Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ያረፉትም በ ደጋ ደሴት ጣና ሃይቅ ነው። ሌላው የዲን ዳንኤል ጥያቄ አባይ አልተጠቀሰም ከአክሱም ነው። መልስ ይህ የተለመደ ነው ዘርዓ ያዕቆብ ምን አልባት እውነተኛ ሰው ካልሆነ እውነተኛ ሃሰብ ነው። ብዙ ሰዎች ተመሳስለውና መስለው የመኖርን ጥበብ የሚማሩት ከሰው ጋር የመኖር ህልውናቸውን ላለማጣት ሲጥሩ ነው። ህዝብ በጀምላ የሚያስበውን እያሰቡ ፈላስፋ መሆን ይከብዳል ወጣ ማለት አላባቸው መጠየቅ መጠራጠር የሚባል ነገር አለና። መልስ ጥያቄውን ማንሳቱ በቂ ነው። ከፕላቶ ትምህርቶች መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሰው ሰው ሲሞት የማትሞት ነፍስ ብለን የምንጠራት የእያንዳንዳችን እውነተኛ ማንነት አማልክት ወደሚገኙበት በመሄድ በዚያ ለፍርድ ትቆማለች ይህ ደግሞ ጥሩ ሰዎች በመተማመን ክፉ ሰዎች ደግሞ በከፍተኛ ፍርሃት የሚጠብቁት ነገር ነውን። አዋቂነት የሚቻል ነገር ከሆነ የታወቀ እና ያልታወቀ ማለት ምንድር ነው። ፍልስፍናዊ ባህሎች የምዕራቡ ዓለም ፍልስፍና የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይኸውም በ ዓክልበ ዓም የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ የአሁኑ ቱርክ ን ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው።
ዘርዓ ያዕቆብ ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ አንዳንዶች ሐተታ ዘርዓ ያዕቆብና ወልደ ሕይወት በገፖኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ከሁለት ዓመት የብቸኝነት የምርምርና የተመስጦ ዘመን በኋላ ማኅበረሰቡን ተቀላቀለ። በዘርዓ ያዕቆብ ኢትዮጵያዊነት ላይ የነ ዓለማየሁ ሞገስን ሙግት በማካተት በርካታ ሙያዊ ትንታኔዎችን በማቅረብ ሁለቱ ሐተታዎች የአንድ ሰው ሥራ እንዳልሆኑ በማስረጃ በማስደገፍ እንዲሁም ዘርዓ ያዕቆብና ወልደ ሕይወት በገፖኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ ሚዛን የሚደፋ ሙግትና ድምዳሜ ያቀረበልን ግን በትውልድ ካናዳዊ በምርጫ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ክላውድ ሳምነር ነው። የዘርዓ ያዕቆብ ፍልስፍና መሠረታዊ ይዘቶች ትንታኔ የዘርዓ ያዕቆብ ፍልስፍና በጣም እምቅ የሆነ ጠንካራ ሙግቶች የያዘና ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን ስለሚዳስስ በዚህ አጭር ጽሑፍ ሙሉ ይዘቱን ማሳየት ከባድ ነው። ሌሎች ጉዳዮች ከተግባራዊነት አንጻር ስንመዝነው ከዘርዓ ያዕቆብ ረቂቅ ፍልስፍና ይልቅ የወልደ ሕይወት ተግባራዊ ፍልስፍና ስለ ግላዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች መሬት ድረስ ወርዶ ያብራራል። ፈላስፋው ዘርዓ ያዕቆብ ኢትዮጵያዊ አይደለም ከሚሉት ውስጥ ጥልቅ የሆነው እና የሌሎችን በተለይም የኮንቲ ሮሲኒንን ሃሳብ የሚያንፀባርቀው ዲን ዳንኤል ክብረት ስለሆነ የሌለውን ፈላስፋ ፍለጋ እና ሌሎች በሚል ካሳተመው መፅሀፍ የጠቀሳቸውን የኮንቲ ሮሲኒና ራሱ ዳንኤል ክብረት የጨመራቸውን ሃሳቦች የዘርአ ያእቆብ የዓለም ስሙ ወርቄ ነው ወርቄ የሚል የስም አወጣጦች በአማራው አካባቢ እንጂ በአኩስም አካባቢ የተለመደ ስሞ አይደለም ዳ ኡርቢኖ መፅሃፉን እንደጻፈው የሚታማውን በደብረ ታቦር አካባቢ ሲኖር የሰማውን ስም መሆን አለበት የተጠቀመው አክሱምም ቢሆን አክስም ውስጥ የተወለደበትን ቦታ አካባቢ ግን አይነግረንም ኡርቢኖ አክሱም አካባቢ ስለነበረ ነው ይህን የትውልድ ቦታ የመረጠው ብሎ መገመት ይቻላል ኢትዮጵያውያን ዘርዓ ያዕቆብ የሚባል ፈላስፋ መኖርን እራሱ ያወቅነው ከአውሮፓውያን ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሱ የሚወራ አፈታሪክ እንኳን የለም። ዘርአ ያእቆብ ትርጓሜ መጻሕፍት እንደተማረ ይነግረናል በቤተ ክርስቲያን የመጻሕፍት ትርጓሜ ትምህርት ብሉይ ሐዲስ ሊቃውንትና መጻሕፍተ መነኮሳት ናቸው ዝርዝር ማቅረብ የሚወደው ዘርአ ያእቆብ ጠቅልሎ መጻሕፍትን ተማርኩ የሚለውን ለመቀበል አስቸጋሪ ነው ያውም በዐሥር ዓመት የሐዲሳት ትርጓሜ ብቻ አምስት ዓመት ይፈጃልና ስለ መምህርነቱ ሲነግረን በአክሱም መጻሕፍትን ለአራት ዓመት አስተምር ነበር ይላል የመጻሕፍት አስተማሪ የሚባል መምህር በቤተ ክርስቲያን የለም የሐዲሳት መምህር የብሉያት መምህር የሊቃውንት መምህር የመጻሕፍተ መነኮሳት መምህር እንጂ ዘርአ ያእቆብ ዳዊትን በነጠላ ያውቀዋል ሐዲስን አንብቦታል ዘርአ ያዕቆብ ሊቃውንቱ ከሚታወቁበት ከትርጓሜ ሊቃውንት ከመጻሕፍተ መነኮሳት ከፍልስፍና መጻሕፍት ፈጽሞ አይጠቅስም ዘርአ ያዕቆብ ዳዊት ከማወቅ ሐዲስን ከማንበብ የዘለለ የብሉይ ትምህርት የለውም ስለዚህም ከብሔረ ኦሪት አሟልቶ መጥቀስ ስላልቻል ሙሴ ሩካቤ ሁሉ ርኩስ ነው አለ ይለናል። ለምን ቢባል ዘርዓ ያዕቆብ ከካቶሊክ እና ከአይሁዳዊነት ይልቅ ኦርቶዶክስን ያውቃታል የአውሮፓ የማህበራዊ ትችት ፈላስፎች ስለ ኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ባህል እና እምነት ሳይሆን በየ ሀገሮቻቸው ስለሚገኙት ቤት እምነቶች ነው የሚጽፉት ዘርዓ ያዕቆብም ያደረገው ይህንኑ ነው ታላቁ ብዕረኛ ቶማስ ፔይን የሚተቸው በቅርብ የሚያውቃቸውን ቤተ እምነቶች ነው ታዲያ ዘርዓ ያዕቆብ ኦርቶዶክስን አብዝቶ የሚነቅፈው ስለሚያውቀት እና ስለሚመለከተው ነው ይህኔ ወደ ሌሎቹ ቢያተኮር ኑሮ ኢትዮጵያዊ አይደለም ለማለት ትልቅ ማስረጃ ያደርጉት ነበር እነ ዲን ዳንኤል። ፈላስፋው ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ በሰፊው የፃፈው ምንኩስና በሰው ልጆች ላይ የጣለውን ጠባሳ ለማስረዳት ነው ለፈለስፈው ከተፈጥሮ የሚያፈነግጥ የሀይማኖት ሰርዓት ከእግዚአብሔር አይደለም ይላል ልክ ነው ተፈጥሮአችን እንድንጋባ እንድንባዛ እንድንደሰት እንጅ እንድንመነኩስ አይደለም ወንጌል ግን ተፈጥሮአችንን ስለኮነነብን ከእውተኛው አምላክ አይደለም ዘርአ ያእቆብ ልጅ የወለደበትን ጊዜ ጥቅምት ገገ ቀን መሆኑን ይነግረናል ኢትዮጵያዊ ጸሐፊ ቢሆን ይህ ልማድ አይኖረውም ነበር እንኳን ያኔ በዐፄ ምኒልክ ዘመንም የልጆች ልደት አይታወቅም ነበር የነገሥታቱ ካልሆነ በቀር መልስ ዲን ዳንኤል የማውቀው በነገሮች ላይ እጅግ አሳማኝ ሀሳቦችን እያነሳ ሲሞግት ነው በፈላስፍው ዘርዓ ያዕቆብ ላይ ያነሳቸው ሃሳቦች ግን በቀላል አመክነዮ ውደቅ የሚሆኑ ናቸው ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸውን የተወለዱበትን ቀን አያስታውሱም ማለት ተገቢ ነውን። ሁለቱም እዚያው ደንቢያ ውስጥ የሚኖሩና ቀድመው የሚተዋወቁ ሰዎች ካልሆኑ በቀር ዘርአ ያዕቆብ እንደሚለው ወልደ ዮሐንስ አኩስማዊ ነው በኋላ ግን በደንቢያ አድባራት ላይ ተሾመ ነገሥታት በባህላቸው አብዛኛውን ጊዜ ሰውን የሚሾሙት በተወለደበት ቦታ ነው እናም ወልደ ዮሐንስ የዚያው የደንቢያ ሰው ቢሆን ነው ደንቢያን የተሾመው ስለዚህ ፈላስፋው ዘርአ ያዕቆብ ይኖር የነበረው ማኅደረ ማርያም አጠገብ ሳይሆን አይቀርም እናም አክሱማዊ ነኝ ማለቱ ዋሽቷል መልስ ይህ ሀሳብ መሰረት ያለዉ መከራከርያ ነዉ ትችቱን ዘርዓ ያያቆብ ኢትጵያዊ ነዉ የሚሉትም የጋሩታል በተለይ ፕር ጌታቸዉ ሀይሌ ይህ መከራከርያ ለኔም ግራ ገብቶኛል እሰከአሁን የዘረዘረኳቸዉ እና ቀጣይም የምዘርዝራቸዉ የሀሳብ ደርቶውች ናቸዉ ይህኛዉ ግነም ፈታኝ ነዉ እንደ ማንኝዉም ግለሰብ ግምቴን ማሰቀመጥ ግን ግድ ይሆንብኛል። ዘርአያቆብና ወልደ ዮሀንሰ ትዉልድ ቦታቸዉን በተመለከተ በሀተታዉ ግልፅ ያላሆነ መሆኑ እና ብዙ ተመራማሪዎች ጥርጥሬያቸዉን መግለፅቸዉ ሙሉ ሀተታዉን ዋጋቢስ አያደርገዉም ቢያንሰ ሁለቱ ግለሰቦች የደንቢያ ሰዎች መሆናቸዉና አለመሆናቸው ሰለልተረጋጋጠ የደንቢያ ሰዋች እንኳ ቢሆኑ አዉሮፓዊያንም ቢሆኑ እኛ እምንፈልገዉ ፍልስፍናዉን ነዉ ዳ ኡርቢኖ ለዲ አባዲ የላከውና በግእዝ የጻፈው የገንዘብ መጠየቂያ ደብዳቤውና በሐተታ ዘርአ ያዕቆብ ላይ ዘርአ ያዕቆብ ሀብቱን ድግፍ የጠየቀበት መንገድ ተመሳሳይ ነው በደብዳቤውና በመጽሐፉ ውስጥ ተመሳሳይ የግእዝ ቃላት ይገኛሉ ለምሳሌ ፍሬ ጻማየ የሚለው አገላለጥ በሐተታ ዘርአ ያዕቆብ ሁለት ጊዜ በሐተታ ወልደ ሕይወት አንድ ጊዜ ይገኛል በዳ ኡርቢኖ ደብዳቤም ይሄው አገላለጥ ይገኛል በተጨማሪም በ በመጋቢት ወር ርዳታን አስመልክቶ በጻፈው ደብዳቤ ላይ ሀብታም በከብት ደኃ በጉልበት የሚል ገለጣ ተጠቅሟል ይህ አባባል ለአንቶኒዮ ዲ አባዲ በ በተላከው የ ሐተታ ዘርአ ያእቆብ ቅጅ የላቲኑ ደብዳቤ ላይ ይገኛል። መልስ ይህ ኡርቢኖ ለአለቃዉ ዲ አበዲ ገንዘብ እንዲሰጠዉ እና እርዳታዉ እንዳይለየዉ የሚማፀንበት ደብዳቤዎች ከሀተታ ዘርአያየያቆብ ጋር መመሳሰል ያዉም በቃላት ደረጃ እንዲይመዉ የሚገረመዉ ኡርቢኖ ጌታዉን ዲ አበዲን እና ደብተራዉ ዘርአ ያቆብ ጌታዉን ሀብቱን እርዳታ የጠየቁበት መንገድ ቢለያይ ነዉ የሚለምን ሰዉ መለማመጥድ አለበት ይህን ሁለቱንም አድርገዉታል በቅዱሰ ገብርኤል ቀን ስለቅዱሰ ገበርኤል ብለዉ የሚለምኑ ሰዋች አንድ ሳይሆኑ አንድ አይነት ሀሳብ ሰላላቸዉ ነዉ የቅዱሰ ገበርኤል ቀን ሰለቅዱሰ ጊዮርጊስ እያለ ቢለምን ብዙ ላያገኝ ይችላል ዳ ኡርቢኖ በኢትዮጵያ የመጻሕፍትህ ጠባቂ አንባቢ ጸሐፌና ተርጓሚ ሲል የገለጠበት መንገድ ራሱን ከሚሲዮናዊነቱ ይልቅ በእነዚህ መስኮች አሠማርቻለሁ ብሎ እንደሚያስብና አለቃው ዲ አባዲም በዚህ መንገድ እንዲያስበው እንደሚፈልግ ያሳያል ዘርአ ያእቆብም ተመሳሳይ ሞያ ነበረው መልስ ኡርቢኖ እና ዘርአ ያኦቆብ ተመሳሳይ ሙያ የላቸዉም ምን አልባት ሁለቱም ሙይ ቀይረዋል። የዳ ኡርቢኖ እና የወርቄ የክርስትና ስም ተመሳሳይ ነው ወርቄ የክርስትና ስሙ ዘርአ ያእቆብ ሲሆን የዳ ኡርቢኖ ደግሞ ሠርባሀፀኡ ያዕቆብ ነው የመጽሐፉ ቀዳማዊ ስም ሐተታ ያዕቆብ ወይም መጽሐፈ ያእቆብ ነበር። ዳ ኡርቢኖ በኋላ የሐተታ ያዕቆብ ጸሐፊ የኢትዮጵያ የክርስትና ስም ቅርጽ ያለው ስም ዘርአ ያእቆብ ብሎታል መልስ በእርግጥ በፓወር ግእዝ ካላንደር ኦገሰት ቀን ስተረጎመዉ ዓም ይሆናል ድንቅ ግጥጥምሽ ነዉ እኔና ዲን ዳንኤል የተወለድንበት ቀን ተመሳሳይ ቢሆን ችግሩ ምንድን ነዉ። ዳ ኡርቢኖ በግንቦት ለአንቶንዮ ዲ አባዲ በጻፈው ደብዳቤ ላይ ሰውን የዚህ ዓለም ማዕከል አድርጎ የሚያይበትን አመለካከቱን አንጸባርቆ ነበር ይህም አስተሳሰብ በሐተታ ዘርአ ያእቆብ ላይ በዚያው መልኩ ይገኛል ዘርአ ያዕቆብ ተፈላስፎ የእግዚአብሔርን መኖር ያመነው ፍጡር ያለ ፈጣሪ ሊኖር አይችልም ከሚለው ሐሳብ ተነሥቶ ነው ይህ አስተሳሰብ ደግሞ በካቶሊክ ትምህርት ቤቶች በስፋት ይሰጥ የነበረው የቶማስ አኩዊኖስ ፍልስፍና ነው ዳ ኡርቢኖ ወደ ግእዝ በተረጎመው በቅርጣግና ሌሊቶች ፐከፀ ርበከ እዘፀከ እና በሐተታ ዘርአ ያእቆብ መካከል ተመሳሳይ የሆኑ የሰዋሰው አገባቦችና አገላለጦች አሉ መልስ መልካም ኡርቢኖ በኢትዮጵያ ባህልና በዘረዓ ያዕቆብ ፍልልስፍና ተፅዕኖ ስለወደቀ ተመሳሳይ ይዘት ያለዉ ደበዳቤ ቢፅፉ አይገርምም በተለይም ወደ መጨረሻዉ ኡርቢኖ አኗኗር ፈላስፋዉ ተፅዕኖ ስላደረገበት የሚፅፈዉ ደብዳቤ ከአንድ ሰባኪ መነኩሴ የማይጠበቅ ፍልስፍና አንፀባርቋል ኢትዮጵያ ዉሰጥ ለመኖር ስሊም ካቶሊክ አይደለሁም ያለበት ጊዜም ነበር። የገፖ ክዘመን ድንቅ ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ ዘርዓ ያዕቆብ በሚያሳዝን የሲቃ ድምጹ ዘመን በማይሽረው ሀትታው እንዲህ ይላል ከሁሉ ሰው ከፈረንጆቹና ከግብፃዊያን ጋር እስማማለሁ እኔ በሃገሬ መፅሃፍት ሳስተምር ብዙዎቹ ጓደኞቸ ጠሉኝ በዚህ ዘመን የባልንጀራ ፍቅር ጠፍቶ ነበርና ቅናት ያዛቸው ከአክሱም ካህናት አንድ ወልደ ዮሃንስ የተባለ ጠላቴ የንጉስ ወዳጅ ስለነበረ ወደ ንጉሱ አፄ ሱስንዮስን ገብቶ እንደዚህ አለው ይህ ሰው ህዝብን ያሳስታል ስለሃይማኖታችን ኦርቶዶክስን እንነሳና ንጉሱን እንግደለው ካቶሊክ ስለነበርን ፈረንጆቹንም እናባራቸው ይላል እያለ ይሄን እና ይሄን በመሰለ ውሸት ከሰሰኝ እኔም ይህን አውቄ ገና ለገና ዐጉሱን ይገድለኛል ብዮ ፈርቼ የነበረኝን ሶስት ወቄት ወርቅና የምፀልይበትን መዝሙረ ዳዊት ይዝ በሌሊት ሸሸሁ ወዴት እነደምሄድ ለማንም አልተናገርኩም ወደተከዜ በረሀ ገባሁ በነጋታውም ራበኝ ከሀብታሞች ገበሬዎች እንጀራ ለመለምን እየፈራሁ ወጣሁ ሰጡኝና በልቼ እየሮጥኩ ሄድኩ እንዲህ እያልኩ ብዙ ቀን ቆየሁ በኋላም ሰው የለለበት በርሃ አገኝሁ መልካም ዋሻም አገኘሁና ሰው ሳያየኝ በዚህ ዋሻ እኖራለሁ ብየ ወሰንኩ ቁጥር የሌለው ክፋታቸውን አውቄ ከሰዎች ጋር መኖር ጠላሁ ሌሊት መጥተው የበርሃ አራዊት እንዳይበሉኝም በድንጋይና በአሽዋ አጥር ዋሻየን አጠረኩ እሚፈልጉኝ ሰዎች ወደኔ ቢመጡ የማመልጥበት መውጫ አዘጋጀሁ ሱስንዮስ እስኪሞትም ድረስ በዚያ ሁለት ዓመት ቆየሁ ሐተታ ዘርዓ ያዕቆብ ምዕራፍ ወርቄ ማለት የመናገር ነፃነቱን ተነፍጎ ራሱን ደብቆ የኖረ ታልቅ የማለዳ ኮከብ ነበር። አንደኛው ፍልስፍና ጠያቂ ምክንያታዊና ሂሳዊ መሆኑ ሁለተኛው የሚያተኩረው በተናጠል ጉዳዮች ላይ ሳይሆን ባጠቃላይ ጉዳዮች ላይ መሆኑና ሦስተኛው የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ስለዓለም ስለ ሰውና ስለ ሰው ልጅ አስተሳሰብ አጠቃላይ ጉዳዮች መሆኑ ነው። የሰው ልጅ ፍልስፍናን ለምን ይፈልጋል። በተናጠል ነገሮች ዙሪያ የሚነሱ ጥያቄዎችና ችግሮች በተፈጥሮና በማሕበራዊ ሳይንሶች የሚጠና ሲሆን እነዚህ ሳይንሶች ስለዓለም ስለሰውና ስለ ሰው አስተሳሰብ ሊያጠኑአቸውና ሊመልሱአቸው የማይችሉአቸው አጠቃላይ ጥያቄዎችና ችግሮች ለፍልስፍና የሚተው ናቸው በሰው ልጅ የታሪክ ሂደት ውስጥ በመጀመሪያ ሰው ላነሳቸው ጥያቄዎች ምክንያታዊ የሆኑ መልሶችን መስጠት የሞከረው ፍልስፍና ነው። ለዚህ ነው በዕድገት ታሪኩ ውስጥ የሰው ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ምክንያታዊ አስተሳሰብ ፍልስፍና ነው የሚባለው በተለያዩ ነገሮች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሌሎች የዕውቀት ዘርፎች በታሪክ ሂደት ውስጥ ከፍልስፍና እየወጡ የራሳቸውን ነጻ አውድ ሲፈጥሩ እነርሱ የማይደርሱባቸው ጉዳዮች ለፍልስፍና ብቻ የሚተው ሆነ ዛሬ ሰው ካነሳቸው ጥያቄዎች መካከል የተወሰኑት በተግባራዊ ሳይንሶች የተመለሱና የሚመለሱ ናቸው። የማይታወቁትንና በትንሹ የሚታወቁትን ነገሮች በሚገባ የማወቅና ምክንያታዊና ሂሳዊ በሆነ መንገድ የማሰብ ፍላጎት በሰው ልጅ ተፈጥሮ ውስጥ አለ። አርስቶትል እንዳለው ያአወቀው አላወቀው ሁሉም ሰው ፍልስፍና አለውጊ እናም ሁሉም ሰው በተወሰነ ደረጃ ፈላስፋ ነው። ከዚህ አንጻር ሲታይ የፍልስፍና ዋና ጉዳይ የሰውን ልጅ አዕምሮ ማልማት ነው።