Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ያኢትሦጵዖ መግብና መድኒት ባከሥክኳጣ ኦብዞለክ ዩዐ ልክዐ ዐክሀ ልሀፐዝዛዐፕኘ የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን የትምባሆ ቁጥጥር መመሪያ ጥቅምት አዲስ አበባ መግቢያ የትምባሆ ምርት በጤና በማህበራዊ በኢኮኖሚ እና በአካባቢ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያስከተለ የሚገኝ በመሆኑ ትምባሆን መጠቀም እንደካንሰር የመተንፈሻ አካል ህመም የልብ የደም ስር እና ሌሎች በሽታዎች እንዲሁም የአካል ጉዳት እና ሞት እንደሚያስከትል በሳይንስ የተረጋገጠ በመሆኑ በኢትዮጵያ የትምባሆ ተጠቃሚ ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ እና በአግባቡ ቁጥጥር ካልተደረገበት የበለጠ እየጨመረ የሚሔድና የጤና መታወክ በማስከተል የዜጎች የህክምና ወጪ እንዲጨምርና አገሪቱ ለመደኃኒት ግዢ የምታወጣው ወጪና የውጭ ምንዛሬ ከፍተኛ በማድረግ ምርታማነትን በመቀነስና መሰል ጉዳት በማድረስ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እየፈጠረ የሚገኝ በመሆኑ ትምባሆ ቀጥተኛ ተጠቃሚው ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ ለጭሱ የተጋለጡ ሰዎችን ጤና የሜጎዳ በመሆኑ ለህዝብ ክፍት የሆኑ ቦታዎችና የሥራ ቦታዎች ከትምባሆ ጭስ ነጻ እንዲሆን ማድረግ አፈጻጸሙን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን በምግብ እና መድኃኒት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል ክፍል አንድ ጠቅላላ አጭር ርዕስ ይህ መመሪያ የትምባሆ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ትርጓሜ በዚህ መመሪያ ውስጥ አዋጅ ማለት የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር ነው የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ ማለት መገናኛ ብዙሃንን የውጭ ማስታወቂያን የቴሌኮምን የፖስታ የኢንተርኔት ድረገፅ እና የፋክስ አገልግሎትን ሲኒማን ፊልምን ቪዲዮን ወይም መሰል የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ ነው ይዘት ማለት ትምባሆን ጨምሮ የትምባሆ ምርት ግብአት ግብአቱን ለማምረት የሚጠቅሙ ንጥረነገሮች ጭማሪዎች ለዝግጅት የሚያግዙ ነገሮች ትምባሆ ውስጥ የሚገኝ ቅሪት እና ከማሸጊያ ወደ ትምባሆ ምርቱ የሚገባ ንጥረነግር ነው ማጨስ ማለት የተለኮሰ ሲጋራ መያዝ ወይም የሲጋራ ጭሱን በትንፋሽ ወደ ውስጥ መሳብ ወይም ወደ ውጭ መልቀቅ ሁኔታ ወይም እነዚህ መፈጸም ነው ባለስልጣን ማለት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን ነው በአዋጁ ትርጉም የተሰጣቸው ሆነው በዚህ መመሪያ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉ ቃላትና ሐረጋት በአዋጁ የተሰጣቸው ትርጉም ይኖራቸዋል ማንኛውም በወንድ ጸታ የተገለጸ አገላለጽ ሴትንም ይጨምራል የአፈጻጸም ሁኔታ በዚህ መመሪያ ውስጥ በፌዴራል ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆኑ ጉዳዮችን ባለስልጣኑ የሚያስፈጽም ይሆናል የዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ እንደተጠበቀ ሆኖ ባለስልጣኑ ለክልል ጤና ተቆጣጣሪ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ያድርጋል የትምባሆ ቁጥጥር ስራዎችን በትብብር ይሰራል ክልሎች በአዋጁ የተቀመጡ መሰረታዊ መስፈርቶችና መመዘኛዎችን በተከተለ መልኩ በክልል በሚፈጸሙ ጉዳዮች የየራሳቸውን መመሪያ ሊያወጡና ሊያስፈጽሙ ይችላሉ ክፍል ሁለት የትምባሆ ምርት ልዩ ፈቃድ አሰጣጥ ስለልዩ ፈቃድ አሰጣጥ ባለስልጣኑ በዚህ መመሪያ መሰረት የትምባሆ ምርት ልዩ ፈቃድ ይሰጣል ማንኛውም ሰው በትምባሆ ምርት ማምረት ወደ አገር ውስጥ ማስገባት ማከፋፈል ወይም ጅምላ መሸጥ ስራ ከመሰማራቱ በፊት ልዩ ፈቃድ ከባለስልጣኑ ማግኘት አለበት ማንኛውም ሰው ልዩ ፈቃድ ከባለስልጣኑ ለማግኘት በዚህ መመሪያ የተቀመጡ ሁኔታዎችን ማሟላት ይኖርበታል ልዩ ፈቃድ ስለመጠየቅ ማንኛውም ሰው ከባለስልጣኑ ልዩ ፈቃድ ለማግኘት ባለስልጣኑ ባስቀመጠው የመጠየቂያ ስርዓት ጥያቄ ማቅረብ አለበት ልዩ ፈቃድ ጠያቂው የሚከተሉትን መረጃዎች መግለጽ አለበት ሀ የጠያቂው ድርጅት ስምና አድራሻ ለ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ስምና አድራሻ ሐ ልዩ ፈቃዱ የሚጠየቅበት የስራ ዓይነት ትምባሆ ለማምረት ለማስመጣት ለማከፋፈል መ የተጠየቀበት ቀን እና ሠ በመጠየቂ ስርዓቱ የተቀመጡ ሌሎች መረጃዎች በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት የሚቀርብ ጥያቄ የሚከተሉትን ሰነዶች በአባሪነት መያዝ አለበት ሀ ድርጅቱ የተቋቋመበት ሰነድና የንግድ ፈቃድ ቅጂ ለ ሥራው የሚከናወንበት ቦታ የድርጅቱ ከሆነ የይዞታ ማረጋገጫ ወይም በክራይ ከሆነ የጸና የክራይ ውል ቅጂ ሕ የአገልግሎት ከፍያ መክፈሉን የሚያረጋግጥ ደረሰኝ እና መ በመጠየቂያ ስርዓቱ የሚጠየቁ ሌሎች ሰነዶች የትምባሆ ምርት ልዩ ፈቃድ በስራው ዓይነት ለማምረት ለማከፋፈል እና ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት በሚል ለእያንዳንዱ ተነጣጥሎ የሚሰጥ ይሆናል አንድ ሰው በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ ከተዘረዘሩት ከአንድ በላይ በሆነ ስራ ውስጥ ለመሰማራት የፈለገ እንደሆነ ለየብቻ ልዩ ፈቃድ መጠየቅና ማግኘት አለበት ይህ ሁኔታ የትምባሆ አምራች ለጅምላ አከፋፋይ ለማስረከብ ስራን አይመለከትም የልዩ ፈቃድ ማረጋገጫ ኃ ባለስልጣኑ ለልዩ ፈቃድ የቀረበ ጥያቄን ተቀብሎ ከመረመረ በኋላ ተገቢው ሁኔታ መሟላቱን በማረጋገጥ የልዩ ፈቃድ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ይሰጣል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት የሚሰጥ የምስክር ወረቀት የሚከተሉትን መረጃዎች የያዘ ይሆናል ሀ የድርጅቱ ስምና አድራሻ ለ ልዩ ፈቃዱ የተሰጠበት የስራ ዓይነት ሐ ልዩ ፈቃዱ የተሰጠበት ቀን መ ልዩ ፈቃዱ የሚያበቃበት ቀን እና ሠ ፈቃዱን ያጸደቀው ኃላፊ ስምና ፊርማ በባለስልጣኑ የተሰጠ ልዩ ፈቃድ በድርጅቱ ስራ በሚያከናውንበት ቦታ በግልጽ መቀመጥ አለበት ልዩ ፈቃድን ስለማደስ እና ለውጥ ኃ በዚህ መመሪያ አንቀፅ መሰረት የተሰጠ ልዩ ፈቃድ በየዓመቱ መታደስ አለበት ልዩ ፈቃድ የሚታደሰው ፈቃዱ የተሰጠበት ጊዜ ለመጠናቀቅ ሁለት ወር ሲቀረው ጀምሮ በላው ጊዜ ይሆናል ልዩ ፈቃድ የሚታደሰው ሀ ባለልዩ ፈቃዱ ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ለ በባለስልጣኑ የሚጠየቁ መረጃዎችን ያቀረበ እንደሆነ እና ሐ አስፈላጊውን ክፍያ የፈጸመ እንደሆነ ነው በንኡስ ርፎ መሰረት ያልታደሰ ልዩ ፈቃድ በደንብ በሚወሰን ቅጣት እስከ ሁለት ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ ለማሳደስ ይቻላል በንኡስ አንቀጽ በተጠቀሰው ጊዜ ያልታደሰ ልዩ ፈቃድ እንደተሰረዘ ይቆጠራል በንኡስ አንቀጽ በተጠቀሰው በቅጣት የማሳደሻ ጊዜ ውስጥ እያለ ፈቃዱ ሳይታደስ ወይም በንኡስ አንቀጽ መሰረት በቅጣት የማሳደሻ ጊዜው በማለፉ የተሰረዘ እንደሆነ ልዩ ፈቃዱ የተሰጠበትን ስራ ማከናወን የተከለከለ ነው በንኡስ አንቀጽ ቁ መሰረት ልዩ ፈቃዱ የተሰረዘበት ሰው በቅጣት ከማሳደሻ የመጨረሻው ጊዜ ጀምሮ ባለው አንድ ዓመት ውስጥ በማንኛውም የትምባሆ ንግድ ስራ ለመሰማራት አይችልም የትምባሆ ምርት ይዘት እና ተያያዥ መረጃን ይፋ ማድረግ ማንኛውም የትምባሆ ምርት አምራች ወይም አስመጪ በትምባሆ ምርት ውስጥ ያሉትን ይዘቶች እያንዳንዱን የትምባሆ ምርት አይነት እና ነጠላ ምርቱን በብራንድ ግንድ ውስጥ ስላሉ እያንዳንዱን የብራንድ ምርቶችን ለማምረት ጥቅም ላይ ያዋላቸውን ይዘቶች በተመለከተ በዚህ መመሪያ በተቀመጠው ቅጽ መሰረት ለባለስልጣኑ መረጃውን ይፋ ማድረግ አለበት በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ባለስልጣኑ ስለንግድ ድርጅቱ አጠቃላይ መረጃ በትምባሆ ምርቱ ወይም ልቀት የሽያጭ መረጃሻ እና የምርቱን ውህድ ጎጂ ባህሪያቶችን እና የታወቁ ወይም የተለዩ ቅንጣቶች የተመለከቱ ተጨማሪ መረጃዎች እንዲያቀርቡ ሊያዝ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ እና መሰረት የሚቀርብ የትምባሆ ምርት ይዘት በተለይም የምርቱ ውህድ ጎጂ ባህሪያት የኒኮቲንና ኬሚካሎች መጠን በሶስተኛ ወገን ላብራቶሪ የተረጋገጠ መሆን አለበት ስለይዘትና ልቀት ገደብ የትምባሆ ምርት ይዘት እና ልቀት ባለስልጣኑ ከሚያስቀምጠው መጠን በላይ መሆን የለበትም የትምባሆ ምርት ሊይዘው የሚገባ የኒኮቲንና ሌሎች ኬሚካሎች መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ የሚሄድ መሆን አለበት ኛሙና ስለመሰብሰብ እና መፈተሽ ባለስልጣኑ ለቁጥጥር ዓላማ ወይም ልዩ ፈቃድ ለመስጠት ዓላማ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የትኛውንም የትምባሆ ምርት ናሙና ከማምረቻ ቦታ ከመግቢያ ኬላ ከመሸጫ ስፍራ ተከማችቶ ካለበት ቦታ ወይም ምርቱ በህጋዊም ሆነ በህገወጥ መንገድ ከሚገኝበት ቦታ እና ሰው ላይ ለመውሰድ ይችላል ባለስልጣኑ በንኡስ አንቀጽ መሰረት የሰበሰበውን ናሙና ወይም ለልዩ ፈቃድ የቀረበ ናሙና ሲኖር የትምባሆ ምርቱን በራሱ ወይም ዕውቅና ባለው የሶስተኛ ወገን ላብራቶሪ እንዲፈተሽና እንዲለካ ሊያደርግ ይችላል በምርመራ ከተፈቀደ ይዘት ውጭ ወይም መጠን በላይ መሆኑ የተረጋገጠ እንደሆነ የምርቱ ባለቤት ወጪውን እንዲሸፍን መደረግ አለበት ከዚህ ውጭ ላለሁኔታ የላብራቶሪ ፍተሻ ወጪውን ባለስልጣኑ የምርቱን ባለቤት እንዳስፈላጊነቱ ሊጠይቅ ይችላል የትምባሆ ምርት ወደ አገር ውስጥ ማስገባት ማንኛውም ሰው የትምባሆ ምርት ወይም ጥሬ ዕቃ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት የሚችለው ከባለስልጣኑ የተሰጠ የማስገቢያ ፈቃድ ሲኖረው ብቻ ነው የትምባሆ ምርትን ለግል ፍጆታ ወደአገር ውስጥ ይዞ መግባት የሚቻለው በግምሩክ ኮሚሽን በተወሰነው መጠን ብቻ ይሆናል ማንኛውም ሰው የግምሩክ ኮሚሽን ለግል ፍጆታ ይዞ እንዲገባ ከፈቀደው መጠን በላይ ይዞ የተገኘ እንደሆነ ምርቱ ተወርሶ መወገድ አለበት ሀህወጥ የትምባሆ ምርት መቆጣጠር ባለስልጣኑ በየወቅቱ ህጋዊ ምርቶችን ስም ለባለድርሻ አካላት ያሳውቃል በዚህ መመሪያ አንቀጽ እና መሰረት ለባለስልጣኑ መረጃ ያልቀረበበትን እና ስለምርቱ ስም አርማ ወይም መለያ እንዲያውቀው ያልተደረገ ምርት ማምረት ማስመጣት ማከፋፈል መሸጥ ማከማቸት ማጓጓዝ ወይም በማናቸውም ሁኔታ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው ባለስልጣኑ ህገወጥ ምርቶችን በየወቅቱ ለባለድርሻ አካላት ያሳውቃል አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስዳል እንዳግባብነቱም የሚመለከተው አካል የአስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ እና በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑያደርጋል ባለስልጣኑ አግባብነት ካለው አካል ጋር በመሆን ህጋዊ የትምባሆ ምርት ከህገወጥ ምርት መለየት የሚቻልበትን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስርዓት ይዘረጋል ስለትምባሆ ምርት ማሳወቅና ለውጥ ማንኛውም የትምባሆ አምራች ወይም አስመጪ የሚያመርተውን ወይም የሚያስመጣውን ምርት ይዘት ስምና የንግድ ምልክት ለባለስልጣኑ ማሳወቅ አለበት ልዉፎ ፈቃድ ተሰጥቶት ያለ ሰው ያሳወቀውን የትምባሆ ምርት ስም የንግድ ምልክት ይዘት ቅርጽ ማሸጊያ ወይም ማንኛውም የተፈቀደ መረጃ ላይ ለውጥ ከማድረጉ በፊት ለባለስልጣኑ ማሳወቅና ማስፈቀድ አለበት ልዩ ፈቃድ የተሰጠው ሰው አዲስ መለያ የትምባሆ ምርት ከማምረቱ ወይም ከማስመጣቱ በፊት ለባለስልጣኑ ማሳወቅ አለበት ክፍል ሦስት ትምባሆን ማስተዋወቅ ፕሮሞሽን እና ስፖንሰር ማድረግ ትምባሆን ማስተዋወቅና ፕሮሞት ማድረግ በአዋጁ አንቀጽ ትምባሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በማንኛውም መንገድ ማስተዋወቅ ክልከላ የሚከተሉትን ያካትታል ሀ በድምፅ በምስል ወይም በተንቀሳቃሽ ምስል የግንኙነት መንገዶች በህትመት በስዕል ወይም መልዕክት ለማስተላለፍ በሚችል ማንኛውም መንገድ ትምባሆን ስለትምባሆ ጽሑፍ ወይም ከትምባሆ ጋር ተያያዥ የሆነ ጉዳይን ማሳየት መግለጽ ወይም መጠቆም ለ በቴሌቪዥን በሬድዮ በስልክ በማህበራዊ ትስስር ገጽ በኢንተርኔት ወይም በመሰል የግንኙነት ዘዴ ትምባሆን ወይም ከትምባሆ ጋር ተያያዥ የሆነ ጉዳይን ማሳየት መግለጽ ወይም መጠቆም ሐ የትምባሆ ምርትን ወይም የትምባሆ ምልክትን ወይም ስዕልን ወይም የትምባሆ ገላጭ ሁኔታ በችርቻሮ መሸጫ ቦታዎች ላይ ማስቀመጥ ወይም ማሳየት መ የዋጋ ቅናሽ እንዳለ መግለጽ ሠ የትምባሆ ምርት የብራንድ ስም መለያ የንግድ ምልክት የድርጅት አርማ የንግድ መለያ ወይም ሌላ ተመሳሳይ መለያን የትምባሆ ምርት ካልሆኑ ሌሎች ምርቶች ወይም አገልግሎቶች ጋር ማያያዝ ወይም ትምባሆ ነክ ያልሆኑ ምርቶችን ወይም አገልግሎቶችን በተመሳሳይ መንገድ ከትምባሆ ምርት ጋር ቁርኝት ወይም ተያያዥነት እንዳላቸው መግለጽ ወይም ማሳየት በአዋጁ አንቀጽ ትምባሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በማንኛውም መንገድ ፕሮሞት ማድረግ ክልከላ የሚከተሉትን ያካትታል ሀ የትምባሆ ምርትን ወይም የትምባሆ ድርጅት ስም ወይም ትምባሆ የተመለከተ መልዕክት ስዕል መግለጫ ወይም መሰል ጉዳይ የያዘ እንደቁልፍ መያዣ ቲሸርት ኮፍያ ዣንጥላ መለኮሻ ወይም ሌላ ማንኛውም ቁስ ከትምባሆ ጋር ወይም ለብቻው ለሰው መስጠት ለ የድርጅቱን አርማ ወይም የትምባሆ ምልክት ያለው ወይም የድርጅቱ መለያ ወይም የትምባሆ ምልክት ባይኖረውም በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ከትምባሆ ጋር ግንኙነት ባለው ሁኔታ ያለን ቁስ ማቅረብ ወይም ማሰራጨት ሕ የገንዘብ ወይም የቁስ ስጦታ መስጠት ወይም ማቅረብ መ ናሙናን ጨምሮ የትምባሆ ምርትን በነጻ ማቅረብ ሠ የትምባሆ ምርቶችን ለገዛ ሌሎች እቃዎችን የሚገዛበትን ነፃ ኩፖን መስጠትን ጨምሮ ሌሎች ተመሳሳይ የምርቃት አይነት ተግባሮችን መፈፀም ረ መረጃን ጨምሮ ቀጥታ ግለሰቦች ላይ በማነጣጠር መልዕክት ወይም ደብዳቤ መላክ በስልክ መገበያየት የሸማቾ ችቅኝት ወይም ጥናት ማካሄድን እና ተመሳሳይ አይነት የፕሮሞሽን መንገዶች መጠቀም ሀገጉወጥ የትምባሆ ምርት መከላከል ወይም ሌላ ህጋዊ ጉዳይን በማስታከክ የትምባሆ ምርትን ወይም ድርጅቱን ማስተዋወቅ ወይም ፕሮሞት ማድረግ የተከለከለነው ቸርቻሪዎች የተወሰነ የትምባሆ መጠን ያለውን ምርት ሲሸጡ ሽልማት መስጠትን ጨምሮ ሌሎች የማበረታቻ ፕሮግራሞችን ለማስፈጸም ሽያጭን በሚያበረታታ መንገድ ለቸርቻሪዎች የሚደረግ ክፍያ ወይም ሌላ ድጋፍ ማድረግ የተከለከለ ነው የትምባሆ ምርት ማስታወቂያ በማሰረጨት የተሳተፈ ሰው መረጃውን በሚቆጣጠርበት ሁኔታ ላይ ካለ የተከለከለውን ስርጭት የማስነሳት ወይም እንደአግባቡ መረጃው ወይም ስርጭቱ ተደራሽ እንዳይሆን ተገቢ የሆነ እርምጃ መውሰድ አለበት ስለተፈቀዱ የንግድ መረጃዎች በዚህ መመሪያ አንቀጽ የተመለከተው ክልከላ ቢኖርም የሚከተሉት መረጃዎች የተፈቀዱ ናቸው ሀ አግባብ ባለው ህግ መስፈርት እና ወሰን መሰረት የትንባሆ ምርት የንግድ ምልክት ብራንድ ስም ምርት ስም እና የአምራች ስምን በትንባሆ ምርት ማሸጊያና ገላጭ ጽሑፍ ላይ ማሳየት ለ በትንባሆ አምራች አስመጪ አከፋፋይ ሻጭ ወይም እነዚህን በሚወክል ሌላ ሰው የተደረገ ምንም አይነት የገንዘብ ወይም የአይነት ክፍያ ሳይኖር በመገናኛ ብዙሀን ላይ የትምባሆ ምርትን ወይም ትምባሆን መጠቀም በተመለከተ በአጋጣሚ ወይም በታሪካዊ እውነታ ወይም ምክንያታዊ በሆነ የጋዜጠኝነት ወይም የስነጥበብ ስራ ላይ ወይም ትምህርታዊ ለሆነ አላማ የሚደረግ ገለጻ ሐ በትንባሆ አምራች አስመጪ ጅምላ አከፋፋይ ሻጭ ወይም እነዚህን በሚወክል ሌላ ሰው የተደረገ ምንም አይነት የገንዘብ ወይም የአይነት ክፍያ ሳይኖር የትምባሆ ምርትን ወይም ትምባሆን መጠቀም በሚመለከት እውነተኛ የፖለቲካ ማህበራዊ ወይም ሳይናሳዊ አስተያየት መ ለንግድ ስራ አስተዳደር ወይም የኮርፖሬሽን ሪፖርት ማድረግ የሚገባ እንደ የአካባቢ ጥበቃ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮችን እና መሰል በህግ የሚጠበቁ ጉዳዮችን ለሚመለከታቸው አካላት በትንባሆ ኢንዱስትሪ የሚሰራጭ መረጃ ወይም ሪፖርት ሠ የንግድ ውሳኔ ለመወሰን ለማስቻል ዓላማ ለትምባሆ ነጋዴ የሚሰጥ መረጃ ረ በትምባሆ ኢንዱስትሪው የሚዘጋጅና ተደራሽነቱ ለትምባሆ ኢንዱስትሪው ሰራተኞች ኮንትራክተሮች አቅራቢዎች እና ለሌሎች የትምባሆ ንግድ አጋሮቹ ብቻ የሆነ የዜና መጽሔት በትምባሆ አምራቹ አስመጪው ወይም ጅምላ ቫሻጩ የሚዘጋጅና የዜና መጽሔት እና በገዢዎቻቸው ንግድ አጋሮች በሰራተኞች ወይም ሸሪኮች መካከል በሚኖር የንግድ ግንኙነት ስለትምባሆ ምርቱ ስለባህሪው ስለመገኛ እና ዋጋው ስለምርቱ ምስል ምርቱ ስለተሰራበት አካል እና ስለአስተሻሸጉ ትክክለኛውን ወይም እውነተኛውን መረጃ ከመግለጽ በስተቀር ማንኛውንም አይነት መረጃ መግለፅ የተከለከለ ነው በንኡስ አንቀጽ በ ፊደል ሐ መሰረት ገለጻ ሲደረግ ወይም ሲተላለፍ ትምባሆ መጠቀም ጤናን እንደሚጎዳ ወይም ሌላ ተመሳሳይ መልእክት ከፕሮግራሙ በፊት መገለጽ አለበት ክፍል አራት ለትምባሆ ጭስ ከመጋለጥ ስለመጠበቅ እና ስለትምባሆ ምርት ሽያጭ ከትምባሆ ነጻ ስለማድረግ ባለስልጣኑ በአዋጁ አንቀጽ መሰረት ትምባሆ ማጨስ እና መጠቀም የተከለከለባቸውን ቦታዎችና አገልግሎቶች እንዳስፈላጊነቱ ከክልል ጤና ተቆጣጣሪ አካላት ጋር ተፈጻሚ መሆኑን ይከታተላል እንዳስፈላጊነቱ ለክልሎች ድጋፍ ያደርጋል በአዋጁ መሰረት ከትምባሆ ጭስ ነጻ መሆን የሚገባው ተቋም ግዴታውን ያልተወጣ እንደሆነ ባለስልጣኑ በራሱ የሚወስዳቸው እርምጃዎች ሲኖሩ መውሰዱ እንደተጠበቀ ሆኖ ድርጅቱን የሚቆጣጠረው አካል ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድበት አስፈላጊውን መረጃ ይሰጣል ትምባሆ ማጨስ ወይም መጠቀም በተከለከለባቸው ስፍራዎች ተቋማትና አገልግሎት መስጫ ለትምባሆ ማጨሻ ወይም መጠቀሚያ ቦታ ማዘጋጀት የተከለከለ ነው ከትምባሆ ጭስ ነጻ የማድረግ ኃላፊነት በአዋጁ አንቀጽ ከትምባሆ ነጻ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት ሰው ኃ ትምባሆ ማጨስ ወይም መጠቀም በተከለከለበት ቦታ ማንኛውም ሰው እንዳይጠቀም ለማድረግ የሚያስችል ማጨስ የተከለከለ መሆኑን የሚያሳየውን ምልክት መለጠፍ እና ሰዎች ይህን በመተላለፍ ሊጠቀሙ ሲሞክሩ ማስቆም አለበት በንኡስ አንቀጽ መሰረት ለማስቆም ሲሞክር ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው ቢኖር ኃላፊነት ያለበት ሰው ቦታ ላይ ማጨስ በህግ የተከለከለና ተቋሙም ሆነ ተጠቃሚው በህግ እንደሚጠየቅ በመግለጽ አገልግሎቱን ማቋረጥና ቦታውን ለቆ እንዲወጣ ማድረግ አለበት የማስቆም ኃላፊነት ያለበት ሰው በንኡስ መሰረት አገልግሎቱን አቋርጦ እና ቦታውን ለቆ እንዲሄድ ጠይቆ ተጠቃሚው ፈቃደኛ ያልሆነለት እንደሆነ ለማንኛውም ጤና ተቆጣጣሪ አካል ወይም ለፖሊስ ማሳወቅ አለበት የሲጋራ መተርኮሻ አስትሬይ ወይም ትምባሆ ለመጠቀም ወይም ተያያዥ አገልግሎት የሚሰጥ እንዳይኖር ማድረግ አለበት በተቋሙ ወይም በማጓጓዣው የትምባሆ ማስታወቂያ ወይም ፕሮሞሽን እንዳይከናወን መከላከልና እና ሊሆኑ የሚችሉ ማናቸውም ጉዳዮችን ማስወገድ አለበት በሚያስተዳድረው ተቋም ወይም ማጓጓዣ የተከለከለባቸው ቦታዎች ትምባሆ እንዳይሸጥ ማድረግ የትምባሆ ቁሩ ወይም ተረፈ ምርት እና ሽታ የጸዳ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት ስለትምባሆ ምርት ሽያጭ ኃ በአዋጁ አንቀጽ መሰረት ዕድሜው ዓመት ላልሞላው ሰው መሸጥ እና እንዲሸጥ ማድረግ ክልከላ ተግባራዊ የሚሆነው የገዢውን ወይም የሻጭን ዕድሜ በአካላዊ ሁኔታ ወይም በመታወቂያ በማረጋገጥ ይሆናል በንኡስ አንቀጽ መሰረት ዕድሜን በአካላዊ ሁኔታ መለየት የሚቻለው ማንኛውም መደበኛ ሰው የትምባሆ ሻጩን ወይም ገዢውን አካላዊ ሁኔታ በማየት በማያጠራጥር ሁኔታ የሞላው መሆኑን ለመገመት የሚቻል ሲሆን ነው በንኡስ አንቀጽ መሰረት በአካላዊ ሁኔታ በማያጠራጥር ሁኔታ ዕድሜውን ለመለየት አስቸጋሪ ከሆነ ዕድሜው መታወቂያውን በማየት መረጋገጥ አለበት የትምባሆ ምርት ማሸጊያ እና የምርቱ ቅርጽ የትምባሆ ምርት ተቀዳሚ ማሸጊያ ባለስልጣኑ በየወቅቱ የሚወጣውን የጽሑፍና የምስል የጤና ማስጠንቀቂያ የያዘ ሆኖ ኃ በአንድ የመለያ ስም ወይም ምልክት ብራንድ የተለያዩ ቀለሞች ወይም ስሞች ወይም ቅርጽ ያላቸውን የተለያዩ የትምባሆ ምርት ማምረት ማስመጣት ማከፋፍል ወይም መሸጥ የተከለከለ ነው ማንኛውም የሲጋራ ምርት ተቀዳሚ ማሸጊያ ቅርጽ አራት መዓዘን ሆኖ የጎን ስፋት ከ ሳንቲም እና ቁመት ከ ሳንቲም ያነሰ መሆን የለበትም የሲጋራ ቅርጽን ይህ መመሪያ በሚወጣበት ወቅት ካለው መደበኛ ቅርጽ ያነሰ ወይም ሳቢ ለማድረግ የተለየ የሆነ ለማምረት ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ለማከፋፈል ወይም ለመሸጥ አይቻልም በመደበኛ ሁኔታ ያለውን ቅርጽና መጠን ላይ ለመጨመር ቅድሚያ ለባለስልጣኑ ማሳወቅና ፈቃድ መገኘት አለበት ባለስልጣኑ የሲጋራ ቅርጽ ላይ ለውጥ ጥያቄን ተቀብሎ መፍቀድ የሚችለው ቅርጽ በማንኛውም ሁኔታ ሳቢ ወይም ትምባሆን የማያበረታታ መሆኑን በማረጋገጥ መሆን አለበት የትምባሆ ኢንዱስትሪ ጣልቃ ገብነትን ስለመከላከል ኃ በመንግስት እና በትምባሆ ኢንዱስትሪ መካከል የሚደረግ ማንኛውም ግንኙነት በጽሑፍ ሆኖ በህግ የተቀመጡ ገደቦችንና ክልከላዎችን ባከበረ ሁኔታ መሆን አለበት በተፈቀደ ሁኔታ ቢሆንም በመንግስት እና በትምባሆ ኢንዱስትሪ መካከል የሚደረግ ማንኛውም ግንኙነት ግልጽነት ባለው ሁኔታ ሆኖ በማንኛውም መንገድ ትምባሆን የሚያስተዋውቅ ወይም ተጠቃሚነት የሚያበረታታ መሆን የለበትም የብሔራዊ የትምባሆ ቁጥጥር ጥምረት አባላት ተቋማቸው ከኢንዱስትሪው ጋር ስለሚያደርጉት ግንኙነት የሚያውቁትን ወይም ማወቅ የሚገባቸውን መረጃ ለባለስልጣኑ የማቅረብ ኃላፊነት አለባቸው ባለስልጣኑ የህግ ጥበቃ ያላቸው የንግድ መረጃዎች እንደተጠበቁ ሆነው የትምባሆ ኢንዱስትሪ እንቅስቃሴን የተመለከቱ አስፈላጊ መረጃዎችን እንደአግባቡ ለህብረተሰቡ ይፋ ያደርጋል በህግ ከሚጠየቁ ክፍያዎች በስተቀር በትምባሆ ኢንዱስትሪ ለመንግስት የሚደረግ ማንኛውም የገንዘብ ወይም የዓይነት ስጦታ የተከለከለ ነው የትምባሆ ኢንዱስትሪ በማንኛውም መንገድ የማህበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የገንዘብ ወይም የዓይነት አስተዋጽዎ ማድረግ ለኩነት ስብሰባ ስልጠና ወይም መሰል ዝግጅት እንዲካሄድ የገንዘብ ወይም የዓይነት ድጋፍ ማድረግ ወይም ባለሙያ መመደብ የተከለከለ ነው የጥቅም ግጭትን ስለመከላከል የመንግስት ሰራተኛ ሆኖ በትምባሆ የንግድ ስራ ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚሳተፍ ማንኛውም ሰው በማንኛውም ዓይነት የትምባሆ ቁጥጥር ተግባር ውስጥ ለመሳተፍ አይችልም ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የትምባሆ ኢንዱስትሪ የደገፈው የጥናት ስራ ውስጥ ጥናቱን ለማከናወን ወይም ለመገምገም ለመሳተፍ አይችልም የመንግስት ሠራተኛ በዚህ አንቀጽ የተመለከቱ ድንጋጌዎች ጥሰት የፈጸመ እንደሆነ የሚመለከተው ተቋም እና የፍትህ ተቋም አግባብነት ያለውን እርምጃ እንዲወስድ ባለስልጣኑ ወይም የክልል ጤና ተቆጣጣሪ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋሉ ሪፖርት ማቅረብ ማንኛውም የትምባሆ ኢንዱስትሪ በየዓመቱ ለባለስልጣኑ የስራ እንቅስቃሴውን የተመለከተ ሪፖርት ማቅረብ አለበት በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት የሚቀርብ ሪፖርት ሀ በዓመቱ የተመረተ ምርት በጥቅል ለ በዓመቱ የተመረት ምርት ብዛት በብራንድና በዓይነት ለይቶ ሐ ከውጪ ወደ አገር ውስጥ የገባ ምርት ጠቅላላ መጠኑን በብራንድና በዓይነት ለይቶ መ ወደ ው አገር የተሳከ ጠቅላላ መጠን በብራንድና በዓይነት ለይቶ ሠ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ የገባና ጥቅም ላይ የዋለ የጥሬ ዕቃና ግብዓት ዓይነትና መጠን ረ በአገር ውስጥ የተገኘና ለምርት የዋለ ግብዓትና ጥሬ ዕቃ ዓይነትና መጠን ሰ ከአምራች ወይም አስመጪ ድርጅት ትምባሆን በጅምላ የሚረከቡ አከፋፋዮች ብዛትና በዓመቱ እያንዳንዱ አከፋፋይ ከድርጅቱ የወሰደው መጠን ሸ ድርጅቱ ሪፖርቱን በሚያቀርብበት ወቅት ያለው የክምችት መጠን እና ቀ ድርጅቱ ምርቱን የሚሸጥበት ዋጋ በምርት ዓይነት እና ብራንድ ንጽጽር ያካተተ መሆን አለበት በዚህ አንቀጽ መሰረት የሚደረግ ሪፖርት በበጀት ዓመቱ መዝጊያ ከሰኔ ባለው ጊዜ ውስጥ ለባለስልጣኑ መቅረብ አለበት ክፍል አምስት የአስተዳደራዊ እርምጃ ስርዓት ጠቅላላ በዚህ መመሪያ የተካተቱ ክልከላዎች በአዋጁ አንቀጽ ሆ የሚታዩና ኃ ዴሠ ፍመ አስተዳደራዊ እርምጃ አወሳሰዱም በአዋጁ አንቀጽ በዚህ መመሪያ እና አግባብነት ባላቸው ሌሎች ህጎች መሰረት የሚፈጸም ይሆናል በአዋጁ በደንቡና በዚህ መመሪያ የተቀመጡ ክልከላዎችን በተላለፈ ሰው ላይ ባለስልጣኑ እንደጥፋቱ ዓይነትና ክብደት መሰረት በፌዴራል ደረጃ ቁጥጥር በሚደረግባቸው ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስዳል እንዳግባብነቱ ክልሎች እንዲወስዱ ድጋፍ ያደርጋል የዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ እንደተጠበቀ ሆኖ ክልሎች በአዋጁ የተቀመጡ መሰረታዊ መስፈርቶችና መመዘኛዎችን በማይጥስ መልኩ በክልል ስልጣን ስር ባሉ ጉዳዮች ላይ የየራሳቸውን የትምባሆ ቁጥጥር መመሪያ ሊያወጡና ሊያስፈጽሙ ይችላሉ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰደው የጥፋቱን ክብደት የአፈጻጸሙን ሁኔታ እና ያደረሰውን ወይም ሊያደርስ ይችል የነበረውን የጉዳት መጠን በማገናዘብ ይሆናል የአስተዳደራዊ እርምጃ ሥርዓት በአዋጁ በደንቡ ወይም በዚህ መመሪያ የተመለከተ ክልከላ ወይም ግዴታ ሆኖ መ ዴሠ ድርጊቱ በማንኛውም ህግ ወንጀል ሆኖ ያልተደነገገ እንደሆነ ክልከላውን በተላለፈው ሰው ላይ የሚወሰድው አስተዳደራዊ እርምጃ ሀ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ለ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና በደንብ የሚወሰን መቀም ሕ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን ልዩ ፈቃዱን እስከ አንድ ዓመት ለሟሆን ጊዜ ማገድ መ ለአራተኛ ጊዜ ሲሆን ልዩ ፈቃዱን መሰረዝ ይሆናል በአዋጁ በደንቡ ወይም በዚህ መመሪያ የተመለከተ ክልከላ ወይም ግዴታ ሆኖ ድርጊቱ በማንኛውም ህግ በወንጀል የሚያስቀጣ እና የወንጀል ቅጣቱ ቀላል እስራት እንደሆነ ልዩ ፈቃዱ እስከ አንድ ዓመት ለሚደርስ ጊዜ ይታገዳል በንኡስ አንቀጽ መሰረት ልዩ ፈቃዱ ታግዶበት የነበረ ሰው ዳግመኛ በንኡስ አንቀጽ የተመለከተውን ድርጊት የፈጸመ እንደሆነ ልዩ ፈቃዱ እስከ ሁለት ዓመት ለሚደርስ ጊዜ የሚታገድ እና በደንቡ መሰረት መቀጮ የሚጣልበት ይሆናል በአዋጁ በደንቡ ወይም በዚህ መመሪያ የተመለከተ ክልከላ ሆኖ ድርጊቱ በማንኛውም ህግ በወንጀል የሚያስቀጣ እና የወንጀል ቅጣቱ ጽኑ እስራት እንደሆነ ወይም በንኡስ አንቀጽ ወይም መሰረት ቀደም ብሎ በልዩ ፈቃዱ ላይ የእገዳ እርምጃ ተወስዶበት እንደሆነ ልዩ ፈቃዱ ይሰረዛል በዚህ አንቀጽ ከንኡስ አንቀጽ ባሉት ድንጋጌዎች የሚወሰዱት እርምጃዎች እንደተጠበቁ ሆኖ በትምባሆ ምርቱ ላይ እንዳግባብነቱ የመያዝ የመውረስና የማስወገድ እርምጃዎች ሊወሰድ ይችላል የንኡስ አንቀጽ አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ ሀ እንዲሸጥ ያልተፈቀደ የትምባሆ ምርት ለ የፀና የጤና ማስጠንቀቂያ የሌለው የትምባሆ ምርት ሕ የተከለከለ ይዘት ያለው የትምባሆ ምርት መ ልዩ ፈቃድ በሌለው ወይም ያልታደሰ ልዩ ፈቃድ ባለው ሰው የተመረተ የተከማቸ የተጓጓዘ ለሽያጭ የቀረበ ወይም በማንኛውም ሁኔታ በገበያ ውስጥ የተገኘ የትምባሆ ምርት ሰ ልዩ ፈቃዱ ታግዶ ባለበት ወቅት ከመታገዱ በፊት በአጁ ይገኝ የነበረ ህግን የተከተለ ምርት ካልሆነ በስተቀር በታገደበት ሰው እጅ የተገኘ የትምባሆ ምርት ረ በህጉወጥ መንገድ የተመረተ ወይም ወደ አገር ውስጥ የገባ የትምባሆ ምርት የተገኘ እንደሆነ የሚወረስና የሚወገድ ይሆናል የትምባሆ ምርትን ስለመያዝ ማንኛውም የጤና ተቆጣጣሪ የትምባሆ ምርቱ በህገወጥ መንገድ የተመረተ ወደ አገር ውስጥ የገባ ለገበያ የቀረበ የተከማቸ የተጓጓዘ ስለመሆኑ ወይም በህግ የሚጠየቁ የጤና ማስጠንቀቂያ ወይም ሌሎች መስፈርቶቹን ያላሟላ የትምባሆ ምርት ወይም ልዩ ፈቃድ ባልተሰጠው ወይም ያልታደሰ ልዩ ፈቃድ ባለው ሰው እጅ የተገኘ የትምባሆ ምርት ወይም ልዩ ፈቃዱ ታግዶ ባለበት ወቅት በታገደበት ሰው እጅ የተገኘ የትምባሆ ምርት መያዝ አለበት በንኡስ አንቀጽ መሰረት የተያዘ ምርት እስኪወረስ ድረስ ተጠብቆ ይቆያል ስለመውረስ ባለስልጣኑ በዚህ መመሪያ አንቀጽ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ የተወሰደበት ወይም በአንቀጽ መሰረት የተያዘ ወይም ባለቤት የሌለው ህገወጥ የትምባሆ ምርት ሲኖር እንዳግባብነቱ ምርቱ እንዲወረስ ይወስናል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት ባለስልጣኑ የመውረስ ውሳኔ ከማሳለፉ በፊት ምርቱ ባለቤት ያለው ከሆነ ሀሳቡንና ማስረጃ ካለው እንዲያቀርብ እድል መስጠት አለበት ስለማስወገድ በዚህ መመሪያ አንቀጽ መሰረት የተወረሰ የትምባሆ ምርት መወገድ አለበት ባለስልጣኑ የተወረሰው የትምባሆ ምርት አከባቢን በማይጎዳበት እና ተመልሶ ጥቅም ላይ ሊውል በማይችልበት ሁኔታ መወገዱን ማረጋገጥ አለበት በወንጀል ተጠያቂ ስለማስድረግ በዚህ መመሪያ የተመለከቱ ክልከላዎች አግባብ ባለው ህግ የወንጀል ድርጊት ሆነው የተደነገጉ እንደሆነ ባለስልጣኑ አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰዱ በተጨማሪ የድርጊቱ ፈጻሚ በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆን ለሚመለከተው አካል ተገቢውን መረጃ ይሰጣል ክፍል ስድስት የትምባሆ ቁጥጥር ብሄራዊ አስተባባሪ አካል መቋቋም በአዋጁ አንቀጽ መሰረት የኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ብሄራዊ አስተባባሪ አካል ከዚህ በኋላ ብሄራዊ ጥምረት እየተባለ የሚጠራ አካል በዚህ መመሪያ ተቋቁሟል የብሄራዊ ጥምረቱ ተጠሪነት ለባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ይሆናል ዓላማ የብሄራዊ ጥምረቱ ዓላማ በትምባሆ ቁጥጥር ላይ የወጣውን የአለም ጤና ድርጅት የትምባሆ ቁጥጥር ማእቀፍ ኮንቬንሽን የኮንቬንሽኑን አተገባበር መመሪያ እና አገሪቱ ያወጣችውን የትምባሆ ቁጥጥር የህግማ ዕቀፍ በፌደራል መንግስት ደረጃ ያለውን አፈጻጸም ማስተባበር በተለያዩ የፌደራል መንግስት ተቋማት ያለውን የትምባሆ ቁጥጥርን ውጤታማነት መከታተል የትምባሆ ቁጥጥር ላይ የሚመለከታቸው የፌደራል መንግስት አካላት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር የሚሰራ ተግባራቶችን እና ሊኖር የሚገባ ትስስርን ማጠናከር ነው የብሔራዊ ጥምረቱ አባላት የብሔራዊ ጥምረቱ አባላት በአዋጁ ማስፈጸሚያ ደንብ የሚወሰኑት ናቸው ባለስልጣኑ የጥምረቱ አባላት ተገቢውን ተሳትፎ እንዲያደርጉ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ አለበት ሥልጣንና ተግባር የብሄራዊ ጥምረቱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል የትምባሆ ቁጥጥር የህግ ማዕቀፎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ይከታተላል ይገመግማል ለገጠሙ ችግሮች የመፍትሔ አቅጣጫ ያስቀምጣል የትምባሆ ቁጥጥር ተግባራት በጥምረቱ አባል ተቋማት መፈጸሙን ይከታተላል የልምድ ልውውጦች ያደርጋል የትምባሆ ቁጥጥር የህግ ማዕቀፎች ስለመፈጸቸው ለማረጋገጥ እንዳስፈላጊነቱ የመስክ ቅኝት ያደርጋል ለስራው አፈጻጸም የሚያገዙ የተለያዩ ንኡስ ኮሚቴዎችን ያቋቁሟል ያደራጃል ይቆጣጠራል ህብረተሰቡ ስለትምባሆ ጎጂነት እና ክልከላዎች ጥልቅ ግንዛቤ እንዲኖረውና በመከላከሉ ላይ ተሳትፎ እንዲያደርግ የህብረተሰብ ንቅናቄ እንዲደረግ ያደርጋል ለክልል የትምባሆ ቁጥጥር አስተባባሪ አካል ድጋፍ ያድርጋል በዋና ዳይሬክተሩ የሚሰጡ ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል የብሄራዊ ጥምረቱ አደረጃጀት የብሄራዊ ጥምረቱ በባለስልጣኑ የሚወከል አንድ ሰብሳቢ ጸሐፊ እና አባላት እና እንዳስፈላጊነቱ ንዑስኮሚቴዎችይኖሩታል የሰብሳቢ ጸሐፊ እና አባላት ሀላፊነት የብሔራዊ ጥምረቱ ሰብሳቢ የጥምረቱን ሥራ በበላይነት ይመራል ስብሰባዎችን ይመራል ዕቅድ ያዘጋጃል በጥምረቱ ይሁንታ አግኝቶ በባለስልጣኑ ሲጸድቅ ተግባራዊ መደረጉን ይከታተላል ቧራዑ የብሔራዊ ጥምረቱ ጸሐፊ የስብሰባዎችን አጀንዳ ያዘጋጃል ውይይቶችን ይዘግባል የሚወሰኑ አቅጣጫዎች ለአባላት ተደራሽ እንዲሆኑ ያደርጋል የብሔራዊ ጥምረቱ አባላት ጥምረቱ ዓላማውን ሊያሳካ የሚችልበትን ጥረት ሁሉ ያደረጋሉ ተቋማቱን የሚወክሉ ባለሙያዎች የትምባሆ ቁጥጥር ተግባራትን በተቋማቸው ያስተባብራሉ በብሔራዊ ጥምረቱ የሚቋቋሙ ንኡሳን ኮሚቴዎች የተቋቋሙበት ጉዳይን ያከናውናሉ ለኮሚቴው ሪፖርት ያደርጋሉ የብሔራዊ ጥምረቱ የውስጥ አሰራሩን በተመለከተ ለራሱና በእርሱ ለተቋቋሙ ንኡሳን ኮሚቴዎች ሊያወጣ ይችላል የብሄራዊ ጥምረቱ ስብሰባ የብሄራዊ ጥምረቱ በየሶስት ወሩ መደበኛ ስብሰባ የሚኖረው ይሆናል ነገርግን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሰብሳቢው በማናቸውም ጊዜ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል ከብሄራዊ ጥምረቱ አባላት ከግማሽ በላይ ከተገኙ ምልዓተ ጉባኤ ይሆናል የብሄራዊ ጥምረቱ ውሳኔ የሚተላለፈው በአብለጫ ድምጽ ሲደገፍ ይሆናል ሆኖም ድምጹ እኩል ለእኩል የተከፈለ እንደሆነ ሰብሳቢው ወሳኝ ድምጽ ይኖረዋል የዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ የብሄራዊ ጥምረቱ የራሱን የስብሰባ ሥነሥርዓት ውስጠ ደንብ ያወጣል ሁኔታው የሚጠይቅ ካልሆነ በስተቀር የብሄራዊ ጥምረቱ ስብሰባ በባለስልጣኑ ዋና መስሪያ ቤት የሚከናወን ይሆናል የበጀት ምንጭ የብሄራዊ ጥምረቱ አስፈለጊ ወጪዎች በባለስልጣኑ እና አጋር ድርጅቶች የሚሸፈን ይሆናል ክፍል ሰባት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ስለንግድ ሰንሰለት የትምባሆ ምርት አምራች ወይም አስመጪ የትምባሆ ምርትን ለመሸጥ የሚችሉት ከባለስልጣኑ የተሰጠ የጸና ልዩ ፈቃድ ላላቸው ሰዎች ብቻ ይሆናል የአገልግሎት ክፍያ በዚህ መመሪያ መሰረት ከባለስልጣኑ አገልግሎት የሚሰጠው ሰው አገልግሎት ማግኘት የሚችለው በአገልግሎት ክፍያ ደንብ መሰረት የአገልግሎቱ ክፍያው በመክፈል ማረጋገጫ ሲያቀርብ ይሆናል ተፈጻሚነት የማይኖራቸው ህጐች የትምባሆ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር በዚህ መመሪያ ተሸሯል መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ ይህ መመሪያ ከቀን ዓም ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆናል ሄራን ገርባ ዋና ዳይሬክተር የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን የትምባሆ ምርት ይዘትን ይፋ ማድረጊያ ቅጽ የድርጅቱ ስም የድርጅቱ የልዩ ፈቃድ ቁጥር ፈቃዱ የተሰጠበት ቀን የተሰማራበት የትምባሆ ንግድ ስራ ዓይነት ማምረት ማስመጣት ማከፋፈል የምርት ዓይነት እና ይዘት ዝርዝር በሚከተለው ሰንጠረዥ ውስጥ ይገለጽ የምርት አስተያየት ዓይነት የብራንድ ዓይነት በውስጡ በውስጡ የምርቱ ያለው የያዛቸው ምንጭ የንጠረ ነገር ጎጂ ንጥረ በአገር ዓይነቶችና ነገሮች ውስጥ መጠን የሚመረት ከውጪ የሚመጣ ሲጋራ ሲጋር ሲጋሪሎስ ፒፓ በትቦ የሚጨስ ትምባሆ ሱረት ሌላ የትምባሆ ምርት መረጃውን ያዘጋጀው ሰው ወይም ክፍል ሥም።