Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የይዞታ መሬቱን የለቀቀ ማናቸውም ባለይዞታ በመሬት ማስለቀቅና ካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ ከባለይዞታዎች ለሚቀርቡ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ተገቢ ምላሾችንና ማብራሪያዎችን ይሰጣል ግልጽነት የተላበሰ አሰራር እንዲሰፍን ያደርጋል ለልማት ተነሽዎች የዘላቂ መልሶ ማቋቋሚያ ድጋፍ በገንዘብ በቦታ አቅርቦት በመሰረተ ልማት ዝርጋታና ሌሎች መሰል ድጋፎች የማከናወን ኃለፊነትና ግዴታ ይኖርበታል የግምት ስራ ወጪዎችን በተመለክተ ለሀዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሰፈረ ንብረት ስለዛክከፈል ካሳ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በወጣው ደንብ ደንብ ቁጥር መሰረት ለሚሠየመው የንብረት ገማች ባለሙያ ቡድንና እንዳሰፈላጊነቱም ለካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ የሚከፈለውን አበል ጨምሮ በዚህ መመሪያ መሠረት ንብረት ለመገመት አስፈላጊ የሆኑ ወጪዎች እንደ አግባብነቱ በወረዳው አማካኝነት የሚሸፈን ይሆናል ።
መመሪያ ቁጥር ዓም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የገጠር መሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ለንብረት ካሣ የሚከፈልበትን እና የልማት ተነሽዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም ተሻሽሎ የወጣ የአፈጻጸም መመሪያ የተሻሻለው የክልሉ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም መወሰኛ አጅ ቁጥር እና ደንብ ቁጥር እንዲሁም ከፌደራል አዋጅ ቁጥር እና ደንብ ቁጥር ዓም ጋር ተጣጥሞ ተግባራዊ እንዲሆን በማስፈለጉ የክልሉ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም መወሰኛ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ እኖ ይህንኑ ለማስፈጸም በወጣው ደንብ ቁጥር አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ በ እሰከ በተዘረዘሩት ድንጋጌዎች መሰረት የገጠር መሬትን ለሕዝብ ጥቅም ለማዋል ሲባል ለማንኛውም የገበር መሬት ባለይዞታ በቅድሚያ ተገቢውን ካሣ እንዲያገኝ በማድረግ በተለያዩ የኑሮ አማራጭ የስራ ዘርፎች በዘላቂነት እንዲቋቋሙ የሚያስችል ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ መንግስት ለሕዝብ ጥቅም ለሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች መሬትን በመጠቀሙ እና የክልሉ ከተሞች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፉ የነዋሪዎቹም ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ በከተሞች ፕላን መሠረት ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ለመሠረተ ልማት ለኢንቨስትመንትና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውል የከተማ መሬትን መልሶ ማልማት አስፈላጊ በመሆኑ እንዲሁም በዝክር ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች መሬት አዘጋጅቶ ማቅረብ በማስፈለጉ የመሬት ይዞታ እንዲለቅ ለተደረገ ባለይዞታ የሚከፈለውን ካሣ ለመተመን እንዲቻል ግምት ውስጥ መግባት የሜገባቸውን መሠረታዊ መርሆዎችን ለይ ማሻሻል በማስፈለጉ ለልማት የሚፈለገውን መሬት የማስለቀቅ ካሣውን የመተመን የመክፈል እና የልማት ተነሺዎችን በዘላቂነት መልሶ የማቋቋም ሥልጣንና ኃላፊነት ያለባቸውን አካላት በግልጽ ለይቶ ለመወሰን በማስፈለጉኑ የአማራ ብሄራዊ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ተሻሽ በወጣው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም መወሰኛ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና በደንብ ቁጥር በተሠጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል ክፍል አንድ ጠቅላላ ድንጋጌ አጭር ርዕስ ይህ መመሪያ የገጠር መሬት ይዞታ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የሟለቀቅበትንነ የንብረት ካሳ የሚከፈልበትንና የልማት ተነሽዎችን በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም እንዲቻል የወጣ መመሪያ ቁጥር ዓም ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ትርጓሜ የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ ዓመታዊ ገቢ ማለት ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ በአንድ የምርት ዘመን በይዞታ መሬቱ ላይ ከተከናወነ ከማናቸውም ሰብል ልማት ቋሚ ተክልና የመኖ ልማት በአማካይ ምርታማነት ተሰልቶ በወቅቱ የገቢያ ዋጋ ታስቦ የሚገኝ ገቢ ነው ጥወቅቱ የገበያ ዋጋ ማለት እንደ አግባቡ ኃላፊነት በተሰጠው መንግስታዊ ተቋም በንብረት ገማች ባለሙያዎች ወይም በህጋዊ አማካሪ ድርጅት የካሳ ግመታ በሚከናወንበት ዕለት ወይም ጊዜ የተጠና እና ጥናቱ የተደረገበትን የገቢያ መረጃ መነሻ አድርጎ የሚወሠን የንብረት ወይም የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ዋጋ ነው ዋገማች ባለሙያ ቡድን ማለት በመሬት ይዞታ ላይ ቋሚ ንብረትና የለማን ፃብት ለመቁጠር የካሳ መጠን ለመተመን የስራ ልምዱና እውቀተ እንዳለው ታምና ጉዳዩ በሚመለከተው የወረዳም ወይም የከተማ አስተዳደር የተደራጀ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ስር የሚሰሩ የባለሙያዎች ቡድን ጡ የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ ማለት በድንግል መሬት ወይም ለረዥም ጊዜ ከምርት ተግባር ውጭ ሆኖ በቆዬ ይዞታ ላይ ይህንኑ ለእርሻ ሥራ ለማዘጋጀት ሲባል በምንጣር ድንጋይ በመልቀሯ ዚህ ተር ሥራ የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉትን ሥራዎች እና መሬቱን በማስተካከል ለተከናወኑ ተግባራት የዋለ ወጪ ነው የህዝብ ጥቅም ሣለት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማጎልበት አግባብ ያለው የፌዴራል ወይም የክልል አካል በመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ወይም በልማት ዕቅድ ወይም በመሠረተ ልማት መሪ ፕላን መሠረት ለሕዝብ የተሻለ የጋራ ጥቅምና ዕድገት ያመጣል ተብለ የተወሰነው ነው የንብረት ካሣ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሟወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው የመፈናቀያ ካሣ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስን ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው መልሶ ማቋቋም ማለት ለልማት ተብሎ በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው የልማት ተነሺዎች ዘላቂ የቧ ምንጭ አንዲኖራቸው የሚሰጥ የሜደረግ ድጋፍ ነው ቀመር ማለት ለህዝብ ጥቅም በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሠፈረ ንብረትና ለለማ ቋሚ ንብረትና ሃብት ወጥ የሆነ የካሣ ስሌት የሚሰራበት ዘዴ ነው የማቋቋሚያ ፓኬጅ ማለት ለህዝብ ጥቅም ሲባል ከመሬት ይዞታቸው የሚነሱ ባለይዞታዎች ከንብረት ካሣ እና መፈናቀያ ካሣ በተጨማሪ በአካባቢያቸው ከሚካሄደው ልማት ተጠቃሚ የሣሆኑበት እና ዘላቂ የሆነ የገቢ ምንጭ ሊኖራቸው የሚያስችል አስፈላጊ የሆነ የመስሪያ ቦታ አቅርቦት የገንዘብ የሥልጠና እና የማማከር አገልግሎት ተሰጥቷቸው ወደ ስራ የሚገቡበት እና ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሁኔታ በፓኬጅ ተቀርጾ ተግባራዊ የሚደረግበት ነው የጉዳት ደረጃ ማለት የይዞታ መሬት የለማ ቋሚ ንብረት ወይም ኑሮው የተመሠረተበት የገቢ ምንጭ በተለያየ ደረጃ ለልማት ሲባል ይዞታውን በመለቀቁ የሚደርስ ጉዳት ነው ማጨሻ ቦታ ማለት ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ በይዞታው ላይ የመኖሪያ ቤት ሰርቶ በእርግጥም እየኖረበት ያለ ቦታ ነው ቢሮ ማለት የአብክመ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ነው የተፈጻሚነት ወሰን ይህ መመሪያ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን ካሣ የሚከፈልበትንና ተነሺዎች መልሰው በዘላቂነት የሚቋቋሙበትን ሁኔታ በሚመለከት በክልሌ ውስጥ ባሉ የከተማም ሆነ የገጠር አስተዳደር በማገኝ የገጠር መሬት ላይ ተፈጻሚ ይሆናል መርሆዎች የመሬት ይዞታ ለሕዝብ ጥቅም እንዲለቀቅ የሚደረገው በመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ወይም በከተሞች መዋቅራዊ ዕቅድ ወይም በመሠረተ ልማት መሪ ፕላን መሠረት መሆን አለበት ለሕዝብ ጥቅም መሬት ሲለቀቅ የሚከፈል ካሣና የሰጥ የማቋቋሚያ ድጋፍ የተነሺዎችን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሻልና የሚያስቀጥል መሆን አለበት በክልሉ መንግሥት ለሜከናወን ልማት የይዞታ መሬትና የቋሚ ንብረት ሲነሳ የሚከፈል ካሣ ተመን ተመሳሳይ መሆን አለበት ለሕዝብ ጥቅም መሬት እንዲለቀቅ ሲደረግ አሰራሩ ግልጽ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነትን የተላበሰ መሆን አለበት ክፍል ሁለት ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅባቸው ሁኔታዎች መሬት የማስለቀቅ ሥልጣን ኮን የከተማ ወይም የወረዳ አስተዳደር በፌዴራል መንግሥት ወይም በክልል መስተዳድር ምክር ቤት ለህዝብ ጥቅም ሊውል ይገባል ተብሎ የተወሰነውን መሬት የማስለቀቅ ሥልጣን አለው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው ቢኖርም ለሕዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሜለቀቀው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የተሻለ ልማት ያመጣል ብሎ የፌዴራል መንግሥት የክልል መንግስት የከተማና የወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት በመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ወይም በልማት ዕቅድ ወይም በመሠረተ ልማት መሪ ፕላን መሠረት ታምኖበት ሲወሰን መሬት እንዲለቀቅ ይደረጋል የመሬት ይዞታ ባለመብትነትን ስለማጣራት የልማት ተነሺዎች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው የመሬት ባለይዞታነትን የሚያረጋግጥ የማረጋጐዔ ደብተር ማስረጃ ወይም ሠነድ በሕግ ሥልጣን የተሰጠው አካል በሚያወጣው መርሃግብር መሠረት ማቅረብ አለባቸው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ማስረጃ የቀረበ። ሬት ላይ ሰብል ቋሚ ተክል ወይም ሌላ ንብረት ከሌለ ባለይዞታው የመፈናቀያ ካሣ ከተከፈለው በኋላ በ ቀናት ውስጥ ይዞታውን ለወረዳው ወይም ለከተማው አስተዳደር ማስረከብ አለበት በሕገወጥ መንገድ በተያዘ ቦታ ላይ ለሰፈረ ለተፈራ ንብረት ካሣ መክፈል ሳያስፈልግ ለሰባት የሥራ ቀናት የሚቆይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ወይም በቦታው በሰፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ እንዲለቀቅ ይደረጋል የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ባለይዞታ ወይም ባለንብረት በዚህ አንቀጽ ንዑሰ አንቀጽ እና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ያለ በቂ ምክንያት ይዞታውን ካላስረከበ የከተማው ወይም የወረዳው አስተዳደር መሬቱን ለመረከብ የፖሊስ ኃይል መጠቀም ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት በፖሊስ ኃይል እንዲለቅ የተደረገ ባለይዞታ ግንባታ በህግ አስገዳጅነት እንዲፈርስ የተደረገ እንደሆነ ያንባታውን ለማፍረሰ የወጣውን ወጪ ባለይዞታው እንዲሸፍን ወይም ባለይዞታው ከሚከፈለው የካሳ መጠን ላይ እንዲቀነስ ሊወሰን ይችላል ማንኛውም ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ያለውን የዛፍ ተክል ቆርጦ ለማንሳት ፈቃደኛ ካልሆነ ለባለይዞታው የተወሰነው ካሳ ተከፍሎት ዛፉን መቁረጥ አስፈላጊ ከሆነ በጨረታ እንዲሸጥ ተደርጎ ገንዝቡ በከተማ ወይም በወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ተቋም በኩል ገቢ እንዲሆን ይደረጋል ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የሚለቀቁ መሬቶችን ስለ ማሳወቅና የለማ ንብረት ቆጠራ ጥሪን ስለማስተሳለፍ በፌደራልም ሆነ በክልልም ደረጃ የሚቀርቡ የመሬት ማስለቀቅ ጥያቄዎችን አስመልክቶ ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ወይም የልማት ፕሮጀክቱ ባለቤት ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የሚፈለገውን መሬት ለማስለቀቅ እንዲቻል የይዞታውን ስፋት መሬቱ የሚገኝበትን ትክክለኛ ስፍራ መሬቱ የተመረጠበትን አግባብና ሌላ አማራጭ አለመኖሩን ከሚያብራራ መግለጫ ጋር መረጃዎችን በካርታ በማስደገፍ በመሬቱ ላይ የታቀደው ስራ ከመጀመሩ ቢያንስ ከአንድ ዓመት በፊት ለቢሮው ወይም ለተዋረድ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም እንዲታወቅ ማድረግ ይኖርበታል በተዋረድ የሚገኘው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም የቀረበውን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ንብረቶቹ እንዲነሱና መሬቱ እንዲለቀቅ ለባለይዞታዎቹ ያሳውቅ ዘንድ በመሬቱ ላይ የታቀደው የልማት ስራ ከመጀመሩ ቢያንስ ከ ወራት በፊት የወረዳ ወይም የከተማ አስተዳደር እንዲያውቀው ያደርጋሉ ለሀዝብ ጥቅም ሲባል የሚለቀቁ መሬቶች አካባቢ ለሚገኘው ህብረተሰብ ስለታሰበዉ ልማት ስለሚለቀቁት መሬቶች ስፋት መሬቱ ስለተመረጠበት አግባብና ስለ አጠቃላይ አፈጻጸሙ በቂ ግንዛቤ አንዲኖረው በቅድሟያ መደረግ ይኖርበታል የሚፈለገው መሬት ለህዝብ ጥቅም መሆኑን የተወሰነበትንና የማስለቀቂያ ትእዛዝ የከተማ ወይም የወረዳው አስተዳደር አግባብ ላለው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም መላክ አለበት የገጠር መሬት አስተዳዳርና አጠቃቀም ተቋም ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትንና የንብረት ካሳ የሚከፈልበትን ሁኔታ አስመልክቶ ለልማት የተፈለገውን መሬት ስፋት በካርታ በማስደገፍ መሬቱ የሚለቀቅበትንና ንብረቶቹ የሚነሱበትን ጊዜ ሊከፈለው የሚገባውን ካሳ ምትክ መሬት ስለመኖሩ ወይም ስለ ለመኖሩና ሰለ ቅሬታና ይግባኝ አቀራረብ በማብራራት ለባለይዞታው ከ ቀናት በፊት በቅድሚያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የመስጠት ኃላፊነት አለበት መሬቱ በወረዳ ወይም በከተማው አስተዳደር ወይም በህብረተሰቡ አነሳሽነትና ጥያቄ እንዲለቀቅ የሚያስፈልግና ካሳ ከፋዩም ወይም ትክ መሬት የሚሰጠው ህብረተሰቡ ራሱ ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ መሬቱ የሚገኝበት ቀበሌ ህዝብ በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉ የግድ ሲሆን ይኸው ለወረዳ ወይም ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ቀርቦ ካልፀደተ ተፈፃሚ አይሆንም ማንኛውም ባለይዞታ ለህዝብ ጥቅም መሬቱን እንዲለቅ ውሳኔ የተሰጠበት እንደሆነ መሬቱ በሚለካበትና የለማ ንብረቱ በሚቆጠርበት ወቅት ይሀንኑ በቦታው ተገኝቶ እንዲያስለካ እንዲያስቆጥርና መተማመኛ እንዲፈርም በአካል ሊነገረው ወይም በጽሁፍ ማስታወቂያ ወይም በግል ለባለይዞታውና ለቤተሰቡ አባላት በሟደርስ ደብዳቤ መልእክቱ እንዲደርሰው ይደረጋል በንብረፐጉ ቆጠራ ወቅት የምንጠቀመው የመሬት ልኬታ መረጃ ከእጅ ሯጅፒኤስ ውጭ ባለ የተሻሻሉ የቅየሳ መሳሪያዎች ተለክቶ የሚገኘ መረጃን መሆን ይኖርበታል ለካሳ ትመና አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ስለማሰባሰብ በዚህ መመሪያ መሰረት የንብረት ገማች ባለሙያዎች ለንብረት ግመታ ስራው የሚሰበስቧቸው የመሬት ልኬታና የመሬት ሃብት መረጃዎች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ዝርዝሮች ሊይ ሀ የመሬቱ ባለይዞታዎች ሙሉ ስም ከነ አያት እና የመኖሪያ አድራሻ ለየባለይዞታው የይዞታተጠቃሚሟነት ማረጋገጫ ማስረጃዎች ማለትም የይዞታ መሬቱ መለያ ቁጥር የይዞታው ሰፋትመሬቱ የሚገኝበት ልዩ ሰፍራ ወይም አዋሳኞቹ እና ከይዞታው የሚቀነሰው መሬት በሄር የማሳ ካርታ የሚያመለክት መረጃዎች መሟላት ይኖርባቸዋል። የካሣ ግመታ ስለማካሄድ ለሀዝብ ጥቅም ሲባል ህጋዊ የመሬት ይዞታ በሚለቀቅበት ጊዜ የሚከፈለው የካሳ ክፍያ ሀ በይዞታው ላይ የተደረገውን ቋሣ ማሻሻያ እንዲሁም ለይዞታው ያወጣውን የጉልበትና የገንዘብ ወጩ የሚሸፍን ለ በይዞታ መሬቱ ሳይ ያፈራውንና አንስቶ ሊወስደው የማይችለውን ንብረት ደግሞ ባለበት ሁኔታ ለመተካት የሚያስችል መሆን አለበት ንብረቱ ከተነሣ በኋላ እንደገና ተተክሎ መስጠት የሚገባውን አገልግሎት ወይም ጥቅም እንደነበር ወይም ከቀድሞው ባልተለዬ ሁኔታ መስጠት የሚችል ሲሆን ካሳው ንብረቱን በነበረበት ሁኔታ መልሶ ለመተካት ለንብረቱ ማንሻ ማዛወሪያና መልሶ ለመትከያ የሚውሉትን የማቴርያል የጉልበት የአስተዳደርና ሌሎች ወጪዎች የሚሸፍን ይሆናል ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ መሬቱን ከአንድ ዓመት በላይ እስከ ሚመለስበት ጊዜ እንዲለቅ የተደረገ እንደሆነ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንተጽ መሰረት አንስቶ መውሰድ ላልቻለውና በመሬቱ ላይ ላፈራው ቋሚ ንብረት ወይም ሳደረገው ቋሚ የመሬት ማሻሻያ ከሚከፈለው የካሳ ክፍያ በተጨማሪ እስኪቋቋም ድረስ ሊያጣው ይችል የነበረውን ጥቅምና ጉዳቱን ለማካካስ የሚያስችል የመፈናቀያ ካሣ የይዞታ መሬቱ እስኪመለስ ድረስ በሚለቀቅባቸው ጊዜያት ልክ ተባዝቶ ይከፈለዋል የመፈናቀያ ካሣው መጠን የቅርብ አምስት ዓመታት አማካይ ምርታማነትና የወቅቱን የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ሆኖ በመኸር በቀሪ ዕርጥበት በበልግ ወይም በመስኖ የሚለሙ መሬቶችን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ በ ተባዝቶ የሚፈፀም ይሆናል በመሬት የማስለቀቅ ሂደት አንድ አነስተኛ የማሳ መጠን ሊኖረወ ከሚገባው ስፋት በታች የሆነና በቅርጽም ሆነ በመጠን እራሳቸውን አስችሉ ለማልማት አመች ያልሆኑ ቁርጥራጭ መሬቶች ከተፈጠሩና ለባለይዞታው ጉልህ ጠቀሜታ የሌላቸው ስለመሆኑ ከተረጋገጠ በቅድሚያ ለቁርጥራጭ ይዞታዎቹ ብቻ ለይቶ ካሳን በማስላት እንዲህ ያለው ይዞታ ወደ አጎራባች ማሳ እንዲካተት ማድረግና የካሳ ክፍያውንም ይዞታውን በተጨማሪነት የተረከበው ባለይዞታ አመች በሆነ የአከፋፈል ስርዓት እንዲከፍለው ይደረጋል ሆኖም ግን ይህንን ዓይነቱን የመሬት ይዞታ የአጎራባች ማሳዎች ባይዞታዎች ሊረከቡት ፈቃደኛ ካልሆኑ ካሳው ከተለቀቀው ይዞታ ንብረት ግምት ጋር ተዳምሮ እንዲከፈልና ይዞታው በጋራ ሃብትነት እንዲያገለግል ይደረጋል ለሀዝብ ጥቅም ሲባል ከሚለቀቀው መሬት ጋር ሲወዳደር በስፋቴ በምርታማነቱ እና ከመኖሪያ ቤቱ ባለው ርቀት ተመጣጣኝ የሆነና በቀላሉ ታርሶ ምርት ሊያሰገኝ የሚችል ትክ መሬት የሚሰጠው መሆኑ በከተማ ወይም በወረዳው አስተዳደር እና አግባብ ባለው የገጠርመአስአጠተቋም በኩል የተረጋገጠለት ማንኛውም ባለይዞታ መሬቱ ለአንድ ዓመት የሚያስገኘውን አማካይ ዓመታዊ ገቢ ወይም የቅርብ አምስት ዓመታት አማካይ ምርታማነት በወቅቱ የገቢያ ዋጋ ተሠልቶ የመፈናቀያ ካሳ እንዲያገኝ ይደረጋል ትክ መሬት ካለ ወይም ከተገኘ በቀዳሚነት የሚሰጠው መሬታቸውን በቋሚነት ለሜለቁ ባለይዞታዎች ይሆናል በግል ይዞታ መሬት ላይ በጽሁፍ በተደረገና የኪራይ ውል ለመመዝገብ ስልጣን ባለው አካል የተመዘገበ የኪራይ መሬት ሌላ አማራጭ መሬት ባለመኖሩ የውለታ ዘመኑ ከማብቃቱ በፊት ለህዝብ አገልግሎት እንዲለቀቅ የተደረገ እንደሆነ ካሣው ለመሬቱ ባለይዞታ ይከፈለዋል መሬቱን ያከራየው ሰው ለተከራዩ በጽሁፍ በተገለጸው የኪራይ ውል መሰረት በቅድሚያ ለተከፈለ የቀሪ የኪራይ ዘመን ብቻ በካሣ ከተገኘው ገንዘብ ተሰልቶ ይከፈለዋል በጽሁፍ በተደረገው ውል መሰረት ከተደረገው የኪራይ ውል ዘመን በላይ የሚከፈለውን የመፈናቀያ ካሳ በስሌቱ መኗረት ቋሚ ባለይዞታው እንዲያገኝ ይደረጋል ሆኖም በጽሁፍ ላልተደረገና ላልተመዘገበ የኪራይ ውል ካሳው የሚከፈለው ለባለይዞታው ብቻ ይሆናል በሊዝ የተሰጠ መሬት የውሉ ዘመን ከማብቃቱ በፊት ሊለቀቅ የሚችለው መንግሥት ሳፀደቃቸው የልማት ፕሮግራሞች ማስፈፀሚያነት በወረዳ ወይም በከተማ አስተዳደር ውሳኔ ሲታመንበት በመሬቱ ላይ ላፈራው ቋሚ ንብረት ለሊዝ ባለመብቱ ከሚከፈለው ካሳ በተጨማሪ ያልተጠቀመበት የሊዝ ክፍያ ካለው ተመላሽ ይደረግለታል ነግር ግን የቋሚ የማፈቀያ ካሳ አይከፈለውም ለሀዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቀው መሬት ላይ የሚገኝ የጮታን መካነ መቃብር የፈረሰ እንደሆነ ለዚሁ የሚከፈለው ካሳ መካነ መቃብሩን ለማንሳት ተለዋጭ የማረፊያ ቦታ ለማዘጋጀት አጽሙን ለማዛወርና ለማሳረፍ እንዲሁም ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለሚደረግ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ስርዓት ማስፈፀሚያ የሚያስፈልጉትን ወጪዎች ያጠቃልላል ለተጠቀሱት ወጪዎች በወቅቱ የገቢያ ዋጋ መሰረት የአካባቢውን የእቃ የትራንስፖርት አገልግሎትና የሰው ጉልበት ግምት ውስጥ እንዲገባ ይደረጋል በይዞታ መሬት ላይ በለማ ንብረት ዋጋ ግመታ ውስጥ ስለሚካተቱ ጉዳዮች በዚህ መመሪያ መሰረት የሚካሄድ የንብረት ግመታ በይዞታው ላይ ለማው ቋሚ ንብረትና በመሬቱ ላይ የተደረጉ ቋሚ ማሻሻያዎችን መሰረት ያደረገ በመሆኑ የሚከተሉትን ዝርዝር ጉዳዮች የሚያካትት ይሆናል ለመኖሪያ ቤት ለሰብል መጋዘን ለእንሰሳት መጠለያ ቤትና ለመሳሰሉት አገልግሉቶች የተከናወኑ ግንባታዎች በባለይዞታው አማካኝነት የለሙ ቋሚ ተክሎች ዛፎችና ወቅታዊ ወይም ዓመታዊ ሰብሎች የመሬት ልማት በተደረገባቸው ድንግል መፊቶች ላይ መሬቱን ለተፈላጊው አገልግሎት ለማዋል ሲባል የምንጣሮ መሬት የማስተካከል ድንጋይ የመልቀም ወይም ይህንኑ የመሳሰለ ማናቸውም ተግባር ቋሚነት ያለውና ከመሬቱ ጋር የተያያዘ አጥርና የእንሰሳት በረት ወይም ጉረኖ በአገልግሎት ላይ የሚገኝ የመስኖ አውታርና የውሃ ማፋሳሻ ቦዮች ግንባታ ለአፈር እና ውሃ እንክብካቤ ሲባል ተሰርተው በአገልግሎት ላይ ሉ የአፈር ጥበቃ ሕዳጎች ሌሎች ቋሚ የመሬት ማሻሻያ ስራዎች ተቆፍረው አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉ የውሃ ጉድጓዶች የጎለበቱ ምንጮች ኩሬዎችና ሌሎች ውሃ እንዲያጠራቅሙ የተሰሩ ግንባታዎች በፃጠሸ መሬት ላይ የሚገኝ ሳር የመኖ ዛፎችና ከንብረቶቹ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶች ወይም የተደረጉ ማሻሻያዎች በገጠር መንግስታዊ ወይም መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የመሬት ይዞታቸው ለልማት ሲነሳ የንበረትና የቋሚ ማሻሻያ ካሳ ስለሚከፈልበት ሁኔታ በተሻሻለው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅና ደንብ መሰረት በክልሉ ውስጥ ሥራቸውን የሚያካሂዱ መንግስታዊ መቤቶች ድርጅቶችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተግባራቸውን እንፌያከናውኑ የተሰጣቸው የይዞታ መሬት ለህዝብ ጥቅምና ለሃገራዊ ልማት አስፈላጊ ሆኖ ከይዞታቸው በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ እንዲለቁ ውሳኔ የተሰጠ እንደሆነ በመሬቱ ላይ ላለሙት ቋሚ ንብረትና ላከናወኑት ቋሚ የመሬት ማሻሻያ ወጭዎች ወደነበሩበት ሁኔታ መልሶ ለመተካት የሚያስችል ካሣ ተከፍሏቸው እናወይም ትክ መሬት ተሰጥቷቸው እንዲለቁ ይደረጋል የመሬት ይዞታ መብት በሚታጣበት ጊዜ ስለሚከፈል ካሣ ማንኛውም ባለይዞታ በመሬት ይዞታው የመጠቀም መብቱን በህግ አግባብ እንዲያጣ ሲወሰን ወይም የባለይዞታነት መብቱ በህግ ሲቋረጥ በልማት ምክኒያት ይዞታው የተነሳበትን ባለይዞታ አይመለከትም ባለይዞታው በመሬቱ ላይ ያለማውን ቋሚ ንብረት አንስቶ የመውሰድ ወይም አንስቶ መውሰድ የማይችለውን ደግሞ በዚህ መመሪያ ስለቋሚ ንብረት ካሳ አከፋፈል በተደነገገው መሰረት በቅድሚያ ተመጣጣኝ ካሳ እና የመሬቱን ለምነት ጠብቆ ለማቆየት ያወጣውን የማሻሻያ ወጪ ያገኛ ሆኖም የመፈናቀያ ካሣ የማግኘት መብት አይኖረውም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖቀዶም ባሉት አሰራሮች የገጠር መሬት ይዞታ አግኝተው ነገር ግን በተሻሻለው የገጠር መሬት አስተዳዳርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር መሰረት የይዞታ መብታቸውን በህግ ሲያጡነ በመሬት ላይ ላፈሩትና አንስተው ለማይወስዷቸው ቋሚ ንብረቶች ተገቢው የንብረት ካሳ በህጉ መሰረት መሬቱን በሚረከበው አካል ክፍያ ይፈጽማል መሬቱን የሚረከበው አካል መክፈል የማይችል ከሆነ ወይም ፈቃደኛ ካልሆነ መክፈል ለሚችል አካል መሬቱ ይተላለፋልይሰጣል መሬቱን በራሱ ፍላጎት በፈቃደኝነት ለሚለቅ ባለይዞታ ስለሚከፈል ካሳ ማንኛውም ባለይዞታ የመሬት ይዞታ መብቱን በራሱ ፈቃድ መተውን በፈቃደኝነት የለቀቀው መሬት የሚገኘበትን ልዩ ሥፍራ መጠኑን ከነአዋሳኞቹ ለቀበሌው መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ ከ ወራት በፊት በማመልከትና ከመቼ ጀምሮ መራቱን እንደሟለቅ በጽሁፍ አስታውቆ መልቀቅ ይችላል ባለይዞታው የይዞታ መብቱን በራሱ ፈቃድ ስለመተው በጽሁፍ ካመለከተ በይዞታ መሬቱ ላይ ያለማውን ቋሚ ንብረት አንስቶ የመውሰድ እንዲሁም አንስቶ መውሰድ የማይችለውን ደግሞ በዚህ መመሪያ ስለቋሚ ንብረት ካሳ አከፋፈል በተደነገገው መሰረት በቅድሟያ ተመጣጣኝ ካሳ ሊከፈለው ይገባል ነገር ግን የካሳ ክፍያውን የሚፈጸመው መሬቱን የሚረከበው አካል ሲሆን ለመሬት ለቃቂቁው የመፈናቀያ ካሳ አይከፈለውም የመተላለፊያ መስመር በሚዘረጋበት ጊዜ ስለሚከፈል ካሳ በአንድ ባለይዞታ መሬት ውስጥ የመስኖ ቦይ ወይም መተላለፊያ መንገድ የሚያልፍ ሆኖ ከተገኘና ይኸው ቦይ ወይም መስመር ባለይዞታው በመሬቱ ላይ ሊያገኝ የሚችለውን ጥቅም የሚያሳጣው መሆኑ ከወዲሁ ከታወቀ ይህንኑ ለማካካስ የመተላለፊያ አገልግሎቱን የሚያገኘው በዚህ መመሪያ መሠረት ለባለይዞታው ያጣዋል ተብሎ ከሚገመተው አገልግሎት ወይም ጥቅም ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ካሣ ይከፍለዋል። ንብረት ማካካስ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከፍተኛውን የመሬት ይዞታ የሚረከበው ሰው በመሬቱ ላይ የለማ ንብረት ወይም ተጨማሪ ሙሬት ለነበረው ባለይዞታ በዚህ መመሪያ መሠረት ተመጣጣኝ ካሣ ይከፍለዋል ከመስኖ ልማት ጋር ተያይዞ የመሬት ሽግሽግ ሲደረግ ስለሚከፈል ካሳ በመስኖ መሬት ሽግሽግ ወቅት ከባለይዞታው በተቀነሰ መሬት ላይ ለለማ ማናቸውም ቋሚ ንብረት መሬቱ የደረሰው ማንኛውም አርሶ ደር በዚህ መመሪያ ስለ ንብረት ካሳ አከፋፈል በተደነገገው መሰረት የሚወሰነውን ካሣ በቅድሚያ ለቀድሞ ባለይዞታው በመክፈል መሬቱን ይረከባል በመሬት ሽግሽግ ወቅት ለሌላ ተጠቃሚ በደረሰ መሬት ላይ የለማው ቋሚ ንብረት የተፈጥሮ ዛፍ ካልሆነ በስተቀር የቀድሞው ባለይዞታ ይህንኑ ቆርጦ እንዲያነሳ ከተደረገ በኋላ ለባለድርሻው ይሰጠዋል ቋሚ ንብረት ያለበት መሬት የደረሰው አርሶ አደር በመሬቱ ላይ ለለማው ቋሚ ንብረት የሚከፍለውን ካሳ በአንድ ጊዜና በቅድሚያ ለመክፈል አቅም የሌለው ሆኖ የተገኘ እንደሆነ ይህንኑ ገልጾ ለወረዳዉ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽቤት በጽሑፍ ማመልከት አለበት በዚህም መሰረት ሀ የወረዳ ጽቤቱ በጽሑፍ የቀረበለትን ማመልከቻ ተቀብሎ ባለይዞታዉ በእርግጥም በአንድ ጊዜና በቅድሣያ ካሳዉን የመክፈል አቅም እንደሌለዉ ካረጋገጠ የካሳ ባለመበቱ ጋር በሚደረግ ጉይይትና ስምምነት መሰረት ካሳ መክፈል የሂገገባው የመስኖ መሬት ተጠቃሚ ከአንድ ዓመት ተኩል ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በሶስት ዙር ከፍሎ እንዲያጠናቅቅ ግዴታ እንዲገባ በወረዳው ጽቤት የማመቻቸት ስሰራ ይሰራል በዚህ መሰረት ችግሩን መፍታት ካልተቻለ የካሣ ክፍያውን መክፈል ለሚችል በመስኖ መሬት የመጠቀም መብት ላለው ለሌሳ ተጠቃሚ መራቱ ይሰጣል ለ ይህም ሆኖ ችግሩን መቅረፍ ካልተቻለ በወረዳው የመሬት አሰተዳደርና አጠቃቀም ጽቤት አማካይነት የካሳ ባለመብቱንና ካሳ መከፈል የሚገባውን አካል በማወያየት የክልሱን የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ህግ በማይጻረር መልኩ በሌላ አካባቢያዊ መፍትሄ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ይደረጋል በመስኖ ልማት ወቅት በተካሄደ የመሬት ሽግሽግ ምክንያት ቁርጥራጭና የተበጣጠሱ መሬቶች አንድ አነስተኛ የማሳ መጠን ሊኖረው ከሚገባው ስፋት በታች ሲሆኑ ወይም በቅርጽና በመጠን እራሳቸውን አስችሎ ለማልማት አመች ካለመሆኑ የተነሣ ወደ አጎራባች ማሳ እንዲካተት በተደረገ መሬት ላይ ለሠፈረ ንብረት በዚህ መመሪያ መሰረት መሬቱን የሚረከበው ባለይዞታ በቅድሚያ ካሳ እንዲከፍል ይደረጋል ይኸው መሬት የሌላ ባለይዞታ ድርሻ አለመሆኑ ከተረጋገጠና በትርፍነት የተያዘ ከሆነ ለመሬቱ የሚከፈለው ካሳ ለወረዳው ገንዘብና ኢኮኖሂ ትብብር ጽቤት ወይም ስልጣን ሳለው አካል ገቢ ተደርጎ ለልማት እንዲውል ይደረጋል በጊዚያዊነት የተለቀቁ መሬቶች አገግመው ለባለይዞታው ተመላሽ የሚደረግበት ሁኔታ በዚህ መመሪያ መሰረት ለተለዋጭ መንገድ ለድንጋይ ለግሪጋንቲ ማምረቻ ለአሽዋና አፈር ማውጫም ሆነ ማጓጓዣ ወይም ለሊላ አገልግሎት ለተወሰነ ወራት ወይም ዓመት በጊዜያዊነት የተለቀቀ መሬት ወደ ባለይዞታው በሚመለስበት ወቅት መሬቱ ከመለቀቁ በፊት ሲሰጥ የነበረውን ኣገልግሎት እንደቀድሞ መስጠትና የተፈጥሮ ሃብቱ እንዲያገግም በሚያስችለው ደረጃ ላይ መሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል በጊዚያዊነት የተለቀቀው መሬት በሚመለስበት ወቅት በደረሰበት ጉዳት ምክንያት ለባለይዞታው የሚሰጠው ምርት እንደሚቀንስ ወይም ለተወሰኑ አመታት ከነአካቴው ምርት እንደማይሰጥ አግባብ ባለው የመሬት አጠቃቀም ባለሙያዎች በኩል የተረጋገጠ እንደሆነ መሬቱን ወስዶ ለልማት ያዋለው አካል ለባለይዞታው የመፈናቀያ ካሣ ክፍያውን ይፈጽማል በጊዜዊነት የተጠየቀን መሬት አስመለክቶ መሬቱ ከመወሰዱ በፊት አመላለሱን አስመለክቶ መሬቱ ስለማገገሙ ወይም የማያገግም ከሆነም ስለ ካሳ ክፍያ መሬት ጠያቂውና መሬቱን የሚያሰለቅቀው አካል ቅድሚያ የጋራ ስምምነት ላይ መደረስ ይኖርባቸዋል ስለካሳ አተማመን በዚህ መመሪያ መሠረት ለህዝብ ጥቅም ወይም አገልግሉት ሲባል በሚለቀቅ የመሬት ይዞታ ላይ ለለማ ንብረትና ቋሚ ማሻሻያዎች የሚከፈለው የዛሳ መጠን አተማማን ወይም የሚሰላበት ቀመር በዚህ መመሪያ ተደንግጓል ስለካሳ ስሌት ቀመር በመሬት ላይ ለለማ ንብረት የግንባር ካሣ ግምት የሚሰላበት ዘዴ የቤት የመጋዘን የመጠለያና ሌሎች ግንባታዎች ካሳ ግመታ አሰራር ሀ የቤት የመጋዘን የመጠለያና ሌሎች ግንባታዎች ካሣ የሚሰላው የሚፈርሰውን ግንባታ መልሶ ለመግንባት የሚያስችል የወቅቱን የካሬ ሜትር ወይም የነጠላ ዋጋ በማውጣት ይሆናል ለ ከቤቱ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የግቢ ንጣፍ በረንዳ ሴፕቲክ ታንክና ሌሎች ስትራክቸሮችን ለመስራት የሚያስፈልገውን የወቅቱን የገበያ ዋጋ ሐ ቤቱ በመነሳቱ ምክንያት የተገነቡ የአገልገሎት መስመሮችን ለሣማፍረሰስ ለማንሳት መልሶ ለመገንባትና ለመትከል የሚያስፈልጉትን ወጪዎች ግምት ይሬኔምራል መ በዚህ አንቀጽ በፊደል ተራ ቁጥር ህ ላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ በመሬቱ ላይ ላደረገው የቋሟ ማሻሻያ ያወጣውን የገንዘብና የጉልበት ወጭ የሚተካ ካሳ ይከፈለዋል ሠ ቤቱ የሚፈርሰው በከፊል ከሆነና የቤቱ ባለቤት ቦታውን ለመልቀቅ ከመረጠ ለሙሉ ቤቱ ካሣ ይከፈለዋል ረ ቤቱ የሚፈርሰው በከፊል ከሆነና የቤቱ ባለቤት በቀሪው ቦታ ላይ ለመቆየት ከመረጠ ለፈረሰው የቤት አካል ብቻ ተሰልቶ ካሣ ይከፈለዋል ሆኖም የቤቱ ባለቤት በቀሪው የቤቱ አካል የመቆየት ምርጫ አግባብ ባለው የከተማም ሆነ የቀበሌ ማዕከል ኘላን መስረት ተቀባይነት ያለው መሆን አለበት ሰ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ከፊደል ተራ ቁጥር ህ እስከ ረ የተደነገገጡ እንደተጠበቀ ሆኖ የቤት የመጋዘን የመጠለያና ሌሎች ግንባታዎች ካሳ ግመታ አሰራር ቀመር የወቅቱ የግንባታ ወጩ የማቴርያል የጉልበት የገንዘብ ወጪ በመሬት ላይ የተደረገ ቋሚ ማሻሻያ ምንጣሮ መሬት ማስተካከል ድንጋይ ለቀማ ሌሎች የመሬት ልማት ሥራዎች ወጪ የቀሪ ዘመን የመሬት ሊዝ ተመላሽ ክፍያ ቢኖር የአጥር የእንሰሳት በረት ወይም ጉረኖ ስራዎች ካሣ አተማመን ሀ የግንብ አጥር ካሣ የሚሰላው የሚፈርሰውን አጥር መልሶ ለመስራት የሚያስፈልገው የወቅቱ የካሬ ሜትር ወይም የነጠላ ዋጋ በማውጣት ይሆናል ለ ከግንብ ውጪ ለሆነ የአጥር አይነት የወጣበትን ወጪ በወቅቱ ገበያ ዋጋ ተሰልቶ ካሳ ይከፈለዋል ሐ አጥሩ ተነስቱ መልሶ ለማጠር የሚቻል ከሆነ የሚከፈለው ክፍያ ተዛውሮ የሚተከል ንብረት እንደሚከፈለው ይሆናል ነገር ግን የአጥሩ ባለቤት ካሳ አንዲከፈለው ወይም መልሶ ለማጠር እንደሚፈልግ ምርጫ ይሰጠዋል መ የአጥር ካሣ ቀመር የአጥሩ አጠቃላይ ርዝመት በሜትር የአጥሩ ቁመት በሜትር የአጥሩ ወርድ በሜትር ሠ የእንሰሳት በረት ወይም ጉረኖ ስራዎች ካሣ የወቅቱ የግንባታ ወጪ የማቴርያል የጉልበት የገንዘብ ወጪ የሰብል ካሣ አተማመን ሀ የሰብል ካሣ የሚተመነው ሰብሉ ለመሰብሰብ ደርሶ ቢሆን ኖሮ ሊሰጥ የሚችለውን የምርት መጠንና ምርቱ ሊያስገኝ ይችል የነበረውን ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሠረት በማድረግ ይሆናል ለ በመሬቱ ላይ የተደረገ ቋሚ ማሻሻያ ካለ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፊደል ተራ ቁጥር ሀ ከሚከፈለው ካሳ በተጨማሪ ያሻሻለበት የገንዘብና የጉልበት ወጭ የሚተካ ካሳ ይከፈለዋል ሐ ሰብሉ ለመሰብሰብ የደረሰ ከሆነ ባለንብረቱ በካሣ ክፍያ ፋንታ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሰብሉን ሰብስቦ መውሰድ ይችሳላል ነገር ግን ሰብሌን ሰብስቦ ማንሳት የማይችል ከሆነም የሰብል ካሳ ተሰልቶ ይከፈለዋሪ መ የመኽር የሰብል አብቃይ ካሳ የመኸር መሬት ስፋት በሄር አእ በአንድ ሄር መሬት የሚገኝ ምርት በኩንታል አ የሰብለ የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር በኩንታል የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ ሠ የበልግ የሰብል አብቃይ ካሳ የበልግ መሬት ስፋት በሃር አ በአንድ ሃር መሬት የሚገኝ ምርት በኩንታል አ የሰብሉ የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር በኩንታል የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ ረ የቀሪ ዕርጥበት የሰብል አብቃይ ካሳ የቀሪ ዕርጥበት መሬት ስፋት በሄር ሄ« በአንድ ሄር መሬት የሟገኝ ምርት በኩንታል የቀሪ ዕርጥበት ለሚያለመ አካባቢዎች ብቻነ የሰብሉ የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር በኩንታል የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ ሰ የመስኖ የሰብል አብቃይ ካሳ በመስኖ የሚለማ መሬት ስፋት በሄር አ ከአንድ ሄር መሬት ላይ የሚገኝ ምርት በኩንታል የሰብሉ የወቀቱ የገቢያ ዋጋ በኩንታል ሄ ምርቱ በሚሰበሰብበት ጊዜ የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ በዓመት ከ አስከ ጊዜ ለያለሙ መሬቶች ብቻገ ሸ የሰብል ተረፈ ምርት ካሣ የቦታው ሰፋት በሄርነ። ተደርጎ ግለሰቦቹ በአካል ሲቀርቡ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውን ሲልኩ ክፍያውን እንዲወስዱ ይደረጋል ነግር ግን በግመታው ላይ ቅሬታ ከላቸው በህጉ በተቀመጠው ስርዓት መሰረት የሚፈጸም ይሆናል በሰፈራና በመሬት ድልድል አማካኝነት የተገኘ የመሬት ይዞታ ሲለቀቅ በሚከፈል ካሳ ላይ ስለሚሰጥ ውሳኔ የክልሉ መንግስት በሚያዘጋጀው የሰፈራ ፕሮግራም በፈቃደኝነት ተሳትፎ ምትክ መሬት ተሰጥቶት ማም ምርጫው በሰፈረበት አካባቢ ለመኖር መሆኑን በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከሰፈራ በፊት ይኖርበት ለነበረው ቀበሌ መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሜቴ እና ለቀበሌው አስተዳደር በፅሁፍ ያሳወቀ አርሶ አደር በመሬቱ ላይ ያለማውን ቋሚ ንብረት አንስቶ የመውሰድ እንዲሁም አንስቶ መውሰድ ለማይችለው ደግሞ በዚህ ሠመሪያ ስለ ቋሚ ንብረት ካሳ አከፋፈል በተደነገገው መሰረት በቅድሚያ ተመጣጣን ካሳ እና የመሬቱን ለምነት ጠብቆ ለማቆየት ያወጣውን ወጪ አግባብ ካለው የቀበሌ አስተዳደር ወይም ይዞታውን ከሚረከበው አዲስ ባለይዞታ እንዲያገኝ ይደረጋል የቀበሌው አስተዳደር በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የተወሰነውን ካሳ ለመክፈል አቅም የሌለው በሚሆንበት ጊዜ መሬቱን የተረከበው አካል ክፍያውን ይፈጽማል ማንኛውም ባለይዞታ በዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች መሰረት በሚሰጥ ውሳኔ ላይ ቅር የተሠኘ እንደሆነ በ ቀናት ውስጥ ቅሬታና አቤቱታውን ለካሳ አጣሪ ኮሚቴ ማቅረብ ይችላል የገጠር መሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ባልወሰዱ ባለይዞታዎች ላይ ስለሚሰጥ ውሳኔ በክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ስርዓት ማስፈፀፈያ ደንብ መሰረት ያለበቂና ሕጋዊ ምክንያት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ሳያወጣ የተገኘ ማንኛውም ባለይዞታ መሬቱን ለሕዝብ ጥቅም እንዲለቅ የተወሰነበት እንደሆነ ያለ ካሳ እንዲለቅ ይገደዳል በካሳ ግመታና አከፋፈል ወቅት በተሳሳተ ወይም በተጭበረበረ ማስረጃ ለሚጠየቅ የካሳ ክፍያ የሚሰጥ ውሳኔ በሃሰተኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ የተካሄደ መሬት የመለካትና የሃብት ቆጠራ ሥራ ህጋዊ ውጤት አይኖረውም መሬት የመለካትና የንብረት ሃብት ቆጠራ ሥራው በሚካሄድበት ወቅት ሆነ ብሎ መረጃዎችን ማዛባትና የካሳ ክፍያ እንዲፈጸም ማድረግ በህግ ተጠያቂ ያደርጋል ማንኛውም ባለይዞታ ነኝ ባይ በማናቸውም ሁኔታ የሰጠው መረጃ ትክክለኛ ሆኖ ካልተገኘና ይዞታውም የእርሱ አለመሆኑ ከተረጋገጠ የጠየቀውን የካሣ ክፍያ አያገኝም ክፍያውን ከወሰደ በኋላም ቢሆን በተሳሳተ ማስረጃ የተከፈለ መሆኑ ከተረጋገጠ በህግ ተገዶ እንዲመልስ ይደረጋል በፈጸመው የማጭበርበር ስራ በህግ ተጠያቂ ይሆናል በዚህ መመሪያ መሠረት ባለይዞታዎች ድንበር መግፋታቸው ከተረጋገጠና ችግሩ በአዋሳኝ ባለይዞታዎች ስምምነት ካልተፈታ ይኸው እስኪስተካከልና ስሌቱ በዚያው መሥረት እስኪታረም ድረስ በተጨማሪ ለተያዘው መሬት ወይም ለተገፋው ድንበር የተጠየቀው የካሳ ክፍያ ሊፈፀም አይችልም በዚህ መመሪያ መሠረት የንብረት ገማች ቡድን በፈፀመው የመሬት መለካትና የሃብት ቆጠራ ተግባር ስህተት ምክንያት በማንኛውም ሰው ላይ ጉዳት የደረሰ እንደሆነ የጉዳቱን ካሣ በመክፈል ረገድ ሀሳፊነት ያለበት አግባብ ያለው የወረዳ ወይም የከተማ አሰተዳደር ይሆናል ሆኖም የወረዳው ወይም የከተማ አስተዳደር ለተጐጅው የከፈለውን የጉዳት ካሣ እንዲተካለት ጥፋቱን የፈፀመውን ሰራተኛ ወይም የገማች ባለሙያዎች ቡድን እንደአግባብነቱ በተናጠል ወይም በቡድን በህሀግ ተጠያቂ ያደርጋል የከፈለውን ገንዘብ ያስመልሳል በክርክር ላይ ስላሉ የመሬት ይዞታዎች የካሳ አከፋፈል ሂደት ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የይዞታ መሬት እንዲለቀቅ በሟሜሚደረግበት ወቅት የሚነሳ ማናቸውም የይገባኛል ጥያቄ መጀመረየ በክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም የህግ ማዕቀፍ መሰረት በሽምግልና ታይቶ በዕርቅ እንዲፈታ ይደረጋል በዚህ አንቀጽ ንፁስ አንቀጽ ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በባለይዞታዎች መካከል በህግ ክርከር ላይ ያለ መሬት ወይንም የይገበኛል ጥያቄ የቀረበበት ይዞታ የካሳ ግምት ክርክሩ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ለጊዜው በወረዳው ወይም በከተማወይም በወረዳ አስተዳደር ስም በሚከፈት ዝግ የባንክ ሂሣብ ተቀመጦ ውሳኔ እንዳገኘም ካሣው ለባለመብቱ ይከፈሳል። በከተማ የአስተዳደርና የፕላን ወሰን ወይም በገጠር በልማት ምክንያት በቋሚነትም ይሁን በጊዚያዊነት ለሚነሱ የገጠር መሬት ባበይዞታዎች የማጨሻ ቤታቸው ለፈረሰባቸው ምትክ ቦታ አንዲያገኙ የሜደረግ ሆኖ ግንባታውን አጠናቀው እሰኪገቡ ድረስ ሀ በተሰጠው የግንባታ ፈቃድ መሰረት ቤቱን አጠናቀው እስኪገቡ ድረስ በወቅታዊ የኪራይ ግምት ተሰልቶ የአንድ ዓመት የቤት ኪራይ ክፍያ እንዲከፈላቸው ይደረጋል ለ በጊዜያዊነት ለሚነሱ ባለይዞታዎች ቤታቸውን ለቀው ወይም ከመኖሪያ ቦታቸው ተነስተው ለሚቆዩበት ጊዜ በወቅታዊ የኪራይ ግምት ተሰልቶ የቤት ኪራይ ክፍያ ይፈጸመላቸዋል ነገር ግን የቤት ኪራይ ክፍያው የሚከፈለው ወደ ቀድሞ የመኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው እስከሚገቡበት ጊዜ ድረስ ላለው ተሰልቶ ይከፈላቸዋል ክፍል ስድስት ስለቅሬታ አቀራረብና ውሳኔ አሰጣጥ መረጃ ስለመጠየቅን ስለመቀበል ስለገማች ቡድን ተግባርና ኃላፊነት ለሕዝብ ጥቅም መሬት የሚለቁ ባለይዞታዎች ቅሬታ አቀራረብና ውሳኔ አሰጣጥ በሚከተለው መልኩ ተደንግጓል ለሀዝብ ጥቅም ሲባል የሚለቀቅን የገጠር መሬት ይዞታ ወይም በመሬት ላይ የተደረገን ቋሚ ማሻሻያ አስመልክቶ የሚቀርብ ማናቸውም አቤቱታ መሬቱን ላስለቀቀው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ውሳኔው በተሰጠ በ ቀናት ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ጉዳዩን አግባብ ካላቸው የህግ ማዕተፎችና ሰነዶች ጋር በማገናዘብ በ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለቅሬታ አቅራቢ ወገኖች የጽሁፍ ውሳኔ እንዲደርሳቸው ያደርጋል በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ምላሽ ያላገኙና ለህዝብ ጥቅም ሲባል በሚሰጥ የመሬት ማስለቀቅ ውሳኔ በንብረት ግምታ የካሳ መጠንና አከፋፈል ውሳኔ ላይ ቅር የተሰኘ የመሬት ባለይዞታ ቅሬታአቤቱታ የሚቀርበው በከተማ ወይም በወረዳ አስተዳደሩ ተቋቋመው የካሣ ቅሬታ አጣሪ ኮሜቴ ይሆናል ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የይዞታ መሬቱን የለቀቀ ማናቸውም ባለይዞታ በመሬት ማስለቀቅ ሂደቱና አስተዳደራዊ ውሳኔው ቅር ከተሰኘ እንዲለቀቅ ትእዛዝ የተሰጠበትን መሬት ለወረዳው ወይም ከተማ አስተዳደር ማስረከቡን የሚያረጋግጥ ሰነድና ሌሎች ይግባኙ የቀረበበትን ምክኒያት የሚገልጹ መረጃዎች ኮፒ በማያያዝ በወረዳው ወይም በከተማ አስተዳዳሩ ለተቋቋመው የካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ መሬቱን እንዲለቅ ትዕዛዝ ከተላለፈበት ወይም ውሳኔ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ባሉ ቀናት ጊዜ ውስጥ በጽሁፍ ማቅረብ ይችላል ቅሬታ አቅራቢው ቅሬታ የቀረበበትን ማሳ የቅሬታው መነሻ ምንጭ ይዞታው የሚገነበት ቀበሌ ንቀበሌና ጎጥ የሚገልጹ መረጃዎኙ ከቅሬታ ማመልከቻው ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርበታል ባለይዞታው የካሣ ክፍያውን ከተቀበለ በኋላ በካሳው መጠንም ይሁን በንብረት አገማመቱ ላይ ቅሬታ ማቅረብ አይችልም በንብረት ገማች ቡድንባለሙያዎች በኩል በተወሰነው የካሳ መጠን ወይም በካሳው አከፋፋል ላይ ቅር በመሰኘቱ አቤቱታና ይግባኝ በማቅረቡ ለህዝብ አገልግሎት መለቀቅ የሚገባው መሬት ርክክብ እንዲታገድ ወይም እንዲዘገይ አያደርገውም በመሆኑም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠርት ይግባኝ የሚያቀርብ የመሬት ይዞታ ማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ባለይዞታ ይግባኙ ሊታይለት የሜችለው እንዲለቀቅ ትዕዛዝ የተሰጠበትን መሬት ለወረዳው ወይም ለከተማ መሬቱን ማስረከቡን የሚያረጋግጥ ሰነድ ከይግባኝ አቤቱታው ጋር አያይዞ ካቀረበ ብቻ ይሆናል የካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴው የቀረበውን የአቤቱታና ቅሬታ ማመልከቻ መሰረት በማድረግ አግባብ ያላቸውን ሰነዶች በመመርመር ጉዳዩ የሚለከታቸውን አካላት በማነጋገር እና ስራ ላይ ከዋሉ የህግ ማዕፎች ጋር በማገናዘብ አቤቱታው በደረሰው በ ቀናት ጊዜ ውስጥ ውሳኔውን ለአቤቱታ አቅራቢዎች ወይም ለተወካዮቻቸው ለወረዳው ወይም ለከተማ አስተዳደር የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም በጽሁዓ ውሳኔ መስጠት አለበት ቅሬታ ያቀረበው ባለይዞታ ወይም ተከራካሪ ወገን በካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ ቅር ከተሰኘ ይግባኙን ውሳኔው በተሰጠው በ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለዞን ከፍተኛ ፍቤት ማቅረብ ይችላል በከፍተኛ ፍቤት የተሰጠው ውዕ ያልረካ አስከ ሰበር ሰሟ ማቅረብ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ አመልካቹ ይግባኝ ሲጠይቅ የውሳኔውን ግልባጭ አዘጋጅቶ ለመስጠት የሚወስደውን ጊዜ አይሬጨምርም መረጃ ስለመጠየቅና ስለመቀበል በዚህ መመሪየ መሠረት የንብረት ገማች ወይም የካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴዎች ለሚያከናውኗቸው ተግባራት አስፈላጊ የሆኑትን መረጃዎች አግባብ ካላቸው የፌዴራል የክልል የወረዳ የከተማ የቀበሌ ወይም ሌሎች አካላት የመጠየቅና የማግኘት መብት አላቸው በዚህ አንቀጽ መሰረት ጥያቄ የቀረበለት ማንኛውም አካል የተጠየቁትን መረጃዎች የመስጠት ግዴታ አለበት ነ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ለካሳ ግመታ የሚጠይቃቸው የምርታማነትና የወቅቱ የገቢያ ዋጋ መረጃዎች አለመኖራቸው ሲረጋገጥ ቡድኑ የግል የአሰራር ስልትና ዕውቀት በመጠቀምና ቅኝታዊ ጥናት በማካሄድ መረጃዎችን ይሰበስባል ያደራጃል ጥቅም ላይ እንዲውል ያደርጋል ስለንብረት ገማች የባለሙያዎች ቡድን ተግባርና ኃላፊነት የንብረት ገማች ባለሙያዎች ቡድን በዚህ መመሪያ መሠረት ዮሚሜሚከተለት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል የካሳ ግመታ ዓላማውን ለባለይዞታዎቹ በግልጽ ያስረዳለሌ ያብራራሉሌ ለሀዝብ ጥቅም ሲባል የሚለቀቀው መሬት ተወስኖ በደረሰበት በ ቀናት ውስጥ የመሬቱ ባለይዞታ አጎራባች ባለይዞታዎች የቀበሌው መሬት አስተዳደር ተወካይ በተገኙበት ለልማት የተፈለገውን የይዞታ መሬት አጠቃቀምና ስፋት የምርታማነት ደረጃ የመሬት ባለይዞታዎችን ማንነትና በመሬቱና በቋሟ ንብረቱ ላያ ያላቸውን መብት የባለይዞታዎች መሰረታዊ መረጃ በመሬቱ ላይ ያፈሩትን ንብረት ማለትም ቤት አጥር እርከን የውሃ ጉድጓድ ዛፎችና ቋሟ ተክሎት ወዘተ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን በአዋጅ ደንቡና በዚህ መመሪያ ለማስፈፀም በሚዘጋጅ የቴክኒክ ማስተገበሪያ ሰነድ መሰረት መረጃዎችን ትመና በሚያመች መልኩ ይሰበሰባል ያጣራል ይመረምራል ሀብረተሰቡ ያስገመግማል ያደራጃል የመሬት ምዝገባና የመለካት ስራ እንዲሁም የንብረት ቆጠራ በሚካሄድበት ጊዜ የመሬት ባለይዞታዎች አጎራባች ባለይዞታዎች የቀበሌ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ ተወካዮች እንዲገኙ ጥሪ መደረጉን ወይም አስፈላጊው ጥሪ ደርሷቸው አለመገኘታቸውን በማረጋገጥ የመሬት መለካት መመዝገብና የንብረትና በመሬቱ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎችን የቆጠራ ተግባር ያከናውናል የመሬት ልኬታና በመሬት ላይ ያፈሩት ንብረት ቀጠራ ባለይዞታዎችን ያሳተፈ መሆኑን ለማረጋገጥ በመሬት ምዝገባውና በንብረት ቆጠራው ላይ ባለይዞታዎቹና የንብረት ገማች ቡድን አባላት በመተማማኛ ቅጹ ላይ እንዲፈርሙበት ያደርጋል በመሬት ልኬታና በንብረት ቆጠራ የተሰባሰቡ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በማቅረብ የማስተቸትና ባለቤትነታቸውን የማረጋገጥ ስራ ያከናውናል ለንብረት ግመታ ስራ አስፈላጊ የሆኑ የቅርብ አምስት ዓመታት የምርታማነት መረጃና ወቅታዊ የገቢያ ዋጋ እና ሌሎች ለትመና ሰራው አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ከሚመለከታቸው የወረዳው ወይም የከተማ መስሪያ ቤቶች ህጋዊ ጥያቄ በማቅረብ ተረጋግጠው ለገጠር መሬት አስተዳርና አጠቃቀም ተቋም መሰጠት አለበት እንዳስፈላጊነቱም ተጨማሪ መረጃ ሲያሰፈለግ የገማች ባለሙያዎች ቡድን ጥናት እያካሄደ ያልተሟሉ መረጃዎችን ይሰበሰባል ያደራጃል ይተነትናል በመሬት ልኬታ በንብረት ሃብት ቆጠራና ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ከሚመለከታቸው አካላት የተሰባሰቡ መረጃዎችን ጥቅም ላይ በማዋል የካሳ ትመና ያካሄዳል ካሳ ገማች ቡድኑ የሚያከናውናቸውን ማናቸውም ተግባራት በሚመለከት የተሟላ ቃለጉባኤ ይይዛል ቃለጉባኤዎችና ሌሎች መረጃዎች ከካሳ ሰነዱ ጋር አብረው ተሰነደው ወይም ተደራጅተው እንዲያዙ የደርጋል በካሳ ግመታ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች አስተያየቶችና አቤቱታዎችን ተቀብሎ እንደተገቢነቱ ወቅታዊ ምላሾችንና ማብራሪያዎችን ይሠጣል አግባብነት በሌላቸው የይዞታ ማረጋገጫ ሰነዶችና ሆነ ተብሎ በተጭበረበረ ማስረጃ ባለይዞታዎችን ለመጥቀምም ሆነ ለመጉዳት በሚካሄድ አሰራርና ትክክለኛ ባለይዞታውን በአግባቡ ባለመለየት ምክንያት ካሳ እንዲከፈል አድርገው የተገኙ እንደሆነ ለተጎጅው የሚገባውን ካሳ ከመሸፈን በተጨማሪ በተናጠልም ይሁን በቡድን በህግ ተጠያቂ ይሆናሉ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በግለሰቦች መካከል በሚደረግ ክርክርም ይሁን በግለሰብ ደረጃ የሚቀርብ የካሳ ይገመትልኝ ጥያቄ በተዋረድ በሚገሄው የገጠር መሬት አስተዳዳርና አጠቃቀም ተቋም ተፈጻሚ አይሆንም የወረዳ ወይም የከተማ አስተዳደር ተግባርና ኃላፊነት ለሀዝብ ጥቅም በሚለቀቀው መሬት ላይ በሚካሄደው የንብረት ግምት መሠረት ተገቢው የካሣ መጠን እንዲከፈል ወይም ትክ መሬጐ እንዲሰጥ የመወሰን ስልጣን የወረዳው ወይም የከተማ አስተዳደር ይሆናል የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ አጠቃላይ ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ የወረዳው ወይም የከተማው አስተዳደር የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ኃላፊነቶችን ይወጣል ለህዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቀው መሬት የሚነሳውና የሚገመተው ንብረት ከገማች ባለሙያዎች አቅም በላይ የተለዬ እውቀትና ልምድ የሚጠይቅ ሆኖ የተገኘ እንደሆነ በተዋረድ ባለው የገር መሬት ፎረ ወንያኑ አስተዳዳርና አጠቃቀም ተቋም በኩል ጥያቄው ሲቀረብ ንብረቱን ለመገመት የሚችሉ ልዩ ሙያና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች እንዲካተቱ ያደርጋል የመሬት ማስለቀቅ እና ግመታ ስራው የሚካሄድበትን ጊዜና ሁኔታ ይወስናል የመሬት ምዝገባና የመለካት ስራ እንዲሁም የንብሪት ቆጠራ በሚካሄድበት ወቅት የመሬት ባለይዞታዎች አጎራባች ባለይዞታዎች የቀበሌ አስተዳደርና የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተወካዮች እንዲገኙ ትዕዛዝ ይሰጣል ተግባራዊነቱን ይከታተላል ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የይዞታ መሬታቸውን ለለቀቁ ባለይዞታዎች ፀድቆ የተላከው የካሳ ክፍያ ለትክክለኛ ባለይዞታዎች ወይም የመሬቱ ተጠቃሚዎች መድረሱን ይከታተላል ያረጋግጣል ካሳ የተከፈለበትን መሬት ለልማት መለቀቁንና መተሳለፉን ያረጋግጣል መሬቱ ለመሬት ጠያቂው ካልተላለፈ የማስተካከያ ዕርምጃ ይወስዳል የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች መሬት የሚለቁ ባለይዞታዎቹን ለዘለቄታው ማቋቋም የሚያስችሉ አማራጮች እንዲያቀርቡ ያደርጋል መፈጸማቸውንም ይከታታላል ይቆጣጠራል አስፈላጊውን ምክርና ድጋፍ መሰጠቱን ያረጋግጣል በልማት ምክንያት ከመሬታቸው የተነሱ ባለይዞታዎችን በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም ኃላፊነታቸውን የማይወጡትን የመንግሰት የስራ ኃላፊዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ያደርጋል ከመሬት ማስለቀቅ ካሳ ግመታና ክፍያ ጋር በተያያዘ ለሚቀረቡ ትሬታዎችና አቤቱታዎች በወረዳው ወይም በከተማ አስተዳደሩ አባላት ያሉት የካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ ይቋቋማል የካሳ አጣሪ ኮሚቴው በመሬት ማስለቀቅና ካሳ ክፍያ የሚቀረቡ ቅሬታዎችን በህጉ መሰረት በማጣራት የውሳኔ አስተያየት ሲያቀርብ መርምሮ ይወሰናል ለቅሬታ አቅራቢው በፁሁፍ ምላሽ ይሰጣል ስለ መሬት አቅርቦት ጠያቂ አካላት ማንኛውም የልማት አስፈፃሚ መስሪያ ቤት ባቀረበው የመሬት ይለቀቅልኝ ጥያቄ መሰረት በሚለቀቁ የይዞታ መሬቶች ላይ ለሜከናወኑና ከንብረት ግመታም ሆነ ከካሣ አከፋፈል ጋር የተያያዙ ተግባራት እውን የሆኑ ዘንድ አስፈላጊው ሎጅስቲክስ እንዲሟላ ያደርጋል እንደ ልማቱ ዓይነት መሬት ጠያቂው አካል የካሣ ክፍያና የዘላቂ መልሶ ማቋቋም የድርጊት መረሃ ግብር እንዲቀረፅና በዚሁ መሰረት ተግባራዊ እንዲደረግ ሰነድ አዘጋጅቶ ያቀርባል በተዘጋጀው የድረጊት መርሃ ግብር መሰረት የልማት ተነሽዎችን የዘላቂ መልሶ ማቋቋም ድጋፍ ኋንዲያገኙ የማድረግ ግዴታ ይኖርበታል የሚፈለገውን የይዞታ መሬት በትክክል የሚያመላክት የፕሮጀክት ዲዛይን በማዘጋጀት ለገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም በወቅቱ መድረሱን የማረጋገጥ ማናቸውም የፕሮጀክት ዲዛይን ለውጥ በሚደረግበት ወቅት በተቻለ ፍጥነት ለውጡን የማሳወቅ ከለውጡ ጋር በተያያዘ አስቀድሞ የተከፈለ የካሳ ክፍያ ስለመኖሩ የማጣራት የቅርብ ክትትል እንዲካሄድ ያደርጋል የካሣ ክፍያውን ያካሂድለት ዘንድ ለየትኛውም አካል ህጋዊ ውክልና ሊሰጥ ይችላል ስለአከፋፈሉም የራሱን ውስጣዊ የአሰራር መመሪያ ያዘጋጃል የዘፍያ ትዕዛዝ የተሰጠባቸውን የካሳ ሰነዶች በግልዕ ማስታወቂያ ለባለይዞታዎቹ ያሳውቃል እንደ መሬቱ አስፈላጊነትና እንደ ውሳኔዎቹ አመጣጥ ቅደም ተከተል ለባለይዞታዎቹ አግባብ ባለው የአከፋፈል ስልት ክፍያው እንዲፈፀም ያደርጋል በባለይዞታዎች ስም የባንክ ሂሣብ እንዲከፈትና ክፍያው በቀጥታ ወደ ሂሣባቸው እንዲተላለፍላቸው አበክሮ ይሰራ ፈል ኃ የክፍያ አፈፃፀሙን በተመለከተ ለወረዳው ወይም ለከተማ አስተዳደርና ለሚመለከተው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ወቅታዊ መረጃዎችን ይሰጣል ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ ከባለይዞታዎች ለሚቀርቡ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ተገቢ ምላሾችንና ማብራሪያዎችን ይሰጣል ግልጽነት የተላበሰ አሰራር እንዲሰፍን ያደርጋል ለልማት ተነሽዎች የዘላቂ መልሶ ማቋቋሚያ ድጋፍ በገንዘብ በቦታ አቅርቦት በመሰረተ ልማት ዝርጋታና ሌሎች መሰል ድጋፎች የማከናወን ኃለፊነትና ግዴታ ይኖርበታል የግምት ስራ ወጪዎችን በተመለክተ ለሀዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሰፈረ ንብረት ስለዛክከፈል ካሳ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በወጣው ደንብ ደንብ ቁጥር መሰረት ለሚሠየመው የንብረት ገማች ባለሙያ ቡድንና እንዳሰፈላጊነቱም ለካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ የሚከፈለውን አበል ጨምሮ በዚህ መመሪያ መሠረት ንብረት ለመገመት አስፈላጊ የሆኑ ወጪዎች እንደ አግባብነቱ በወረዳው አማካኝነት የሚሸፈን ይሆናል ።