Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي
  • قائمة القراءة
  • مختصر
  • كتاب مسموع
  • بحث
  • تحميل
  • myzon
  • تسجيل الدخول
  • تسجيل
English  አማርኛ  Français  العربية
كتاب اليوم

የኢማን ምጥቀት መለኪያዎች.pdf


  • word cloud

የኢማን ምጥቀት መለኪያዎች.pdf
  • Extraction Summary

የኢማን ምጥቀት መለኪያዎች ለሳ ምሮረ ዐዐ ዉይም ዐዐ ዴያዕ ለባ ፈግሞፐድጵዖኖ የአሳታሚው መብት በሕግ የተጠበቀ ነው። እነዚህን ሰዎች እየያዙ የሚያመጡልኝ ሰዎች መድቤ ካመጡልኝ በላ የጀማአ ሶላትን ዳግመኛ እንዳይተው ለማስጠንቀቅ አስቤያለሁ ኡሙ ደርዳአ ረዐ እንደሚከተለው ብላለች አቡ ደርዳዕ ረዐ ወደእፄ ሲመጣ ተናድዶ ነበር እኔም ምንድን ነው የገመትከው። ለአላህ ምስጋና ይድረሰው በዚህ ዓለም ላይ ለልጆቻችን ያለብንን ኃላፊነት በእርሱ መልካም ፈቃድ እነሆ ፈፀምን ከዚህ በኋላ የሚቀረን በልባችን ሙሉ እምነት እንደጨበጥን ወደርሱ መሄድ ብቻ ነው ሙዛፊር የተባለው የቱርኮች ወታደራዊ መኮንን በዳርዳኔል ጦርነት ታላቅ ጀብዱ የፈፀመ ነው ከዚያም ወደምስራቁ አቅጣጫ ተዛውሮ በታላቅ ጀግንነት ሲዋጋ ክፉኛ ቆስሎ ወደቀ ነፍሱ ልትወጣ በተቃረበችበት የመጨረሻ ሰዓት በምላሱም ሆነ በዓይነ የፈለገውን ነገር መግለጽ አይችልም ነበር ከዚያም ከኪሱ ውስጥ አንድ ፖስታ አወጣና ከመሬት ላይ ከተንጣለለው ደሙ በእንጨት እያጠቀሰ እንደሚከተለው በማለት ጻፈ ቂብላ በየት በኩል ነው።

  • Cosine Similarity

አላህ ይህን በጐ ሥራችንን ይቀበለን በዚህ ዓይነት ሁኔታ እዳው የተከፈለለት ሰው ማን እንደከፈለለት ሳያውቅ ባለቤቱም ማን እንደከፈለው ሳያውቅ አዳውን ይሰርዛል እነዚያ ሰዎች ግዴታ ያልሆኑ ምጽዋቶችን በግልጽ ከመስጠት ይልቅ በድብቅ መስጠቱ የሚመረጥ መሆኑን ጠንቅቀው ያውቃሉ ስለሆነም ይህን በመሰለ ዘዴ የቻሉትን ያክል የሚሰጡትን ምጽዋት ምስጢራዊ ለማድረግ ይጥራሉ እነዚህ አባቶቻችን የቀኝ እጃቸው የሰጠውን የግራ እጃቸው እስከማያውቅ ድረስ መልካም ሥራቸውን ይህን ያክል ይደብቁ ነበር ሰዎች ሁለት ነገሮችን እንዲረሱ የአላህ ምርጥ ባሮች ይመክሩ ነበር የሰራኸውን መልካም ሥራ አታስታውሰው እንደዚያ ካደረግህ በሰራኸው ሥራ ከመኮፈስና ልብህን ከማሳበጥ ትድናለህ ባንተ ላይ የተሰራብህን መጥፎ ነገር አርሳ እንደዚያ ካደረግህ በልብህ ላይ የጥላቻና የብቀላ ዘር ሥሩን እንዳይሰድና እንዳይበቅል ታደርገዋለህ ባጭሩ ኢኽላስ እንደ ፈርጥ የሚቆጠር ዛብት ሲሆን ማግኘቱና ደብቆ ማስቀመጡ ቀላል አይደለም ምክንያቱም ልቦች ከአላህ ጋር በጥሩ ሁኔታ የሚገናኙት በርሱ በኩል ነውና ኢኽላስ ክቡር የሆነ ባህሪ ሲሆን የአንድን ባሪያ ደረጃ ከፍ በማድረግ በዚህም ሆነ በመጪው ዓለም ከአላህ ጋር ያቀራርባል ልቅና የተገባው ጌታ ኢኽላስ የሚጐድላቸውን መልካም ምግባራት ፈጽሞ አይቀበልም በፍርዱ ቀን ለእርካታ ወይም ለታይታ የተሰሩ መልካም ሥራዎች የልብን በሽታ የሚያጋልጡ ሆነው የሚቀርቡ ሲሆን በሰሪው ፊት ላይ እንዲለጠፉም ይደረጋል ኢኽላስ ግን የልእልና ባለቤት በሆነው አላህ ዘንድ ክቡርና የባሮቹን ደረጃ ከፍ ማድረጊያ ሆኖ የሚቀርብ ሲሆን በቅርቢቱም ዓለም ለእድሜ መርዘምና ለሲሳይ መስፋት ሰበብ ይሆናል ምዕራፍ ሶስት ተቅዋ ተቅዋ ማለት ከአላህ ጋር የሚያራርቅን ማንኛውም ነገር ከልብ ማራቅ ወይም ከአላህ ሌላ የሆነን ነገር በልብ ውስጥ አለማተለቅ ማለት ነው ተቅዋ ማለት አንድ አማኝ አላህን ብቻ ጠባቂው ተንከባካቢው ሲሳይን ሰጪውና ሁሉን ነገር አድራጊው አድርጐ መያዝ ማለት ሲሆን ከእርሱ ጋር ከሚያራርቀው ነገር መቆጠብን ያመለክታል ነቢዩ ሰዐወ አቡ ዘርን ረዐ በገሰጹበት ንግግራቸው ተቅዋ ማለት በአላህ ዓይን ሰዎች የሚመዘኑበትና ደረጃ የሚያገኙበት መስፈርት ነው እንዲህ ነበር ያሉት አንተ ከቀዩም ሆነ ከጥቁሩ ሰው የበላይ አለመሆንህን እወቅ አንተን ከፍ የሚያደርግህ ነገር ተቅዋህ ብቻ ነው አህመድ የተባረኩት ነቢይ ሰዐወ እንዲህ አሉ እኔ ከሁላችሁም አላህን በመፍራት በላጫችሁ ነኝ ቡኻሪና ሙስሊም የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ተቅዋን በአያንዳንዱ የሕይወት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ሲያስገቡት ይታዩ ነበር ለዚህም ነው የአርሳቸውን ሱና መተግበር አላህን ፈሪ ተቅዋ ያለው ሰው ለመሆን አስፈላጊ ነው የሚባለው ነቢዩ ዒሣ ዐሰ ተቅዋን በሚከተለው አኳንሏቷን ባማረ ሁኔታ ገልፀውታል ተቅዋ የሚለው ቃል የመጣው ወቃ ከሚለው ስርውቃል ሲሆን ይህ ማለት መጠበቅ መከላከል ማለት ነው እንዲሁም ከማንኛውም ጣኦታዊነት መራቅ ለአላህ ታማኝ መሆንና ቅድስና እንደማለት ነው አንድ ሰው ወደርሳቸው መጣና አንዲህ በማለት ጠየቃቸው አንተ የደግነትና የጽድቅ መምህር ሆይ። ሙስሊም አላህ ሆይ። ሳሀም መታጋህ ልታፖጎጾ ሪኒይጣ ጴዖታጎቻሥ ታቀማፇ በሌላ በኩል ደግሞ ተውባና አስቲግፋር አንድ ሰው በዚህችም ሆነ በመጪው ዓለም ለሚደርስበት ቅጣት የማምለጫ ሰበቦች ናቸው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ አሉ የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ ለሕዝቤ ሁለት ዋስትናዎችን እንደሰጣቸው በመግለጽ የሚከተሉትን ሁለት የቁርአን አንቀፆች አውርዶልኛል አንተ በውስጣቸው እያለህ አላህ የሚቀጣቸው አይደለም አላህም እነርሱ ምህረትን የሚለምኑ ሲሆነ የሚቀጣቸው አይደለም አንፋል እኔ ከሕዝቤ ስለይ ሁለተኛውን የመዳን ዋስትና እተውላቸዋለሁ እርሱም እስቲግፋር ሲሆን ከአላህ ቅጣት ያድናቸዋል እስከ ፍርዱ ቀን ድረስም ይጠብቃቸዋልሸ ቲርሚዚ ተውባና እስቲግፋር ወደ አላህ መቃረቢያ የሆኑ ሁለት ስኬታማ መንገዶች ናቸው ምክንያቱም አውነተኛ የሆነው ባህሪያቸው እንደሚያሳየው ሁለቱም የፃሃቀኛ መፀፀትና የአላህን አርዳታ የመሻት ውጤቶች ናቸውና እስቲግፋርን ለብቻው ከወሰድነው ወደ አላህ በመመለስ ሂደት ላይ ጉልህና የማይተካ ሚና የሚጫወት ሲሆን ባሪያው ከአላህ ጋር ግንኙነቱ እንዲታወክ የሚያደርጉትን መንፈሳዊ ጉድፎች መጥረጊያ ማጽጃ መሣሪያ ነው በሌላ በኩል ደግሞ ተቀባይነት ያለው ተውባ በባሪያውና በጌታው መካከል የተደነቀረውን መሰናክል በማስወገድና መንፈሳዊውን ግርዶ በመግፈፍ ግንኙነታቸውን የማስተካከል ሄደት ነው ይህም ለስኬት በሚበቃ ጊዜ ባሪያው ከአላህ ዘንድ ውዴታን እንዲያተርፍ ምክንያት ይሆንለታል ኃያሉ አላህ እንዲህ ይላል ፕኘኝ ዶጮ በ ቁ ረፈ ፈኔ ኃሀ ዕነሃጠለፇህ ሇመሳሇቻሃ ይመቆዳሳ ፖኖራሪዎቻም ይመቆሳ ተቻው ሪነያፇራሀ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በንጹህ ተውበት ወደርሱ የሚቃረቡትን ባሪዎቹን ምን ያህል እንደሚደሰትባቸው ለማሳየት የሚከተለውን ሐዲስ ተናገሩ አነስ ኢብኑ ማሊክ ረዐ እንዳወሩት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በምሳሌ ሲያስረዱ አንዲህ ብለዋል አንድ ሰው ስንቅ የተጫነች ግመሉ ጠፋችበት እስኪደክመው ድረስ ፈለጋት እንደማያገኛት ተስፋ ቆርጦ ከአንዲት ዛፍ ስር ቆም አለ በዚያው እንቅልፍ አሻለበው ሲነቃ ግመሉን ከአጠገቡ አያትና ከደስታ ብዛት የሚሆነውን አጣ በሐሴት ከመስከሩ የተነሳ አላህ ሆይ አንተ ባሪያዬ እኔ ደግሞ ጌታህ ነኝ በማለት ተሳሳተ አላህ ባሪያው ሲቶብት ከዚህ ሰው የበለጠ ይደሰታል ሙስሊም ቲርሚዚ በሌላ ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የኢስቲግፋርን ጥቅም ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል ለውዬው አላህን ምህረት መጠየቅ እስካላቆመ ድረስ የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ ከጭንቅ የሚወጣበትን መንገድ ያሳየዋል ከፃዛዘኑ ያላቅቀዋል እንዲሁም ከማያስበው በኩል ሲሳዩን ይሰጠዋል አቡ ዳውድ ስለሆነም ለአንድ የአላህ ባሪያ ትልቁና ጠቃሚው ጉዳይ ነፍሱንና ልቡን ቀልቡን ማጽዳት ነው እንግዲህ ስለተውባና እስቲግፋር ስናነሳ እነዚህን ሁለት ጠቃሚ ነገሮች አንድ ሰው የራሱ ካደረገ ወደ አላህ በሚወስደው ቀና ጉዳና ሲራጠል ሙስተቂም እንደ በር አድርጐ ሊቆጥራቸው ይችላል ከዚያ በኋላ መልካም ሥራዎችን በጥራትና በብዛት ማስከተሉ የግድ ነው አንድ ሰው የግዴታ የአምልኮ ተግባራትን ከፈፀመ በጊላ አስፈላጊና ሱና የሆኑ መልካም ሥራዎችን ያስከትል ከዚያ በኋላ የተለያዩና ውብ የሆኑ ምግባራትን ለምሳሌ የሌሎችን ሰዎች መብቶች መጠበቅ የወላጆችን ፃቅ መወጣት የተቸገሩትን ለአላህ ብሎ መርዳት አንዲሁም ሁሉንም ፍጡራን በፃዛዘኔታ በርህራሄና በይቅር ባይነት መመልከት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ በጎ ምግባራት ናቸው የሰናይ ምግባራት ገጽታዎች የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል እናንተ ሰዎች ሆይ። ማረኝ የነቢዩ ሰዐወ ባለቤት የነበረችው ዓኢሻ ረዐ አንድ ጊዜ እንዲህ በማለት ጠየቀቻቸው የአላህ መልእክተኛ ሆይ። ለዘመቻ የተዘጋጀልኝን ማንኛውም ነገር ለዚህ ወጣት ስጭው አንድም ነገር ወደኋላ እንዳታስቀሪ ይህ የአላህ ዛቅ ነውና ምናልባትም በዚህ ሰበብ በረከት እናገኝ ይሆናል ሙስሊም ይህ የነቢዩ ሰዐወ ባልደረባ የእርሳቸውን ትእዛዝ በሙሉ ልብና በታላቅ ስሜት በመታዘዝ ባለቤቱ ለእርሱ ያዘጋጀችለትን ስንቅ በሙሉ ምንም ነገር ሳታስቀር እንድትሰጠው አዘዛት በዚህ ድርጊቱ ያንፀባቀረው ለአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ያለውን ፍቅር ሙሉ ታዛዥነትና ታማኝነት ሲሆን መልካም ሥራ የመስራት ተነሳሽነቱንም አሳይቷል ኢብን ኡመር ረዐ እንዲህ ብለዋል መካ በተከፈተበት ቀን ነቢዩ ሰዐወ ወደ ካእባ ካመሩ በላ ከጠባቂዎቹ አንዱ የሆነውን ኡስማን ቢን ጦልዛን ረዐ ቁልፉን አንዲያመጣ ጠየቁት ኡስማን ረዐ ቁልፉን ወደያዘችው እናቱ በመሄድ እንድትሰጠው ጠየቃት ይሁን እንጂ ጣኦት አምላኪ የነበረችው አናቱ ቁልፉን ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነችም በዚህ ጊዜ ኡስማን ረዐ እንዲህ አላት ወላሂ ወይ ትሰጭኛለሽ ካልሆነ ደግሞ ይህንን ሰይፌን ከሰገባው አመዝዘዋለሁ ሴትዮዋ ቁልፉን ከእጁ ላይ አስቀመጠችለት ወስዶ ለአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አስረከበ ነቢዩ ሰዐወ የካዕባን በር ከፍተው ወደ ውስጥ ገቡ ኡሳማ ቢላልና ኡስማን አላህ የሁሉንም ሥራ ይውደድላቸውና አብረዋቸው ገቡ ነቢዩ ሰዐወ ካዕባ ውስጥ ገብተው ሳይወጡ ለረዥም ጊዜ ከቆዩ በኋላ በመጨረሻ ወጡ የእርሳቸውን መውጣት ተከትለውም ብዙ ሰዎች ወደ ውስጥ ለመግባት ተራኮቱ ወደ ውስጥ ከገቡት ሰዎች መካከል የመጀመሪያው ኢብን ኡመር ረዐ ነበር ልክ እንደገባም ቢላልን ረዐ ከበሩ አጠገብ ቆሞ አገኘው ከዚያም የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የት ጋ ሆነው ሰገዱ። አኔ በጣም ብዙ መጥሮ ነገሮችን ፈጽሜያለሁ ድምጴን ከአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ድምጽ በላይ ከፍ ሳደርግ ነበር ሁሉም መልካም ሥራዬ ዋጋ ቢስ ነው እኔ ለአሳት የተዘጋጀሁ ነኝ በማለት መለሰለት ያ ሰው ወደ ነቢዩ ሰዐወ ተመልሶ ከቴጌደ በላ ሳቢት ረዐ የተናገረውን ነገር ሁሉ አጫወታቸው በዚህ ጊዜ ነቢዩ ሰዐወ እንዲህ አሉ ድና አርሱ ለእሳት ሳይሆን ለጀነት አንደሆነ ንገረው ቡኻሪና ሙስሊም ሳቢት ረዐ በተፈጥሮው ድምጹ አስገምጋሚ ስለነበር የአላህን ትእዛዝ እንደጣሰ በመቁጠር ነበር በሃዘን የተቆራመደው የሁን እንጂ ድምጹ እንደዚያ መሆኑ የተፈጥሮው ክፍል በመሆኑና አርሱም እውነተኛ ልብ ቀልብ የነበረው ሰው በመሆኑ የእርሱ ጉዳይ በልዩ ሁኔታ የሚታይ ሆነ ከዚያ በኋላ ያ ባልደረባው ከነቢዩ ሰዐወ የሰማውን ታላቅ የምስራች ይዞለት በመሄድ በጀነት አበሰረው ይህ ባልደረባው ራሱ በጣም መልካም የሆነና አርአያነት ያለው ተግባር የፈፀመ ሲሆን ነቢዩ ሰዐወ አንዳች ነገር ሽተው ወይም ጠይቀው ያንን ነገር ወዲያውኑ እንዲያገኙ ለማድረግ መረባረብ የሁሉም ባልደረቦቻቸው ተግባር ነበር ማለት ይቻላል የአብደላ ኢብን ረዋፃ ረዐ ባለቤት እንዲህ ትላለች አላህ መልእክተኛ ሰዐወ ኹጥባ ዲስኩር ሊያደርጉ ሚንበር ላይ ወጥተዋል በተመሳሳይ ጊዜ ነቢዩ ሰዐወ ሚንበር ላይ ወጥተው የሚቀመጡበትን የሶላት ጥሪ አብደላህ ረዐ ከሩቅ ቦታ ሲሰማ እየፈጠነ መጣ ምንም እንኳን መስጊድ ባይደርስም ባለበት ቦታ ቁጭ አለ ይህ የአብደላህ ረዐ ሁኔታ ሲነገራቸው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ አሉት ልቅና የተገባው አላህ እርሱንና መልእክተኛውን የመታዘዝ ጉጉትህን ይጨምርልህ አብደላህ ኢብን አባስ ረዐ እንዲህ ብሏል ኡየይና ቢን ሂስን የወንድሙን ልጅ ሁር ቢን ቀይስን ረዐ ሊጠይቀው መዲና መጣ ሁር ከኡመር ረዐ የመማከርት ቡድን አባላት አንዱ ነው በዚህ ቡድን ወይም ኮሚቴ ውስጥ ምሁር እስከሆነ ድረስ ወጣትም ይሁን ሽማግሌ ይካተት ነበር በዚህም ምክንያት ኡየይና የወንድሙን ልጅ ሁርን እንዲህ አለው የወንድሜ ልጅ። ሰውየው እንዲህ አለ ሁልጊዜም ቢሆን ፈጣሪህን ታዘዝ ሙስሊሞችን አገልግል ምክርህንም ለግሳቸውሸ ባጭሩ መታዘዝ ታላቅ የሆነ የፍቅር ማሳያ ምልክት ነው እንዲህ የሚል አባባል አለ ያፈቀረ ታዛዥ ነው ስለዚህ ጌታቸውን የሚወዱ አማኞች ሁልጊዜም እርሱን በሚታዘዙበት ሁኔታ ላይ መገኘት አለባቸው እርሱን በሙሉ ልብና በታዛዥነት በመገዛት የተፈፀመች ኢምነት ነገር የእርሱን ትእዛዝ ባለማክበር ከሚፈፀም ተራራ የሚያክል በጐ ምግባር ትበልጣለች ምክንያቱም ባርነት የሚጀምረው እርሱን በመታዘዝና ለእርሱ በማደር ነውና ሰይጣን ከፈጣሪው ጋር የተጣላውና ከባለሟልነት የተባረረው ፈጣሪውን በሚገባ ባለማምለኩ አልነበረም ከዚያ ይልቅ የአላህን ትአዛዝ ባለማክበሩና በመኩራቱ ነው ምዕራፍ ስድስት በአምልኮ ጥንቁቅ መሆን ይህ አጽናፈ ዓለም የመለኮታዊው ክብር ባለቤት የሆነው ብቸኛ አምላክ የአጅ ሥራና የእርሱም ታላቅነት የተገለፀበት ክንውን ነው በዚህ አጽናፈ ዓለም ውስጥ ካሉ ፍጡራን ሁሉ ማእከላዊ ሥፍራ የተሰጠውና ታላቅ ጥበብ የተንፀባረቀበት ፍጡር ደግሞ የሰው ልጅ ነው ሰው የተፈጠረው ለታላቅ ዓላማ ሲሆን ይኸውም ፈጣሪውን ማምለክ ነው በብዙ የቁርአን አንቀፆች ኃያሉ አላህ የሰው ልጅ ዘላለማዊ የሆነ አካላዊና መንፈሳዊ ፍዳ ሲከፍል እንዳይኖር ሰላማዊ ቀልብ ይዞ ወደርሱ እንዲሄድ ያስገነዝባል አምልኮት ማለት አንድ ባሪያ የመጪው ዓለም ወይም የፍርዱ ቀን ከመከሰቱ በፊት ለጌታው ያለውን ታማኝነት የሚያረጋግጥበት የቃል ኪዳኑ ምልክት ነው የአምልኮት ጊዜያት የሰው ልጅ ወደፈጣሪው ይበልጥ የሚቀርብባቸው ቅጽበቶችና የጊዜ ክፍልፋዮች ናቸው ነገሩን ከሌላ አቅጣጫ ስንመለከተው ደግሞ አላህን በብቸኝነት ማምለክ በዚህ ዓለም ላይ የሰላምና የምቾት ምንጭ ሲሆን የሰውን ልጅ በመጪው ዓለም ይደርስብኛል ብሎ ከሚያስበው የቅጣት ፍርፃትም ነጻ ያደርገዋል አምልኮት ለአንድ የአላህ ባሪያ የመረጋጋቱ ምንጭ የልቡ አረፍት የመንፈሱ ስክነት በአጠቃላይ ሰብአዊ ክብሩ ከፍ የሚልበት መለኮታዊ በረከት ነው እንግዲህ ከዚህ ሁሉ መንደርደሪያ ሃሳብ የምንወስደው ቁም ነገር የአምልኮታችንን ጉዳይ እንዲህ በቀላሉ እንዳናየውና ትኩረት ሰጥተን ራሳችንን እንድናስተካክል ሲሆን በመጪው ዓለም የሚኖረን ስኬትና ውድቀትም በአምልኮታችንና ከአላህ ጋር ባለን ቀረቤታ ላይ የተመካ መሆኑን ነው የሰናይ ምግባራት ገጽታዎች ሁላችንም ብንሆን በቀጥታ ከፈጣሪያችን ጋር ወደምንገናኝበት የሶላት አምልኮ ከመሄዳችን በፊት የተሟላ ውዱእ ማድረግ ግዴታችን ነው ይህን ጉዳይ ቸል ማለት ወይም እንደነገሩ መያዝ በዋነኛው የአምልኮ ተግባር በሶላታችን ላይ አፍራሽ ተጽእኖ ይኖረዋል አንድ ጊዜ ነቢዩ ሰዐወ የሱብህን ሶላት እያሰገዱ ነበር የሩምን ምዕራፍ እያነበቡ ሳሉ የተወሰነ ቦታ ላይ ተሳሳቱ ሶላቱ እንደተጠናቀቀም ነቢዩ ሰዐወ ወደ ሰጋጆቹ ፊታቸውን አዙረው እንዲህ አሉ አንዳንድ ሰዎች ውዱእ ሳይኖራቸው ወደ መስጊድ ይመጣሉ ይህም ሰይጣን በምናነብበው የቁርአን አንቀጽ ላይ ተጽእኖ እንዲያደርግ በር ይከፍታል ወደ መሰጊድ ስትመጡ የቻላችሁትን ያክል ተጠንቅቃችሁ ውዱእ አድርጉ ስለዚህም አካልን መታጠብና የተሟላ ውዱእ ማድረግ ሶላታችን ተቀባይነት ይኖረው ዘንድ መውሰድ የሚገባን ወሳኝ እርምጃ ነው በተጨማሪም አንድ ሰው የቻለውን ያክል ውዱእ ያለው ቢሆን ይህ ታላቅ የሆነ ፀጋ ነው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሁሉንም ሥራቸውን ውዱእ ያላቸው ሆነው መፈፀም ይመርጡና ይወዱም ነበር አቡ ጁፃይም ረዐ እንዳስተላለፈው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አንድ ጊዜ ከጀመል ግምብ በኩል ሲመጡ አንድ ሰው አገኛቸውና ሰላምታ አቀረበላቸው እርሳቸው ግን ለሰላምታው አፀፋ አልመለሱለትም ነበር ሰውየው ወዲያው ወደ ግምቡ በመሄድ በመዳፎቹ ግድግዳውን ከመታ በኋላ አጆቹንና ፊቱን በማበስ ተየሙም በማድረግ ተመልሶ መጣና ሰላምታ አቀረበላቸው አርሳቸውም ለሰላምታው አፀፋውን መለሱ ቡኻሪ በዚህ ድርጊታቸው የአላህ ነቢይ ያስተላለፉት መልእክት አንድ ሰው ምንጊዜም ቢሆን ውዱአ ያለው ሆኖ መንቀሳቀስ አንዳለበት ነው ይህም አንድ ሰው የሚሰራውን ሥራ ሆ ሥራ የግዴታ ባይሆን እንኳን ውዱእ ካደረገ በኋላ ቢጀምረው ትሩፋቱ የበለጠ አንደሚሆን ነው በአንዳንድ ዘገባዎች መሠረት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ትጥበት በወጀበባቸው ጊዜ በግድግዳ ላይ መዳፎቻቸውን በማኖር ተየሙም ያደርጋሉ ይህንም ያደርጉ የነበረው ዋናውን ትጥበት ከመፈፀማቸው በፊት ያለ ውዱእ እንዳይሆነ በመፍራት ነው ፃይሰሚ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ይህን በመሰለ ሁኔታ ነበር ሕዝባቸው አካላዊና መንፈሳዊ ንጽናህውን እንዲጠብቅ ያስተምሩት የነበረው አንድ አለት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን ወደ አንድ የመቃብር ሥፍራ ፄዱ። ሀ ነዋፊል ሱና የአምልኮ ተግባራት ሱና ሶላቶች ግዴታ ፈርድ የሆኑ ሶላቶችን የሚደግፉና ወደ አላህ ለመቃረብ ምክንያት የሚሆኑ ናቸው የሰው ልጅ ተፈጥሮ ሆኖ ግዴታ ሶላቶችን በተሟላና አላህ በሚፈልገው መልኩ መስገድ አይቻልም የቱንም ያክል ጥረትና ጥንቃቄ ቢደረግ እንኳን ስህተቶች መፈጠራቸው የግድ ነው በዚህም የተነሣ ሱና ሶላቶችን ከመስገድ ውጭ ይህንን ክፍተት ወይም ጉድለት የመጠገኛ ሌላ መንገድ የለም የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አንዲህ ብለዋል በፍርዱ ቀን አንድ ባሪያ መጀመሪያ የሚጠየቀው ሶላቱን የተመለከተ ጥያቄ ነው ግዴታ የተደረጉበት ሶላቶች የተስተካከሉ ከሆነ የእርሱ ጉዳይ ቀላል ስለሚሆን ሌላ ችግር ሳይገጥመው ፈተናውን ያልፋል ሶላቱ ያልተስተካከለ ከሆነ ፈተናውን ስለሚወድቅ ከባድ ችግር ይገጥመዋል የሰውዬው ግዴታ ፈርድ ሶላቶች ችግር ካለባቸው እጅግ ኃያሉና የላቀ የሆነው አላህ እንዲህ ይላል ባሪያዬ አንዳች ዓይነት የሱና ሶላት አንዳለው ፈልጉለትሽ ሱና ሶላቶች በፈርድ ሶላት ላይ የተከሰተውን ጉድለት ያካክሳሉ በዚህ ዓይነት በሌሎች ጉዳዮቹም ምርመራው ይቀጥላል ቲርሚዚ አዚህ ላይ ግዴታ ፈርድ የተደረጉ ሶላቶችንም ሆነ ሌሎች የአምልኮ አይነቶችን ችላ ብለን ሱና በሆኑት ላይ ትኩረት እናድርግ የሚል የተሳሳተ ግምት ሊኖረን አይገባም ግዴታ የሆኑትን ብቻ እየሰሩ ሱናዎቹን ችላ ማለቱም ትክክል አይደለም ትክክለኛው አቋም የግዴታ ሶላቶችን በአግባቡ መስገድና ሱና የሆኑትን ደግሞ አቅም በፈቀደና የቻሉትን ያክል ለመስራት ጥረት ማድረግ ነው የአላህ መልክተኛ ሰዐወ እና የተከታዮቻቸው አቋምም ይኸው ነው በሌላ በኩል በተለያዩ ሸሪዓዊ ምክንያቶች ግዴታ ፈርድ ሶላቶቻቸውን ሳይሰግዱ ያሳለፉ ሰዎች ቀዷ ማካካሻ ሶላታቸውን በመስገድ ያካክሱ ሱና ሶላትን ጨርሶ መተው ግን ትክክል አይደለም ምክንያቱም አንድ ሰው ያልሰገዳቸውን የግዴታ ሶላቶች በተለይ መስገድ ከሚጠላባቸው ወቅቶች ፀሐይ ስትወጣና ስትገባ አካባቢ በስተቀር በማንኛውም ጊዜ መስገድ ስለሜቻል ነው ሆኖም ግን ሱና ሶላቶች ለምሳሌ ኢሸራቅ ተፃጁድ ወዘተ ወቅታቸው ካለፈ ቢሰገዱም ተቀባይነት ስለሌላቸው ወቅታቸውን ጠብቆ መስገድ ይመረጣል አንድ ባሪያ ፈርድ የሆኑ ነገሮችን ከመፈፀም ውጪ ወደ አላህ የሚቀርብበት መንገድ የለም ከዚያ በኋላ ሱና የሆኑ ተግባራትን በመፈፀም ወደ አላህ ይበልጥ አየቀረበና እየተጠጋ ይመጣል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንደተናገሩት አላህ የሚከተለውን በሐዲሰል ቁድስ እንዲህ ብሏል የአኔን ወዳጅ የሚተናኮል እአፋለመዋለሁ ባሪያዬ ከእኔ ጋር ሊቃረብ የሚችለው ግዴታ ያደረግኩበትን ነገር ሲፈጽም ነው ባሪያዬ ነዋፊል ትርፍ በሆኑ ነገሮች ወደእኔ በሚቃረብበት ወቅት እወደዋለሁ ከወደድኩት ደግሞ የሚሰማበት ጆሮ የሚያይበት ዓይን የሚዳስስበት አእጅ የሚሄድበት እግር እሆነዋለሁ ቢጠይቀኝ አሰጠዋለሁ ጠብቀኝ ካለኝም እጠብቀዋለሁ ቡኻሪ ሱና ነዋፊል የሆነ የአምልኮት ዓይነቶች የአንድን አማኝ ሰው መንፈስ በማንቃትና ልቡ ሕያው ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ በኩል ያላቸው ተጽእኖ ታላቅ ነው ነፍስን በማጽዳት የአማኙን ሰው ፊት በብርዛን ፀዳል ያደምቁታል እነዚህ አማኝ የሆነ ሰው በቅርቢቱ ዓለም ከሚያገኛቸው ሽልማቶች የተወሰኑት ሲሆኑ በመጪው ዓለም ደግሞ ታላቅ የሆነ ፀጋ ይሸለማል የሰናይ ምግባራት ገጽታዎች የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ቀናትና ሌሊቶች በሱና ዒባዳዎች የፈኩ ነበሩ ከተለያዩ ፈርድ ሶላቶች በፊትና በኋላ ይሰግዲቸው የነበሩ የሱና ሶላቶች የኢሽራቅ ዱዛ ሰላት ከሌሊቱ ግማሹን ወይም አብዛኛውን ክፍል የሚሸፍነውና ከወረደላቸው ቁርአን ብዙ ሱራዎችን የሚቀሩበት የተፃጁድ ሶላት ዋና ዋናዎቹ ናቸው ከዚህም በተጨማሪ ሱና ጾሞች ለድሆች በየጊዜው የሚሰጧቸው ችሮታዎች ሰደቃ በአላህ መንገድ ላይ የሚያደርጉት ያላሰለሰ ትግል እንዲሁም ሁልጊዜም ከሚያምረው ፊታቸው ላይ እንደውብ ጽጌረዳ ፈክቶ የሚያታየው ፈገግታቸው ሁሉ ከበጐ ምግባሮቻቸው የሚቆጠሩ ናቸው አንድ የሚያስደስት ነገር በገጠማቸው ወይም አስደሳች ዜና በሰሙ ጊዜ ሱጁድ ያደርጋሉ ይህንም የሚያደርጉት አላህ ለዋለላቸው ፀጋ ምስጋናቸውን ለመግለጽ ነው የተለያዩ ተፈጥሯዊና ያልተለመዱ የሆኑ ነገሮች ለምሳሌ የፀሐይ ግርዶሽ ኃያል አውሎ ነፋስ ወዘተ ሲፈጠር ተናንሰውና ተዋርደው ከዚያ መዓትና ከቁጣው ይሰውራቸው ዘንድ ጌታቸውን ይማፀኑታል ዝናብን ሲሹ በሽታና ድርቅን ለማስወገድ ወዘተ እንዲሁ ወደ ፈጣሪያቸው ያጐነብሱና ሱጁድም ያደርጉ ነበር በወርፃ ረመዳን ደግሞ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ከአዘቦቱ የኢባዳ ተግባራቸው እጅግ በተሻለና በጋለ ስሜት ነበር ፈጣሪያቸውን የሚያመልኩት የተራዊህ ሶላቶችን ከቤተሰባቸው ጋር ይሰግዳሉ የመጨረሻዎቹን አስር ቀናት ደግሞ መላ ቤተሰባቸውን ጭምር ለኢባዳ ያተጉ ነበር እንዲሁም በመስጊድ ኢእቲካፍ በማድረግ ወደፈጣሪያቸው ይበልጥ ይቃረባሉ ከረመዳን በኋላም የተለያዩ የሱና አጽዋማትን ለምሳሌ ሰኞና ሐሙስን አዘውትረው ይያዖሙ ነበር ለዚህ ድርጊታቸው የሚከተለውን ምክንያት ይሰጣሉ የሰው ልጆች ሥራ ሁሉ ሰኞና ሐሙስ ቀናት ወደ ኃያሉ አላህ ይቀርባሉ እኔም ፆመኛ ሆቼፄ ሥራዎቼ እአንዲቀርቡልኝ አሻለሁ ቲርሚዚ እንደ ሒጅራ አቆጣጠር ኛው ኛውና ኛውን የወሩን ቀናትም መፆም ያዘወትሩ ነበር በአነዚያ ቀናት ተከታዮቻቸውም እንዲፆሙ ይመክሯቸው ነበር ኢብን አባስ ረዐ እንዲህ ይላሉ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በጦርነት ጊዜ ይሁን በሰላም ጨረቃ ሙሉ የምትሆንባቸውን ቀናት የሚፆሙ ሲሆን ይህንንም ሁልጊዜም አቋርጠው አያውቁም ነሳኢ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ከሸዋል ወርም ስድስት ቀናትን የአሹራን ፀኛና ዐኛና ኛ ቀናት በፆም ያሳልፉ ነበር ሙስሊም የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የሐጅንና ኡምራን ፈዳኢል ምንዳ ሁልጊዜም ይገልጹና በእነዚያም ቀናት አላህን ከማመስገን ከማወደሰና የእርሱን ምሕረት ከመከጀል አይወገዱም በእነዚያ ጊዜያት በራሳቸውና አቅም በሌላቸው ተከታዮቻቸው ስም የመስዋእት እንስሳ ያርዳሉ ራቢዕ ቢን ካዕብ እንዲህ ይላል እኔ ሁልጊዜ ለነቢዩ ሰዐወ ውዱእ የሚያደርጉበት ውፃና ሌላም የሚፈልጓቸውን ነገሮች ማታ ማታ አቀርብላቸው ነበር በዚያ ጊዜም እንዲህ ሲሉ እሰማቸዋለሁ ሰሚአላሁ ሊመን ፃሚዳህ ከዚያም ደግሞ እንዲህ ይላሉ አልዛምዱሊላሂ ረቢል አለሜን ኢብን ሰዕድ አንድ አለት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ አሉኝ የምትፈልገውን ነገር ጠይቀኝ እኔም እንዲህ አልኳቸው እኔ ከእርስዎ ጋር በጀነት አብሬ መሆን ነው የምፈልገው ነቢዩ ሰዐወ ይህን እንደሰሙ እንዲህ አሉ ሌላስ የምትጠይቀኝ ነገር የለህም። እኔም ይህን ብቻ ነው የምፈልገው አልኳቸው ይህን እንደሰሙ እንዲህ አሉኝ እንደዚያ ከሆነ ሱጁድ በማብዛት እርዳኝ ሙስሊም ይህ ሱጁድ ተብሎ በታላቁ ነቢይ ሰዐወ አፍ የተጠቀሰው ሌላ ሳይሆን መደበኛ የሆነውና ነዋፊል የሆኑት ሶላቶች ናቸው በእነዚህ ሁሉ ብዙ ሱጁዶች ይኖራሉ ስለሆነም ጀነት መግባትና በዚያም ውስጥ የአላህ ነቢይ ሰዐወ ጐረቤት ለመሆን የሚሻ ብዙ መስገድና ሱጁዱንም በማብዛት ወደ አላህ እንዲቃረብ ያሻል ማለት ነው የነቢዩ ሙሐመድ ሰዐወ መኖሪያ የሆነችው ጀነት ከሌሎች ነቢያት መኖሪያ ትበልጣለች ስለሆነም አንድ ሰው በጀነት ውስጥ ወደ ነቢዩ ሰዐወ ለመጠጋት ከፈለገ በሱናቸው ላይ ቀጥ ማለትና ግዴታ የተደረገብትንና ነዋፊል ሶላቶችንም በጥልቅ ተመስጦና በብዛት መስገድ ይጠበቅበታል ኡሙ ዛቢባ ረዐ እንዲህ ብላለች የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ሲሉ ሰማኋቸው ከግዴታ ሶላቶች በተጨማሪ በየአለቱ የሚሆኑ ሱና ሶላቶችን ሙአከድ የሚባሉትን ቀብሊያና ባዕዲያ የሰገደ አላህ በእርግጠኝነት በጀነት ቤት ይገነባለታል ይህን መልካም ዜና ከነቢዩ ሰዐወ ከሰማሁ በቷላ ከእነዚህ ነፍል ሶላቶች አንዱንም አልተውኩም ኸይበር በተከፈተበት እለት አንድ ሰው ወደ ነቢዩ ሰዐወ መጣና እንዲህ አላቸው የአላህ መልእክተኛ ሆይ። ምናልባት የተሻለ ምንዳ ያስገኝልኛል ብዬ የማስበው መልካም ሥራዬ ይህ ነው ቡኻሪ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በህልማቸው ቢላል ረዐ በጀነት ውስጥ ከፊት ለፊታቸው ሲራመድ የጫማውን ኮቴ አዳመጡ ኃያሉ አላህ ለነቢዩ ሰዐወ ይህን ያሳያቸው ሱና የሆኑ መልካም ምግባራትን በመስራት ላይ እንድንበረታና ዘውታሪም እንድንሆን በመሻቱ ነው አንድ እለት አቡ ቀታዳ ረዐ ወደ ነቢዩ ሰዐወ መስጊድ ገባ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በባልደረቦቻቸው መካከል መቀመጣቸውን ባየ ጊዜ ፄደና ከጐናቸው ተቀመጠ ይህን ጊዜ ነቢዩ ሰዐወ ወደ አቡ ቀታዳ ዐ ዞሩና እንዲህ አሉት ከመቀመጥህ በፊት እንዳትሰግድ ያገደህ ነገር ምንድን ነው። ዕይ ይይፅሰሩሥ ያያሃሩ ሥታ ይነጋራፖቻዎጳ ሪነሳዓም የሰናይ ምግባራት ገጽታዎች አቡ ሁረይራ ረዐ እንዲህ ብለዋል ሎ በአንድ ዘመቻ ላይ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በዴካንና በኡስፋን መካከል በሚገኝ ቦታ ላይ ቆይታ አድርገው ነበር አጋሪዎቹ እንዲህ አሉ ሙስሊሞቹ ከአባቶቻቸውና ከወንዶች ልጆቻቸው ይልቅ አብልጠው የሚወዱት ሶላት አላቸው ይህም የአስር ስግደት ነው ለዚያ ሰዓት ሁላችሁም ተዘጋጁና አንድ ላይ ሆነን እየሰገዱ አያሉ አናጠቃቸዋለን በዚህ ጊዜ መልአኩ ጂብሪል ወደ አላህ መልእክተኛ ሰዐወ በመውረድ በአንኒሳእ ምእራፍ ዐኛው አንቀጽ ላይ በጦርነት ጊዜ እንዴት የጀመዓ የሕብረት ስግደትን እንደሚፈጽሙ በማብራራት ገለፀላቸው ቲርሚዚ ሙስሊሞች በተጋጋለ ጦርነት ላይ ቢሆኑ እንኳን ሶላታቸውን በጀመዓ የመስገድ ግዴታ እንዳለባቸው ይህ ክስተት ያሳየናል ጃእፈር ቢን አምር ከአባቱ የሰማውን ገጠመኝ እንዲህ በማለት ይተርካል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የበግ ጠቦት አግር ቆርጠው መብላት ሲጀምሩ ተመለከትኩ በዚያው ቅጽበት ለሶላት ጥሪ አዛን በመደረጉ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን ቢላ አስቀምጠው ውዱእ እንደ አዲስ ሳያደርጉ ወደ መስጊድ ሄደው ለሶላት ቆሙ ቡኻሪ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሶላትን በጀመዓ ለመስገድ እጅግ ጉጉ ስለነበሩ የመጀመሪያው ጥሪ መሰማት ሲጀምር ነው ምግባቸውን ጥለው ወደ መስጊድ ያመሩት አርሳቸው የመጀመሪያውን ጥሪ ሲሰሙ መዓዝ ይጀምሩ እንጂ ሶላቱ አስኪጀመር ድረስ የቀረበላቸውን ምግብ በልተው ሊጨርሱ ይችሉ ነበር የአላህ መልእክተኛ ዐወ ይህችን ዓለም ተሰናብተው ለመሄድ ያበቃቸው በሽታ ይዚቸው እንኳን እጅግ አድርጐ ያስጨንቃቸው የነበረው የጀመዓ ሶላት ጉዳይ ነበር አነስ ረዐ እንዳወሩት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሶላታቸውን በጀመዓ መስገድ ያልቻሉት ለመጨረሻዎቹ ሶስት ቀናት ብቻ ነበር ቡኻሪ ዓኢሻ ረዐ እንዲህ ትላለች ባልደረቦቼ ሶላታቸውን ሰገዱን። ከዚያም ከአቡበከር ረዐ አጠገብ ቆሙ ከዚያም አቡበከር ረዐ ነቢዩን ሰዐወ ሲከተሉ ሕዝቡ ደግሞ አቡበከርን ተከትሎ በመስገድ ሶላቱ ተጠናቀቀ ቡኻሪ አነስ ረዐ የሚከተለውን አውርተዋል አንድ ጊዜ አቡበከር ሶላት እያሰገዱ ነበር አለቱ ሰኞ የነበረ ሲሆን ሁላችንም መስመራችንን ሶፍ አስተካክለን ቆመናል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የክፍላቸውን መጋረጃ አንስተው ቆመው ይመለከቱን ጀመር ፊታቸው እያበራ በፈገግታ ደምቀው ጥርሶቻቸውም ይታዩ ነበር የአላህን መልእክተኛ ሰዐወ በዚያ ሁኔታ ስናያቸው በጣም ከመደሰታችን የተነሣ ሶላታችንን ለማቋረጥ ደርሰን ነበር አቡበከር ረዐ ምናልባት ነቢዩ ሰዐወ ከኋላ እየመጡ እንደሆነ በማሰብ የሚያሰግዱበትን ቦታ ለቅቀው ወደ ንጊላ በመመለስ ከመጀመሪያው ሶፍ ለመቀላቀል አቅማምተው ነበር ሆኖም ግን ነቢዩ ሰዐወ ሶላታቸውን እንዲጨርሱ ምልክት ከሰጧቸው በቷላ መጋረጃቸውን ዘግተው ወደ ክፍላቸው ገቡ ይህ ነበር ለመጨረሻ ጊዜ ያየናቸውና ወደዚያኛው ዓለምም የሄዱበት አለት ቡኻሪ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ቀደም ሲል በተጠቀሰው ሁኔታ የተደሰቱትና ፈገግታ የታየባቸው ባልደረቦቻቸው በልበ ሙሉነት የጀማዓ ሶላታቸውን በመስገዳቸው ነበር ያ በዳመና እንደተሸፈነች ጀንበር ብልጭ ብሎ የጠፋው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ፈገግታ በዚያ ቦታ ይሰግዱ ለነበሩ ባልደረቦበቻቸው የሕይወት ሙሉ የደስታና የተስፋ ምንጭ ነበር ከዚያ በኋላ መጋረጃቸውን መልሰው ወደ ክፍላቸው ገብተው ብዙም ሳይቆዩ ይህችን ዓለም ተሰናብተው ለመፄድ ከጣእራቸው ጋር መታገል ጀመሩ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሊሞቱ አቅራቢያ ለመጨረሻ ጊዜ የተናገራቸው ቃላት እንዲህ የሚሉ ነበሩ ለጎላታችሁን ሶላታችሁን። አሉ አልመጡም የሚል መልስ ሰጧቸው በዚህ ጊዜ እንዲህ አሉ እነዚህ ሁለት ሶላቶች የፈጅርና የኢሻ ሶላት ናቸው በመናፍቃን ላይ ከባድ የሚሆኑት እነዚህ ሶላቶች የያዙትን ትርፍና ትሩፋት ብታውቁ ኖሮ በእንብርክካችሁ እየዳሃፃችሁ መጥታችሁ በጀመአ ትሰግዱ ነበር የመጀመሪያው አወል ሶፍ ልክ እንደመላእክት ሶፍ ነው የሚቆጠረው በአርሱ ውስጥ ያለውን ትሩፋት ብታውቁ ኖሮ ቦታውን ለመያዝ ትሽቀዳደሙ ነበር አንድ ሰው ከሌላ ሰው ጋር በመሆን የሚሰግደው ሶላት ብቻውን ከሚሰግደው ሶላት ይልቅ ብዙ ትሩፋትና ብዙ ምንዳን ያስገኝለታል ከሁለት ሰዎች ጋር በመሆን የሚሰገድ ሶላት ከአንድ ሰው ጋር ሆኖ ከሚሰገድ ሶላት ይልቅ በላጭና ብዙ ትርፋማ ነው የሰጋጆች ቁጥር በበዛ ቁጥር የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ ይደሰታል አቡዳውድ ነሳኢ አብደላህ ኢብን መስኡድ ረዐ እንዲህ ብለዋል በአላህ እምላለሁ መናፍቅ ከሆነና መናፍቅነቱም በሁሉም ሰው ዘንድ የታወቀ ከሆነ ሰው በስተቀር ሶላቱን የሚተው ሰው አላየሁም በአላህ አምላለሁ አንድ የታመመ ሰው በሁለት ሰዎች ተደግፎና እግሮቹን መሬት ላይ እየጐተተ መጥቶ በሁለቱ ሰዎች መካከል በሶላት ሶፍ ላይ ቆሞ ሲሰግድ አይቻለሁ ሙስሊም አንድ እለት አብደላህ ኢብን ኡመር ረዐ በገበያ ውስጥ ይዘዋወሩ በነበረበት ጊዜ የሶላት ጊዜ ደረሰ ከዚያም ልክ የሶላት ጥሪ አዛን ሲሰሙ ሙስሊሞች ሱቆቻቸውንና መደብሮቻቸውን እየዘጉ ወደ መስጊድ ሲያመሩ ተመለከቱ ይህን እንዳስተዋሉም እንዲህ አሉ እነዚህ ሰዎች የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ እንደሚከተለው በማለት በቁርአን ካወደሳቸው ሰዎች ውስጥ ናቸው ቱረ ሪሠሪ «ራሠ ይሠ ሥሦሠቓ። የአላህ መልእክተኛ ሆይ። ፅሰፅቋዚዜዞ ኋኔ ይፖያፉ ያጳኋኔም ይመታ ጳኋርታ ፈምመሩ ይዕደጎና ሪኒጎሳያፇራያሃቹ ዱዓ በሚደጋገምበት ጊዜ በአንድ አማኝ መንፈስ ውስጥ ይቀረጻል ከዚያም አንዳች ዓለማዊ ወይም መንፈሳዊ አክል ሲገጥመው ያንን በሰገባ ውስጥ አየተቀመጠ የተሳለ ሰይፍ በሕሊናው ማኀደር ቅርጽና መልክ ይዞ የተቀረፀ ዱዓ በማውጣት ሥራ ላይ ያውለዋል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ከሶላታቸው በተጨማሪ እንባቸውን እያፈሰሱና ተረከዛቸው እስኪያብጥ ድረስ አላህን በጽኑ ይማፀኑትና ይለምኑት ነበር አጭርና ልባዊ የሆነን ልመና ዱዓ የመውደዳቸውን ያክል ከልብ ያልሆነን ማነብነብ ይጠሉ ነበር ተከታዮቻቸውንም እንደሚከተለው በማለት ይመክራሉ ባሪያው ወደ ጌታው ይበልጥ ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ላይ ሲሆን ነው ስለዚህ ሱጁድ ባደረጋችሁበት ጊዜ ብዙ የምትፈልጉትን ነገር አላህ ያሳካላችሁ ዘንድ ለምኑት ሙስሊም አንድ አማኝ ሁልጊዜም በፀሉትና አላህን በመለመን በዱዓ መትጋት የሚገባው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በእምነት ወንድሙ የሆነ ሰውም ዱዓ እንዲያደርግለት መጠየቅ ይኖርበታል ይህ ሰው ምናልባትም ድፃ ደካማ ወይም ችግረኛ ቢሆን እንኳን አላህ የእርሱን ልመና ሊሰማው ይችላል ምክንያቱም የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል አንድ ሙስሊም ለሌላው ወንድሙ በሌለበት ከሚያደርግለት የበለጠ በፍጥነት ተቀባይነትን የሚያገኝ ዱዓ የለም ቲርሚዚ የሰናይ ምግባራት ገጽታዎች የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አንድ ጊዜ እንዲህ አሉ ሙስሊም ሰው አላህን አንዳች ነገር ከጠየቀ የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ የፈለገውን ነገር ይሰጠዋል ወይም ደግሞ ሊሰጠው በነበረው መልካም ነገር ተመጣጣኝ የሆነ መጥፎ ነገርን ያስወግድለታል ይህም የሚሆነው ሰውየው የጠየቀው የተከለከለን ሐራም ነገር ካልሆነና ዝምድናንም ካልቆረጠ ነው ይህን ያዳመጠ አንድ ባልደረባቸው እንዲህ አለ እንደዚያ ከሆነ አላህ ብዙ ነገሮችን እንዲሰጠን እንፈልጋለን የአላህ መልእክተኛ የአላህ መልክተኛ ሰዐወ እንዲህ በማለት መለሱ የአላህ ፀጋ እናንተ ከምትጠይቁት ነገር ሁሉ በላጭ ነው ቲርሚዚ ኃያሉ አላህ ከልብ በኢኽላስ የተደረገን ዱዓ ውድቅ አያደርግም ይሁን አንጂ የተወሰኑ ጉዳዮች ከአርሱ ቅድመ ውሳኔ ቀደር ጋር የማይሄዱ ከሆኑ ምንም እንኳን በልባዊነት ኢኽላስ የተጠየቁ ቢሆንም ለጊዜው ላይቀበላቸው ይችላል እንደዚያም ቢሆን የአላህ አገልጋይ የሆነ ባሪያ ምን ጊዜም ቢሆን ተስፋ መቁረጥና አጆቹን ወደ ፈጣሪው ከመዘርጋት መገታት የለበትም ምክንያቱ በአንዲህ ዓይነት ጊዜ የሚደረግ ዱዓ ለመጪው ዓለም ከመልካም ሥራ ክምችት ውስጥ ገብቶ ይቀመጣልና ኃያሉ አላህ እንዲህ አለ ። በዚህ ጊዜ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሆይ ችኮላ ማለት ምንድን ነው። ሙኀዝ ኝ ዴነ ጎነሬያም ታይ ሯይ ዝቻይ ለፖፖወቹ ለፇም ሰወራቻ ታ ጭ ነሀ ሐሐ ሄታው ታማራ ሪነዕታው ሪነጸሰ ና ወወ ይህን የተናገሩት ሄፃይማኖታቸውን የሚያጠናክር ልጅ እንዲሰጣቸው አላህን በተማፀኑበት ጊዜ ነበር ያንን ልመናቸውን የተቀበለው አላህ ያህያ የሚባል ምርጥ የአላህ ባሪያና ነቢይ በመስጠት ለጥያቄያቸው መልስ ሰጥቷል አንድ ጊዜ የአላህ መልእክተኛ ሰወ አንድ ሰው በእርሳቸው ላይ መጀመሪያ ሰለዋትና ሰላምታ ሳያወርድ ዱዓ ሲያደርግ አዩትና እንዲህ አሉ ይህ ሰው ትፅግስት የለውምሻ ከዚያም ያንን ሰው ጠሩትና ለመላው ሕዝባቸው የሚሆን ማስገንዘቢያ አንዲህ በማለት ሰጡ ከእናንተ አንዳችሁ ዱዓ ሲያደርግ በመጀመሪያ አላህን ያመስግን ከዚያም በእኔ ላይ ሶለዋትና ሰላምታን ካወረደብኝ በኋላ ሚፈልገውን ነገር ይጠይቅ ቲርሚዚ የአላህ መልክተኛ ሰዐወ አንድ አማኝ ሰው የኃይማኖት ወንድሙ ለሆነ ሰው እርሱ ባለበት ወይም እርሱ በሌለበት ዱዓ ያድርግለት በማለት መክረዋል ኡመር ረዐ ኡምራ ለማድረግ ፈቃድ ይሰጧቸው ዘንድ ሲጠይቋቸው አንዲህ አሏቸው ወንድሜ ሆይ። በዱዓህ ውስጥ ጨምረን የእኛን ነገር እንዳትዘነጋው ቲርሚዚ ኡመር ረዐ እነዚህን ቃላት ከክቡሩ ነቢይ ሰዐወ አፍ እንደሰሙ ምን እንደተሰማቸው እንዲህ በማለት ተናገሩ መላውን ዓለም ቢሰጡኝ እንኳ እነዚህን ቃላት ስሰማ ካደረብኝ ደስታ የበለጠ አልደሰትም አቡዳውድ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል አንድ ሙስሊም በኃይማኖት ወንድሙ ለሆነ ሰው እርሱ በሌለበት ዱዓ ቢያደርግለት ተቀባይነት ያገኛል አንድ ሰው ለወንድሙ ዱዓ ባደረገ ቁጥ መልአክ ከጐኑ ይሆንና ለእርሱ እንዲህ እያለ ዱዓ ያደርግለታል አላህ ያንተንም ዱዓ ይቀበልህ ተመሳሳዩንም ነገር ላንተ ይስጥከህ ሙስሊም ኢብኑ ማጀህ ስለሆነም እኛ ሁላችን በእምነት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ለሆኑት ሁሉ አላህ የዚህንም ሆነ የመጪውን ዓለም መልካም ነገር እንዲለግሳቸው ልንለምንላቸው ይገባናል ማለት ነው በዚህች ጠፊ ዓለም ከሁሉም ነገር በላይ ሊኖረን የሚገባው ነገር ተቅዋ የአላህ ፍራቻ ነው ይህን ተቅዋ እንዲሰጠንም ነው በሶላታችን ላይ ሁልጊዜም አላህን የምንጠይቀው አንድ ሰው ወደ አላህ መልእክተኛ ሰዐወ መጣና እንዲህ አላቸው የአላህ መልእክተኛ ሆይ። እኔ ወደ አንድ ቦታ ልጓዝ ፈልጌያለሁ ዱዓ ያድርጉልኝ እርሳቸውም እንዲህ አሉት አላህ ተቅዋ ይስጥህ ሰውዬውም ሌላ ነገርም ይጨምሩልኝ የአላህ መልክተኛ አለ አላህ ኃጢአትህን ይማርህ አሁንም ይህ ባልደረባቸው እንዲህ አለ እናትና አባቴ መስዋእት ይሁኑልዎና አሁንም ይጨምሩልኝ የአላህ መልክተኛ ነቢዩ ሰዐወ እንዲህ አሉ የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ የትም ቦታ ብትሆን መልካም ነገርን ለመሥራት ያግራልህ ቲርሙዚ አንድ እለት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የሚከተሉትን የነቢዩላህ ኢብራዛምን ዐሰ ቃላትና የነቢዩ ዒሣን ዐሰ ዱዓ ፀሎት እንዲህ በማለት አነበቡ ጌታዬ ሆይ። ከአንተም ሌላ አምላክ የለም አንተ ባለፀጋ ነህ እኛ ደገሞ ድፃ ነን ዝናብ በእኛ ላይ እንዲዘንብ አድርግ የምትሰጠንንም ዝናብ ለእኛ ጥንካሬና ጉልበት የሚያላብሰን አድርገው ዘላቂና ዘውታሪም አድገው ይህን ካሉ በኋላ አጃቸውን ወደ ላይ አነሱ እጆቻቸውን በጣም ከፍ ከማድረጋቸው የተነሣ የብብታቸው ነጩ ክፍል ይታይ ነበር ከዚያም ጀርባቸውን ወደሰዎች አዞሩ ይህን ሲያደርጉ እጃቸው አሁንም ወደ ላይ እንደተዘረጋ ነበር ከዚያም ፊታቸውን ወደ ሰዎች አዞሩ በመጨረሻም ከሚንበራቸው ላይ ወርደው ሁለት ረክዓ ሶላት ሰገዱ የልቅና ባለቤት የሆነው አላህ ወዲያውኑ ዳመናዎችን ላከ ዳመናው በጉርምርምታና በመብረቅ እየታገዘ ሰማዩን ይገምሰው ጀመር በአላህ ፈቃድም ብዙም ሳይቆይ መዝነብ ጀመረ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ወደመስጊዳቸው የመመለስ እድል እንኳን ሳያገኙ ከሰማይ ላይ እንደጉድ ይቀዳው ጀመር የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ለሶላት የወጣው ሕዝብ ዝናብ ሸሽቶ ሲሮጥ ተመልክተው ፈገግ ካሉ በኋላ እንዲህ አሉ አላህ የፈለገውን ነገር ለመስራት እንደሚችል እንዲሁም እኔ ባሪያውና የአላህ መልእክተኛ መሆኔን አመሰክራለሁፅ አቡዳውድ ሰዎች ዝናብን በመከጀላቸው ከላይ በተመለከትነው ሁኔታ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ዱዓ ወዲያው ተቀባይነት አግኝቶ ሊዘንብ ችሏል ከዚያን ጊዜም አንስቶ ዝናብ ሲጠፋና ድርቅ ሲያይል ይህን ሱና በመከተል አላህን መለመን ተገቢ መሆኑ ሲወርድ ሲዋረድ መጥቷል የነቢዩ ባለቤት ዓኢሻ ረዐ እንዲህ ትላለች አንድ ሌሊት ከእንቅልፌ ስነቃ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ከጐኔ እንደሌሉ አረጋገጥኩ ምናልባት ሌላዋ ሚስታቸው ጋር ሄደው ይሆናል ስልም አሰብኩ ዙሪያውን በአጄ አየዳበስኩ መኖራቸውን ለማረጋገጥ ስሞክር እጄ እግራቸውን ነካ በዚህ ጊዜ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሱጁድ ላይ መሆናቸውን አወቅኩ ከዚያም እያለቀሱ እንደሚከተለው በማለት አላህን ሲማፀኑ ሰማሁ አላህ ሆይ። ዳረሷጳም ኃ ፈሪሥቻ ይ ሾ ፅው ይ ጳረፖዎ ያሪድ ና ዳ ጋያ ኋኗርት ታፖው ያሜናኙ ርታም መደጳረ ታት ፖመጎፖ መያፖናፖው ያሚያረጋው ፖትምፖ ይ ዕባድ ና ሪነዳያቃራፖ የሰናይ ምግባራት ገጽታዎች የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ለአላህ የነበራቸውን ናራቻ አብዱላህ ቢን ሺህር ረዐ ሲገልጽ እንዲህ ይላል አንድ ጊዜ ወደ አላህ መልእክተኛ ሰዐወ ስፄድ እየሰገዱና እያለቀሱም ነበር ለቅሷቸው የፈጠረውን ድምጽ ሳዳምጠው ደረታቸው የሚፈላ ይመስል ነበር አቡዳውድ አህመድ ዓኢሻ ረዐ እንዲህ ብላለች አቡ ጃህም ረዐ በአንድ ወቅት በጥልፍ ያሸበረቀ ቀሚስ ለአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በስጦታ አበረከተላቸው እርሳቸውም ለብሰው ሰገዱበት ሆኖም ግን ሶላታቸውን እንደጨረሱ እንዲህ አሉ ይህን ቀሚስ ለአቡ ጃህም መልሱለት ዓይኖቼ በጥልፎቹ ላይ ተማረኩ ሶላት ውስጥ መሆኔን እንኳን አእስክዘነጋ ድረስ ረበሸኝ ሙወጠእ ቡኻሪ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የሐጅን ሥርአት ለሕዝባቸው በሚገባ ያስተማሩት በመሰናበቻው ሐጀ ጊዜ ነበር ልክ እንደሌሎች የአምልኮት ክፍሎች ሁሉ ሐጅም ጥልቅ ተመስጦና ኹሹዕ እንደሚያስፈልገው በዚያ ጊዜ አብራርተዋል በዚያው ጊዜ ነቢዩ ሰዐወ በአረፋ ቀን ከአረፋት ወደ ሙዝደሊፋ እየተመለሱ ሳሉ የተወሰኑ ሰዎች ከኋላቸው አየጮሁና ግመሎሉቻቸውንም እየደበደቡ ያስጓራቸው ነበር ነቢዩ ሰዐወ ወደነዚያ ሰዎች በዘንጋቸው እያመለከቱ እንዲህ አሉ ሰዎች ሆይ። ረጋ በሉ ራሳችሁንም ተቆጣጠሩ በመቸኮል የምታገኙት ምንዳ አጅር አታገኙም ቡኻሪና ሙስሊም ዓሊ ረዐ እንዲህ አሉ ቢዩ ሰዐወ አንድ ሰው ሶላት ላይ ሆኖ በጺሙ ሲጫወት ተመልክተው አንዲህ አሉ ልቡ ውስጥ ኹሹዕ ለአላህ በአክብሮት መተናነስ ቢኖረው ኖሮ እጆቹም አካላቱም አደብ ይኖራቸው ነበር እናቷ ኡሙ ሩማን ረዐ አንድ ጊዜ እንዲህ እንዳሏት ዓኢሻ ረዐ አስተላልፋለች አንድ ጊዜ እየሰገድኩ አያለሁ ወዲያና ወዲህ እወዛወዝ ነበር ይህን ሁኔታዬን ያስተዋሉት አቡበከር ረዐ በኃይል የገሰጹኝ ከመሆነ የተነሳ ሶላቴን ላቋርጥ ምንም ያህል አልቀረኝም ነበር ከዚያ በኋላ የአላህ መልክተኛ ሰዐወ የሚከተለውን ተናግረዋል ብለው ተረኩልኝ አንዳችሁ ሶላት ላይ ከቆመ መላ አካላቱ ተረጋግቶና በታላቅ አክብሮት መሆን አለበት ልክ እንደ አይሁዳውያን ወደኋቷላና ወደፊት መወዛወዝ የለበትም እግሮችና እጆች አንድ ቦታ ላይ ረግተው መቆማቸው ሶላታችን የተሟላ እንዲሆን ከሚያደርጉት ሁኔታዎች አንዱ ነው ነቢዩ ሱለይማን ዐሰ ምንም እንኳን ስፍር ቁጥር የሌለውን ዛፃብትና ታላቅ ንግሥና ቢሰጣቸውም ከዚህች ዓለም ውዴታ ከቁሳዊ ፍቅር ራሳቸውን በማራቅ ቀለል ያለ ሕይወትን ይመሩ ነበር በዚህ ባህሪያቸውም በመግፋት አላህን የሚፈሩ ትሁትና የማይኮሩ ነበሩ የአርሳቸውን ባሕሪ ይበልጥ የሚያንፀባርቅ አባባል ከዚህ በታች ተጠቅሷል ያንን ሁሉ ማለቂያ የሌለው ፀጋ የተሰጡት ሱለይማን ዐሰ አላህን እጅግ ከመፍራታቸው የተነሣ በሕይወታቸው አንድም ጊዜ እንኳን ወደ ሰማይ ተመልክተው አያውቁም ኢብን አቢ ሸይባ አብደላህ ቢን አቡበከር ረዐ እንዲህ አለ አቡ ጦልፃ ረዐ አንድ አለት በአትክልት ማሳቸው ውስጥ ይሰግዱ ነበር በዚያው ቅጽበት ዱብሊ የተባለ ወፍ ከማሳቸው ለመውጣት መንገድ አየፈለገ ወዲያና ወዲህ ይበር ነበር ይህ ሁኔታ አቡ ጦልዛን ያስደነቃቸው በመሆኑ ለሰከንዶች ያክል በዓይናቸው ተከትለውት ወዲያና ወዲህ አሉ ከዚያም ጽሞናቸውን ወደሶላታቸው ሲመልሱ ስንት ረከዓ እንደሰገዱ ዘነጉት ይህ ወፍ ሶላታቸውን በኹሹዕ እንዳይሰግዱ በማድረግ የረበሻቸው በመሆኑ ወደ ነቢዩ ሰዐወ ፄደው የሆነውን ነገር ካጫወቷቸው በኋላ እንዲህ አሉ የአላህ መልአክተኛ ሆይ። አቡዳውድ በሌሊት ሁለት ረከዓ ሶላት እየሰገደ ቁርአን ከሚያነብ ሰው የበለጠ አላህ ማንንም አያዳምጥም ባሪያው በሶላት ላይ እስካለ ድረስም የአላህ እዝነት በእርሱ ላይ ይሰፍናል ባሪያው አላህን ከምንም በላይ ይበልጥ የሚቀርበው ቁርአንን በሚያነብበት ገዜ ነው ቲርሚዚ በሐዲስ እንዲህ የሚሉ አባባሎች ተጠቅሰው ይገኛሉ ቁርክንን አላህ ካሳወቃቸውና በአእምሯቸውም ከያዙት ከፃፈዙት በኋላ ትኩረትና በቂ ጊዜ ሳይሰጡት በመቅረታቸው የሚረሱት ሰዎች ታላቅ ኃጢአት እንደፈጸሙ ይቆጠርባቸዋል አቡዳውድ ብሌላ በኩል ደግሞ አንድ ሰው በልቡ ውስጥ ምንም ዓይነት የቁርአን አንቀጽ የማይገኝ ከሆነ እንደ ወና ቤት ይቆጠራል ቲርሚዚ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አንዲህ አሉ ልብ ብረትን እንደሚያገኘው ዝገት ብጤ ይዝጋል የአላህ መልእክተኛ ሆይ። የአላህ መልእክተኛ። እኛም የአላህ መልእክተኛ ሆይ። መስጊድ ውስጥ አንድ ሰው አለ ከዚህ ሰው የበለጠ ቁርአንን ባማረ ሁኔታ የሚያነብ ሰው ሰምቼ አላውቅም በዚህ ጊዜ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ወደ መስጊድ ሄደው ሰውየው ሳሊም ረዐ መሆኑን ከተመለከቱ በኋላ ተመልሰው እንዲህ አሉ ከሕዝቤ ውስጥ ይህን የመሰለ ሰው እንዲኖር ላደረገው አላህ ምስጋና ይገባው ኢብኑ ማጃህ አህመድ ሐኪም አንድ ጊዜ የአላህን መልእክተኛ ሰዐወ አንድ ባልደረባቸው እንዲህ በማለት ጠየቃቸው የአላህ መልእክተኛ ሆይ። ለጥቂት ጊዜ አረፍ እንበልና በጌታችን ላይ ያለንን አምነት እናድስ ዚክር እናድርግ አንድ ባልደረባቸው ይህ የአብደላህ ረዐ ድርጊት ስላልገባው ወደ ነቢዩ ሰዐወ በመሄድ ስለሁኔታው ነገራቸው ነቢዩ ሰዐወ ጉዳዩን ከሰሙ በኋላ እንዲህ አሉ አብደላህ ኢብን ረዋፃ አላህ ይዘንለት መላእክት የሚያደንቁትን ለዚክር መሰባሰብ ያፈቅራል አህመድ አብደላህ ቢን ሸዳድ ረዐ እንዲህ ብሏል በኒ ኡዝራ የሆኑ ሶስት ሰዎች ወደ አላህ መልእክተኛ ሰዐወ ዘንድ ከመጡ በቷላ ኢስላምን ተቀበሉ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ጥያቄ አቀረቡ እነዚህን ሰዎች የሚንከባከብልኝ ማን ነው ጦልዛ ረዐ እንዲህ አለ እኔ እንከባከባቸዋለሁ የአላህ መልእክተኛ አነዚህ ሰዎች ከጠለዛ ረዐ ጋር ሳሉ የአላህ መልእክተኛ አነስተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ወደ አንድ ቦታ አሰማሩ ከሶስቱ ሰዎች አንዱ ከዚያች አነስተኛ ቁጥር ያላት ሰራዊት ጋር አብሮ ከዘመተ በኋላ በዚያ አያለ ተሰዋ ሸሂድ ሆነ ከዚያም የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሌላ አነስተኛ ሰራዊትን የያዘ ጓድ ለዘመቻ አሰማሩ ከእነዚህ ጋር ሁለተኛው ሰው አብሮ ዘመተ ሆኖም ግን እርሱም ተሰዋ ሸሂድ ሆነ ከዚያ በኋላ ሶስተኛው ሰው ከጥቂት ጊዜ በኋላ በአልጋው ላይ እያለ ሞተ ጦልፃ ረዐ አንዲህ ይላል እነዚህን ሶስት ሰዎች በሕልሜ በጀነት ውስጥ አየሁዋቸው ከአልጋው ላይ ሆኖ የሞተው የመጀመሪያው ነው ቀጥሎ ደግሞ ለዘመቻ በሁለተኛ ዙር ወጥቶ የተሰዋው ሆነ የመጨረሻ ደረጃን የያዘው በመጀመሪያው ዙር ዘምቶ የተሰዋው ሆነ በዚህ ሁኔታ በጣም ተደንቄና በትንሹም ቢሆን ተናድጄ ወደ ነቢዩ ሰዐወ በመሄድ ስለሁኔታው ሳጫውታቸው እንዲህ አሉ ይህ ሊገርምህ አይገባም በአላህ ዓይን ሁልጊዜም በቋሚነት ተስቢህ ተክቢርና ተህሊል ከሚልና ሕይወቱን በኢስላም አስተምህሮቶች ከሚመራ ሰው የበለጠ መልካም ሰሪ የለም አህመድ አንድ እለት ኡፍቴድ ወደገጠራማው የቱርክ ግዛት ከተማሪዎቹ ይረሳዎቹ ጋር ሄደ ከዚያም ውብ በሆነው የገጠር ቀበሌ ሲዘዋወሩ ተማሪዎቹ ማራኪ የሆኑ የአበባ ዝንጣፊዎችን እያመጡ ለመምህራቸው ማበርከት ጀመሩ ይሁን እንጂ በኋላ ላይ አዚዝ ሙሐመድ ሁደይ በመባል የሚታወቀው ዝነኛ ተማሪያቸው አንዱ ግንዷ የተሰበረና እንደመጠውለግ ያለች አበባ ይዞ በመምጣት ለመምህሩ ከሰጠ በቷላ ጭንቅላቱን አቀረቀረ። አላህ ሆይ። የአላህ ነቢይ ሰዐወ አንዲህ ብለዋል ከሞት በኋላ ፀፀት የማይዘው አንድም ሰው የለም የአላህ መልእክተኛ ሆይ። ረም አፇኃጎፖወሃ አንድ እለት የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው የአላህ መልአክተኛ ሆይ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

تعليقات:


memezon

خيارات التنزيل | تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي | كتاب اليوم

© dirzon | شروط الخدمة | خصوصية | حول | خدمات | اتصال