Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ይኸውም የቀድሞውንና የዛሬውን ታሪክ ካለማንበባቸውና ካለመረዳታቸው የተነሣ ነውና ውሻው ጌታውን በጣም ይወደው ነበረ። ወዳጃሻችሁንም በፍጹም ልባችሁ ከወደዳችሁት በመከራችሁ ቀን አይለያችሁም ዘጠነኛ ስለ አንበሳና ስለ አይጥ አንበሳ በዱር ውስጥ የሚኖሩ ከብቶች አግኝተህ እንኳን አንዲት ፍየል ብዙስ ብትበላ ምን ኃጢአት አለ ጌታሽ ከሰው ጋር እስቲነጋገር ከመንገድ ወጥተሽ ሠርዶ እየነጨሽ የቆየሺው ትልቅ ኃጢአት አይደለምን አግዚአብሔር ምግባችንን የነሣን ለካ ባንች ኃጢአት ኑርዋል አንችን ከመካከላችን ካላጠፋን አግዚአብሔር አይታረቀንም ብለው ወዲያው ጽፈው ባንገቴ ላይ አሰሩልኝ ደብተራ አሻግሬም ይህን ሁሉ የልጁን ጉድ ሳያይ እንኳን ሞተ አላት ወዳጄ ልቤና ሴሎችም አይበቃህምን ደግሞ እነዚህን ሊቃውንቱን ምን አደረጉ ልትላቸው ይሆን አሏቸው መምሬ ሰባጋዲስም ስለ ተፈቀደላቸው እያመሰገኑ እጅ ከነ በኋላ ተናገርማ ካላችሁኝ መልአከ ኃይል ተስፋዬና ዓቃቤ ሰዓት ዘወልደ ማርያም በገባዔው ፊት ቆመው ጥፋቱን ሁሉ በእኛ በቀሳውስቱ ላይ አያስመሰሉ ለተናገሩት ሁሉ ምላሹን እንዳልሰጥ ያለቀውን ነገር እንደ ገና መጀመር ይሆንብኛልና ሳያውቁብን ቀሩ እንዳትሉ ብቻ ባጭሩ አድርጌ እናገራለሁ ባለፈው ዘመን ስንሠራቸው ከነበረው ሥራዎች ሁሉ እንደ ነውር ሆነው የተቆጠሩብን አሥር ነገሮች ናቸው ኛ በየድግሱና በየተዝካሩ ቤት ስለ መስክር ኛ ቀሳውስት ብር እየሰጡ ቅስና ስለ መሾማቸው ለድኃ ትንሽ ፍታት ለባለጠጋ ትልቅ ፍታት ስለ መደረጉ።
ስለ የሌት ወፍ ጳ ብ ስለ የጦጣ ፍርድ ስለ አንበሳና ስለ ነብር ስለ ጅብና ስለ አህያ ባል ንጀርነት ማውጫ ስስ አንድ ቅምጥል የበግ ግልገል ህ« አንድ ዳውላ አህል ስስ ተስረቀበት ሰው ስለ የእንግሊዝ ንጉሥ ጆርጅ ኛ ስለ የጀርመን ንጉሥ ስለ አንድ ሽማግሌ ሰውና ስለ አንዲት ሴት ልጅ ክፍል የልብ አሳብ የብርሃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ አቶ ክብረትና ገነሆይ ንጋቷ ጽዮን ሞገሳን ስለ መውለዳቸው ስለ ጽዮን ሞገሳ እጮኛስለ ብርሃኔ ብርሃኔ ጽዮን ሞገሳን ለማግባት ቁርጥ አሳብ ስለ ማድረጉ ጽዮን ሞገሳ ስትምሕርት ወደ ደብረ ሊባኖስ ስለ መውረድዋ ጽዮን ሞገሳ ትምሕርቷን ጨርሳ ወደ ሀገርዋ ስለ መመለስዋ ስለ ብርሃኔና ጽዮን ሞገሳ የቃል ኪዳን ጋብቻ ስለ ጽዮን ሞገሳ ልጅ መውለድ ንንን ን ቸቸ ስለ ሥላሴ በዓል ዝክርና ስለ ብርፃኔ ሞት ክፍል አዲስ ዓለም የቅኖችና የደግ አድራጊዎች መኖሪያ ስለ ዓወቀ ትውልድና ወደ ፓሪስ ስለ መሔዱ ስለ አቶ አንደ ልቡ መታመምና መሞት ስለ አቶ እንደ ልቡ ተዝካር ስለ ተዝካር የተደረገ ጉባዔ ዜዜ። እኔም እጅግ አደነቅሁ ማድነቄም ምግብነቱ ከሀገሬ ምሣብ ልዩ ስለሆነ ነው ዮሐ ፃ የሀገሬ ምግብ እንጀራና የከብት ሥጋ ነው ያውም ማታ በልተውለት ለጧት ኣይገኝም እንዲህም እየተደነቅሁ ስሔድ ሐራ ጥቃ የሚባሉ ሰዎች አገኘሁ ስሰ ዛፉም ጠየቅኋቸው እነሰም ጥንኑ ወዳጄ ልቤና ሴሎችም በውነቶ ዛፍ ነበረ አሁን ግን ዛፍነቱ ቀርቶ ሰው ሆነዋል አሉኝ አኔ ግን ስቄባቸው ሔድሁ ጥቂትም ከሔድሁ በኋላ አወጣኪን አገኘሁት ስሰ ዛፉም ጠየቅሁት እርሱ ግን ወደኔ ዘወር በሎ ጤና የለህምን ሰው መምሰሉ በቀረ በስንት ዓመቱ ዛሬማ ፍጹም ዛፍ ሆኖ የለምን አለኝ እፄም ስቄበት መንገዴን ሔድሁ ከዚህ በኋላ ሳላስበው በድንገች ወደ ሰሜን ዞርሁ በሰሜን ያሱ ለዎች የዛፉን ነገር ጠንቅቀን እናው ቃለን ይላሉ እኔም ወደ እነርሱ ሔጄ ጠየቅኋቸው ነገር ግን አንድ ነው ሁለት ነው በማሰት ክርክር ይዘው ነበሩና እኔን ከቁም ነገር ስላሳልቆጠሩኝ የእነርሱ ክርክር መጨረሻ ሳይኖረው ጊዜ በዚህ ቆሜ ልቀር ነውን ብዬ ወደ ምሥራቅ ዞርሁ በምሥራቅም ያሉ ሰዎች አንድ መሆኑን ዘወትርም ዛፍና ሰው መስሎ መታየቱን አስረዱኝና አጅግ ደስ አለኝ ማቴ ፅ ቆሮ ቿ ዮሒ ወ ወኋ ምዕራፍ የ ስለ ሦስተኛው ዛፍ በዚሁ በምሥራቅ ሀገር ከወዲያ ወዲህ ስመላለስ በነፋሻ ስፍራ የበቀለ አንድ ዛፍ አገኘሁ ይህም ዛፍ በልምላሜም በቅጠልም በርዝመትም አስቀድሞ ያየኋቸውን ሁለቱን ዛፎች ይመስላል የበቀለበት ስፍራ ተራራማ ስለ ሆነ ነፋስ ይወዘውዘው ነበረ የዚህንም ነገር እየመረመርሁ ስሔድ መቅዶንዮስን አገኘሁት የዛፉንም ነገር ያውቀው እንደ ሆነ ብዬ ጠየቅሁት እርሱም እንዲህ የሚያስደንቅህ የዚህ የዛፍ ነገር ነውን ከዚህ የሚበልጡትን ሁሰቱን ዛፎች አይተህ በሆነ ምንኛ ባደዴነቅህ ኖሯል ይህ ዛፍ በሁስቱ ዛፎች ዘንድ የቁጥቋጦ ያህል ነው አለኝ እኔ ግን ስቄበት ሔድሁ ጥቂትም እንዳለፍሁ ዘወር ብዬ ብመሰከት ያ ያየሁት ዛፍ እንደ ርግብ ክንፍ አውጥቶ ሲበር አየሁት ከዚህም በኋላ እያደነቅሁ መንገዴን ሔድሁ ያ ወዳጄ ልቤም ካማርኛ ይልቅ የግፅዝ ቋንቋ ያውቅ ነበርና ወመጋቋፅሰዕያ ቀዱዶዕ ጴታውሪጓ ፖጎሪልዶ ወፀዐመጋፈረዕ ፅዚ ለጽ ዲሪ ዳለመጩጠውረሮ ዳመፊዕ ጴዳጎያ የዳዊት መዝሙር ይዘምር ጀመረ መዝ ዛል ወሀ ዳጄ ልቤ ምዕራፍ ፀ ስለ ትዕቢትና ስለ ትሕትና መጣላት ከዚህ በኋላ ድንቁርና ወደ ምትባል ሀገር ደረስሁ በቢያችም ሀገር ትዕቢት የሚባል ሌባ ጌታ ሆኖ ይኖር ነበር ሌብነቱን ግን የሚያውቅበት አልነበረም ደግሞ ትሕትና የሚባል ሰው የጨዋ ልጅ ጊዜ ያዋረደው በዚያችው ሀገር ራሱን ቀብሮ ይኖር ነበር እኔም ለሁለቱም ወዳጅ ሆጌፄጌ በሁለቱም ቤት ስበላ ስጠጣ ብዙ ቀን ተቀመጥሁ ዳሩ ግን ትዕቢት ሌባ መሆኑን አላወቅሁም ነበር ትዕቢትም በትሕትና ላይ ክፉ ክፉ ወሬ እያወራ ይነግረኝ ነበረ ትሕትናም በሰማ ጊዜ ነገሩን አንዳልሰማ እየሆነ ዝም ይል ነበረ አንድ ቀን ትሕትና ወደ ቤቱ ጠርቶኝ ትንሸ ጨዋታ ስንጫወት ትዕቢት አግረ መንገዱን ሲያልፍ አየኝና ተቆጥቶ ጨርቁን ባፍንጫው ላይ አድርጐ አለፈ ጥቁትም አንደ ሔደ ከሐሜት ጋራ በመንገድ ተገሩች ሐሜት ቶሎ ብሎ ጌታው አቶ ትዕቢት ከወዴት ይመጣሉ ው ከወደ ሰይጣን ልብ አለው ምነው አዝነዋል አለው ኃዘን ይብዛብኝንን ሰው ሁሉ ወረተኛ ነው ይህን ባጠገባችን የቆመውን ሰው ይህን ዓለም መጻሕፍትን ሲዞር አግኝቼው ወደ ቤቴ ወሰድሁት ደግሞ ሱሪህን እስከ ተረከዝህ አድርግ ዓይንህን ተኳል ጨርቅህን አፍንጫህ ላይ አድርግ ሰላምታ ሲሰጡህ ዝም በላቸው ብዬ የሀገሩን ሥርዓት አስተማርሁት አሁን ግን ሁሉንም ትቶት ከትሕቶና ጋራ ሲጫወት አየሁት ትሕትና ስንኳን አንግዳ የሚቀበልበት ራሱን የሜረዳበት ገንዘብ አያገኝም አሰ ትዕቢትም ከሐሜት አፍ ይህን በሰማ ጊዜ ደስ አለውና ትሕትና የሚያውቀው እንግዳ መጥቶብኛልና እንጀራ አበድሩኝ ማለት ነው አንጂ ባለ ገንዘብማ ከሆነ ልጆቹ ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃንና ሰማዕታት የሚበሉትና የሚጠጡት አጥተው በረኃብ ለምን ይተላለቁ ነበር አለ ማቴ ጵ ጩ ና ችም ትፅቢት ይህን ሁሉ ነገር ሲናገር ትሕትና ጆሮውን ጣል አድርጐ ይለማ ነበርና በነገሩ ስለ ተናደደ በትሩን ይዞ ወደ ትዕቢት ቀርቦ አንተ ሌባ ምነው ብችልህ ብችልህ አምቢ አልህ የዚያ የሐስተኛ የዲያብሎስ ልጅ መሆንህን ረሳኸውን። ነፍሴን አየወጋኝ ከማኽል ራሴ ከክርስቶስ የሚሰየኝ ነበር ጥቂትም በጎነት ባገኘሁ ጊዜ እያዘገምሁ መንገዴን ጀመርሁ በመንገዴም በስተ ግራ ረጅም ተራራ ነበረ ስሙም ንፍገት ይባላል አንዳንድ ለዎችም ፍቅረ ንዋይ ይሉሱታል እኔም በዚያ ላይ ወጥቼ ይህን ዓለም ለማየት አሰብሁ ያ ወዳጄ ልቤ ግን ገመምተኛ ነህና አትችልም ብሎ ክከለከለኝ ይሀንንም ስንነጋገር ግያዝ ከወደ ተራራው መጣ ስለ ተራራውም ጠየቅሁት ግያዝ መለሰ ለኔ መልካም ቤት በተራራው ጫፍ ተሠርቆቶልኛል አንተም ትንሽ ዛኒጋባ መሳይ አሠርተህ ኖ ህ ነበረ አለኝ ነገ ይ የን አኬ ይሀን ዓሰም መጻሕፍትን ለመዞርና ለማየት ነውና ሁሉንም ነገር ከወዳጄ ልቤ ጋራ ተማክሬ እነግርዛለሁ አልሁት ከግያዝም ከተሰያየን በኋላ ወደ ወዳጄ ልቤ ቀርቤ በንፍገት ተራራ መኖር ሰኔ ይመቸኝ ይሆንን ብዬ ጠየቅሁት ወዳጄ ልቤም ጸረ ወዲያ ምን ያደርግልኝ ብለህ ነው እኔ አውቀው የለምን አለኝ እኽ እንደ ምን ነው አልሁት ወጂሟ ልቤ ሀ የንፍገት ተራራ አሁን አንተ እንደምታየው እጅግ ረጅም ነው ወጥቶ በጫፉ ላይ የቆሙ እንደ ሆነ በምድር ያለው ሁሉ ሰውም ከብቱም ወርቁም ብሩም እህሉም ጥቂት መስሎ ይታያል ዳግመኛ በዚሀ ምድር ያለው ገንዘብ ሁሉ ያንድ ሰው ቢሆን ላንድ ቀን አራት የሚበቃ አይመስልም ይልቁንም በንፍገት ተራራ የቆመ ሰው አባቱንና እናቱን ወንድሙንና አኅቱን ዘመዱንና ወዳጁንም ለይቶ ማወቅ አይችልም አለኝ ይሀን ሁሉ ሲነግረኝ ወጥቼ አያሰሁ በማለት ልቡናዬ ተስፋ አልቆረጠም ነበር ነገር ግን ባንድ ስፍራ ቆሜ ሳመነታ ጊዜው መሸ ከኔም ጋራ ሰይፍም ጋሻም ጦርም አልነበረም ያ የሚሰብረውን አሸቶ የሚዞረው አውሬ ቢመጣ ያፉ ጉርሻ ነኝ እንጂ የማመልጥበት ስፍራ አልነበረኝም ፅ ጴጥ ቿ እንዲሁም ስጨነቅ ከንፍገት ተራራ በስተቀኝ አንድ ቤት አየሁና ቶሎ ብዬ ወደዚያ ሔድሁ አንድ ብላቴናም በደጅ ቆሞ አገኘሁ ወዳጄ ሆይ ስምህ ማነው አልሁት አብሮ መብሳት አባላለሁ አሰኝ ይህ ቤት የማነው አልሁት የብላታ ቸርነት ነው አለኝ አባከህ ንገርልኝ አልሁት አርሱም ቅን ብላቴና ኑሮ ቶሎ ገብቶ ነገረልኝ ብላታ ቸርነትም በሰሙ ጊዜ እጃቸውን ዘርግተው ሲበሩ መጡና ይዘውኝ ገቡ ከገባንም በኋላ የሚያስፈልገኝን ነገር ሁሉ አቀረቡልኝ የመኝታም ጊዜ ሲደርስ ወደ መኝታ ቤት ይዘውኝ ሔዱ በቪያም መልካም ምቹ አልጋ አሳዩኝ እኔም እጅግ ደክሞኝ ነበርና ቶሎ ተኛሁፎ ወዳጄ ልቤ ግን እጅግም እንቅልፍ አልነበረበትምና ባጠገቤ ተኝቶ ያጫውተኝ ነበረ በነጋም ጊዜ ሰመንገዴ ስለ ቸኩልሁ ቶሎ ታጠቅሁ ብላታ ቸርነትም ለመንገዴ የሚበቃ ስንቅ ሰጡኝ ዳግመኛም ወደ ንፍገት ተራራ መውጣት እንዳላስብ መክከሩኝ ምክንያቱንም ብጠይቃቸው ከተራራው መርዘም የተነሣ ራስ እያዞረ ይጥላል አሉኝ እኔም ብላታ ቸርነት በሠሩልኝ ሥራ ሁሉ እጅግ ደስ ስላለኝ ወደ ሀገሬ ስመለስ መጥቼ አሰናበትዎታሰሁ ብያቸው መንገዴን ሔድሁ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ምዕራፍ ስለ ምእመን ሠርግ ተነሣሁ ከዚህም በኋላ ምሥራቅ ምሥራቁን ስመዞር በምሥራቅም ያላየሁት ሀገር አልነበረም መንገዱ ግን አጅግ አስቸጋሪ ነበረ ማቴ ከ መሪ ባልነበረኝ ባንዱ ፈርፈር ውስጥ ወድቄ እቀር ህሎ ቤቴ ከወጣሁ ቀኑ ወደ አሰብሁበት ስፍራ ባልደረስሁም ነበረ ነገር ግን ከ ብዙ ነበረና ስንቅ አለቀብኝ ወዳጁ ልቤም ችግሬን አይቶ የሕይወት እንጀራ የሚሸጥበት ገበያ ሞልቶ የሰምን ሔደን እንግዛ አለኝ ዮሐ ነገሩስ መልካም ነበረ ነገር ግን የያዝነው ገንዘብ ጥቂት ነውና በዚህ ያህል ዋጋ የሕይወት እንጀራ አንሸጥም ብለው ቢመልሱን እንዴት እንሆናሰን እንዲህ በረኃብ ተጨንቀን ሳለን የመንገዱን ድካም አስኪ ተመልከተው አልሁት እንዲሁ ባንድ ሥፍራ ቆመን ይህን ስንነጋገር ወደ ሰሜን ብመለከት በምሥራቅና በሰሜን አዋሳኝ ብዙ ሰዎች ነጫጭ ልብስ ሰብሰው በትልቁ አዳራሽ ደጅ ከወዲያ ወዲህ ሲመሳለሱ አየሁ ፈጥ ወደ እርሳቸው ሔሒድሁ በደረስሁም ጊዜ ይህ አዳራሽ የማነወ ብዬ ጠየቅኋቸውፅ የታላቁ ንጉሥ ቤት ነው ነገር ግን አሁን በውስጡ ያለው ሰው ባለኪራይ ነው አሉኝ ሁላችሁ ነጫጭ ልብስ ለብሳችሁ ከወዲያ ከወዲህ የምትመላስሱሉት ስለ ምን ነው ዛሬ ያመት በዓል ነውን አልኋቸው አንኳን አንኳን ይህን ቤት የተከራየው ሰው ልጁን ምአመንን ከወንጌል ጋራ ሲያጋባው ነው ስለዚህ አሁን ወደ ሠርጉ ለመሔድ ቸኩስናል ነገር ሠርገኞች እጅግ ጥቂቶች ሆነን ተቸግረናልና የሠርግ ልብስ እንዳለህ ከ ጋራ እንሒድ አሉኝ አባካችሁ ጥቂት ቆዩኝና በከረጢቴ ጥቂት ገንዘብ ባገኝ ወደ ገበያ ሔጄ የሠርግ ልብስ ልግዛ አልኋቸው ወዳጄ ልቤ አይሆንም በጊዜ ግቡ ተብለናል ጊዜው የመሸ እንደሆነ በሩ ይዘጋብናል በሩም ከተዘጋ በኋላ ክፈቱልን ብንል የሚከፍትልን አናገኝም አሉኝ ማቴ ድ እኔም ጥንቱን ባልነገራችሁኝ እንኳ መልካም ነበረ አሁን እንደምን ልሁን እያልሁ እለቅስባቸው ጀመርሁ እነርሱም አይዞህ አታልቅስ ንስሐ የሚባለውን ወንዝ ተሻግረነው እንሔዳለንና ልብስህን በዚያ ታጥባለህ እኛም አንድ ለዓት ያህል አንቆይፃሰን አሉኝ እኔም እጅግ ደስ አስሰኝ የደስታዬም ምክንያት ተርቤ ነበርና ከዚያ ከሠርጉ አንጀራ ለመብላት አስቤ ነው ማቲ ከዚህም በኋላ ንስሐ ወደሚባለው ወንዝ ደረስን። ያሟሟቱም ነገር እንዲህ ነው ከሀገራችን በወጣንበት ዕለት ጊዜ መሸብንና በዱር ውስጥ አደርነ በዚያም ወምበዶች መጥተው ቀሚሳችንን ከነመደርቢያችን ወሰዱብን በነጋም ጊዜ መንገድ አላፎች አገኙን አነርሱም ትብትባቸውን ሁሉ አሸክመው ሁለት ምፅራፍ መንገድ ወሰዱን ከዚያም በኋላ በጥፊ እየመቱ ወደ አደባባይ አቀረቡን ማቴ ወ ጣ በዚያም ሌቦች ብለው ፈ ዳዓ ግ ተን ፈረዱብን ከተፈረደብንም በኋላ ዓ ዛ ከብዙ ቀንም በኋላ ሁሉ አሳላፊ ነው ወደ ምትባል ከተማ ደረስን በዚያች ሀገርም ያሉ ሰዎች ለጊዜው በመልካም አቀባበል ተቀበሉን ካንድ ዓመት በኋላ ግን አንድ ምቀኛ ሰው ተነሥቶ ይሀ ምእመን የሚባል ሰው ምንም እርሉ ደግ ቢሆን ሚስቱ ወንጌል ክፉ ናትና ሚስቱን ይዞ ካገር ካልወጣ ለሕዝቡ ሁሉ ጤና አይገኝም ብሎ ላገረ ንዢው ነገረው በዚሁ ምክንያት ካገር እንድንወጣ ታዘዝን አኛም ቀን ለቀን የሔድን እንደ ሆነ ያው ምቀኞችን ያየንና ደግሞ አንድ ክፉ ነገር ተናግሮ እጃችንን ያሲዘዋል ብለን ስለ ፈራን በሌሊት ለመሔድ ተማክርን ሌሊትም በሆነ ጊዜ አውራ መንገዱን ትተን ጠባቡን መንገድ ይዘን ሔድን ማቴ ነገር ግን የጨለማ ጊዜ ነበርና መንገድ ጠፍቶብን ዱር ለዱር ስንሔድ አውሬ በድንገት መጥቶ ባሌን ምእመንን ነጥቆ ወሰደብኝ ብጮሀም የሚደርስልኝ ሰው አላገኘሆም ፐ ጉ በማግሥቱም በራሴ ላይ ትቢያ ነስንሼ ልብሴን ቀድጄ እያለቀስሁ ብቻዬን ስሔድ መታመኔ በእግዚአብሔር ነው ወደ ምትባል ከተማ ደረስሁ የዚያችም ከተማ ንጉሥ በሰገነቱ ላይ ተቀምጦ አይቶኝ ኖሮ ያች ሴት ምንድር ናት እስቲ ጠይቃት ብሉ አንድ አሽከር ላከልኝ እኔም ለመላክተኛው መክጁዬን ሁሉ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻው አጫወትኩት እርሉም ሔዶ በነገረው ጊዜ ብዙ አዘነልኝና ወደ እንግዶች ማደሪያ ቤት ውሰድዋት ብሉ አዘዘልኝ በማግሥቱም ማኅበረ መላእክት የሚባሉትን ጭፍሮች ጠርቶ አጐበር ሠርታችሁ አጉጐበሩን ወርቀ ዘቦ ግምጃ አልብሳችሁ ጭፍሮችን ሁሉ በየወገናችሁ ሰብስባችሁ አልቃሽ አቁማችሁ ስለ ባሏ ስለ ምአመን አልቅሱላት ብሎ አዘበ እነርሉም ጌታቸው እንዳዘዛቸው አጉበሩን ሠርተው በታሳቁ ሜዳ አስቀመጡት አኔም አጉበሩን እየዞርሁ አለቀስ ጀመርሁ በዚያ ጊዜ ጭፍሮች ሁሉ ልዩ ልዩ ባንዲራቸውን ይዘው በክፍል በክፍሉ ሊመጡ ጀመሩ መጀመሪያ ማኅበረ ነቢያት የሚባሉት ጭፍሮች መጡ ባንዲራቸውም ብጫ ሆኖ በውስጡ ዓይን ተሥሉበታል ቀጥሎም የንጉሥ ልጅ መጣ የርሱም ባንዲራ ቀይ ሆኖ በውስጡ የመስቀል ምልክት አኣለበት በስተቷላሳውም ማኅበረ ሐዋርያት የሚባሉት ጭፍሮች የጌታቸውን ባንዲራ የሚመስል ባንዲራ ይዘው መስጡ ቀጥሎም ማኅበረ ሰማዕታት የሚባሉት ጭፍሮች መጡ ባንዲራቸውም ቀይ ሆኖ ሰይፍ ተሥሉበታል ቀጥሎም ማኅበረ ጻድቃን የሚባሉት ጭፍሮች መጡ ባንዲራ ጥቁር ሆኖ በላይ የዱር አውሬ ተሥሉበታል ቀጥሉም ማኅበረ ምእመናን መጡ ባንዲራቸውም አረንጓዴ ሆኖ በላዩ የዓለም ካርታ ተሥሉበታል ከነዚህም ሁሉ መካከል ዳዊት የሚባል በገና መች ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር ዳድቀዕ ዕመ ሳሦ ይፈሪ መይያን መ ያሆያ ፈያኖዕ እያለ በገናውን ሲደረድር ያየው ሰው ሁሉ በእንባ ይራጭ ነበረ የነሱም መመ ቁ ሠ ወዳጄ ልቤ አኔም ይህን ሁሉ ባየሁ ጊዜ የባሌ ኀዘን እየጻናብኝ ሔደ በዚያ ጊዜ አልቃሾች እንዲህ ብለው አለቀሉ ዘመዶቹ ጠሉት አርሱም ተበደለ የዱር አውሬ ሆኖ ስው አልቀርብ እያለ ዋይ ዋዬ ዋይ ዋዬ መቼ ክፉ ነበር አርሱ ለወደደው ሰውስ ይቅርና አውሬ እንኳ ለመደው ዋይ ዋዬ ዋይ ዋዬ ምእመን ሰላምታ ሲጽፍ አየሁት የተላከ ብሎ ይድረሱን ከሞት ዋይ ዋዬ ዋይ ዋዬ አንዲሁ ከጧት እስክ ማታ ስናለቅስ ውለን ፀሐይ ስትጠልቅ ተለያየን እኔም እንግዴህ ዓይናችሁን ለማየት እንኳ ፈቃድ የለኝምና በፅለተ ምጽአት ለመፋረድ ያብቃን ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ ባ ዓመት በሮምያ ከተማ ተጻፈ ምዕራፍ ስለ ፍቅርና ስለ ተንኩል ከዚህም በኋላ ወደ ሰሜን ዞርሁ የሰሜን ሀገር መንገድ በዚያም በዚህም ያስኬዳል ግን ቶሎ ብዬ ወደ ደቡብ ሔድሁ በደቡብም ጠደ ምሥራቅ ተመለስሁ በሰሜንና በደቡብ በምፅራብም ዞሬ ተመልሼ ማረፊያዬ በምሥራቅ ነበረ በምሥራቅም ሀገር ፍቅር የሚባል ሰው በጌትነት ይኖር ነበረ ሮሜ አርሱም እጅግ መልካም ሰው ስለ ሆነ ወደ ቤቱ የሚመጡትን እንግዶች ሁሉ ይቀበል ነበረ ነገር ግን ቅናትና ምቀኝነት የሚባሉ ጐረቤቶች ነበሩትና እንግዶች ሁሉ ወደ ፍቅር ቤት ሲሔዱ ያዩ እንደ ሆነ ፍቅር ዛሬ በቤቱ የለምና ወደኛ ዘንድ መጥታችሁ አደሩ እያሉ ከደጅ ይወጠስዱዋቸው ነበረ ወዳጁ ልቤና ሴሎችም አንድ ቀንም በሩቅ ቆሜ ስመሰከት ተንኩል የሚባል ሰው ሦስት አጋሰሶች ጭኖ ሲመጣ አየሁት ወደ ፍቅር ቤትም ለማደር አስቦ ኖሮ አቃንቶ ሔደ ፍቅርም ተንኩል ወደርሱ ሲመጣ ባየ ጊዜ ቅንነት የሚባለውን አሽከሩን ጠርቶ እንግዳ መጥቶአልና ወጥተህ ተቀበል አለው ጭነቱም እስቲራገፍ ብዙ ዩ በቢያ ጊዜ ቶሎ ብሎ ሚስቱን ገርነትን ጠርቶ ምነው እንግዶቹ ጠፉ ይሆን እስኪ ብቅ በይና እያቸው ያልሆነ አንደ ሆነ አኔም እመጣለሁ ጸላት አሷም ገና ብቅ ስትል ተንኩል ጭነቱን አራግፎ ነጫጭ ልብሱን ለብሶ እየሳቀና ደስ እያለው ሲመጣ አገኘችውና ወደ ቤት አስገባችው የተጫነውም ምንም እንደ ሆነ አላወቁም ተንኩል ግን ፍቅርን ከዚያ ሀገር ለማጥፋት አስቦ ነበርና ምስክር የሚሆኑ ሰዎች በሣጥን ውስጥ አግብቶ ምግባቸውን ጨምሮ ቆልፎባቸዋል አሳቡም ፍቅርን ክፉ ነገር ለማናገርና እነዚያን ሰዎች ምስክር ለማድረግ ነበር የራትም ጊዜ ሲደርስ ፍቅር ወደ ተንኩል ቀርቦ ጌታ ሆይ እባክህ አንግዴህ አህል እንቅመስ እአለው ተንኩል መለሰ ጌታው ምን ከፋኝ ነገር ግን ጭነቴ በደጅ እንደ ወደቀ ነው አስቀድሞ ጭነቱን አስገብተን ከዚያ በኋሳ ለራት ብንቀመጥ መልካም ይመስለኛል አሰ ፍቅርም አሽከሩን ቅንነትን ጠርቶ ምነው እንዲህ አደረግኸኝ ጭነቱን በጊዜ አታስገባም ኖሯልን አለው እመቤቴ ሰእንግዳ እግር ውኃ አሙቅ ብለውኝ ነበረ አለ በል እኮ አሁንም በቶሎ አስገቡ ብሎ ተመሰለሰ ጭነቱም ከገባ በኋላ ለራት ተቀመጡ እራትም ከተበላ በኋላ ጨዋታ ጀመሩ ተንኩል በመጀመሪያ እንዲህ አለ ወዳጄ ፍቅር ሆይ እኔ በሀገሬ ሳለሁ አባትህ ክርስቶስ ከሞተ ወዲህ ከታናሽ ወንድምህ ከትሕትና ጋራ በዚህ ሀገር የመኖራችሁን ወሬ ስምቼ ነበር ነገር ግን ወንድምህ ትሕትና እንዳንተ አልተመቸውም አሉ ወዳጄ ልቤ ፅ አሁንም እንዳንተ ያለ ሰው ለጌታ ሳያድር መኖር አይገባምና ለዚህ ሀገረ ገዢ ለሰይጣን አሽከር ብትሆን መልካም ነው ቤትህም ይታፈር ነበር አንጂ መቼ ለሁሉ መሣፈሪያ ትሆን ነበረ ፍቅር ደግ ሰው ነው እያሉህ እውነት ይመስልፃልን አትስማ ሁሉም ትዳሩን እያበጀ ነው እኔ ዛሬ ወዳንተ መምጣቴ ይህን ልመክርህ ነው እንጂ ምንም ሌላ ጉዳይ የለኝም እንግዲያውማ ቅናትና ምቀኝነት ያባቴ የሄሮድስ የአኅቱ ልጆች አይደሉምን እርሳቸውን ትቼ ወዳንተ መምጣቴ ለምን ይመስልፃል ምክሬን ስማ እያለ ሊነግረው ጀመረ ፍቅርም እስቲ እኮ ለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ያውቃል አለው ከቢዚህም በኋላ ወደ መኝታ ቤት ሔዱ። የሐዋ ሔዶም ያየውን ሁሉ ለወንድሙ ለምቀኝነት ነገረው ምቀኝነትም መለለ ወንድሜ ቅናት ሆይ ከቶ ይህ ፍቅር የሚባል ሰው በምን ታደለ እኛ በገዛ ሀገራችን ተንቀን ተጠልተን መኖር አርሱ ተአከብሮ ተወዶ መኖር ምን ይመስልፃል በል እስኪ ሌላውስ ይቅርና ያጐታችን የፄሮድስ ልጅ ተንኩል እንኳ ወደ ፍቅር ቤት ሔዶ ይደርን ይህን ሰው ከዚህ ሀገር ካላጠፋን ምን ኑሮ አለን እንዲህማ ከሆነ አሽከሮችስ ሚስቶችስ ቪኖሩን ምን ይሆኑናል ወደርሱ ቤት የሚመጡ ብዙ ናቸውና እነዚያን እያዩ እየተዉን ይሔዳሉ እንጂ ከኛ ጋራ የሚኖሩ ይመስልሃልን እያለ ጣቱን ያጮህ ጀመረ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ይህም ከሆነ በኋላ ተንኩል በፍቅር ቤት ዋለ አደረ የሚሔድበትም ጊዜ በደረሰ ጊዜ ሔዶ በጭነቱ መካከል ተቀመጠ ፍቅርንም ቆይታ አለኝ ብሎ ጠራው ፍቅርም በመጣ ጊዜ ተንኩል ነገር ጀመረ ወዳጄ ፍቅር ሆይ በዚህ ሀገር የምትኖረው ከቶ ስለ ምን ነው ርስትህ ጉልትህ በምዕራብ ህገር ይሆኑን ሰምቼ ነበረ ዘሌዋ ርስትህን ጉልትህን ለማንም ከብት መቋሚያ አድርገህ በቪህ ሀገር መቀመጥህ ለማን ደስ ይበለው ብለህ ነው ከደግነት የሚቆጠርልህ መስሎህ ነውን አለው በዚያ ጊዜ ሞኙ ፍቅር ሆይ እውነት መሰለውና ይልቁንም ተንኩል የቅናትና የምቀኝነት ያጐታቸው የፄሮድስ ልጅ መሆኑን ዘነጋውና የልቡን ምሥጢር ሁሉ ሊነግረው ጀመረ ተንኩል ሆይ እንግዲህ አብረን በላን አብረንም ጠጣን ምን እሰውርፃለሁ እነዚህ ጐረቤቶቼ ቅናትና ምቀኝነት ጠላቶቼ ናቸው እነርሱ በቤታቸው ቁጭ ብለው አሽከሮቻቸውን አይሁድን ከሳሽ አድርገው ልከው አባቴን ክርስቶስን አስገደሉት እኔም ያን ጊዜ ገና ልጅ ነበርሁ አሁን ግን ሰውነቴ እያደገ ነገሩ ይቆጨኝ ጀመር ገዳዮችንም በጠቋሚ አገኘኋቸው እነዚያንም ለመግደል ሳስብ የነፍስ አባቴ መምሬ እውቀቱ መጥተው በምን ነገር አይሁድን ልትገድል ታስባለህ ጌቶቻቸው ምቀኝነት ቢያዙዋቸው እምቢ ይበሉ ብለህ ነውን አሉኝ ከዚህም በኋላ ቅናትና ምቀኝነት ያሉበትን ስፍራ እየጠያየቅሁ አገኘሁት አሁን እነርሱን ከስሼ በፍርድ እንዳስገድላቸው ያገሩ ዳኛ ሰይጣን የሚባለው ጠላቴ ነውፊ ለነርሱ ግን አያታቸው ነው ዮሐ ቋ ነገሩ ቢቸግረኝ ወደዚህ ሀገር መጥቼ ቤት ሠርቼ ተቀመጥሁ አሳቤ ግን ጊዜ ሲመቸኝ ቢሆን እኔ ራሴ ባይሆን እጅ አዛውሬ አነርሱን አስገድዬ ያባቴን ደም እወጣለሁ ብዬ ነው እንዲያውም አባታቸው ሰይጣን ያየ እንደ ሆነ ህገር አስጩሆ ያሲዘኛል ብዬ ነው እንጂ ቀን ለቀንም ገድያቸው ብሔድ አልፈራም ነበር ወዳጄ ልቤ የዚህ ሀገር ሰው ሁሉ እንዴት ጠልቷቸዋል ይመስልፃል ሥራቸው ሁሉ ባልና ሚስት ማፋታት አሽከርና ጌታ ማለያየት ድኃና ባለጠጋ ማጣላት አባትና ልጅ ማረጋገም ወንድምና ወንድም ማጋደል ነው ማቴ ል እንዲህ እያደረጉ ሀገር አውከዋል እያለ ም ሉ ዘረገፈለት ስጤሩን ሁለ ተንኩልም ይህን ሁሉ ምሥጢር በሰማ ጊዜ ለካ እንደ ዚህ ፃውን እኔ ይኸን ሁሉ ነገር መቼ ለማሁ እንዲህስ ከሆነ ያሰብከውን ይፈጽምልህ ብሎ ጭነቱን ጭኖ ተነሣና ተሰነባብተው ሔደ ። ናሳ ዕሉል ከዚህም በኋላ ወደ መግደያው ስፍራ ደረሉፁ ቅናትና ምቀኝነትም ፍቅርን ደብድበው ጣሉት ገደልነውም ብለው ወካዎ እያሉ ሔዱ ለተንኩልም ብዙ ሽልማት ሸለሙት ደግሞ ተካፍስው የያዙት ርስት ጭካኔ የሚባል ነበረር ያንን ስተንኩል ብቻ ሰቀቁለት ምፅራፍ ስለ ፍቅር ሕይወት ከዚህም በኋላ የፍቅር ወዲጆች ሬሳውን አንሥተው ሊቀብሩ መጡ በቀረቡም ጊዜ ጥቂት ጥቂት ሲተነፍስ አገኙት ከዚያም ቶሎ አንሥተው ልቡና ወደሚባሰው ቤታቸው ይዘውት ሔዱ ብዙ ቀንም አስታመመሙት እኔም ወደ ተኛበት ቤት ገብቼ እግዚአብሔር ይማርህ እንደምነህ አልሁት ፍቅርም መሰሰ ዛሬስ በጐ ነኝ በእግዚአብሔር ቸርነት ከሞት የተረፍሁ ይመስለኛል ቁስሉም ሊጠግ ጀምሯል አለ እንኪያ ምነው ወደ ደጅ ብቅ አሰማሰትህ አልሁትፁ እስካሁን ድረስ ግርሻውን ፈርቼ ነው እንግዲህ ወዲህ ግን ብቅ እላለሁ አስሰ አሁንም ምሕረቱን ይላክልህ ደኅና ሰንብት አልሁት ወንድሜ ሆይ ማን ትባላለሰህ የመጣህበትስ ከወዴት ነው ከዚህ ቀድሞ የተዋወቅን አይመስለኝም አለ እኔ ይህን ዓለም ሰመዞር የመጣሁ እንግዳ ነኝ በሽታህን ብሰማ ልጠይቅህ ብዬ መጣሁ አልሁት እግዚአብሔር ይጠይቅህ አሁን ምን አደከመህ ከዚህ ሀገር ያሱት ወዳጆቼማ እግዚአብሔር ይማርህ ብለው እንኳ ሳይልኩብኝ አልቀሩምን ምን ይሆናል ክፉ እንዳይሆነ እንዲህ አንዳንድ ለው ይገኛል ደግ እንዳይሆኑ ደግሞ ሰው እንዲህ ያስቀይማል የእግዚአብሔርን ቸርነት ተመልክቶ ሁሉንም ነገር እንዲያው መተው ይሻላል በል አሁንም ቢያበቃኝ ሰወደ ፊቱ እንጠያየቅ አለኝ መሆኑንማ በዮሐንስ ቤት አይቸሣለሁ ንግግርና ጨዋታ ግን የለንም አልሁት ፅፎ ዮሐ ይሆናል ይሆናል እርሱ አጅግ ወዳጄ ነው አሁን ስንኳ ሦስት ጊዜ ያህል እየመጣ ጠየቀኝ አለሰኝ እኔም በዚሁ ሀገር የምሰነብት ከሆነ መሸብህ በቶሎ ሒድ ምናልባት ሰው ሰመሆን ባባትህ አሽከር ስዎች በቁጥር የበዙ ነበሩ ሀ እየመጣሁ አጫውትህ ነበረ ነገር ግን አቶ እንደ ጊዜው አስጠርተውኝ ወደ እርሳቸው መሔዴ ነው ከዚያም በቶሎ እመለሳለሁ አሁን ዝም ብዬ እንዳልቀር የኩራት ይመስልብኛል ብዬ ፈራሁ ያንተ ታናሽ ወንድም ትሕትና ወንበር ዘርግቶ ያስተምራል እኔንም አስተምርዛፃለሁ ብሉኛል ከርሱ ጋራ ሁለት ዓመት ያህል ሳልቀመጥ አልቀርም አንተስ ከሞት ከተረፍህ ወደ ወንድምህ ቤት ሳትመጣ ትቀራሰህን ያን ጊዜ በውል እንተዋወቃሰን ወይም ወዳገሬ ስመሰስ መጥቼ እስናበትፃለሰሁ ብዬው መንገዴን ሔድሁ ምዕራፍ ስለ አቶ እንደ ጊዜው ከዚህም በኋላ ወደ አቶ እንደ ጊዜው ቤት ሔድሁ አቶ እንደ ጊዜውም በታላቅ ወንበር ተቀምጠው ነዘረ በርሳቸውም ቤት የሚኖሩ ሁሉም አቶ እንደ ጊዜውን ከበው ተቀምጠዋል አቶ እንደ ጊዜው ሲስቁ ሁሉም ይስቃሉ ዝም ሲሱም ዝም ይላሉ ሲዋሹም አነርሱ እውነት እውነት ይላሉ ከርሳቸው ተለይተው ምንም የሚሠሩት ሥራ የሰም እኔም ወደ እርሳቸው ገብቼ ጌታ አቶ እንደ ጊዜው ሆይ እኔን ስለምን አስጠሩኝ አልኋቸው አርሳቸውም በመልካም ቃል መለሱልኝ አንተም ታውቃሰህ ቤተ ሰዎቼ እንደ በዙ ገንዘቤም ሥፍር ቁጥር እንደሌለው አሁንም የገንዘቤን ዘገብአና ዘወጽአ እየጻፍህ ለቤተ ሰዎቼ በየጊዜው ምግባቸውን እየስጠህልኝ ከእኔ ጋራ እንድትኖር ነዋ አሉኝ ነገሩስ መልካም ነው የሚሰጡኝ አልኋቸው ምግብህን ከበሰስ ፍሬ እንደ ፈቀድህ ትበላለህ ምግቤንና ደመወዜን እንደምን ነው ደሞዝህንም ባመት የዘላሰም ሞትን እሰጥፃለሁ አሉሱኝ አኔም ቶሎ ብዬ ጌታው አቶ እንደ ጊዜው ሆይ ይህስ ከቶ አይሆንልኝም እፄ እምቢ ብዬ ነው እንጂ የታላቁ ንጉሥ ልጅ ከእኔ ጋራ ሁን ምግብህን ከሰማይ የወረደ እንጀራ ደሞዝህንም የዘላሰም ሕይወን እሰጥዛለሁ እያለ ያባብለኛል ዮሐ ል ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ዳግመኛ ይህንን ዓለም ዞሬ ሳልጨርስ ደብዳቤ ጸሐፊ አልሆንዎም ደግሞ ሁሉንም ነገር ከወዳጄ ልቤ ጋራ መክሬ እነግርዎታለሁ አሁንም ጤና ይስጥልኝ ብያቸው መንገዴን ሔድሁ ከዚህም በቷላ ላቶ እንደ ጊዜው ጸሐፊ መሆን ጥቅም ይገኝበት እንደ ሆነ ብዬ ለወዳጄ ልቤ ባማክረው ወንድሜ ሆይ ምነው ሁሉን ታስባለህ ላቶ እንደ ጊቤው ጸሐፊ ከመሆን ለምኖ መብላት አይሻልምን አለኝ እኔም እውነትህ ነው ብዬ ያቶ እንደ ጊዜውን ነገር ቸል አልሁት ምዕራፍ ስለ ትምሕርት ቤት ከዚህም በኋላ ወደ ትሕትና ቤት ሔድሁ እርሱም በወንበር ተቀምጦ ያስተምር ነበረ ከርሱ የሚማሩ ለዎች ስንት ይመስሏችኋል እነ ንጽሕና እነ እውቀት እነ እውነት አነ ዝምታ እነ ትዕግሥት እነ ድኅነት እነ የዋህነት እነ ሰላም የጥበብ መጀመሪያ ፈሪፃ እግዚአብሔር እንኳ ከርሉ ይማር ነበረ መዝ ቶ በዚህም ሁሉ ላይ ድኅነት አለቅነት ተሾሞ ነበረ እኔም ወደ አለቃው ሔጄ ትምሀርት ለመማር መጥቻለሁና ንገርልኝ አልሁት እርሉም ሔዶ በነገረው ጊዜ ከተማሪዎቹ አንዱን ጠርቶ ይህን ለው ቶሎ ቶሎ አስተምረው ብሎ አጋጠመኝ ከዚህም በኋላ ዳዊት ለመማር ጀመርሁ ነገር ግን ልፍ ታዩ ፍምዶሙ የሚለውን ለማጥናት አልቻልሁም መዝ ልጳ ይህንም ትቼ የዜማ ትምህርት ጀመርሁ ነገር ግን የዜማ ትምህርት አጅግ አድካሚ ስለ ሆነ ጥቂቶችን ብቻ በቃሌ አጠናሁ እነርሱም ከዚህ ቀጥለው ያሉት ናቸው ሪጮምሥ ታታ ጋፊሬ ወሪፊሷ ሄኔ ታያ ሉ ወምታ ጋመ ዝን ይዐሏ ሃኔ ታያ ሐዉጳድ ሄኔ ታያ ወሐመጋረፅ ዎቀዱሰ ጋፉሪ ዳኦዕ ታሪሪም ፖታ። ማቴ ቋ ሌላውስ ይቅርና ታላቁን ጀግና ክርስቶስን ሐሙስ ማታ ከዱር ውስጥ አውጥቼ ዓርብ በቀትር በንጨት ላይ አሰቅዬ ያስገደልሁት እኔ የበሰው ጌታ ቅናት አይደለሁምን ዮሒ ቿ ጓ ደግሞ ለርሱ አሥራ ሁለት አሽከሮች ነበሩትና እነዚያን ሁሉ ወደ ሔዱበት ስፍራ እየተከተልሁ በሞት ያጠፋኋቸው እኔ አይደለሁምን ይሀም ሁሉ ሐስቴ አንደ ሆነ እናንተ ሁላችሁም መስክሩብኝ እንዲያውስ እኔ ባልኖር የሲኦል መንግሥት ትጸና ኖሯልን አሁንም ወንድሞቼ ሆይ ካይናችሁ ያውጣኝ ብሎ ተቀመጠ ወዳጄ ልቤም አቶ ቅናት ሲፎክር ግድግዳውን ተጠግቶ ቆሞ ነበረና እርሱ ሲቀመጥ አይቶ መሰንቆውን አንግቶ እንደ ገና ተው ሰንጐ መገን ይል ጀመረ ተው ሰንጐ መገን ተው ሰንጐ መገን ቼ ቼ ቼ ታላቁ ጌታ ሲወለድ ባገር ንጉሠ ፄሮድስ ደንግጦ ነበር ኢየሩሳሌም እርዳ ነበር ያገር ሕፃናት መች ያልቁ ነበር የፍጀው ጌታ ተንኩል ባልነበር በዚያ ጊዜ አቶ ተንኩል ሰይፉን ውልቅ አድርጐ ይፎክር ጀመረ ሀካኪ ዘራፍ ሀካኪ ዘራፍ በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ ያሱትን ሕፃናት ያስፈጃቸው ማነው አኔ የፍጀው ጌታ አይደለሁምን ማቴ አንዲያውስ ካቶ ቅናት በቶር በጦርነት ጊዜ የሚቀድመኝ ማነው ዘወትርም በጦርነት ድል ማድረጌ ፊት ሰፊት ተዋግቼ ወዳጄ ልቤ አይደሰም መሣሪያዬን ሰውሬ ይዢ ዱር ለዱር ስሔድ አድሬ ጧት በድንገት ኣደጋ አየጣልሁ ነው አሁንም ካይናቸሁ ያውጣኝ ብሎ ተቀመጠ ይህም ሁሉ ሲሆን ሰአዝማሪው እስኪ አንድ ዋንጫ ጠጅ ስጡት ብሎ የሚናገር አልነበረም በዚያ ጊዜ ወዳጄ ልቤ ቆጨውና ወደኔ ቀርቦ አቶ ተንኩልን ላዋርደው አሰኝ ቢመታሀሳ አልሁት አስቄበት የሆነው ይሁን አለ አንተ እንደ ወደድሀ አድርግ እኔ ግን ውርድ ከራሴ ነው አልሁት ከዚሀ በኋላ ቃሉን ከፍ አደረገና አቶ ተንኩል ያንተም ግዳይ ከግዳይ ተቆጠረና ትፎክራለሀን አለው በቪያም ጊዜ ሁሉም ዝም ብለው ይሰሙ ጀመሩ ተንኩልም በንፍረት ቃል እንዴት አንተ አሰው በቤተ ልሔም ገደልሁ ብለህ የፎክርክው ገና ጡት የሚጠቡትን ሕፃናት ከናቶቻቸው እጅ አየቀማሀ ኣይደለምን አለጡው ለካ ሁሉም በዚህ ነገር ሆድ ለሆድ ሲተማሙ ቆይተው ኖረው ዳር እስከ ዳር ከት ብሰው ሳቁበት አቶ ተንኩልም አጆግ አፈረ ወዳጄ ልቤ ግን አቶ ተንኩልን ፈራና እስኪነጋ ድረስ ድምጡ ሳይለማ አደረ ምዕራፍ ስለ ንጉሥ መልአክት ከዚህም በኋላ እነጋጋሰሁ ሲል ከበር ውጭ ጩኸትና ፍጅት ሆነ ሠርገኞችም እድመኞችም ከወዲያ ወዲህ ይራወጡ ጀመር አኔም ባሰሁበት ስፍራ ቆሜ እየተንቀጠቀጥሁ ወደ ወይዘሮ ዓለሚቱ ቤትም የገባሁበትን ቀን ረገምሁ ከሙሽሮቹም አንዱ ወደ ወይዘሮ ዓለሚቱ ሲሮጥ ሔደና እመቤቴ ሆይ ጉድ ፈላብን አላት አንዴት አሰችው ሽ አንቺን ያሳደገሽ አግዚአብሔር የሚባለው ታላቁ ንጉሥ ተቆጥቶብሻል መሰለኝ አላት ዘፍጥ ቶ ል ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ምንስ ቢሆን ያሳደግኋት ጌታዋ እኔ አይደለሁምን የመጀመሪያ ባሏ አዳም እንኳ አታክልት ሲሰርቅ ተይዞ በታላቁ ወህኒ በሲኦል ቢታሠር የእኔ ልጅ ዕዳውን ከፍሎ አእስፈታው ፅ ጴጥ ፅ ፄ እርሷንም እንዲህ እንዳላየ ማየቴ ምንአልባት ብትመከር ዘመዶችዋንም ብትመክር ብዬ ነበረ እንጂ እንግዲያውማ ባንድ አፍታ ድራሽዋን ለማጥፋት እችል አልነበረምን ሉቃ ቋ ምንስ ልጅዋ ቢሆን ጠሳቴን ምኞትን በከተማዬ እንደ ምን ትዳረው ወዳጆቼን ሁሉ የገደለ የርሷ ልጅ ምኞት አይደለምን አሁንም ወደ ዓለሚቱ ቤት የገቡትን አድመኞችንና ሠርገኞችን ሙሽሮቹንም ይዛችሁ አምጡ ብሎናል ብለው ሞትና መቃብር መጥተዋል አላት ብቻቸውን ናቸውን አለችው ደግሞ ብቻቸውን እረ እልፍ አእላፋት ወታደሮች አስከትለው ነው አላት ስማቸውን ታውቀዋለህን አለችው ዋና ዋኖችን አውቃቸዋለሁ አላት አነማን ናቸው አለችው እነ ቁርጠት ቁርጥማት ፍልጠት ምች ውጋት ተስቦ መጋኛ ንዳድ ፈንጣጣ ኩፍኝ ቂጥኝ ጨብጥ ቁምጥና ሳል ያይን ሕማም የልብ ሕማም ሌሎችም ብዙ አሉ አላት እርስዋም እያጉረመረመች ወደ ቤትዋ ገባች እነዚያ ወታደሮች ግን ወደ ሠርጉ ቤት ጉበተው ከሠርገኞች ወገን አንዱንም ሌላውንም እየያዙ ለሞት ይስጡ ጀመሩ ሞትም ስመቃብር እያሳለፈ ይሰጥ ጀመረ መቃብርም ክያዘ የማይለቅ ጽኑ ጀግና ነበረ ይህም ሁሱ ሲሆን ሠርገኞች በር ዘለን ቅጥር ጥሰን እንሽሽ ብሰው አያስቡም ነበር አንዳንዱስ እንዲያውም ይስቁ ነበሩ እንዲህም ሲስቁ እያንጠለጠሉ ይወስዱዋቸው ጀመር መዢ ሮኃ ቋ ጋአ ነገር ግን የወይዘሮ ዓለሚቱ ቅጥር ግቢዋ ሰፊ ነበረና ታዘው የመጡት ወታደሮች ሠርገኞቹንና አድመኞቹን ሁሉ ባንድ ጊዜ ጨርሶ ለመያዝ አልሆነላቸውም ወዳጄ ልቤ አንዳንዱም ከተያዙ በኋላ አየተለማመጡ ተለቀቁ ነገር ግን የኋላ ኋላ ወደ ዓለሚቱ ሠርግ የታደመ ሰው ሁሉ ተይዞ መታሰሩ አይቀርም ወደ ሠርጉም የመጡትን ሰዎች ሁሉ ንጉሠ በሺወርኒ አስቆጥሯቸዋል ይባላል አኔና ወዳጄ ልቤም ለጊዜው ሳንያዝ ከወታደሮቹ አመለጥን ምዕራፍ ስለ ማቴዎስና ስለ ሉቃስ ስለ ሙሴም ጨዋታ ከዚህ በኋላ ወደ ምሥራቅ ዞርሁ በዚያም ማቴዎስ የሚባል ሰው ቤቱን በህገር መዳረሻ ሠርቶ አገኘሁ እኒም ወደ ቤቱ ሔጄ ጌታዬ ሆይ እባክህ አሳድረኝ እልሁት እደር አለኝ ማቴ ጥቂትም እንደ ቆየን ሉቃስ የሚባለው ባልንጀራው መጣና ጨዋታ ጀመሩ ሁለቱ ሲጫወቱ ቃላቸው አንድ ነው ግን የሉቃስ ቃል ትንሽ ረዘም ይላል ሉቃስም ንግግሩን ጀመረ ወንድሜ ማቴዎስ ሆይ ያ ባለጠጋ እንዲያ ሲቀማጠል ኖሮ ሞተ ግን በሞተበት ቀን ሰው ሁሉ ደስ አለው እንጂ አንድ ሰው እንኳ አላሰቀሰለትም አለ ሱቃ ሸ ማቴዎስ መለሰ ወንድሜ ሉቃስ ሆይ ድኃ መሆን ምንኛ መልካም ነው ይመስልሃል አሰ ማቴ ይህንስ አኔም ብዬ ነበረ አለ ሉቃ ከዚህም አያይዘው ያሰሚቱን ነገር አነሀ ማቴዎስ ጀመረ ንጉሥ ተቆጥቶ ወደ ዓለሚቱ ቤት የገቡትን ሠርገኞቹን ሁሉ አሲዞ ወሰዳቸው ሲሉ ሰማሁ እንዲያውም እስከ እርስዋ ድረስ ተይዛ ልትጋዝ ነው ብሎ የንጉሠ ልጅ ነገረኝ አለው ማቴ ፀ ቋሯ ሉቃስ መለሰ አርስዋ ተይዛ ብትጋዝ እጅግ መልካም ነገር ነው ሉቃ ስንት ሰዎች ያበላሸች ይመስልፃሃል የጳውሎስ አሽከር ዴማስ የሚባለው አንድ ቀን ወይዘሮ ዓለሚቱን ቢያይ ጌታውን ትቶ ወዉደ እርስዋ ነጐደ ጢሞ ፀ ጃ ወዳጄ ልቤና ሴሎችም የወይዘሮ ዓለሚቱን ነገር ስንቱን ልንገርህ የርሷንስ ነገር ወንድማችን ዮሐንስ ይንገርህ እርሱ ጥቂትስ ስንኳ አይፈራትም ነበረ ሳትታሰሪ የቀረሽ እንደ ሆነ ምን አለ በዬኝ ይላት ነበረ ዳግመኛ ሰው ሁሉ እንዳይወዳት ይመክርባት ነበረ ጳ ዮሒ ማቴዎስ መለሰ የርሷስ ነገር መቼም አንድ ጊዜ የታወቀ ነው ኸረ ደግሞ ይህ የርስዋ ዲቃላ ምኞት እንዲህ እድርጐ የጠገበበት ምክንያቱ ምንድር ነው የለው ሚከት ያየ እንደ ሆነ በላይዋ ልሙት ይላል መልካም ፈረስ መልካም በቅሎ ያየ እንደ ሆነ የኔ በሆኑ ይላል እገሌ ተሾመ ሲሉ የለማ እንደ ሆነ ምነው እኔ በሆንሁ ይላል ከቶ የርሱ ነገር ብልፃቱ ጠፋኝ አለ ማቴ ሉቃስ መለለ ይህ ይደንቅፃልን ወደ ድግስ ቤት የጠሩት እንደ ሆነ ከርሱ የሚበልጡ ብዙ ሽማግሎች ሳሉ ወደ ላይ ወጥቶ በመጀመሪያው ወንበር ይቀመጣል ኋላ ግን ያ የጠራው ሰው መጥቶ እየጐተተ አውርዶ በታችኛው ወንበር ያስቀምጠዋል አለ ሉቃ ይህንንም ሲጫወቱ የምዕራብ ሀገር ባላባት ሙሴ መጣ ምን ትጫወታላችሁ አላቸው አንድ ጥጋበኛ ሀገር አዋኪ ምኞት የሚባል ሰው አለና የርሱን ነገር እንጫወታሰን አሉት ሙሴ መለለ ኽኸኸ አርሱ ነውን እረ ገና እርሱንማ አውቀው የለሞይ ነገሩን ሁሉ በደንጊያ ጽፌ አኑሬዋለሁ ይህንኑም ለእስራኤል ፅለት ዕለት አነብላቸው ነበረ ዘጸ ዳግመኛ እርሱ ብቻ አይምሰላችሁ ሌሎችም ዘጠኝ ባልንጀሮች አሉት ዘጸ ስማቸውም ከዚህ እንደሚከተሰው ነው ጣዖት ማምለክ ለጣዖት መስገድ የእግዚአብሔርን ስም ከንቱ ማድረግ ሰንበትን መሻር አባትና እናትን ማዋረድ መግደል መስረቅ መሴሰን ባሰት መመስከር እነዚህንም ሁሉ የሚመክርና የሚያበረታ ምኞት ነው አሰ አኔም ከሙሴ ጋራ እጅግም አልተዋወቅም ነበረና ስፈራ ስቸር ጌታው አቶ ሙሴ ምኞት ከዚህ ሀገር የሚሔድበት ጊዜ የሰምን አልሁት ወዳጄ ልቤ ጃሜ ሞኝ ነህን እናቱ ወይዘሮ ዓለሚቱ ካልሞተች እሉ ወዴት ይሔዳል አለኝ እንኬያስ እርሱ ወደ ሌለበት ሀገር መሔድ ይሻላል አልሁት ሙሴ መለሰ ዛሬ ገና ያልሰማው መጣ ሌላውስ ይቅርና ወደ ገነት ገብቶ እናታችን ሔዋንን ከአግዚአብሔር ጋራ ያጣላት ማን መሰለህ ምኞት አይደለምን ዘፍ ቶ አባብ መጥታ ያንን ቅጠል ብዬ እያለች ለሔዋን ስትመክር ምኞት በዚያ ባልነበረ ትበላው ኖሯልን ምን ይሆናል ቀረና የርሱንስ ነገር አለማንሣቱ ይሻላል ማቴዎስ መለሰ ምኞትን ጉድ ያደረገው የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ብቻ ነው አንጂ አሰ እንደምን አልሁት በገዳም ተቀምጦ አርባ ቀን አርባ ሌሊት በጾም ጊዜ ሰይጣን የወይዘሮ ዓለሚቱን ገንዘብ ሁሉ ይዞ መጣ ምኞትም ከርሱ ጋራ ነበረ ምኞት ከሰይጣን ጋራ መምጣቱ ክርስቶስ ይህን ገንዘብ አልቀበልም ያለ እንደ ሆነ ይህን ሁሉ ገንዘብ እንዴት ትመልሳለህ ኽረ ተቀበል ብሎ ለመምከር ነበረ ማቴ ፀ ክርስቶስ ግን የሁለቱንም አሳብ ያውቅ ነበረና ገና ሲመጡ በሩቅ ባያቸው ጊዜ ከሙሴ አጅ አንድ በትር ነጠቀና አበረራቸው በዚያ ጊዜ የሰይጣንን ሩጫ ያየ ሰው ከመቅጽበት ዓይን እልም ብሎ ጠፋ ምኞትም ከዚያ የበረረ ዓለሚቱ ቅጥር ደረሰ አለኝ ማቴ ፅ ያፅ ለምኞት የደረሱ ልጆች አሉትን አልሁት እንዴታ ነገር ግን ዲቃሎች ናቸው እንጂ ከሚስቱ አይደሉም አለኝ ስማቸውን ታውቀዋለህን አልሁት እኔ አላውቅም ግን ከሀገራቸው የመጣ ሰው ጳውሎስ የሚባለው ያንደኛውን ስም ሆድ አምላኩ ሲል ሰምቻለሁ ፊሊጵ ደግሞ የሁለተኛውን ስም ወንድሜ ሉቃስ ያውቀው ይሆናል አውን ወንድሜ ሉቃስ ሆይ የምኞት ልጅ የሆድ አምላኩ ታናሽ ወንድም ማን ይባላል አለው ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ሉቃስ መለሰ እንዲህ የምትጨነቁት የርሱ ስም ጠፍቷችሁ ነውን ልጅ ስብስቤ የሚባለው አይደለምን አለ ሉቃ ጳ ሴት ልጅሳ የለችውምን አልኋቸው ማቴዎስ መለሰ እአርስዋንስ ዱሮ ቀራጭነት ተሾሜ ሳለሁ ወደ ገበያ እየመጣች አውቃታለሁ አለ ማን ትባላለች አልሁት አለማፈር ትባላለች አክስቾቿ ግን ድፍረት ትላታለች አለኝ እኸ እርስዋ ናትና እርስዋማ ያቶ። ነገር ግን ወዳ ልቤ ክመዶቹን ናፍቋልና ስለዚህ ወደ ሀገሬ ለመሔድ እቸኩላለሁ ጤና ይስጥልኝ ወደ ፊት በደኅና ለመገናኘት ያብቃን ብዬው መንገዴን ሔድሁ ምዕራፍ ስለ ወዳጄ ልቤ ቁጣ ከዚያም ጥቂት እንደ ሔድን ወዳጄ ልቤ ተቆጣና ቆም ብሉ አንድ ጊዜ ስማኝ ልንገርህ አለኝ እኔም በል እስቲ ተናገር አልሁት እንግዴህ አንተ ካገኘኸው ሰው ሁሉ ጋራ ስትቆምና ስትጫወት ጊዜው በከንቱ ሊያልቅ አይደለምን ብትወድ የመጣህበትን ነገር በቶሎ ጨርሰህ ወደ ሀገራችን አንመለስ ወዳጄ ልቤ አንተ በስም የንጉሠ ልጅ አሽከር ትባላለህ ነገር ግን አንድ ቀን ስንኳ እርሱን ተከትለህ አገልግለኸው አታውቅም በድንገት አስጠርቶ አገልግሎትህን ቢጠይቅህ ምን ልትመልስለት ይሆን ሀገር ላገር እየዞርህ ይህን አየሁ ይህን ሰማሁ ብትል ከቁም ነገር የሚቆጥርልህ ይመስልሃልን ሮሜ ይልቅስ ጋሻ ጦርህን ይዘህ ጌታህን ብትከተል መልካም ነበረ ነቢያትና ሐዋርያት ጻድቃንና ሰማዕታት ሰፊ ሰፊ ሀገር እየተሾሙ መኖራቸው ጌታቸውን ቢያገለግሉ አይደለምን አሁንም አንተ ጌታህን አገልግለው ዛሬ አሽከር ቸግሮታልና ደስ ያሰኘኸው እንደ ሆነ አንድ ርስት ሳይተክልህ አይቀርም ሲኦል ወርዶ ጢስኛ ሁኖ ከመቀመጥ ደጅ ጠንቶ ርስት መተከል አይሻልህምን ወይስ በሲኦል የሚኖሩ ጢሰኞች ባመት ባመት የሚገብሩትን ግብር አታውቅምን ያንዱ ስው ግብር እሳት ጨለማ የማይሞት ትል ጥርስ ማፋጨት ልቅሶ ነው እስኪ አስተውለው አንድ ሰው ባመት ይህን ያህል እየገበረ መኖር እንደ ምን ይችላል ማቴ ቶ ጣ አኔ ይህን ያህል ዘመን ካንተ ጋራ መንከራተቴ ስንቅህን የሚሸከምልህ ሰው አታገኝም ብዬ ነው እንጂ ትቸሀ እአሔድ አልነበረምን አንዳንድ ቀን እንኳ የተለየሁህ እንደ ሆነ ችጋር ይዞህ ይውላል ድካሜ ሁሉ ላንተ ብዬ ነው እንጂ ለራሴ ምንም አላስብም እንግዲያማ ላቶ እንደ ልቡ አሽከር ብሆን አንድ ትልቅ ጥቅም ሳላገኝ የምቀር ኑሯልን ከዋልሁ ካደርሁም ዘንድ ልጃቸውን ወይዘሮ ይፋትን ይድሩልኝ ነበር አሁንም ቁርጡን ንገረኝ ከዚያ ወዲያ የማደርገውን አደርጋለሁ አለኝ አኔም በትሕትና ቃል ወዳጄ ልቤ ሆይ ያላንተ ምን ዘመድ አለኝ ከቤቴም ስነሣ አንተን ተማም ነው እንጂ አንተ አይዞህ ባትለኝ ጥንቱንም አላስበው ነበረ አሳቤም ይህን ዓለም መጻሕፍትን በምሥራቅና በምዕራብ በሰሜንና በደቡብ ለመዞር እንደ ሆነ ታውቃለህ አሁን ግን ከተቆጣህ ይቅርብኝ እኔም ባስበው ይህን ዓለም እስከ ሞቴ ቀን እንኳ ብዞር ሣ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም የምጨርሰው አይመስለኝም በውነትም አንተ እንደ ነገርከኝ አንዳንድ ቀንም ቢሆን ጌታዬን ማገልገል ይሻለኛል ነገር ግን በምሥራቅ ሀገር ያየናቸውን ሀገሮች ስማቸውን አየጻፍን ወዲያውም ዛፉን ተራራውን አያየን ወዳጆቻችንንም ሁሉ እየተሰናበትን ወዳገራችን አንመለሳለን ደግሞ አንድ ነገር ልንገርህ አኔ ሰኑሮ የምሥራቅን ሀገር መርጫለሁ ለምቾትማ የምፅራብ ሀገር ይመቻል ግን ሰዎቹ ወሬ ያበዛሉ በሰሜንም ሀገር መኖር መልካም ነበረ። ግን ሰዎቹ ሁልጊዜ ይጣላሉ ዘወትርም እንደ ተካሰሱ ይኖራሉ በደቡብም ሀገር መኖር መልካም ነበረ ግን የደቡብ ሀገር ሰዎች ከእውነተኞቹ ሐሰተኞቹ ይበዛሉ በምሥራቅም ሀገር መኖር ግን ምንም ሀገሩ አስቸጋሪና አድካሚ ቢሆን ሰዎቹ አጅግ መልካሞች ናቸው ነገራቸውም አጭርና እውነት ነው ዳግመኛ ብዙ ወዳጆች አለኝና ሀገሩ ባይመቸኝ ስንኳ ስለ ወዳጆቼ ብዬ በምሥራቅ ሀገር ለመኖር አስቤአለሁ አልሁት ወዳጄ ልቤ መለሰ ይሁን መልካም ነው አንተንማ አንድ ስፍራ ከያዝህልኝ እኔስ ለምን እሰይፃለሁ የሚስቆጣኝና የሚያበሳጨኝ ይህ ሀገር ላገር መዞርህ ነው እንጂ አንድ ስፍራ መያዝህን መቼ እጠላለሁ አሁንም ያሰብኸውን አድርግ አለኝ ወዳጁ ልቤ ሆይ ሁልጊዜ እኔ አስቀይምፃለሁ እንጂ አንተ አስቀይመኸኝ አታውቅም እግዚአብሔር ይባርክህ የቀናውን መንገድ ይምራህ አልሁትና መንገዳችንን ሔድን ምፅራፍ ስለ ትልቅ አዳራሽ በምሥራቅ ሀገር ጥግ ጥጉን ስሔድ አንድ ታላቅ አዳራሽ አየሁና ቶሎ ብዬ ወደዚያ ሔድሁ በስተውጭም እጅግ ያማረ ነበረና ገብቼ ለማየት ቸኩልኩ ነገር ግን ወደ በር በደረስሁ ጊዜ ምናልባት በረኛ ይኖራል ብዬ ደጀ ሰላሙን ለመግባት ስለ ፈራሁ አንድ ሰዓት ያህል ተቀመጥሁ ቢሆንም ግባ የሚል ወይም ተመስስ የሚል አንድ ሰው ስንኳ ወዳጄ ልቤ ያዳ አልነበረምና ወደ አዳራሹ ቀረብሁ አዳራሹም ተቆልፎ ነበረ በዚህ ነገ ተጨንቄ ሳለሁ ከወደ ጓሮ አንድ ብላቴና መጣ ማን ትባላስህ አልሁት መልካም አሳብ እባላለሁ አለኝ ይህ አዳራሽ የማነው አልሁት የንጉሠ ልጅ የክርስቶስ ነው አለኝ ለምን ጉዳይ ብሎ ሠራው አልሁት ሰልብስ ማጠቢያና ሰመሣሪያ መስቀያ ብሎ ነው በስተ ውስጡ ሁሰት ክፍል አለው ባንድ ወገኑ ከሰይጣንና ከአይሁድ ጋራ የተዋጋበት የጦር መሣሪያ ተስቅሎበታል በሁለተኛውም ወገን አሽከሮቹ ልብሳቸውን ያጥበብታል አለኝ ራኢ ጂቶ ፀ የጦር መሣሪያው ጥሩ ጥሩ ነውን አልሁት አእንዴታ ግን ከባድ ከባድ ነው ክርስቶስ ኃይለኛ ነበርና ሁሉንም ይዞ ተሰልፎ ነበረ እንጅ ሌላ ሰውስ ቢሆን አንዱን መሣሪያ ስንኳ ይዞ ሊስሰፍ አይችልም ነበር አለኝ የጦር መሣሪያው ስንት ነው አልሁት እኔ የማውቀው አሥራ ሰባት ይሆናል ቁጥሩም ከዚህ እንደሚከተሰው ነው አሥራት ስድብ ጥፊ ግርፋት የሾህ አክሊል መሰቀል ችንካር ምራቅ በትር ልግጫ ሐሞት መራራ ራቁትነት ውኃ ጥም ሞት በጦር መወጋት መቃብር ስሙን የማላውቀው ሌላም ብዙ መሣሪያ አስ አለኝ ማቴ ክርስቶስ ከአይሁድና ክሰይጣን ጋራ ሲዋጋ ይህን ሁሉ የጦር መሣሪያ ይዞ ነውን አልሁት አንዴታፎ ያውስ አንድ ሰዓት ብቻ ነውን ከአሙስ ማታ ጀምሮ አስከ አርብ ዘጠኝ ስዓት ድረስ ነው እንጂ አለኝ ይህንም ከነገረኝ በኋላ ወደ መጣበት ዘወር አለ አኔም ወደ አዳራሹ ውስጥ ገብቼ መሣሪያውን ሁሱ ለማየት አሰብሁ ነገር ግን በሩ ተቆልፎ ነበርና ደጅ ብመታ የሚከፍትልኝ አላገኘ ሁም ከዚህም በኋላ በራሴ አውቀት የሚባል መክፈቻ ነበረኝና ተኪሴ አውጥቼ ወደ ቁልፉ ውስጥ አግብቼ በል ና ተከፈት እያልሁ እታገል ጀመርሁ ነገር ግን ብደክም ብደክም ማን ፍንክች ይበል ያ መልካም አሳብ የሚባል ብላቴና በሩቅ ቆሞ ይመሰከተኝ ኑሮ ሲሮጥ ወደኔ መጥቶ ምነው ምን ያስህ ደፋር ነህ በሌላ መክፈቻ አከፍታለሁ ብለህ እንዴህ ስትታገል ይህ ቁልፍ ቢሰበር እንዴት ልትሆን ኖሯል። አንዱ አጥቦ ሲወጣ ሌላው ይገባል አጅግም ተደነቅሁ ሰመንገዴ ባልቸኩልሁ እነርሱን ስመሰከት በኖርሁ ነበረ ባዳራሹም በስተቀኝ በኩል በመዘውር ገብቶ የሚፈስ ውኃ እየሁ የጥሩነቱ ነገር እጅግ ያስደንቃል በስተላይም ወገን ዕሺ ወኃ ያሟወጠማ ቋያሃጎሪም ለይጠማም የማል ጽፈት ተሰቅሎ ይታያል ዮሒ ፀ ወዳጄ ልቤ አኔ ግን መቅጃ አልነበረኝምና በእፍኝ እየዘገንሁ ፉት ፉት አድርጌ ወጣሁ ምዕራፍ ስለ ትልቅ ኃዘን በዚያም ወራት አንድ ቀን ክቀትር በኋላ ባንድ ስፍራ ተቀምጩ አንገቴን ከጉልበቴ ጋራ እያስታገልሁ አዝን ጀመርሁ ወዳጄ ልቤም ወደኔ ቀርቦ ምነው ዛሬ እንዲህ አድርገህ አዝነዛል አለኝ ወደ አዳራሹ ውስጥ በገባሁ ጊዜ የውኃ መቅጃ ባስመያዜ እየተናደድሁ ነው አልሁት ተጠምተዛፃልን አለኝ መጠማትስ አልተጠማሁም ነገር ግን ውኃ መቅጃ በነበረኝ እኔም በብዙ እጠጣ ነበር ደግሞ በመቅጃው ይፔክበት እወጣ ነበር አልሁት አንተን ካለልጠማህ ለማን ብለህ ይህን አሰብህ አለኝ ሞኝ ነህን አሁን ባለልጠማ ሌላ ቀን መጠማቴ ይቀራልን ደግሞስ ስንቱ ጐረቤቶቼ በውኃ ጥም ይተላለቁ ይመስልዛል ከዚያ ውኃ ቀድቼ በነበረ ይህን ጊዜ አንዳንድ ጉንጭ ሙሉ አቀምሳቸው ነበርሁ ዘነጋኸውን ያ ባለጠጋ ዘመዳችን ንጉሥ አስጠርቶት በሔደ ጊዜ ስለ በረሃው ጽናት ውኃ ጥም ይዞት አንድ ጠብታ ውኃ የሚያቀምሰኝ ሰው ባገኘሁ እያለ ሲያሰቅስ ወድቆ አልቀረምን ሉቃስ የዚህ ነገር ትዝ እያለኝ ብዙኀ አዘንሁ አልሁት ወዳጄ ልቤም ይህን ስነግረው ስቅስቅ ብሎ አሰቀሰ አንባውም በጉንጩ ይወርድ ጀመር ወዳጄ ልቤ ሆይ ስለ ምን ታለቅሳስህ አሁን በነገርሁህ ነገር ነውን ወይስ ሌላ ነገር ትዝ ብሉህ ነው አልሁት ሌላ ነገር ትዝ ብሎኝ አይደለም ነገር ግን የባለጠጋውን ነገር ብታነሣ የወደቀበት ስፍራ ትዝ አለኝና ነው አንዴት ያለ ነው አልሁት ስፍራውም እጅግ በረፃና ጐድጓዳ ስለ ሆነ መሬቱ እንደ አሳት ይግላል የፀሐይ መቀት ሲፋጅ ፀሐይ ቦታዋን ለቃ ትታ የወረደች ይመስላል ሽ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ዳግመኛ የምድር አራዊት ሁሉ እባብም ዘንዶም ጊንጥም በየመንገዱ ዳር ተጋድመው የሰውን እግር ይጠብቃለ በዚያ መንገድ የሚሔዱ ለዎች ሁሉ ምላሳቸው በውኃ ጥም ይታሠራል ጥርሳቸውንም ያፋጫሉ ወዲያም ወዲህም ቢመለከቱ አይዚችሁ የሚል አንድ ሰው ስንኳ አያገኙም መዝ ሣቶ በስተላይ ወገን ጥቂቶች መንደሮች ይታያሉ ነገር ግን በዙሪያቸው አልም ያለ ገደል ነው ለውስ ይቅርና አሞራ ስንኳ አያልፍበትም ኢዮብ እግር ክፉ ነውና ምናልባት የኛም መንገድ ባለጠጋው በሔደበት የሆነ እንደ ሆነ እንዴት እንሆናለን ብዬ ያዘንሁበት ምክንያት ይህ ነው አለኝ በእውነትም ይህ ነገር እጅግ የሚያሳዝን ነው ነገር ግን ንጉሥ ባስጠራን ጊዜ የክርስቶስ ሞት የሚባለውን ካርታ ያገኘን እንደ ሆነ ያንን እያየን ደጋ ደጋውን እንሔዳለን ትልቁስ ጭንቀት የክርስቶስ ሞት የሚባለውን ካርታ ያላገኘን አንደ ሆነ ነው ካርታውንም ካላገኘን ወደ አንዱ ፈረፈር ወድቀን አንቀራለን እንጂ ያ ባለጠጋ የሔደበትን በረፃ እንዘልቃለን ብለን አናስብም አልሁት እውነት ነው ግን ለሁሉም ነገር የተቀደሰ ፈቃዱ ይሁንልን አሜን አለኝ ይህንም ተነጋግረን መንገዳችንን ለመሔድ ጀመርን ምዕራፍ ስለ ዕድሜ ተራራ ከዚህም በኋላ ዕድሜ የሚባለውን ተራራ ለማየት ሔድሁ በጥጉ ቆሜ ብመለከት ፄኖክና ኤልያስ ወደ ጫፉ ወጥተው ፊጥ ብለው ተቀምጠው ይታያሉ ዘፍጥ ሮ ነገ ል መቼም አሳብ አይቀርምና ምናልባት እኔም ብወጣ እንደርሳቸው ወደ ጫፉ እደርስ ይሆንን ብዬ ወደ ተራራው እግር ቀረብሁ ነገር ግን በዕድሜ ተራራ እግር የስንት ፍጥረቶች ሬሳ አየሁ ብላችሁ ታምኑኛላችሁን ሰማይና ምድር ወረቀት መላእክት ው ዴዳጄ ፌድ ቼስ ጸሐፊዎች ባሕር ቀለም ሆኖ ተጽፎና ተቆጥሮ ያልቅ አንደ ሆነ ነው እንጂ አንድ ሰው ሊጽፈውና ሊቆጥረው አይችልም የሰው ወገን ሬሳ ባንድ ወገን የእንስሳ ወገን ሬሳ ባንድ ወንን የአራዊት ወገን ሬሳ ባንድ ወገን የአዕዋፍ ወገን ሬሳ ባንድ ወገን የተንቀሳቃሽ ወገን ሬሳ ባንድ ወገን እነዚህ ሁሉ እንደ ቅጠል ረግፈው ይታያሉ ሬሳውንም ሁሉ በየወገኑ ካየሁ በኋላ ቀና ብዬ ወደ ዕድሜ ተራራ ብመለከት እንስሳውም አራዊቱም አዕዋፉም ተንቀሳቃሹም የሰው ወገን ሁሉ ወደ ዕድሜ ተራራ ለመውጣት ይፍጨረጨራሉ ነገር ግን ያንን የዕድሜ ተራራ እስከ ጫፉ የወጣ ፍጥረት የለም አኩሉ ከተራራው መካከል ሲደርሱ ይወድቃሉ እኩሉም ገና ጥቂት ከፍ አንዳሉ ይወድቃሉ አኩሉም ገና እንድ ጊዜ እንደ ተራመዱ ይወድቃሉ እኩሉም ገና እንወጣለን ብለው ሲያስቡ ይወድቃሉ ይህንም አይቼ ብኩ አለቀስሁ ያ ወዳጃ ልቤ ግን እጅግ ቸኩሎ ነበረና እንሒድ እንጂ በዚህ ቆመን እንኖራለን ይህ እሁን የምታየው ሁሉ ላንተ እንግዳ ቢሆንብህ አታድንቅ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲሁ ነው አለኝ ምንስ ቢሆን ክርስቲያን አይደለሁምን። ደግሞም እነዚህ ሰዎች ይህን የዕድሜ ተራራ በገዛ ኃይላቸው ሊወጡ ባልቻሉም ነበር ስለዚህ ያወጣቸው ጌታ ያውቅላቸዋል ራእ ል ግን ሁሉንም በዓይን ለማየት ያብቃን በጆሮም ለመስማት ያብቃን አሁንስ መንገዳችንን እንሒድ ምንም ቢሆን የደበብን ሀገር ሳናይ ወዳገራችን አንመለስም አልሁት ምዕራፍ ስለ ደቡብ መንገድ ከዚህም በኋላ ወደ ደቡብ ሀገር ሔድሁ የደቡብ ሀገር ሰፊ ሜዳ ነበረና በእግሬ ሔጄ ወደ አሰብሁበት አንዳልደርስ አወቅሁ ስለዚህ አንዲት ሰጋር በቅሎ ገዛሁና ስሟን ማንበብ ብቻ ብዬ አወጣሁላት በሁለት ዓይን ልጓም ለጉሜ ወዳዴ ልቤን አፈናጥጩ አንድ ጊዜ ሾጥ ባደርጋት የሚበልጠውን ሜዳ አሳለፍሁት በዚያም ምርማሪ የሚባል ሣር የበቀለበት መስክ አገኘሁ ይህ መስክ የማነው ብዬ ብጠይቅ የባሻ ማስተዋል ነው አሉኝ እርሳቸውስ ደግ ሰው ናቸው አንድ አፍታ ባግጣት የሚቆጡኝ አይመስለኝም ብዬ ልጓሟን አውልቄ ለቀቅኋት ጥቂትም እንደ ነጨች እንደ ገና ለጉሜ አስግር ጀመርሁ ሀ ዳ ና ሌሎች ነገር ግን የደቡብ ሀገር እጅግ ሰፊ ስለ ሆነ ፊት ለፊት አልዘልቀውም ብዬ ባንድ ወገን አቋርጨ ወደ ምሥራቅ ተመለስሁ ወዳጄ ልቤም ምነው ባቋራጭ መንገድ ተመለስህ ይህን ጊዜ እኔ ብዬሀ በሆነ እልክህ ይመጣ ነበረ አለኝ እንኳን እንኳን አንተ እንደ ሰለቸኸኝ አውቄ ወደ ምሥራቅ ሀገር ሔደን ወዳጆቻችንን ሁሉ ተሰነባብቲን ወዳገራችን እንድንመለስ ብዬ ነው እንጂ ለሌላ ነገር ብዬ እይደለም አልሁት ይህስ ከሆነ መልካም ነው አለኝ ምዕራፍ ስለ መሰነባበት ይህንም ከተነጋገርን በኋላ ወደ ምሥራቅ ሀገር ደረስሁ የምሥራቅ ሀገር ግን ለበቅሉ የማይመች ወጣ ገባ መሬት ነበረና በቅሉዬን ማንበብ ብቻን ለሊቀ ካህናት መራቀቅ ሸጥሁላቸው በእግሬም ለመሔድ ጀመርሁ ነገር ግን ዱሮ በቅሎ ተለመደና እግሬ ይደካክም ጀመረ ከዚህም በኋላ እያዘገምሁ ወደ ድኅነት ቤት ደረስሁ ባየኝ ጊዜ እጅግ ደስ አለው ከሰላምታም በኋላ ስለ ልጆቼና ስለ ሚስቴ ጤና ጠየቀኝ ደኅና ናቸው እግዚአብሔር የዕለት ምግብና ያመት ልብስ አልነሣቸውም አልሁት ፅ ጢሞ ቶ ከዚህም በኋላ ወደ ቤት ገባን እርሱም ቶሎ ብሎ እንጀራውን በሌማት ጐመኑን በድስት አድርጐ አቀረበልኝ እኔም ባርከህ ቀድለህ ስጠኝ ብዬ ፈጣሪዬን ለምኝ እስክጠግብ በላሁ ከበላሁም በኋላ ይህን የበላሁትን ለጤና አድርግልኝ በመንግሥተ ሰማያትም መንፈሳዊ ምግብ አእንድትመግበኝ እለምንፃለሁ ብዬ ፈጣሪዬን አመስግጌ ወደ መኝታ ቤቴ ሔድሁ በነጋም ጊዜ ለመሔድ ተነሣሁ ድኅነትም ብዙ መንገድ ሸኝኝ ምክርም መከረኝ ምክሩም እንዲህ ነበር ብልጥግና የሚባል ወምበዴ ተነሥቶ ስውን ሁሉ ሊፈጅ ነው አሁንም አንተ ተጠንቅቀህ ሒድ አለኝ ጢሞ ወዳ ር እንደምን አድርጌ እጠነቀቃለሁ እነሆ አንተ አንደምታየኝ ባዶ እጄን ነኝ ቢመጣብኝስ በምን እመልሰዋለሁ አልሁት እርሱም ወደ ቤቱ እየሮጠ ተመልሶ ይበቃኛል የሚባል አፎቄውን ይዞልኝ መጣ ያንንም በጫንቃዬ ላይ አድርጌ እየተጐማለልሁ ሔድሁ ትሕትናንም ለመሰናበት ሔድሁ ተስነባብተንም ስሔድ ስለ መንገዴ መከረኝ ምክሩም እንዲሀ ነበር በዚህ ወራት ትፅቢት የሚባል አንበሳ ከበረክ መጥቶ መንገደኞችን ሁሉ እየለበረ ሊጥል ጀምሯል አሁን ስትሔድ ስንኳ ብዙ ሬሳ ወድቆ ታገኛለህ አንተ ግን ተጠንቅቀህ ሒድ አለኝ እነሆ አንተ እንደምታየኝ በእጁ መሣሪያ የለኝም እንደምን ልጠንቀቅ አልሁት በዚያ ጊዜ አላዋቂ ነኝ የምትባል ሽጉጡን ከወገቡ አውልቆ ሰጠኝ ያንንም ታጥቄ ያላሳብ መንገዴን ሔድሁ ብላታ ቸርነትንም ለመስናበት ሔድሁ እርሳቸውም ሸኝተውኝ ሲመለሱ ስለ መንገዴ መከሩኝ ምክሩም እንዲህ ነበር ንፍገት የሚባል ኦቦ ሸማኔ እጅግ ከፍቷልና ተጠንቅቀህ ሒድ አሉኝ ያለ መሣሪያ እንዴት አድርጌ ለመጠንቀቅ እችላለሁ አልኋቸው ያለውን መስጠት የሚባል ጋሻቸውን ከክንዳቸው አውልቀው ሰጡኝ እኔም ያንን አንግቤ ያለ ፍርፃት ሔድሁ ምዕራፍ ስለ ወንጌል መሰነባበት ከዚህም በኋላ የምእመን ሚስት የነበረችውን ወንጌልን ለመሰናበት ያለችበትንስ ስፍራ አስጠይቂ ሔድሁ ባየችኝም ጊዜ እያለቀሰች ወደ እኔ መጣች ከለላምታም በኋላ ወደ ቤት አንግባ አለችኝ እኔ ግን ቸኩየ ነበረና እዚሁ ተስነባብተን ልሒድ አልኋት ምነው ወዳጄ ይሀን የሚያህል ዘመን ተለያይተን ኖረን መቼ ። ማቴ ጄ ቶ ወዳጄ ልቤ ል የነዚያ ሰዎች ደም ፍዳው ደረሰብሽ አዩው ዛሬ አንድ ሰው አይገባ በበርሽ ጢሞ ፀ አንድ ዓይን ነሽ አሉ መልክሽ አያምር ይዘሻል መሰለኝ የመስተፋቅር ማቴ ባላገሮች ሁሉ ተማማሉብሸ ወደ አረመኔ ሀገር ወስደው ሊጥሉሽ የሐዋ አኒያስ ባያውቁ ነው ባይጠረጥሩሸ ካረመኔ ወገን ትውልድ እንዳለሽ ማቴ ቿ ወዴት ባገኘሁት አንድጠይቀው ጳውሎስ ነው አሉ ዘርሽን የሚያውቀው ሮሜ ፅጵቶ ትውልድሽ ቢጠፋኝ ምንም ባላውቀው መጀመሪያው ግንዱ ቆርነሌዎስ ነው የሐዋ ጓ ይፔዢሽ ወደ ሰማይ ይፔሽሸ ወደ ሰማይ አንች አጋዳይ ይፔሽ ወደ ሰማይ አንግዲህም ስንዘፍን ሌሊቱ ወለል አለ በነጋም ጊዜ ለመሔድ ነሣሁ ከወንጌልም ጋራ ለመሰነባበት ስንነጋገር ወዳጄ ሆይ ስንቅ ይሃልን አለችኝ ምንም የለኝም አልኋት እንዴት ያለህ ክፉ ሰው ነህ ብዙ ምሥጢር ተጫውተን ሳለን ኣንደ ሌላ ሰው ሁሉ ዝም ብለህ ትሔዳለህን አንግዲህ ወዲህ አንደዚህ ለ የልግም ሥራ አትሥራ አሁንም አንድ አፍታ ቆየኝ አለችኝና ወደ ቤቷ እየሮጠች ሔዳ ስንዴ እንጀራና ጥቂት የወይን ጠጅ ይዛልኝ መጣች በዚህ ሀገር ስንዴ እንጀራ ውድ ነው ባደርህበትም ስፍራ በሥጋ ብትለውጠው ለወጣል አያለች በልብሴ አስቋጥራ ሰደደችኝ ምዕራፍ ስለ ፍቅር መሰነባበት ከዚህም በኋላ ፍቅር ታሞ ወደ ነበረበት ሀገር ሔድሁ አርሱም ትንሸ የሸማ ቁራጭ በራሱ ላይ አስሮ ባደባባይ ኩርምት ብሎ ተቀምጦ ነበር ወዳጄ ልቤና ሌሎችም እኔንም ባየ ጊዜ ባንድ እጁ ምርከዙን ባንድ እጁ ምድሩን ይዞ በግድ ተነሣና ሊቀበለኝ መጣ። ልዴ ሆይ ሰው ሳይኖር ብቻህን ከሴት ጋራ አትነጋገር ባልዋም አለመኖሩን በደጅ ጠይቀህ ከደጅ ተመለስ እንጂ ወደ ቤት አትግባ ሰው ሳይኖር ብቻህን ከሴት ጋራ ንግግር የተነጋገርህ እንደ ሆነ ግን ምንም ሌላ ምስጢር ባይኖራችሁ በመነጋገራችሁ ብቻ መጠርጠር አይቀርም ልጄ ሆይ ለልጆችህ የምታወርሳቸው ብዙ ገንዘብ በሣጥን ውስጥ ከማስቀመጥ አንተ በሕይወተ ሥጋ ሳለህ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እውቀትን እንዲማሩ ገንዘብህን ብትሰጣቸው ይሻሳል ባልዋም ለሞተባት ሴት አባታቸውም ለሞተባቸው ልጆች እጅህ አጭር አይሁን ልጄ ሆይ ሚስትህ ያስቀናችህ እንደ ሆነ ከቤትህ አስወጥተህ ስደዳት እንጂ የርሷን ነፍስ ወይም የሌላ ስው ነፍስ ለማጥፋት አታስብ እርሷን ወይም ሴላውን ሰው ገድለህ ኋላ ከመጠጠት እርሷን አስወጥተህ ሌሳይቱን አግብተህ ብትኖር ይሻልፃል ልጄ ሆይ በጌታህም ቤት ቢሆን በሌሳም ስፍራ ቢሆን ገንዘብ ወይም ሌላ ዕቃ ወድቆ ብታገኝ አታንሣ ብታነሣውም መልሰህ ለጌታህ ወይም ሰዳኛ ስጥ እንጂ ሰውረህ አታስቀር ልጄ ሆይ በፍጹም ልብህ ለማትጠደው ሰው ቤትህንና የቤትህን ዕቃ አታሳይ ልጄ ሆይ ገንዘብህን ለጠጅና ለጠሳ ከማውጣት ለወተትና ለማር አውጣ ለአረቄና ለስቢርቶ ከማውጣት ለጠጅና ለጠሳ አውጣ በጣም ካልቸገረህ በቀር ውኃ ብቻ አትጠጣ ምሳህን እስክትጠግብ ብላ ማታ ግን ምግብህም መጠጥህም በልክ ይሁን ሥጋ ዘወትር አትብላ የአታክልት ምግብ አዘውትር በ በ ቀን የሚያስቀምጥ መድኃኒት ጠጣ ሀኪሞች ያልመረመሩትን ዐዋቆች ነን የሚሉ ሰዎች የማሱትን ሥር የበጠሱትን ቅጠል መድኃኒት ነው ብለህ ለመቅመስ እጀግ አትድፈር ልክና ሜዛን ስለ ሌለው ሰውነት ይጉዳልና ተጠንቀቅ ለልጅ ምክር ለአባት መታሰ ልዴ ሆይ ከብዙ ሰዎች ጋራ ተቀምጠህ በምትበላበት ጊዜ ቶሎ ቶሎ አትጉረስ ቶሎ ቶሎም አትጠጣ በቤትህ ውስጥና በሚስትህ ፊት ግን እስክትጠግብ ብላ አስክትረካም ጠጣ ነገር ግን እስክትጠግብ በልተህ እስክትረካም ጠጥተህ ጥቂት የእንቅልፍ እረፍት ሳታደርግ ሥራ አትጀምር ከቤትህም ወጥተህ አትሒድ የእንቅልፍ እረፍት ለማድረግ ጊዜ የማታገኝ እንደ ሆነ ግን እስክትጠግብ አትብላ አስክትረካም አትጠጣ ልጄ ሆይ በዕድሜ ያረጀ ሽማግሌና ልጅ የሌለው ሰው ካልሆነ በቀር ርስቱን ወይም ቦታውንና ቤቱን ቢያወርስህ አትቀበለው ካልተቺገረና ካተጨነቀ በቀር ርስቱን ለሌሳ ሰው አያወርስምና በተቻለህ ነገር ርዳው እንጂ ርስቱን አትውስድበት ደግሞ በሙግትም ቢሆን በጉልበትም ቢሆን ድኃውን ከርስቱና ከቤቱ አታስወጣው ዕዳም ቢናርበት የሚከፍልበት ቀን ስጠው እንጂ በግድ ይዘህ ርስቱንና ቤቱን አታሽጠው ልዴ ሆይ ንጹሕ አለመሆንህን እግዚአብሔር ያውቃልና በእርሱ ፊት ንጹሕ ነኝ አትበል። ወይም በታጠቅሁችቶ ሰይፍ እንገቱን ብመታው ቆርጨ እጥለው ነበረ ግን ይህን ማድረግ አይገባም ብዬ ወደ እርሱ ቀርቤ እንዲነሣ ቀሰቀስሁት የሚተኛበትም መልካም ሥፍራ አሳየሁት ይህ መልካም ሥራ አይደለምን አለው አባቱም ይህን በሰማ ጊዜ የልጁን አንገት አቅፎ ይዞ ልጄ ሆይ ልጄ ሆይ ከዚህ የሚበልጥ መልካም ሥራ የለምና ይህ አልማዝ የሚገባው ላንተ ነው ብሎ አልማዙን ሰጠው ልጆቼ ሆይ አናንተም ጠላቶቻችሁን ውደዱ ለሚጠልዋችሁም መልካም አድርጉ ጊዜ ተመችቶናል ብላችሁ ጠላቶቻችሁን ለመጉዳት አታስቡ ሁለተኛ ስለ ሁለት ባልንጀሮች ሁለት ባልንጀሮች ባንድነት ሲሔዱ በድንገት ዳልጋ አንበሳ መጣባቸው በዚያ ጊዜ አንዱ ባልንጀራውን ትቶ እየሮጠ ሔዶ ወደ ዛፍ ላይ ወጣና የዛፉን ቅጠል ከለላ ሰጥቶ ተቀመጠ ያ ሌላው ግን የሚያደርገው ነገር ቢቸግረው ዳልጋ አንበሳ የሞተ ሰው አይበላም ሲባል ይሰማ ነበርና እንደ ሞተ ሰው ሆኖ በመንገዱ ላይ ተኛ ዳልጋ አንበሳውም በላዩ ቆሞ እያገላበጠ አፍንጫውንም አፉንም ጆሮውንም ልቡንም ያሸተው ጀመረ እርሱ ግን ፈጸሞ እንደሞተ ሰው ዝም አለ በዚያ ጊዜ በውነት የሞተ ሰው መስሎት ትቶት ሔደ ባልንጀራውም በዛፉ ላይ ሆኖ ቁልቁል ያይ ነበረና ዳልጋ አንበሳው ትቶት እንደ ሔደ አይቶ ከዛፉ ወርዶ ወደ ባልንጀራው ቀርቦ ሱካርና ወተት የልጆች ማሳደጊያ ወንድሜ ሆይ ዳልጋ አንበሳው አፉን በጆሮህ ላይ ተክሎ ባየሁት ጊዜ የበላህ መስሎኝ እጅግ ደንግጩ ነበረ አለው ባልንጀራው መለሰ አይደለም አይደለም ያንጊዜስ አንድ ትልቅ ነገር በጆሮዬ ነገረኝ አለው አንዴት ያለ ነገር ነገረህ አለው በመከራና በጪንቅ ቀን ጥሎ የሚሸሽ ሰው ባልንጀራ አትሁን አለኝ አለው አርሱም ያደረገውን ያውቃልና ሰምቶ ዝም አለ ልጆቼ ሆይ በመከራና በጪንቅ ቀን ባልንጀራችሁን አትጣሉት ባልንጀራችሁም የሚጠቀምበትን ሥራ ሥሩ እንጅ እናንተ ብቻ የምትጠቀሙበትን ሥራ አትሥሩ ካልታመነም ስው ጋር ባልንጀርነት አታድርጉ ሦስተኛ ስለ የብራማ ካህን ብራማ ወይም ብራህማ ህንዶች አንደ አምላከ የሚያመልኩት ነው የብራማ ካህናት ደግሞ እንደዚያው አንደ ሕጋቸው ከኃጢአት ሁሉ የራቁ ንጹሐን ናቸው ይባላሉ ከብራማ ካህናቶች አንዱ ወደ ገበያ ወጥቶ የፍየል ወጠጤ ገዝቶ በጫንቃው ተሸክሞ ወደ ቤቱ ሲመለስ ሦስት አታላዮች አዩት እነርሱም ይህን ካህን አናታለው ብለው ተማከሩና ቀደም ቀደም አያሉ ሒደው በሦስት ስፍራ ላይ አየተቀመጡ ቆዩት። ንጉውሁም እኽ አለው ደግሞ ሌላዬቱ ገብረ ጉንዳን ገባችና አንድ ቅንጣት ስንዴ ይዛ ወጣች ወዳጄ ልቤና ሌሎችም አለው ንጉሥም ተቆጣና ይህንማ ስትነግረኝ ሰንብተህ የለምን ሌላ ተረት እንዳለህ አምጣ አለው ንጉሥ ሆይ ተረትስ ሞልቶኛል ነገር ግን የተጀመረውን ሳልጨርስ ሌላ መጀመር አይገባኝም ጐተራው እጅግ ታላቅ ነው ስንዴውም ብዙ ነው አለው በዚያ ጌዜ ንጉሥ እጀግ ተናደደና ሁለተኛ ይህን ተረት አትንገረኝ እጅግ ሰለቸኝ ልጄንም ሰጥቼፃለሁ መንግሥቴንም አውርሼሃዛለሁ አለው ሰውዬውም የንጉሁን ልጅ አግብቶ መንግሥቱን ወርሶ በዙፋኑ ተቀመብጠ ልጆቼ ሆይ የሚረባውን ነገር ትታችሁ የማይረባውን ነገር አትፈልጉ ቀልድና ጨዋታም አትውደዱ ወደ ጨዎታ ይሦዖ ዕመጨድ ወድ ልሳቀሖ ይፉ መጨድ ይይገ የተባለውን ነገር አስቡ ሰባተኛ ስስ አንድ ጫማ ሰፊ አንድ ጫማ ለፊ ከጧት እስከ ማታ በእጁ ጫማ ሲሰፋ ባፉ ሲዘፍን ይውል ነበረ በጐረቤቱም አንድ ባለጠጋ ነበረና አንድ ቀን ወደ አርሱ መጥቶ ወዳጀ ሆይ እንዲህ ሌት ቀን ስትደክም ባመት ምን ያ ታተርፋለህ አለው ስማ ሰፊውም እየሳቀ መለሰ ጌታ ሆይ እኔ ያመት ትርፍን አላስብም ነገር ግን አሳቤ ሁሉ አጄ ወደ አፌ የሚያቀርበው የዕለት ምግብ እንዳልቸገር ብቻ ነው አለው ባንድ ቀን ምን ያህል ታተርፋለህ አለው ጌታዬ ሆይ አንድ ቀን ብዙ አንድ ቀን ጥቁት እሠራለሁ ትርፉ በምን ይታወቃል አለው ባለጠጋውም እንግዲህ ወዲህ እኔ ያለችግር አኖርፃለሁና ከኔ ዘንድ መቶ ምዝምዝ ወርቅ ውሰድና በጥንቃቄ ጠብቀህ አኑር በትገረህም ጊዜ የሚበቃህን ያህል እንዲ በከንቱ አታባክን ብሎ ሰጠው ሱካርና ወተት የልጆች ማሳደጊያ እርሱም ይህን ያህል ገንዘብ ባይነ ስንኳ አይቶ አያውቅም ነበረና ደስ እያለው ተቀብሎ ወደ ቤት ሔደ ነገር ግን ይጠፋብኛል ብሉ ሲጨነቅ ሌሊቱን ሁሉ ካይኑ እንቅልፍ ሸሸ በሌሊትም የለው ድምጽ በሰማ ጊዜ ገንዘቡን የሚቀማ ወምበዴ የመጣ ይመስለዋል ነፋስም ቤቱን ባነቃነቀው ጊዜ ገንዘቡን የሚሰርቅ ሌባ የመጣ እየመሰለው ይጨነቅ ጀመረ እንዲህም እየሆነ ብዙ ቀን ተቀመጠ ነገር ግን ልቡ የዚህን አሳብ የማይችለው ሆነ ከእለታት አንድ ቀን እንዲህ ሊጨነቅ አደረና በማግሥቱ በማለዳ ተነሥቶ ወደዚያ ባለጠጋ ቤት አየሮጠ ሔዶ ለኔስ የቀድሞ ኑሮዬ እጅግ ይሻለኛል። ንጉሥም በማግሥቱ አስፈርደው ገደሉት ልጆቼ ሆይ ንጉሥ አምቢተኞችን ሁሉ ለመቅጣት ከእግዚአብሔር ሰይፍ ተቀብሏልና የንጉሥን ትአዛዝ ጠብቁ አሥራ ዝጠነኛ ስለ አንድ ሸማግሌ ሰውና ስለ አንዲት ሴት ልጅ በመስኮብ ሀገር ሦስት ሴቶች ልጆች ያሉት አንድ ሽማግሌ ነበረ ከሦለቱ አንዲቱ በመልኳና በጥበብዋ አጅግ ስመ ጥሩ ናት አንድ ቀን ወደ ገበያ ሲወጣ ልጆቼ ሆይ ከገበያ ምን ገዝቼላችሁ ልምጣ አላቸው ሁለቱ ልጆቹ ጌጥ ገዝተህልን ና አሉት አንዲቱ ግን እኔ ምንም አልፈልግም ነገር ግን የምመክርህን ምክር ስማኝ አለችው ለጊዜው ነገሩ ከበደው ነገር ግን ልጁ አጅግ ብልህ መሆኗን ያውቃልና ይሁን ንገሪኝ አላት ወይንማውን በሬ ወደ ገበያ አውጥተህ ስትሸጥ ዋጋ ንገር ያሉህ እንደ ሆነ የንጉሥን ግራ ዓይኑን አምጡና በሬውን ውሰዱ በላቸው አለችው እርሉም በገበያ ተቀመጠና የበሬውን ዋጋ ንገር ሲሉት ልጁ እንደ መከረችው የንጉሥን ግራ ዓይኑን አምጡና ውሰዱት ይል ጀመረ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ይህን ወሬ ንጉሠ ለምቶ እጁን ይዛችሁ አምጡልኝ ብሎ አዘዘ ሽማግሌውም በቀረበ ጊዜ ንጉሥ ሆይ እንደዚህ ያደረገችኝ ልጄ ናትና ማረኝ እያለ ይለምን ጀመረ ንጉጮም ይህን በሰማ ጊዜ ሔደህ ልጅህን አምጣትና አምርፃለሁ አለው ሽማግሌውም እያዘነና እየተንቀጠቀጠ ሔዶ ልጁን ይዞ ወደ ንጉሠ ቀረበ ንጉጮም ልጅቱን ባያት ጊዜ ለበሬው ዋጋ የንጉሥን ግራ ዓይን አምጡና ውሰዱ በላቸው ብለሽ ለአባትሽ የመከርሽው ስለምን ነው ዕኦላት ንጉሥ ሆይ አልቀጣሽም ብለህ ማልልኝና አነግርፃለሁ አለችው አልቀጣሽም ብሎ ማለላት ንጉሥ ሆይ ድኃና ጌታ ተጣልተው ወዳንተ የመጡ እንደ ሆነ በቀኝ የቆመውን ጌታውን ብቻ ታያለህ አንጂ በግራ የቆመውን ድኃውን አታይም ስለዚህ መቸም ግራ ዓይንህ ሥራ ካልያዘልህ ብዬ ነው አለችው ንጉሥም የልጅቱን ንግግር ሰምቶ እጀግ አደነቀ ወዲያውም ወንድ ልጁን ጠርቶ ልጄ ሆይ በመልክና በአውቀት ከርሷ የምትሻል ሌት የለችምና እርሷን አግብተህ መንግሥቴን ይዘህ ኑር አለው። ነገር ግን በድንገት ጽዮን ሞገሳን በማግኘቱና አዲስ አሳብ ስለ ተነሳበት ጊዜውን አሣልፎ ወጣ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ብርሃኔም ጽዮን ሞገሳን ከማየቱ አስቀድሞ ዘመዶቹን ለማየት ወደ እቲሳ የሚወርደው ባመት አንድ ጌዜ ብቻ ነበር ከዚያ ወዲህ ግን ዘመዶቼ ናፍቀውኛል እያለ በሁለት በሁለት ወር ይመላለስ ጀመር አእቲሳም ደርሶ በማናቸውም ምክንያት ቢሆን ወደ አቶ ክብረት ቤት ሳይፄድና ከጽዮን ሞገሳ ጋራ ሳይነጋገር አይመለስም ነበር ጽዮን ሞገሳ ግን በብርፃኔዩልብ የጋብቻ አሳብ መኖሩን ምንም አታውቅም ነበርና በገርነት ልብዋን ከፍታ ታነጋግረው ነበር እንጂ እንደ ልጅ አገረድ አንገቷን ደፍታ ፊቷን አዙራ አታነጋግረውም ነበር ምዕራፍ ብርሃኔ ጽዮን ሞገሳን ለማሜግባት ቁርጥ አሳብ ስለ ማድረጉ ብርሃኔም የጽዮን ሞገሳ አድሜዋ ዓመት መሆኑን ጠይቆ ባወቀ ጊዜ ወደ እናቱ ዘመዶች ሔዶ ጽዮን ሞገሳን ለማግባት ማሰቡን ገልጦ ነገራቸው ዘመዶቹም ባንድ ወገን የአጸኅታቸው ልጅ ለዚህ ማዕረግ ስለ መድረሱ በሁለተኛውም ወገን ከሌላ ሀገር ሳይሆን ከዚያው ከእናቱ ህገር ሚስት ለማግባት ስለ ማሰቡ እጅግ ደስ አላቸውና ነገ ጧት ወደ አቶ ክብረት ቤት ሔደን ልጆህን ጽዮን ሞገሳን ለእኅታችን ልጅ ለብርሃኔ ስጥልን ብለን እንለምንልፃለን አሉት ብርፃኔም የዘመኑን እውቀት የተማረ ብልህ ነበርና ይህስ ከቶ ምንም ቢሆን አይሆንም ነገር ግን እኔው ራሴ ልጅቱን ለብቻዋ ጠርቼ እነግራታለሁና የምትመልሰውን ነገር ከስማሁ በኋላ የሚያስፈልገውን ነገር ታደርጉልኛላችሁ አላቸው ከዚህም በኋላ የጽዮን ሞገሳ አባት አቶ ክብረት በእቲሳ ብዙ አታክልት ነበረውና ወደ ማታ በአታክልት ውስጥ ገብታ ሎሚና ትርንጎ ስትለቅም ብርፃኔ በድንገት ደረሰና እርስዋን ለማግባት ማሰቡን ገልጦ ነገራት የልብ አሳብ የብርሃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ አርስዋም ይህን ነገር በለማች ጊዜ ደነገጠችና እረ በስመ አብ በል አሁን የእኔ እድሜ ገና ዓመት ነው ዳሩ ግን ዓመት ሳይሆነኝና አካለ መጠን ሳላደርስ ምንም ቢሆን ባል አላገባም አለችው ብርሃኔ እስከ ዓመት ባል ሳታገቢ መቆየትሽ ስለ ብሎ ጠየቃት ገ ጽዮን ሞገሳ ዓመት ሳይሆነኝና አካለ መጠን ሳላደርስ ሥጋዬ ሳይሞላና አጥንቴ ሳይጠነክር ባል አግብቼ የፀነስሁ አንደ ሆነ ሕፃኑ ብርቱ አይሆንም እኔም በደህና ለመገላገል አልችልም ምናልባትም እስከ ሞት ያደርሰኝ ይሆናል አለችው። አሁንም ፈቃድሽ ካልሆነ ምን አደርጋለሁ ወደ ፊት እግዚአብሔር የሚያደርገውን እጠብቃለሁ በደህና ሰንብቺ ብሎ ከአታክልቱ ውሸዥ ወጥቶ ሔደ ነገር ግን የጽዮን ሞገሳን ጋብቻ የፈሰገው በፍጹም ልቡ ስስ ሆነ ተቆጥቶ ለመሔድ አልቻለምና ጥቂት መንገድ ከሄደ በኋላ ተመልሶ መጣ ጽዮን ሞገሳም ከዓይንዊ እስቲርቅ ድረስ ቀማ ትመሰከተው ነበርና ተመልሶ ሲመጣ ባየችው ጊዜ በፍጥነት ቀርባ ተመልሶ የመጣበትን ምክንያት ጠየቀችው ብርሃኔም ጋብቻው እንዳይቀርበት ስለ ተጨነቀ ምናልባት አንድ ሌላ ምክንያት ለመፈለግ መሆኑን ነገራት ጽዮን ሞገሳም እኔ አንተን ለማግባት ፈቃዴ መሆኑ እርግጥ ነው ነገር ግን አካለ መጠን ሳላደርስ ምንም ቢሆን ባል አላገባምና እኔን ለማግባት ቁርጥ አሳብ አድርገህ እንደ ሆነ እስከ ሁለት ዓመት ታግሠህ ቆይ አለችው ብርፃኔም መታገሠንማ ከዚህስ የበለጠ ዘመን ብታገሥ ምን ጉዳት አለብኝ ነገር ግን የሸመገሉ አባትና እናት ጠባቂ የሌላቸው ቤተ ስዎች አሉኝና ጋብቻው በቶሎ እንዲሆን ማሰቤ ስለዚህ ነበር ካልሆነም ምን አደርጋለሁ እኔኑ እግዚአብሔር ባያድለኝ ይሆናል አሁንም በደህና ሰንብች ብሎ መንገዱን ጀመረ ነገር ግን አንድ ምዕራፍ ያህል ከሔደ በኋላ እንደ ገና ተመልሶ መጣ ጽዮን ሞገሳም ሦስተኛ ተመልሶ ሲመጣ ባየችው ጊዜ የፊተኛውን አሳቡን ሰውጦ አካለ መጠን አስትታደርሺ አታገሣለሁ ለማለት የተመለስ መስሏት በደስታ ልትቀበለው ሔደችና የተመለሰበትን ምክንያት ጠየቀችው እርሱም አንች አካለ መጠን ለመድረስ የቀረኝ ሁለት ዓመት ብቻ ነው ብለሽኛልና እንደዚህ ከሆነ እስከ ሁለት ዓመት በግብረ ሥጋ የልብ አሳብ የብርሃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ ወ አንዳልገናኝሽ ልማል ልገዘትና የጋብቻውን ሥርዓት እንድንፈጽም ፈቃድሽ እንዲሆን ልጠይቅሽ ተመልሼ መጣሁ አላት ጽዮን ሞገሳም ይህን የመለለ የማይገባና እውነት ያልሆነ ነገር በመስማቷ እጅግ አዘነች ወዲያውም ፊቷን ወደ እርሱ አቅንታ ወዳጄ ሆይ እሰከ ዛሬ ድረስ ባለተያየትህና በንግግርህም ሁሉ አዋቂና አስተዋይ ትመስለኝ ነበር ለካ እንደዚህ ሞኝና ዝንጉ ኖረፃልን ብርሃኔና ጽዮን ሞገሳ በልብ አሳብ እንደ ተስማሙና ጋብቻቸውን እንደ ፈቀዱ። ነገር ግን ጥቂት የሚያሳዝነኝ ወደ ደብረ ሊባኖስ ወርደሽ በሴቶች ገዳም የተቀመጥሽ እንደ ሆነ ወደዚያ ስፍራ ወንድ አይገባምና አስከ ሁለት ዓመት ዓይን ላይን ሳንተያይ መቆየታችን ነው አላት ጽዮን ሞገሳም መለስች ወዳጄ ሆይ ይህን የመሰስ አሳብ ማሰብህ እጅግ ያስደንቃል እኔስ ሁለት ዓመት ሙሉ አባትና እናቴን ዘመዶቼንስ ሁሉ ሳላይ እንደምን የምቆይ መሰለህ ጥንቱንም ይህን አሳብ ባስብሁ ጊዜ ባመት ሦስት ጊዜ ለእንቁጣጣሽ ለልደትና ስፋሲካ ወደ ሀገሬ አየመጣሁ አባትና እናቴን ለማየት ቁርጥ አድርጌ ነውና አንተ እነዚህን ሦስቱን ጊዜዎች እየጠበቅህ ወደ እቲሳ ብትመጣ ልታየኝ ትችላለህ አለችው ብርፃኔም ይህን በመስማቱ የበለጠ ደስታ አደረገና ባመት ሦስት ጊዜ ካየሁሽ ሌላ ምን እፈልጋለሁ ነገር ግን ስሁሉም ነገር የልብ አሳብ የብርፃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን እንግዲህ እኔም ወደ ሀገሬ መውጣቴ ነውና በደህና ያገናኘን ብሎ ተሰነባብተው ተለያዩ ምዕራፍ ጽዮን ሞገሳ ለትምሕርት ወደ ደብረ ሊባኖስ ስለ መውረድዋ ጽዮን ሞገሳ ከብርፃኔ ጋራ ከተሰነባበተች በኋላ በአባትዋና በእናትዋ ፊት ቆማ እንደዚህ እያለች ትናገር ጀመረች አስካሁን ድረስ የተማርሁት ትምሕርት ሥጋዬን የምረዳበት ባልም ሳገባ ባሴን ደስ የማሰኝበት ሥጋዊ ትምሕርት ነው እንጂ ነፍሴ የምትድንበትን እግዚአብሔርን እገልግዬ ደስ የማሰኝበትን መንግሥተ ስማያትን የምወርስበትን መንፈሳዊ ትምሕርት አልተማርሁምና ወደ ደብረ ሊባኖስ ወርጄ በሴቶች ገዳም ተቀምጩ መንፈሳዊ ትምሕርት እንድማር ትፈቅዱልኝ ዘንድ እለምናሰሁ አለቻቸው አባትና እናትዋም ይህን የመሰለ ትልቅ ነገር ስትናገር በሰሙ ጊዜ ደነገጡ። ወደ ቤቱም ከተመለሰ በኋላ የማስታወሻውን መጽሐፍ ከውጥቶ ቢመለከት በገዳም የምቀመጠው ሁሰት ዓመት ብቻ ነው ብላ አስቀድሞ በቃልዋ እንደ ነገረችው ዘመኑ ልክ ሆኖ ስለ አገኘው በንግግርዋ የምትጸና ቃልዋንም የምታከብር መሆኗን ተረዳውና እጅግ ደስ አለው ነገር ግን የጋብቻውን ነገር ከጽዮን ሞገሳ በቀር አባትና እናትዋ ወይም ሌላ ዘመድ ባዕድ አያውቁም ነበርና ነገሩን ለአባትና ለእናትዋ ማስታወቅ የሚገባ ስለ ሆነበት ከተጉለት ወደ እቲሳ ወረደ የወረደበትም ወር መስከረም ነበርና እንደ አጋጣሚ ለመስቀል በዓል አንድ ቀን ሲቀረው ደረሰ በማግሥቱም ደመራ ተደምሮ ካህናቱም ባላገሩም ሴቱም ሕፃናቱም ተሰብስበው ካህናቱ በመስቀሉ አብርፃ ኢዮሐ ኢዮሐ ሲሉ ወንድ ወንዱም ኢዮሐ አበባዬ አበባሽ ሰአበባ እልል ብዬ ልግባ ሲሉ ልጅ አገረዶችም በራሳቸው ላይ የመስቀል አበባ እያሠሩ በደመራው ቀኝና ግራ ቆመው ነበርና ብርዛኔ ወዲያና ወዲህ እየተዘዋወረ የበዓሉን ማማር ሲመለከት በድንገት ጽዮን ሞገሳን አይቶ በቁመትዋ ማደግ በመልኳ ውበት እጅግ ደስ አለው እርስዋ ግን በዚህ ወር ሕርፃኔ ወደ እቲሳ ይመጣል ብላ ምንም አልጠረጠረችም ነበር የደመራውም በዓል ተጨርሶ ወንዶችም ሴቶችም በየቤታቸው ሲመለሱ ብርፃኔ በመንገዱ ዳር ቆሞ ጽዮን ሞገሳ ስታልፍ ለማየት ሲጠብቅ ነበርና ባኳያው ስትደርስ በፍጥነት ቀርቦ ሰላምታ ሰጣትተ እርስዋም ሁለት ዓመት ሙሉ ምንም መልኩን ባይንዋ ሳታየው ብትቆይ በልብዋ ውስጥ እንደ ሥዕል ተሥሉ ይናር ነበርና ብርፃኔ መሆኑን በቶሎ አወቀችው ከቢህም በኋላ ባንድነት ወደ አባትዋ ቤት ሔደው በደስታ ሲጫወቱ አመሹ አቶ ክብረት ሁለት ዓመት ሙሉ ዓይንህን አላየነውም ነበር ለካ ቀድሞ እየመጣህ የምትጠይቀን ለጽዮን ሞገሳ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ስትል ኖሯልን እያለ ነገሩን ሳያዞር በገርነት ይናገር ጀመር በጣም በመሸ ጊዜ ግን ለመኝታው ወደ ዘመዶቹ ቤት ሔደ በማግሥቱም የመንደሩ ሰው ሁሉ ወንዱም ሴቱም የደመራ አመድ ለመርገጥ የአሽክት ሐረግ እየያዙ ይሔዳሉና ብርፃኔ ለዚሁ ብሎ በመንገድ ዳር ቆሞ አሽክት ሲነቃቅል ጽዮን ሞገሳ እንደ አጋጣሚ ቻዋ መጣኾችኾ ግ ዚም ጀምሮ አስከ ደመራው ስፍራ ብቻቸውን ስለ ሆኑ የጋብቻ ምስጢራቸውን ገልጠው ለመነጋገር ተመቻቸውና እንግዱህ ወዲህ አባትና እናቴ ይስሙትና ነገር ቢጨረስ መልካም ነው ብላ እርሉ የፈራውን እርስዋ ደፍራ ነገረችው ከዚህም በኋላ ባንድነት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው ቅዳሴ ስምተው ሲመለሉ እንደ ገና ወደ አባትዋ ቤት ወስዳ ምሳውን ጋበዘችው በዚህም ቀን ወደ ማታ ወደ እቲሳ ገዳም መምሕር ወደ አባ ተስፋ ሥላሴ ሔዶ አባቴ ሆይ ያቶ ክብረትን ልጅ ጽዮን ሞገሳን በቃል ኪዳን ለማግባት አስቤ ከእርስዋ ጋራ መነጋገርና መላላክ ከጀመርሁ ሁለት ዓመት ሆነ አሁንም ከእርስዋ ጋራ ተነጋግሬ ጨርሻለሁና ለአባትና ለእናትዋ ነግረው አንዲያስፈቅዱልኝ እለምንዎታለሁ ይህንም ማለቴ ለልማዱ ብዬ ነው አንጂ ባይፈቅዱ እንኳ በእኔና በእርስዋ መካከል ነገሩ የተቆረጠ ሆኗልና ለማስናክልና ለማስቀረት የማይችሉ መሆናቸውን ገልጠው ይንገርዋቸው ብሎ ጉልበታቸውን እየሳመ ናገ ። ወዲያውም የሠርጉ ቀን ከፋሲካ በኋላ በሚያዝያ ቀን አንዲሆን ተነጋግረው ተስማሙና ብርዛኔ በጥቅምት ቀን ከእቲሳ ተነስቶ ወደ ተጉለት ወጣ ስለ ደስታውም ብዛት የመንገዱ ድካም አልተሰማውም ነበር ምዕራፍ ስለ ብርሃኔና ጽዮን ሞገሳ የቃል ኪዳን ጋብቻ ብርፃኔ የጋብቻውን ነገር ለመጨረስ ወደ እቲሳ ወርዶ ነገሩን ጨርሶ ከተመለሰ በኋላ ዘመድ አዝማዱን ሰብስቦ ከጽዮን ሞገሳ ጋራ መነጋገሩን ሳይገልጥ ሚስት ለማግባት ቁርጥ አሳብ ማድረጉን ብቻ ነገራቸው ነገሩን በሰሙ ጊዜ እንደዚህ ከሆነ የእገሴን ልጅ ቢያገባ ይሻላል አያሉ ሁሉም በልባቸውማማረጥ ጀመሩ ከመካከላቸው አንዱ አጎቱ ተነሥቶ አንኮበር ወጥቼ ሳለሁ ያቶ ገብረ ሥላሴን ልጅ አጅግ የተዋበች ቆንጆ አይቻለሁና እርስዋን ያግባ ብሎ ተናገረ ደግሞ አንዱ ዘመዱ ተነስቶ ወደ ሰላ ድንጋይ በወጣሁ ጊዜ ባንድ ከበርቴ ቤት አድሬ ማለፊያ የደረሰች ልጃአገረድ አይቻለሁና እርስዋን ብናጋባው ይሻላል ብሎ ተናገረ ሦስተኛው ዝመዱ ግን ብርፃኔ የሚያገባትን ሴት አስቀድሞ ሳያስብና ሳይዘጋጅ የነገረን አይመስልምና ሚስት ለማግባት ፈቃድህ ከሆነ የማንን ልጅ እናጋባህ ብለን ብንጠይቀው ይሻላል ብሎ ተናገረ በዚህም ነገር ሁሉም ከተስማሙ በኋላ ብርፃኔን ጠርተው ሚስት ለማግባት ቁርጥ አሳብ ማድረግህን ብታስታውቀን እጅግ ደስ የልብ አሳብ የብርፃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ አለን ነገር ግን አሳብህ እንደምን ነው እኛ ፈልገን ብናጋባህ ትወዳለህን ወይስ አንተው ራስህ ፈልገህ ትነግረናለህ ብለው ጠየቁት ብርሃኔም ይህም ጥያቄ በሰማ ጊዜ እኔ ዛሬ እናንተን ሰብስቤ ማስታወቄ ያለ ፈቃዳችን ሚስት አገባ ብላችሁ እንዳትቀየሙብኝ ነው አንጂ የማገባትንስ ሚስት ከሁለት ዓመት አስቀድሞ መርጩ ነገሩን ጨርሻለሁ ባለቤቱ ያልወደደውን ምግብ በግድ ቢያበሉት ጤና አንዳይሆነው እንደዚሁ ራሱ ባለቤቱ ያልመረጣትን ሚስት ዘመዶቹ በግድ ቢያጋቡት ፍቅራቸው የጸና አይሆንም ስለዚህ ለእኔ የምትስማማኝን ሚስት ራሴ መርጫለሁና እናንተን በዚህ ሀገር አላደከማችሁም አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ አባትና አናቱ ለብቻው አድርገው ለማግባት ያሰባት ሴት ሀገርዋ ወዴት አባትዋም ማን እንደ ሆነ ጠየቁት። ምናልባትም በማናቸውም በሽታ የታመምሽ አንደ ሆነ ለልጁ የላም ወይም የፍየል ወተት እያፈሉ ሲበርድ ይስጡት እንጂ አንች እንዳታጠቢው ተጠንቀቂ የላም ወይም የፍየል ወተት ባይገኝ እንኳን እንደ ገንፎ ወይም እንደ ሙቅ የመሰለ የእህል ምግብ ወይም የሥጋ መረቅ መስጠት ነው በልብሱ ላይ ሽንቱን የሸናበት አንደ ሆነ ወይም ሌላ እድፍ ነገር ያየሽበት እንደ ሆነ ልብሱን ለውጠሽ ሌላ የታጠበ ልብስ አልብሽው ለመቸውም ቢሆን ቢገኝ አራት ባይገኝም ሁለት ጥብቆ እያሰፋሽ አያለዋወጥሽ ማልበስ ነው በሳምንት በሳምንት አንዳንድ ማንካ የጉሎ ዘይት ወይም ሌላ የሚያስቀምጥ መድኃኒት ማጠጣት ነው መድኃኒቱ ግን ሀኪም ያልፈቀደውና ያልተፈተነ እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል ደግሞም ባለቀስ ቁጥር ጡት አትስጭው ነገር ግን ጧት አንድ ጊዜ ደግሞ በሦስት ሰዓት አንድ ጊዜ በስድስት ሰዓት አንድ ጊዜ በዘጠኝ ሰዓት አንድ ጊዜ ፀሐይ ሲጠልቅ አንድ ጊዜ አጥቢው ሌሊትም እንደዚሁ ሁለት ጊዜ ብቻ አጥቢው ከአታክልትም ሙዝ በህረ ሎሚ ድንች ይህን የመሰለ ሁሉ ለልጅ መልካም ነው ለማናቸውም ቢሆን በወር በወሩ አንችን ልጅሽንም ሀኪም ቢመረምራችሁ መልካም ነው የልብ አሳብ የብርሃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ ድሄሂ ይህንም የመከርሁሽን ሁሉ ብታደርጊ ልጅሽ በጤና ያድግልሻል አንችም ያለኀዘን ትኖሪያለሽ እያለ እጅግ ደስ በሜያሰኝና ወደ ልብ የሚገባ ምክር መከራት ጽዮን ሞገሳም ከወንበር ላይ ተነሥታ ቆማ ሀኪሙ ስለ መከራት ምክር ሁሉ አመስግና ወደ ቡልጋ ሔደች ቡልጋም በደረሰች ጌዜ የሀኪሙን ነገር ለዘመዶችዋ ነገረቻቸው እነርሱም ሕፃነ በስምንት ቀን እንደ ዳነ መልኩም እንደ ተለወጠና እንዳማረበት አይተው ሀኪም ማለት እንደ እግዚአብሔር ነውን እያሉ አደነቁ ጽዮን ሞገሳም ባልዋ ብርዛኔ ለቅበላ ወደ ተጉለት እንድትመለስ አስታውቋት ነበርና ቅበላ መድረሱን አይታ ከዘመዶችዋ ተሰናብታ ወደ ተጉለት ወጣች ልጀዋም በአንቀልባ የታዘለ እንደ ሆነ እንደ ፊተኛው እንዳይታመም ስለ ፈራች ወደ አዲስ አበባ በወሰደችበት ቅርጫት ውስጥ ክግብታ ወንዶች አሽከሮች እየተፈራረቁ ተሸክመውት ወጡ ብርሃኔም ሚስቱ ጽዮን ሞገሳ የባልዋን ትአዛዝ ፈጻሜ መሆኗን ያውቅ ነበርና ለቅበላ ስምንት ቀን ሲቀረው እስከ ደብረ ብርሃን ወጥቶ ተቀበሳት የተወደደች ሚስቱንና ልጁንም በማየቱ እጅግ ደስ አለው ወደቤታቸው በደረሱ ጊዜ ዘመድ አዝማዱ ሁሉ ተሰብስበው አንኳን ደህና ገባሸ እያሉ ሰላምታ አቀረቡላት ሁለት ቀንም ካረፈች በኋላ በየጎረቤትዋ እየሔደች የባሏን ዘመዶች ሽማግሎችንና ባልቴቶችን ስትጠይቅ ሰነበተች ከዚህም በኋላ ብርሃኔና ጽዮን ሞገሳ በደስታ ነዋሪዎች ስለ ሆነ በኩረ ጽዮንን በወለደች በሦስተኛው ዓመት ሴት ልጅ ወለደችና የክርስትና ስምዋ ወለተ ጽዮን ተባለ። እንግዴህ በእኔ ወገን የምመክርዎ በጉባዔው ፊት ሲቀርቡ አጥፍቻለሁ ማረኝ አዲስ ዓለም የቅኖችና የደግ አድራጊዎች መኖሪያ ብለው በዓወቀ እግር እንዲወድቁና ነገሩ እንዲቀር ነው ብሰው ከልብ የሆነ እውነተኛ ምክር መክርዋቸው መምሬ ለባጋዲስም መካሪና ዘመድ አያሳጣዎ ብለው መርቀው ተሰናበቱ ከዚያም ሲወጡ በየተራ አየሔዱ የሜካኤልን የጊዮርጊስን የመድኃኔ ዓለምን አለቆች ቢጠይቋቸው ከማርያም አለቃ ጋራ የተማከሩ ይመስል ቃላቸው አንድ ስለ ሆነ መምሬ ሰባጋዲስ ሳይጠራጠሩ ምከራቸውን ተቀበሉ ባራተኛውም ቀን ከወዳጃቸው ከመምሬ አሰጋኸኝ ጋራ ተሰነባብተው ወደ ተጉለት ተመለሱ ምዕራፍ ስለ ሁለተኛው ጉባዔ ነገር በዓወቀና በመምሬ ሰባጋዲስ መካከል በተነሣው በተዝካር ነገር ሊቃውንቱና መምሕራነ ጉባዔ አድርገው የተዝካር ነገር ከጨረሉ በኋላ ዓቃቤ ሰዓት ዘወልደ ማርያም ሌላውንም በስሕተት የገባውን ለመሙላት አሳባቸውን ገልጠው ቢናገሩ በየቤታቸው ስናስብበት ከርመን ሁለተኛውን ጉባዔ በሚመጣው ዓመት በኅዳር ቀን እናደርጋሰን ተባብለው ተለያይተው ነበርና አሁን ቀጠሮ ስለ ደረሰ ቀደም እያሉ በኅዳር ፅ ቀን እንጦጦ ራጉኤል ፉ ይዳ ደረ ኃፀኃ ገቡ መልአክ ፀሐይ ክንፉ ብቻ የልብ በሽታ ነበረባቸውና ጾመ ፍልሰታን በጥሬና በውኃ እጾማለሁ ብሰው የልባቸው በሽታ ተቀስቅሶባቸው ጳጉሜ ሲገባ አረፉና በደብረ ሊባኖስ ተቀበሩ እጨጌውም ሊቃውንቱና መምሕራኑ በዚያው በቀጠሮው ቀን መምጣታቸውን በሰሙ ጊዜ የደብረ ሲባኖስን ገዳም መጋቢና ፀባቲውን አስከትለው በኀዳር ሄ እንጦጦ ራጉኤል ደረሉ በማግሥቱም በማሰዳ መጥተው በጉባዔው በተቀመጡ ጊዜ ሊቃውንቱና መምሕራኑ እየመጡ እንደ ማዕረጋቸው ተራ በየመንበራቸው ተቀመጡ ወዳጄ ልቤና ሌሎችም ከዚህም በኋላ ፓትርያርክ ጐሹ ተነሥተው ከእጨጌው ፈቃድ ከተቀበሉ በኋላ ጉባዔ የሆነበትን ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ነገር ይናገሩ ጀመሩ አባቶቼና ወንድሞቼ ሆይ አስቀድሞ የእግዚአብሔር ስሙ የተባረከ ይሁንና ከዚህ ቀንና ሰዓት ስለ አደረሰን ባንድነትም ስለ ሰበሰበን እናመሰግነዋለን አሁን ዛሬ በዚህ ጥዋካዔ የተሰበሰብንበት ምክንያቱ ከዚህ ቀድሞ በዓወቀና በመምሬ ሰባጋዲስ መካከል የተነሣውን የተዝካርን ነገር ተነጋግረን ስንጨርስ ዓቃቤ ሰዓት ዘወልደ ማርያም ተነሥተው በስሕተት ገብቶ ልማድ ሆኖ የኖረውን ትንንሹን የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት እንድናሻሽል ቢነግሩን በየቤታችን ስናስብበት ከርመን ክረምት ውጭ በኅዳር ቀን ተገናኝተን አንድንጨርስ ተስማምተን ተለያይተን ነበርን የዛሬው ጉባዔ ምክንያቱ ይህ ነው እኔ በበኩሌ የተማሩትን ወዳጆቼን ሰብስቤ ባማክራቸው ሁሉም የዓቃቤ ሰዓት ዘወልደ ማርያም አሳብ መልካም ነው ብለውኛልና ሌላ የምጨምርበት ነገር የለኝም ስለዚህ አናንተ በየተራ እየተነሣችሁ ለዚሁ ነገር አሳባችሁን አስታውቁና በበዛው ወገን ነገሩ ይቆረጣል አሏቸው ከዚህም በኋላ መልአከ ገነት አንግዳ ተነሥተው እንደ እኔ አሳብ የሆነ እንደ ሆነ እስካሁን በልማድ ስንሠራው በኖርነው ባለፈው ሥራችን እግዚአብሔር ይቅር ይበለን እንጂ ለወደ ፊቱ ዓቃቤ ሰዓት ዘወልደ ማርያም እንደ ተናገሩት ቢሆን መልካም ነው አሉ።