Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የመስቀሉ መንገድ ኔህዐ ምዕራፍ ዐምስት የደቀ መዝሙር ትርጉም ደፇ መሃሙረ ዕያመምሀሆሩ ጴይዕያጳሳ ዋም ፊጽም ዖታግሪ ያሖ ኋደ መምሀፍሩ ይሆናሃልያ ሐሥ ፀሪዐ ደቀ መዝሙር ቃሉን ተናግሮ ማንን ነው የሚያስደስተው። ብሎ መመርመር ማለት ነው ዕብ ስለዚህ ክርስትና ለብቻ የሚኖርበት ሃይማኖት ሳይሆን አንዱ ከሌላው ጋር በመተሳሰብ የሚኖርበት የፍቅር ማኅበር እንደ ሆነ ያሳየናል መስቀል ምንድን ነው።
ቅዱስ ጳውሉስ ሐዋርያነት በጌታ የተሰጠ ልዩ የአገልግሎት ሥልጣን እንደ ሆነ ሲገልጽ እርሱም አንዳንዶቹ ሐዋርያት ሌሎችም ነቢያት ሌሎቹም ወንጌልን ሰባኪዎች ሌሎችም እረኞችና አስተሣሪዎች እንዲሆኑ ሰጠ ኤፌ በማለት ያስታውቃል ከዚህ በመነሣት ሌሎቹ የጌታ ደቀ መዛሙርት ክርስቶስን እየመሰሉ እንዲኖሩ የተጠሩ አገልጋዮች ሲሆኑ የሐዋርያነት ሥልጣን ዐደራና አገልግሎት ያልተሰጣቸው ስለ ሆኑ ሐዋርያት አልተባሉም እንጂ አገልግሎትና ኀላፊነት የላቸውም ማለት አይደለም ስለዚህ ሐዋርያት የጌታ ደቀ መዛሙርት ሆነው ልዩ ሥልጣን ሲኖራቸው ደቀ መዛሙርት ግን የሐዋርያነት ልዩ ሥልጣን የሌላቸው የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸው የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት የተለዩ ናቸው የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከላይ ከተመለከትናቸው ከሙሴክመጥምቁ ዮሐንስከፈሪሳውያንም ሆነ ከዓለማውያን ፈላስፋዎችና ከሌሎች ከሐሰተኛ መሲሷሕ ተከታዮችና የሃይማኖት ድርጅት መሥራች ከሆኑ መምህራን ካፈሩአቸው ደቀ መዛሙርት ፈጽሞ የተለዩ ናቸው የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት እርሱን የሚመስሉ ናቸው ስንል እርሱ ልዩ እንደ ሆነ ሁሉ ደቀ መዛሙርቱም ከሌሎች ፈጽሞ የተለዩ ናቸው ማለታችን ነው ደቀ መዛሙርቱ ከሌሎች የሚለዩባቸውን ዋና ዋና የልዩነት ነጥቦች ከዚህ በመቀጠል ለመመልከት እንሞክራለን የኢየሱስ ደቀ መዝሙርነት ሐብተ ወልድና በማግኘት ይጀምራል የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ለመሆን አስቀድሞ የእግዚአብሔር የጸጋ ልጅ መሆን ያስፈልጋኃል ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው እንደሚል እውነት እውነት እልሃለሁ ሳው ዳግመኛ ካልተወለደ በስተቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥተ ዲገባ አይችልያሃ ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው ዮሐ በማለት ጌታችን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው ገማናቸውም ሰው መንፈሳዊ ሥራን ለመሥራትና ክርስቲያን ለመባል አስቀድሞ መንፈሳዊ ልደት ሊያገኝ ይገባዋል ዳግም ያልተወለደ ፍጥረታዊ ሰው ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም ቆሮ እንደ ተባለው ክርሰቲያን ለመባል ከውኃና ከመንፈስ በመወለድ የእግዚአብሔርን የጸጋ ልጅነት ማግኘት ይጠበቅበታል ከውኃና ከመንፈስ መወለድ ማለት በቃልና በመንፈሱ ዐዲስ ልደትን በመቀበል ምሥጢረ ጥምቀትን መፈጸም ማለት ነው ጥምቀት ማለት ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆን ማለት ነው ቅዱሰ ጳውሎስ ጥምቀት በሞቱና በትንሣኤው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድ መሆን መተባበር እንደ ሆነ ሲገልጽ ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን። ማስተዋልን ይሰጠናል የእግዚአብሔር መንፈስ የጥበብና የማስተዋል የምክርና የኀይል የዕውቀትና እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ ነው ኢሳ ስለዚህ መጻሕፍትን አንብበን እንድንረዳ ማስተዋልን እንድናገኝ ልቡናችንን ይከፍትልናል አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሌን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉን ያሳስባችኋል ዮሐ እንደሚል መጻሕፍትን ያጻፈና ትንቢትን ያናገረ መንፈስ ቅዱስ መጻሕፍትንና ቃለ እግዚአብሔርን በመተርጎም ምስጢራትን መረዳት እንድንችል ያደርገናል ለአገልግሎት ብቃትን እንድናገኝ ያደርጋል ማደሪያውን በቤተ ክርስቲያን ያደረገ መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ ምእመን እንደ ወደደ የጸጋ ስጦታን ይሰጣል በቆሮ በቤተ ክርስቲያን የጸጋ ስጦታን በማደል ምእመናንን ወደ ፍጹም የክርስቶስ ሙላት እንዲደርሱ ያንጻል ያበረታልም ኤፌ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን በማደር ዳግም እንድንወለድ ከማድረጉም በላይ በቀረው የክርስትና ሕይወታችን ወደ እውነት ሁሉ በመምራት የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንድናውቅ በማድረግ ክርስቶስን እየመሰልን እንኖር ዘንድ ብቃት እንድናገኝ ይረዳናል በዐጭሩ ስናጠቃልለው የሥላሴ አንዱ አካል የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ በውስጡ ያላደረበት ሰው የእግዚአብሔር ወገን ወይም ክርስቲያን ስላልሆነ ወደ ደቀ መዝሙርነት ወይም ኢየሱስን ወደ መምሰል ማደግ እንደማይችል እንረዳለን ስለዚህ የጌታ ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ለመምሰል የሚያስችለውን ብቃት የሚያገኘው የአብና የወልድ ሕይወታቸው የሆነ ጌታ መንፈስ ቅዱስ በውስጡ ሲያድርበት ብቻ መሆኑን ያረጋግጥልናል የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ በመሆን ክብሩን እንድንቀድስ ርስቱንም እንድንወርስ እንዲህ ዐስቦልን የጸጋው ተካፋዮች ካደረገን በቀረው ዘመናችን እንደሚገባ ልንመላለስ ይገባል የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ነን በማለት የምንኩራራበትና የምንመጻደቅበት ሳይሆን ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን በመፍራት በንጽሕና እንድንኖር የሚያስጠነቅቀን ጐዳይ ነው እስራኤል ከግብጽ ነጻ ያወጣቸውንና በምድረ በዳ የመራቸውን መንፈስ ቅዱስ ስላስመረሩት አልጠቀማቸውም ዕብ እንዴ ተባለው በምድረ በዳ ቀርተዋል እኛም መንፈሱን በማስመረር እንዳናሳዝነው ኤፌ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ በቅድስና ልንኖር ይገባል የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር እርሱን እንዲመስል የጠራው መምህሩ ምን ጊዜም ዐብሮት ይኖራል የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ከሌሎች ደቀ መዛሙርት የሚለየው ተዘተለኝ ያለው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዝሙሩ ጋር እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ዐብሮት መኖሩ ነውእንግዲህ ሂዱናእያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ ማቴ በማለት ምንም እንኳ ጌታችን በክብር በአብ ቀኝ ቢቀመጥም በቤተ ክርስቲያንና በምእመናን መካከል በመገኘት እስከ ዓለምሦ ፍጻሜ ድረስ ዐብሮ ይኖራል ማቴ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር እርሱን እንዲመስል የጠራው መምህሩ በአብ ቀኝ ተቀምጦአል የጊታ ደቀ መዝሙር ከሌሎች ደቀ መዛሙርት የሚለየው በመከራውና በችግሩ ጊዜ ሊረዳው የሚችል የታመነ ጌታ የሆነ ክርስቶስ ሊቀ ካህናት ሆኖ በአብ ቀኝ መቀመጡና በሚያስፈልገው ጊዜ የሚረዳውን ጸጋ ሁሉ ስለሚሰጠው ነው ሐዋርያው ጳውሎስ በታላቅ ፈተና ውስጥ የነበሩትን የዕብራውያን ክርስቲያኖች እንዲጸኑ ጸጋን ወደሚሰጣቸው ጌታ እንዲቀርቡ በመልእክቱ ከኀጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ ዕብ በማለት ያበረታቸዋል ስለዚዙ ክርስቲያን በመከራውና በፈተናው ሲረዳው የሚችል ሊቀ ካህናት በሰማይ ስላለው በእምነት በመቅረብ ፈተናውን የሜያሸንፍበትን ጸጋ ለማግኘት መቻሉ ክርስትናን እጅግ ልዩ ያደርገዋል ለደቀ መዝሙር የአገልግሎቱን ዋጋ ብድራት የሚከፍለው እርሱን እንዲመስል የጠራው ኢየሱሰ ክርስቶስ ነው ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋል እያንዳንዱ በሥጋው ለሠራው በጎም ሆነ ክፉ ሥራው ዋጋውን የሚከፍል እግዚአብሔር ነው ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው የሚከፍል ጌታ እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ ራእ ብሎ እንደ ተናገረው ጌታ ለደቀ መዝሙሩ ዋጋውን ይከፍለዋልና ክርስቲያን ዋጋውን ከሰው አይጠብቅም የዚህ ዓለም ሐሰተኛ የሃይማኖት መምህራን ለራሳቸውም ሆነ ለደቀ መዛሙርቶቻቸው ዋጋቸውን የሚከፍላቸው ሰው ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሕያው ስለ ሆነ ለእያንዳንዱ ደቀ መዝሙር ዋጋውን ሰለሚከፍል የኢየሱስ ደቀ መዝሙር መሆን ልዩ ነው ወገኔ ሆይ። ከሰው የምንጠብቅ ከሆነ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት መሆን ባላስፈለገን ነበር ከላይ በጌታ ደቀ መዛሙርትና በሌሎች ደቀ መዛሙርት መካከል ያለውን ልዩነት ስንመለከት የጌታ ደቀ መዛሙርት ከእግዚአብሔር የተወለዱ በውስጣቸው መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው የሚያገለግሉት ጌታ ዐብሮአቸው የሚኖር በመከራቸውና በፈተናቸው ጊዜ የሚረዳቸውዣአገልግሎት ዋጋቸውን የሚከፍል የጠራቸው ጌታ ራሱ ኢየሱስ ክርስቶሰ በመሆኑ ከሌሎች ደቀ መዛሙርት ፍጹም የተለዩ እንደ ሆኑ ተገንዝበናል ስለዚህ በክርስቶስ ባገኘነው ጸጋ ድኅነትና በመንፈስ ቅዱስ እየታገዝን ራሳችንን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆንን በማመን በጎውንና መልካሙን ሁሉ ለማድረግ በክርሰቶስ እንደ ተፈጠርን ዐውቀን እኛ ፍጥረቱ ነንና እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን ኤፌ እንደሚል ይህን ተረድተን ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አኣታሳዝኑ ኤፌ በማለት በሐዋርያው እንደ ተመከርን በንግግራችንና በምግባራችን ለቤዛ ቀን የታተምንበትን ቅዱሱን መንፈስ ሳናሳዝን እግዚአብሔርን በመፍራት በቅድስና እርሱን እየመሰልን ልንኖር ይገባል በዚህ ሁሉ የምንረዳው ክርስትና በራስ ጥረትና ችሎታ ብቻ መከናወኑን ሳይሆን በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና ፊል እንደሚል በእግዚአብሔር ጸጋ የተጀመረው ክርስትና በእርሱ ቸርነት ከፍጻሜ እንድንደርስ የሚያስፈልገንን ሁሉ በመስጠት የሚያጸናን እግዚአብሔር መሆኑን ነው በመሆኑም ክርስትና በወደደንና ራሱን ስለ እኛ ሲል እስከ ሞት ድረስ አሳልፎ በመስጠት ባዳነን ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ላይ የተጀመረና የተመሠረተ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱሰ ርዳታና በእግዚአብሔር ቸርነት እስከ ፍጻሜ የምንደርስበት ስለ ሆነ ሃይማኖታችንን አጽንተን እንጠብቅ ምዕራፍ ሁለት የደቀ መዝሙር አስፈላጊነት ር ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው ዮሐ መዓ መ እግዚአብሔር ሰውን በመልኩና በምሳሌው ፈጠረው ዘፍ ሰው እግዚአብሔር ከፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሌ ይልቅ እጅግ የተወደደና ውብ በመሆኑ የፍጥረቱ ሁሉ አዛዥናዛዥና ገዢ አድርጎ ሾመው አምላክነት ከሃሊነትማእምረ ኩሉነትና ምሉእ በኩለሄነት የእግዚአብሔር ባሕርይ መሆኑን ሲያጠይቅ ይህቺን ፍሬ እንዳትበላ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ በማለት ከለከለው ዘፍ ፁ አዳም የእግዚአብሔርን ባሕርይ ለራሱ ለማድረግ በሰይጣን ተታሎ ባደረገው ዐመፅ ኀጢአትን በመሥራቱ ከክብሩ እንደ ወደቀ በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ሦስት እንመለከታለን አዳምና ዘሩ በሙሉ ከወደቁበት ኀጢአትና የዘላለም ሞት ነጻ የሚያወጣቸውንና ወደ ቀደመው ክብር የሚመልሳቸውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣትና በሥጋ መገለጥ በናፍቆት ሲጠባባቁት የነበረ ተስፋቸው ነው ዘፍ ኾ ስለዚህ ክብር መመለስ የእግዚአብሔርን ማዳን አስመልክቶ አበው ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ተነድተው ሌጥ ትንቢት ተናገሩ ሊያዩትና ደግሞም ከሚገለጠው ክብር ተካፋይ ለመሆን እጅግ ይናፍቁ ነበር ሌጴጥ ሱባዔ የተቄጠረለትትንቢት የተነገረለትምሳሌ የተመሰለለት ጌታ የዘመኑ ፍጻሜ ሲደርስ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ፍጹም ሰው በመሆን ትንቢቱ ፍጻሜ አገኘ ገላ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድና ተስፋ ዘመኑ ሲደርስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ፍለጋ ወደዚህ ምድር በመምጣት ከኀጢአትና ከሞት አዳነን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ እንደ ምሕረቱ መጠን ለዐዲስ ልደት በሚሆንው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም ቲቶ ስለ ሰው ልጅ ሲል መከራ ተቀበለሞተተቀበረበሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ቆሮ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና ኤፌሪጋ የኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ምን ያሳየናል የእግዚአብሔርን ፍቅር ስለ እኛ ስለ ኀጢአተኞች ሲል መከራ መቀበሉንና መሞቱን ስናስብ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የምሕረቱንና የፍቅሩን ታላቅነት ያሳየናል ፍቅርም እንደዚህ ነው እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኀጢአታችንም ማስተሰረያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም ዮሐ ዮሐ ይመ በማለት ነባቤ መለኮት ሐዋርያው ዮሐንስ የክርስቶስ መሞት ለእኛ ያለውን ጥልቅ ፍቅር የገለጠበት እንደ ሆነ ያሳየናል ሐዋርያው ጳውሎስም ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያሰረዳል ሮሜ በማለት የእግዚአብሔር ሰውን መውደድ በክርስቶስ ሞት እንደ ተገለጠ ይገልጽልናል የኀጢአታችንን ስርየት የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ሥቃይና መከራ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ብቻ ሳይሆን የእኛን ኀጢአት አስከፊነትና በሌላ በምንም ነገር የኀጢአት ስርየት ልናገኝ እንደማንችል ያመለክታል ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ በሌጥ ዕብ ይመ በማለት የኀጢአት ስርየት የሚገኘው በእርሱ ሞትና ደም ብቻ እንደ ሆነ ያስገነዝበናል ቅዱስ ያሬድን አኮ በወርቅ ኀላፊ ዘተሣየጠነ በደሙ ክቡር ቤዘወነ ትርጐም የገዛን በኀሳፊና በጠፊ ወርቅ ብር አይደለም በከበረ ደሙ ገዛን እንጂ መዋስዕት በማለት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈውን እውነት ደግፏል እንዲሁም የኢየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆንና መከራ መስቀሉን መሞቱንና መነሣቱን ስናስብ የዝነመ እሳትን ፍርድ አስከፊነት እናያለን ከገሀነመ እሳት ፍርድ የምንድንበት ሌላ መንገድም ያለመኖሩን ሰውም ራሱን በራሱ ሊያድን እንደማይችል በሰማይም ሆነ በምድር ከእርሱ በቀር ሌላ የመዳን መንገድ እንደ ሌለ እንረዳለን መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ሰም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና የሐዋ እንደሚል ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ኢየሱስ የአግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ከተገለጹት ብዙ ማስረጃዎች መካከል አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ሕያው ሆኖ መነሣቱ ነው ትንሣኤው ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ሞት ሊይዘው የማይችል አምላክ መሆኑንም የሚያረጋግጥልን ዋና ምስክር ነው ሮሜ ራእ የሕይወት መገኛ መሆኑን ትንሣኤው በእርሱ ለሚያምኑት ሁሉ ትንሣኤ ልቦናን በመስጠት የጸጋ ልጅነትን የሚያስገኝ የእግዚአብሔር መንፈሳዊ ኀይል በመሆን ለሙታን ሕይወትን ሊሰጥ የሚችል ጸጋ እንደ ሆነ ያስረዳል ቅዱስ ያሬድ ዘበትንሣኤሁ ነሐዩ ኩልነ ትርጐም በትንሣኤው ሁላችን እንድናለን ብሎ ከገለጸው በእርሱ የሚያምንና የሚቀበለው ሁሉ የዘላለም ሕይወት ለማግኘት ዋስትና ኣንደ ሆነ እንረዳለን ሮሜ ኑ የትንሣኤንና የፍርድን አይቀሬነት ያረጋግጣል የክርስቶስ ትንሣኤ የሙታንን መነሣትና የፍርድን አይቀሬነት ከወዲሁ እንድናስተውል ያደርገናል ጌ። ዮሐ ምዕራፍ ሦስት ክርስቲያን ሁሉ ደቀ መዝሙር እንዲሆን ተጠርቷል ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኩር ይሆን ዘንድ አስቀድሞ ያወቃቸውን የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልሮሜ የኔታ ጥበቡ ሰብስበው የሚያስተምሯቸውን ተማሪዎች ክርስቶስ ወደዚህ ምድር ለምን እንደ መጣ የሚያውቁትን እንዲናገሩ ጥያቄ ጠየቋቸው ከተማሪዎቹ መካከል አንዱ በፍጥነት ለመመለስ ተነሣ የኔታም በል እስቲ ማስረሻ ስለ ክርስቶስ የምታውቀውን ንገረን አሉት ማሥረሻ ግን እእእ የኔታ በፊት ባደንብ ዐውቀው ነበር ዛሬ ግን ረስቼዋለሁ አላቸው የኔታም እጅግ በጣም የሚገርም ነው ከተማሪዎቼ ሁሉ ስለ ክርስቶስ የሚያውቅ አንድ ሰው ቢገኝ እርሱም ረስቶታል ብለው በጣም ዐዘኑ ተብሎ እንደ ተረት ይነገራል ስለ ደቀ መዝሙር አስፈላጊነትና ስለ ክርስቲያን የመጨረሻ ግብ በምናጠናበት ጊዜ የየኔታ አነጋገር እኛንም የሚመለከተንና ብንጠየቅ ለመመለስ የምንቸዝዢ ይመስለኛል የክርስቲያን ግቡ ኢየሱስ ክርስቶስን መሦሰል ነው ይህ ማለት እርሱ በምድር ሲኖር በቅድስና በፍቅር በይቅርታ ወዘተ ያለ ኀጢአት እንደ ተመላለሰ እርሱን እየመሰሉ ብኑሮውና በትምህርቱ አብነቱን መከተል ማለት ነው ሐዋርያው ዮሐንስ እንዴት በክርስትና ሕይወት መመላለስ እንዳለብንና እርሱን ስለ መምሰል ሲናገር በእርሱ እንዳለን በዚህ እናውቃለን በእርሱ እኖራለሁ የሚል አርሱ እንዴ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል ዮሐ በማለት ክርስቶስን በአኗኗራችን ልንመስለው እንደሜገባን ያሳስበናል በሌላ አባባል የክርስትና ግቡ ክርስቶስን መምሰል እንደ ሆነ ሁሉ ኢየሱስን መምሰል ማለት ደግሞ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆን ማለት ነው ምክንያቱም ደቀ መዝሙር ግለት መምህሩን የሚመስል ስለ ሆነ ክርስቶስን እንዲመስል የተጠራ ክርስቲያን ሁሉ ወደ ደቀ መዝሙርነት ማደግ እንዳለበት ያስረዳናል እዚህ ላይ በእግዚአብሔር ቤት ስንኖር ክርስቲያናዊ እድገት እንዳለ እንመለከታለን ይህም እያንዳንዱ ክርስቲያን ወደ ደቀ መዝሙርነት ደረጃ እንዲያድግ እንደ ተጠራና ክርስቶስን እየመሰለ ማደግ ያለበት መሆኑን ያስገነዝበናል የክርስትና ግቡ ኢየሱስን እየመሰሉ መኖር ማለት ሲሆን እርሱን የመምሰሌ ሂደት ከመለኮታዊ ባሕርይ በቀር በቃሉ ብርሃንነት እርሱን በማወቅ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ እርሱን እየመሰሉ ማደግ እርሱን እየመሰሉ መኖርም ማለት ነው በየዕለቱ ሕይወታችንን ስንመለከት ድካማችንና ውድቀታችንን ስናይ እንኳንስ ክርስቶስን መምሰል ቀርቶ መልካም ናቸው ብለን በአእምሮአችን የሣልናቸውን ሰዎች እንደማንመስል ራሳችንን በማየት ክርስቲያንነታችን ክንቱ እንደ ሆነ ልናስብ እንችላለን ወይም ደግሞ ክርስትና በቃል የሚነገር እንጂ በሕይወት የማይኖሩት ሊመስለንና ተስፋ ሊያስቄርጠን ይችላል ይሁን እንጂ ክርስቶስን መምሰል ወይም ወደ ፍጽምና መድረስ ወይም ደቀ መዝሙርነት በአንድ ጊዜ የሚመጣ ሳይሆን ክርስቲያናዊ የእድገት ሂደት ነው ዮሐ ይመ ይህንንም የክርስቲያናዊ እድገት ሂደት ከአበው ትምህርት በመነሣት በሦስት ደረጃዎች ከፍለን ማየት እንችላለን ክርስቲያኖች የሚደርሱበት የመንፈሳዊ ሕይወት እድገት ደረጃዎች ወጣንያንማአእከላውያንና ፍጹማን በመባል ይታወቃሉ ወጣንያን ወጣንያን የሚባሉት ገና የክርስትና ሕይወትን ሁ ብለው የጀመሩ ጀማሪ ክርስቲያኖች ናቸው እስመ ሐዲስ ተክል አነ እኔ ዐዲስ ተክልነኝ ቅዱስ ያሬድ ድጓ እንዳለው እነዚህ የክርስትናን ኑሮ ለመኖር የተጠሩ ዐዲስ ክርስቲያኖች በክርስቶስ አምነው የተጠመቁና የልጅነትን ሀብት የተቀበሉ ወይም ዳግም የተወለዱ ነገር ግን ገና ያላደጉ ሕፃናት ናቸው ንኡሰ ክርስቲያን በመባልም ይታወቃሌ ክፉውንና በጎውን የማይለዩ ዕብ በሃይማኖትና በምግባር ያልጐለበቱና በትምህርት ነፋስ የሚንሳፈፉ ናቸው ቅዱስ ጳውሎስ ሕፃናት ለሆኑ የኤፌሶን ምእመናን እንደ ስህተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም ኤፌ እንደ አላቸው ዐይነት በቆሮንቶስም ለሚገኙ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቴያን ለሚያስቸግሩ ወጣንያን ክርስቲያኖች ደግሞ የሥጋ እንደ መሆናችሁ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሌም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ ገና ሥጋውያን ናችሁና እስከ አሁን ድረስ ገና አትችሌም ቆሮ በማለት እንደ ገለጣቸው ያሌ ናቸው ሕፃናት ስለ ሆኑ በትምህርት ነፋስ ስለሚዋዥቁ እርስ በእርሳቸው ስለሚጨቃጨቁ ወደ መንፈሳዊ ብስለት ያልደረሱ ምእመናን መሆናቸውን ያመለከታል ወጣንያን በመንፈስ ሕፃናት በመሆናቸው በጣም ጥንቃቄና እንክብካቤ የሚያስፈልጋቸው ክርስቲያኖች እንደ ሆኑ በማሰብ ወደ ብስለት እንዲያድጉ ሊመከሩና ተኩትኩተው ሊያድጉ የሚገባቸው ክርስቲያኖች ናቸው ወጣንያን ክርስቲያኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መኖራቸው ቤተ ክርስቲያን ለምለም ማሕፀን እንዳላት ወላድ ሴት የተባረከች መንፈስ ቅዱስ በውስጧ የሚመላለስባት መሆኗን የሚያሳይ ምልክት በመሆኑ የሕፃናት በቤተ ክርስቲያን መወለድና መብዛት የሕያውነቷ ማስረጃ ነው ነገር ግን የተወለዱት ልጆቿ ጊዜያቸውን ጠብቀው የማያድጉ አስተማሪዎችና ፍጹማን ወደ መሆንም አድገው ለቤተ ክርስቲያን አለኝታ መሆን በሚገባቸው ሰዓት ወጣኒ ሆነው የሚገኙ ከሆነ የጤነኛነት ምልክት አይደለም ልጅ ተወልዶ ጊዜውን ጠብቆ ተመጣጣኝ ምግብ እየተሰጠው የማያድግ ከሆነ በሽተኛ እንጂ ጤነኛ ስላልሆነ ምርመራ ሊደረግለትና ሊታከም ይገባዋል ቤተ ሰቡ ሁሉ በእርሱ ይታወካልና እንዲሁ ሁል ጊዜ ዐድሮ ጥጃ የሚሆኑ ምእመናን በዐዳዲስ ትሦዝርት ስለሚወሰዱና በምእመናንም መካከል ጭቅጭቅና ንትርክ የሚፈጥሩት እነርሱ ስለ ሆኑ በሸታቸው የራሳቸው ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንም ነው ማእከላውያን ማእከላውያን የምንላቸው ወደ ፍጽምና ደረጃ ያልደረሱትን ከሕፃንነት የወጡትን ራሳቸውን ችለው ክፉውን ከደጉ ለይተው የሚያውቁ ብጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም ዐውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል እኔም የዘለዓለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ ለዘለዓለምም አይጠፉም ከእጄም ማንሦ አይነጥቃቸውም ዮሐ የተባለው ቃሉንነ የእረኛቸውን ድምፅ ለይተው የሚሰሙ ክርስቶስን በቃልም በሥራም ሊመስሌት የሚሞክሩትን ክርስቲያኖች ሁኔታ የሚያሳይ የክርስትና ሕይወት ደረጃ ነው ፍጹማን ፍጹማን የምንላቸው ቅዱስ ጳውሎስ ከእምነታቸው ወደ ኋላቸቐቸው ለመመለስ ለሚፍገመገሙ ለዕብራውያን ክርስቲያኖች ጸንተው እንዲቆሙ በጻፈው መልእክቱ ወተት የሚጋት ሁሉ ሕፃን ስለ ሆነ የጽድቅን ቃል አያውቅምና ነጠንካራ ምግብ ግን መልካሙንና ክፉውን ለመለየት በሥራቸው የለመደ ልቡና ላላቸው ለፍጹማን ሰዎች ነው ዕብ በእምነታቸውና በምግባራቸው የበቁትን ትሩፋት የሚሠሩትን በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ገድላቸው የሚኖሩትን ለራሳቸው ሳይሆን ለሌላው ሳው የሚተርፍ የተትረፈረፈ የክርስትና ሕይወት ያላቸውን ክርስቶስን የሚመስሉ ሆነው እኔ ከርስቶስን እንደምመስል እናንተም እኔን ምሰሉ እያሉ የሚያስተምሩትን። አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው ወልድ የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ የለውም በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው ዮሐ ይህም የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የሚክድ እግዚአብሔር እንደሌለውና የእግዚአብሔር ወገን እንዳልሆነ ያስረዳናል ብዙ ሐሰተኛ ክርስቶሶች አሉና እውነተኛውን ክርስቶስን ከሐሰተኞች ክርስቶሶች የምንለየው በቃሉ ነው በቃሉ ላይ ከተገለጸው ክርስቶስ አጐድለው ወይም ጨምረው ክርስቶስን የሚገልጡ ሐሰተኞች ከመሆናቸውም በላይ የሐሰተኛው ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ናቸው ክርስቲያን እንደ ሆኑ የሚናገሩ ኣንዳንድ የእምነት ድርጅቶች ክርስቶስ ጥሩ መምህርና ጥሩ ሰው እንደ ነበረ ቢናገሩም አምላክነቱን ሞትና ትንሣኤውን አዳኝነቱንና ዳግም ምጽአቱንነ ፈራጅነቱንም ጭምር እንደሚክዱ ይታወቃል እነዚህ የሃይማኖት ድርጅቶች በስም ክርስቲያን ነን ይበሉ እንጂ ኢየሱስ ክርስቶስን በሚገባ አላወቁትምና ዕውቀታቸው ጐደሎ ስለ ሆነ የጌታ ደቀ መዛሙርት ሊሆኑ ወይም ክርስቲያን ተብለው ሊጠሩ አይችሉም በእምነት መኖር እምነት የክርስትና ሩልፍ ጐዳይ ነው ያለ እምነት እግዚአብሔርን ማወቅም ሆነ ወደ እርሱ መቅረብ አይቻልም ዕብ ስለ እምነት ሐዋርያው ጳውሎስ ለዕብራውያን ክርስያኖች ሲጽፍላቸው እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው ዕብ በማለት በዐይነ ሥጋ ሊታይ የማይቻለውን እግዚአብሔርን በአምነት ልናየው እንደምንችል ያረጋግጥልናል እምነት እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ እንደሚፈጸም የምናረጋግጥበት ዋስትናችን መሆኑን ያሳየናል ስለዚህ እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር የሰጠንን ተስፋ የምናረጋግጥበትና እግዚአብሔርን የምናይበት ዐይናችን እግዚአብሔር እንዳለ ለሚያምኑትም ዋጋ እንደሚሰጥ አስቀድመን የምናውቅበትና የምናረጋግጥበት መሣሪያችን የእግዚአብሔርን ጸጋ የምንቀበልበት እጃችን እምነት እንዴ ሆነ እንረዳለን ዕብ ስለዚህ ክርስቶስን ማን እንደ ሆነምን እንዳደረገልን ገእኛ ምን እንደምንመስል በቃሉ የተገለጸውንና የተረዳነውን ሰምተን በማመን ክርስቶስን በእምነት እናየዋለን እርሱንም ለመምሰል ዕለት ዕለት በፊቱ በእምነት አእንቀርባለን ከዚህ በመነሣት እምነት የሌለው ሰው ኢየሱስ ክርስቶስ ማን እንደ ሆነ ሊያውቀው ስለማይችል የጌታችን ደቀ መዝሙር ወይም ክርስቲያን ሊባል አይችልም ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ማድረግ ግንኙነት ክርስቶስን በደንብ ለማወቅና እርሱን ለመምሰል አስፈላጊ ከሆኑት ዋና ነገሮች መካከል አንዱ ነው ደቀ መዛሙርት ከኢየሱስ ጋር ዐብረውት ይውሉ አብረውትም ያድሩ ስለ ነበር ክርስቶስን አብረውት በቁዩበት ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በሚገባ ያውቁት ነበር ዐብሮ መዋል ዐብሮ ማደር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ስለ ሆነ የባሕርይ ዝምድናን ያመጣል ከጥሩ ጋር የዋለ ጥሩነትን ከክፉ ጋር የዋለ ደግሞ ክፋትን ይወርሳል አብረኸው የምትውለው ባልንጀራህ ማን እንደ ሆነ ንገረኝና አንተ ማን እንደ ሆነህ እነግርሃለሁ እንደሚባለው ሰው ዐብሮት ከሚውለው ጋር ባሕርይ እንደሚወራረስ ለማሳየት የተነገረ አባባል ነው ከክፉ ሰው ጋር የሚውል መልካም ሰው መልካም ባሕርዩ ይበላሻል ቆሮ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የዋለ ሰው የክርስቶስን መልካም ባሕርይ ይወርሳል ስለዚህ ክርስቶስን ለመምሰል ዐብሮ መዋል ያስፈልጋል ከክርስቶስ ጋር ዐብሮ መዋሉን ያበዛ ሰው ክርስቶስን የመምሰሉ ባሕርይ የጐላ ይሆናል ከክርስቶስ ጋር ዐብረን መዋልና ከእርሱ ጋር መነጋገር መገናኘትና ዐብረን መዋል ከምንችልባቸው መንገዶች መካከል አንዱ ጸሎት ነው ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርበት ሕይወታችንን የምንሰጥበት ፈቃዳችንን የምናሳውቅበት ክርስቶስን በአካለ መንፈስ የምናገኝበትና እርሱን የምናይበት እግዚአብሔር ለልጆቹ ያዘጋጀው ጸጋ ነው ታዲያ አዘውትረን የምንጸልይ ከሆነ ዐብረን ከጌታ ጋር እየዋልን ነው ማለት ነው ስለሆነም ጸሎት ለእግዚአብሔር አቤቱታ የምናቀርብበት ብቻ ሳይሆን የእርሱ ፈቃድና ባሕርይ በሕይወታችን እንዲቀረጽ ከእርሱ ጋር የምንገናኝበት የምንነጋገርበትና የምንስማማበት ብቸኛ መንገድ ነው ጸሎት ለእግዚአብሔር የምንናገረው ብቻ ሳይሆን ከእርሱ የምንሰማበት ነው ጸሎት ከእግዚአብሔር የምንቀበልበት ብቻ ሳይሆን ራሳችንን ፈቃዳችንንና ማንነታችንን ለእርሱ የምንሰጥበት ነው ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ወደ እኛ የሚቀርብበት ነው ጸሉት የእግዚአብሔርን ፊት የምናይበት ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት ማንነታችን የሚታይበት ነው ስለዚህ እርሱን እንድናውቀውና እንድንመስለው የምንሻ ደቀ መዛሙርት ሁል ጊዜ በጸሎት በፊቱ መገኘት ይገባናል ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን መካፈል ደቀ መዝሙር ኢየሱስ ክርስቶስን እየመሰለ እንዲኖር ከሚያደርጉት መንገዶች መካከል አንዱ በየጊዜው ምስጢደ ዮርባንን መቀበሌ ነው እንካችሁ ይህን ብሉ እንካችሁ ይህን ጠጡ። የሚል ጥያቄ ማንሣታችን ተገቢና መልካም ዋያቄ ነው ጌታችንም የምንለይበትን ሲናገር እንዲሀ አለ የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ ማቴ ብሎናል ስለዚህ አንድን ሰው እውነተኛ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆኑንና ያለ መሆኑን የምንለየው በዘሩ በጾታው በዕውቀቱ ወይም በንግግሩ ሳይሆን የጌታ ደቀ መዝሙር ነኝ የሚለው ሰው በርግጥ ሕይወቱ አኗኗሩ ንግግሩና ምግባሩ ክርስቶስን ይመስላል ወይ ብለን ሕይወቱን በማየት መሆን ይኖርበታል ስለዚህ እውነተኛ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ሦን ዐይነት ምግባር እንዳለው ከዚህ ቀጥሎ ለማየት እንሞክራለን ትሕትና ከእኔም ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና ማቴ በእግዚአብሔር ዘንድ የሰው ማንነቱ አንዱ ከሌላው የሚለየው በዘሩ በሀብቱ ወይም በሥልጣኑ ሳይሆን በሕይወቱ ነው ዛፍ በፍሬው እንደሚታወቅ እንዲሁ ደቀ መዝሙርም በፍሬው ይታወቃል የኢየሱስን ደቀ መዛሙርት በርግጥ የእርሱ እንደ ሆኑ የምንለያቸው በሕይወታቸው በሚያፈሩት መንፈሳዊ ፍሬ ሲሆን ከነዚህ መሠረታውያን ባሕርያት መካከል አንዱ ትሕትና ነው የክርስትና ግቡ ምንድን ነው ብለን ብንጠይቅ የተበላሸነውንና እግዚአብሔርን በማሳዘን ከክብሩ የወደቅነውን እኛን ወደ እግዚአብሔር ክብር እንደርስ ዘንድ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር በመምጣት የተበላሸ ሕይወታችንን በመቀየር በቅድስና እርሱን እየመሰልን ከእርሱ ጋር ለዘላለም እንድንኖር ማድረግ ነው ምክንያቱም በሐሳባችንና በክፉ ሥራችን ጠላቶች በመሆን እርሱን ደስ ማሰኘት ያልቻልነው ሰዎች በፊቱ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆነን ለመንግሥቱ እንድንበቃ በክርስቶስ እንደ ገና መፈጠራችን ለዚሁ ነው ቆላ ትሕትና ራስን ባዶ ማድረግ ነው ከክርስቶስ ባሕርያት መካከል ትሕትና አንዱ ነውዷ ይህን አስመልክቶ ሐዋርያው ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች ክርስቶስ በፍጹም ትሕትና ራሱን ባዶ እንዳደረገ የጻፈላቸው እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልፄቂጠረውም ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ በምስሌም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ ፊልጵ በማለት ነበር ክርስቶስ እርሱ ሁሉ ያለው የሰማይና የምድር ፈጣሪ ሆኖ ሳለ የሰውን ልጅ ከሞት ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ለብሶ ከድንግል ማርያም መወለዱን መሞቱንና መነሣቱን ስንመለከት የምንረዳው ፍጹም ትሕትናውን ነው ትሕትና የአገልጋይነት መንፈስ ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እዚህ ምድር የመጣው ሊያገለግል እንጂ እንዲያገለግሉት አልነበረም እንዲሁ የሰው ልጅም ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም» ማር እርሱ እልፍ አእላፋት መላእክት ሌሊትና ቀን የሚያገለግሉት የጌቶች ሁሉ ጌታ ሁሉ የሚንበረከክለት የነገሥታት ሁሉ ንጉሥ ሆኖ ሳለ የፈጠረውን የሰውን ልጅ ለማገልገል ራሱን ዝቅ በማድረግ እስከ ሞት ድረስ መታዘዙ ፍጹም ትሑትነቱን ያሳየናል ይህን ስንመለከት ትሕትናው እኛን ብቻ ሳይሆን መላእክትንም ሁሉ የሚያስገርም ነው እርሱ አምላክ ሆኖ ሳለ በአካለ ሥጋ በሰዎች መካከል ተገኝቶ የደቀ መዛሙርቱን እግር ለማጠብ መነሣቱ እንደ ባሪያ ተንበርክኮ የበታቾቹን ማገልገሉ በትሕትና ራሱን ዝቅ ስለ ማድረጉ ወደር የማይገኝለት ከመሆኑም በላይ ለሰው አእምሮ እጆግ የሚገርም ነው ይህን የተመለከተ ቅዱስ ጴጥሮስ የጌታችን ዝቅ ብሎ እግር ለማጠብ መነሣት ስለ ከበደው ጌታ ሆይ የእኔን እግር ልታጥብ አይገባህም ብሎ ሲከላከል እንመለከታለን ዮሐ አንዳቸው ብቀኝ አንዳቸው በግራ በሥልጣን ላይ መቀመጥና ባለ ሥልጣን መሆንን እንጂ ዝቅ ብለው ሌላውን ሰው በትሕትና ማገልገል የማይፈልጉትን ደቀ መዛሙርቱን ማቴ ጌታችን እርሱ ትሑት እንደ ሆነ የሚከተሉትም ሁሉ ትሑታን እንዲሆኑ በተለያየ መንገድ ያስተምራቸው ነበር ስለ ራሳቸው ታላቅነት ብዙ ይጨነቁ ለነበሩት ደቀ መዛሙርቱ ስለ ትሕትና በምሳሌ ሲያስተምራቸው እንዲህ አደረገ ሕፃን በመካከላቸው አቁሞ እንዲህ ካልሆናችሁ ወደ መንግሥተ ሰማይ አትገቡም ይላቸው ነበር ማቴ በስቅለቱ ዋዜማ እርሱ ኀጢአትን ያላወተ ቅዱስነቱ ስለ ሰዎች ኀጢአት ሲል በፈቃዱ በመስቀል ለመቱ በሚጨነቅበት ምሽት ደቀ መዛሙርቱን ያስጨነቃቸውና ያሳሰባቸው በኢየሩሳሌም ስለሚያገኙት ሥልጣንና ክብር ከመካከላችን ማን ታላቅ ይሆናል የሚል ነበር ይህን የተመለከተ ጌታ ስለ ትሕትና ማስተማሩ ሊታለፍ የማይገባው መሠረታዊ ጐዳይ ነበርና በስቅለቱ ዋዜማ እግራቸውን በማጠብ ትሕትና ማለት ምን ማለት እንደ ሆነ እንዲያውቁ ራሱ ተንበርክኮ በማጠብ ካሳያቸው በኋላ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ እናንተ ደግሞ እርስ በእርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባቸኋል እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተም ደግሞ እንዲሁ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና ዮሐ በማለት እንዲህ እንዲያደርጉ አዚል ጌታችን ደቀ መዛሙርቱ ትሑታን እን መንገድ ቢያስተምራቸውም ሊገባቸው እንዳልቻለ ሁዲ እኛም ዛሬ የትሕትና ምስጢር ገብቶን እየታዘዝን ይሆን። ብለን ብንጠይቅ መልሱ የትሕትና ጐድለት ሊሆን ስለሚችል ራሳችንን ቆም ብለን መመልከት ያስፈልገናልደቀ መዝሙርነት በትሕትና ሌላውን ለማገልገል ራስን መስጠት እንጂ እንደ ዓለማዊ ሹመት ክብርና ዝናን ለማግኘት የሚደረግ ፍልሚያ አይደለም በቃሉ የሚኖር ነው እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ» ዮሐ መጽሐፍ ቅዱስ የእምነታችን መሠረት ነው የክርስትና እምነት የተመሠረተው በማያልፈውና ዘለዓለማዊ በሆነው የእግዚአብሔር ቃል ላይ ነው እግዚአብሔር ዘላለማዊ እንደ ሆነ ሁሉ ቃሉም ዘለዓለማዊ ነው ጌታችን ስለ ቃሉ ዘለዓለማዊነት ሲናገር ሰማይና ምድር ያልፋሉሌ ቃሌ ግን አያልፍም ማቴ በማለት ያረጋግጥልናል እግዚአብሔር ማን ነው ምንስ ይመስላል ተብለን ብንጠየቅ በቃሉ ራሱን እንደ ገለጠው ነው ብንል ትክክል ነን እግዚአብሔርን እናውቃለን ለሚሉ ነገር ግን አግዚይኦብሔርን ላላወቁ አይሁዳውያን የቃሉን ገላጭነት አስመልክቶ እርሱን ለማወቅ የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ እንደሚጠበቅባቸው ጌታችን ሲናገር በእናንተ ዘንድ የሚኖር ቃሉ የላችሁም» በማለት ዮሐ ይወቅሣቸው ነበር የክርስትና እምነት የተመሠረተው በእግዚአብሔር ቃል ላይ ነው ስንል በክርስቶስ ላይ ነው ማለታችን ነው አስቀድሞ በእግዚአብሔር ዘንድ የነበረ አካላዊ ቃል ሰማይንና ምድርን የፈጠረ አምላክ በዘመን ፍጻሜ ሰዎችን ለማዳን ሥጋ ለብሶ ዮሐ ተዋሕዶ ወደዚህ ምድር እንደ መጣ በማመን ነው ቅዱስ ያሬድ በዘልደት ድጓ እንደ ጻፈው «ወአመ በጽሀ ጊዜሁ ፈነዎ እግዚአብሔር ለወልዱ ወተወልደ እም ብእሲት ከመ ያድኅን አባግኢሁ ይርዳዕፅ ዘተኃጉለ ያስተጋብእ ዝርዋነ መጽአ ሐቤነ ትርጐም ጊዜው ሲደርስ አብ አንድ ልጁን ላከ ከሴትም ተወለደ ይኸውም የጠፋውን ሊፈልግ የተበተነውን ሊሰበስብ በጎቹን ሊያድን ነው ክርስቶስ ሰማይና ምድር ከመፈጠሩ በፊት ሕያው ሆኖ ዓለማትን እንደ ፈጠረ ሁሉ ሥጋ ለብሶ በመካከላችን ማደሩ የተገለጠውም በዚሁ መጽሐፍ ነው ዮሐ ያለ ክርስቶስ ክርስትና የለም ስለዚህ ክርስትና ሰው በጥበቡ የመሠረተው የሰው ሃይማኖት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለሰዎች የተገለጠ ብቸኛ ሃይማኖት ነው ሃይማኖት እንተ እምኀበ አብ ተፈጥረት ኀበ ወልድ ታበጽህ ወኀበ መንፈስ ቅዱስ ትትፌጸምትርጉምሃይማኖት ከአብ ዘንድ የተፈጠረች በወልድ የተገለጠች በመንፈስ ቅዱስ የተፈጸመች ናት ቅያሬድ ድጓ የክርስትና ሃይማኖት መሠረቱ የእግዚአብሔር ቃል ነው ስንል መጽሐፍ ቅዱስ ነው ማለታችን ነው አንድ በጣም የማልረሳው ነገር መጽሐፍ ቅዱስን አዘውትሮ የሚያነብን አንድ ልጃቸውን የተመለከቱ ሽማግሌ ሰው ይህ ልጅ መናፍቅ ሆነ እንዴ ሁል ጊዜ የማየው መጽሐፍ ቅዱስ ሲያነብ ነው ብለው የጠየቁኝ ነው በአንዳንድ አላዋቂ ሰዎች ዘንድ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ መናፍቅነት ይመስላቸዋል ከሌሎች ሃይማኖታውያን ድርጅቶች ሁሉ በፊት የክርስትና እምነታችን ብቸኛ መመሪያና የሃማኖታችን መሠረት የተጣለው በመጽሐፍ ቅዱስ መሆኑን ባለማስተዋል የዘነጉ ይመስሳል ኢትዮጵያ አገራችን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከ ጊዜ በላይ የተጠቀሰች አገር ስትሆን ነ ከንጉሥ ሰሎሞን የንግሥና ዘመን ጀምሮ ነነጊ የብሉይ ኪዳን ባለቤትና ከክርስቶስ ፅርገት ማግስት ጀምሮ በ ዓም ከአይሁድ ቀጥሎ በመጀመሪያ የክርስቶስን ጌትነትና አዳኝነት አምና በመቀበል ወንጌልን ለሕዝቧ ያወጀች የክርስትና እምነት ባለቤት መሆኗን በሐዋርያት ሥራ ሐዋ የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ የባኮስን ታሪክ በማንባብ መረዳት ይቻላል ስለ ክርስቶስ የሚመሰክሩትና በእርሱ እንድናምን አምነንም የዘላለም ሕይወት እንድናገኝ የተጻፉልን ቅዱሳት መጻሕፍት ናቸው ዮሐ ኾ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፈውን ቃል ብሌይንና ሐዲስን ማወቅ እግዚአብሔር ለሰዎች የገለጠውን ሕይወት ማለትም ክርስቶስን ማወቅ ማለት ነው ሰለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዐይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም ይኋ እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን ሕይወትም ተገላጠ አይተንማል እንመሰክርሣለን ከአብ ዘንድ የነበረውንሥ ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን በዮሔ በማለቱ መጻሕፍት የሚናገሩት ስለ ክርስቶስ መሆኑን እንረዳለን ጸሐፍት ፈሪሳውያን ቃሉን እናውቃለን ብለው በቃላቸው ቢያነበንቡትም ሕይወት ወደ ሆነው ጌታ መጥተው ሊያምኑና ክርስቶስን በአምላክነቱና በመሚሕነቱ ሊመለከቱ ባለመቻላቸው ጌታችን በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም በማለት ሲገሥጻቸው እንመለከታለን ስለዚህ መጻሕፍት በራሳቸው ሕይወትን የሚሰጡ ሳይሆኑ መጻሕፍት የሚናገሩት ሕይወት ስለሚሰጠው ጌታ ክርስቶስ ስለ ሆነ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ያስፈልጋል ክርስቲያን ቃሉን ማወቅ አለበት ሲባል ወደ ቃሉ ባለቤት ቀርቦ ራሱን መስጠት አለበት ማለት ነው አንዳንዶቻችን የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ ለክርስቲያን ምን ይጠቅመዋል በልቡ እግዚአብሔር አለ ብሎ ካመነ በቂው አይደለም ወይ ብለን ልናስብ ለቃሉም ትኩረት ላንሰጥ እንችላለን ነገር ግን የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን እንደሚያስፈልገው ከዚህ በመቀጠል ለማየት እንሞክራለን የእግዚአብሔርን ቃል የማወቅ ጥቅም የእግዚአብሔር ቃል ዳግም የተወለድንበት ስለ ሆነ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ሌጥሮስ ሲጽፍ የተወለዳችሁት ከእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋው ዘር ነው ጴጥ እንዲሁም ቅዱስ ያዕቆብ ለፍጥረቱ የበኩራት ዐይነት እንድንሆን በእውነት ቃል ኣስቦ ወለደን ያዕ በማለት ክርስቲያን ከቃሉ የተወለደ መሆኑን ያስረዳናል ስለዚህ የተወለድንበትን ቃል የቻልነውን ያህል ማወቅ ያስፈልገናል የእግዚአብሔር ቃል ሀብተ ውልድናን ላገኘ ክርስቲያን የነፍስ ምግብና የሕይወትም እንጀራ ስለ ሆነ ነው ቅዱስ ጴጥሮስ ስለ እግዚአብሔር ቃል ምግብነት ሌሕጥ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት የቃልን ወተት ተመኙ ሲለን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የእግዚአብሐርን ቃል ምግብነት አስመልክቶ ከይሲ ዲያብሎስ በምግብ ሊፈትነው ሲመጣ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም በማለት የቃሉን ምግብነት በማሳየት ዲያብሎስን ድል ሲነሣው እንመለከታለን ሉቃ ቶ የእግዚአብሔር ቃል ለክርስቲያን የሕይወትና የኑሮ መመሪያው ስለ ሆነ ነው በዚህ ግራ በሚያጋባና ትክክለኛውና የተሳሳተው መንገድ በማይታወቅበት ዓለም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመኖር በቃሉ መመራት እጅግ አስፈላጊ ነው የቃሉን መሪነት በዘመኑ የተረዳው ቅዱስ ዳዊት ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው መዝ በማለት በዚህ ምድር የሕይወት መመሪያ ሆኖ ቃሉ እንዳገለገለውና እንደ ጠቀመው ያሳየናል ቅዱስ ጴጥሮስም እጅግ አስቸጋሪ በሆነ የመከራና የስደት ሕይወት ውስጥ ይኖሩ ለነበሩት ክርስቶያኖች ሲጽፍላቸው ሰው በጨለማ ሲሄድ መብራትን ተጠንቅቆ እንደሚይዝ እንዲሁ የእግዚአብሔርን ቃል ተጠንቅቀው እንዲይዙ በመልእክቱ ሌጥ ያስጠነቅቃቸዋል የእግዚአብሔር ቃል ለክርስቲያን የሕይወትና የኑሮ መስተዋት ስለ ሆነ ነው የእግዚአብሔር ቃል ውስጣዊና ውጫዊ ማንነታችን ማን እንደ ሆንና ምን እንደምንመስል በእግዚአብሔርና በራሳችን ፊት ፍንትው አድርጎ የሚያሳየን መስታወት ነው ቅዱስ ያዕቆብ ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል ራሱን አይቶ ይሂዳልና ያፅ በማለት የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ብቻ ራስን በመስተዋት ማየት እንደ ሆነ ያሳየናል ሐዋርያው ጳውሎስም ከቃሉ ማንም ሊሰወር እንደማይችል ሁሉም ሰው በእርሱ ፊት የተራቁተና የተገለጠ መሆኑን እንዲህ በማለት ጽፎልናል የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና የሚሠራም ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል እኛን በሚቄጣጠር በእርሱ ዐይኖች ፊት ሁሉ ነገር የተራቄተና የተገለጠ ነው እንጂ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም ዕብ የእግዚአብሔርን ቃል ስናነብ ቃሉ በሁለት ዐይነት መንገድ ማንነታችንን ያሳየናል ማለትም በቃሉ ውስጥ ራሳችንን ስንመለከት በክርስቶስ ውስጥ ወይም ከክርስቶስ ውጭ ልንመለከት እንችላለንና ልናስተውል በጥንቃቄና በመንፈስ ቅዱሰ አብርሆት ህጠበበ ልናነበው ይገባናል በመጀመሪያነ ማናችንም በቃሉ ውስጥ ራሳችንን ከክርስቶስ ውጭ የምናይ ከሆነ እጅግ ኀጢአተኞችና ደካሞች መሆናችንን እንረዳለን በዚህ ምክንያትቾ ከንቱነታችንን በማየት ራሳችንን እንጠላዋለን ወደ እግዚአብሔር ፊት ለመቅረብም ሆነ ስሙን ለመጥራት እንፈራለን እንደ ቃሉም መኖር ስለማንችል በፍርድ ውስጥ እንዳለን እንገነዘባለን እንደዚህ አድርገን በቃሉ ራሳችንን የምንመለከትና ማንነታችንን የምንረዳ ከሆነ ስለ ራሳችን መጥፎነት ብቻ እናውቃለን ስለ ራሳችን ብቻ ሳይሆን ቃሉን ለምንነግራቸውም ሰዎች ያለን አመለካከት መጥፎ ስለሚሆን መጥፎነታቸውን ብቻ የምንናገር ሁል ጊዜም ወቀሣን የምናበዛ የፍርድ ሰዎች እንሆናለን ብዙ ሰባኪዎች ራሳቸውን በዚህ ዐይነት መንገድ ስለሚመለከቱ ሰውን የሚያጽናና ቃል የላቸውም ሁል ጊዜ የወቀሣ ቃልን ያቀርባሉ በሌላ በኩል ደግሞ ታቃታሉን ስናነብ ክርስቶስን ብቻ ሳይሆን ራሳችንን በክርስቶስ ውስጥ እንዳለን እናዩለን በዚህም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅርና ርኀራጌ ከማወቃችንም በላይ በእምነት በኩል የእግዚአብሔር ልጆች እንደ ሆንን ገላ እንመለከታለን ቃሉ እንደሚል ራሳችንን በክርስቶስ ውስጥ እንዳለን አድርገን ካየነው በርግጥ ክርስቲያኖች ነን በክርስቶስ ክርስቲያን እንደ ተባልን እግዚአብሔርም ለእኛ ያለውን ፍቅርና ባእርሱ የተደረገልንን ቸርነት ስለምንመለክከት እግዚአብሔርን እጅግ እናመሰግነዋለን በእርሱም እንመካለን የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነውቆሮ ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ራሳችንን የምንመለከተው ከክርስቶስ ጋር እንደ ሞትንና በክርስቶስ ሕያው ሆነን እንደምንኖር ነው ሮሜ ቆሮ እንዲህ አድርገን ቃሉን የምንረዳና የምናነብ ከሆነ ቃሉን ለሌላው ስንነግር እኛ ፍጹም ኀጢአተኞች መሆናችንንና ክርስቶስ ለእኛ ያደረገልንን ቸርነት በመግለጽ የእግዚአብሔርን ፍቅር እንናገራለን» ለሚሰማንም ሁሉ የሚያጽናና ቃል እናቀርባለን ኀጢአተኞችንም ወደ ክርስቶስ ተመለሱ በማለት የእግዚአብሔርን ምሕረትና በጎነት በማሳየት በንስሓ እንዲመለሱ እንመክራለን እንጂ በሰዎች ላይ ፈራጆች አንሆንም ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ቃል በማወቁ ከስሕተት ይጠበቅበታል ሰው ቃሉን እንደሚገባው ካላወቀና ካልተረዳ ከእግዚአብሔር መንገድ እንደሚወጣና እንደሚሳሳት የታወቀ ነው ጌታችን በምድር በሚያስተምርበት ዘመን በስሜትና በቅናት በመነሣሣት ትምህርቱንና ራሱንም ጭምር ይቃወሙት ለነበሩት ጸሐፍት ፈሪሳውያን ለመሳታቸውና ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጭ ለመሄድ የዳረጋቸው ፃኢፃሃዚአብሔኤርን ታል ያለማወቃቸው እንደ ሆነ ሲናገር እንዲህ አለ ሥጳሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል አታፁቱምና ትስታላችሁ ማቴ ሰው ዐዋቂ ነኝ በሚልበትና በመሰለው መንገድ በሚጓዝበት በዚህ የመጨረሻ ዘመን ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል ምን ያህል ማወቅ ይጠበቅብን ይሆን። አዎ ዓለም ጥበቧና ዕውቀቷ በበዛ ቱሩኑጥር አሳሳቹ ብዙ ነውና አሁን ካወቅነው በላይ ዕለት ዕለት ቃሉን ማወቅ ይጠበቅብናል ቅዱስ ዳዊትም አንተን እንዳልበድል ቃልህን በልቤ ሰወርሁ በማለት ቃሉን በልባችን መዝገብ ካኖርን ከስሕተትና እግዚአብሔርን ከመበደል እንደሚጠብቀን ገልጧል ጦዝ በ የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ እንደ ፈቃዱ ለመኖር ይረዳናል ከላይ ለማየት እንደ ሞከርነው እግዚአብሔርን እፈልጋለሁ እንዴ እርሱ ፈቃድ እኖራለሁ ብሎ የሚያስብ ሰው የግዴታ ቃሉን ለማወቅና ለማንበብ ከአባቶች እግር ሥር ቁጭ ብሉ መማር እንደሚገባው ሚችለውን ያህል ማወቅ እንዳለበት እንረዳለን ካላወቀ ግን በልማድ ክርስቲያን ተብሎ ከመጠራት በቀር ለስሕተት የተጋለጠና እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት የማይችል እንደ እግዚአብሔር ፈቃድም የማይኖር ሰው ነው ቃሉን በሚገባ ስለ ማወቅ ከላይ በመጠኑም ቢሆን ለማየት ሞክረናል ይሁን እንጂ ቃሌን ብቻ ማወቅ ክርስቲያን መሆን ማለት አይደለም ያወቅነውን ቃል በተግባር ማዋል ይጠበቅብናል ምክንያቱም ቃሉን ዐውቆ የማያደርገው ከሆነ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራን ሰነፍ ሰውን ይመስሳል ማቴኑ ቃሉን ሰምቶ የሚያደርገው ግን ቤቱን በዐለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመሰላል በማለት ጌታችን ቃሉን ሰምቶ ስለ ማድረግ ያስተምረናል ቅዱስ ያዕቆብም ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል ራሱን አይቶ ይሄዳልና ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል ያዕ በማለት ቃሉን ሰምተን እንድናደርገው ያሳስበናል ይሁን እንጂ ቃሉን ያላወቀ ሰው ለማድረግ ስጸሚችገር አስቀድሞ ቃሉን ማወቅ ቃሉን ያወቀ ሰው ደግሞ ያወቀውን መታዘዝና ማድረግ ይጠበቅበታል መታዘዝ በየትኛውም የሃይማኖት ተቋም ውስጥ የሚያስፈልግ መሠረታዊ የእምነት መገለጫ ነው ትእዛዝ የሌለበት ሃይማኖት የማይታዘዝም ምእመን የለም እምነትና መታዘዝ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው አንዱ ከሌላው ተለይቶ አይታይም ሐዋርያው ያፅቆብ በዘመኑ የነበሩትን የንግግር ብቻ ክርስቲያኖችን አስመልክቶ ሲጽፍላቸው ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው» ያዕ በማለት ያለመታዘዝን ከንቱነትና ከሥራ የተለየ እምነትን ሕይወት አልባነት ያሳየናል ጌታችን ስለ ደቀ መዝሙርነት ባሕርይ ለተከታዮቹ ሲናገር ቃሌ በእናንተ ዘንድ ቢኖርና በቃሌ ብትኖሩ በአውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ ሲላቸው ምን ማለቱ ነው የሰማችሁትንና ያወቃችሁትን ቃል በሥራ ላይ ማዋል አለባችሁ ማለቱ ነው በቃሉ መኖር ማለት ማውራት ማለት አይደለም ስለዚህ ደቀ መዝሙር ማለት የእግዚአብሔርን ቃል የሚያወራ ሳይሆን አስቀድሞ ቃሉ በእርሱ ዘንድ ያለውና ያወቀውንም ቃል በሥራ የሚተረጉምና እምነቱን በሥራ የሚያሳይ ማለት ነው የጌታ ደቀ መዝሙር በቃሉ መኖር ካለበት በቃሉ ለመኖር አራት መሠረታውያንነገሮች ያስፈልጉታል በቃሉ ለመኖር የሚያስፈልጉ መሠረታውያን ነገሮች ቃሉን መስማት የፄታ ደቀ መዝሙር ቃሉን መስማት አለበት ማለትም ቃሉን በመስማት ቃሉ በውስጡ ሊኖረው ይገባል ቃሉ ከሌለውና ቃሉን ካልሰማ የሚታዘዘውን እንዴት ያውቀዋል። ትክክለኛውንና ያልተበረዘውን የእግዚአብሔርን ቃል መስማት የመጀመሪያው የደቀ መዝሙር ተግባር ነው አንድ ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት ከሚችልባቸው መንገዶች መካከል ዋናውና መሠረታዊ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብና መማር ነው መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ማለት ከእግዚኣብሔር ዘንድ በመንፈስ ቅዱስ ርዳታ መስማት ማለት ነው በተጨማሪ ደግሞ ከቤተ ክርስቂያን አባቶች እግር ሥር ቁጭ ብሎ መማር ስብከትን ማዳመጥ ወዘተ ጠቃሚ ሲሆን በትክክል እግዚአብሔር ለልቡ እንዲናገረውና ማድመጥም እንዲችል በጸሎት በፊቱ መቅረብ ይጠበቅበታል ያለ ጸሎትና ያለ መንፈስ ቅዱስ ርዳታ የሚደረግ ንባብና ዕውቀት ከዕውቀትነት ያለፈ አይሆንም ቃሉን ማሰላሰል የጌታ ደቀ መዝሙር ያነበበውንና ከእግዚአብሔር የሰማውን ቃል ማሰሳሰል ይገባዋል ቅዱስ ዳዊት ብፁዕ የሆነ ሰው ቃሉን ሌትና ቀን ያሰላስላል ይሳል መዝ እግዚአብሔርን እየፈራ እንደ ቃሉ ለመኖር የሚያስብ ሰው ቃሉን በተግባር ከማዋሉ በፊት በልቡ ያሰላስለዋል ሰው በልቡ ከሞላው ይናገራል በልቡ ያሰበውንና ያወጣ ያወረደውን ያንኑ ያደርጋልናኑ ስለዚህ ቃሉን ግንበብና ማሰላሰል መልካም ሥራ ለመሥራትና መልካም ንግግርን ለመናገር ጠቃሚና ዋና ጐዳይ ነው ቃሉን ማመን የጌታ ደቀ መዝሙር ያወቀውንና ያሰላሰለውን ቃል ማመንና መወሰን ይኖርበታል እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው ሮሜ እንደሚል እንዲሁ የሰማው ቃል በእምነት ከራሱ ጋር መዋሐድ አለበት ዕብ ያን ጊዜ በሙሌ ፈቃደኝነትና በሙሉ ልብ የሰማውንና ያሰላሰለውን ቃል በተግባር ለመተርጎም ይነሣል በማሰላሰልና የእግዚአብሔርን ቃል በመስግት ጌዜ በጸሎት በእግዚአብሔር ፊት መቄየቱ መንፈስ ቅዱስ ቃሉን ሰምቶ አንዲያምንና እንዲያስተውል ስለሚረዳው ዕውቀቱ በጸሎት የተደገፈ መሆን ይኖርበታል ቃሉን በተግባር ማዋል የጌታ ደቀ መዝሙር ያወተውን ጠይም የሰማውንና ያሰላሰለውን ቃል በተግባር ማዋል ይገባዋል ይህ የመጨረሻውና እግዚአብሔርም ከእኛ የሚፈልገው ቃሉም ለእኛ የተሰጠበት ዋነኛ ዐላማ ነው ብዙ በማወቃችን ከሌላው የተሻለ ዕውቀት ስላለን በሌላው ባላወቀው ሰው ላይ ልንኩራ እንችላለን ዕውቀት ያስታብያል ቆሮ የእግዚአብሔር ቃል ግን በማወቅ የሚያበቃና የምንታበይበት ፅውቀት። በማለት ግራ ተጋብተው በጥርጥርና በማመንታት ውስጥ ባሉበት ወቅት ስለ ራሱ ማንነትና እውነተኛነት ሊያስረዳቸው ሞክሮአል ይሁን እንጂ እነርሱ ሊያምኑት ስላልቻሉ በዮሐ ባለው ክፍል ውስጥ ከእግዚአብሔር የሆኑትንና ያልሆኑትን ለመለየት የምንችልባቸውን መስፈርቶች እንመለከታለን የጌታ ደቀ መዝሙር የእግዚአብሔርን ቃል ብቻ ይናገራል ጌታችን ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፁ ሲያስተምር ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለምፈቃዱን ሊያደርግ የሚወድ ቢኖር እርሱ ደህ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቢሆን ወይም እኔ ከራሴ የምናገር ከሆነ ያውቃል አለ ጌታችን የእርሱ ቃል የአባቱ ሆኖ እያለ የአባቴን እንጂ የራሴን ቃል አልናገርምና በዚህ ከእግዚአብሔር እንደ ሆነሁ ዕወቁኝ ካለ የጌታ ነኝ የሚል ደቀ መዝሙር ትምህርቱ በርግጠኛነት የክርስቶስ እንጂ የራሱ ወይም የሌላ ሊሆን አይችልም ስለዚህ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር መሆኑን እና አለመሆኑን ያምናውቀው ቃሉ የማን እንደ ሆነ በመመልከት ነው አገልጋዩ የሚናገረው ቃል የእግዚአብሔር ቃል ብቻ መሆን አለመሆኑን መመልከት ይኖርብናል ኣየጌታ ደቀ መዝሙር የቃሌን አገልግሎት ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ይሰጣል ጌታችን ይህን የምናገረው አባቴ ይከብር ዘንድ ስለ አባቴ ክብር እንጂ ለራሴ ክብር አይደለም አለ ክአራሱ የሚናገር የራሱን ክብር ይፈልጋል የላከውን ክብር የሚፈልግ ግን እርሱ እውነተኛ ነው በእርሱም ዐመፃ የለበትም ዮሐ አርሱ ከአባቱ ጋር አንድ ሆኖ ሳለ ይህን ካለ ኢየሱስ የአባቱን ቃል ለአባቱ ክብር ከተናገረ የጌታ ደቀ መዝሙር የሚናገረው ቃል ለእግዚአብሔር ክብር እንጂ ለራሱ ክብር ሊሆን አይችልም የእግዚአብሔርን ቃል ለራሱ ክብርና ዝና የሚጠቀምና ከእግዚአብሔር ይልቅ ለራሱ ወይም ለድርጅቱና ለወገኑ ክብር የሚያደላ ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ ፊል እንደ ተባለ ለታይታ የሚሰብክና የሚናዢ ከሆነ እውነተኛ ሳይሆን ሐሰተኛ ደቀ መዝሙር ነውና ሐሰተኛነቱን በዚህ እናውቀዋለን ሰለዚህ ሰባኪ የሆነ የፄታ ደቀ መዝሙር የቃሉን አገልግሎት ክብር ለእግዚአብሔር መስጠት ይኖርበታል ዴየጌታ ደቀ መዝሙር ቃሉን የሚሰብክ ብቻ ሳይሆን የሚያደርግምነው ፈሪሳውያን በጣታቸው እንኳ ሊነኩት የማይፈልጉትን ሸክም በሰዎች ላይ መጫናቸው የግብዝነታቸው ዋና ምልክት እንደ ሆነ ጌታችን ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም ማቴ በማለት ገሥጸአቸዋል የፄታ ደቀ መዝሙር እንዲህ የሚያደርግ ከሆነ ግብዝ እንጂ እውነተኛ አይደለምኑ እናት ለልጁ የሚጥመውንና መልካሙን ከመጥፎው ለይታ ቀምሳ አጣጥማ እንደምትሰጥ ሁሌ የጌታ ደቀ መዝሙር ቃሉን በሕይወቱ ተርጐሞና ተለማምዶ ካየው በኋላ ይህ ጠቃሚ ነው ብሎ ለሰሚዎቹ ይናገራል እንዲያደርጉትም ያሰተምራል እንጂ የማያደርገውንና ያላደረገውን ቃል እንዲሁ ለንግግር ይመቻል ብሎ አይሰብክም አያስተምርምም የማያደርጉትን አድርጉ ብለው የሚያስተምሩ ነገር ግን ንግግራቸውና ሥራቸው የተለያየ ወይም የሚናገሩ ግን የማያደርጉ ከሆኑ በርግጠኛነት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አይደሉሌም ስለዚህ የፄታ ደቀ መዝሙር ቃሉን የሚያስተምር ከሆነ አስቀድሞ የሚያደርገው ለመሆኑ ማረጋገጫ ነው ዷፋየታ ደቀ መዝሙር ለእግዚአብሔርና ለቃሉ ታግኝ መሆን ይጠበቅበታል ደቀ መዝሙር ቃሉን ተናግሮ ማንን ነው የሚያስደስተው። በዐዲስ ኪዳን የተገለጠው «ፍቅር የሚለው ቃል አጋፔ ከሚል የግሪክ ቃል እንደ መጣ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ይናገራሉ አጋፔ ማለት እግዚአብሔር ሰውን የወደደበትን ፍቅር የሚያመለክት ነው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ራስን ስለ ሌላው ሲባል አሳልፎ እስከ ሞት ድረስ መስጠትን ያስረዳል ይህም በበደላችንና በገጢአታችን ሙታንና የእግዚአብሔርም ጠላቶች ሆነን ሳለን ከወደደን ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ እኛን ጠላቶቹን ከሞትና ከዘላለም ፍርድ ለማዳን ሲል እግዚአብሔር አንድያልጁን እስከ ሞት ድረስ አሳልፎ እስከ መስጠት ድረስ የወደደበትን ፍቅር የሚያሳይ ነው ዮሐ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኀጢአተኞች ሞቶኣአልናአግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል» ሮሜ ሬ አጋፔ ማለት ጠላትን እስከ ሞት ድረስ መውደድ ማለት ው የእግዚአብሔር ፍቅር ነባቤ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የአጋፔ ፍቅር ባለቤት እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን ሲገልጥ ፍቅርም እንደዚህ ነውእግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኀጢእታችንም ማስተስረያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም በዮሐ በማለት የእግዚአብሔር ፍቅር ለእኛ ለኀጢአተኞችና ለጠላቶቹ ሲል ምትክ ሆኖ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶሰን በመስቀል ላይ እንዲሞት በማድረግ ፍቅሩን እንደ ገለጸልን ይነግረናል በቅድመ ሁኔታ ላይ አልተመሠረተም ሰው በባሕርዩው ሌላውን የሚወድበት ፍቅር የተመሠረተው በቅድመ ሁኔታ ላይ ነው ይወደኛል ይጠቅመኛል ይስማማኛልደስ ይለኛል ብሎ የገመተውን የራሱን መመዘኛ የሚያሟላለትን ሰው መርጦ ያፈቅራል የሰው ፍቅሩ በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ የማይስማማውንና በአስተሳሰቡም ሆነ በሥራው ከእርሱ ጋር የማይገጥም ከሆነ ይጠሳል ማናችንም ብንሆን አስቀድመን ሁኔታዎችን አይተን ስለምንወድ ሁኔታዎችን ኣይተን ደግሞ እንጠላለን ፍቅራችን በሁኔታዎች ላይ የተመሠረተ ስለ ሆነ የሚለዋወጥና ወረተኛ ነው የእግዚአብሔር ፍቅር አጋፔ ግን እንደዚህ አይደለም በእኛ መልካምነትና አንዳች ያደርጉልኛል ብሎ ሳይጠብቅ እንዲሁ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ኀጢአተኞች ሆነን ሳለን ስለ ወደደን ፍቅሩ ዘላለማዊና የማይለዋወጥ መሆኑን እንረዳለን ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ኀጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶልናልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል ሮሜ ካለ በኋላ ይልቁን አሁን መታረቁን ባገኘንበት በፍቅሩ እንመካለንደግሞም ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየኝ የለም በማለት ለመመካት የቻለው እግዚአብሔር ጠላቶቹ ሆነን ሳለን በማይለወጥ ፍቅሩ ከወደደን ዛሬ እርሱን አምነን በቤቱ ለንኖር የምንመካው በእርሱ ፍቅር እንጂ በእኛ መልካምነት ሊሆን አይችልም በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት የተገለጠ ነው የእግዚአብሔር ሰውን መውደዱ የተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሆነ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ፍቅር መገለጫ ነው ቲቶ ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል ወአብጽሆ እስከ ለሞት ትርጉም ወልድን ከልዕልናው ሰቦ ለሞት ያደረሰው ሰውን መውደዱ ነው ቅዳሴ ማርያም እንደሚል እግዚአብሔር ሰለ ወደደን ክብሩን ጥሎ ወደዚህ ምድር የሰውን ሥጋ ለብሶ መጣ በከብቶች በረት ተወለደእንደ ሰው በሳላ ጠጣ ተራበ ገተጠማ ታዘዘ ታመመ መከራችንን ተቀበለሞተተቀበረ በሞቱ አዳነን ያዳነን እኛ ስላደረግነው መልካም ሥራችን ሳደሆን ሰለ ወደደን ነው የእግዚአብሔር ፍቅር አጋፔ የመዳናችን ምክንያት ነው ያለ ኢየሱስ ክርሰቶስ መስቀል የእግዚአብሔርን ፍቅር ማወቅ አይቻልም ክርስቶስን ማወቅ ማለት የእግዚአብሔርን ፍቅር ማወቅ ማለት ነው ክርስቶሰን የማያውቅ ሰው ፍቅር ምን እንደ ሆነ አያውቅም እግዚአብሔርን እናውቃለን የሚሉ እንደ እስልምና ያሉ ብዙ ሃይማኖቶች ስለ እግዚአብሔር ማንነት የሜገልጹ ከዘጠና ዘጠኝ በላይ ስሞች ቢኖሩአቸውም የኢየሱስን ሞትና ትንሣኤ ስለማያውቁ እግዜአብሔር ፍቅር ነው የሚል ስም በመጽሐፋቸው በቁርአናቸው ውስጥ የላቸውም መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን አጋፔ የሚገልጽ መጽሐፍ እንጂ የእግዚኣብሔርን መቅሠፍትና ቀጣ ብቻ የሚፃዓልጽ መጽሐፍ እንዳልሆነ ልናውቅና ክርስቲያኖችም እግዚአብሔር በፍቅሩ ያዳነንና ልጆቹ ያደረገን መሆኑን ልንረዳ ይገባል ለእግዚአብሔር ፍቅር የምንሰጠው መልስ እግዚአብሔርን መውደድኑ ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው እግዚአብሔርን እጠላዋለሁ ብሎ የሚናገር እንደሌለ እሙን ነው የክርስቶስ ፍቅር የገባውና እግዚአብሔር ያደረገለትን ያወቀ ክርስቲያን እግዚአብሔርን እወደዋለሁ ማለቱ አይቀርም ታዲያ እግዚአብሔርን መውደዱ በምን ይታወቃልፃ ይህ መሠረታዊና ተገቢ ጥያቄ ነው እግዚአብሔርን ዐውቀዋለሁ ደግሞም አመልከዋለሁ የሚል ሰው ፍቅር የሃይማኖቱ መሠረት ነው ፍቅር ከማንኛውም ነገር በማስቀድም ለእግዚአብሔር የሚሰጠው መልስ ነው እግዚአብሔርን መውደድ እርስ በርሳችን የመዋደዳችን የአገልግሎታችንና ለሌሎች መልካም ለማድረግ የሚያስችለን ኀይል ነው ይህ እግዚአብሔርን የመውደድ የፍቅር ባሕርይ የሚመነጨው እግዚአብሔር እኛን የወደደበትን የፍቅሩን መጠን ስንረዳ ነው ይኸውም እርሱ አስቀድሞ ስለ ወደደን እኛም እንወደዋለን ዮሐ ስለዚህሦሥ እኛ በተወደድንበት በእርሱ ፍቅር እርስ በርሳችን እንዋደዳለን ዮሐ ዮሐ እርስ በእርስ መዋደድ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅርና እኛም ሊኖረን የሚገባንን የፍቅርን ዐይነት አጋፔየሚለውን የግሪክ ቃልነ እርሱ ስለ እኛ ኒፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን ዐውቀናል እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል ዮሐ በማለት እርስ በእርሳችን ሊኖረን የሚገባው የፍቅር ዐይነት የእግዚአብሔር ፍቅር ዐይነት ማለት አጋፔ መሆን እንዳለበት ያስረዳናል ሠናየ ግበሩ ቢጸክሙ አፍቅሩ እስመ ዘአፍቀረ ቢጾ ይነስዕ እሴቶ እምኀበ አብ እምሰማይ ትርጉም መልካምን ሥሩ ወንድሞቻችሁንም ውደዱ ወንድሙን የሚወድ ከሰማያዊ አባት ዘንድ ዋጋውን ይቀበላልቅያሬድ ጸመ ድጓ ስለዚህ እግዚአብሔርን መውደዳችን የሚታወቅበት አንዱ ምልክት ዐብሮን ያለውን በአርኣያ ሥላሴ የተፈጠረውን ወንድማችንን ስንወድ ነው ሐዋርያው ዮሐንስ ስለ እውነተኛ እግዚአብሔርን መውደድ ሲጽፍ ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል። ብሎ መጸለዩ ተገቢ ነው መዝ አላና ዘሩ አብሔር ምሳሌ የተፈጠረው ነም በኀጢአት ምክንያት እግዚአብሔር የሚፈልገውን ዐይነት ፍሬ ሊያፈራ ስላልቻለ ዐዲሱ ዘር ፍሬ ለማፍራ ወ ዚህ ምድር እንደ መጣ ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕራፍ ዐምስት ላይ በአዳም ምክንያት ሞትና ርግማን እንደ መጣፍ በኢየሱስ ክርስቶስ ግን ጽድቅና ሰሳምን እን ን ያስተምረናል እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋደው መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን ኤፌ እንደሚል ክርስቶስ ወደዚህ ምድር ለመምጣት የቻለበት ዐቢይ ምክንያትና ግብ ፍሬ እንድናፈራ እንደ ገና ሊፈጥረን ነው ስለዚህ ሰው መልካም ፍሬ ለማፍራት ከመቻሉ በፊት የልጅነትን ሀብት ማግኘት ያስፈልገዋል ከወይኑ ግንድ ጋር መተባበር እኔ እውነተኛ የወይን ግንድ ነኝ እናንተ ቅርንጫፎች ናችሁ ያለ እኔ በእራሳችሁ ፍሬ ልታፈሩ አትችሌም በማለት የተናገረዉ ክርስቶስ የዐዲሱ ሰውና የእውነተኛ ፍሬ መገኛ ምንጭ መሆኑን እናያለን ሀቆሮ ስለዚህ ሰው በራሱ ችሎታ ብቻውን መልካሙን ፍሬ በሐልዮ በነቢብም ሆነ በገቢር ማፍራት ስለማይችል ጌታችን እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሌምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል ዮሐ በማለት ከክርስቶስ ጋር የግድ ኅብረት ማግረግ እንዳለብን ታዘናል ይህ መጣበቅ ይህ አንድነት የወይኑ ግንድ ቅርንጫፍ የመሆን ጐዳይ በመንፈስ ቅዱስ አሠራር በእግዚአብሔር ጸጋ ሀብተ ውልድና ሰናገኝ ስለ ተከናወነ ክርስቲያን ሁሉ ፍሬ ለማፍራት የሚችልበት ቅድመ ሁኔታ ዐዲስ ፍጥረት በመሆን እንደ ተሟላለት ያሳየናል ፍሬያማነት ከክርስቶስ ጋር በመጣበቅ ፍሬ ማፍራት ነው ስንል የክርስቶስን ምሳሌነት በውስጣችን በማፍራት መኖር ማለታችን እንደ ሆነ ግልጽ ሊሆንልን ይገባል መልካሙ ፍሬ የክርስቶስ ባሕርይ ስለ ሆነ ፍሬ ማፍራት ማለት እንደ ክርስቶስ መልካም ማሰብ መልካም መናገር መልካም ማድረግ ማለት ነው እነዚህን መልካም ባሕርያት እንድናፈራ በክርስቶስ ዐዲስ ፍጥረት ከመሆናችንም በላይ ፍሬውን ማፍራት እንድንችል መንፈስ ቅዱስ ስለሚረዳን መልካሙ ፍሬያችን የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ በመባል ይታወቃል ገላ በቃሉ መኖር ደቀ መዝሙር ፍሬ ለማፍራት ዳግም የተወለደ ዛከወይኑ ግንድ ጋር የተጣበቀመሆኑ ብቻ በቂ አይደለም ራሱ የሚወጣቸው ኀላፊነቶች አሉበት እንደሚገባ ፍሬ ለማፍራት ከሚያስችሉት ኀላፊነቶች መካከል ጥቂቱን ለማየት እንሞክራለን ቃሉን መታዘዝ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ምስጉን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ ዛፍ ይሆናል መዝ እንዳለው መንፈሳዊ ፍሬ ማፍራት የእግዚአብሔር ቃል በቀጥታ ከእኛ ጋር ባለው ግንኙነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ቃሉን መታዘዝና ሁል ጊዜ ማሰሳሰል ያስፈልጋል ዮሐ ጸምና ጸሎት በየዕለቱ ፍሬ ሊሰጠው ወደሚችል አምላክ በጾምና በጸሎት መቅረብና ርዳታን መለመን መማጸን ኢሳ ንስሓ መግባት በኀጢአት በሚወድቅበት ጊዜ ሳይውል ሳያድር ንስሓ በመግባት ከክፉ ሥራው መመለስና የንስሓ ፍሬን ማፍራት በዮሐ ማቴ በቤተ ክርስቲያን ምስጢራት መካፈል በቤተ ክርስቲያን ምስጢራት መካፈልእንዲሁም በቤተ ክርስቲያን ሥርዐተ ጸሎትና በግል ጸሎት በየዕለቱ መሳተፍ ፍሬያማነትን እንድናገኝ ከእኛ የሚጠበቁ ተግባራት ናቸው የመንፈስ ቅዱስ ርዳታ የመንፈስ ቅዱስ ርዳታ ከክርስቲያኑ ጥረት በተጨማሪ ፍሬ ለማፍራት መሠረታዊና በቀላሉ የማይታይ ዋና ጐዳይ ነው የቱንም ያህል ቃሉን ብናነብብንታዘዝተጸጽተን ንስሓ ብንገባ በምስጢራት ብንካፈልክራሳችን የሚጠበቅብንን ድርሻ ተወጣን እንጂ በራሳችን ጥረትና ችሎታ ፍሬ ማፍራትና እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አንችልም ምክንያቱም የመንፈስ ፍሬ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሕርይ ነው ስለዚህ ማንም ሰው በራሱ ይህን ባሕርይ ሊያመጣ አይችልም ይህን ባሕርይ በእኛ ውስጥ ሊያፈራና ማንነታችንን ሊቀይር የሚችለው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነው የፍሬው ተጠቃሚ ገበሬው ነው ፍሬ የሚያፈራ ተክል ፍሬውን የሚጠቀምበት ወይም የሚበላው ራሱ ሳይሆን ፍሬው ለተካዩ ወይም ለባለቤቱ ነው እንዲሁም ክርስቲያን በሚያፈራው መንፈሳዊ ፍሬ ተጠቃሚ የሚሆነው ራሱ ሳይሆን ፍሬ እንዲያፈራ የተከለውና በክርስቶስ እንደ ገና የፈጠረው እግዚአብሔር ነው ብዙ ፍሬ ብታፈሩ አባቴ በዚህ ይከብራል ስለሚል ክብሩ ለእግዚአብሔር ነው ዮሐ ዙ ይህ ማለት ባለ ብዙ ፍሬ የሆነው ክርስቲያን ምንም አይጠቀምም ማለት አይደለም ጥቅሙን በሌላ መንገድ ያገኘዋል ይኸውም ጸሎቱ ይሰማለታል እግዚአብሔር ጸሎቱን ከሚሰማለት በቀር የታደለስ ማን አለ። እግዚአብሔር ጸሎቱን ከሰማለት እግዚአብሔር ዐብሮት ከሆነ ከዚህ የበለጠ ለሰው የሚደረግለት ነገር ስለሌለ የሚያስፈልገውን ሁሉ ያገኛልና ትልቅ በረከትና ትልቅ ሰጦታ ነው ከላይ ለማየት እንደ ሞከርነው ክርስቲያን መሆን ማለት መልካሙን የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለማገልገል መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት የተጠራ ለዚህም ሲባል ከክርስቶስ ጋር የተጣበቀ ሰው ማለት ነው አንድ አትክልተኛ ገበሬ ተክሉ ፍሬ ካላፈራለት እንደሚነቅለው ሁሉ ፍሬ የማያፈራን የስም ክርስቲያን መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቄረጣል ወደ እሳትም ይጣላል ማቴ እንደ ተባለ እግዚአብሔር ይቄርጠዋል ስለዚህ ከክርስቶስ ጋር መጣበቅና ጸንቶ መቄየት ለፍሬያማነት አስፈሳጊ ነው ፍሬያማነት በባሕርያችን እንዲሁም በአገልግሎታችን ዩሚገለጥ የክርስቲያኖች ማንነት ነው ይልቁንም የጌታ ደቀ መዝሙር በኑሮው በንግግሩና በሐሳቡ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ማለት ፍትቅር ሰላምደስታ ትፅግሥት የዋህነትቸርነት ብጎነት እምነት ራስን መግዛት በሙላት የሚታይበት ሊሆን ይገባል የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ የጌታ ደቀ መዝሙር ለሠሆኑ በሕይወቱ የሚታይ ምልክት ነው ማቴ ይህ ፍሬ የሌለው የጌታ ደቀ መዝሙር አይደለም በተጨማሪም ደቀ መዝመር ለሌሎች ሰዎች የክርስቶስን አምላክነትና አዳኝነት የሚመሰክርና የሚያስሰተምር እግዚአብሔርንም ሰውንም የሚያገለግል በመሆኑ የአገልግሎት ፍሬዎች ይኖሩታል ጴጥ ሮሜ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ማሕየዊ የሆነ መንፈስ ቅዱስ በምእመናን ውስጥ ማደሩ ዮሐ ምእመናንን በዚህ ክፉ ዓለም ሲኖሩ ለማጽናናት ስለ ሆነ አጽናኝ ጳራቅሊጦስ ተብሎአል ጌታችን በምድራዊ አገልግሎቱ ደቀ መዛሙርቱን ካለባቸው ድካምና መንፈሳዊ ዐቅም ማጣት የተነሣ ጐድለታቸውን እየሞላ አለማወቃቸውን በማስተማር እያስወገደ አደራረጉን እያሳየ ከከሕተታቸው እንዲታረሙ እየመከረተሰፋ ሲቁቂርጡ አይዚችሁ እያለሲፈሩ እያደፋፈረ ተኣምራትን በማድረግ አለኝታነቱንና አምላክነቱን በመግለጽ ያጽናናቸውይረዳቸው እንደ ነበር ከቅዱስ ወንጌሉ እንረዳለን ጌታችን ወደ አባቱ ተመልሶ እንደሚሄድ በሚነግራቸው ጊዜ ሁሉን ትተው የተከተሉት ጌታ ጥሎአቸው መሄዱ አስደንግጦአቸው ሲታወኩ አባት እንደ ሌላቸው ልጆች ትቼአችሁ አልሄድም ስፍራ አዘጋጅቼ ተመልሼ አመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ ዮሐ እኔ ብሄድ ይሻላችኋል ከሄድሁ በኋላ ከናንተ ጋር የሚኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል ዮሐ በማለት ከእኛ ጋር ለዘላለም ዐብሮን የሚኖር አጽናኝ እንደሚያስፈልገን ዐውቆ አስቀድሞ ስለ አጽናኙ መላክና አስፈላጊነት የተሰፋ ቃልን ሰጥቶአቸዋል ይህንንም ተስፋ ከዕርገቱ በፀሥረኛው ቀን ከትንሣኤው በዐምሳኛው ቀን ወደዚህ ምድር በመምጣት ተስፋው ፍጻሜ አግኝቶአል አጽናኙ ወደ እዚህ ምድር የሚመጣበትንና በምእመናን ውስጥ የሚያድርበትንም ምክንያት ጌታ በወንጌሌ ሲገልጽ እርሱ ያስተምራችኋል ይመራችኋል ያሳስባችኋል ኀይልን ይሰጣችኋል የምልክላችሁንም መንፈስ ለብሳችሁ ምስክሬ ትሆናላችሁፍሬም ታፈራላችሁ በማለት ፍሬ እንድናፈራ ዐብሮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስን ላከልን ከአብ ከተላከልን ዮሐ ቲቶ ከመንፈስ ቅዱስ ዐበይት ሥራዎች መካከል አንዱ በምእመናን ውስጥ መልካሙን ባሕርይየመንፈስ ፍሬን እንድናፈራ ማድረግ ነው ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን የመንፈስ ቅዱስን ሥራ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅርነ ደስታ ሰላም ትዕፅግሥት ቸርነት በጎነትእምነት የውሃትራስን መግዛት ነው በገላ በማለት ተጠቅሶ እናገኛለን የመንፈስ ፍሬን ማፍራት ማለት የክርስቶስን ሕይወት መላበስ ማለት ሲሆን በሌላ አባባል ኢየሱስ ክርስቶስን መምሰል ማለት ነው ስለዚህ የክርስትና ፍጻሜው ክርስቶስን መምሰል ነው እንዳልነው ሁሉ የመንፈስ ፍሬን ማፍራት የክርስትና ግቡና ፍጻሜውም የእግዚአብሔር ክብር እንደ ሆነ ከዚህ እንረዳለን የባሕርያቱ ቀኑጥር ዘጠኝ ሲሆኑ በአንድ ምእመን ውስጥ ሳይነጣጠሉ በአንድነት ስለሚገኙ አንድ ፍሬ እንጂ ብዙ ፍሬዎች አይደሉም ሁሉም ባሕርያት በክርስቲያኑ ውስጥ የሚታዩ ናቸው አንድ ክርስቲያን ፍቅር ኖሮት ደስታ ወይም ሰላም ላይኖረው አይችልም አንዱ ክርስቲያን ከሌላው የሚለየው በፍሬዎቹ የጥራት መጠን ማለትም በሕይወቱ ውስጥ በሙላት መገለጥና ያለ መገለጥ ብዙ በማፍራትና ባለማፍራት ደረጃ እንጂ ፍሬ የሌለው ክርስቲያን የለም ፍሬ ከሌለው ክርስቲያን ነው ለማለት አይቻልም ምክንያቱም ፍሬ ለማፍራት ዘሩ በውስጡ ይኖራልና ነው ፍሬ የሌለው ዛፍ ለተካዩም ለራሱም አይጠቅምምና ባለቤቱ ይቄርጠዋል ሌቃ» ፍሬ ሳናፈራ መቂቁየታችን አግዚአብሔር ተደስቶብን ያለ ፍሬ እንድንኖር ፈቅዶልን ሳይሆን ከታላቅ ትዕግሥቱ የተነሣ ፍሬ እስክናፈራ ድረስ ጊዜ መስጠቱ ነው ፍሬ የማያፈራውን ዛፍ ወደ እሳት እንደሚጥሉት እንዲሁ ፍሬ የማያፈራ ክርስቲያን ይጣላል ይቅር ባይ እግዚአብሔር ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ ኤፌ ይቅርታ በበዳይና በተበዳይ መካከል የሣከናወን ጐዳይ ነው በዳይና ተበዳይ ከሌለ ይቅርታ የሚባል ነገር የለም ምንጊዜም ይቅርታ የሚያደርገው ተበዳይ ሲሆንነ በበዳዩ ላይ ቅጣት እንዳይደርስበት ሲል በደሉን መተውን መርሳትንም ያመለክታል ከዚህ በመነሣት ይቅርታን ማግኘት ማለት በዳይ በበደሉ ምክንያት ማግኘት የሚገባውን ቅጣት አለ ማግኘቱን ያሳያል ምሕረት ማድረግ የእግዚአብሔር ባሕርይ ነው መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረው ሰው እግዚአብሔርን መበደሉንና እግዚአብሔር ደግሞ ኀጢአተኛውንና በደለኛውን የሰውን ልጅ ከወደደው ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደሉ ምክንያት የሚደርስበትን ቅጣት ተመልክቶ ስለ ዐዘነለት በአንድ ልጁ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ይቅርታ እንዳደረገለት የሚገልጽ የይቅርታ መጽሐፍ ነው የጌታችን በመስቀል ላይ ደሙን ማፍሰሱና ሥጋውን መሞረሱ ስለ ምሕረት የተደረገ ቤዛነት ነው ማቴ የፍቅር ውጤት ነው ይቅርታ የፍቅር ውጤት ነው ፍቅር የኀጢአትን ብዛት ይሸፍናል እንደሚል ሁሉ ዴጥ ፍቅር በሌለበት ይቅርታ የለም እግዚአብሔር ይቅር ያለን ስለ ወደደን ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ እንጂ እኛ ስላደረግነው መልካም ሥራ ወይም ከእኛ የሚያገኘው ጥቅም አጓጐቶት አይደለም የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ነው ይቅርታ ማግኘት መብት አይደለም በየትኛውም ሕግ በደለኛ መቀጣት አለበት የበደል ደመወዙ ሞት ነውና ሮሜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ያገኘነው ምሕረት መብታችን ሳይሆን በጸጋ የተሰጠን የእግዚአብሔር ቸርነት ነው ስለዚህ ነው ቅዱስ ዳዊት እአንደ ምሕረትህና ቸር ነትህ ብዛት መተላለፌን ይቅር በል መዝ ያለው ይቅርታ የእግዚአብሔርን ጸጋ ያሳያል ጸጋ ማለት ማግኘት የማይገባንን ስጦታ ማግኘት ማለት ነው በደለኛ በኀጢአቱ ምክንያት ማግኘት የሚገባውን ፍርድ ሳይሆን ማግኘት የማይገባውን ልጅነትን በክርስቶእጳ ማግኘቱ የእግዚአብሔርን ወደር የማይገኝለት ጸጋ ያሳያል የጸጋ ልጆች ተባልን ይህ ጸ።