Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي
  • قائمة القراءة
  • مختصر
  • كتاب مسموع
  • بحث
  • تحميل
  • myzon
  • تسجيل الدخول
  • تسجيل
English  አማርኛ  Français  العربية
كتاب اليوم

ሞቶ መነሳት.pdf


  • word cloud

ሞቶ መነሳት.pdf
  • Extraction Summary

ማኾም ከእኔ ቢሮ ይልቅ እዝያው ፎቶ ሴክሽን እንደሚሻል ግልፅ ነው ። በጣም ከሚገርመው ነገር ግን ወያኔ የፈጠራ ድርሰት በእኔን በጓደኛዬ ላይ ማስወራቱ ነው ። አስመራ በአጭር እርቀት ላይ ነጋ ጠባ የማየው ክልል ነው ። እጅግ ወደ መሬት ዝቅ ብሎ በበረረ ቁጥር የነዳጅ ፍጆታው እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ነው ። ታድያ የሳዑዲ ግዛት ከመራቁ ጋራ ነዳጁ በሰላም የምፈልገው ከተማ ላይ ያደርሰኛል ማለቱ አስተማማኝነቱ እጅግ አነስተኛ ነው ። ከሁሉም ከሁሉም ግን ገና በጊዜ በ ዓ ም ወያኔ የአገር ጠላት ነውና ከእሱ ጋር ብንሰራ እንጀራ አይውጣልን በማለት ብን ብለው ወደ ሳዑዲ በኤል አውሮፕላን የኩበለሉት የስራ ባልደረባዎቼና ጓደኞቼ ከአመት የሳዑዲ የስደት ኑሮ በኋላ አሁንም በወያኔ ድንበር ዘለል ነፍሰ ገዳዮች ሀይወታቸው ማለፉ እጅግ እያሳዘነኝ የምኖርበት ኩነት ነው ። ከረዥም ጊዜ በኋላ ግን ሁለቱን በእጄ የሰለጠኑትን ወጣት የአየር ሃይል አብራሪዎችን በሃይሉ ገብሬንና አብዮት ማንጉዳይ በአዲስ አበባ እየተደረገ የነበረውን የጅምላ ግድያ ተባባሪ ላለመሆን ወደ ጅቡቲ ጥገኝነት ፍለጋ ቢሄዱ በለጋ እድሚያቸው የሰውን ስጋ በቁሙ ለሚበሉ የሰው ጅቦች አሳልፈው መስጠታቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ በላይ ጠላቱ የጅቡቲ መንግስት መሆኑን ሳስበው በቁጭት ነው። አሟሟቱ እጅግ አንጋጋሪ እንቆቅልሽ እንደሆነ ነው ።

  • Cosine Similarity

እኔም ከአዲስ አበባ መኖርያ ቤቴን ለቅቄ ደብረ ዘይት ከትሚያለሁ ጠዋት የስልጠና ስኳድሮንከሰአት በኋላ ደግሞ ከተዋጊ ስኳድሮን ጋር መደበኛ ተግባሬን በማከናወን ላይ ነኝ በአበሻ ግንቦት ቀን በፈረንጆቹ ደግሞ ጁን ነው በጠዋቱ የስልጠና በረራዎችን አከናውኙ ከሰዓት በኋላ ደግሞ የውጊያ ስኳድሮን ሚግ አውሮፕላንን የውስጥ አካል የፋሟሚላራይዜሽን ትውውቅ የክፍል ውስጥ ትምህርት እየወሰደኩኝ ነው በአበሻ ከቀኑ ሰዓት ይሆናልበፈረንጆቹ ከሰዓት በኋላ ሰዓት ሻለቃ በሪሁ የተባለ በአየር ሃይል የመከላከያ ሴኩሪቲ ሰራተኛለብርቱ ጉዳይ እንደሚፈልገኝ ይነግረኛል ትምህርት ላይ ነኝና እንደጨረስኩ እንደምንነጋገር ተስማምተን ውጪ ይጠብቀኛል ሻለቃ በሪሁ ኪዳነ ማለት ከአየር ሃይሉ ዋና አዛዥ ጀነራል አበበ ተ ሃይማኖት የበረሃ ስሙ ጆቤ ጋር በቅርብ ከሚሰሩ የትግራይ ተወሳጆች መካከል አንደኛው ነው ከመከላከያ ዋናው መሥሪያ ቤት ጋር የተያያዘ የደህንነት ሥራ ሲሰራ የኖረ ሲሆን አየር ሃይልም ከመጣ በኋላ ያንኑ የጆሮ ጠቢነት ሥራን የሚያከናውን ነው እግረመንገዱን ግን በአየር ሃይል የበረራ ት ቤት የበረራ ሙያ ሥልጠና እንዲያደርግ ተፈቅዶለትበመጀመርያ ደረጃ የበረራ ስኳድሮን ውስጥ ተመድቦ በችሎታ ማነስ ከበረራ ሙያ የተባረረ ሲሆንለወያኔዎች በሚሰጥ ልዩ ችሮታ ብቻ በሄሊኮፕተር ስኳድሮን አዛዥ ሆኖ ተመድቦእየሰራያለነው እኔና አንድ የሥራ ባልደረባዬ የክፍል ውስጥ ትምህርታችንን ጨርሰን ስንወጣ በሪሁን ባለማግኘታችን አንዲት ለስኳድሮናችን የተመደበች መኪና እያሽከረከርኩኝ በቀድሞው ስያሜው የጀግኖች አምባበወያኔዎች ዘመን ግን የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ተብሎ ከሚጠራው ቅጥር ግቢ ለቀን ስንወጣበሪሁ ከኋላ በከፍተኛ ፍጥነት እያሽከረከረ ይደርስብኝና በምልክት ካስቆመኝ በኋላወደ እኔ በመቅረብ ለከፍተኛ የሥራ ጉዳይ እንደፈሚልገኝና እርሱ በያዛት መኪና አብረን እንድንሄድ በጠየቀኝ መሰረት የያዝኳትን መኪና ከጎኔ ለነበረው የሥራ ባልደረባዬ ሰጥቼ በበሪሁ መኪና ወደ ዋናው የአየር ሃይል ግቢ አመራን በመንገዳችን ላይ ግን ሱዳን ኤርትራን ደግፋ ልትወረን ጦሯን ወደ ድንበር እያስጠጋች ነውና የኢትዮጵያንና ሱዳንን ወሰን የሚያካልል ለበረራ የምንጠቀምበትን ማፕ ካርታ ከእኔ ቢሮ ፈልጌ እንዳገኝለት ይጠይቀኛል የነገረኝ ታሪክ እውነትነት ሊኖረው እንደሚችል ባልጠራጠርም ከእኔ ቢሮ ማፕ መፈለጉ ግን አልመስልህ አለኝ ይህንን ለሚያክል የአገር ጉዳይ በዚህ ሳይ በሪሁን ለሚያክል ምርጥ የወያኔ ካድሬ የአየር ሃይሉ የኤሪያል ፎቶ ሴክሽን ክፍል በሰፊው ክፍት ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ አልነበረኝም። የአብረሃ ከሚከተለን መኪና ውሥጥ ካሉ ሰዎች ጋር በምልክት መነጋገሩ በዚህ እየመሸ ባለ ሠዓት እነዚህ ሁለት ሰዎች መካከል መገኘቴ የሬድዮ ግንኙነቱ በአጠቃላይ ከእኔ ጋር አንድም የጋራ የሆነ ጨዋታ በመካከላችን ያለመነሳቱና ከሁሉም በላይ ግን ከእኔ ቢሮ ማፕ ካርታ ፈልጎ ቢሮዬ ከደረስን በኋላ ግን የማኙ የካርታው ሥም ያለመነሳቱ ሁሉንም በአንድ ጊዜ ስመዝነው አደጋ መስል ነገር ውሥጥ እሆን ያለሁት ። እዚያው አየር ሀይል ደጃፍ ላይ አየር ሀይሎችን እያየሁ አደግሁ ከዚያም እዚያው አየር ሀይል ተቀጠርኩ። ወለሉ ላይ የፈሰሰው ሸንት መሰል ነገር ግማታም ፈሳሽ ምን አልባትም እዚህች ጠባብ ክፍል ውሥጥ ሌላ የእኔ ቢጤ ይኖር ይሆን የሚለውን ጥያቄ በአእምሮዬ ውሥጥ አጫረው ። በሃሳብ ደንዝፔ ከአንድ ቦታ ሳልነቃነቅ ተገትሬ ባለሁበት ሰዓት የአለሁባት ክፍል በር ተከፈተና ባትሪ የያዙ ሁለት ሰዎች ወደ ውስጥ በመግባት ግራና ቀኝ ደግፈውኝ ወደ ውጭ እንድራመድ ትእዛዝ ሰጡኝ ። አሁንም ሁለቱ በትግሪኛ ተነጋገሩና ከዚያም ወደ እኔ በመዞር በሰላም ሁሉንም እንድትነግረን እድል ተሰጥቶህ ልትጠቀምበት ፈቃደኛ አልሆንክም ስለዚህ የ ሰዓት ጊዜ እንሰጥሃለንና ተጠቀምበት ብለው ደግፈው ያመጡኝን ሰዎች ጠርተው በተለመደው የትግሪኛ ቋንቋ የሆነ ነገር ብለዋቸው በመጣሁበት ዓይነት እግሬን የታሰርኩበት ሰንሰለት እንደልብ ስለማያራምደኝ ግራና ቀኝ ደግፈው ቀስ እያልኩ እየተራመድኩ ወደዚያች መልኳን እንኳ በእርግጥ ወደ ማላውቃት ጨለማ ክፍሌ መልሰውኝ በሩን በጀርባዬ ቆለፏት። ለምን ያክል ሰዓት አንድ ቦታ ቆሜ በሃሳብ እንደምብሰለሰል መገመት አልቻልኩም እንጂ መቀመጥ ከነመኖሩም ረስቼዋለሁ ። ይሄ ደግሞ እጅግ ቅስም ይሰራል በዚህ ዓይነት አሰቃቂ አኳኋን በግምት ለአንድ ቀናት እንደቆየሁ አንድ ቀን ከለመድኩት ሰዓት ውጪ የክፍሌ በር ተከፍቶ ሁለት ሰዎች እየተጣደፉ በመግባት ግራና ቀኝ ደግፈው አይኔን በመሸፈን ይዘውኝ በመውጣት መኪና ላይ ጭነውኝ መንገድ ቀጠልን ። እርግጠኛ ነኝ ከ ደቂቃ በላይ ተጉዘናል መጨረሻ ግን መኪናዋ ሙሉ ለሙሉ ቆመችና ግራና ቀኝ ደግፈውኝ ወረድኩ ። ይህንን ቅዝቃዜና ዝምታ መቋቋም እንደማልችል ከውዲሁ ለእራሴ ነገርኩት አሁንም እንደበፊቱ እኩለ ሌሊት ግድም ይመስለኛል ሰዓት መለየት በእጅጉ ጠፍቶብኛል እዚያችው ከጠባቡዋ ክፍሌ ጐን በተሰራች ሽንት ቤት እንድጠቀም ያደርጉኛል ባትሪ የያዙ ሰዎች ከመሆናቸው በስተቀር አንድም ጊዜ ፊታቸውን ለማየት አልታደልኩም ። ቁጥራቸውን ባላውቅም የእጅ ባትሪ የያዙ ሰዎች ወደ ውስጥ አበሩብኝ ኩርምት በዬ ቁጭ እንዳልኩኝ ነው ቆጣ ባለ ድምፅ ና ውጣ የሚል ድምፅ ተሰማኝ ዛሬ የመጨረሻዬ መሆኑ ነው ። ይመስለኛ ሁለት ሰዎች መሃል ነው የተቀመጥኩት አልፎ አልፎ በትግሪኛ ይነጋገራሉ ረዥም ጉዞ ተጉዘናል በየመሃሉም መኪናው ለአጭር ጊዜ ይቆማል ሰው ወርዶ ተመልሶ ሲሳፈር ይሰማኛል ። መኪናው ሙሉ ለሙሉ እንደቆመ ከረዥሙ መኪና ላይ ደጋግፈው አንድ በር ከፍተው አይኔ ላይ የታሰረውን ፈትተውልኝ ወደ ውስጥ ገባ አድርገው በሩን በጀርባዬ ላይ ጠረቀሙት። አሁንም ቀናቱ አንድ ሁለት እያሉ ያልፋሉ ። የተዘጋ ቤት ጨለማ ክፍል ። አንድ ቀን እንዲሁ እንደወትሮው በሬ ተከፈተ አለፍ አልፍ እያለ የተፈፀመ በመሆኑ ብዙም አልተደነቅሁም እንደተለመደው ባትሪ በእጃቸው የያዙ ሰዎች በሩ ላይ ቆመው ወደ ውጪ እንድወጣ ጠየቁኝ መልስ ሲያጡ ግን ቀርበውኝ ደጋግፈው አንሱኝና የሆነ ነገር በትግሪኛ ተነጋግረው ተመልሰው በሩን ዘግተውብኝ ተመለሱ ። በግምት ከአንድ ሰዓት ያክል ቆይታ በኋላ በሩ እንደገና ተከፈተና ወደ ውስጥ ገብተው እግሬ ላይ ያለውን ሰንሰለት ፈቱልኝ ቀኖ ብዬ ሰውዬውን ለማየት ሞከርኩ ዙሪያዬ በእጃቸው የያዙት ባትሪ ከሚፈጥረው ብርሃን በስተቀረ ምንም ማየት አልቻልኩም የእግሬ ሰንሰለት በመፈታቱ እስከ ዛሬ ስደነግጥ ከነበረው በላይ ደነገጥኩ እንዴ ለምን የሚል ቃል ሳላስበው ከአፌ ወጣ ሳቅ ተሰማኝ የመገረም ሳቅ ። ፀሀይ ያልነካው አይነት ሆኖ ጠይም ፊቱ እንደመቅላት ፈካ ያለ ይመስለኛል አንድ ነገር ግን በልቤ ጠረጠርኩ ያሳሰረኝ ይሄ የቅርብ ወዳጄና የስራ ባልደረባዬ ይሆን ። አባቱም በአየር ሀይል መስሪያ ቤት ወስጥ ባለ ከፍተኛ ማዕረግ ባለቤትና ለረዥም ጊዜ አገልግለው በጡረታ በክብር ከመስሪያ ቤቱ የተሰናበቱ የአየር ሀይሉ ዕንቁ ልጅ ናቸው ። ከጐኔ የተቀመጠው ጓደኛዬ ዳንኤል ወደ ደብረ ዘይት ከተማ እየገባን ስንመጣ አልፎ አልፎ ወደ እኔ ይመለከት ጀመር ። አንዴ ሆዴ ሲሸበር አንድ ጊዜ ደግሞ በአሳለፍኩት መከራ እየተከዝኩኝ እግዚአብሄርም መከራ በቃህ እንዲለኝ እየተማፀንኩት በተጨማሪም አይኔ እያየ ባለው ሁኔታ እየተገረምኩ እያለሁ መኪናዋ አየር ሀይል ጠቅላይ መምሪያ ህንፃ ፊት ለፊት ቆመች ። ይህንን ሰው አየር ሀይል ውስጥ ከ ዓመታት በላይ አውቀዋለሁ በማናጅመንት ዲፓርትመንት ውስጥ ከቅርብ ጓደኛዬ ጋር አንድ ላይ ይማሩ ነበር ። እዚያው የእስረኞቹ አለቃ መኝታ እያዘጋጀልን ነው ለእኔና ለጓደኛዬ አንድ ክፍል ውስጥ ፍራሽ ሲዘረጉልን አያለሁ እስረኞቹ ስላላወቁ ነው እንጂ እኔና ጓደኛዬን በአንድ ክፍል ውስጥ መታሰር ማደር መፈቀዱን ማመን አልቻልኩም ። ትናንትና ከነበርኩበት አሰቃቂ የብቸኝነት ጉሮኖ በአንድ ቀን ከሰው ጋርና ከጓደኛዬ ጋር በአንድ ክፍል ውስጥ በነፃነት ይለቁናል ብዬ ማመንን በፍፁም አልቻልኩም እንዲህ ማድረግ ከተቻለስ ሁለት አመት ሙሉ የሰውን ፍጡር ከነነፍሱ መቅበር ለምን አስፈለገ መልስ ያላገኘሁለት እንቆቅልሽ ከቁርስ በኋላም ሰው ሁሉ ግቢው ውስጥ ፈሶ ስለ እኛ ያንሾካሹካል አሁንም ደፍሮ ወደ እኛ የቀረበ የለም እኔና ጓደኛዬ ለብቻችን ገንጠል ብለን እያንዳንዱን ገጠመኝ እናወራለን ። ወይ ጊዜ አልኩኝ በልቤ ሰው ኑሮውን የመስላል የሚባለው እውነት ነው ለካ ኩ ል ተመስገን አበበ ማለት አንድ ጊዜ ጎንደር ነኝ ሌላ ጊዜ ደግሞ ትግሬ ለመሆን እየተዘበራረቀበት የተቸገረ ግለሰብ ነው ። በአንድ ጊዜ ድንገት ለኢትዮጵያ ዋና አስፈላጊ ሰው የሆንኩበት ምክንያት እንዲያው ጨዋታ መሰለኝ ነገ ተመልሼ እመጣለሁና አስብበት ለሚለው ቀልድ ግን ፈጣን መልስ ሰጠሁት ምንም የማስበው ነገር የለኝም የምትለኝን ሁሉ ለመፈፀም ዝግጁ ነኝ አልኩት ። በተለያዩ አውደ ውጊያዎች በአየር ላይ የጠላትን አውሮፕላን በማጋየት ጀግንነቱ የተመሰከረለት ከፍተኛ መኩንን ቀደም ሲል ለእናት አገሩ ዳር ድንበር መከበር ሲፋለም ከምድር በተተኮሰበት ፀረ አውሮፕላን ሚሳኤል ተመቶ በጃንጥላ ከወረደ በኋላ በጠላት እጅ በመውድቅ ለስምንት አመታት ሲንገላታ ኖሮ በስተመጨረሻ በተደረገለት ምህረት በህይወት በመመለስ ጣፋጭ ኑሮውን ሀ ብሎ ማጣጣም በጀመረበት ሰዓት ምህረት ካደረገለት መንግስት ጋር በተቀሰቀሰ ፋይዳ ቢስ ጦርነት ገና በመጀመሪያው የውጊያ ውሎው ወደ ጠላት ግዛት ዘልቆ በመግባት እንቅስቃሲያቸውን ለመግታት እያደረገ በነበረው ጀግንነታዊ ተግባር ላይ ድንገት አውሮፕላኑ በአየር ላይ እንዳለ ከምድር በተተኮሰበት ፀረ አውሮፕላን በመመታቱ ህይወቱን ለማትረፍ በጃንጥላው ቢወርድም በአሳዛኝ ሁኔታ ለሁለተኛ ጊዜ ምህረት ባደረገለት መንግስት እጅ መውደቁን የሰማሁ ዕለት ልጆቹን እያሰብኩና የእሱንም ተግባቢና ሰው አክባሪ ተጫዋች ባህሪውን ከሁሉም በላይ ግን በአስተማሪነቱ ያካፈለኝን ሙያዊ ዕውቀት በትዝታ እየከለስኩ ሃዘን ዘልቆ ተሰምቶኝ አይኔ እምባ አቅርሯል በሌላም ጐኑ ደግሞ ወያኔ አየር ሀይሉን በእራሱ ሰዎች የመተካት ህልሙን እውን ለማድረግ ሲጣደፍ በነበረበት ወቅት በችሎታ ማነስ ከበረራ ሙያ የተባረሩት ሁሉ ሳይቀሩ አውሮፕላን ለማስነሳት በመሞከር ርቀው እንኳ ሳይጓዙ እዚያው ደጃፍ ላይ እየተፈጠፈጡ እራሳቸውን ለሞት የሀገር ሃብት የሆነውንም አውሮፕላን ለውድመት ማብቃታቸው የቁጥሩ ብዛት እጅግ ሲዘገነነኝ ስመ ጥሩውን የኢትዮጵያ አየር ሀይል በዚህ አይነት ታሪኩን ማጉደፋቸው ግን ለሀገርም ለወገንም አሳፋሪ ጥቁር ነጥብ ነበር ። ዛሬ ጓደኛዬ ዳንኤል በየነ በህይወት የለም ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

تعليقات:


memezon

خيارات التنزيل | تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي | كتاب اليوم

© dirzon | شروط الخدمة | خصوصية | حول | خدمات | اتصال