Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሚስኪን እናቱ ታወሱት ባህር ማዶ እርቆ ለትምህርት እና ለስራ እንደሚርቅ ሲያቁ በለሊት ነበር ነብሳባታቸውን ጠርተው ፅበል አስረጭተው በሰበብ አስባቡ ከተሜ በወጣ ቁጥር ማተብ ሲበጥስ ነገሩ አላምር ቢላቸው ከመሄዱ በፊት እምነት መሀተቡን እንዳይበጥስ አስገዝተው አሰሩለት የእናቱ የእምነት እዳ መስታውቱን ሰሎ በሀሳብ ታየው እንባው ጉንጮቹን ዳብሰው ከመታጠቢያው ወረዱ አሁን ነገሩ ሁላ ግራ ሆኖበታል ዶከተር አብርሀም ለማንም እሚያወራው ጉዋደኛም ሆነ ዘመድ የለም የተጠጋው የነካው ሁላ እንደሚረግፍ ነው የነገሩት ብቸኛ ማምለጫው ወይ ሞት ወይ የነሱ ከባድ መንገድ ብቻ ነው በሁለት ሀሳብ ተወጥሮ ማምሻውን ጋዋኑ ላይ የተወለት መልከት ትዝ አለው አሱ ቀድሞም ፋታ የነሳው ጉዳይስ ነበር። ዶከተር ዋሲሁን ከተሳለበት ቢላስር ሆኖ በሰመመን ብዙ ሄደ በዚ መሀል ነበር ባዳ የተባሉት አውሬ የተባሉት ግብረገብ የጎደላቸው አእራስወዳዶች የተባሉት በነጮች ከ ወገኔ ሀገሬ ባልኩዋቸው ሰውች መሀል ከ ሲኦል አወጡኝ ደሜን እኩዋን በውሀ ሲጠራርጎ አይጠየፉም ነበር ራፋዬል ባሮን አማካኝነት ተቀላቀልኩ ከዛ በውኃላ የሸሸሁት ዳባ መልኩን ቀይሮ ለሰይጣን ስራ መስዋት አረገኝ ልርቀው ብልም አማልችለው ከባድ ሰንሰለት አንገቴ ላይ ገባ በሚስጥራዊው መህበር ስር ወደኩ ብላ ጀርባዋ ላይ ያለውን የ ተኩላ ምልከት እና የ አይን ምልክት አሳየችው እና ይሄ የ ጨለማው ገዢ ፈረስ ነኝ ብለህ አራስህን ለመስዋእትነት መስጠት ይህ እንደ ምልከት ነው። ከዛም በላይ የታሰርከበት ሰንሰለት ነው በጅ የያስከውን አንድ ኢትዮሏያዊ አዛውንት ናቸው ከመልከት ጋር ይሄን ሳጥን በሬ ላይ ተቀምጦ አገኝውት ምን እየሆነ እንዳ ለመረዳት እስከሚያቅተኝ ድረስ ግራ ተጋባው እና ለ ቻርልሰን ፈጸሞ ሊታየው አልቻለም ተሰውሮት ነበር ብዙ ተከረከረኝ ላሳምነው አልቻልኩም ስለሚታየኝ መስቀል በመጨረሻ በካሚራ ይዢ ላሳየው ብሞከር ፈፅሞ ካሜራው በሚሰጠው ምልከት ላይም መስቀሉ ሊታይ አልቻለም በመጨረሻ ቻርልስ ነገሩን በሌላ ጉዳይ ተዘናግቶ እረሳው እኔም ይሄ ነገር ከ እኔ ህይወት ጋር ምን ተዛምዶ አዉ ስል ብዙ ጊዜ ከራሴ ጋር አወራለሁ ዛሬ ግን በግልጽ ሀይሉን ባንተ ምከኒያት አየሁት አሁን በጥቂቱም ቢሆን አንድ ሸከም ከላዬ አንደወደቀ ይሰማኛል ዶር ዋሲሁን ቅድስትን ጠበቅ አርጎ ወደ አራሱአቀፋት። መንዝ ማለት የቅዱሳን ማረፈያ ማለት ነው መንዝ ሦስት ቅዱሳን ወንድማማቾች ናቸዉ ጌራማማ እና ላሎ ኛ ትልቁመንዝ ጌራ መሐልሜዳ ትልቅ እና ሰፊው ግዛት ነው ። በዚህ ስር መንዝ ቀያ የሚባለው በአለም የጥበብ ቦታ ጥበበኞች ጥንት ጀምሮ ጥበበኞች ቤት የቤት ዕቃዎች ስፊቶቸ አፈረን ድንጋይን የሚያቀልጡ ብረት የሚሰሩ ጦሩን ጋሻውን ጎራዴውን ጥበብን የሚሰሩበት ጥበበኞቸ የነበሩበት ድንቅ ቦታ ነው ተኛ ትንሹ መንዝ ላሎ ወገሬ አፍቀራ አካባቢ የነገስታት መወለጃ መቀያየርያ መሾሚያ ያጠፋ የማቆያ የማስተማርያ ቦታም ነበር ወንዞች የሚገኛበት አዳባይ ወንዝ ያለው እዛ ነው ።
የሉሲፈር በትር ከሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን መከህከ ዶር ዋሲሁን በሁለት ሃሳብ ልቡ ተከፍሎዋል ምከኒያቱም የሚወደዎ ጃከሰን የሚስጥረኛዉ መህበር አባል መሆኑን እና አሱንም እስካሁን ከትትል እያረገበት እንደሆነ በቀዝቃዛዋ በርሊን አንድ ካፌ ዉስጥ ሳቅ በተሞላዉ ጨዋታቸዉ መሃል ከተደወለለት ጥሪ በዉሃላ አረዳዉ በሚስቱ ብርቱ ጥረት እና በሱ ከባድ ፍላጎት የተነሳ ወደ እዚ ሚስጥራዊ መሃበር እንደገባ ከገባም በዉሃላ ብዙ ሚስጥራዊ ስራዎችም ለመሃበሩ እንደሰራ እሱም አንዱ የስራዉ አካል እንደነበር በሚስጥራዊዉ መሀበር ዶር ዋሲሁን ከተመለመለ ቡሃላ ጊዜዉ እስኪደርስ ከትትል እየተደረገበት እንደነበር እንግሊዝ ዉስጥ በከፍተኛ መአረግ እሚያስመርቅ ዉጤት ሳይኖረዉ በመሀበሩ ትእዛዝ እንደተመረቀ ከዛም አልፎ ጊኒ ኮትዲቫር ሴኔጋልን ጨምሮ ለእነሱ አላማ በአፍሪካዉያን ስነልቡና የባህል ህከምና አሰጣ እንዲሁም በአፍሪካዉያን የጤና ስርአት ላይ ሰፊ ጥናት አንዲያካሂድ እንዲሁም ሲንጋቦር እና ታይዋን እንዲሁም ቻይና የባህል እክምና ጥበብ ላይ ምርምር እንዲያካሂድ ከዛም አልፎ ሆላንድ እና ጀርመን በህክምና እንዲያገለግል በቂ የስራ ልምድ አና እዉቀት አንዲያገኝ እንደተሰራ አሳካሁንም ግራጁዌወት ካደረገ ቡሃላ የስራ እድልም ሆነ ከኢትዮሏያ ጀምሮ አዉን እስካለባት ጀርመን ለእዚ መድረስ የነሱ እጅ እናዳለበት በቀላሉ አረዳዉ በወቅቱ ከቀልድ የቆጠረዉ ዶረ ዋሲሁን በፈገግታ ቢያልፈዉም ከኢትዮሏያ አንስቶ አሁን ህከምና እሚሰጥበት ሆስቢታል ድረስ የተፃፃፋቸዉን ኢሜሎች ላይ እስከዛሬ ግልዕ ያሎኑለትን ምልከቶች ማለትም ኢሜል ሱደረግለት ስድስተኛዉ መስመር ስድስተኛዋ ፊደልጋር ያለች ምልከት እንዲሁም የብቃት ማረጋገጫ ማስረጃዎቹ አንዲሁም የትምህርት ማስረጃዎቹ ላይ ያለችዉን ጥያቄ ስቶንበት የኖረችዉን ምልከት ጃከሰን አንብርት ላይ አንድወቅት ባህሩ ዳርቻ ላይ ሲዝናኑ ተመልከቶ በጠየቀዉ ጊዜ ጆንሰንም ያዉ ወጣት ስቶን እምታደርገዉን አታቅም መጀመሪያጊዜ ያፈቀርኩዋት ቫቤላ ትባላለች መጀመሪያጊዜ ያፈቀርኩዋት ቫቤላ ትባላለኝ ዩከሬናዊ ሴት ናት አዚ ጀርመን በንቅሳት ሰራ ትተዳደር ነበር እና ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ የፈፀምኩት ከሱዋጋ ነበር አዲስ እና አማላቀዉን ዓለም ነብር በደቂቃዎች ያሳየቺኝ ታዲያ ይሄ ጣፋጭ ጊዜ ገላዩ ላይ ማስታወሻ ሆኖ እንዲኖር የራስሽን ጥሩ ምልከት አኑሪልኝ አልኩዋት ታዲዲያ ይሂንን የተኩላ አራስ ምልክት ብልቴ ላይ ልትስል ሰትል እንደማየሆን ከዛ በተሻለ ደረቴን መርቼ ደረቴን ሰጠዋት አሱዋ ግን አንብርቴን መረጠች ሲል በወቅቱ እንዲ ሲል ዋሸቶታል ዉሸት ለጆንሰን የገለባያህል ቀላል ነዉ ደጋግሞ ዋሽቶት ተጋጭተዋል ነገር ግን ጆንሰን የተላከበት አላማ ነበረዉ እና ደጋግሞ ይቅርታ ጠይቆታል ዋሲሁን ቤተሰቡም ላይ ይሄ የዉሸት አመሉ ደጋግሞ አይቶታል እናቱን መኪና አደጋ ደርሶበት ሆስፒታል እንዳል አርድቱዋት ወደዛ ስትከንፍ ለከባድ አደጋ ተጋልጣ ሶሰቴ ቀዶ ጥገና አርጋለች አባቱንም እንዲሁ ዋሽቶት በፈጠረዉ ስህተት ለእስር ዳርጎታ በዛ የተነሳ ለእናት እና ላባቱ መለያየት ምክኒያት እንደሆን ባዶቅት ከባለቤቱ ያፍ ወለምታ ሰምቱዋል በዚ የተነሳ በሀሪዉ እንደሆነ ተረድቶ በየዋህ እነቱ እና ለሱ ባለዉ ጥሩ አመለካከት ምከኒያት ጥሩ ወዳጅ ሁነዋል የተዋወቁት ሊቨርኾላይ በተዘጋጀ እንድ የህከምና ፌስቲቫል ላይ ሲሆን ዋሲሁን ባቀረበዉ የባህል መድሀኒቶች ጥናት ላይ ባቀረበዉ እጅግ አንደተደነቀ አሱም በሙያዉ ፋርማሲስት እንደሆን ከ ሚላኖ እንደመጣ ነገር ግን ዶረ ዋሲሁን አምኖርባት ጀርመን የትዉልድ ሀገሩ አንደሆነች የምዕራቡዋ ጀርመን ተወላጅ እንደሆነ በመንገር በቅርቡ ወደትዉልድ ሃገሩ ጋዙን ጠቅሎ እንደሚመጣ እና ጥሩ ወዳጅም አንደሚሆኑ በመንገር ነበር ትዉዉቃቸዉ የጀመረዉ በርሊን በሚገኝዉ ግዙፍ አፓርትመት መጨረሻላ በሚገኘዉ መኖሪያ ቤቱ ዉስጥ ዶረ ዋሲሁን ሻዉሩን ከፍቶ እርቃኑን እንዳለ በሃሳብ ነጉዱዋል አይኑ በርበሬ መስሉዋል ሰዉነቱ ትኮራምቶ ፀሀይ የበላዉ የልተወጠር ቆዳ መስሉዋል ወስጡ የቀረዉን የጆንሰንን መርዶ ወሃዉ ያፀዳዉ ይበስል ደጋግሞ ጭቅላቱን አሸ ጮከ በማለትም ለምን ለምን ለምን እኔን ቆይ ለምን እኔን ቆይ ለኔ የሄን ሁሉ ለምን ወይኒ ወይኔ ዋሲሁን ከመታጠቢዉ ወቶ ፊቱን በፎጣ እየጠራረገ መስታዉቱ ላይ አፈጠጠ ዋሲሁን ሳር ሳሩን ሳር ሳሩን ስትበላ ገደል ጋር ነህ አሁን በል ወይ ዝለል ወይ ብሎ ሳይጨርስ ስልኩጠራ ካትሪን ነበረች ባስጨኩዋይ ሆስፒታል እንዲደርስ አንድ ሰዓት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ሰርጀሪ መደረግ ያለበት ሰዉ አንዳለ ነገረቸዉ ኬዙ ምንድ ነዉ ሲል ጠየቃት ከባድ የመኪና አደጋ እንደሆን ነገረቺዉ ቆይ ተረኛዉ ሀኪም ሉቫንዶቭ የለም እንዴ ሲለ ጠየቃት ከሱ አቅም በላይ እንደሆነ ሪፖርት አርጉዋል ደሞም ሰሞኑን ከህመም አንዳገገመ ለእንዲ ያለ ከባድ ኬዝ አቅም እንደሌለዉ ነገረችዉ ምን ምን ማደርግ እዳለባቸዉ አዞ ሲበር ወደ ሆስፒታሉ ገባ እንደደረሰ ወደ ቀዶ ጥገናዉ ከፍል እያመራ ሳለ ጥቁር ወጠምሻ ቅጥር ነብሰ ገዳይ የመሰሉ ሁለት ነጮች ገላመጡት ዋሲሁንን አይታ የሆነ የመረበሽ ስሜ ቱስጥ ገብተዉ ሲነጋገሩ ከመቅስፈት ተመልከቱዋል በቀጥታ ወደሰርጀሪ ከፍል ገባ አነ ካትሪን አንዲሁን ሌሎች እረዳቱዋ ሰዉዩዉን በቻሉት አቅም ለማትረፍ ከሞት ጋር ግብግብ ናቸዉ ዶረ ዋሲሁን ፈጥኖ ተቀላቀላቸዉ ሰዉየዉ ከፍተኛ ደም ከግንማሩ እና ካፍንጫዉ ይፈሳል በዚ የተነሳ የልብ ምቱ እየወረደ ነዉ ካትሪን በድንገት ዜሮ የሆነዉን የልብ ምቱን ለመመለስ ደጋግማ የግንበኛመለሰኛ በመሰሉ የልብ ምትን መመለሻ መሰሪያ ደጋግማ ደረቱ ላይ በማሳረፍ ሰወዩዉን በኤሌከትሪከ ሾኪንግ ልብ ምቱን ለመመለስ ትጥራለች ዋሲሁን የያዘቺዉን ተቀብሉዋት በተራዉ የሰዉዬዉን ልብ ምት ለመመለስ ደጋግሞ ሞከረ አጋጣሚዉ ቀናዉ እና የሰዉዩዉን ልብ ምት ለመመስ ተቻለ ኢትዮያዊ መሆኑን የሰውዬውን መልከ ተረድቶ ዶከ ዋሲሁን ገምቱዋል በፍጥነት እሚፈሰዉን ደም ለማቆም ቀዶ ጥገናዉ ማስጀመር እንዳለባቸዉ በማመን መረባረብ ጀመሩ ዋሲሁን ተጠግቶ የሰዉዩዉን የጉዳት መጠን ለመመልከት ሞከር ሰዉዬዉ ለተአምር ከሰመመኑ ነቃ በማለት አይኑን በጥቂቱ በቻ ገለጥ በማርግ በደም የተጨማለቀ እጁን እንደምንም በማሳት ዋሲሁን አረጉዋዴ ጋዉን ላይ ጆንሰን እንብርት እና እሱ ዶከመቶች ላይ ያስተዋለዉን የተኩላ አራስ በደሞ እንደነገሩ ሰርቶ ፀሃ ብሎ ፃፈበት ወዲያዉ መልሶ እራሱን ሳተ መምታት የጀመረዉ የልብ ምቱ ላይመለስ መልሶ አቆመ ዶረ ዋሲሁን ጋዉኑ ላይ ደም በነካ ጣቱ የፃፈዉን በፍፁም አላስተዋለዉም ዳግመኛ የቆመች ትርታዉን ለመመለስ ግብ ግብ ላይ ናቸዉ ነገር ግን አልተሳካም ነበር ሰዉዩዉ ላይመለስ አሸለበ ዋሲሁን ተስፋ በመቁረጥ እና በድካም ስሜት ዉስጥ በመሆን የለበሰዉን ጋዉን ሲያወልቅ ጋዋኑ ላይ በደምየተጣፈ አንድ ፁሁፍ እና ተኩላ አሜመስል ስዕል ተመለከተ ደንግጦ ግራ በመጋባት ስሜት ሆስፒሉን ለቆ ወደመኪናዉ ሲያመራ መኪናዉ በር ላይ ጆንሰነንን አገኘዉ ወደ አንድ ቦታ ሁኑኑ ሊወስደዉ እንደሚፈልግ አስቸኩዋይ እንደሆነ ነገረዉ ዋሲሁን በፍፁም ፍቃደኛ እንዳሎን ነግሮት ወደመኪናዉ ሊገባ ቁልፎቹን ሲያወጣ አምልጠዉት አመሬት ወደቁ ሊያነሳ ጎንበስ ሲል ማጅራቱ ላይ መርፌሲገባ ተሰማዉ እራሱን ስቶ ወዲያዉ መሬት ወደቀ ዋሲሁን አንድ ጥንታዊ አሚመስል ያምሰኮ ስፍራ አራሱን አገኘ አንድ እድሜአቸዉ ገፋ ያሉ አዛዉንት ከፊት ለፊቱ ተመለከተ ሰዉየዉ ጠጋ ብለዉ ወደ ጆሮዉ ፍጡር ለፈጣሪዉ መታዘዝ አለበት አንተን ደግሞ ሉሲፈር ታላቁ መንፈስ ፈጥሮሀል ከዛ ብስባሽ ዉስጥ አዉቶሀላ ያዘጋጀህ ለዚ አላማ አልነበረም አንተሌላ አቅዱ ነበርከ ለዛ ከፍተኛ ዘግጅት ላይ ነበርን ነገር ግን ከቁጥጥራችን የወጣ አሁን አዲስ ነገር አለ እና በፍጥነት ተጠራህ የጠራህ ፈጣሪህ ነዉ ስለዚ እጅ መንሻህን ለፈጣሪህ ታቀርባለህ ላንተ ሉሲፈር ዋጋ እማይተመንለትን የ ዓለም ጸጋ ሰቶሀል ዋጋህን ልትከፍል ጊዜው ደርሱዋል ከሁለት ቀን በውኃላ ያለህበት ሆስፒታል በቂ ጉርሻ ጋር ያየር ትኬትን ጨምሮ ወዳ ቺካጎ ይልከሀል እዛ አሚቀበል ሰው አለ ሌላው መረጃ አዛው ስደርስ ትሰማለህ ከዚህ ሀገር እስከምቶጣ ከማንም ጋር ግኑኝነት እንዳይኖርህ ትዛዝ ተላልፈህ ሰው ብታገኝ ያሰው ያን ምሽት አያድርም ይወግዳል ደሙም ለልኦል አምላካችን ጥቂቱ መሱዋት ይሆናል ግን ይሄ የደም ዋጋ ላንተ ስርየት አይሆንም ከማንም ጋር ዩዘ እንዳትፃፍ እራስህን ከዚ ሀገር እስከምቶጣ አግልል ። አካባቢውን የፖሊሶች ለቅስፈት ተቆጣ ጠሩት መግቢያ እና መውጫዎች ሁላ ፖሊሶች ፈሰዋል ዋሲሁን አንገቱ ላይ ጣልባረጋት አስካርፕ አራሱን ለመሸፈን እየታገለ እጁን ኪሱ ከቶ ወደዋናው መንገድ ሊደርስ ሲል አንድ ፖሊስ ከውኃላ አስቆመው ዋሲሁን አሁን ሰውነቱ ይበልጥ መራድ ጀምሩዋል ምን ቢጠየቅ ምን አንደሚመልስ አያቅምፖሊሱ ተጠጋ እና ወረቀቱ ላይ ያነበበውን ቃል ደገመለት ያረፈደ እንደካደ ይቆጠርበት እኔ የሱ ባሪያ ነኝ ደሜም ከሱ ወዝ ይቀዳል ከዚ ለቀ ወደ ተጠራህበት ሂድ አለዚያ ጭንቅላትህን አንተም ትሰጣለህ አለው ዋሲሁን ጥሎት ፍጥነቱን ጨምሮ ከቦታው ሸሸ እየተቻኮለ ወደ አየር መንገዱ ታከሲ በመያዝ አቀና ታከሲ ውስጥ ያለው ሬዲዮ የቻይና ህዝብ በ አዲሱ ተላላፊ ቫይረስ በከፍተኝ ሁኔታ እያለቀ እንደሆነ የሙዋቾች ቁጥር በሺውች እየሆነ በ ቫይረሱ የተጥቁት ደሞ እንደበለጡ መጠሪያው የ ኮሮና ቫይረስ እንደሚባል እናወደ ሌሎች ሀገሮችም በከፍተኛ ሁኔታ አየተዛመተ አንደሆነ ይዘረዝራል ዶር ዋሲሁን ነገሩ አሁን በጣም እየተገለጠለት ነው ሰውዬው ያሉት ደጋግሞ አሁንም ጆሮ ላይ ጮኸበት ፐርሰንት የ ዓለምን ህዝፅብ ለመቀነስ በጥንቃቄ ያቀዱትአላማ መንገዱን ስቱዋል ፍጥነቱን ጨምሮ ካሰቡት በላይ ገዳይ ለመሆን መገድ ላይ ነው ይባስ ብሎ ከትባቱ ሊሰራ አልቻለም ዶረ ዋሲሁንን እረጅም አመታት ወስደው በትምህርት እና በስራ ያሹት አፍሪካ ላይ ላሰቡት አላማ ቀኑ ሲደርስ አጥምቀው ሊልኩት ነበር ነገር ግን በዚ ክስተት ምክኒያት ለ አዲሱ ቫይረስ ከትባት ከሌሎች አባላት ጋር በመሆን ጊዜ ወስዶ እንዲያዘጋጅ ቀድመው በወንጀል አጥምቀው ከፊት ያቆሙት እንዲሁ እያሰላሰለ ቦታው ደረሰ ወደ አሜሪካ እሚበረው አውሮፕላን ገና አንድ ሰዓት አንደሚቀረው ተመለከተ ከ በላዩ አንድ የጀርመን ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰበር ዜናው ዶከተር ዋሲሁንን ፎቶ ሙሉ በሙሉ በመልቀቅ ከስር ኢትዮጴያዊው ዶክተር አሚሰራበት ሆስፒታል በድገተኛ አደጋ የገባውን ሰው እና አንድ ሌላ ለጊዜው ማንነቱ ያልተለየን ግለሰብ መኖሪያ ቤቱ በር ላይ በዘግናኝ ሁኔታ ገድሎ እንደተሰወረ በዝርዝር ያቀርባሉ ዶዋዲሁን ብርክ ያዘው ሰውነቱ መቀጥቀጥ ጀመረ የያዘውን ሻንጣ በቁሙ ለቀቀው የትም ወዴትም መሄድ ቀርቶ አሁን ማሰብም ከባድ ሁኑዋል ስልኩ በድንገት ጠራ አዛው ጀርመን እምትኖር በቅርቡ የተዋወቃት ኢትዮጵያዊቱዋ ሄለን ነበረች ዜናውን አይታ እንደደወለች ገምቱዋል አሁን አንስቶ ምንም ቢላትን አንደማታምነው ያቃል ማንንም እንዳያናግር ማስጠንቀቂያም ደርሶታል ስልኩን ማንሳት ትቶ ምንም እንዳልተፈጠረ በመረጋጋት ወደ መጸዳጃ ቤት ገባ ሁሉ ነገሩ በነሱ ከትትል ስር መሆኑን ተረድቱዋል ግን ፈፅሞ እጅመስጠት እንደሌለበት ገምቱዋል አሁን ጀርመን ላይ ያለው ጉዳይ አብቅቱዋል ግን ወደ አሜሪካም አንደማይሄድ ለራሱ ምሉዋል ግን ቢገሉኝስ እሚል ፍርሀት አድሮበታል ሆስፒታል ውስጥ በድገተኛ ገብቶ ሂወቱ ያለፈው ልጅትዝ አለው ጋዋኑ ላይ የተወለት መልከት ግን እሱን የመመርመር ዩዜ የለውም ምናልባት ይጠቅመኝ ይሆን ሲል አሰበ ስልኩ ላይ በዚ ሀሳብ እንደተወጠረ መልከት ገባ ከፍቶ ሲመለከተው መፅዕዳጃ ቤት በቂ ጊዜ አሳልፈሀል በፍጥነት ጀርመንን ለቀ ውጣ እሚል ነበር ዶር ዋሲሁን ግራ ተጋባ አሁን በ አነሱ መመሪያ እና ሀሳብ መሰረት እየሄደ ነው አበቃልኝ ሲል አሰበ ወንጀል እንደሰራ ዜና ተሰርቶበታል ነገር ግን ወንጀለኛ እሚሆነው ይሄን ጉዞ አሻፈረኝ ብሎ ጀርመን ከቆየ ብቻ ነው ከሰዓታት በውኀላ ዘብጥያ እንደሚወርድ ከዛም ሲከፋ ሞት እንደሚጠብቀው ያቃል። ቅድስት አንድ ሀይቅ ዳር የተነሳችው ፎቶ ነው በመዋኛ ልብስ ነች ከንዱዋ ላይ ከዚ ቀደም በተለያየ ቦታ ያየው የ ተኩላ ምልክት ነበር ከንዱዋ ላይ የተመለከተው ዋሲሁን ዶር ዋሲሁን ደጋግሞ አይኑን ባለማመን ተመለከተው አው ያድገተኛ ክፍል ህክምና ላይ በደሙ ጋውኑ ላይ የተወለት ስእል አሁን ከስር ያስለቀቀችው ቅድስት ላይ ተመልከቱዋል ዶር ዋሲሁን ቅድስት ሳሎን ዉስጥ ከተሰቀሉት ፎቶዎቹዋ ላይ አይኑን አንደተከለ ለደቂቃዎች ቆየ በተለይ ያን የተኩላ ምስል ከንዱዋ ላይ ተነቅሳ እሚያሳየዉን ፎቶ ዶር ዋሲሁን ከጨለማዉ ሞት ጋር ከባድ ትግል እያረገ እንደሆነ በይበልጥ ተረዳ ከ መት በፊት ነበር ዶር ዋሲሁን ጀርመን ዉስጥ በድብቅ የተቁዋቁዋመዉን የምርምር ቡድን እንዲቀላቀል በአለቃዉ ትእዛዝ የተሰጠው ዋሲሁንም አሚቀላቀለዉ የምርምር ቡድን ሚስጥራዊነቱ ሳይሆን በከፊል የተመለከታቸዉን የቡድኑ አባላት ስምዝርዝር ነዉ ያነበባቸዉ ስሞች ሁላ አሱ ትልቅ ቦታ አሚሰጣቸዉ አዉቅ መምህራን እና የህከምና ባለሙያዎች ናቸዉ ታዲያ ይሄ ደስታዉ አመድ የለበሰዉ የምርምሩ አላማዉ እና አቅዱን ከተረዳ በኃላ ነበር ነገር ግን እራሱን ለማግለል ፈፅሞ አማይችልበት የምድር ዉስጥ እጅግ ዘመናዊ ዋሻ ዉስጥ መሆኑ ነበር እዚ ችግር ዉስጥ የከተተዉ አለቃዉ እነደሆነ አንጂ ከሀገሩ ሲወጣ ጀመሮ ለእዚህ እቅድ ታጭቶ መሆኑን ፈፅሞ አልተረዳም ነበር ሁሉንም የተረዳዉ ጉዋደኛዉ ጀስቲን ሁሉንም ያረዳዉ ቀን ነበር አሱም አባል አንደሆነና እንዲከታተለዉ ሚሸን ተሰቶት እንደሆነ እና አሁን ጊዜዉ እንዳበቃ እና አባል በመሆን ማድረግ ያለበትን በሚሰጠዉ ትዛዝ መሰረተ እንዲያደርግ ነበር ከእዛ ትልቅ ምርምር ዋሻ ማምለጥ ባይችልም ያለዉ አማራጭ ያሰቡት የሰይጣንን ስራ አግር በእግር እየተከተሉ ስሩን በመያዝ እንዳያገግም መበጠስ እንዳለበት ለራሱ ቃል ገባ አዎ ምከኒያቱም የያዙት አደገኛ አላማ ሰይጣናዊ ስለ ነበር አላማቸዉ የእነሱን አባላት ሳይነኩ የበዛዉን የዓለምን ህዝብ በከፊል እንኩዋን ባይሆን እሩቡን መቀነስ ነበር እሳቢያቸዉ ዶር ዋሲሁንም የቫይረሱ ጉዳይ ላይ አጋጣሚ ሆኖ ባይሳተፍም የከትባት እና የመዳኒቱ ጉዳይ ላይ ዶር ዋሲሁን የ አንበሳዉ ድርሻ ይወስዳል ሙከራዉ ተጠናቆ ዉጤታማ መሆኑን በደብ ተረጋግጦ ሲያበቃ ቫይረሱ ወደ ምድር ሲበተን የአዉሬዉን ምልከት በከንዳቸዉ እና በግንባራቸዉ ካላደረጉ በወረርሺኙ መአበል እንደሚመቱ በመግለፅ ዋሲሁን በሌለበት ለድላቸዉ ዉስኪ ሲጋጩ በድብቅ ተመልከቱዋል ለዛም ነዉ አንድ ቀን በማያስጠረጥረዉ መልኩ ከሌሎቹ አባላቶቹ ጋር የደረሰበትን የክትባት አና መድሀኒት ግኝት እንዳይሰራ በጥበብ ያመከነዉ ወረቀት ላይ የቀሩትንም በጥንቃቄ አንድ በአንድ ነበር የቀየረዉ አሁን ላይ ያን ቀን ሲያስበዉ በጀብደኝነቱ ከት ብሎ ይስቃል የተንኮል ጊዜዉ አልቆ ሙሁራኑ ከምድር በታች ካለዉ የምርምር ዋሻ ከወጡ በዉኃላ ዶር ዋሲሁን ማናቸዉንም አላገኛቸዉም ሳይገደሉ እንዳልቀር ጭምጭምታዉን በአንድ ወቅት ሰምቱዋል ምናልባት እሱን የተዉት ለተጨማሪ የተንኮል መሳሪያ እንድሆን ይሆናል ይላል ዶር ከሄደበት ሀሳብ የተመለሰው ከውጪ በሰማው ከፍተኛ ግርግር ነበር ወደ በሩ በርጋታ በማምራት ላይ እንዳለ ቅድስት ከውስጥ አራሱዋን በፎጣ ጠቅልላ ቀድማው ወደ በሩ አመራች በሩን እንደከፈተቸው ከፊቱዋ ካለው ቤት ሁለት ከ እራስ ጸጉራቸው እስከ እግር ጥፍራቸው ነጭ ጭንብል የለበሱ የ ህከምና ባለሙያውች አንዲት በ አድሜያችው ጠና ያሉ ህመምተኛን እያጣደፉ ይዘዋቸው ወደ ሊፍቱ አመሩ አንዲት ልጅ የ አፍ መሸፈኛ ማስክ አርጋ አያለቀሰች ትከተላቸዋለች ከቅድስት እና ከ ዶር ዋሲሁን ሌላ ማንም በሩን ከፍቶ የወጣ ዶር ዋሲሁን ምን እንደተፈጠረ ጠየቃት። ካጋጆቹ አንደኛው ወጣ መሳሪያውን አቀባብሎ ሊገላት ሲል ቀድማው መታችው ቀሪዎቹንም ፈጠን ብላ ከቅልጥፍና ጋር ገደለቻቸው ነገር ግን ከመሞት ይልቅ ሰውነታቸው ወደ ጥቁር ተኩላነት እየተቀየረ ልብሳቸው ተቀዳዶ ሰውነታቸው ጸጉር መልበስ ጀመረ ጥርሳቸውም ሰውኛ ቀርቶ የ አውሬ ሆነ በ አንዴ ወደ ግዙፍ ተኩላነት ተቀየሩ የሉሲፈር በትር ከፍል ወደ ጥቁር ተኩላ እነት የተቀየሩት የ ዶር ዋሲሁን አጋቾች ውስጥ አንደኛው ወደ ቅድስት መንደርደር ሲጀምር አንዱም የመጀመሪያውን ተከትሎት ወደ ቅድስጥ እሮጠ የቀረውም እንደ ሁለቱ እራሱን መቀየር ሲጀምር ዶር ዋሲሁን ከመኪናው ፈጥኖ ወጣ አስፓልቱ ላይ ካንዱ ወድቆ ያገኝውን ሽጉጥ በማንሳት ወደ ውኃላው ሸሸሸ ነገር ግን ከተቀየሩት ሶስተኛ መኪናውን ሲያሸከረከር የነበረውን በመጨረሻም አራሱን አንደ ሁለቱ ወደ ጥቁር ተኩላነት የቀየረው ሰው ወደ ዋሲሁን በከፍተኛ ፍጥነት መሮጥ ጀመረ ቅድስት በከፍተኛ ፍጥነት ወደ አሱዋ እሚመጡት ተኩላውች ምንም የመረበሽ አልፈጠረባትም ፈጥና ከላይ የለበሰችውን ሹራብ አውልቃ ከጀርባዋ ያለውን ንቅሳት ወደ ተቀየሩት ተኩላውች በመዞር አሳየቻቸው ሰውነቱዋን ለታሪከ እንዳይቀር ፈትፍተው ሊናጠቁዋት በከፍተኛ ቁጣ ጥርሳቸውን አስለው ወደሱዋ እሚሮጡት ተኩላውች ከመቅስፈት ዞራ ጀርባዋ ላይ ያለውን የተኩላ ንቅሳት ብታሳያቸው ባለቤቱን እንዳየ ውሻ ጭራቸውን ቆልተው ወደ ውኃላ የ አስፓልቱን አቁዋርጠው ጥቅጥቅ ወዳለው ጫካ ሸሹ ዋሲሁን ደጋግሞ እየተጠጋው ወዳለው ጥቁር ተኩላ ቢተኩስም ፈጽሞ ሊመታው አልቻለም እርቀታቸው ጠቦ እየሸሸ ያለው ዶር ዋሲሁን ላይ ከጀርባው ተከመረበት ዋሲሁን እላዩ ላይ የወደቀው ግዙፍ ጥቁር ተኩላ ፈጽሞ ሊቁዋቁዋመው አልቻለም ወደቀ ዋሲሁን በደመ ነብስ መወራጨት ያዘ እጅግ የተቆጣው ተኩላ ዶር ዋሲሁን ከጀርባው በጥርሱ በመያዝ ወደ ላይ አንጠልጥሎት ወደ ጫካው እሮጠ ዶር ዋሲሁን ከጀርባው ከፍተኛ ህመም ቢሰማውም ከሚጎትተው ተኩላ ለማምለጥ በቻለው አቅም ታገለ ። በሩ ተከፍቶ አንድ ሰው ዶር ዋሲሁን ወዳለበት ገባ ዋሲሁን ሰውዬን እንዳየው ደንግጦ ከወገቡ ቀና ለማለት ሞከረ ነገር ግን ፈፅሞ አቃተው ከጎኑ ያለው የልብ ምት መቆጣጠሪያ መሳሪያ ድንጋጤውን በድምጽ ደጋግሞ እየጮኸ ፍርሀቱን ተናገረ ቅድስት ከፍሉን ለቃ ተነስታ ወጣች ከዛ ግዙፉ ሸበቶ ሰውዬ ወደ ዋሲሁን በእርጋታ ዶከተር ዋሲሁን እራሱን ያገኝበት አልጋ ላይ የ ከፍሉን በር ከፍተው በገቡት መጀመሪያ በገዛ ጉዋደኛው ታፍኖ ከተወሰደ በውኃላ ከፍተኛ ትእዛዝ ና ማስፈራሪያ ሲያደርሱት የነበሩት አዛውንት ነበሩ ዶረ ዋሲሁን አልጋው ላይ እንዳለ ወደ ውኃላው አፈገፈገ ጀርባው ላይ ያለው ቁስል ከፉኛ ተሰማው ሸብቶው ሰውዬ ጠጋ በማለት ከማይሆን ነገር ጋር እየታገልከ ነው ዶከተር ባንተ ምከኒያት በቀን ከ ሺ ያላነሰ ሰው አንደ ቅጠል እየረገፈ ነው ይሄ የመጨረሻችን ጥያቄ ነው የከትባቱን ፎርሙላ እና የመዳኒቱን ቀመር እዚሁ አልጋ ላይ ትሰጥናለህ ሰዓት ይበቃል ሰውዬ ከፍሉን ጥለው ተመልሰው ሲወጡ ቅድስት ተመልሳ ገባች አልጋው ጫፍ ላይ መታ ተቀመጠች ሰውነቱዋ ተላልጦ ተጎድቱዋል ፊቱዋም ተበሳቁሉዋልአተኩራ ውደሱ እያየች ቫይረሱ በከፍተኛ ተሰራጭቱዋል ማንም ማንንም ማዳነልቻለም ያገገመውም መልሶ እየታመመ ነው አቃለው ስጋትህ አና ስሜትህን አረዳለው ግን አሁን ለዚ መፍትሄ መሆን አለብህ ለምቶዳት ሀገር ስትል ይሄን ድርግ አለችው ዶር ዋሲሁን አልጋው ላይ በእርጋታ እየተመቻቸ መስማማቴን ቀደም ብዬ አንቺው ቤት አያለሁ እንደ ገለፅኩ እረሳሽ እስኪ መልሽልኝ እዛ ቦታ ለምን መጣሽ አሳልፈሽ ከሰጠሺኝ በውኃላ ለምን ተመልሰሽ መተሽ ያንን ሁላ ግርግር ፈጠርሽ እዚስ አንዴት ልገኝ ቻልኩ። ከሱ በላይ የቅድስት አሱን አለመግደል አስገርሞታል የተኛበትን ትራስ ሁለት ቦታ በጥይት በስታዋለች ያግኝችው ግን ትከሻውን ብቻ ነበር ይሄ ደሞ እሱን ላለመግደል ያረገችው እንጂ ስታው እንደማይሆን ተረድቱዋል ግን ለምን እንድተርፍ ፈለገች ምናልባት ሌላ አቅድ ይኖራታል ወይም ሌላ አለ ዋሲሁን ክፍሉን ለቆ ለመውጣት ያለበትን ውኔታ እና አካባቢውን እየቃኝ የእጁን ህመም መቁዋቁዋም ግን ከብዶታል በእርጋታ ዙሪያውን እየቃኝ ወጣ ሁሉም ነገር ፅጥ እንዳለ ነው አንድ አፓርትመንት ውስጥ እንዳለ አውቁዋል ኮሪደሩን ይዞ በመውጣት ላይ አያለ ከዚ ቀደም እራሳቸውን ወደ አውሬነት የቀየሩትን ሁለት ግዙፍ ሰውች አሱ ወዳለበት ሲመጡ ተመለከተ ፈጥኖ አንድ መታጠፊያ ላይ ዞር በማለት አመለጣቸው ከዚ ቀደም ከ ሆስፒታል ሲያመልጥ ከነበረው ምንም አልተለየም የታካሚ ቀሚስ እና አንድ ከፍት ጫማ ነበር ያረገው በልቡ ይፅልይ ጀመር ሰውቹ አልፈውት ወደ ከፍሉ ሲገቡ ፈጠን በማለት የ ሊፍቱን መጥሪያ ተጭኖ ጠነቀ ነገርግን ዘገየበት ሰዎቹ ከ ህከምና አልጋው ከፍል ሲያጡት ፈጥነው ተመልሰው ሲወጡ ኮሪደሩ ላይ ሊፍት ሲጥብቅ አዩት ለመያዝ ወደ አሱ ፈጠኑ ዋሲሁን ወደ እሱ እሚመጡትን ተመልከቶ ሊፍቱን ደጋግሞ በመደብደብ ጠራው አጋጣቢ ሆኖ ሊፍቱ እሱ ጋር ደርሶ ተከፈተለት ዋሲሁን ወደ ሊፍቱ ፈጥኖ ሲገባ አእሚያሳድዱትም እሮጠው በቻሉት ፍጥነት እሮጠው ሊፍቱ ሊዘጋ ሲል አንደኛው ፈጥኖ እጁን በመከተት እንዳይዘጋ አገደው ሊዘጋ የነበረው ሊፍት ተከፈተ ዋሲሁንን አዛው ሊፍት ውስጥ በቦክስ ጠመዱት ዋሲሁን በከባድ ህመሙ ላይ የነሱ ተጨምሮ አራሱን ሊስት ምንም አልቀረውም አምትፈልጉትን እንዳታጡ እባካችሁ በቃኝ ከዚ በላይ አትጉዱኝ ሲል ለመነ በጥይት ከተመታው ከንዱ ጋር ተዳምሮ ከ አፍንጫው እና ካፉ አሚወርደው ደም እጅግ አዳከመው ሊፍቱ መሬት ደርሶ ሲከፈት ግን ቅድስት መሳሪያዋን ወድራ ሞት ደግሳ ነበር ሁለቱን ወጠምሾች የጠበቀጫቸው ግንባር ግንባራቸውን ብላ ገደለቻቸው በድብደባ እና በደም የሰከረውን ዶር ዋሲሁን ደግፋ ከ ኢፓርትመቱ ወጣች ነገርግን ዙሪያዋ ምንም አይነት መኪና አላገኝችም ምን ማረግ እንዳለባት ግራ ተጋብታ ሳለ አንድ ጥቁር መርቸዲስ ፊታቸው መቶ ቆመ መስታውቱን ዝቅ አርጎ አንድ ሰው በፍጥነት አንዲገቡ ነገራቸው ሰውዬውን ስታይ ቅድስት የጨለመ ተስፋዋ በራ ዋሲሁንን እንዲገባ አርጋ እሱዋም ተከትላው ከጎኑተቀመጠች አንድገባች ቅድስት የ ዩኒቨርስቲ ጉዋደኛዋ ደቡብ አፍሪካዊው ራዎል ነበር ቅርብ ከነበሩዋት ሴት ጉዋደኞች በተሻለ ከ ራውል ጋር ጥሩ ግኑኝነት አላት ጨዋታ አዋቂእና ቁምነገረኛ ነው እያለች ብዙ ጊዜ ለጉዋደኞቹዋ ታሞካሸዋለች ካንድ ቀን ለሊት የዘለለ የወሲብ ታሪከ የላቸውም ያንንም ቀን መደረግ አልነበረበትም ትላለች ግን ስለሆነ አትፅትም የጉዋደኛዉ ፓርቲ ላይ ገብዙዋት ብዙ ስለጠጣች እንዲሁን ሄሮይንም ወስዳ ስለነበር ነው ከ ጉዋደኝነት ውጩንድም ቀን ስለ ቀሪው ግኑኝነት አስባው አታውቅም አደዛዥ እጽ ያስጀመረችዉም እሱዋ ነች በሱ የተነሳም ለብዙ ተደራራቢ እስርም ተዳርጉዋል ያበመሆኑ አሁን ላይ ቅድስት ትፅፅታለች የነበራትን ዱርዬ እና አስቀያሚ ህይወት ራዎልንም እንዲካፈል አድርጋለች ከ አፅ አዘዋዋሪውች ጋር ህገወጥ ስራን አንዲሰራ አድርጋ ለች በዛ የተነሳም ከቤተሰቡ አቆራርጣ ብቸኛ አርጋዋለች በተደጋጋሚ የሱ ስሜት እንደተቀየረ ቢነግራትም ፈጽሞ በዛ መንገድ እንደማትቀበለው ነግራዋለች ከ ገዛ ጉዋደኛው ጋር ፍቅር ስሰራ ስለደረሰባት በዛ ንዴት ነበር የገዛ ጉዋደኛዋን ደፍሮ ዘብጥያ የወረደው ማረሚያ ቤት ውስጥም እስረኛ ገድሎ በሌላ የነብስ ማጥፋት ወንጀል ተከሶ ዓመት እስሩ ወደ አድሜ ልከ የተፈረደበት ራዎል በእስር ላይ እያለ ነበር ታዲያ ለ ጭለማው መህበራት ስር የተመለመለው ከ እስር ከመፈታትም በላይ አሁን ባለ ብር እና ሀብታም ሆኑዋል በዛው ልከ ታዲያ ለብዙ ግዳጆችተልኮ ብዙ ከፉ ስራን ሰርቱዋል ገድሉዋል አስገድሉዋል ። አሁን ዓለም ለ ራዎል ልዩ ናት ሌላ ስብእና እና አዲስ ማንነትን ሰታዋለች ከ እስሩ ከተፈታ አንዴ ብቻ ነበር ቅድስትን ያገኛት ባደረገው ድርጊት ብታፍርበትም ናፍቆቱዋን ግን አቻለችውም ነበር ከንፈሩን ምጥጥ አርጋ ነበር ደስታዋን የገለጸቸችለት አዎ አሁን ይወዳታል ስትስመው ከንፈሩን አልከለከላትም በሱዋ ብዙ ፈተናን ቢያሳልፍም ካሳለፈው እሬት ጊዜ ጥቂት ስማው እምታጣፍጠው ከንፈሩ የመረረውን ታሪኩን ታስረሳዋለች የ ቅድስት ወብ ከንፈሮች እና አይኑዋ ለ በቀል የተሳሉ ሰይፎችን ከ ሰገባ ይመልሳሉ ይላል ግን ልቡዋን አውጥቼ ለውሻ ብሰጠው ደስ ባለኝ ይላል እራውል የቅድስት ልብ ከ አሞት ይቆመጥጣል ልቡዋ ለ አሱዋ ሳይሆን ለ ውሻ ይገባል ይላል እራውል ስለ ቅድስት ባሰበ እና በተከዘ ቁጥር ከእስር ላይ እያለ ለ ሰይጣኑ በሀበር ያስመለመለችው ቅዴድስት ነች ይሄን አውነት ያወቀ ቀን ደውሉላት ነበር አንተን ለማስፈታት ከዚ የተሻል አማራጭ አልነበረኝም ብላዋለች ቅድስት ግን ለ አሱ አስባ ሳይሆን ላሰቡት አላማ ከሱ የተሻል ስላላገኝች ነበር አሁን ባስቸጋሪ ጊዜ ደርሶላታል ግን ህንድ እንደነበር ነው እምታቀው አሁን እዚ የ ራዎል መገኘት አስገርሙዋታል አሁን እሱን እምታስብበት ጊዜየላትም ምከኒታቱም ዋሲሁን ብዙ ደም እየፈሰሰው ነው የደረሰበት ድብደባ አሱዋ ከተኮሰችበት ጋር ተዳምሮ ህመሙ ጠናበት አሁን ወዴትም ሆስፒታል ይዛው ልቴድ አትችልም ምከኒያቱም ሆስፒታሉ በሙሱ ሌላ ኢመርጀንሲ የመቀበል አቅም ላይ አደሉም ሁሉም በኮረና ታካሚውች ተጨናንቀዋል ከሚድነው የሚሞተው ቁጥር አየጨመረ ነው ሀኪሙም ሆነ ነርሱ ሁሉም ጊዜ የለውም ምን ማድረግ አንዳለባት ግራ ታጋብታ ባለችበት ሰዓትመኪናዋን ትራፊክ ይከተላት ጀመር ቅድስት ራኦልን በፍጹም እናዳያቆም ለመነችው አሱም ፍጥነቱን ጨምሮ ነዳው ፖሊሶቹ መከታተላቸውን ከሆነ ሜትር በውኃላ አቆሙ ወደዴት እየወሰዳቸው እንደሆነ ጠየቀችው እኔ አእማቀው የግል ህክምና በመኖሪያ ቤቱ አሚሰጥ ጉዋደኛ አለኝ ወደዛ እኔዳለን በወቅቱ ሁኔታ ምናልባት ላያስገባንም ይችላል ግን እድላችንን እንሞከር አላት በ ግንባር መስታውቱ በኩል ቅድስትን እያያት ቅድስትም ቀጠለች እና እንዴት እዚ ልትመጣ ቻልክ አለችው ራዎልም በግንባር መስታውቱ ሰረቅ አርጎ አያት እና ቻርልሰን ያንቼለቃ ነው እንድረዳሽ የላከኝ አላት ቅድስት በውስጡዋ ነገር ይመላለስ ጀመር ቻርልሰን አንዴት ራዎልን ሊልከው ቻለ ራውል በእነ ሞርጋን ከንፍ የሰለጠነ አንደሆነ ታቃለች ምናልባት በድብቅ ለ ቻርሊ ይሰራ ይሆን ስትል አሰበች ወደ አንድ ሰፊ ግቢ ገቡ በ አበቦች እና በትላልቅ ፋውንቴኖች የተዋበ ሰፊ ግቢ ራውል መኪናዋን ካቆማት በውኃላ የውኃላውን በር ከፍቶ ቅድስትን በማገዝ ዋሲሁንን ደግፈው ወደ ህንፃው ገቡ እስካሁን አንድም ሰው አላጋጠማቸውም የሰፊውን ከፍል ኮሪደን በቀያይ መብራቶች አጊጡዋል ግን በከፊል በጭለማ የተዋጠውን ሰፊውን ክፍል ኮሪደር ጨርሰው ወደ አንድ ጠባብ ከፍል ገቡ አሁን ቅድስት ውስጡዋን ጥርጣሬ እየገባው ነው ከውሀላቸው በሩን ከፍቶ ሞርጋን ወደ ከፍሱ ገባ ቅድስት ፈጥና ከጀርባዋ ሽጉጥ ልታወጣ ብትሞከርም ራውል ቀደማት እና ሽጉጡዋን አስጥሎ በጥፊ አጎናት ቅድስት ተገዳግዳ በጀርባዋ ወደቀች ዋሲሁን ሰውነቱ ዝሎ እና ተዳከሞ ስላለ አፍጹም ቅድስትን ሊያድናት አልቻለም ራዎል እዛው የተኛችበት ሆዱዋላይ አረግጦ ያዛት ሞርጋን ወደ ቅድስት በርከከ በማለት አንድ በ አንድ ጥፍርሽን ጸጉርሽን እነቅለዋለሁ በጣቶችሽ እና በጸጉርሽ ልከ ስቃይሽን አንድ በ አንድ አዳም ጠዋለሁ ጥቁር እንደምጠላ እኮ ነግሬው ነበር አላዳመጠኝም ያ ደደብ አለቃሽ ሰውነትሽን ቆራርጩ አሁን አልከለታለሁ ብሉዋት ከኪሱ ከተር አወጣ እና ጣቱዋ ላይ አስገባ ቅድስት የስቃይ ድምፅ ታሰማ ጀመር ሞርጋን ከተሩን ማጥበቅ ሲጀምር ዶር ዋሲሁን በከፍተኛ ህመሙ ውስጥ ሆኖ ቅድስት አንድ ነገር ብትሆን አፉውስጥ ያለውን ከፍተኛ የ አሲድነት መጠን ያለውን ትንሸዬ የፕላስቲከ ቅንጣት በጥርሱ እንደሚያፈርጠው እና ላንዴ አና ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚሞት እሱም ህልሙን እንደያዘ አንደሚቀር ነገረው ሞርጋን በሳቅ ቤቱን ሞላው እና ቅድስት ጣቶችላይ ያረገውን ከተር መልሶ አጠበቀው ዶረ ዋሲሁን በህመሙ ውስጥ ሆኖ ከትከት ብሎ እሱም ሳቀ እና እሱዋን ለቀቃት አና አንተ ሞኝ አሚጠቅምህን ልስጥህ ቻርልሰን በብዙ እየቀደመህ ነው ከሱ ጥቂት ኮዶችን ደብቄዋለሁ ግን አይደርስበትም ማለት አደለም ግን ቅደመው ጣት መቁረጥህን ትተህ አንተ ሞኝ ልሞት ደቂቃውች ነው የቀሩኝ እሱዋን ካለቀከ ይዝፔአ መቃብር ነው አምወርደው አንተ ሙትቻ አለው ሞርጋን ቅድስት ጣቶች ላይ ያስገባውን ከተር አወጣው እና ቅድስትን በካልቾ አጎናት እና ወደ ዋሲሁን ሄዶ እ ፍጠን ንገረኝ አለው ድምፅ መቅጃ ከኪሱ አያወጣ ቅድስትን መጀመሪያ ከፍሉን ለቃ አንድቴድ አድርግ አለው ሞርጋን ቅድስትን እንዲለቃት በምልከት ለ ራዎል ነገረው ራውል ቅድስትን ከመሬት ፅጉሩዋን ይዞ አነሳት ቅድስት ቅድም ያስጣላትን ሽጉጥ በጥንቃቄ አንስታው እራዎልን እግሩ ላይ ተኮሰች አራውል እመሬት ላይ ወደቀ ሞርጋን ሽጉጡን አውቶ ቅድስት ላይ ደቀነ ቅድስትም አንደዛው ደቀነችበት አንቺ እባብ ምንድነው ያረግሽው በነብስ ከዚ አምቶጪ መስሉሽ ነበር አላት ሞርጋን ራዎል እግሩን ይዞ መሬት ይንፈራፈራል በዚ መሀል ዋሲሁን ቀደመና አጠገቡ ከወደቀው ራዎል ላይ ሽጉጥ ስሞ ሞርጋን ደረት ላይ ተኮሰ ሞርጋን በዛ ቁመቱ መሬት ላይ አረፈ ቅድስት ፈጥና ዶር ዋሲሁንን ይዛ ከቦታው ሸሸች ኮሪደሩን ጨርሰው እንደወጡ በርላይ ተኩስ ሰምተው እሚመጡትንየ ሞርጋን ጠባቂዎችን ተምለከቱ ምንም አማራጭ ስላል ነበር ከጠባቂዎቹ ጋር ተኩስ ገጠመች ቅድስት ከ አቅሙዋ በላይ ሲሆን ዋሲሁንን እንደደገፈች ወደ ውኃላ ሸሸች ጥባቂዎቹ አየተቃረቡ ሲመጡ አንድ ቦታ መሸሸግ እንዳለባቸው ቅድስት ለዋሲሁን ነግራው ተደበቁ ዋሲሁን አሁን ከወትሮው ከፍተኛ ድካም እና አራሱን ያዞረው ጀመር ቅድስት ነገሮች ካቅሙዋ በላይ እየሆኑባት መጡ አራሱዋን ወደ ተኩላ መቀየር እንዳለባት ወሰነች ግን ከዋሲሁን ክንድ ላይ ደሙ እንሳይፈስ ያሰረበትን ጨርቅ ፈታ ደሙን አፉዋን ገጥማ መጠጥቸው ቅድስት አይኑዋ መቅላት ጀመረ እራሱዋን ከግንብ ጋር አያማታች ውጣ ከዚ አንደምንም አያለች ጮኸችበት አራሱን መሸከም ያቃተው ዋሲሁን እንደ ምንም እንደ ሰካራም እየተንገዳገደ እና አየተጋጨ የቅድስትን ሽጉጥ ይዞ ሸሸ ጠባቂውቹ ዋሲሁንን አይተው ተከተሉት ዋሲሁ እየተኮሰ ወደውኃላው ሸሸ ቅድም ከወጣበት ኮሪደር አንድ ጥቁር ተኩላ ወደሱ ሲመጣ ተመለከተው መገመት አላቃተውም ቅድስት ናት ብሎ አሰበ ነገር ግን ቅድስት አልነበረችም ሞርጋን ነበር ምከኒያቱም በከፊል ጽጉሩ በደም ተጨማልቁዋል ዋሲሁን አሁን ለመሸሽ አቅም አያጣ መጣ እራሱዋን ወደ ይቀጥላል ተኩላ ነት የቀየረችው ቅድስት ሞርጋን ዋሲሁን ጋር ከመድረሱ በፊት ቀድማ መንገድ ዘጋችበት ዋሲሁን እንደምንም መሸሽ ጀመረ መኪናዋ ጋር ሲቃረብ ራውል ተኩሶ የመኪናዋን ጎማ አስተኛት ዞር ሲል እራሳቸውን ወደ አውሬነት የቀየሩት ሞርጋን አና ቅድስት ትግል ገጥመዋል ራውል እግሩን እየጎተተ ከጠባቂዎቹ ጋር ወደ ዶር ዋሲሁን መጣ ዋሲሁን ለራሱ ሽፋን እየሰጠ የ ሞርጋን ጠባቂውቹ መኪና ውስጥ ገባ ባለው አቅም መኪናዋን አስነስቶ ሸሸ ቅድስት ከሞርጋን ጋር ግብ ግብ ላይ ናት ሊያውም የ አውሬ ጠብ ሰው በበሀሪው ያልፈታውን ጠብ በ አውሬነቱ ሲወጣው ይከፋል ቅድስት ያቅመሙዋን ከ ሞርጋን ጋር ታገለች በመጨረሻ የ እነ ራዎል እና የጠባቂውቹ ተኩስ ሲጨመርባት አራሱዋን ለማዳን ሸሸች ባገኘቸው ባላት አቅም በ አውሬነት ጠባዩዋ እሮጠች ሞርጋንም ባውሬ መልኩና ጠባዩ ተከተላት ዋና መንገዱን አልፋ ጫካውስጥ ገቡ ሞርጋን ፈጽሞ ሊለቃት አልቻለን አሳደዳት። በሩ ተከፍቶ ሰው ሲገባ አንኩዋል አልሰማም ነበር የዋጠው መዳኒቶች ከ ህመሙ ጋር ተጨማምረው አድከክመውታል ግን በሩ ተከፍቶ ሰው ወደ ውስጥ ገብቱዋል ዋሲሁን ከሰዓታት በውሀላ ከወሰደው እንቅልፍ ሲነቃ ከፍሉ ውስጥ የደም ነጠብጣብ ተመለከተ የ እሱን ማፅዳቱን ያስታውሳል ነጥብጣቡን ተከትሎ ወደ ውስጥ እየገባ ድንገት ቀደም ሲል በከፍል ቅድስት አራሱዋን ወደ ተኩላነት ቀይራ ከ ሞርጋን ጋር ግብግብ እንደገጠመች ዶር ዋሲሁንም ከወሰደው እንቅልፍ ሲነቃ ከበሩ ጀምሮ የደም ነጠብጣብ እንደተመሰከተ ያንን ነጠብጣብ ተከትሎ ወደ ውስጥ እየሄደ ነበር ያቆም ነው ዶር ዋሲሁን የደም ነጠብጣቡን እየተመለከተ ኮሪደሩን ይዞ በእርጋታ ሲሄድ የደም ነጠብጣቡ ሄዶ ሄዶ መታጠቢያ ቤቱ ሲደርስ ይቆማል ዋሲሁን በእርጋታ የመታጠቢያ ቤቱን በር ከፈተው ከፍሉ በደም ጎርፍ ተጨማልቆ ወለሉ ላይ ቅድስት እራሱዋን ስታ ተዘርራለች ዋሲሁን ፈጠን ብሎ ከወገቡዋ አነሳት እና አንገቱዋ ስር በህይውውት መኖሩዋን ቼክ አረገ የልብ ምቱዋ እየቀነሰ ነበር ዋሲሁን ፋጥኖ አነሳት እና መኝታ ቤቱ አልጋ ላይ ወስዶ አረጋት ሃኪም ስለሆነ ማድረግ ያለበትን የመጀመሪያ አርዳታዎች ሁሉንም አረገ ነገር ግን ቅድስት የልብ ምቱዋ ፍጹም እየቀነሰ እና እያጠረ ነበር ብዙ ደም ስለፈሰሳት ደም ካላገኘች እንደምትሞት ዋሲሁን አሰበ ጉልኮስም ያስፈልጋታል በህይወት ለመቆየት ሌላ ምንም አማራጭ አልነበረም ምን አንደሚያረግ መላ አጣ ከተማ ውስጥ ሆነ ከዛ ውጪ መቀሳቀስ አይቻልም እኩዋን ህከምና ማግኘት ይቅር እና መውጣትም አይቻልም በዛላይ የደም አይነቱዋን አያውቀውም መፍጠን እንዳለበት ተረድቱዋል በዘገየ ቁጥር ቅድስት እያመለጥችው እንደሆነ ተረድቱዋል በዚ መሀል ነበር አንድ ሀሳብ ወደ ውስጡ የገባው የደም ዝውውሩዋን በጥቂቱም ቢሆን ለ አንዴ እንዲነቃ የልብ ምቱዋን እንዲጨምር ማረግ ከዛም የ አውሬነት ጸባይዋን በማምጣት እንድትነከሰው ለ አንዴ ማድረግ ይሄን ደሞ አድርጋዋለችከ ሞርጋን ለማምለጥ አሁን ቤቱዋ ውስጥ ምናልባት ያስቀመጥችው አነቃቂየ አድገኛ እጽ እንዳለ ማሰስ ጀመረ ብዙም አለፋም በ አይነቱ ከነ መርፌው ተሰድሮ ከመጠጥ ባንኮኒው በላይ በጥንቃቄ ተሰድረው ተመለከተ ጊዜም አላጠፋም ፈጥኖ በተረዳው መልኩ በማደባለቅ ወጋት ምናልባት ህይወቱዋንም ሊነጥቃት ይችላል ግን ምንም አማራጭ የለኝም ሲል ደጋግሞ ጮኸ ቅድስት ከወገቡዋ ብቻ ከፍ እያለች መንፈራፈር መንፈራገጥ ጀመረች ዋሲሁን ፈጠን ብሎ ያሸገውን ቁስሉን ፈቶ ደሙን እንድትመጥ ሰጣት ቅድስት ገፍትራው መንፈራገጥ መንፈራፈሩዋን ቀጠለች ዋሲሁን ከገፈተረችው በመነሳት በድጋሚ ከንዱን ወደ አፉዋ አስጠግቶ እንድትነከሰው ሰጣት ቅድስት ግን ብዙ ሳትቆይ መልሳ አራሱዋን ሳተች ዋሲሁን ደጋግሞ ከላይዋ ላይ በመውጣት በጥፊ ያጣድፋት ጀመር በ አፉም ደጋግሞ ተነሽ ተነሸ እያለ ደጋግሞ ጮኸ ሞርጋንቤት ሞርጋን በመጠኑ የተጎዳውን ፊቱን በመስታውት እያፅዳ ደጋግሞ ይዝታል አልምራትም አልምራቸውም ይላል በመጨረሻም መስታውቱን በቦክስ እየመታው አንዴት አንዴት እኔ ላይ ትበረታለች አንዴት አጁዋን ታነሳለች እንዴት ታመልጠኝ አገላታለሁ አያለ በተአምር አንዴት እንዳመለጠቸው ሲያስብ ለራሱም ገረመው ጫካ ውስጥ እራሳቸውን ቀይረው ክፉኛ ተፋለሙ ቅድስት ግን ፈጽሞ አልቻለችውም ነበር በስተመጨረሻ ቀስ ብላ በጥበብ በወጥመድ እንዲያዝ አደርጋለች ። ኬሊሮፍ በቡጢ ጠረፒዛውን መቶ ሁላችሁም ሊዚ ትከፍላላችሁ አንተም ሆንክ ሞርጋን አለ ወደ ቻርልሰን አያፈጠጠ ከዛም ኬሊሮፍ አሁኑኑ ለ ጤና ሚንስትሩ ሪፖርት አርጉ አሙዋሙዋታቸው በግል የጤና ችግር አንደሆነ መግለጫ ይስጥበት ብሎ አፉላይ መሸፈኛ ማስኩን አርጎ ከፍሉን ለቆ ወጣ ቻርሊም ቅድስት ባደረሰችበት ከህደት ውስጡ እየነደደ ኬሊሮፍ ተከትሎት ወጣ ቅድስት ከሰመመኑዋ ስትነቃ እራስዋን አልጋዋ ላይ አንሶላ ውስጥ ውስጥ አገኘች ሰውነቱዋን ገላዋን ዳበሰች በ ፓንት እና በ ጡት ማስያዣ ናት ሰውነቱዋ ተሞነጫጭሮ እና የተወሰነ ተጋግጦ ተመለከተች ከንዶቹዋ ታስረዋል ቦታው ላይ ህመም ይሰማታል ምን እንደሆነች ለማስታወስ ሞከረች ካልጋው ልቶርድ ስትል ትኩስ ሾርባ እና ጁስ ዶር ዋሲሁን ይዞ ወደ ከፍሉ ገባ ቅድስት ደንግጣ ከ አልጋው ለመውረድ ሞከረች ዋሲሁን ፈጠን ብሎ የያዘውን እያስቀመጠ እንድትረጋጋ ይለምናት ጀመር ቅድስት ቅድስት ተረጋጊ ተረጋጊ ሰውነትሽ በጣም ተጎድቱዋል አሁን በቂ እረፍት ማድረግ አለብሽ በዛ ላይ በቂ ህከምና አላገኘሽም ግዴለም ተረጋግተሽ ይሄን ቅመሺ አላት እና ያመጣውን ምግብ ጉልበቱዋ ላይ አስቀመጠው ቅድስት ሁሉ በገር አዲስ ሆኖባታል የ ዋሲሁንን ሁኔታ በጥርጣሬ ነው እምትመለከተው ደምህ ገላዬ ላይ ይሸተኛል አእጎዳሀለው አሁንም አራቅ ካጠገቤ ብላ ያመጣላትን ሾርባ አሽቀንጥራ ደፋቸው አራሱዋን መቆጣጠርም ሆነ መረጋጋት አቃጣት ዋሲሁን ወደ ውኃላው መሸሸ ጀመረ ጭንቅላቱዋን ይዛ ጮኸች ካጠገቡዋ ያገኘችውን የራስጌ መብራት ነቅላ ወደ ዋሲሁን ወረወረችው ዶር ዋሲሁን ወደ በሩ ሸሸ ነገር ግን ቅድስት ቀድማው ነበር በሩን ዘግታ ቆመችበት ዋሲሁን ሰው እንደዚህ ሲሆን ሲመለከት የመጀመሪያው ነው ስለ ውብቱዋ ያለ እረፍት አራሱን እስኪረሳ ሲመለከታት የነበረቸው ሴት ውበቱዋን በስዕል ሊተርከው ቀለም አማይበቃጥ እያለ ሲያሞግሳት የነበረችው አንቁ ያላት ሴት ጨለማ ለብሳ አጋንት ሲጫወትባት ገላዋ ወደ ጥቁር ተኩላ ሲቀየር ሀጫ በረዶ የመሰሉ ጠቢብ ያነጻቸው እነዛ ውብ ጥርሶቹዋ ደም የነካ ቢላዋ ሲያከሉ ሲመለከት አራሱ ጠላ አለንጋ የመሰሉ ውብ ጣቶቹዋ ተድበልብለው የተኩላ እግር ሲሆኑ ተመለከተ ዋሲሁን ከጸሎት ውጪ ምንም ተ አምር እንደማያድ ነው ተረዳ ቅድም ቅድስት እንድትተርፍ ደሜን ያጠጣዋት ለካ ለተሸከመችው መንፈስ ነበር አሁን ለንስሀም ጊዜ እማይሰጥ የሞት ጥላ ሊያፍነኝ ቆሙዋል አለ ዋሲሁን ወደ ተኩላ እነት አንድ በ አንድ እየተለወጠች ያለችው ቅድስት ተመልከቶ ። ደም ያሰከረው ተኩላ ዋዲሁንን ሊውጠው ተጠጋ ወደ ተኩላነት መልሳ ከተኛችበት አልጋ ላይ ተቀይራ ከፍሉን አምትንጠው ቅድስት ዋሲሁን ያወደሰላት ያሞገሰላት ወብቱዋ በደቂቃውስጥ የተኩላ አካል ሆኖ ዶር ዋሲሁንን ለመገነጣጠል ወደ ዋሲሁን ሲጠጋ ነበር ያቆም ተረካችንን ያቆም ነው ዋሲሁን አሁን ሊናጠቀው ካሰፈሰፈው አውሬ እንዴት ማምለጥ እንዳለለበት ግራ ተጋብቱዋል እራሱን ለመከላከል ወደ ውኃላው ሸሸ ተደናቅፎ በጀርባው ወደቀ በወደቀበት ወደ ውኃላው ሲሸሽ አንድ ሳጥን ከተደግፎ ቆመ ከላይ ታች እምቶ ነው ወደ ተኩላ እነት የተቀየረችው ቅድስት አሁን ወደ ዋሲሁን ሞትን ስላ ተጠጋች ዋሲሁን በደመነብስ ያገኘውን ሁላ መወርወር ጀመር በ አጋጣቢ የወረወረው ትንሽዬ ሳጥን ተከፍቶ ከውስጡ በ ቶ ቅርጽ የተሰራ እንጨት ወደቀ ከመቅጽፈትተኩላው ወደ ውኃላ ሸሸ አቃውን እየገለባበጠ ለመሸሽ ሞከረ ዋሲሁን ጊዜ ሳያቃጥል የወደቀውን በ ቶ ቅርፅ የተሰራ ውን ቅርጽ ይዞ ወጣ እና በሩን ከ ውጪ ቆለፈው ተኩላው ከበሩ ጋር ያለ አረፍት መጋጨት ጀመረ በሩ እየተሰነጠቀ እየተሰበረ መጣ ከ ደቂቃውች በውኃላ ግን ሁሉም ነገር ጸጥ አላ ተኩላው በሩን መደብደብ አቁሞ ጸጥ አለ ዋሲሁን የውጩ መውጫው በር ላይ ሆኖ አሚሆነውን ይከታተል ነበር በ ቆ ቅርጽ የተሰራውን መስቀል አተኩሮ እያየው በውኃላ ላይ ወደ ውኃላው ያዘ እና ወደ ቆለፈው በር ተጠጋ ከበሩ የቅድስት እሚያሳሳ እንባ ሰማ በሩን ከፍቶት በ አርጋታ ወደ ውስጥ ገባ ስቅስቅ አያለች እራሱዋን አንሶላ ውስጥ ደብቃ ወለሉ ላይ ተቀምጣ ታለቅሳለች ዋሲሁን ተጠቅግቶ አስሩዋ ተቀመጠ እና ወሰራሱ አስጠግቶ አቀፋት ኩምሽሽ ብላ ፈረቱ ላይ ልጥፍ አለች ዋሲሁን ጸጉሩዋን እየዳበሳት ወደ አንገቱ በደብ አስጠጋት እና በ አንድጁ ስለያዘው ሚስጥራዊ በ ቆ ቅርፅ ስለተሰራው መስቀል ያስብ ጀመረ ይሄን መስቀል እናቱ ደጋግመው አንገቱ ላይ እንዳትፈታው እያሱ በንሰሀ አባታቸው እያስባረኩ ሲያስሩለት እና ነግሬ ሀለው ልጄ ከ አርጉስ መንፈስ እና ከ አጋንት ይጠብቅሀል ፈረንጅ ሀገር ስትሄድ አውቀቱን ብቻ ሳይሆን መእአቱንም ነው አምታመጣው ልጄ በቁዋጫ ለሌለው መከራ እንዳትገባ ከንገትህ መሀተብህን አትበጥስ ይሉት ነበር ደጋግሞ ይሄን ነገር ስለማህተቡ ሲያስብ ያስታውሰዋል በተለያየ አጋጣሚ ካገቱ ላይ አውልቆታል የናቱን መሀላ እና አደራ ባስታወሰ ቁጥር ያንገበግበዋል ማህተብ መበጠስ እምነትን ከመከዳት በላይ ቃልንም በስበር ነው ለእሱ እናቱ ካንገቱ ላይ አንዴ በጡ ጊዜ ለ ነብስ አባታቸው ነግረው ከመሄዱ በፊት ያስገፅሱት ታወሰው በቀኝ አጃቸው መስቀላቸውን ግራ እና ቀኝ አንያማቱ ማዕተብህን በአንገትህ እሰረው ስትሔድ ይመራሃል ስትተኛ ይጠብቅሃል ምሳ ማዕተብ አተበ አመለከተ ባረከ ከሚለው የግአዝ ቃል የተገኘ ነውይህም ማለት መታወቂያ ምልከት ማለት ነውይህም ያመኑትንና የተጠመቁትን ካላመኑትና ካልተጠመቁት የሚለዩበት የከርስቲያን መታወቂያ ነው የዚህ ምልክት መሠረቱና ምሳሌውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ከተቀበለው ጸዋትወ መከራ አንዱ በገመድ ታሥሮ መጎተቱ መሆኑንየሚያመለከት ነው ዮሐ ቅዱስ ዳዊትም በመዝ ላይ ወወሀብኮሙ ትአምርተ ለአለ ይፈርሁከ ከመያምሥጡ አምገጸቅስት ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ለሚፈሩ ምልከትን ሰጠሃቸው ይላል አጋንንት የከፋትን ቀስት በዚህ ዓለም በመወርወር የሰውን ልብ ስለሚወጉ ከዚህ ለመዳን ማዕተብን ማድረግ ታላቅ መንፈሳዊ አውቀት ነው ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሲያስረዳ ሥላሴ ማዕተበ ብርሃን ኃይል ሃይማኖቶሙ ለከርስቲያንሥላሴ ለከርስቲያን ሁሉ የሃይማኖታቸው ጉልበት መታወቂያ የብርሃን ማዕተብ ምልከት ነው ከርስቲያን በማተቡ መነኩሴ በቆቡ እንዲታወቅ ማዕተብ አልባ መሆን ደግሞ ከርስቲያን ይሁን ያልተጠመቀ መሆኑ ለማወቅ ያስቸግራል ልጄ ለ አንድ እናትህ ስትል ስማ ለ እምነትህ ስትል ቃልህንም ጠብቅ እያሱ የገፅሱትን አስታውሶ ቆዘመ ከመሀተቡ ጀርባ ዛሬ ስላየው ስለዚ ቶ መስቀል የራሱን እንድምታ እና የ ሰ አዓሊው ጉዋደኛው ሮቤል አንድ ጥናታዊ ጹሁፍ በቀረበበት መድረከ ላይ የስነ መለኮት ተመራማሪው እና የ ሀይማኖት መምህሩ መጋቢ ሀዲስ ዶር ሮዳስ አለማየው በውቅቱ ያሉትን አስካሁን ያስታውሳል አሁን ደሞ ነገሩን በ አይኑ ባየ ጊዜ ተደነቀ ይሄ ቶ ቅርጽ ያለው መስቀል ምስጢሩ የገዘፈ እና በትርጉሞች የተሞላ ፊደል የ ቶ ፊደል ምስጢር ምንድነው። በድንገት ግን ጸጥታውን የከባድ መሳሪያ እሩምታ ከፍሉን አናወጠው ቅድስትም ዋሲሁንም አንድ ጥግ ፈልገው ከጥይቱ ለመዳን ተሸሸጉ ቤቱ በደቂቃ ውስጥ የ ጦር አውድማ መሰለ ዋሲሁን ከጥይቱ ለመሸሽ ሲቻኮል መስቀሉዋን የነበረበት ወለሉ ላይ እረስቱዋታል ቆከሱ ቀጥሉዋል ሁለት ክምር እሚያካከሉ አውቶማቲክ ከላሽ የያዙ ሰውች ወደ ውስጥ ገቡ እና መሳሪያቸውን ያርከፈከፉት ጀመር አሁንም እባዋ እየወረዳ ነው ቀና ብላ አየችው እና አሰላ ውስጥ ባለች ትንሽ መንደር ነበር የተወለድኩ የተወለድኩ ቀን አባቴ በባላንጣው ተገደለ እናቴ በስቃይ እኔን ከመገላገሉዋ በላይ ያባቴ ሞት ውስጡዋን በላት አውታ እማትጨርሰው ሀዘን ልቡዋ ገባ ቦታውን ለቀን ናዝሬት መጣን ህመሙዋ ግን እየበረታባት መጣ እኔ እድሜዬ አመት ደርሶ ነበር እናቴን ህመሙዋ ጠና እና ከ አልጋ ላይ መውረድ አቃጣት ሁሉም ነገር እኔ ላይ ወደቀ ብዙም ሳይቆይ አንድ ቀን ተከራይተን ከምንኖርበት ቤት ጎን አንደኛው ተከራይተው በሚኖሩ ጎረምሶች ሲጠጡ አምሸተው አይኑዋ እያየ መንቀሳቀስም ሆነ ቀና ማለት አእማትችለው እናቴ እና እኔን ተፈራርቀው ደፈሩን እናቴ የዛኑለት ማታ ህይወቱዋ አለፈ እኔም ብዙ ደም ስለፈሰሰኝ መንቀሳቀስም ሆነ መቆም አንዳቃተኝ ሁለት ቀን እናቴ እሬሳ ስር ቆየሁ ማንም አይቀርበንም በፊትም እናቴ ቡዳ ናት እየተባለች አገቱዋን ደፍታ ከማንም አርቃ ነው ከሰል በመቸርቸር ነበር እምትኖረው እራሴን ላጠፋ የ እናቴን መዳኒቶች ሁሉንም አንድ በ አንድ ዋጥኩዋቸው የ አናቴ በመንደሩ መጠላት የሰማቸው አከራይ እናቴ መታመሙዋን አኩዋን ሳትረዳ የውጪልኝ ጭቅጨቃዋ የየለት ስራዋ ነበር አጋጣሚ ሁለት ቀን ጠፍታ የዛለት በሩን ሳታንኩዋኩዋ ገንጥላ ገባች የ እናቴን እና የ እኔን ሁኔታ ስታይ ቤቱን በጩኸት አደበላልቃ የመንደሩን ሰው ሰበሰበች የወሬ ሱስ የጠማው መንደሬ ሁላ አፉን እየያዘ እያየን ይወጣ ጀመር ፖሊስ መቶ እኔንም እናቴንም እስኪያነሳን ማንም ቀርቦ ውሀ እኪ ያለኝ የለም አረፋ ሲደፍቀኝ እና ሲያስመልሰኝ ቆይቶ አራሴን ሳትኩ አንተ አሞትለታለው አምትለው መህበረሰብ በ እኔም በእናቴም ስቃይ ላይ ጨፈረ አዛች መቃብር ቤት ውስጥ ሆፔ አፋቸውን ሸፍነው ካዩኝ ውስጥ የእኔም የ እናቴም ደፋሪውች ነበሩ አየህ አንዳንዴ ገዳይህም ፈራጅ ሆኖ ከሸንጎው ታየዋለህ ከንፈሩን ከሚመጥልህ ውስጥ አፈር እሚነሰንስብህ ቀባሪህም አለ አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥእራሴን አገኘዉት ማንም ቤተሰብ እና ዘመድ ስለሌለኝ ከህመሜ በቅጡ ሳላገግም አውጥተው እንደውሻ ኮሪደር አግዳሚላይ ጣሉኝ በመትረፌ ፈጣሪን አረገምኩ እራሴን ጠላሁ ከስሬ ደም እየፈሰሰኝ ነበር ከሆስፒታሉ እየተንገዳገድኩ ወጣሁ እና እራሴን መኪና ውስጥ ከተትኩ ለካ ሞትም አንደ ሰማይ ይርቃል እንኩዋ ሰው መኪናው ነብሴን ተጠየፋት ጭራሽ የሰው አውሬ መጨዎቻ ሆንኩኝ ዳግመኛ ጎዳና ላይ በደም መጨማለቄን ስቃይ ላይ መሆኔን እኩዋን ማዘንባልቻለ ሊቀ ሰይጣን ዳግም ተደፈርኩ ህመሜ ጠንቶብኝ ነብሴ መቃተት ጀመረች ሲኦልን በሰው ልጅ አየውት ከባድ ዝናብ ለሊቱን እዛው የወደኩበት ጎዳና ላይ ዘነበብኝ ድመት ሳቶን እኔ ነበርኩ ነብስ ያለኝ ስቃዬ ከ ከብርዱ ጋር ተዳምሮ አራሴን ሳትኩ ስነቃ ሰውነቴ ተገላልጦ እርቃኔን መንገዳር አራሴን አገኘሁት አሁንም ከ ሰይጣን የከፋው የሰው ልጅ ከቦኝ አርቃኔን ይመለከታል ድንገት ከየዩ በማድረግ እባካችሁ ላላነበበው አድርሱልን ውድ አንባቢይ የቅድስት ቤትን ሞርጋን ከቦ በ ጥይት እየማሰው ከቆየ ቡኃላ እሱ ያሰማራቸው ቀድመው በጥይት የበሳሱትን በር ገፍተው ወደ ውስጥ አንድ በአንድ ገቡ ቅድስትእና ዋሲሁን ተቃቅፈው ሶፋው ጀርባ ተሸሽገዋል አሁን ምንም ማምለጫ እንደሌላቸው ተረድተው እጃቸውን ለመስጠት እሚጠብቁት የቶከሱን ማቆም ብቻ ነበር ዋሲሁን በ ቶ ቅርጽ የተሰራውን የ እንጨቱን መስቀል ጠበቅ አርጎ ይዞታል ሞርጋን በስተ መጨረሻ ወደ ውስጥ ገባ እና አንቺ ውሻ ፍጠኝ ውጪ ሲል ጮኸ ቅድስ የመስቀሉን ቅርጽ በ አርጋታ ተቀብላው ሶፋው ስር ከተተችው እና ከ ዋሲሁን ላይ ተነስታ እጁን ሰጠች ሞርጋን ተንደርድሮ በመምጣት ቅድስትን አነቃት ጊዜ ሳያጠፋ በቦክስ የጣድፋት ገባ ቅድስት መቁዋቁዋም አልቻለችም መጨረሻ ላይ ወደቀች ይሄን መታገስ ያቃተው ዶር ዋሲሁን መስቀሉዋን ሶፋስር ከቶ ሞርጋን ላይ ተጠመጠመበት ነገር ግን ዳፋው ለዶር ዋሲሁንም ተረፈ ዱላውን መቁዋቁዋም አስኪያቅተው ቀጠቀጠው ። ዶር ዋሲሁን ከሀሳቡ ተመለሰ ሰውነቱ አጁም አግሩም ደንዝዙዋል ፈተው ከወንበሩ ላይ አንስተው ወለሉ ላይ ጣሉት ቅድስትንም እንደዛው ሞርጋን መሳሪያውን አቀባብሎ ዶር ዋሲሁን ግባር ላይ ሊተኩስ ሲል ዶር ዋሲሁን በግዕዝ የተወሰኑ ቃላትን ማነብነብ ጀመረ የዚን ጊዜ የሞርጋን አጆች በቀጥቀጥ ጀመሩ አራሱን መቆጣጠር አልቻለም እንደ አውሬ ያጉዋራ አና ይጮኸ ጀመር የሱ ጥበቃዎች ተጠግተው ሊያረጋጉት ሲሉ እያነቀ ዝታላቸው በመጨረሻ ዋሲሁን ላይ ሊሰፍር ሲል ዋሲሁን ያለማቁዋረጥ ያለ ፍርሀት ያነበንብ ጀመር እሚናገረው በግእዝ ቁዋንቁዋ ነው ሞርጋን ፊቱ ይበልጥ እየቀላ አይኑም ጭምር ደም ይመስል ጀመር ጋርዶቹ ዋሲንን ከሚናገረው ሊያስቆሙት ዱላ ሊሰነዝሩ ሲል ቅድስት እመሬት የተዘረረችበት ላይ ሆና አንደምንም ብላ ሞርጋን የጣለውን መሳሪያ አንስታ በጥይት ለቀመቻቸው በውኃላል ላይ ቅድስትም መንቀጥቀጥ እና መዝለፍለፍ ስትጀምር እንደ ሞርጋን ዋሲሁን በሁለት እጁ አንስቱዋት ሸሸ ሞርጋን እየጮኸ ይንፈራፈራል ገሚሱ ጠባቂዎቹ በ ሞርጋን ተወርውረው ወድቀዋል ሌላው ቅድስት በተኮሰቸው ጥይት ተመተው ወድቀዋል ጊዜ ሳያጠፋ ዋሲሁን ቦታውን ለቆ ሸሸ በር ላይ አላዩዋ ላይ ቁልፉ የተረሳ መኪና አገኙ አስነስተው በፍጥነት ሸሹ ነገር ግን ከራዎል አላመለጡም ይከተላቸው ጀመር ቅድስት ሰውነቱዋ ዝሉዋል ከፍተኛ ህመም ላይ ናት ፍጥነቱን ጨምሮ አሚከተላቸው ራዎል ባላሰበው አጋጣሚ ከባስ ጋር ተጋቶ ከመንገዱ ቀረ ዋሲሁን መንገዱን ቀይሮ ጭር ባለው የኒዮርክ ጎዳና ገሰገሰ ግን የት ማን ጋር እንደሚሄድ አያቀው ቅድስት አንደምንም ብላ ከወንበሩ ቀና በማለት የመኪናውን ኪሶች በረበረች አምታቃቸውን ጥቂት እከክብሎች እና ማነቃቂያ መርፌዎች አገኘች ፈጥናም በመኪናው ወንበር ቀበቶ ከንዱዋን አሰረች እናእራሱዋን ወጋች አፍታም ሳትቆይ ከነበረችበት ነብስ ዘርታ መኪናውን ለኔ ስጠኝ ብላ ከ ዋሲሁን ተቀበለችው መኪናዋን ወደ አና ፖሊን ሜሪ ላንድ አቀኑ ለ ሁለት ቀናት ከቆዩ በውኃላ እራሳቸውን ቀይረው ሀሰተኛ ፓስፖርት በማዘጋጀት ወደ ጆርጂያ ውስጥ ወደ እምተገኝው አትላንታ አቀኑ ሁለት ቀናትንም አዛው አሳለፉ። የከተማው ስም «ዋሺንተን» የአገሩን መጀመርያውን ፕሬዚዳንት ጆርጅ ዋሺንግተን ስም ነው እምትጠራው ካሉዋት የ አየር ማረፊያዎች ውስጥ አንዱ የሆነው ክክ እከ ልበ በአዲሱ ወረርሽኝ ምክኒያት ጽልመት ለብሱዋል በቀን ብዙ ሺህ መንገደኞችን አሚያስተናግደው አየር መንገድ ዛሬ በመንገደኝ እርሀብ ወድቁዋል ጥቂት እሚባሉ መንገደኞች ውስጥ ሁለት አዛውንት ባል እና ሚስቶች ለመብረር ተገተዋል ነገሮች ሁላ ተቀይረዋል ላፌውች የስጦታ አቃ መሸጫ ሱቆች ሁሉም ተዘግተዋል ሁለቱ አዛውንት ባለትዳሮች እንደሌሎቹ አፋቸውን በጭንቭል ግጥም አርገው አስረው ወደ ኢትዮጳያ ከሰዓታት በውሃላ እሚበረውን የ ኢትዮጳያ አየር መንገድ ንብረት የሆነውን አይሮፕላን በመጠባበቅ ላይ ናቸው የሙቀት ምልከታቸውን ተለከተው ወደ መተላለፊያ ተርሚናሉ ሻንጣቸውን ይዘው ሊገቡ ሲል ወዲያው ነበር ሁሉም ነገር ባለበት አንዲቆም ማንም አንዳይንቀሳቀስ ኮሪደሩ ላይ ባለው አስፒከር ተነገረ ፖሊሶች እና ሲቪል የለበሱ ሰውች ወዲያው አየር መንገዱን ወረሩት እነሱን ተከትሎ የሰማይ ስባሪ አሚያከለው ሞርጋን ገባ እያንዳንዱ ሰው አንዲፈተሽ አዘዘ ሁሉም ሰው ላይ ቅኝት ይደረግ ጀመር ከሁሉም ሁለቱ አዛውንት ቀልቡን ሳቡት በእርጋታ ወደ አጠገባቸው ተጠግቶ ፓስፖርታቸውን ጠየቃቸው ሽማግሌው እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ሱፍ ጃኬታቸው ውስጥ ያለውን ፓስፖርታቸውን አውተው ሰጡት አሮጊቱዋ ግን ዝም አሉ ሞርጋን ደግሞ ጠየቃቸው አሳቸው ግን አሁንም ዝም አሉ ሞርጋን ንዴቱ አየናረ ሲሄድ ሽማግሌው ተመልከተው ያለ አጋዥ መሳሪያ መስማት እንደማትችል ነገረው ሞርጋን ወደ ሽማግሌው ዞር በማለት ታዲያ ለማቀርብላቸው ጥያቄ እንዲሰሙ አሚያረጋቸው መሳሪያው የታል አለ ሽማግሌው ሞርጋን ለሰስ ባለ የጥርጣሬ አስተያየት ጠየቃቸው ሽማግሌውም ቀስ ብለው ከ ባለቤታቸው ከ አዛውንቱ ቦርሳ ገቡ አና ውስጥ እጃቸው ሁለት ቦታ ነካ ቀጭን ዘመናዊ አውቶማቲክ መሳሪያ እና ለህመምተኞች አሚታዘዝ የጆሮ ማዳመጫ መሳሪያ የሽማግሌው እጅ ግን መሳሪያውን ነበር የጨበጠው በዚ ሁኔታ ላይ እያሱ ነበር አንድ የፖሊስ አባል ሞርጋን ሲል የተጣራው በፍጥነት ወደ ካሜራ መቆጣጠሪያው እሩም እንዲመጣ የተጠራው ሞርጋን ጥቂት ካመነታ በውኃላ እየተጫኮለ ወደ ተጠራበት አመራ የተጠራጠሩት አንድ ምስል እንዳለ አና እንዲመለከት ነበር የጠሩት ዋሲሁን እቅስቃሴው አንዲቀጥል እና የበረራ ሰዓቶች እንዳይስተጉዋጎል አደረገ ቪዲዮውን ሞርጋን አንድ ባንድ ተንቀሳቃሽ ምስሉን መመልከት ጀመረ ግን ሀሳቡ ሁላ እነዛ ሁለት አዛውንቶች ላይ ነበር ድንገት አንድ ምስል ተመልከቶ ቪዲኦ ኦፕሬተሩን እንዲያስቆመው አዘዘ ምስሉን በማጉላት ዘ በማረግ ተመለከተው ሁለቱ አዛውንቶች ናቸው በ ተርሚናሉ መተላለፊያ ላይ ባስፖርታቸውን እያሳዩ ይታያል ፓስፖርት የያዙት የ አሮጊቱዋ አጅ ላይ አንድ ጠባሳ ይታያል በዛም ላይ ቀጫጭን አብለጭላጭ ጌጦች ታስረውበታል ሞርጋን ምስሉ ወደ አንድ ትውስታው መሀደር ወሰደው ቅድስት ባገኛት አጋጣሚ ሁላ ስውነቱዋን ይመለከታል በተለይ ያገኛት ቀን መላ አካሉን ሲነዝረው ተሰምቶታል የተደበቀ ምትሀታዊ ውበት ሲል አሞካሽቱዋታል ጽጉሩዋንከንፈሩዋንአይኑዋንዳሌዋንጡቱዋን ሁሉንም አንድ በአንድ አስታወሰ ግን አሁ እጁዋላይ ካለው ምልከት ላይ ቀርቱዋል ሞርጋር ወዲያው ነበር ያቺ ሴት ቅድስት ናት ብሎ ሲሮጥ ወጣ በስልክ መነጋገሪያው በፍጥነት ተርሚናሉን ዝጉት ሲል ጮኸ ነገር ግን አረፍዶ ነበር በቃ መንገደኛ ስላልነበር አይሮፕላኑ ያሉትን ከጣት ቆጠራ አማያልፉትን ሰውች ይዞ ማኮብኮብ ጀምሩዋል ሞርጋን በንዴት አጠገቡ ያለውን የፖሊስ አባል በቦክስ ነረተው ፍለፊቱ ያሉትን ሰዎች ሁላ መደብደብ እቃ መሰባበር ጀመረ በፍጥነት የ አየር ትራፊከ ተቆጣጣሪዎቹ አይሮፕላኑ ወደ ተነሳበት እንዲመለስ አዘዘ ነገርግን ይሄን ማድረግ አንደማይችል መለሱለት ሞርጋን ወደ መቆጣጠሪያው ከፍል በማናለብኝነት በጉልበት በመግባት አይሮፕላኑ ተመልሶ እንዲያርፍ ሲል አስገደዳቸው አንደኛው የ አየር ተቆጣጣሪ ሁለቱን ባል አና ሚስት አዛውንቶች ይዞ አሚበረውን አይሮፕላን በፍጥነት መስመሩን በመመለስ አንዲያርፍ ለደንህነት ስጋት የሆኑ ሰዎች አይሮፕላኑስጥ ስለገቡ ከ ቢሮ ስለሚፈለጉ በፍጥነት መልሶ እንዲያሳርፍ አዘዙት ከ ደቂቃ የ አየር ላይ ቆይታ በውኃላ አይሮፕላኑ መልሶ አረፈ ሞርጋን መቆሙን አንዳረጋገጠ አይሮፕላኑን አስከብቦ ጊዜ ሳያባከን ወደ ውስጥ ገባ ነገር ግን ሁሉንም ቢያስስ ሁለቱ አዛውንት ባል አና ሚስቶች አይሮፕላን ውስጥ አልነበሩም ሞርጋን ደጋግሞ ደጋግሞ ፈለገ ፈጽሞ ሊያገኛቸው አልቻለም የውኃ ሽታ ሆኑ ሞርጋን እንዲ ከ አይምሮው በላይ ሰው ሲሆንበት የመጀመሪያው ነው ንዴቱን ከልከ አለፈ እየተጣደፈ አይውር መንገዱን ለቆ ሄደ ዋሸንግተን ዲሲ አንግዳ ማረፊያ ውስጥ ዋሲሁን ቅድስት ባረገችው ነገር ተናዶ ጠየቃት ለምንድ ነው እንድንመለስ የፈለክሽው ድጋሚ ልትሸጪኝ ድጋሚ አሳልፈሽ ልሰጪኝ። ሞርጋን በእርጋታ ወደ ቅድስት መጠጋቱን አቆመ እና ተረጋጊ ተርጋጊ መኪናውስጥ ነው በዚ ሰዓት ታቂያለሽ ያንን መስቀል መንካት አልችልም ሲላት ካፉ ቀበል አርጋ ጥሩ እንግያውስ እኔም አልነካውም አሱ ሻንጣ ውስጥ ይከተዋል መንገድ ልቀቅ አንድ ነገር እሞከራለሁ ብትል አፈነዳልሀለው ቅሉን አለችው ወደ ሞርጋን መኪና ዋሲሁንን ከተንበረከከበት አንስታ እየወሰደችው ወደመኪናው አስጠግታ ልትከፍት ስትል አንድ አራሱን የቀየረ ተኩላ ከጀርባዋ ተከመረባት እና ከዋሲሁን ነጥቆ ከዛፍ ጋር ወርውሮ አጋጫት እና እላዩዋ ላይ ተወርውሮ ሲከመርባት ቅድስት እራሱዋን ለማዳን በያዘችው መሳሪያ ደጋግም ወደ ተኩላው ተኮሰች ጥይቱ ያሰከረው ተኩላ ወደ ውኃላው ሲሸሽ ሞርጋን ተጠጋ እና መሳሪያ ወድሮ መሳሪያውን ጣይ አላት ጸጉሩዋን ጨምድዶ ከመሬት እያነሳት ዋሲሁን መኪናውን ከፍቶ በፍጥነት መስቀሉን ፈለገው ፍጹም ሊያግኘው አልቻለም የቻለው ቦታፈልገ እና በ ወፍራም ፈር ያለው ጨርቅ ተጠቅልሎ አገኝው በፍጥነት በማንሳት የቶ ቅርፅ ያለውን መስቀል በመያስ ወደ ጫካው እሮጠ ከውኃላው ሌላኛው እራሱን የቀየረው ተኩላ የከተለው ዋሲሁን በቻለው ፍጥነት አሮጠ እና አንድ ዛፍ አገኘ አና አንደምንም ወጣተኩላው ግን ደርሶበት ዛፉ ላይ ወቶ ተከተለው ዋሲሁን ዛፉ አንሸራቶት አመሬት ላይ ወደቀ አካሄዱ እና ሽሸቱ ሁላ በግምት ነበር የጭለማው ሀይል ምንም አያስተያይም ከጀርባው ተኩላው ሲከመርበት ዋሲሁን በያዘው መስቀል መታው እንደ ቀስት ነበር ከላዩ ላይ ተወርውሮ የተሽቀነጠረው ዋሲሁን ቀና ብሎ ጨረቃዋን ፈለገ ዳመናው ገልጡዋት አሁን ሙሉሆና ነበር ሲበር ወደ መጣበት ወደ ቅድስት እሮጠ አሁን መስቀሉ እጁ ላይ እንደ ጽሀይ ያበራል ወለል አርጎ ቦታውን ያሳየው ጀመር ።