Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي
  • قائمة القراءة
  • مختصر
  • كتاب مسموع
  • بحث
  • تحميل
  • myzon
  • تسجيل الدخول
  • تسجيل
English  አማርኛ  Français  العربية
كتاب اليوم

መግባት እና መውጣት በዕዉቀቱ ስዩም.pdf


  • word cloud

መግባት እና መውጣት በዕዉቀቱ ስዩም.pdf
  • Extraction Summary

» አለኝ «ጆሮዬን ከሰገራዬ ጋራ ምን ያገናኘዋል። ወይስ አሜሪካ ሲገቡ የወንደላጤ እና የባለትዳር በር የተለያየ ነው።» «የግሌ አይደለም ካንድ ጉሬዛ ጋራ ተዳብዬው ነው።» «ከዚህ በፊት እንደገለጽሁት በእኛ መንደር ፎቶ ከተነሠት ይልቅ ሞተው የቶነሠሥ ይበዙ ነበር በተለይ ፎቶ ለብቻ መነሣት እና ጉርድ ፎቶግራፍ አምጣ ሲለኝ የእንጀራ አባቴ በቁም የተነሣውን ፎቶ ከወገቡ በላይ በመቀስ ቆርጩ ወስጃለሁ ከእኛ መገባትና መውጣት ቀና ብዬ በሽብር ዐየዋለሁ ምን አሸበረኝ።» በማለት መክሊት ከሐሳኬ መሰሰችኝ ከምዑዝ ጋራ ነው ቀጠሮሽ።» መልሳ ጠየቀችኝ ሙጨ ወ መ መገዛትና ውጣት «ጣማችሁ ልትደግሙት ነው። ምን አደርጋለሁ።

  • Cosine Similarity

በትምህርት ቤቱ ሥር ቤተ መጻሕፍት ቤተ ሰገራ እና ሽንት ቤት እንዲሁም ቤትሆቨን በተባለ ያገራቸው ሰው የተሰየመ ካፍቴሪያ ይገኛል ወደ ካፍቴሪያው የተለያዩ ሰዎች ይመጣሉ በተለይም ጀርመኖች ጀርመንኛ ቋንቋ የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እንዲሁም ጀርመኖች በሚገኙበት ካፌ ስለ ገቡ ብቻ ጀርመን አገር የገቡ የሚመስላቸው ቦዘኔዎች ይመጣሉአባባሉ የጓደኛዬ የምዑዝ ነው ወደ ቤትሆሸን ካፌ የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ወንዶች እና ሴቶች የአንድ አገር ልጆች አይመስሉም ምነው ቢሉ ሴቶቹ እንኳን ዐይናቸው መነጽራቸው የሚያማልልላቸው ያነገቡት ግዙፍ ቦርሳ እና የለበሱት ልብስ የሚያምርባቸው ትኩረትን ሁሉ በቁጥጥር ሥር የሚያውል ዐምባገነን ቂጥ የሚከተላቸው ሲያወሩ እና ሲሥቁ በራስ መተማመን የሚታይባቸው ናቸው ወንዶቹ በበኩሳቸው እንኳን ሱሪያቸው ቆዳቸው የሰፋባቸው ምቾታቸው ኅቡእ የገባባቸው እምብዛም የማይሥቁ ሳት ብሏቸው ከሣቁ እንኳ ሳል የሚያደናቅፋቸው አገጫቸውን እጃቸው ላይ ፌሬ ው ው መገባትና መውጣት አስደግፈው ለረጅም ጊዜ ስለሚቆዝሙ ራሳቸው ባንገታቸው ሳይሆን በአጃቸው ድጋፍ የቆመ የሚመስልባቸው ናቸው በቤትሆቨን ካፍቴሪያ ውስጥ ጠዋት የማስተናገድ ሥራ እየሠራሁ ከሰዓት የጀርመን መንግሥት በፈቀደልኝ መሠረት በነጻ የቋንቋ ትምህርት እየተማርሁ ትንሽ እንደ ቆየሁ ጆሮዬን ያመኝ ጀመር ሕመሙ እንደ ጀመረኝ ጆሮዬ የወትሮ ልምዱን ትቶ አዲስ አሠራር አመጣ በል ሲለው አዛብቶ ይሰማል ካፍቴሪያው ግድግዳ ላይ በተንጠለጠለው ቴሌቪዥን የቢቢሲ ዜና ስከታተል ጆሮዬ ዝፎ ዐየል የሚለውን ኬነ ል ብሎ ይሰማል የርዩከ አገሮች የሚለውን የዐርዐ አገሮች ብሎ ይተረጉማል አንዳንዴ ደሞ ባከራዬ ቤት ጣራ ላይ ከጭስ ማውጫው አጠገብ እንደ ተሰቀለው የወሬ መግላሊትርዲሽ መረጃ ከሩቅ ይጠልፋል ሕመሙ በጆጀመረኝ ሰሞን ካንገት በላይ ሕክምና ወደሚሰጥበት ማእከል ሄድሁ ዶክተሩ ጓንቱን አጥልቆ በጆሮዬ ቀዳዳ አጮልቆ አእምሮዬን የሚሰልል ይመስል ግማሽ ሰዓት ተለግቦ ቆየ ሲጨርስ ራሱን ነቅንቆ ጓንቱን አውልቆ እስኪርቢቶ ካነሣ በኋላ «የሰገራ ምርመራ ያስፈልግፃል ቀጣዩ ክፍል ሄደህ ሁለት መቶ ብር ከፍለህ ናሙና ስጥ። » ሲል ጠየቀኝ አንድ ቀን ለማስታወስ ሞከርሁ የእንጀራ አባቴ በጣም ጥሩ ሰው ነበር በሕይወቱ አንድ ጊዜ ብቻ ነው የመታኝ እሱም እንዴት ነበር። » አልሁ «ምን ያማታል አዲስ ጉትቻ ገዝታ ነው» አሉ አቶ ተሻገር እየሣቁ ይሄኔ በር ተከፈተና የግራ ጎረቤቴ በላቸው ሁለት ሙዝ እና ሁለት ብርቱካን እንዲሁምአምስት ካከለኛ ዱባዎች በፌስታል መገባትና መውጣት መገባትና ጠወጣት አንጠልጥሎ ገባ ወዲያው ለአከራዮቼ የተናገርሁትን ለእሉም ደግሜ የሚለውን መጠባበቅ ጀመርሁ አንባቢ ከፈቀደልኝ አሁን ደግሞ ስለ አብሮ ተክከራዬ ስለ በላቸው ኑሮ ጥቂት ልናገር በላቸው ዕድሜው ለሥራ ሲደርስ ባንድ ትልቅ መጽሐፍ መደብር ውስጥ ተቀጥሮ ይሠራ ነበር የመደብሩ ባለቤት ብዙ መጻሕፍትን ከሕንድ ቢያስገባም አንባቢውን አብሮ ስላላስገባ ለኪሳራ ተዳረገ ጨርሶ ከመንኮታኮቱ በፊት ግን መደብሩን ወደ ምግብ ቤት ለመቀየር ወሰነ ይሁን እንጂ ከመጽሐፍ መደብር ወደ ምግብ ቤት የሚደረገው ሸግግር በጣም ሥር ነቀል እንዳይሆን ስለ ፈራ በመካከል አንድ መሸጋገርያ እንዲኖር አደረገ በመጽሐፍ መደብር እና በምግብ ቤት መካከል ያለው ብቸኛ መሸጋገርያ በምግብ ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ነው በዚህ መሠረት ሊቃውንት የጻፏቸውን ዞርሃ ከ ክዉ ልከሃከ ርጺ ፐከሬ የ ፈ ኪ ፐከፍ በክ ከ ከየ የሚሉ ይገኙበታል ቀጥሎ ፖስተሮች እና የአገር ካርታዎች በሚንጠለጠሉበት ቦታ ጭልፋዎችን እና ትሪዎችን ደረደረ በኋላም ክና ዘሼ የነበረውን የመደብሩን መጠሪያ ርዚ ፀዘርከጄ ብሎ በማሸጋሸግ የሬስቶራንቱን ሥራ በይፋ ጀመረ በላቸው በመጽሐፍ መደብሩ ውስጥ የነበረው ሥራ የሚሠጣ የሚገባውን መፈተሽ ሲሆን ከለውጡ በኋላ ደግሞ በሥጋ ቆራጭነት ተመድቦ ማገልገል ጀመረ በራሱ አባባል ከሰው ሽንጥ ወደ በሬ ሽንጥ ተሸጋገረ ማለት ነው በሳቸው ምኞቱ ትልቅ ደመወዙ ትንሽ የሆነ ሠራተኛ በመሆኑ ይህን ለማካካስ የብልጠት መላዎችን ይከተላል ይባላል ለምሳሌ አንደ ደንበኛ ወደ ሥጋው ሱቅ ይመጣና አንድ ኪሎ ሽቨ ባዊ መገዛትና መውጣት ቁረጥልኝ ብሎ ያዘዋል በላቸው በቢላዎው ወደ ምግብ ቤቱ በር እየጠቆመ «ግቡ ይመጣልዎታል» ይላል ደንበኛው ከፍሎ ወደ ውስጥ ሲዘልቅ በላቸው ሩቡን ኪሎ ጎምዶ ለራሱ ያስቀራል ከጊዜ በኋላ ደንበኞች እንደተታሰሉ ሲገባቸው እዚያው ቆመው ማስመዘን ጀመሩ በላቸው ስልቱን ቀየረ ከሥጋው ትንሽ ቆረጥ አድርጎ ሚዛኑ ላይ ካስቀመጠ በኋላ ሚዛኑ እንዲደፋ ጉልጥምት የሚያህል አጥንት ጣል ያደርግበታል አጥንቱ ሲያልቅ ቢላዎውን ከሥጋው ጋራ አብሮ ይመዝነዋል አሁን እንግዲህ በላቸው ችግሬን ከሰማ በኋላ «ግዴለህም አንድ በጣም የታወቁ የባህል ሐኪም አሉ እሳቸው ጋራ ፄደህ ትታከማለህ» አለኝ እኔን ትቶ አጥሚቴን እየተመሰከተ «ጎበዝ ሐኪም ናቸው። ፌዴ ው ው መገባትና መውጣት «አለ» «እንግዲያውስ ቡና አምጭልኝነ መክሊት ሣቀችና የታዘዘችውን አመጣችለት ጀርመኑ ከላይ ያሉትን ነገሮች የዘረዘራቸው ለፄለን እና ምዑዝ አማርኛ እንደሚችል ለማሳየት ነው ትዝ ይለኛል ለመንፈቅ ያህል እግዜር ይስጥልኝ ከሚለው የለማኝ ማባረርያ ሐረግ በስተቀር ሌላ አማርኛ አያውቅም ነበር አሁን ግን በተለይ ሴትን እና ልማትን የሚመለከቱ ቃላትን እና ሰዋስው ጠንቅቆ ያውቃል መክሊት ከቆይታ በኋላ እንደገና ሳትጠራ ተመለሰችና ንጹሑን ጠረጴዛ ትወለውል ጀመር እየወለወለች ትልልቅ ጡቶቿን ለጀርመኑ ታስጎበኘዋለች ጀርመኑም ታዛቢ መኖር አለመኖሩን ግራ እና ቀኝ ሰልሎ ካረጋገጠ በኋላ ጡቷን በከፍተኛ ትጋት መመልከት ይጀምራል አስተያየቱ ደሞ ከመጥባት አይተናነስም አንዳንዴ ካፌው ጭር ሲል ጀርመኑ መክሊትን ይጠራትና «ማኪያቶ አምጭልኝነ ብሎ ካዘዛት በኋላ ዞር ስትል «ነጣ ይበል ታዲያ» ይልና ከማኪያቶው ንጣት ጋራ የሚያያዝ ይመስል ቂጧን በጥፊ ቸብ ያደርገዋል እኔ ከሥራዬ በቀር ሴት ቀና ብዬ አይቼ አላውቅም አንድ ቀን ብቻ ማንኪያ ወድቆብኝ ለማንሣት ባጎነበስሁበት እግረ መንገዴን ወደ መክሊት ቂጥ ተመለክከትሁ ያኔ በጣም ከመደነቄ የተነሣ ማንኪያው ከወለሉ ዐይኔ ከመክሊት ቂጥ ላይ ሳይነሣ ብዙ ጊዜ በማለፉ ሥራ አስኪያጁ መጥቶ አቃናኝ እኔ እና በዚህ ማስታወሻ ላይ በዝሮዝር የማላካትታቸው ሌሎች ሁለት ተስተናጋጆቸ ወዲያ ወዲህ ስንዋከብ መክሊት መገባትኝዓ መውጣት ግድግዳ ተደግፋ እና ፈገግ ብላ ወደ ጀርመኑ ትመለከታለች «ከፈረንጁ ጋራ መውጣት ትፈልጊያለሽ። » አልኋት አንድ ቀን «ከዚህ አገር መውጣት እፈልጋለሁ። እኔ ሳመነታ አንዱ ከጀርመን መጥቶ ቀደመኝ መክሊት የምትኖረው በአንድ ክፍል ቤት ውስጥ ከወንድሟ ጋራ ነው ወንድሟ ከኮምቦልቻ እስክ አዲስ አበባ በሚሠራው የመንገድ ሥራ ላይ ቻይናዎች ቀጥረውት ለጥቂት ጊዜ እንደ ሠራ ጥሎት ወደ አዲስ አበባ በመመላስ ከእኅቱ ጋራ አብሮ መኖር ጀመረ እናም በአንድ ክፍል ውስጥ በጥቂት ርምጃዎች ርቀት ዙጹጤ ው መገባትና መውጣት በተዘረጉ ሁለት አልጋዎች ላይ ማዶ ለማዶ ሆነው ይተኛሉ ጠዋት ወደ ካፌ ከመምጣቷ በፊት ቁርሱን ሠርታ ትራሱ አጠገብ አስቀምጣለት ትሄዳለች ስትመለስ ካልጋው ሳይወርድ ይጠብቃታል ልብስ ለመቀየር ወይም ለመታጠብ ስትፈልግ «ወደ ቀጣዩ ክፍል ግባ» ትለዋለች በእሷ እና በወንድሟ ቋንቋ ወደ ቀጣዩ ክፍል ግባ ማለት «ወደዚያ ዙር» ማለት ነው ወደ ሌላ አቅጣጫ ዞሮ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ይገተራል ወንድሟን ብዙ ላለማስቆም በችኮላ እና በስጋት ትለባብሳለች ወንድሟ ከክፍሉ መውጣት ሞቱ ነው አንዳንዴ ብቻዋን መሆን ስትፈልግ «አስኪ ዞር ዞር ብለህ ና» ትለዋለች በረንዳው ላይ ዞር ዞር ብሎ ይመለሳል እጮኛዋ ሳሚ ወንድሟን በጣም ይጠላው ነበር ለምሳሌ አንድ ቀን አጮኛዋ የወንድ እና የሴት ነገር ለማድረግ ወደ ቤቷ መጣ ወንድምዬው ግን አይገባውም ፀጉሩን እያፍተለተለ አልጋው ላይ ከመጎለቱም በላይ ከእጮኛዋ ጋራ የፍልስፍና ውይይት ለመጀመር ሁሉ ቃጣው ቢጠብቁት ቢጠብቁት አልወጣ ስላለ መክሊት ሳሙና ገዝቶ እንዲመጣ ጠየቀችው ወንድሟ ግን «ይኸው ሳሙና» ብሎ አንድ ደርዘን ከአልጋው ሥር አወጣ ቢጨንቃት ኦሞ እንዲገዛ ላከችው ወንድሟ ተነሥቶ ከመውጣቱ መክሊት እና እጮኛዋ ተያይዘው አልጋ ላይ ወደቁ ይሁን እንጂ የሚፈልጉትን ያህል አልተደሰቱም ወንድምዬው ካሁን አሁን ይመጣብናል ብለው ሰለ ሰጉ ወሲቡን አጣድፈው ጨረሱት ወንድምዬው ግን አለወትሮው ዘግይቶ በዝናም በስብሶ ገብቶ ጠፈጠፉን ከፀጉሩ ላይ እያራገፈ ጠሉን ከፊቱ ላይ እየጨመቀ ጥግ ፈልጎ ቁጭ አለ መክሊት ገና እንዳየችው ፊቷን በመዳፏ ውስጥ ቀበረች ለወሲብ ስትል ከቤቷ አጣድፋ ስላስወጣችው እና ዝናቻ ስለ አስመታችው ወንድሟ መግባትና መውጣት ው ዬኤ እንዳዘነባት ገብቷታል ለወንድሟ ስትል ወሲቡን አላግባብ ስላጣደፈችው እጮኛዋም ተቀይሟታል ከሁለት ያጣች በመሆኗ አዘነቹ ወንድምሸ አሁን ምንም አይሠራም። ለምን ወንድሜ ሆነ አላለሁ ለምን ከጎረቤታችን አብራክ አልተገኘ ም እላለሁ አንዳንዴ ደሞ ምናለ ያለወላጅ ተገኝቼ ቢሆን አላለሁ ሰው አንደ ዛፍ ለብቻው ከመሬት ብቅ ማለት ቢችል እንዴት ር ተን መገባትና መውጣት ጥሩ ነበር ከጥቂት ጊዜ በኋላ መክሊት የዓመት ፈቃዷን ወሰደች መክሊት ከካፌው ከቀረች በኋላ ጀርመኑም መምጣት አቆመ አንድ ቀን ከሥራ በቷላ ተቀጣጥረን ከጀርመኑ ጋራ ለመሰንበት እንደ ወስነች ነገረችኝ እናም ከዚህ በኋላ ባንድ ጊዜ ሁለት ቤቶችን ማስተዳደር ስለማትችል ወንድሟን ለማሰናበት እንደ ቆረጠች ነገረችኝ ወንድሟን አፍ አውጥታ ውጣ ለማለት ስለማትደፍር የማሰናበቱን የቤት ሥራ እኔ እንድወስድ ተማፀነችኝ የተሰጠኝ የቤት ሥራ ለእኔ የሚከብድ አልነበረም እርሷን የሚያስደስታት ከሆነ ወንድሟን እንኳን ከቤቷ ከምድሪቷ ማሰናበት አይከብደኝም በማግሥቱ አነጋግ ላይ እነ መክሲት ቤት ገብቼ በወንድሟ አልጋ አጠገብ ቁጭ ብያለሁ ወንድምዬው አጭር ነው ወይስ ረጅም። » ሲል ጠየቀኝ «ሥራ ከመግባቴ በፊት የምነግርህ ብርቱ ጉዳይ አለኝ» አልሁት «መርዶ እንዳይሀሆኝ ብቻ ዛረኦለማልቀስ አልተዘጋጀሁም መገባትና መውጣት እንዴት መጀመር እንዳለብኝ ስላላወቅሁ ዝም ብዬ ግድግዳውን ማዬት ጀመርሁ ግድግዳው ላይ ግዙፍ ፍሬም ያለው ፎቶ ተሰቅሏል በፎቶ ግራፉ ውስጥ መክሊት ለሰስዊዘርላንዱ አምባሳደር ቦምቦሊኖ እና ሻይ ስታቀርብ ትታያለች ከሩቅ እኔ የሻይ ማለቢያ ማሽኑን ስወለውል እታያለሁ «ዐየህ ባሁኑ ጊዜ መክሊት » ብዬ ጀምሬ ቆምሁ ወንድምዬው ለማስታረቅ የመጣሁ ሳይመስለው አልቀረም ከመታረቁ በፊት ትንሽ ለመግደርደር ያህል «የመክሊትን ነገር ተወው» ካለ በኋላ እንድቀጥል ዐይን ዐይኔን ያየኝ ጀመር «መክሊት እና አንተ በዚህ ቤት ውስጥ በመረዳዳት አብራችሁ ቆይታችኋል መክሊት ሥራ ትሠራለች ምግብ ታበስላለች ልብስ ታጥባለች ገበያ ትሄዳለች ከገበያ ትመለሳለች አንተም በበኩልህ ያከናወንሃቸው ተግባሮች ብዙ በመሆናቸው ልዘርዝራቸው ብል ጊዜ አይበቃኝም» «የእኔ ሲሆን ጊዜ አይበቃህም። «አገር ቤት እያለሁ ዳገት ላይ ቁጭ ብዬ ልቦለድ ማገበብ እወድ ነበር አልሁ ምዑዝ ቀና ብሎ በሚያባባ አስተያየት ከተመለከተኝ በኋላ «ልቦለዱን እኔ ላውስህ እችላለሁ ዳገቱን ደግሞ ሌላ ሰው ይተባበርህ» ብሎ አላገጠብኝ ትንሽ ቆይቶ ግን ጸጸት ተሰማው መሰል የአንድ ብር ጉርሻ አስቀምጦልኝ ወጣ የአናዛዥነት ተስጥኦ ነበረኝ የቀረብቷኋቸው ሰዎች ከተላመድኋቸው በኋላ ከምድር ተነሥተው ምስጢራቸውን ይዘከዝኩልኛል ከምዑዝ ጋራ ጓደኛ ከሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላም የሆነው እንዲህ ነበር አንድ ቀን ምዑዝ የካፌው ሽንት ቤት ውስጥ ገብቶ ወዲያው ተመልሶ ከመጣ በቷላ «ሽንት ቤቱ ውስጥ ሶፍት የማታስቀምጡት ለምንድን ነው። » አልሁት «ሴቶችን ፈልጌ» ሲል መለሰልኝ ዐየህ ካገር ፍቅር የሚገኘው ደስታ በየዘመኑ ይለያያል ምንጅላቶቻችን በአክሱም ሥልጣኔ ጊዜ ይሰማቸው የነበረው የአገር ፍቅር ስሜት ለእኛ አይሰማንም በአክሉም ሥልጣኔ ጊዜ የነበረው የሴት ገላ ጣዕም ግን አሁንም አለ በረጅም ፒዜ ልምዴ ቆንጆ ቆንጆ ሌቶች ሽዴዙዮጵቪሺቪሲቪሺንሲሲሲንሲሲሲሱንኣጻቪን ሠ መገባትና መውጣት ሩሩ የት እንደሚገኙ ዐውቃለሁ የቋንቋ ትምህርት ቤት ቆንጆ ሴቶችን እንደ ማግኔት ይስባል ፈረንጅ ቦይፍሬንድ ለማጥመድ ያቀዱ ሴቶች እዚያ ይከማቻሉ እና የፈለጉትን ፈረንጅ እስኪያገኙ ድረስ አብሯቸው የሚያዘግም ቢያገኙ አይጠሉም ሁለተኞኛ እንደ ሄለን ያሉ በውጭ አገር ባል ያላቸው ከባላቸው ጋራ ለመቀላቀል ቋንቋ የሚማሩ ሴቶች አሉ እኒህ ሴቶች ለጊዜው ብቸኛ ስሰሆኑ በብቸኝነታቸው መግባት ትችላለህ ከእኒህ ሴቶች ጋራ ያን ነገር ብትጀምር ባላቸው ራቁቴን በምወራጭበት ሰዓት መኝታ ቤት ድረስ ገብቶ በሽጉጥ ያዳፍነኛል ብለህ አትሰጋም ሴቶቹ ጉዳዩን በጥናት ስለሚያሳብቡት ለሸውክኛ ትዝብት የተጋሰጡ አይደሉም በዚያ ላይ እኒህ ሴቶች በኢኮኖሚም በስሜትም ባንተ ላይ ጥገኛ አይሆኑም ለቋንቋ ትምህርት የሚከፍሉት ገንዘብ ካላቸው ድፃ አይደሉም ሌላው እንደምታውቀው ፍቅር ሲውል ሲያድር ጭቆና ይሆናል እኒህ ሴቶች ግን ለጥቂት ጊዜ አብረውህ ቆይተው ወደ ውጭ ይሻገራሉ ገላቸውን እና ጸጸታቸውን ይዘው ይሄዱልፃል በዚያ ላይ ብዙ ያበሻ ወንድ የሴቶችን ያህል ቋንቋ ስለማይማር ያን ያህል ተፎካካሪ አይኖርብህም እንገዲህ ይህን ምስጢር ለብቻዬ ስለማውቅ ከብዙ ቤላ አቢሲኒያዎች ጋራ በሞኖፖል ተደስቻለሁ ግን ምን ዋጋ አለው። ፃ የኛም ነገር ከዚህ አይለይም ዐየህ በታሪክ እንደተመለከትነው ጀግናው ተዋግቶ ደካማው ተራብቶ የሌሎችን አገር ይቀማል ጀግና በደሙ ወላድ በስፐርሙ አገር ያቀናል ኣፍ ለምን ይሄን ትተን ስለሌላ ነገር አናወራም ምዑዝ ስለ ሌላ ነገር የሚሰው ስለ ሴት ነው ከአገር ወሬ ለማምለጥ ስለ ሴት ማውራት ይጀምራል ግን ስለ ሴት እያወራ ሳያውቀው ስለ አገር ማውራቱን ይቀጥላል ለካ ሴት የአገር ቁራኛ ኖራለች ሁለቱ ተቆላልፈወ የምዑዝን ጠረጴ ራስ ቫ ሲዞሩት ፍ ብዙ ሰዎች ምዑዝ በኔ ሕይወት እና ጠባይ ላይ ጫና ያሳደረ ይመስላቸዋል ይህን ጉዳይ በተወሰነ መንገድ አውነት ነው ግን ከምንቀራረብበት የምንለያይበት ይበዛል ይህን በተሻለ መንገድ ለማብራራት አንድ ትዝታ ልጨምር ዴዴ ው ው አልዓዛር ምዑዝ ለወንድ ብልት የሰጠው ስያሜ ነው ለመጠቆም ሳይሆን አይቀርም ሽ የየየ ሞቶ የመነሣት ባሕርይውን መገባትና መውጣት አንድ ቀን ቁጭ ብዬ ሳስብ የመክሊት ፍቅረኛ አቶ ያን አባቴ እና ምዑዝ ባንድ መሥመር ተገናኝተው አገኘኋቸው አቶ ያን በቴምብር ውስጥ ካልሆነ በቀር በዱር ውስጥ እምብዛም የማይገኙ የዱር እንስሳት ተከባካቢ ድርጅት ውስጥ ይሠራል እንዲህ ዐይነቱ ነገር የዘመኑ ፋሽን ነበር እኔ በምኖርበት ሠፈር እንኳ በዱር እንስሳት ዙሪያ የሚሠሩ ብዙ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ይገኛሉ ለምሳሌ አሳዳጊ አልባ ግልገል ነብሮች ጡጦ አጥቢ ድርጅት የአንበሳ ጋማ አበጣሪ ድርጅት ሽልምልማቸው የደበዘዘ የሜዳ አህዮች ቆዳ አድማቂ ድርጅት የቀጭኔዎች አንገት ርዝመት ደረጃ መዳቢ ድርጅት የተሰደዱ ወፎች ናፋቂ ድርጅት ወዘተርፈ ከነዚህ ሁሉ በብልጽግና ብልጫ ያለው ጀርመን በቀል የሆነው አቶ ያን የሚሠራበት ድርጅት ነው ይባላል የአቶ ያን ድርጅት ለእንሰሳት በጣም ከማሰቡ የተነሳ «ኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ ቢከሠት ሣር በል እንስሳትን ወደ ኬንያ ወይም ወደ ኮንጎ በመውሰድ አስግጦ ሲጠግቡ ወደ አገራቸው በመርከብ የመመለስ አቅም አለው» ይባላል አቶ ያን ካፌው ውስጥ ቡና አየጠጣ ዶክተር ሰሎሞን ይርጋ የተባሉ ምሁር የጻፉትን «አጥቢዎች» የተባለ መጽሐፍ ያነባል መጽሐፉ ውስጥ ስለ አጋዘን ስለ ድኩላ ስለ ኒያሳ ስለ አንበሳ ስለ ሳላ ስለ ጅብ ስለ ዝሆን ስለ ሌሎችም አጥቢ እንስሳት የቀረቡ ጥናቶች እና ሥዕሎች ይገኛሉ አቶ ያን የዚህን መጽሐፍ አንድ ቅጅ ገዝቶ ሲያበረክትልኝ የሕይወቴን አንድ ክፍል የሚያሳስብ ነጥብ አገኘሁበት ከዛሬ ብዙ ዓመታች በፊት እፍዓቴ እኔን ነፍስ ጡር ሳለች መገባትና መውጣት ን «የአንበሳ ሥጋ አማረኝ» ብላ አባቴ እንዲያመጣላት አጥብቃ ለመነችው አባቴ ሐሳቧን እንድትቀይር በማግባባት ወይም በማስፈራራት ፈንታ ለእሷ ያለውን ፍቅር ለማሳየት አሮጌ ቼኮዝ ጠመንጃውን ተሸክሞ ለአደን ይወጣል ለአደን የመረጠው ቦታ በጊዜው በደብረ ማርቆስ የሚገኝ የእንስሳት መደብር የነበረ ውሥር። አለኝ ባኮረፈ ድምፅ «እኔ ሻማ ማብርያ መገባትና መውጣት መሙ መቅረዝ ሳበረክትላት ሌላው በጎን ጄኔረተር አበርክቶላት ይሆናል በሌላ ቀን የጀርመንኛ ቋንቋ ተማሪዎች እና ጥቂት ከውጭ የመጡ ተስተናጋጆች ካፌውን ሞልተው አትሌቶቻችን የሚያደርጉትን ውድድር በቴሌቪዥን እየተመለከቱ ነው ምዑዝ ለአትሌቲክስም ሆነ ከአትሌቲክስ ለሚገኝው ብሔራዊ ድል ደንታ እንደሌለው ሲነግረኝ ቆይቷል ያም ሆኖ አሁን ከተመልካቾች መሀል ቁጭ ብሎ የቴሌቪዥኑን ስክሪን እና የሄለንን ፊት እያፈራረቀ ሲመለከት ያዝሁት ውድድሩ ሊጠናቀቅ ሁለት ዙር ሲቀረው ቀነኒሳ በቀለ ከተወዳዳሪዎች መካከል አፈትልኮ ሲወጣ ምዑዝም ከተመልካቾች መካከል አፈትልኮ በመውጣት ከፄለን አጠገብ ቁጭ አለ ሄለን በስሜት ውስጥ ሆና የምታደርገውን ላታውቅ የሌላ ሰው የሻይ ስኒ አንሥታ ጠጣቹ ቀነኒሳ የመጨረሻው ዙር ፍጻሜ ላይ ሲደርስ ካፌው ተደበላለቀ ብርጭቆዎች እና ጠርሙሶች ከቀነኒሳ ሪከርድ ጋራ ከብረው ተሠባበሩ ፄለን ብድግ ብላ ስትጮህ ምዑዝ ዘልሎ ከተጠመጠመባት በኋላ በግርግር መሀል ሩብ ከንፈሯን ግማሽ ጉንጧን ይስም ጀመር ቀጥሎ የተደረገውን ለማየት አልቻልሁም ሳይፈቀድለት ወደ ካፌው የገባ ሎተሪ አዚሪ በደስታ አብዶ ቀነኒሳን ያገኘ ይመስል እኔን ከነትሪዬ ተሸክሞ ወደ ደጅ አወጣኝ በማግሥቱ ምዑዝ ሄለንን እየጠበቀ ለእኔ እና ለመክሊት የሚከተለውን ተናዘዘልን «ፄለንን ማሳመን ከቻልሁ ሕይወቴ ወደ ሌላ ምዕራፍ ይሸጋገራል ይኸውእናንተ ምስክሮች ናችሁ መንዘላዘል ሩሩ ው ው መገባትና መውጣት ው አቀማለሁ ሥራ እይዛለሁ አዎ ለምን ወፍጮ ቤት ውስጥ አይሆንም። ያ ያ አለ ጀርመኑ ራሱን እየናጠ ዶበዚህ ሎጂክ መሠረት የቡና ማፍያ የተገኘው ከጣልያኑ ማፉያነው» አለ ምዑዝ ዝ አንተን አስተያየት የጠየቀህ የለም» ሄለን መለሰች ይፄ ብቻ አይደለም ሲል ቀጠለ ምዑዝ ሥርወ ቃሉ እንደሚጠቁመው ከሆነ ጅብ ለመጀመርያ ጊዜ የተገኘው ጅቡቲ ውስጥ ነው ሄለን እና ጀርመኑ የተመካከሩ ይመስል ሰዓታቸውን እኩል አይተው በአንድ ጊዜ ብድግ አሉ አብረው ትንሽ ከተራመዱ በኋላ ጀርመኑ አንድ ነገር ሲናገር ሄለን ወደ ኋላ ቀርታ ከወገቧ ታጥፋ በጣም ሣቀች ምዑዝ ለማጥናት የፈለገ ይመስል ጥቂት መገባትና ፀሀሠሀውጣባት ወረቀቶችን አውጥቶ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠ ግን ወዲያው በንዴት በረጅሙ ሲተነፍስ ወረቀቶቹ በእስትንፋሱ ኀይል ተገፍተው ኮበለሉ ጥቂት ቆይቶ ወጥቶ ሲሄድ ከደብተሩ ጋራ ሜኖውን ደርቦ ይዞት እንደ ሄደ ገባኝ መገባትና መውጣት ምስሌሴጁ ሰው ሁሉ መለዮ ለባሽ ነው መለዮውን እስከ ወዲያኛው አይቀይርም ደብረ ማርቆስ ሳለሁ የወዛደሩ ፓርቲ ንፈኛ አባል በመሆን የምትታወቅ አንዲት ሴት ነበረች ሴትዬይቱ በየቤቱ እየዞረች «ለሌኒን ሐውልት ማሠርያ የሚሆን መዋጮ አምጡ» በማለት ድሆችን ታስመርር ነበር የሕዝብ ሐዘን ከባድ ነውና እሷ በአባልነት የታቀፈችበት መንግሥት ከጥቂት ዓመታት ቆይታ በኋላ ተገረሰሰ ይሄኔ ሴትዬይቱ በቀድሞው ሥራዋ ተጸጽታ ከወዛደሩ ፓርቲ ወጥታ ጽንፈኛ ሃይማኖተኛ ሆነች ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በየቤቱ እየዞረች «ለቤተ ክርስቲያን ማሠርያ የሚሆን መዋጮ አምጡ» በማለት ድሆችን ማስመረሯን ቀጠለች በ«ቶማስ ወንጌል» እንደ ተጻፈው ከኢየሱስ በስተግራ በኩል የተሰቀለው ሌባ በመስቀል ላይ ሆኖ ከኢየሱስ ግራ ኪስ አምስት ብር ሰርቋል የሦስተኛ ክፍል አስተማሪያችን ጋሽ ዐወቀ ከመሞታቸው ጥቂት ቀናት አስቀድሞ ለጥቁር እንቦሳ የጤና ኮሌጅ ተማሪዎች መገባትና መውጣት ማስተማርያ እንዲሆን አስከሬናቸውን በኀምሳ ሺሕ ብር ሸጡት ዛሬ የሕክምና ተማሪዎች የሰው ቅልጥም ከዬት ጀምሮ የት ላይ እንደሚያበቃ ለመረዳት ሲሹ የጋሽ ዐወቀን አስከሬን እንደ ብራና ይገልጣሉ ጋሽ ዐወቀ ድሮ ቆመው ዘንድሮ ተጋድመው ያስተምራሉ የምዑዝ መለዮ ሴት አውልነት ነው ክሞተ በኋላ ዐመሉ ይቀየር ይሆን። አለጃከክጥቂት ጭውውት በኋላ ከፄለን ጋራ ጨጨ መ ው መ መ መ መ መ መገባትና መውጣት ድ ን ፍቅር ከጀመርሁ አንድ ዓመት ሞላኝ ዛሬ ለምን እንደ መጣሁ እስኪ ገምት። » እንጃ የሆነ ጊዜ ላይ ሊፍቱ ሳይበላሽ አልቀረም» አልሁት ምዑዝ ሙነቅ ጀመረ ሣቁ ሲያልቅ ታሪኩም አብሮ አለቀ መገባትና መውጣት ምስሌጁ የጊዜ ነገር ይገርመኛል አዲስ አበባ ውስጥ ጊዜ በሣር በቅጠሉ ውስጥ አድፍጧል በግድግዳ ላይ በቴሌቭዥን ላይ በሞባይሌ ላይ ሳይቀር ሰዓት አለ በመዲናይቱ የስልክ ግንኙነት ከተዳከመ ወዲህ ሞባይሌ በሲም ካርድ የሚሠራ የኪስ ሰዓት ሆኗል ልጅ እያለሁ እንዲህ ያለ ዕድል አልነበረም ያኔ ለመደባደብ ካልሆነ በቀር ሰዓት ልይ ብሎ የሸሚዙን እጅጌ የሚሰበስብ ሰው በመንደራችን አልነበረም ትዝ ይለኛል ከሰኞ እስክ ዓርብ ማለዳ የገቢ ምንጫችን ቡና ቡና ብሎ የሚጀምር ኅብረ ዝማሬ ከሬዲዮኑ ሆድ ሲወጣ አማዬም ተማጀቷ ትወጣና «ተነሥ የትምህርት ሰዓት ደርሷል» በማለት ከዕንቅልፌ ትቀሰቅሰኝ ነበር ዘወትር ሰባት ሰዓት ላይ እኛ ቤት ቡና ይፈላል እናም የቡና ወቀጣ ድምፅ ከእኛ ቤት ሲወጣ መንደርተኞች ከቀኑ ሰባት ሰዓት እንደ ሆነ ያውቃሉ የእኛ ቤት የቡና ሙቀጫ በአደባባይ ላይ እንደ ተተከለ የሕዝብ ሰዓት ነው በሕይወቴ ለመጀመርያ ጊዜ ቡና የተጫወተው ሚና ጊዜን መጠቆም ነው ስለ ጊዜ እና ቡጭይህንና የፍሰለውን በሐሳቤ ሳወጣና ሳወርድ «ቡና እንደ ወረደ አምጣልኝ» የሚል የአንድ መግባትና መውጣት ው ተስተናጋጅ ትእዛዝ አናጠበኝ እነሆ ዛሬም በቤትሆቨን ካፌ ውስጥ ከቡና ማለቢያ ማሸኑ ፊት ለፊት ቆሜያለሁ የካቫፌው የፊተኛው የመስተዋት በር ሲከፈት መክሊት እና ፍቅረኛዋ አቶ ያፇ ተከታትለው ገቡ አቶ ያፇለመክሊት ይዞላት የመጣውን የተጠቀለለ ሹራብ እና በዳመና ጊዜ ራሱን በራሱ የሚዘረጋ አውቶማቲክ ጃንጥላ አቀብሏት ጉንጧን ስሞ ከተሰናበታት በኋሳ ደጅ ላይ ወዳቆመው መኪና ተመለሰ መክሊት የተሰጣትን ስጦታ አንጠልጥላ በብዙ ፈገግታ እና ልበ ሙሉነት ካፌውን መሀል ለመሀል ሠንጥቃ ዐዉደ መልበሻ ክፍል ገብታ ለጊዜው ከተሰወረች በኋላ ዩኒፎርሟን ለብሳ ተመለሰች የኋለኛው ክፍል በር ሲጢጥ ብሎ ሲከፈት ማም የተሳናቸው ሦስት የጀርመን ሴቶች ተከታትለው ገቡ በነገራችን ላይ «ማቄጥ የተሳናቸው» የሚለውን ሐረግ ከምዑዝ የተዋስሁት ሲሆን። «ቂጥ ማውጣት የተሳናቸው» የሚል ትርጉም አዝሏል የማዘል ነገር ከተነሣ ተከታትለው ከገቡት የጀርመን ሴቶች አንደኛ ዋ በጉዲፈቻ የተገኘ ጥቁር ሕፃን አዝላ ነበር ሕፃኑ በፊት በኩል በመታዘሉ በጉዲፈቻ ከመወሰዱ በፊት ከሚያውቀው አስተዛዘል ስለተለየበት በፊቱ ላይ ግራ መጋባት ይታያል ከኢትዮጵያውያን በተለየ ፈረንጆች ሕፃናትን እንደ ካንጋሮ በፊት በኩል ያዝላሉ አንድ ቀን ምዑዝ የአስተዛዛል አቅጣጫ ወላጆች ለልጆቻቸው ያላቸውን አመሰካከት ይገልጻል» ብሎ ነበር ፌ ሕፃኑን በፊት በኩል ስታዝለው ሕፃኑ አንድም የመጭው ዘመን ሰው መሆኑን እየነገርኸው ነው አንድም ከእኔ ይልቅ ለአንተ ቅድሚያ እሰጥሃለሁ ማለት ነው በመሀል መክሊት ዴጌ ው መገካትና መውጣት አቋርጣው እንዳንተ አተረጓጎም ከሆነ ኢትዮጵያውያን እናቶች ልጆቻቸውን በጀርባቸው የሚያዝሉት ከልጆቻቸው ራሳቸውን ስለሚያስቀድሙ ነው አለችው አልወጣኝም አለ ምዑዝ «ኢትዮጵያውያን እናቶች ልጆቻቸውን ከኋላ በኩል በጀርባቸው የሚያዝሉት ከፊት ለመፍጨት እንዲያመቻቸው ነው ወደ ካፌው ክፍል ልመለስ ማቄጥ የተሳናቸው ጀርመኖች ከተቀመጡባቸው ሁለት ወንበሮች ቀጥሎ የተቀመጠ ብልጭልጭ የለበሰ ተስተናጋጅ በክፍሉ ውስጥ ላሉ ሁሉ በሚሰማ ድምፅ ጮህ ብሎ እባካችሁ አስተናጋጆች ቴሌቪዝዮኑን የኢትዮጵያ ጣቢያ ላይ አድርጉልኝ ያገሬን ቴሌቪዝዮን ካየሁ ዐሥር ዓመት ሆነኝ» በማለት ተናገረ የዚህ ተስተናጋጅ ዓላማ ዐሥር ዓመት ሙሉ ውጭ አገር ኖሮ መምጣቱን ከኋላው ተቀምጠው በርገር ለሚጎራርሱ ሴቶች ማሳወቅ ነው ከጥቂት ሰከንዶች በኋላ የቴሌቪዥኑ ጣቢያ ሲቀየር እሱ ቴሌቪዥኑን ትቶ ቴሌቪዥኑን የከፈተችውን መክሊትን መመልከት ጀመረ ባጋጣሚ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የልማት ፕሮግራም ላይ የሚከተለው ዜና እየታየ ነበር በአማራ ክልል ዳሉናርሯና ኋናውጋ ወረዳ በሚገኝ አንድ የገጠር ቀበሌ ውስጥ ከዳገት ላይ አዲስ ጅረት ስለ ፈለቀ የቀበሌው ሲቀ መንበር ጅረቱን መርቀው ከፈቱ የቀበሌው ሊቀ መንበር በጅረቱ ምረቃ ላይ ለተገኙት አርሶ አደሮች እንደ ተናገሩት ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ሦስት ጅረቶች መፍለቃቸውን አስታውሰው ይህም የመልካም አስተዳደር ውጤት መሆኑን ገልጸዋል መገባትና መውጣት ር የፊተኛው በር እንደገና ተከፈተና አብርሃም አረንጓዴ ማንቆርቆርያውን አንጠልጥሎ ክገባ በኋላ ወደ ጆሮዬ ተጠግቶ ስማ። መገባትና መውጣት ኢራ ጀምሮ «ጥለውኝ ሞተዋል እናት እና አባቴ» ብሎ ከማጠናቀቁ በፊት አባተ ደርሶ እጅጌውን ይዞ ወደ በሩ ጎተተው ይሁን እንጂ አንዲት የቋንቋ ተማሪ ሴትዮ ከወንበሯ ብድግ ብላ በአባተ ጆሮ የሆነ ነገር ስታንሾካሹክ አባተም ራሱን ሲያነቃንቅ አየሁት ከዚያ አባተ ልጁን ብቸኛ ወንበር ላይ ጎልቶት ወደ ጓዳ ገባ ልጁ እንደ ተጋበዘ እንጂ ምን እንደተጋበዘ ስላላወቀ በጉጉት ወደ ጓዳው በር ይመለከት ጀመርፅ ከጥቂት ደቂቃዎች በቷሳ አባተ በቲማቲም የተጠበሰ ሥጋ ይዞ ከወጣ በኋላ በልጁ አቅጣጫ መጥቶ መጥቶ መጥቶ ከልጁ በኋላ በተቀመጠ ተስተናጋጅ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠው ልጁ ምራቁን ሲውጥ ጉሮሮው እንደ ቴርሞሜትር ከፍ ዝቅ ስትል ዐየሁ አባተ እንደ ገና ወደ ጓዳ ገብቶ ሲወጣ ሻይ እና ጥቂት የተቆረሰለት ዳቦ በትሪ ይዚል ልጁ ዳቦውን እና ሻዩን ሲያይ «ይለፈኝ በሚል ዐይነት ጣራ ጣራውን መመልከት ጅመረ አባተ ግን አላለፈውም የያዘውን ሳሕን ጠረጴዛው እስኪርድ ድረስ ከፊቱ አስቀምጦለት ፄደ ልጁ የቀረበለትን መብላት ሲጀምር ከላይ እስከ ታች ገመገምሁት «የጥበብ መጀመርያው እግዚአብሔርን መፍራት ነው» የሚል ጥቅስ የተጻፈበት ለዐዋቂ የሚሆን ቲቭርት ለብሶ ነበር በርግጥ በጥቅሱ ላይ ያለው «እግዚአ» የሚለው ቃል በእድፍ ስለ ተዋጠ «የጥበብ መጀመርድ ብሔርን መፍራት ነው» የሚለው ጹሑፍ ብቻ ይታያል አጠገቤ የተቀመጠችው መክሊት ወሬዋን ቀጠለች ከያን ጋራ ወደ ጀርመን ልበር ጥቂት ቀን ሲቀረኝ ለሳሚ ምርር ያለ ደብዳቤ እጽፍለታለሁ። » «እኔ ሕፃን በነበርሀብት ጊዜ ፎቶግራፍ መነሣት በጣም ከባድ ነበር እንዲያውም ከዚህ በፊት እንደገለጽሁት በእኛ መንደር ፎቶ ከተነሠት ይልቅ ሞተው የቶነሠሥ ይበዙ ነበር በተለይ ፎቶ ለብቻ መነሣት እና ጉርድ ፎቶ መነሣት ፎቶውን እንደ ማባከን ይቆጠራል ካሜራ ያዥ ጋራ የመገናኘት አጋጣሚ ያለው ሰውዬ ዘመድ እንኳን ቢያጣ ከጠመንጃው እና ከውሻው ጋራ አብሮ ይነሣ ነበር ትዝ ይለኛል የሦስተኛ ክፍል ተማሪ ሳለሁ የትምህርት ቤታችን የመዝገብ ቤት ሐሳፊ የወላጅህን ጉርድ ፎቶግራፍ አምጣ ሲለኝ የእንጀራ አባቴ በቁም የተነሣውን ፎቶ ከወገቡ በላይ በመቀስ ቆርጩ ወስጃለሁ ከእኛ መገባትና መውጣት ቤት ትንሽ ፈንጠር ብለው የሚኖሩ አንድ የሀብታም ቤተሰብ አባላት በሁለት ዓመት አንዴ ፎቶ ይነሠ ነበር ታዲያ አንድ ቀን ፎቶ አንሺው ካሜራውን ሲያቀባብል በፎቶ ተነሺዎች ጀርባ የማልፍ አስመስዬ እግሬን እያዘገየሁ ተራመድሁና አብሬ ፎቶ ተነሣሁ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ባለቤትዬዋ ለእንግዳ የፎቶ አልበም ሲያስጎበኙ «ይህ ባለቤቴ ነው ይህ ልጄ ነውይህ ደግሞ በስሕተት የገባ የጎረቤት ልጅ ተረከዝ ነው ብለው ያሳያሉ ሌላ ጊዜ ደግሞ የፋፋ ዱቄት ፋብሪካ ለፖስተር የሚሆን የሕፃን ምስል ፈልጎ እኛ ሰፈር ሲመጣ ዐይኑን በእኔ ላይ ጣለ «በጣም ወፍራም ሕፃን ነበርህ ማለት ነው። ብዬ ለመዘራክከር ሞከርሁ በዘበኛ አባረሩኝ መ መ መገባትና መውጣት ትዝ ይለኛል ለመጀመርያ ጊዜ አንጋፋው ደራሲ የካፌያችንን ወለል ሲረግጡ ተስተናጋጆች ዐይናቸውን ማመን አቅቷቸው በአቅራቢያቸው ያገኙትን ወረቀት እና ወረቀት ነክ ነገር በሙሉ በመያዝ ሊያስፈርሟቸው ተሸቀዳደሙ ታላቁ ሰውም ለጊዜው አድናቂዎቻቸውን በጥንቃቄ ለመያዝ ጣሩ ብዕራቸውን በቄንጥ ከደረት ኪሳቸው ላይ ላጥ ያደርጉና ፊርማ ጠያቂውን እና ፊርማ መቀበያ ደብተሩን በፈገግታ አፈራርቀው ከተመሰከቱ በኋላ በሠዓሊ የእጅ ጥራት ፊርማቸውን ያሰፍራሉ እንዲያውም አልፎ አልፎ ከፊርማቸው አጠገብ «ሕዝባችሁን እንድታገለግሉ አደራ እላለሁ» የሚል ምራቂ ማሳሰቢያ ጣል ያደርጉ ነበር ቀስ በቀስ ያስፈራሚዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ ግን የአንጋፋው ደራሲ ትዕግሥት እና ብዕር እያለቀ ሲፄድ ይታይ ነበር አሁን ከፊት ለፊታቸው የተገተረውን ፊርማ ጠያቂ ቀና ብለው ለማየት ሳይቸገሩ ደብተሩን ከመመንጨቅ በማይተናነስ አሳሳብ ስበው ከበደ የሚል የሚነበብ ሳይሆን የሚገመት ፊርማ ያስቀምጡ ጀመር አንድ ቀን እንዲያውም ምርር ብለው በገዛ ፊርማዬ አካኪ አካኪቪች አደረጋችሁኝ» ብለው አካኪ ዘራፍ አሉ ከጊዜ በኋላ ምዑዝን ጠይቄ እንደ ተረዳሁት አካኪ አካኪቪች በሩሲያ ልቦለድ ውስጥ የሚገኝ ጹሑፍ በመገልበጥ የሚተዳደር ገጸ ባሕርይ ነው የሆነ ጊዜ ላይ ታላቁ ሰው ተስተናጋጅነታቻውን ሁሉ ሳይዘነጉት አልቀሩም አንድ ቀን ከሚያስፈርሟቸው ሰዎች ጋራ ተደባልቄ የተጠቀሙበትን ቢል ባቀርብላቸው ቀና ብለው ሳያዩኝ በቢሉ ላይ ፊርማ እና በርታ» የሚል ቃል አስፍረው ገፉልኝ እየዋለ እየሰነበተ ተስተናጋጆች ታላቁን ሰው ተላመዷቸው ፌሬ መገባትና መውጣት በአንጋፋ ከያኒነታቸው ሳይሆንበአንጋፋ ተስተናጋጅነታቸው ያስታውሷቸው ጀመር በተለይ አንድ ተስተናጋጅ በአንድ እጁ ሞባይሉን ከጆሮ ግንዱ አጣብቆ መልአክት እየተቀበለ በሌላው እጁ ኪሱ ውስጥ ገብቶ የሚጽፍበት ቢያጣ ከፊት ለፊቱ አቀርቅረው ግጥም እየጻፉ ከነበሩት ባለቅኔ እጅ ብዕራቸውን ነጥቆ ወሰደ ከዚህ ገጠመኝ በኋላ ባለቅኔው ብዕር መያዝን እርም አሉ የድንገቴ ግጥም ሲመጣላቸው መክሊትን አጣድፈው ይጠሯትና ጸፊ» ብለው ያዚታል እርሷም የደንበኞችን ትእዛዝ በምትመዘግብበት ደብተር ግጥማቸውን ትመዘግባለች አንድ ቀን ትንሸ ሲያሰላስሉ ቆይተው ጠሯትና የሚከተለውን በቃላቸው ማጻፍ ጀመሩ ዖጎጅው ጳድ ሪድሷ ሺሮውያ ወደ ጋጪዉፅቃ ያጋጪሚዳታ መውጣማፉየ ያመረ ፅው ውፇ ይጠራጳ ያኋኒሪ ቅማምያ ፖቋ ታ ብለው ቤት መድፊያውን ሳይጨርሱ መክሊትን ሌላ ተስተናጋጅ ስለ ጠራት መጻፏን አቋርጣ ፄሄደች በዚህ ምክንያት ታላቁ ሰው ልባቸው ተሠብሮ ወጡ ከዚያ በኋላ ወደ ካፌው አልተመለሱም ሕይወታቸው ካለፈ ክብዙ ጊዜ በኋላ የስንች መደምደሚያ ታላት ምን ይሆን። ፈረንጅ ሁሉ እንደ ሀብታም ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንደ መገባትና መውጣት ድፃ ስለሚቆጠር ክፈረንጃ ጋራ የተገኘች ያበሻ ሴት ገላዋን በገንዘብ የለወጠች እንደ ሆነች ተደርጋ ትወሰዳለች አለቀ ሥራ ፍቅር ከጾታ ጋራ ያልተገናኘ ጓደኝነት ክግምት አይገባም አዝናለሁ ሌላው እንዲህ ቢያስብ አይገርመኝም አሪፍ ጭንቅላት አለው ብዬ የማስበው ምዑዝ እንዲህ ሲያስብ ግን ያሳዝናል «ማዘን የለብሽም በሌላ ጊዜ ምዑዝ ከዚህ የተሰየ ነገር ብሏል» አልሁ «ምን አለ። » አለች በኩሪፊያ ከንፈሯን ጥላ ከፈረንጅ ጋራ ያላቸው ግንኙነት የረጂ እና የተረጂ ያልሆነ ተፈጥሮ ባጎናጸፈቻቸው ኀይል ተማምነው የሚኖሩ ሁለት ዐይነት ጥቁሮች በአፍሪካ ይገኛሉ እነርሱም የሶማሌ የባሕር ሽፍቶች እና የኢትዮጵያ ቆነጃጅት ናቸው ብሏል «ሊል ይችላል ግን በፊት የተናገረውን የሚክስ አባባል አይደለም» ከተቀመጠችበት አልጋ ተነሣችና በድፃ አገር መኖር ግን እንዴት ጣጣ ነው» ብላ ተከዘች ይኸው እንግዲህ ትካዜዬን አስረክቤያት ወደ ፈገግታዬ ተሸጋገርሁ በድፃ አገር ለመኖር የሚደረገው ግብግብ አሥቂኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጎልቶ ታሰበኝ አሁን ለምሳሌ በየሳምንቱ የምከታተለው ጤናችን» የተባለ በብዙ ቅጅ የሚታተም ጋዜጣ አለ በአገራችን ከጤነኛው በሽተኛው በቁጥር ስለሚበልጥ በሕክምና ዙሪያ የሚጽፍ ጋዜጣ በብዙ ቅጂ ቢሸጥ አይገርምም ግን ሁሌ ፋሲካ የለም ሥ በአንድ ወቅት ሕዝቡ ከሕክምና ይልቅ ወደ ፖለቲካ ማዘንበል አመጣ ከፓናዶል ይልቅ የፓናል ውይይትን መምረጥ ጀመረ ይሄኔ የጋዜጣው አዘጋጅ ከጊዜው ጋራ ራሱን ለማወዳጅት በጤና ዴዴ ጮ ዴዴ ጨመ መግባትና መውጣት መመለስ ጀመረ እኔም ተደርቤ ገባሁ ከውስጥ ምዑዝ እና መክሊት አፍ ለአፍ ገጥመፀሀጠሩ እና ሊሥቁ ዐየኋቸው መክሊት አሁንም አሁንም በሣፅሯበች ትከሻው ላይ ስትደገፍ ታዘብኋት አጋጣሚውን ህዝመው ጭር ያለውን ቤት የድርያ ቤት አድርገውት እንደ ሓሦቢዬ ነገረኝ። የምዑዝ ፀጉር በደንብ መስተካከሉ ሰውነቱ እና ልብሱ መጽዳቱ በኑሮው ላይ የተከሠተውን ግዴለሽነት ከማዬት አላገደኝም ቡናውን እየጠጣ እጅብ በለው የተቀመጡትን ተስተናጋጆች ፍዝዝ ብሎ ሲመለከት ቆየ ክፍሉ መሀል ላይ ጥቂት ጓደኛ ተስተናጋጆች ጠረጴዛ ከብበው ተቀምጠው ነበር ከመካከላቸው አንዱ ብድግ ብሎ ወደ ውስጥ ግባና ትንሽ ቆይቶ መክሊትን አስከትሎ ወጣ መክሊት በሻማ የተከበበ ትልቅ ኬክ ይዛ በውስጥ ዐዋቂ ፈገግታ ፈገግ ብላ ኬኩን ካንዲት ሴት ፊት ለፊት አስቀመጠችው ጠረጴዛውን ከብበው የተቀመጡት የልጅቱ ጓደኞች ብድግ ብለው ጎረቤት አገር በሚሰማ ድምፅ ዕሮርጀጄደይ ይ እያሉ መዘመር ጀመሩ ባለልደቱ ልጅ ነገሩን እንዳልጠበቀችው ለማስመሰል ዐይኗን አፍጥጣ መዳፎቿን አፏ ላይ ጭና ጥቂት የመደናገጥ ትዕይንት ካሳየች በኋላ ብድግ ብላ እየሣቀች ጓደኞቿን ተራ በተራ ትስም ጀመር በዙሪያው ተቀምጠው ሲበሉና ሲጠጡ የቆዩ ሌሎች ተስተናጋጆች የሁካታውን መንሥኤ ለማጣራት ዞር ብለው ካዩ በኋላ የዕዩን ዕዩን ነገር መሆኑን ሲያውቁ በማዬት ላለመተባበር በፍጥነት ወደ ሳሕናቸው እና ወደ ብርጭቋቸው አቀረቀሩ ድ መገባትና መውጣት መግዛት ሊኖርበት ነው ከሌሊት ማጅራት መቺዎች ራሉን ለመከላከል ሽጉጥ መግዛት ሊኖርበት ነው ወዘተ ቅሉን በመስኮት በኩል ሲወረውረው ተጨማሪ ቁሳቁስ በበሩ በኩል ይገባበታል «ከሄለን ጋራ መኖር እንደ ጀመርን አብረን የምንቀጥል አይመስለኝም ነበር ግን ሳላስበው በኮተት አሸነፈችኝ አንድ ቀን ትልቅ ቁም ሣጥን ገዛች በማግሥቱ ትልቅ የቴሌቪዥን ማስቀመጫ ወደ ቤታችን ገባ ከዚያ ብዙ ዐይነት ብርጭቆዎች መአት ዐይነት ማንኪያዎች እና ሳሕኖች ቤቱን ሞሉት አንድ ቀን ከፄለን ጋራ ምርር ያለ ጠብ ተጣልተን ውጭልኝ ብዬ ጮሁባት እሺ ብላ ተነሣች ወዲያው ግን ዕቃዋን ለማስጫን የሚወስደው ጊዜ እና የተወሳሰበ ሂደት ሳስብ አብሬያት መኖር የሚቀል ሆኖ ታየኝ «አንዳንዴ ሳስበው ዕጣ ፈንታ የሆነ ሸክም ታሸክመኛ ለች ሸክሙን ለማቅለል ብልጠትም ሆነ ጸሎት ማድረግ ከንቱ ነው ድሮ ለምሳሌ ብዙ ጉልበት የሚባክነው በሸክም ነበር አሁን ቴክኖሎጂ ነገሮችን እያሳነሳቸው መጣ ትንንሽ ነገሮች ደግሞ በቀላሉ ይሰወራሉ እና ድሮ በሸክም የምናጠፋውን ጉልበት ዘንድሮ በፍለጋ እናጠፋዋለን ከፄለን ጋራ በተጋባን በማግሥቱ ከመሥሪያ ቤት ስንመለስ ከግቢያችን ፊት ለፊት አንድ ሰካራም ሽንቱን ይሸናል መሽኛው ትልቅ በመሆኑ ሸንቶ ሲያራግፍ አጠገቡ የነበረውን የመገገድ መብራት አምፖል አቃጠለው በአደባባይ የሚሸኑ ወንዶች በአካባቢ ላይ ከሚፈጥሩት ብክለት በላይ በትዳር ላይ የሚፈጥሩት ችግር ይበልጣል ዐየህ ሚስቶች ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው የባላቸውን መሣሪያ ከሌላው ጋራ ሊያወዳድሩ ይችላሉ ሰውዬው መገባትና መውጣት መጠጥ ነበር ተጋባዥች ብዙ ጥሬ ሥጋ ሲበሉ አይቻለሁ እና የጥንቱ የጀርመን ቋንቋ መምህሬ ተጠርቶ ነበር ብቻ እሱ ምንም የኢትዮጵያን ባህል ቢያከብር ጥሬ ሥጋ መብላት አልፈለገም እና ምን አደረገ። የሚል ስጋት ተሰምቶኝ ነው አጭሩ ስውዬ በቃሉ ምላሽ መስጠት አልፈለገም በጎይል ተንደርድሮ የረጅሙን ሰውዬ ወገብ አቀፈው ረጅሙ ሰውዬ ብድግ ብሎ ጠርሙሱን በጥንቃቄ አጠገቡ ካለው ጠረጴዛ ላይ ካስቀመጠ በኋላ ጎንበስ ብሎ የአጭሩን ሰውዬ አንገት አነቀ ፊቱ ላይ ደለው ፈገግታ ግን ባጭሩ ስውዬ አንገት ላይ ሜዳሊያ የሚያጠልቅ እንጂ የሚያንቅ አይመስልም ነበር በዚህ መሀል በሰላሙ ጊዜ አስተናጋጅ በቀውጢው ጊዜ ቦዲጋርድ በመሆን በካፌው ውስጥ የሚያገለግለው አባተ በደረቱ አየሩን እየገፋ ደረሰና ባንድ እጁ ያዊሩን ስውዬ ኮሌታ በሌላ እጁ የረጅሙን ሰውዬ እጅጌ ጨምድዶ ይዞ «እኪህ ሰው እየተዝናና ስለሆነ ጨጨ መ መ መመመ መው መገባትና መውጣት ድዛፃ ስለሚቆጠር ከፈረንጅ ጋራ የተገኘች ያበሻ ሴት ገላዋን በገንዘብ የለወጠች እንደ ሆነች ተደርጋ ትወሰዳለች አለቀ ሥራ ፍቅር ከጾታ ጋራ ያልተገናኘ ጓደኝነት ከግምት አይገባም አዝናለሁ ሌላው እንዲህ ቢያስብ አይገርመኝም አሪፍ ጭንቅላት አለው ብዬ የማስበው ምዑዝ እንዲህ ሲያስብ ግን ያሳዝናል «ማዘን የለብሽም በሌላ ጊዜ ምዑዝ ከዚህ የተለየ ነገር ብሏል» አልሁ «ምን አለ። » አለች በኩሪፊያ ከንፈሯን ጥላ «ከፈረንጅ ጋራ ያላቸው ግንኙነት የረጂ እና የተረጂ ያልሆነ ተፈጥሮ ባጎናጸፈቻቸው ጎይል ተማምነው የሚናሩ ሁለት ዐይነት ጥቁሮች በአፍሪካ ይገኛሉ እነርሱም የሶማሌ የባሕር ሽፍቶች እና የኢትዮጵያ ቆነጃጅት ናቸው» ብሏል «ሊል ይችላል ግን በፊት የተናገረውን የሚክስ አባባል አይደለም» ከተቀመጠችበት አልጋ ተነሣችና «በድፃ አገር መኖር ግን እንዴት ጣጣ ነው» ብላ ተከዘች ይኸው እንግዲህ ትካዜዬን አስረክቤያት ወደ ፈገግታዬ ተሸጋገርሁ በድፃ አገር ለመኖር የሚደረገው ግብግብ አሥቂኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጎልቶ ታሰበኝ አሁን ለምሳሌ በየሳምንቱ የምከታተለው ጤናችን» የተባለ በብዙ ቅጅ የሚታተም ጋዜጣ አለ በአገራችን ከጤነኛው በሽተኛው በቁጥር ስለሚበልጥ በሕክምና ዙሪያ የሚጽፍ ጋዜጣ በብዙ ቅጂ ቢሸጥ አይገርምም ግን ሁሌ ፋሲካ የለም ሥ በአንድ ወቅት ሕዝቡ ከሕክምና ይልቅ ወደ ፖለቲካ ማዘንበል አመጣ ከፓናዶል ይልቅ የፓናል ውይይትን መምረጥ ጀመረ ይሄኔ የጋዜጣው አዘጋጅ ከጊዜው ጋራ ራሱን ለማወዳጅት በጤና መገባትና መውጣት ጨመሙመጨ መመመ መመለስ ጀመረ እኔም ተደርቤ ገባሁ ከውስጥ ምዑዝ እና መክሊት አፍ ለአፍ ገጥመው ሲያወሩ እና ሲሥቁ ዐየኋቸው መክሊት አሁንም አሁንም በሣቅ እያሳበበች ትከሻው ላይ ስትደገፍ ታዘብኋት። » አልሁት ከዓመታት በፊት የገጠመውን አስታውሼ «እነግርዛለሁ» አለና ሊቀጥል ሲል መክሊት አጠገባችን መጥታ ቆመች ፊቱ በፈገግታ ተሞልቶ ሲመለከታት የኔ ፊት ባላየውም ሲቀላ ታወቀኝ ፊቴን ለመደበቅ ወደ መታጠቢያ ቤት ሄድሁ ከጥቂት ቆይታ በቷላ ስወጣ መክሊት እና ምዑዝ በክፍሉ ውስጥ አልነበሩም አባተ ብቻ ከመስኮት መስኮት እየዘለለ የመስኮቶችን መዘጋት ያረጋግጣል መገባትና መውጣት ምስሌፍ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ መክሊት አቶ ያን ቤት ጠቅልላ መኖር ጀመረች የአስተናጋጅነት ሥራዋን ጨርሶ አቆመች በእሷ ምትክ ለታሪክ የማይበቁ ሁለት ሴት አስተናጋጆች ተቀጠሩ ለጊዜውም ቢሆን ከመክሊት እና ከምዑዝ ጋራ አልፎ አልፎ መገናኘታችን አልቀረም አንድ እሑድ አመሻሽ በሠፈራችን በሚገኝ ኢንተርኔት ካፌ በረንዳ ላይ ተቀምጩ መክሊትን አጠብቃለሁ በአስተናጋጁ ምትክ መንገድ ለመንገድ የሚዞር መጽሐፍ ሻጭ መጥቶ አጠገቤ ቆመ አልገረመኝም የተቀመጥሁበት በረንዳ ከካፌው ይልቅ ለጎዳናው ይቀርባል መጽሐፍ ሻጩ በደረቱ ከተሸከመው የመጽሐፍ ነዶ መሀል «ፍቅር እስከ መቃብር» የሚል ወፍራም ጥራዝ ታየኝ አቶ ሐዲስ መጽሐፋቸው እንደ አጠና በሸክም ገቢያ የሚወጣ መሆኑን ቢያውቁ ኖሮ የገጹን መጠን ያሳንሱት ነበር ብዬ አሰብሁ የልጁን ሸክም ለማቅለል ብዬ አንድ ትልቅ ጥራዝ ገዛሁትና ወደ ጎዳናው መመልከት ጀመርሁ ጎዳናው ዳር መፄጃ የሌላቸው ወጣቶች ፈንጠር ፈንጠር ብለው ቆመው ከሚያውቁት አልፎ ሂያጅ ሰላምታ እንደ ምጽዋት ይጠብቃሉ ችጋር ሣር በል ያደረጋቸው ከሲታ የከተሜ ውሾች የሚቀመስ ፍለጋ አለቱን ፅንጨቱን ያሸታሉ የተሠበሩ መኪኖችን የሚያነሣ ላንድሮቨር ጺዲ ። ሰም ያማዕፇያና ፈጎው ያታ ዳድታደርሂታፖ ዳመጨይቀቼጎሪ ከሰላምታ ጋራ የሰማኒያ ሚስቱ በከንፈር ቀለም የታተመ ማሕተም አለው መገዛትና መውጣት ያም ሆነ ይህ ምዑዝ እና መክሊት አልጋ ውስጥ አብረው አመሹ ማታ ላይ ምዑዝ ወደ ቤቱ ለመፄድ ሲዘጋጅ መታጠቢያ ቤት ገብቶ ዘጋመክሊት ስትነግረኝ ከመታጠቢያ ቧንቧው የሚወርደው ውኃ ሽሸሽሽ የሚል ድምፅ ሲያሰማ ከየት መጣ የማይባል ንዴት ሰንጎ ያዛት ምዑዝ ወደ ሚስቱ ከመመለሱ በፊት የእሷን ጠረን ከገላው እያባረረ እንደ ሆነ ገባት ሊታጠብ ሲነሣ እንዳይታጠብ ለምን አልከሰከልኩትም ሻወሩ ተበላሽቷል ብዬ ለምን አልዋሽሁትም ብላ ተጸጸተችፊ ያለበትን ሁኔታ ለመረዳት አላቃታትም አሷን እሷን እየሸተተ ቢፄድ ከሚስቱ ጋራ ሊጣላ ነው ትዳሩ ሊፈርስ ነው መክሊት ይህ እንዲሆን አትፈልግም ግን የሚስቱን ስሜት ለመጠበቅ ሲል የእሷን ክብር ማቁሰል ትዳሩን ለማዳን ሲል የእሷን ቤት መድፈሩ ተሰማት ሽሸሸሸ የሚለው ድምፅ ሲቀጥል ፍቅሯ ከጉድፍ ጋራ በመታጠቢያው ሳሕን በኩል ወርዶ ሲወገድ ያየች መሰላት በሕይወቴ አንድ ከማላውቀው ስሜት ጋራ ስፋጠጥ ተሰማኝ ይገባፃል የምልህ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

تعليقات:


memezon

خيارات التنزيل | تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي | كتاب اليوم

© dirzon | شروط الخدمة | خصوصية | حول | خدمات | اتصال