Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ይፈጠራል ወይስ ራሱን በራሱ ያኖረ መሆን አለበት ካልሆነማ ከባዶ ነገር ላይ እንዴት ይሄ ግዙፍ ዩኒቨርስ መጣ።ኣዮ ኣመ በሕይወት ላሉት የሚያበዛ እና መኖራቸውን የሚያሰፋ ከሆነ እንዴት የማይታየው ፍቅር በመሞቱ ራሱን አያበዛም። ነፍስና መንፈስ ምድር ላይ ብቻ ኗሪና ከሞት በኃላ የማይኖሩ ከሆነ ስለዘላለም ዕውቀት ውስጣቸው ሊቀመጥ አይችልም ነበር ምክንያቱም ከሚችሉት በላይ ይሆንባቸው ስለነበር ስለሚያፈርሳቸው ነው ስለሆነም ከሞት በኋላ ዘላለማዊ ህይወት አለ።
ሳይንሱ ይለናል ሙቂቷ የአየር ኳስ ዓለምን ፈጠረች በመፈረካከስ ወይም በመቀዝቀዝ ዛፃይማናት ይለናል ፈጣሪ ነበረ ከዚያም በሥልጣት ዓለምን ፈጠረ የኔ ጥያቄ ግን ለሳይንስም ለእግዜር ሙቋንም ጋዝ ሆነ ፈጣሪን በተዓምር ማነው ያኖራቸው በሉ መልሱልኝ ለምን ግራ ይግባኝ ለምን ይቸግረኝ በቢለየን ቁጥር ወገን በዓለም ኖርኝ ለጊዜው የኔ መልስ እንደሚከተለው በአጭሩ ተጽፏል በጋራ እናንብበው በፍልስፍናና በእኔ አስተሳሰብ ፈጣሪ ለራሱ በራሱ ነው ገደብ ራሱን በራሱ አኑሯል እግዚአብሔር ወሰን የሌለው ነው በኃይል በክብር አቻ የሌለወ ነው በሥልጣን በበትር ዘመን የሌለው ነው ዘላለም የሚኖር ጊዜ የማይወስነው አስደናቂ ተዓምር ስለሆነ እግዚአብሔር ማነው የሚፈጥረው በወሰን አልባው ላይ የበላይ የሚሆነው በወሰን አልባ ላይ ሌላ ወሰን አልባ አካል አለ ብንል አስቀድሞ እግዚአብሔር ያለወሰን ሲቀጥል በወሰን አልባ ላይ ሌላ ወሰን አልባ ቢመጣ ቢደረብ አይሆነውም ካባ ስለዚህ አግዚአብሔር ወሰን ስለሌለው የቀደመው አባት ወላጅ ስለሌለው ራሱን በራሱ ያኖረ ራሱ ነው በኃይል በጉልበት በእውቀትም በጥበብ በሁለም ነገር በላጭ ስለሌለው በፍፁም አይኖርም እሱን የሚያኖረው መደምደሚያ አግዜር ዘለዓለማዊ ነው እንደያልተወሰነ ቀጥታ መስመር ዱው በዚህ ቀን ተፈጠረ ማለት አይቻልም የተፈጠረበት ቀን አይታወቅም ስለሆነም አይፈጠርም እሱ ፈጣሪ ነው ነበር አለ ይኖራል የፈጣሪን መኖር ሊያስረዱ የሚችሉ ፍልስፍናዎች ምክንያቶች ወይም አስተሳሰቦች ምንም እንኳን ስለፈጣሪ መኖር ብዙ ምክንያታዊነት ወይም ፍልስፍና ማቅረብ ቢቻልም ሦስቱን ዋና ዋናዎቹን ምክንያቶች ማየት ብቻ በቂ ነው አነሱም የማስረጃ ብልጫ የየበሳይነት አስተሳሰብ የታላቁ ጥበብ አስተሳሰብ የፍቅር አስተሳሰብ ናቸው እያንዳንዳቸውን ተራ በተራ እንመልከት የማስረጃ ብልጫ የበላይነት አስተሳሰብ ሀ ፈጣሪ የለም የምንል ሰዎች ወስን በሌለው ዓለም ላይ ዞረን አለመኖሩን ማስረዳት ይጠበቅብናል ማንም በወሰን አልባው ዩኒቨርስ ሊጓዝና ሊዞር አይችልም ምክንያቱም በ የሰው ዕድሜ የሰዎች ሁሉ ዕድሜ ቢደመር ገደብ የለሹን ህዋና ምድር መዞር ስለማይችልና አንዳንድ የዩኒቨርስ ቦታዎች እንደ ቤርሙዳ ትሪያንግል ያሉ አደጋ የበዛባቸውና ሊታሰሱ የማይችሉ ስለሆኑ ነው ስለሆነም የእግዜርን አለመኖር የለም ብሎ ከመናገር ውጪ እስከ አሁን አለመኖሩን ያሳየን የለም የለም ባዮች የእግዜርን መኖር ሊያስረዱን ካልቻሉ አለ ባዮች የሚሉትን እንስማ እስኪ አለ ባዮች ፈጣሪ መኖሩን ማረጋገጥ ቀላል ነው አድካሚ ዙረትም ሳያስፈልግ መኖሩን እናስረዳለን ይላሉ እንዴት ሲባሉ ፈጣሪ ድንቅና ተዓምራት ሲያደርግ በሽተኞችን ሲፈውስሰይጣንን ሲያወጣ እናሳያለንበመንፈስም ለመረዳት ካሻህ እናስለማምድሃለን ይላሉ ስለዚህ በድንቅና በታምራት መልስ የሰጠን ፈጣሪ አለ የለም ከሚሉት በተሻለ በዚህ መንገድ እናሳምናለን ብለው መልስ ይሰጣሉ ድንቅና ተዓምራት የአጋጣሚ ግጥምጥሞሽ ቢሆኑስ ሲባሉ እንዴት ሁሉም ድንቅና ታምራት ግጥምጥሞሽ ሊሆኑ ይችላሉ ብለው ጥያቄውን በጥያቄ ይመልሳሉ ለ ድንቅና ታምራት ሁሉ የአጋጣሚ ግጥምጥሞሽ ነው ብሎ የሚክድ ሰውም ካለ ይህንኑ አቋሙንና እምነቱን ይዞ ስለፈጣሪ መኖር ማስረዳት ይቻላል መንገዱ «የጥርጣሬ ቀመር» ይባላል እነሆ ቤት ውስጥ ቁጭ ብለህ መፅሐፍ እያነበብክ ሳለ ቤታችሁ አጠገብ የጥይት ተኩስ ድምፅ ሰማህ እንበል ግምትህ ወይም ጥርጣሬህ ሊሆን የሚችለው ሰው ቆስሏል ወይም አልቆሰለም የሚል ነው የተኮሰውን ሰው አላየህም ጥይቱ የተተኮሰው ሰው ለማቁሰል ወይም ለሌላ ምክንያት እንጂ ከዚህ ውጭሊሆን አይችልም ጥይቱ ሲተኮስ አለማየትህ እና ድምፁን መስማትህ ብቻ ስለውጤቱ ተጠራጣሪ አደረገህ ቢያንስ ተፈጥሮአዊ ውቀት እንደሚነግረንጌ ፈጣሪ ይኖራል ወይም አይኖርም ብሎ የሚጠራጠር ፍጡር ሰው ብቻ ነው እንለላት ወይም ተክሎች ተጠራጣሪ ስለመሆናቸው ማስረጃ ንም እንድትጠራጠር ምክንያት የሆነህ ያሳየኸው እግዜር ነው ብታየው ኖሮማ አትጠራጠርም ነበር ያላየኸው የጥይት ተኩስ ድምጽ እንዳጠራጠረህ ሁሉ እግዜር አለ ወይም የለም ብሎ ያጠራጠረህ ድምጽ አሰየጥይቱ ጩኸት አለ መጠራጠር መኖሩ እንድትጠራጠር ያደረገህ ኃይል መኖሩን ያሳያል አትርሳ። ስለዚሀ ፈጣሪ የለም ባዮች ለፈጣሪ በእምነት ቀጠሮ ሊይዙለት ይገባል በአንዱ ፃይማኖት ወይም እምነት ፈልገው ካጡት በሌላ ሊፈልጉት ግድ ነው ምክንያቱም ለመምረጥ ነፃ ፈቃድ ስለተሰጣቸው ድርጊታቸው አግባብ ነው ፈጣሪም ይደግፈዋል መ የለውጥ አስተሳሰብ ተፈጥሮ ዩኒቨርስ ሥርዓቱን ጠብቆ ይኖራል ቀናትና ሌሊት ሳያቋርጡ ይፈራረቃሉ ቢያንስ የተፈጥሮ ህግ ወይም ቀመር የማይለወጥ ሥርዓት አለው ሰው የሚታየውን ዓለም ለውጥ ማየት ይችላል አንዳንዴም ለውጥን ሲያባብስ ሲያዘገይ ወይም ሲቆጣጠር ይስተዋላል በኛ እውቀት የሚታወቅ የማይለወጥ ብቸኛ ነገር እራሱ ለውጥ ብቻ ነው የለውጥ መርህ አይለወጥም ሰው የሚታዩት ለውጦች ተመልካች አንዳንዴም ተቆጣጣሪ የተሻለ ጠቢብና ተንታኝ መሆኑ ለውጦች በጠቢብ ይታያሉ የሚል አንድ የለውጥ መርህ ይፈጥራል የዩኒቨርስ ለውጦች እንዲህ ከሆኑ ይህ መርህ በዩኒቨርስ ለሚኖረው የሰው ልጅም ስለሚያገለግል የማይታዩት ነፍሱና መንፈሱ ከሰው ሥጋ ሲለዩ የነሱን ለውጥ ተመልካች ከነሱ የበለጠ ጥበብ ያለው አዋቂ ፈጣሪ ሊኖር ግድ ነው ለምን ቢባል ማንኛውም ለውጥ በተሻለ ጠቢብ ይታያል የሚለው የለውጥ መርህ የማይለወጥ ስለሆነ ነው ፈጣሪ ከማይታዩት ነፍስና መንፈስ የበለጠ ጥበብ ያለው የማይታይ ኃይልና የነሱን ለውጥ ተመልካች ነው እግዜር ከሰው የበለጠ ጥበብ አለው ምክንያቱም የሰውን ለውጥ ተመልካች ነውና ነው ሠ የተለመደ የህይወት አስተሳሰብ ይህ እጅግ በጣም ተጠራጣሪ ለሆኑ ሰዎች የሚቀርብ ምክንያት ነው አዲስ አውቀት ፍልስፍና ግኝት በተለያዩ አዋቂዎች ሂዩሂውተን ጋሊሊዮ አርኪሜድስ ሶቅራጥስ ፕሌቶ ወዘተ ሲገኙ እነዚህ ግኝቶች በሁሉም ሰዎች ተቀባይነትን ያገኛሉ ከእነዚህ አዋቂዎች በዕድሜ የሚበልጡ ሰዎችም ሆኑ ያነሱት የቀደሙም ሆኑ ወደፊት የሚመጡ ትውልዶች የእነሱን እውነት ተቀብለውት ይኖራሉ ዩኒቨርስ ህዋና ምድር ግዜፉ ዓለም በራሳቸው ያለ ፈጣሪ ለረዥም ጊዜ ኖረዋል ብለን አንገምት እየኖሩ እያለ በመሀል ከእነሱ የበለጠ ጥበብ ያለው የሆነ ኃይል በአዲስ አስተሳሰብ ፍልስፍናና ጥበብ እንዲሁም ችሎታ በለጣቸው ህይወት ያላቸውንና የሌላቸውን ያዛቸውና ይመራቸው ጀመር ከዚያም እሱ የሁሉም የበላይ በመሆን የቀደሙትን ህዋና ምድር ግዙፉን ዓለም በእሱ ጥበብ ማንነት ገዝቶአቸው ፈጣሪ ሆነባቸው የታላቁ ጥበብ አስተሳሰብ ዩኒቨርስ እንዴት አንደተፈጠረ ሊሆን የሚችል ግምት የእኛ ተፈጥሯዊና ተለምዷዊ እውቀት እንደሚነግረን አራት ዓይነት ስለ ዩኒቨርስ አመጣጥ ሊገመቴ የሚችሉ መላ ምቶች አሉ እነሱም ቅጽበታዊ ለውጥ አዝጋሚ ለውጥ እንዳለ እራሱን በራሱ ማኖር እና በፈጣሪ መምጣቱ የሚሉት ናቸው የትኛው ሊሆን እንደሚችል እስኪ ተራ በተራ እንመልከተው ። ዩኒቨርስ ህዋና ምድር በይዘትና በጊዜ ያልተወሰነ ነው ይሁንና ያልተወሰነው የአስከሳች ኃይል ክፍል ነው በአካላዊ ማንነቱ ሲታይ ቁስ አካል ዩኒቨርስ ያልተወሰነ ነው እንዲሁም የሰው ዕውቀት የመሐንዲሱ ዕውቀት ነገሮችን አፅንቶና አረጋግቶ ቤት ይሠራል በተመሳሳይ ሁኔታ ያለ አስከሳች ኃይሉ ዕውቀት ተፈጥሯዊ ህንፃ ዩኒቨርስ ተረጋግቶና ፀንቶ ሊኖርና ሊገነባ አይችልም ዩኒቨርስ የአስከሳች ሃይሉ ክፍልና በአስከሳች ፃይሉሱ ዕውቀት ወይም ፎርሙላ የመጣ ነው አስከሳች ፃይሉ አካላዊ ወሰን አልባነት ያለው ብቻ ቢሆን ዩኒቨርስ ህዋና ምድር አስቀድሞ አካላዊ ወሰን አልባ ስለሆነ በዚህ ላይ ሌላ ወሰን አልባ አስከሳች ሃይል ቢኖር እኩል ይሆናል እንጂ የሚበልጠው አይሆንም ስለዚህ አስክሳች ፃይሉ ከአካላዊ ወሰን አልባነት ያለፈ የበላይነት ኖሮት ዩኒቨርስን የራሱ አንድ ክፍል እንዲያደርግ መንፈሳዊ ዕውቀታዊ ጥበባዊ ወሰን አልባነት ሊኖረው ያሻል በጥበብና በመንፈስ በልጦት አንድ ክፍል ሲያደርገው ዩኒቨርስን እንዳስከሰተው እንረዳለን የፊዚክስ ሕግ ቢኖርም በመሐንዲሱ አማካይነት ጥቅም ላይ ካልዋለ ህንፃባ አይገነባም ዩኒቨርስን ማስገኘት መፍጠር የሚችሉ ቀመሮች በተፈጥሮ ቢኖሩም በአንድ አዋቂ ቀማሪ ጥቅም ላይ ካልዋሉ ተፈጥሯዊ ህንፃን ዩኒቨርስ ሊገነቡ አይችሉም ዩኒቨርስ በአስከሳች ፃይሉ ቀመር ከአስከሳች ሃይሉ የተወሰነ ክፍል ተፈጥሮ አስከሳች ፃይሉ ላይ የሚኖር መሆኑን የለውጥ መርህ የማይቀየር መሆኑ ያስረዳናል የዩኒቨርስ አፈጣጠር ስንገምት ከአስከሳች ፃይሉ የተነገሩ ቃላት የአስከሳች ፃይሉሱ አንድ ክፍል ላይ የዚሁ ዛይል ቀመር ተደምሮበት እሱ ላይ የሚኖር ሌላ የአስከሳች ዛይል ክፍል ዩኒቨርስ ሲሰራ ሲፈጠር ብናስብ እንደ አንድ ምሳሌ ልንወስደው የምንችለው ሁኔታ ነው ዩኒቨርስን ያስክሰተ አስከሳች ሃይል ራሱን ወደ ዩኒቨርስነት በአዝጋሚ ወይም በቅፅበታዊ ለውጥ አይቀይርም ሰው በተፈጥሮው አዋቂ ፍጡር ስለሆነ ማሰብ ስለሚችል ራሱን የሚያጠፋው ካበደ ወይም አደጋን ለማስወገድ ሲፈልግ ነው ስለ አስከሳች ፃይሉ ዕውቀት ተከታዩ አጭር ማጠቃለያ ይዚል «አንዳንድ ጊዜ አስቸጋሪ የማይፈታ ጥያቄ ነገር ወይም ጉዳይ ሊያጋጥም ይችላል ይህ ሲሆን የተለያዩ መንገዶችና አማራጮችን ተከትለን ጉዳዩን ለማቃለል እንሞክራለን ቢያንስ ስለ ጉዳዩ ወይም ችግሩ ማስብ መገንዘብ ማየት እንችላለን ነገር ግን ስለአስከሳች ኃይሉ ያለን ግንዛቤና እውቀት ከዚህ በጣም የተለየ ነው ስለእሱ የምናውቀው ዩኒቨርስን ማስከስቱን ከእኛ እውቀት አንጻር ሲታይ አራሱን በራሱ ያኖረ መሆኑን ነው በግማሽ ወይም በጥቂት ሙከራ እሱን ማየትና የሆነ ቀመር ፎርሙላ በመጠቀም ልንደርስበት አንችልም በምክንያታዊነት ብቻ ከመንፈሳዊ መረዳት ውጪ ፈልገን ማንነቱን አናገኘውም በአእምሮአችን አልፈታ ካለን ከማንኛ ውም እንቆቅልሽ የበለጠ ከባድ ነው ስለዚህ አስከሳች ኃይሉ ከአእምሮ በላይ ነው እንላለን በዓለም ላይ ያሉ እንቆቅልሾች ከአእምሮአችን በላይ ቢሆነም በዩኒቨርስ ህግና ቀመር ቁጥጥር ስር ናቸው ነገር ግን በራሱ ጽኑ የሆነ አስከሳች ኃይል ከምክንያት ውጤት ህግና ከዩኒቨርስ ቀመር በላይ የሆነ መገኘት ውስጥ ያለ ነው ስለዚህ እሱን በዓለም ላይ ከከበደንና ካስቸገረን ነገር ጋር አኩል ማድረግ የለብንም ከዚህ ነገር በእጅጉ ይከብዳል ይህ አስከሳች ኃይል እንደ ሰው በዩኒቨርስ ቀመር አይገዛም ሰው በዩኒቨርስ ቀመር እየተመራ ስለሚኖር ኦክስጅን ካጣ ይሞታል አስከሳች ኃይሉ ግን እንደዛ አይደለም ስለዚህ አስከሳች ኃይሉ ከሰው የበለጠ ጥበበኛና አዋቂ ነው በራሱ ፀንቶ ኖሯል ምክንያቱም አርሱ ከማንኛውም በዩኒቨርስ ቀመር ከሚኖርና ከሚተዳደር ነገር በላጭ ነው ሰው ዩኒቨርስ ከሌለ መኖር አይችልም አስከሳች ኃይሉ ግን ይትላል ምክንያቱም በዩኒቨርስ ሀልዎት ላይ አልተደገፈምና ነው ይህችን ዩኒቨርስና ቀመሮቿን ያስገኘ አስከሳች ኃይል ከሰው የበለጠ ጥበብ ያለው ነው ደግሞም በለውጥ መርህ ወሰን አልባው ዩኒቨርስ የአስከሳች ኃይሉ ክፍል መሆን የሚችለው አስከሳቹ የበለጠ ጥበብ እውቀት ፍላጎት መንፈስ ወዘተ ኖሮት ይህንን አካላዊ ወሰን አልባነት ያለውን ዩኒቨርስ አንድ ክፍል ሲያደርገው ስለሆነ የምድርና ህዋ አስከሳች ኃይል የላቀ ጥበብ ያለው ነው ዩኒቨርስን ለመገንባት ለመሥራት የተጠቀመባቸው ቀመሮች ያለ አዋቂ ጥበበኛ ቀማሪ ዩኒቨርስ የተባለውን ተፈጥሮአዊ ህንጻ ይገነባሉ ብሎ ማሰብ ስለሚያስቸግር አስከሳች ኃይሉ የላቀ ጥበብ አለው» አስከሳች ኃይሉ ከሰው የበለጠ ጥበብ አለው አዝጋሚ ለውጥ ከዝቅተኛ የአውቀት ደረጃ ወደ ከፍተኛ አውቀት ደረጃ የሚያሸጋግር ስለሆነ ጥበበኛጡ አስከሳች ኃይል በምንም መልኩ ራሱን ዝቅ በማድረግ ወደኋላ አውቀት ወደ ሰው ዕውቀት ወይም ዕውቀት የለሸ ዩኒከቨርስነት ሊለወጥ አይችልም ምናልባት ዳይኖሰር የተባለ እንስሳ ከገፀምድር ጠፍቷል ቢባል ይህ አንዱ የዩኒቨርስ ቅንጣት ክፍል በዩኒቨርስ ቀመር ሕግ የመስተጋብር ሕግ እንደአጠቃላይ የዩኒቨርስ መጥፋት ስላልሆነ የአስከሳች ኃይሉ አንዱ ቅንጣት ጠፍቶ እንኳ ቢሆን የአስከሣች ። በባዶ ነገር ላይ ራሱን ችሎ የመኖር ብቃት ያለው ፈጣሪ ነበር ስለዚህ ዩኒቨርስ ቢኖርም ባይኖርም ባዶ ነገር ላይም ሳይቀር መኖር ይችላል የሰው ጥበብና የአስከሳች ኃይሉ ጥበብ በንጽጽር ሲታይ ብዙ ጊዜ ያላየነው አስከሳች ሃይል አንዴት ይፄን ትልቅ ወሰን አልባ አካል ዩኒቨርስን ይፈጥረዋል ብለን እንጠይቃለን መልሱ ኢንጂነር በዕውቀቱ ከዩኒቨርስ ማቴሪያል ተጠቅሞ የሚታይ ህንፃ ከሠራ የማይታየው አስከሳች ኃይል በማይታይ ዕውቀቱ ዩኒቨርስን ቢሠራ ምን ያስገርማል። ስለዚህ ታላቁ ጥበብ አለ እሱም ፈጣሪ ነው ምክንያቱም የለውጥ መርህና ማንነቱ አረጋግጦልናል የፍቅር አስተሣሠብ ይህ የዩኒቨርስ ህዋና ምድር የሚታዩ እና የማይታዩ ነገሮች አፈጣጠር መላ ምት ከነፔ ነው ወይም በአጭሩ ስለዓለም አመጣጥ ግምት ሊሰጥ የሚችል ነው ሀ የፍቅር አስፈላጊነት ፍቅር ሲሞት ያለውን ማንነቱን በሰጠ ጊዜ ሌላ አኩል የሆነ ፍቅር እምኃበ አልቦ ባዶ ነገር ላይ ይፈጥራል ፍቅር ሁልጊዜ ሕያው ነው ፍቅር ሞተ ማለት ያለውን ማንነቱን አሱነቱን ለሌላ ሰጠ ማለት ነው ፍቅር ደግ ከመሆኑ አንፃር ሌሎች ፍጥረቶች የሚያልፉበትን የዕድገት ደረጃ ለመጋራት ሲል ሳይሞት ራሱን ሳይሰጥ የተወሰነ ጊዜ ይቆያል ይህ የመቆያ ጊዜ የህያውነቱ ጊዜ ይባላል በህያውነቱ በአድገቱ በመቆያው ጊዜ ፍቅር ነፀብራቆችን ይሠራል በሞተ ጊዜ ደግሞ እኩል የሆነ ንጹህ ፍቅር ያስገኛል ህዝቦች አገሮችና ሰዎች በፍቅር በትብብር እና በመረዳዳት አብረው ይኖራሉ ፕላኔቶች መስመራቸውን ይዘው ባይጓዙ ወይም ፍቅር ጠልተው ቢጋጩ ኖሮ ምድር ትደረማመስ ነበር አኛም አንጠፋ ነበር ተከባብሮና ተፋቅሮ መኖር ህይወት ያለውም ሆነ የሌለው ፍጥረት ሕልውና መሠረት ነው አንዳንድ ጊዜ ግጭት እንኳ ቢነሳ ለቀጣዩ የሰዎችና የሕዝቦች ግንኙነት የበለጠ ፍቅር ለማምጣት ችግር ፈጣሪውን አስጊውን ለማስወገድ ተብሎ የሚደረግ ነው ግጭት በዳዩን በማስወገድ ተበዳዮች ፍቅራቸውን የበለጠ ለማሳደግ የሚፈጽሙት ተግባር ነው ግጭት የተከበረውን ፍቅር የበለጠ ለማጠናከር የሚደረግ ጥረት ነው ይህ ዓለም ህዋና ምድር ያለፍቅር መኖር ካልቻለ ማንነቱ ፍቅር ከሆነ ምናልባትም የፍቅር ነፀብራቅና ውጤት ሊሆን ይችላል ለ ጠጣር ፈሳሽ ጋዝ ጊዜ ሁኔታዎች የተባሉትና ነፀብራቆች እንዴት ተፈጠሩ። ግምታዊ መላ ምት እንዳልነው ፍቅር ሁለት ሂደቶች አሉት የሕያውነት እና የሞት ሂደቶች በሕያውነት ጊዜው ነፀብራቅ ርበርርአ ብቻ ይፈጥራል ከዝቅተኛው አስከሞት ጊዜው ፍቅር ጊዜ ሁኔታ ጠጣር ፈሳሽ ጋዝ የተባሉ ነፀብራቆችን ይፈጥራል ሒ የፍቅር ዘላለማዊነት ሳያቋርጥ መባዛት ፍቅር ባዶ ነገር ላይ የመኖር ብቃት አለው ሞቶ አያለ ህያው ነው ወደ ባዶነት በሞት የተቀየረ ሲመስለን እንኳ ፍቅር ግን ሌላ ፍቅር ፈጥራል ይህ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት በመጀመሪያ ሊኖር የሚችለው ወይ ባዶ ነገር ነው ወይም የሆነ ነገር ነው ባዶ ነገር ኖሮ ከሆነ በሱ ላይ ፍቅር የመኖር ብቃት ስላለው ፍቅር ነበረበት ማለት ነው የሆነ ነገር ከነበረ ደግሞ ይህ የሆነ ነገር የፍቅር ነጸብራቅ ነበር ያ ማለት ከዚያ በፊት ፍቅር መኖሩን እና ነጸብራቅ መፍጠሩን ያሳያል ማለት ነው ያ የሆነ ነገር መቅ የአየር ኳስ ከ ር ወይም ሌላ ሊሆን ይችላል የነፀብራቅ መኖር የፍቅር መኖርን ያስረዳል አሜባ ራሱን ከፍሎ በመራባት ክ ይባዛል ይራባል ፅ አሜባን በማይክሮስኮፕ ማየት እንችላለን ፍቅርን ግን አናየውም የምናየውና የሚሞተው አሜባ ራሱን በመክፈል በሞት ካባዛ እንዴት የማይታየው ፍቅር በሞት ራሱን እያባዛ ለዘላለም አይቀጥልም እፉኝት በመሞቷ ብዙ ልጆች ከወለደች እንዴት የማይታየው ረቂቁ የማይሞተው ፍቅር በሞት ራሱን አያባዛም ፍቅር ሲሞት ሌላ አኩል የሆነ ወንድም ፍቅር ይፈጥራል ይህ የተፈጠረው ወንድም ፍቅር ደግሞ የሕያውነቱን ጊዜ ጨርሶ ሲሞት ሌላ እኩል ፍቅር ወንድም ፍቅር ይፈጥራል መጪውም ፍቅር እንደዛው ሳያቋርጥ እየተባዛ ይቀጥላል የፍቅር ነፀብራቅ ህዋ ምድር ጊዜ ያልተወሰኑ የማያልቁ የሆኑት ፍቅር ለዘላለም ስለሚባዛ ነው የፍቅር ተፈጥሮው ሌሎችን መውደድ ነውወ ፍቅር ከሞተ ደግሞ ሌሎች የሚወዳቸውን ሊያጡ ነወ ስለዚህ ሌሎች ፍቅር አንዳያጡ በማሰብ ለዘለዓለም ይኖራል አንድ ሰው ለሌላው ቢሞት በሕይወት ያለው ሰው ሊኖር የቻለው ሟቹ ስለሞተለት ነው በሕይወት ያለው ሰው ለሌላው መሞትን ተምሯል ሟቹ በመሞቱ በሕይወት ያለው ሰው ውድድር ቀርቶለት በደስታ ይኖራል የአፍቃሪ መሞት ፍቅርን መድፍ ጋመ መመው። ፍቅር በሰው ሞት የሚጨምር ከሆነ የማይታየው ፍቅር በባዶ ነገር ወይም በሞተ ነገር ላይ የመኖር ብቃት ቢኖረው ምን ይገርማል መ ጊዜ እንዴት ተፈጠረ። ጊዜ ከፍቅር ጋር አብሮ የሚሠራ ጓደኛ ነበር ፍቅር ምንም ነገር ላይ ባዶ ነገር ላይ ስለሚኖር ጊዜም አብሮ ነበር ፍቅር ሁልጊዜ እየተራባ ስለሚኖር ለመራቢያ ለመባዣ ጊዜን ይጠቀም ነበር ጊዜ በምቾት በደስታና በሰላም ከፍቅር በተሻለ ሁኔታ ይፈሳል ጊዜ የፍቅር ነፀብራቅ ነው ፍቅር ለመሞትና ለሕያውነቱ ቆይታ የተጠቀመበት ጊዜን ነው ጊዜ ከሌሎች ነፀብራቆች ቦታ ምድር ሕዋ ሁኔታ ጋር አብሮ ይሠራል ስለዚህ ጊዜ ፍቅርን አንተ ከኔ ጋር እየሠራህ እኔን ብቸኛ አደረከኝ ብሎ ሊከሰው አይችልም ፍቅር ላንተም እኮ ቦታና ሁኔታን በነፀብራቅ በርርቨ ፈጥሬልፃለሁ ይለዋል ሠ የፍቅር እውቀት ሁሉም ነገሮች የአሱ ነፀብራቅ ስለሆኑ ፍቅር ስለሁሉም ያውቃል ስለጊዜ ቦታ ሕዋ ወዘተ ያውቃል ቀዳሚ ፍቅር ፍቅር ለዘላለም ስለሚኖር ቀዳሚ ፍቅር የሚባል የለም ቀዳሚ ፍቅር የተባለው ለአነጋገርና ለመግባባት ተብሎ ነው ከሚባዛው ወንድም ፍቅር እኩል ስለሆነ የትናንቱንም የአሁኑንም የወደፊቱንም እኩል እውቀት አለው ፍቅር ራስ ወዳድ አይደለም ራስ ወዳድ ቢሆን ኖሮ ራሱን ብቻ ባየ ነበር ራስ ወዳድ የሆኑ ፍጡሮች እራሳቸውን ብቻ እንጅ ሌላውን ማየት አይወዱም ነገር ግን ፍቅር ራስ ወዳድ ስላልሆነ ነፀብራቅ ፈጥሮ እነሱን ይመለከት ጀመር ነፀብራቆች ፈሳሽ ጠጣር ጋዝ ጊዜ ሁኔታ ሕዋ ምድር ወዘተ ለምን ፈጠርከን ሊሉ አይችሉም ምክንያቱም ሁሉም ውስጥ የፍቅር ሕያውነት ማንነት ስጦታ ስለአለና አሱ ሳያቋርጥ እየሞተ እያለ እነሱ ግን ፀንተው ያለሞት ስለሚኖሩ በተሻለ ምቾትና ደስታ ያሉ ስለሆነ ፍቅርን መክሰስ አይችሉም አንዱ ነፀብራቅ ከሌላው ጋር የመደጋገፍ መረዳዳትና መስተጋብር የፈጠረው ሁሉም ውስጥ የጋራ ፍቅር ስላለ ነው ስለዚህ ሁሉም ነገር ውስጥ የፍቅር ማንነት ስለአለ ፍቅር ሁሉን አዋቂ ሲሆን እየተባዛ ሰለሚቀጥል ለዘለዓለም ኗሪ ነው ምዕራፍ ሦስት ዘለዓለም የዘለዓለም ሕይወት እውነት ወይስ ተረት። የዘላለም ሕይወት አለ ወይስ የለም የሚለው እግዚአብሔር አለ ወይስ የለም አንደሚለው እኩል አጠያያቂና ከባድ ጥያቄ ነው ሁለቱ ጥያቄዎች ተያያዥነት አላቸው ስዎች የሰማዩን ማን አየው በማለት በኃይማኖታቸውም ሆነ በኑሯቸው ከሞት በኋላ ስላለው ሕይወት እርግጠኛ ባለመሆናቸው ከምክንያታዊነት አንፃር ይህንን ጉዳይ ለማስረዳት መሞከሩ ተገቢ ሆኖ ተገኝቷል የነፍስና የመንፈስ የማወቅና የመረዳት ችሎታ መርህ የሰው ልጅ ዩኒቨርስ ህዋና ፕላኔቶች ወይም ጊዜ ሳያቋርጡ ለዘለዓለም እንደሚቀጥሉ ማስተዋል ይችላል ሰው ማወቅና መገንዘብ የሚችለው በነፍስና በመንፈሱ ነው በሥጋው ማወቅ ቢችል ኖሮ ነፍስና መንፈሱ ከተለዩት በኋላ ሥጋ ዕውቀት ሲኖረው እናይ ነበር ተፈጥሯዊ ወይም ልማዳዊ ዕውቀት እንደሚነግረን ስለ አንድ ነገር ወይም ሰው ማወቅና መረዳት የሚቻለው ከእርሱ ጋር አብረን ስንኖር ወይም ግንኙነት ማድረግ ስንችል ነው የኛ ነፍስና መንፈስ በአርግጠኛነት ጊዜ የማያቋርጥ ዘለዓለማዊ መሆኑን ወይም ዩኒቨርስና እንቅስቃሴው ዘለዓለማዊ መሆኑን ያውቃሉ ታዲያ የሰው ነፍስና መንፈስ ከሞት በኃላ ለዘላለም የማይኖሩ ወይም ግንኙነት የማይኖራቸው ከሆነ እንዴት ስለጊዜ ወይም ዩኒቨርስ ዘላለማዊነት ሊያውቁ ቻሉ።