Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የደቂቀ እስጢፋኖስ ትምህርትና የአባ እስጢፋኖስ ገድል ጦጵያ ላይ ዓሥር ሞቱ ከዚህ በኋላ ጥቂት አረፉ ንጉጮ ደግሞ ጠራቸው ከወንድሞቹ ጋራ ከፊቱ ቆመ ሰላም ላንተ ይሁን ቢለው ሰላምታህን አልፈልግም ካንተ ጋራ ወዳጅነት የለኝም የሚል መልስ ሰጠው ሞገሳዊው አቡነ ዕዝራን በጥድፊያ አውጥተው ከአንድ ወንድም ጋራ ከምድረ በዳ ደበቁት ሲመለስ የከስዋን ቤተ ክርስቲያንን አቃጥለዋት ኖሮ ቃጠሎውን አየና አለቀሰላት ወንድሞችን ነቢዩ በጽዮን ቃጠሎዋ ላይ መኖር ይሻለናል ብሏልና አትፍሩ አላቸው ወንድሞች እግዚአብሔር ይረዳናል አሉት ደግሞ ሰይጣን ደስ እንዳይለው ተነሥ እንሥራት አላቸው ሠሯት እንደበፊቱ አደሷት በጠና በሽታ ላይ እዚያ ወንድሞችን ለነፍስና ለሥጋ በሚጠቅም በምዕዳንና ተግሣጽ እያጽናናቸው ኖረ ከዚያ በኋላ ዕረፍቱን እንዲያረዱ ወንድሞች ወደ ከስዋ ሳሙነገሥ ግዕዙ የሚለው ብእሴ እግዚአብሔር የግዚአብሔር ሰው ወይም አቡነ ይሥሐቅን ይሆናል ፎዉ ህበሃ ህህ ሀ።
አፄ ዘርአ ያዕቆብ አባ እስጢፋኖስን እስጢፋ ተከታዮቻቸውን ደቂቀ እስጢፋ የእስጢፋ ልጆች ነበር የሚላቸው አባ እስጢፋኖስን ለምን እስጢፋ እንደሚላቸው አልነገረንም ግን ንጉሥ የሽሙጥ ስም ማውጣት ይችልበት ነበረ ደቂቀ እስጢፋኖስ ሽሙጡ እንደገባቸው ከሆነ እስጢፋ በግብጽ ቋንቋ የሰይጣን ስም ስለሆነ የእግዚአብሔርን ቤት አስተዳዳሪ ሰይጣን እኛን ልጆቹን የሰይጣን ልጆች ለማለት ነው ይላሉ እነሱም አጻፋውን ሲሰጡት ድብ ፀር ጅብ ጠላትአያ ጂቦ ዝራጉን ድራጎን ይሉት ነበር የሃይማኖት ውዝግብ የዘመኑ ዋና ዋና አከራካሪ ጥያቄዎች ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ ስለ ሰንበት አከባበር ስለ ቤተ ክርስቲያን የሕግ መጻሕፍት ሞጐጥር ቅድስት ድንግል ማርያምን የቅዱሳንት ሥዕልን መስቀልን ስለማክበር ስለ ክርስቶስ ሁለተኛ መምጣትና ከጻድቃኑ ጋራ አንድ ሺህ ዓመት ስለ መንገሥ ማለት ስለ ደብረ ዮን ወይም ስለ ስምንተኛው ሺህ ነበረ ፎርቪቪርከርክ ር ኽፎህ ዐክቪህሃር ከፀ ዥዐኳከ ከ ርቪኪር ከ ሾዐህቨርርበከ ከ ቢርርከከ ርክር ርህፖርያ ህ ኮሀ ለምሳሌ ዘሚካኤልና ገማልያል የሚባሉ ሁለት ሊቃውንት አልቦቱ መልክዐ ለእግዚአብሔር ከመ መልክዐ ሰብእ እግዚአብሔር የሰውን መልክ የሚመስል መልክ የለውም በማለታቸው ንጉሥ ተቆጥቶ ሊከራከራቸውና ሊረታቸው የሊቃውንት ጉባኤ ሰብስቦ ነበረ የዘመኑ ታላላቅ ሰዎች እነማን እንደነበሩ በከፊልም ቢሆን ለማወቅ የቻልነው ንጉሥ በጉባኤው ላይ የነበሩትን ሰዎች የስም ዝርዝር ስለመዘገበልን ነው ርክርከሮሄ ፐከፀ ነ ዐ ከ ከህ ከከ ከፀ ክህከ ፖር ሃ ዐዐ ሄድሐ ያው ወዳግመጮሯ ጀእብ ሸ አዚህም ገጽ እና እ ህበሃ ህህ ሀ መግቢያ አሁን ገድሎቻቸውን ወደ አማርኛ ተርጉሜ እዚህ ያቀረብኩት አባ እስጢፋኖስና ተከታዮቻቸው ከአፄ ዘርአ ያዕቆብ ጋራ የሚያጣላቸው ጉዳይ ንጉሥ እንደሚለው ከሆነ ለመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያምና ለክቡር መስቀል ስለማይሰግዱ ነው እነሱ የሚሉት ደግሞ ይሄ ሰበብ ነው የሚያሳድዳቸው ለሱ ስላልሰገዱለት ነው አባ እስጢፋኖስና ተከታዮቻቸው ስግደትን ከአምልኮት ጋራ ስላያያዙት ከሰው ጋራ ሰላምታ ሲሰጣጡ እንኳን አንገታቸውን ሰበር አያደርጉም ሰነዶቻቸው እንደሚመሰክሩት ስግደት ለእግዚአብሔር ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ በቀር ለሌላ አይገባም ይላሉ ንጉሥን ከችሎቱ ለጉባኤ የተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉም ራሳቸውን ዝቅ በማድረግ ምናልባትም ከመሬት ሳላይ በመውደቅ ሰላምታ ሲሰጡት እነአባ እስጢፋኖስ ከፊቱ እንደ ጂብራ ተገትረው ይቀራሉ ለምን አታጎነብሱም ሲላቸው ለሰው መስገድ አይገባም ለሰው መስገድ አምልኮ ባዕድ አምላክ ያልሆነን ማምለክ ነው ይገባል ካልክ ሕግ ይዳኘን ብለው ምንም ነገር ሳይፈሩ በሕግ ቀጥ አድርገው ይከራከሩታል ጻድቆች ሳይቀሩ ለታላቅና ለባለሥልጣን ሰላምታ ሲሰጡ እንደሚያጎነብሱ እንደሚሰግዱ መጽሐፍ ሲጠቅስባቸው ለማስረጃነት ከነሱ ድክመት ይልቅ የማያልፈው የእግዚአብሔር ቃል ይበልጣል ከኔ በቀር ለሌላ ለማንም አትስገዱ ብሏል ይሉታል በእምነታቸው ሲጸኑበት አይቀጡ ቅጣት ይቀጣቸዋል ሕግ የሚሉት በብሉይና በሐዲስ ውስጥ ያሉትን የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትና በመጽኃሪፊ ፈኖዶፅዕና ያዕመጽኃፊ ዲድዕዎልያ ውስጥ የተደነገገውን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ነው ይኸም ሆኖ የነሱ ምንጮች ናቸው እንጂ ዘርአ ያዕቆብ በተወልን ሰነዶች ውስጥ ስላልሰገዱልኝ ተጣላኋቸው ሲል አላገኘሁም እንዲህ ብሎ ይጽፋል ተብሎም አይገመትም አይጠበቅምም ለንጉሠ ላለመስገድ የሰጡት ምክንያት በቂ ቢመስልም ጦሩ እየተሰበቀ ሰይፉ እያውለበለበ ፊት ለፊት ሲመጣባቸው ለንጉሥ አንገትን ሰበር አድርጎ እጅ መንሣት አምልኮ አይደለም ብለው ማምለጥ ሲችሉ እስከመጨረሻው እንዲጨክኑ ትልቅ ተጽዕኖ ያደረገባቸው አንድ ከመጽሐፈ መነኮሳት ያገኙት ታሪክ ይመስለኛል ታሪኩ እንዲህ ይላል ደግሞ ያ ወንድም አባ ቆረኒስ ከአስቄጥስ የወጣሁ ጊዜ ያለኝን ነገረኝ የግብጽን ምድረ በዳ አልፌ እዚያ ትንሽ ሰሌን ስጐነጉን ብዙ እርኩስ መንፈሶች በጣም በሚያስፈራ ግርማ ሆነው ወታደሮች መስለው ሦሠሪምሪ ማረዖያፖም ገጽ በእጅ የተቀዳ መጽኃፈ ሷኖፎዶዕ በታላላቅ ቤተ ክርስቲያኖችና በውጪ አገርም በአንዳንድ የምርምር ቤተ መጻሕፍት ይገኛል ግን ስላልታተመ ሁሉም በቀላሉ አግኝቶ የሚጠቅሰውን አንድ ምንጭ መጥቀስ አልተቻለም ነርር ልበ ዐፀርዘዐ ዐዘዐናርዕዐ ርዐ ሂ ዐ እ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ መጡ ከነዚያ መንፈሶች ውስጥ ጥቂቶቹ ወደኔ ወደ ውስጥ ገቡና ተነሥ ውጣ ንጉሥጮ ጠርቶሃል አሉኝ አልወጣም አልኳቸው የምጐነጉነውን ከእጄ ነጠቁኝና ና ተነሥ ንጉሥ ጠርቶሃል ስንልህ ቁጭ ብለህ ትጐጉነጉናለህ። ያልተለመዱ የአንድ አካባቢ ቃላትንም ለምሳሌ የፍራፍሬዎችን ስም ሲሰጡን በትክክል ለመስጠታቸው ማስረጃ የለንም ሌላው ስሕተት ሰዋስዋዊ ነው ሄሮድ ያው ወዳንው ውስጥ ብዙ ጊዜ አንድና ብዙ ወንድና ሴት ሩቅና ቅርብ ይምታታሉ ለምሳሌ ወይራራ የምትባለዋን አንስታይ ፆታ ወንዝ ወታደሮቹ ሞልታ አገኗት ለማለት ወረከብዋ ምልእተ ወይም ወረከብዋ በዘመልአት በማለት ፈንታ ወረከብዎሙ በዘመልአ ሞልቶ አገኗቸው ይላል እንደዚህ ያለ ስሕተት በአማርኛና በትግርኛ ተናጋሪዎች ዘንድ ይኸንን ያህል የተለመደ አይደለም በትግሬዎች ዘንድ የተለመደ ስሕተት እሙንቱ በማለት ፈንታ እምንቱ ማለት ነው ይኸም በድ ለያው ወንው በብዙ ይታያል ማንም የሚያደርገው ስሕተት ዘርፍና ተዛራፊን ማማታት ነው ይህም በሄድቋ ዳያዕው ወጳግው አልፎ አልፎ ይታያል ለምሳሌ በወንዚ ውሐ ለማለት በማየ ፈለጋ በማለት ፈንታ በፈለገ ማያ በውሐዋ ወንዝ ሲል ይገኛል የድሐ ያው ወጳንው ጸሐፊዎች ትግሬ ወይም አማራ ብቻ ላለመሆናቸው ማስረጃው ግዕዙ ብቻ ሳይሆን ገለጻውም ምልክት አለበት ከዚያ ይኸ ተንኮለኛ ዘርአ ያዕቆብ ቅዱሳኑ ደቂቀ እስጢፋኖስ በምድሩ እንዳይኖሩ ባጠበበባቸው ጊዜ እስከ ብሔሩ ዳርቻ ነዋሪዎቹ ቤታቸው ከዛፍ ላይ ከሆነው እስከ ምድረ ፀጋም ግራ ምድር ደረሱ የዚህ አገር ሰዎች አገርና አገር የቅርብና የቅርብ መዋጋት ልማዳቸው ነው አንዳንዶቹ ምድር ቆፍረው ለሰው ለከብት ለንብረት መኖሪያ ዋሻ ያበጁና ከዋሻው በላይ ቤታቸውን ይሠራሉ ጦርነት ሲያይልባቸው በየሽንቁሮቹ ይገባሉ ወደ ክርስቲያኑ ምድር ሲዘምቱ ወንድ ወንዱን ይገድላሉ የዓመት የመንፈቅ ሕፃን እንኳን አይተዉም መነኩሴም ካህንም አይምሩም ቤተ ክርስቲያናቸውን ይመዘብሩታል ሴቶቻቸውንና ንብረታቸውን ሁሉ ይማርኩና ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ ከነሱ ውስጥ አንድ ሰው የሰው ግድያውን ከዓሥር ካደረሰ አንገቱና እጆቹ ላይ ቀይ ፈትል ያስራል የደም ምልክት ነው በሌላ ላይ ይኸንን ሲሠሩ ቅዱሳኑን ተቀበሏቸው የሚገባውን ደግ ሥራ ሁሉ ሠሩላቸው ከሀገራችን ኑሩ አሏቸው እግዚአብሔር ለቅዱሳኑ እስከ ጊዜው ዕረፍት ስለሰጣቸው አመሰገኑት እዚያ ኖሩ ከተበተኑበትም ተሰባሰቡ ከዚያ ሀገር ሰዎች ከወንዱም ከሴቱም ብዙዎችን ወደ ትምህርታቸው መለሱ ከዓለም ወጥተው መንኩሰው ሰማዕት እስከ መሆን ደረሱ እግዚአብሔር ያንን ሀገር ለቅዱሳኑ በሚፈልጉት ሁሉ ከፍቶላቸው ቤተ ክርስቲያን እስከ መትከል ደረሱ የወንድሞቻቸውንም ተዝካር አወጡ መቸም ሁሉም በሰማዕት አያልቁም ይኸንን ጽሑፍ ያቆዩልን ከነሱ ውስጥ የተረፉት የትግራይና እነዚህ የግራ ምድር ሰዎች ይመስሉኛል እ ህበሃ ህህ ሀ መግቢያ የመተርጐም ችግር ከዘመን ብዛት የተነሣ አማርኛ ከግዕዙ እየራቀ በመሄዱ ይሁን ወይም ከላይ በተቸሁት ምክንያት ወይም በሌላ ግል ባልሆነልኝ ምክንያት ገድሎቹን ከግዕዝ ወደ አማርኛ ቃል በቃል ስተረጐጉማቸው አንዳንድ ቦታ ላይ ሐሳቡ ግልጽ ሳይሆን ይቀራል እንደዚህ ሲሆንብኝ እንዳለ ጥዬው ከማለፍ በቅንፍ ውስጥ ማሟያ ቃላትና በግርጌ ኅዳግ ማብራሪያዎች ሰጥቻለሁ በጣም ጥቁት ጊዜ ደግሞ ግዕዙን የማይተረጐም መልእክቱን ግን የሚጠብቅ አማርኛ አምጥቻለሁ ቅንፎቹ አንባቢን እንደማያደናቅፉ ተስፋ አለኝ ዘዴው ያቀፏቸውን ቃላት እንጂ ቅንፎቹን እንዳላዩ እያዩ ማንበብ ነው ይኸም ሁሉ ሆኖ አንዳንድ ላቃናቸው ያልቻልኳቸው ዓረፍተ ነገሮች ቀርተውኛል ትርጉማቸው ከሚያስቸገሩ ቃላት ውስጥ ከዚህ ቀጥሎ ያሉት ይገኙባቸዋል ሀዢ ምድር ብሔር ምንጮቹ አንድን ቦታ ሀገር ወይም ምድር ወይም ብሔር ሲሉት የቦታውን ሁኔታ ማለት ጥበት ስፋቱን ወይም የሰዉን ሰፈራ ስለማላውቀው እንዳለ ለመተው ሞክሬያለሁ ግን ያንኑ ቦታ አንድ ምንጭ ለምሳሌ ሀገር ሲለው ሌላው ብሔር ብሎት ይገኛል ሀገር በመሠረቱ ከተማ መንደር ሲሆን ክፍለ ሀገርንም ቀበሌን ወረዳን አውራጃን ጠቅላላውን ሀገርም ሀገር ብለውት ይገኛል ስለዚህ እነዚህ ቃላት የሚያመለክቱትን ቦታ በአጠራሩ ሁኔታውን ማወቅ የሚቻል አይመስለኝም ብሔር ትርጉሙ ሀገር ሲሆን በብዙ ጥር በሐውርት ሲል ሕዝቦች ማለትም ይሆናል ምድር ብቻ ነው ሕዝብን የማያመለክት መካን ካ ሳይጠብቅ የመካን ጥሬ ትርጐሙ ቦታ ነው በተጨማሪ ዛሬ ማእከል የምንለው እንደ ገዳም ያለ የትምህርትና የሃይማኖት ቦታ ለምሳሌ መካነ ሥላሴ የንጉሥ እና የጳጳስ ግቢ ሁሉ መካን ይባላሉ መኩንንመኮንን ቃሉ የተገኘው ኩነነኮነነ ከሚለው የግዕዝ ግስ ሲሆን ትርጉሙ አንደኛ ፈረደ ዳኘ እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ ማቴ ሁለተኛ አገር ገዛ አገር አስተዳደረ ነው መኩንን መኮንን ማለት ዳኛ ፈራጅ ገዢአስተዳዳሪ ማለት ነው እዚህ መጽሐፍ ውስጥ የተረጎምኩት ሀአገረ ገዢ እያልኩ ነው መኩንን የሚሉት የጠቅላይ ግዛትየአውራጃ አስተዳዳሪውን ነው ለምሳሌ መኩንነ ትግራይ መኩንነ ፈጸጋር ይላል የወረዳ ገዢዎችን ስዩም ነው የሚሜሏቸው ይኸንን ሹም እያልኩ ተርጉሜዋለሁ ማኅበር ማኅበር የሚሉት የአንዱን ገዳም መነኮሳት ነው በእንግሊዝኛ ኮሚዩኒቲ የሚባለው ነው ማኅደር ቃሉ ኀደረ አደረ ከሚለው ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙ መኖሪያ ማለት ነው መነኮሳቱ የግል መኖሪያቸውን በአትም ሆነ ጾማእት ወይም በገዳሙ ውስጥ ያለውን የግል መኖሪያ ማኅደር ይሉታል እ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ምሥዋዕ ሠውዐ ሠዋ ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙ መሠዊያ ማለት ነው በብሉይ ዘመን እንስሳት ይሠዉበት የነበረው ነው በሐዲስ በክርስትና ዘመን በእንስሳቱ ቦታ ርባን ሥጋ ክርስቶስ ተተክቷል ሠራዊት የዚህ ቃል ጥሬ ትርጉም ሕዝብ ነው የወታደርን ሕዝብ ብቻ የሚያመለክት አይደለም በአማርኛም ቢሆን ባለመሣሪያውን ሠራዊት የጦር በሚል ቃል ካላብራራነው ብቻውን ባለመሣሪያ ወታደርን አያመለክትም የጦር ሠራዊት ማለት ይኖርብናል መሣሪያው ጦር መሆኑ ስለቀረ ጦርነት የጦር ሠራዊት የሚሉት ቃላት ሁሉ አርጅተዋል እንግዲህ ምንጮቹ ሠራዊት ሲሉ ወይ ሕዝብ ወይም የጦር ሠራዊት ማለታቸው ሊሆን ይችላል ስብሐት እና አኩቴት እነዚህ ሁለት ቃላት ምስጋና በሚለው ትርጉጐማቸው ሲመሳሰኩ ስብሐት ከምስጋና ጨመር ያደርጋል ክብርን ከፍ ከፍ ማድረግን ይጨምራል ስለዚህ አኩቴትን እየተረጐምኩ ስብሐትን እንዳለ ትቸዋለሁ በአት እና ጾማእት እነዚህ ሁለት ቃላት ተመሳሳይነት አላቸው ባሕታውያን የሚሜደበቁባት ዋሻ ጉሮኖ ሲሆኑ ካስፈለገ ጓዳ እና ጎጆም በበአትነት እና ጾማእትነት ያገለግላሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ አባ ጳንጠሌዎን ዘጾማእት ይባላሉ ከዋሻቸው አይወጡም ነበር ንጉሥ ካሌብ ወደ ብሔረ ሳባ ሲዘምት እዚያው እዋሻቸው ውስጥ ሆነው ነው የጸለዩለትና የባረኩት ተግሣጽ እና ምዕዳን እነዚህ ሁለት ቃሳት ተፈራራቂዎች ሲሆኑ ትርጐማቸው ምክር መጽናኛ ትምህርት ስብከት ማለት ነው እንዳሉ የተውኳቸው ምናልባት ለኔ ያልታየኝ ልዩነት ሊኖርባቸው ይችላል ብዬ በማሰብ ነው ነጋዲ ጋ ሳይጠብቅ የተቀደሰ ቦታ ጎብኝቶ ለመጽደቅ ወይም ሸቀጥ ካንዱ አገር ወዳንዱ አገር እየወሰደ ለመሸጥ የሚጓዝ ማለት ነው ነጋዴ ጋ ጠብቆ የሚለው ቃል ከዚህ ጋራ ግንኙነት አለው የተቀደሰ ቦታ ጎብኝቶ ለመጽደቅ የሚጓዘውን ዐረቦች ሓጅ እንግሊዞች ፒልግሪም ይሉታል አረሚ የአረሚ ዋና ትርጉሙ አረመኔ የሚተዳደርበት የሃይማኖት ሕግ የሌለው ማለት ነው ምንጮቹ ግን እስላሞቹንም አረሚ ይሏቸዋል ዓረቦች ካፊር እንደሚሉት ነው አቡን በአሁኑ ጊዜ ይህ ቅጽል የሚሰጠው ለጳጳስ ብቻ ነው ቀደም ብሎ ግን የመነኮሳት በተለየም የጻድቃን መነኮሳት መጠሪያ ነበረ ለምሳሌ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ጳጳሳት አልነበሩም ደቂቀ እስጢፋኖስም አባቶቻቸውን አቡነ እገሌ የሚሉት ይኸንኑ ልማድ ተከትለው ነው እንጂ ጳጳሶች ስለሆኑ አይደለም ጳጳሶች አልነበሩም ቃሉ ምናልባት ታሪክ ሳይኖረው አይቀርም ግብጾች መነኩሴን አቡነ እገሌ ጳጳስን አንባ እገሌ ነው የሚሉት። በእውነት ፍርድ ከሆነ የኔን አነጋገርና የነሱን አነጋገር መርምር በነሱ አነጋገር ብቻ የምትፈርድ ከሆነ ግን እነሆ ግፌ ካንተም ጭምር ነው ቅዱሱ እንደዚህ ሲለው አበምኔቱ በጣም ተቆጣ ቅዱሱን እነሆ አጋንንት አድረውብሃል ነገርህ ከሰይጣን ኃይል የመጣ ነው አለው ቅዱሱ ስድቡን ሰምቶ ለእግዚአብሔር ሶስት ጊዜ ሰገደ አበምኔቱ ቅዱሱን በተጨማሪም እንዲህ አለው ካሁን ጀምሮ በወንድሞች ማኅበር ማቴ አባ እስጢፋኖስ የቤተ ክርስቲያን ትምህርታቸውን ያገኙት ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ መሆኑን ለማሳየት የገባ አጻጻፍ ነው ወደ ብቃት ዓለም መሸጋገሪያው የሚመሰለው በመርከብ ጉዞ ነው ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል ስብሰባ እንጂ ተለይተህ በማደሪያህ አትቀመጥ ቅዱሱ እሺ አለው ከዚያ ቅዱሱ ወደ ማኅበራቸው እየሄደ ለአስኬማው ትሕርምት የሚገባውን ምግቡን አንድ ጊዜ ብቻ ይቀበል ጀመር በዚህ ሁኔታ ግማሽ ዓመት አሳለፈ ከዚያ አበምኔቱ ቁጣው ሲበርድለት ቅዱሱን ወደ ቤቱ ሰደደው ቅዱሱ የግፉን ትእዛዝ ፈጽሞ ከአንድ ወንድም ጋራ ወደ አንዲት ኮረብታ ሄደ እዚያ በብቸኝነት ኖረ ከዚያ ለቅዱሱ አንድ ራእይ ታየው ትልቅ ባሕር በፊቱ ተንጣልሏል ብዙ መነኮሳት ባሕሩን ሲያዩ እንደ አንበጣ ክንፋቸውን እየዘረጉ ተወረወሩበት። እንደዚሁ አንተም የሰውን ስድብ አትፍራ ቅዱሱ አባቴ እየዞርኩ እንዳስተምር አታስገድደኝ ግን ወደኔ ለመጣ እናገራለሁ ጳጳሱም የእግዚአብሔር መንፈስ በላይህ ስሳለ በል እንዳልከው አድርግ አለው ከዚያ በኋላ የቅስና ሹመት ሰጠው ቅዱሱ በዚያን ጊዜ እድሜው ቋወ ዓመት ሆኖት ነበረ ከዚያ ቅዱሱ ለሚከሱት ምስክር ትሆነው ዘንድ የሃይማኖት ጦማር በጳጳሱ ፊት ጽፎ በጳጳሱ ተባርኮ ወደ መኖሪያው በሰላም ተመለሰ ከምኩራብ በፊት ማለት ከአይሁድ ሃይማኖት በፊት ማለት ነው ዓለም መታደስ የሚለው በክርስቶስ ሰው መሆንና በሞቱም የተጀመረውን የሐዲስ ኪዳንን የዓመተ ምሕረትን ሕይወት ነው በሔዋን ምክንያት የገነት በር ተዘጋ በድንግል ማርያም ምክንያት ደግሞ እንደገና ተከፈተልን ያለውን የኀሙስ ውዳሴ ማርያም ያስታውሰናል በዚህ አንቀጽ ውስጥ የዘመኑን የሀገራችንን ሊቃውንት ያነታርኩ የነበሩ ሁለት የሃይማኖት ጥያቄዎች ተመልሰዋል አንዱ ስለ ሥላሴ ትርጉም ሌላው ስለ ሰንበት በዓልነት ናቸው ሰንበት የሚሉት ቅዳሜን ነው በአፄ ዘርአ ያዕቆብ ዘመን ከብዙ ውዝግብ በኋላ ቅዳሜ እንደ እሑድ በዓል እንዲሆን ተወሰነ ክበርርከአ ሃር ሀዘዐ ዐርሀጀ ሪርፎና ሀዕህሪሆና ዐሮ ከቪደቪ ነ በሺ ኮርፀጸከ ገፎበ ላኩሃኗ እሸከዐከሃ ከ ሃ ርከርከፀጽ ፕከ ሾርጧአበ ህ ከከከ ዐ ከ ከ ከህርከ ዐ አባ እስጢፋኖስና ተከታዮቻቸው ይከሰሱባቸው ከነበሩት ጉዳዮች አንዱ ምሥጢረ ሥላሴን የአምላክን አንድነትና ሶስትነት ትርጉሙን አያውቁትም የሚል ነበር ራእ ቀጂው ሰዋስው አሳስቷል ግዕዙ የሚለው መጽሐፈ ሃይማኖት ነው ማንኛውም የተጻፈ ነገር በግዕዝ መጽሐፍ ይባላል ይኽም መጽሐፍ ብቻ ሳይሆን ደብዳቤንና ማንኛውንም ሰነድ ይጨምራል እዚህ ላይ መጽሐፍ የሚለውን ግዕዝ ጦማር ብዬ የተረጐምኩት ጦማር በመንፈሱ ከተራ ደብዳቤ ትንሽ ክብደት ያለው ደብዳቤ ስለሆነ ነው ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል የመጀመሪያው ስደት ቅዱሱ ወደሱ የሚመጡትን በመጻሕፍት ሕግ እንዲቆሙ አስተማራቸው የሰባልዮስን ስሕተት ከልባቸው ለማስወገድ ወለል ባለች በሥላሴ እምነትንም አስተማራቸው ደግሞ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ የጠበቁና ዓለምን ያሸነፉ ለቅዱሳን ከተሰጣቸው የጸጋ ሀብት ከሞትና ከትንሣኤ ሥጋ በፊት አሁን በሥጋ እያሉ በትንሣኤ ነፍስ ለመቀበል እንደሚበቁ አስረዳቸው ቃሉን የተቀበሉ ብዙዎች ሆኑ በቀኖናው ሥርዓት በሚያርፉበት ጊዜ የሰንበታትንና የበዓላትን ትምህርት ለመስማት ከቅዱሱ ማደሪያ ይሰበሰቡ ጀመር እየተማሩ በቃልም ሆነ በምግባር ከማወላወል ይጠበቁ ጀመር የደብሩ ሰዎች በቅዱሱና ከሱ በሚማሩት ላይ ተቆጡ ግን የሚያደርጉትን አጡ በአንዳች ነገር ላይ ሲከራከሩት እነሱው ተመልሰው ይረታሉ በዚያ ላይ ራሷ ትምህርቱ ሥራቸውን ነቃፊ ሆነች ከቅዱሱ የሚማሩትን ከዮርባንና ከገበታቸው ያገሏቸው ጀመር በሁሉም ስም የሚናገሩት ጠበቆቻቸው ተነሥተው ቅዱሱን እንዲህ ሲሉ በእግዚአብሔር ስም ተናገሩት ከደብራችን እንድትወጣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ይዘንሃል ቅዱሱ ከደብሩ ሰዎች የመጣበትን ስደት ሲሰማ አበምኔቱ ከነሱ ጋራ ተስማምቶ እንደሆነ ወይም ይፈርድለት እንደሆነ ሊጠይቀው ወደሱ ሄደ እሱም የማደሪያውን በር ዘግቶ እንዳይገባ ከለከለው ቅዱሱ ሁሉም በመባረሩ እንዳበሩ ሲያውቅ ማደሪያውን ትቶ ግፉን ተሸክሞ ተሰደደ ጓብዙዎች አብረውት ተሰደዱ በዚህኛው ስደቱ እስከ ጣና ባሕር ደረሰ በኋላ ተመልሶ ወገራ ላይ ተቀመጠ ከዚህ በኋላ ጥቂት ቆይቶ ያ ያባረረው አበምኔት እንዲህ ሲል ወደ ቅዱሱ ላከበት እርጅናዬን ይቅር በለው ባንተ ላይ ካደረግሁት ኃጢአቴ ጋራ እንድሞት አትተወኝ አሁንም ኃጢአቴን ይቅር ብለህ እንድትመጣ ይሁን ላገኝህ እፈልጋለሁና ሰባልዮስሰብልያኖስ በሶስተኛው ምእት ዓመት የኖረ የሎንያ ሊቢያ ኤሏስ ቆልስ ነበረ። አበምኔቱ ቅዱሱን እንዲህ አለው ያደረግንብህን ክፋት ሁሉ ይቅር በለን አሁንም በደብሩ ከኖርክ እግዚአብሔር ለሐዋርያት የሰጠውን የጸጋውን ዋጋ ይስጥህ ወደ ምድረ በዳ ከሄድክም በምድረ በዳ ለነበሩ ቅዱሳን የተሰጠውን ስጦታ እንደዚያ ይስጥህ በጀመርከው ሁሉ እግዚአብሔር አብሮህ ይሁን እስከመጨረሻው አሸናፊነትን ይስጥከክ ወደፈለክበት ሂድ ባደረስንብህ በደል አትቀየም ደራሲው መነኮሳት በማለት ፈንታ የደብሩ ሰዎች ማለቱ መልእክት ይኑረው አይኑረው ግልጽ አይደለም ምንኩስናቸውን ማቃለሉ ወይም ያልመነኮሱትን ለመጨመር ሊሆን ይችላል በምድረ በዳ የነበሩ ቅዱሳን የሚባሉት በእንግሊዝኛ ቪ ከ ይባላሉ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል ቅዱሱ ከኔ በኩል ክፉ ነገር አይመጣባችሁም ግን ይቅር እንዲላችሁ በእግዚአብሔር ዘንድ ንስሐ ግቡ አላቸው ሁለተኛ ስደትየደብረ ገርዜን መመሥረት ከዚያ ደብር ወጥቶ ከመጀመሪያው ጀምሮ በስደቶቹና በእስራቶቹ ከቅዱሱ ጋራ ተካፋይ ከነበረው ደቀመዝሙሩ ከገብረ ክርስቶስ ጋራ ከተከዜ ወንዝ አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ ሌሎች ወንድሞችም ያስተማራቸውን ውሳኔዎች እየጠበቁ በአቅራቢያው ተቀመጡ የእግዚአብሔርን በረከትና ሕይወት ካሁን እስከ ዘላለም እንድታገኙባት እግዚአብሔርን ስለሠራው ሁሉ ለመባረክ በሁሉም ነገር እንደዚህ ጸንታችሁ በደብረ ገርዜን ኑሩ አላቸው የዚያች አገር አካባቢ መምህራን የቅዱሱን ዜና ሲሰሙ በጣም ታወኩ ትምህርቱን ለማስቀረት ፈልገው ዶልተው ከሀገረ ገዢው ዘንድ ሁለት ጊዜ ጉባኤ አደረጉ ቅዱሱ የእግዚአብሔርን የትእዛዙን ቃል ለምስከራ እየጠራ በሕግ ሰይፍ ገጠማቸው የቅዱሱን ነገር ጠንካራነት በመፍራት የምንኩስናውን መጽሐፍ እንደማያውቁት ሆነው እስከ መካድ ደረሱ የቅዱሱን የትምህርቱን ዘር ጅ ሳይፈልጉ እየሰሙ ተሸክመው ወደየደብራቸው ተመለሱ ደቀ መዝሙሮቻቸው የቅዱሱን ስብከት ሰምተው እርስ በርሳቸው በሐሳብ እየተለያዩ በየአድባራቸው ንትርክ ተፈጠረ ደጎቻቸው እየተጨመቁ ወጥተው ስብከቱን እስኪቀበሉ ድረስ የቅዱሱ ትምህርት በውበቷ ተዘረጋች የብቸኝነቱን የብሕትውናውን ሥርዓት የጀመሩት አባታቸው አባ እንጦንስ ወይም እንጦንዮስ የሚባሉ የግብጽ ሰው እንደሆኑ ከላይ በኅዳግ ቀጥር እና ስር ተገልጧል የአበምኔቱ ምርቃት አባ እስጢፋኖስ የደረሱበትን ብቃት አለማወቃቸውን ያሳያልጹ በምድረ በዳ ለነበሩ ቅዱሳን የተሰጠው ስጦታ ብቃትና ራእይ ማየት ነው አባ እስጢፋኖስ ከዚያ ደረጃ እንደደረሱ ገድላቸው ይመሰክራል የአባ አበክረዙን ገድል እንደሚለው አባን የፈቷቸው ልጆቻቸው ከባለሥልጣኖቹ ዘንድ ተሯሩጠው ሹሙን እንደሚያመጡባቸው ስላወቁ ነው ስለ ደብረ ገርዜንና ስለ አቡነ ይሥሐቅ ኅዳግ ገጽ ን ተመልከት እዚህ ሳይ መምህራን የተባሉት የአድባራት አበምኔቶች ናቸው የምንኩስና መጽሐፍ ወይም መጽሐፈ መነኮሳት የሚባሉት አንደኛው በአክሱም ዘመነ መንግሥት የተተረጐመው የአባ ጳኩሚስ ሥርዓት ሥርዓት ዘአዘዞ መልአከ እግዚአብሔር ለአባ ጳኩሚስ የሚባለው ነው ዲልማን አሳትሞታል ለህፎ ከበከኪ ርዐዐዐ ሀዐርዐ ሌሎቹ ገነት ገነተ መነኮሳት እና ዜና አበው የሚባሉት የመነኮሳት ፍልስፍና የተሰበሰበባቸው መጻሕፍት ናቸው እነሱን ቪክተር አራስ አሳትሟቸዋል ነር ለ ዐርርፀዐ ዐዐናርዉ ርርዐ ሃ ህ ኒር ላሸ ሥ«ዐፀገርዐዘ ሀዐሦርፎ ርርዐ ሃ ህነሃዉ ከነአባ እስጢፋኖስ ዘመን በኋላ ወደ ግዕዝ የተተረጐሙ ሌሎቹ መዳጋጠፉፍሦ መዕዞሶጎፖ የሚባሉት ማር ይሥሐቅ ፊልክስዩስ አረጋዊ መንፈሳዊ ናቸው ኢትዮጵያ ከነአንድም ትርጉማቸው ካንዴ በላይ ታትመዋል ፖነ መዳዱጓፉሦሥ መዕዖጎፖ ዳርሃነም ፅ ማሂ ይዕጋዎቀ ያኛ ሪፊፈሷያዕጾዕ ሇረ ያረሃነ ያነ ያኛ ለሬጋሯ መጋፇፈጎዊ አዲስ አበባ ሀ ዓ ም ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ከዚያ በኋላ ዝናው በዚች መንግሥት አገሮች ሁሉ ተሰማ ብዙዎች ወደሱ መጥተው በትምህርቱ ስብከት ተጠመዱ በእያንዳንዱ ማኅበራቸው በየቱ በቡድኖች እንዲከፈሉ ለያንዳንዱም ማኅበር ከማህላቸው ተግባረ እዳቸውን ሲያካሂዱ ትእዛዝ በመስጠት የሚያገለግላቸውን የመረጡትን ቀዋሚ እንዲያደርጉ ሥርዓት አወጣላቸው ደግሞ ከማኅበሩ ተላላኪዎችቀዋሚዎች ሁሉ በላይ ሆነው የሚያዝዙ ከማኅበሩ ሁሉ ሁለት አዛች እንዲመርጡ አዘዛቸው በየአድባራቸው እንዲሁ እንዲሆን አደረከኸ ለምግባቸው የእንጀራ የአትክልት የውሐ መለኪያዎች አበጀላቸው ብዙ በመቀበል ከዚያ እንዳያበልጡ በትንሽነቱም ምክንያት የደረሳቸውን እንዳይለውጡ አዘዛቸው ስለ ልብስም እስከ ትንሹ ነገር ድረስ እኩል እንዲያደርጉ እንጂ ማንም ቢሆን በማሻሻል ሳቢያ እንዳይጨምር ለማሳጠርም እንዳይቀንስ እንደዚሁ አዘዛቸው በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ እንዳለው የሐዋርያትን ቅድስት ሥርዓት ሠራላቸው እንዲህ አላቸው በሰላም ሰንሰለት ተያይዛችሁ በአንድ ልብና ነፍስ ኑሩ ከናንተ ማንም ካለው አንድ ሐሳብ በቀር ስለ ልብስም ሆነ ስለ ምግብ በመሄድም ሆነ በመመለስ ጊዜ በሐሳብም ሆነ በግብር ሌላ አይኑረው ለጽድቅ ሥርዓት ባሮች ሁኑ እንጂ በጠላት በሰይጣን ከመያዝ ይልቅ የወንድሞቻችሁን ደስታ በመቀበል የጠፊውን ሥጋችሁን ጠባይ ካዱ በእጃችሁ ሥራ ኑሩ የሰዎችን የድካም ፍሬ በከንቱ አትውሰዱር ጥሪትም ምንም አይኑራችሁፁ በሚያረጅበትና በሚበላሽበት ቦታ ማለት በምድር ላይ ጥሪት አታብጁ የጌታን ቃል ተከታዮች ሁኑ እንጂ ጥሪታችሁ ትልና ምስጥ ከማያገኘው ከመንግሥተ ሰማያት እንድትሆንላችሁ ሁል ጊዜ አድርጓትም ከድካማችሁ የተረፈውን ምግብም ሆነ ልብስ ጌታ ላዘዘለት ስጡት ለሚመጣው ጊዜ ብላችሁ ለማግስት አታስተርፉት አምላካችን በየዓመቱና በየዘመኑ ክረምትን በማመላለስ ፍሬዎችን በመስጠት በረከት በመስጠት ለፍጡሮቹ ያዘጋጀውን የቸርነቱን ሥርዓት ተመልከቱ እናንተም እንደ ጌታ ትምህርት የዛሬውን ለዛሬ የሚመጣውን ደግሞ ለሚመጣው ዓመት አድርጉ እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብጽ ያወጣቸው ጊዜ ከምድረ በዳ አስቀምጦ ለምግባቸው መና አዘነበላቸውሱ ለየቀኑ ብቻ የሚሆነውን እንዲሰበስቡ ለማግሥት እንዳያሳድሩ አዘዛቸው አንዳንዶች ባለማመናቸው ቃሉን ጥሰው ለማግሥት የሚሆን አሳደሩ ስለዚህ ያሳደሩት ተላ ገማም ይኸም ለምንኩስና ምልክት ነው ደግሞ ሐዋርያት ቅድስት ሥርዓት የሚለው በሐ ሥራ ያለውን የማኅበር ኑሮ ነው የወንድሞችን ደስታ ከራስ ጥቅም አብልጦ መቀበል ከሌላም ቦታ ደጋግመው የተናገሩት ትምህርታቸው ነው ማቴ ዘፀ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል እንደዚሁም የዕለት ምግባችንን ዛሬ ስጠን እያልን እንድንለምነው በቅዱስ ወንጌል አዝዞናል በመሰብሰብም ሆነ በሐሳብ ሌላ ትርፍ ነገር እንዳንፈልግ ሳያከማቹ በቀላል በመኖር ወፎችን እንድንመስላቸው ያዘናል ወፎች ሲያባርሯቸው በቀላል ይበራሉ ምክንያቱም የሸክም ክብደት የለባቸውም እናንተም እንደዚሁ ከሚበሰብስበት ቦታ ሳታከማቹ በቀላል ኑሩ። አብ የወለደ ወልድ ከአብ የተወለደ መንፈስ ቅዱስ ከአብ የወጣ የአብና የወልድ መንፈስ ይባላሉሶስት ህላዌዎች ሶስት ገጾች ሶስቱም በመለኮት በክብር በኃይል በአገዛዝ በችሎታ በሥልጣን በፈቃድ በሥራ እኩሎች ናቸው ይኸንን እምነት ሰምተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ ልባቸው ጭማሪ ወይም ቅነሳ በሌለበት በሶስትነት ህልው ለሆነው አምላክ እየተገዛ አመሰገኑት እንደ ቤተ ክርስቲያን መምህሮች የግብራቸው ውበት የሰማይ አባታቸው ይመሰገናል ያለው የጌታ ቃል በሱ ሳይ ተፈጸመ ንጉሠ የቅዱሱን የትምህርት ውበት ጥንቃቄውን ሲረዳ ቅዱሱን ከፊቱ በሚያቆምበት ዕለት በሰፈሩ ያሉት መነኩሴዎች ሁሉ እንዲሰበሰቡ ዓዋጅ እንዲነገር አዘዘ ጳጳሱን አባ ሚካኤልንም ጠራው የድንኳኑን ካህናትና መጻሕፍትን በማወቅ የተሾሙትን ሁሉ ጠሯቸው ከአንድ ሺህ በላይ የሚሆኑ መነኮሴዎች ተሰበሰቡ እነዚያም ከሳሾች አብረውት ነበሩ እነሱን ሁሉንም ለብቻቸው ከፊቱ አቆማቸው ቅዱሱንም ከፊቱ እንዲቆም አስገባውና ከደቀመዛሙርቱ ጋራ ለብቻው አቆመው ቅዱሱ አባታችን ለንጉሠ ለነፍሱ በሚገባት ቅድስት ቡራኬ ሰላምታ ሰጠው ከዚያ ንጉሥጮ ቅዱሱን የመጣህበትን ጉዳይ ተናገር አለው ቅዱሱ እንዲህ ሲል መልስ ሰጠ ጸሎተ ሃይማኖት ከላይ ኅዳግ ጥር ን ተመልከት ጮማቴ በአፄ ይሥሐቅ ጊዜ ጳጳሱ አባ በርተሎሜዎስ ነበሩ የሚባለው አባ ሚካኤልና አባ ገብርኤል ከኤኢስ ቆልሱ ከአባ ዮሐንስ ጋራ ወደኢትዮጵያ የመጡት አፄ ይሥሐቅ ከሞተና አፄ ዘርአ ያዕቆብ ከነገሠ በኋላ በ ዓ ም እንደሆነ ነው በ ርር »ዐ ወሮሀፀ ህርር ሪፀ ዘርጀና ሪህ ሄዐዕ ወዳወህ ርርዐ ሂ ዐ ደቂቀ እስጢፋኖስ ግንኙነት የነበራቸው ግቢያቸው በራራ ደቡብ ከነበረው ከአባ ገብርኤል ጋራ ነበረ ግን አባ ሚካኤል ቀደም ብለው ለመምጣታቸው ይኸና ሌሎች ምንጮችም ያመለክታሉ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል አስረው አመጡኝ እንጂ እዚህ አመጣጤ በፈቃዴ አይደለም ግን ከፊትህ እንድቆም የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆኗል እኔም ይኸንን ወድጀዋለሁ ሆኖም እዚህ የሚያመጣኝ ከሥጋ ግዛት የሚፈለግ የሥጋ ጉዳይ የለኝም ያለኝ ሌሎቹ ወንድሞች ከእኔ ጋራ የሚካሰሱበት የመንፈስ ጉዳይ ነው ሕጉን ለመረዳት የልብህን ዓይኖች እግዚአብሔር ያብራ በሥራ ላይ እንድታውለውም ኀይል ይስጥህ እግዚአብሔር ፍርዱንና እውነቱን በአንተና ነገሬን በሚሰሙት ሁሉ ይሹም እንግዴህ ቃሌን ስማኝ እግዚአብሔር ስሙ ይባረክና በሥራው ሁሉ የተባረከ ነው ሰማይን አቁሞ ምድርንም መሥርቶ በውስጣቸው ለሥጋ የሚገባ ሕይወታችንን የምናቆይበት የተድላ በረከት አዘጋጀ በሰማይ ጠፈር ላይም ብርሃኖችንፀሐይን ጨረቃን ኮከቦችንጊዜዎችን ሰዓቶችን ሳምንቶችን ወራቶችን ዓመቶችን እንድናውቅባቸው ሾማቸው በተመረጠበት ዓመት ለሚገለጠው የዓለም ምስጢር ምሳሌ አደረጋቸው ጌታ ዝግጅቱን ሁሉ ሲጨርስ በስድስተኛው ቀን ሰውን ከልጁ ከማርያም ሰው ሆኖ ለሥራው በሚገለጽበት አምሳል ፈጠረውና አዳም አለው በሰባተኛዋ ቀን አረፈባት ባረካትቀደሳትም ባደረገው ቀጠሮ ጊዜ ጽዮን ስትሞላና አዲሱ የዓለም አባት ሲገለጽ ልበ ግዙሮች ከእሱ ጋራ እንዲያርፉ ለሚሰጠው ጸጋ ምልክት ሲሰጥ የሁል ጊዜ ኪዳን አደረጋት በሰው ልጅ ነፍስ ጠፈርም ሾማትና በምክሩ እንዲኖር አዘዘ ሁለት ማእዶችም ዘረጋለትአንድ የመንፈስ አንድ የሥጋ መንፈስ ቅዱስን ለነፍሱ ምግብ የገነትን ተድላ ለሥጋው ሰጠው የሰው ልጅ ይኸ ሀብት በእጁ እያለለት ለነፍሱ ሞትን እስኪያመጣ ድረስ በጠላት ምክር ተደለለ ጌታም ጸጋውን ገፈፈውና በምክሩ ሳጥን ደበቀው ሰውም ራሱና ዘሩ ሁሉ በሐዘን ማጥ ሰጠመ ልጆቹ መሬት ስለክፋታቸው እስክታጉረመርም ድረስ የሞት እሾክ አፈሩ እግዚአብሔር ኪዳኑን ለመጠበቅ ለጽድቅ ተክል ከኖኅና ከልጆቹ በቀር ማንንም ሳያስተርፍ ብዙዎቹን በጐርፍ ግሠጻ አጠፋቸው ደግሞ ከትውልድ በኋላ ሲበዙ ግምብ ገነቡ እዚያም ቋንቋቸውን ከፋፈለው ደግሞ ከፈጣሪ ይልቅ የጃቸውን ሥራ በማስበለጥ ለአማልክት ለመሠዋት ዳከሩ እግዚአብሔር አብርሃምን መረጠና በዘሩ የምድር ሕዝቦች ሁሉ እንዲባረኩ ከሱ ጋራ ኪዳን አደረገ ከዚያ ደግሞ የሰዶም ሰዎች አስቄጡት በላያቸው ላይ እሳት አዘነበባቸውፁ ሎጥንና ልጆቹን ከመጥፋት አዳናቸው በተመረጠበት ዓመት የሚገለጠው የዓለም ምስጢር የሚሉት ወይ ክርስቶስ የተወለደበትን ወይም ክርስቶስ እንደገና ሲመጣ ከጻድቃኑ ጋራ አንድ ሺህ ዓመት የሚነግሥበትን ወይም ከምጽአት በኋላ ያለውን የዘላለሙን ኑሮ ነው ስለ ደብረ ዮን መግቢያውን ተመልከት ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ግብጾች እስራኤላውያንን በግድያና በመራር አዝዝ አሰቃዩዋቸው እግዚአብሔር እስራኤላውያንን በሙሴ እጅ ረዳቸው ወደ ምድረ በዳም አወጣቸው የግብጽን ሰዎች ግን ከባሕር አሰጠማቸው ለእስራኤል ሕጉን እንዲጠብቁ ኦሪትን ሰጣቸው እነሱ ግን ልባቸውን ወደ ግብጽ አዞሩ ባለማመን አስቆጡት በምድረ በዳ እስኪፈጃቸው ድረስ የተረፉትን ለአብርሃም ከማለለት ምድረ ርስት አገባቸው ቀጥሎ ከትውልድ በኋላ ዳዊትን ነግሦ ሕዝቡን እንዲጠብቅ በእውነተኛ ምርጫ ጠራው መጨረሻ ለሌለው መንፈሳዊ መንግሥቱ አርአያ አደረገው እሱም እስከአንቀላፋ ድረስ አገለገለው እስራኤል ግን ሕግን ቸል በማለትና ስለ መምጣቱ የሚያበሥሩትን ነቢያት በመግደል እሱን ማስቆጣቱን አንተውም ቢሉ የባቢሎንን ንጉሥ ላከባቸው እሱም አጋዛቸው ከሀገራቸውም አፈለሳቸው ባደረገው ቀጠሮ የሚፈጽመውን ኪዳኑንም በማስታወስ በደላቸውን ይቅር ብሎ ከድ ዓመት በኋላ እንደገና ወደ ምድራቸው መለሳቸው እስራኤልን ለበዓሉ ዕለት በብዙ መግለጫ ጋበዛቸው የግብዣው ጊዜ ሲደርስ በአስደናቂ መገለጥ ያለሰው ዘር ከንጽሕት ድንግል የዳዊት ልጅ ሰው ሆኖ ከዓለም በፊት ያዘጋጃትን ምክሩን ፈጸማት ፈጣሪ እራሱ እንጂ ሌላ ላልፈጠረው ፍጡሩ ሕይወት በመስጠት የሥራውን ውበት ገለጸ የተጋበዙ እስራኤል ግን ቃሉን ችላ አሉ እንዲያውም ቀኑበት ሰደቡት ለሞት እስኪያደርሱትም አሰቃዩት ያለኃጢአት በተፈጸመችበት የሞት ሕመም ሰይጣንን አድድኖ በጥፋቱ የታደነ አዳምን በትክክል ፍርድ ነጠቀው ጌታ ሁሉንም ፈጽሞ የሞት እንቅልፍ በመስቀሉ አልጋ ላይ አንቀላፋ ደምና ውሐ እስኪፈሰው ድረስ ጉኑን በጦር ወጉት በዚህም ቤተ ክርስቲያን ታነጸችነ የነፋስና የጎርፍ ሞገዶች ማናወጥ በማይሆንላቸው የሰንፔር አልማዝ በሆኑ ቅዱሳን ሐዋርያቱ ላይ መሠረታት በሥጋው ጠፍሯት ጨረሰና በጠፈሩ ላይ ከራሱ ብርሃን የሥርዓት ሕግ ብርሃኖችን ተከለ በድግሱ ቤት የተቀመጡት በብርሃኑ እንዲደሰቱ በሌሊት እሾህ እንዳይደናቀፉ የዕለቱን ሰዓታት ዓሥራ ሁለቱን ጊዜያት በብርሃናቸው እንዲያዩ ታሪኩ የሚናገረው እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሚሠራለትን ቸርነትና የሰው ልጅ ግን መልሶ መላልሶ በደለኛ መሆኑን ስለሆነ እስራኤላውያን ወደ ግብጽ መውረዳቸውንና የወረዱበትን ምክንያትና በደላቸውን ሳይተርክ ታሪኩን በማሳጠር ድንገት ግብጾች እስራኤላውያንን በግድያና በመራር አገዛዝ አስቃዩዋቸው ያለው በአንዳች ስሕተት ምክንያት መሆን አለበት ታሪኩ ያጠረው እጄ የገባውን መጽሐፍ የቀዳው ሰው መሥመሮች ቢዘል ነው ከቅድስት ድንግል ማርያም ማለት ነው ከዘመኑ የቤተ ክርስቲያን ሥነ ጽሑፍ ጋራ ሲተያይ በእስጢፋኖሳውያን ዘንድ የማርያም ስም ብዙ አይታይም ለጂቃ ማቴ ሰንፔር በእንግሊዝኛ ሀከቨር ነው ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል የማይጠልቁ ኮከቦችን ፈጠረ ቃሉን ችላ ያሉ እስራኤላውያን ግን ትንቢትን ክህነትን መንግሥትን ወስዶባቸው ለቤተ ክርስቲያኑ ሰጣት ለሕጉ የሚታዘዙት የዚህን ዓለምና የሚመጣውን ዓለም ሕይወት በእጥፍ ድርብ እንዲያገኙ በውስጧ የጥቅም ዋጋ አኖረ ስለዚህ ንጉሥ ሆይ እኔም ፈለጉን ለመከተል ራሴን በመስጠት በዚህ መገዛት ስር ለመዋልና ራሴንም አፍአዊ ከሆነ የሌሊት ስሕተት እንድድን ባወጣልኝ ሕግ መሠረት ራሴን ለማንጻት ወደድኩጹ ከዚያ እንደ ፍላጎቴ ለመኖር የሚወዱ ባልደረቦች አገኘሁ የእርሻውን ጌታ የአገዛዝ ትእዛዝ ንገረን አሉኝ እሱ በሕማሙ እንደጠቀመኝ ልጠቅማቸው ወደድኩ በከንቱ ያለዋጋ ከሰጠኝ እንድሰጥ አዞኛልና ዌ በቤቱ ጠፈር ውስጥ ስለተሰቀሉት ብርሃኖች ትእዛዝ ስመክራቸው በሕጉ ፈለግ መኖር ጀመሩ ከዚያ በኋላ ሌሎች ወንድሞች የሀገራችን ትምህርት ያልሆነ ታስተምራለህ ሲሉ በጥል ተነሠብኝ የዚች ሀገር ትምህርት ምንድነው። ሪፓ ቫዐዖ ይገገወህ ርር ሃ ኮ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ከዚህ በኋላ ንጉሥ ነገር በማጣፈጥ ወደ ቅዱሱ እንዲህ ሲል ላከበት ሰላም ላንተ ይሁን ለእግዚአብሔር ቀናተኛ እንደሆንክ ዜናህን አሁን ሳይሆን ከመንገጐዜ በፊት ሰምቻለሁ አሁንም ሃይማኖቴን ስለሚመለከት እንድንወያይ ወደኔ መምጣትህን አታዘግይ ላገኝህና በሕጉ ፈለግ መሠረት ሁሉንም ለእግዚአብሔር ላስተካክል እወዳለሁ እንዳይቀር በዚህ ላይ የእግዚአብሔርን ስም ጠርቶ ጨምሮበታል ይኸም ሆኖ ብፁዑ መሄድ አልፈለገም ነበረ ነገር ግን መኳንንቱና መልእክተኞቹ ስለወተወቱት በስንት ጭንቅ እሺ አላቸው ቅዱሱ ለልጆቹ እንዲህ አላቸው ለክፋታቸው ምክንያት እንዳይኖራቸው ስለ ሃይማኖት እንነጋገር ብንለውና በእግዚአብሔር ስም ብንይዘው እምቢ አለን እንዳይሉን በሉ ኑ እንሂድ አባታችን ለመሄድ መስከረም ቀን ተነሣ በጥቅምት ቀን ከንጉሥ ሰፈር ደረሰ ንጉሥ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከሰው ጋራ ባለበት ጊዜ ከፊቱ አቆመው ግን አላነጋገረውም ብዙ ጊዜ እንደዚህ አደረገ ከፊቱ እያቆመ አያነጋግረውም ደግሞ ጠርቶ እንደበፊቱ ከፊቱ አቆመው የሠራዊቱን ታላላቆችና መነኩሴዎችንም ወደ ውስጥ አስገባ ከዚያ የመንግሥቱን ጉዳይ በትጋት ማካሄድ ጀመረ ከንጉሥ ጋራ የመጀመሪያው ግጭት ራሱ ንጉሥ በከሰሰው በአንድ ሰው ላይ ሁሉም ፍርድ እንዲሰጡ አዘዘ። አባቶቻችን ይኸንን ሁሉ ልማድ ለተዝካራቸው እንዲሆን አዘጋጅተውልናል እናንተ ንጉሦቻችንም የመሠዊያ ቀንዶች የነፍሳችንና የሥጋችን አባቶች ናችሁ አሉት መጽሐፉ እርስ በርሳቸው ገጸ በረከት ይሰጣጣሉ እንዳለው እርስ በርሳቸው ተመሰጋገኑ ከጥቂት ጊዜ በኋላ የከሰሱትን መነኩሴዎች ወደየሀገራቸው ሰደዳቸው ቅዱሱ ግን ስላላሰናበተው እስከ ሁለት ወር ድረስ ታገሠ ከዚህ በኋላ የደብተራዎቹን አለቆች እንዲህ ሲል ወደ ንጉሠ ዘንድ ላካቸው አስተካክላለሁ ያልከውን አላስተካከልክም እነሆ የወንጌልን ሥርዓት የሚቃወሟትን ሁሉ አሰናበትካቸው ማስተካከል ካልፈለጋችሁ በሕጋችንና በእጅ ሥራ ድካማችን እንድንኖር አሰናብቱን በምድርህ ላይ እንደዚህ እንድንኖር ካልፈቀድክ ወደ ምድረ በዳችን ስደደን ለኛ የሰማይ ወፎችን ተመልከቱ ያለው የጌታ ቃል ይበቃናል ይኸንን ሁሉ ካልፈቀድክና ሌላ ያሰብከው ካለህ አሁን ፈጽምልን የደብተራዎቹ አለቆች ይኸንን ለንጉሥ ሲነግሩት በእጄ የሰማዕትነት ሞት ይፈልጋል ግን አያገኝም ወደ ደብርህ ተመለስ በሉት አላቸው አሰናበቷቸው ከዚያ ቅዱሱ በጥር ቀን ከንጉሥ ሰፈር ተነሣና የካቲት ቀን ከማደሪያው ደረሰ አዲስ የገዳም ኑሮ ልጆቹ ካወጣላቸው ቀኖና ጋራ ልባቸው በሚዛን ሳይ እኩል እስኪሆን ድረስ ኑሯቸው በቃልም በምግባርም ትክክል እንዲሆን ይጉበኛቸው ነበረ እንዲህም ይላቸው ነበረ መዝ ራእ ማቴ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል ድኾችን የምትረዱበትን አሁኑኑ በድካማችሁ ላብ ማርኩ ምክንያቱም እንደዚህ መጣር ሁል ጊዜ አይቻልም ጌታ በዓለም ውስጥ ያለውን ለማድረግ የማይቻልባት ሌሊት ትመጣለች እንዳለው የሚሆንበት ሁኔታ ይመጣል እናንተ ይኸንን የያዛችሁትን በምትሠሩበት ጊዜ ዓይናችሁን በወደፊቱ ላይ አትኩሩ ጌታ እኔን ካሳደዱ እናንተንም ያሳድዷችኋል እንዳለው ሰማዕትነት እስከሚፈጸም ድረስ ከዚህ መሰደድና መታሰርም ይኖራል ደግሞ ግን እኔ ዓለምን እንዳሸነፍኩ በዚህ እመኑ በርቱም ይህቺ ኑሯችሁ እንደዚያን ጊዜዋ የአባቶች መንገድ ናት እነሱ የመርከባቸውን ፍጻሜ ያሳረፉበትን ታዩ ዘንድ የልባችሁን ዓይን አንሥወደ ቀድሞው ሳይሆን ወደ ላይኛው እንጂ ነቢዩ ከጌቶች ማእድ ከተቀመጥክ አንተም እንደነሱ ማቅረብ እንዳለብህ ዕወቅ ያለው ስለዚህ ነው ጌታም እንዲህ ሲል ያስረዳናል እንዳትሳሳቱና እንዳትደናቀፉ ይኸንን ነግሬያችኋለሁ ከምኩራባቸው ያስወጧችኋል ከዚህ የሕይወት ምንጭ ሲጠጡ የመላእክትን ሕይወት አግኝተው የሥርዓት ውበት በላያቸው ላይ መዓዛዋን አሳየች ከዚህ በኋላ ተከታዮቹ ብዙዎች ሆኑ ገዳሞቻቸውም በውጪና በውስጥ በበረከት ፍሬ እየሞሉ ከአንድ ወደ ሁለት ከሁለት ወደ ሶስት እጥፍ ሆኑ የድካም ላባቸውን ድኾች እንዲካፈሉት ከየአትክልት ቦታቸው እያመጡ በቅዱሱና በማኅበሩ ሁሉ ፊት በማቅረብ በረከት ለመስጠት ይሽቀዳደሙ ጀመር ቅዱሱ ያንን በረከት ተቀብሎ ጠዋት ጠዋት ከ ሰዓት በኋላ ከጸጥታ ማደሪያው ይመጣና በገዳሙ በራፍ ላይ ለድኾችና ለምስኪኖች ሲያካፍል ይውላል ጸሎት ለማሳረግ ካልሆነ በቀር ምንም ሳያቋርጥ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ እንደዚህ ያደርጋል ብዙዎች ከበሽታቸው ፈውስ እየፈለጉ ከቅርብና ከሩቅ ሀገሮች ወደሱ ይመጡና ቅዱሱ እጁን ሲያሳርፍባቸው ከተላላፊ በሽታቸው እየዳኑ ፍስና ሥጋን በመርዳት ለሀገራችን ትልቅ መከታ ተገኘ እያሉ ሁሉም እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ ከሀገሪቱ ታላላቆችም ብዙዎች ከትምህርቱ ገቡ ያ በሁሉም ስም ነገረ ፈጅነት የተሾመው የመነኩሴዎቹ አለቃ ሳይቀር በቅዱሱ ላይ የደረሰውን ስድብ ለመሸከም እሱም ተደመረ በራስ ሸበት ጊዜ አዛውንትነት አግኝቶ ከቅዱሱ ጋራ እስራትን ግርፋትን ከሀገር ወደ ሀገር መሰደድን ተካፈለ ዮሐ ዮሐ ዮሐ የምንኩስና ሥርዓት ሲፈጸም ለመንኳሹ የሚነበብለት ነው ነር ለ ሥወሠገ ርዐዘ ፀሀዐርር » ዮሐ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ያለ ንጉሥ ፈቃድ የእስጢፋኖስ ስም ከፍ ከፍ አለ ከዚህ በኋላ ንጉሥን እነሆ ያለ አንተ ፈቃድ የእስጢፋኖስ ስም ከፍ ከፍ አለ ሀገሮቹ ሁሉ ትምህርቱን ከማድነቅ ገቡ እሱ ደግሞ እንዳይሰግዱልህ ማሳመፅ ይዚል ብለው እስኪያሳስቡት ድረስ ቅናት በምድር ክቡሮች በሆኑት ላይ በዛች በእንደዚህ ያለ አነጋገር ቅዱሱን ለማስገደል ብዙዎች ስሕተት ፈለጉበት በዚያን ጊዜ ከዕለታት አንድ ቀን ቅዱስ አባታችን ደቀ መዝሙሩን ገብረ ክርስቶስንና ያንን አብሮት የሚከተለውን ወንድም ጠርቶ እንዲህ አላቸው በዚች ሌሊት ትልቅ ሐዘን ወደቀብኝ አስፈሪ አንበሶች እንደማይ ሆንኩ ደግሞ ብዙ መነኩሴዎች የማውቃቸው ስም ያተረፉና ሌሎችም ነበሩ መነኩሴዎቹ እነዚያን አስፈሪ አንበሶች ሲያዩ በጣም ፈሩ ሊቀርቧቸው አልቻሉም ከፊታቸው አርዝመው ሸሹ እኔ ግን ቀረብኳቸው ሰላምታ ተሰጣጥተን በማህላችን የፍቅር ስምምነት ተፈጥሮ እንደ አንድ ሆንን ብዙዎች አብረውኝ ሆኑ ከዚያ ቀጥሎ እነሆ ከአንበሳዎቹ አንዲቷ ከባልደረቦቿ ተለይታ ብቻዋን ስትሄድ አየሁ በመሄዲ ምክንያት በቀሩትና በሷ ማህል ትልቅ ሐዘን ወደቀ እኔም አለቀስኩ እናት ከልጆቿ እንደምትለይ መሰለኝ እንደዚህ በሐዘን ላይ እንዳለሁ ነቃሁ እንባዬ መኝታዬ ላይ ሲወርድ አገኘሁት ይህ ምልክት ስላለፈው ይመስላችኋል ወይስ ስለሚመጣው። ምክንያቱ ብዙ ገድልና ችግር ስለሚጠብቀኝ ነው ስለዚህ መጨረሻዬን አልነገሩኝም ግን በዚች ሌሊት ትልቅ ለቅሶ ደረሰብኝ ወንጌላዊው ዮሐንስ ለደቀ መዝሙሩ ለሞትም ሆነ ለሕይወት አልተገለጠልኝም እንዳለው ለኔም እንደዚሁ ሆኖብኛል ለማንኛውም የምድር ክቡሮች ክቡራነ ምድር የሚላቸው የአድባራት አበምኔቶችን ነው አጻጻፉ ዓለምን በመናቅ መነኮሳት ሆነው ሳለ ተመልሰው ምድራውያን መሆናቸውን ሲያሳይባቸው ነው እዚህ ምድር የሚለው ኢትዮጵያን ነው ካለፈው አተረጓጐማቸው እንደሚታየው አስፈሪ አንበሶች የሚሏቸው ሰይጣን የሚያመጣባቸውን የሰማዕትነት ፈተናዎችን ነው ያለፈው የሚሉት ከድንቁ በፊት የደረሰባቸውን ፈተና እና ጊዜ የተገረፉትን ሰማዕትነት መሆን አለበት ስብከቱ ለቅዱስ ዮሐንስ ላ ህ ርዐዘሮዘሪፎና ዐ ሀገሮ ዐ ዣ ከኪ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ የአባ እስጢፋኖስ ገድል ጸልዩ ምክንያቱም ዘመኑ የገድል ዘመን ነው ጌታ ጦርነት ውጊያ የጦርነት ድምፅ ትሰማሳቸሁ ብሏልና ስለ ደብረ ዮን ጉባኤ ተጠራ ከዚህ ነገር በኋላ ብዙ ሳይቆይ የትግራይ አገር መነኩሴዎች ሁሉ አክሱም ላይ ተሰብስበው ከቅዱሱ ጋራ በደብረ ጽዮን ጉዳይ እንዲከራከሩ ከንጉሥ ዘንድ መልእክት መጣ ይህ የሆነው እነሱ በፈጠሩት ነገር ለመነታረክ እንጂ የሕግ ትምህርት እንዲያገኙ ፈልገው አልነበረም የንጉሥ ሎሌ ወደ ቅዱሱ መጥቶ እዚያ ሄዶ በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲከራከር የንጉሥን መልእክት ነገረው ቅዱሱ ይቺ ነገር እነሱ ያወጧት የከሳሾቹ ተንኮል እንደሆነች ስላወቀ ለሎሌው አልሄድም በከንቱ ነገር ምክንያት ልደክም አልፈልግም የሚፈልጉት የመንፈስ ጉዳይ ከሆነ የደብረ ጽዮንን ምስጢር እንዲረዱ የወንጌልን ፈለግ ይከተሉ የሚፈልጉት የነገር ዋዛ ከሆነ እነሆ ባልደረቦቻቸው ከንጉሠ አዳራሽ በከበረ ልብስ እየተመኩ አሉላቸው የመንፈስ መንግሥትን ማየት ግን በምግባር እንጂ በነገር አይደለም አለው የንጉሥ መልእክተኛ ሄዶ ይኸንን ለነዚያ ለከሳሾቹ ለጉባኤው አለቆች ነገራቸው በቅዱሱ ላይ ያሰቧት ክፉ ምክር ስለከሸፈባቸው በጣም ተቆጡ ከዚያ በኋላ ምክር ያዙ አንዳንዶቹ ክስ ለመመሥረት ሎሌውን ተከትለው ወደ ንጉሠ ሄዱ አንዳንዶቹ የቅዱሱን ገዳም ለመዝረፍና ልጆቹን ለማሰር ተቃጠሩ ገዢው የሚፈልገው እንደዚህ እንዲሆን ነውና የንጉሥ ጥሪ ንጉሠ ደግሞ እንደገና ሎሌውን እንዲህ ሲል ወደ ቅዱሱ ላከው እዚህ ሆነህ ስለ ሃይማኖት ጉዳይ እንድንወያይ ወደኔ ና ደግሞ ቅዱሱን በግድ እንዲልከው በጎን የሽሬን ገዢ አዘዘው እነሱ አባታችንን ሲያጣድፉት እነዚያ መነኮሳት ደግሞ ከቅዱሱ ገዳሞች አንዷን ደብር ከበቧትና ድካማቸውን ሁሉ ምንም ሳይተዉ ለተጐርባን ኅብስት ያዘጋጁትን ሳይቀርእንደ ዘላን ዘረፉት ልብሳቸውንም ገፈፏቸው ደበደቧቸው አሰሯቸው የቅዱሱ ልጆች ማቴ ማር ስለ ደብረ ዮን መግቢያውን ገጽ ተመልከት እንደ ዘላን ዘረፉት የሚለው አነጋገር ታሪክ ሊኖረው ይችላል ንጉሥም አባ እስጢፋኖስን ሰማዕት የሚያደርጉህ ብዙ አረሚዎች ሀገርህ አሉልህ ያለውም ከዚህ ጋራ አብሮ ይሄዳል ምናልባት የኢትዮጵያ ዘላኖች የሰሜን አፍሪካ በርበሮች በግብጽ ገዳማት ላይ ያደርጉት እንደነበረው ገዳማቱን ይዘርፉ መነኮሳቱን ይገድሉ ኖሯል ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ምንም ሳይመልሱላቸው በተኩሎች ማህል እንዳሉ በጎች ሆኑ ብቻ እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ነበረ እግዚአብሔር ዋጋቸውን በዚህ ዓይነት ከፍሏቸዋልና አገረ ገዢው ሲሰማ ከንጉሥ ሎሌ ጋራ ወደዚያ ሄደና በግድ አስጣሏቸው ስለቀሙት ንብረት ግን ማንም አልከሰሳቸውም የንጉሥን ልብ ዐውቀውታልና ከዚያ ኅዳር ቋ ቀን ቅዱሱ ለመሄድ ተነሣና ጥር ቀን ከንጉሥ ሰፈር ደረሰ ያ ሽማግሌ አባ በርተሎሜዎስም አብሮት ነበረ። እንደታመምክ ሰማሁ አሁንም እግዚአብሔር ይማርህ ባለፈው ጊዜ በተጣላንበት ጉዳይ አትዘን እኔም ያለፈውንም የሚመጣውንም ትቻለሁቡ ቅዱሱ ለላካቸው ይኸንን ላስታወሰህ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው በተጨማሪም ትእዛዙን እንድትፈጽም ልብህን ያብራልህ በሉት አላቸው ከዚያ በኋላ ንጉሥ አጠገቡ ማደሪያ እንዲሰጡት ትእዛዝ ሰጠ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ምግባቸውን እንጀራ ይልክላቸው ጀመረ ከገዳማቸው ካመጣቸው አንድ ዓመት ከተፈጸመ በኋላ በመልእክት እንዲህ ሲል አሰናበታቸው ምንኩስናችሁን ጻማችሁን አድባራችሁን እግዚአብሔር ይባርክ በሰው መመካት አንተ እንዳልከው በእውነት ኃላፊ ነው አሁንም በእግዚአብሔር ተመኩ ወደየአድባራችሁ ተመለሱ ቅዱሱን የበሽታው ጣር ለቀቀው ከማደሪያው ለመውጣትና ለመግባት ጥቂት በጥቂት ይንቀሳቀስ ጀመረ ግን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰማዕትነቱን እስከፈጸመበት ጊዜ ድረስ አርዝሞ ለመሄድ አልቻለም መሸከሚያ ወንበር አበጅተውለት በታኅሣሥ ቀን ከንጉሥ ሰፈር ለቀቁና የካቲት ቀን ከማደሪያቸው ደረሱ አዲስ ክስ ግርፊያና እስራት ከጥቂት ጊዜ በኋላ እነዚያ ሰብቀኞች ደግሞ ተበጠበጡ ንጉሥጮንም እንዲህ ሲሉ በጠበጡት እነዚህን እንደዚህ ዝም ካልካቸው ሁሉም የነሱን ፈለግ ይከተሉና ለመንግሥትህ ሥልጣን የሚሰግድ አይኖርም ከዚያ በኋላ ንጉ ቅዱሱን አባታችንንና ያንን አቡነ በርተሎሜዎስን ከደብሮቻቸው አውጥተው ደብረ ማዕፆ ወደሚሏት ሀገር እንዲሰዷቸው አርባ አርባ እንዲገርፏቸው አዘዘ ከዚያ የንጉሙ መልእክተኛ ወደ ቅዱሱ መጣና ንጉሥ ሰላም ላንተ ይሁን ይልሃል አለው ቅዱሱ የጌታ ሰላም ከሱም ጋራ ይሁን አለው ለንጉሠ ስገድ እኮ አለው ቅዱሱ እኔ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ ለሌላ አልሰግድም አለው መልክተኛው ቅዱሱን እንዲያስሩት አዘዘ እንደታዘዙት አስረው ከደብሩ አወጡት ያንንም ቅዱስ ሽማግሌ አስረው አመጡት ሁለቱን በአንድነት ወደ ደብረ ማዕፆ ወሰዷቸው ጥር ቷ ቀን የአፍሐሮም ዋሻ ወደሚሏት ዋሻ አመጧቸው። ከመቃብሩ ፈውስ ማግኘት አስቆጣ ደግሞ መቃብሩን የጐበኙ በሽተኞች ፈውስ እንደሚያገኙ ተሰማ በዚህ ሁሉ ምክንያት የቅዱሱን አስከሬን ከመቃብር አውጥተው ወደሱ እንዲያመጡት እስኪያዝ ድረስ ልቡ ተቃጠለ በቁጣ አረረ ሰማዕትነቱን ከፈጸመ ከሁለት ዓመት በኋላ ጥር ቀን ከመቃብር አውጥተው ወደ ንጉሥ ወሰዱት እዚያ ወስደው ከሰፈሩ አጠገብ ካለው ቤተ ክርስቲያን አስቀመጡት የመገነዣውን ልብስ ሲገልጡት አስከሬኑን ከቀድሞው ሳይለወጥ አገኙት ገና በዚያን ጊዜ የሞተ ይመስላል በሕዝብ ዘንድም ከዚህ በታች ያለውን ዓዋጅ እንዳወጀ የራሱ መጽሐፍ ይመሰክራል በሁለት መንገድ ድንግል የሆነች የማርያም ምእመናን የሆናችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ሆይ ስለ ደቂቀ እስጢፋ እንዲህ እላችኋለሁ እነሱን በእንግድነት የተቀበለ ከነሱ ጋራ ምንም ነገር የሠራ በቤቱ በቤተ ክርስቲያኑ በርስቱ ያስቀመጣቸው ሹም ከሆነ ይሻር ቤቱም ገንዘቡም በሞላ ይዘረፍ ርስቱ ለባዳ ይሁን ሊቃነ ካህናትና ንቡራነ እድ የቤተ ክርስቲያን ሹሞች ሁሉ መነኩሴዎችም ሕዝብም እነሱን ደብቀው ከተገኙ የነሱ ግብር አበሮች ሆነዋልና ቅጣታቸው ከዚህ የባሰ ይሁን ሹሼመታቸው የቤታቸው ንብረት በሞላ ርስታቸውም ለሌላ ሰው ይሁን እነዚህ ደቂቀ እስጢፋ በእርግጥ በሁለት መንገድ ድንግል ለሆነች ለማርያምና ለአንድ ልጁ መስቀል ለመስገድ እምቢ ያሉ አይሁድ ናቸው የሚገባቸው ቅጣት ሞት ነው ያገኛቸው ክፉ ቅጣት ይቅጣቸው ሆኖም ቃላቸውን እንድንሰማና እንዲፈረድባቸው ከችሉታችን ያምጧቸው እንጂ መግደልስ አይግደሏቸው ለእስጢፋ ሰላምታ ሲሰጥ የተገኘ ሰውም ቅጣቱ ደቂቀ እስጢፋን እንደተቀበሏቸው ይሁን በከ ር ይፖዐ ፀፀዐ ርሮ ዐር ዘፀርፎሠና ሪፓ ሄዐዕ « ያገ ርርዐ ነ ሀ ሀየበ ህበሃ ህሀ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ሬሳቸው እስላም አገር እንዲቃጠል ትእዛዝ መጣ ከ ወር በኋላ ደግሞ ንጉጮ ወደ ደዋሮ ምድር ጻክራ ወደምትባል ከተማ እንዲወስዱት አዘዘ ምክንያቱም እዚያ የዓደል ገዢ የሆነ የእስላሞች መቃብር ስላለና የዓደሉ ገዢ ንጉሙን ይቃወመውና በሥጋ ልማድ እርስ በርሳቸው ይዋጉ ስለነበር ነው ይኸ የክርስቶስ መልእክተኛ የሆነ አባታችን ቅዱስ እስጢፋኖስ ግን ዓለምን የሚቃወማት የምድር ዳርቾች ሁሉ አስተውለው ወደ እግዚአብሔር ይመለሱ የሕዝቦች አገሮች ሁሉ ከሱ ፊት ይስገዱ መንግሥት የእግዚአብሔር ናትና ተብሎ እንደተጻፈው ለክርስቶስ መንግሥት ምስክር በመሆን በሃይማኖት ሰይፍ ነበረ ንጉሥ በዚህ ተቆጥቶ እንደዚህ ያለውን የክርስቶስ መልእክተኛ ከሚበላሸው ከዚያ ከሌቦች መልእክተኛ ጋራ አስተካከለው በአንድ ልጁ የሕማማት ሰሞን የቅዱሱን ሥጋ እዚያ ወስደው የጌታ ስቅለት ዕለት የፋሲካ ዓርብ ከጻክራ አመጡት በማግሥቱ በሰባተኛይቱ ዕለት በፋሲካ ዋዜማ ሚያዝያ ቀን የሀገሩ ሰዎች በንጉሙ ትአዛዝ እዚያ እስላሞች መቃብር ዘንድ ተሰበሰቡ መልእክተኛው የቅዱሱን አስከሬን ከፊታቸው አስቀመጠና የንጉሥን መልእክት እንዲህ ሲል ነገራቸው ይህ ሰው ከሐዲ ነው አገሩን ሁሉ ወደ ትምህርቱ ሲያስክድ ነበረ ጠባዩ ሁሉ እንደዚህ አስላም ነው ስሙ እስጢፋኖስ ነው አሁንም በድኑን ውሰዱና በእሳት አቃጥሉት ቅዱሱ ሰማዕትነቱን ከፈጸመ ጀምሮ እስከዚያች ዕለት ሁለት ዓመት ከ ወር ሆኖ ነበረ። ቅዱሶች ያለው መላእክትን ይሆናል ቤቴል ማለት በዕብራይስጥ የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው በብሉይ ኪዳን ቦታው ቤቴል የተባለው መላእክት ስለወረዱበት ነው ዘፍ ታዲያ ይህ ታሪክ የሚታወቀውና የሚታመንበት በክርስቲያኖቹና በአይሁድ ዘንድ እንጂ በእስላሞቹ ዘንድ አይደለም ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ የቀሞጥራቸው መብዛት አሰጋጓደኛም ከዳ ከዚያ ደግሞ ቅዱሳኑ በትግራይ ብሔሮች በየገዳማቸው ሆነው አርስ በርሳቸው ምዕዳን እያሰማሙና የአባታቸውን ውሳኔዎች እየጠበቁ የትምህርታቸውን ቃል ብዙዎች እስኪቀበሉና በንጽሕ ሥርዓት አብረዋቸው እስኪሆኑ ድረስ የነፍስና የሥጋ ምግብ የሚሆነውን ቃለ መለኮት እያስተማሩ ተቀመጡ የቅዱሳን ደቀ መዛሙርት ሥራ እንደሚለው በነጋ ቀሩጥር እግዚአብሔርን የሚያምኑ ይጨምራል በመጽሐፈ ፍጥረትም እንደዚሁ ይላል የእስራኤል ልጆች ግብጾች ባሰቃዩዋቸው መጠን ይበዙ ነበረ በዚህ ምክንያት ጠላት ተቆጥቶ የክፋቱን መርዝ በብዙዎች ልብ ሞጀረው ከዚያ ትዕግሥትን ባለመቻል እንደ ስሙ ያልሆነ በሥራው ስምያል የሆነ ሳሙኤል የሚባል ወንድም ከማኅበር ተለይቶ ወደ ንጉሠ ሄዶ ቅዱሳኑን በብዙ ውሸት ነገር እንዲህ ሲል ከሰሳቸው እነሱ ከነመምህራቸው ካሉበት እመራለሁ እንዲያውም እሱ ከፊተኛው አባታቸው የጸናና የከፋ ነው ንጉሥ ይኸንን ሲሰማ በጣም ተቆጣ ቁጣውን የሚያበርዱለት ወታደሮቹን ላከ ያም አሳባቂ አብሯቸው ነበረ ዴስአ ከምትባለው የቅዱሳኑ ገዳም መጡ ብዙዎቹን ያዚቸው መኖሪያቸውን ዘረፉት የደከሙበትን ሁሉ ወሰዱት እነሱንም አስረው ወስደው ሌሎቹን ወንድሞቻቸውን እስኪያመጡ ድረስ በዘበኞች እጅ ከመንገድ አስቀመጧቸው ምክንያቱም ንጉሥ ከተገኙበት ቦታ ሁሉ እንዲሰበስቧቸው አዝዞ ነበረ ቀጥሎ መንበርታ ወደምትባል ወደ ሌላ ሀገር ሄዱና እዚያ ያሉትን ቅዱሳን ያዙዋቸው የደከሙበትን ሁሉ ወሰዱት እነሱንም አስረው ወንድሞቻቸው ወዳሉበት ወሰዷቸው ከዚያ ወደ ትግራይ አገረ ገዢ ሄደው ዐጋሜ ውስጥ ያሉትን ቅዱሳን እንዲይዛቸው የንጉሥን መልእክት ነገሩት አገረ ገዢው ሰምቶ ከንጉሥ መልእክተኛ ጋራ ሊፈልጋቸው ሄደ ቅዱሳኑ ካሉበት ሀገር ደርሰው እነሱን በመፈለግ ደከሙ ከሀገሩ ሹማምንት ጳዱን በግዛቱ ያሉትን ቅዱሳን እንዲይዝና እንዲሰጣቸው ይህን ቢያደርግ በሀገሪቱ በሞላ የበለጠ ሹመት እንደሚሰጡት ቃል ገቡለት እሱም በምክራቸው ተደልሎ ቅዱሳኑን በምድረ በዳና በየዋሻው ካሉበት ሄዶ ያዛቸው መቼም የዚህ ዓለም ድኾች ሕጋቸው እንደዚህ ነው የደከሙበትንም ወሰዱባቸው እነሱንም ወደ አገረ ገዢው ወስደው ከፊቱ አቆሟቸው ስለሁሉም ነገር ጠየቃቸው በማህላቸው አእምሮና የመንፈስ ቅዱስ ልቦና ያለባቸው ካህናት ነበሩ አንዱ አቡነ ይሥሐቅ ለማኅበር ቅድስት ሥርዓት መከታ የሆነ የዕንጐ ሳጥን ነው ሌላው በጽድቅ ሰማዕት የሆነው ባለመልካም መታሰቢያ መልከጸዴቅ ሲሆን ሌሎችም መነኩሲቶችና ቅዱሳን አብረዋቸው የሐ ሥራ ዘፀ ስምያል ስማዝያል የሚባለውን የክፉ መንፈስ ስም መጥራቱ መሰለኝ ሄኖ እብርከ ላ ኗከከ ርክዉቨቪ ክብቭከ እ በ ሯሀዐ»ር »ዐዐጳ ዐ ያዘዐርጳ ሃ ዩ ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ነበሩ። በተበሳ ግንድ አሰሯቸው ጐኑጥራቸው ወ ሲሆን ከነሱ ውስጥ ቱ መነኩሲቶች ነበሩ እዚያ እያሉ ወንድሞች በእግዚአብሔር ሰላም ገድላቸውን ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ይሁን ለዘላለምም ይጠብቀን አሜን በጓትር ካሉትም ወንድሞች ገድላቸውን በጌታ ሰላም እዚያው ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ይሁን ለዘላለሙም ይጠብቀን አሜን አቡነ ይሥሐቅና ሊቀ ማኅበሩ ይኸም አቡነ ይሥሐቅ በእስራትና በከባድ ገድል በብዙ ትዕግሥት የደረሰበትን ስቃይ ሁሉ እየተቀበለ ከእነሱ ጋራ ኖረ ወንድሞች ሁል ጊዜ ወደ ላይኛው እንዲያስቡ እንጂ ሐሳባቸውን ከላይ ወደ ጠፊ ዓለም ፍለጋ እንዳያወርዱ ምዕዳን ያሰማቸው ነበረ ከወንድሞች ጋራ በእስራት ከወሰዱት ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ ምክር ወደ ቀድሞ ገዳማቸው እስኪመለሱ ድረስ ዓመት ያህል እዚያው ኖረ እዚያ በነበሩበት ጊዜ ሊቀ ማኅበሩ በአረሚ ብሔር እንደበተኗቸው ስለሰማ ጓ አኗኗራቸውን ለማወቅ ጎበኛቸው ከነሱ ዘንድ ሲደርስ ሰላም ለናንተ ይሁን አላቸው ወንድሞቻቸው እንዴት እንዳሉም ነገራቸው ታላቅ ደስታ ተደሰቱ እግዚአብሔር ስለሠራላቸው ሁሉ ስብሐት አቀረቡለት ከዚያ ወንድሞችን ሁሉ ሰበሰባቸውና በአረሚ ብሔር ከምትኖሩ ወደ ክርስቲያኑ ምድር ብትመለሱ ይሻላችኋል አላቸው ወንድሞች እሺ አሉትና ከዚያ ወጥተው እግዚአብሔር ወደአዘጋጀላቸው ቦታ ሄዱ አቡነ ይሥሐቅ ግን ከሊቀ ማኅበሩ ጋራ ሄደ አብረው ብሔረ ትግራይ እስኪደርሱ ድረስ ከእሱ አልተለየም ከዚያ ከተሰደዱበት እንደተመለሱ ማኅበር አቋቁመው በኃጢአት የተበተኑ ብዙ ነፍሶች ሰበሰቡ ቤተ ክርስቲያን ተክለው ርባን አሳረጉ የወንድሞቻቸውን ተዝካር አወጡ። ፎ ሃ ነ ማቄይ ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ውስጥ በእስራት አስቀመጣቸው እዚያ በብዙ ጣር በረኀብ በውሐ ጥም በመራቆት ጥረው እዚያው በወባ በሽታ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ ጸሎታቸው ለዘላለም ከኛ ጋር ትሁን አሜን አሜን አባ ተወልደ መድኅንና የደብረ እምፍራዙ መጋቢ ያም አባ ተወልደ መድኅን የአለቆች ማኘኪያ በሆነችው በጉንጽ ዓመት ከ ወር ያህል በእስራት ቆይቶ ቅዱስ አቡነ እስጢፋኖስ ለኛ መታሰቢያ ይሆነን ዘንድ በቅዱሱ ጌታ በብዙው ጻማው በትንሹ እንኳን ማንም ሳይረዳው እዚያ ገድሉን ፈጽሞ ነበረ እሱም ገድሉን አሟልቶ ከንጉሥና ከመኳንንቱ የሚመጡ ሥቃዮችን አሳልፎ ሰማዕትነቱን ሠኔ ቀን ፈጸመ ያም የደብረ እምፍራዝ መጋቢ በንጉሠ ትእዛዝ እዚያ የታሰሩት ወንድሞች እና ሊጠይቃቸው የመጣ ወንድም ሰማዕትነታቸውን እዚያ በጥሩ ገድል በጌታ ሰላም ፈጸሙ ጸሎታቸው ለዘላለም ከኛ ጋራ ትሁን አሜን የዝራጐን ልጅ ብርሃነ መስቀልና ጉጐዳሌ ከተበተኑት ወንድሞች ውስጥ የአባታችንን ዐፅም ሲያፈልሱ ግድም ኬላ ላይ ተይዞ በምድረ አመዳ እስረኛ ከሆነው ከእግዚአብሔር ሰው ከገብረ ማርያም አጠገብ በአረሚ ቤት ታስሮ የነበረ አንድ ብርሃነ መስቀል ዓምደ መስቀል። ሥልጣናቸው ምን እንደሆነ አይታወቅም ግን ከብዙ የግዕዝ ምንጭ ይገኛሉ የንጉሥ የንስሐ አባት ሽመይ እና ሲመይ ከሌላ ቦታ ደግሞ ሲማይ ሽሜ የአንድ ቦታ ተለዋዋጭ ስሞች ናቸው የአባ በኪሞስ ሀገረ ስብከት ነበረ ርክርከፀክ ፐከፀ እከከኪር በርሃ ዐ ከ ፌ እ በኪ ከ ሊቀ ደብተራ ቢፋሞን እና ንቡረ እድ እስጢፋኖስ ዘሚካኤልና ገማልያል እግዚአብሔር መልክ የለውም ስላሉ በተከሰሱ ጊዜ ጉዳዩን ባየው ሸንጎ ላይ ተገኝተዋል ርክቬከርክ ር ፐከዕ ሃ ፖ ከ ኬህቄ ዐያ ከከ ከፎ ሃበ ርጋፖርራ ሃ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ከዚያ አንዱ ወንድም መምህራችን ጻድቅና ሕግ ፈጻሚ ነው እንጂ እርኩስ አይደለም አለ እሱንም አነቀው ቅዱሳኑ ሁሉም አቡነ እስጢፋኖስ ቅዱስ ነው ቅዱስ ነው ቅዱስ ነው አሉ ሊደበድቧቸው በቁጣ ተነሥባቸው ቅዱሳኑ ክርስቶስ ክርስቶስ ክርስቶስ እርዳን እያሉ ጮኹ ይኸንን ብለው ከመሬት ላይ ወደቁ እላያቸው ላይ ወጡባቸውና እንደ ዐውድማ ነዶ ብዙ ድብደባ ደበደቧቸውፁ ልብሳቸውን ቆባቸውን ጥምጥማቸውን የአንገታቸውን የማተብ ፍሬ የጃቸውን መስቀል ቀበቷቸውን በትራቸውን ሳይቀር ወሰዱባቸው ከአስኬማቸው እራፊ በቀር ምንም አላስተረፉም ከዚያ ጳጳሱን በል ንጉሥ እንዳዘዘህ አውግዝ አሉት እምቢ አለ የጳጳሱ ታላቅ ወንድሙ አባ ሚካኤል እዚያ ነበረ ከአባ ገብርኤል በፊት ጀምሮ ጳጳስ ነበረ በዚህ ቀን ነገሩን እንዲሰማ ተሸክመው አምጥተውት ነበረ ነገራቸውን ሲሰማ ጥሩ ሆኖ አገኘው ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታቸውንም ወደደ ወንድሙን አብረሃቸው ብትሞት ይሻልሃል ብሎ መከረው ከዚያ ከጳጳሱ ሎሌዎች አንዱ ደብረ ዮን የሚባለው የጳጳሱ ቃል ለማስመሰል የጳጳሱን እጅ ይዞ ወደ ላይ አነሣና እነዚህን መነኩሴዎች ክህነታቸውንም ምንኩስናቸውንም አግደናል በእንጀራም በውሐም አትቀበሏቸው የሚቀበላቸው የተወገዘ ይሁን አለ ጳጳሱ ግን ደብረ ጽዮን አለ እንጂ እኔ አንደዚህ አላልኩም አላወገዝኩም አለ ጳጳሱ አባ ገብርኤል ቅዱሳኑን ይወዳቸዋል ይቀበላቸዋልም ለመሞት ግን መንፈስ ይፈልጋል ሥጋ ግን ይደክማል እንዳለው እንደ ወንጌሉ ቃል ሆኖ አልጨከነም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ንጉሥ ጳጳሱን እስከ ዕለተ ሞቱ ተቀየመው በማንኛው ያለፈቃዱ የክህነት ሥራ ሳይቀር ያስገድደዋል ሲታመም እንኳን አያሳርፈውም በዚህ ምክንያት ጳጳሱ ያጥር ነበር እስኪሞት ድረስ እንደአጣረ ኖረ አዘራት ወደምትባል ምድር ግዞት ቅዱሳኑን ወደ ንጉጮሙ መውሰድ ጀምረው ሳይደርሱ እንዲመለሱ ትእዛዝ ሰጠ ሲመለሱ ጸሕጋ ከምትባል ሀገር ደረሱ እዚያ ሰንበትን አከበሩ በዚያች ሌሊት ሐምሌ ሀ ቀን አንዱ ወንድም ሰማዕትነቱን ፈጸመ ያም ከምድረ ምራዋ ያመጡት ገብረ ሚካኤል የሚባለው ወንድም በጌታ ሰላም አረፈ ጸሎቱና በረከቱ ከኛ ጋራ ትሁን አሜን ከዚያ መካን ሰዎች ጸድ ካህን ስለ ወንድም ገብረ ሚካኤል በሌሊት ራእይ በዚች መካን ትልቅ ኮከብ ሲወድቅ አየሁ ይህ ሰው በእርግጥ ጻድቅ ነው ስለዚህ ተገለጠልኝ አለ ቅዱሳኑን ግን ንጉሥጮ ወዳዘዘበት አዘራት ወደምትባል ምድር ወሰዷቸው እዚያች ሀገር በጽኑ ገድል በብርድ የሚለብሱትን ሁሉ ማር ጽሕጋ። ወታደሮቹ ንጉሥ እንዳዘዛቸው አደረጉ የእጃቸውንና የእግራቸውን ጫፍ ጫፉን ቄረጡና ከደጅ አውጥተው ጣሏቸው ጥራቸው ነበረ እዚያ ሰማዕትነታቸውን በጌታ ሰላም ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ይሁን ለዘለዓለምም ይጠብቀን አሜን አሜን ከዚያ ንጉሥ በጠባቂዎቹ እጅ ያሉትን የቅርቦቹንም የሩቆቹንም ከ ቦታ እንዲሰበስቧቸው አዘዘ ጸዱን ወንድም ጠባቂው ልብሱን ገፍፎ ከላዩ ላይ ከአንዲት አስኬማው በቀር ምንም ሳያስተርፍ አንገቱን ከጉልበቱ ጋራ በቀበቶው አስሮ አመጣው እሱ ግን ከቁርጦቹ ውስጥ ስለነበረ ከተሰበሰቡበት ዘንድ ሲጥለው ተቁጣጣሪው አልቀበልህም መዝ የሏላጦስን ቃል ሲጠቅስ ነው ማቴ ኤልዛቤል የእሥራኤልን ነቢያት ያስፈጀች የእስራኤል ንጉሥ የአክዓብ እቴጌ ነች ነገሥ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ አለው እዚያው ተወው አውሬዎቹ በሕይወት ያሉትን ሰዎች ከቤት ሲጎትቱ እሱን ግን ሳይነኩት እዚያው ሶስት ቀን ቆየ በጣሉት በአራተኛው ቀን እዚያው ሰማዕትነቱን በጌታ ሰላም ፈጸመ ጸሎታቸው ለዘለዓለም ከኛ ጋራ ትሁን አሜን አሜን አሜን ለመቀጣጫ በአምስት ከተሞች ተወገሩ ከዚያ ይኸ ተንኮለኛ ከልቡ ምርረት ብዛት ከቅዱሳን ቱን መርጦ ከአምስት አገሮች ወስደው በዚያ ሀገር ያሉ ሰዎች እንዲፈሩና ቅዱሳኑን እንዳይቀበሏቸው እጃቸውንና እግራቸውን ቆርጠው በድንጋይ እንዲወግሯቸው አዘዘ። አላቸው ማንነታቸውን ሲነግሩት የቅዱሱ ልጆች መሆናቸውን ዐወቀ ከዚያ በቁጣ ተነሥቶ ከሎሌው ጋራ እስኪደክሙ ድረስ በበትርና በዱላ ደበደባቸው ይኸንን የደረሰበትን ሁሉ ታጋሽ ወንድም እንደገና ብትር አንሥቶ ራሱን ሲመታው ደሙ በላዩ ላይ ፈሰሰ ሴትየዋ ሰጥታቸው የያዙትን ያላቸውን ሁሉ ምንም ሳያስተርፍ ወሰደባቸው ቁጣውን አስተንፍሶ እንደወደቁ ትቷቸው ሄደ ወንድሞቻቸውን ሁሉ እንደዚሁ ያደርጉባቸዋል የቅዱሱ ልጆች መሆናቸውን ሲያውቁ በመንደርም ሆነ በመንገድ ወይም በዱር ይደበድቧቸዋል ከብዙ ችግር ላይ ይጥሏቸዋል እንደከብት ዕራቁታቸውን እስኪሆኑ ድረስ ልብሳቸውንና ገንዘባቸውን ይወስዱባቸዋል አንዳንድ ቀን ወደ ሀገረ ገዢዎቻቸውና ወደ ታላላቆቻቸው ወስደው በብዙ ጭንቅ ይነዘንዚቸዋል ሰዎች እንደ ገዢያቸው ይሆናሉ ተብሉ እንደተጻፈው ገዢው የሚፈልገው እንዲህ እንዲሆን ነው መዝ ሲራ ለልመና ንጉሠ ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ለጸሎትና ለመተረብ ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲመጡ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ እንዳትሳሳቱና እንዳትደናቀፉ ይኸንን ነግሪያችኋለሁ ከምኩራባቸው ያስወጧችኋል ነገር ግን የገደላችሁ ሁሉ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ያገባ ይመስለዋል ያለው ቃል ይፈጸምባቸው ዘንድና ስለ ስሜ በሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ ያለው ይደርስባቸው ዘንድ እየሰደቡና እያሸሟጠጡ ወደ ውጪ ያሶጧቸዋል ይኸ የሚደርስባቸው ስለዚህ ነው ያ የሚደርስበትን ሁሉ ታጋሽ ወንድምም ከጓደኛው ጋራ በአስጨናቂ ድካም ፍርድ ለሚጸድቀው እስኪመጣ ድረስ ግፋቸውን ተሸክመው ለተገፉ የሚበቀል እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ መኖሪያቸው ተመለሱ የመነኮሳት ሕጋቸው እንደዚህ ነው በየቀኑ ሞትን ይቅመስ ስቅላቱንም ይታገሥ ይላልና በእንደዚህ ያለ ገድል ብዙ ዓመት ቆይተው በጌታ ሰላም ምስክርነታቸውን እዚያው ፈጸሙ ቀሩጥራቸው ነው ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን ያ የደረሰበትን ሁሉ ታጋሽ ወንድም ከአንዲት መነኩሲት ጋራ ቀርቶ ነበረ ከሕመም መኝታቸው ተነሥተው ለመውጣትና ለመግባት እስኪያቅታቸው ድረስ ጅዙ ቀን ያህል ከትልቅ በሽታ ወደቁ ከዚያ እግዚአብሔር ከወንድሞቻቸው ዘንድ እርዳታ አመጣላቸው የመጡት ይላላኳቸው ጀመረ ከዳኑም በኋላ ወደ ወንድሞች ማኅበር ወሰዷቸው እሷም ገድሏን ከማኅበርተኞቿ ጋራ በአበው ሕግ በመልካም ጻማና በጣፋጭ ገድል ፈጸመች ከሰዎችና ከሰይጣናት የመጣ ብዙ ሥቃይ አሳልፋ በጌታ ሰላም አረፈች ጸሎቷና በረከቷ ለዘለዓለም ከኛ ጋራ ይሁን አሜን ያ ወንድም ግን ከዚህ ተንኮለኛ ቀጥሎ ከሚመጣው ሌላ ንጉሥ ገና ብዙ ቅጣት ስላለበት እስከ ጊዜው ድረስ እግዚአብሔር እየረዳው ኖረ ባለጋራን ለማጥቃት የጠቀመ ዓዋጅ ከዚያ ይኸ ተንኮለኛ በቅዱሳኑ ላይ ሊያጠብባቸው እና የሚቀበሏቸውም ፍርሃት እንዲያድርባቸው አስቦ እንዲህ ሲል ዓዋጅ እንዲያስለፍፍ አዘዘ እነሆ ደቂቀ እስጢፋኖስ የተገኙበት ቤቱ ይዘረፍ ገንዘቡ ይውደም የቀበሌው ርስትም ለባዳ ይሁን በጠዋትም ሆነ በምሽት ወደኛ ሲያመጧቸው እነሱን ሳይገድሉ መሥዋዕት አያሳርጉ ይኸንን ሳታደርጉ ብታሳርጉ መሥዋዕታችሁ የረከሰ ይሁን እኔም ባሳደርግ መንግሥታችን ለባዳ ይሁን ይኸንን ሲል ጊዜ እውነትን ለሚፃረሩ ሰዎች ሰበብ ሆናቸው ጉዳይ ያስጨነቃቸው ሁሉ ማሳበቢያ እነሱን ይፈልጉ ነበረ የንጉሥን ፊት ዮሐ ማር ። ዐፖዐያ ሪው ሂ » ሀፖያ መዕጋዝሽ ርርዐ ህ ከ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ማግኘት ሲያቅታቸው እነሱን ይፈልጋሉ በርስት ክፍያም ሆነ ወይም በሌላ ነገር አንዱ በሌላው ላይ ሲያይል ማሸነፊያ እነሱን ይፈልጋል መኳንንት ከመኳንንት ጋራ ሹም ከሹም ጋራ ባሪያ ከነፃ ጋራ ባሪያ ከጌታው ጋራ ሎሌ ከአገረ ገዢ ጋራ ዲያቆኖች ከቄሶች ጋራ ደኻ ከሀብታም ጋራ ሲጣሉ እነሱን ይፈልጋሉ በተለየም በየገዳማቱ ያሉ መነኩሴዎች ገዳማቸው እንዲጸናላቸው ሲሉ ደቂቀ እስጢፋኖስ ያሉበትን ሲያውቁ ደም ለማፍሰስ ይሮጣሉ ምግብ አልጫ ሲሆን በጨው ያጣፍጡታል እንደዚሁ ለጉዳያቸው ጨው ሆኑላቸው ከዚያ ፍሬ ሊባኖስ የሚሉት ከካህናተ ደብተራ የሆነ የሰይጣን መልእክተኛ ተነሣ የብሔሩ ስም ዓለት ነው የዚህ የሰይጣን መልእክተኛ ዘመድ የሆነ ሰው በዚያ ብሔር ተቀብሎ ያስቀመጣቸው ቅዱሳን ነበሩ ዘመዱ በነገር ያይልበት ነበረ ከሱ ጋራ ሲጣላ ጊዜ ቅዱሳኑን እንዲይዝ መልእክተኞች እንዲሰጠው ንጉሥን ጠየቀው መልእክተኞች ሰጥተውት ሄደ ቅዱሳኑ ካሉበት መጥቶ ቱን ያዛቸውና ከንጉሥ ዘንድ አመጣቸው ንጉሥ ያን ጊዜ በመንግሥቱ መካን በአእጉባ ነበረ ከንጉሥ ፊት አቆሟቸው ለንጉሥ ስገዱ የመምህራችሁንም ስም ስደቡ አሏቸው ቅዱሳኑ እኛ አንሰግድም መምህራችንንም አንሰድብም ቅዱስ ነው አሉ ንጉሥ የቃላቸውን ፍጻሜ ሲያውቅ ወዲያው እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን እንዲቄርጧቸው በድንጋይም እንዲወግሯቸው አዘዘ ወታደሮቹ እንዳዘዛቸው አደረጉ ሰማዕትነታቸውን እዚያው በጌታ ሰላም ፈጸሙ ጸሎታቸው ለዘለዓለም ከኛ ጋራ ትሁን አሜን አሜን የምድረ ፀጋም ኢትዮጵያውያን ይኸ ተንኮለኛ ቅዱሳኑ በምድሩ እንዳይኖሩ ባጠበበባቸው ጊዜ እስከ ብሔሩ ዳርቻ ነዋሪዎቹ ቤታቸው ከዛፍ ላይ ከሆነው እስከ ምድረ ፀጋም ግራ ምድር ደረሱ። ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው አመሰገኑት እዚያ ኖሩ ከተበተኑበትም ተሰባሰቡ ከዚያ ሀገር ሰዎች ከወንዱም ከሴቱም ብዙዎችን ወደ ትምህርታቸው መለሱ እንዲያውም ከዓለም ወጥተው መንኩሰው ሰማዕት እስከ መሆን ደረሱ እግዚአብሔር ያንን ሀገር ለቅዱሳኑ በሚፈልጉት ሁሉ ከፍቶላቸው ቤተ ክርስቲያን እስከ መትከል ደረሱ የወንድሞቻቸውንም ተዝካር አወጡ ደግሞ ያ ተንኮለኛ እጉበ በምትባለው ምድር በነበረበት ጊዜ ቅዱሳኑን እንደታሰሩ ወደ እሱ አመጧቸው መምጣታቸውን ለንጉሥ ነገሩት እሱም አጠገቡ እንዲያኖሯቸው አዘዘ እዚያ ያባቶቻቸውን ሥርዓት እንደጠበቁ በትልቅ በሽታ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ ቀሩቱጥራቸው ቿ ነው ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን ገድለ መርቆርዮስ ከዘመን በኋላ ቅዱሳኑ በስደት በምድረ ቀወት ከዋሻ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ የሰይጣን መልእክተኛ ቅዱሳኑን በገዳማቸው ካስቀመጧቸው ሰዎች ጋራ ሲጣላ ጊዜ ከሀገሩ ሹም ዘንድ ሄዶ ቅዱሳኑ ያሉበትንእነዚህ እተጣላቸው ሰዎች ገዳም ውስጥ መኖራቸውንነገረው አገረ ገዢው ሎሌውን ሰጥቶት ሊያመጣቸው ሄደ ቅዱሳኑን ያዛቸው ወስዶ ከንጉሥ አደባባይ ሲያደርሳቸው ከሰቀላው ሰፈር አቆሟቸው ለንጉሥ እንዲሰግዱ መምህራቸውንም እንዲሰድቡ አዘዚቸው ዱ መርቆርዮስ የሚባለው ወንድም እኛ አንሰግድም መምህራችንንም አንሰድብም ቅዱስ ነው አለ ይኸንን ወንድም ከንጉሥ ፊት ሲያቆሙት እና ሲቀጡት ይኸ አምስተኛው ነው መጀመሪያ ያባታችንን ዐፅም ሲያፈልስ በግድም ኬላ ላይ የተያዘ ጊዜ ገርፈው ለብቻው አንፈር ከምትባል ሀገር ወስደውት ነበረ ሁለተኛ ጋስ ከምትባል የአረሚዎች ብሔር ወስደውት ነበረ ሶስተኛ ሲያቆሙት ቅጣቱ ብዙ ነበረ አራተኛ አቁመውት ቅዱሳኑን አባታችሁ የት ነው ባሏቸው ጊዜ ለንጉሥ ሎሌዎች መምህራችን የጌታን ሥቃይ ተካፍሏል ሲላቸው አፍንጫውንና መላሱን ቄርጠው ቋንጃውን አውጥተውበት ነበረ እነሆ አሁን አምስተኛው ጊዜ ነው አልሰግድም አልሰድብም ሲል ጊዜ ይህ ተንኮለኛ ዓይኑን እንዲያወጡት አዘዘ። ቃውሀያፖ ሪድ ዥ ዐይ ህረፖቋ ጩዕኦጋ ኮ መጽሐፉ ላይ ገጽ የጻፈበት ሰው እዚህ ላይ ቀጥር ዘለለ ማለት ነበረበት ቨ ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ከዚያ ወደነዚያ መነኩሲቶች መለስ ብሎ እንዲህ ሲል ምዕዳን አሰማቸው ጨክኑ ልባችሁ ይጠንክር እንዳትክዱ ዛሬ የእሳቷን ባሕር የምንሻገርባት ቀን ናት ዛሬ ተስፋችንን የምናገኝባት ቀን ናት ከዚያ ወታደሮቹ ንጉሥ እንዳዘዛቸው አደረጉ አፍንጫቸውን ከከንፈራቸው ጋራ ቄረጡትና በድንጋይ ወገሯቸው እዚያ መስከረም ቀን ሰማዕትነታቸውን በጌታ ሰላም ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን የምድረ ፀጋም ዘመቻ ከዘመኖች በኋላ ቅዱሳኑ ሙደዌ ከምትባል ምድረ ፀጋም የግራ ምድር በነበሩበት ጊዜ በንጉሠ ትእዛዝ በዚያች አገር ላይ ጦር መጣ ነ የንጉሥ ወታደሮች ቅዱሳኑን እዚያ አገቿቸው ያዚቸው ደበደቧቸውና በትላልቅ ማነቆ አስረዋቸው ወደ ንጉሠ ወሰዷቸው ሲጓዙ ከሚያድሩበት ሲደርሱ ወገባቸውን እጃቸውን እግራቸውን በገመድ ያስሯቸዋል ከንጉሠ እስኪያደርሷቸው ድረስ እንደዚህ ያደርጉባቸው ነበረ በዓይናቸው ፊት ምሕረት የሌላቸው መራር ሕዝብ ናቸው ሲደርሱ ይዘው ከአመጡት ከአንድ ደስክ ጋራ ከንጉሥ ፊት ለፊት አቆሟቸው ንጉሥ ይሰግዱ እንደሆነ መምህራቸውንም ይሰድቡ እንደሆነ ጠየቀ። የሚሸነፍ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ከነሱ ውስጥ ቿቱ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን አሜን የተረፉትም እስከ ጊዜው ድረስ በእስር ቤት ኖሩ የግራ ሰዎች ወረራ የንጉሥ ሎሌ አባትህ የት ነው ያለው ጊዜ መምህራችን የጌታን ሥቃይ ተካፍሏል ያለው መርቆርዮስ የሚባለው ወንድም ገድሉን ፈጽሞ በወንድሞች ማኅበር ሳለ የግራ ሰዎች ያስለመዱት ጦራቸው በሀገሪቱ ላይ መጣ ቅዱሳኑን እዚያ አገጂቸው ያ ወንድም በግራ ሰዎች ጦር ሰማዕትነቱን ፈጸመ ወንድሞችም ከሱ ጋራ ሰማዕትነታቸውን በታኅሣሥ ወር በሀ ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን በዚያ ዓመት ቅዱሳኑ ሰማዕትነታቸውን የፈጸሙት በነዚያ የግራ ሰዎች ጦር ነው ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን ጉዳት ያደረሰው ከዳተኛ ወንድም ቅዱሳኑ በዚያች ቆገት በምትባለው ሀገር ሳሉ ወንድም እንደ ወንድሞቹ ንጹሕ ሥርዓት መጠበቅ ባለመቻል ከነሱ ተለየ እንዲያውም ሊከሳቸው ወደ ንጉሥ ሄደ በጠባዩ የሚተባበረው ጓደኛ አገኘ። አለው ከዚያ ንጉሠ እንዲገርፉት በቁጣ አዘዘ ታላቅ ግርፊያ ገረፉት ደግሞ ንጉሥ በእስር ቤት ካሉት ቅዱሳን ሌላ ሰው እንዲያመጡለት አዘዘ ወታደሮቹ ኢሳይያስ የሚባል ወንድም እያጣደፉ አመጡት ያ ወንድም የንጉሥን ወታደሮች እናንተ የእውነት ጠላቶች ዐውቀናችኋል ልማዳችሁ ነፍስ መግደል ነው አላቸው እየደበደቡ ከንጉሥ አደረሱት እሱንም እንዲገርፉት ንጉሥ አዘዘ ታላቅ ግርፊያ ገረፉት በዚያች ዕለት ኅዳር ቀን ሰማዕትነቱን ፈጸመ ሌላው በማግሥቱ በጳ ቀን አረፈ የታሰሩትም ሰማዕትነታቸውን በዚያው ቀን ፈጸሙ ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን አሜን እስረኛ ጎብፒዎቹ ታሰሩ ወንድሞች በእስር ቤት ያሉትን ጐብኝተው ሁኔታቸው እንዴት እንደሆነ እንዲያውቁ ቅዱሳኑ ወንድሞች ልከው ኖሮ ከንጉሥ ሰፈር ውጪ ደርሰው ስለ ወንድሞች ነገር ሲያጠያይቁ የንጉሥ ተላላኪዎች እነሱንና ከንጉሥ ሰፈር የነበሩትን ሌሎቹን ወንድሞች ይዘው ከእስር ቤት አስገቧቸው እጃቸውንና እግራቸውን አሰሯቸው እስከ ጊዜው እዚያ ኖሩ ከዚያ ከብዙ ጭንቅ ምግብ ከማጣት ከመራቆት ጋራ ትልቅ በሽታ ወደቀባቸው በዚህ ሥቃይ እዚያው ገድላቸውን ፈጸሙ ጸሎታቸውና በረከታቸው ከኛ ጋራ ይሁን አሜን የተረፉትም በዚያ ጭንቅ እስከ ጊዜው ኖሩ ያላለቀ የብሔረ በሊ የግዞት ጉዞሰይፌን አታደንዝብኝ ከብዙ ዘመን በኋላ ንጉሠ በእስር ቤት ያሉትን ቅዱሳን አውጥተው ወደ ብሔረ በሊ እንዲወስዷቸው አዘዘ ጥር ቀን ወደ ማታ ግድም አወጧቸው በበሽታ ላይ ያሉትን መሄድ እንደማይቻላቸው ሲያዩ ከእስር ቤት አውጥተው ከአረሚ ቤት ጣሏቸው መሄድ የሚችሉትን በዚያች ሌሊት ወደ ታዘዙበት ወሰዷቸው ሲጓዙ ቀጸም ከምትባል አገር ደረሱ ለኢባ ቅርብ ናት የድ ሰዓት ጉዞ ናት እዚያ አደሩ ማቴ ያዕ ለደብረ ብርሃን ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ከዚያ ያንን ተንኮለኛ በቅዱሳኑ ላይ ክፋት እንዲሠራባቸው ሐዘን አንቀጠቀጠው በማግስቱ በጠዋት በጋላቢ ፈረስ የተቀመጠ መልእክተኛ እንዲህ ሲል ላከ እሺ ይሉህ እንደሆነ ለንጉሥ ስገዱ በላቸው እምቢ ካሉህ ። ይላል አሁንም ከመናገር መሥራት ከመሠዋት መስማት ይሻላል የነሱም ዋጋቸው በእግዚአብሔር ዘንድ ነው እኛም በረከታቸው በአምላካችንና በአምላካቸው በእግዚአብሔር እንዲደርሰን ለዘለዓለም ተስፋ እናደርጋለን አሜን አሜን ከዚያ በዚያው ዓመት እንደገና በእግዚአብሔር ቃል በትልቅ በሽታ ጥሪ መጣላቸው በዚያ ዘመን ከግንቦት ጀምሮ እስከ ኅዳር ድረስ ሰማዕትነታቸውን ወንዱም ሴቱም ቱ በመልካም ገድል ያባታቸውን ሥርዓትና ውሳኔዎች በመጠበቅ ፈጸሙ አንዳንዶቹ ከክፉ አጋንንትና የንጉሠ የሰይጣን መልእክተኞች ከሆኑት ከታወቁት ሠራዊቱ ብዙ ሥቃይ ያሳለፉ መንፈሳውያን ሽማግሌዎች ነበሩ አንዳንዶቹ በእግዚአብሔር ቃል የሚተዳደሩ ጽኑ ጎልማሶች ነበሩ አንዳንዶቹ ንጹሖች ሕፃናትና ደስተኛ ድንግሎች ነበሩ አንዳንዶቹ የእድሜያቸውን ማለቂያ የተናገሩ የበቁ ነበሩ ሹም ተስፋነ ክርስቶስ ጠላት ሆነ በዚህ በሽታ በነበሩበት ጊዜ ተስፋነ ክርስቶስ የሚሉት የዚያ ሀገር ሹም ተነሣባቸው የቅዱሳኑ ጠላት ሆነ በዚያ ዓመት ከንጉጮ ፊት ሲመለስ ዮሐ ምናልባት ነር ለሸ ወገርዐዘ ሀዐዖርፎ ርርር ሀ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ከጻድቃኑ ጋራ ተጣላ ቤቶቻቸውን አቃጠለ ገንዘባቸውን ወስዶ ከሀገሩ አባረራቸው እነሱም በዚያ በክረምት ዝናም በሌሊት ብርድ በበሽታ ሲንከራተቱ በጌታ ሰላም ገድላቸውን ፈጸሙ ጸሎታቸውና በረከታቸው ከኛ ጋራ ትሁን ለዘለዓለም ትጠብቀን አሜን አሜን አባ ብእሴ ሰላምና አባ ሳሙኤል ጠሳት ሆኑ በዚያው ዘመን በየአድባራቱ ያሉ ብዙ መነኮሳት ተነሥተው ከንጉሥ ዘንድ ሄዱና ደቂቀ እስጢፋኖስ የመንግሥትህን ብሔሮች ሞሏቸው ብዙዎችንም ወደ ትምህርታቸው መለሱ አሁንም የምታደርገውን ዕወቅ ጌታችን ንጉሥ ሆይ ሲሉ ቅዱሳኑን ከሰሷቸው ይኸንን ሰምቶ ዝም አለ ደግሞ ሌሎች መነኩሴዎች ተነሠ የአንዱ ስም ብእሴ ሰላም የሰላም ሰው ሲሆን የሥቃይና የደም ሰው እንጂ እንደ ስሙ ሰላማዊ አይደለም እግዚአብሔርን አይፈራ ሰውን አያፍር ሁለተኛው ሳሙኤል ይባላል ለንጉጮ ጌታችን ንጉሥ ሆይ ደቂቀ እስጢፋኖስ ያሉበትን እኛ እናውቃለን አሁንም የምታደርገውን ዕወቅ አሉት እነዚህ መነኩሴዎች ከብዙ ተላላኪዎች ጋራ ወደ ውድ ። አላቸው ፅ ወንድም ቅስናችንን ዛሬ ከእናንተ እንቀበላለን አለ ከዚያ ያ መነኩሴ ቅስናህ ዛሬ ከአንድ ወታደር ጦር ይቺን ጦር ማግኘት ነው አለ ወንድም ልማዳችሁ ደም ማፍሰስ እንደሆነ ዐውቀናል እናንተ ገዳዮች እኛ ስለ ክርስቶስ ሟቾች ነን አለ ያ መነኩሴ ተቆጣና እስጢፋ እርኩስ ነው ብላችሁ መምህራችሁን ስደቡ አላቸው ቅዱሳኑ በየቃላቸው አቡነ እስጢፋኖስ ቅዱስና ጻድቅ ብርሃን ገላጭ ነው አቡነ እስጢፋኖስ ቅዱስ ጻድቅ ጠላት አሸናፊ ነው አቡነ እስጢፋኖስ ቅዱስ ጻድቅ የክርስቶስ ተከታይ ነው አሉ ከዚያ እንደ ንጉሥ ቃል እንዲገድሏቸው አዘዘ እዚያ በዕለተ እሑድ በጦር ገደሏቸው ከነሱ ውስጥ ከነጓደኛዋ ከነሱ ጋራ ያመጧት አንዲት መነኩሲት ቅዱሳኑን ሲወጓቸው ስታይ እላያቸው ላይ ወድቃ ልብሳቸውን ያዘች እሷንም ጓደኛዋንም እዚያው ወጓቸው በምድረ አምለከ የገደሏቸው ቀጥራቸው ነው በጐንደት የተገደሉት ሰማዕትነታቸውን በጌታ ሰላም የተቀዳጁት በማግስቱ መጋቢት ቀን ነው ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ይሁን ለዘለዓለም ይጠብቀንም አሜን ከዚያ ልብሳቸውን ቆባቸውን ቀበቷቸውን አስኬማቸውን ወሰዱባቸው በሬሳቸው ላይ ካለው ልብስ አንዳችም አላስቀሩም ዕንጨት ከምረው እሳት አነደዱና ልብሶቹን ጨመሩበት የቅዱሳኑን ሬሳና እሳቱን እየዞሩ በከበሮና በክራር የወንጀል ዜማ አዜሙ በማግስቱ በጐንደትም እንደዚሁ አደረጉ ጌታ እግዚአብሔር ለኃጢአተኞች ጉድጓድ እስኪቄፍርና ለሚጸድቅ ፍርድ እስከመጣ ድረስ ታግሷል በምድረ ቆገት የተያዙ ወንድሞች በዚያ ዕለት እሑድ ቀን በምድረ ቆገት ወንድሞች ያዙ ከተደበቁበት አወጧቸው በፊት ላኖራቸው ሰው እንዲህ ብለው ነገሩት እዚህ አንተ ዘንድ ቅዱሳን አግኝተናል አሉት ሲሰማ የቅዱሱ ልጆች የተገኙበት ቤቱ እንዲመዘበር እሱንም እንዲገድሉት ንጉሥ ዐዋጅ እንዳስለፈፈ ስለሚያውቅ ፈራ ስለዚህ ራሱ ወደ አገረ ገዢው ወስዶ ለሞት አስረከበው አገረ ገዢው ለንጉጮ ይሰግዱ መምህራቸውንም ይሰድቡ እንደሁ እንደ ልማዱ ጠየቃቸው ሳሙኤል የሚባለውን በፊት መስቀለ ሰላም ባለ ጊዜ የንጉሥ ሎሌ ለእስላም መስቀል አለ ብሏቸው ይኸንን ወንድም አሳብቆበት በዚህ ምክንያት ብዙ ቀጥቶት ነበረ በተንኮለኛ እጅ መድኃኒት በመጠጣትና በድብደባ ብዙ የቀጣው ወንድም ነው ያቺ ዕለትም እኛ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ በቀር ለሌላ አንሰግድም መምህራችንንም ቅዱስና ጻድቅ ነው አንሰድብም አሉ ከዚያ አገረ ገዢው በጦር እንዲወጓቸው አዘዘ ወታደሮቹ ወጓቸውና እዚያ በምድረ ጉንደት ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ የምስክርነት መቀዳጀታቸው የሆነው በመጋቢት ወር በ ቀን በጌታ ሰላም ነው ጸሎታቸው ከኛ ጋራ ትሁን አሜን ከሣቴ ብርሃን መዝ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ልብሳቸውንም በወንድሞቻቸው ላይ እንዳደረጉት በእሳት አቃጠሉባቸው ጸድቅ በቀልን ባየ ጊዜ ደስ ይለዋል በኃጢአተኛ ደምም እጁን ይታጠባል እንደተባለው የሚበቀልበት ጊዜ ይመጣ የለምን። ወደ ሌላም ወስዶት ክፉ ሞት ሞተ አባ ዘታኦስ ዘሰርማት ያመጡት ጉዳት ቅዱሳኑ በጐንደት በተገደሉ በ ዓመት ዘታኦስ የሚባል መነኩሴ የሰርማት መምህር ስለ ቅዱሳኑ የውሸት ደብዳቤ ፎ ከንጉሠ ዘንድ አመጣ ንጉሠ የደብዳቤዋን ቃል ሰምቶ ዓምዱ ለሚባለው ለፈጸጋር አገረ ገዢ በሀገሩ በግዛቱ ያሉትን ቅዱሳን እንዲያመጣቸው ነገረው እሱም እነሱ ዘንድ ያሉትን ቅዱሳን እንዲሰጧቸው የንጉሥን ተላላኪዎች ለሀገሩ ሹማምንት ላከላቸው የንጉሥ ተላላኪዎች ከነዚያ ሹማምንት ጋራ በየሀገሩ ሄዱ ዘታኦስ የሚባለው መነኩሴም አብሯቸው ሆኖ ተላላኪዎቹን ወደ ቅዱሳኑ ወሰዳቸው ቅዱሳኑ በስደት በሀገሩ ዱር ይኖሩ ነበረ እንኮይ ናኬ ኮሽም ጣንጦ ቀምጠሮ የሚባሉ የዛፍ ፍሬዎችና ከስራ ስርም ቀጠቤሉ ኡስስ የሚባሉ ከዛፍ ቅጠልም ቀረም የሚባል ከምድር አትክልትና ከእህልም ሲያገኙ ይበሉ ነበረ ከሰው ሲደርሱም ወንዱንም ሴቱንም ያስተምሩ ነበረ እነሱም ሲያዳምጧቸው ሕሊናቸውን ሰቅለው ነበረ ከዓለማቸው እየወጡም ከነሱ ጋራ ይደባለቁም ስለነበረ ብዙዎች ሆኑ ሲዲ የሚባለው የዚያ ሀገር ሹም በዚህ ምክንያት ቂም ነበረው እነዚያን የንጉሥ ተላላኪዎች ምክንያት አግኝቶ በውሾች እና በሰዎች አደናቸው ከዱር ሰበሰባቸው በማነቆ እንደታሰሩ ወስደው ከንጉሥ አደባባይ አመጧቸው ንጉሠ በዚያን ጊዜ ከደብረ ብርሃን ነበረፁ ለንጉሠ ነገሩት ንጉሥ ወደ ሰፈሩ ውስጥ በስተግራው የነፋስ መምጫና የብርድ መውረጃ በሆነችው በመጋራዳ በኩል እንዲያስገቧቸው አዘዘ ወታደሮቹ እንዳዘዛቸው አደረጉ የካቲት ቀን አስገቧቸው እህልም ውሐም ሳይሰጧቸው ፀ ቀን ተቀመጡ ከዚያ በእህልና በውሐ የሚረዷቸው ወንድሞች መጡ እሱም ቢሆን አተርና ምስር ሌላም እህል ነው አንዳንድ ቀን ሲበዛ አንድ እጅ ሙሉ ይደርሳቸዋል ያነሰ ቀን ለ ለ ያዳርሱታል እንጀራ ሲያገኙ አንዳንድ ቀን አንዱ ለአራት ይደርሳቸዋል አንዳንድ ቀን አንዱ ለቱ ይደርሳቸዋል ውሐም እንደዚሁ ነው እነዚያ የሚረዷቸው ወንድሞች ከእስር ቤት የሚያገቡላቸው ራሳቸው አይደሉም ምክንያቱም ጠባቂዎቹ ማንንም ሰው ወደ ቅዱሳኑ እንዳያስገቡ ከነሱም ማንም እንዳይወጣ ንጉሥ አዚቸው ነበረ ስለዚህ የሚረዷቸው ወንድሞች መግባት አይችሉም ነበረ ዘበኞቹ እዚህ በጐንደን ተብሎ ነው የተጻፈው አሁንም በጐንደን ብሎታል ትክክሉ የቱ እንደሆነ አጠራጠረ ልከፀዉ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ እንዲያገቡላቸው ዋጋ ይከፍሏቸው ነበረ ዘበኞቹ ተቀብለው ያገቡላቸዋል እነሱን ግን እንዲገቡ አይፈቅዱላቸውም ስለዚህ ከምእመናንም በእህልና በውሐ የሚረዷቸው ነበሩ ንጉሥ ይኸንን ከአሳባቂዎች ሰምቶ ዘበኞቹን እንዲህ ሲል አዘዘ እኔ በቀጣሁት ሰው ላይ ደግ የሚሠራ ሰው ማነው። እነሱም እንደዚሁ እርስ በራሳቸው ምዕዳን ይሰማማሉ ጸዱ ሌላውን የአንጾክያን የአርመንያን ሰማዕት የሩን ማቴ ማቴ መዝ መዝ ራእ ራእ ዘርአ ያዕቆብ ሴቲቷን ማርያም ናት ነው የሚለው ርክቬፎከ ሪ ገዐዐቋሟ ዐ ይዞዖሪርዐያ ረቋ ዐፅ ዐ ያድሀቨዐህፀ ዐገፀዘሀፀ ርክብናፀዘፀ ሥርር በ ዐዐ ሉቃ ዮሐ የፈጃቸው የፋርስ ንጉሥ ነው ሰማዕትነታቸው የሚከበረው ሚያዝያ ቀን ሲሆን የገድላቸው ምንባብም ለዚሁ ቀን ከስንክሳሩ ተመዝግቧል ጐጥራቸው ነው ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ወታደሮች የናግራን የቀደሟቸውን ወንድሞችን ሰማዕትነት ያስታውስ ነበረ መነኩሲቶቹንም እንደዚሁ ምዕዳን ያሰሟቸው በተግሣጽም ያጠነክሯቸው ነበረ የንጉሠ የመጨረሻ ሙከራ ንጉሥ ልብሳቸውን በገፈፈ በአራተኛው ቀን በብዙ ነገር እንዲደልሏቸው ዐዋቂዎችና አስተዋዮች ላከባቸው ወደነሱ መጡ ቅዱሳኑ ግን ምግብ አጥተው ከልብስ ተራጐተው እዚያ ወድቀዋል እያንዳንዳቸውን በብዙ ልመናና ለምትጠፋው የሥጋ ሕይወት ተስፋ በመስጠት አባበሏቸው ቅዱሳኑ ግን ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም የሚለውን የመጽሐፍ ቃል እያስታወሱ በአምላካቸው ኀይል ጠነከሩ አባባዮቹ ሄዱ ቅዱሳኑም የአምላካቸውን እርዳታ ተስፋ በማድረግ በብርድ በመራቆት በብዙ ገድል እዚያው ኖሩ በአንዳንዶቹ ሲያፌዙባቸው እጆሯቸው ውስጥ ጉንዳን ይጨምሩባቸዋል አንዳንዶቹን በድንጋይ በብትር በጥፊ ይመቷቸዋል ደግሞ ልንዘረዝራቸው ያልቻልነው ብዙ ሥቃዮች አሉ አንዳንዶቹ ሣር እስከ መብላት ደርሰዋል ይኸንን ሁሉ ሰማዕትነታቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ታግሠዋል ከዚያ መጋረዶ ባገቧቸው በድፎጸ ቀን ከንጉሥ ፊት አቆሟቸው በብዙ ነገር ተሟገታቸው በማግሥቱ ልብሳቸውን እንዲገፏቸው አዘዘ ልብሳቸውን በገፈፏቸው በአራተኛው ቀን አባባዮች ላከባቸው በአባበሏቸው በሶስተኛው ቀን ንጉሥ ጉባኤ ጠራ ቅዱሳኑን ከንጉሥ ፊት እንዲያቆሟቸው አዘዘ በፊት በሌላ ምድሮች በገሰምቤ ያኖራቸውንም እንዲያመጧቸው አዘዘ ወንድሞቻቸውን ሲረዱ ይዘው ያን ዕለት እስር ቤት ያገቧቸውን ከከተማው ውጪ ያሉትን በማጋረዶ ውስጥ ያሉትን በመድኃኒት ቤት ያሉትን ሁሉንም በአንድነት ሰብስበው ወንዱንም ሴቱንም እንደ ከብት በአንድ በኩል እራቁታቸውን ከፊቱ አቆሟቸው ያቺንም የታጠቋትን ገፈፏቸው ወታደሮቹ እነዚህ ለንጉሥ በመስገድ የማይገዙ እርኩሶች ናቸው እያሉ በብዙው ይሰድቧቸውና ያንጓጥጧቸው ይተፉባቸው ራሳቸውን ይኩረኩሟቸው በአንካሴና በጦር ይጓጉጐጧቸው ከምድር ላይ ይወቋቸው ነበር ከዚያ ንጉሥ እንዳስለመደው ይሰግዱለት እንደሆነ የመምህራቸውን ስም ይሰድቡ እንደሆነ ለመጠየቅ ላከባቸው ይኸንኑ ነገሯቸው ቅዱሳኑ እነዚህ ሁሉ ሥቃዮች የደረሱብን ለምን ሆነና ነው። እነሱም ከኛ ጋራ ለመሞት ከጨከንክ ጥሩ ነው እንዳልከው ይሁን አሉት ምዕዳን እያሰሙት በዚያ ገዳም አንድ ዓመት ኖረ ከዚያ ሰይጣን ከፍ ከፍ ብሎ ምአድ በምትባለው ደብር ያሉትን መነኮሳት አስነሣቸውር መጥተው ያዙትና ወደ ደብራቸውም ወሰዱት ለንጉሥ እንዲሰግድና የዚህን የቅዱስ አባታችንን ስም እንዲሰድብ ጠየቁት እኔ የቅዱሱን ስም አልሰድብም ለንጉሥራም አልሰግድም አልታዘዘልኝም አላቸው እንደሚገድሉት በብዙ የሚያስፈራ ነገር አስፈራሩት እሱ ግን በሕግ ከሐዲዎች ሞገድ የማይነቃነቅ በሃይማኖት የአለት ድንጋይ ላይ የተመሠረተ ስለነበረ ነገራቸውን ከምንም አልቄጠረውም ሲከራከሩትም የእግዚአብሔር መንፈስ በላዩ ስላለ በተናገሩት ሁሉ ያሸንፋቸው ነበረ ከዚያ መሸንገል ሲያቅታቸው ስለፈሩትና ጠባዩን ስላወቁ ከገዳሙ መለሱት ከዚያ ሰዎች ተከታዮች ተወለዱለትና ብዙዎች ሆኑ የመጡትን ሁሉ የጽድቅ ሥራ መሥራት ከፈለጋችሁ ወደነዚያ ቅዱሳን ወደ ደቂቀ እስጢፋኖስ ሂዱ እያለ ምዕዳን ያሰማቸው ነበረ እነሱም ቃሉን እየሰሙ ምክሩንም እየተቀበሉ ይመጣሉ በትምህርቱ የዳኑና ከሕይወት በር የደረሱ ብዙዎች ናቸው ሲሞት አብሮት ለነበረው ሰው አሁንም ልጄ የምነግርህን ስማኝ እነሆ ወደ አምላኬ መሄዴ ነው አንተም ነፍስህን ጠብቅ ከእነዚህ ከቅዱሳን ከደቂቀ እስጢፋኖስ ዘንድ በቀር ከሌሎች ደብሮች መኖር አትፈልግ አለው ከዚያ ሰማዕትነቱን እዚያ በ ወር በጌታ ሰላም ፈጸመ ጸሎቱ ለዘለዓለም ከኛ ጋራ ትሁን አሜን አሜን ልከዉ ህበሃ ህህ ሀ ገድለ አበው ወአኀው ያም ሰው ከቅዱሳኑ ጋራ ተደባልቆ አብሯቸው ወንድሞቹን እያገለገለ በመልካም ገድል ኖረ ከዚያ ከብዙ ዓመታት በኋላ በንጉሠ አደባባይ የታሰሩትን ወንድሞች እንዲረዳ የወንድሞቹ ማኅበር ላኩት እሱንም ከጓደኛው ጋራ ያዙት ከእስር ቤት አስገቡትነ እዚያ ገድሉን በመልካም በከባድ በሽታ ፈጸመ ጸሎቱ ከኛ ጋራ ትሁን እስከ ዘለዓለም ይጠብቀን አሜን በነዚያ ዘመኖች ከሀገር ወደ ሀገር እየተሰደዱ ሰማዕትነታቸውን የፈጸሙ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ብዙዎች ናቸው በየዋሻው በመንገድ ላይ በዱር በምእመናን ቤቶች በንጉሠ አደባባይ ገና ከእስር ቤት ሳያስገባቸው በወታደሮቹ እጅ እንዳሉ በክፉ ሰዎች እጅና ጥሩ ነገር በሚጠላ ሰይጣንና ክፉ ጋኔኖቹ ብዙ ሥቃያት ያሳለፉ ቀተሩጥራቸው ነው ጸሎታቸው ልመናቸው የጻማቸው በረከት ለዘለዓለም ከኛ ጋራ ይሁን አሜን አሜን በድብ ፀር ዘመን ዘብር ከምትባል ሀገር ጀምሮ ደብረ ብርሃን ዝማ ጐዘም እስኪደርስ ከነዚህ አገሮች በስተ ግራ በኩልና በንጉሥ አደባባይም ሁሉ ሰማዕትነታቸውን በመልካም ሰማዕትነትና በመንፈሳዊ ገድል ከፈጸሙት ውስጥ ቀሩጥራቸውን ያወቅነው የቅዱስ ብፁዓዊ እስጢፋኖስ ወንድና ሴት ልጆች ሰማዕታትና ጻድቃን ጠቅላላ ድምር ፀ ነው የማናውቀውን እሱ ንብረቱን ይሰብስብ እሱ ራሱ አምስት ወፎች። አቡነ አበክረዙንና የቅዱሱ ረዳት ተነሥተው ከአባ በርተሎሜዎስ ደብር መጡ አላገኙትምነ ለደበሩ ሰዎች እነሆ ምንም ኃጢአት ወይም አበሳ የሌለበትን ደኻ ሰው ሊገድሉት ይፈልጋሉ ረድታችሁን ለአገሩ ሹም እንድትነግሩት እንፈልጋለን አሏቸው እነዚያ ሄዱና ለአበምኔቱ እናንተው ንገሩት ጳጳሱ አሁን እዚህ የለም አሏቸው ወንድሞች በጎ ነገር እንዳላገኙና የሚረዳቸውም እንደሌለ ሲያውቁ እዚያ እስክንሄድ ድረስ አባታችን ይሞታል እኛው ራሳችን ወደ ሹሙ ሄደን እንንገረውና አቤት እንበል ተባባሉና ከሀገሩ ሹም ዘንድ ሄደው አባታቸውን በእግር ብረት እንዳሰሩትና እንዲሞት እንደዘጉበት ነገሩት ይኸንን ነገር ሲሰማ እንደዚህ ተፈጽሞ ከሆነ አብሬያችሁ ሄጄ እዚያው አእዳኛችኋለሁ አላቸው ከዚያ አብሯቸው መንገድ ጀመረ ወደዚያ ሊደርሱ ሲሉ አብሯቸው ያለውን ሶስተኛውን ወንድም የቅዱሱን ሁኔታ ሞቶም እንደሁ ወይም በሕይወት እንዳለ ለማወቅ አስቀድመው ላኩት በዚያ ደብር ውስጥ ሰላም የሚሠራ ሽማግሌ መነኩሴ አለ ትዕግሥቱን ያደንቅ ስለነበረ በሌሊት ራእይ በእስር ቤት የተዘጋበትን አቡነ ቅዱስ እስጢፋኖስን የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወርዶ እንደጐጉበኘው ቅዱሱ ባለበት ቤት ውስጥም እንዳበራ መንፈሳዊ ሰላምታ ኅዳግ ፉጥር ን ተመልከት ደብር የመተዳደሪያ ምንጭ ስለሆነ ጳጳሱም የራሳቸው ደብር አላቸው አነጋገሩ ሰላም የሚሠሩ ብፁዓን ናቸው እንዳለው ነው ማቴ ልዘክየዉህበ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ እንደሰጠው የብርሃን ውበት የተሞላች ቅድስት ፊቱን እንደሳመው አየ ራእዩን እንዳየ ከአበምኔቱ ዘንድ ሄዶ ይህ ሰው ከሞተ የሀገሩ ሹም ደብራችሁን ያጠፋዋል ከሱ ጋራ ሰላም አድርጉ ከእስራቱም ፍቱት ስላለው አበምኔቱና የደብሩ ሰዎች ይኸንን ሲሰሙ ሐሳቡን ወደውት ቅዱሱን ከእስር ቤት አውጥተውት ኖሮ አስቀድመው የላኩት ወንድም ሲደርስ ቅዱሱን ከእስራቱ ተፈትቶ አገኘው መልክተኛው ወደ ሀገሩ ሹም ሄደው የሆነውን ሁሉ እንደነገሩት ሹሙም ከእጃቸው ሊያድነው እንደመጣ ነገረው ቅዱሱ ሰምቶ ለዚያ ወንድም ከእስራት ፈተውኛል ከነሱ ጋራም ታርቀናልና የሀገሩን ሹም እንዳያመጡት ለወንድሞች ንገራቸው አለው እሱም ይኸንኑ ነገራቸው። አላቸው እነሱም ኑሯቸውን ሁሉ ነገሩት ቅዱሱ እዚህ መኖር አይስማማችሁም ወደ ክርስቲያኑ ምድር ውጡ ብትኖሩም ብትሞቱም እዚያ ይሻላችኋል አላቸው እነሱም አባ ሆይ አንተ እንደምትለው ጥሩ ነው በፊቱንም ቢሆን እዚህ ያለነው ፈቃድ ስላላገኘን ነው እንግዴህስ የሚያስተክዘን ነገር አይኖርም እንዳልከን ይሁን አሉት ቅዱሱ እኛም እኮ የመጣነው በእግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ በፈቃዳችን አይደለም አሁንም ውጡ አትጠራጠሩ የእግዚአብሔርን ቃል ብትሰሙ ይሻላል አላቸው በተግሣጽ እያጽናና ስለ ሁሉም ነገር ምዕዳን አሰማቸው የምታስረዳ መንፈሳዊት የንጽሕና ምግብ ሰጣቸው ከዚያ ደግሞ በጓትር በእስራት ላይ ወዳሉት ወደ ሌሎቹ ወንድሞች ሄዱ ለነሱም ለወንድሞቻቸው እንደነገራቸው ነገራቸው እነሱም ጥሩ ነው አባት ሆይ በቃልህ ረድኤት ለሰጠን ለእግዚአብሔር ስብሐት ይሁን አሉት ከዚያ እያንዳንዳቸው ወንድሞች በእስራት እንደ ዓለም በቃኝ ሆኖ የፖለቲካ እስረኞች የሚታጎሩበት በገደል የተከበበ ጠባብና ጎድጓዳ ቦታ መሆን አለበት በሄድቋሐ ሐይፁሀ ዳዕጪፉሃዕና ዕዳ ሀዲድ ማረያም ታሪ ውስጥም ተነሥቷል ጐንጽ የሚለው የቦታዋ ስም ትርጉሙም ጉንጭ ማለት ነው ይኸም ማኘኪያ ከሚለው ጋራ ይሄዳል የእስር ቤቱ ስም ቤተ መዛግብት እንደሆነ በድሰሐ ሐይን ዳዕጪፉኖዕ እና በድሐ ለሐፁቦን ሪህራ ውስጥ ተነግሯል አቡነ ተክለ ሐዋርያትም አፄ ዘርአ ያዕቆብ ደጃፍ በግልቢያ ጨዋታ ደኻ በፈረስ እየተረገጠ ሲሞት አይተው ቢቆጡት የተቀባ ንጉሥ እንዴት ትደፍራለህ ብሎ እዚሁ ቦታ ምንድቅ ጉድጓድ ውስጥ አስሯቸው ነበረ ርክርከፀክ እቪክቨ ላከህበ ከ ክኬሃ ከ ከ ከ ዐ ር ያብዐሀፀ ፀ ዐዐሆ ሀ ዐዘዐያሮ ኖዐያዐዘርዐ ርር ኛኞ ከቅሃበ እሀ ሀ ልዘየዉህበ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ወደተበተኑበት ወደየቀበሌው ሄደ በየሀገሩ ተመላለሰ ጐጉበኛቸው እጅ ነሣቸው ስለ ማንኛውም መከራቸው ልባቸውን ከመንገዳገድ መለሰው የእርዳታ ምርኩዝ ሰጣቸው ከመስቀል ላይ ለመውጣት እንዲችሉ በእምነት አጸናቸው ሱባኤ ከዚያ በነሱ ተባርኮ ሽማግሌው በርተሉሜዎስ ታስሮ ወዳለበት ወደ ሳጉራ ሀገር ተመለሰ የሠራውን ሁሉ ነገረው እሱም በሚገባ የበረከት ቃል ባረከው ቅዱሱ ወደዚህ ልመጣ ስል አንተ ዘንድ በደኅና እንዲያደርሰኝ ስለ እስረኞች ወንድሞች ያሰብኩትንም ሁሉ እንዲያስፈጽመኝ በማኅበሩ ምክር ልዩ ጸሎት አድርጌ ነበረ እግዚአብሔር ደጉን ሁሉ ሠራልኝ ምንም ክፉ ነገር አላደረሰብኝም አሁንም አንተ ዘንድ ላደርገው እፈልጋለሁ አለው ወደ ዱር ሄዶ እንዲጸልይ ሽማግሌው ፈቀደለት ካጠገባቸው ራቅ ካለ ቦታ ማደሪያ ሠሩለት እዚያ የጓ ቀን ጾም ምህልላ አደረገ አምስት ቀን እህል ውሐ ፈጽሞ በመተው ይጸጾምና በሰንበቶቹ ቀን ጾም እንዳይሆንበት ትንሽ ውሐና ቅጠል ይቀምሳል በዚህ ጊዜ የሰይጣን ፈተና መጣበት ፈርቶ ምህልላውን ይተው እንደሁ ወይም ይበረታበት እንደሁ ሁል ጊዜ ሊሰልለው በጦርነት ላይ እንዳሉ ብዙ ሠራዊት ድምፅ የሚያስፈሩ ክፉ አጋንንት ላከበት ከሱ ጋራ በግላጭ ሲተያዩ ይደነግጡና ይሸሻሉ በላዩ ላይ ያለው የእግዚአብሔር ብርሃን ያበናቸዋልሱ ሰይፍህን በጠላትህ እጅ ላይ አውርድበት ተብሎ በነቢዩ ምስከራ እንደተጻፈው የክንዱ የማማተብ ምልክትም ያባርራቸዋል ነፍሱን ሊያሸብሯት ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ እንደገና ዝምቦች በበክት ላይ እንደሚያደርጉት ግር ብለው ይሰበሰባሉ ግን በእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ስለሚጠበቅ ሊነኩት ሥልጣን አልነበራቸውም ብፁዕ እስጢፋኖስ እግዚአብሔር እጁን ያሳረፈበት ሰው ይሰጣችኋል ያለው ቃሉ እንዲፈጸም እስከ ዕለተ ሞቱ የክፉዎች ሰዎች አጅም ሆነ የእርኩሶች አጋንንት እጅ በክፉ ነገር አልነካውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ካልሆነ በቀር በኔ ላይ ክፉ ልታደርግ እንደማትችል አውቃለሁ እኔ ግን ስለ ስሙ በሞት ጥላ መካከልም ብሄድ ክፉ ነገርን አልፈራውም እስኪለው ድረስ ለማስፈራት በግላጭ ይመጣበታል እንደዚህ ሁል ጊዜ ይጐበኘዋል ግን ለዘመቻ እንደተዘጋጀ ሰው በጦር መሣሪያ ተዘጋጅቶ ያገኘዋል አጠገቡ ያሉት ወንድሞችም በሄዱ ቀጥር ይኸ ሌሊት ሌሊት እንደ ብዙ ሰው ድምፅ የምንሰማው ምንድን ነው። ልዘክየዉህበ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ከዚያ በኋላ በዚያ ዓመት ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥሪ መጣ ከነሱ ውስጥ አንዷ በጥሪው በሽታ ላይ እንዳለች አቡነ እስጢፋኖስ በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ ይኸም ሽማግሌ አቡነ አበክረዙን መነኩሲቶች ለአቡነ ቅዱስ እስጢፋኖስ እነሆ መንፈስ ቅዱስ ምስክራቸው የሆነ ንጹሖች ድንግሎች ብሎ ሲያስረክባቸው እሱም ተቀብሎ ለእግዚአብሔር ሲያስረክባቸው ራእይ አየሁ አለች ቅዱስ አበክረዙን እንዳለውና እንደ መነኩሲቷ ራእይ ሆነ የእግዚአብሔር ጥሪ ወደነሱ መጥቶ ቱ ከወንድሞች ቱ ፍጻሜያቸው ሆነ ራእይ በጊዜው ይደርሳል መንፈስ ቅዱስ በላዩ ያለ ሁሉን ያውቃል እሱን ግን የሚያውቀው የለም እንደዚሁ ይኸም አቡነ አበክረዙን ሥራውን የሚያውቁት ሰዎች ካልሆኑ በቀር ለትምክሕት ለሌሎች ሳያሳውቅ በጥሞና ኖረ የአባታቸውን ተዝካር ሲያወጡ ተከበቡ በእንደዚህ እንዳሉ የአቡነ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተዝካር ዕለት ደርሶ ቅዱሳኑ የተዝካር በዓል ሊያደርጉ በተሰበሰቡበት የንጉሥ መልእክተኞች ከብዙ ሠራዊት ጋራ ሆነው መጡ የቅዱሳኑን ሰፈር ከበቧት በደረሱበት ያለውን ሀገር ሁሉ አጠፉት ቅዱሳኑን ደብረ ቅፍርያ በምትባል የታሰሩትን ጭምር ሰብስበው ሁሉንም በአንድነት ወደ ንጉሥ ወሰዷቸው ወስደው ምን እንዳደረጓቸው በገድላቸው መጽሐፍ ውስጥ አለ አቡነ አበክረዙንን ግን እግዚአብሔር ስለደበቀው አላገኙትም ግን ከሀገር ወደ ሀገር ከምድረ በዳ ወደ ምድረ በዳ ስለሚያሳድዱት ማረፊያ እስኪያጣ ድረስ የሀገር ጥበት ደረሰበት ከዚያ ንጉሥ እንደገና ደግሞ በዚያው ዓመት እዚያ አገር በየቀበሌውና በየገዳሙ የተረፉትን ቅዱሳን እንዲሰበስቡ መልእክት አስተላለፈ እንዳዘዘው ሁሉንም ሰበሰቡለት ከ መነኩሲቶችና ከ ቅዱሳን ሽማግሌ ቄሶችከአባ አቡናፍርና ከጓደኛው ከዮሐንስበቀር የተረፈ አልነበረም እነሱም ቢሆኑ በምድረ በዳ በብዙ ችግር ላይ ነበሩ ቅዱሱ ከዚያ ሲሄድ መነኩሲቶቹ አንተ ከዚች ሀገር ከሄድክ ከወንድሞችም ሌሎች ካላገኘን ታዲያ አባት ሆይ እኛ እንዴት እንሆናለን። ድንጋጤና ታላቅ መገረም ወደቀባቸው የቅዱሳኑን ንብረትና ልብሳቸውንም መለሱላቸው ቅዱሳኑም ከተከዜ አጠገብ ደወልወላ ከሚባል ቦታ እስኪደርሱ መንገዳቸውን በሰላም ቀጠሉ እዚያ አረፉ ቅዱሱ ድካማችንን ተሸክሞ እዚህ ሳደረሰን እግዚአብሔር ስብሐት ይግባው አለ ወንድሞችንም ሰይጣን አፍሯልና አትፍሩ ሊከተለን አይችልም አሁን እንግዴህ እረፉና እግዚአብሔርን አመስግኑ የእስራኤል ነቢይ ኤልያስም ስለ እግዚአብሔር ቀንቶ በኤልዛቤልና በንጉሥ አካአብ እንደዚህ እስከ ደብረ ኮሬብ ድረስ ተሰዷል ወደ ሕዝቡ እስኪመለስም ድረስ እዚያ ኖሯል አላቸው ወንድሞች ይኸንን ከቃሉ ሲሰሙ እግዚአብሔርን አመሰጉት ስብሐትም አቀረቡለት እዚያ ሳምንት ያህል አረፉ በተምቤን ምድረ በዳ ከዚያ በኋላ ከዚያ ወጥተው በተምቤን ምድረ በዳ ወዳሉት ወንድሞች ሄዱ ቅዱሱ እዚያ ወር ያህል ተቀመጠ እዚያ የመኖሩን ዜና ሌሎች ወንድሞች ሲሰሙ እንደለመዱት የሩቆቹም የቅርቦቹም ወደሱ እየመጡ የቃሉን ምዕዳንና በረከቶቹን አግኝተው ወደየገዳማቸው ይመለሱ ነበር ቅዱሱ እዚያ ያሉትን ወንድሞች መሥዋዕት እንዲያዘጋጁ አዘዛቸው እንደዚያ አደረጉ ከዚያ በኋላ ከገዳሞቹ ወደ አንዲ ከስዋ ወደምትባለዋ ሄደ ከእሷ ከወጣ ፀ ዓመት ከ ወር ሆኖት ነበረ እዚያ ሀገር ያሉ ወንድሞች ተሰባሰቡና ስለሱ እግዚአብሔርን አመሰገኑ እሱን በማግኘታቸው ታላቅ ደስታ ተደሰቱ ልባቸው አስክትበራ ድረስ በምዕዳን እያጽናናቸው አብሯቸው ቆየ የውጪና የውስጥ የእጅ ሥራቸውን እግዚአብሔር አሳመረላቸው ከዚያ በኋላ ቅዱሱ የእግዚአብሔርን ስብሐት የምታሳርጉበት መሠዊያ ከማህላችሁ ሥሩ አላቸው ወንድሞች ካሁን በፊት የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን አጠፉብን ክርስቲያን ሆነው ሳለ በእሳት አቃጠሉት አሁንስ ቢሆን ማን ይተውልናል ብለን እንደክማለን። ይኸንን ያሉት አባ እስጢፋኖስ ይሆናሉ ልዘየዉህበ ህበሃ ህህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ አሁንም እናንተም በጽድቅ ሥርዓት ከኖራችሁ እኔም አብሬያችሁ አለሁ እናንተም ከኔ ጋራ አላችሁ በአባቶቻችሁ የጽድቅ ሥርዓት ሁሉ ካልሄዳችሁ ግን ከድካማችሁ ንጹሕ ነኝ በዚህ ምክንያት አይኩንነኝም ሲጠይቀኝ እንዳስተማርኩ እንደነገርኳችሁም እናገራለሁ አሁንም መነኩሴዎችም ሆናችሁ መነኩሲቶች በመንፈሳዊ አባታችሁ ሥርዓት እንዳላችሁ ብትሞቱ ይሻላችኋል መጽሐፍ ካብ የሚንድ እባብ ይነክሰዋል ይላል በሌላ ቦታ ደግሞ አባቶችህ የሠሩትን ሥርዓት አትናድ ይላል እንደዚሁ አሁንም ወደ ፈተና እንዳትገቡና የመንፈሳዊ አባታችሁን ሥርዓት እንዳትንዱ እንግዴህ መጥፋትን ከፈለጋችሁ ጉዳቱን በኋላ ታገኙታላችሁ አሁን እርግጥ በሕይወት ትንሽ ያስቆያችኋል ስለሚጣሏችሁ ታገሥ ምክንያቱም ትዕግሥት ያለውን እግዚአብሔር አይተወውም የቀድሞዎች ብዙዎች የተከተላቸውን ደስታ ያገኙት ትዕግሥታቸውን በማራዘም ነው እንደዚሁ አሁንም የመሥዋዕቱ ዕጣን በሠመረበት እግዚአብሔር ይኖራል የሜታበየውን በትሑቱ እጅ ያስገዛዋል እንደዚህ ሁል ጊዜ በድቅ ቃል ሁሉ ምዕዳን ያስሰማ ነበረ እንዲህም ይል ነበረ እንግዲህ አሁንም እናንተ ወንድሞች ሆይ ትጉ ምክንያቱም ልባዊ ትጋት ሁልጊዜ አይገኝም ከደብሩ ከጫፉ እስክትደርሱ ድረስ ትጉ እንጂ ከጭኑ ቁጭ አትበሉ ከወንድሞች አንዱ ሰምቶ እኔስ እውጪ በሀገር ከምገኝ ይልቅ በደብሩ በተራራውበደብሩ ጭን ብገኝ ይሻለኛል እላለሁ ደብር መውጣት ግን ይርቅብናል አለ ሽማግሌው በደብሩ አራዊት ያገጂችኋል ግን በድንጋይ ተደባዳቢዎች ጥቂቶች ናቸው አለው ለቅርቦቹም ለሩቆቹም እንደዚህ ይነግራቸው ነበረ አንድ ጊዜ ወደ ምድረ በዳ ይሄዳል አንድ ጊዜ ደግሞ ወደ ደብሩ ይመለሳል ያ የውሸት አሳባቂ በፊት እንዳደረገው ሀገር ለማበላሸት የቅዱሱን ዜና በደረሰበት ይሰልል ነበረ በፊት የእግዚአብሔርን የመሠዊያ ቦታ አቃጠለው የወንድሞችን የድካማቸውን ፍሬ ለእርዳታ ባመጣቸው የንጉሥ ሠራዊት አስከብቦ አጠፋው የፈለገውን ሁሉ ፈጽሞ ወደ ንጉሥ ተመለሰ ደግሞ እንደገና እርዳታ ይዞ መጣ አሉ ምክንያቱም በፊት ስላላገኘው ከንጉሥ እና ከመነኮሳቱ ዘንድ አጥብቆ የውሸት ነገር ያሳብቅ ነበረ ወንድሞች በሰሙ ጊዜ አባ አበክረዙንን እዚች ሀገር እንዳለህ ተሰምቷልና ወደ ምድረ በዳ ዞር በል አሉት ወደ ምድረ በዳ ሄደ እዚያ ባለበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ እያሳየው የሚሆነውን ሁሉ ያውቅ ነበረ መንፈስ ቅዱስ ያናገረውን ብዙ ነገር ተናግሯል ስለ ልዑሉ የሕጉ ሥርዓት በጸሎትና በስግደት በጣም ይተጋና ይደክም ነበረ። እኔም እንደነሱ ዕብራዊ ነኝ እሥራኤላውያን ቢሆኑም እኔም እንደነሱ እስራኤላዊ ነኝ የሚለው መጽናኛ ቃል ምልክት አላችሁ ቀድሞ ያወቃቸውን ሕዝቡን እግዚአብሔር አልጣላቸውም ብቻ በእግዚአብሔር ጽኑ ይኸንን ብሎ ዝም አለ ያቺን ሰዓት ከዚህ በፊት በብፁዕ አባ መቃርስ ዘንድ እንደሆነው ቅዱሱ ከሰይጣንና ከሰዎች ጋራ ይነጋገርባት ነበረ ሰይጣን አባ መቃርስን ከልጅነቱ ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞቱ ሊከሰው ይፈልገው ነበረ ግን በሁሉም በኩል ፍጹም ሰው ስለነበረ ምንም የሚወቀስበት ነገር አልተገኘበትም ነፍሱ በምትወጣበት ጊዜም ሰይጣን በአየር ላይ ሆኖ መቃሪ መቃሪ አመለጥከኝ አለው ቅዱሱ አሁንም ገና አላምንህም አለው እንደዚሁ ይኸም ቅዱስ አባታችን በፊት ከሰው ተለይቶ በነበረበት ጊዜ እንደ ደረሰበት የሚያስደነግጥ ግርማ ሲደርስበት በሥሉስ ቅዱስ ስም አማተበ ያ የውሸት ከሳሽ አፍሮ ወጣ በሽንገላ በመጣበት ጊዜ ሁሉ አዘውትሮ ያሸንፈዋል ያን ጊዜም ከሱ ለዘላለም በረጅሙ እስኪርቅ ድረስ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል አሸንፎ አባረረውጹ በዚያች ጊዜ ቅዱሱ ዝም አለ ዘለዓለማዊ ዕረፍትና ቀብር ያቺ ሌሊት በሞላ በጣም የምታስፈራና የምታስደነግጥ ሆነች የሰውም ሆነ የአራዊት ድምፅ አልነበረባትም ምድረ በዳው ሰው ካለበት ሩቅ ነበረ እሱን ይጠብቁት ከነበሩት ከጥቂቶቹ ወንድሞች በቀር ሌላ ማንም አልነበረም ቆሮ እኔም እንደነገሥቱ እስራኤላዊ ነኝ ማለታቸው ነው ር ለ ሥቨወገርዐዘ ፀሀዐህሀርፀ ርርዐ ሂ ሀ ልዘዚየዉህበ ህበሃ ህህ ሀ የአባ አበክረዙን ገድል ጊዜው ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሲሆን በሁሉ ጊዜና በሁሉ ሰዓት ከሰው እጅና ከሰይጣናት ይጠብቀው በነበረ በእግዚአብሔር ጸባዖት ሰላም እንደጣፋጭ እንቅልፍ በወንድሞች እጅ መካከል አረፈ ለእግዚአብሔር በፍጥረት ሁሉ አፍ ስብሐት ይገባዋል አሜን ጠረኑ የጣፈጣቸው ወንድሞች እስኪያደንቁ ድረስ በላዩ እጅግ ጥሩ መዓዛ ነበረበትፎ ከዚያ ቅዱሳን ወንድሞች ተሰብስበው ምርር አድርገው እያለቀሱ በአበው ሕግ በክብር ገነዙትነ የጻድቃንና የታጋዮች ተስፋና ከዳግም ትንሣኤ አስቀድሞ የምትሆነው የነፍስ አስቀድሞ መነሻ የሆነውን ጐርባን ቀደሱ ሁሉንም እንደተጻፈው ፈጽመው በአየር ወር ሀ ቀንይኸውም ግንቦት ነውከሰው ከተደበቀ ምድረ በዳ በጌታ ሰላም ቀበሩት ጸሎቱና በረከቱ ለዘለዓለም ከኛ ጋራ ይሁን አሜን አሜን ይኸንን ገድል የጻፈውን ያስጻፈውን ያነበበውን የተረጐጉመውን ቃሎቹን በእምነት የሰማውን እግዚአብሔር በአንድነት ይማራቸው ለዓለመ ዓለም አሜን ከመግቢያው ጋራ ለማስታረቅ በአየር በግንቦት መሆኑ ነው ልዘየዉህበ ህበሃ ህህ ሀ የፎሮኖ ጣዝ ወኖሀ ሮ ተፈልመቀመ አድ ዛፋጦዴ ሇወፍ መሥመር ። ሪ ሀ ለያዐርዘሪ ዘዐቨ ጅዩቬርክኮ ሀኮ ፆቭሪዐሮር ፅሀፐርዐያዝዘ ዘሪደፀዘወገህዘ ሃዐዐሪ «ዐዘ «ሮሃ ርፀ ፅፀዘርያ ሠዐዘ ዐፀ ሂዐዐና «ዐዘ ርፀ ፀዘርዘ ሥያወይ ርኝርዐ ህዐ ዐበሸይ ጀሰጽ ከርከ ርጩቪበ ለከሃኬ እሸዐበሀከሃኗቨር ከሃ ሃ ከ ኮዐ ኗቨከ ላ እብርከ ኣፀከቧር ኗህዌ ያዐነ ለ ለሪ ህያዕፀያ እሄዘከሻ ዘነ ዘዘዐ እዐሪ ፈቃ ሀዐህሀ ፀር ጽፀሮፀሪ ፓ ሺቫዐኦ ርርዐ ሄዐ ሃ ኣእር ርገናሮፀዘ ሀዘ ያገ እሃ ቪፎርበከህኪ ሃቢ ዐፖጀና ዐ ዐደ ዕፖዐ ሪር ለሀዐ ዕዐሮዐ ላፎወሀጋ ርርዐ ሃ ፀሃላል ሀበዐሃ ህሀሃ ሀ መጠቀም የቦታና የሰው ስም ኅ ኅዳግ ክ በ ሀ ሀብተ ማርያም አባ ኅ ኅ ሀብተ ሥሳሴ አባ ኅ ሀብተ ጽዮን ወንድም ሀገረ ማርያም ሀገረ ሳጉራ ሀገረ በሊ ሀገረ ኢባ ሀገረ እብሶ ሀገረ ደም ሃሌሎደብረ ሃሌ ሉያ ኅ ሃሌሎዎች ሄሮድስ ንጉሥ ኅ ሄኖስ የብሌዩ ኅ ሄኖክ ነቢይ ህንድ ለ ለክማ ኅ ሉቃስ ወንጌላዊ ኅ ሌሉተር ማርቲን ሊቃኖስ ወንድም ሊቢያሎንያ ኅ ሊባኖስ ኅ ሊንቼ ሕዝባዊ አካዴሚ ላከማ ላይ ሳይ ግብጽ ኅ ሌዊ የብሌዩ ኅ ሌዋውያን ኅ ልዑል ሠምራ የአባ ዕዝራ እናት ልዮን የሮማ ሊቀ ጳጳስ ሎስ አንጀለስ ሎንያሊቢያ ኅ ሉጥ የብሌዩ እፎህ ሀ ሕሐ ሐምሎ ሐረዘወይላ ሐርላ ሐይት መንዞ ሐይጉምዜ ሐዲያ ሓረት ዘዊላ ኅ ሓንባር ጎድባ ሔዋን የብሉይዋ ኅ ሕዝቅኤል ነቢይ ሕጉር ኅ መ መልከጸዴቅ አባ መሐረቅ ዴር መሐግል ኅ መረግድ መርቆርዮስ ከሳሽ መርቆርዮስ ወንድም መርቆርዮስ ሠዓሊ መርቆሬዎስ ዘሄባ ኅ መርዋ መስፍን ወልደ ማርያም ፕሮፌሰር መቃርስመቃርዮስመቃሪ አበ መነኮሳት ኅ መቅዶንዮስ ኅ መታር አባ መንቆርዮስ ወንድም መንበርታ መንግሥተ ሰማያት መእድ መካነ መስቀል ኅ ህበሃ ህህ መካነ ሥላሴ መካነ ሰላምጌ መካነ ኢየሱስ ኅ መካከለኛው ምሥራቅ ኅ መክሲሞስ መምህር መክብዩ እማሆይ መዓራ መደባይ መድኃኒነ እግዚእ ዘበንኩል ኅ መገረደ ኅ መገራን መገርዶ መጋረዳ መጋረዶ መጋራዳ መጋርዳ ኅ ሙሴ ነቢይ ኅ ኅ ኅ ሙዓለ መሀፒል ሙደዋ ሚሳኖ ሚኒሶታ ሚናስ አባ ሜካኤል መልአክ ሜካኤል ጳጳስ ኅ ኅ ኅ ኅ ማሄሂኮ ኅ ማርቆስ ሐዋርያ ማርቆስ መንበረ ኅ ማርቆስ ጳጳስ ማርታ አማረ ወይዘሮ ማርያ ማርያም ባለሽቶዋ ማርያም ሠምራ እማሆይ ማርያም ቅድስት ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ማቴዎስ ወንድም ማቴዎስ ወንጌላዊ ማቴዎስ ሊቀ ጳጳስ ኅ ማአድ ኅ ማዕቀበ እግዚእኤዎስጣቴዎስ ደቂቀ ኅ ኅ ማየ ኅ እፎህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ማየ ጣፋት ማያ ማጋረዶ ሜሮን ሜዶን ሜዶን ራጊስ ምሕማድ ገራድ ኅ ምሥራቅ አማረ ወይዘሮ ምራዋ ምርጋይ ምስር ምአድ ምዕራብ ምድረ ክርስቲያን ምድረ ፀጋም ምድያም ምድረ ሞርዲኒ አንቶኒዮ ሲኞኛር ኅ ኅ ሠ ሠለስቱ ደቂቅ ኅ ሠምረ ሚካኤል ተላላኪ ሣህለ ሥላሴ ራስ ኅ ሥሩግ ረፈ ረሜ ሪ ላንፍራንኮ ፕሮፌሰር ራጉኤል የብሉዩ ራፋ ርቱዓ ሃይማኖት መምህር ርክነ ሮማ ኅ ኅ ሮማውያን ኅ ኅ ሮም ሮም ሰገድ ልዑል ሰ ሰለስቱ ምአት ኅ ሰለስቱ ደቂቅ ኅ ኅ ሰላማ ጳጳስ ሰላምጌ ሰልገኒ ሰሎሞን ንጉሥ ኅ ኅ ሰሜን አፍሪካ ኅ ሰርመትሰርማት ኅ ኅ ሰባልዮስሰብሌኔስሰብልያኖስሰብልዮስ መናፍቅ ኅ ኅ ህበሃ ህህ መጠቀም ሰንደፋ ኅ ሰውኔ ሰዶም ሰገቢ ሰፍ ሱርስት ኅ ሱርያል መልአክ ሲመይሲማይ ሽሸሜ ኅ ሲሞን ኅ ሲሬ ሲኖዳ አርሳይመትረይስ ሲኖዳ አባ ሲኖዶስ ኅ ኅ ኅ ኀኅ ኅ ኅ ኅ ሲኦል ሲዲ ሹም ሲዶና ሳሙኤል የከዳ ሳሙኤል ከሳሽ ኅ ሳሙኤል ወንድም ሳሙኤል ዘቆየፃጻ ኅ ኅ ኅ ኅ ሳሙኤል ወልደ ሕልቃና ሳሙኤል ዘዋልድባ ኅ ሳሙኤል ዘጣሬጣ ኅ ሳሚስ የብሉዩ ሳራ የአባ እስጢፋኖስ እናት ሳባ ኅ ሳኦል ኅ ኅ ሳጉራ ሳፍሰፍ ኅ ኅ ሴም የብሌዩ ሴት የብሉዩ ኅ ሪናዶሯቃ ሴዋ ሸዋ ስማዝያል መልአክ ኅ ስምዖን የብሌዩ ስምዖን ቀሲስ ስምዖን ዘዓምድ ስምያል መልአክ ኅ ስረጵታ ስቡሐ ዓ ስፔንሰር ሶርያሶርያዊ ኅ ኅ ኅ ሶስና ሸ ሺሬፊሸሬ ሽመይሸሜ ኅ እፎህ ሀ ቀ ቀሌምንጦስ አባ ቀንጡራሬቀንጦራር ኅ ቀንጦራርቀንጡራሬ ኅ ቀወት ኅ ቀውስጦስ አቡነ ኅ ቀይ ባሕር ኅ ኅ ቀጸም ቁስጥንጥንያ ቂርቆስ ሰማዕት ኅ ቂስ የብሉዩ ኅ ኅ ቂሶ ቃኤል የብሉዩ ቄርሎስ ቅዱስ ኅ ቄሳር ቄዳር ኅ ቄጠመይ ቅብጥ ኅ ቅዱስ ዮሐንስ ዩኒቨርሲቲ ቅዱስ ዮሐንስ ዩኒቨርስቲ የማይክሮፊልም ቤተ መጻሕፍት ቅዳ ቅፍርያ ቆላ ኅ ቆረኒስ አባ ቆገት ቁራጽ ቁርቋራቋርቋራ ኅ ቁቴስጠንጢኖስ ቁየጻቁየፃ ቀስቋም ኅ ተቀስስጥንጥንያ ኅ በ በሊ በላዔ ሰብእ በረካባረካ በራራብራራ ኅ ኅ በርስበይ ሥልጣን ኅ በርሶማ አባ በርበሮች ኅ በርተሎሜዎስ ዲያቆን በርተሉሜዎስ አባ ኅ በርተሉሜዎስ ጳጳስ ኅ ኅ ኅ ህበሃ ህህ በርናባስ ሐዋርያ በስሩ አባ ኅ በትራ በኀይለ ማርያም ሹም በእደ ማርያም አፄ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ በኪሞስ አባ ኅ በኬት ገዳመ በኩረ ዮን ሹም በዐልቶ በድላይ ኢማም ጎ ኅ በግዑ በጸሎተ ሚካኤል አቡነ ኅ ቢዘን ኅ ቢፋሞን ቀይሰ ሐፀይ ኅ ባለ ተጉዛጉዛ ባሌ ኅ ባሕረ ሳፍ ኅ ባሕርይ አባ ባረካ ባሮክ ነቢይ ባሴ ሬኔ ኅ ባስልዮስ ቅዱስ ኅ ባስልዮስ የከዳ ባቢሉን ኅ ቤሉ ሮቤር ቤተ ልሔም ቤተ ማርያ ቤተ ማርያም ኅ ቤተ ኢየሱስ ቤቴል ኅ ብሔረ ሳባ ኅ ብራራ ብርሃነ መስቀል የአባ እስጢፋኖስ አባት ብርሃነ መስቀል ወንድም ብርሃነ መስቀል ወንድም ብርሃን መዋኢ ወንድም ብእሴ ሰላም ከሳሽ ብእሴ እግዚአብሔር ኅ ቦሩ ሜዳ ኅ ቦሻ ተ ተምቤን ተስዓቱ ቅዱሳን ኅ ተስፋነ መስቀል የአባ አበክረዙን አባት ተስፋነ ክርስቶስ ሹም ተንቤን ተከሥተ ብርሃን ከሳሽ ተከዜ እፎህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ኅ ኅ ኅ ተክለ ሐዋርያት አቡነ ኅ ተክለ ኢየሱስ ንቡረ እድ ኅ ተክለ ውሸት ተወልደ መድኅን አባ ቱርክ ታብርሃ ጽዮን ልዕልት ታውኒ ታየ አሰፋ ዶር ታደሰ ታምራት ፕሮፌሰር ኅ ኅ ታዴዎስ ዘባልታርዋ ኅ ታድኅነነ ማርያም የአባ አበክረዙን እናት ቴዎድሮስ አባ ትግራይ ኅ ኅ ቶማስ ሐዋርያ ቸ ቸሩሊ ኤንሪኮ ቻይናውያን ኀ ኀበሲ ኀድገ አንበሳ ነ ኒቂያ ኒው ዮርክ ኒው ዮርክ ሕዝባዊ ቤተ መጽሐፍት ናሖም ሊቀ ካህናት ናቡቴ ኅ ናቡክድናጸር ኅ ናታን የብሉዩ ናኤል አባ ኦድ አፄ ኅ ኅ ኅ ኅ ናዕዴር ናግራ ናፖሊ ኅ ንስጥሮስ መናፍቅ ኅ ኅ ና ና ህበሃ ህህ መጠቀም ንግሥተ ማርያምንግሥት ማርያም ምእመንት ኅ ኖብ አባ ኅ ኖብ ሰማዕት ኅ ኖብ የአባ አበክረዙን ጓደኛ ኖኅ የብሉዩ ፅአ አለመሌ አለዳስ ኅ አልመሊክ አልአሽረፍ ሰይፉ አድዲን በርሰበይ ኅ አልበራድዒ ያዕቆብ ኅ አልቤታ አመዳ አማሚሾች አማሌቅ አማራ ኅ አማር አሜሪካን አምለከ አምኀ ለጽዮን ዓቃቤ ሰዓት ኅ አምኀ ማርያም እማሆይ አምኀ አስፋው አቶ አረሚአረማዊአረማውያን ኅ ኅ አሩሲአርሲ ኅ አራማሮ አራስ ቪክተር ኅ አርመንያአርማንያ ኅ አርሲአሩሲ ኅ አርሴማ ቅድስት ኅ አርሶ አርዮስ መናፍቅ ኅ ኅ አርዳሚስ ጣዖት አሮን የብሌዩ አሮን ወንድም አሮን ዘክትር ኅ አስመራ ኅ አስቄጥስ አስናእስና አሽሪፍ ንጉሠ ምስር ኅ አበስኪሮን አባ አበኔር አበክረዙን ሰማዕት እፎህ ሀ አበክረዙን አባ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ አበዘት አቡናፍር አባ ኅ አቤል የብሌዩ አብረታአብሬታ አብሩታ ኅ አብረኮሮስ ወንድም አብርሃ አፄ አብርሃም የብሉዩ ኅ አብርሃም ባለ ተጉዛጉጐዝ አብሮኮሮስ ወንድም አቦርዮስ መናፍቅ አትናቴዎስ ዲያቆን አናና አንበሳ ለፀርበፀር አፄ ኅ አንጎት አንጢዲቆንማርያስ አንጾክያ አንፈር አኖርዮስ አቡነ አኖርዮስ ወንድም አክሱም ኅ ኅ ኅ አክሱም ዮን ኅ አክዓብአካአብ ንጉሥ ኅ አውሮፓአውሮፓውያን አዘራት አዛፍ ኅ አዜብ አያ ጂቦ አይሁድአይሁዳዊ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ አይራራ ኅ አደል ኅ ኅ አዲስ አበባ አዲስ አበባ የአርኬዎሎዢ ኢንስቲትዩት ቤተ መጻሕፍት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ቤተ መጻሕፍት አዳም የብሉዩ ኅ ኅ አድሙት አድማስ በፀር አፄ አዶናይ ኅ አገው አግበራ አጵሉን ጣዖት ህበሃ ህህ አጽብሐ አፄ አፍሐሮም ዋሻ አፍቲክስ መናፍቅ ኢሳይያስ ብሕት ወደድ ኅ ኢሳይያስ ነቢይ ኢሳይያስ አባ ኅ ኢባ ኢትዮጵያኢትዮጵያውያን ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኢየሉጣ ሰማዕት ኅ ኢየሩሳሌም ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኢየሱስ ኅ ኅ ኢየሱስ ሞአ አቡነ ኢያሪኮ ኅ ኢያሱ ነቢይ ኢዮስያስ ንጉሥ ኢዮብ የብሌዩ ኤልሳዕ ነቢይ ኤልዛቤል የብሉይዋ ኅ ኅ ኤልያስ ነቢይ ኤሞር ኤርምያስ ነቢይ ኤርምያስ አባ ኤሳው ኤውሳጦን ኤዎስጣቴዎስ አቡነ ኅ ኅ ኤዴሳ ኅ ኤዶምያስ ኤኢፋንያ ኤፋት ኅ ኤፌሶን ኤፍሬም ቅዱስ እለ ቄራጸይ እለ አዝጓጓ ኅ እለ ከዲሕ ኅ እፎህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ እለ ወጺፍ ኅ እለ ገበዝ ኅ ኅ እምፍራዝ እሥራኤልእሥራኤላውያን ኅ ኅ እስራኤልእስራኤላዊ ኅ ኅ ኅ ብ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ እስክንድር አፄ ኅ ኅ እስክንድርያ ኅ እስጢፋፈ ኅ እስጢፋኖሳዊእስጢፋኖሳውያን ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ እስጢፋኖስ ወንድም እስጢፋኖስ ወንድም እስጢፋኖስ የሲመይ ነብርእድ ኅ እስጢፋኖስ ሰማዕት ኅ እስጢፋኖስ አባ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ እስጢፋኖስ አባ አበክረዙን እስጢፋኖስ የአባ ዕዝራ ወንድም እስጥምቡል ኅ እስፓኝ እብሶ እብነ ሕልክም ቀዳማዊ ምኒልክ እነ ቄሪጥ ኅ እናርያ እንግሊዝእንግሊዞች እንጦንስእንጦንዮስ አባ ኅ ኅ እንጦንስ ወልደ እኅተ እጉባእገብበእጐጉባ ኅ ኅ ኦሮሞችኦሮሞዎች ኅ ህበዐሃ ህህቨ መጠቀም ከ ከልአት ኅ ከሰም ከስዋ ኅ ከነዓን ኩር ስታኒስላው ኅ ኪሩቤል መልአክ ኪራም የብሉዩ ኅ ኪሮስ ወንድም ካሌብ አፄ ኅ ካኩ አንድሬ ኅ ካይሮ ኅ ፊረነ ኅ ኬር ወሰን ሹም ኬጢ የብሌዩ ኅ ኩላ አራይ ክርስቶስክርስቶሳውያን ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኩሰያት ደብረ ክሳድ እንባ ክብራ ክብርተ ማርያም እማሆይ ኮሌጅቪል ኮንቲ ሮሲኒ ካርሎ ወ ወለቃ ወላስማ ኅ ወላይታ ወልመወልማ ኅ ወራሪ ኅ ወራውሬ ወርወር ወርዕ ወያኔ ወይራራወይራር ወድውድ ኅ ወገራ እፎህ ሀ ወጊ ዋሊ ኅ ዋላ ዋልያ ዋሠጋ ኅ ዋሰል ዋዝርማ ውታፋ ውዱ ጣፈጠ ካሱ አቶ ውድ ኅ ዐ ዐረብ ዐርበት ዐቅበ ሚካኤል አባ ዕዝራ ዐጋሜ ዓለማየሁ ሕፃን ዓለት ዓምደ መስቀል ወንድም ኅ ዓምደ ጽዮን አፄ ኅ ዓምዱ ራስ ዓረቦች ዓዝርዕዝራ አባ ዕዝራ ኅ ዓደል ዓዳል ዓጋት ዓጸላ ዔሳው የብሉዩ ዕብራዊዕብራውያን ኅ ዕዝራ ነቢይ ፅዝራ አባ ኅ ዕዝራ አባ ዖዝዮን ንጉሥ ዘ ዘሚካኤል መምህር ኅ ኅ ኅ ዘርአ ያዕቆብ አፄ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኀ ኅ ህበሃ ህህ ዘርዓ ያዕቆብ ፈላስፋ ዘብር ዘታኦስ የሰርማት መምህር ዘንትር ዘንጉ ዘአማኑኤል ወንድም ዘአዶናይ አባ ዘካርያስ ነቢይ ኅ ዘካርያስ ዘጊፋ ኅ ዜራናቋ ዜጋ ዝማ ዝራጉን ኅ ዝቀላይ ዞሲማስ አባ ዣ ዣን ዜላ ንግሥትኢቴ ኅ የ የገስብም የጋድ ያሬድ ቅዱስ ያሳይ ዘማንዳምባ ኅ ያንጎ ያዕቆባውያን ኅ ኅ ያዕቆብ ሐዋርያ ያዕቆብ የብሌዩ ያዕቆብ ወንድም ያዕቆብ አልበራድዒ ኅ ያዕቆብ ዘሥሩግ ያግብአ ጽዮን አፄ ያፍቅረነ እግዚእ ባለ መድኃኒት ያፈቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤን ኅ ይሁዳ የተለየው ሐዋርያ ይሥሐጓቅ የብሉዩ ይሥሐቅ አፄ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ይሥሐቅ አባ ኅ ኅ ኅ ይሥሐቅ ጳጳስ ይሥሐቅ ጳጳስ ኅ ይሥሐቅ የአባ ዕዝራ አባት ይባራ ይጌይስ ይፋት ኅ ዮሐኒ አባ ኅ ዮሐንስ አቡነ እፎህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ዮሐንስ ምእመን ዮሐንስ መጥምቅ ኅ ዮሐንስ ሊቀ ጳጳስ ኅ ኅ ዮሐንስ ኤሏስ ቆፅስ ኅ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዮሐንስ ራእይ ኅ ዮሐንስ ሳባ ኅ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ኅ ዮሐንስ ዘጉራናቋ ኅ ዮሴፍ የብሉዩ ዮሴፍ ቅዱስ ኅ ዮናስ አባ ደ ደሐረጎት ደመቀ ብርሃኔ አቶ ደምበላ ደርግ ደቂቀ ማቲያን ደቂቀ ሲኖዳ ደቂቀ ተክለ ሃይማኖት ደቂቀ አምኀ ደቂቀ አባ ዕዝራ ደቂቀ አባ ዮናስ ደቂቀ ኤዎስጣቴዎስማዕቀበ እግዚአእ ኅ ኅ ኅ ኅ ደቂቀ እስጢፋ ኅ ደቂቀ ጳኩሚስ ኅ ደብረ ሃሌ ሉያ ሃሌሎ ኅ ደብረ ሊባኖስደብረ አስቦት ኅ ደብረ መዓራ ደብረ መገራን ደብረ ማርቆስ ደብረ ማርያም ኅ ደብረ ማፅዖ ደብረ ምጥማቅ ኅ ኅ ደብረ ሰላም ደብረ ሰማዕት ደብረ ሲና ደብረ ቅፍርያ ደብረ ቆየጻቄየጻ ኅ ደብረ ዮስቋም ኅ ደብረ በግዑ ደብረ ቢዘን ኅ ደብረ ብርሃን ኅ ኅ ደብረ አስቦትደብረ ሊባኖስ ኅ ህበሃ ህህ መጠቀም ደብረ አባ ሳሙኤል ደብረ እምፍራዝ ደብረ እግዚአብሔር ደብረ ከስዋ ደብረ ኩሰያት ደብረ ኮሬብ ደብረ ዲጋ ደብረ ዳሞ ኅ ደብረ ገረዛን ኅ ደብረ ገርዜን ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ደብረ ዮን ኅ ኅ ኅ ደብረ ጽዮን ሎሌ ደብረ ፋራን ደንጎ ደዋሮ ኅ ደውለይ ደውላይ ዱስአ ዴስአ ዲልማን ኅ ዲቦ ዲያብሉስ ዲዮስቆሮስ ሊቀ ጳጳስ ዲዮቅልጥያኖስ ኅ ዲድርከም ዲድስቅልያ ዳሞ ዳገ ዳንኤል ነቢይ ዳንኤል ዘፀዓዳ አምባ ኅ ዳዊት ነቢይንጉሥ ዳዊት አፄ ዳዓላ ዴር መሐረቅ ኅ ዴር አልመግጠስ ኅ ዴስአ ድምያኖስ ወንድም ድራጎን ድሮር ድብ ፀር አፄ ኅ ድንበሐት ድድኖ ድግኑ ጀ ጀርመን ጀቅማቅ ሥልጣን ኅ ኅ እፎህ ሀ ጂብራ ጅብ ጠላት ኅ ገ ገሊላ ገላውድዮስ አባ ገማልያል መምህር ኅ ኅ ኅ ኅ ገሪማ አባ ኅ ገርዜንገሪዘን ግ ኅ ገርጌሳ ገሰምቤ ገበሉል ገበዘ አክሱም ኅ ገብረ መሲሕ አባ ገብረ መስቀል አባ ገብረ መስቀል አፄ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ነጋዲ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አቡነ ገብረ ሚካኤል ወንድም ገብረ ማርያም ወንድም ገብረ ማርያም ወንድም ገብረ አምላክ አባ ኅ ገብረ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ገብረ ክርስቶስ ምእመን ገብረ ክርስቶስ ወንድም ገብረ ክርስቶስ ዘቢታንያ ኅ ገብረ ዋሕድ ወንድም ገብርኤል መልአክ ኅ ገብርኤል ጳጳስ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ገነት ኅ ኅ ገኒገኝገይኒ ኅ ኅ ገዘሞ ዝበ ኅ ገይኒ ኅ ገይኒም ገደዶ ጉራጌዎች ጉንዳጉንዴ ጊዘበ ጊዮርጊስ ሰማዕት ጊዮርጊስ ወንድም ኅ ጊዮርጊስ ዘጋስጫዘሰግላ ኅ ኅ ኅ ጋሞ ህበሃ ህህ ጋሳጋስ ኅ ጋዘም ጌዴዎን ወልደ ዮአስ ግሪክ ኅ ኅ ኅ ግራ ምድር ግድም ግፍሜላ ጎልጎታ ጎጃም ኅ ጐሐርብ ኅ ጉን ጐንደትጐንደን ኅ ጐዘም ጐዛምጐዘም ጉጐራጌጉራጌዎች ግብጽግብጻዊግብጾች ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ኅ ጐንጥ ኅ ጐንጽ ኅ ኅ ኅ ኅ ጉጐዝምጉዛም ጐዳሌ ኅ ጓትር ኅ ጠ ጠዞ ጠፋንይ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ ጢሮስ ኅ ጣና ኅ ኅ ጤማይ ጤጠይጤጤ ጥልብያኮስ ኅ ጥናትና ምርምር ቤተ መጻሕፍት የኢትዮጵያ ጦቢት ብሉይ ጦቢያ ብሉይ ጦዘጠዞ ኅ ጦጵያ እፎህ ሀ ደቂቀ እስጢፋኖስ ጨ ጨርቆስቂርቆስ ሰማዕት ኅ ጳ ጳራቅሊጦስ ጳንጠሌዎን ዘጾማእት አባ ጳንጠቆስጤ ጴላጦስ ኅ ኅ ጳኩሚስ አባ ኅ ኅ ጳውሊ አባ ጳውሎስ ወንድም ጳውሎስ ሐዋርያ ኅ ኅ ጳዝዮን ጴጥሮስ ሐዋርያ ኅ ኅ ጴጥሮስ ወንድም ጺጸ ጸሕጋ ጽሕጋ ጸጋ ሥሉስ ወንድም ጺማ ጻክራ ጽሕጋ ኅ ጽዮን ኅ ፀ ፀጋም ምድረሰብአ ፈ ፈላሲዎች ፈላሻዎች ፈረንሳይ ፈራጎ ፈርዖን ኅ ኅ ፈጸጋር ፊልልስ ሐዋርያ ፊልልስ አቡነ ኅ ፊቅጦር ወንድም ፊቤን ህበዐሃ ህህቨ እፎህ ሀ መጠቀም ፋርስ ኅ ፋሲለደስ ግብጻዊ።