Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ወደዚህች አገር የሳከንም ምሥራቅ ሜኖናይት ሚስዮን ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ አገኘነው በወቅቱ ከእግራችን በታች ምግብ ፍለጋ ወዲህ ወዲያ የሚርመሰመሱትን ጉንዳኖች በማመላከት ይህ ግለሰብ እንዲህ አለኝ እነዚህ ጐንዳኖች ጓደኛ ለመሆን ከፈለግህ ብቸኛው መንገድ ጐንዳን መሆን ነው ያለብሆ ንግግሩን በመቀጠል እግዚአብሔር በመሲሑ በኩል ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ መሲሕ የሚለው ስም ምን ማለት ነው። በመቶ ሚሊዮኖች የሚገመቱ የዓለም ሕዝቦች የወንጌልን እውነት ባልሰሙበት ሁኔታ እንደ ክርስቲያን ክርስቶስን መከተል ማለት ትርጐሙ ምንድን ነው። ከዚያ በኋላ የነበረን ውይይት በጣም ጥሩ ነበር ለአራት ሰዓት ያህል ውይይት ካደረግን በኋላ ከተማሪዎቹ መካከል ብዙዎቹ ውይይቱ ሊላም ጊዜ እንዲቀጥል ተስማሙ ከተማሪዎቹ ተለይተን ልንሄድ ስንዘጋጅ በውይይቱ ውስጥ ከነበሩት መካከል አንዱ እንዲህ አለ ዛሬ በዚህ ከሰዓት በኋላ በመካከላችን እንግዳ አብሮን አለ ተለይቶን መሄድ የሚወድ አይደለም እንግዳው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው እርሱም በመካከላችን መገኘት ብቻ ሳይሆን የውይይታችን ማዕከላዊ ስፍራ ይዞ ነበር። እንዴት ዐይነት አሳዛኝ ጥፋት ነው።
ተሳታፊ በነበርሁበት በመካከለኛው ምሥራቅ ኮንፈረንስ ላይ ታዋቂው የእስልምና የነገረ መለኮት ሊቅ የሆነው ጳጳስ ኬኔት ክራግ ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ሲገናኙ የሚለያዩባቸው ርእሰ ጐዳዮች እንዳሉ ሁሉ አንድ የሚያደርጋቸውም ርአሰ ጐዳዮች አሉ ብለው ነበር አንዳንድ ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች በእስልምናና በወንጌል መካከል ያለውን አንድነት በማጐላት ልዩነቶችን ችላ ብለዋቸዋልር ሌሎች ደግሞ በልዩነቶቹ ላይ ትኩረት በመስጠት የሌሳኛው እምነት ፈጽሞ ሐሰት ነው ባዮች ናቸው ይህ መጽሐፍ ለሚያስማሙን ነጥቦች አክብሮት በመስጠት ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች የአብርሃምን አምላክ የማምለካቸውን ጐዳይ ትኩረት ይሰጥበታል እኔም የእስልምናና የወንጌል ጥሪ በዕለታዊ ኑሮአችን ምን እንደሚመስል የሙስሊሙን ማኅበረሰብ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን የሚስዮናዊነት ሥራ ባሕርያትና አካሄድ የሚዳስስ ነው በድሩ ቀትራጋ እና እኔ በጻፍነው መጽሐፍ ማጠቃለያ ላይ የሁለታችንንም ምልከታ የሚገልጽ አስተያየት ሰጥተናል በአንድነት በሚገኘው ደስታና በልዩነታችን መኻል የሚፈጠረውን የልዩነት ስሜት ተጋርተናልሱ ይህንም ጐዳይ እንዲህ ገልጸነዋል አንድ የሚያደርጉንን መሠረተ እምነቶች በጽናት ብናወድሳቸውም ዐቢይ በሆኑ አስተምህሮዎችም ላይ ልዩነት እንዳለን ከሙሉ ልብ የምንቀበለው ጐዳይ ነው በእስልምና የአላህ ምሕረት በከፍተኛ ደረጃ የተገለጸው ፍጹም በሆነው ሕግ በኩል ነው በክርስትና እምነት ደግሞ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጸው በመሲሑ በክርስቶስ መከራ በመስቀል ላይ ሞቱ በትንሣኤውና በሕይወቱ በተገለጠው የማዳን ፍቅሩ ነውፁ እነዚህ ቀላል የሚባሉ ልዩነቶች አይደሉም ምክንያቱም ስለሰው ሕይወት መሠረታዊ ጥያቄዎች በጥልቅ የሚነኩ ጐዳዮች ናቸውና ክርስቲያንም ሆነ ሙስሊም የሆነ ማንኛውም ሰው እነዚህ ልዩነቶች አላስፈላጊ ወይም ዐቢይ ጐዳዮች አይደሉም ብሎ መናገርም ሆነ ማመን አይችልም ይህ ውይይት ጨዋነት የተላበሰ ቀጥተኛ እንዲሁም በመከባበር ላይ የተመሠረተ ነበር መጽሐፉም በክርስቲያኖችም ሆነ በሙስሊሞች ዘንድ ጥሩ ተቀባይነት ያገኘ መጽሐፍ ነው ነገር ግን ከበድሩ ጋር ውይይቱን ከጻፍን በኋላ የዚህ ተከታይ ክፍል በእስልምናና በክርስትና እምነት መካከል ያለውን የግንኙነት ባሕርይ ጠለቅ ባለ መልኩ በተለይም ደግሞ ከራሴ ተሞክሮ በመነሣት ለመጻፍ ፈልጌ ነበር በማንኛውም ጊዜ ሙስሊሞችን በመስጊድ አግኝቼ ስለ ወንጌል ያላቸውን አተያይ ስሰማ ስለ ወንጌል ያለኝን መረዳት የበለጠ ግልጽ ያደርግልኛል ምክንያቱም መረዳታቸው ከቃለ እግዚአብሔር ጋር የሚጋጭ እንዲሁም እርስ በርሱ የተምታታ ነው ብዙ ጊዜ እስልምና የክርስትና አቻ ተፎካካሪ ሃይማኖት እንደ ሆነ አድርጎ ራሱን ያቀርባል ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ዐይነቱ ተግዳሮት በሚገጥማት ጊዜ በወዲያ ወገን ያለውን ገለጸ መስማት ብቻ ሳይሆን ስለ ወንጌል ትምህርት የጠራ መረዳት ታገኛለች በዚህ መጽሐፍ የውይይት መንፈስ ባዘለ መልኩ በእስላማዊ የአስተሳሰብ ዐውድ ውስጥ መሲሑ ምን እንደሚመስል ለማስረዳት ጥረት አድርጌያለሁ ክርስቶስን በሙስሊም ዐውድ መመልከትና ትንተና መስጠት ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ሁሌ የሚዘነጉትን የወንጌል ክፍል በጠለለ መልኩ እንዲረዱት ያደርጋቸዋልስለዚህ የዚህ መጽሐፍ ቀዳማይ ተደራስያን ክርስቲያኖች ናቸው ሙስሊሞችን ግራ የሚያጋባቸው ክርስቲያኖች መሲሑን እንደሚያምኑ ነገር ግን የመጽሐፍ ቅዱሱን ኢየሱስ በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው የመካዳቸው ጐዳይ ነው የዕለት ተዕለት ሕይወታቸው መሲሑን ያለመምሰሉ ጐዳይ ነው ፍጥረተ ዓለም ሁሉ ለአላህ ፈቃድ መዝት አለበት የሚለውን የሙስሊሞች አስተሳሰብ ክርስቲያኖች ሁሉ ትልቅ ስፍራ እንደሚሰጡት እሙን ነው ወንጌልን በተመለከተ ከመስሊሞች በኩል የሚሰነዘረው ሒስ ክርስቲያኖች ጠንቃቃ የነገረ መለኮት ሰዎች እንዲሆኑ የሚጠይቅ ነው። ሱራ ቤተ ከርስቲያደገ ቤተ ክርስቲያን ማለት ጉባኤ ማለት ነው በአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል በግሪክ ቋንቋ ኤክሌሲያ ተብሎ ይጠራል ይህም ለአንድ ዐይነት ዐላማ በአንድ ቦታ ተሰብስበው የተበተኑ የሰዎችን ኅብረት ያመለክታል። ምስክርነቱም የቤተ ክርስቲያን መሠረት ነው በዓለም ዙሪያ ያሉ ቤተ ክርስቲያናት በሙሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታና አዳኝ እንደ ሆነ ይመሰክራሉ ሐዋርያው ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያንን ቅዱስ ሕዝብ ጴጥሮስ ሲል ገልጾአታል ዳሩ ግን በአዲስ ኪዳን ልክ እንደ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከፖለቲካ ወይም ከግዛታዊ ሥልጣን ጋር የተያያዘ አይደለም ቤተ ክርስቲያን አንደ ቅዱስ ሕዝብ ከሌሎች ሕዝቦች መካከል ለድነት የተጠሩ ሰዎች ኅብረት ናት ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል ክርስቶስን ጌታና አዳኝ አድርገው የተቀበሉ ሰዎችን ሁሉ የሚጠቀልል ስም ሲሆን ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚቀላቀሉትም በኀጢአታቸው ንስሓ በመግባትና በመጠመቅ ነውሱ ትክክለኛ አማኝ መሆናቸውም ሆነ ከክርስቶስ አካል ጋር መቀላቀላቸው የሚታወቀውም በሕይወታቸው ከሚታዩት መንፈሳዊ ፍሬዎች ነው የግዛትና የፖለቲካ ዝኒ ከማሁ የእንግሊዝኛው ቅጅ እንዲህ ይላል ገከህ ር ከ ጸኮ። በጊዜው የቤተ ክርስቲያን የታሪክ ጸሓፊ የነበረው አውሳብዮስ ጳጳሳት ቂቄስጠንጢኖስን ያጀቡት እግዚአብሔር ድል እንዲሰጠው በጸሎት ለመርዳት ነው ሲል ጽፎአል ከዚህ የተነሣ የፐርዥያውያን ቀፍጣ በክርስቲያኖች ላይ ያለ ልክ ነደደ ከሃያ ዓመታት በላይ በፐርዥያ ግዛት ያሉት ክርስቲያኖች በረቀቀ ዘዴ ታደኑ ተገረፉ ተገደሉ በዚህ ታላቅ ስደት የፐርዥያ ቤተ ክርስቲያን ወደ መጥፋት ደረሰች ከዚያ በኋላም ስደቱ ካስከተለው ጥፋት ማገገም አልተቻለም በምሥሬራቅ አስሪ የነበሩት ቤተ ክርስቲያናት ይህ ዐይነቱ የነገሮች አካሄድ በምሥራቅ እስያ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ወዲያውኑ ከምዕራብ ቤተ ክርስቲያን ራስዋን ማራቅ እንዳለባት ግልጽ አደረገላት ቄስጠንጢኖስና እርሱን ተከትለው የተነ መሪዎች ኋላም ቅዱስ የሮም ግዛት የምሥራቋ ቤተ ክርስቲያን የምዕራቧ ቤተ ክርስቲያን አካል ስለመሆኗ አቋሟን እንድትገልጽ ግፊት ተደርጐጉባታል ምንም እንኳ ከምዕራባውያን ክርስቲያኖች ጋር አንድነቷን ብትገልጽም ንስጥሮሳውያን ክርስቲያኖች እንደ መናፍቃን ተቁጥረው ነበር ዳሩ ግን አረንድ ቲኦዶር ቫን ሊወን የተባለው የደች የሃይማኖት ታሪክ ጸሓፊ በቤተ ክርቲያን መካከል የነበረው ክፍፍል ለእስልምና መስፋፋት በር እንደ ከፈተ ይናገራል እንዲህ ሲልም ጸፎአል እስላማዊ ኀይሎችከየትኛውም የክርስቲያን የመናፍቅ አስተምህሮ ቡድኖች በጣም በሳቀ መልኩ ፀረቢዛንታይን አስተምህሮ አሠራጭተዋል ሆኖም በምዕራቧ ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት ላይ ከነበረው የተቃውሞ መግለጫ የተነሣ ሁሉም ክርስቲያኖች ወደ እስልምና አልተለወጡም ሀ ሀያ ርዘፀዘዘዘይ ባዐ ሀ እፅኪ ልገፎበ ከፀ ሃዉ ፀፀህዛሃቢ ርቪዘወህ ሀ ሀ ያከትሄ እዘረፀቫ ሀ« ፀፀ ነርቪ ከ ጽርርበ ህዩርከ ከሃ ኗከ ኘ ከል ር ዝኒ ከማሁ ጋቶ አንዳንድ ጊዜም የምሥራቅ እስያ ቤተ ክርቲያናት ወንጌልን በማሠራጨት የራሳቸውን እምነት ተገቢነት ይገልጡ ነበር ለአንድ ሺህ ዓመታት ያህል ሚስዮናውያንን ወደ ማዕከላዊው የእስያ ክፍል በመላክ የምሥራቹን ቃል አሠራጭተዋል እነዚህ ጥቂት ቤተ ክርስቲያናት የመንግሥት አጀንዳ ያልያዘ የወንጌል ተልእኮ ፈጽመዋል ከቁስጠንጢኖስ በኋላ ለመስፋፋት ሲባል ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት አብረው ከሚያዘጋጁት ሚስዮናዊ አገልግሎት ጋር ሲነጻጸር ከፍ ያለ ልዩነት ነበረው የምሥራቅ ቤተ ክርስቲያናት ሁሌም በቀጥር አነስተኛ አብዛኛውን ጊዜ የሚሰደዱና አንዳንዴም እስከ መጥፋት የሚደርሱ ናቸው ይሁንና ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት ለአንድ ሺህ ዓመታት ያልተቋረጠ የወንጌል ሥርጭት እስከ ቻይና ድረስ በሚዘልቅ አገልግሎት ይሰጡ ነበር። ስለዚህም በመድብለ አማልክት አምሳላክያን የአምልኮና የሰላም ቀጣና ተብሎ ይጠራ የነበረው ስፍራ ማለትም ካዕባ የአንድ አምላክ ማለትም የአላህ የሰላም ስፍራ ተብሎ ተጠራ ይህም ማለት የመስጊዱ ሰላምና ዐረባዊ የሆነው የባህላዊው ሃይማኖት ሰላም ተቀላቀሉ ማለት ነው ደከርስቲያናች መገኘት በእስልምና አስተምህሮም ሆነ በቁርአን ውስጥ ላሉ መሠረተ እምነቶች በምንጭነት ከሚጠቀሱት ውስጥ ክርስትና ሁለተኛውን ስፍራ ይይዛል እንደማንኛውም የዐረብ ሕዝብ መሐመድ ስለክርስቲያኑ ማኅበረሰብ በዐረብያ ዙሪያ ስላሉ ክርስቲያን ነገሥታትና ስለ ክርስትና እምነት ያውቁ ነበር የክርስቲያኖችና የአይሁዶች የአስተሳሰብ የአኗኗርና የእምነት ዘይቤዎች በዐረቦች የዕለት ተዕለት ኑሮ ውስጥ ይንጸባረቁ ነበር መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ እንኳ ባይሆንም ስለክርስትና እምነት በቃል ብቻ ሰምተው የክርስትናን እምነት ከተቀበሉ ክርስቲያኖች ጋር መሐመድ የቅርብ ግንኙነት ነበራቸው በሙስሊሞችና በክርስቲያኖች መካከል ይህ ዐይነቱ ግንኙነት እንደ ነበረ ቁርአን የተወሰኑ ፍንጮችን ይሰጣል ግንኙነቱ አንዳንዴ በመከባበር ላይ ሀ ሮጳ ልበ ልነጎ ነ ክፎበእ ለ ፀ ገቹ ህ ርዑዜ ኛጺ ር ጀርበከፎከክ የዬ ለቨህዘወዘቋ ጠ ዘህ ርክሃክስዘ ርሄፎዐ ዐ ደይቐዐዘፀ እልግሄበዐቢ ከፕ ርዐከፔ የተመሠረተ ሲሆን በሌላ ጊዜ ደግሞ አንደኛው ወገን ሌላኛውን ወገን በመንቀፍ ላይ ያተኩረ ነበር ሙስሊሞች የኢየሱስ ክርስቶስን ማንነት በተመለከተ በክርስቲያኖች ዘንድ አለመግባባቶችና ውዝግቦች እንደ ነበሩ ያውቁ ነበር ከላይ ለማየት እንደ ሞከርነው የእስልምና አንደኛው ተልእኮና ግብ ይህንን ግርታ በማጥራት ለክርስቲያኖች ስለክርስቶስ ማንነት ትክክለኛ የሆነውን ትምህርት መስጠት እንደ ሆነ ሙስሊሞች ጠንካራ አቋም ነበራቸው በዚህ ዘመን ያለችውን የአፍሪካ ቤተ ክርስቲያን ስንመለከት በሺህ የሚቄጠሩ ቤተ እምነቶችን እናገኛለን ቤተ ክርስቲያናቱ ከሚሰጡአቸው ትምህርቶች ውስጥ የተወሰኑት ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ወጣ ያሉ ሲሆን በአንጻሩ ደግሞ ሁሉም በሚስዮናውያን የተተከሉ ቤተ ክርስቲያናትን የሚያሒሱየሚተቹ ናቸው ምናልባት የመጀመሪያው የሙስሊም ማኅበረሰብ በተወሰነ መልኩም ቢሆን የዋናው ክርስቲያናዊ እንቅስቃሴ ሒስ አቅራቢ አንደ ሆነ ማሰቡ በጣም የራቀ ይሆንን። በእስልምና ሃይማኖትና በአይሁድ እምነት መካከል ጐልሕ መመሳሰሎች አሉ ከመመሳሰሎቹ ውስጥ ጥቂቶቹ እግዚአብሔር የፍጥረተ ዓለሙ ፈጣሪ ነው እግዚአብሔር ቅዱሳት መጻሕፍትን ለነቢያቱ ሰጥቶአል ነቢያትን ልኮአል ለእግዚአብሔርለአላህ ሕግ መገዛት ይገባል የሚሉት ትምህርቶች ይገኙበታል ይሁን እንጂ መሐመድ በተለይ በመዲና ከነበሩት አይሁድ የሚበዙቱ እንደ እግዚአብሔር ነቢይ አድርገው ስላልተቀበሏቸው ማዘናቸው አልቀረም በመዲና በሙስሊሞችና በአይሁዶች መካከል የነበረው ግንኙነት አንዱ ሌላውን በመንቀፍ ላይ ያተኩረ ሲሆን ኋላም ግጭትን አስከትሎአል የግጭቱ መንሥኤም አይሁዶች የሙስሊሞችን እንቅስቃሴ ለማዳከም እያሜሩ ናቸው የሚል ጥርጣሬ በሙስሊሞች ዘንድ ስለነበር ነው በተለይ በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጅማሬ ወቅት አይሁዶች የጉላ ሚና ቢኖራቸውም ግንኙነታቸው ባመዛኙ ፍጥጫ የነገሠበት ነበር በቁርአን ውስጥ የሚገኙት ማኅበረሰባዊ ሕጎችና ማኅበራዊ ግንኙነቶችን በተመለከተ የይሁዲ እምነት ያለው አስተምህሮ የመመሳሰሉ ጐዳይ የሚያስደንቅ ነው በፉለር የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት የእስልምና ሃይማኖት ምሁር የሆነው ዱድሌይ ውድቤሪ ስለ እስልምና እንቅስቃሴ ሲናገር እስልምና የአይሁድ እምነት በድኅረ ክርስቶስ ዘመን ያለውን እምነት የሚመስል ሃይማኖት ነው ይላል መሐመድ ከአይሁዶች ጋር ዕርቅ ለመመሥረት ያደርጉ የነበረውን ፍላጎትና ጥረት እርግፍ አድርገው የተውት ነገሮች በዚህ መልክ እየተካረሩ በመሄዳቸው ነበር ነገር ግን በሙስሊሞችና በአይሁዶች መካከል የነበረው ቅራኔ መፈታት ስላልተቻለ መሐመድ የሃይማኖት ሥርፀቶች ለውጥ አደረጉ በዚህም መሠረት ቀድሞ ወደ ኢየሩሳሌም አቅጣጫ ይሰገድ የነበረው ሶላት ወደ መካ እንዲዞር እንዲሁም በአይሁድ የሰንበት ቀን ወይም በክርስቲያኖች የአምልኮ ቀን እሑድ የነበረው የሙስሊሞች የአምልኮ ቀን ወደ ዐርብ እንዲዞር ተደረገ በሙስሊሞችና በአይሁዶች መካከል የነበረው ቅራኔ እየተባባሰ ሲሄድ በአይሁድ የሥርየት ቀን የነበረው የሙስሊሞች ጸጾም በወር ተራዝሞ ወደ ረመዳን ወር እንዲሸጋገር ተደረገ ከእነዚህ ለውጦች በኋላ ሙስሊሞች እምነታቸውን ከአይሁዶችና ከክርስቲያኖች እምነት በተለየ መልኩ እንዲደራጅና እንዲቀጥል ጥረት የማድረግ እንቅስቃሴ ጀመሩ ደስብርዛም ምነት ሐኒፍ የተሰኘው የእምነት ቡድን በዐረብ ምድር ከሚገኙት እምነቶች አንዱ ሲሆን በእስልምና ውስጥ ትቶት ባለፈው አሻራ በአራተኝነት ይፈረጃል የሐኒፍ እምነት አስተምህሮ ያተኩረው በፈጣሪ አንድነት ላይ ነው አንዳንድ የሐኒፍ እምነት ተከታዮች ስለአብርሃም በቂ ግንዛቤ የነበራቸው ሲሆን የአብርሃምን አምላክ እንደሚያመልኩ ይገልጻሉ የመሐመድ የእምነት ጉዞ ከሐኒፍ እምነት ተከታዮች ጋር በአያሌው የተጣጣመ ነበር። በሚያደርጉትም የወንጌል ሥርጭት መካከለኛው እስያንና ቻይናን በወንጌል ለመድረስ ችለዋል ከዚህ በተጨማሪ በዐረብያ ምድር የክርስቲያኑ ማኅበረሰብ እንዲሁም ተበታትነው ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖች ይገኙ ነበር ዳሩ ግን በዐረብያ ክርስቲያኖች ይኑሩ እንጂ በዐረብኛ ቋንቋ የተዘጋጀ መጽሐፍ ቅዱስ አልነበራቸውም ዐረቦች በዚህ ዐይነት ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ነበር መሐመድ የቁርአን መልእክት ከአላህ ዘንድ ተቀብያለሁ ያሉት ሱራ ራ ይህ ክሥተት ለዐረቦች አስደናቂ ተኣምርና ከዓለም ሥልጣኔ ወደ ኋላ ለቀረችው የዐረብ ምድር ታላቅ የምሥራች ነበር በሌላ አንጻር ደግሞ የክርስቲያኑ ማኅበረሰብ በነገረ መለኮታዊ ጐዳዮች በተለይም ደግሞ የክርስቶስ ባሕርያትን በተመለከተ ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ነበር ቤተ ክርስቲያናት ከመንግሥት ጋር ሊኖራቸው የሚገባው ግንኙነት ምን መልክ ይኑረው የሚለውን ጥያቄ ለመመለስም ጭንቅ ውስጥ ነበሩ ከከ ጸክ ነሐ ከፎበዚ ገሪ ይወህ ጩሠር ዲዝ በከፍ ቶ እነዚህ ሁለቱ ጐዳዮች ማለትም የክርስቶስ ባሕርያትና የቤተ ክርስቲያንና የመንግሥት ግንኙነት የቤተ ክርስቲያን ቀዳሚ አጀንዳዎች ነበሩ ከእነዚህ ጐዳዮች ጋር በተያያዘ በክርስቲያኖች መካከል የነበሩት ችግሮች በኛው ክፍለ ዘመን በነበረው የሙስሊሞችና የክርስቲያኖች ማኅበረሰብ ላይ ተፅዕኖ ነበረው ከዚህ በመነሣት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የነበሩ ችግሮች ለሙስሊም ማኅበረሰብ መፈጠር ያደረጉትን አስተዋጽኦና የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከቤተ ክርስቲያን ጋር የነበረውን ግንኙነት ለመዳሰስ እንሞክራለን ጺዩሱስ ማን ነጡ። በኛው ክፍለ ዘመን የአርዮስ ትምህርት ግብፅን ዐልፎ እንደ ሰደድ እሳት ወደ ሌሎች አካባቢዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተዛመተ ከጣዖት አምልኮ ወደ ክርስትና ለመጡ ክርስቲያኖች የአርዮስ ትምህርት የሥላሴን አስተምህሮ ለመረዳት የተሻለ አማራጭ ሆኖ ስላገኙት የአርዮስን ትምህርት መርጠዋል የሮማ ንጉሠ ነገሥት የነበረው ቁስጠንጢኖስ እንኳ ሳይቀር በክርክሩ ተሳትፎአል የሮም ንጉሥ የሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ጳጳሳት በኒቂያ ተሰብስበው በክርስቶስ ማንነት ላይ እንዲነጋገሩና ውሳኔ እንዲያሳልፉ ሲያደርግ ክርስቲያኖች በሙሉ ሊደነቁ እንደሚችሉ ማሰብ እንችላለን የመደነቃቸውም ምክንያት ከጥቂት ዓመታት በፊት ማለትም እንደ ጐርጐሮሳውያኑ የዘመን አቁጣጠር ከ ዓም ላይ ቤተ ክርስቲያን በሮም መንግሥት ከፍተኛ ስደት ሲደርስባት ስለ ነበር ነው እንደ ጐርጐሮሳውያኑ የዘመን አቄጣጠር በ ዓም ይኸውም ስደቱ ካበቃ ከ ዓመት በኋላ ቁስጠንጢኖስ ሕጋዊ የሆነ የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ በኒቂያ እንዲዘጋጅ አደረገ በዚህ ጐባኤ ወደ ሦስት መቶ የሚደርሱ ጳጳሳት ተካፋዮች ነበሩ ስብሰባው ለሦስት ወራት ያህል የተካሄደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ጉባኤው በክርስቶስ ማንነት ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ስለ ክርስቶስ ማንነት የሚከተለውን መግለጫ አውጥቶአል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአምላክም አምላክ ከብርሃንም ብርሃን ከእውነተኛ እግዚአብሔር እውነተኛ እግዚአብሔር የተወለደ ነገር ግን ያልተፈጠረ ከአብ ጋር አንድ ዐይነት ባሕርይ ያለው ነው ይህ የሃይማኖት መግለጫ የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ በመባል ይታወቃል ሽስዕምናዓ የስርድሳውያገ ጸምነት እየዋለ እያደር የአርዮሳውያን እንቅስቃሴ እየተዳከመ ሄደ። አስገራሚው ጐዳይ ግን አርዮሳውያን ከተነሠ ከሦስት መቶ ዓመታት በኋላ የእስልምና እምነት ሲቄረቁር ቁርአን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት የሚያስተምረው ትምህርት ከአርዮስ አስተምህሮ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ሆኖ መገኘቱ ነው በእስልምና ሃይማኖት ኢየሱስ ክርስቶስ ኢሳ የተከበረ ነው ቢባልም እንኳ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መገለጥ ነው የሚለው የክርስቲያኖች እምነት በሙስሊሞቹ ዘንድ ተቀባይነት የለውም ሙስሊሞች የኢየሱስን መሲሕነት ቢቀበሉም የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚለውን ጐዳይ አጥብቀው ይቃወማሉ ስለዚህ የአርዮስ አስተምህሮ ከቤተ ክርስቲያን ቧቢወገድም የአስልምና እምነት ከአርዮስ ትምህርት ጋር ተመሳሳይ የመሆኑ ጐዳይ የአርዮስ አስተምህሮ መልኩን ቀይሮ ተገለጠ ማለት ይቻላል። በሰሜን አፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚኖሩ አብዛኞቹ ሙስሊሞች የዘር ሐረጋቸውን ስንቄጥር እንዝላቶቻቸውና እንጅላቶቻቸው በአንድ ዘመን ክርስቲያኖች የነበሩ ናቸው ክርስቲያኖች ወደ እስልምና እንዲቀየሩ ያደረጋቸው የእስልምና እምነት አስተምህሮዎች ክርስቲያኖችን የሚስቡ ስለሆኑ ብቻ ሳይሆን በሙስሊም ግዛቶች ውስጥ የሚኖሩ ክርስቲያኖች የእስልምናን ሃይማኖት እንዲቀበሉ ጫና ይደረግባቸው ስለ ነበር ነው ይ በሰው ዐይን የማይደሞሳ ክምነት የክርስትና እምነት እንቅስቃሴ የጀመረው ዝቅተኛ ኑሮ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል ነው በናዝሬት ከተማ የምትኖር ድንግል በግርግም የተኛ ሕፃን መንጐቻቸውን በኩኬረብቶች አካባቢ የሚያሠማሩ እረኞች ከምሥራቅ የመጡ የከዋክብት ተመራማሪዎች ወደ ግብፅ የተሰደደ ቤተሰብ ከኢየሩሳሌም ውጪ በኩረብታ ላይ ያለ መስቀል ዓሣ ያጠምዱ የነበሩትን ደቀ መዛሙርት በሐይቅ ዳር ያገኝ የትንሣኤ ጌታ እነዚህ ሁሉ ክሥተቶች የተፈጸሙት በሰው ዐይን እዚህ ግቡ በማይባሉ ሰዎች እንደ ሆነ ሁሉ ቤተ ክርስቲያንም እንደዚህ ዐይነቱን የኅብረተሰብ ክፍል በወንጌል በመድረስ ወንጌል በሰው ሕይወት ውስጥ የሚያስከትለውን መለኮታዊ ኀይል በማሳየት ታላቅ ተሐድሶን አምጥታለቹች ነገር ግን በንጉሥ ቁስጠንጢኖስ አማካይነት የተካሄደው ለውጥ በምዕራቧ ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ጳጳሳት በማኅበረሰቡ ውስጥ እጅግ ትልቅ ሥልጣን እንዲኖራቸው አድርጉአል ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን ዝቅተኛ ከሚባለው የማኅበረሰብ ክፍል ተነሥታ የሥልጣን ማዕከል ወደ መሆን እንዲሁም የነገሥታትን ሥልጣን ጠባቂ ወደ መሆን ተሸጋግራለች በተመሳሳይ ሁኔታ እስልምናም ያቄጠቁጠው ዝቅተኛ ከሆነ የማኅበረሰብ ክፍል ነው የዐረቡ ዓለም የኀይል የበላይነት ያልነበረውና በሠለጠኑት የጐረቤት መንግሥታት ክፉኛ የሚናቅ አካባቢ ነበር ከእስልምና በፊት ዐረቦች ትኩረት የተሰጣቸው ሕዝቦች አልነበሩም የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ጠንክሮ ለዓለም ሕዝቦች ሁሉ ምስክር አንዲሆን ያደረገው የአላህ ቸርነት እንደ ሆነ ሙስሊሞች ያምናሉ ሙስሊሞች ከአነስተኛና ከተናቀ የዐረብ ጐሣ የተነሣው የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ኡማ በተከፋፈሉት ክርስቲያኖችና አይሁዶች መካከል ሰላምን የማምጣት ተልእኮ ከፈጣሪ ዘንድ እንደ ተሰጠው ጠንካራ እምነት ነበራቸው ኡማው በወቅቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ክርስቶስን አስመልክቶ ይካሄዱ የነበሩትን እሰጣገባዎች የመፍታት ተልእኮ አለው የሚል እምነት በሙስሊሞች ዘንድ አለ ሙስሊሞች የዓለም ማኅበረሰብን በተመለከተ ትልቅ ራአይ እንዳላቸው ያምናሉ ሙስሊሞች የነቢያት መደምደሚያ በሆነው ፊደል ባልቁቄጠረውና ያለወላጅ ባደገው መሐመድ አማካይነት የተጀመረው ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ለዓለም ሕዝቦች ሁሉ የቁርአንን እውነት የመመስከር ኀሳፊነት ከአላህ ዘንድ እንደ ተሰጠው ይናገራሉ በሌሎች ሕዝቦች ዘንድ ተንቆ የነበረውም የዐረብኛ ቋንቋ አላህ የመጨረሻውን መገለጥ ያስተዋወቀበት ቋንቋ እንደ ሆነ ሙስሊሞች ያምናሉ በሙስሊሞች አመለካከት በሌሎች ሕዝቦች የተረሱት ዐረቦች አላህ ለዓለም ሁሉ ሕዝብ የሚሆን መልእክት በእነርሱ በኩል ልኳል የሚል ጽኑ እምነት አላቸው ለሁሉ ቦታ የሚሆን እምነት ሙስሊሞች የእስልምና ሃይማኖት በዓለም ላሉ ሕዝቦች ሁሉ የሚሆን እምነት እንደ ሆነ ያምናሉ ከዚህ የተነሣም ሙስሊሞች ሰዎች የእስልምናን ሃይማኖት እንዲቀላቀሉ ጥሪ ከማቅረብ ባለፈ እስልምናን የተቀበሉ በአላህ አገዛዝ ሥር መኖር እንደሚጀምሩ ይናገራሉ በእስልምና ሃይማኖት የምስክርነት አገልግሎትና የግዛት ጥያቄ አብረው የሚታዩ ጐዳዮች ናቸው በሙስሊሞች አመለካከት የአላህ መገለጥ ቁርአን የአላህን ፍጹም ፈቃድ የሚያስታውቅ ስለሆነ እስልምና አንድን አካባቢ ሲቄጣጠር በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ሁሉ በአላህ መንግሥት ቀጥጥር ሥር እንደ ሆኑ ይታሰባል የአስልምና ቀዳማይ ተልእኮ ፍጽምናን በማኅበረሰብ ውስጥ ማስረጽ ነው ይኸውም እስልምና ፍጹም ሃይማኖት ቁርአንፍጹም የሆነ የአሳህ መገለጥ መሐመድፍጹም ሰው የሸሪአ ሕግፍጹም የሆነ መሪ እንዲሁም የሙስሊም ኡማሚዛናዊና ምርጥ ማኅበረሰብ የሚሉት ናቸው። በዚሁ ስፍራ አብርሃምና ልጁ እስማኤል የእግዚአብሔር ቤት እንደ ገና አንጸው ነበር እግዚአብሔር አዳምና ሔዋን እንዲሁም ዘሮቻቸው በምድር ላይ እንዲኖሩ ያደረጋቸው ለኀጢአታቸው መቀጣጫ አይደለም እነርሱም ሆኑ የሰው ዘር በሙሉ የሚወለደው የውርስ ኀጢአት ኖሮበት አይደለም አዳምና ሔዋን ሲፈጠሩ በመልካም አብነት ፍትራህ ነው የሰው ልጅም እንደዚሁ ነው ማንኛውም ሰው የሚወለደው ጥሩ ሙስሊም ሆኖ ነው ሰዎች ቢያውቁም ባያውቁም እግዚአብሔር የፈጠራቸው ከወሰነው መልካም ነገር አኳያ ነው ወደ እውነት ተዘንባይ ሆነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዙዋት ሬ የአላህን ፍጥረት መለወጥ የለም ይህ ቀጥተኛ ሃይማኖት ነው ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም ሱራ በቅንፍ ያለውን ይጨምራል በሙስሊሞች አመለካከት ሕፃናት ሁሉ ጥሩ ሙስሊሞች ሆነው ይወለዳሉ ነገር ግን ባለማወቅ ወይም በተሳሳተ ትምህርት ምክንያት ከእውነተኛው መንገድ ይወጣሉ እነዚህ ኀጢኣት የሌለባቸው ሕፃናት እንዴት መኖር እንዳለባቸው የሚያሳይ ምሪት ያስፈልጋቸዋል ምሪቱም የእስልምና እምነት ነው የእስልምና አስተምህሮ ምሪቱ አዳምንና ሔዋንን እንዲሁም ሰዎችን በሙሉ ምድርን ኀላፊነት በተሞላበት ሁኔታ እንዲጠብቁአትና እንዲንከባከቧት ረድቶአቸዋል። እንዲሁም ሰው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ባለመጠበቁ የተነሣ በኀጢኣት ወድቆአል አዳኝም ያስፈልገዋል የሚለው አስተምህሮ በአያሌው ረብሾታል ሰው በኀጢአት ስላልወደቀ ለድነት ወደ ትክክለኛው መንገድ የሚመራው ምሪት እንጂ አዳኝ አያስፈልገውም ሲል ይህ ኢማም አጥብቆ ተከራከረ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ በመካከለኛው ለንደን በሚገኝ መስጊድ ውስጥ በነበረን የማታ ውይይት እንዲህ ስል ተናገርሁ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሰው ተፈጥሮ የሚያስተምረው ትምህርት ለእውነታ የቀረበ ነው ኀጢአተኛ መሆናችንን በግልጽ ያስተምራል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በስም የተጠቀሱት ነቢያት እንኳ እንከን አለባቸውኹ የእምነት ሰው የነበረው አብርሃም እንኳ ሚስቱን እህቴ ናት በማለት ውሸት በመናገሩ ኀጢአት ሠርቶአል ኢማም በመስጊድ ውስጥ ጸሎት ለሚያደርሱ ሰዎች መሪ ነው ወይም ታዋቂ የሆነ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ መሪ ነው በሺአይት ሙስሊሞች ዘንድ ደግሞ የዘር ሐረጉ ከመሐመድ ወገን የሆነ የሃይማኖቱ መሪ ነው ሬፖ ይህ ቃል ከአፌ እንደ ወጣ በመስጊዱ ውስጥ የነበሩ አምስት መቶ የሚሆኑ ሙስሊሞች በአንድነት ይህ በፍጹም አይሆንም። ዋነኛው እውነታ ግን ሰዎች የተፈጠሩት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ለማድረግ ነው የሚለው ነው እግዚአብሔር እኛ ለእርሱ የቃል ኪዳን ሕዝቦቹ እንድንሆን ይፈልጋል ቁርአን ደግሞ አዳም የእግዚአብሔርን መንፈስ እንደ ተቀበለ ይናገራል የሙስሊም ነገረ መለኮት አስተማሪዎች በዚህ ጐዳይ ላይ እየተከራከሩ ይገኛሉ ነገር ግን ብዙዎቹ የሚያምኑት ሰዎች የእግዚአብሔር ወኪል ኸሊፋ እንዲሆኑ ሥልጣን የሚሰጥ መንፈስ ነው ወደሚለው ሐሳብ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ትዳር የሚያስተምረው ትምህርት የሚገኘው ስለኤድን ገነት በተጻፈው ታሪክ ውስጥ ነው ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ሰዎች ስለ ትዳር ያለውን ሕግ መጠበቅ እንዳልቻሉ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ይሁንና ስለ ጋብቻ ያለው አስተምህሮ መሠረት የተጣለው በአዳምና ሔዋን የትዳር ግንኙነት ውስጥ ነው ከመሠረተ ሐሳቦቹ ውስጥ አንድ ሥጋ ሬሄ መሆናቸው አንድ ወንድ ለአንድ ሴት በእግዚአብሔር የተመሠረተና ሊፈርስ የማይችል ጥምረት እንዳላቸው የሚያሳይ ነው ልጆች ስጦታ ናቸው ግዴታ ግን አይደሉም ባል ራሱን እንደሚወድ ሚስቱን እንዲወድና እንዲከባከብ የሚለው ሕግ ግልጽ የሆነ ኅብረትና መተማመን እንዲሰፍን የሚያደርግ ነው እንዲሁም ያለ ትዳር መኖር ተቀባይነት ያለው ሲሆን የሰዎች ደስታ ፍጹም የሚሆነው ግን ከእግዚአብሔር ጋር ባላቸው ኅብረት እንጂ በጋብቻ አይደለም ጋብቻ አስፈላጊ ነገር ቢሆንም ሳያገቡ መኖርም ተፈቅዶአል ቁርአን የጋብቻን ትርጐም ከመጀመሪያዎቹ ጣምራዎች አዳምና ሔዋን ሕይወት ጋር በማያያዝ ያስተምራል ሱራ ነገር ግን ቁርአን ስለ ጋብቻና ስለሴቶች ዘርዘር ያለ ሐሳብ ይሰጣል። ስል ጠየቅሁትኹ በጣም ደስታ በተሞላበት ፊት እንዲህ ሲል ነገረኝ ስሜ መሐመድ የኡመር ልጅ የአህመድ ልጅ የፍዶው ልጅ የሮብሌህ ልጅ የአቡበክር ልጅ የኦዶዋ ልጅ የጉኤልድ ልጅ የሐለኔ ልጅ የሳማተር ልጅ የዩሱፍ ልጅ የጉኡድአዴህ ልጅ የጉሬይ ልጅ የባስጋብ ልጅቿጅ የሁሴይን ልጅ የመሐመድ ልጅ የአብደላህ ልጅ የሳሞታሊስ ልጅ የሐዋድሌ ልጅ የመሐመድ ልጅየእኔ ጐሣ አባት ነው የጐሣው አባት የሆነውን የዘር ሐረግ ቁጠራ የጨረሰው የነቢዩ መሐመድ ልጅ የሆነችው ፋጡማ ላይ በመድረስ ነውጻ ይህ ፊደል ያልቁጠረ እረኛ ልጅ የነቢዩ መሐመድ ዘር በመሆኑ እንዲሁም እስልምና በደም ሥሮቹ ውስጥ እንዳለ በማሰብ በደስታ ተፍነከነከ ዳሩ ግን በዚህ የዘር ሐረግ ቁጠራ አብዝቶ የመደሰቱ ጐዳይ በጥንቃቄ መታየት አለበት ቁርአን ትክክለኛ የአብርሃም ዘሮች የሚባሉት እግዚአብሔርን ያመኑ ሰዎች እንደ ሆኑ በሱራ ላይ በትክክል አስፍሮአል ርፎ ሀአፈ ነ ከበ ኦ ር ርነ ከሰው ሁሉ በኢብራሂም ተገቢዎቹ እነዚያ የተከተሉትና ይህ ነቢይ እነዚያም ያመኑት ናቸው አላህም የምእመናን ረዳት ነው ዩበኩር ፅጆ እስማኤል የአብርሃም የመጀመሪያ ልጅ ነው በሴማውያን ባህል መሠረት የቤተሰብን ኀላፊነት የሚሸከመው የመጀመሪያ ልጅ እንደ ሆነ የሙስሊም ነገረ መለኮት ምሁራን ይናገራሉ የአብርሃምና የይስሐቅ ታሪክ በጣም አስደናቂ ታሪክ ነው ነገር ግን ለዓለም ሕዝብ ሁሉ የበረከት ምንጭ የሆነው የኅብረተሰብ ክፍል የሙስሊሙ ማኅበረሰብ እንደ ሆነ ይህም በረከት የመጣው በአብርሃም የመጀመሪያ ልጅ በእስማኤል በኩል ነው ሲሉ እነዚህ ምሁራን ያስረዳሉ ምሁራኑ እግዚአብሔር እስራኤልን የመረጠው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ እንደ ሆነ ከሱራ በመጥቀስ ይሞግታሉ እግዚአብሔር ለአብርሃም አንተንና ዘርህን ለሕዝብ ሁሉ ኢማም መሪ አደርጋችኋለሁ ሲል የሰጠው ተስፋ በመሐመድ መምጣት ምክንያት በአሁኑ ዘመን በሙስሊሙ ኡማ አማካይነት ተፈጽሞአል ሲሉ እነዚህ ሙስሊም ምሁራን ያስረዳሉ በእርግጥ አብርሃም አይሁድም ሆነ ክርስቲያን አልነበረም ነገር ግን እንደ አላህ ፈቃድ ለአላህ የሚሰግድና ለአላህ የሚታዘዝ ሰው ነበር የአላህን ፈቃድ የፈጸመው በእስልምና እምነት ነው ሱራ ር አብደላ ዩሱፍ ዓሊ የተባለው የእስልምና ሃይማኖት ምሁር እግዚአብሔር ለእስራኤል የጸጋ ስጦታ ሰጥቶአል የሚለው ክርክር ግሩም በሆነ ሁኔታ ተጠናቋል አሁን መዞር ያለብን በአብርሃም በኩል ለዐረቦች የመጣውን መንፈሳዊ ስጦታ ወደሚመለከተው ጐዳይ ነው ብሏል የሙስሊሙ ዓለም በእስማኤል በኩል አገኘሁት በሚለው መንፈሳዊ በረከት ሐሴት ያደርጋል ሙስሊሞች ይህ ታሪክ ምክንያታዊና አመክንዮአዊ ነው የሚል እምነት አላቸው የአብርሃም የመጀመሪያ ልጅ የሆነው እስማኤል ከብዙ ዓመታት በኋላ የእምነትና በዐረብያ የሙስሊም ማኅበረሰብ መመሠረት የሚያበሥር ችቦ ይዞ ቢነሣ የሚያስደንቅ አይደለም የመጨረሻው ነቢይ የእስማኤል ዘር እንደሚሆን ግምት ነበር ሙስሊሞች እስራኤል ከዓለም ሕዝብ መካከል የተመረጠች የመሆኗ ጐዳይ እየደበዘዘ መምጣቱ እግዚአብሔር የሙስሊሙን ማኅበረሰብ የዓለም ሕዝብ ሁሉ ብርሃን እንዲሆን « ለዚ ሀ ሀዘ ቶ ለመምረጡ ሁነኛ ማስረጃ ነው የሚል እምነት አላቸው እግዚአብሔር ለሙስሊሙ ማኅብረሰብ የሰጠው አገልግሎት ውስን ለሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ለእስራኤል ከሰጣት አገልግሎቶች እጅግ ከፍ ያለ እንደ ሆነ ይታሰባል አንድ የሙስሊም ሼክ በአግባቡ የማገናዘብ ችሎታ ያለው ሰው ውሎ አድሮ የእስልምናን ትክክለኛነት መረዳቱ አይቀርም ብሎ ሲናገር ሰምቼአለሁ አብርሃምና ይስሐቅ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ይስሐቅ የሚያቀርበው ታሪክ ከእስልምናው አቻ ታሪክ በጣም በተለየ መንገድ እንድንመለከተው ያደርገናል ቁርአን ስለ አብርሃምና ስለ እስማኤል ያለውን ትምህርት ተመልክተናል አሁን ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ አብርሃምና ስለ ይስሐቅ ምን እንደሚያስተምር እንመልከት ይህ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ የምናካሂደው ጥናት ይሆናል ምክንያቱም እስልምና ይስሐቅ ተባርኮአል ስለሚል እንዲሁም በተመሳሳይ ሁኔታ መጽሐፍ ቅዱስ እስማኤልም ተባርኮአል ስለሚል ነው። መጽሐፍ ቅዱሳዊው ነገረ መለኮት ደግሞ በይስሐቅ በኩል በረከት ለሰዎች ሁሉ እንደ መጣ ሲያስተምር የእስማኤልንም መባረክ ይቀበላል በእርግጥ በዘፍጥረት ሳይ ትልቅ ሕዝብ እንዲሁም ፀሥራ ሁለት አለቆች ከአብርሃም የመጀመሪያ ልጅ ከእስማኤል እንደሚወጡ ጌታ እግዚአብሔር ተናግሮ ነበር በሁሰት ዕጆች መካከስ ደስ ትግዕ በይስሐቅ ሕይወት ውስጥ የተፈጸመው አስደናቂ ነገር በወንጌል ውስጥ ላለው አስደናቂ ነገር ምልክት ነው ይስሐቅ ለአብርሃምና ለሣራ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጣቸው ነጻ ስጦታ ነው የወንጌልም ባሕርይ እንደዚሁ ነው በወንጌል ውስጥ ለሰዎች የተሰጠው የእግዚአብሔር ስጦታ ከሰዎች ፍልስፍና እንዲሁም ሃይማኖታዊ ከሆነ ሥርዐት እጅግ ያለፈ ነውፁ ማንኛውም ዐይነት ሰብአዊ ሥነ አመክንዮ ፍልስፍና ወይም ሃይማኖት በወንጌል ውስጥ ያለውን እውነት የተከተለ ወይም ግምት ውስጥ ያስገባ አልነበረም እግዚአብሔር በሰው ታሪክ ውስጥ ሰው ሆኖ በመገኘት ከሰዎች ጋር በመኖር ለሰዎችና በሰዎች ምክንያት መከራ ተቀብሎ ፍቅሩን ለእኛ ይገልጣል ብሎ እንኳን በውኑ በህልሙ ያሰበ እንኳ የለም ለእኛ የተሰጠን ስጦታ ይህ ውድ የሆነ የምሥራች ወንጌል ነው ይህ ስጦታ በእኛ ጥረት ወይም መልካም ሥራ ምክንያት ያገኘነው ሳይሆን በእምነትና በምስጋና የምንቀበለው ነው ከአብርሃም ዘመን ሁለት ቪህ ዓመት በኋላ አዲስ ኪዳን በአብርሃም ቤት ውስጥ በሣራና በአጋር እንዲሁም በይስሐቅና በእስማኤል መካከል የነበረው ግጭት ምን ዐይነት የነገረ መለኮት ገጽታ እንዳለው በስፋት ያብራራል ሓትያ ራ ሐዋርያው ጳውሎስ በአብርሃም ቤት የነበረው ትግል በተራ እምነትና እግዚአብሔር በመሲሑ በኢየሱስ በኩል በገለጠው እምነት መካከል ያለውን ትግል የሚያሳይ ምሳሌ እንደ ሆነ ተናግሯል የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት አብርሃም ከአጋር ጋር የነበረው ጥምረትና የእስማኤል መወለድ ሰዎች እግዚአብሔርን ለማስደሰት የሚያደርጉትን ጥረት የሚያሳይ ተምሳሌት እንደ ሆነ ይገልጻሉ በሌላ በኩል ደግሞ የይስሐቅ መወለድ እግዚአብሔር ያለ ሰው አነሳሽነት በራሱ የጊዜ ሰሌዳ ለአብርሃምና ለሣራ የሰጣቸው ነጻ ስጦታ ነው ማንኛውም ዐይነት ሃይማኖታዊ ሥርዐት ይስሐቅን አላስገኘም የሁለቱ ሴቶችና የሁለቱ ልጆች ታሪክ የሚያሳየን የማይገባንን የእግዚአብሔርን ጸጋ በእምነት በመቀበልና የእግዚአብሔርን ተስፋና በረከት የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዐቶችን በመፈጸም ከእግዚአብሔር እጅ ለመቀበል የሚደረገውን ሙከራ በንጽጽር የሚያሳይ ነው ሐዋርያው ጳውሎስ እነዚህ ሁለት የተለያዩ ጐዞዎች የእግዚአብሔርን ጸጋ በሃይማኖታዊ ሥርዐቶችና በሰብአውያን ጥረት ለማግኘት የሚደረግ ጐዞ እንዲሁም በእግዚአብሔር ጸጋ የሚገኝ ችሮታ ተምሳሌቶች እንደ ሆኑ ጽፎአል። ምዕራፍ ስምስት መሪዎች ዩነቢያት መደምደሚደመሲሑ ኢየሱስ መሲሕ ነው ኢየሱስ መሲሕ እንደ ሆነ ሙስሊሞችም ሆኑ ክርስቲያኖች በአንድ ይስማማሉ እንዲሁም ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ነቢያት የእግዚአብሔር ቃል እንዳበሠሩ ከሙሉ ልብ ያምናሉ ነገር ግን በእስልምናና በክርስትና ስለ መሲሑና ስለ ነቢያት የሚሰጠው ትርጓሜ እጅግ ለየቅል ነው ለምሳሌ ሙስሊሞች ሁሉ መሐመድ የነቢያት መደምደሚያ ናቸው እንዲሁም መሐመድ የእግዚአብሔርን የመጨረሻ እንዲሁም የተጣራና የማይለወጥ መልእክት ሰብከዋል ብለው ያምናሉ ነገር ግን ክርስቲያኖች የመሐመድ መልእክት የመሲሑን መልእክት ተክቶአል የሚለውን የእስልምና ትምህርት ፈጽመው አይቀበሉም ምክንያቱም ክርስቲያኖች ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታና አዳኝ ነው ብለው ከሙሉ ልብ ስለሚያምኑና ስለሚመሰክሩ ነው ይህም ምስክርነት ሙስሊሞች ስለ መሲሑ ካላቸው እምነት በእጅጉ የተለየ ነው መሲሑን በተመለከተ በክርስቲያኖችና በሙስሊሞች መካከል ያለው ልዩነት በቀላሉ የሚታይ ጐዳይ አይደለም ይህ ምዕራፍ ይህን ርእሰ ጐዳይ በተመለከተ በሁለቱ ሃይማኖቶች መካከል ያለውን መሠረታዊ ልዩነት መዳሰስ የትኩረት አቅጣጫው ነው ስለ መሲሑ ሕይወትና አገልግሎት የክርስቲያኖች መሠረተ እምነት ምንድን ነው። እግዚአብሔር ይመጣል ብሎ ለሰው ልጆች የሰጠው ተስፋ ሰኩናው የሚቀጠቀጠው ወይም መከራን የሚቀበለው አዳኝ መሲሑ እንደ ሆነ ክርስቲያኖች ያምናሉ በእስልምና እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ምሪትን ይሰጣቸው ዘንድ ተስፋ እንደ ገባላቸው ሲታመን በክርስትና በመጽሐፍ ቅዱስ ግን እግዚአብሔር ሰዎችን ለማዳን ምሪትን ሳይሆን መድኀኒትን እንደ ሰጠ ያስተምራል መጽሐኗ ቅዱሳዊ ተስፋጠሲሑ አዳምና ሔዋን በኤድን ገነት ኀጢአት ከሠሩበት ጊዜ ጀምሮ መሲሑ እስከ መጣበት ጊዜ ድረስ እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ አማካይነት ደግሞ ደጋግሞ ያስረገጠው ተስፋ በሞትና በኀጢአት ላይ ድል የሚነሣውን ቤዛአዳኝ እንደሚልክልን ነው በዚህ አጭር አሰሳዊ ጥናት እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋና ኪዳን የሚገልጹትን መልክቶች በጥልቀትና በዝርዝር እንመለከታቸዋለን እግዚአብሔር በየዘመናቱ ያስነሣቸው ነቢያት በሙሉ ይህን የተስፋ ልጅ አስመልክቶ ትንቢት ተናግረዋል ነቢዩ ኢሳይያስ ይህን የተስፋ ቃል አስመልክቶ ከየትኛውም ነቢይ ይልቅ በዚህ መልኩ በግልጽ ተናግሮአል ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር ኀያል አምላክ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያድነውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል ኢሳይያስ ኢሳይያስ ከኖረበት ከብዙ ዓመታት በፊት እግዚአብሔር አብርሃምን ሲጠራው ስለዚህ ተስፋ ገልጦለት ነበር። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን ዘፍጥረት የመሲሑን ቤዛዊ ሥራ የሚገልጽ ተስፋ ነው የሚል እምነት የላቸውም አብዛኞቹ ሊቃውንት እንዲሁም በርካታ ቤተ ክርስቲያናት ይህ ኪዳን በመሲሑ በኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ እንደ ተፈጸመ ከሙሉ ልባቸው ያምናሉ ወደማሳይህ ምድር ውጣ የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ ይህ የተስፋ ቃል የአብርሃምን እምነት የተጋሩትን የእግዚአብሔርን ሰዎች ማመልከቱ እሙን ቢሆንም በሌላ አንጻር ደግሞ ስለ መሲሑ መምጣት የሚያስተምር እንደ ሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዳሉ ገላትያ እግዚአብሔር በአብርሃም የእምነት መስመር እንዲመላለሱ የእስራኤልን ሕዝብ የቃል ኪዳን ሕዝብ አድርጐ መረጠ እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ የመረጠው ለዚህ ተልእኮ ለዓለም ሁሉ ብርሃን እንዲሆኑ በማሰብ ነበር ኢሳይያስ ይህን የቃል ኪዳን ሕዝብ ስናስብ ልንደነቅ እንችላለን እስራኤላውያን የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ሕዝብ መሆን ማለት ምን ማለት እንደ ሆነ መረዳት ሲጀምሩ በግብፅ የፈርዖን ባሮች ሆኑ ሪ ያ አብርሃም ከኖረበት ከአምስት መቶ ዓመት በኋላ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፅ ባርነት ነጻ ያወጣቸው ዘንድ ሙሴን ላከላቸው እግዚአብሔር ሙሴን የተገናኘበትና የጠራበት ሁኔታ እጅግ አስደናቂ ነበር ይህ የጥሪ ሁኔታም የመሲሑን አገልግሎት ፍንትው አድርጐ የሚያሳይ ነው እግዚአብሔር ለሙሴ የመገለጡ ጐዳይ ለእስራኤላውያን የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ሕዝብ የሚል ማንነት አጐጉናጽፎአቸዋል። የነቢያት መደምደሚያ በእስልምና ሃይማኖት መሐመድ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ረሱል እንደ ሆኑ ሙስሊሞች ያምናሉ ይህ እርሳቸው ለሰው ልጆች የአላህን መልእክት የሚናገሩ ነቢይ ናቸው ማለት ነው እስልምና በዓለም ላይ ላሉ ሕዝቦች ሁሉ ነቢያት ተልከውላቸዋል ሲል ያስተምራል ነገር ግን መልእክተኛ ረሱል የሚለውን ቦታ የሚጐናጸፉት እግዚአብሔር መጻሕፍትን እንዲጽፉ መገለጥን የሰጣቸው ሰዎች ነቢያት ብቻ ናቸው መሐመድ የመጨረሻ መልእክት የሆነውን ቁርአን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቀበሉ የመጨረሻው መልእክተኛ ናቸው መሐመድ የነቢያት ሁሉ ማሳረጊያማክተሚያ ናቸው ይህም ማለት እርሳቸው በመጨረሻው ዘመን የመጡና የነቢያት ሁሉ መደምደሚያ ናቸው ማለት ነው ስለ ነቢዩ መሐመድ ቁርአን እንዲህ ይሳል መሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድ ሰው አባት አይደለም ግን የአላህ መልእክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው ሱራ አንተንም ለሰዎች ሁሉ በመላ አብሳሪና አስፈራሪ አድርገን ቢኾን እንጂ አልላክንህም ግን አብዛኞቹ ሰዎች አያውቁም ሱራ እርሱ ያ አጋሪዎቹ ቢጠሉም መልእክተኛውን በመምሪያ መጽሐፍ በእውነተኛው ሃይማኖትም በኢስላም ከሃይማኖት ሁሉ በላይ ዶፋ ሊያደርገው የላከ ነው ሱራ በቅንፍ ያለውን ይጨምራል መሐመድ የመጨረሻ ነቢይ ሲሆኑ የቀድሞ ነቢያቶች ያስተማሩትን ትምሀርት ለማጽናትና ለማብራራት የተላኩ የእግዚአብሔር መልእክተኛ « ናቸው ሙስሊሞች ቀደምት ነቢያት የመጨረሻ ነቢይ ስለሆኑት ስለመሐመድ ተልእኮ እንደ ተነበዩ ጠንካራ እምነት አላቸው ከዚህም የተነሣ አንዳንድ ሙስሊም ምሁራን ስለ ነቢዩ መሐመድ መምጣት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ትንቢት ተነግሮ እንደ ሆነ በሚል መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት ጀምረዋል መጽሐኗ ቅዱስና መሐመድ ሙስሊሞች ስለ መሐመድ መምጣት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ትንቢት ተነግሮአል የሚለውን ግምታዊ ትምህርት እውን ቢሆን በሚል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት ነቢያትና ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገሩዋቸውን ንግግሮች በጥንቃቄ እያጠኑ ነው። በብሉይ ኪዳን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የተነገሩ ትንቢቶች ለመሐመድ የተነገሩ ናቸው ሲሉ ይከራከራሉ ለምሳሌ የሚከተለውን ክፍል እንደ ማስረጃ ያቀርባሉ እግዚአብሔርም አለኝ የተናገሩት መልካም ነው ከወንድሞቻቸው መካከል እንደ አንተ ያለ ነቢይ አስነሣላቸዋለሁ ቃሌንም በአፉ አደርጋለሁ ያዘዝሁትንም ቃል ሁሉ ይነግራቸዋል በስሜም የሚናገረውን ቃሌን የማይሰማውን ሰው እኔ እበቀልለታለሁ ዘዳግም ሙስሊሞች ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሙሴ ስለ መሐመድ መምጣት የተናገረው ትንቢት ነው ሲሉ በእርግጠኝነት ይገልጻሉ ሙስሊሞች በተለየ ሁኔታ እንቄቅልሽ የሚሆንባቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ነቢዩ መሐመድ የተናገረው አንዳችም ትንቢት የለም የሚለው ጉዳይ ነው ይህ ጐዳይ ለሙስሊሞች እንቄቅልሽ የሆነበት ዐቢይ ምክንያት ቁርአን በሱራ እንዲህ ስለሚል ነው የመርየም ልጅ ኢሳም የእስራኤል ልጆች ሆይ እኔ ከተውራት በፊት ያለውን የማረጋግጥና ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልእክተኛ ስሙ አሕመድ በሆነው የማበሥር ስሆን ወደናንተ የተላክሁ የአላህ መልእክተኛ ነኝ ባለ ጊዜ አስታውስ በግልጽ ታምራቶች በመጣቸውም ጊዜ ይህ ግልጽ ድግምት ነው አሉ ቁርአን ስለ ነቢዩ መሐመድ መምጣት ኢየሱስ ትንቢት ተናግሮአል ካለ ትንቢቱ በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ ተጽፎ ይገኛል። ነቢዩ ዮናስ ለነነዌ ሰዎች የንስሓን መልእክት በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማኒ በመባል የሚታወቅ የፋርስ የኢራን ተወላጅ ማንቼይዝም በመባል የሚታወቅ መናፍቃዊ እንቅስቃሴ ጀምሮ ነበር ይህ ሐሰተኛ መምህር ኢየሱስ ይመጣሳችኋል ያለው መንፈስ ቅዱስ እኔ ነኝ ይል ነበር ቤተ ክርስቲያን ይህን መናፍቃዊ እንቅስቃሴ በአንድ ድምፅ ኩንናዋለች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚናገረውን ትንቢት ስለ ነቢይ የሚናገር ነው የሚለው ይህ ዐይነቱ ትምህርት መሐመድ ከኖረበት ከብዙ መቶ ዓመት በኋላ የተጀመረ መናፍቃዊ ንቅናቄ ነው ፈዕ እንዲሰብክ በተላከ ጊዜ ላለመታዘዝ ከእግዚአብሔር ፊት ሸሸ በሐዲስ ኪዳንም በጳውሎስና በባርናባስ መካከል ግጭት ነበር ኢየሱስ በተያዘ ጊዜ ጴጥሮስም ሆነ ሌሎች ሐዋርያት ወደ ኋላ ሸሸተዋል ነገር ግን በእስልምና ነቢዩ መሐመድ ለሙስሊሞች እውነተኛ ምሳሌ እንደ ሆኑ ይታመናል መሐመድ በእስልምና እምነት የመጀመሪያው ሙስሊም ናቸው። መሐመድ ከኀጢአት ነጻ የሆነ ሕይወት ኢስማ ኖረዋል ማንኛውም ሰው እንደ አላህ ፈቃድ እንዲኖር ለ እያዐ ጸበህዘቫዘ ቡርፎነሃ ነዐ ርንኗያዕሰ በሃፎርቪሃ ፎሑ ሽ ፈሪዕጋ የመሐመድ የኑሮ ዘይቤ እውነተኛና ፍጹም ምሳሌ ስለሆነ በዚያ መሠረት መኖር አለበት ቀስ በቀስ መሐመድ ምንም ዐይነት ኀጢአት አልሠሩም የሚለው አስተምህሮ በሰፊው መሠራጨት ጀመረ ሙስሊሞች ቁርአን ፍጹም ተኣምር ከሆነ መልእክቱን የተቀበሉት ነቢይ ኀጢአት የሌለባቸው መሆን አለባቸው ይላሉ ይህ አስተምህሮ በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ማርያም ኀጢአት የለባትም ከሚለው አመለካከት ጋር ይመሳሰላል የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የነገረ መለኮት መምህራን ክርስቶስ ኀጢአት አልባ እስክ ሆነ ድረስ ድንግል ማርያምም ኀጢአት ሊኖርባት በፍጹም አይችልም ሲሉ ይከራከራሉ ምንም እንኳ ሙስሊሞች ነቢዩ መሐመድ ኀጢአት ሠርተው አያውቁም የሚል አቋም ቢኖራቸውም ቁርአን ከዚህ አስተሳሰብ ጋር የሚቃረኑ ትምህርቶችን ያስተምራል ለምሳሌ ሱራ ባለው ክፍል የሕይወትን መመሪያ በመፈለግ አንድ ዐይነ ስውር ሰው የእርሳቸውን ዕገዛ በመሻት እርሳቸው ዘንድ በመምጣቱ ፊታቸውን አጨፍግገው ከእርሱ ዞር በማለታቸው እግዚአብሔር እንደ ገሠጻቸው ይናገራል ነቢዩ መሐመድ ለሠሩት ኀጢኣት ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትን እንዲጠይቁ ቁርአን ሲያዛቸው እንመለከታለን ሱራ ይሁንና እስልምና መሐመድን ያለ ልክ ከፍ ከፍ አድርጉአቸዋል ቁርአን እግዚአብሔር ለመሐመድ አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ ሱራ ሲል ተናግሮአቸዋል። ኢየሱስ በሚያስተምረው ትምህርት የተቃኘ ነው በእርሱ አገሳለጽ ኢየሱስ ሙስሊማዊ ነቢይ ነው ካ ይ እዘ ፀቋ ዚ ኞ ፐ ከ እ ክነ እ ሃ በሃ ቲወሬ አንዳንድ የእስልምና ቡድኖች ኢየሱስ በመጨረሻው ዘመን ወደ ምድር ዳግም በመምጣት ሰዎችን ለመጨረሻው ፍርድ ያዘጋጃል ብለው ያምናሉ የዚህ አመለካከት ምንጩ በሱራ ላይ የመጨረሻው ዘመን ምልክት የኢየሱስ ጸግም ምጽአት ነው የሚለው የቁርአን አስተምህሮ ነው ስለኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ያለው ሌላኛው አመለካከት ኢየሱስ ከሌሎች ነቢያት ጋር በመሆን ለእግዚአብሔር ንጹሕ አምልኮን ለማቅረብ እንዲሁም በጽድቅ ለመኖር ይመጣል የሚል ነው ይህ ኢየሱስ ለሙስሊም መናንያን ጠባቂ ቅዱስ ነው ኢየሱስ በሱፊ ሙስሊሞች ዘንድ የተከበረና የተመሰገነ ቢሆንም የኢየሱስን የሕይወት ዘይቤ በመከተሉ በኩል ወይም ይህን ጐዳይ ይተገብሩታል የሚለውን ጥያቄ በእርግጠኛነት መመለስ ያስቸግራል ኢየሱስን በየበረሃው በሚገኙ ዋሻዎች የሚከተሉት መነኩሳት ከተከተሉት ይበቃል የተባለ ይመስላል ምንም እንኳ ሙስሊሞች በየዘመናቱ ኢየሱስን እናከብረዋለን ቢሉም ስለ ኢየሱስ ያላቸው አመለካከት ቤተ ክርስቲያንም ሆነች ወንጌላት ስለ ኢየሱስ የሚያስተምሩት አስተምህሮ ለዘመናት ሳይጣጣሙ ኖረዋል ታሪፍ ካሊዲ ስለ ሙስሊሙ ኢየሱስ እንዲህ የሚል አስተያየት ሰጥቶአል ይህ ኢየሱስ የተራራው ስብከት ወይም ምሳሊያዊ ንግግሮች ወይም ስለ ሕግና ስለመንፈስ ወይም ስለመስቀል አላስተማረም። ህ ርሆ ዘሄ የዐርክ ፈ ይመስላቸዋል በተጨማሪም ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ማርያምን አግብቶ ልጅ ወለደ ብለው ያምናሉ የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ አላቸው እንዲሁም ክርስቲያኖች መሲሑ እግዚአብሔር ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ከሙስሊሞች አስተምህሮ መረዳት ይቻላል በመጨረሻዎቹ ምዕራፎች ስለክርስትና እምነት በሙስሊሞች ዘንድ ስላለው የተሳሳተ ግንዛቤ እንመለከታለን በእስልምናና በክርስትና እምነት መካከል ያለው መሠረታዊ ሳዬፍነት ምንጩ ስለ እግዚአብሔር ማንነትና ስለሰው አጠቃላይ ሁኔታ ያለው አስተምህሮ ነው እስልምና የእግዚአብሔርን ልዕልናና ታላቅነት የሚነካ ማንኛውንም ዐይነት ትምህርት በአጽንኦት ይቃወማል በአንጻሩ ደግሞ ሙስሊሞች የክርስቲያኖች ወንጌል የእግዚአብሔርን ልዕልናና ታላቅነት ያሳንሳል የሚል እምነት አላቸው እግዚአብሔር በመሲሑ ውስጥ በመስቀል ላይ ሆኖ የጠፋውን ሰው ወደ ራሱ በመጥራት ከራሱ ጋር በማስታረቅ በእርሱ የሚያምኑትን ሰዎች ያድናል ለሚለው ትምህርት ሙስሊሞች ሲመልሱ ይህ ዐይነቱ ተግባር ልዑል በሆነው ኀያል አምላክ ላይ እንዴት ሊፈጸም ይችላል።