናችራን እንዳለና ርና ። መጋቧ መይሶ ምነ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የእውነተኛ ነገር ጥላዎች መጽሐፍ ቅዱሳችን በዘላለሙ አምላክ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የተፃፈ ስለሆነ ስህተትና ነቀፋ የሌለበት በእግዚአብሔር የዘላለም አሳብ መሠረት የሰፈረና ለሰው ልጆች ያለውን የዘላለም አሳብ የገለፀበት ዛሬም የሚሠራ ሕይወትና መንፈስ ያለበትን ቃል የያዘ መጽሐፍ ነው ቃሉን በፃፈው በመንፈስ ቅዱስ በኩል ዛሬም ሲተረተር እጅግ አስደናቂ ምስጢር እንደያዘ እንረዳለን በመጽሐፈ እስቴር የተገለጹ ድርጊቶች ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ ታላቅና እስደናቂ ምስጢር የያዙ ናቸው ይህም ቤተክርስቲያን ከተጠራችበት ክብር አንስቶ የጥሪዋ ዓሳማና ውበት እንዲሁም የጥሪዋ የማጠቃለያ ሥራና ቤተ ክርስቲያን ከዚህ ምድር እስከምትወሰድበት ጊዜ ድረስ ቁልጭ ባለ መልኩ ተገልጦ እናየዋለን እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት በክብርም በዓይነትም በጣም ልዩ የሆነውን በእዲስ ኪዳን ያለውን ዕቅድ የገለጸበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው በመሆኑም አማኞች ሁሉ አውቀውት እግዚአብሔር ባዘጋጀልን የዘሳለም በረከት ውስጥ እንድንኖር ስለሚረዳን በማስተዋል እንመለከተዋለን በዕብራውያን መጽሐፍ ላይ በስው እጅ ሳይሆን በጌታ ወደ ተተከለችው ስማያዊ ቅድስተ ቅዱሳን ደሙን ይዞ ስለገባው ታላቅ ሊቀ ካህን ስለሆነው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሰፀ በኋላ ስለ ብሉይ ኪዳን የሊቀ ካህናት እገልግሎት ሲገልጽ ግን እነርሱ የሚያገለግሉት ለስማያዊ ነገሮች ምሳሌና ጥላ በሆኑት ነገሮች ነው ዕብ ይለናል በብሉይ ኪዳን የነበሩ አንዳንድ አገልግሎቶች ለእውነተኛው ነገር ጥላ ወይም ምሳሌ እንደሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳችን ይነግረናል ሙሴ ድንኳኒቱን በሚሰራበት ጊዜ እግዚአብሔር በተራራው ላይ እንደተገለጠልህ ዓይነት ሁሉን ነገር በጥንቃቄ አድርግ ዕብ ብሎ ያዘዘው እግዚአብሔር እንደ ጥሳ ለሚያልፍ ነገር ብቻ አስቦ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ሳለው ለክርስቶስ ጥላ ወይም ምሳሌ ስለሆነ ነበር ከዚህም የተነሳ በድንኳኑ ውጭና ውስጥ ለምሳሌ የናስ መሠዊያ የመታጠቢያ ሳህን የወርቅ መቅረዝ የኅብስት የአውነተኛ ነገር ጥላዎች ገበታ የዕጣን መሠዊያ መጋረጃውና የኪዳኑ ታቦት የመሳሰሉት ሙሉ ለሙሉ የክርስቶስን ጥላ የሚያሳዩ ናቸው ሙሴ በጥንቃቄ ከሠራው ክድንኳኑ ሌላ በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደ ምሳሌ ወይም ጥላ አድርገን የምንወስዳቸው ብዙ ነገሮች አሉ ጌታ ኢየሱስ ራሱ በምድር በነበረ ጊዜ ስለ ራሱ ከብሉይ ኪዳን በምሳሌ ወይም በእውነተኛው ነገር ጥላ እየጠቀሰ ካስተማራቸው ውስጥ ለምሳሌ ሙሴ በበረሓ አባብን ከፍ አድርጎ እንደሰቀለ እንዲሁም የሰው ልጅ ክፍ ብሎ ሊሰቀል ይገባዋል ዮሐ ዘ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንዳሳለፈ እንዲሁ የሰው ልጅ በመቃብር ውስጥ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ያሳልፋል ማቴ ዮናስ በመጽሐፍ ደረጃም ብንወስደው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ለእዲስ ኪዳን እውነቶች በምሳሌ ወይም በጥላ ያለቀመጠው ብዙ ነገር አለ ከነዚህም መጻሕፍት ውስጥ እንዱ መጽሐፈ አስቴር ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሴት ስሞች ከተጠቀሱት ሁለት መጽሐፍት ውስጥ አንዱ መጽሐፈ አስቴር ሲሆን ሌላኛው መጽሐፈ ሩት ነው አስቴር ማለት ኮከብ ማለት ነው መጽሐፈ አስቴር በፋርስ መንግሥት ጊዜ በእሥራኤል ምርኮኞች ላይ የደረሰውን ስደትና ከዚያም ግሩምና ታላቅ በሆነ መንገድ መዳናቸውን እንዴት እንዳገኙ የሚተርክ ነው መጽሐፈ አስቴርን ማን እንደጻፈው ባይታወቅም ነገር ግን የፋርስን ቤተ መንግሥት የአኗኗር ሁኔታና እንዲሁም የቤተ መንግሥቱን ደንቦች በሚገባ የሚያውቅ አይሁዳዊ መሆኑ አያጠራጥርም በመጽሐፈ አስቴር የንጉሥ እርጤክስስ ስም በጣም ብዙ ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን ከጾም በስተቀር ምንም ዓይነት ስለ አይሁዳውያን የሃይማኖት ሥርዓትና ሕግ እንዲሁም ስለ ፀሎት መጽሐፉ ውስጥ የምናየው ምንም ነገር የለም በተጨማሪም እንደ መኀልየ መኀልይ መጽሐፍ በመጽሐፈ አስቴርም ውስጥ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻው በአንድም ስፍራ የእግዚእብሔር ስም አልተጠቀሰም በዚህ ምክንያት በመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በመጠኑም የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ቢሆን መጽሐፈ አስቴርን እንደ አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አድርገው ለመቀበል ያንገራገሩበት ጊዜ ነበር ምንም እንኳን በመጽሐፉ ውስጥ የእግዚአብሔር ስም ባይጠቀስም ነገር ግን እግዚአብሔር ታላቅ የሆነውን የማዳን ሥራውን ለሰዎች እንደሚገባ አድርጎ በተጨባጭ ሁኔታ በትዕይንት የገለጸበት በመሆኑ መጽሐፉ በፍጥነት ተቀባይነትን ማግኘት ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር የማዳኑን ሥራ የሚገልጥ ታዋቂና አስደናቂ መጽሐፍም ሆኗል በመጽሐፈ አስቴር ትልቅ የእግዚአብሔር ፈቃድ በሰዎች በነገሮች በጊዜያቶች በታሪክና በሕዝቦች ውስጥ የተክናወነበት ነው መጽሐፈ አስቴር ስላለፈው ታሪክ የሚነግረን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ለእግዚአብሔር ሕዝብ ትልቅ መልእክት ያለው መጽሐፍ ነው ስለሆነም የመኀልየ መኀልይ መጽሐፍ ምንም ጥርጥር በሌለበት ሁኔታ ስለ ቤተ ክርስቲያንና ስለ ክርስቶስ በምሳሌ የተቀመጠ እውነት እንደሆነ ሁሉ መጽሐፈ አስቴርም ያለ ምንም ጥርጥር የቤተ ክርስቲያን ጥላ ወይም ምሳሌ ሆኖ በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ የሰፈረ እንደ ሆነ ይህቺን መጽሐፍ አንብበን ስንጨርስ የምንረዳው ነው ቤተ ክርስቲያን የተጠራችበትን ክብር ከክብር የጎደለችውን ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም እግዚአብሔር በመጨረሻው ዘመን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንዴት የተሐድሶን ሥራ እንደጀመረና የመጨረሻዋን ዘመን ቤተ ክርስቲያን እስከ ፍፃሜዋ ድረስ ከማየታችን በፊት በመጽሐፈ አስቴር ውስጥ የተጠቀሱትንና አሁን ላለችው ቤተ ክርስቲያን በነገር ጥሳ ወይም በምሳሌነት የተቀመጡትን ስዎች በማነፃፀር እንመለከታስን ንጉሥ አርጤክስስ በብሉይ ኪዳን ክእሥራኤል ንጉሦች ውስጥ በጣም ታዋቂ ከሆኑት አንዱ ንጉሥ ስለሞን በብዙዎች ዘንድ የክርስቶስ ምሳሌ እንደሆነ ይታመናል ይስበካልም ከዚሁ ጋር አያይዞ ንግሥት ሳባ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ እንደሆነች ይነገራል በተስይ የመኀለየ መኀልይ ዘስለሞን መጽሐፍ ስናነብ ሙሽራው ክርስቶስ እንከን ስለማይገኝላት ስለ ሙሽራይቱ ቤተ ክርስቲያን ሲገልጽ ሙሽራይቱ ደግሞ ፍፁም ስለሆነው ስስ ሙሽራው በቅኔ በጣም ግሩምና ድንቅ አገሳለጽ ተገልጾ እናየዋለን መጽሐፍ ቅዱሳችን ንጉሥ ሰለሞን የክርስቶስ ምሳሌ ነው ብሎ በቀጥታ አይነግረንም ነገር ግን ጌታ ኢየሱስ ክአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ግንኙነት ስተረዳ ሰው የመኅለየ መኀልይ መጽሐፍ በምሳሌነቱ የቤተ ክርስቲያንና የክርስቶስ እንደሆነ ያለምንም ጥርጥር ይቀበለዋል ስለሆነም ንጉሥ ሰለሞን የክርስቶስ ምሳሌ እንጂ ክርስቶስ አይደለም ጥሳ እንጂ እውነተኛ አዳኝ አልነበረም ምክንያቱም ከሰለሞን የሚበልጠው እውነተኛው ክርስቶስ ተገልጧልና ማቴ እንዲሁም ልክ እንደ ንጉሥ ሰለሞን በመጽሐፈ እስቴር ንጉሥ አርጤክስስ የክርስቶስ ምሳሌ ነው ምናልባትም የንጉሥ አርጤክስስ ምሳሌነት ለብዙዎቻችን አዲስ ሊሆንብን ይችላል ነገር ግን ይህቺን መጽሐፍ ወደ ውስጥ እያነበብን ስንገባ ከሌሎች የመጽሐፉ ትዕይንቶች ጋር ቁልጭ ባለ መልኩ የምንረዳው ነው በተለይ በመጽሐፉ ውስጥ የእግዚአብሔር ስም አለመጠቀሱ ፀሎትና የሃይማኖት ሥርዓት አለማየታችን ከንጉሠ በላይ የሆነ ሲፈራና ሲመለክ የሚታይ ምንም ነገር አለመኖሩ ንጉሥ አርጤክስስ በመጽሐፈ አስቴር ላይ ተዋናይ ሆኖ ትዕይንቱን የሠራው ሊመጣ ላለው የእውነተኛ አምሳክ የክርስቶስ ምሳሌ መሆኑን ያሳየናል ምክንያቱም ምንም ዓይነት ወደ እግዚአብሔር የቀረበ ፀሎት አለመኖሩ የሚያመለክተው ንጉሥ አርጤከስስ የክርስቶስ ምሳሌ ስለሆነ አስቴር ልመናዋን ፀሎቷን ሁሉ የምታቀርበው ወደ ንጉሥ ነበር ስለዚህ አስቴር ክንጉጮ ጋር ተነጋገረች ማለት በምሳሌነቱ ቤተ ክርስቲያን ፀሎቷን ሁሉ ወደ ክርስቶስ አቀረበች ማለት ነው አይሁዳውያንን ከጠላቶቻቸው የማዳኑ ኃይልና ትእዛዝ መጀመሪያ የሚወጣው ክንጉሥ አርጤክስስ ነበር የማዳኑ ኃይል ግን ለሌሎቹ የሚገለጸው ሚስቱ በሆነችው በአስቴር በኩል እያለፈ ነበር እንዲሁም ብዙዎችን የሚያድነው ኃይልና ትእዛዝ ክክርስቶስ የሚወጣ ሲሆን ነገር ግን የክርስቶስ የማዳኑ ኃይል ለሌሎች የሚደርሰው ልክ እንደ ንግሥት አስቴር በቤተ ክርስቲያን በኩል ነው እንግዲህ ይህንን በመሳሰሉ ሁኔታ ንጉሥ አርጤክስስ እንዴት የክርስቶስ ምሳሌ እንደሆነ ሰፋ ባለ መልኩ በዚች መጽሐፍ ውስጥ እንመለከታለን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ንግሥት አስጢን ንግሥት አስጢን የንጉሥ አርጤክስስ የመጀመሪያ ሚስቱ ናት ከዛም ለንጉሠ አልታዘዝም ብላ እምቢ ያለች ሴት ነች ያስማችው እምቢ የሚል ድምጽ ንጉሥ አርጤክስስን በጣም አስቆጥቶት ንግሥት አስጢን የንግሥናዋ ማዕረግ እንዲገፈፍና ሚስቱ ተብሳ ሁለተኛ እንዳትቀርብ ውሳኔ የተላለፈባት ሴት ነበረች ይህቺ ንግሥት አስጢን በመጽሐፈ ኣስቴር ሳይ በቀጥታ ምሳሌነትዋ ከክብር የጎደለችውን ቤተ ከርስቲያን የምታመለክት ናት ምክንያቱም ልክ እንደ ንግሥት አስጢን የመካከለኛዋን ዘመን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ አልታዘዝም እምቢ በማለት የራሷን ወግና ሥርዓት ስታንጸባርቅ ከእውነተኛው ወንጊል የራቀች በመሆን ንግሥት አስጢን ከንጉጮ እንደተለየች ቤተ ክርስቲያን ፈጽሞ ከክርስቶስ የተለየችበት ብዙ ዘመናት ነበር ስለዚህ ንግሥት አስጢን ከንጉሠ ክብር ተለይታ በሥራዋ ሙት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት ንግሥት አስቴር ንግሥት አስቴር ለሁለተኛ ጊዜ ተፈልጋ የመጣች የንጉሠ አርጤክስስ ሚስት ናት አስቴር ንጉሥን በተለየ መንገድ በውበትዋ የማረከች ደስ ያስኘች ሴትና ንግሥት አስጢን እምቢ ብላ የጣለችውን የንግሥና ዘውድ የደፋች ናት ይህ ብቻ ሳይሆን ጠሳትዋን ሃማን እስከ መጨረሻ ተዋግታ ድል የነሳችና ለህዝቧ ፍፁም እረፍትን ያመጣች ማሸነፍን እንጂ መሸነፍን የማታውቅ ሴት ናት ከዚህም የተነሳ በነገር ሁሉ ከንግሥት አስጢን በተሻለ ሁኔታ የንጉጮ ሚስት የሆነች ናት አስቴር በምሳሴነትዋ በቀጥታ የምታመለከተው የመጨረሻዋን ዘመን ቤተ ክርስቲያን ነው ምክንያቱም ቤተ ከርስቲያን በመካከለኛው ዘመን ከክርስቶስ ተለይታ ብዙ የዝምታ ዘመናት ያሳለፈች ቢሆንም ነገር ግን እንደገና የተሐድሶ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን በመምጣቱ ንግሥት አስቴር ተፈልጋ እንደመጣች ሁሉ እግዚአብሔር እንደገና የወንጌልን እውነት ይዘው የሚያገለግሉትን ሰዎች ፈልጎ አለነሳ ከዚያም በየዘመናቱ የወንጌል እውነቶች እየታደሱ አሁን ቤተ ክርስቲያን ያለችበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ንግሥት አስቴር የንግሥናዋን ዘውድ ደፍታ ጠሳትዋን ሙሉ በሙሉ እንደረገጠች ቤተ ክርስቲያን ከአሁን በኋላ የሚጠብቃት የንግሥናዋን ዘውድ ደፍታ ጠላቶችዋን ሙሉ በሙሉ መርገጥ ነው እንዲሁም ንግሥት አስቴር በነገር ሁሉ ከንግሥት ኣስጢን እንደምትሻል ሁሉ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዲሁ ከፊተኛው ር የእውነተኛ ነገር ዊሳዎች ዘመን እጅግ የተሻለች ናት ምከንያቱም ከፊተኛው ቤት ከብር ይልቅ የኋለኛው ቤት ክብር እጅግ ይበልጣል ሐጌ ስለዚህ አስቴር የንግሥናዋን ዘውድ ደፍታ ሙሉ ለሙሉ ጠላቶችዋን የምትረግጠው የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት መርዶክዮስ ንግሥት አስቴርን ያሳደጋትና ለንጉሥም ሚስት እንድትሆን ወደ ንጉጮ ያቀረባት ነው ይህ ማለት የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ከርስቲያን ምሳሌ የሆነችውን አስቴርን ያሳደጋት እንዲሁም የክርስቶስ ምሳሌ ከሆነው ከንጉሥ አርጤክስስ ጋር አንድ አካል እንድትሆን ወደ ንጉሥ ያቀረባት መርዶክዮስ ነው በተመሳሳይ መልኩ ስዎችን በወንጌል ማርኮ ወደ ክርስቶስ የሚያቀርበው መንፈስ ቅዱስ ነው እንዲሁም ከክርስቶስ ጋር አንድ አካል እንዲሆኑ የአካል ጥምቀትን የሚያጠምቅ መንፈስ ቅዱስ ነው ቆሮ ስለዚህ የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎት እንደ ጥሳ ወይም ምሳሌ ሆኖ ሲያገለግል እንመለከታለን ይህ ብቻ አይደለም መርዶክዮስ በጣም የታወቀበት ምክንያት የክርስቶስ ምሳሌ የሆነውን ንጉሥ አርጤክስስን ከሞት በማዳኑ ነው በሮሜ መልእክት እንደምንመለከተው ኢየሱስ ክርስቶስን ከሞት ያስነሳው የእግዚአብሔር መንፈስ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ይነግረናል ሮሜ እንዲሁም ደግሞ መርዶክዮስ ንጉሥ አርጤክስስን ከሞት አድኖአል አንተን ንጉሥን ከሞት ያዳነ መርዶክዮስን አስ ስለዚህ ንጉሥ አርጤክስስን ከሞት ያዳነው መርዶክዮስ ኢየሱስን ከሞት ያስነሳው የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው ጃንደረቦች በመጽሐፈ አስቴር ላይ የጃንደረቦችን አገልግሎት ስንመለከት የመጨረሻ ዘመን ምሳሌ የሆነችውን አስቴርን ማገልገልና እርስዋ ለንጉሥ መልካም ሚስት እንድትሆን በነገር ሁሉ መርዳት ነው አስቴር በመርዶክዮስ አማካይነት ንጉ ወዳለበት ቤተ መንግሥት ስትመጣ እርስዋን ለማስተናገድ መጀመሪያ የተቀበሳት ጃንደረባው ነበር ልክ እንደዚሁ በመንፈስ ቅዱስ ኣማካይነት በክርስቶስ ሥራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስንገባ እኛን ለማገልገል ለመጠበቅና በሚያስፈልገን ነገር ሁሉ ስለመርዳት በመጀመሪያ የሚያገኙን መላእክት ናቸው ዕብ ስለዚህ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ጃንደረቦቹ ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግሉ መላእክት ምሳሌ ናቸው ሌላው ጃንደረቦቹ የመላአክት ምሳሌ የሆኑበት አያገቡም አይጋቡም መላአክትም እንዲሁ በተጨማሪም በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ያሉ ጃንደረቦች የንጉሥን ትእዛዝ ብቻ ነው የሚፈጽሙት በሰዎችና በንጉ መካከል ገብተው የሰዎችን ነገር ለንጉ አያቀርቡም ነገር ግን የወጣውን የንጉሠን ትእዛዝ ተቀብለው ንጉጮንና ሕዝቡን ያገለግላሉ በሌላ አገላለጽ መካከለኛ አይደሉም መካከለኛ ሆኖ በቆመው በክርስቶስ ሥራ አገልግሎታቸውን ይፈጽማሉ ሃማን ሃማን የጠላታችን የሰይጣን ምሳሌ መሆኑን ለሁላችንም ግልጽ ነው ነገር ግን የሃማን ጥልቅ የሆነውን ምስጢራዊ አሠራር ማወቅ በጣም አስፈላጊ ነው ይህንን ምስጢር ካወቅን አሁን ቤተ ክርስቲያንን የሚዋጋትን መንፈስ ጠንቅቀን እናውቀዋለን የሃማን ምስጢራዊ የሰይጣን አሠራር በግብጽ ውስጥ በአንድ የመሪዎች መንፈሳዊ ፕሮግራም ላይ ትልቅ የማስተማር ፀጋ ባላቸው በዶር መክዲ በኩል እግዚአብሔር ስለ ክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ ሲያስተምረን ስስ ሃማን ያለኝን እውቀት መንፈስ ቅዱስ በልዩ ልዩ መንገድ ገልጾ አስተማረኝ የሃማን ማንነት ሥራና እንዲሁም አመጣጡን በደንብ ለመረዳት ከመጽሐፍ ቅዱስ የተለያዩ ክፍሎችን ከዚህ በመቀጠል እናያለን ኦግዚአብሔር የራሱ የሆነ ዕቅድ ለፈጠረው ሕዝብ እንዳለው ሁሉ ሰይጣንም የራሱ ዕቅድ አለው የእግዚአብሔር ዕቅድ የሰይጣንን ራስ ቀጥቅጦ ለሕዝቡ ደህንነትን ማውረስ ሲሆን የሰይጣን ዕቅድ ደግሞ የእግዚአብሔርን ዕቅድ ሥራ እውነት በሚመስል ውሸት ማበላሸት ነው እግዚአብሔር ለአዳምና ስሔዋን የሰጣቸውን ዕቅድ ሰይጣን በውሸት ካበላሸሽው በኋላ እግዚአብሔር እንደገና አዳምና ሔዋን የጣሉትን ዕቅድ ለማንሳት ተስፋን ሰጠ ተስፋውም በአንተና በሴቲቱ መካከል ጠላትነት እንዲኖር አደርጋለሁ የእርስዋ ዘርና የአንተ ዘር ዘወትር ጠላቶች እንደሆኑ ይኖራሉ የእርስዋ ዘር የአንተን ራስ ይቀጠቅጣል አንተም የእርስዋን ዘር ተረከዝ ትነክሳለህ ዘፍ የእውነቲኛ ነገር ጥሳዎች ይህም ተስፋ ከሴቲቱ የሚወለድ ማለትም ከአንዱ ትውልድ ወደ ሌሳ ትውልድ እየተሸጋገረ ሥጋን ለብሶ ከድንግል ስለሚወለደው የሰይጣንን ራስ ስለሚቀጠቅጠው ስለ ክርስቶስ የተሰጠ ተስፋ ነበር የእግዚአብሔር ዕቅድ የእባቡን የሰይጣንን ራስ መቀጥቀጥ ነው እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ እውን ለማድረግ ሥጋ የለበሰ ሰው ይፈልጋል እንዲሁ ሰይጣን የራሱን ዕቅድ ማስትም የእግዚአብሔር ዕቅድ በዚህ ምድር እንዳይገለጽ የሚዋጋበትን ሥጋን የለበሰ ሰው ይፈልጋል የእግዚአብሔር ዕቅድ ተስፋ ባለበት ቦታ ሁሉ ሰይጣን ያንን ተስፋ ለማበሳሸት የሚጠቀምበት የራሱ ትውልድ አለው በዘፍጥረት ምዕራፍ እግዚአብሔር ዕቅዱንና ተስፋውን የሚፈጽምበት የእባቡን ራስ የሚቀጠቅጠው ከእርሱ እንዲመጣ አቤልን መረጠ በተመሳሳይ ጊዜ የአግዚአብሔርን ዕቅድ የሚያበላሽና ከምድረ ገጽ የሚያጠፋ የሰይጣን እሠራር በቃየን ተገለፀ ወንድሙንም ገደለ የእግዚአብሔርን ዕቅድ እበላሸ ስለዚህ በዘፍጥረት ሦስት ላይ እባቡ እንደተረገመ ሁሉ ቃየንም ተረገመ የተረገምህ ሁን ወንድምህን በገደልከው ጊዜ አፍዋን ከፍታ ደሙን በጠጣችው ምድር ላይ ተቅበዝበዝ ዘፍ እንደገና ተስፋውንና ዕቅዱን ይዞ እንዲነሳ እግዚአብሔር እብርሃምን መረጠ አብርሃም ከእርሱ በሚወለደው በዘሩ የምድር ሰዎች ሁሉ እንደሚድኑ ተስፋን ተቀበለ ያም ዘር ክርስቶስ ነበረ ገላ ነገር ግን ይስሐቅ ከመምጣቱ በፊት የክርስቶስን ዘር ሊያጠፋ በእጋር በኩል የሰይጣንን አሳብ የያዘ እስማኤል ተወለደ ዘፍ እስማኤል ጦርነትን ማጥፋትን ማበላሸትን የእግዚአብሔርን ዕቅድ ማሳደድ የሚወድ ነበር እግዚአብሔር አብርሃምን ተስፋውን የሚያበላሽ ከተስፋው ልጅ ጋር አብሮ መቀመጥ አይችልምና አጋርን ከነልጅዋ አባርር አለው ባላ አብርሃም እስማኤልን አባረረ ባያባርር ኖሮ ተስፋውን ያበላሽና ይደመስስ ነበር የተወለደው ይስሐቅ የእግዚአብሔር ዕቅድ ተስፋ ማስፈፀሚያ ዘሩ ነበር ስለዚህ ሚስቱ ርብቃ መንታ ልጆችን ፀንሳ ሳስ ገና በማህፀን ሳሉ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እርስ በርሳቸው ይገፋፉ ነበር ይህም ነገር ርብቃን አስጨንቋት በፀለየች ጊዜ እግዚአብሔር በማሕፀንሽ ያሉት ሁለት ሕዝቦች ናቸው እርስ በርሳቸው የማይስማሙ ሁለት ወገኖች ትወልጃለሽ አንዱም ከሌላው የበረታ ይሆናል ታላቁም ለታናሹ አገልጋይ ይሆናል ዘፍ የእግዚአብሔር ቃል ስስነዚህ ሁለት ወገኖች ሕዝቦች ሲነግረን ያዕቆብ በቤት ውስጥ መዋል የሚወድ ጭምት ነበር ኤሳው ግን በዱር መዋል የሚወድ አዳኝ ጦረኛ ነበር ይለናል ኤሳው የእግዚአብሔርን ፅቅድ ይዞ በተነሣው በያዕቆብ ላይ በጠሳትነት ተነሳ ወንድሙንም ሊገድለው ፈለ ምንጊዜም የእግዚአብሔርን ዕቅድ አሳብ ተስፋ ባለበት ስፍራየክርስቶስን ነገር ለማበላሸት ከምድር ሳይ ለማጥፋት ከርስቶስ የሚባል ስሙም ዘሩም እንዳይኖር ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ የመጣ የክርስቶስና የአካሉ የቤተ ክርስቲያን ጠላት አለ ቃየል አስማኤል ኤሳው የሥጋዊ ክርስቲያን ምሳሌዎች ብቻ አይደሉም ነገር ግን የክርስቶስና የአካሉ የቤተ ክርስቲያንን መምጣት የሚቃወም የፀረ ክርስቶስ መንፈስ ምሳሌዎች ናቸወ ከዚህ በኋላ ያለውን ኣሳብ በደንብ ኣድርገን አንመልከት የእግዚአብሔርን ፅቅድ የያዘውን ያዕቆብን ሲያጠፋ የተነሣው ኤሳው ሒታዊያንን አገባዘፍ ይህ ብቻ አይደለም ተስፋ የተቀበለውን ይስሐቅን ሊያጠፋ ከተነሳው ከእስማኤል ልጅ ጋር ተጋባ ዘፍ ከሒታዊያን ሴቶች የዓዳ ከምትባለው ሚስቱ የመጀመሪያ ልጁን ኤልፋዝን ወለደ ኤልፋዝም የጭን ገረድ ከሆነችው ከቲምናዕ ዐማሌቅን ወለደ ስለዚህ ከኤሳው ዘር ኤልፋዝ ተገኘ ከኤልፋዝ ዘር ደግሞ የነገድ አለቆች ነበሩ ከነዚህም ውስጥ ቴማን ኦማር ጸፎ ቀናዝ ቆራሕ ገዕታምና ዐማሌቅ ነበሩ። ዘፍ ከእነዚህ ነገድ ውስጥ የከርስቶስን ሥራ ለማበላሸትና ለመደምሰስ የእግዚኣብሔርን ሕዝብ በምድረ በዳ ለማጥፋት በቃየን በእስማኤልና በኤሳው የነበረው አሳብ በዐማሌቅ ላይ አረፈ ከዚህም በኋሳ ዐማሌቅ የእግዚአብሔር ሕዝብ ዋነኛ ጠላት ሆኖ ተገኘ ሌሎች ነገዶች ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር የሚዋጉበት የተለያየ ምክንያት የነበራቸው ው ር ጥላዎ ሲሆን ዐማሌቅ ግን የእባቡን ራስ የሚቀጠቅጠውን ክርስቶስ የሚመጣበትን ዘር ለማበላሸት ለማጥፋትና በዚህ ምድር ሳይ መታሰቢያ እንዳይኖረው በተለየ መንገድ የሚዋጋ መንፈስ ነበር የእግዚአብሔር ሕዝብ ከግብጽ ከባርነት ቤት ሲወጡ ዐማሌቅ ተዋጋቸው የዐማሌቅ አመጣጡ እስራኤላውያንን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ነበር እግዚአብሔርም በእርሱ ዕቅድ ላይ የወጣ መንፈስ ስለሆነ ዐማሌቅን መታሰቢያ እስከማይኖረው ድረስ እደመስሰዋለሁ አለ ሙሴም ተነስቶ እግዚአብሔር ዐማሌቃውያንን ለዘሳስም ይዋጋቸዋል አለ ዘፀ የዐማሌቅ መንፈስ በግልጽና በስውር ቤተ ከርስቲያንን ስለሚዋጋ እስከ ዛሬ እግዚአብሔር ዐማሌቃውያንን ይዋጋል እግዚአብሔር ሙሴን እንደገና ዐማሌቅን ፈጽሞ ማጥፋት እንዳለበት ትእዛዝ ሰጠው ስለዚህ እግዚአብሔር አምሳካችሁ ምድሪቱን አውርሶአችሁ በዙሪያችሁ ከሚኖሩ ጠላቶቻችሁ ሁሉ በሚያሳርፋችሁ ጊዜ በምድር ላይ ማንም የሚያስታውሳቸው እስኪጠፋ ድረስ ዐማሌቃውያንን ሁሉ ይደምሰሱ ይህን ከቶ አትርሱ ዘዳ እዚህ ሳይ እግዚአብሔር ለሙሴ በማስጠንቀቂያ ቃል ከቶ አትርሱ ብሉታል ምክንያቱም ዐማሌቅ ካልተደመስስ የእግዚአብሔርንዕቅድ ለመደምሰስ ይነሳልና ነው በሳኦል ዘመነ መንግሥትም እግዚእብሔር ፀማሌቅን ለመቅጣት በወሰነ ጊዜ በነቢዩ ሳሙኤል በኩል ለሳኦል ትእዛዝ ሰጠው እግዚአብሔር ዐማሌቃውያንን ለመቅጣት ወስኖአል እስራኤሳውያን ከግብጽ በወጡበት ጊዜ የእነዚህ የዐማሌቃውያን የቀድሞ አባቶቻቸው ተቃውመዋቸው ነበር ሄደህ በዐማሌቃውያን ሳይ አደጋ በመጣል ያሳቸውን ሁሉ ደምስስ ከነሱ ምንም ነገር አታስቀር ወንዶችን ሴቶችን ልጆችንና ህፃናትን ከብቶችን በጎችን ግመሎችንና አህዮችን ሁሉ ግደል ሳሙ እግዚአብሔር ዐማሌቃውያን መታሰቢያ እንዳይኖራቸው ከምድረ ገጽ እንዲጠፉ ይፈልጋል ደግሞም ዐማሌቅን ለዘላለም ለመዋጋት ወስኖአል የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስተያን ሳኦል ግን እግዚአብሔር የሰጠውን ትእዛዝ ሙሉ በሙሉ አልፈፀመም ዐማሌቃውያንን ከምድረ ገጽ አሳጠፋም ነበር የዐማሌቅ ንጉሥ የነበረው አጋግ በሕይወት ማርኮ ሕዝቡን ሁሉ ፈጀ ነገር ግን ሳኦልና ሠራዊቱ የአጋግን ሕይወት አተረፉ እንዲሁም ምርጥ ምርጥ የሆኑትን በጎችና የቀንድ ከብቶች የሰቡ ሠንጋዎችና ጠቦቶችን ከዚህም ጋር መልካም የሆነውን ነገር ሁሉ አላጠፉም እነርሱም ያጠፉት የማይረባውንና የማይጠቅመውን ነገር ብቻ ነበር ሳሙ ሳኦል የእግዚአብሔርን ሥራ የሚያበላሸውን የክርስቶስን መንፈስ የሚቃወመውን ዋናውን የዐማሌቅን ንጉሥ አጋግንና በዐማሌቅ መንፈስ የተያዙ ያልተቀደሱ የቀንድ ከብቶች የሰቡ ሠንጋዎችና በጎችን ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ ወደ ተቀደሰ ምድር አስገባ እንዲያውም ከብቶቹን ለእግዚኣብሔር መስዋእት አድርጎ ሊያቀርባቸው ወደደ በዚህ ምከንያት እግዚእብሔር ሳኦልን በማንገጮ ተጸጽቶ ከንጉሥነት ክብር ሻረው እግዚአብሔር በዐማሌቅ መንፈስ ላይ ከፍተኛ የሆነ አቋም አለው ምክንያቱም ዐማሌቅ በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር ሊያደርጋቸው ባለው ዕቅድ ሳይ የሚወጣና ለማጥፋት የሚነሣ ስለሆነ እግዚአብሔር ደግሞ ዐማሌቃውያንን ወደ ተቀደሰ ስፍራ በሚያመጡ እንደ ሳኦል ባሉ ላይ ወዲያው ነው የውሳኔ ቃሉን የሚያሰማው ሳሙኤልም ሳኦል ወደ ተቀደስ ስፍራ ያስገባውን ንጉሥ አጋግን አምጡልኝ አለ ነቢዩ ሳሙኤልም ለአጋግ እንዲህ አለው የአንተ ሰይፍ ብዙዎች እናቶችን ልጅ አልባ እንዳደረገቻቸው የአንተም እናት ልጅ አልባ ሆና ትቀራለች አለው ከዚህ በኋላ በጌልገሳ በሚገኘው በእግዚአብሔር መሠዊያ ፊት አጋግን ቆራርጦ ጣለው ሳሙ እዚህ ላይ የምንመለከተው ትልቅ የሆነውን የዐማሌቅን ኣሠራር ነው ንጉሥ አጋግ እርሱ ራሱ ዐማሌቅ ነበር የክርስቶስን ሥራ የእግዚአብሔርን ዕቅድ በሚያበላሽ መንፈስ የተያዘ ነበር የእርሱም ሰይፍ ብዙ እናቶችን ልጅ አልባ ያደረገ ነው ብዙ እናቶች ልጆቻቸውን በማሳደግ ሳይ ሳሉ ንጉሥ እጋግ እየመጣ ልጆቻቸውን ከእነርሱ ይነጥቃል ሥራውም ማጥፋትና ማበሳሸት ነውና አማሌቁ ሃማን የቤተ ከርስቲያን ምሳሌ የሆኑትን ያውም ልጆች ያፈሩትን በሰይፍ ያጠፋ እንደነበር ሁሉ ዛሬም ቤተ ክርስቲያንን ፌሬ የእሠነተኛ ነገር ጥላዎች የሚዋጋበት አሠራሩ ሁሉ ተመሳሳይ ነው ይኸውም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አማኞች በመንፈስ ቅዱስ ያፈሩትን ፍሬና ያላቸውን ፀጋ የሚያስጥል የሚነጥቅ የሚገድልና የሚያጠፋ ነው እንግዲህ ከዘፍጥረት ጀምሮ እስከ ሳኦል ዘመነ መንግሥት ዐማሌቅ ምሳሌነቱ ሊገለጥ ያለውን የእግዚአብሔርን ዕቅድ በመቃወም በማፈራረስና በማበላሸት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት የሚነሳውን የሰይጣን አሠራር የሚወክል ነው እንዲሁም በመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን ሳይ የሚወጣው የዚህ መንፈስ ምሳሌ የሆነው ሃማን ላሙኤል የገደለው የንጉሥ አጋግ ዝርያ ነበር ንጉሥ አጋግም ዐማሌቅ ነበር ሃማን የአጋግ ዝርያ ስለሆነ ዐማሌቅ ነው የሃማን አባት ማዳታ ተብሎ የሚጠራው የአጋግ ዝርያ ነበር አስ እና ይላል ስለዚህ በመጽሐፈ አስቴር ጥናታችን ሃማን እንዴት የእግዚአብሔርን ዕቅድ ለማጥፋት እንደተነሣና በመጨረሻም እግዚአብሔር ለዘላለም ስለሚዋጋው በመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የእግርዋ መረገጫ በመሆን መታስቢያ እስከማይኖረው ድረስ ከምድረ ገፅ እንደጠፋ እንመለክታለን ቤተ ክርስቲያን የተጠራችበት የክብር ስፍራ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከዚህ በኋላ ንጉሥ አርጤክስስ በመናገሻ ከተማ በሆነችው በሱሳ በሚኖሩ ሁሉ ለሀብታሞችም ለድኾችም እንደገና ሌላ ግብዣ አደረገ በቤተ መንግሥቱ የኣትክልት ቦታ የተደረገው ያ ግብዣ አንድ ሳምንት ሙሉ ቆየ በዚያም የነበረው አደባባይ ከነጭ ጥጥ በፍታ በተሠሩ ሰማያዊ ቀለም ባሳቸው መጋረጃዎች የተጌጠ ነበር መጋረጃዎቹም ከሐምራዊ በፍታ በተሠሩና የብር ቀለበት በተበጀላቸው ገመዶች በዕብነ በረድ ምሰሶዎች ሳይ ተንጠልጥለው ነበር ከወርቅና ከብር የተሠሩ ድንክ አልጋዎችም ነጭና ቀይ ቢጫና ሰማያዊ ቀለማትን በሚፈነጥቅ የዕብነ በረድ ወለል ላይ ተደርድረው ነበር አንዱ ከሌላው ጋር በማይመሳሰል በልዩ ልዩ የወርቅ ዋንጫ መጠጥ ይታደል ነበር ንጉጮም የቤተ መንግሥቱ የወይን ጠጅ በልግስና እንዲሰጥ አደረገ ለመጠጡም ብዛት ገደብ አልነበረውም ንጉም ማንኛውም ሰው የሚፈልገውን ያህል መጠጣት ይችል ዘንድ ለቤተ መንግሥቱ አገልጋዮች ትዕዛዝ ስጥቶ ነበር አስ ከዚህ በላይ ባለው የመጽሐፈ አስቴር የንባብ ክፍል ውስጥ የተጠቀሱትና ልናያቸው የሚዝባንን ቤተ ክርስቲያን የተጠራችበትን ክብር የሚገልጹ ጠቃሚ እውነቶችን አንድ በአንድ እንመለከታለን ለሀብታሞችና ለድኾች የተዘጋጀ ግብዣ በዘመናችን የሚደረጉ ግብዣዎች ብዙ ዓይነት ባህሪዎች አላቸው ብዙዎቹ ጋባዥች በግብዣቸው ሳይ የሚጠሩት ይጠቅመናል የሚሉትን እንደሆነ ማስተዋል ይቻላል በተለይ በዚህ ዘመን የአሳብ መበላለጥ ጎልቶ በሚታይበት ድብቅ የዘረኝነትና የቀለም ጥሳቻ በሚካሄድበት ሰዎችም የጎሪጥ በሚተያዩበት ዘመን የግብዣ ጥሪዎችም ይህንን ስልፍ ተከትለው በመሄድ ብዙ ልዩነት ያደርጋሱ ብዙ ነገር የተሟላላቸው ናቸው የሚባሉት የዘመናችን ሀብታሞች ነገሥታት እንዲሁም መንግሥታት ግብዣዎቻቸው የቱንም ያህል የተሳካለት ቢሆንም የተሟላ አይደለም ተ ክርስቲያን የተ ራ የንጉሥ አርጤክስስ ግብዣ ግን ከዚህ የተለየ ነበር ምሳሌነቱም በሉቃስ ወንፄዔል እንደተጠቀሰው የራት ግብዣ አዘጋጅቶ ጥሪ ከጠራው ሰው ጋር ይመሳሰላል ኢየሱስ ግን እንዲህ አለው አንድ ሰው ትልቅ የራት ግብዣ አዘጋጅቶ ብዙ ሰዎችን ጠራ ሉቃ ቲ አንዲሁም መንግሥተ ሰማይ ለልጁ ሠርግ ያዘጋጀ ንጉሥ ዝሣ ትመስላለች ማቴ የቀት » መጽሐፈ አስቴር ምዕራፍ ሳይ ንጉሠ ታሳቅ ግብዣ አዘጋጀ የንጌጮን ግብዣ ለድኾችም ለሀብታሞችም የተዘጋጀ ነበር ይህም ጌታ የተናፃረው የመንግሥተ ሰማያት ግብዣ ምሳሌ ነው በዚህ ግብዣ ሳይ ሰው ሁሉ ድኸው ሀብታሙ የተማረውም ያልተማረውም ከቋንቋና ከዘር የተጠራበት ነበር ምክንያቱም የግብዣውን ሁሉን አቀፋዊነት በማስመልከት ሐዋርያው ጳውሎስ ለቲቶ በቲቶ ሳይ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጦአል ብሎት እንደነበር መመልከት ይቻሳል ስለዚህ የንጉሥ አርሔክስስ ግብዣ ሰዎች ሁሉ የተጠሩበት የመንግሥተ ሰማይ ግብዣ ምሳሌ ነው በአትክልቱ ቦታ የተሰወረው ታላቅ ሀብት ጌታ ኢየሱስ ክርሰቶስ ምድር ላይ በተመላለሰበት ጊዜ ለተከታዮቹም ሊያስተውሉት በሚችሉ በአካባቢያቸው ባሉ ነገሮች ምሳሌ እየተጠቀመ ያስተምራቸው ነበር በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ መንግሥተ ሰማያትን በእርሻ ውስጥ ከተሰወረ ሀብት ጋር አወዳድሮ ያስተማረው ትምህርት ከብዙዎቹ መካከል አንዱ ነው ቀጥሉም ኢየሱስ እንዲህ አለ መንግሥተ ሰማይ በአርሻ ውስጥ የተሸሸገውን ሀብት ትመስሳለች አንድ ሰው ይህን ህብት ባገኘ ጊዜ መልሶ ደበቀው ከደስታውም ብዛት የተነሣ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ሄደና ያለውን ሁሱ ሸጦ ያንን እርሻ ገዛ እንደገናም ኢየሱስ እንዲህ አለ መንግሥተ ሰማይ ጥሩ ዕንቁ ለመግዛት የሚፈልግ ነጋዴን ትመስላለች ነጋዴውም እጅግ ክቡር የሆነ ዕንቁ ባገኘ ጊዜ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ያንን ዕንቁ ገዛ ማቴ እንዲሁም ንጉሥ አርጤክስስ በአትክልቱ ስፍራ ያደረገው ታሳቅ ግብዣ ብዙ ሀብትና ክብር ያለበት ስፍራ ጌታም እንዳለው ያለንን ሁሉ የሚያሸጥ የተሰወረ ሀብት በንጉሥ በአርጤክስስ ግብዣ ላይ በአትክልቱ ስፍራ ነበር ከነዚህ ሀብቶች መካከል የመጀመሪያው መጋረጃዎቹ ሲሆኑ እነዚህንም ከዚህ በመቀጠል እንመሰከታቸዋለን ሠ መጋረያዎቻ በዚያም የነበረው አደባባይ ከነጭ ጥጥ በፍታ በተሠሩ ሰማያዊ ቀለም ባላቸው መጋረጃዎች የተጌጠ ነበር አስ በንጉሥ አርጤክስስ የክብር ግብዣ ላይ ከሚገፔት ታላላቅ ሀብት መካከል የመጀመሪያዎቹ በነጭ በሰማያዊና በሐምራዊ ቀለማት ያሸበረቁ መጋረጃዎች ነበሩ መጽሐፍ ቅዱሳችን ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ጥላ ነው ይለናል በአዲስ ኪዳን ክርስቶስ ለሰዎች የፈፀማቸው ድርጊቶችና የሰጣቸው መንፈሳዊ በረከቶች በብሉይ ኪዳን በምሳሌ መልክ የተቀመጡ ናቸው ይህንን ከተረዳን መጋረጃዎቹ የሚያመለከቱት ክርስቶስ ሥጋን ለብሶ መምጣትና ስለአኛ በመስቀል ላይ መሞቱ የሥጋው መቆረስ የደሙ መፍሰስ ወደ እግዚአብሔር ሰማያዊ ክብር የሚያደርሰንን የመስቀሉን ሥራ የዕብራውያን ፀህፊ መጋረጃ ብሎ እንዲህ ሲል ይገልፀዋል እንግዲህ ወንድሞች ሆይ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል አንድንገባ ድፍረት ስላለን ዕብየቀት ቤተ ክርስቲያን የተጠራችበት የክብር ስፍራ በንጉሥ አርጤክስስ ግብዣ ሳይ የነበሩ መጋረጃዎች በነጭበሰማያዊና በሐምራዊ ቀለሞች ያሸበረቁ ሲሆኑ ነጭ ቀለም ምሳሌነቱ ክርስቶስ ጽድቃችን መሆኑን የሚገልጽ ነው ሰማያዊው ደግሞ በክርስቶስ የሚገኝ የሰማያዊ አገር ዜግነት የሰማያዊ በረከት ተካፋዮች መሆናችንን የሚያረጋግጥ ነው በክርስቶስ የሚገኘው ድቅና በረከት ለሰው ልጆች ግልጽ ሆኖ እንዲታይና በዚህም ድቅና ሰማያዊ በረከት ሰዎች እንዲያልፉ እንደ መጋረጃ ሆኖ የተንጠለጠለው ሐምራዊ ቀለም ባላቸው ገመዶች ነበር ሐምራዊ ማለት ደም የሚመስል ቀይ ማለት ሲሆን በምሳሌነቱ በመስቀል ላይ የፈሰሰው የክርስቶስን ደም ያመለክታል እዚህ ሳይ የምንመለከተው ትልቅ ነገር በክርስቶስ አማካኝነት የተገኘው ድቅና ሰማያዊ በረከት ክላይ ወደ ታች ለሰው ልጆች የተንጠለጠለው በክርስቶስ ደም አማካኝነት መሆኑን ነው መጋረጃዎቹ እርስ በርሳቸው እንደተያያዙ የክርስቶስ ደሙ ጽድቅና ሰማያዊ በረከቱ ሁሉም በአንድ ላይ የተያያዙ ናቸው ያለ ደሙ ድቅንና ሰማያዊ በረከትን መውረሰ አይቻልም ስለዚህ ማንም ሰው ወደ ንጉጮ ግብዣ ሲመጣ በመጀመሪያ የሚያገኘው የተሰወረ ትልቅ ሀብት ኃጢአተኝነትና ዓለማዊ ምኞትን የሚያስክድ ከኩነኔና ከመርገም ነፃ በሚያወጣ አቻና ወደር በማይገኝለት በጌታችን በኢየሱስ ደም ታጥቦ መንፃት ነው ቲቶ አንዲሁም የተገባን ሆነን ነጭ ልብስ ለብሰን ከጌታ ጋር ለዘላለም ሊያኖረን የሚያስችለንን የክርስቶስን ጽድቅ መልበስ ሮሜ በተጨማሪም በክርስቶስ የተገኘውን ሰማያዊ በረከት ተካፋዮች መሆን ነው ኤፌ ማንም ሰው እነዚህን መጋረጃዎች ሳያልፍ በንጉሥ የማዕድ ግብዣ ላይ መቀመጥ አይችልም ማቴ እንግዲህ መጋረጃዎቹ በጌታችን በኢየሱስ ደም በእርሱ ድቅ የሰማያዊ አገር ዜጎች የእግዚአብሔር መንግሥት ወራሾች እንድንሆን የሚያበቁን የደሙን መፍሰስ የሥጋውን መቆረስ የሚያመለክቱ የመስቀሉን ምስጢር የያዙ ናቸው ያታሇፕ ያረድ ምፅዕሪዎቻ ምድ መጋረጃዎቹም በሐምራዊ በፍታ በተሠሩ የብር ቀለበት በተበጀላቸው ገመዶች በዕብነ በረድ ምሰሶዎች ላይ ተንጠልጥለው ነበር አስ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን በዚህ ጥቅስ ላይ እንደምንረዳው መጋረጃዎቹ የተንጠለጠሉት በዓምዱ ላይ ነበር መጋረጃውን ማለትም ደሙን ጽድቁንና ሰማያዊ በረከቱን ለሰው ልጆች እንዲታይ ከፍ አድርጎ የያዘው ዓምዱ ነው ይህ ዓምድ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው ጌታ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ስለመንፈስ ቅዱስ ሲገልጽላቸው እርሱ በመጣ ጊዜ ስለ ኃጢአት ስለ ፍርድና ስለ ጽድቅ ሰዎችን ያስረዳል እንዲሁም የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ እኔን ያከብረኛል ዮሐ ስለዚህ ዓምዱ መጋረጃውን ከፍ አድርጎ በማንጠልጠል የክርስቶስን ደም ጽድቅና በእርሱም የሚገኘውን ሰማያዊ በረክት በማሳየት በዚህ ምድር ላይ ክርስቶስን በማክበር ለሰው ልጆች የመስቀሉን ሥራ መግለጥና ማሳየት ነው ሌላው ይህ ዓምድ ቤተ ክርስቲያንን የሚመራ ዓምድ ነው ማንኛውም ሰው ግብዣውን አክብሮ ከመጣ እጅግ ውብና ድንቅ በሆነ በመጋረጃው በኩል በማለፍ ያለ አንዳች ዋጋ እንዲያው በፀጋው መዳን ያገኛል ኤፌ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን በመጋረጃው በኩል ስማለፍ ብቻ የተጠራች ሳትሆን መጋረጃውን ከያዘው ከዓምዱ ፊት ለፊት ልትቀመጥ የተጠራች ናት እስራኤላውያን የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ወይም ጥላ ናቸው እነርሱን በምድረበዳ ቀን በደመና ዓምድ ሌሊት በእላት ዓምድ የመራቸው ዛሬም ቤተ ክርስቲያን በተጠራችበት የክብር ሥፍራ እለ ይህ ዓምድ እንዲሁ ዝም ብሎ ለዕይታ ብቻ የቆመ ሳይሆን ሕያው ሆነው መጋረጃውን አልፈው የገቡትን ሰዎች ለመምራት ፊት ለፊታቸው የቆመ ዓምድ ነው ዓምዱ ቀን በደመና ማድረግ የሚገባንን የሚነግረንና በሌሊት የጠላት አሠራር በበዛበት እንኳ በእሳት እየተገለጠ ሕዝቡን የሚመራ ዓምድ ነው ክሱኮትም ተጓዙ በምድረ በዳውም ዳር በኤታም ሰፈሩ በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና ዓምድ ሊያበራላቸው ሌሊት በእሳት ዓምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ ዘፀ የቀት የደመና ወይም የእሳቱ ዓምድ ሲነሳ የእስራኤልም ሕዝብ እብሮ ይነሳ ነበር ዓምዱ እንድ ቀንም ቢሆን አንድ ወርም ካልተንቀሳቀሰ እነርሱም አይንቀሳቀሱም ነበር ምክንያቱም የሚመራቸው ዓምድ ከፊት አሕ ክርስቲያን የቲጠራችበት የክብር ስፍራ ለፊታቸው ያለውን ነገር ሁሉ የሚያውቅ ነበርና ይህ ዓምድ የቤተ ክርስቲያን ክብርዋና ጌጥዋ ነው ቤተ ክርስቲያን ክብር አላት ጌጠኛም እንድትሆን ተጠርታለች በተጨማሪም የገሃነም ደጆች የማይቋቋሙዋት ጠንካራም ነች እንግዲህ የቤተ ክርስቲያን ክብሯ ጌጧና ጥንካሬዋ ከፊት ለፊት የቆመው ዓምድ ነው መጋረጃውን ካለፍን በኋላ በዓምዱ ፊት ለፊት ስንቀመጥ ከዓምዱ በሚወጣው እሳታማዊ ነፀብራቅ ቤተ ክርስቲያን ከክብር ወደ ክብር የምትለወጥ ናት እንጂ የዚያን ይሻር የነበረውን መጨረሻ ትኩር ብለው የእስራኤል ልጆች እንዳይመለከቱት በፊቱ መጋረጃ እንዳደረገው እንደ ሙሴ አይደለንም የአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ጌታ በመረቀላት በአዲስና በሕያው ጎዳና ምህረቱንና ማለቂያ የሌለውን የጌታን ክብር ትኩር ብላ የምትመለከት ናት ሜታ ግን መንፈስ ነው የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ አርነት አለ እኛ ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያንን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን ቆሮ የቀት በግብዣው ላይ የቆመው ዓምድ ከሚያንፀባርቀው ክብር የተነሣ ቤተ ክርስቲያን ዕድፈት የፊት መጨማደድና ነውር የሌለባት ክብርትና ጌጠኛ እንድትሆን ያደርጋታል ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በተጠራችበት የግብዣ ስፍራ ያለው ሌላው ትልቅ ሀብት ቀን በደመና ሌሊት በእሳት ዓምድ የሚመራ በእሳት የሚናገር በእሳት የሚያሻግር እንዲሁም ክብርዋ ጌጥዋ ጥንካሬዋ የሚሆናት አመፅንም ከመካከልዋ የሚያስወግድ እሳታማዊ ዓምድ ነው ጋ ያወረቀና ዖሇረ ድዕ ልልጋዎቻ ከወርቅና ከብር የተሠሩ ድንክ አልጋዎችም ነጭቀይቢጫና ሰማያዊ ቀለማትን በሚፈነጥቅ የዕብነ በረድ ወለል ላይ ተደርድረው ነበርአስ ቤተ ክርስቲያን እንድታርፈበት የተዘጋጀላት የክብር አልጋ ከእንጨት ወይም ከገመድ የተሠራ አይደለም ቤተ ክርስቲያን ከወርቅና ከብር በተሠራ አልጋ እንድታርፍ ተጋብዛለች በጥንት ጊዜ በእስራኤል ድኾች የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከነልብሳቸው መሬት ላይ ይተኙ ነበር ሀብታሞች ደግሞ ከእንጨት ከሰሌን እንዲሁም ከተለያየ ቆዳ በተሠሩ አልጋዎች ይተኙ ነበር የእስራኤል ልጆች ከግብጽ ከወጡ በኋላ ምድሪቱን በመውረር ላይ አያሉ ካስደነቃቸው ነገር አንዱ የብረት አልጋ ያለው ንጉሥ ማግኘታቸው ነበር ዘዳ ነገር ግን ወደ ንጉሥ ግብዣ የተጠሩ ድኾችም ሀብታሞችም ነበሩ በዘመናቸው ሁሉ በወርቅ አልጋ ላይ ተኝተው አያውቁም ንጉሠ ወደ ግብዣው ሲጠራቸው ግን በወርቅና በብር አልጋ ላይ ሊያሳርፋቸው ነበር በተመሳሳይ መልኩ ለቤተ ክርስቲያን ዕረፍትን ሊሰጥ የተገለጠው ጌታ ጥሪውን በማቴዎስ ወንጌል እንዲህ እያለ ይገልፃል እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ ማቴ የቀት ድንኩን የወርቅ አልጋ ለቤተ ክርስቲያን ያዘጋጀላት ጌታ እራሱ ነው ነገር ግን በመኃመኃ ላይ ንጉሥ በድንኩ አልጋው ላይ ዐረፍ ብሎ ሳለ የሽቶዬ መዓዛ ቤቱን ሁሉ ሞላው እዚህ ላይ የምንመለከተው ድንኩ አልጋ የንጉሥ ማረፊያም እንደሆነ ነው መጽሐፍ ቅዱሳችን ቤተ ከርስቲያንን እንደ ሴት ሚስት ከርስቶስን ባል አድርጎ ይመስለዋል ከዚህ የተነሣ ቤተ ክርስቲያን በድንኩ የወርቅ አልጋ ሳይ ብቻዋን ልታርፍ ሳይሆን የተጠራችው ካሳረፋት ጌታ ጋር ጊዜ የምትወስድበት የእርሱን ማንነት የምትረዳበት ከእርሱ ጋር በመዋል እርሱን የምትመስልበት የክብር አልጋ ነው እዚህ ላይ ትልቅ የምንረዳው ነገር ቢኖር ንጉሠ በወርቅ ድንክ አልጋ ላይ ከእርስዋ ጋር ሲያርፍ ነው ከእርስዋ የሚወጣው መዓዛ ቤቱን የሚሞላው በሌላ አገላለጽ ቤተ ከርስቲያን ብቻዋን ያለ ንጉሠ የሽቶዋ መዓዛ ቤቱን አይሞላም አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት የሽቶአቸው መዓዛ የማይወጣው ከወርቁ አልጋ ርቀው በራሳቸው አልጋ ላይ ብቻቸውን ስላረፉ ነው ከንጉሥ ጋር ጊዜዋን የማታሳልፍ ቤተ ክርስቲያን የእርሱን አሳብ የማትረዳ ራእይ የሌላት የክርስቶስን መዓዛ የማትሸት ከማረፍ ይልቅ የተኛችና ያንቀላፋች ድምፁንም የማትስማ ነች ቤተ ከርስቲያን በወርቁ ተ ብር ስፍ አልጋ ላይ ስታንቀላፋ የምታስማው ድምፅ በቃኝ ጠግቤአለሁ ሀብታምም ሆኛለሁየሚጎድለኝ ምንም የለም ያለኝም ይበቃኛል የሚል ነው ነገር ግን ግብዣው የተዘጋጀላት በወርቁ አልጋ ላይ ከንጉሠ ጋር አርፋ ሰማያዊውን ራእይ እየተቀበለች ከርስቶስን በመምስል የጌታን ክብር እንድታንፀባርቅና ሰማያዊውን ምስጢር እንድትገልጥ እንጂ ብቻዋን በአልጋው ላይ በመቀመጥ ምንም የሌላት ምስኪን እንድትሆን አልተጠራችም እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን ያገኘችው ሌላው ሀብት ከንጉሠ ጋር በአንድነት የምታርፍበት የወርቁ አልጋ ባለቤት መሆን ነው መ ዖሟፈቀንዎፖቅ ፇሐማፖታ ያፋሦ መሠረታ ከወርቅና ከብር የተሠሩ ድንክ አልጋዎችም ነጭና ቀይ ቢጫና ሰማያዊ ቀለማት በሚፈነጥቅ የዕብነ በረድ ወለል ላይ ተደርድረው ነበር አስ በዚህ ክፍል ላይ ቤተ ክርስቲያን በወርቁ አልጋ ላይ ያረፈችው ልዩ ልዩ ቀለማትን በሚፈነጥቅ ዕብነ በረድ ወለል ላይ ነበር ወይም አልጋዎቹን የተሸከመው ልዩ ልዩ ቀለማትን የሚፈነጥቅ የዕብነ በረድ መሠረት ነበር ይህንን ከፍል ከዮሐንስ ራእይ ጋር ስናስተያየው ኛ መሠረቱ የወርቁን አልጋ እንደተሸከመ እንዲሁም በራእይ መጽሐፍ ላይ እንደተገለፀው የወርቁን መቅረዝ የተሸከመው ከክርስቶስ ነው መሸከሙን የምናውቀው በቁጥር ሃያ ላይ በቀኝ እጄ ያየሃቸው የስባቱ ከዋክብት ና የሰባቱ የወርቅ መቅረዝ ምስጢር ይህ ነው ና የሚለው አያያዥ ቃል ሁለቱንም እንደያዛቸው ይገልፅልናል ኛ አልጋውን የተሸከመው የዕብነ በረድ ወለልመሠረቱ የተለያየ ቀለማትን እንደሚፈነጥቅ ሁሉ እንዲሁም በራእይ ። ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብ ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ ኢሳ የቀት ንጉሥም ማንኛውም ሰው የሚፈልገውን ያህል መጠጣት ይችል ዘንድ ለቤተ መንግሥቱ አገልጋዮች ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር አስ በግብዣው ላይ ግዴታ የለም ማንኛውም ስው ለመጠጣት ፈቃደኛ ከሆነ መጠጣት ይችላል ከጠገበም ማቆም ይችላል ነገር ግን ሰው አስከፈለገው ድረስ ነውና ገደብ የለውም እግዚአብሔር ከመዐዱ በግድ አያጎርስንም እጃችንን ሰንዝረን መብላትና መጠጣት የእኛ ድርሻ ነው እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና ዮሐ እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን የተጠራችበት የክብር ስፍራ አላት በዚህም የክብር ስፍራ እጅግ ውብና ውድ የሆነ የተሰወረ ሀብት እንዳለና ቤተ ክርስቲያን የዚህ ሀብት ወራሽ እንድትሆን የተጠራች እንደሆነች አንድ በአንድ ተመልክተናል እነዚህ አሳቦች ለሚቀጥለው ትምህርታችን በጣም ጠቃሚ ስለሆኑ የምዕራፍ ሁለት አሳቦችን አንደያዝን ወደሚቀጥለው እንሄሂዳለን ምዕራፍ ሦስት ከክብር የጎደለችው ቤተ ክርስቲያን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ይህ ኗ ፇደ ቤተ ክርስቲያን በመንፈሳዊ አገሳለጽ የክርስቶስ ሚስት ተብላ እንደምትጠራ መጽሐፍ ቅዱሳችን ይነግረናል እንዲሁም ንጉሥ አርጤክስስና ንግሥት አስጢንም የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናቸው ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ሚስት ተብላ ልትጠራ የምትችለው ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን ባዘጋጀላት የመስቀሉ ሥራ ካለፈች በኋላ ነው እንዲሁም ንግሥት አስጢን የንጉሥ ሚሰት ስለሆነች ንጉሥ ባዘጋጀው የግብዣ ቦታ ያለፈች ነበረች ማለትም በመጋረጃው በዓምዱ በድንክ አልጋው በሚፈነጥቅ የዕብነ በረድ መሠረት በንጉሥ የወርቅ ዋንጫ በልግሥናውና ገደብ በሌለው በረከት ውስጥ ያለፈች ነበረች ከዚህ የተነሣ ንግሥት አስጢን እጅግ ውብ ነበረች ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ሥራ ላይ በበዓለ ኀምሳ ቀን በምድር ላይ በመንፈስ ቅዱስ ከተመሠረተች በኋላ በሚያስደንቅና ታላቅ በሆነ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ያዳናትን ጌታ ክብሩን በመግለጥና በማሳየት የተሰጣትን የወንጌል አደራ በሚገባ ተወጥታለች ክዚያም ቤተ ክርስቲያን ቀስ በቀስ ዓለማዊ ምኞትንና አሠራርን ወደ ውስጥዋ በማስገባት በተለይ በ ዓም ገደማ ፍፁም ከወንጌል እውነት ወጥታ በጨለማ ትመላለስ እንደነበር ከታሪክ መረዳት ይቻሳል እንዲሁም እጅግ ወብ የነበረችው ንግሥት አስጢን እንዴት ንጉሥ ካዘጋጀላት የክብር ግብዣ እንደተንሸራተተችና ከወንጌል እውነት እርቃ ከክብር የጎደለች አንደሆነች የዚህም አስደናቂ የሆነውን ምስጢር የያዘውን የእግዚአብሔር ቃል እንዴት ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስ ካዘጋጀላት ክብር ወይም ሙሳት እንደጎደለች በማነፃፀር እንመለክታለን ይህ በዚህ እንዳለ ንግሥት አስጢን ደግሞ በበኩልዋ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ለሴት ወይዛዝርት ግብዣ አድርጋ ነበር ግብዣው በተጀመረ በሰባተኛው ቀን ንጉሥ አርጤክስስ በወይን ጠጅ ረክቶ ደስ ባለው ጊዜ አስ ከላይ ባለው ጥቅስ መጀመሪያ ላይ ይህ በዚህ እንዳለ የሚለው ቃል ከቁጥር ዘጠኝ በላይና ከቁጥር ዘጠኝ በታች ያለውን አሳብ ያገናኘ ነው ይህ በዚህ እንዳለ ሲል ቤተ ክርስቲያን የተጠራችበት ክብር መጋረጃው የደመናውና የእሳት ዓምዱ የወርቅና የብሩ አልጋ የወርቁም ዋንጫና የንጉሥ ልግስና እንዳለ ማለቱ ነው ጌታ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ሰባዎቹ ደቀመዛሙርት ለአገልግሎት ልኮ ተመልሰውም በእነርሱ መካክል ምን እንደተሠራ ነገሩት ይህን በሰማ ጊዜ ሥልጣን እንደተቀበሉ ስማቸው በሰማያት እንደተፃፈ አይቶ በዚህ ስዓት በመንፈስ ቅዱስ ሐሜት አደረገና የሚል ቃል እናገኛለን ሉቃ በተመሳሳይ ሁኔታ ይህ በዚህ እንዳለ ግብዣው በተጀመረ በሰባተኛው ቀን ንጉሥ እርጤክስስ የቤተ ክርስቲያን ክብርና የተደረገሳትን ልግሥና በመመልክት የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ በሆነው በወይን ጠጅ ሐት ባደረገ ጊዜ ንግሥት አስጢን ልብሰ መንግሥትዋን ለብሳ ዘውዷን ጭና ባጠገቡ እንድትቀመጥ ፈለገ ንጉሠ ይህን ያደረገው ንግሥት ኣስጢን እጅግ የተዋበች ስለነበረች ለባለ ሥልጣኖችና ለእንግዶች እንድትታይ ፈልጎ ነበር እርስዋ ግን ወደ ንጉሠ ለመቅረብ እምቢ አለች እምቢ ያለችበት ምክንያት ለብቻዋ መክበር ስለፈለገች ነበር ለብቻዋ ለመክበር ፈለገች ይህ በዚህ እንዳለ ንግሥት አስጢን ደግሞ በበኩልዋ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ለሴት ወይዛዝርት ግብዣ አድርጋ ነበር እስ በዚህ ጥቅስ ላይ በበኩልዋ የሚል ቃል እናገኛለን ይህ ማለት የንጉሥ የክብር ግብዣ እያለ ንግሥት አስጢን ደግሞ በበኩልዋ በራስዋ ፈቃድ ለብቻዋ ንጉሥ አርጤክስስ በሌለበት ስፍራ እራስዋን ለማክበር በበኩልዋ ግብዣን አዘጋጀች የንጉሥንም ግብዣ ናቀች ባሏ ክብርዋ እንደሆነ ዘነጋች በንጉሥ ክብር ሳይሆን በራስዋ ኃይልና ብርታት መመካት ጀመረች ሰው ያደረጋትን የንጉሠን ምህረትና ቸርነት ረሳች የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርሰቲያን ን ኢእ ሙሙ ቷ ሙ በንጉሠ የወርቅ ዋንጫ ሳይሆን በራስዋ ጣሳ ማስተዋል ጥበብና እውቀት ግብዣን አዘጋጀች እንደ ሎዶቅያም ህብታም ነኝ ባለጠጋም ሆኛለሁ አንድስ እንኳን አያስፈልገኝም ያለኝ ይበቃኛልየምትል ሆነች ነገር ግን ያለ ክርስቶስ ክብር ስለሌለ ደኻ የተራቆተችምስኪንዕውር ጎስቋላ መሆንዋን የረሳች ነበረች በመጽሐፍ ቅዱስ የተፃፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፈዋልና ዛሬም ቢሆን እንደ ንግሥት አስጢን በአምሳካቸው ተደግፈው ሳይሆን በራሳቸውና ባሳቸው ነገር በመመካት ከንጉሠ ክብር እየተንሸራተቱ ያሉ ሎዶቅያዊ ሕይወት ያላቸው አብያተ ክርስቲያናት ብዙ ናቸው ንግሥት አስጢን በበኩልዋ ግብዣን ያዘጋጀችው ለሴት ወይዛዝርት ነበር ለሴት ወይዛዝርት ግብዣን ያደረገችበት ምክንያት በሴት ወይዛዝርት ዘንድ ሙገሳን ክብርና ዝናን ፈልጋ ነበር የንጉን ዕቅድ ከማድረግና ከመክበር ይልቅ የወይዛዝርትን ሙግሳ የምትፈልግ የአስጢን ዓይነት አመለካከት ወይም ፍልስፍና ያሳት ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ከመስመር የወጣች አንድም የምታውቀው የሴሳት ፍፃሜዋም እጅግ አሳዛኝ ነው ሌላው በበኩልዋ ግብዣን ያደረገችው የንጉሠን ክብር ሳይሆን የራስዋን ክብር አመለካከትና ሥርዓት በሴት ወይዛዝርት መካከል ስማንፀባረቅ ፈልጋ ነበረ የንጉሥን የክብር ጥሪ እምቢ ያለችው ልክ እንደ ንግሥት አስጢን በተመሳሳይ ሁኔታ በመካከለኛው ዘመን ከወንጌል እውነት ወጥታ ከክብር የጎደለችው ቤተ ክርስቲያን ንጉሠን ፊት ለፊት እያየች በእውነትና በመንፈስ ማምለክንና ማገልገልን ትታ በወግና በሃይማኖት ቀንበር ብቻ የምትመላለስ ቤተ ክርስቲያን ሆነች ከንጉሙ በምታገኘው ፀጋ ሳይሆን በዚህ ዓለም ጥበብና ማስተዋል ማገልገልን ፈለገች በዘመናችን አገላለጽ ብንገልፀው ከወግና ከሥርዓት ዩኒቨርስቲ ተመርቃ የወጣች ከአሥር ደቂቃ በላይ መስበክ የማትችል የስብከት አቋቋምና የማይክራፎን አያያዝ ሥርአት ያላት ለሰዎች ጆሮ እንዲስማማ የስብከቱ ተረትና ቀልድ መሆን አንዳለበት የምታምን ሰዎች ከቤተ ክርስቲያን እንዳይቀሩ ጠንክር ያለ ትምህርት መስጠት የማትችል ወዘተ ከንጉሠ ርቃ በበኩልዋ ግብዣን ባዘጋጀችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትልቅ ቦታ ያዘ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ያልተለማመደችውን ዓለማዊ ምኞትና ጥበብ ንግሥት አስጢን ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስገባች ከዚህ የተነሣ ስም ብቻ ያላት ነገር ግን የሞተች ሆነች ራእ ዘውዷን ለመጫን እምቢ አለች የንግሥት ኣስጢን ጥሪና እምቢታ ከዘመናችን ቤተ ክርስቲያን ጥሪና እምቢታ ጋር ተመሳሳይ ነው የንጉሠ ፍላጎት ቤተ ክርስቲያን በተዘጋጀላት ክብር ውስጥ ብቻ እንድትሆን ሳይሆን ከዚህ በበለጠ ክብርና ውበት ደምቃ ከጎኑ እንድትቀመጥ ከፍ ከፍም ብላ እንድትታይ ንግሥተ አልባሳትዋንና ዘውዷን ጭና በጣም አሸብርቃና ደምቃ ወደ ሙላቱ እንድትደርስ ፈልጎ ነበር ይህንንም ያደረገበት ምክንያት በጣም ውብ ስለነበረች ነው ንጉጮ ይህንን ያደረገበት ምክንያት ንግሥት አስጢን እጅግ የተዋበች ስለነበረች ባለሟሎች ለሆኑት ባለ ሥልጣኖችና ለእንግዶቹ ሁሉ እንድትታይ ፈልጎ ነበር አስ ንግሥት አስጢን ገና የእምቢታ ድምፅ ከማሰማትዋ በፊት በንጉሥ ዘንድ እጅግ የተዋበች ነበረች ነገር ግን ውበትዋ ከራስዋ የመነጨ ሳይሆን በንጉሥ ግብዣ ላይ ካለው ዓምድ እንዲሁም የተለያዩ ቀለማት ካለው ከመሠረቱም ከሚፈነጥቅ ውበት የተነሣ እጅግ የተዋበች ነበረች የኣዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን በመካከለኛው ዘመን ከእውነት መንገድ ከመውጣትዋ በፊት እጅግ የተዋበች ነበረች ለዚህ እውነት ከመጽሐፍ ቅዱሳችን የሐዋርያት ዘመን ቤተ ክርስቲያን ማየት ይቻላል ቤተ ክርስቲያን እጅግ የተዋበች ነበረች ስንል ምን ማለታችን ነው። እንግዲህ መልካም ፈቃድህ ቢሆን ንግሥት አስጢን ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ ፊት መቅረብ ከቶ አንዳይፈቀድላት የሚገልጥ ውሳኔህን በዐዋጅ አስተሳልፍ ይህም ውሳኔ ከቶ የማይለወጥ ሆኖ ለዘላለም ይጸና ዘንድ በፋሪስና በሜዶን ሕግ ውስጥ እንዲመዘገብ ትእዛዝ አስተሳልፍ የአስጢንንም የንግሥነት ማዕረግ ከእርስዋ ለተሻለች ለሌላ ሴት ስጥ አስቴ ስለዚህ ንግሥት አስጢን የእውነት ዓምድና መሠረት ባለበት የአግዚአብሔር ማደሪያ በሆነው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሆንዋን በመዘንጋት በራስዋ እመለካክት በሴት ወይዛዝርት ለመክበርና ለመሞገስ በመፈለግ ለንጉጮ የዘውድ መጫን ጥያቄ እምቢ አልፈልግም አልታዘዝም በማለትዋ ልክ የመካከለኛዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ክወንጌል እውነት ፍፁም ወጥታ ከክርስቶስ ተለይታ የሞተች እንደነበረች ንግሥት አስጢንም እምቢ በማለትዋ የንግሥነት ክብርዋ ተገፈፈ ከንጉሠ የተለየች ሙት ሆነች ንግሥት አስጢን ዘውዷን ለመጫን እምቢ ስትል ንጉሥ የአርሱን ክብር የምታንፀባርቅ ሌሳ ሴት ስለሚያስፈልገው የአስጢንን የንግሥነት ማዕረግ ክአርስዋ ለተሻለ ለሌላ ሴት እንዲስጥ ተወሰነ የተሻለ የሚለው ቃል በጣም አስፈላጊ ነው የተሻለ ማለት ለምሳሌ ከመገናኛዎች ውስጥ ስልክን ብንወስድ ከዚህ ቀደም ከነበረው የስልክ መገናኛ አሁን ያለው የስልክ መገናኛ እጅግ የተሻለ ነው ከዚህ ቀደም የነበረው የስልክ መገናኛ ማገናኘት ያገናኛል ድምፅንም ያስተሳልፍ ነበር ነገር ግን እንደ አሁኑ ዘመን የተቫለ አልነበረም አሁን ያሉት የስልክ መገናኛዎች በፊት ከነበሩት የስልክ መገናኛዎች የተሻሉና ላቅ ያሉ ናቸው በመጀመሪያ ክነበሩ የስልክ መገናኛዎች አንዱ በማዞሪያ የሚደወልባቸው ነበሩ ከዚያ የተሻሉ በመምጣታቸው አሁን በየትኛውም ስፍራ ይዘናቸው መጓዝ የምንችል ተንቀሳቃሽ የስልክ መገናኛዎች ተሠርተዋል ከዚህም አልፎ አሁን ዓለማችን የኢንተር ኔት የስልክ መገናኛዎች ላይ ደርሳለች የኢንተር ኔት የስልክ መገናኛዎች ከመጀመሪያው ስልክ ጋር ስናወዳድራቸው ልዩነታቸው ቃል አስሰከምናጣለት ድረስ በዓይነትም በክብርም በሞገስም በሁሉም ነገር የተሻሉ ናቸው የእግዚአብሔር ቃል ስለመጀመሪያውና ስለመጨረሻዋ ዘመን የቤተ ክርስቲያን ክብር ሲነግረን ከፊተኛው ቤት ክብር ይልቅ የኋለኛው ቤት ክብር እጅግ ይበልጣል የተሻለ ነው ሐጌ ስለዚህ ከንግሥት አስጢን አጅግ የተሻለች ሌላ ሴት አለች ንግሥት አስጢን ክብርዋን የጣለችው ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነች ነገር ግን በክብርም በሞገስም በዓይነትም ከንግሥት አስጢን የተሻለች የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን አለች አንዳንድ ሰዎች ያሉበት የኢንተር ኔት የመገናኛ ዘመን እንደሆነ አያውቁም ምኞታቸውና ራእያቸው ዛሬም በማዞሪያ ስልክ መጠቀም ነው የበፊተኛው ቤት ክብር ስንል የብሉይ ኪዳን የፊደልና የሕግ አገልግሎት ማለታችን አይደለም የምገልፀው ስለ እዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ነው የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሁለት ላይ የተመሠረተችና በታላቅ ክብር የተመላለሰች ነበረች ከዚያም በመካከለኛው ዘመን ክርስትና የመንግሥት ሃይማኖት ሆኖ ቤተ ክርስቲያን በባህልና በሃይማኖት ቀንበር ተይዛ ከክብር የጎደለችውን የመካከለኛዋን ዘመን ቤተ ክርስቲያን አጠቃሎ ማለት ነው ነገር ግን ከእሁን በኃላ የምናያት የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ክብርዋ ሞገስዋ ቅባትዋ አገልግሎትዋ አንደ ኢንተር ኔት ቴክኖሎጂ እጅግ የተሻለ ነው በመሆኑም አንባቢያን ሊያስተውሉት የሚገባ ነገር ቢኖር ከመንፈሳዊ ማዞሪያ የስልክ መገናኛ አገልግሎት ወጥተው ወደ መንፈሳዊ ኢንተር ኔት የተሻለ አገልግሎት መድረስ እንደሚችሉ ነው ስለዚህ በሚቀጥለው ምዕራፍ ለንጉሥ የመጣችውን በነገር ሁሉ ከንግሥት አስጢን የተሻለችውን የንግሥነት ዘውዷን ለመድፋት ወደ ንጉሠ የቀረበችውን የተሻለችውን ሴት ሁኔታ እንመለከታለን ምዕራፍ አራት የተሐድሶ ሥራ በመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን መጀመር የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የተሐድሶ ዘመን ዘግየት ብሎ የንጉሥ ቁጣ ከበረደ በኋላ እንኳ ንግሥት አስጢን ሰላሳደረገችው ነገርና በእርስዋም ላይ ስለተላለፈው ዐዋጅ ማስላስሉን ቀጠለ ስለዚህ የንጉሠ የቅርብ አማካሪዎች ከዚህ የሚከተለውን አሳብ አቀረቡለት ውብ የሆኑ ወጣት ልጃገረዶች ለአንተ ይፈለጉልህ በንጉሠ ነገሥትህ ግዛት በየአገሩ ባለ ሥልጣኖችን በመሾም ውብ የሆኑትን ልጃገረዶች እየመረጡ መናገሻ ከተማ በሆነችው በሱሳ ውስጥ ለአንተ የተመረጡ ሴቶች መኖሪያ ወደ ሆነው ቤት እንዲያመጡዋቸው ይደረግ የዚህም ቤት ኃሳፊ ባደረከው በጃንደረባው በሄጋይ ቁጥጥር ሥር ይጠበቁ የጐንጅናም ክብካቤ ይደረግላቸው ከእነርሱም መካከል በይበልጥ የምትወዳትን መርጠህ በአስጢን እግር ተተክታ ንግሥት እንድትሆን አድርግ አስ ከላይ ባለው ጥቅስ መጀመሪያ ላይ ዘግየት ብሎ የሚል ቃል እናገኛለን ይሀ ማለት በንግሥት አስሰጢንና በንግሥት አስቴር መካከል የሦስት ዓመት ልዩነት ነበር ንጉሥ አርጤከስስ ለእርሱ የምትሆነውን የተሻለችዋ ሴት እስክትገኝለት ድረስ የሦስት ዓመት የዝምታ ጊዜ አሳልፎአል ወይም ሦስት ዓመት ዘግየት ብሎ ነበር እንግዲህ ይህ ዘግየት ብሎ የሚለው ቃል የአስጢን የንግሥናዋ ማዕረግ ከተገፈፈበት ጀምሮ ሌላ የተሻለች ሴት ለንጉሠ እስከተገኘችበት ድረስ የጊዜ ገደብ እንዳለ የሚያመለክት ቃል ነው ይህ ቃል በቤተ ከርስቲያን ታሪክ ውስጥ ተፈጽሞ እናገኘዋለን ጌታ ኢየሱስ መጥቶ ለእስራኤላውያን እሰከታየበት ጊዜ እስራኤላውያን የአራት መቶ ዓመታት የዝምታ ጊዜ አሳልፈው ነበር እንዲሁም ቤተ ከርስቲያን ሙሉ በሙሉ ከወንጌል እውነት ከወጣች በኋላ ማርቲን ሉተር የመጀመሪያውን የደህንነት ተሐድሶ እስከ ጀመረበት ጊዜ ድረስ ቤተ ክርስቲያን የ ዓመታት የዝምታ ጊዜ ወይንም የጨለማ ዘመን እንዳሳለፈች ይነገራል በዚህ ጊዜ ብዙ የጠሳት አሠራር ወደ ሞተችው ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ቦታ ያዘ ሙት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ያስተናገደችው የጠላት አሠራር ውጤት እስከ እሁን ድረስ በመታደስ ላይ ነው ገና ሙሉ ለሙሉ ቤተ ከርስቲያን መታደስን አሳገኘችም ሙሉ ለሙሉ የቤተ ክርስቲያን መታደስ ሲፈፀም የዛን ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ይመጣል ስለዚህም ነው ሐዋርያው ጴጥሮስ በሐዋርያት ሥራ ሳይ እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልናያለው ሐሥ የቀት ጌታ ኢየሱስ ያለና የነበረ የሁሉም ነገር መጀመሪያ ነው በምድራዊው የአገልግሎት ጊዜው ሥጋን ለብሶ እንደተገለጠ ከዚያም ሥራውን ከፈፀመ በኋላ ለስዎች ስጦታን ሰጥቶ ወደ ሰማይ እንደ ዐረገና በአባቱም ቀኝ እንደተቀመጠ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ነገር ግን ጴጥሮስ ሲናዢ ክርስቶስ ወደ ሰማይ የወጣው ስማይም የተቀበለው ሁሉ ነገር እስከሚታደስበት ዘመን ነው ይስናል ስለዚህ ጴጥሮስ በትንቢት መንፈስ ሊመጣ ያለውን ስለ ቤተ ከርስቲያን የመታደስ ዘመን ነው የተናገረው ከዚህ የትንቢት ቃል የተነሣ ያለንበት ይህ ዘመን ሁሉ ነገር የሚታደስበት ዘመ ው በሐዋርያት ሥራ ላይ ያለው ጴጥሮስ የተጠቀመበት ቃል ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት የሚለው ትክክለኛ አገላለጽ አንድ የነበረን ነገር ነገር ግን በአንድ አጋጣሚ የተበላሸን ያንን የተበሳሸን ነገር እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ማደስ መሥራትና መገንባት የሚለውን ቃል ትርጉም ይሰጠናል እግዚአብሔር ሁሉንም በሚያውቀው እውቀቱ የመካከለኛውን ዘመን ቤተ ከርስቲያን ያውቃት ስለነበር በጴጥሮስ አፍ ከዚያን ዘመን በኋላ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት በማለት ገለፀው እዚህ ላይ ነገር ሁሉ የሚል ቃል አለ ሁሉ በሚለው ቃል መሠረት ሁሉም ነገር እንደሚታደስና ሳይታደስ የሚቀር ነገር እንደሌለ ያመለክታል በሌሳ አገሳለጽ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነገር ሁሉ ሳይታደስ ጌታ ኢየሱስ አይመጣም ጌታ ኢየሱስ መምጣቱ ስለማይቀር ደግሞ ሁሉ ነገር ይታደሳል ከዚህ የተነሣ ቤተ ክርስቲያን በመካከለኛው ዘመን ከወንጌል እውነት ሙሉ በሙሉ ወጥታ ሃይማኖታዊ መልክ ብቻ ይዛ ለብዙ ዝመን ከኖረች በኋላ በ ዓም የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ማርቲን ሉተር ታላቁን ተሐድሶ በመባል የሚታወቀውን መዳን የሚገኘው በአምነት እንደሆነ በመግለጥ የመጀመሪያ የደህንነት ተሐድሶ ተጀመረ ከዚያም በየዘመናቱ ተሐድሶን ያገኙትን የእግዚአብሔር ቃል እውነቶችን ከዚህ በታች እንመለከታቸዋለን ተሐድሶ የተገኘባቸው አማካኝ ዓም እኤአ እና መታደስን ያገኙ የቃሉ እውነቶች በ ሰው የሚፀድቀው በእምነት እንደሆነ በ ። የሐዋርያትና የነቢያት ቅባት መነሣትና ይህንንም ቅባት ተጠቃሚ የሚሆኑ ሰዎች መነሣት በ ሽ የነቢያትና የሐዋርያት ቅባት እየተስፋፋ መሄድ አቋሟ የተስተካከለ ቤተ ክርስቲያን ቀደም ብለን አንዳየነው ከዝምታ ጊዜ በኋላ በመጀመሪያ እግዚአብሔር የደህንነት ተሐድሶ እደረገ በአስቴር ላይ ውብ የሆኑ ልጃገረዶች ይፈለጉልህ የሚል ቃል እናገኛለን ስስዚህም ተፈልገው ብዙ ልጃገረዶች ወደ ሱሳ ከተማ መጡ ልጃገረዶቹ ተፈልገው መጡ እንጂ ፈልገው አልመጡም ነበር እግዚአብሔር ተሐድሶ ሲያስነሳ በምህረቱና በፍቅሩ እንደገና የሰው ልጆችን መፈለግ ጀመረ ወደ ሱሳ ከመጡት ከብዙ ልጃገረዶች መካከል እንድዋ እስቴር ነበረች እስቴርም ከሌሎች ልጃገረዶች ልዩ የሚያደርጋት ሌሎቹ ልጃገረዶች ራሳቸውን በራሳቸው ያቀረቡ ሲሆን እስቴር ግን ለንጉጮ የቀረበችው በመርዶክዮስ ምሪት ነበር የእግዚአብሔር ቃል በአንዱ መንፈስ በክርስቶስ ሥራ ወደ እግዚአብሔር ቀርባችኋል ይላል ቤተ ክርስቲያንንም ወደ ንጉሠ የሚያቀርባት ወስዶም በክርስቶስ አካል የሚያጠምቃት መንፈስ ቅዱስ ነው ቆሮ እስቴር ወላጆቿ እናት እባት የሞቱባት ምንም የምትተማመንበት ያልነበራት ልጃገረድ ነበረች ከዚያም ጊዜ ጀምሮ መርዶክዮስ ሊያሳድጋት ወሰዳት ሊያሳድጋት ሲወስዳት ምንም የምትመካበት ትምክህት ያልነበራት ነገር ግን በሚያሳድጋት በመርዶክዮስ ብቻ የምትመካ ነበረች ስለዚህም መርዶክዮስ ወደ ራሱ አሳብ በማስገባት በልዩ ክብካቤ አሳደጋት እስ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት በማድረግ ለልዩ ዓሳማው እንዲለያት የምትፈልግ ቤተ ክርስቲያን የምትመካበት ምንም ነገር የሌላት ትምክህትዋን ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የጣለች መሆን አለባት ከዚህም የተነሣ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ አስቴር ሲገልጽልን «አርስዋም ቁመናዋ የተስተካከለ እጅግ ውብ ልጃገረድ ነበረች አስ በዚሁ የንባብ ክፍል ላይ ቁመናዋ የተስተካከለ የሚል ሀረግ እናገኛለን ንግሥት አስጢን ወደ ንጉሥ መቅረብ እምቢ ካለች ወዲህ ብዙ የዝምታ ዓመታት ነበሩ በዚህ ጊዜ ንጉሠ ብቻውን ነበር ከጎኑም ንግሥተ አልባሳትዋንና ዘውዷን ጭና የምትቀመጥ ንግሥት አልነበረችውም አሁን ግን የተሐድሶ ዘመን ሲጀመር ንጉሠ የሚፈልጋት ቁመናዋ የተስተካከለን ሴት ነው ቁመና የሚለው ቃል አቋምን የሚያመለክት ነው እስቴር የተስተካከለ አቋም ያላት ነበረች ቤተ ክርስቲያን የተስተካከለ አቋም እንዳይኖራት ከሚያደርጉት ምክንያቶች እንዱ ያልተስተካከለ አመራር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲኖር ነወ እንደ አስቴር በመንፈስ ቅዱስ ከመመራት ከመደገፍና የጠራንን ጌታ ከማየት ይልቅ እንደ አስጢን የራሳችንን ጥቅምና ክብር እንዲሁም የተቀመጥንበትን ወንበር ማየት ስንጀምር አቋማችን እየተበላሸ ይሔዳል አቋም የሌላት ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ሌሎችን ማቆም አትችልም ከዚህም የተነሣ ምእመኑ የተፍረከረኩ ይሆናሉ አቋም የሌላት ቤተ ክርስቲያን በማፅበል የምትንገላታን ጀልባ ትመስላለች አስቴር ግን ሳመነችበት ነዝር ወደ ኋሳ የማትል ብዙ ልጃገረዶች እንኳን ወደ ሱሳ ከእርስዋ ጋር ለንጉሥ ቢቀርቡም ሌሎቹ አቋማቸውን አላስተካከሉም ብላ እመለካከትዋን የማትለውጥ እንደ ንግሥት አስጢን በሴት ወይዛዝርት መካከል መወደስን የማትወድ ንጉሥ ብቻ እንዲከብርባት የምትፈልግ ጌታዋን ያለማስተዋል በመሮጥ ሳይሆን ጥልቅ በሆነ መረዳትና ማስተዋል ማገልገል የምትፈልግ አቋም ያላት የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነች የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ማን ናት ብለን ስናስብ በመጨረሻው ዘመን የሚኖሩ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ተብለው ይጠራሉ የሚል አመለካከት ሊያድርብን ይችላል ነገር ግን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ተብላ የምትጠራው በመጨረሻው ዘመን እግዚአብሔር ሊያደርግ ያስውን ሥራና ተ ተ ሩ በመ መንጌ ቤተ መጀመሁ የእግዚአብሔርን የዘመኑን አሳብ የተረዳች በተረዳችው አላብ መሠረት ዋጋን ከፍላ የምትጓዝ አቋም ያላትና ወደ መቲ የምትገሰግስ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ያቺ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ተብሳ ትጠራለች አንዲሁ አቋሟን ሳታስተካክል የንግሥት አስጢንን አመለካከት ይዛ የምትጓዝ ቤተ ክርስቲያን የንግስት አስጢን ዓይነት አመለካከት ርዝራዥ ያላት ቤተ ክርስቲያን ተብሳ ትጠራለች እንጂ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ተብላ አትጠራም የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን መሪዎችዋና አገልጋዮችዋ ባላቸው እውነተኛና ግልፅ አቋም ሰዎችን ይማርካሉ እንጂ በወሬና በቅስቀሳ ሰዎችን ለመማረክ አይሞክሩም የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን አቋሟን ግልጽ አድርጋ በመናገር እንዲከተልዋት ታደርጋለች እንጂ አቋሟን ባለመግለጥ የሚከተልዋትን ግራ ስለዚህ ጌታን መከተል በአቋም ቤተ ክርስቲያንን መምራት ደ ት ደግሞ በታላቅ አቋም መሆን አለበት አስቴርም አቋም ያሳት ስለነበረች በጃንደረባው በሄጋይ ፊት ሞገስ እገኘች እስቴርም ሄጋይን ደስ አስኘችው በፊቱም ሞገስ አገኘች አስ አቋም ያላት ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ዘንድ መላአክት ፊት ምስክርነት ስለምታገኝ ግርማና ክብር አላት። እንዲሁም በሰይጣንና በመንግሥቱ ላይ የአስፈሪነት ግርማና ሞገስን የምታገኝ ቤተ ክርስቲያን አቋም ያላት ናት በአስቴር ምዕራፍ ላይም ባያት ሁሉ ዘንድ ሞገስን ያገኘች ነበረች የሚል ቃል እናገኛለን ሞገስ ሊያስገኝላት የቻለው ዋናው ነገር አቋሟ ነበርአቋም ያላት ቤተ ክርስቲያን እንደ ንፍታሌም በሞገስ የጠገበች ናት በሞገስ ከጠገበች ደግሞ የእግዚአብሔርን በረከት ትሞላለች የተስፋ ቃሉንም ትወርሳለች ዘዳ ስለዚህም እንደ አስቴር እያንዳንዳችን አቋም ኖሮን ሞ ገስገ እንድናገኝና ቤተ ክርስቲያናችንና አገልግሎታችን በፊቱ እንዲከብር ጌታይፈልጋልእንግዲህ እግዚአብሔር ከመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያገ በመጀመሪያ አቋምን ይፈልጋል የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የጊዜ ተጠቃሚ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ጊዜም ሳይባክን ወዲያውኑ ጥሩ ምግብ እንዲስጣትና የሰውነትዋ ቅርጽ በመታሸት እንዲስተካከል በማድረግ በቁንጅና ክብካቤ እንድትጠበቅ ወሰነ አስ በዚህ ጥቅስ መጀመሪያ ላይ ጊዜ ሳይባክን የሚለውን ቃል እናያለን በንግሥት አስቴር የምትመሰለው ቤተ ክርስቲያን አቋም ስላላት ጊዜዋን በከንቱ ነገር ላይ ማባከን አትፈልግም ንጉሥም የእርስዋ ጊዜ እንዲባክን አልፈለገም በንግሥት አስጢን የምትመሰለው ቤተ ክርስቲያን ግን አቋሟን ያበላሸችና አምቢ ያለች ስለነበረች ቤተ ክርስቲያን ማግኘት የሚገባትን በረክት በጊዜው እንዳታገኝ ጊዜ አባክናለች አሁን ግን አስቴር አቋሟን አስተካክላ ብቅ ስትል በከንቱ ያለፈውን ጊዜ ለመበቀል ንጉሥ ጊዜ መፍጀት አልፈለገም ከዚህም የተነሣ በጃንደረባው በሄጋይ አማካኝነት ጊዜ ሳይባክን ጥሩ ጥሩ ምግብ እንዲሰጣት ተወሰነ እዚህ ላይ ምግብ የእግዚአብሔር ቃል ምሳሌ ነው ስለዚህም ጊዜ ሳይባክን አቋም ላላት ቤተ ክርስቲያን ጥሩ ጥሩ የእግዚአብሔር ቃል መገለጥ እንዲፈስላት ንጉሠ ወስነ ከውሳኔው የተነሣ አስደናቂ የሆነ የቃሉ መገለጥ አቋም ባሳት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አሁንም እየፈሰሰ ነው በዚህም አያበቃም በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የሚመጣው የቃሉ ምስጢር ገና ተጀመረ እንጂ አላበቃም ነገር ግን አንድ መገንዘብ ያለብን ነገር ንጉሥ አቋም ካሳት ቤተ ክርስቲያን ጋር ጊዜው አንዳይባክን ወስኖአል የሰው አመለካከት ሥርዓትና ወግ የንጉን ውሳኔ ሊሽረው ስለማይችል ያለን አማራጭ ጌታ ጊዜው ሳይባክን ቀብቶ በሚሰጠን አገልጋዮች በኩል የሚመጣውን የቃሉን እውነት ተቀብሎ መታዘዝ ብቻ ነው አቋም ያላት ቤተ ክርስቲያን ከንጉሥ ጋር ጊዜዋን የምታጠፋ ንጉሙም በጊዜው የሚሰጣትን የቃሉን እውነት የምትመገብና ሌሎችንም የምትመግብ ናት አስጢን ግን የባሏን የንጉጮን የክብር ግብዣ መመገብ ሲገባት በክብር ስፍራ ተቀምጣ መመገብ እምቢ እንዳለች ሁሉ ዛሬም ጌታ ራ በመ ዋ ዘመ መጀመ ያዘጋጀውን የክብር ግብዣ ለመመገብ የማትዘጋጅ ቤተ ከርስቲያን ሌሎችን መመገብ ፈጽሞ አትችልም የእግዚአብሔር ቃል ፍቺ ወደ አገልጋዮች የሚፈሰው አገልጋዮች አቋም ሲኖራቸው ነው አቋም ከሌሳቸው የሚቀበሉትን የእግዚአብሔር ቃል ወደ ሌሎች ማስተላለፍ አይችሉም ለምን ቢባል ፈሪሳዊያንና የምኩራብ አለቆችን ስለሚፈሩ አቋም ወደ ሌላቸው አገልጋዮች የቃሉ መገለጥ አይመጣም ለውጥ ከፈለግን አቋም እንዲኖረን ያስፈልጋል እግዚአብሔር ቃሉን ገልጦላቸው ተሐድሶን ያመጡ ሰዎች አቋም ያሳቸው ሩ ስለሆነም በመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጊዜ አይባክንም እግዚአብሔርም አስደናቂ የሆነውን የቃሉን ምስጢር እየገለጠ ይመግባታል በኤፌሶን ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት ይመግበዋል ይንክባክበውማል ተብሎ እንደተጻፈው ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን የሚመግባት በኤፌሶን ላይ እንደተገለፀው እንደ ውኃ አጥቦ በሚያነጻው ቃሉ ነው ይህም ጌታ ከመምጣቱ በፊት ቤተ ክርስቲያን እንድትቀደስና የፊት መጨማደድና ነውር የሌለባት ሆና እንድትገኝ ነው የጌታ መምጫ ደግሞ ስለተቃረበ ጊዜ ሳይባክን ጌታ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን የምትዘጋጅበትን ጥሩ ጥሩ ምግብ እየመገባት ነው ጥሩ ምግብ የምትመገበውን ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ቃል ሲገልጽልን ሙሽራይቱ ውዴ ክሌሎች ጐልማሶች ጋር ሲነጻጸር በዱር ዛፎች መካክል አምሮ እንደሚታይ የፖም ዛፍ ነው እኔም እጅግ ደስ ብሎኝ በጥላው ሥር ዐረፍሁ ጣፋጭ ፍሬውንም በመመገብ ተደሰትሁ ወደ ምግብ አዳራሹ አስገባኝ ፍቅሩንም እንደ ሰንደቅ ዓላማ በእኔ ላይ ከፍ ከፍ አደረገ እኔ በፍቅሩ ተይዥ ስለታመምሁ ዘቢብ እየመገባችሁ አበረታቱኝ በፖም ፍሬም አስደስቱኝ መኃመኃ በዚህ ክፍል ሳይ ሙሽራይቱ ቤተ ክርስቲያን በብዙ ኃያላን መካክል ወደር በማይገኝለት በክርስቶስ ጥላ ሥር ቁጭ ብላ ጣፋጭ የሆነውን የፓም ፍሬ ትበላ ነበር አንዲሁም ወደ ምግብ አዳራሹ ገብታ ወይን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ትመገብ ነበር በመኃመኃ ላይ ደግሞ ሙሽራው ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ምግብ አዳራሹ ገብታ ስለተመገበችው ቤተ ክርስቲያን ስለ ሙሽራይቱ ሲመሰከርላት የእስትንፋስሽ መዓዛ እንደ ፖም ፍሬ ሽታ ነው የአፍሽም መዓዛ እንደ መልካም ወይን ጠጅ ነው ይሳታል መኋመኃ እንግዲህ በዚህ ባለንበት ዘመን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ጊዜዋን ሳታባክን ወደ ንጉሠ የምግብ አዳራሽ የገባች በወርቁ አልጋ ላይ ዐርፋ ጣፋጭ የሆነውን የቃሉን መገለጥ እየተመገበች የእስትንፋስዋን መልካም መዓዛ የምታሸትት ጉባኤዋን በወይን ጠጅና በፓም መዓዛ የምታውድ ሙሽራው እስኪመሰክርላት ድረስ የተለወጠች በእግዚአብሔር ቃል የተሞላች ነች ሀ ያሬ ያቋ ምግዝ ይኖሪዎለኋ ይ ስ ያጄሥይኦኑ ሪሥቻ ሯራለ ይ ለፅፓ። ሦስተኛ በአካሉ በቤተ ክርስቲያን ውሰጥ ሰዎች የተለያየ አገልግሎት እንዲይዙ አደረገ ቆሮ እንዲሁም በተመሳሳይ ሁኔታ በኤፌሶን ምዕራፍ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ሲገልጽ አንድ አካል አለ ይለናል ያም አካል ክርስቶስ ራስ የሆነበት ነው በቁጥር ሰባት ሳይም በአካሉ ውስጥ ክርስቶስ ለመስጠት በወሰነው መጠን ለያንዳንዳችን ጸጋ ሰጥቶናል ይላል በቁጥር ዐሥራ አንድ ላይ የሰጠውን ስጦታ ሲያስቀምጠው እርሱም አንዳንዶቹ ሐዋርያት አንዳንዶቹ ነቢያት አንዳንዶቹ የወንጌል ሰባኪዎች አንዳንዶቹ የምእመናን እረኞች አንዳንዶቹ አስተማሪዎች እንዲሆኑ ስጦታዎችን ሰጠ በማለት ያጠቃልሰዋል ፅን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንግዲህ ክርስቶስ ጎልተው የሚታዩ ስጦታዎችን ለአካሉ ለቤተ ክርስቲያን ሰጥቷል በመካከለኛው ዘመን የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እውነት ኣልታዘዝም ስትል ያጣችው እጅግ ያስዋባትን የአገልግሎት ስጦታን ጨምሮ ነበር እምቢ ስትልም በአካሉ ውስጥ ያሉትን ሐዋርያቶችን ነቢያቶችን ወንጌል ሰባኪዎችን እረኞችን አስተማሪዎችን ሁሉ አጣችቾ ቤተ ክርስቲያን ካለነዚህ የአገልግሎት ስጦታዎች ቁመና ያላት አካል ብቻ ነገር ግን ቅርጽ የጎደላት የማትማርክ ትሆናለች በሌላ አገላለጽ ክርስቶስ ኢየሱስ አካል የሚሆኑ ብዙ ሰዎች ስበሰበ ሁሉንም ቦታ ቦታ አስያዛቸው አንድም አካል ሆኑ አካሉም ቅርጽ እንዲኖረውና የሚማርክ እንዲሆን አምስቱን የመንግሥቱን ታሳላቅ የአገልግሎት ስጦታዎችን አስቀመጠ ቀደም ብለን እንዳየነው ከንግሥት አስጢን ውድቀት በኋላ እግዚአብሔር እንደገና ተሐድሶን ሲያደርግ በመጀመሪያ የደህንነትን ተሐድሶ ከዚያ በኋላ ቤተ ክርስቲያን አቋም ያላት እንድትሆንና ጥሩ ጥሩ ምግብ እንድትመገብ ተደረገ ቅርጽ ስላልነበራት ግን በመታሸት ቅርጽ እንድትይዝ የተሐድሶ ሥራ በአስቴር ምዕራፍ ላይ መጀመሩን ተመልክተናል ስለዚህ አስቴር አቋም ያላት የእግዚኣብሔርን የቃሉን መገለጥ የምትመገብ እንደውም ባያት ሁሉ ፊት ሞገስን ያገኘች ነበረች ነገር ግን አስቴር ቅርጽ እንዲኖራት ወደ መታሻ ክፍል ገባች ማሰት ንግሥት እስጢን የጣለችውን የቤተ ክርስቲያን ውበትና ቅርጽ የሆኑትን የአገልግሎት ስጦታዎች ለመቀበል ቅርጽ እንደሌላት አምና አስቴር በዘይትና በከርቤ በጣፋጭም ሽቶ በመታሸት ቅርጽ ወደምትይዝበት ክፍል እራስዋን አስገባች ይህንንም በደንብ ለመረዳት ቤተ ክርስቲያንን ቅርጽ ስለሚያስይዝዋት የአምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች በመጠኑ በሚቀጥለው ምዕራፍ እንመለከታለን ምዕራፍ አምስት ቤተ ክርስቲያንን ቅርጽ የሚያስይዝዋት አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን በአገልግሎት ቅባት የሚገኘውን ዋጋ መቀበል በኤፌሶን ላይ እንደምንመለከተው ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን ስጦታን ሰጥቷል ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮን ማረከ ለስዎችም ስጦታን ሰጠኤፌ ኢየሱስ በምድር በነበረበት ጊዜ በእነዚህ የአምስቱ የአገልግሎት ቅባት በሙላት አገልግጳል ቅባት የሚተላለፍ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱሳችን በብዙ ቦታ ይነግረናል ለምሳሌ እግዚአብሔር ሙሴን እንዲረዱት ለሽማግሌዎቹ በሙሴ ሳይ ከነበረው መንፈስ ቅባት አካፈላቸውዘጉኢያሱ ሙሴን ተከትሎ እንዲያገለግል ሙሴ እጁን ጫነበት የጥበብን መንፈስ ተቀበለ ዘዳ ኤልያስ ወደ ሰማይ በወጣ ጊዜ በመጎናፀፊያው ላይ ያለውን ቅባት ለኤልሳዕ አስተላለፈ ነገ እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሳይ በወጣ ጊዜ በእርሱ ሳይ ያለውን ቅባት አንድ ሰው ሊሸከመው ስለማይችል በአምስት ቦታዎች በመከፋፈል ሐዋርያት ነቢያት ወንጌሳውያን እረኞችና አስተማሪዎች ብሎ ቅባቱን እከፋፍሎ ለቤተ ክርስቲያን ስጦታን ሰጠ ይህም ስጦታ በቤተ ክርስቲያን የሚሠራው ቤተ ክርስቲያን እንድትታነጽ የእግዚአብሔርንም ልጅ በማወቅና በማመን ወደሚገኝ እንድነት ደርሳ ክርስቶስ ፍፁምና ሙሉ እንደሆነ ቤተ ክርስቲያንም ሙሉ ሰው እንድትሆን ነው ኤፌ እነዚህ አምስቱ የክርስቶስ የመንግሥቱ ታሳላቅ ስጦታዎች ናቸው ያለነዚህ ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያን ወደ ፍፁምነት አትገባም ሙሉ ሰውም አትሆንም በኤፌሶን ላይ ክርስቶስ ለመስጠት በወሰነው መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተስጥቶናል የሚል ቃል እናገኛለን ይህ መጠን የሚለው ቃል ሁሉም የየራሳቸው የሆነ ከጌታ የተቀበሉት የቅባት መጠንና የተለያዩ የአገልግሎት ድርጊቶች ተግባር እንዳላቸው ያሳያል ሌላው ነዝር እነዚህ አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች ጌታ ኢየሱስ በሰዎች ውስጥ ነው ያስቀመጠው ጌታ ኢየሱስ ባገለገለበት ስፍራና አገልግሎቱን በተቀበሉበት ስፍራ በውስጡ ያለው ቅባት እየፈሰሰ ሌሎችን ይነካ ነበርጌታ ሰባዎቹን ደቀ መዛሙርት ሥልጣንና ከእርሱም ኃይል ቅባት ቤተ ከርስቲያንን ቅርጽ የሚያስይዝዋት አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች ካካፈላቸው በኋላ ወንጌልን እንዲሰብኩና እንዲያስተምሩ ተአምራትንም እንዲያደርጉ ላካቸው ሉቃ ሲልካቸውም አገልግሎት የሚተሳለፍ ክጌታ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ቁልፍ የሆነ ምስጢር እንዲህ በማለት ገለፀላቸው እናንተን የሚሰማ እኔን ይሰማል እናንተን የማይቀበል እኔን አይቀበልም እኔን የማይቀበልም የላከኝን አይቀበልም ሉቃ እዚህ ላይ ልናስተውል የሚገባን ነገር ኢየሱስን ቀብቶ የላከው እግዚአብሔር አብ ነው ኢየሱስን የማይቀበል ሁሉ የላከውን አብን አልቀበልም ማለቱ ነው እንዲሁም ጌታ ኢየሱስ የራሱን ቅባት በአምስት ቦታ ከፋፍሎ ቀብቶ የላካቸውን ሰዎች አንስማም ብንል ጌታን አለመስማት ነው አንቀበልም ብንል ደግሞ የሰጦታውን ምንጭ ሰጪጌታን አንቀበልም ማለታችን መሆኑን መዘንጋት የለብንም እንዲሁም በሌላ ስፍራ ጌታ ገልጽ ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ያገኛል ማቴ ይህንን ጥቅስ ስናይ ነቢይን የሚቀበል የነቢዩን ዋጋ ያገኛል እይደለም የሚለው ነገር ግን የነቢይን ዋጋ ያገኛል ነው የሚለው ይህ ማለት አንድን ነቢይ ነቢይ የሚያስብለው የነቢይነትን ቅባት ከጌታ ስለተቀበለ ነው ያለበለዚያ ግን ነቢይ ተብሎ ሊጠራ አይችልም ነቢይን የሚቀበል በነቢዩ ውስጥ ያለውን እጅግ የከበረ ዋጋ ያለውን ቅባት ተጠቃሚ ይሆናል ማለት ነው ስለዚህ ነቢይን የሚቀበል ነቢይ ሆኖ በተጠራው ሰው ውስጥ ያለውን ኢየሱስ ያስቀመጠውን ዋጋ ያለውን የነቢይን የቅባቱን ድርጊት ተቀባይ ወይም ተጠቃሚ ይሆናል ዋጋ የሚለው ቃል ውድ የክበረ ጥቅም ያለው መሆኑን የሚያመለክት ነው አንዳንድ ቤተ ክርስቲያን ነቢይ ሆኖ የተጠራውን ሰው ይቀበላሉ ነገር ግን ነቢዩ በተሰጠው ቅባት የሚያስተላልፈውን ዋጋ ያለውን መልእክቱን ግን አይቀበሉም እንዲሁም ብዙ አብያተ ክርስቲያናት እረኞች አላቸው እረኞችም አሉን ብለው ይናገራሉ ነገር ግን በእረኛው ውስጥ እግዚአብሔር ያስቀመጠውን ዋናውን የእረኛውን የቅባቱን ድርጊት የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን አይቀበሉም ነገር ግን ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል ሲል ነቢይ የሚለው ስም ስላለው ሳይሆን ነቢይ ስለሆነ ከእግዚአብሔር የከበረውን መልእክት ያመጣልናል በቅባቱ እንጠቀማለን ብላ የምትቀበል ቤተ ክርስቲያን የነቢይን የቅባቱን ድርጊት ዋጋ ያለውን የከበረውን ነገር ታገኛለች እንጂ ሰዎችን ተቀብላ የአገልግሎት ቅባታቸውን ድርጊት ካልተቀበለች ዋጋ የለውም ስለዚህ ወንጌሳዊን ብቻ የምትቀበል ቤተ ክርስቲያን የወንጌላዊውን ቅባት ብቻ ተጠቃሚ ትሆናለች አስተማሪን የምትቀበል የአስተማሪውን ቅባት ብቻ ተጠቃሚ ትሆናለች እንዲሁም እግዚአብሔር በመጨረሻው ዘመን በቤተ ክርስቲያን ሐዋርያት ነቢያት ወንጌሳውያን እረኞችና አስተማሪዎች እንዲኖሩ ይፈልጋል ያለነሱ የቅባት አገልግሎት ቤተ ክርስቲያን ልትይዝ የሚገባትን ቅርጽ አትይዝም የአምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች አስፈላጊነት በዚህ ርዕስ ክመጽሐፍ ቅዱስ ኣንዳንድ ቦታዎችን በማየት አምስቱ ታላላቅ የክርስቶስ ስጦታዎች ለቤተ ክርስቲያን እንዴት አስፈላጊ እንደሆኑ ዛሬም የአገልግሎት ስጦታ ያላቸው አገልጋዮች ለክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ሰጪና ጠቃሚ እንደሆኑ እንመለከታለን ሐዋርያት ሐዋርያትና ነቢያት ተመሳሳይ ኣገልግሎት አላቸው ይህም እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ እንድትመሠረት አድርጓል ወይም የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ በሐዋርያትና በነቢያት የተጀመረ ነው እነዚህ ሁለቱ አገልግሎቶች ባለንበት ዘመን ለቤተ ክርስቲያን በጣም ጠቃሚዎች ናቸው ምክንያቱም እነርሱ የመሠረቱትን ሕንጻ እነርሱ መጨረስ አለባቸው ካለ ሐዋርያትና ካለ ነቢያት የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ፍፁም ሙላት አትገባም ፌሕፒ ከርስቲያንን ቅርጽ የሚያስይዝዋት አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች የሐዋርያትና የነቢያት ቅባት ልክ እንደዘሩባቤል ቅባት ነው የእግዚአብሔር ቃል ስለ ዘሩባቤል ሲናገር የዘሩባቤል እጆች ይህንን ቤት መሠረቱ የእርሱም እጆች ይፈጽሙታል ጠካ የቀት የቤተ መቅደሱ ሥራ በዘሩባቤል ተጀምሮ በዘሩባቤል እንደ ተፈፀመ አንዲሁም የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ሥራ በሐዋርያትና በነቢያት ቅባት የተመሠረተ ሲሆን በእነርሱም ቅባት የመቅደሱ ሥራ ይፈጸማል ሐዋርያት ነገሮችን የመጀመር ቅባት የመፈጸም ቅባት የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን በትክክል የመገንባት ቅባት የሰይጣንን ክበባ በጣጥሶ የሚያልፍ የጦርነት ቅባትና እንዲሁም ክመንጋው ነውርን እየመነጠረ የሚያወጣ ቅባት አላቸው ይህም አገልግሎት ቤተ ክርስቲያን ቅርን እንዳትለቅ ትልቅ ቦታ አለው ስለዚህም በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ስምንት ላይ ካለው ክፍል ወስደን ቤተ ክርስቲያን እንዴት በሐዋርያት ቅባት ቅርጽ እንደምትይዝ እንመለከታለን ደተዎረዖታ ቀያ ፅዕማርዖ ዜፇ ያረዕጂያ በእስጢፋኖስ ሞት ምክንያት እማኞች ወደ ተለያዩ አገር ሲበተኑ ወንጌላዊ ፊሊፅስ ወደ ሰማርያ ክተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው ሕዝቡም የያፊሊጳስን ቃል ሰሙ በሌላ አገላለጽ ሕዝቡ በፊሊፅስ ውስጥ ያለውን የወንጌላዊ ቅባት ተቀበሉ ብዙ ሰዎች ጌታ ኢየሱስን የግል አዳኛቸው አድርገው ተቀበሉ ብዙ ተአምራት በፊሊፅስ አገልግሎት ተደረገ ሽባዎችና አንካሶች ተፈወሱ እርኩሳን መናፍስት በታላቅ ድምፅ እየጮሁ ክሰዎች ላይ እየለቀቁ ወጡ ይህ ሁሉ ሲሆን በሰማርያ አንድ ሲሞን የሚባል ታላቅ ጠንቋይ ነበር በሚያደርገውም የጥንቆጳ ሥራ የሰማርያን ሰዎች ታላሳቆችንና ታናናሾችን ያሳተ የእግዚአብሔር ኃይል ይኬ ነው ብለው ሰዎች ያደምጡት የነበረ ክብዙ ዘመን ጀምሮ በጥንቆላ ሥራ የታወቀ ነበር ሲሞን በፊሊጳፅስ አገልግሎት ጌታ ኢየሱስን አምኖ ተቀበለ እንዲሁም ተጠመቀ ከዚህም አልፎ ከፈሊፅስ ጋር ይተባበር ነበርሐሥ እዚህ ላይ ፊሊፅስ የተቀባ ወንጌላዊ ነበር በድንቅና በተአምራት ወንጌልን ይሰብክ ነበር ጠንቋዩ ሲሞንን እንኳ ሳይቀር በወንጌሳዊ ቅባት ወደ ጌታ አምጥቷል ነገር ግን በሰማርያ ከተማ ከዚህ በላይ መሄድ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን አልቻለም ነበር ምክንያቱም በኤፌሶን ላይ እንደምናየው ለወንጌሳዊ የተስጠው የቅባት መጠን ስላለው ቅባቱም ወንጌልን ከመስበክ ሰዎችን ወደ ጌታ ከማምጣትና በድንቅና በተአምራት ሰጦታ ሥጋዊ ከሆነ በሽታ ሰዎችን ከመፈወስ አሳለፈም ነበር ነገር ግን በዚሁ በምዕራፍ ላይ በኢየሩሳሌም የነበሩ ሐዋርያት የሰማርያ ስዎች የእግዚአብሔርን ቃል መቀበላቸውን በሰሙ ጊዜ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ወደ ሰማርያ ሳኩሳቸው ይሳል እዚህ ሳይ ለምንድነው የላኩላቸው። አንተ ሁሉን ታውቃለህ አኔ እንደምወድህም ታውቃለህ አለው ኢየሱስም እንዲህ አለው በጎቼን አሠማራ ዮሐ ያዕቆብ ያየው ጌታ የሚፈልጋትን ቤተ ክርስቲያን በሦስት የተከፈሉ የሚመገቡ ግልገሎች የሚጠበቁ ጠቦቶችና የሚሰማሩ በጎች ያሉበትን እውነተኛ የካራን ቤተ ክርስቲያንን ነበር የካራን ቤተ ክርስቲያን ስንል ሙላት ያላት ቤተ ክርስቲያን ማለታችን ነው የበግ መንጋዎቹም በጉድጓድ ዙሪያ ነበሩ የሚጠጡትም ከአንዱ የውሃ ጉድጓድ ነበር በጎቹም ሌሳጉድጓድ አያውቁም በአካባቢው ሌላ ምንም የለም ሁሉም በጎች ከአንዱ ከኢየሱስ ይጠጡ ነበር ብዙ ቤተ ክርስቲያን ከየት እንደመጣ በማይታወቅ ውሃ አንዳንዴ ከአግዚአብሔር ቃል ውጭ የሆነ ለመንጋው ምንም ጥቅም የማይሰጥ የማያረካ ጥምን የማይቆርጥ ውሃ ለበጎች ይቀርባል በካራን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ግን ምንም ሌላ ውሃ የለም ቀጥታ በጎቹ ከአንዱ የውሃ ጉድጓድ ከኢየሱስ ይጠጡ ነበር ሌላው ያዕቆብ እረኞች የውሃውን መክደኛ ድንጋይ ከጉድጓድ ሲያንከባልሉ ተመለከተ መንጋዎቹ ሁሉ እዚያ ከተሰበሰቡ በኋሳ አረኞች ድንጋዩን አንከባለው ከጉድጓዱ ውሃ ያጠጡአቸው ነበር መንጋዎቻቸውን ካጠጡ በኋሳ ግን ድንጋዩን መልሰው በጉድጓዱ አፍ ላይ ይከድኑታልርዘፍ እውነተኛ የእረኝነት አገልግሎት እንግዲህ ይህ ነው ድንጋዩን ከጉድጓድ እያንከባለሉ ለበጎች ውሃ ማጠጣት በኤፌሶን ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ አንዳንዶችን የምአመናን እረኞች አድርጎ ከቅባቱ አካፍሎ ሰጥቶአል ነገር ግን እውነተኛ የእረኝነት ጥሪ የሌሳቸው ከቅባቱ ያልተካፈሉ አንዳንድ ሰዎች ድንጋዩን ለማንከባለል ይሞክራሉ ነገር ግን ባልተሰጣቸው የቅባት መጠን ድንጋዩን ለማንከባለል መሞከር በፍፁም የማይቻል ነው ምክንያቱም የድንጋዩ ማንከባለያ ቁልፍ የቅባቱ ኃይል ነውና በካራን ግን እውነተኛ የበጎች እረኞች ስላሉ ድንጋዩን ማንከባለል ለእነርሱ በጣም ቀሳል ነው ስለዚህ እውነተኛ እረኛ ማለት በሕይወት ምንጭ በክርስቶስና በሦስት ቦታ በተከፈሉ የበግ መንጋዎች መካከል ቆመው ድንጋዩን የሚያንከባልሉ ናቸው ለዚህም ነበር ሙሴ ስለ እረኛ በዘጉልቁ መት ክርስቲያንን ቅርጽ የሚያስይዝዋት አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች ላይ ሲጸልይ በመጀመሪያ የጠቀሰው የሕይወት ሁሉ ምንጭ የሆንክ እግዚአብሔር አምሳክ ሆይ ያለው ሙሴ ስለ እረኛ ሲጸልይ ይህንን ያለበት ምክንያት የሕይወት ሁሉ ምንጭ በሆነው በእግዚአብሔርና በእረኛ መካከል ምን ዓይነት ግንኙነት እንዳለ በሚገባ ስለተረዳ ነበር ያዕቆብ አውነተኛዋን የካራን ቤተ ክርስቲያን ማየት ብቻ ሳይሆን እርሱም ከዚች ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ጋር አንድ ሆነ ያዕቆብ የአጎቱን የሳባን በጎች እየነዳች ስትመጣ ራሔልን አይቶ ወደ ጉድጓዱ ሄደ ጉድጓዱ የተከደነበትንም ድንጋይ አንከባሎ በጎቹን አጠጣቸው ዘፍ ያዕቆብ በነገር ሁሉ ብቃትን አገኘ ከዚያን በኋላ ራሔልን ሳማት ከደስታውም ብዛት የተነሣ አለቀሰ ዘፍ ያዕቆብ ድንጋዩን ካንከባለለ በኋላ ራሔልን ሳማት ምክንያቱም ራሔል የካራን ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነበረች ዘፍ ከራሔል ጋር በመሳሳሙ ከካራን ቤተ ክርስቲያን ጋር አንድነቱን ገለጠ ከዚያም ከደስታውም ብዛት የተነሣ አለቀሰ ያዕቆብ ያለቀሰው ብቃትን በሚሰጥ መንፈስ እውነተኛውን አገልግሎት ለማገልል በመቻሉ ነበር ርብቃ ወደ ነገረችው አሳብ በመድረሱ ራእዩ በመፈፀሙ ከዚህ በላይ ለአገልጋይ የሚያስደስተው ነገር ስለሌለ ያዕቆብ ከደስታው ብዛት የተነሳ አለቀሰ በዘመናችን ያሉ የቤተ ከርስቲያን እረኞች በነገር ሁሉ ብቃትን አግኝተው ለማገልገል የሚችሉት የማንንም ወደ እግዚአብሔር ክብር የማያደርለ አሳብ ሳይሰሙና ሳይፈሩ የጠራቸውን ጌታ ብቻ በማየት ብዙ ትርምስ ያለበትን ከኤሳው ዕቅድ ጋር የተቀላቀለውን እንደ እግዚአብሔር ቃል ያልሆነውን የቤተ ክርስቲያን አመራርና ሰው ሠራሽ ሥርዓት ዶክትሪን ዋጋ ከፍለው በቤርሳቤህ ጥለው ወደ ካራን ጉዞ ሲጀምሩ የዛን ጊዜ እንደ ኢያሱ በነገር ሁሉ ብቃትን የሚሰጥ መንፈስ ይቀበላሉ ኢያሱ ዐማሌቅን አይፈራም አግዚአብሔር ወደ አሳየው ምድር ለመግባት ቁርጥ ውሳኔ ያደረገ ሰው ነበር ከዚህም የተነሣ ሕዝቡን ለመምራት ብቃትን የሚሰጥ መንፈስ የተሞሳ ነበር በመጨረሻው ዘመን አግዚአብሔር ብቃትን የሚሰጥ መንፈስ የተሞሉ እረኞችን ይፈልጋል ስለዚህ ዐማሴቅን የማይፈሩ የአግዚአብሔርን የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የዘመኑን ዕቅድ የተረዱ ዋጋን ከፍለው በቤርሳቤህ ብቃት እንደማይገኝ አውቀው እንደ ያዕቆብ ቤርሳቤህን ትተው እውነተኛውን አገልግሎት ለማገልገል በቅባቱም ኃይል ድንጋዩን ሰማንከባለል ወደ ካራን የሚወጡትን በሦስት የተከፈሉ መንጋዎችን ለመመገብ እንደ ኢያሱና እንደ ያዕቆብ በሁሉም ነገር ብቃትን የሚሰጥ መንፈስ የተሞሉ አረኞች በመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይነሣሉ ወጋ ለረኛ ፈቃቀ ሀሁና ያማግገሩ መፅሳስልኋ ዖሟቃም ዕው በካህኑ በአልዓዛርና በመሳው ማኀበር ፊት እንዲቆም አድርገው ዘጉ እረኛ ማለት ከላይ ባለው ጥቅስ መሠረት በካህኑና በማኅበሩ ፊት የሚቆም ነው በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ሙሴን በአንተ ፊት ወይም በስባዎቹ ፊት የሚቆም አላለውም እንዲሁም በእግዚአብሔር በእራሱ ፊት እንዲቆም አላዘዘውም ነበር አግዚአብሔር የመረጠው ሊቀ ካህኑን አልዓዛርን ብቻ ነበር ይህም የአዲስ ኪዳን ጥላ የሆነ የማይሻር ቃል ነው ዛፊም ቢሆን እረኛ የአዲስ ኪዳን ሊቀ ካህናችን በሆነው በክርስቶስ ኢየሱስና በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መካከል የሚቆም ነው ቀደም ሲል በካራን ያሉ እረኞች በምንጩና በበጎቹ መካከል እንደቆሙ ተመልክተን ነበር እዚህ ላይ ምአመናን መረዳት ያለባቸው ነገር ቢኖር እረኞች የተለዩ ሰዎች ስለሆኑ አይደለም በክርስቶስና በምእመናን ፊት የሚቆሙት እንደ ማንኛውም አማኝ ክጨለማው ዓለም የወጡ ከሰይጣን መንጋጋ ያመለጡ በእግዚአብሔር ምሕረት በክርስቶስ ደም የነፁ ናቸው ልክ ኢያሱ በግብፅ በባርነት ቤት እንደነበረ የነበሩ ናቸው ነገር ግን በኤፌሶን ላይ አንዳንዶችን የምእመናን አረኞች አደረገ በሚለው ቃል መሠረት ልክ ኢያሱን ለእረኝነት እንደመረጠው ክርስቶስም ምርኮን ማርኮ ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ካዳናቸው ክብዙ ቅዱሳን መካከል አንዳንዶችን እረኛ እንዲሆኑ ከእርሱ የአረኝነት ቅባት አካፈላቸው ስለዚህ ከራሳቸው የተነሣ ሳይሆን ከተቀበሉት ቅባት የተነሣ በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያንና በክርስቶስ ፊት ለመቆም የበቁ ናቸው ስለሆነም የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ራስ ናቸው አረኞች በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያንና በክርስቶስ መካከል ሆነው የአግዚአብሔርን የልቡን አሳብ ለሕዝቡ የሚያስተሳልፉና የእግዚአብሔርን ማንነት በምእመኑ መካከል በመግለፅ ፍቅሩን ቸርነቱን ምሕረቱን ቤቷ ክርስቲያንን ቅርጽ የሚያስይዝዋት አምስቱ የአገልግሎት ስጦታዎች የይቅርታውን ብዛትና እንዲሁም እግዚአብሔር የሚባላ እሳት የፍርድም አምሳክ እንደሆነና ከሕዝቡም የሚፈልገው ነገር እንዳለ በማሳወቅ ከመንጋው ነውርን ፅድፈትና የፊት መጨማደድን የሚያወጡ ናቸው እውነተኛ እረኞች እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያለውን አሳብ ወደ ምእመኑ የሚያጓጉዙ ናቸው አንድን የመጓጓዣ ዕቃ መጓጓዣ የሚያሰኘው ስለሚያጓጉዝ ነው ኸለበለዚያ ግን ስም ብቻ ያየዘ ዕቃ ነው የሚሆነው እንዲሁም እረኞች አውነተኛውን የእግዚአብሔርን አሳብ ለሕዝቡ መግለፅ ካልቻሉ ሰም ብቻ የያዙ ድርጊት የጎደሳቸው ናቸው በጢሞቴዎስ መልእክት ላይ ምንም እንኳን እረኛው ጢሞቴዎስ የሚል ባናገኝም ወጣቱ ጢሞቴዎስ የእረኝነት አገልግሎት እንደሚያገለግል ሐዋርያው ጳውሎስ በላከለት መልእክቱ ላይ ቁልጭ ብሎ የሚታይ ነው ጢሞቴዎስ በእረኝነት አገልግሎቱ በእግዚአብሔርና በሕዝቡ መካከል የሚቆም ስለሆነ ብዙ ኃላፊነት እንዳለበት ጳውሎስ ያሳስበው ነበር በተለይ በአንደኛ ጢሞቴዎስ እና በሁለተኛ ጢሞቴዎስ ሳይ ጢሞቴዎስ በእግዚአብሔር ፊት የቆመ አረኛ በመሆኑ እራሱን ያለ ዕድፈትና ያለ ነቀፋ እንዲጠብቅ በጊዜውም አለጊዜውም በመፅናት በማስተማር በመምክር በመዝለፍና በመገሰፅ የእግዚአብሔርን አሳብ በትክክል ማስተላለፍ አንዳለበት እንዲሁም የቆመው በማን ፊት እንደሆነ በማሳሰብ የተሰጠውን የወንጌል አደራ እንደሚገባ እንዲወጣ ይመክረዋል ስለዚህ እረኞች ከእነርሱ በታች ሳሉት ሽማግሌዎች ዲያቆናትና አገልጋዮች እንዲሁም ለምእመናን የእግዚአብሔርን የልቡን አሳብ በመግለፅ የሚያስተዳድሩ ናቸው ዛሬ የአንዳንድ ቤተ ክርስቲያን እረኞች የስም ባላባት ብቻ ሆነው ነው የሚታዩት በጣም የሚገርመው ነገር ደግሞ አንዳንዶቹ እግዚአብሔር ለምን እረኛ እንዳደረጋቸው እንኳ በቅጡ አያውቁም አንዳንዶቹ ደግሞ ያሉበት መንፈሳዊ ደረጃ ክምእመኑ እንኳ ተለይቶ አይታይም ወይም አይታወቅም አንዳንዶቹ ደግሞ ሰው ባወጣው ሥርዓትና ትብታብ ተይዘው እውነተኛውን የእግዚአብሔር አሳብ ሳያገለግሉ ዓመታትን ይቆጥራሉ ያለ እግዚአብሔር አሳብ ወደ ሙላቱ መድረስ ስለማይቻል የሚመሩትንም ሕዝብ ክብዙ የእግዚአብሔር ክብር የጎደሉ ያደርጓቸዋል ክዚህ የተነሣ እየጠፋ ላለው ነገር ተጠያቂ የሚሆኑት እረኞች ናቸው እንደነዚህ ያሉ የቤተ ክርስቲያን እረኞች ይህ ዘመን የተሐድሶ ዘመን መሆኑን አውቀው መንቃት አለባቸው ካልነቁ የእረኝነት በትራቸውን ወይም መቅረዛቸውን ደመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስተያን ከእጃቸው የሚወስድ ጌታ በደጅ እንዳለ ጠንቅቀው መረዳት አለባቸው ምክንያቱም ይህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ቅርጽ አየያዘች ያለችበት ዘመን ነውና መላረኛ ማጎሩ ይታፅያሯያታ ያሯድ ይሥራለማ ጥትፉሪ ዕው መላው የእሥራኤል ማኅበር እርሉን ይታዘዙት ዘንድ የሥልጣንህ ተካፋይ አድርገው ዘጐ ይህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ቅርፅ እየያዘች ያለችበት የተሐድሶ ዘመን በመሆኑ በተለይ የመሪዎች አገልግሎትና አቀማመጥ የሥልጣንም አጠቃቀም ትልቅ መታደስ የሚያስፈልገው ስለሆነ በጥቂቱ ስፋ አድርገን እንመለከተዋለን ብዙ ጊዜ የአግዚአብሔር ቃል መገለጥ ካለማግኘታችን የተነሣ በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቤተ ክርስቲያን መሪዎች የተብራራ ጉዳይ የለም በማለት ብቻ ለብዙ ዘመን የቤተ ክርስቲያን አመራር እንደ እግዚአብሔር ቃል ባልሆነ ሁኔታ ተመርቶአል እግዚአብሔር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ በሆነበት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ሥልጣን ወይም አዝዝን አስቀምጧል እግዚአብሔር የሥርዓት አምላክ ነውና እግዚአብሔር ለእረኝነት ለመረጠው ለኢያሱ መላው የእስራኤል ማኅበር እንዲታዘዙለት ሥልጣን ስጥቶት ነበር በ ዓም የታተመው የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ሥልጣን የሚለውን ቃል ፍቺውን ሲያስቀምጠው በነገር ሁሉ የመምራት የመፍረድ የመግዛትና ማንኛውንም ነገር የማድረግ ሙሉ መብት ይለዋል እግዚአብሔር ለኢያሱ የእረኝነት ሥልጣን ሲሰጠው መላውን የእስራኤል ማኅበር ሊመራ መፍረድ በሚገባው ነገር ላይ ሊፈርድ ሊያስተዳድር በነገር ሁሉ ሳይ መብት ያለው አድርጎ ነበር ሥልጣን የስጠው ሙሴ ለኢያሱ ሥልጣኑን ካስተላለፈ በኋላ ሕዝቡን ለመምራት ከኢያሱ በላይ ሥልጣን ያለው አልነበረም በማኅበሩ ፊት ሙሴ የመረጣቸው ሽማግሌዎች የሕዝቡ አለቆች እግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ የተጠሩ ሌዋውያንም ነበሩ ነገር ግን ሁሉም ከኢያሱ ሥልጣን በታች ነበሩ ሁሉም ይታዘዙለት ነበር ምክንያቱም አግዚአብሔር በማኅበሩ ሁሉ ላይ የሾመው እረኛ ነበርና ቱ የ ጋሌ ባለንበት ዘመን በተለያዩ ቦታዎች የብዙ አብያተ ክርስቲያናት ትልቅ ችግር ባለሥልጣኑ ማን እንደሆነ ስለማይታወቅ ነው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ተቆጣጣሪ ወይም ባለሥልጣን ከሌላት ብዙ የእግዚአብሔር ሥራ እንደሚበላሸ ግልፅ ነው በአንድ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አንድ የበላይ ባለሥልጣን ወይም ተቆጣጣሪ የግድ ያስፈልጋል ይህም የእግዚአብሔር አሠራር እንጂ የሰው አሠራር አይደለም ብዙ ጊዜ የምናመካኘው ነገር ቢኖር እረኛው ሙሉ ሥልጣን መያዝ የለበትም ምክንያቱም ሥጋ የለበሰ ሰው ስለሆነ የግድ ከሽማግሌዎች ጋር በእኩል ሥልጣን መሄድ አለበት የሚል ምንም ቦታ ሊሰጠው የማይገባ አመለካከት አለ ኢያሱ በዘጉልቁ ለሁለተኛ ጊዜ የተቆጠሩትን ስድስት መቶ ሺህ በምድረ በዳ የተወለዱትን አዲሱን ትውልድ እየመራ በሙሉ ሥልጣን ከነዓን ያደረስው ብረት ለበስ ሰው ወይም ሥጋ የሌለው መንፈስ ብቻ ስለሆነ አልነበረም እግዚአብሔር ሕዝቡን እንዲመራለት ስለመረጠውና ስለቀባው ብቻ ነበር በሁሉም ነገር እረኛውና ሽማግሌዎች በእኩል ሥልጣን በአንድ ቤተ ክርስቲያን መቀመጥ የእግዚአብሔር ቃል የማይደግፈን ለእግዚአብሔር ሥራ ትልቅ እንቅፋት የሆነ ከእግዚአብሔር ቤት ውስጥ መወገድ ያለበት ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር መሥራት የሚፈልገው እራሱ በስጠን ሥልጣን አማካኝነት ነው እግዚአብሔር ስለ ቤተ መቅደሱ አሠራር ለሙሴ ሲነግረው በተራራ ላይ እንዳሳየሁህ አንድትሠራው ተጠንቀቅ ቭፀ ሙሴ ከእግዚአብሔር በተቀበለው አሠራር ነበር አንዲሠራ የተነገረው ከእግዚአብሔር ባልተቀበልነው አሠራር ቤተ ክርስቲያንን ለመምራት መሞከር ያዕቆብ እንደሚለን በእውነት ላይ መዋሸት ነው በሰማያዊ ጥበብ ሳይሆን በምድራዊ ጥበብ ቤተ ክርስቲያንን ለመምራት መሞከር ነው ይህም ምድራዊ ጥበብ ከሥጋ ከዓለም ከሰይጣን እንጂ ከእግዚአብሔር አይደለም ያዕ ቤተ ክርስቲያን በብዙ ሰዎች በምድራዊ ጥበብ በእኩል ሥልጣን ስትመራ ሁሉም የየራሱን ሥልጣን ለማንፀባረቅ ሲል ሁሉም በመራራ ቅናት በአድመኝነትና በራስ ወዳድነት ይያዛሉ ምድራዊ ጥበብ ባለበት ሁሉ ሁከትና ክፉ ሥራ ይገኛል ያዕ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ባለ ሥልጣን ስታጣ በተለይም ቤተ ክርስቲያንን በመምራት ላይ ባሉ ሰዎች መካከል ሁል ጊዜ ሁከት አድመኝነትና ክርክር ይሆናል ነገር ግን ይህ የመጨረሻዋ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንዳይሆን እግዚአብሔር በሽማግሌዎችና በእረኞች መካከል የሥልጣን ልዩነት አስቀምጧል ሽማግሌዎች በእረኞች ስለሚመረጡ በሥልጣን ከእረኞች በታች ናቸው ሐዋርያው ጳውሎስ ጢሞቴዎስን በኤፌሶን ቲቶን በቀርጤስ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያደራጁ የቤተ ከርስቲያን ሽማግሌዎችንም እንዲሾሙ በመልእክቱ ላይ ይገልፅላቸዋል ጢሞ ቲቶ እዚህ ላይ የምንረዳው ትልቅ ነገር አለ ይኸውም ጳውሎስ ሽማግሌዎችን ሾመ ጢሞቴዎስና ቲቶም ጳውሎስ በሰጣቸው መመሪያ መሠረት ከምእመኑ በመምረጥ ሸማግሌዎችን እንዲሾሙ ነገራቸው እንዲሁም ሙሴ ሥራው በከበደው ጊዜ ረዳት የሚሆኑትን ሽማግሌዎች ሙሴ የሚያውቃቸውን መርጦ እንዲሾም እራሱ አግዚአብሔር ነው ለሙሴ የመምረጡን ሥልጣን የሰጠው እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው ለሕዝብ አመራር በመስጠት የታወቁ ሰባ ሰዎችን ምረጥ እነርሱንም ስብስበህ እኔ ወደምመለክበት ድንኳን አምጣቸውና በአጠገብህ ይቁሙ ዘኑ ሙሴ የማስተዳደር ጸጋ ያላቸውንና የሚያውቃቸውን በታማኝነት ይረዱኛል የአግዚአብሔርንም ሥራ በቅንነት ይሠራሉ የሚላቸውን በተቀበለው ቅባት በኩል በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት መርጦ ሾመ እዚህ ላይ ማስተዋል የሚገባን ሽማግሌዎች በተቀቡ ሰዎች አማካኝነት በመንፈስ ቅዱስ ስለሚሾሙ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስተዳድሩበት የሚጠብቁበት ፀጋ ይቀበላሉ ነገር ግን እንደ እረኛ ቅባት ፈፅሞ አይሆንም ሙሴጳውሎስ ጢሞቴዎስና ቲቶም ሽማግሌዎችን የመሾም ሥልጣን እንደነበራቸው እንዲሁም ባለንበት ዘመን በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሚያውቃቸውን ለአገልግሎት ይረዱኛል የሚላቸውን የማስተዳደር ጸጋ ያላቸውን እውነተኛ ቦታቸውን የሚያውቁትን ሽማግሌዎች የመሾም ሥልጣን ያለው እረኛው ነው ምናልባት የዘመኑ ፈሪሳውያን ይህ እውነት ሊያስቃቸው ይችላል ነገር ግን የታላቁ የአምላካችን አሠራር ነውና ለእግዚአብሔር አሠራር ራሳችንን አጋልጠን መስጠት አለብን ባሁኑ ዘመን በብዙ ቦታዎች የቤተ ክርስቲያን አሠራር እንደ እግዚአብሔር ቃል ሳይሆን በኮሚቴና በእጅ ብልጫ ሆኖ እናገኘዋለን ግርግር ለሌባ ያመቻል እንደሚባለው ሁሉ እንዲሁም የኮሚቴና የእጅ ብልጫ አሠራር ለሰይጣን የስርቆት ሥራ አመቺ በር መክፈት ነው ስለዚህ እንደ እግዚአብሔር ቃል ካልሆነ አሠራር ቤተ ክርስቲያን ወጥታ ወደ ።