Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ጋ ሇ በታደሰ ቴለሎሳልባኖ ዬተከዐፀፀበ ዐፀፀክጾጴልተዐ ፀየዐሀከቲ ቲዐ ሃዑሀ ርሃ ከሀ ጅዩ ከቪዐጴ ዘበዩፀህ ሞት የተፈረደባቸው ሺህ የኢትዮጵያ ሠራዊት የመጨረሻ ቀናት ዕጣ ፈንታ ከመሀልና ከቅርብ ሆኙ ተካፍያለሁ በዚህ ላይ ከዚህ ሁኔታ ከ ዓመታት በኋላ ከምርኮ መልስ በ ዓም አዲስ አበባ ከተማ ደምስሰን አዲስ ሥርዓት ለኪትዮጵያ ሕዝብ እንሠጣለን ሲሉ እኛ ልክ እንደ ልደት ቀናችን ነበር የቆጠርነው «የአሥመራው ሙከራ መክሸፉን በሬዲዮ ሲነገር መስማታችንም ቢሆን የተለየ ደስታ ፈጥሮልናል ምክንያቱም ጄኔራል ደምሴ ቡልቶ ጄኔራል ወርቁና ሌሎችም የደርግ ጄኔራሎች ሾተዋል ጄኔራል መርዕድ ንጉ ሞተዋል ሰእኛ እነዚህ ጠንካራ የሚባሉ ጄኔራሎች ከሞቱ የኤርትራ ሕዝብ ነዓነት በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ማለት ነው። ይህን መንግሥቱ ኃይለማርያም ይደርሳል እኮ ነው እያንዳንዱን ጄኔራል ልብ ያሳጣው እንጂ መንግሥ ኃይለማርያምን መገልበጥ ምን ይከብድ ነበር። ጆሮ ጠቢ የተባሉት የመረጃ ተባባሪዎች ደግሞ ቁጥር ስፍር የላቸውም በመሆኑም መንግሥቱ ኃይለማሪያምን ለመገልበጥ ዓሊ አንተ እንዳልከው ከባድ ነው። ምናልባት ከጊዜ በኋላ ደርግ ከወደቀ ወደ መፃል ሀገር ለመሄድና ቤተሰቦቻችንን ሰመገናኘት እንበቃ ይሆናል «ዓላህ አኩበር» ደርግ ካልወደቀም ሻዕቢያ በሚሰጠን ዕድል ውጭ ሀገር ሄደን እንኖር ይሆናል እኔ በተፈጥሮዬ ከዓላህ ጋር ያለኝ ፍቅር ትልቅ በመሆኑ የወደፊት ዕድሌ የተሳካ ሊሆን ይችላል የሚል እምነት አለኝ አሉና ራሣቸውን ነቀነቁ ጄኔራል ጥላሁንም በእግዚአብሔር በኩል ያለውን ተናገሩ አዎ ከእግዚአብሔር በስተቀር መጭውን ጊዜ ማንም አያውቅም በመሆኑም በህይወት ካለን ነገ ብዙ ነገር ማየት እንችላለን የሆነው ይሁን አሁን ከሻዕቢያ ጋር በተሰ። ሚኖርበት ላንድ ጊዜ ።ወ ዩ ሪክ ፍጻ ት ብቡ ጊዜ ። የኢትዮጵያ ትውልድ ፊት አልሸነፍም የአፄ ቴዎድሮስን ዕድል በማግኘቴም በጣም እኮራለሁ እኒ አሁን የተዘጋጀሁለት ሞት ዘለዓለማቋ ክብርና ሕይወት ይሰጠኛል በቫዕቢያ እንደእነ ጄኔራል ጥላሁን እና ጄእራል ዓሊ ሐጂ ተማርኬ የሻዕቢያን መሪዎች ዓይን ማየት ግንየሞት ሞት ነው ጀግንነት ማለት በሁሉም መልኩ ለጠላት ምቹ ሆኖ ያለመገኘት ነው።
ይህ እኔም ያለችኝን ትንሽ ነገር ይፔ እንድሰለፍ ረድቶኛል በየካቲት ወር ዓም በአብዮታዊ ሠራዊት እና በሻዕቢያ መካከል በቀይ ባህር አውራጃ በምፅዋ ግንባር ከባድ እና አሰቃቂ ውጊያ ተካሂደዋል ለአስር ቀናት ቀንና ሌሊት ለ ሰዓታት በእያንዳንዷ ሰኮንድና ደቂቃ እንደ ቅጠል የረገፉት የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት ጎን ተሰልፌ ተፋልሜአለሁ የሠራዊቱን ተጋድሎ እና የመጨረሻ ዕጣ ፈንታ መስክሬአለሁ በምፅዋ ግንባር የተደረገው ፍልሚያ ለኢትዮጵያ ህዝብ ለሠራዊቱና ቤተሰቡ ይህን የታሪክ መጽሐፍ ለማዘጋጀት ችዬአለሁ በየትኛውም ሥርዓተ ማህበሮች የመከላከያ ሠራዊት የሚታዘዘው ስልጣን ላይ ሳለው መንግስት ነው የገባውን ቃል የሚፈጽመው ለወከለው ህዝብ እና ሰንደቅ ዓላማ ባንዲራ ነው የመንግስት መለዋወጥ ክስተት የነበረ እና ለወደፊቱም የሚኖር ነውቋ ዋናው ጉዳይ የመከላከያ ኃይል ስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ስልጣን ላይ ለመቆየት ብቻ የቆመ ሳይሆን የሀገሪቷን ሉዓላዊነት ከጠላት ነቅቶ መጠበቅ እና ህገ መንግስቱን ያለምንም እንከን ማክበር ስልጣን ላይ ላለው መንግስት መታዘዝና በተባለው ሠዓት ሥራ ይ ማዋል ነው በዚህ የምጽዋ ውጊያ ታሪክ እና የኢትዮጵያ ሠራዊት እጣ ን በሚያሳይ መጽሐፌ ውስጥ የሚያረገግጠው ታላቅ የዓላማ ጽናት አለ የኛ ነበልባል ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ተሰማ የኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል በላይ አስጨናቂ የኛ ነበልባል ክፍለ ጦር ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ ቫለቃ ሮሬሳ ዲዲ የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ፖለቲካ ኃላፊ ሻምበል ሸዋን ታዬ ዓለሙ በምፅዋ ውጊያ ታላቅ ተጋድሎ አድርገዋል በመጨረሻም እነዚህ ከፍተኛ መኮኖች ወታደራዊ ሹመት ለሰጣቸው መንግስት እና በግንባር ቀደምትነት ለወከላቸው የኢትዮጵያ ሀዝብ በገቡት ቃል ኪዳንና ባላቸው የዓላማ ጽናት መሠረት በጠላት አልማረክም ብለው ውድ ህይወታቸውን በምፅዋ ወደብ ላይ በራሳቸው ጊዜ አጥፍተዋል ኣ ለሚመሩትም ሠራዊት ጥሩ ምሳሌ ከመሆን አልፈው የቆየውን የኢትዮጵያ ሠራዊት ጀግንነት ለጠላት አስመስክረዋል በምፅዋ ውጊያ አብዮታዊ ሠራዊት መራራ ተጋድሎ አድርጎ በሻዕቢያ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶ በመጨረሻም በሻዕቢያ አሸናፊነት አስራ ሰባት ሺህ አብዮታዊ ሠራዊት በምፅዋ በረሀ የህይወትና የአካል መስዋዕትነት ከፍለዋል የተቀሩት ደግሞ ተማርከው ወደ ሳህል በረሀ ተወስደው እኔን ጨምሮ ፍዳቸውን አይተዋልነ በሻዕቢያ ጥይት ተደብድበዋል ኔ የዚህ መጽሐፍ ዳራሲ በምፅዋ ግንባር ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ የውጊያ ሰዓት ድረስ ተሳትፌ የኢትዮጵያን ሠራዊት ሽንፈት ተጋርቼአለሁር በውጊያውም ቆስዬ በሻዕቢያ ተማርኬ ከምፅዋ ወደ ናቅፋ ሳህል አውራጃ አንደርበብ በተባለ ቦታ የሻዕቢያ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት ተወስጄ ከፍተኛ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ምርመራ ተደርጎብኛል ጭልጥ ባለ የበጋ በረሃ የሳህል ሀሩር በጉድጓድ እስር ቤት ታስሬ ፍዳዬን አይቻለሁ እንደዚህ ዓይነቱ መከራ ውስጥ አልፌ ይህን ጽሁፍ ለማዘጋጀት መብቃቴ ራሱ ከሙታን ዓለም ተመልሼ የመታየት ያህል መስሎ ታይቶኛል በመጨረሻም ከሻዕቢያ የምርኮ ጣቢያ «ሐራርብ» ከተባለ ቦታ ለሻዕቢያ ምሽግ መስሪያ ወደ ደጋው ኤርትራ የሚጫን የአንጨት ግንድ ቆረጣ ከሌሎች በቁጥር ሁለት መቶ ከሚሆኑ የኢትዮጵያ ምርኮኞች ጋር ለእንጨት ቆረጣ ተሰማርቼ በሻዕቢያ አባል ላይ አደጋ አድርሼ ከሻዕቢያ ተጽዕኖ የማምለጥ አጋጣሚ በማግኘቴ ወደ ምድረ ሱዳን በመሰደድ በካርቱም ኢትዮጵያ ኤምባሲ ድጋፍ ወደ ሀገሬ ኢትዮጵያ ሰኔ ቀን ዓም ገባሁ የመከራ የስቃይ ህይወቴም ገና ቦሌ አየር ማረፊያ ስደርስ ከአውሮፕላን ወርጄ የሀገሬን ምድር ስስም ከቻሉት ሁሉም ያልፋል እንድል አስገድዶኛል በሠራዊቱ ቤት የተቀጠርኩት መስከረም ቀን ዓም በቀድሞ ጎጃም ክፍለ ሀገር መተከል አውራጃ ወንበራ ወረዳ ሏህ ለሠራዊቱ አባልነት ተመልምዬ ወታደራዊ እውቀት ቀስሜ የሠራዊቱ አባል ከሆንኩ በኋላ ምሥራቅ ጦር ግንባር ከዛም ወደ ኤርትራ ዘመትኩ ቀጥሎም የካቲት ተብሎ ይታወቅ ወደነበረው የፖለቲካ ትምህርት ተቋም በ ዓም መጨረሻ ከአስመራ አዲስ አበባ በመምጣትም የተሰጠኝን ኮርስ አጠናቅቄ ፖለቲካ ሰራተኛ ሆንኩኝ ከዛም በኤርትራ በሁለተኛ አብዮታዊ ሠራዊት በኛ ብርጌድ በኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ በሰንጥቅ ሜካናይዝድ ብርጌድ በአስመራ ዙሪያ ጥበቃ ብርጌድ በኛ ብርጌድ የሻለቃ ኮሚሳር ከዛም የኛ ብርጌድ ባህልና ስፖርት ጉዳይ ኃላፊው በመጨረሻም የኛ ክፍለ ጦር ቀሪ ክፍሎች ፖለቲካ ኃላፊ እና በአስመራ የክፍለ ጦሩ ፖለቲካ ኃላፊ ተወካይ ሆፔ በኃላፊነት ቦታ ላይ ሰርቼአለሁ በምፅዋ ውጊያ ስካፈል ለአመራሩ እና ለሠራዊቱ በቀረበ ቦታ ሆዬ ወታደራዊ ግዳጄን በመወጣት ላይ ነበርኩ ለተደረገው ወታደራዊ ፍልሚያ የሞት ሽረት ጦርነት የሚጠበቅብኝን በፖለቲካ ሰራተኝነቴ ተወጥቼአለሁ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የሻ አለቃ ታደሰ ተብሉ የተጠቀሰው እኔው የመጽሐፉ ደራሲ ነኝ ይህ ለታሪኩ አፃፃፍ እና አገላለጽ እንዲያመች በማለት የተጠቀምኩበት ዘዴ መሆኑን ከወዲሁ አሳስባለሁ በዚህ መጽሐፍ የተካተቱት የምፅዋ ውጊያ እና ሠራዊቱ ሸንፈት አጠቃላይና ዝርዝር ሁኔታዎች ውጊያው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ በተግባር የተሳተፉኩባቸውና በዓይኔ ያየኋቸው ናቸው ምናልባት እኔ አቅሜ በፈቀደ ሁሉ የምጽዋን ውጊያ ታሪክ መልክ መልኩን አስይዢ ለማቅረብ ሞክሬአለሁ ከአቅም በሳይ ሆኖብኝ ሳልገልጽ ያለፍኩት ካለ ወይም ሳልዳስስ ያለፍኩት ጥቃቅን ነገሮች ካሉ ግን በውጊያው የተሳተፈ የሠራዊቱ አባልም ሆነ ቀረቤታ ያለውን ይቅርታ እየጠየኩ በዋናነት በታምር የየካቲት ዓም የምፅዋ ውጊያ ታሪክ ከዚህ ውጭ እንደማይሆን እምነቴ የፀና ነው በመጨረሻም ለክቡራን አንባቢያን አነስተኛ ማሳሰቢያ በትህትና አቀርባለሁ ይህም ይህ መጽሐፍ ከመጀመሪያው ገጽ ጂኣገ እስከ መጨረሻው በትዕግስት ካልተነበበ በስተቀር የምጽዋን ውጊያና የ የኢትዮጵያ ሠራዊት ዕጣ ፈንታ እውነታ ለመጨበጥ አስቸጋሪ በሆኑ የሚታዩብኝ ድክመቶችም ካሉ ማሻሻል እንድችል በመጽሐፉ የተካተቱ ምዕራፎችና ማጠቃለያ ሐሳብ እንድታነቡልኝ እንድታስተምሩኝ ለበለጠ ዓላማ እንድታነሳሱኝ አደራ እላለሁ ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ ኣቨ መግቢያ የካቲት ወር ደመና በቀይ ባህር አውራጃ ጥቅጥቅ ብሉ ሰማያዊውን ሰማይ ጋርዶታል ነገሩ የተገላቢጦሽ ነው በመሀል ሀገር ያለው ክረምት ከሰኒ እስከ ነሐሴ ወር ነው የቀይ ባህር አውራጃ ክረምት ግን ከጥቅምት እስከ ሚያዝያ አጋማሽ ድረስ ነው የምፅዋ ከተማ ህዝብ ቀን ከለሊት መንቀሳቀስ የሚችለውም በዚህ በክረምቱ ወራት ነው ከሰኔ እስከ መስከረም ባሉት ወራት በምፅዋ የሐሩር ወቅት ነው በዚህ ወቅት ምፅዋ ሙቀት ስለሚበዛበት በተለይ ከቀትር በኋላ ሰው ከቤት አይወጣም ጭር ብሎ ሰው በአካባቢው የሌለ ይመሰላል ምፅዋ በዓመት በአማካኝ ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሞቃት ነች በዓለም አቀፍ ወደብነት የምትታወቀው የምፅዋ ከተማ በቀይ ባሀር ዳርቻ ባፅዕ ጥዋለት እዳጋ ግራር ርዕሰ ምድሪ ወዘተ በመባል የሚታወቁ ክፍለ ከተሞችን ያካተተች ብትሆንም ከየካቲት ቀን እስከ የካቲት ቀን ዓም ድረስ ግን እጅግ ዘግናኝ ሁኔታ ነው የታየባት የደም ጎርፍ የጎረፈባት የሬሳ ክምር መረማመጃ መንገድ ያሳጣትና የሰው ሥጋ እንደቅርጫ ስጋ ተከፋፍሎ በየጥጋ ጥጉ የወደቀባት ከተማ ሆነች በባሩዱ ሽታና በየስፍራው ወድቆ ውሎ በአደረ ሰው አስከሬን መጥፎ ጠረንም ተሞላች ። » ሞት የተፈረደባቸው ሺህ የኢትዮጵያ ሠራዊት በሚሜል ርዕስ የቀረበው ታሪክም የዚህ የግል የጦር ሜዳ ተሳትፎዬና ልምዴ ውጤት ነው በመሆኑም በቅርብ የተከታተልኩትን በማስታወሻዬ ጽፌ ያቆየሁት በጥንቃቄ ያዘጋጀሁትን እውነተኛ የምፅዋ ውጊያ ታሪክ ለንባብ አብቅቻለሁ ከደራሲው ኣጂ ክ ምስሌሴፍ ስገድ ዖጦሂንቶ ቱያመረ የኛ ነበልባል ክፍለጦር ቀዳሚ መምሪያ ሦስት እግረኛ ብርጌዶችን ይዞ ከምፅዋ ከተማ ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኝ ሸኢብ ስለሞና በተባለች የገጠር መንደር ሰፍሯል ሻዕቢያ ደግሞ ከአፋቤት አምስት እግረኛ ብርጌድ ሁለት ሜካናይዝድ ብርጌድ እና አንድ ኮማንዶ ብርጌድ ይዞ ጥር ዐ ቀን ከሌሊቱ ዐ ሰዓት በዚች በሸኢብ ሰለሞና መንደርና አካባቢ በተሰለፈው አብዮታዊ ሠራዊት ላይ በእግረኛና ከባድ መሳሪያ ታግዞ የማጥቃት ጦርነት ጀመረ በሸኢብ እና በሰለሞና ግንባር ኛ ኛ ኛ እና ኛ የወገን ብርጌዶች ነበሩ እነዚህ ብርጌዶች በአሉበት በዚህ በሰለሞና ግንባርም በአብዮታዊ ሠራዊትና በሻዕቢያ መካከል ውጊያ መጀመሩን በክፍለጦሩ ተረኛ መኮንን በኩል ለፀኛ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ለብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ተሰማ ተነገራቸው ጄኔራል ተሾመ ቀጭን ረዥም ቁመትና ረዥም አንገት ትላልቅ ዓይኖች ያሏቸውና ዕድሜአቸው ከ ዓመት የማያንስ ጄኔራል ናቸው ጄኔራል ተሾመ ጊዜ አላጠፉም ምዕዋ ከሚገኘው ቤተ መንግሥት መኖሪያ ቤታቸው ሆነው ይህን አደጋ እንደሰሙ ወዲያው ተነስተው በዋዝ ጂፕ መኪና እየገሰገሱ ከምፅዋ አካባቢ ኪሎ ሜትር ርቆ ወደሚገኘውና ፎርቶ ተብሎ ወደሚታወቀው ማዘዣ ጣቢያቸው አመሩ ማዘዣ ጣቢየቸው እንደደረሱም እጅግ ኙ በፈጠነ ሁኔታ ዓይነቱ ተብሎ በሚታወቅ የጦር ሜዳ መገናኛ ሬዲዮ ግንኙነት ተመሥርቶ ከሰለሞና ግንባር ቀዳሚ መምሪያ አዛዥ ከሌተናል ኮሎኔል አፈወርቅ ተኸለ ጋር ንግግር ጀመሩ የመገናኛ ሬዲዮኑን ሀንድሴት ራሳቸው ነበሩ የያዙት የዕለቱ የጦር ሜዳ ሬዲዮ ግንኙነት የሚካሄደው በኛ ክፍለ ጦር መገናኛ ሻምበል ነበር የኛ ክፍለ ጦር ቀዳሚ መምሪያ ቀጭኔ የሚል የምስጢር ስም ተሰይሟል «ይሰማሃል ቀጭኔ። ዘንድሮ ዋጋሽን ታገኛለሽ ለሁሉም ጠብቂኝ» የሚል መልስ ሰጥተዋት ዛንድሴቱን ለመገናኛ ሬዲዮ ሠራተኛው መለሱለት የሬዲዮ ፍሪኩዌንሲ ቀይር የሚል ምክርም ሰጡ ሬዲዮ ሠራተኛውም የጦር ሜዳ ሬዲዮ ፍሪኩዌንሲውን ቀይሮም ለክፍሎች ገለጸ ከጄኔራል ሁሴን ጋር የተደረገው ግንኙነት ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ነው የሆኑት ቃላቸው ተግባራዊ መሆን የጀመረ ይመስላል ሚግ እና የተባሉት የሩሲያ ስሪት ሁለት ተዋጊ አውሮፕላኖች ከአሥመራ ወደ ሰለሞና ግንባር መጥተው በሻዕቢያ ይዞታ ላይ ቦምብ አዘነቡና ወደ አስመራ ተመለሱ በሌላ በኩል ደግሞ ሁለት ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች የጠላትን የኋላ ወረዳ እያሰሱ በጠላት ደጀን ጦር ላይ ከባድና ቀላል ፈንጂዎችን በማዝነብ ውጤታማ ሥራ ሠሩ ቀጥሎም አራት ተዋጊ አውሮፕላኖች መጡና በአካባቢው አንዣበው በቀጥታ ወደ ጠላት ይዞታ አመሩ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በከባድ ፍንዳታዎች አካባቢውን አናወጡት የኛ ዘርዓይ ደረስ ሜካናይዝድ ብርጌድ አዛዥ ለጄኔራል ተሾመ በአስተላለፉት የሬዲዮ መልዕክት ቆንጆ ነው የጠላት ታንክ እየነደደ ይታየኛል በማለት አውሮፕላኖቹ ጥሩ ውጤት ማስገኘታቸውን ገለጹ ጄኔራል ተሾመ ይህን እንደሰሙ የኛ ዘርዓይ ደረስ ሜካናይዝድ ብርጌድ አዛዥ ያላቸውን አቅም ሁሉ እንዲጠቀሙና በጠላት ላይ መልሶ ማጥቃት እንዲሰነዘር አሳሰቧቸው የወገን ጦር ጋሀተላይ ደርሶ ወደ አንተ እየገሰገሰ ነው በማለትም አበረታቷቸው ብርጌድ አዛዝ በተራቸው በስራቸው የሚገኙትን የሻለቃ አዛዥች በሬዲዮ በማግኘት ያበረታቷቸው ገቡ «ከበላይ አካል በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ሁላችሁም ወደ ፊት ተንቀሳቅሳችሁ በጠላ ላይ ጥቃት ሰንዝሩሱ ረዳት ጦርም እየደረሰ ነው አይዚችሀ የሚል ማበረታቻ መሰል ትዕዛዝም አስተላለፉ ከዚህ በኋላም ሁሉም የኛ ዘርዓይ ደረስ ሜካናይዝድ ብርጌድ ሻለቃዎች ወደፊት በመግፋት በሻዕቢያ ላይ ማጥቃት ሰነዘሩኔ ብዙ ሳይመክት የሻዕቢያ ሠራዊት ይዞታውን ለቆ ወደ ኋላ ሸሸ ይህ ውጤትም የአብዮታዊ ሠራዊቱን አባላትን ሞራል በማነሳሳቱ ተከትለው ሻዕቢያን በማባረር ኪሎ ሜትር ያህል ወደፊት ገፉ ይሁንና የሻዕቢያን ሽሽት ያስከተለው ወታደራዊ የበላይነት በመገኘቱ አልነበረምና ሁኔታው ከቆመበት ተለወጠ ሻዕቢያ የሸሸው የአብዮታዊ ሠራዊት ማጥቃት ከአቅሙ በላይ ሆኖበት ሳይሆን ለወታደራዊ ታክቲክ አፈፃፀም ስለነበር ኛ ዘርዓይ ደረስ ሜካናይዝድ ብርጌድ ወዲያውኑ በጠሳት ወጥመድ ውስጥ ወደቀ ሻዕቢያ በቆረጣ ከኋላው በመግባት መከላከሉን ወደ ማጥቃት ቀየረው የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ሻለቆችን መውጫ መንገድ ዘግቶ ያዘ ይህን ሲያደርግ ኪሣራው የተወሰኑ ታንኮቹ መቃጠል ብቻ ነበር የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት በበኩላቸው ለቆረጣው ቶሎ ሳይፈቱ ከሻዕቢያ ጋር የጨበጣ ውጊያ በማድረግ አንገት ለአንገት ተናንቀው መስዋዕትነት ከፈሉ ከዚህ በኋላ ነበር የብርጌድ አዛን የሬዲዮ ጥሪ ጄኔራል ተሾመ የተቀበሉት የኛ ዘርዓይ ደረስ ሜካናይዝድ ብርጌድ አዛዥ በተጣደፈ ድምጽ ለጄኔራል ተሾመ ሁኔታው መለወጡንና ጠላት የበላይነት መያዙን አሳወቁ በቃ ከዚህ በኋላ አንገናኝም የጠላት ሁኔታ ከአቅም በላይ ነው አሁን ከጠላት ጋር ስለተቀላቀልን ወገንንና ጠላትን ለመለየት ተቸግሬአለሁ የሻለቃ አዛዝች ግንኙነት አቋርጠዋል እኔ ያለኝ ዕድል የራሴን ሽጉጥ መጠጣት ብቻ ነው ለዚህም ተዘጋጅቼአለሁ ከዚህ በኋላ የምንገናኝ አይመስለኝም የብርጌዱ መምሪያ አባላትም ተበታትነዋል እኔም ዙሪያዬን በጠላት ተከብቤአለሁ መውጫ መንገድ ፈልጌ ሰብሬ ለመውጣት እሞክራለሁ ከአልሆነ ግን ራሴን አጠፋለሁ» አሉ ይህን የሰሙት ጄኔራል ተሾመ ያሉበት መሬት የከዳቸውን ያህል ደነገጡ ትንሽ ከድንጋጤያቸው የባነኑት ተዋጊ አውሮፕላኖች ስድስት ሆነው ሲመጡ ነበር በሂደት እንደታወቀው የተቀላቀለውን የወገንና የጠላት ጦር አንድ ላይ እንዲመቱ ከጄኔራል ሁሴን ትዕዛዝ ተሰጥቶአቸው ኖሯል በአካባቢው ቦምብ አዘነቡ የቦምቡ ፍንዳታም አካባቢውን አሸበረ የተቆራረጡ ጥቁር ደመናዎችም በሰማይ ላይ ፈጠረ ሻዕቢያ በበኩሉ በተዋጊ ጀቶች ላይ ዘ የተባለ አየር መቃወሚያ ጥይት እንደ አሸን ያፈላባቸዋል በአማካይ ለአንድ አውሮፕላን አየር መቃወሚያዎች ይተኩሱ ነበር ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ፓይለቶች ደፋር ስለነበሩ ሻዕቢያ ሊገታቸው አልቻለም ጄኔራል ተሾመም ሁኔታውን እንደለወጡት ተስፋ አድርገው የኛ ዘርዓይ ደረስ ብርጌድ አዛዥን በሬዲዮ አገኗቸው የአዛዝ መልስ እንደገመቱት አልነበረምቂ «በጣም ይገርማል። » አሉ ጄኔራል ጥላሁን ለዚህ የጄኔራል ተሾመ መልስ ሁለት ብርጌድ በቂ አይደለም ቢያንስ ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አራቱን ብርጌዶቹን ይዞ መምጣት አለበት ያለበለዚያ ኃይሌት ያለው የጋሀተላይ ዋናው የአስፋልት መንገድ በጠላት እጅ ይወድቃል» ነበር በአውነትም ያን ዕለት ሻዕቢያ ትልቅ ፍልሚያ በጋሀተላይ አካባቢ አደረገ በመድፍ አስተኳሾቹ አማካይነት የኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር ሁለት ብርጌዶች ጋሀተላይ አካባቢ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸው ስለተነገረው በሻዕቢያ አቅም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የመድፍና ቢ ኤም ጥይቶችን አዘነበ የተወሰኑ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላትም ተሰዉ የተወሰኑም ቆሰሉ ሻዕቢያ ተከታታይ የከባድ መሣሪያ ጥይት እንደ በረዶ አዘነበ በዚህ መልክ ሻዕቢያ ማጥቃት እየሰነዘረ ሁለት የሜካናይዝድ ብርጌዶች የካቲት ቀን ከቀኑ ዐዐ ሰዓት ከጋሀተላይ ወደ ሰለሞና ግንባር በእግር እንዲንቀሳቀሱ በጄኔራል ተሾመ ትዕዛዝ ተሰጣቸው በዚችው ሰዓት ሻፅቢያ በበኩሉ የሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ጉሮሮ የሆነውን የምፅዋ አሥመራ መንገድ ለመዝጋት የሚቀረው ዐ ኪሎ ሜትር ብቻ ነበር ይህንንም ለበላይ አለቆቹ በጦር ሜዳ ሬዲዮ ሪፖርት እያቀረበ መሆኑን ሬዲዮ ሠራተኛቸው የጠላትን ግንኙነት ጠልፎ መስማቱን ለጄኔራል ተሾመ ነገራቸው ይህ ሲነገራቸው ጄኔራል ተሾመ ደነገጡ ጄኔራሉ ሲደነግጡና ሲቆጡ ዓይናቸው የነብር ይመስላል በነብር ዓይናቸው «የሻዕቢያ ምስጢር በቀላሉ አይገኝም እንዴት ለማግኘት ቻልክ። ሁለቱም የሜካናይዝድ ብርጌዶች ሳይወዱ በግድ ወደ ኋላ ማፈግፈግ ጀመሩሱ በዚህ ወቅት ሻዕቢያ ከዐዐ ያላነሱ ተዋጊዎቹን ከጀርባቸው አስገብቶ ነበርና በመቁረጥ በሁለቱም የሜካናይዝድ ብርጌድ ጦሮች ላይ ከባድ ጉዳት አደረሰ ከአርባ ደቂቃ ውጊያ በኋላም ሁለቱ ብርጌዶች ጠላት ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ለጄኔራል ተሾመ ገልጠው ወደ ኋላ ማፈግፈጋቸውን ቀጠሉ ይሁንና ሻዕቢያ ተከታትሎ በማጥቃቱ የእጅ በእጅ ውጊያን ያካተተ ከባድ ፍልሚያ ተካሄደ በእጅ ቦምብ በሳንጃ በጥይትና በሳውንቸር በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፋጨፉ ውጊያው ይበልጥ መራራ በሆነበት ሰዓት ላይም ሻዕቢያ ተጨማሪ ኃይል ከኋላ አምጥቶ አፈሰሰ በታንክና በዘመናዊ አየር መቃወሚያ የተደገፈ ኃይል ነበርዘ እናም እነዚህን የኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር ሁለት ብርጌዶች በታተናቸው በጣም ፈጣን ማጥቃት በመሰንዘር ከፊት ለፊቱ በተጋፈጡት የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ላይ ከፍተኛ የሰውና የንብረት ውድመት አስከተለ ከሰለሞና ግንባር ጀምሮ እያዋጉና እያፈገፈጉ የተመለሱት ጄኔራል ቱሾመ ይህን ሁኔታ እንደተረዱም በቀጥታ ወደ ጋሀተላይ ዋና የመኪና አስፋልት መንገድ ተንቀሳቀሱ ከዚያም ወደምፅዋ ለመቀጠል በማሰብ ጋሀተላይ ሲደርሱ የተመለከቱት ያላሰቡትን ነበር የቆሰሉ የወገን ጦር አባላት በብዛት በመንገዱ ግራና ቀኝ ወድቀዋል ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመረዳት ይመስላል «ከዚህ ቦታ በምትችሉት አቅም ተንቀሳቀሱ» ብለው ጥብቅ ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ የምፅዋን መንገድ ይዘው ወደ ዶጋሌ ጉዞ ቀጠሉ ሻዕቢያም የጀመረውን ማጥቃት በስፋት በማፋፋም ወደግቡ ገስገሰ እናም የካቲት ቀን ዓም ከቀኑ ዐዐዐ በዓት ላይ ከምፅዋ አሥመራ የሚወስደውን ዋናውን የመኪና መንገድ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተቆጣጠረ ይህ ዋና መንገድ በሻዕቢያ እጅ በመውደቁ ምክንያትም አብዮታዊ ሠራዊት ለሁለት ተከፈለ አብዛኛው ወደ ምፅዋ ተቆረጠ የተወሰነው ወደ አሥመራ በኩሯ ቀረ በሁለቱም አቅጣጫ የተቆረጠው ሠራዊት አስፋልት መንገድ ይዞ ቁደ ምፅዋና ደንጐሎ ከማፈግፈግ በስተቀር አማራጭ አልነበረውም ሻዕቢያም እግር በእግር ከአለ ያለ ኃይሉ የተወሰነውን በቀጥታ ወደ ደንጐሎ አሠማራ ደንጐሎ የሚገኙት የኛ ብርጌድ መምሪያና ሻለቃዎች ነበሩ ከሻዕቢያ ጋር መፋለም ቢጀምሩም ሻዕቢያ እጅግ ዘመናዊ የሆነውን ዐ ሚሊ ሜትር መድፍና ቢኤም በእ ባለ አርባ አፈሙዝ የመሳሰሉ ከባድ መሣሪያዎችን በመያዙ ሊቋቋሙት አልቻሉም በወቅቱ ከኛ ብርጌድ አዛዥ ለጄኔራል ተሾመ በሬዲዮ እንደተነገራቸው ሻዕቢያ እነዚህን መሣሪያዎች ጋሀተላይ ደናዳይ የሚባለው የእርሻ ልማት ባለሀብት በገደበው ግድብ አካባቢ ተክሎ በታችኛው ደንጐሎ በላይኛ ው ደንጐሎና በጊንዳዕ ከተማ ላይ የተኩስ ውርጅብኝ አወረደ በተለይ በላይኛው ደንጐሎ የሚገኘው የኛ ብርጌድ መምሪያ በቫዕቢያ ከባድ መሣሪያ ፈራረሰ የእሳት ቃጠሎ ተነሳ በአብዮታዊ ሠራዊት ላይ ብቻ ሳይሆንም በዕለቱ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ጭምር ከባድ ጉዳት እና ኪሣራ ደረሰ ምስዬይፍ ሦስት ሐደው ዖዕፍ ይታ ጄኔራል ተሾመ የውጊያውን ሂደት በሬዲዮ እየተከታተሉ ከጋሀተላይ በቀጥታ ዶጋሌ ገቡ ዶጋሌ ኮረብታማ ቦታና ከምዕዋ በግምት ዛያ አምስት ኪሎ ሜትር ርቃ ትገኛለች ዶጋሌ የምትባል ወንዝም አለች ርዝመቱ ከዐዐ ሜትር ያላነሰ ዘመናዊ ድልድይ ያሻግራታል ዶጋሌ ራስ አሉላ አባነጋ ጣሊያንን ድል የመቱባት ወንዝ ናት ጥር ቀን በመንግሥቱ ኃይለማሪያም የተመረቀው የራስ አሉላ አባነጋ የመታሰቢያ ሐውልት የቆመውም በዚችው ዶጋሊ ወንዝ አካባቢ ባለችው ኮረብታ ላይ ነው ዶጋሌ ከዘመናዊ ድልድይ በስተቀር ቤትም ሆነ መንደር የላትም ጄኔራል ተሾመ የራስ አሉላ መታሰቢያ ሐውልት በቆመበት ኮረብታማ ቦታ ላይ ወጡና ጄኔራል ጥላሁንን አንዲያገናኛቸው የሬዲዮ ሠራተኛውን አዘዙት ጄኔራል ጥላሁን ቀረቡ ከጥቂት የሬዲዮ ግንኙነት ቃላት በኋላ «ለምንድን ነው ግንኙነት የተቋረጠው። በዚህ መሠረትም ጄኔራል ተሾመ ወደ ቀይ ባህር ሆቴል ስልክ ደውለው ጄኔራል ጥላሁንን ቢፈልጉ አሁን በመኪና ወጡ የሚል መልስ ተሰጣቸው ይህን መልስ እንደሰሙ በጦር ሜዳ ሬዲዮ እንዲያገናኛቸው መገናኛ ሠራተኛውን አዘዙት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ተገናኙ እንደፈለጓቸው ሲገልጡላቸውም ጀኔራል ጥላሁን ባሕር ኃይል መደብ ቤዝ ከባህር ኃይሉ አዛዥ መኖሪያ ቤት ማረፋቸውንና ቀይ ባህር ሆቴል ራት ሊበሉ መሄዳቸውን ነገሯቸው ጄኔራል ተሾመም ከዚህ ልውውጥ ቀጥለው አንድ የሻዕቢያ ምርኮኛ ተይዞ መጥቶ ቃሉን ተቀብለነው ወደ ክፍለጦሩ እስር ቤት ልከነዋል ጠቃሚ መረጃዎችን ሰጥቶኛል በማለት ሪፖርት አደረጉ ጄኔራል ጥላሁንም ሁኔታውን ለጄኔራል ሁሴን አሳውቅ የምርኮኛውን ሙሉ ቃልም አሁን ቶሎ ብለህ ላክልኝ አሉና ተሰነባበቱ ምስሌፍ ስድስት ፀታ ቅጣቶ ቅፉ ጄኔራል ተሾመ ከመረጃ ኃላፊው ቢሮ ወጡና ራሳቸው ቢሮ ገቡ ከምሽቱ ዐዐ ሰዓት ሊሆን ደቂቃ ይቀራል የሻዕቢያ ሰፊ ማጥቃት ዓላማው ቀይ ባህር አውራጃን ለመቆጣጠር ከሆነ ይህ አደገኛ ዓላማው በምን ዓይነት ሁኔታ መክሸፍ እንዳለበት አሰላሰሉ ምንም አማራጭ የለም ረዳት የሚሆን ሁለት ተዋጊ ክፍለጦር በተጨማሪ ወደ ጊንዳዕና ምፅዋ በመምጣት ሻዕቢያን እንዳልነበረ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ሣፃሣብ መጣላቸው ይህን ዛሣባቸውን በምን መልኩ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ ለማሰብም ጊዜ አልወሰደባቸውም እሱም ለጄኔራል ሁሴን አህመድ ሪፖርት ማድረግ ነው ጄኔራል ተሾመ ቁጥሩ ዐ የሆነውን የጽሕፈት ቤታቸውን ስልክ አነሱና በዐዐ ቁጥር በቀጥታ ወደ አሥመራ ደወሉ ስልኩን ያነሱት በቀጥታ ጄኔራል ሁሴን ነበሩ የተለመደውን ሰላምታ ተለዋውጠው ጄኔራል ተሾመ በራሳቸው ላይ የመኪና አደጋ ደርሶባቸው መትረፋቸውን አንድ የሻዕቢያ ምርኮኛ መያዙንና ቃል መስጠቱን ገለጹላቸው ጄኔራል ሁሴንም «አይዞህ። እንደምንም ብለህ ሻዕቢያን ማዋረድ አለብህ» አሉና «በአሁኑ ሰዓት የጠላት ሁኔታ እንዴት ነው» አሏቸው ጀኔራል ተሾመም ወደዋናው ነገር ገቡ «በሁሉም ግንባር ውጊያው ከምሽቱ ዐ ሰዓት ጀምሮ ጋብ ብሏል ነገር ግን ጠላት ተጨማሪ የሰው ኃይል ወደ ጋሀተላይ በመኪና እያመላለሰ ነው የመኪና መብራት በብዛት ይታያል አንድ የሻዕቢያ ወንበዴ ተማርኮ እንደነገርኩህ በእጃችን ይገኛል ስለ ጠላት ጠይቀነው የሰጠን መረጃ በጣም ቆንጆ ነው ጠላት ያለ የሌለ ኃይሉን ይዞ ነው የመጣው በመሆኑም በጣም ተዋጊ የሆኑ ሁለት ክፍለጦሮች ካልተላኩልኝ በስተር የምፅዋ ጉዳይ አደጋ ላይ ሳይወድቅ አይቀርም» አሉ ጄኔራል ሁሴን ምርኮኛው ተራ ተዋጊ ወይም መሪ ስለመሆኑ ጠየቁ ጌታዬ «በሻዕቢያ ዐኛ ብርጌድ ውስጥ ሻምበል ኃይሊ አዛዥ ነው የዐኛ ክፍል ተማሪ የነበረ እና ከአዲቀይህ ከተማ ወደ ጠላት የተቀላቀለ ነው» አሉ ጄኔራል ተሾመ ጄኔራል ሁሴን «በጣም ጥሩ ነው ሄሊኮፕተር በጠዋት ወደ ምፅዋ እልክልፃለሁና በአጅብ አድርገህ ወደ አሥመራ ላክልኝ ረዳት ጦር ያልከው ደግሞ ኛ ተራራ ክፍለ ጦር ጊንዳዕ ደርሶ ከጠላት ጋር በውጊያ ላይ ይገኛል ጠንካራ ክፍለ ጦር ስለሆነ ሻዕቢያን እየቀጠቀጠ ወደ መጣበት ይሸኛል አይዞህ የኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ጐበዝ አዋጊ ነው እንደነገርኩህ ሁሉ ኛ ተራራ ክፍለ ጦር ማለት የሻዕቢያ ጌታ መሆኑን ሻዕቢያ አሳምሮ ያውቃል» አሉ ጄኔራል ተሾመ ሻዕቢያ በጊንዳዕ ግንባር የሚያደርገው ውጊያ የማስመሰል እንደሆነና ምፅዋ ዒላማው መሆኑን ያውቃሉ ይህንኑ ለጄኔራል ሁሴን በመግለፅ የምፅዋ አሥመራ መንገድ ስለተዘጋ በአውሮፕላንም ቢሆን ተጨማሪ ሠራዊት ወደ ምፅዋ ቢልኩልኝ አይከፋም በማለት አሳሰቧቸው የጄኔራል ሁሴን መልስ የሚያበረታታ ነበር «በነገው ዕለት ኛ ተራራ ክፍለ ጦር ዋናውን የአስፋልት መኪና መንገድ ከሻዕቢያ ተጽዕኖ ነዓ ስለሚያወጣ ሁሉም በምድር ይደርስፃል ምንም ችግር የለም ከሻዕቢያ ጋር እኮ ለብዙ ጊዜ እንተዋወቃለን አለሁ ለማለት ነው እንጂ ምን ያመጣል። » አሉና አሰናበቱት ሁለት የሚሊቴሪ ፖሊስ አባላት ወደ ኛ ክፍለ ጦር መረጃ ሃላፊ ቢሮ ገብተው በነገው ፅለት ምርኮኛውን ይዘው አሥመራ እንዲሄዱ ግዳጅ ተሰጣቸው በወቅቱ የክፍለጦሩ ገንዘብ ቤት ኃላፊ ሻለቃ ለገሠ ምዕፅዋ ባዕዕ ስለነበሩም የመረጃ ኃላፊው ከራሱ ለሁለቱ ሃያ ስምንት ብር የውሎ አበል ከፍሏቸው ተሰነባበ በወቅቱ የአንድ ተራ ወታደር ደመወዝ ከእነቀለቡ አንድ ወ አሥራ ሁሰት ብር በመሆኑ የቀን አበል ሰባት ብር ብቻ ነበር ምስሌፍ ስባት ዕይሦኛ ጾንዳታ የካቲት ቀን ለየካቲት ቀን አጥቢያ ዓም ጄኔራል ተሾመ ከአሸለባቸው እንቅልፍ ሲባንኑ የእጅ ሰዓታቸው ልክ ከሌሊቱ ዐዐ ሰዓት ይላል ያደሩት ከምፅዋ ከተማ በስተምዕራብ በኩል ፎርቶ ተብሎ በሚታወቀው ተራራ ላይ ባለው የኛ ክፍለ ጦር ማዘዣ ጣቢያ ነው ፎርቶ ከምፅዋ ወደ አሥመራ መውጫ በስተግራ በኩል ዐዐ ሜትር ያህል ገባ ብሎ የሚገኝ ቦታ ነው ከፍታው ከባህር ወለል በላይ ከዐዐ ሜትር አያንስም ፎርቶ የጣሊያንኛ ቋንቋ ነው ይህ ተራራ የጣሊያን መንግሥት ኤርትራን በቀኝ ግዛት ይኮ በነበረ ጊዜ ሠራዊቱ በሲሚንቶና በድንጋይ የገነባው ጠንካራ ምሽግ አለው ጄኔራል ተሾመ የጦር ሜዳ ሬዒዮ ሠራተኛውን ጠሩና አዲስ ነገር እንዳለ ጠየቁት የደረሰውን መረጃ አቀረበላቸው በኢምበረም በዶጋሌ በጊንዳዕ ግንባሮች የሻዕቢያ ወንበዴዎች ከሌሊቱ ዐዐ ሰዓት ጀምሮ መጠነ ሰፊ ጦርነት ጀምረዋል ውጊያው በቀላልና ከባድ መሣሪያ የተደገፈ ነው አብዮታዊ ሠራዊታችን እየተፋለመ በመከላከል ላይ ይገኛል ጠላት ኢምበርም እና ዶጋሌን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል የተቆጣጠረውም ማምሻውን ነው ይህ በእንዲህ እንዳለ የኛ ብርጌድ ሠራዊት በሻዕቢያ ውጊያ ከባድ ጉዳት ደርሶበታል ደንጐሎ በጠላት ተጽአኖ ስር ወድቋል ከትላንት ከቀኑ ዐዐ ሰዓት ጀምሮ እስከ አሁኗ እኩለ ሴሊት ድረስ በተደረገ ውጊያ የሚሆኑ የሠራዊቱ አባላት የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉና የቆሰሉ በመሆናቸው ከፍተኛ የሰው ኃይል እጥረት አጋጥሞታልፎ ብርጌዱ ውጊያውን መቋቋም አልቻልኩም እያለ ነው የወገን ጦር ከደንጐሎ ጦር ሠፈር ወደ አምባቲካላ ጦር ሠፈር ስለማፈግፈጉ የብርጌድ አዛገ መልዕክት በሬዲዮ አስተላልፈዋል እምባቲካላ ከአሥመራ አርባ ኪሎ ሜትር ነው የምትርቀው ከዚህም ሌላ የዐኛ ሚሊሺያ ብርጌድ ከምፅዋ ከተማ በስተ ሰሜን ምዕራብ በኢምበርም አካባቢና በቀይ ባህር ጠረፍ ላይ ከሻዕቢያ ጋር ከፍተኛ ፍልሚያ እያደረገ ነው ጄኔራል ተሾመ ይህን ሪፖርት ሲሰሙ ቢደነግጡም ኮስተር ብለው ሜካናይዝድ ብርጌድ አዛዝዩን እንዲያገናኛቸው ጠየቁት መገናኛ ሠራተኛውም ከ ደቂቃዎች ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ከኛ ብርጌድ አዛዥ ጋር አገናኛቸው ጄኔራል ተሾመ የኛ ብርጌድ አዛዥ እንደቀረበ ለመነቃነቅ መዘጋጀቱን ጠየቁት ዝግጁነቱን ሲገልጽላቸው ፎሮ ወይም ዙላ አካባቢ አንድም ሰው ሳይቀር ይዞ በአስቸኳይ ምፅዋ እንዲገባ ከጥብቅ አደራ ጭምር አላሳሰቡት ፅቃና ሠራዊት የሚጭኑ ተሽከርካሪዎች የተላኩላቸው መሆኑንና ከጥቂት ጊዜ በኋሳ እንደሚደርሱ በእርግጠኝነት ተናገሩ ፎሮ እና ዙላ የተባሉት የጥንት የኢትዮጵያ የባህር ወደቦች ሲሆኑ የኢትዮጵያ ንጉሶች ይገለገሉባቸው እንደነበር ተጽፏል ከምፅዋ የሚርቁት ከፃምሣ ኪሎ ሜትር አያንስም የካቲት ቀን ከጠዋቱ ነ ሰዓት ላይ የጦሩ ሄሊኮፕተር ከአሥመራ መጣች እና ምፅዋ አየር ማረፊያ አረፈች ጄኔራል ተሾመ ማዘዣ ጣቢያቸው ባለበት ተራራ ላይ ሆነው በጦር ሜዳ መነጽር ይመሰከታሉ ከፄሊኮኾተሯ ከአሥራ አምስት ያላነሱ የወታደር ልብስ የለበሱ ሰዎች ወረዱፁ ሁለት ቶዮታ ላንድክሩዘሮች እና አንድ ዋዝ ጂፕ መኪናዎች ቀርበው ከሄሊኮፕተሯ ለወረዱት እንግዶች ወታደራዊ አቀባበል አድርገውላቸው ወደ ምፅዋ አመሩ ጄኔራል ተሾመ ከፄሊኮፕተሯ ከወረዱት መለዮ ለባሾች መካከል ጄኔራል መኮንኖች እንደሚገኙ ተረድተዋል ይሁንና የጦር ሜዳ ሬዲዮ ሠራተኛቸው ከሄሊኮፕተሯ የወረዱት እነማን እንደሆኑ እንዲያጣራ አዘዙት ለማጣራት ከዐ ደቂቃ የሚበልጥ ጊዜ አልወሰደበትም ወዲያውኑ ከሄሊኮፕተር የወረዱት የባህር ኃይል ባለሥልጣናት መሆናቸውን የመጡበት ዋና ዓላማ እሁድ የካቲት ቀን ዓም በሚከናወነው የባህር ኃይል ዕጩ መኮንኖች ምረቃ በዓል ላይ ለመገኘት መሆኑንና የባህር ኃይል በዓል በከፍተኛ ደረጃ እንደሚከበር አጣርቶ ነገራቸው ጄኔራል ተሾመ የሬዲዮ ሠራተኛውን ሪፖርት በጥሞና በመከታተል ላይ እያሉ ግን አንድ አስደንጋጭ ነገር ተከሰተ የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ከዶጋሌ አቅጣጫ ተተኩሶ ተተኳሹ በምፅዋ አየር ማረፊያ አካባቢ ወደቀና ከፍተኛ ፍንዳታ አሰማ በዚህ ሳያበቃም ሻዕቢያ በተጨማሪ ሦስት የከባድ መሣሪያ ጥይቶችን በሰከንዶች ልዩነት አከታትሎ በምፅዋ አየር ማረፊያ አካባቢ አዘነበ በአጠቃላይ አራቱ የከባድ መሣሪያ ፍንዳታዎች በምፅዋ ነዋሪ ሕዝብ ወታደራዊና ሲቪል ባለሥልጣናት ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤ አስከተሉ የፈነዱበት ሰዓት የምፅዋ ወደብ ሠራተኞች ነዋሪው ሕዝብ የመንግሥት ሠራተኛውና ተማሪው የሚተረማመሱበት ከጠዋቱ ዐዐ ሰዓት አካባቢ ነው በዚህ ቀውጢ ውስጥ ሄሊኮፕተሯ ከምፅዋ አየር ማረፊያ ተነስታ በረረች። መጀመሪያ አቅጣጫዋን ያደረገችው ከፍታ ለመጨመር ወደ ቀይ ባህር ነበር የምፅዋ አየር ማረፊያ የሚገኘው ከምፅዋ ከተማ በስተ ምዕራብ በመሆኑ ሄሊኮፕተራ በምፅዋ ከተማ ላይ አልፋ ወደ ቀይ ባህር አቀናች በዚህ አቅጣጫ ግን ብዙ አልገፋችም ጥቂት እንደተጓዘች እንደገና ከፍታዋን ጨምራ ወደ ኋላ በመዞር ወደ አሥመራ አመራች ጄኔራል ተሾመም ሁኔታውን ሲከታተሉ ቆይተው የምፅዋ አየር ማረፊያ በሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ስለመደብደቡ በቀጥታ ለሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት መምሪያ ሪፖርት አቀረቡ ሪፖርቱን የተቀበሏቸው ጄኔራል ሁሴን ነበሩ ሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ በምፅዋ አየር ማረፊያ ላይ የተኮሰበት ዋና ዓላማ ከአሥመራ ወደ ምዕዋ የመጣችውን ሄሊኮፕተር መምታት እንደነበር አካተዋል ሙከራው አለመሳካቱን ጥይቶቹ የመድፍ መሆናቸውንና ከዶጋሌ አቅጣጫ እንደሚተኮሱ በመግለፅ ጭምር ነበር ሪፖርት ያቀረቡት ጠላት ዛሬ ሲነጋጋ ከዐዐ ሰዓት ጀምሮ የተጠናከረ ማጥቃት በማድረግ ላይ ይገኛል የኛ ብርጌድ በአሁኑ ሰዓት ማዘዣውን አምባቲካላ ላይ አድርጐ በጊንዳዕ ከተማ አካባቢ ከጠላት ጋር ውጊያ ቀጥሏል ኃይል ከተጨመረለት ደንጐሎ ከተማን መልሶ ከጠላት እጅ ማውጣት እንደሚችል ዛሣብ ስለቀረበ በነፋሲት በኩል ዕርዳታ እንዲደርስለት ሲሉም አሳሰቡ ጄኔራል ሁሴንም ከአዳመጡ በኋላ የኛ ተራራ ክፍለጦር በአሁኑ ሰዓት ከኛ ብርጌድ ጋር ተገናኝቶ በጊንዳዕ አካባቢ በከባድ ውጊያ ላይ እንደሚገኝ ገለጡላቸው አያይዘውም ተዋጊ አውሮፕላኖች ስለሚሳኩላቸው አስተኳሾች ተጠቅመው ሻዕቢያን እንዲቀጠቅጡ አሳሰቧቸው ዛሬ የካቲት ቀን ከጠዋቱ ዐዐ ሰዓት ጀምሮ ጠላት በጊንዳዕ ከተማ አካባቢ ከባድ ውጊያ ላይ ነው ያለው ከምፅዋ ይልቅ የጊንዳዕ ከተማን ለመያዝ ከፍተኛ መረባረብ እያደረገ ነው በማለትም ስለአጠቃላይ የጊንዳዕ ሁኔታ ግንዛቤ አስጨበጧቸው ይህ አቀራረባቸው የሻዕቢያ ትኩረት በምፅዋ ላይ አለመሆኑን ይጠቁም ስለነበረ ጄኔራል ተሾመ «አይደለም ጌታዬ ጠላት ያለውን ጠንካራ ኃይል ያሰለፈው በጊንዳዕ ውጊያ ሳይሆን በምፅዋ ግንባር ነው» በሚል ለማስተካከል ሞከሩር ጥንቃቄ የተሞላበት አነጋገር ነበርቂ ጄኔራል ሁሴንም ጉዳዩን ተገንዝበውታል ለሁሉም ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባና ሻዕቢያ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ሳይሆን ከምፅዋ ሌላ ከከረን ወደ አፋቤት በሚወስደው መንገድም ግዝግዛ ላይ ውጊያ እያደረገ በመሆኑ በበኩልህ መበርታት አለብህ በሚል ማሳሰቢያ ተሰናበቱ ከዚህ ሪፖርትና የሃሣብ ልውውጥ በኋላ ተሰነባብተው እንደተለያዩ ጄኔራል ተሾመ ወደ ኛ ክፍለጦር መረጃ መምሪያ የውስጥ ስልክ ደወሉ ስልኩን ያነሳው ወታደር በጐሰው ሞሲሣ ይባላል የመረጃ መምሪያው ኃላፊ ፀሐፊ ነው ማንነቱን ከጠየቁትና ከመለሰላቸው በኋላ አየር ማረፊያ አካባቢ የወደቀው የጠላት ከባድ መሣሪያ ያደረሰውን ጉዳት ጠየቁት በሰውና በእንስሳት ላይ ጉዳት መድረሱን ማለትም እንጨት ጭነው ወደ ምፅዋ ከተማ በመጓዝ ላይ የነበሩ ሁለት የአሳውርታ ብሔረሰብ ዘላኖችና ሦስት ግመሎች መሞታቸውን አንድ ግመል ደግሞ እግሩ ተቆርጦ መውደቁን ሪፖርት አደረገ ረፖርቱን የሰሙት ጄኔራል ተሾመም ሁኔታውን እየተከታተለ ሪፖርት እንዲያቀርብላቸው ነግረውት ስልኩን ዘጉት ጄኔራል ሁሴን እንዳሉትም አራት ተዋጊ አውሮፕላኖችና ሁለት ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች በዶጋሌ አካባቢ አንዣበቡ በኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አውሮፕላን አስተኳሾች አማካይነትም በሻዕቢያ ላይ የቦምብ ናዳ አወረዱ በተለይ ተዋጊ ሄሊኮፕተሮቹ የቦምብና የጥይት በረዶ በሻዕቢያ ተዋጊዎች ላይ አዘነቡ አካባቢው በጥቁር ጭስ ተሸፈነ አራቱ ተዋጊ አውሮፕላኖች ወደ አሥመራ ሲሄዱ ሌላ አራት ተዋጊ አውሮፕላኖች መጡና በተሰጣቸው ኢላማ ላይ እጅግ ከባድ የተባለ የቦምብ ምት ሰነዘሩ የዶጋሌ በረሃን ሄሊኮፕተሮቹና ተዋጊ አውሮፕላኖቹ በመተባበር በከባድ ፈንጂዎች ፍንዳታ አናወጡት የጄኔራል ተሾመ ሬዲዮ ሠራተኛ የጠላትን የጦር ሜዳ ሬዲዮ ፍሪኩዌንሲ ፈልጎ በማግኘት የሻዕቢያ ሬዲዮ ሠራተኞችን እየተከታተለ ሁኔታውን ለጄኔራል ተሾመ ያሳውቃል የሻዕቢያ ሬዲዮ ሠራተኞች አብዛኞቹ ሴቶች ናቸው የሚጠራሩት በቁጥር ነው «የፋሽስት ደርግ» የውጊያ አውሮፕላኖች ሰፊ ጥፋት ማድረሳቸውን ያስተላልፋሉ ሬዲዮ ሠራተኛው በበኩሉ በተጣራ ሁኔታ ትግሪኛ ይሰማ ስለነበረ ለጄኔራል ተሾመ ከትግሪኛ ወደ አማርኛ ተርጉሞ የጠላት ሬዲዮ ኦፕሬተሮች በኛ ተዋጊ ጄቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው የሚያወሩትን ያስተላልፋል ን በዚህ ወቅት ጄኔራል ተሾመ ያሳዩትን ደስታ መግለጽ ያስቸግራል ደጋግመው ጀግናው ጄኔራል ሁሴን ምን ላድርግልህ። ጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጠላትን አይቀጡ ቅጣት እየቀጣ ከፍተኛ ውጤት አምጥቷል ብዙ የጠላት ታንክና ተዋጊዎች ተደምስሰዋል ጠላት ይህን በራሱ መገናኛ ሬዲዮ በግልጽ አያወራ ነው ሻዕቢያ ከአቅሙ በላይ ካልሆነ ምስጢሩ አይገኝም ዛሬ ግን ሬዲዮ ሠራተኞቹ እንደ አበደ ሰው ነው በግልጽ የሚለፈልፉት አሉ ጄኔራል ሁሴንም ይህን ሪፖርት ተቀብለው «በርታ የእ ጀግና አሁንም ባልተቋረጠ ሁኔታ ተዋጊ ጄቶች በጠላት ላይ ያዘንባሉ እኔም ምናልባት ከሰዓት ወደ ምፅዋ ሳልመጣ አልቀርም አሁን ከአሥመራ ወደ ምፅዋ የሚወስደውን አስፋልት መንገድ ይ ወደ ጊንዳዕ ግንባር እየተጓዝኩ ነው ከአሁን ጀምሮ የሬዲዮ ኙነታችን መቋረጥ የለበትም» በሚል ማበረታቻና ትዕ ደመደሙት ምስሌፍ ስምኀት ሠሪጀጀዩ ምቋዎኞ የካቲት ቀን ከቀኑ ዐ ሰዓት ላይ አንዲት ሄሊኮፕተር ከቀይ ባህር ለምፅዋ ከተማ በስተምሥራቅ በኩል ዝቅ ብሳ እየበረረች መጣችና በምፅዋ ወደብ እና ከተማ ላይ አልፋ ከምፅዋ ከተማ በስተምዕራብ በ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው አጂፕ ነዳጅ ማከፋፈያና ዲፖ አካባቢ አረፈች ጄኔራል ተሾመ በጦር ሜዳ መነጽር ይከታተሏታል የወታደር ልብስ የለበሱ ተሳፋሪዎች ከፄሊኮፕተሯ ሲወርዱ ተመለከቱና አንድ ቶዮታ ላንድ ክሩዘር እና ሁለት ዋዝ ጂፖች ቀርበው ከሄሊኮፕተሯ የወረዱትን በመያዝ በቀጥታ ወደ ኛ ክፍለ ጦር መምሪያ አቅጣጫ አቀኑ ጄኔራል ተሾመ ይህን ካስተዋሉ በኋላ ከማዘዣቸው በመውጣት ሾፌራቸውን ጠርተው ወደ ክፍለጦር ተንቀሳቀሱ ከ ደቂቃ በኋላ ኛ ክፍለጦር መምሪያ ሲደርሱ መጀመሪያ ያገኙት የክፍለጦሩን ልዩ ልዩ ሻለቃ አዛዥ ሻምበል በላይን ነበር እናም የመጡትን እንግዶች ማንነትና አመጣጣቸውን ጠየቋቸው ሻምበል በላይም «ከመጡት ባለሥልጣናት መካከል እኔ የማውቀው ጄኔራል ሁሴንን ብቻ ነው የተቀሩትን ጄኔራሎች ማወቅ አልቻልኩም ጅጄኔራል ተሾመን ፈልገን ነው አሉኝ እኔም «ጄኔራል ተሾመ ያሉት ክፍለጦር ማዘዣ ጣቢያ ነው አልኳቸው በመጡባቸው መኪኖች ወደ ምፅዋ ባህር ኃይል መደብ አምርተዋል ከዚህ ከተንቀሳቀሱ አንድ ደቂቃ ቢሆን ነው በማለት መለሱ እንዲህ ተነጋገሩና ጄኔራል ተሾመ ወደ ጽሕፈት ቤታቸው አመሩ እየፈጠኑ ቢሯቸው ገቡና ወንበራቸው ላይ ትንሽ አረፍ ብለው ከተከዙ በኋላ ስልክ አንስተው ወደ ምዕዋ ባህር ኃይል መደብ አዛዥ ደወሉ ስልኩን ያነሱት ኮሞዶር ፊሊጸስ ነበሩ ሰላምታ ተለዋውጠው እንዳበቁ ኮሞዶሩ በጣም አስቸኳይ ስብሰባ ስለአለን እጠብቅዛለሁ ና» አሏቸው ጄኔራል ተሾመ ጊዜ አላጠፉም ወዲያው በመነሣት በዋዝ ጂፕአቸው ተሳፍረው ወደ ኮሞዶር ፊሊጸስ ቢሮ አመሩነ ከምዕዋ ባህር ኃይል መደብ ሲደርሱ ግቢው አሸብርቆ ደምቋል በየቦታው ወቅታዊ መፈክሮች ተለጥፈዋል ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማና የባህር ኃይል ዓርማ ተሰቅለዋል አንኳን ለኛው ዓመት የባህር ኃይል ምስረታ አደረሳችሁ» የሚልና በትልቁ የተፃፈ መልዕክትም ተለጥፏል በግቢው የሚታየው የሰዉ ሽርጉድ ልዩ ነበር የባህር ኃይል ዕጩ መኮንኖች ምረቃና የባህር ኃይል የተመሠረተበት ቀን በየዓመቱ ይከበራል ግቢው በጠቅላላ ይህን የሚያመለክት ነበር ጄኔራል ተሾመ ከመኪና ወረዱና የጦር ሜዳ መነጽራቸውን በአንገታቸው ላይ እንዳጠለቁ ኮሞዶር ፊሊፅስ ቢሮ ገቡ ኮሞዶር ፊሊፅስ የሰሜን የባህር ኃይል መደብ ቤዝ ዋና አዛዥና ኢትዮጵያ የተባለችው ተዋጊ የጦር መርከብ አዛዥ ናቸው ኮሞዶር ፊሊጳስ ከተቀመጡበት ወንበር ተነስተው ጄኔራል ተሾመን በመጨበጥ የሚቀመጡበትን ወንበር አሳዩአቸው የቃላት ሰላምታ ተለዋዋጡ ጄኔራል ተሾመም ከሰላምታው ቀጥለው የባህር ኃይል መደብ በጣም አሸብርቋል ሠርገኛ ትመስላላችሁ ቆንጆ ዝግጅት ነው» በማለት አድናቆታቸውን ገለጹ ኮሞዶር ፊሊጳስ እንደ መሣቅ ብለው «አዎ። ይህን ግዳጅ በድል እንደምትወጣ እርግጠኛ ነበርኩ» አሉ ዓይናቸው እንባ እያቀረረ የግንባራቸው የደምስሮች ተገታትረዋል መሀረባቸውን ከኪሳቸው በማውጣት አፍንጫቸውን ጠረግረግ ዓይናቸውን አበስ አደረጉና ከማዘዣ ጣቢያቸው ዛምሣ ሜትር ያህል ራቅ ብለው ከአንዲት ቁጥቋጦ ብጤ አጠገብ ቁጭ አሉ የደስታ ሲቃቸውን ዋጥ አደረጉና ወደሬዲዮ ሠራተኛው በመዞር የ አለቃ በንቲ ቶሎ ብለህ ለሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት እና ለመክት ዕዝ የዶጋሌን ከጠላት ነዛ መውጣት ሪፖርት አድርግ ሌላው በጣም ርቦኛል ዛሬ እኮ ምግብ የተባለ አልቀመስኩም የሚቀመስ ነገር ፈልጉና አምጡልኝ» አሉ ጄኔራል ተሾመ መልስ አልጠበቁም የጦር ሜዳ መነጽራቸውን ወደ ዶጋሌ በረፃ አነጣጠሩና ተመሰከቱ ፀሐይ ልትጠልቅ ቀይ ሆና የብርፃነንና የሙቀት ኃይሏን አጥታለችቹ ዶጋሌ በረፃ ገና ወለል ብሎ ይታያል የከባድ መሣሪያ ብልጭታና የቀላል መሣሪያ አብሪ ጥይቶች ከዶጋሌ በስተምዕራብ የወገን ጦር ከሻዕቢያ ጋር የሚያደርገውን ፍልሚያ አጉልተው ያሳያሉ ጄኔራል ተሾመም ይህን ፍልሚያ በጦር ሜዳ መነጽር ለተወሰኑ ደቂቃዎች ተከታተሉት ተሾመ ልባቸው በደስታ ተሞላ ፈገግታ በፈገግታ ሆኑ ይህ ፈገግታ ብዙ ሰዓት አልቆየም ሻዕቢያ ዶጋሌን በመልቀቅ የሸሸው የኛ ሜካናይዝድ ማጥቃት ከአቅሙ በላይ ሆኖበት ቢሆንም ከምሽቱ ዐ ስዓት ሲሆን ግን በሜካናይዝድና ኮማንዶ ብርጌዶቹ ታጅቦ ተመለሰ በኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ላይም ከባድ ማጥቃት ስነዘረ በወታደራዊ ስልታዊ አነጋገር የጠላት መልሶ ማጥቃት ይባላል ሽዕቢያ እጅግ ከባድ ማጥቃት ስነዘረ ከዚያ በፊት በኤርትራ ውጊያ ታይቶ የማይታወቅ ነበር ሽዕቢያ በዚህ ውጊያ ብዛት ያላቸው ታንኮችና ብረት ለበስ የጦር መሣሪያ ተሽካሚ የሆኑ ቢቲአሮችን አስልፏል ይህን የሻዕቢያን አመጣጥ የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድና የኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር ታንከኛ ብርጌዶች አንድ ላይ በመሆን ለማክሸፍ ቢሞክሩም አልተሳካም ሽዕቢያ በእግረኛ ውጊያና በከባድ መሣሪያ አጠቃቀሙ ከአብዮታዊ ጦር በልጦ ተገኘ በተደረገውም ውጊያ ሻዕቢያ ከምሽቱ ሰ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ሲሆን ዶጋሴን እንደገና ተቆጣጠረ ከዶጋሌም አልፎ ወደ ምዕዋ ዐ ኪሎ ሜትር እስከሚቀረው ድረስ ተጠጋ ከምሽቱ ዐ ሰዓት አካባቢም ሻዕቢያ የወገንን ጦር ለማስደንገጥና ሞራሉን ለመግደል ይመስላል ከዶጋሴ ግንባር የከባድ መሣሪያ ጥይቶችን በማስወንጨፍ በምዕዋ ወደብ ላይ አኣዘነበ እንዳሰበው ሆነለት በወደብ ሠራተኞች በምፅዋ ነዋሪዎች በቀይ በህር አውራጃ የመንግሥት ሠራተኞች በፖሊስ ሠራዊት አባላት በወደቡ ፊናንስ ፖሊሶች በኢሠፓና የደህንነት ሠራተኞች ላይ ከባድ ድንጋጤን አስከተሰ በምፅዋ ወደብ ቆመው ፅቃ በማራገፍ ላይ የነበሩ ስምንት ዓለም አቀፍ ከባድና መካከለኛ የንግድ መርከቦችም ተደናግጠው ወደ አሰብና ዳህላክ ደሴቶች ለመነታቃነቅ ትርምስ ፈጠሩ ድሉ ተገላብጦ ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ የጦር አባላት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የህይወት መስዋዕትነት ከፈሉ ቆሰለ የተቀሩት ደግሞ በወፍ ዘራሽ ተበታትነው ወደ ምዕዋ አፈገፈጉ ዕቢያ መጠነ ስፊ ማጥቃት በማድረጉ የበላይነቱን አረጋገጠ ጄኔራል ተሾመ ክፉኛ ደነገጡ የችግሩን አሳሳቢነትም ለጄኔራል ሁሴን ነገሯቸው ጄኔራል ሁሴን ይህን እንደሰሙ በተደናገጠ አነጋገር ለጄኔራል ተሾመ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጡ። እነርሱም ቢሆኑ ከ ዓም ጀምሮ አልፎ አልፎ በኢትዮጵያ ባህር ኃይል ተዋጊ መርከቦች ላይ መጠነኛ ጥቃት አድርሰው ይሸሻሉ እንጂ ከዚህ ያለፈ አይሞክሩም ነበር ለዚያውም አንዳንድ ጊዜ ማምለጥ አይሳካላቸውም ነበር በኢትዮጵያ ባህር ኃይል ቃፒ መርከቦች እየተመቱ ይሰጥሙ ነበር የተማረኩም የሻዕቢያ ጀልባዎች ነበሩ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በሰሜንና ደቡብ ቀይ ባህር እየተዘዋወሩ አለን ለማለት ያህል ትንኮሳ ያካሂዱ ነበር ለምሳሌ በተደጋጋሚ በአሰብ ነዳጅ ማጣሪያና ወደብ እንዲሁም በምዕዋ ባህር ኃይል መደብና ወደብ ላይ ግራሪፒ የተባለ የቢኤም ከባድ መሣሪያ ጥይት ተኩስው አደጋ ለማድረስ ሞክረዋል ይህ ሙከራም በሌሊት ክፍለ ጊዜ ብቻ ጨለማን ተገን አድርገው የሚያደርጉት ነበር በባለሥልጣናቱም በባሕር ኃይሉም በሠራዊቱም የሻዕቢያ ባሕር ኃይል እስከዚች ዕለት ከዚህ የተለየ መልክ አልነበረውም የየካቲት ቀን ውጊያ ትንሽ ከበድ ይላል የባህር ውጊያ ቀላል አይደለም አልሞት ባይ ተጋዳይነት ዓይነት ነው ጄኔራል ተሾመ ከማዘዣ ጣቢያቸው ቁጥሩ ዐዐ በሆነው የስልክ መስመራቸው ወደ ባህር ኃይል ቁጥሩ ዐ ስልክ ላይ ደውለው ጠየቁ የጠላት ውጊያ መሆኑ ተነገራቸው ይህንን ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ ጉዳይም አሥመራ ስልክ ደውለው ለጄኔራል ሁሴን ነገሯቸው ጄኔራል ሁሴን ሁኔታወን እንደሙ ይህም ትንሽ ቀደም ሲል ከባህር ኃይሉ አዛዥ ተደውሎ እንደተነገራቸው ለጄኔራል ተሾመ ገለጽላቸው «በጣም የሚገርም ነው» አሉ ጄኔራል ተሾመ በእርግጥም በመገረም ቀጥለውም «ትልቅ ውጊያ እኮ ነው ምናልባት ሻዕቢያ የሱዳንና የግብፅን ወይም የሊቢያን ባህር ኃይል ተደግፎ የሚዋጋ ይመስለኛል እንጂ በምንም ዓይነት እንደዚህ ዓይነት አቅም የለውም የሚል ማብራሪያ አከሉ በመጨረሻም ውጊያው ከምድር ውጊያ ባልተናነስ እየተካሄደና እየተጧጧፈ እንደሚገኝ እንዲሁም የምድሩ ሲያስገርም የቀይ ባህር ውጊያ በዚህ ዓይነት መነሳቱ በጣም ትልቅ አደጋ እንደሆነ የፈለገው ይሁን ግን እስከ መጨረሻው ከሻዕቢያ ጋር እንደሚፋለሙ ገልጠው ከጄኔራል ሁሴን ጋር ተሰናባበቱ የጄኔራል ተሾመ ሬዲዮ ሠራተኛ የባሕር ኃይልን ሬዲዮ ጠልፎ ይሰማል ሌፍተናንት ኮማንዶር ማትዮስ የተባሉ የባሕር ኃይል አዋጊ መኩንን ከተዋጊ መርከብ ላይ ለሰሜን ቀይ ባሕር ዋና አዛዥ ያስተላለፉት መልክት ነው እንደሚተላለፈው መልዕክት የባህር ኃይል ተዋጊ መርከቦች ከሻዕቢያ ባህር ኃይል ጋር ባደረጉት ውጊያ ቀንቷቸዋል አምስት የሻዕቢያ ተዋጊ ጀልባዎች ተመተው ሰጥመዋል ይህን የጦር ሜዳ ሬዲዮ ሠራተኛው እንደሰማ ለጄኔራል ተሾመ ነገራቸው የኢትዮጵያ ባህር ኃይልና የሻዕቢያ ባህር ኃይል ተዋጊዎች ውጊያ ከምሽቱ ዐ ሰዓት ተጀምሮ ከምሽቱ ዐዐ ሰዓት ላይ አበቃ በሌላ በኩል ከምሽቱ ሰዓት ላይ ሻለቃ ኃይሉ አየለ ለጀኔራል ተሾመ በውስጥ ስልክ ደውለው የታዘዙትን መፈፀማቸውን ሪፖርት አደረጉ ባዘዙኝ መሠረት የገንዘብ ቤት ኃላፊው ሻለቃ ለገሠ ኃይሉ የሂሣብ ሹሙ የሆነውን ሻለቃ ባሻ በቀለ ለሜሣ ሻለቃ ዓለማየሁ አየለ እንዲሁም ሁለት ፀሐፊዎች የክፍለጦሩን ሠራዊት ደመወዝ የበጀት ስነድና የኢሠፓ መሠረታዊ ድርጅት ሰነድ ጭነው በኡራል መኪና ተሳፍረው ወደ ምዕዋ ባህር ኃይል መደብ ቤዝ ተልከዋል የገንዘብ እጥረት እንዳያጋጥመን ብዬ ከሻለቃ ለገሠ እጅ አንድ ሺህ ብር ተቀብዬ በእጄ ይገኛል የተቀበልኩት ከመዝናኛ ክበብ ገንዘብ ላይ ነው የሚል ሪፖርት አቀረቡ የጄኔራል ተሾመ መልስ «በጣም ገበዝ አመሰግናለሁ» የሚል ነበር ይህ ንግግር እንዳበቃ ጄኔራል ተሾመ ሬዲዮ ሠራተኛው ከምፅዋ ባህር ኃይል አዛዥ ጋር እንዲያገናኛቸው አዘዙትና ሬዲዮ ሠራተኛውም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከኮሞዶር ፊሊጳስ ጋር አገናኛቸው ስለሁኔታውም ዛሳብ ተለዋወጡ ኮሞዶሩም «ሻዕቢያ ዛሬ ጉድ ሊያፈላ ተነስቶ ነበር በጀግናው የባህር ኃይላችን አፈር ድሜ ግጦ አብዛኛዎቹ ከነጀልባቸው ቀይ ባህር ውስጥ ሲሰምጡ የተቀሩት ተበታትነው ሸሽተዋል አሁን ሠላም ወርዷል» አሉ ጄኔራል ተሾመም «በጣም ይገርማል ሁኔታውን እስከመጨረሻው ተከታትያለሁ የቀላልና የከባድ መሣሪያ ውጊያ ነበር ሻዕቢያ በቀይ ባህር ላይ ሽብር ለመፍጠር የተጠቀመበት ዘዴ ነው አሉና ወደ ደወሉበት ጉዳይ ተመለሉ የክፍለጦራችንን ዶክመንትና ገንዘብ ወደ ዳህላክ ደሴት በተዋጊ መርከቦች እንዲላክ እንድትተባበሩን ወደናንተ ተልኳል እንዴት ነው። ነርሷም ተቀብላ ለመጠጣት ግራ እጂን የግዲን ዘረጋች ድሬሰሩ ወይም ሐኪሙ «ውኃ ጥሩ አይደለም እንዳትጠጪ» እያለ ለመከልከል ሞክሮ ነበር አልተቀበለችውም በሴትዮዋ ድጋፍ ጠጣችና በረንዳው ላይ ጋደም አደረጓት ዓይኗን አሸልባ እንቅልፍ ቢጤ ወሰዳት ሴትዮዋ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሊቀሰቅሱዋት ሞከሩ ሲትዮዋ በከንቱ ነው የሚለፉት መልኳ ጠይም ፀጉሯ ረዥምና ውብ የሆነች ነርስ ህይወት አለፈች በተንጋለለችበት ቦታ የቀረው በድኗ ነው የግራ እጂ ጣቶች አንድ የቃል ኪዳን ቀለበትና ሁለት ሌላ የወርቅ ቀለበቶች እንደታጠቁ ታጥፈው ወደ መዳፏ ያመለክታሉ የዚች ነርስ ዓይነት በዚያች ሰዓት ብዙ ንፁሓን አሟሟታቸው ዘግናኝ ነበር ሻዕቢያ ባደረገው መጠነ ሰፊ ማጥቃት የወገን ጦር በጣም ተዳከመ በኛ ነበልባል ክፍለጦር ማዘዣ ጣቢያ ላይ የከባድ መሣሪያ ጥይት እንደበረዶ ወረደበት ከፍታ ነጥቡ በግምት ፅዐዐ ሜትር የሆነውና ፎርቶ ተብሎ የሚታወቀው የክፍሰጦሩ ማዘዣ ጣቢያ በጥቁር ጭስ ተሸፈነ ጄኔራል ተሾመ የካቲት ቀን ከጠዋቱ ሰዓት ሲሆን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ፎርቶ ማዘዣ ጣቢያቸውን ለቀው ወረዱ ቀድማ ከማዘዣ ጣቢያው በመውረድ ወደ ምጽዋ የሚወስደውን መኪና መንገድ ይዛ አንድ የግራር ዛፍ ከለላ በማድረግ ወደቆመችው ዋዝ ጂፕ መኪናቸው በእግራቸው ፈጠን ፈጠን እያሉ አመሩ ከዚያም ከመኪናዋ ውስጥ ገብተው ወደ ምጽዋ ከተማ የሚሄደውን አስፋልት መንገድ ይዘው ሦስት ኪሎ ሜትር ያህል ተጓዘ ወደ ጉርጉሱም መዋኛና መዝናኛ መታጠፊያ መንገድ ላይ ሲደርሱም መኪናዋን ከዋናው መንገድ አውጥተው በማቆም በጦር ሜዳ መነጽር በጉርጉስም አቅጣጫ ያሉትን ጉብታ መሬቶች ይመለከቱ ጀመር አብዮታዊ ሠራዊት በተዝረከረከ አካሄድ የመኪና መንገዱን ይዞ ወደ ምፅዋ ከተማ ሲሸሽ አዩ በዶጋሌ በኩልም ውጊያው ተጧጡፏል አብዮታዊ ሠራዊት ማለትም የኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር ታንከኛ ብርጌድ የኛ ክፍለጦር ታንከኛና አየር መቃወሚያ ሻለቆች ታንክ በታንክ ውጊያ ከሻዕቢያ ጋር እየተፋለሙ ነው በኢትዮጵያ ሠራዊት በኩል ዘጠና ታንኮች በሻዕቢያ ደግሞ አርባ ሰባት ታንኮች ተጋጥመዋል በሁለቱም ወገኖች ከባድ ፍልሚያ ይካሄዳል አንድ ከታንክ የሚተኮስ ጥይት ሌላውን ታንክ ያጋያል በተላለፈ የሬዲዮ መልዕክት አሥራ ስድስት የአብዮታዊ ሠራዊት ታንኮች ጋዩ ከነሹፌሮቻቸው የነደዱም አሉ በሻዕቢያ በኩል በአጠቃላይ ዘጠኝ ታንኮች ነደዱ አምስቱ በላውንቸርና አራቱ ደግሞ ከታንክ በተተኮሱ ጥይቶች የተመቱ ነበሩ በዚህ ጊዜ ሦስት ተዋጊ ፄሊኮፕተሮችና አራት ተዋጊ ጄቶች እየተፈራረቁ በሻዕቢያ ላይ የቦምብ ናዳ አወርደዋል ሻዕቢያ ሊበገር አልቻለም ከሁለት ብርጌድ በላይ የሚሆኑ አዲስ ኃይል ተዋጊዎችን በዶጋሌ ግንባር በኩል አስመጥቶ ውጊያ ውስጥ በማስገባት ተጠናክሮ ቀጠለ ሻዕቢያ ኃይሉን እንዲህ እያጠናከረ ወደምፅዋ ተጠግቶ የካቲት ቀን ከጠዋቱ ዐዐ ሰዓት ሲሆን ፎርቶ ተብሎ የሚታወቀውን የኛ ነበልባል ክፍለጦር ማዘዣ ጣቢያ ተቆጣጠረ ከዚያም ባለዐ ካሊበር ከባድ መትረየስ በፎርቶ ላይ ጠምዶ አማቴሬ ተብሎ በሚታወቀው የምዕዋ አካባቢ ሜዳ ላይ ተዝረክርኮ ወደ ምፅዋ ከተማ ይጓዝ በነበረው አብዮታዊ ሠራዊት ላይ የመትረየስ ጥይት አርከፈከፈ በጥቃቱም ቁጥራቸው ቀላል ባልሆነ የሠራዊት አባላት ላይ ጉዳት አደረሰ የአማቴሬ ሜዳ የደም ሜዳ ሆነ አማቴሬ የሚባለው ምፅዋ የሚገኝ ገለጣ የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳ ነው የኛ ነበልባል ክፍለ ጦር የእግር ኳስ ቡድን ጨዋታ የሚለማመደውና የክፍለጦሩ ብርጌዶች የዋንጫ ውድድር የሚያደርጉት በዚህ ሜዳ ላይ ነው የካቲት ቀን ግን በዚች ኳስ ሜዳ በተወሰኑ ደቂቃዎች ብቻ በግምት ዐ የሚሆኑ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ሕይወት በሻዕቢያ ቀላልና ከባድ መሣሪያ እሩምታ ተኩስ አለል ከ በላይ ቆሰሉ በአጠቃላይ በሜዳዋ አካባቢ ከ ደቂቃ ላላነስ ጊዜ ሻዕቢያና አብዮታዊ ሠራዊት ተዋግተው ሁለቱም መስዋዕትነት ከፍለዋል በሻዕቢያ በኩልም በግምት ከ ያላነሱ አባላቱ ሲሞቱ ከዐ ያላነሱ ቆስለዋል የሻዕቢያ ሙትና ቁስለኛ በዚህ መጠን የበዛው ተዋጊ ሄሊኮፕተሮችና ተዋጊ ጄቶች በሻዕቢያ ላይ ባዘነቡት ጥይትና ቦምብ እንዲሁም የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ሻዕቢያን ለመከላከል ባደረጉት ፍልሚያ ነው የካቲት ቀን ሻዕቢያ በጣም ኃይለኛ ውጊያ ያደረገባት ቀን ነች ውጊያው በጠቅላላ በኢትዮጵያና በሻዕቢያ ሠራዊት አቅም የሚደረግ አይመስልም ነበር በተለይ ከጠዋቱ ዐዐ ሰዓት እስከ ዐ ሰዓት ለዘጠና ደቂቃ ያህል በሁለቱ መካከል የተደረገው ውጊያ በታሪክ የምንሰማውንና በፊልም የምናየውን የናዚ ጀርመንና እና የሶቪየት ሕብረትን የኛውን የዓለም ጦርነት ውጊያ ይመስላል በዚህ ከባድ ጦርነት በግምት በኢትዮጵያ በኩል ወታደሮች የህይወት መስዋዕትነት ሲከፍሉ ከሺህ ወታደሮች በላይ ቆስለዋል ከ ያላነሱ በሻዕቢያ ተማርከዋል አብዛኛዎቹ የተማረኩት ቆስለው ነው በሻዕቢያ በኩል በግምት ሺህ አባላቱ ሞተዋል ከዐዐ ያላነሱ ቆስለዋል አሥራ ሁለት የሻዕቢያ ተዋጊዎች ተማርከው በአብዮታዊ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ቢውሉም አሥራ ሁለቱም አጸያፊ ስድብ በመሳደብና ምራቃቸውን በተቆጣጠሯቸው አብዮታዊ ሠራዊት አባላት ላይ እየተፉ በማስቸገራቸው በኮሎኔል በላይ አስጨናቂ የኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ትዕዛዝ ከምፅዋ አየር ማረፊያ በስተሰሜን ዐዐ ሜትር ያህል ርቆ በሚገኝ የጥድ ዛፍ ስር ተረሽነዋል አሥራሁለቱንም የሻዕቢያ ምርኮኞች እጃቸውን ወደ ኋላ አስረው የረሸኗቸው የፅኛ ነበልባል ክፍለጦር የሚሊቴሪ ፖሊስ ሁለት አባላት ናቸውፅ የክላሽኒኮቭ ጠመንጃ ጥይት አርከፈከፉባቸው። በወደቁበትም የአሥራ ሁለቱንም ጭንቅላት በድጋሚ በጥይት በመምታት መሞታቸውን አረጋግጠው ከቦታው ወደ ምፅዋ ተንቀሳቀሱ ምዕዋ በዕለቱ እሣት የሚነድባት ምድጃ ሆነች ሻዕቢያ በዶጋሌ አካባቢ ያለውን ኮማንዶ ሠራዊቱን በጠቅላላ በማንቀሳቀስ በታንክና ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች አስደግፎ ወደ ምፅዋ ከተማ አካባቢ በማስጠጋት ባደረገው ውጊያ በአካባቢው እሣተ ጉሞራ የፈነዳ መሰለ ከዚህ በዕለቱ በሻዕቢያና በአብዮታዊ ሠራዊት መካከል በተደረገው ውጊያ የሰው ልጅ የሚተርፍ አይመስልም ነበር ጄኔራል ተሾመ በኛ ክፍለ ጦር መምሪያ አካባቢ ሆነው የሀሉንም ብርጌድ አዛዥች በሬዲዮ ያስተባብሩ ነበር ይሁንና ሁኔታው እየከረረ መጣ የሻዕቢያ ሠራዊት ድሉን በማስፋት በኮማንዶ ውጊያ ተደግፎ የካቲት ቀን ከጠዋቱ ደቂቃ የምፅዋን አየር ማረፊያ ከፎርቶ በተጨማሪ ተቆጣጠረ የምፅዋ አየር ማረፊያ ከኛ ነበልባል ክፍለጦር መምሪያ የሚርቀው በግምት ከአንድ ኪሎሜትር አይበልጥም የአየር ማረፊያውንና የክፍለጦሩን መምሪያ መሐል ለመሐል የሚለየው ወደ አሥመራ የሚወስደው የአስፋልት ዋና መንገድ ነው ከአስፋልቱ የክፍለጦሩ መምሪያ ከዐዐ ሜትር የበለጠ አይርቅም አየር ማሪፊያውም ከአስፋልት መንገዱ እንዲሁ ከዐዐ ሜትር የበለጠ አይርቅም የሻዕቢያ ሠራዊት ምዕዋ አየር ማረፊያ አካባቢ ሆኖም በኛ ነበልባል ክፍለጦር መምሪያ ላይ የዘ አየር መቃወሚያ ከባድ መሣሪያ ጥይት እንደ በረዶ አዘነበበት በመምሪያው የነበሩ አባላትም አንዳንድ ርምጃዎች መውሰድ ጀመሩ ንብረት የሚያሸሹም በጠላት እጅ እንዳይገባ የሚያደርጉም ነበሩ ወታደር በጐ ሰው ሞሲሳ የተባለ የኛ ክፍለጦር መረጃ መምሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በጽሕፈት ቤቱ ዶክሜንቶች ላይ ዛያ ሊትር የሚሆን ቤንዚን አርከፍክፎ እሣት ለቀቀበት በዚህ የተነሳ መምሪያው በኃይለኛ የእሣት ቃጠሎ ተያይዞ ጭሱ ሰማዩን አጠቆረው ሻዕቢያም ጭሱን እያየ በሁኔታው በመበረታታት ይመስላል በአካባቢው ላይ የከባድ መሣሪያ እሩምታ ማውረዱን ቀጠለበት ይህን ያዩት ጄኔራል ተሾመ ከጠዋቱ ዐዐ ሰዓት ገደማ ላይ ወደቢሮአቸው ወደ ኛ ነበልባል ክፍለጦር መምሪያ ጽህፈት ቤት በመግባት ከወንበራቸው በስተጀርባ ግድግዳ ላይ ተሰቅሎ የነበረውን የጓድ መንግሥቱ ኃይለማርያም ባለወርቃማ ፍሬም ፎቶና የቀይ ባህር አውራጃን ወታደራዊ ካርታ ብቻ ከወሰዱ በኋላ ቢሮአቸውን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደ ፎርቶ ማዘዣ ጣቢያቸው ሁሉ ለቀው ወጡና መሐል ምፅዋ ከተማ ወደሚገኘው ቤተመንግሥት በዋዝ ጂፓቸው አመሩ ጀኔራል ጥላሁንና ጄኔራል ዓሊ ሐጂ ቀደም ሲልም በነበሩበት በምፅዋ ባህር ኃይል መደብ ቤዝ ናቸው ጄኔራል ተሾመ ምፅዋ ቤተ መንግሥት እንደደረሱ የቤተመንግሥቱን ፎቅ ግድግዳ ከለላ አድርገው መኪናቸውን አቆሟት ከሻዕቢያ ቦሚተኮስ ጥይት እንዳትመታባቸው ነበር ከዚያም ሁኔታውን በስፋት ለመቆጣጠር በቤተ መንግሥቱ ፎቅ አናት ላይ ወጡና በጦር ሜዳ መነጽራቸው ዕዳጋ ተብሎ የሚታወቀውን የምፅዋ ክፍለ ከተማ መቃኘት ጀመሩ የሻዕቢያ ተኩስ ተስፋፍቷል የሻዕቢያ ታንኮች ኛ ነበልባል ክፍለጦርን አልፈው ወደ ምፅዋ ባህር ኃይል ቤዝ እየገሰገሱ ነው በአካባቢው ከነበሩት የአብዮታዊው ሠራዊት ግማሾቹ ወደ ምዕዋ ወደብና የተወሰኑት ወደ ባህር ኃይል ቤዝ የሚወስደውን መንገድ ይዘው በሁለት አቅጣጫ ሻዕቢያ እንዳይጠጋቸው በከፍተኛ ወኔ እየተዋጉ ነው ሌላው በተለይ ወደ ምዕዋ ወደብ ያፈገፈገው የአብዮታዊ ሠራዊት አካል በወደቡ የነበረውን የእርዳታ ስንዴ እያጋዘ ምሽግ ይሰራል ወደ ባህር ኃይል ያፈገፈገውም እንዲሁ በምፅዋ ባህር ኃይል መዳረሻ አካባቢ ከሚገኘው የጨው ፋብሪካ በባለፃምሣ ኪሎ ግራም ጆንያዎች ተሞልቶ ለጭነት የተዘጋጀውን ጨው እያጋዘ የጋራና የግል ምሽግ ይሰራል በዚህ ዓይነት በየቦታውም ከአብዮታዊ ሠራዊት ግማሹ ይዋጋል ግማሹ ምሽግ ይሠራል ጄኔራል ተሾመ በቤተ መንግሥቱ አናት ላይ ሆነው ይህን ሁኔታ በመከታተል ላይ እያሉም ከአየር ማረፊያው አቅጣጫ በቤተ መንግሥቱ ላይ የከባድ መሣሪያ ጥይት ተተኮሰ ለጥቂት ነው የሳታቸው ከጐናቸው በኋላው የቤተ መንግሥቱ ህንፃ አካል ላይ ሲያርፍ ከፍተኛ ፍንዳታ ተሰማ የቤተ መንግሥቱ የመስኮት መስታወቶች ረገፉ የቤተ መንግሥቱ ሁለተኛ ፎቅ አንድ ክፍል ግድግዳ በጥይት ፈርሶ ትልቅ መስኮት የተከፈተለት አስመሰለው ጄኔራል ተሾመም ከዋና ዒላማነት ቢያመልጡም ከፍንጥርጣሪው አልዳኑም ከግራ ጭናቸው ላይ የመቁሰል አደጋ ደረሰባቸው ይሁንና ቁስሉ ከባድ ስለአልነበረም ከፎቁ ወርደው በቤተመንግሥቱ በረንዳ ላይ በመቀመጥ አቶ ጉርሜሣ የተባለ ዘማች የጤና ባለሙያ በጥጥና በአልኮል የመጥረግ የመጀመሪያ ዕርዳታ ተደረገላቸው ቁስሉ ቀላል ስለነበረ ለጄኔራል ተሾመ የተደረገላቸው የመጀመሪያ ሕክምና ከዚህ አላለፈም ፋሻም አሳስፈለገም ከዚህ በኋላ ጄኔራል ተሾመ እያነከሱ የቤተመንግሥቱን ግድግዳ ከለላ በማድረግ በጦር ሜዳ ሬዲዮ የብርጌድ የታንክና መድፈኛ አዛዝችን ማስተባበር ጀመሩ በመካከሉም ስለሁኔታው ከ አለቃ ታደሰ ጋር ውይይት ያደርጉ ነበር። ይህ የእርዳታ ጦር አስኪደርስልን ድረስ በአሁኑ ዓይነት መከላከል አለብን ወደ ምፅዋ የሚገባው በባህር በተከበበ አንድ ኪሎ ሜትር የድልድይ መንገድና የባቡር ሐዲድ ነው ስለዚህ ሻዕቢያ ይህን መንገድ ይዞ መግባት እንዳይችል ማድረግ አለብን» የሚል የልበ ሙሉነት መልስ ነበር የ አለቃ ታደሰ «ጌታዬ እኔ ከሻዕቢያ ጋር ላለፉት አሥራ አራት ዓመታት ስዋጋ የቆየሁ ሰው ነኝ ሻዕቢያ በከባድ መሣሪያ ብቻ እየቀጠቀጠ ይጨርሰናል ወይም በኃይል ሰብሮ ገብቶ ያጠፋናል ከዚህ ሁሉ ወደ ምፅዋ ወደብ የገባው አብዮታዊ ሠራዊት አሁን ተመልሶ እንዲወጣ ማድረግ አለብን በሜዳ ላይ ይለይልን በቀይ ባህርና በሻዕቢያ ተከበን መኖር አንችልምኔ በጣም ከባድ አደጋ ነው ጌታዬ አለ አለቃ ታደሰ የክፍለጦሩ ፖለቲካ ሠራተኛ ነው ጄኔራል ተሾመ ትንሽ ካሰላሰሉ በኋላ «ውጊያው እኮ ቀጥሏል ወጥተን ብንዋጋ የወገን ጦር እርዳታ ካልደረሰልን ብቻችንን ሆነን ሻዕቢያን ወደመጣበት መመለስ ያስቸግራል የምዕዋ ከተማን መግቢያ በር ከዘጋን ግን ዙሪያው ቀይ ባህር ነው መግባት አይችልም በመሆኑም እዚህ ሆነን እንከላከላለን» አሉ ይህ ሣሃሳብ እንደጠበቁት ውጤት አላመጣም ሻዕቢያ ከቀኑ በዐዐ ሰዓት የምዕዋ ባህር ኃይል ቤዝን ለመቆጣጠር ተንቀሳቀሰ ይዞት የመጣውን ጦር መሣሪያና ከሰው ኃይልም ዐ በመቶውን ወ ባህር ኃይል ግቢ ማጥቃት እንዲሰነዝር አስደረገ በማጥቃቅ ርምጃው አብዛኛዎቹ የወገን ታንኮች በሻዕቢያ እጅ ወደቁ የተቀሩጎ ለሁለት ተከፍለው ወደ ምፅዋና ወደ ባህር ኃይል ግቢ አፈገፈጉ በዚህ ጊዜ ሁለት የሻዕቢያ ታንኮችም ከወገን ታንኮች ተመሳስለው አብዮታዊ ሠራዊቱን አልፈው ወደ ምፅዋ ባህር ኃይል መደብ ቤዝ ገቡ የጠላት መሆናቸው የታወቀው ከባህር ኃይፅ ኳስ ሜዳ ላይ ሆነው በመድፎቻቸውና በላያቸው ሳይ በተጠመዱቅት መትረየሶች በሚያፈገፍገው አብዮታዊ ሠራዊት ጀርባ ላይ ጥያ ሲያርከፈክፉ ነበር ከዚህም አልፈው ከምፅዋ ወደብ ቁስለኞችንእ የሲቪል ባለሥልጣናትን የሠራዊቱን ቤተሰቦችና የተወሰኑ የባህር ኃይል አባላትን ከምፅዋ ወደብ ወደ ዳህላክ ደሴት ይዞ ይንቀሳቀስ የነበረውን መርከብ በመድፍ ጥይት በመምታት ሲያቃጥሉና በ የሚቀጠሩ ኢትዮጵያውያን ሲሰምጡ ደግሞ ይበልጥ ተረጋገጠ መርከቡ የሰመጠው ከምፅዋ ወደብ በቀይ ባህር ላይ በግምት ማይል የበለጠ ሳይርቅ ነው በታንኮቹ ተደብቀው ወደግቢው የገቡ ከአሥራ ሁለት የማያንሱ የሻዕቢያ ተዋጊዎችም በፒኬኤም መትረየየ እሩምታ ተኩስ ግቢውን ቀውጢ አደረጉት የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት በሁኔታው በጣም ተደናግ ነበር ይሁን እንጂ አልሞት ባይ ተጋዳይ በመሆን ሰርገው በገ የጠሳት ታንኮችና ሠራዊት አባላት ላይ በወሰዱት ፈጣን ማጥቃት ሁለቱ ታንኮች ከነምድብተኞቻቸው ተቃጠሉ አሥራ ሁለቱ የሻዕቢያ ተዋጊዎችም አንዱም እጅ ሳይሰጥ አቅማቸው የፈቀደውን ያህል ጉዳት ካደረሱ በኋላ ተደመሰሱ በባህር ኃይል ግቢ መለስተኛ ሠላም ተፈጠረ ሻዕቢያ የማጥቃት ዕድሉን ተነጠቀ በዚህ መልክ በባህር ኃይል ቤዝ ላይ የሰነዘረው ማጥቃት ቢከሽፍበትም ግን ርምጃው አልተገታምፎ ወደ ጡዋለት ምፅዋ ወደብ እንዲገቡ ግዳጅ ሰጥቶ ከቀኑ ዐዐ ሰዓት ላይ የተባሉ ሦስት ታንኮችና አንድ ብረት ለበስ ተሽከርካሪ አሰማራ ከዕዳጋ ሐሙስ ከተማ ወደ ምፅዋ መግቢያውንና አንድ ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን ድልድይ አቋርጦ ጡዋለት የተባለውን የምፅዋ ክፍለ ከተማ ለመቆጣጠርም በእነዚህ ታንኮቹና በብረት ለበስ ተሽከርካሪው ተኩስ ከፈተ በበረዶ ፋብሪካው በቀይ ባህር ሆቴልና በቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ የከባድ መሣሪያ ጥይት አዘነበ ተቋማቱ ፈራረሱ። በመሆኑም የአብዮታዊው ሠራዊት አባላት በጨበጣ ውጊያ በሻዕቢያ ተዋጊዎች ላይ የበላይነት ነበራቸው ብዙዎቹን በሳንጃ ገድለዋል በመሆኑም የካቲት ቀን ከቀኑ በዐ ሰዓት ላይ ሻዕቢያ ተዳከመና የምፅዋ ባህር ኃይል መደብን ቤዝ የመያዝ ፍላጐቱ ሟርሰ በመጨረሻም ወደ ኋላ አፈገፈገና የከባድ መሣሪያ ጥይት ናዳ ማውረድ ጀመረ የምዕዋ ባሕር ኃይል መደብ ከዚህች ዕለት ቀደም በአሉት ተናት ሲዋብ ነበር የቆየው ባሕር ኃይሉ የተመሠረተበት ኛ ዓመት የካቲት ቀን ይከበር ነበር በዚችው ዕለት ዕጩ መኮንኖችን በሻምላና በምክትል መቶ እልቅና ማዕረግ ለማስመረቅ ፕሮግራም ነበር በእነዚህ ምክንያቶች የባህር ኃይል መደብ ሙሽራ ይመስል ነበር አበቦች በየቦታው ፈክተው ይታዩ ነበር የምፅዋ ባህር ኃይል መደብ በሰላም ጊዜ ያለው ጽዳት እጅግ ከፍተኛ ነበር በአንድ ቀን ውጊያ ግን በሠራዊት ደምና ሥጋ ተጨማለቀ ሬሳው የፈራረሰ ቤትን ለመሥራት የተቆለለ የፍርስራሽ ድንጋይ መሰለ ህንጻው ፈራረሰ አስጠሊታ ሆነ በአንዲት ቀን ጀምበር በግምት ዐ ሺህ የከባድ መሣሪያ ጥይት አርፎበታል ሻዕቢያ ምፅዋን ለመቆጣጠር የካቲት ቀን ባደረገው በዚህ ውጊያ ምፅዋን የመቆጣጠር ፍላጐቱ በመቶ የተሳ ቢሆንም ከፍተኛ ጉዳት ስለደረሰበት ከምሽቱ ዐዐ ሰዓት ውጊያው ሙሉ ለሙሉ በሁሉም አቅጣጫ ቀቆመ ሰላም ወረደ ከሻዕቢያና ከአብዮታዊው ሠራዊት አባላት የሚተኮስ ምንም ዓይነት ቀላልና ከባድ መሣሪያ አልነበረም ጥቅጥቅ ያለ አስፈሪ ጨለማ ምፅዋን ዋጣት የባሩድ ሽታና መጥፎ ጠረን አካባቢውን አልብሶታል ከሩቅ ግን የሻዕቢያ ኪነት ቡድን ይዘፍናል እልልታና ዜማ በድምጽ ማጉያ ይሠማል በአብዮታዊው ሠራዊት ሰፈር ፀጥታ ሰፍኗል ምንም ነገር አልነበረም ሁሉም ወታደር ቦታ ይዞ የሻዕቢያን መምጣት ይጠባበቅ ነበር ጄነራል ተሾመ ከምሽቱ ዐዐ ሰዓት ላይ ለጄኔራል ሁሴን የሚከተለውን ቴሌግራም ወደ አስመራ ሳኩ ምጽዋ የካቲት ቀን ለሁለተኛ አብዮታዊ ሠራዊት ምክትል አዛዥ ሰዓት ዐዐ ወይም ከምሽቱ ዐዐ ሰዓት አሥመራ ጥር ዐ ቀን ዓም በሰለሞና ግንባር እኩለ ሌሊት ውጊያ የጀመሩ የሻዕቢያ ወንበዴዎች በአሁኑ ሰዓት ምፅዋን ለመያዝ ዛሬ የሞት ሽረት ውጊያ በማድረግ ላይ የዋሉ ሲሆን ከምሽቱ ዐ ሰዓት ጀምሮ ውጊያው ጋብ ብሏል የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ሻዕቢያ የምፅዋ ከተማን የባህር ኃይል ቤዝ እንዳይቆጣጠር ያደረጉትን ተጋድሎ ታሪክ ሲዘክር ይኖራል ሻዕቢያ ከፊት ለፊታችን ቀይ ባህር ከጀርባችን ሁነው አፋጦን ነፍስ ግቢ ነፍስ ውጪ ዓይነት ቀለበት ውስጥ ገብተናል ያለን ኃይል በባህር ኃይል ቤዝና በምፅዋ ከተማ ተጠቃሎ ከሻዕቢያ ጋር የመጨረሻውን ፍልሚያ በማድረግ ላይ ይገኛል ይሁን እንጂ ሻዕቢያ ምድር ይዞ በምፅዋ ምዕራባዊ ክፍል ሆኖ መብረቃዊ የከባድ መሣሪያ ድብደባ እያካሄደብን ነው የዋለው ነገም ቢሆን በዚሁ መልኩ መቀጠሉ አይቀሬ ነው በመሆኑም ጊንዳዕ ግንባር ያለው አብዮታዊ ሠራዊት ሻዕቢያን አባሮ ካልደረሰልን በስተቀር የሚጠብቀን አደጋ እጅግ የከፋ እንደሚሆን ይገመታል የእርዳታ ጦር በአስቸኳይ ይድረስልን ተዋጊ አውሮፕላኖች በነገው ጠዋት በሻዕቢያ ላይ ቦምብ ማዝነብ አለባቸው ሻዕቢያ ያለምንም ፍርሐት ሜዳ ላይ እየተተረማመሰ ይገኛል ይህን ሁኔታ ተመልክተው አፋጣኝ ውሳኔ ላይ እንዲደርሱልን በትህትና አመለክታለሁ ብጄ ተሾመ ተሰማ የሯ ነበልባል ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ይህ ቴሌግራም በክፍለጦሩ ልዩ መገናኛ አማካይነት ለሁለተኛ አብዮታዊ ሠራዊት ተሳላከ ልዩ መገናኛ ማለት ኮደር ሬዲዮ ተብሎ የሜታወቅና ሶቭየት ሕብረት ሰራሽ የሆነ በፍጹም በጠላት የማይጠለፍ ሬዲዮ ነው ይህ መሣሪያ የሰጡትን ጽሁፍ ፊርማና ማህተም እንዳለ በፎቶ ኮፒ መልክ የሚያስተላልፍ የማይጠለፍና ልክ እንደ ፋክስ የጽሁፍ አስረጅ የሚሰጥ እጅግ ዘመናዊ የጦር ሜዳ ግንኙነት ሬዲዮ ነው ጄኔራል ተሾመ ይህን ቴሌግራም ከላኩ በኋላ አሁን ጦርነቱ ጋብ ብሏል ስለዚህ የብርጌድና የሻለቃ አዛዝፐች እንዲሁም የክፍለጦሩ ስታፍ መኮንኖች ወደ ምፅዋ ቤተመንግሥት እንዲመጡ በሬዲዮ ይጠሩና አጭር ስብሰባ ይደረግ ለነገ ግዳጅ ሊዘጋጁ ይችላሉ በማለት ለጦር ሜዳ ሬዲዮ ሠራተኛቸው ትዕዛዝ ሰጡ። ጄኔራል ተሾመም የቀረበላቸውን ቁርስ በልተው የሻይ ኩባያቸውን አነሱ ገና ግማሽም ሳያደርሱት ግን ታይቶ የማይታወቅ አደጋ ደረሰ ምስሌፍ ከሥሌ ከገድ ዖው ሥ ያቀሯጀሜ መሀያ የካቲት ቀን ከሌሊቱ ዐዐዐ ሰዓት ለየካቲት ንጋት ላይ የከባድ መሣሪያ ጥይት በምፅዋ ከተማና በምዕዋ ባህር ኃይል መደብ ላይ ከነበ በቤተመንግሥቱ ግቢ በደቂቃዎች ውስጥ ከፃያ ያላነሱ የከባድ መሣሪያ ጥይቶች ፈነዱ በተወሰኑ የሠራዊቱ አባላት ላይ የመቁስል አደጋ ሲደርስ ሁለት የሠራዊቱ አባላት እግራቸውን ተቆረጡ ጥቃቱ እየበረታና እየቀጠለ ፄደ የከባድ መሣሪያ ብልጭታ አካባቢውን የነጐድጓድ ብልጭታ ያህል ያበራዋል የሻዕቢያ የከባድ መሣሪያ አብሪ ጥይትም በምፅዋ ከተማ ሰማይ ላይ እየፊነዳ ከፍተኛ ብርፃን በመስጠት ምፅዋ ከተማንና የባህር ኃይል መደቡን የቀን ብርፃን ያለብሰዋል ሲቪሉ ሕዝብና የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ይተራመሳሉ ትርምሱም አብዛኛው የምፅዋ ቤቶች በሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ተደብድበው በእሳት በመያያዛቸው ምክንያት የተፈጠረ ነው ይሁንና ሰው ነፍሱን ለማዳን ከቤት ወደ ጐዳና ላይ ስለወጣ አልዳነም የበለጠ የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ጥይት ቁርስ ሆነ አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሰው ሥጋ በቅርጫ መልክ ተቆራረጠ የካቲት ቀን ከጠዋቱ ሰዓት ላይ ደግሞ ሻዕቢያ በሜካናይዝድና እግረኛ ኃይል ተደግፎ የምፅዋን ባህር ኃይል መደብ ለመያዝ እጅግ አስፈሪ የሆነ የጨበጣ ጦርነት ጀመረ አብዮታዊ ሠራዊት የከፈለውን መስዋዕትነት ከፍሎ ምፅዋን እንዲያቆይና የእርዳታ ጦር በምድርና ባህር እስኪደርስለት ወጥሮ እንዲዋጋ ጄኔራል ተሾመ ለሁሉም የጦር አዛገች ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን ቀጥለዋል የሻዕቢያ ሠራዊት በበኩሉ ከአዛዣቹ ያለ የሌለ ጉልበቱንና ኃይሉን ተጠቅሞ ምፅዋ ከተማንና የምጽዋ ባህር ኃይል መደብን እንዲቆጣጠር ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተስጠው ያስታውቃል ጦርነቱ ቀጠለሰ ሻዕቢያ በመጀመሪያ ደረጃ ለመቆጣጠር የፈለገው ምፅዋ የሜገኘውን የኢትዮጵያ ባህር ኃይል መደብ ስሰነበረ ከባድ ማጥቃት በባህር ኃይል ላይ ስነዘረ ግራር በተባለ አካባቢ እጅግ ከባድ ጦርነት ነበር ጄኔራል ተሾመ በባህር ኃይል መደብ የነበሩትን የጦር አዛዥች አይዞአችሁ እያሉ በጦር ሜዳ ሬዲዮ ያስተባብራሉ ሻዕቢያ በከባድ መሣሪያ ድብደባና በሜካናይዝድ ኮማንዶ ኃይል ተደግፎ በማጥቃት የባህር ኃይል መደብን ይዘው ይዋጉ የነበሩትን የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ለማዳከም ይሞክራል የባህር ኃይል ተዋጊ መርከቦችም በበዙላቸው በባህር ላይ ሆነው የቢኤምና የመድፍ ጥይቶች በሻዕቢያ ላይ ያዘንባሉ ባህር ኃይል የነበሩ የአብዮታዊ ሠራዊት ታንኮች ደግሞ የሻዕቢያን ታንኮች አላላውስ ብለዋል ጄኔራል ተሾመ «አይዞአችሁ የእኔ አንበሶች። ለሻዕቢያ ተገቢውን ቅጣት ስጡት «ሞት አይቀርም ስም አይቀበርም እያሉ ያዋጋሉ በዚህ ሁኔታ ውስጥ በዚያ ከተሰለፉት አብዛኛዎቹ የሻዕቢያ ታንኮች ጋዩ ቪ ከዕዳጋ ከተማ ወደ ምፅዋ ባህር ኃይል መደብ የሚወስድ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚሆን የመኪና መንገድ አለ በሰፊ ሜዳ ላይ የተዘረጋና ወደ ባህር ኃይል ሲገባ በቀኝ በኩል በቀይ ባህር የተከበበ በመሆኑ ሻዕቢያ ይህን ፈታኝ ሜዳ አልፎ ነው የባህር ኃይል መደብን መያዝ የሚችለው ሻዕቢያ ይህን ሜዳ ለማቋረጥ ቢሞክርም አአተሳካለትም ከፍተኛ ፈተና ገጠመው በባህር ኃይል መደብ ተከማችተው ይገች የነበሩት የአብዮታዊ ሠራዊት ታንኮች ባለ ዐ እና ሚሊ ሜትር መድፎች ባለ ሚሊ ሜትር ሞርተሮች ዘ ብረት ለበስ ቢቲአር ተሽከርካሪዎች ቀላልና ከባድ መትረየሶች ያነጣጠሩት በዚች መንገድና በሻዕቢያ ከባድ መሳሪያ ቀጣና ላይ ስለሆነ መላ አልተቻለም ይህን የሞት ቀጣና የሆነ መንገድ የደፈረ የሻዕቢያ ተዋጊ የሚጠብቀው ያለጥርጥር ሞት ሲሆን ይህን መንገድ አቋርጣለሁ ያለ የሻዕቢያ ታንክም በታንክ ተመቶ መንደዱ አይቀሬ ነው ሽዕቢያ ይህን ተረድቶ የመጀመሪያ ሙከራውን በማቆም ሌላ ዘዴ ለመፈለግ ጊዜ የወሰደበት አይመስልም የካቲት ቀን ንጋት ላይ ጀምሮ የከባድ መሣሪያ ውርጅብኝ የሚያወርደው በባህር ኃይል መደብ ላይ ብቻ ሳይሆን በምፅዋ ከተማ ላይም ጭምር ነበር ስለዚህ የባህር ኃይል መደብን ለመያዝ በመረጠው አዲስ ዘዴ በምፅዋ ከተማ ላይ የሚያዘንበውን የከባድ መሣሪያ ጥይት ወዲያውኑ በማቆም ያለውን የከባድ መሣሪያ አፈሙዝ በጠቅላላ ወደ ባህር ኃይል መደብ አዞረው እጅግ አሰቃቂ እልቂት ደረሰ በባህር ኃይል ግቢ የነበሩ ህንዓዎች ፈራረሱ ግራር የተባለች ክፍለ ከተማና የምፅዋ ሆስፒታል በጠቅላላ ወደሙ ጄኔራል ተሾመ ሻዕቢያን ይከላከሉ የነበሩ ታንኮችና መድፎች ባልተቋረጠ ሁኔታ የምዕዋን ባህር ኃይል መደብ ሰመቆጣጠር የሚተረማመሰውን የሻዕቢያን ታንክና እግረኛ እንዲደበድቡ ለኮሎኔል በላይ አስጨናቂ ትዕዛዝ ሰጡ በላይ አስጨናቂም ጀግንነት በተሞላበት ሁኔታ ሸራ በሌላት ዋዝ ጂፕ መኪና በምፅዋ ከተማ ውስጥ እየተዘዋወሩ ሁሉም የከባድ መሣሪያ ምድብተኞች ተኩሱን እንዲያፋፍሙ ትዕዛዝ ሰጡ ከሻዕቢያ እና ከአብዮታዊ ሠራዊት የሚተኮሱት የከባድ መሣሪያ ጥይቶች ፍንዳታ በምፅዋ አካባቢ ከባድ እሣተ ገሞራ የፈነዳ አስመሰለው ሻዕቢያ በባህር ኃይል መደብና አብዮታዊ ሠራዊት ደግሞ በሻዕቢያ የውጊያ ወረዳ ላይ የሚያዘንቧቸው የከባድ መሣሪያ ጥይቶች የባህር ኃይል መደብ እንዲሁም የምዕዋ አየር ማረፊያ ሜዳና ዕዳጋ ከተማ ተቀጠቀጠጡ ጄኔራል ተሾመ በሌላም በኩል ተዋጊ የጦር አውሮፕላኖች ከአሥመራ ተነስተው ሻዕቢያን እንዲደበድቡ ከሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ዘመቻ መምሪያ አዛፐች ጋር ተነጋግረው ስለነበር አውሮፕላኑም በጦርነቱ ተሳተፈ በመጀመሪያ አራት ተዋጊ ጄቶችና አራት ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች በጣም ከፍ ብለው በመብረር በምዕዋ ከተማ ላይ አንዣበው ወደ ቀይ ባህር አለፉ ቀጥለው ዝቅ ብሰው በመምጣት በዕዳጋ ከተማና አካባቢዋ በሚተረማመሰው የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያና እግረኛ ተዋጊ ላይ ቦምብ አዘነቡ ከባድ ፈንጂዎች ስለሚጥሉ የአካባቢው መሬት ተናወጠ የሻዕቢያ አየር መቃወሚያ ምድብም በዘ አየር መቃወሚያ ሰማዩን አናወጠው የአውሮፕላን ድብደባው ከባድ ጉዳት በሻዕቢያ ላይ አድርሷል በምፅዋ አየር ማረፊያ አካባቢ ታንኮችን አጋይቷል ታንኮችን በሚመታበት ጊዜ ታንኩ የታጠቃቸው ጥይቶች ተቀጣጥለው ስለሚፈነዱ እጅግ የሚዘገንን ድምፅ ይሰማ ነበር ይህን መሰል ተከታታይ ፍንዳታ ለግማሽ ሰዓት ያህል ቆይቷል ይህ የሆነው የካቲት ቀን ዓም ከጠዋቱ ዐ ሰዓት አካባቢ ነበር ውጊያው ከሌሊቱ ዐዐዐ ሰዓት ስለጀመረ በየሰከንዱ የሰው ህይወት እየተቀጠፈ እስከ ጠዋቱ ሰዓት መዝለቁ እጅግ ከባድና መራራ ሁኔታ ነውፎ ባልተቋረጠ ውጊያ ውስጥ ለኗዐዐ ሰዓት መቆየት ማለት ቀላል አይደለም ሹ ሻዕቢያ ለከባድ መሣሪያዎቹ እዲሁም ለተዋጊ ጄቶቹና ሄሊኮፕተሮቹ ድብደባ አልተበገረም ያሰ የሌለ ኃይሉን ይዞ «ባህር ኃይል መደብ ወይም ሞት» ብሏል በምድር ውጊያ የሰለጠኑ ኮማንዶ ብርጌዶችን አሰልፎ ገፋበት በመሆኑም በአውሮፕላን ድብደባው ምክንያት ለተወሰነ ሰዓት አቋርጦት የነበረውን የምፅዋ ከተማን ድብደባ ጀመረ በምዕዋ ከተማና በባህር ኃይል መደብ ላይ አሰቃቂ የከባድ መሣሪያና የአርፒጂ ላውንቸር ጥይት አዘነበ በዚህ ድብደባ በወገን ላይ በደረሰው ሽንፈትም የሞት ቀጣና ተብሎ የተከለለውንና የምጽዋ ባህር ኃይል መግቢያ የሆነውን የመኪና መንገድ ሜዳ አቋርጦ አለፈ የጨው ፋብሪካውን ግራር የተባለችውን የምፅዋ ከተማ ክፍልና ባህር ኃይል መደብ አካባቢ የሚገኘውን የምዕዋ ሆስፒታልን በሙሉና በከፊል ተቆጣጠረ አብዮታዊ ሠራዊት ክፉኛ ተዳከመ ሻዕቢያ ተጨማሪ ተዋጊ ብርጌዶቹን አመጣና በከፍተኛ የውጊያ ግብግብና ጨበጣ የካቲት ቀን ዓም ከጠዋቱ ቁዐዐ ሰዓት የምፅዋ ባህር ኃይል መደብን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጠረ የባህር ኃይል መደቡን በመቆጣጠሩ ሽዕቢያ በውጊያ ታሪኩ ጨብጦት የማያውቀውን ድል ጨበጠ የካቂት ቀን ብርጋዲየር ጄኔራል ጥላሁን ክፍሌ የመክት ዕዝ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል ዓሊ ሐጂ የኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ካፒቴን ፀጋዬ መኮንን የስሜን ቀይ ባህር ኃይል ምክትል አዛዥና ሌሎችም ከምክትል መቶ አለቃ እስከ ሻለቃ ማዕረግ ያላቸው የአብዮታዊ ሠራዊት አዛፐች ተማረኩ በአብዮታዊ ሠራዊት ላይ የማይቀለበስ አደጋ ተፈጠረ ሻዕቢያ በጠራራ ፀሐይ ቦባህር ኃይል ግቢ ውስጥ ከበሮ እየደለቀ ጨፈረ። ሻዕቢያ ተኩስ በሚጀመርበት ስዓት በአንድ ደቂቃ ከፃያ ያላነሱ የከባድ መሣሪያ ጥይቶችን ወደ ምዕዋ ከተማ ስለሚወረውር ፋታ የማይሰጥ ጦርነት በመሆኑ ሰው በደቂቃ ልዩነት ወይም ለመብላት የጓጓላትን አንዲት የረሃብ ወቅት ጉርሻ አላምጦ ሳይውጥ ሞት ይጐነጫል በዚህ ውጊያ ብዙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት በጀግንነት ተዋግተው አዋግተዋል የዚህ ታሪክ ፀሐፊ በነበረበት የሠራዊቱ አመራር አካባቢም ጄኔራል ተሾመ ኮሎኔል በላይ አስጨናቂ ሻለቃ ሮሪሣ ዳዲ ሻምበል አስናቀ ሻምበል ባሻ አማረ የመቶ አለቃ ሐይማኖት ወታደር ሸንገረፋ ሻምበል ሸዋንታዬ ዓለሙ መጋቢ አለቃ አያሌው ሻለቃ ኃይሉ አየለ ሻምበል ዓለም ሻምበል ወንድወስን የተባሉት የሠራዊቱ አመራሮችና ፀሐፊው በፍጹ ጀግንነት አብዮታዊ ሠራዊትን አስተባብረው አዋግተዋል የካቲት ቀን ደግሞ የሠራዊቱ ከባድ መሣሪያ ምድብተኞች ማለትም ታንከኛ መድፈኛና አየር መቃወሚያዎች አዳናዔና ከባድ መትረየሶችን በአንድነት በማስተባበርና በሻዕቢ ምሽግና ይዞታ ላይ የእሩምታና የተባበረ ተኩስ በመተኮስ የሻዕቢያን ከባድ መሣሪያ ድብደባና የእግረኛ ተዋጊዎቹን እንቅስቃሴ ለመግታት ያደረጓቸው ሙከራዎች የተሳኩ ነበሩ ስለዚህ የዚች ዕለ ፍላጐቱም ሳትሳካ ቀረች ሽ በዚች ዕለት ሻዕቢያ ምፅዋን ለመቆጣጠር ያልቻለበት ምክንያትም አለ ይህም ከዕዳጋ ወደ ምዕዋ የሚወስደው መንገድ መዘጋት ነው ቀደም ሲል እንደተገለጸው ከዕዳጋ ከተማ ወደ ምፅዋ መስል የመኪና መንገድና የባቡር ሐዲድ ከግራ ከቀኝ በኩል ጥል ት ባለው የቀይ ባህር ውኃ የተከበበ ነው ይህ መንገድ ሻዕቢያ የ ቀን ዓም በታንከኛ ሠራዊቱ እያጠቃ ምዕዋን ለመያሽ ሲሞክር አንድ ታንክ በአብዮታዊ ሠራዊት ታንክ ተመቶ በጉ አግድም መንገዱን ዘግቶ በመቆሙ ከዕዳጋ ከተማ ወዴ ባፀዕ ምፅዋ ያለው መንገድ ተዘግቷል የካቲት ቀን በዚያው ሁ ስለአለ የሚያሸጋግረው ድልድይ መሰል መንገድ ሙሉ ለ ለትራፊክ እንደተዘጋ ነው በዚች መንገድ በተሽከርካሪ ለማለፍ መንገዱን ዘግቶ የተቃጠለውን የሻዕቢያን ታንክ ቅሪት በሌላ ወይም በከፍተኛ ክብደት ማንሻ አንስቶ ወደ ቀይ ባህር ውኃ « የግድ ነው ይህ ግን በውጊያው ሁኔታ ውስጥ የሚቻል አልነበረ በመሆኑም ሻዕቢያ ከምፅዋ በስተምዕራብ የምትገኘውን የዕዳጋ ከተማንና የኢትዮጵያ ባህር ኃይል መደብን በቁጥጥሩ ስር አድርጐ የማጥቃት ውጊያውን በከባድ መሣሪያ ከመቀጠል በስተቀር አማራጭ አልነበረውም ከመንገዲ መዘጋት በተጨማሪ አብዮታዊ ሠራዊት በባህር የተከበበችውን የምፅዋ ከተማን ይኮ የመከላከል ውጊያ በከባድ መሣሪያና በተዋጊ ጦር አውሮፕላኖች እያደረገ ነው ስለዚህ ሻዕቢያ የካቲት ቀን ከቀኑ ዐዐ ሠዓት ጀምሮ የተማመነበትን የከባድ መሣሪያ ድብደባ አማራጩንም አቆመ ጄኔራል ተሾመ በዚህ ሰዓት ምዕዋ ቤተመንግሥት ነበሩ የምፅዋ ቤተመንግሥት ጥንታዊ ህንዓ በመሆኑ ከጠንካራ ድንጋይ የተገነባ ባለ ሁለት ደረጃ ፎቅ ነውር ሦስት ብሎኮች አሉሕ ይህ ቤተ መንግሥት ለሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ድብደባ የተጋለጠ ነበር የካቲት ቀን ዓም ከቀኑ ፅዐዐ ሰዓት ላይ ጄኔራል ተሾመ የፅኛ ክፍለ ጦር መምሪያ መኮንኖችን የብርጌድ አዛዝችንና ካድሬዎችን በዚህ ቤተመንግሥት ሰበሰቡ በስብሰባው ላይ የተገኙት ሻለቃ ሮሪሣ ሻለቃ ኃይሉ ሻምበል አበበ ኮሎኔል በላይ የዛአለቃ ታደስ ሻምበል ባሻ አማረ ሻምበል ሽሸዋንታዬ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ብርጌድ አዛዝችና ሻለቃ አዛዝች ነበሩ ስብሰባውን በንግግር የጀመሩት ጄኔራል ተሾመ ነበሩ በንግግራቸውም ጓዶች አሁን የፈለኳችሁ ለአጭር ጊዜ ስብሰባ ነው ይኸውም ሻዕቢያ ከየካቲት ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በከባድ መሣሪያ ጥቃት በሚዘገንንና ሰብአዊነት በጐደለው አኳኋን በአብዮታዊ ሠራዊት አባላትና በምፅዋ ከተማ ነዋሪዎች ላይ ከባድ አደጋ አድርሷል እያደረሰም ነው በዚህና በከባድ መሣሪያው ጋጋታና ውርጅብኝ ዓላማና ጽናታችን ባይበገርም በየቦታው የወደቀውና የተቆለለው የሰው አስከፊን መጥፎ ሽታ አካባቢውን አውዶታል ይህ ደግሞ ለተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች ይዳርገናል። ነገ ተገደው ለፍርድ ይቀርባሉ የኢትዮጵደ ሕዝብ እንደነዚህ ዓይነቶችን ፈሪዎችና ሆዳሞች እንደማይምር ግልጽ ነው» አሉ የመጨረሻ ንግግር ሳይሆን አይቀርም ሽዕቢያ ያን ዕለት ምንም ዓይነት የመሣሪያ ድምፅ ሳያሰ አደረ በተረፈችዋ ሌሊት በምፅዋ አካባቢ ጊዜያዊ ሰሳም ተፈጠረ ምስሌ ስሥሌ ከሴት ረቻኛ ወድያኝ የካቲት ቀን የተፈጥሮ ግዴታ ነውና ጠዋት ሆነ ጉምና ደመና የቀይ ባህርን ዕይታ ጋርዶታል ፀሐይ ከደመናውና ከጉሙ ጀርባ ሆና ምዕዋ ከተማን ለማየት ተጨንቃለች ይህን ቀን ከአለፉት የጦርነት ቀናት የሚለየው የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ድብደባ አለመኖሩ ነው የከባድ መሣሪያ ድብደባ ቆሟል ወታደሩም ሆነ ነዋሪው ሕዝብ ትንሽ ተንፈስ ብሏል የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ድብደባ የቆመው ከየካቲት ቀን ከዐዐ ሰዓት ጀምሮ ነው የሻዕቢያ የእጅ ስጡ የገደብ ሰዓት ደረሰ ጄኔራል ተሾመ እስከመጨረሻው የደማችን ጠብታና እስከ ሕይወታችን ፍፃሜ እንዋጋለን የሚል አመራርና ትዕዛዝ ለሁሉም የጦሩ አመራሮች ስለሰጡ ከጠዋቱ ቱዐዐ ሰዓት ጀምሮ የሁሉም አባላት ጣቶች በመሣሪያዎቻቸው ምላጮች ላይ ነበሩ ሻዕቢያም ምፅዋ አካባቢን ለቆ የፄደ ይመስላል ምንም ዓይነት የጠላት እንቅስቃሴ አይታይም ይሁን እንጂ ከቀኑ ዐዐ ሰዓት አንድ መልኳ አረንጓዴ የሆነ የቤት መኪና ከዕዳጋ በከባድ ፍጥነት እየበረረች ወደ ባህር ኃይል መደብ ገብታ ተሰወረች ሻዕቢያ በአካባቢው መኖሩ በእርግጥኝነት ተረጋገጠ መኪናዋ ከተወሰት ደቂቃዎች ቆይታ በኋላ ወደ ዕዳጋ ከተማ በከባድ ፍጥነት ተመለለሰች በከባድ ፍጥነት ትብረር እንጂ ርቀቷ አብዮታዊ ሠራዊት በመትረየስ መምታት የሚችልበት ርቀት ነው ማለትም የተመላለሰችው ከአብዮታዊ ሠራዊት በአንድ ኪሎ ሜትር ተኩል በሚገመት ርቀት ነው ፒኬኤም በተባለ መትረየስ ጠመንጃ ደግሞ እስከ ኪሎ ሜትር ርቀት ድረስ መግደልና ማቁሰል ይቻላል የሆነው ይሁን ከአብዮታዊ ሠራዊት የተተኮስ ነገር የለም ሻዕቢያ የሰጠው የድርድር ቃል ተቀባይነት ማጣቱን ያረጋገጠው የካቲት ቀን ዓም ከቀኑ ዐዐ ሰዓት ላይ ይመስላል የከባድ መሣሪያ ጥይት እሩምታውን አወረደው የአብዮታዊ ሠራዊት አባላትና ሰላማዊ ሰዎች ተጨፈጨፉ በድንገት በዘነበው በዚህ የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ እሩምታ ብዙ ሰው ተጐዳ ሕይወቱን እጅ እግሩንና ሁለት ዓይኑን ያጣ ጥቂት አይደለም ይህ መብረቃዊ ውርጅብኝ ሻዕቢያ በምፅዋ የተከማቸውን አብዮታዊ ሠራዊት ተስፋ ለማስቆረጥ ያደረገው ነው ከቀኑ ዐ ሰዓት እስከ ምሽቱ ዐ ሰዓት ለተከታታይ ዐ ሰዓት ቀጠሰ በዚህ ዕለት ያለቀው አልቆ የቀረው ቀረ ሌሊቱም እንደልማዱ ፀጥ አለ የካቲት ቀን ጠዋት ከተማዋ ሕይወት ያለባት አትመስልም ሻዕቢያ በዚች ዕለት ተኩስ የጀመረው ከንጋቱ ሰዓት ላይ ነበርፊ እስከ ቀኑ ፅዐዐ ሰዓት ድረስ ያለ የሌለውን የከባድ መሣሪያ ጥይት አወረደው አብዮታዊ ሠራዊትም አቅሙ በፈቀደ ሁሉ ያሉትን ከባድ መሣሪያዎች አስተባብሮ ሻዕቢያ ወደሚተኩስበት አቅጣጫ እየተኮሰ ተክላከለ ተዋጊ የጦር አውሮፕላኖች ሚግና ሚግ እንዲሁም ኤም ፄሲኮፕፐተሮች በበኩላቸው በሻዕቢያ ላይ የቦምብ ናዳ በተከታታይ አወረዱ ሻዕቢያ የሚወርድበት የአውሮፕላን ቦምብ ሳይበግረው የከባድ መሣሪያውን ድብደባ ቀጠለበት አየር ኃይል ሻዕቢያን በቦምብ ይደበድባል ሻዕቢያ ደግሞ ምፅዋ ከተማ ያለውን አብዮታዊ ሠራዊት በከባድ መሣሪያ ክፉኛ ይደበድባል እስከ ቀኑ ዐዐ ሰዓት ድረስም በዚህ ዓይነት ቀጠሰ ሻዕቢያ የካቲት ቀን ከቀኑ ዐ ሰዓት ላይ የከባድ መሣሪያ ድብደባውን ሙሉ ለሙሉ አቆመ ሰላም ወረደ ይሁንና ብዙ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ክፉኛ ተጎድተዋል የምፅዋ ከተማ መንገዶችና ቤቶች ዶዘር ያረሳቸው ይመስላሉ ብሽ በተለይም የቀይ ባህር ተወላጅ የሆኑ የአፋርና የአሳውርታ ብሔረሰብ አባላት እጅግ ተጎዱ ከዐዐ ያላነሱ በሕዝባዊ ሠራዊት ሠልጥነውና ታጥቀው ከአብዮታዊ ሠራዊት ጐን ተሰልፈው ነበር ቀደም ሲል በአካባቢ ሚሊሺያነት ሻዕቢያን ለመዋጋትና የአካባቢውን ሠላም ለመጠበቅ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው ሻዕቢያ የስንዴ ሠራዊት» በትግሪኛ ሥርናይ ሠራዊት እያለ ይጠራቸዋል በምፅዋ ከተማ ከሠራዊቱ ጋር ስለነበሩ በብዛት የከባድ መሣሪያ ጥይት ሰለባ ሆነዋል ከእነዚህ ሚሊሺያዎች አብዛኛዎቹ የጀብሐ አባላት የነበሩ ናቸው ለአብዮታዊ ሠራዊት እጅ ሰጥተው ሻዕቢያን ለመደምሰስ ቆርጠው የተነሱም ነበሩ በዕለቱ ከመካከላቸው ከሰባ ያላነሱ የአካባቢ ሚሊሺያዎች ሞተዋል ብዙዎችም ቆስለዋል እነዚህን የአካባቢ ሚሲቪያዎች የስንዴ ሠራዊት» ል ስም ሻዕቢያ የሰየማቸው መንግሥት ለነዚህ ሚሊሺያዎች በየወሩ በነፍስ ወከፍ አንድ ኩንታል ስንዴ እና ሦስት ሊትር ዘይት ለቀለብ እየሰጣቸው ስለሚያሠራቸው ነው ስንዴውም ከዓለም ማሕበረሰብ ለረዛሃብ ተረጂዎች የሚለገስ ሲሆን በነፃ ከሚሰጣቸው የአካባቢያቸውን ፀጥታ እየጠበቁ እንዲታደላቸው የተደረገ ነው የሻዕቢያ ተኩስ ሙሉ ለሙሉ እንደቆመ ጄኔራል ተሾመ ኮሎኔል በላይ አስጨናቂ ሻለቃ ሮሪሣ ዳዲ ቫለቃ ኃይሉ አየለ ሻምበል አዲሱ መቶ አለቃ ዛይማኖትና የ አለቃ ታደሰ በምፅዋ ቤተ መንግሥት አጭር ስብሰባ አደረጉ የስብሰባው ዓላማ በምዕዋ ስለሚገኝ አንድ የአብዮታዊ ሠራዊት የመሣሪያ ግምጃ ቤት ጉዳይ መነጋገር ነበር ስብሰባው በጄኔራል ተሾመ ማብራሪያ ተጀመረ «ሻዕቢያ በፈሪ ዱላ እየደበደበን ነው ይህ ሁሉ የሚወርድብን የከባድ መሣሪያ ጥይት የራሳችን ነው ከምፅዋ ወደ ጉርጉሱም በሚወስደው መንገድ ከአማተረ አልፎ በስተቀኝ በአለው ቦታ የሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ከባድ መሣሪያ ጥይት ግምጃ ቤት አለ ከዐ ሺህ ቶን ጥይት አንድም ጥይት ሳይወጣ እንዳለ በጠላት እጅ ወድቋል ሻዕቢያ ይህን ሁሉ የከባድ መሣሪያ ጥይት ነው በእኛ ላይ የሚያወርድብን በጣም ያሳዝናል እኒ በተቻለ ፍጥነት እንዲቃጠል አዝ ነበር ነገር ግን ተግባራዊ አልሆነም አሉ ሻለቃ ኃይሉ አየለ ያልተቃጠለበትን ምክንያት «አዎ ትዕዛዙን የተቀበልኩት እኔ ነኝ ቤንዚን ተርከፍክፎበት እንዲቃጠል ዘጩጩ ጩ ያ ሸዐሠ ጪጩ« በምጽዎ ውሂያ በሻቢያ ስባድ መግፈዖ ያወደመውና በጠ ቀቀ ቦፉቃጠፅው ያምህዎ መናዊ ሆሰፒታል ። ሽ ዩ ትዕዛዝ ልሰጥ ካሰብኩኝ በኋላ የከባድ መሣሪያ ጥይት ቃጠሎ ከተነሳ የመድፍ ጥይት እየፈነዳ ምፅዋ ከተማን ሳይቀር ሙሉ ለሙሉ ያወድማል አሰቃቂ አደጋም ያደርሳል ብዬ ስለሰጋሁ ተውኩት ምክንያቱም አንድ የከባድ መሣሪያ ጥይት ከፈነዳ ከአምስት እስከ አሥር ኪሎ ሜትር በራሱ ጊዜ በሮ ጥፋት ማድረስ ስለሚችል ፈርቼ ነው በተረፈ ጄኔራል ያሉት ትክክል ነው በማለት ተናገሩ ጄኔራል ተሾመ ቀደም ሲል ጥር ቀን በግምጃ ቤቱ ያሉ የከባድ መሣሪያ ጥይቶች ወደ አሥመራ እንዲጓዙ ከሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ድርጅት መኩንን ጋር ተነጋግረው ነበር ለሁለት ሣምንት በዐዐ ከባድ የጭነት መኪኖች እንዲያጓጉዙ ውሳኔ ላይ ደርሰው ነበር ከጥር ጀምሮ እንዲጓጓዝ ቢነጋገሩም የበላይ አካል ችግር ስለሌለ ቀስ በቀስ ይጓጓዛል እንዲሁም ዐዐ የጭነት መኪና የሚሆን አለ ከተባለና ይህም በአሥራ አምስት ቀን ውስጥ ከሚነሳ ቀስ በቀስ እስከ አራት ወር ድረስ ቢጓጓዝ መልካም ነው የሚል ሣዛሣብ አቅርቦ እንዳሰቡት ሳይሆን ቀረ እንደሁለቱ አዛዝች ዛሣብ ከጥር ቀን ጀምሮ ወደ አሥመራ ቢዓጓዓጓዝ ኑሮ የተወሰነ የከባድ መሣሪያ ጥይት አሥመራ ይገባ ነበር ወይም ተጠቃሎ ይነሳ ነበር ይህን ሁኔታ ጄኔራል ተሾመ ከቁጭት ጋር ለተሰብሳቢው ገለጡ ይህን ከሰሙ በኋላ ሻለቃ ሮሪሳ አሁንም ቢሆን በጦር ተዋጊ አውሮፕላኖች እንዲመታ ቢደረግስ የሚል አስተያየት ስለሰጡ ስብሰባው በዚሁ ተስማምቶ ጄኔራል ተሾመ ለጄኔራል ሁሴን በጦር ሜዳ ሬዲዮ ስለጉዳዩ አሳሳቢነት ሪፖርት አደረጉ ከግማሽ ሰዓት በኋላም አራት ተዋጊ ጄቶችና ሁለት ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች መጥተው የከባድ መሣሪያ ጥይት ተከማችቶበታል የተባለውን አካባቢ እጅግ ከባድ በሆነ ቦምብ ደበደቡ የሆነ ሆኖ የተገኘ ውጤት የሰለም የጥይቱ ማከማቻ ቢቃጠል ኑሮ የማያበራ ፍንዳታ ይከማ ነበር ምንም ነገር ኩሽ ሳይል ቀረ ጄኔራል ተሾመ ሻዕቢያ ማለት እኮ ተንኮለኛ ማለት ነው የከባድ መሣሪያ ማከማቻውን እንዳገኘ ውሎ ሳያድር ጥይቱን ወደ ሌላ ቦታ አጓጉዞት ይሆናል» በማለት ሣሣባቸውን ወደሌላ ጉዳይ አዞሩ የተዋጊ ሄሊኮፕተሩ አብራሪ ፓይለትም ከኛ ክፍለጦር አውሮፕላን አስተኳሽ ጋር ባደረጉት የሬዲዮ ግንኙነት የከባድ መሣሪያው ጥይት ተከማችቶበታል በተባለው ቦታ ላይ ምንም ነገር እንደማይታይ ተናግረው ወደ አሥመራ አቀት ምስሌፍ ስሥሌሴ ስምስት ም ያንዲራ የካቲት ቀን ዓም ከቀኑ ዐዐዐ ሰዓት ላይ ነጭ ባንዲራ ከፍ አድርገው የሚያውለበልቡ ሁለት ሰዎች ከሻዕቢያ ይዞታ አካባቢ ብቅ አሉ ሻዕቢያ ከአለበት ቦታ አስፋልት መንገዱን ይዘው ወደ ምዕዋ ከተማ መጡ የሲቪል ልብስ የለበሱ ሲሆን የሚጓዙት ጐን ለጐን ሆነው ነው ከዕዳጋ ከተማ ነዳጅ ማደያ አካባቢ እስኪደርሱ ሁሉም በጥሞና ይከታተላቸው ነበር ማደያው አካባቢ ሲደርሱ ግን ኮሎኔል በላይ አስጨናቂ «ምንድናቸው እነዚህ። ዐዐ ሰዓት አካባበ አቆመ ጄኔራል ተሾመ በተፈጠረው ሰላም ተደስተው በምዕዋ ዓለ አቀፍ ወደብና በተለያዩ የምፅዋ ከተማ ክፍሎች እየተዘዋዋ ሠራዊቱን አስተባበሩ የሠራዊቱ አባላትም የሻዕቢያን የጀልባ ወረ ለመመከት በምፅዋ ዙሪያ በቀይ ባህር ውኃ ጠረፍ ላይ በሦስ በሦስት ሜትር ርቀት ልክ እንደ ሽቦ አጥር ሰንሰለት እንዲሰሩ አደረጉ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ አላማ በምፅዋ ከተማ ህንፃዎች ላይ ያተኮረ ስለሆነ ነውሱ በመሆኑም አብዛኛዎቹ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት በዚህ ዘዴ ከሻዕቢያ ከባደ መሣሪያ ድብደባ ድነዋል ሻዕቢያ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት በምፅዋ ከተማ ህንፃዎች ውስጥ የመሸጉ መስሎት ብዙዎቹን ሕንፃዎች በከባድ መሣሪያ ደብድቧቸዋል የተዋበችና በወቅቱ የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ወደብ የነበረችው ምፅዋ ከተማ በሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ጥይቶች ፈራርሳለች ያምሩ የነበሩ ግንብ ቤቶች ገና አዲስ ቤት ለመስራት ከገልባጭ መኪና የተራገፈ ድንጋይ መስለዋል ጄኔራል ተሾመ ከ አለቃ ታደሰ እና ከሻምበል ወንድወሰን ጋር በመሆን በአብዛኛው የምፅዋ ወደብ የባህር ጠረፍ እየተዘዋወሩ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላትን አስተባብረው ከሌሊቱ ዐዐ ሰዓት ወደ ምፅዋ ቤተ መንግሥት ተመለሉሱ ሲደርሱ ከባህር ኃይል ግቢና ከዕዳጋ ከተማ በሚወነጨፉ የሻዕቢያ ታንኮችና ጥይቶች የምፅዋ ቤተመንግሥት ሙሉ ለሙሉ ፈራርሶና በየቦታው በተነሳ እሣት ተቃጥሎ እየጨሰ አገኙት ጄኔራል ተሾመ በጣም ተገረሙ ፊታቸውን ወደ ዛ አለቃ ታደሰ በማዞርም ደህና የነበረው ጥንታዊ የምፅዋ ቤተመንግሥት ዶግአመድ ሆነ አይደል። ብቻ ዛሬ ሌሊት የሞት ሽረት ትግል አድርገን ማንነታችንን ማስከበር አለብን» አሉ ጄኔራል ተሾመ በቆራጥነት ሻዕቢያ በምድር በከባድ መሣሪያ የሚያደርገውን ውጊያ አቁሞ ሌላ መላ እየፈለገ ነበር ጄኔራል ተሾመ ንግግራቸውን እንደጨረሱ ሁለት ሻምበል ጦር ወደ ምፅዋ ወደብ እንዲሄድ ሁለት ሻምበል ጦር ከዕዳጋ ከተማ ወደ ምፅዋ መግቢያውን በር እንዲቆጣጠርና አንድ ሻምበል ጦር በቤተመንግሥቱ ዙሪያ ተሰልፎ የሻዕቢያን ማጥቃት ለማኮላሸት እንዲንቀሳቀስ ምደባ ተደረገ ጄኔራል ተሾመ ለምፅዋ ወደብ የተመደበውን ሁለት ሻምበል ጦር ይዘው ተሰማሩ ከሌሊቱ ዐዐዐ ሰዓት አዲስና ከባድ የጦርነት ሁኔታ ተከሰተ ሻዕቢያ አቋርጦት የነበረውን ድብደባ በምድርና በባህር ጀመረ በምፅዋ ከተማ ላይ የከባድ መሣሪያ ጥይት ናዳ አወረደ ከምፅዋ በስተምሥራቅ ከቀይ ባህር ላይ ከተዋጊ ጀልባዎች የቢኤምና መድፍ ጥይቶች ተወነጨፉ ከምድር ከተለያዩ አቅጣጫዎች የታንክና የሌሎች ከባድ መሣሪያዎች ጥይቶች ልክ እንደ በረዶ በምፅዋ ከተማ ላይ ዘነቡ ይህን በመሰለ የከባድ መሣሪያ ተኩስ ሽፋንም የሻዕቢያ ተዋጊዎች ከዕዳጋ ከተማ በቀጥታ ወደ ጡዋለት በመግባት አንድ የምፅዋን ክፍለ ከተማ ተቆጣጠሩ ከዚያም በታንክና ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች ከባህር ኃይል ግቢ በቀጥታ በምፅዋ ወደብ በተከማቸው አብዮታዊ ሠራዊት ላይ ተኩስ ከፈቱ ብዙ የሠራዊቱ አባላትም ተጐዱ በሌላ አቅጣጫም ሻዕቢያ በከባድ እንቅስቃሴ የምፅዋን ቤተመንግሥት ለመቆጣጠር ከምሽግ ወጥቶ ወደፊት ገፋ ከአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ጋርም የእጅ በእጅ ውጊያ በቤተመንግሥቱ አካባቢ ጀመረ ሰዓቱ ለየካቲት ቀን አጥቢያ ከንጋቱ ዐ ሰዓት ነበር በሁሉም አቅጣጫዎች የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት በከባድ ጀግንነት ከሻዕቢያ ጋር በጥይት በእጅ ቦምብና በላውንቸር ተጨፋጨፉ መሬቱ እየነጋ ሲሄድ የምዕዋ ከተማ በአስከሬን ክምር በለው ሥጋ ብጥስጣሽና በደም ጐርፍ ጨቅይታለቹ ድመትና ውሻ የመረጡትን አስከሬን ይጐትታሉ አንዳንድ ቦታ ደግሞ የሰው አስከሬንና የውሻ ሬሳ ጐን ለጐን ተኝቷል በጣም የሚዘገንን ዕልቂት ነበር የከባድ መሣሪያ ጥይት የቆራረጠው የሰው አካል በየቦታው ዕጣ ያልወጣለት የቅርጫ ሥጋ መደብ መስሷል ብርጋዴር ጄኔራል ተሾመ ተሰማ የጀግናው ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥና የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ተሸላሚ የካቲት ዓም ከሻዕቢያ ጋር የሞት ሽረት ውጊያ ካደረጉ በኋላ በመጨረሻ የካቲት ቀን የገዛ ሽጉጣቸውን ጠጥተው ቀይ ባህር የገቡ «የምፅዋ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ናቸው» ጀግናው ብጄኔራል ተሾመ ተነ በምፅዋ ውጊያ ከተሰው በኋላ የኢትዮ መንግሥት መጋቢት ዓም የላቀ የ ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ሸልሞአቸዋል ለቤተሰባቸው የሜዳሊያው ምስክር ወረቀት ሰጥቶአቸዋል ምስሌፍ ስሥሬ ስካት ዘፖሪያ በሰፊዎቻ የካቲት ቀን ዓም ምፅዋ ከተማ ለተከማቸው አብዮታዊ ሠራዊትና አመራሩ ክፉ ቀን ነበረች ሻዕቢያ ደግሞ እንደ ልደት ቀን ይቆጥረዋል ምክንያቱም ለመጀመሪያ ጊዜ ምፅዋ ከተማን የረገጠው በዚች ዕለት ነውና ሻዕቢያ በዐ ዓም ከጀብሃ ተዋጊዎች ጋር በመሆን አብዛኛ ውን የኤርትራ ግዛት ተቆጣጥሮ ነበር አሥመራ ባሬንቱ ምፅዋና ዓዲቀይህ ከተማ የነበሩትን የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ደምስሶ እነዚህን ከተሞች መቆጣጠር ግን አልቻለም በመሆኑም የሄያ ስምንት ዓመታት ምኞቱን ሻዕቢያ በምፅዋ እውን ያደረገበት ቀን የካቲት ቀን ናት ጄኔራል ተሾመ ተሰማ የካቲት ቀን ዓም ከጠዋቱ ዐ ሰዓት ላይ በምፅዋ ከተማ ርዕሰ ምድርዕ በተባለ አካባቢ በከባድ መሣሪያ በፈራረሱ ቤቶች ጥግ ሆነው የተወሰኑ የጦር መኮንኖችን እና ባለሌላ ማዕረግተኞችን ሰብስበው ንግግር አደረጉ «ሻዕቢያ ያለ የሌለ ኃይሉን ተጠቅሞ በእጅ ቦምብና በክላሽ በአሁኑ ሰዓት የከተማ ውስጥ ውጊያ በማድረግ ላይ ነው ሻዕቢያ የከባድ መሣሪያ ድብደባ አቁሞ በእግረኛ ብቻ ለመዋጋት አዲስ ተዋጊ ኃይሱን በመኪና እያመላለሰ ዕዳጋ ከተማ ላይ እያከማቸ ነውፎ በአዲስ ጉልበት ተዋግቶ ምፅዋን ለመያዝ ቆርጦ ስለመነሣቱ ጥርጥር የሰውም አኔ የሚፈለግብኝን አደራ ተወጥቼአለሁ ከጥር ዐ ቀን እስከ ዛሬ የካቲት ቀን የሞት ሽረት ትግል አድርጌያለሁ የሻዕቢያን የጥፋት ዓላማ ለመግታት ያላደረኩት ጥረት የለም ከዚህ በኋላ ግን የራስን ህይወት በክብር ከማጥፋትና ለኢትዮጵያ ጀግኖችና ታሪክ ጸሐፊዎች ታላቅ ተምሳሌት ከመሆን ሌላ አማራጭ የለኝም ጀግንነት ማለት በሁሉም መልክ ለጠላት ምቹ ሆኖ አለመገኘት ማለት ነው በዚች የኢትዮጵያ ሕዝብ የባህር በርና ዓለም አቀፍ ወደብ በሆነችው በምፅዋ ከተማና በቀይ ባህር ጠረፍ ላይ ቆሜ ሽጉጤን ለመጠጣት ዝግጁ ሆኙአለሁ በእውነት እኔ ዛሬ በሞት በታሪክና በመጭው የኢትዮጵያ ትውልድ ፊት አልሸነፍም የአፄ ቴዎድሮስን ዕድል በማግኘቴም በጣም እኮራለሁ እኔ አሁን በሻዕቢያ እንደእነ ጄኔራል ጥላሁን እና ጄኔራል ዓሊ ሐጂ ተማርኬ የሻዕቢያን መሪዎች ዓይን ማየት ግን የሞት ሞት ነው «አፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዞች እጅ ወድቀው ከመዋረድ ሞትን መርጠው የራሳቸውን ህይወት መቅደላ ላይ አጠፉ እኔ ደግሞ በተራዬ ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት የተሰጠኝን የጄኔራልነት ማዕረግ ሳላስደፍር ለመንግሥትና ሕዝብ በገባሁት ቃል መሠረት አቅሜ የፈቀደውን ያህል ተዋግቼና አዋግቼ ሻፅ አራግፌአለሁ እንደ ጦር መሪም እንደ ተራ ተዋጊም ሁፔ ክላሽኒኮቭ ጠመንጃ ይዝ ተፋልሜአለሁ አሁን ግን ለመጨረሻ መስዋዕትነት ህይወቴን ለማጥፋት የቀሩኝ ጥቂት ደቂቃ ናቸው ገብዝ ስሙኝ። » ሲለው «አንድ ዓይ ነው የተጐዳው እንጂ አንደኛው ዓይኑ ያያል አልፈሰሰም ምንም ችግር የለም እኔ እመራዋለሁ በማለት መልስ ስ ተከላከለለት ታጋዩም በቁጣ «ህይወቱን ለማዳን ፈልገህ ነው እንጂ ሁለት ዓይኑ ጠፍቷል ልቀቀው ልግደለው ዞር በል» ቢለወ አይደለም ጌታዬ ያያል የዓይኑን ብሌን ደም ስለሸፈነው ነው የተገነዘበው የሻዕቢያ ታጋይም ትንሽ እንደ ማስተዋል አለና ሄደ ሳይገድለው በመሄዱም በጣም ተደስቶ እኔ እያለህ አትገደልም አይዞህ ተርፈዛል ምንም የለም» በማለት ዓይኖቹን ያጣውን ጓደኛውን እያበረታታ ከሌሎች ምርኮኞች እኩል ጉዞውን ቀጠሰለ ጉዞው ምርኮኛውን ወደሌላ ሥፍራ ለማዛወር የ ስለነበር ምርኮኛው ከምፅዋ ወደ አሥመራ በሚወስደው የመኪ መንገድ ያለ እረፍት በጥድፊያ በባዶ እግሩ ተጓዘ በውኃ በረፃዛብና በጥይት የተጐዳ ሰውነቱን እየጐጉተተም የካቲት ዓም ከቀኑ ዐዐ ሰዓት አካባቢ ዶጋሌ ወንዝ ደረሰ ዶጋለ ወንዝ ከምፅዋ ከተማ በግምት ሣያ አምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች ምርኮኛው ከወንዙ እንደደረሰ አርፋለሁ የሚል ግምት ነበረው ግምቱ አልሠራም የዶጋሌን ሰፊ አሸዋማ ወንዝ ተከትሎ ወደ ሰሜን አቅጣጫ ሦስት ኪሎ ሜትር ያህል እንዲጓዝ ተደርጐ ምርኮኛው ወንዝ ዳር እንዲያርፍ ትዕዛዝ ተሰጠ የዕረፍቱ ዋና ዓላማ በዕለቱ ግልፅ እንደሆነው ምርኮኛውን የማደራጀትና የፕሮፖጋንዳ ጉዳይ ነበር ወዲያውኑ ከምክትል መቶ አለቃ እስከ ሻለቃ ማዕረግ ያላቸው መኮንኖች ለብቻ ተሰለዩ ከተራ ወታደር እስከ ሻለቃ ባሻ ያሉትም አንድ ምድብ ውስጥ ተጠቃለሉ የእያንዳንዱ ምርኮኛ ስም ዝርዝር ተያዘ የጦር ክፍሉ የትምህርት ደረጃው ብሔሩ ዕድሜው የሥራ ኃላፊነቱ የትውልድ ስፍራው ወዘተ ተመዘገበ ከዚያ በኋላ በመቶ በመቶ ወታደሮች ተቆጥረው አንድ ኃላፊ ከምርኮኛው እየተደረገላቸው የሠራዊት አቋም በመጠኑ ያዙ ለዐ ምርኮኛ ወታደሮች የተሾመው ምርኮኛ ኃላፊ ደግሞ በተራው ሦስት ቦታ ከፍሎ ከመካከላቸው ኃላፊ ሾመላቸውና የስም ዝርዝር እየፃፈ ያዘ ይህ እንደተጠናቀቀ ከቀኑ ዐዐ ሰዓት አካባቢ ሲሆን የቫዕቢያ ኃላፊዎችና የውጪ ጋዜጠኞች መጠጡ ጋዜጠኞቹም የቢቢሲ ናቸው ምርኮኛውን በዘመናዊ የቪዲዮ ካሜራ እና በፎቶ ካሜራ ቀረጹ ከዚያም የእንግሊዘኛ ቋንቋ ችሎታ ያላቸውን የአብዮታዊ ሠራዊት ምርኮኞች ለብቻ ወደ ዛፍ ሥር እየወሰዱ ቃለመጠይቅ አደረጉላቸው ቀኑ ሲመሽ ቃለመጠይቁ አቆመና ጭምር ስለአዳከመውም በየጦር ግንባሩ ሽንፈትን እየተከናነበ ነው ትግራይን ሙሉ ለሙሉና ኤርትራን ከግማሽ በላይ ተገዶ እንዲለቅ ተደርጓል ሠራዊቱ መሪዎቹን ከማጣቱም በላይ አሁን በሥልጣን ላይ ያሉትም ጄኔራሎችና ሌሎች የጦር መሪዎች የውጊያ ፍላጐት የላቸውም በትንሽ በትልቁ የሚገደሉ ስለሚመስላቸውም እኔን ጨምሮ ደርግን ሥልጣን ላይ ለማቆየት የሚታገል የለም በአሁኑ ጊዜ በኤርትራ የሚገኙትን የደርግ ሠራዊት ዕዞች እና ክፍለጦሮችን በተመለከተ ከሦስት ያላነሱ ክፍለጦሮች ያሏቸው አራት ዕዞች አሉ እያንዳንዱ ክፍለጦር ከአራት ያላነሱ ብርጌዶች አሉት የሁለተኛ ሜዛናይዝድ ክፍለጦር የሁለተኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር እንዲሁም ሠንጥቅ ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ በኤርትራ ተከማችቷል ከዚህ ውጭ የኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር እና ኛ ክፍለ ጦር በአሁኑ በምዕዋ ውጊያ ተደምስሰዋል ከ ሺህ ያላነስ ሠራዊት ከውጊያ ውጭ ሆኗል «በአየር ኃይል በኩል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሁለት ሬጅሜንቶች በኤርትራ አሉ ከአሥራ ስምንት ያላነሱ ተዋጊ ጄቶች እና ሄሊኮፕተሮች አሏቸው ባሕር ኃይልም የሰሜንና የደቡብ ቀይ ባህር የኢትዮጵያ ባህር ኃይል መምሪያዎች አሉት እነዚህም የምፅዋ ባህር ኃይል እና የአሰብ ባህር ኃይል መደብ ቤዝ በመባል ይታወቃሉ ሁለቱም ከዛያ ያላነሱ ተዋጊ መርከቦችና የውጊያ ጀልባዎች አሏቸው በአሁኑ በምፅዋ ውጊያ ብዛት ያላቸው ከጥቅም ውዌጭ ሆነዋል ቀሪዎቹ አሰብ እና ዳህላክ ደሴት እንደሚገኙ ይነገራል «በአጠቃላይ ሲታይ በኤርትራ የተከማቸው የደርግ ሠራዊት ግዙፍ ነው የውጊያ ፍላጐቱ ግን ከዜሮ በታች ነው የታጠቃቸው ከባድ እና ቀላል መሣሪያዎች ዘመናዊ ናቸው የመጠቀም አቅሙ ግን ከ በመቶ አይበልጥምሱ የኤርትራ ጦርነት በሠላም ይፈታል ተብሎ ሰአንድ ዓመት ያህል በኤርትራ ጦርነት ስለአልነበረ ከደርግ ጄኔራል ጀምሮ እስከ ተራ ተዋጊ ወታደር ድረስ ያለው ሠራዊት ሠላም እንጂ ጦርነት ፈላጊ አልነበረም «ሻዕቢያ በአሁኑ የካቲት ወር ዓም መጀመሪያ ላይ በምፅዋ ውጊያ ግንባር የጨበጠው ወታደራዊ ድል የዚሁ ውጤት ነው አይታችሁ ከሆነ በምፅዋ ውጊያ የደርግ ሠራዊት ከአምስት ደቂቃ ውጊያ በኋላ ሽሽት ይጀምር ነበር አንድም ጥይት ሳይተኩስ የሚሸሽም ብዙ ነበር እርግጥ ነባር የደርግ ወታደሮች ኃይለኛ የሀገር ፍቅር ስለአላቸው በቆራጥነት ተዋግተዋል ምልምል ወታደሮች እና የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት አባላት ደግሞ ሸሽተው ህይወታቸውን ማትረፍ ስለሚፈልጉ በምፅዋ ውጊያ ታንክ ከነሙሉ ጥይቱ አቁመው ሲሸሹ በዓይኔ አይቻለሁ እኔም ለእናንተ እጄን የሰጠሁት ፈጽሞ የውጊያ ፍላጐት ስለአልነበረኝ ነው ለማን ብኩ እዋጋለሁ ጓደኞቼና የእኔ ኮርስ የሆኑ ጀኔራሎች በመፈንቅለ መንግሥት ምክንያት ከበግ እኩል ታርደዋል ቀሪዎቹ ታስረዋል እኔ ማንን ሥልጣን ሳላይ ለማቆየት ብዬ ነው የምዋጋው። የትግራይ ወያኔ ከትግራይ ውጭ ወደ ወሎ ወደ ጐንደር ወደ ሰሜን ሽዋ እና አፋር ክፍለ ሀገሮች እየዘለቀ በመሆኑ ምክንያት ደርግ ሳይወድ በግድ ምርጥ ክፍለ ጦሮቹንና የውጊያ ልምድ ያላቸውን ወታደሮቹን ከኤርትራ ወደ መሐል ሀገር በመውሰድ ከወያኔ ጋር እየተዋጋ ነው በወለሰጋም ከኦነግ ጋር የሚያደርገው ውጊያ እንዲሁ ከኤርትራ የተወሰነ ተዋጊ ኃይሉን ይዞበታል «ለዚህም አሁን በምፅዋ ግንባር ሻዕቢያ ያገኘው ውጤት ራሱ ትልቅ አስረጅ ነው በምፅዋ ግንባር የተሠለፈው ሠራዊት የሻዕቢያን ማጥቃት በፍጹም መቋቋም አልቻለምፊ ከላይ እንዳልኩት የውጊያ ልምድ ከአላቸው የደርግ ወታደሮች ከ በመቶ በላይ ከኤርትራ ወጥተዋል እርግጥ ደርግ ብልጥ በመሆኑ ነባር ክፍለጦሮቹን ከኤርትራ ቢያወጣም በምትካቸው ብዙ አስገብቷል ምልምል ወታደሮችን እነዚህ ግን በኤርትራ ውጊያ ለማካሄድ የሚያስችሉ አይደሉም የብሔራዊ ውትድርና ለሁለት ዓመት አገልግሎት ለመስጠት ከዘመቱት ወጣቶችም ሆነ ከምልምል መደበኛ ወታደሮቹ አብዛኛዎቹ የውጊያ ብቃት እና ፍላጐት የላቸውም በተለይ የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ለመስጠት የመጡት ወጣቶች ተገደው ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን አቋርጠው የመጡ በመሆናቸው ከመካከላቸው አንድም የውጊያ ፍላጐት ያለው የለም ቺ ሁሉም ማለት ይቻላል በአገኙት አጋጣሚ በውጊያ ጊዜ ለመማረክ ወይም በሰላም ጊዜ ለመክዳት የወሰኑ ናቸው ደርግን ሥልጣን ላይ ለማቆየት መሞት አይፈልጉም እነዚህ ከደርግ ሠራዊት የፅዐ በመቶ ድርሻ ያላቸው ናቸው በመሆኑም የደርግ ኃይል የተዳከመ ነው ሌላ አደገኛ እና የደርግን ሥርዓት ያፈርሳል ተብሎ የታመነ ጉዳይም አለ ይህም የግንቦት ቀን መፈንቅለ መንግሥት በደርግ ሠራዊት ላይ ያስከተለው የመንፈስ ድክመት ነው ያለቁት ጄኔራሎች ደርግን በሥልጣን ላይ ለማቆየት ሲታገሉ የቆዩ የውጊያ ጀግኖች ነበሩ ጄኔራል ደምሴ ቡልቶና ጄኔራል መርዕድ ንጉሴ ተገድለዋል ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ተሰዲል ሌሎች በርካታ መሪዎችም ተገድለዋል ከእነዚህ አብዛኞቹ የታወቁ ጄኔራሎች በመሆናቸው ሠራዊቱ ዛሬ መሪ አጥቷል ይህ የውጊያ መንፈሱን ጭምር ስለአዳከመውም በየጦር ግንባሩ ሽንፈትን እየተከናነበ ነው ትግራይን ሙሉ ለሙሉና ኤርትራን ከግማሽ በላይ ተገዶ እንዲለቅ ተደርጓል ሠራዊቱ መሪዎቹን ከማጣቱም በላይ አሁን በሥልጣን ላይ ያሉትም ጄኒራሎችና ሌሎች የጦር መሪዎች የውጊያ ፍላጐት የላቸውም በትንሽ በትልቁ የሚገደሉ ስለሚመስላቸውም እነን ጨምሮ ደርግን ሥልጣን ላይ ለማቆየት የሚታገል የለም በአሁኑ ጊዜ በኤርትራ የሚገኙትን የደርግ ሠራዊት ፅቦች እና ክፍለጦሮችን በተመለከተ ከሦስት ያላነሱ ክፍለጦሮች ያሏቸው እራት ዕዞች አሉ እያንዳንዱ ክፍለጦር ከአራት ያላነሱ ብርጌዶ አሉት የሁለተኛ ሜዛናይዝድ ክፍለጦር የሁለተኛ አየር ወለድ ከፍለ ጦር እንዲሁም ሠንጥቅ ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ በኤርትራ ተከማችቷል ከዚህ ውጭ የኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር እና ኛ ክፍለ ጦር በአሁኑ በምፅዋ ውጊያ ተደምስስዋል ከዐ ሺህ ያላ ሠራዊት ከውጊያ ውጭ ሆኗል በአየር ኃይል በኩል የኢትዮጵያ እየር ኃይል ሬጅሜንቶች በኤርትራ አሉ ከአሥራ ስምንት ያላነሱ ተዋጊ ጄቶ እና ሄሊኮፕተሮች አሏቸው ባሕር ኃይልም የሰሜንና የደቡብ ቀይ ባህር የኢትዮጵያ ባህር ኃይል መምሪያዎች አሉት እነዚ የምፅዋ ባህር ኃይል እና የአስብ ባህር ኃይል መደብ ቤዝ በመባል ይታወቃሉ ሁለቱም ከዛያ ያላነሱ ተዋጊ መርከቦችና የውጊያ ጀልባዎች አሏቸው በአሁኑ በምፅዋ ውጊያ ብዛት ያላቸው ከጥቅም ውጭ ሆነዋል ቀሪዎቹ አሰብ እና ዳህላክ ደሴት እንደሚገኙ ይነገራል «በአጠቃላይ ሲታይ በኤርትራ የተከማቸው የደርግ ሠራዊት ግዙፍ ነው የውጊያ ፍላጐቱ ግን ከዜሮ በታች ነው የታጠቃቸው ከባድ እና ቀላል መሣሪያዎች ዘመናዊ ናቸው የመጠቀም አቅሙ ግን ከ በመቶ አይበልጥም የኤርትራ ጦርነት በሠላም ይፈታል ተብሎ ሰአንድ ዓመት ያህል በኤርትራ ጦርነት ስለአልነበረ ከደርግ ጄኔራል ጀምሮ እስከ ተራ ተዋጊ ወታደር ድረስ ያለው ሠራዊት ሠላም እንጂ ጦርነት ፈላጊ አልነበረም ሻዕቢያ በአሁኑ የካቲት ወር ዓም መጀመሪያ ላይ በምፅዋ ውጊያ ግንባር የጨበጠው ወታደራዊ ድል የዚሁ ውጤት ነው አይታችሁ ከሆነ በምፅዋ ውጊያ የደርግ ሠራዊት ከአምስት ደቂቃ ውጊያ በኋላ ሸሸት ይጀምር ነበር አንድም ጥይት ሳይተኩስ የሚሸሽም ብዙ ነበር እርግጥ ነባር የደርግ ወታደሮች ኃይለኛ የሀገር ፍቅር ስለአላቸው በቆራጥነት ተዋግተዋል ምልምል ወታደሮች እና የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት አባላት ደግሞ ሸሽተው ህይወታቸውን ማትረፍ ስለሚፈልጉ በምፅዋ ውጊያ ታንክ ከነሙሉ ጥይቱ አቁመው ሲሸሹ በዓይኔ አይቻለሁ እኔም ለእናንተ እጄን የሰጠሁት ፈጽሞ የውጊያ ፍላጐት ስለአልነበረኝ ነው ለማን ብዬ እዋጋለሁ።