Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሰማያዊ አባታችንን እንወቅ ጽዮን የሞተ ልጅዋን ሬሣ በክንዶችዋ ታቅፋለች ስለዚህ በዚህ ከባድ በሆነ ኀዘንዋ ጊዜ ሊያጽናናት የሚችል ማን ነው። የቤተ ክርስቲያንን መሪዎች የሚመርጠውም እግዚአብሔር ነው ዳን እግዚአብሔር በተዘዋዋሪ መንገድ የሚቆጣጠራቸው ሌሎች ነገሮችም አሉ እግዚአብሔር ሕፃናቶቻችንን በቀጥታ አይገድልም ወይም ኃጢአት እንድንሠራ አይፈትነንም ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ራሱን ከገለጠበት ውጭ የሚደረግ እግዚአብሔርን የማወቅ ሙክራ ከቃሉ ጋር ስለማይስማማ አሳቡ ሰው ሠራሽ አሳብ ይሆናል ደግሞም ጣዖት ነው። እርሱ ከሁሉ በላይ ለእኛ ጥቅም የሚሆነውን ሁሉ ያውቃል የልጅ ሞት ወይም የአስከሬናችን መበስበስ አርሱን አያስደንቀውም ሁለተኛ እግዚአብሔር በሁሉ ኃያል ነው።
እግዚአብሔር እኛ በትክክል የእርሱን ማንነት አውቀን ወደ እርሱ እንድንቀርብ ይፈልጋል ስለዚህም አግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ አማካይነት ራሱን ለእኛ ገለጠ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ማንነትና አም ሳል እንዲሁም አንዴት ወደ እርሱ መቅረብ የምንችልበት ብቸኛው የእው ቀት ምንጭ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ቀጥተኛው የአግዚአብሔር ሥራ ውጤት ነው የሰው ልጆች ሊያውቁት የሚገባቸውን እንዲጽፉ በሰዎች ተጠቀመ ርኛ ጢሞ ጋ ኛ ሌሴጥ ከ እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ራሱን ምን እንደሚመስል ይገልጻል ለምሳሌ ዘጸ ራ በዚህ ክፍል አግዚአብሔር ለፈጠረው ሰው ከእርሱ ጋር ሊኖረው ስለሚገባው ግንኙነት ይነግረዋል ስለዚህ እግዚአብሔር ሰው አርሱን አውቀን ብቻ የራሳችንን ጥረት እንድንከተል አልተወንም ነገር ግን በግልጽ ራሱን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ገለጠ ስለዚህ አማኞች ሊፈጽሙት የሚገባው አንዱና ጠቃሚው ነገር እግዚአብሔርን የበለጠ ሊያውቁት እንዲችሉ መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄ ማጥናት ነው ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው የሕይወቱ ዋና ዓላማ ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ነው ፊልጵ ታዲያ እግዚአብሔርን እንዴት ልናውቀው እንቸላለንሃ እዚህ ላይ ትምህርት ለማግኘት ትኩረታችንን በአግዚአብሔር ፍጥረታት ላይ ማድረግ ይኖርብናል እነዚህንም ፍጥረታት ለእግዚአብሔር ፍቅራዊ ቸርነትና ለኃያልነቱ ምሥጋና ማቅረቢያ አድርገን ልንጠቀምባቸው እንችላለን መዝ ሆኖም ከሁሉ በላይ እግዚአብሔር ስለ ራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚነግረንን እውነት በጥንቃቄ ማጥናት አለብን የዚህ አነስተኛ መጽሐፍ ዓላማም እግዚአብሔር ስለ ራሱ ከገለጣቸው እውነቶች ጥቂቶቹን ሰብሰብ አድርጐ ማቅረብ ነው እግዚአብሔር ስለ ራሱ የገለጠውን እውነት ሳናውቅ ብንቀር ጣዖትን እናመልካለን ይህ ደግሞ ከዓለም ይዘን የመጣነውና ስለ እግዚአብሔር ያለን የተሳሳተ አመለካከት ነው በአንጻሩ ስለ እግዚአብሔር ማወቅን ችላ ብንል ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔርን እንደሚገባን ልንወደው አለመፈለጋችንን ነው ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር በሰፊው የሚያስተምረን ቢሆንም እግዚአብሔር ታላቅ ከመሆኑ የተነሣ ሙሉ በሙሉ ስለ እርሱ ለማወቅ አንችልም እግዚአብሔር ከምናውቃቸው ነገሮች በላይ የላቀና የተለየ ስለሆነ ሰዎች እንደ መሆናችን ሙሉ በሙሉ ልንገነዘበው አንችልምጸ በጣም እሩቅ ያሉ ከዋክብት ከመሬት ምን ያህል እሩቅ እንደሆኑ እንደሚነገረን ሳይንቲስቶች ብዙ ቢሊዮን ኪሎ ሜትር ነው ይላሉ እንዲሁ እግዚአብሔርና የእርሱ አሳብ ከምናውቀው ነገር ሁሉ በላይ ነው ኢሳ እንዲሁም ኢሳይያስ «በእውነት አንተ ራስህን የምትስውር አምላክ ነህ» ይሳል ኢሳ ያልተጠበቁ ክስተቶች በሚሆኑበት ጊዜ ይህን ቃል ማስታወስ ይገባናል እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ የሚቆጣጠር ስለመሆኑ ጥርጣሬ በሚሰማን ጊዜ የእግዚአብሔር ድርጊት ምሥጢር መሆኑን ማሰብ አለብን ስለዚሀ አግዚአብሔር አንዳንድ ነገሮችን በምን ምክንያት በራሱ መንገድ እንደሚያደርግ ሙሉ በሙሉ የመገንዘብ ችሎታ ሊኖረን አይችልም እንግዲህ በእምነት መኖር ማለት አንዳንድ ነገሮችን በምንፈጽምበትና ምሥጢሩ ከአቅማችን በላይ በሚሆንበት ጊዜ እንኳን አፍቃሪ የሆነ አምሳካችንን ያለማቋረጥ ማመን እንዳለብን ነው እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል መሠረታዊ ትምህርቶች እግዚአብሔር እኛ ከምናውቀው ነገር በጣም የተለየ ከሆነ ታዲያ ስለ ራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለእኛ የገለጠው ምንድን ነው። ያ ኃይልም በእነርሱ ፈንታ ሆኖ ማንኛውንም ነገር እንዲፈጽምሳቸው ትክክለኛውን ቃል መናገር እንዳለባቸው ወይም የተወሰነ ተግባር መፈጸም እንደሚኖርባቸው ይስማቸዋል መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን እግዚአብሔር ሕያውና የሚሠራ አምላክ ነው ስለዚህ እግዚአብሔር ያስባል ያቅዳል ያደርጋልም ቨጉ ኤር መዝ ዕ እግዚአብሔር የመውደድና የመጥላት ስሜት አለው ኢሳ ዘኳ ራ ከጺ ቱ« ልክ ሰዎች እርስ በርሳቸው እንደሚነጋገሩት ሁሉ እኛም እርሱን ልናነጋግረው እንችላለ ዳሩ ግን አንዳንዶቻችን እግዚአብሔርን ሕያው እንዳልሆነ ኃይል አድርገን በመገመት በዚህ አስተሳሰብ ውስጥ እንወስነዋለን እንዲያውም አንዳንድ ክርስቲያኖች የሆኑ ቃላትን በትክክል በመናገር እግዚአብሔርን መቆጣጠር የሚችሉ ይመስላቸዋል አንዳንዶች የኢየሱስን ስም ደጋግሞ መጥራት አግዚአብሔርን አስገድዶ አንድ ነገር እንደሚያደርግላቸው ያስባሉ ወይም በትራሳቸው ሥር መጽሐፍ ቅዱስን ያኖራሉ ወይም ክታብ በአንገታቸው ላይ ያስራሉ ይህንንም የሚያደርጉት እነዚህ ነገሮች ከክፉ እንደሚጠብቋቸው ወይም መልካም ዕድል እንደሚያመጡሳቸው በማሰብ ነው ነገር ግን በራሱ አምሳል የፈጠረን አምላካችን ከእኛ ጋር ማንነት እንዳለው ሕላዌ ሆኖ ግንኙነት ማድረግ ይፈልጋል እርሱም የማሰብ የመናገር የማፍቀርና የመጥላት ባሕርያትን ሰጥቶናል በእነዚህ ባሕርያት አማካይነትም ከእርሉ ጋር እንገናኛለን ሐቁ ይህ ሆኖ ሳለ እኛ ችላ ስንለውና በምናደርገው ተግባር እርሱን ልንቆጣጠረው ስንጣጣር በጣም ያሳዝነዋል እግዚአብሔር ቅዱስ ነው በጠጺ ኛ ሳሙ ኢሳ ዘሌዋ በ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ባሕሪ «ቅዱስ» ይለዋል አንዳንድ ምሑራን ይህ የእግዚአብሔር ባሕሪ የሌሎች ባሕሪዎቹ መሠረት ነው ይላሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቅዱስ የሚለው ቃል ሁለት ትርጉሞች አሉት አንደኛው መለየት ወይም ልዩ ሆኖ መገኘት ነው ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ቅዱስ ብሎ ሲጠራው እግዚአብሔር በሰማይና በምድር ካሉት ፍጥረታት ሁሉ የተለየ ነው ማለት ይሆናል በዚህ ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር የሚመሳሰል ምንም ነገር የለም የአንዳንድ እምነት ተከታዮች የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ ተከታዮች እግዚአብሔር በሁላችን ውስጥ አለ ስለዚህ ሁላችንም አማልክት ነን ይላሉ መጽሐፍ ቅዱስ ግን ከዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ጋር አይስማማም ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ዘላለማዊው አምላክ ከሰዎች ሁሉ የተለየና ታላቅ መሆኑን ይመሰክራል ኢሳ መዝ በ እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ አስቀድሞ የነበረ አምላክ ነው እርሱን የፈጠረ ሌላ አምላክ ወይም ኃይል የሰለም እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረ በኋላ በዙፋኑ ላይ ሆኖ ዓለምን በመላው እየተቆጣጠረ ይገኛል ፍጥረታት በሙሉ ከእርሱ ጋር ሲመዛዘኑ ኢምንቶች ናቸው ኢሳ ሕይወት ሁሉ በእርሱ ሆነ የሐዋ እግዚአብሔር ታላቅና ከፍጥረታቱም ውጪ የመሆኑ ነገር አያሌ ጠቃሚ ነገሮችን ያሳስበናል ሀ እግዚአብሔር ቅዱስ የተለየ ታላቅና አቻ የሌለው ስለሆነ እንድንፈራው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተደጋግሞ ተነግሮናል በፊቱም ትሑታን አንድንሆን እርሱን በመፍራት በፊቱ እንድንቆም እንዲሁም በፊቱ በታዛዥነት አንድንሰግድለትና እንድናመልከው ያስፈልጋል መዢዐ ራእይብ በእግዚአብሔር ፍቅር ላይ ብቻ በምናተኩርበት ጊዜ አርሱ ሁሉን ቻይ አምላክ እንደሆነና እኛም ፍጥረቱ መሆናችንን አንዘነጋለን በእግዚአብሔር ወዳጆነታችን ላይ ብቻ በምናተኩርበት ጊዜም ስለ እርሱ የሚኖረን አስተሳሰብ የቀለለ ይሆናል ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ታላቅና ኃያል እንደሆነ እንዲሁም ክብርና ሞገሥ እንዳለው ያስተምረናል በፊቱ ልንንቀጠቀጥ ይገባናል ዐኛ ዜና አምልኮአችን ምሥጋናን ብቻ ሳይሆን በታላቁ እግዚአብሔር ፊት የምንቆም መሆናችንንም ማጠቃለል አለበት የዕብራውያን መልእክት እንደሚያስጠነቅቀው «እግዚአብሔር የሚያጠፋ እሳት ነው» ዕብ ለሌ ከእኛ ይልቅ እግዚአብሔር ከፍ ያለ መሆኑን ማስተዋል ይገባናል ማንኛውም ነገር ለእርሱ ክብር እንጂ ለእኛ አይደለም ደኅንነታችንም ቢሆን ለእግዚአብሔር ክብር ነው ኤፌ ብ ስለዚሀ እኛ ራሳችን ምኞታችን ዕቅዶቻችን ወይም ግቦቻችን ለእኛ ከሁሉ የበለጡ ናቸው ብለን ከማሰብ መጠንቀቅ አለብን። እጅግ ከፍተኛውን ሥፍራ የሚይዘው እግዚአብሔርና ከብሩ ነው እግዚአብሔርን በምናመልክበት ጊዜ ወይም ሰውን ወደ ክርስቶስ በምናመጣበት ጊዜ እኛ ሳንሆን እግዚአብሔር የሚከበርበት እንደሆነ እርግጠኞች መሆን አለብን እግዚአብሔር የራሱን ክብር አሳልፎ ለሌላ መስጠትን አይፈቅድም ኢሳ ሐ በጎውንና ክፉውን መወሳን የእግዚአብሔር ሥልጣን ነው እኛ የምንኖርበትን ደንብ አናወጣም ይልቅስ እርሱ እንዴት መኖር እንዳለብን ይነግረናል የርሱ የሚወደን አምላክ እንደ መሆኑ እነዚህ አዛዛት ሁልጊዜ ለጥቅማችን እንጂ ለጉዳታችን አይሆኑም በማንኛውም ጊዜ የራሳችንን ደንብ ስናወጣ ወይም የእግዚአብሔርን ሕጐች ለራሳችን መጠቀሚያ በምናደርግበት ጊዜ እግዚአብሔር የነገሮችና የሁኔታዎች ሁሉ ወሳኝ አምላክ መሆኑን እንዘነጋለን መ እግዚአብሔር ከእኛ ይልቅ ኃያል ከመሆኑ የተነሣ እርሱንም ሆነ መንገዶቹን ሙሉ በሙሉ መገንዘብ አንችልም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተገለጠው ጥቂቱን መማር እንችላለን ነገር ግን ከሆነው ውስጥ አብዛኛው ሳይገለጥ እንደ ተሰወረ ቀርቷል ስለዚህ ድርጊት በምናጉረመርምበት ጊዜ ሁሉ ዘላለማዊ የሆነው ፈጣሪ ከሚያውቀው በላይ ፍጡሩ ይበልጥ ያውቃል ማለታችን ነው ይህ ስሕተት የሆነ አስተሳሰብ ነው ዉጪ የደኅንነትን መንገድ የሚወስነው እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለም የሰው ልጆች ሁልጊዜ የደኅንነትን መንገድ በግለ ጥረታቸው ለማግኘት ይጥራሉ እንደዚሁም እግዚአብሔር እንዲያድናቸው ለማስገደድ አንዳንድ ነገር ለማድረግ ይፈልጋሉ በዓለም ላይ ሃይማኖቶች እንዲህ በዝተው የሚገኙት ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ዘንድ እነርሱ ባዘጋጁት መንገድ ተጉዘው ለመድረስ ስለሚፈልጉ ነው ታዲያ ይህ ሙከራቸው የተሳሳተ መሆኑን ሲነግሯቸው ይቆጣሉ ነገር ግን እግዚአብሔር ታላቅ ልዩና ከፍጥረታት ውጭ በመሆኑ የደኅንነትን መንገድ መወሰን የእርሱ ሥልጣን ብቻ ነው ስለዚህም ነው ኢየሱስ «እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ በእኳ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም» ያለው ዮሒ «ቱ ሁለተኛ ቅዱስ የሚለው ቃል ከኃጢአት ጋር ተያይዞ ቀርቧል መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር በፍጹም ስሕተትና ክፋት ከሆነ ነገር ሁሉ የተለየ መሆኑን ያስተምረናል ያል እርሱ ክፉ የሆነ ነገር ለማድረግ አይፈተንም እግዚአብሔር ክፉ አሳብ የለውም እርሱ ምን ጊዜም ንጹሕ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ አግዚአብሔር ቅርብ መሆኑን ያስረዳል ኤር እግዚአብሔር የትም ይገኛል እርሱ በአንድ ጊዜ በዓለም ባሉ አገሮች ሁሉ ላይ ሊገኝ ይችላል እንደ ወንጌላውያን ወደ ዘላኖች አርብቶ አደሮች ዘንድ ሄደን አብረናቸው ብንኖር እግዚአብሔር አዚያም ለመገኘቱ እርግጠኞች ነን ደግሞም ስደት ቢደርስብን እግዚአብሔር አይለየንም እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር በሚኖሩት ሰዎች ልብ ሁሉ ውስጥ ይኖራል ቢሌ ኢየሱስ ከኃጢአታችሁ የሚያድናችሁ መሆኑን የምታምኑ ከሆናችሁ እርሱ በልባችሁ ውስጥ ይኖራል በካህናታችሁ ልብም ውስጥ ይኖራል በዓለም ዙሪያ በሚኖሩ ልጆቹ ልብ ሁሉ ውስጥ እርሱ ይኖራል ሁላችንም በዚህ ልንበረታታ ይገባናል የትም እንሁን የት በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ እንገኝ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ሮሜ እርሱ ከእኛ የራቀ አይደለም እርሱ ምን ጊዜም ረዳታችን ነው መዝ ስለዚህ እርዳታ ለማግኘት ወደ ጥንት ዝመዶቻችን ቆሌ ወይም ወደ መናፍስት መሄድ የለብንም ደግሞም ጠላታችን የሆነውን ስይጣንን መፍራት አይገባንም ምክንያቱም ከሰይጣን በሳይ የሆነው እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ኤፌ ቆላ ደግሞም ማስታወስ ያለብን ኃጢአት በምንሠራበት ጊዜ እንኳን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር መሆኑን ነው የምናደርገውንም ሁሉ ይመለከታል በምንሰርቅበትም ጊዜ ያየናል በምናመነዝርበትም ወቅት ይመለከታል ስለዚህ ከእርሱ የሚደበቅ ምንም ነገር አይኖርም በኛ ቆሮ ቱ እናንተ የምታደርጉትን እግዚአብሔር አያውቅም ብሎ ሰይጣን እንዳያታልላችሁ በፍጹም ተጠንቀቁ ኃጢአታችሁን ከጓደኞቻችሁ ልትደብቁ ትችላላችሁ ነገር ግን በየትም ስፍራ ከሚገኝ አምላክ ፊት ምንም ነገር ልትሸሽጉ አትችሉም ሦስትነቱ ምሥጢር የሆነ አንድ አምላክ አለ እግዚአብሔር ስለ ራሱ ከገለጣቸው ታላላቅ ከሆኑ ምሥጢራት አንዱና ታላቁ እግዚአብሔር አንድም ሦስትም መሆኑ ነው እንግዲህ ይህ ሁኔታ ከግንዛቤአችን ጋር የማይመጣጠን በመሆኑ ሰዎች ሁሉ ሊገነዘቡት ያልቻሉት ምሥጢር ነው በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የምናነበው አንድ አምላክ እንዳለ ነው በዳግ ማር ብዙ አማልክት የሉም እንዲሁም ሦስት የተለያዩ አማልክትም የሉምራ ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስ የምናመልከው አንድ አምላክ ሦስት አካላት አንዳሉት ይናገራል እነርሱም እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ናቸው ሦስቱም ራሳቸውን የቻሉ ተለይተው በአካል ሦስት የሆኑ ናቸው ሁሉም በእኩልነት አምላክና ሁሉም በአኩልነት አካል ያላቸው ናቸው ምንም እንኳን «ኢየሱስ ብቻ» የሚሉት ክፍሎች ሦስት አካላት የሌሉት አንድ አምላክ ብቻ አለ ብለው የሚያስተምሩ ቢሆኑም በአዲስ ኪዳን ውስጥ እንደሚገኘው የእውነት ቃል ግን እግዚአብሔር አብ ኦግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሁሉም አምላክ ናቸው እግዚአብሔር እንዴት አንድም ሦስትም እንደሚሆን አናውቅም ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ይህን ስለሚያስተምር በእምነት ልንቀበለው ይገባናል ኛ ቆሮ ማስታወሻ ስለዚህ ርእሰ ጉዳይ «ኢየሱስ ክርስቶስ» እንዲሁም «መንፈስ ቅዱስ» በተባሉ ሴሎች መጻሕፍት ውስጥ እንማራለን እግዚአብሔር ታላቅና ኃያል አምላክ ነው ቀደም ባለው ትምህርታችን ላይ እግዚአብሔር ቅዱስ ስለመሆኑ ተምረናል እርሱ በዓለም ላይ ካሉት ነገሮች ሁሉ የተለየ ነው በአእምሮአችን ውስጥ ጣዖትን የምንቀርጸው እግዚአብሔርን በእኛ ምሳሌ በማሰብ ነው በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር ለኃይሉ ወሰን የሌለው ሆኖ ተገልጂል ከዚህም ባሻገር ከእግዚአብሔር የታላቅነት ባሕሪ የሚወጡ ብዙ የተለያዩ ባሕርያት አሉ ሀሁ እግዚአብሔር የሕይወት ሁሉ ምንጭ ነው መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚመሰክረው ነገሮች ሁሉ ካለመኖር ወደ መኖር እንዲመጡ ያደረገው እግዚአብሔር ነው ዕብ ሰይጣንን ጨምሮ የመናፍስትን ዓለም የፈጠረ እርሱ ነው የምናየውን ዓለም በሩቅ ያሉትን ክዋክብት ጨምሮ የፈጠረ እርሱ ነው ሕይወት ያላቸው ሁሉ በሕይወት ለመኖር የአርሱን እንክብካቤ ይሻሉ የየሐዋ እግዚአብሔር «ኑር» በሚልበት ጊዜ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ በአንጻሩ ደግሞ እግዚአብሔር «ሙት» ሲል ይሞታሉ መዝ በዐብ ነገር ግን እግዚአብሔር ለመኖር የማንም ድጋፍ ወይም እንክብካቤ አያስፈልገውም የእኛንም ድጋፍ አይሻም። እርሱ ምንም ነገር አያስፈልገወም የተፈጠሩ ነገሮች ሁሉ ሕልውናቸው ቢጠፋ እግዚአብሔር ግን ይኖራል በጤና ለመኖር የምንተነፍሰው አየር እንደሚያስፈልገን ሁሉ እኛም ሆንን ሴሎች ፍጥረታት ለመኖር እግዚአብሔር ያስፈልገናል ነገር ግን የሚያሳዝነው ነገር በእግዚአብሔር በመታመንና በአርሱ ላይ በመመርኮዝ ፈንታ ብዙ ጊዜ ችላ እንለዋለን በምንታመምበት ጊዜ በመጀመሪያ የምናደርገው ወደ ሐኪም ወይም ወደ ጠንቋይ ፄዶ አርዳታ መፈለግ ነው እግዚአብሔር በሽታን ለመፈወስ መድኃኒት ይሰጣል ነገር ግን ሕይወታችንን ለማትረፍም ሆነ ደስታ ለማግኘት ሐኪምን ወይም ወዳጃችንን ወይም ወላጆቻችንን ብናስቀድም የፈውስ ዋስትናችንን በእግዚአብሔር ላይ አላደረግንም ማለት ነው እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ በሕይወታችን ላይ ችግርን የሚያመጣብን እኛ ምን ያህል በእርሱ እርዳታ ላይ እንደምንመረኮዝ ሊያሳየን ነው የጸሎት ዋና ዓላማ ከእግዚአብሔር ዘንድ አንዳች ነገርን ለማግኘት አይደለም ጸሎት የምናደርገው በነገር ሁሉ አለኝታችን እግዚአብሔር መሆኑን ለመግለጽ ነው ለ እግዚአብሔር ኃያል አምላክ ነው ብዙ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከምናገኛቸው የአግዚአብሔር መጠሪያዎች ውስጥ አንዱ «ሁሉን ቻይ» የሚለው መጠሪያ ነው መዝ ኢሷ ራ ይህ የእግዚአብሔር ባሕሪ የሚነግረን እግዚአብሔር ሁሉን ነገር እንደሚያደርግ ነው እርሱ ወሰን የሌለው ኃይል አለው ለእርሱ የማይቻል ነገር የለም ዘኳ ሉቃስ ማቴዎስ እርሱ ተአምረኛ አምላክ ነው ስለዚህ ለሰው ልጆች አስቸጋሪ የሆነውን ሁሉ እርሱ በቀላሉ ያደርጋል እግዚአብሔር ኃይል ሁሉ ስላለው በምድር ላይ ዕቅዶቹን ለማደናቀፍ የሚችል ምንም ዓይነት ኃይል አይኖርም ምንም እንኳን ሰይጣን ኃይለኛ ቢሆንም ሁልጊዜ ግን በአግዚአብሔር ቁጥጥር ሥር ነው ኢየብ ኹ ኃይለኛና ክፉዎች የሆኑ ምድራዊ መሪዎችም በእግዚአብሔር ቁጥጥር ሥር ናቸው ምሳሌ ወደ ሕይወታችን ጉዳትን የሚያመጡ እንዲሁም ክፋትን የሚያደርጉብን ሰዎች ሳይቀሩ ሁሉም በእግዚአብሔር ቁጥጥር ሥር ናቸው እግዚአብሔር ለሰዎች ምርጫዎችን ሰጥቷቸዋል ፍርድ የሚያመጣባቸውና የሚቀጣቸውም ወይም በሠሩት መልካም ሥራ ዋጋ የሚሰጣቸው በዚህ ምርጫቸው መሠረት ነው ታዲያ ክፉ ቢመርጡም እንኳን የሚገኙት በእግዚአብሔር ቁጥጥር ሥር ነው እግዚአብሔር መጥፎውን ሁኔታ ለእርሱ ክብር ሊጠቀምበት ይችላል ለምሳሌ ስለ ዮሴፍ መመልከት ነው ዘፍጥ እግዚአብሔር ሊቁጣጠረው የማይችለው ምንም ዓይነት ሁኔታ ወይም ክስተት የለም እንዲሁም እግዚአብሔር ዕቅዱን ለመፈጸም ከቁጥጥር ውጭ ሊያደርገው የሚችል ኃይል አይኖርም ደግሞ ሊለውጠው አስቦ አልለወጥም ብሎ ከእርሱ ኃይል ውጭ ሊሆን የሚችልና የሚያስጨንቀው ምንም ዓይነት ችግር ሊኖር አይችልም እኛ አንዳች ነገር ክፉኛ በሚጎዳን ጊዜ ማወቅ ያለብን ሁሉን ቻይ አምላካችን ለዓላማው እንደሚጠቀምበት ነው ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያደርጋቸው የማይቻለው አንዳንድ ነገሮች አሉ እነዚህም ከባሕሪው ጋር ተቃራኒ የሆኑ ነገሮች ናቸው ስለዚህ እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ ሊዋሽ አይችልም መዝ ሖ ዕብ ። እዚህ ላይ ብዙ ጊዜ ትኩረታችንን በአግዚአብሔር ፍቅር ላይ በምናደርግበት ጊዜ እግዚአብሔር ኃጢአትን የሚጠላ መሆኑ አይገባንም ደግሞም በአርሱ ላይ በማመጻቸው ምክንያት የጽድቁንና የደኅንነቱን መንገድ የማይቀበሉትን እንደሚቀጣቸው እንዘነጋለን በአንጻሩ ትኩረታችን በቅድስና ላይ ያደላ ከሆነ ደግሞ እግዚአብሔርን ቁጡ ፈራጅ የማይታወቅና ጨካኝ እናደርገዋለን ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ትክክለኛ ፍርድና የእግዚአብሔር ፍቅር ሁለቱም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የደኅንነት መንገድ በመግለጽ ረገድ በአንድነት ይሠራሉ ሲል ያስተምረናል እግዚአብሔር ፍቅር ነው ኛ ዮሒ «ፁ ብዙ ሰዎች እግዚአብሔርን እንደ አፍቃሪ አባት አድርገው በመመልከት ፈንታ እንደ ቁጡ ፖሊስ ይቆጥሩታልነኹ እንዲያው በሰማይ ሆኖ ኋላ ሊቀጣቸው ኃጢአት በሚሠሩበት ጊዜ ዝም ብሎ ቁልቁል እንደሚመለከታቸው አድርገው ያስባሉ ሌሎች ደግሞ እግዚአብሔር በጥፋታቸው እንዳይቀጣቸው የመልካም ሥራ ፍሬአቸውን ለእርሱ ጉቦ ለማቅረብ ይሞክራሉ ያለዚያ እግዚአብሔርን በሩቅ ስፍራ የሚኖር አድርገው ይመለከቱታል በዚህ ሩቅ ስፍራ አየኖረም አንዳንድ ጊዜ ባልተጠበቀ ሁኔታ በሕይወታቸውና በቤተሰባቸው ላይ በሽታ ልኮ እንደሚገድላቸው ወይም ሰብላቸውን እንደሚያበላሽባቸው አድርገው ያስባሉ በሌላ ጊዜ ደግሞ እግዚአብሔር መልካም ነገሮችን ይሰጠናል ስለዚህ ሰዎች ይህን የሚለዋወጥ አምላክ ማመንም ሆነ መገንዘብ ያስቸግራቸዋል የሚገርመው ግን እግዚአብሔር እንደዚህ ያለ አምላክ አይደለም ከዚህ በላይ ስለ እግዚአብሔር የቀረበው አሳብ እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ራሱን ከገለጠበት ሁኔታ ይለያል እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል በሚገልጸው አሳብ ማዕከል ሆኖ የሚገኘው ፍቅር ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአግዚአብሔር የተሰጡ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ተስፋዎች አሉ ለምሳሌ አንደኛው የተስፋ ቃል በኢየሱስ ክርስቶስ ብናምን ወደ መንግሥተ ሰማይ እንገባለን የሚለው ነው ዮሔ ሌላው ተስፋ እግዚአብሔር አይተወንም ችላም አይለንም የሚለው ነው ዕብ እርሱ በችግራችን ጊዜ እንኳን ከእኛ አይለይም እግዚአብሔር እውነተኛ ባይሆን ናርሮ ሁልጊዜም ትክክለኛ የሆነውን ነገር ሳይናገር ቢቀር እነዚህ ተስፋዎችም ለመፈጸማቸው እርግጠኞች መሆን ባልቻልን ነበር ነገር ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ ተስፋዎቹን ይፈጽማል ስለዚህ ይህ ተስፋና በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ የተጠቀሱ ተስፋዎች ሁሉ በእግዚአብሔር የሚፈጸሙ በማይመስሉን ጊዜዎች ሁሉ እንደሚፈጸሙ ባለመጠራጠር አምነን መጠባበቅ አለብን ሔር ምሳሌ ልንሆን እዚህ ላይ እኛም የእግዚአብ ይገባናል ስለዚህ ማንኛውም የግብዝነት ተግባር ማለትም ውሸት እውነትን አጋንኖ መናገርና ለጥቅማችን ስንል ሌሎችን ማታለል ይህ ሁሉ የእግዚአብሔር ባሕሪና እውነትን የመናገር ተቃራኒዎች ናቸው ብዙ ክርስቲያኖች ሊጠቅሙዋችው የማይችሉ ትንንሽ ነገሮችን ይስርቃሉ ይህም በክፍል ውስጥ ከጓደኛቸው መልሶችን ይኮርጃሉ ወይም ከሥራ ቦታ እስክሪብቶ ይወስዳሉ ነገሩ ምንም ያህል ትንሽ ይሁን ድርጊቱ በእግዚአብሔር ፊት ስርቆት ሆኖ ይቆጠራል እንደዚሁም ሰዎች ጥትም ለማግኘት ሲሉ ትንሽ ውሸትን ይናገሩ ይሆናል ወደ ገበያ ፄደው አንድ ዕቃ በአሥር ብር ቢገዙ ለመሸጥ አሥራ አምስት ብር ይጠይቃሉ ይህ ሁሉ ማጭበርበር እውነትን ብቻ በሚናገረው በእግዚአብሔር ፊት በጣም ስሕተት ነው ለሌ እግዚአብሔር ጻድቅና ፍጹም ነው ዘፍጥ ኤር ዘዳግ መዝ ሮሜ እግዚአብሔር ቅዱስና እውነተኛ ስለሆነ የሚፈጽማቸው ነገሮች ሁሉ ሁልጊዜ ትክክለኞች ናቸው ይህም ከቅድስናና ከፍቅር ባሕሪው ጋር ይስማማል ከእግዚአብሔር የጽድቅ ባሕሪ ውስጥ ሰዎች እየተመሩ የሚኖሩባቸው ሕግጋት ይፈስሳሉ መዝ ባ እግዚአብሔር ጻድቅ እንደ መሆኑ መጠን ሰዎች የእርሱን ምሳሌ ሊከተሉ በሚችሉበት ሁኔታ ሁልጊዜ ራሱን ያመቻቻል በፍጥ ኤር እግዚአብሔር ለእንግዶችና ለመበለቶች ርኅሩኖች እንድንሆን በሚፈልግበት መጠን እርሱም ሲረዳቸው ቸር ነው መዢ ብ እግዚአብሔር ፍጹም ስለሆነ እኛም ከሕግጋቱ ጋር ተስማምተንና ጠብቀን እንድንኖር ይፈልጋል እነዚህ ሕግጋት ከፍቅሩ ይመጣሉ ስለዚህ ሕግጋቱን በሚገባ ተጠቅመንባቸው እንድንኖር ፈቃዱ ነው ለምሳሌ አታመንዝሩ ሲል ያዝዘናል ይህን የሚያዝዘን ደስታችንን ሊከለክለን አይደለም ነገር ግን ከጋብቻ በፊትና ከጋብቻ በኋላ የሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ኃጢአት በባልና በሚስት መካከል ሊኖር የሚገባውን የደስታ ግንኙነት እንደሚገድብ ስለሚያውቅ ነው እግዚአብሔር ባወጣው ደንብ መሠረት የሚኖር ፈራጅ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም በዚህ ሕግ መሠረት እንዲኖሩ ይፈልጋል ያለበለዚያ የፍርዱን ውጤት ይቀበላሉ ስለሆነም እርሱ በሰጣቸው ሕግ ተመርተው የሚኖሩትን መልካም ዋጋ ይሰጣቸዋል በአንጻሩ በእርሱ መመሪያ መሠረት የማይኖሩትን ይቀጣል ሮሜ ዘዳግ መዝ ሮሜ እግዚአብሔር ጻድቅ በመሆኑ ኃጢአተኛን በኃጢአቱ ሳይቀጣው አይተወውም አንድ ውሸታም በሚዋሸበት ጊዜ «ግድ የለም ሂድ ይቅር እልፃለሁ» የሚለው ከሆነ ጻድቅ አምላክ ሊባል አይችልም ግን ጻድቅና ፈራጅ የሆነ አምላክ ሁልጊዜ ወንጀል የሚፈጽሙትን በወንጀላቸው ይቀጣቸዋል ዳሩ ግን በጥፋታቸው ሳይቀጣቸው ዝም ብሎ ቢተዋቸው ጻድቅ አምላክ ሊባል አይችልም በዚህ ምክንያት ነው እግዚአብሔር ኃጢአትን የሚሠራ ይሞታል ያለው በፍጥ ሕዝ ሮሜ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ፍትሕን በመከተል እንደ ሕጉ ቢከታተለን ኖሮ ሁላችንም በተቀጣን ነበር ምክንያቱም ሁላችንም ኃጢአትን ሠርተናልና ነው ሮሜ ፀ ግን እግዚኣብሔር ካለው ርኅራጌና ቸርነት የተነሣ ሁሉም እንዲድኑ ፈቃዱ ነው ስለዚህ ፈራጅ የሆነው አምላክ ኃጢአተኞች የሆኑ ሰዎች ሊድኑ የሚችሉበትን የጽድቅ መንገድ አዘጋጀ ከዚህ የተነሣ ኢየሱስ ክርስቶስን በኃጢአተኞች ፈንታ ይሞት ዘንድ ላከው ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው አግዚአብሔር ጻድቅ በመሆኑ ኃጢአትን ይቀጣል እንደዚሁም እግዚአብሔር «ያጸድቃል» በዚህ ምክንያት በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑት የሚጸድቁበትን ሁኔታ አዘጋጀ ሮሜ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን እግዚአብሔር ጻድቅ ፈራጅ ስለሆነ በምናደርገው ሁሉ በኃላፊነት ይጠይቀናል ስለዚህ የምንናገረው ቃል የምናደርገው ተግባርና እንቅስቃሴአችን ሁሉ ይገመገማል ማቴ በእነዚህ መስፈርቶች መሠረት አንድ ቀን መልካም ዋጋ እናገኝ ይሆናል አለበለዚያም ቅጣታችንን እንቀበላለን ኛ ቆሮ ኛ ቆሮ ክርስቲያኖች ኃጢአትን አቃልለው እንዳይመለከቱ ይህ ከባድ ማስጠንቀቂያ ነው እግዚአብሔር በምንናገራቸው መጥፎ ቃላት በውሸታችንና በራስ ወዳድነታችን ሁሉ ይቀጣናል በአንጻሩ ደግሞ ማንም ሰው በማያውቀው ነገር መልካም ዋጋ ወይም በረከቱን ይሰጠን ይሆናል አንዲት ትንሽ ችሮታ ወይም ሌሎች ያላዩት በምሥጢር ለኢየሱስ የምንፈጽመው አገልግሎት በእግዚአብሔር ዘንድ በረከትን ያሰጣል ማቴ ፊ በእግዚአብሔር ስሞች ውስጥ የተገለጠ የእግዚአብሔር ባሕሪ እንዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ራሱ ያለውን እውነት በተለያዩ ስሞቹ አማካይነት ገልጾአል እኛ የልጆቻችንን ባሕሪ በስሞቻቸው ለመግለጥ እንደምናደርገው ሁሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም የእግዚአብሔር ስሞች ስለ እርሱ ጠቃሚ ነገሮችን ይገልጻሉ በአይሁድ ባሕል መሠረት ስለ እግዚአብሔር በሚናገሩበት ጊዜ የእግዚአብሔር ስም ይላሉ ለምሳሌ ያህል ሰሎሞን «የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው» ምሳሌ ባለበት ጊዜ ለመግለጽ የፈለገው እግዚአብሔር ለሕዝቡ የጸና ግምብ መሆኑን ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከ በሳይ የእግዚአብሔር ስሞች ይገኛሉ ታዲያ እነዚህ ስሞች ስለ እግዚአብሔር የሚያስረዱት ቁም ነገር አለ ይህም ባሕሪውን ተግባሩን ወይም እርሱ ከሰዎች ጋር ስላለው ግንኙነት ነው ለምሳሌ ያህል እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ አምላክ ይባላል እንዲህ የተባለበትም ምክንያት እግዚአብሔር ጠቅላላ ሥልጣን እንዳለው እንዲሁም የሁሉም ነገር ተቆጣጣሪና አስተዳዳሪ መሆኑን ለማስገንዘብ ነው ኢሳ ፋ በዳንኤል ላይ «በዘመናት የሸመገለው» የሚለው አጠራር አግዚአብሔር ለዘላለም ነዋሪ መሆኑን ያመለክታል እንደዚሁም እግዚአብሔር «እግዚአብሔር ዓለት አግዚአብሔር አምባ» ተብሎ በሚጠራበት ጊዜ ይህ ስያሜ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሳይናወጡ ረግተው የሚቆሙበት ጽኑ ዓለት ማለት ይሆናል በዚህ መሠረት ላይ የሚቆም ሕዝብ አይጠፋም በዳግ መዝ እርሱ የነገሥታት ንጉሥ ነው ይህም እርሱ ነገሥታትንና የዓለም ገዥዎችን እንደሚቆጣጠር ያመለክታል እርሱ በዓለም ላይ ማንም የዓለማዊ ነገሥታት አቻ ሳይኖረው ብቻውን በመላው ዓለም ላይ ንጉሥና ገዥ የሆነ አምላክ ነው ኛ ጢሞ « እንግዲህ ከዚህ በላይ የተነጋገርንባቸው ጥቂቶቹ የእግዚአብሔር ስሞች ናቸው መጽሐፍ ቅዱስን በምታነቡበት ጊዜ የምታገኙአቸውን የእግዚአብሔር ስሞች በማስታወሻ ደብተራችሁ ውስጥ ጻፉ እነዚህ ስሞች ስለ እግዚአብሔር ባሕሪ ምንን ይገልጻሉ። እርሱ ሁሉን ይቆጣጠራል የሚደርስብን ማንኛውም ነገር ቢሆን በእርሱ ፈቃድ የሚሆን ነው ሰይጣን ይህን ሁሉ አይቆጣጠርም የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎችም ተቆጣጣሪዎች አይደሉም ነገር ግን ተቆጣጣሪው እግዚአብሔር ነው ሁሉ የእርሱ በመሆኑ ይህን የእግዚአብሔርን ዕቅድ አሸንፈው ሰይጣንም ሆነ ሰዎች ሊያደርጉብን የሚችሉት ምንም ጉዳት አይኖርም የልጅ ሞት የሚሆነው በድንገት ወይም ሰይጣን ወይም ክፉ መንፈስ ከእግዚአብሔር በላይ ስላየሉ አይደለም እግዚአብሔር የአየር ሁኔታንም ይቆጣጠራል እንዲሁም እግዚአብሔር ሰዎችን ይቆጣጠራል እግዚአብሔር የእኛንም ሆነ የሌሎችን ስሕተት ለእርሱ ክብር የሚጠቀምበት ጊዜ አለ ሦስተኛ እግዚአብሔር እኛን በጥልቅ ይወደናል እግዚአብሔር እንባችንን እንደሚያብስልን ተነግሮናል እግዚአብሔር የሚደርስብንንም እያንዳንዱን ኃዘን ያውቃል መዝ ር እርሱ ጨካኝ አምላክ አይደለም ሁላችንም በኃጢአት በወደቀ ዓለም ውስጥ እንኖራለን ብዙ ችግር የደረሰብንም ከአዳም ኃጢአት የተነሣ እግዚአብሔር በላዩ ላይ በላከው እርግማን ምክንያት ነው እግዚአብሔር ልጃችንን የሚወስድብን አንዳች ነገር በማድረጋችን አይደለም ይህ ሰይጣን ሊነግረን የሚሞክረው ነገር ነው እግዚአብሔር ጨካኝ ወይም ችላ ባይ ወይም ተለዋዋጭ አይደለም ነገር ግን እግዚአብሔር ስለወደደን ክቡር የሆነ ልጁ ስለ እኛ ኃጢአት እንዲሞትልን አሳልፎ ሰጠን ሁልጊዜም ቢሆን እርሱ ክቡር የሆነ ስጦታውን ይሰጠናል ሮሜ ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው ከእግዚአብሔር ፍቅር የሚለየን ምንም ነገር የለም ሞት ይመጣ ይሆናል ስደትም ይሆናል ይህ ሁሉ ቢደርስብንም እግዚአብሔር ለወደፊቱም ቢሆን አይወደንም ማለት አይደለም በምን ምክንያት ሥቃይ እንደሚደርስብን ልንገነዘብ አንችል ይሆናል ነገር ግን የልጆቻችን ሞት ቢሆን ወይም የረሃብ አደጋ ሁሉም በሚወድደን አምላካችን ቁጥጥር ውስጥ ናቸው ስለዚህ በጣም ጠቃሚ የሆኑት ነገሮች መጽናናታችን ወይም ቁሳዊ በረከቶቻችን አይደሉም ነገር ግን እግዚአብሔር እምነታችንን ማጠንከርና በእርሱ ምን ያህል እንደምንታመን ማየት ይፈልጋል እነዚህ ነገሮች በመከራ ጊዜ የበለጠ ያድጋሉ ነገሮች እንደፈለግነው ሳይሆኑ በሚቀሩበት ጊዜ እንኳን ቢሆን እግዚአብሔር ራሱን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደገለጠው እምነታችንን በእርሱ ላይ ጥለን ኑሮን መቀጠል አለብን ስለዚህ ወደ ታላቁ እግዚአብሔር ፈጥነን እንሩጥ እርሱ የመጽናናት ሁሉ አምላክ ነው ኛ ቆሮ ።