Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي
  • قائمة القراءة
  • مختصر
  • كتاب مسموع
  • بحث
  • تحميل
  • myzon
  • تسجيل الدخول
  • تسجيل
English  አማርኛ  Français  العربية
كتاب اليوم

ፍርድ ቤቶች የሚመሩባቸው መርሆች.pdf


  • word cloud

ፍርድ ቤቶች የሚመሩባቸው መርሆች.pdf
  • Extraction Summary

ፍቤቶች የሚመሩባቸው መርሆች አዘጋጆች ታደለ ነጊሾ አለማየሁ ተገኔ ማውጫ የጽሑፉ መግቢያ ክፍል አንድ የዳኝነት ነፃነት ዝቅተኛ መስፈርቶችና ከሌሎች ሐገሮች ልምድ ጋር ሲነባፃዓር ምን ይመስላል። በዳኝነት ነፃነትና በፕሬስ ነፃነት መካከል ያለውን ሚዛን እንዴት መጠበቅ ይቻላል ዋቢ ጽሑፎች የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመንግስት የፌዴራል ፍቤቶች ዳኞች ሥነምግባር ደንብ የክልል መንግስታት ሕገመንግስት ፍቤቶች ማቋቋሚያ አዋጆች ሥነምግባር ደንቦችና ሌሎች አዋጆች መንበረ ፀሐይ ታደሰ የኢትዮጵያ ሕግና ፍትህ ገፅታዎች አዲስ አበባ ፐከፀ ሀበበ ከ ሾዩበ መጩበርር ዌጩከር ዐ ።

  • Cosine Similarity

ፍቤቶች የሚመሩባቸው መርሆች አዘጋጆች ታደለ ነጊሾ አለማየሁ ተገኔ ማውጫ የጽሑፉ መግቢያ ክፍል አንድ የዳኝነት ነፃነት መርህ መግቢያ የዳኝነት ነፃነት ምንነት ጊ ህእ ንዓ ሄን ሄሄ ቴቴ ራፊዛራ የዳኝነት ነዓነት ገፅታዎች ኒ ህህ ሄ ሄሄ ሄሄ ቴሄቀቴኀቀኀቀኃቴፋራ የዳኞች ግለሰባዊ ነፃነት ውስጣዊ ነፃነት ተቋማዊ ነፃነት የዳኝነት ነፃነት ለምንን። ራ» የዳኝነት ተጠያቂነት ገፅታዎችና አይነቶች በጠቅላላው የመወያያ ጥያቂ ዢዚ ዜዜፊፊፊ ፊፊ የዳኝነት ተጠያቂነት በኢፈድሪ መግቢያ የፍቤቶችና ዳኞች ለሕግ አውጪው አካል ያለባቸው የመወያያ ጥያቄዎችች ህህ ሄቀሄ ቀቀ የዳኝነት ግልፅነት የመወያያ ጥያቄዎች ዋቢ ጽሑፎች ዐ ክፍል አንድ የዳኝነት ነፃነት መርህ መግቢያ በዚህ ጽሑፍ መግቢያ እንደተመለከተው ፍቤቶች ያላባቸውን ሕገመንግስታዊ ተልእኮ ለማውጣት ሊመሩባቸው ከሚገባቸው መሰረታዊ መርሆች ውስጥ አንድ የዳኝነት ነፃነት ነው የዳኝነት ነፃነት መርህ ተግባራዊ ለማድረግ በቂ የህግ ማዕቀፍ ከጠፀዘቨ መኖር አለመኖሩን እንዲሁም ስለመርሁ ተግባራዊ አፈፃፀም በቂ ግንዛቤ ለመጨበጥ የመርሁ ምንነት ገፅታዎችና የመርሁ አስፈላጊነት በመጀመሪያ ግልፅ መደረግ አለባቸው ከዚህም አንፃር የኢትዮጵያ ሥርዓት ለመፈተሽ የዳኝነት ነፃነትን በተመለከተ አለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ዝቅተኛ መመዘኛዎችንና የሌሎች ሐገሮችን ልምድ ማየቱ ጠቃሚ ነው የዚህ የመጀመሪያ ክፍል አላማም ይሔው ነው ሰልጣኞች ይህን ከፍል ሲያጠናቅቁ ። የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ ነፃ የሆነ የዳኝነት አካል የሚጫወተውን ወሣኝ ሚና ተረድተው በቁርጠኝነት ለተግባራዊነቱ ይነሳሳሉ ይሰራሉ የዳኝነት ነፃነት ምንነት የዳኝነት ነፃነት መርህ በበርካታ ሊቃውንትና ዳኞች ጠበቆች ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት የተነገረለትና የተፃፈበት ጉዳይ ነው በበርካታ ሐገሮችም ህገመንግስታዊ አውቅናና ጥበቃ የተደረገለት መርህ ነው ሆኖም ግን የዳኝነት ነፃነት ተለዋዋጭ ፅንሰ ሐሳብ በመሆኑ ስለዳኝነት ነፃነት መርህ ምንነት ወጥ የሆነ ትርጉም የለም ፀሐፊዎች የዳኝነትን ነፃነትን በተለያየ መንገድ ለመግለፅ ሞክረዋል ለምሳሌ እንደ ኬሮሲን የዳኝነት ነፃነት ማለት ዐፀጋጩፀ ዘዕ ሀፀ ቋሪ ዕፀርሀሮሆ ር ቋርርዐዐዉወሰገርሪፀ ዘሃያሃያ ሀር ዐዘ ዐፀርገ ዐ ፀህዐፀቦርዉ ዕ ቋገሮሪ ህርሬ ፀ ሀዐ ዕፀ ርዐወፔጩዐ ዕገርሂ ገርፀ ዐ ቋ ሀ ሪዐዕህፀ ደ ዐ ዕዌ ሮፌ በተመሳሳይ መልኩ ፒኒ ጄ ዋይት የዳኝነት ነባነትን እንደሚከተለው ገልፆታል ሠሃሪር ዐወፎጋፀወጋዐፀርፀ ገሪፀዐፀዐፀገርፀ ዐ ሀ ዕ ሪ ርህ ሀ ዕዐጋዕሀ ዕህ ሠዐወዐ ሀሀ ሀ ሀ ዐ ቋ የዳኝነት ነፃነት ማለት ዳኞች ካለምንም ውጪ ጣልቃ ገብነት ተፅእኖና ግፊት የቀረበላቸውን ጉዳይ ሕጉንና ማስረጃ ብቻ መሠረት በማድረግ ለመወሰን ያላቸውን ነፃነት እንደሆነ ከላይ ከተጠቀሱት ሁለት ትርጉሞች መረዳት ይቻላል ሆኖም ግን ከላይ የተጠቀሱት ትርጉሞች ሙሉ አይደሉም ትርጉሞቹ የሚያተኩሩት በውሳኔ አሰጣጥ ወይም በፍርድ አሰጣጡ ሒደት ዳኛ ያለው ነፃነት ላይ ነው በዚህ መሰረት የዳኝነት ነፃነት ባለቤት ሀከር። ዳኛ የቀረበለትን ጉዳይ በፍሬ ነገር ማስረጃና አግባብነት ካለው ህግ ላይ ብቻ ተመስርቶ እንዲወስን ሁኔታዎች ሁሉ መመቻቸት አለባቸው ከዚህ ውስጥ የዳኞች ግላዊ ነፃነት ዋስትና እንዲኖረው ማድረግ አንዱ ነው ግላዊ ነጻነት የዳኞች የሥራ ዘመን ከሌሎች የመንግስት አካላት አለአግባብ ተጽእኖና ቁጥጥር ነፃ እንዲሆን የሚጠይቅ ነው የዳኞች ምልመላ ሹመት ዕድገት ዝውውር የሥራ ዘመን ዲሲፕሊን ከሥራ ማሰናበት ሥርዓት እና ሌሎች ሁሉ የሕግ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ የዳኝነት ነፃነት መርህ ይጠይቃል። ዐሃሬባጩርፎ ዐ ፀሀደፀ ዐ ሀዐ ዋዐርዘርዌዐህ ሀከር ወፀፀ ዐ ጩመፀበርዐፀዐጸ ርዐሠ ከዚህ አገላለፅ እንደምንረዳው ተቋማዊ ነፃነት ፍቤትን እንደ ሦስተኛ የመንግስት አካል መቋቋምና መኖርን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን ከሕግ አውጪና ከሕግ አስፈጻሚው ተፅእኖ በተለይም ፍቤትን ማስተዳደር በተመለከተ ነፃ መሆኑን የሚጠይቅ ነው በሌላ አነጋገር ተቋማዊ ነፃነት ፍቤት እንደ ተቋም ከሕግ አውጪውና ከሕግ አስፈጻሚው አካል ተፅእኖ ነባ ሆኖ የራሱን የውስጥ ጉዳይ ለመወሰን ያለውን ነፃነት የሚመለከት ነው የፍቤት የማስተዳደር ነፃነትም ሁሉት አብይ ክፍሎች አሉት እነሱም ዳኞችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞን የማስተዳደር ነፃነትና የፋይናንስ ወይም የበጀት ነፃነት ናቸው ዳኞችን የማስተዳደር ነፃነት የዳኞች ምልመላ ሹመት ዝውውር እድገት ዲሲፕሊን ከሥራ ማሰናበት ደሞዝና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችና እንዲሁም ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን መቅጠርና ማሰናበት በተመለከተ ፍቤት አንድ ተቋም ሊኖረው የሚችለውን ነፃነት የሚመለከት ነው የፋይናንስ ወይም በጀት አስተዳደር ነፃነት ደግሞ ፍቤቶች የሚያስፈልጋቸውን በጀት መጠን ግምት አዘጋጅተው ለሚመለከተው አካል እንዲፀድቅ ማቅረብና በጀቱም ከፀደቀ በኋላ ከሥራ አስፈጻሚው አካል ጣልቃ ገብነት ውጪ በጀቱን የማስተዳደር ነፃነትን የሚያጠቃልል ነው ከፍቤቶች ተቋማዊ ነፃነት ጋር የሚነሳው ጥያቄ ፍቤቶችን ማን ያስተዳድር የሚለው ነው የፍቤቶች የማስተዳደር ኃላፊነትን በተመለከተ የተለያዩ ሞዴሉች አሉ እንደ ፕሮፌሰር ሼሞን ሼቲሪት አራት አይነት የፍቤት አስተዳደር ሞዴሎች አሉ አንደኛው ከ ጁኗርሆር ር ዩሃ የሚባለው ነው በዚህ ሞዴል ፍቤትን የማስተዳደር ኃላፊነት ሙሉ በሙሉ ለፍቤት የተተው ነው ይህ ሞዴል ሁለት ንዑስ ሞዴሎች አሉት። ለምሳሌ ጀርመንና ካናዳ የላይኛዎቹን ፍቤት የማስተዳደር ኃላፊነት የፍቤቶች ሲሆን የበታችኞቹን ፍቤቶች የማስተዳደር ኃላፊነት ደግሞ የሕግ አስፈጻሚው ነው አራተኛው ሞዴል ከልዉዐዉርከ ህቪሃ ከ የሚባለው ሲሆን በዚህ ሞዴል መሰረት ፍቤትን የማስተዳደር ኃላፊነት ከፍቤትና ከሌሎች ከሦስቱም የመንግስት አካላት ማለትም ከሕግ አውጪ ወይምእና ሕግ አስፈጻሚና እንዲሁም ከሌላ አካል ለምሳሌ ከጠበቆች ማህበር ወይም ከሌሎች ሕብረተሰብ ክፍል የተወከሉ ሰዎች ለተውጣጣ አካል የተሰጠ ነው ይህ አካል ቦርድኮሚሽን ኮንፍረንስ የዳኞች ጉባኤ ተብሎ በተለያየ ስም ይጠራል ለምሳሌ ከላቲን አሜሪካ ሀገሮች አርጀቲና ብራዚል ከምፅራብ አውሮፓ ደግሞ ስፔንና ጣሊያንን መጥቀስ ይቻላል በምዕራብ አውሮፓ ሐገሮች የዳኞች ጉባኤ ሕግ አስፈጻሚው በፍቤቶች ላይ ያለውን ሥልጣን ለመገደብ የተቋቋመ ነው በዚሁ መሰረት የዳኞች ሹመት ዕድገትን ሥልጣን ከሕግ አስፈጻሚው ውጪ በማድረግ ራሱን ለቻለ ተቋም እንዲሰጥ ተደርጓል ሐገሮች የራሳቸው ልዩ ሁኔታ ያላቸውን የሕግ ስርዓትና ታሪክ ላይ በመመስረት ከላይ የተጠቀሱትን አንዱን ወይም ሁለቱን በማጣመር ወይም ሌሎች ተመሳሳይነት ያላቸው ሞዴሎችን ሊመርጡ ይትችላሉ ሆኖም ግን የሞዴሎቹ ምርጫ ፍቤቶች ሊኖራቸው በሚችለው ነጻነት ላይ የራሱን አሉታዊ ወይም አውንታዊ ተጽኖ ሊኖረው ይችላል በተጨማሪም የዳኝነት ተቋማዊ ነፃነትን ለመጠበቅ ሌሎች ሊተገበሩ የሚገባቸው መሰረታዊ መርሆች አሉ ከእነዚህ ውስጥ ከመደበኛ ፍቤት ውጪ ጊዜያዊ ፍቤቶችን ማቋቋምን የሚከለከል መርህ ከ ፒ ከር ርህ እና ከውሳኔ በኋላ ያለ የዳኝነት ነፃነት መርህ በከ ፒዉርቬ ዐ በር ህበርበበፎበርር ሊጠቅሱ የሚችሉ ናቸው። በዚህ አካል ውስጥ ከፍቤት የሚወከሉ ሰዎች አብላጫውን ቁጥር መያዝ አለባቸው በዚህ መመዘኛ መሰረት የዳኞች ምልመላ ሹመት ዝውውር እድገት ዲሲፕሊን ከሥራ ማሰናበት እንዲሁም ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን መቅጠርና ከሥራ መሰናበት ከሕግ አስፈጻሚው አካል ውጪ መሆን አለበት በሌላ በኩል የቆየ የዲሞክራሲ ታሪክና ልምድ ባላቸው ሐገሮች የዳኞች ሹመትና ዕድገት ከፍቤት ውጪ በሆነ አካል እንዲከናወን መሆኑ ከዳኝነት ነፃነት መርህ ጋር እንደማይጋጭ በአለም አቀፍ ጠበቆች ማህበር ዝቅተኛ የዳኝነት ነፃነት መመዘኛ ውስጥ ተመልክቷል። ከፀ ሀፀኣከቨ ዐ ከፀ ቧበዐኗ ከ ከ ኗ በኗርሀከ ዐ ርከፀ መሄ ዐ ከፀ አዐርሃ ርፀከፀ ዐከ ከዐህ ቧበዐኗ ፀ ርከዐፍ ዳኞች ቀጥተኛም ሆነ ቀጥተኛ ከልሆነ ገደብ ተፅእኖ ማግባባት ግፊት ማስፈራራት ወይም ጣልቃ ገብነት ነፃ መሆን አለባቸው ስለተባለ ብቻ የዳኝነት ነባነት ሊኖርም ሊረጋገጥም አይችልም የእነዚህ ሁኔታዎች መኖር ወይም አለመኖር በእያንዳንዱ ዳኛ የስብእና ድክመት ወይም ጥንካሬ የሚወሰን ነው አንድ ዳኛ ተገዥነቱን ለሕግ በቻ ከላደረገና ሕግን ብቻ መሠረት አድርጐ የዳኝነት ሥራ ተግባሩን በመፈጸሙ ምክንያት ሊያጋጥመው የሚችለውን ፈተና ለመቋቋም የሙያና የመንፈስ ብርታት ከሌለው ከላይ ለተጠቀሱት አሉታዊ ሁኔታዎች የአንዱ ወይም የሁሉም ባርያ ከመሆን አያልፍም የዚህ አይነት ዳኛ የዳኝነት ነባነት መርህ የግድ የሚላቸው የገለልተኝነት የነፃነት የአመዛዛኝነት እና የደፋርነት ባህሪ ሊኖረው አይችልም በቂ የሕግ አውቀት ያላቸው በፀባያቸው የተመሰገኑ ደፋር ሰብአዊነት የሚሰማቸው ሰዎች በፍርድ ሥራ ሒደት ገለልተኛ በመሆን የሕግ የበላይነትን ያከብራሉ ያስከብራሉም የፍርድ ቤትን ነባነት አሳልፈው አይሰጡም የፍርድ ቤትን ክብር የማስጠበቅ ብቃት ይኖራቸዋል ሕዝብና መንግስት በፍቤት ላይ እምነት እንዲኖራቸው ያደርጋሉ የምልመላ ሂደትም የዚህ አይነት ብቃት ሊኖራቸው የሚችል ሰዎችን ለሹመት የሚያበቃ መሆን አለበት ለዚህም የእጩ ዳኞች ምልመላ እንዴት ይካሄድ የሚለውና የምልመላው መስፈረቶች ምን መሆን አለባቸው የሚለው በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት ያገኘ ጉዳይ ነው አንደ የተባበሩት መንግስታት የፍቤት ነባነት መሠረታዊ መርሆች ለዳኝነት ሥራ የሚመለመሉ ሰዎች የተሟላ ስብእና ችሎታና የሕግ ሙያ ወይም ተገቢ የሕግ ስልጠና ያላቸው መሆን አለባቸው እንደ ዓለም አቀፍ የዳኝነት ነፃነት ዝቅተኛ መመዘኛ የአጩ ዳኛች የምልመላ ሂደት ገለለተኛና ምልመላውም ተጨባጭ መስፈርቶች ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት በምልመላው ሂደት የተመልማዩ የፖለቲከ አመለካከት ወይም ለገዥው ፖርቲ ያለው ታማኝነት ከግምት ውስጥ መግባት የለበትም ምልመላን በተመለከተ ወጥ የሆነ አሠራር የለም የምልመላው ሂደት ከዛገር ዛገር ይለያያል አንዳንድ ዛገሮች ለዳኝነት ሹመት የሚያበቁ መስፈርቶችን በግልጽ ያስቀምጣሉ ለዚህም የኮመን ሎው ስርዓት ተከታይ ከሆኑት አገሮች ውስጥ ከናዳ አንግሊዝ አና ደቡብ አፍሪካን መግለጽ ይቻላል ለዳኝነት ሹመት የሚያበቁ መስፈርቶችን ከማስቀመጥ በተጨማሪ ከአጩነት የሚያግዱ መስፈርቶችን በዝርዝር የሚያስቀምጡ ዛገሮችም አሉ ለምሣሌ በከናዳ የአልኮል ሱስ ወይም የፍትሕ ብሄር ወይም የወንጀል ክስ ያለበት ወይም የወሲብ ጥቃት አቤቱታ ወይም የዲሲኘሊን አቤቱታ ያለበት ሰው በአጩነት ሊቀርብ አይችልም በሌላ በኩል አንዳንድ ሐገሮች ለዳኝነት የሚያበቁ መስፈርቶችን አያስቀምጡም ለምሳሌ ፈረንሳይን ብንወስድ አዲስ የሕግ ሙሩቃን ከሕግ ትምህርት ቤቶች በፈተና ከተመለመሉ በኋላ ወደ ሥልጠና እንዲገቡ ይደረጋል ስልጠናውም ለሰላሳ አንድ ወራቶች የሚቆይ ሲሆን ሥልጠናውን በሚገባ ያጠናቀቁ ሰልጣኞች በጉባኤ ወይም በፍትህ ሚኒስተር አቅራቢነት በሐገሪቱ ፕሬዜዳንት ይሾማሉ ይህ የፈረንሳይ የምልመላ ሒደት የገለልተኝነትን መስፈርት የሚያሟላ ነው ብለው በምሳሌነት የሚጠቅሱ ፀሐፊዎች አሉ በአሜሪካ የፌዴራል ፍቤት ዳኞች በኘሬዜዳንቱ አቅራቢነት በሴኔት ይሾማሉ ፅጩዎችን አጣርቶ ለፕሬዜዳንቱ የሚያቀርበው የሴኔት አባሎች ያሉበት ኮሚቴ ነው ይህ የምልመላ ሒደት ግልፅነትና በተጠያቂነት መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ተብሎ እንደምሳሌ ይጠቀሳል በሌላ በኩል ደግሞ በተለይ የጠቅላይ ፍቤት ዳኞችን ሹመት በተመለከተ የምልመለው ሒደት ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ነው ብለው የሚተቹም አሉ በካናዳ ፌዴራል ዳኞች የሚሾሙት በካቢኔው ነው ዕጩዎች ተጣርተው ለካቢኔው የሚቀርቡት በኮሚቴ ነው የኮሚቴው አባሎችም ከጠበቆች ማህበር ከፍቤትና ከሌሎች ህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡ ናቸው የኮሚቴው አባሎችም የሚሰየሙት በፍትህ ሚኒስተር ሲሆን ኮሚቴውም አመልካቾችን በደረጃ አውጥቶ ለካቢኔው ይቀርባል በአጠቃላይ በምልመላ ሂደት ከሐገር ሐገር የተለያየ ቢሆንም ምልመላ በዘፈቀደ መከናወን የለበትም የምልመላው ሂደትና መመዘኛ መሰፈርቶች እንዲሁም ምልመላውን ለማካሄድ ሥልጣን የተሰጠው አካል ምልመላውን የሚካሔድበት አሠራር በግልፅ መታወቅ አለበትፁ የምልመላው ሂደት ግልፅነት ያለውና ከሙስና የፀዳ መሆን አለበት ወደ ሐገራችን ስንመለስ በኢፌድሪ ሕገመንግስት አንቀጽ ሥር እንደተደነገገው በፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ኘሬዜዳንትና ምክትል ኘሬዜዳንት በፌደራል መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አቅራቢነት በሕዝብ ተወከዩች ምክር ቤት የሚሾሙ ሲሆን የክልል ጠቅላይ ፍቤቶች ኘሬዝዳንትና ምክትል ኘሬዜዳንት ደግሞ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቅራቢነት በክልሉ ምክር ቤት ይሾማሉ የሌሎች ዳኞች የምልመላ ሒደት ከዚህ የተለየ መሆኑና በፌዴራልና በክልሎች መካከለም መጠነኛ ልዩነት ያለ መሆኑን ከዚሁ ከሕገመንግስትቱ ድንጋጌ መረዳት ይቻላል ዳኛ ሆኖ ለመስራት የሚያበቁ መመዘኛዎች በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ማቋቋሚያ አዋጅና በክልሎችም በወጡ አዋጆች ውስጥ ተዘርዝረዋል አነዚህም ለፌዴራል ሕገመንግስት ታማኝ መሆን በክልሎች ደግሞ ለፌዴራልና ለክልሉ ሕገመንግስት ታማኝ መሆን የሕግ ትምህርት ወይም በቂ የሕግ ልምድ መልከም ስምና ፀባይ በወንጀል ተከሶ በፍቤት ያልተቀጣ ፅድሜው ሃፃያ አምስት የሞላው ኦሮሚያ የአዕምሮ በሽተኛ ያልሆነ ጋምቤላና ኦሮሚያ በዳኝነት ሙያ ለመስራት ፈቃደኛ የሆነ ዳ ወ ። የሥራ ዘመን ዋስትና ደግሞ በቂ ችሎታና ጥሩ ስብዕና ያላቸው ሰዎች በዳኝነት ሥራ ላይ እንዲቆዩ ያደርጋል በተጨማሪም አንድ ዳኛ የሚሰጠው ውሳኔ በፖለቲካ አካሉ ተቀባይነት አይኖረውም ይሆናል በዚህ ምክንያትም ከስራ ልባረር አችላለሁ የሚል ፍራቻ በዳኛው አእምሮ እንዳይቀረፅና ዳኛው ሥራውን ላለማጣት ወይም የስራ ጊዜውን ለማራዘም ሲል ከህግ ዉጪ ሊወሰን የሚችልበት ሁኔታ እንዳይኖር ለመከላከል የሥራ ዘመን ዋስትና አይነተኛ መሣሪያ ነው ለዚህም የዳኞች የሥራ ዘመን የሕግ ጥበቃ እንዲደረግላት የዳኝነት ነፃነት መርህ ይጠይቃል የዳኞች የሥራ ዘመን በሕግ አስፈፃሚው አካል በጐ ፍናቃድ ላይ የተመሠረተ መሆን የለበትም የዳኞች የሥራ ዘመን ዋስትና ከሌለውና በሕግ አስፈፅሚው በጐ ፍቃድ የሚወሰን ከሆነ ዳኞች በገለልተኝነት ውሳኔ ሊሰጡ አይችሉም የዳኞች የሥራ ዘመን ዋስትና ሊያገኝ የሚችለው የዳኞችን ሹመት ለሕይወት ዘመን ወይም ዳኛው በህግ የተወሰነ እድሜ እስከሚደርስ ድረስ በማድረግ ነወ ይሔ ብቻ በቂ አይደለም የዳኞችን የሥራ ዘመን ዋስትና አንዲኖረው አንድን ዳኛ በሕግ የተወሰነው የሥራ ዘመን ከመድረሱ በፊት የዳኝነት ሥራ ሊያስነሱት የሚችሉ ምክንያቶች በግልፅ በሕግ ተደንግገው መቀመጥ አለባቸው በሕግ የተወሰነው የሥራ ዘመን ከመድረሱ በፊት ብቃትና የሥነምግባር ችግር ያለባቸውን ዳኞች ከሥራ ማሰናበት ወይም የሥራ ዘመናቸው እንዲቋረጥ ማድረግ የዳኞች የሥራ ዘመን ዋስትና አንዲኖረው ከማድረግ ጋር የሚጋጭ አይደለም የሥራ ዘመን ዋስትና በተባበሩት መንግስታት የፍቤት መሠረታዊ መርሆች አንቀጽ እና ሥር በግልፅ ተደንግጓል የዳኞች የሥራ ዘመን ዋስትና አስፈላጊነት ላይ ምንም ክርክር የለም ብዙ ሐገሮች የዳኞችን ሥራ ዘመን የሕግ ጥበቃ አድርገዋል ብራዚል ኮለምቢያ ቺሊ ፔሩ አርጀንቲና እና አሜሪከ ፌዴራል ዳኞች ለምሳሌ የዳኞች የሥራ ዘመን አስከ እድሜ ልክ ወይም ለሕይወት ዘመን ነው ሕንድ ፈረንሳይ ጀርመን ካናዳ ጋና እና ናይጂሪያን ደግሞ የዳኞች የሥራ ዘመን በሕግ የተወሰነ የጡረታ መውጫ ዕድሜ ድረስ ነው ይህ በሕግ የተወሰነው የሥራ ዘመን ከመድረሱ በፊት አንድ ዳኛ ከሥራ ሊሰናበት የሚችልበት ምክንያቶችም ተቀምጠዋል አንድን ዳኛ የሥራ ዘመኑ ከመድረሱ በፊት ከሥራ የሚሰናበትበት ሥርዓትም እንዲሁ ከሐገር ሐገር ይለያያል እንደ ዓለም አቀፍ የዳኝነት ነፃነት ዝቅተኛ መመዘኛ የዲሲፕሊንና ከሥራ ማሰናበት ሒደት ሚዘናዊ መሆን አለበት ዳኛው የሚቀርብበትን ክስ የማወቅና የመከለከል መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል ማንኛውም የዲሲፕሊን እርምጃ በሥነ ምግባር ደንብ ወይም በፍቤቱ በዳበሩ ደንቦች ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት በተጨማሪም በዳኞች ላይ የሚቀርብ ክስ በፍጥነት መታየት እንዳለበት የዳኝነት ነፃነት መርህ ይጠይቃል የመወያያ ጥያቄዎች በሐገራችን የዳኞች የሥራ ዘመን ዋስትና አንዲኖረው ለማድረግ ምን ምን አርምጃዎች ተወስደዋል ፃ የዳኞችን የስራ ዘመን ዋስትና አንዲኖረው ለማድረግ በፌዴራልና በክልል ደረጃ በቂ የሕግ ማዕቀፍ አለ። ዝውውርና እድገት አንደ አለም አቀፍ የዳኝነት ነጻነት ዝቅተኛ መመዘኛ ዳኞች ከመደበኛው የዝውውር በስተቀር ከፈቃዳቸው ውጪ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መዛወር የለባቸውም አንድ ዳኛ በዚህ መንገድ ብወስን በዚህ ምክንያት ወደ ሌላ ቦታ እዛወር ይሆናል የሚል ፍራች በአምሮው አንዳይቀረጽና ወደ ሌላ ቦታ ላለመዛወር ሲል ከሕግ ውጪ ሊወሰን የሚችልበት ሁኔታ እንዳይኖር የዳኞች ዝውውር በሕግ በግልጽ በተቀመጠ ምክንያት ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት የዳኞች ዕድገት ደግሞ ተጨባጭ በሆኑ መመዘኛ በተለይ ችሉሎታ ስብዕናና ልምድ ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት እድገት እንዴትና በምን መመዘኛ እንደሚሰጥ በህግ በግልጽ መቀመጥ እንዳለበት የዳኝነት ነፃነት መርህ ይጠይቃል በክንዳንድ ሐገሮች የዳኞች ዕድገት አይታወቅም ለምሳሌ ጀርመን ሕንድ ብራዚል ደቡብ አፍሪካ አሜሪካ እንግሊዝና ካናዳ ለሁሉም የፍቤት እርከን ዳኛ የሚመደበው በሹመት ነው በፈረንሳይ ጋናና ጃፓን ደግሞ በእድገት ነው ወደ ሐገራችን ስንመለስ በፌዴራልም ሆነ በክልል የዳኞች ዝውውርና የመወሰን ሥልጣን የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ነው ዝውውር በምን ምክንያትና በምን ጊዜ ውስጥ መፈጸም እንዳለበት የሚገልፅ ሕግ ግን የለም በአማራ ክልል ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዝውውርን የሚመለከት መመሪያ ወጥቷል አድገትን በተመለከተም ግልጽ የሆነ መመዘኛ የለም በአንዳንድ ክልሎች ለምሳሌ ኦሮሚያ ደቡብ ሐረሪ አና ቬኒሻንጉል ጉምዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዳኞች የሥራ አፈፃፀም መለኪያ ፀቨዘከኋበር ህህሀዐበ ተግባራዊ ለማድረግ አንዳንድ ጥረቶች እየተደረጉ ናቸው በሌላ በኩል በፌዴራልና በክልል የዳኞችን ዕድገት የመወሰን ሥልጣን የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ቢሆንም አንድ ዳኛ ከወረዳ ፍቤት ወደ ከፍተኛ ፍቤት ወይም ከከፍተኛ ፍቤት ወደ ጠቅላይ ፍቤት ለመምጣት የምክር ቤት ሹመት ያስፈልገዋል ወይስ አያስፈልገውም ለሚለው ጥያቄ ተመሳሳይ መልስ የለም ለምሳሌ በፌዴራል በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እአና በአማራ አንድ ዳኛ ከፍተኛ ፍቤት ወደ ጠቅላይ ፍቤት ሲድግ በክልሉ ምክር ቤት መሾም አለበት በኦሮሚያ ደግሞ አንድን ዳኛ ከከፍተኛ ወደ ጠቅላይ ፍቤት ወይም ከወረዳ ወደ ከፍተኛ ፍቤት ማሳደግ በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ውሳኔ ብቻ በቂ ነው የትኛው አሠራር ከሕገመንግስቱ ጋር የሚጣጣም መሆኑን ሰልጣኞች ውይይት ሊያደርጉበት ይችላሉ ማጠቃለያ መወያያ ጥያቄዎች በኢፈድሪ ሕገመንግስታዊ ሥርዓት ነዛና ፍትሐዊ የዳኝነት አካል ለመገንባት በቂ የሕግ ማፅቀፍ አለ። በዲሞክራሳያዊ ሥርዓትና በዳኝነት ተጠያቂነት እንዲሁም በግልጽነት መርህ መካከል ያለውን ግንኙነት ማስረዳት ይችላሉ የዳኝነት ተጠያቂነት የዳኝነት ተጠያቂነት ምንነት ለዳኝነት ተጠያቂነት ወጥ የሆነ ትርጉም የለም የተለያዩ ፀሐፊዎች የዳኝነት ተጠያቂነትን በተለያየ መንገድ ለመግለጽ ሞክረዋል። የሚለውና ሦስተኛው የዳኝነት ተጠያቂነት ባለቤት ወይም ባለቤቶች ተጠያቂ የሚሆኑት ምን ሲፈፅሙ ወይም ሳይፈፅሙ ሲቀሩ ነው የሚሉት ናቸው ስለዳኝነት ተጠያቂነት የሚሰጡ ትርጉሞችም ከዚሁ አኳያ ሊመዘኑ ይገባል በቆየው አስተሳሰብ የዳኝነት ተጠያቂነት ባለቤት ተደርገው የሚወሰዱት ዳኞች ናቸው በዘመናዊ የዳኝነት ተጠያቂነት ፅንስ ሐሳብ መሰረት ግን የዳኝነት ተጠያቂነት ባለቤት ዳኞች ብቻ ሳይሆን ፍቤቶችንም እንደተቋም የሚያጠቃልል ነው በተመሳሳይ መልኩ የዳኞች ወይም የፍቤቶች ተጠያቂነት ለሕግ አስፈጻሚ ወይም ለሕግ አውጪው ብቻ አይደለም የዳኞች ወይም የፍቤቶች ተጠያቂነት ለሁለቱም የመንግስት አካሉች ለተከራካሪ ወገኖች ለዳኝነት አካሉ ለራሱ ለሚዲያ ለዕበጠዉ ቡድንና ለሌሎች አካላት ሊሆን ይችላል ዳኞች ተጠያቂ የሚሆኑት አንድን ጉዳይ ሲወስኑ ለሚፈጽሙት ስህተት ወይም መፈፃዓም የሚገባቸውን ተግባር ሳይፈጽሙ ሲቀሩ ብቻ ሳይሆን ከችሎትና ከችሎት ውጪ ለሚያሳዩት ሥነምግባርም ጭምር ነው ፍቤቶችም ዋናው ዓላማቸው ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት በመሆኑ ለህብረተሰቡ ውጤታማ አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለባቸው የመንግስትን ንብረት በአግባቡ መጠቀም ይኖርባቸዋል ስለዚህ ፍቤቶች እንደ ተቋም ለሚያከናውኑት ዳኝነታዊና አስተዳደራዊ ተግባሮች ተጠያቂነት አለባቸው በአንድ ሐገር ለዳኝነት ተጠያቂነት የሚሰጠው ትርጉም የፖለቲካ አካላትና ሕዝቡ የፍትህ አስተዳደርን በተመለከተ በዳኛው ወይም በፍቤቶች ላይ ያላቸውን አስተሳሰብ ጸከኪዐ የሕግና የፖለቲካ ሥርዓትየዳኝነት ሥርዓትና ታሪክ ልምድ በሐገሪቱ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ የሚወሰን ነው ሰፋ ባለ መልኩ ግን የዳኝነት ተጠያቂነት ማለት ዳኞችና ፍቤቶች በሕግና በሥነምግባር ደንቦች መሰረት ለመሥራት ያለባቸው ኃላፊነትና በዚሁ መሰረት እንዲሰሩ ወይም መሥራታቸውን ለማረጋገጥ በሌሎች የሚደረግባቸው ተገቢ ቁጥጥርና ክትትል ለሚፈፅሙት ተግባር ወይም ሳይፈጽሙ ለቀሩት ተግባሮች መጠየቅ ወይም ኃላፊ መሆን ወይም ምክንያት የመስጠት ኃላፊነት ወይም የፈጻሙት ስህተትና ሕገወጥ ተግባር የሚያስከትለውን ውጤት መሸከም ነው ተብሎ ሊገለጽ ይችላል የዳኝነት ተጠያቂነት ለምን። በክባህ ሀበ በበ ፀከፀ በሀዘበፀዬዕቨፀበፀዐ በ ናቸው እንደ ካፒሊቲ በመጀመሪያው ሞዴል መሰረት ፍቤት እና ወይም ዳኞች ተጠያቂ የሚሆኑት ለመንግስት የፖለቲካ አካላት ሲሆን ሁለተኛው ሞዴል ደግሞ ከአንደኛው ሞዴል በተቃራኒው ዳኞችና ፍቤቶችን የመቆጣጠር ኃላፊነት ለፍቤት ለራሱ የተተወ ነው የሶስተኛው ሞዴል ደግሞ የፍቤት እና ወይም ዳኞች ተጠያቂነት ከፖለቲካ አካላት ከፍቤት እና ከሌላ ሕብረተሰብ ክፍሎች ለተውጣጣ አካል ነው እንደ ካፒሊቲ ይፄ ሞዴል የዳኝነት ነባነትና ተጠያቂነት ሚዛናቸውን ጠብቀው እንዲሄዱ የሚያስችል ተመራጭነት ያለው ሞዴል ነው ወንዲል ኤል ግሪፌን የተባለው ፀሐፊ ደግሞ የፖለቲካ ተጠያቂነት ውሳኔያዊ ተጠያቂነት ዐበ ርሀበክህ እና የሥነምግባር ከኋጪ ተጠያቂነት በማለት የዳኝነት ተጠያቂነትን በሦስት ይከፍላቸዋል እንደ ግሪፌን የፖለቲካ ተጠያቂነት ምልመላ የሥራ ዘመን ዋስትና አንዲሁም የዳኝነት ሥልጣን በተመለከተ ዳኞች ለፖለቲካ አካላት ያለባቸውን ተጠያቂነት የሚመለከት ነው በሌላ በኩል ውሳኔያዊ ተጠያቂነት ደግሞ ዳኞች ለሚሰጡት ትዕዛዝና ውሳኔ ተጠያቂ የሚሆኑበትን ሁኔታ የሚመለከት ነው የሥነምግባር ተጠያቂነት ደግሞ ለዲሲፕሊን ክስ መሰረት ለሆነው የዳኝነት ሥነምግባር ጋር የተያያዘ ነው ፕሮፌሰር ሺሞን ሼትሪት በራሱ በኩል የዳኝነት ተጠያቂነት በሦስት ከፍሉታል አነሱም የሕግተጠያቂነት ልዕርዐሀበ። በምሳሌ በማስደገፍ ውይይት ይደረግበት የዳኝነት ተጠያቂነት በኢፌድሪ መግቢያ በኢፌዲሪ ሕገመንግስት ውስጥ ከተቀመጡት መሠረታዊ ሕገመንግስታዊ መርሆች ውስጥ አንድ ተጠያቂነት ነው ተጠያቂነት የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ልዩ ባህሪ ነው በሀገራችንም እየተገነባ ያለው ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ካለተጠያቂነት ሊታሰበ አይችልም የተጠያቂነት መርህም በሶስቱም የመንግስት አካሎች ተፈፃሚነት ያለውና ሊተገብሩት የሚገባችው መርህ ነው ስለዚህ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ነባ የዳኝነት አካልን ብቻ የሚጠይቅ ሳይሆን ነፃና ተጠያቂነት ያለበት የዳኝነት አካል የሚጠይቅ ነው ተጠያቂነት የሌላው የዳኝነት አካል የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ጠንቅ ከመሆን ውጪ የሚፈይደው ነገር የለም ስለዚህ ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው ፍቤቶች ያለባቸውን ሕገመንግስታዊ ተልእኮቸውን ለመወጣት ነፃ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂም መሆን አለባቸው በኢፌድሪ መንግሥት የዳኝነት ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የተለያዩ ሥርዓቶች ተዘርግተዋል የዳኝነት ነፃነትና ተጠያቂነት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች በመሆናቸው የፌዴራልና የክልል ፍቤቶችና ዳኞች ነፃነት ከተጠያቂነት ጋር ጎን ለጎን የሚፄድ ነው በፌዴራልና በክልል ሕገመንግስቶች ውስጥ የዳኝነት ነፃነት የሚመለከቱ ድንጋጌዎች ሁሉ የዳኝነት ተጠያቂነት ገፅታ ወይም ይዘት አሏቸው ስለዚህ በኢፌድሪ መንግስት የዳኝነት ነፃነት ለማረጋገጥ የተዘረጉ ሥርዓቶች ሁሉ የዳኝነት ተጠያቂነትን የሚመለከቱ ናቸው እነዚህ ሥርዓቶች የተለያየ ገፅታ ሊኖራቸው ይችላል የዳኝነት ተጠያቂነት ገፅታዎች ውስጣዊና ውጫዊ ብለን ለመከፋፈል እንችላለን የበለጠ ደግሞ የፕሮፌሰር ሺሞን ሼቲሪት የአመዳደብ ስልት ላይ በመመስረት በኢፌድሪ መንግስት የዳኝነት ተጠያቂነት ለማረጋገጥ ያሉ ሥርዓቶችን የሕዝብ ተጠያቂነት የሕግ ተጠያቂነት ኢመደበኛና ማህበራዊ ቁጥጥር በማለት ከፋፍሎ ማየት ይቻላል ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው የሕዝብ ተጠያቂነት ፍቤቶችና ዳኞች ለሌሎች የመንግሥት አካላትና ለፕሬስ ተጠያቂ የሚሆኑነበትን የሕግ ተጠያቂነት ደግሞ የይግባኝ ሥርዓት የወንጀልና የዲሲፕሊን ተጠያቂነት የሚመለከት ነው በዚህ ክፍል የምናየው ፍቤቶችና ዳኞች ለሕግ አውጪው ያለባቸው ተጠያቂነት የዳኞች የወንጀልና የዲሲፕሊን ተጠያቂነት ብቻ ይሆናል ሌሎቹ ሰልጣኞች በውይይት የሚያደርጉበትና ግማሾቹን ደግሞ ከግልፅነት መርህ ጋር የምናያቸው ይሆናል ፍቤቶችና ዳኞች ለሕግ አውጪው ያለባቸው ተጠያቂነት የሕዝብ ተጠያቂነት ፍቤቶች የሕዝብ ተቋማት ከመሆናቸው የሚመነጭ ነው የፌዴራል ጠቅላይ ፍቤትና በክልል ደግሞ በሶስቱም እርከን የሚገኙ ፍቤቶች በቀጥታ በሕገመንግስቱ የተቋቋሙ ናቸው በሕገመንግሥቱም ሆነ በሌላ ሕግ የተቋቋሙ ፍቤቶች ዋና አላማ ሕጎችን በትክክል በመቶርጎም የሕዝብን መብቶች ፍላጎት ሟሟላት ነው በሌላ በኩል በሕገመንግሥቱ የሉአላዊነት ስልጣን ባለቤት ሕዝቡ በመሆኑ በሕገመንግሥቱ ወይም በሌላ ሕግ የተቋቋሙ ፍቤቶች ሕጉን በትክክል በመቶርጎም የሕዝቡን መብትና ፍላጎቱን በትክክል እያሟሉ መሆኑን ሕዝቡ የማረጋገጥ የመቆጣጠር መብትና ግዴታ አለበት በፍቤቶች ውስጥ የሚሠሩ ዳኞች የዳኝነት ሥልጣን የሕዝብ ሥልጣን ነው ስለዚህ ፍቤቶችና ዳኞች ለሚያከናውኑት ሥራ ሁሉ ለሕዝብ ተጠያቂነት አለባቸው ሕዝቡ የሉአላዊነት ሥልጣኑን ተግባራዊ ከሚያደርግበት መንገድ አንዱ በተወካዮች አማካኝነት ነው የፍቤቶችና የዳኞች የሕዝብ ተጠያቂነት የሚረጋገጠው በሕግ አውጪው በኩል ነው ስለዚህ ፍቤቶችና ዳኞች ለሕግ አውጪው በቀጥታ ተጠያቂነት አለባቸው ይህም ፍቤቶችና ዳኞች ለሕግ አውጪው ያለባቸው ተጠያቂነት በተለያየ መንገድ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል አንደኛው ሹመትና ከሥራ መሰናበት ነው በክፍል አንድ እንደተጠቀሰው የፌዴራል ፍቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት በፌዴራል መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስቴር አቅራቢነት በተወካዮች ምክር ቤት የሚሾሙ ሲሆን የክልል ጠቅላይ ፍቤቶች ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት በክልል ርዕስ መስተዳድር አቅራቢያነት በክልሉ ምክር ቤት ይሾማሉ ከሥራ መሰናበትም ከዚሁ አንፃር የሚታይ ነው ይህ የፌዴራልና የክልል ጠቅላይ ፍቤቶች ፕሬዜዳንቶችና ምክትል ፕሬዜዳንት ለሕግ አውጪው ተጠያቂ መሆናቸውን የሚያመላክት ነው የሌሎች የፌዴራልና የክልል ፍቤቶች ዳኞች ሹመትና ከሥራ መሰናበት ሂደት የሚያመላክተው እያንዳንዱ የፌዴራል ፍቤት ዳኛ ለተወካዮች ምክር ቤት የክልል ፍቤት ዳኛ ደግሞ ለክልሉ ምክር ቤት ተጠያቂነት አንዳለበት የሚያረጋግጥ ነው ስለዚህ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ፍቤት ዳኞችን ሥነምግባር የክልል ምክር ቤቶች ደግሞ የየክልሎቻቸውን ዳኞች ሥነ ምግባር ይቆቀጣጠራሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ፕሬዚዳንት ለተወካዮች ምክር ቤት የክልል ጠቅላይ ፍቤት ፕሬዚዳንቶች ደግሞ ለየክልል ምክር ቤቶቻቸው የፍቤቶችን ሥራ ክንውን ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ አለባቸው በሚቀርበው ሪፖርት በመንተራስ ሕግ አውጪው አካል የፍቤቶችን ሥራ እንቅስቃሴ ይገመግማል አስፈላጊው አርምትና እርምጃዎችን ይወስዳል ወይም እንዲወስድ ያደርጋል ይሄ ሌላው የፍቤቶችን ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የተዘረጋ ሥርዓት ነው የፍቤቶች በጀት የሚያፀድቀው በሕግ አውጪው አካል ነው ይህ ደግሞ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ፍቤት የክልል ምክር ቤቶች ደግሞ የየክልሎቻቸው ፍቤቶች በዕቅዳቻው መሠረት ማከናወናቸውን ለመቆጣጠር ዕድል ይሰጣቸዋል ይሄ ፍቤቶች ለሕግ አውጪው ያለባቸው ተጠያቂነት ተግባራዊ የሚሆንበት ሌላው መንገድ ነው ሌላው የፍቤቶችና የዳኞች ተጠያቂነት ተግባራዊ የሚሆንበት ዘዴ ሕገ አውጪው ሕግ ማውጣት ሥልጣን ጋር የተያያዘ ነው በዚህ ረገድ ሕግ አውጪው አካል የፍቤቶችን ሥልጣን የሚመሰከቱ ሕጎችን በመሻር ወይም በመቀየር የፍቤቶችን የሥራ እንቅስቃሴ ሊቆጣጠር ይችላል የወንጀል ተጠያቂነት የዳኝነት ነጻነት ዳኞችን ከወንጀል ሐላፊነት ነጻ አያደርጋቸውም አንድ ዳኛ የወንጀል ሕግን ተላልፎ ከተገኘ እንደ ማንኛውም ሰው በወንጀል ይከሰሳል ጥፋተኛ ሆኖ ሲገኝም ተገቢው ቅጣት ይቀጣል በወንጀል ሕግ መሠረት ዳኞች የመንግሥት ሠራተኞች በመሆናቸው የወንጀል ሕግ አንቀጽ ዐ እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች በእነሱ ላይ ተፈፃሚነት አሏቸው ዳኞች በሕግ አክባሪነታቸው በሕብረተሰቡ ውስጥ አሪያ መሆን ይጠበቅባቸዋል ዳኞች ሥልጣናቸውን አለአግባብ መጠቀም የለባቸውም ዳኞች የሕዝብ አገልጋይ እንጂ ተገልጋዮች አይደሉም የዳኝነት ሥልጣንን ሕዝቡን ለማገልገል መጠቀም አለባቸው እንጂ ለግል ፍላጐትና ጥቅም ማራመጃ መጠቀም የሌለባቸው መሆኑን ላአፍታ እንኳን መዘንጋት የለባቸውም የፄን በመዘንጋት ፍትህን በጥቅማ ጥቅም በመሸጥና በመለወጥ የዳኝነትን ሥራ ክብር የሚያዋርዱ ዳኞች ከሥራ መሰናበት ብቻ ሳይሆን በሕጉ አግባብ በወንጀል ሊጠየቁ ይገባል በፌዴራልና በክልል ለምሳሌ በኦሮሚያ ጉቦ ሲቀበሉ እጂ ከፍንጁ ተይዘው በወንጀል ተከሰው የተፈረደባቸው ዳኞች አሉ የሔም ዳኞችን የሕግ ተጠያቂነት ያለባቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው የዲሲፕሊን ተጠያቂነት ከሕግ ውጪ የሚሰሩ ዳኞችን ለመቆጣጠርና ለመከታተል የዲሲፕሊን ተጠያቂነት አይነተኛ መሣሪያ ነው በክፍል አንድ እንደተመለከተው በዳኞች ላይ የሚወሰድ የዲሲፕሊን እርምጃ በሥነምግባር ደንብ ወይም በፍቤቶች በዳበሩ ደንቦች ላይ መመሥረት እንዳለበት የዳኝነት ነፃነት መርህ አጥብቆ ይጠይቃል አንድ ዳኛ የዳኝነት ሙያ የሚጠይቀውን ሥነምግባር ካላሟላ የተጠያቂነት መርህ የዲሲፕሊን እርምጃ እንዲወሰድበት ወይም ከሥራው እንዲወገድ ይጠይቃል። የዳኝነት ግልፅነት ግልፅነት የተጠያቂነት መርህ አንድ መግለጫ በመሆኑ ብዙን ጊዜ ከተጠያቂነት መርህ ጋር የሚፄድ ሌላው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሠረታዊ መርህ ነው ቀደም ሲል ከዳኝነት ተጠያቂነት ጋር በማያያዝ ለመጥቀስ እንደተሞከረው የፍቤቶች ሥልጣን ሆነ በፍቤቶች ውስጥ ተመድበው የሚሰሩ ዳኞች ሥልጣን ምንጭ ሕዝቡ በመሆኑ ሕዝቡ ፍቤቶችና ዳኞች የሚጠበቅባቸውን ተግባር እያከናወኑ መሆን አለመሆናቸውን የማረጋገጥ የመቆጣጠር መብት አለው ሕዝቡ በፍቤቶች የሚከናወኑትን ተግባሮች በዳኞች የሚሰጡትን ትዕዛዞችና ውሳኔዎች በማወቅ እያንዳንዱ ዳኛ ይህጉን በትክክል እየተረጎመ መሆን አለመሆኑን ሥራውን በቅልጥፍና አየፈፀመ መሆን አለመሆኑን ማየት መታዘብና ማጋገጥ እንዲችል ፍቤቶችና ዳኞች ሥራዎቻቸውን የግልፅነት መርህን መሰረት አድርገው ማከናወን ሲችሉ ብቻ ነው የግልፅነት መርህ በፍቤቶች በተለያየ መንገድ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል አንደኛውና ዋነኛው ግልፅ ችሎት ነው በፌዴራልና በክልል ፍቤቶች ማቋቋሚያ አዎጆች ውስጥ በሕግ በሌላ አኳኋን ካልተደነገገ በስተቀር ፍቤቶች በግልፅ ችሉት እንዲያስችሉ በፌዴራልና በክልል ፍቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ተደንግጓል ለምሳሌ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፍቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ እና የፌዴራል ፍቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መጥቀስ ይችላል ይህ ፍቤቶች ሥራዎቻቸውን በግልፅነት መርህ መሰረት እንዲፈፅሙ ለማድረግ የተደነገገ ነው ፍቤቶች በግልጽ ችሎት እንዲያስችሉ ማድረግ የህብረተሰቡ ክፍል በዳኞች የሚሰጡትን ውሳኔዎች ትዕዛዞች በሕጉ መሰረት መሆን አለመሆኑን የራሱን ግንዛቤ አንዲኖረው ያደርጋል ግልፅ ችሎት ለፕሬስም ክፍት ስለሚሆን ሕዝቡ የተሟላ መረጃ እንዲኖረው ያደርጋል በተጨማሪም የፍትህ ጥራትና የዳኞች ተጠያቂነትና ከማረጋገጥ አኳያ ግልፅ ችሎት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው የተመቻቸ ሁኔታ እስካለ ድረስ ማንኛውም ዳኛ የዳኝነት ተግባሩን በግልፅ ችሎት የማስቻል ግዴታ አለበት ግልጽነት ማንኛውም ዳኛ ፊን ሊመራበት ከሚገባው የሥነምግባር መርሆች ውስጥ አንዱ መሆኑ በፌዴራልና በክልል ዳኞች የሥነምግባር ደንብ ውስጥ በግልጽ ተደንግጓል ለምሳሌ የፌዴራል ፍቤቶች ዳኞች ሥነምግባር ደንብ አንቀጽ አና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ፍቤቶች የዳኞች ሥነምግባርና የዲስፐሊን ደንብ አንገጽ መጥቀስ ይቻላል ይሔን መርህ ተግባራዊ አለማድረግም የዲሲፕሊን ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል በግልጽ ተመልክቷል ስለዚህ ፍቤቶች በሕግ በተወሰነው መሠረት ስራዎቻቸውን ለሕዝብ ግልጽ በሆነ አካኋን ማከናወን ይኖርባቸዋል ሌላው የግልፅነት መርህ በፍቤቶች ተግባራዊ የሚሆንበት መንገድ የዳኞች ውሳኔዎች ለሕዝቡ እንዲደርሱ በማድረግ ነው የዳኞችን ውሳኔ ለሕዝቡ በተለያዩ መንገድ እንዲደርሱ ማድረግ ይችትላሉ የመወያያ ጥያቄዎች የፍትህ ጥራትና የዳኞች ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አኳያ የዳኝነት ሥራ በግልፅ ችሎት እንዲከናወን ማድረግ ያለው ሚና እንዴት ይገለፃል።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

تعليقات:


memezon

خيارات التنزيل | تحويل إلى قوات الدفاع الشعبي | كتاب اليوم

© dirzon | شروط الخدمة | خصوصية | حول | خدمات | اتصال