Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • ወደ ፒዲኤፍ ቀይር
  • የንባብ ዝርዝር
  • አጠሬራ
  • ኦዲዮ መጽሐፍ
  • ፍለጋ
  • ይስቀሉ
  • የኔዞን
  • ይግቡ
  • ይመዝገቡ
English  አማርኛ  Français  العربية
የዕለቱ መጽሐፍ

ጀብሃ እና ሻቢያ.pdf


  • የቃላት ደመና

ጀብሃ እና ሻቢያ.pdf
  • የማውጣት አጠሬራ

አሁንም እንቀጥል ድድድቱቴቴ የሰልፊ ነጻነት መሪዎች እርስ በርስ ይሻኮቱ ነበር ብያለሁ ታዲያ ታጋዩም ሰለሞንን በፊቱኑ ይጠላው ነበርና ፕሮፓጋንዳውን ሲሰማ ይህ አምባገነን። ከላይ የተዘረዘረው ጥፋት ለሞት የሚያበቃ ነበር። ይህ ጥያቄ አስከ አሁን ድረስ አከራካሪ ሆኖ ዘልቋል ኮሎኔል መንግሥቱ ጄኔራል ታሪኩ ባይረሸን አንኳ አፋቤትን ከመያዝ የሚገድባቸው ሀይል እንዳልነበረ ይከራከራሉ ወጣም ወረደ ግን ሁሉም በአንድ ነገር ይስማማሉ የአፋቤት ሽንፈት የጦርነቱን አቅጣጫ ከመሰረቱ የቀየረ መሆኑን ያለ ምንም ማመንታት ይቀበሉታል ከዚያ በኋላ የነበረው የአብዮታዊ ሰራዊት ጉዞ በኋላ ማርሽ የመጓዝ ዓይነት ነበር ይላሉ በዚህ ረገድ የተለየ አስተያየት የሰጡት ኮል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ብቻ ናቸው እሳቸው እንደሚሉት የአፋቤትን ሸንፈት ያጋነኑት የዓለም ሚዲያዎች ናቸው እንጂ በወቅቱ የሰራዊቱ አቅም አልተነካም ፕሬዚዳንት መንግሥቱ አባባል በኤርትራ ምድር እጅግ ወሳኝ የሆነ ውድቀት የሚባለው በምጽዋ የደረሰው ነው እንጂ በአፋቤት የታየው አይደለም የምጽዋው ውድቀትስ ምን ይመስል ነበር።

  • Cosine ማጠቃለያ

ተኤ ይባላል የታሪከ ሰነዶቸና መላው ኤርትራዊያን ድርጅቱን የሚጠሩት ግን ጀብሃ በሚል አጭር ስም ነው ጀብሃሦ የሚለው ቃል ሟብሃት ታሕሪረል ኤሪቲሪያ ከሚለው የድርጅቱ የዐረብኛ መጠሪያ ተቀንጭቦ የወጣ ነው ይህም ድርጅቱን ከረካ ለይቶ ለመጥራት በሚደረግ ጥረት የተፈጠረ ልማድ ነው የሁለቱ ድርጅቶች የዐረብኛ መጠሪያ አንድ ዓይነት ሆኖ በስሞቹ መጀመሪያ ላይ ባሉት ጀብሃ እና ሀረካ በሚሉት ቅጽሎች ብቻ ነው የሚለዩትነ ተሓኤጀብሃ የተመሰረተው በ በካይሮ ከተማ ነው የድርጅቱ መስራቾች በስደት ላይ የነበሩ ኤርትራዊያን ተማሪዎች የቀድሞ ራቢጣ አና ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ አባላት ከኤርትራ ፓርላማ የኮበለሉ ጥቂት ግለሰቦችና በዐረቡ ዓለም የሚኖሩ ነጋዴዎች ነበሩ ድርጅቱ በምስረታ ጉባኤው ከኤርትራ ነጻነት በስተቀር ሌሎች አማራጮችን አንደማይቀበል አስታወቀ ፌዴሬሽን የሚባለው አስተሳሰር ለኤርትራዊያን በጭራሽ የማያስፈልግ የባርነት እስር ቤት ነው በማለት ደመደመ ከኢትዮጵያ መንግሥትም ጋር በነጻነት ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በሌሎች አጀንዳዎች እንደማይደራደር ገለጸ የኤርትራ ፓርላማ ፕሬዚዳንት የነበረውን ኢድሪስ መሐመድን በሊቀመንበርነት መረጠ ጀብሃ በምስረታው ማግስት ለትጥቅ አመጽ መዘጋጀት ጀመረ በሀገር ቤት ካሉ ባላባቶች ጋር ግንኙነት ከተፈጠረ በኋላ ምዕራባዊው የኤርትራ ቆላ ለትግል ምቹ መሆኑን አመነበት የአካባቢው ታዋቂ ባላባት የሆኑት ሃሚድ ኢድሪስ አዋቴ የሚባሉት የቤኒ አምር ጎሳ ተወላጅ የግንባሩን የትጥቅ ትግል እንዲመሩ ውክልና ተሰጣቸው በኝህ ሰው አስተባባሪነትም አስራ አንድ ሰዎችን ያቀፈ አንድ ቡድን መስከረም በኤርትራ ምድር ለ ዓመታት የሚቆየውን የትጥቅ ትግል በምዕራባዊው የባርካ አውራጃ ጀመረ ሆኖም ሃሚድ አዋቴ ከአንድ ዓመት በኋላ በተደረገ ውጊያ ላይ ተገድለዋል ጀብሃ ወደ ትግሉ ሜዳ የገባው በከረረ ስሜት ነው ከላይ እንደተገለጸው ከኤርትራ ነጻነት በስተቀር በየትኛውም አማራጭ ላይ ለመደራደር ፍቃደኛ አልነበረም የትግል ዓላማው ኤርትራን ነጻ ሀገር ማድረግ ከመሆኑ በመለስ ድርጅቱ በምስረታው ዋዜማ የየትኛው የርዕዮተ ዓለም አቅጣጫ ተከታይ እንደነበረ በትክከል ለመረዳት ይቸግራል በርካታ ጸሓፊያን ተሓኤ መብሃ ብሄርተኛ ከመሆኑ ውጪ የተለየ ጎራ ተከታይ እንዳልነበረ ያስረዳሉ አንዳንዶች ግን ድርጅቱ ከኢራቅና ከሶሪያ በዕሥ ከ ፓርቲዎች ጋር የነበረውን ጠንካራ ግንኙነት በመመልከት ሟብሃ የዐረብ ሶሻሊዝም ፍልስፍና ተከታይ ነበር ይላሉ በርግጥም ሟብሃ በዐረቦች ዘንድ ከፍተኛ እውቅናና ድጋፍ አግኝቶ ነበር ራሱንም እንደ ዐረብ ብሔርተኛ ድርጅት የማየት አዝማሚያዎች ነበሩት ሆኖም ይህንን ሁሉ ለታክቲክ ሲባል የሚያደርገው ነው የሚመስለው ድርጅቱ ዐረባዊ እየመሰለ እና ዐረብኛን የስራ ቋንቋ በማድረግ እየተገለገበት እንኳ ዐረብ ካልሆኑ የኮሚኒስት ሀገራትም ጋር ግንኙነት ነበረው ለምሳሌ ጀብሃ ከኩባ ቻይና አና ሶቪየት ህብረት ከፍተኛ ድጋፍ አግኝቶ ነበር አንዲሁም የሶሻሊዝም ጠላት ናቸው ከሚባሉት ሳዑዲ ዐረቢያን ከመሳሰሉ ሀገራት ጋር የነበረው ግንኙነት በጣም የጠነከረ ነው ጣሊያንን የመሳሰሉ የምዕራብ ሀገራትም የድርጅቱ ደጋፊዎች ነበሩ ከዚህ ሁሉ አንደምንረዳው ድርጅቱ የታከቲከ ወዳጅ እንጂ የርዕዮተ ዓለም ወዳጅ ነበረው ለማለት ይከብዳል የጀብሃ መስራቾች በአብዛኛው የትግረ ቋንቋ ከሚናገሩት የቤኒአምር አሳውርታ እና ቢለን ጎሳዎች የተውጣጡ ነበሩ በዚህም የተነሳ በምስረታው ዘመን ከድርጅቱ አባላት ዘጠና በመቶ የሚሆኑት ሙስሊሞች ነበሩ የድርጅቱ እንቅስቃሴም በቆላማዎቹ የሳህል ከረን እና ባርካ አውራጃዎች የተገደበ ነበር በምስረታው ዘመን ከሀምሳ የማይበልጡ ተዋጊዎች የነበረው ይህ አንቅስቃሴ ከሁለት ዓመታት በኋላ ሰራዊቱን በብዙ እጥፍ በማሳደግ ወደ ሶስት ሺህ አድርሶታል በመጀመሪያዎቹ ዓመታት የአ ሀይለስላሴ መንግስት ጀብሃን እንደ ተራ የሽፍታ ስብስብ ስለቆጠረው በፖሊስ ሀይል አሳድዶ ሊያጠፋው ሞከሮ ነበር በ ከከረን ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ስፍራ ላይ በተደረገ ከባድ ውጊያ በርካታ ፖሊሶች ከሞቱ በኋላ ግን የንጉሥ መንግሥት መደበኛ ሰራዊቱን ወደ ኤርትራ ማንቀሳቀስ ግድ ሆኖበታል ጀብሃ በምስረታው ማግስት ጥርት ያለ የድርጅት መዋቅር አልነበረውም በ ግን የድርጅቱን አመራር ማስተካከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ መዋቅሩን በልዩ ልዩ እርከኖች በመከፋፈል በስራ ላይ አውሎታል በዚህም መሰረት አምስት አባላት ያሉት ላዕላይ ባይቶ ጠፍተኛ ምከር ቤት የሚባለው አካል የድርጅቱ ከፍተኛ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሆኖ ተሰየመ የግንባሩን አጠቃላይ የፖሊሲ ውሳኔዎች የሚያስፈጽመው ይህ አካል ነው ድርጅቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚወከለውም ይኸው ቂያዳ አልአማ ነው ኢድሪስ መሀመድ ኡሥማን ሳልህ ሳቤ ጣሃ መሐመድ ኑር ኢድሪስ ገላውዴዎስ እና አብደላ ኢድሪስ የጀብሃ ስራ አስፈጻሚዎች ነበሩ የስራ አስፈጳሚ ኮሚቴው የሚቀመጠው የድርጅቱ ዋና ጽቤት ባለበት የካይሮ ከተማ ነው ኢድሪስ መሐመድ አና ኢድሪስ ገላውዴዎስ የግንባሩ ፕሬዚዳንትና ምከትል ፕሬዚዳንት ዑስማን ሳልህ ሳቤ የድርጅቱ የውጪ ጉዳይ ሃላፊ ነበሩ ከስራ አስፈጻሚው ኮሚቴው ዝቅ ብሎ ደግሞ አብዮታዊ እዝ የሚባል ምከር ቤት አለ የዚህ እዝ ተቀማጭነቱ በሱዳኗ ከሰላ ከተማ ሲሆን መደበኛ ተግባሩም በአምስቱ ዞኖች የሚከናወኑትን ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ተግባራት ማቀናበርና ማቀላጠፍ ነው ስለዞን አወቃቀር ከታች አንመጣበታሰንቕ የመጀመሪያው የጀብሃ ወታደራዊ አዛዥ ዑመር ኢዛዝ ይባላል ይህ ሰው የብሌን ብሄረሰብ ተወላጅ ሲሆን ጀብሃ እስከዛሬ ካፈራቸው አዋጊዎች በጀግንነቱ የሚወደሰው አርሱ ነው ዑመር ኢዛዝ የተወለደው በከረን ከተማ ነው በወጣትነቱ ወደ ሱዳን ተሰዶ በሱዳን ጦር ሀይል ውስጥ በመቀጠር እስከ ሻምበል ማዕረግ ለመያዝ ችሏል ከርሱ ጋር የተዋጉና አሁንም በህይወት ያሉ የጀብሃ አባላትና መሪዎች በጣም ያደንቁታል ሆኖም በጭካኔው ወደር አንዳልነበረው ታሪኩን የጻፉ ወገኖች ይመሰከራሉ ዑመር ኢዛዝ በ በተደረገ ከባድ በውጊያ ላይ ሞቷል ጀብሃ እስከ ሲያካሄደው የነበረው ወታደራዊ ኦፕሬሽን በአንድ የዘመቻ ማዕከል ነበር የሚመራው በነዚያ ዓመታት ግንባሩ ነጻ ያወጣው ትልቅ ከተማ ባይኖርም ሳህል እና ባርካ በሚባሉት ቆላማ የኤርትራ አውራጃዎች ውስጥ ያለው የገጠሩ ከፍል በቁጥጥሩ ስር ገብቶ ነበር ከ ጀምሮ የአጴጹ ኃይለ ስላሜ መንግሥት የግንባሩን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር በሚል የወሰዳቸው የጅምላ ቅጣቶች ተቃራኒ ውጤቶች ነው የነበራቸው በተለይም የኤርትራ ሀገረ ገዥ የነበሩት ልዑል ራስ አስራተ ካሳ በ ይህቺን ቆላ ሀገር አንደ ተመለጠ ራስ ምድረ በዳ አደርጋታለሁ በማለት በባርካ አውራጃ ከፍተኛ ህዝብ ያለቀበትን ዘመቻ ማካሄዳቸው በታሪከ ምሁራን ተጽፏል በወቅቱ በኤርትራ ከፍለ ሀገር ወታደራዊ ኦፊሰር የነበሩት ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ በጻፉት መጽሐፍ እንደገለጹት ከአምስት ሺህ የማያንሱ ሰላማዊ ኤርትራዊያን ራስ አስራተ ካሳ ባዘመቱት ሰራዊት ተፈጅተዋል አጹ ኃይለ ሥላሴ በራስ አስራተ ካሳ የተወሰደውን ጭካኔ የተመላበት እርምጃ ከሰሙ በኋላ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ እንደሰጧቸው ይነገራል በዚህም የተነሳ ራስ አስራተ በንጉሥ ላይ ቂም ይዘው ከስልጣን ሊያወርዷቸው ሲያደቡ ነበር ሆኖም የራስ አስራተ አርምጃ የትጥቅ አመጹን አባባሰው እንጂ አላቆመውም በተለይ ከመንግስት ጋር ሰላማዊ ግንኙነት የነበራቸው ከርስቲያኖቹ የደጋው ኤርትራ ከፍል ነዋሪዎች በብዛት ወደ በረሃ እየወረዱ ከጀብሃ ጋር መቀላቀል የጀመሩት የራስ አስራተ ጦር በኤርትራዊያን ላይ ያደረሰው ፍጅት ከተሰማ በኋላ ነው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩት እንደ ኢሳያስ አፈወርቂ ወልዳይ ግደይ ሰለሞን ወልደማሪያም ሙሴ ተስፋዮሐንስ ወዘተ የመሳሰሉ ፋኖዎች ጀብሃን የተቀላቀሉት በዚያ ዓመት ነው ከምጽዋ አካባቢም እንደ ኢብራሂም አፋ እና ረመዳን መሐመድ ኑርን የመሳሰሉ ተዋጊዎች ጀብሃን ተቀላቅለዋል ድድድቱቴቴ ጥቅምት ጀብሃ እና ሻዕቢያ ከፍል ሁለት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመሄድ ላይ የነበረው ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ ጀብሃ በኢትዮጵያ ውስጥ መታወቅ የጀመረው በዎቹ ማብቂያ ገደማ ነው በነዚህ ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ኤርትራዊያን የግንባሩን እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅ ረድተዋል በውጤቱም የራስን አድል በራስ መወሰን በሚለው ኮሚኒዝም ቀመስ መርህ የሚያምኑ አንጋፋ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድጋፍ ሰጥተውታል በውጪው ዓለም ጀብሃን በስፋት ያስተዋወቀው ግን ግንባሩ በ የወሰደው አንድ ኦፕሬሽን ነው ይህ ኦፐሬሽን ከዚያ ወዲህ በኢትዮጵያ ታሪከ በድጋሚ ያልታየ በመሆኑ በአጭሩ ብንቃኘው መልካም ይመስለኛል የካራቺ ኦፐሬሽን ሟብሃ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፉ የሚዲያ ማህበረሰብ እይታ ውስጥ የገባው በ አንዲት የአሜሪካ ወታደራዊ ሂሊኮፕተርን በባርካ አውራጃ መትቶ በጣለበት ጊዜ ነው ድርጅቱ በወቅቱ ሂሊኮፕተሯ የተመታችው በይዞታዬ ላይ የስለላ ስራ ስታካሂድ በመገኘቷ ነው የሚል መግለጫ ሰጥቶ ነበር እንዲህም ሆኖ ግን ወሬው ብዙ ሳይወራ በዚያው ተረስቶ ቀረ ከአራት ዓመታት በኋላ ደግሞ የጀብሃ አመራር ድርጅቱን በዓለም ላይ በስፋት ያስተዋውቃል ያለውን ኦፕሬሽን ለማካሄድ ወሰነ ይህንን ለመፈጸም አስፈላጊ ሆኖ የተገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖችን መጥለፍ አሊያም በኤርፖርት ላይ አንዳሉ በቦንብ ማጋየት ነው በዚህ መሰረት በሶስት ከተሞቾ የሚገኙ ኤርፖርቶች ተመረጡ እነርሱም የፍራንከፈርት የሮም እና የካራቺ ፓኪስታን ኤርፖርቶች ነበሩ ኦፕሬሽኑን የሚተገብሩ ፊዳይን የሚባሉ ኮማንዶዎችም ተዘጋጁ ዳይን የዐረብኛ ቃል ሲሆን ሰማዕታት ማለት ነው ቀዳሚ የሆነው የፈራንከፈርት ኦፕሬሽን በመጋቢት ወር ተካሄደ በኤርፖርቱ ቆሞ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ቦይንግ አውሮፕላን በቦንብ ተመታ የጀብሃ ፈዳይኖች እንዳለ አመለጡ። በሚቀጥለው ከፍል አንዳስሰዋለን ድድድቱቴቴ ጥቅምት ጀብሃ እና ሻዕቢያ ከፍል ሶስት ባለፈው ከፍል እንደገለጽኩት ጀብሃ ትግሌን አንደ አልጄሪያ ነጻ አውጪዎች አጠናከርበታለሁ ያለውን የዞን አከፋፈል በስራ ላይ አውሏል ሆኖም በግንባሩ ውስጥ የተከሰተው ቀውስ ከቀን ወደ ቀን እየጠነከረ ነው የሄደው ግንባሩ ኤርትራዊያንን በጎሳ እና በሀይማኖት ይከፋፍላል በማለት የተቆጡ ታጋዮችን ለማለዘብ አንዳንድ ለውጦች ቢካሄዱም ቅሬታዎቹ ሌላ መልከ እየያዙ ቀጥለዋል ለምሳሌ በዎቹ መጨረሻ ላይ ከዩኒቨርሲቲና ከከፍተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤቶች ወደ ድርጅቱ የተቀላቀሉ ወጣቶች ኤርትራን ነጻ የሚያወጣው በላብ አደር መደብ የሚመራ ሀቀኛ አብዮት ነው የሚል መፈከር በማንሳት ግንባሩ የብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ አብዮት ፕሮግራም እንዲያውጅ ይወተውቱ ነበር ይህም ማንባሩ የማርከሲዝም ርዕዮተ ዓለም ተከታይ መሆኑን በይፋ ያሳውቅ እንደማለት ነው በሌላ በኩል የድርጅቱ አመራር በጉባኤ ያልተመረጠ ስለሆነ ጉባኤ ተደርጎ አዳዲስ መሪዎች ወደ አመራሩ መምጣት አለባቸው የሚል ጥያቄ የሚያነሱ ከፍሎች ነበሩ በ መጀመሪያ ላይ የጀብሃ አመራር ለመጀመሪያ ጊዜ ለጥያቄዎቹ አዎንታዊ ምላሽ ሰጠ ቅሬታዎችም ሆኑ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች በድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ እንደሚመለሱ ቃል ገባ ይሁን እንጂ በወቅቱ የሀይለ ሥላሜ መንግሥት በግንባሩ ላይ ሁለተኛ ዙር የማጥቃት ዘመቻ እያካሄደ ስለነበር ጉባኤው ከሁለት ዓመት በኋላ በ ሊደረግ እንደተወሰነ ለጠያቂዎቹ ተገለጸላቸው ነገር ግን ጠያቂዎቹ በዚህ አልረኩም ቢያንስ አስቸኳይ ኮንፈረንስ መደረግ አለበት በማለት ወተወቱ የጀብሃ አመራር በዚሁ በመስማማቱ ኮንፈረንሱ በሳህል አውራጃ ውስጥ በሚገኘው አርዳይብ በተባለ ቦታ ተካሄደ በዚህ ኮንፈረንስ ላይ በውጊያ ላይ የነበሩት አንደኛና ሁለተኛ ዞኖች አልተሳተፉም ሶስተኛ አራተኛና አምስተኛ ዞኖች ብቻ ናቸው ከቦታው የተገኙት በዚህም የተነሳ ከሶስቱ ዞኖች ወደ ጉባኤው የመጡ ታጋዮች የልባቸውን አውጥተው የሚናገሩበት ዕድል ተፈጠረ እነዚህ ዞኖች በምስራቅና ደቡብ ኤርትራ በሚገኙ ቦታዎች የሚቀንሳቀሱ መሆናቸውን አስታውሱ በጀብሃ ላይ ቅሬታ ሲያቀርቡ የነበሩትም በነዚህ ዞኖች ስር የተደራጁት ናቸው በኮንፈረንሱ ላይ ከደጋው የኤርትራ ከፍል ወደ ድርጅቱ የተቀላቀሉ ወጣቶች የዘመናት ብሶታቸውን ይፋ አውጥተው ተናገሩ ለኤርትራ ነጻነት አፋለማሁ የሚለው ድርጅት የፋሺስት አዝማሚያ እየተከተለ ነው በማለት ኮነኑት አሟሟታቸው የተደበቀ የበርካታ ታጋዮችን ስም አየጠሩ ጀብሃን አወገዙት ግንባሩ በአንድ ዓመት ጊዜ ራሱን ካላስተካከለ ከድርጅቱ አንወጣለን የሚሉ መግለጫዎች ተሰሙ የጀብሃ አመራሮች ጫናውን ለመቋቋም ከበዳቸው ሁሉንም አንጣራለን በማለት ቃል ቢገቡም የተሰብሳቢዎቹን ልብ ለማግኘት አልቻሉም በመጨረሻ ግን ሁሉም ከአመት በኋላ በሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ በመስማማት ተለያዩ ከአንድ ዓመት በኋላ ደግሞ የሁሉም ዞኖች ወታደራዊ መሪዎች የተገኙበት አስቸኳይ ኮንፈረንስ አዶብሃ በተባለ ስፍራ ተካሄደ በኮንፈረንሱ ላይ ዱላቀረሽ ከርከር ከተደረገ በኋላ ተቀማጭነቱ በሱዳኗ ከሰላ ከተማ የሆነው ቃኢዳ ሰውራ አብዮታዊ እዝ እንዲፈርስ ተወሰነ ከያንዳንዱ ዞን ስምንት ወጣት ሰዎች የተመረጡበትና አባላት ያሉት ቃኢዳ አልአማ ጠቅላይ መምሪያ ተመሰረተ ሆኖም የካይሮው ላዕላይ ምክር ቤት በነበረበት ይቀጥል ተባለ የድርጅቱ መሪዎች እርምጃውን ህገ ወጥ ቢሉትም የእልአማ አባላት ግን ህጋዊ ነን በማለት በአርምጃቸው ቀጠሉበት ከአዶብሃ ኮንፈረንስ በኋላ በአዶብሃ ኮንፈረንስ ከተሳተፉት መካከል የሶስቱ ዞኖች ሶስተኛ አራተኛ እና አምስተኛ ዞን ታጋዮች ልብ ለልብ ተግባቡ ውለው ሳያድሩም ወታደራዊ ዞን የሚባለውን አከፋፈል ለማፍረስ ተስማሙ የአንዱ ዞን ታጋዮች በሌላኛው ዞን እንዳሻቸው ወታደራዊ ዘመቻ ማካሄድ ይችላሉ በማለትም አሰመሩበት ሊያጠቃቸው የሚመጣውን የመንግሥት ጦር ሀይል በህብረት ለመመከትም ተስማሙ ከጥቂት ጊዜ በኋላም በነዚህ ዞኖች ውስጥ ያሉ ታጋዮች ሰልፊ ነጻነት እና ሀዝባዊ ኃይሊ በሚባሉ ቡድኖች ስር ራሳቸውን አደራጁ ህዝባዊ ኃይሊ በአብዛኛው የምጽዋና የሰምሃር አካባቢ ተወላጆችን ያቀፈ ነው ቁጥራቸው አነስተኛ ቢሆንም በፖለቲካም ሆነ በወታደራዊ ችሎታ አንቱ የተሰኙ ናቸው ረመዳን መሐመድ ኑር ኢብራሂም አፋ እና መስፍን ሐጎስ የቡድኑ መሪዎች ነበሩ የዚህ ቡድን መንቀሳቀሻ ከምጽዋ በስተሰሜን የነበረው የባህር ጠረፍ ነበር ሰልፊ ነጻነት ደግሞ በአብዛኛው የሐማሴን እና የአከለ ጉዛይ ተወላጆችን ነው ያቀፈ ነው አብርሃም ተወልደ ኢሳያስ አፈወርቂ ሀብተሥላሜ ገብረ መድህን ሰሎሞን ወልደማሪያም ወልደ ሚካኤል ኃይለ እና ባራኺ ንጉሠ የቡድኑ መስራቾች ናቸው ኢሳያስ አፍወርቂ የዚህ ቡድን ጊዜያዊ መሪ ሆኖ ተሰይሟል የቡድኑ ዋነኛ መንቀሳቀሻ በደቀምሐረ ወረዳ የሚገኘው የዓላ በረሃ ነው እነዚህ ሁለት ቡድኖች በይፋ ከጀብሃ መገንጠላቸውን ሳያሳውቁ ትግሉን በየፊናቸው ማካሄድ ጀመሩ ጀብሀም ስሙን በድጋሚ ላለማስጠቆር እስከ ቀጣዩ ጉባኤ ድረስ የቡድኖቹን ሁኔታ በዝምታ መከታተሉን ቀጠለ በሌላ በኩል ጀብሃ እስከ ዛሬ ድረስ የሚጸጸትበትን ታሪካዊ ስህተት የፈጸመው በዚሁ ወቅት ነበር ይኸውም የዑሥማን ሳልሕ ሳቤ ከስልጣን መባረር ነው የጀብሃ መሪዎች ሳልህ ሳቤ በደገኞቹ ላይ የሚፈጸመውን ኢፍትሐዊ ቅጣት በመቃወሙ ቂም ይዘውበታል በተጨማሪም ከዐረቦች የሚሰጣቸው አርዳታ ወደ ኤርትራ ምድር የሚገባው በርሱ በኩል በመሆኑ በቅናት ዐይን ይመለከቱት ነበር ስለዚህ እርሱን አባርረው ሳሊህ አህመድ ኢያይ በሚባል ሰው ለመተካት ወሰኑ ይህንንም ሲያደርጉ በልባቸው ሳልህ ሳቤ ሽርሽር እንጂ የበረሃ ትግል የማይቸል ሰው በመሆኑ በሶሪያና ካይሮ ጎዳናዎች ተወስኖ ይቀራል የሚል አስተሳሰብ ነበራቸው ውጤቱ ግን እነርሱ ከጠበቁት ውጪ ነው የሆነው ሳልህ ሳቤ በኤርትራዊያን ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታ ያገኘበትን ገድል ለመፈጸም የተነሳሳው የጀብሀ መሪዎች ይህንን እርምጃ ከወሰዱ በኋላ ነው ሰውዬው ጀብሃዎች እንደገመቱት በዐረብ መዲናዎች አልቀረም በቀጥታ ወደ ሳህል በረሃ መጥቶ ህዝባዊ ሀይሊ ከሚባለው ቡድን ጋር ነው የተቀላቀለው የቡድኑ ታጋዮችም ወዲያውኑ በመሪነት ቦታ ላይ አስቀመጡት ዑስማን ሳልህ ሳቤ በተለመደው የዲፕሎማሲ ጥበቡ ከዐረብ መዲናዎች የሚያሰባስበውን የጦር መሳሪያ ወደ ኤርትራ በረሃ እያመጣ ህዝባዊ ሀይሊ የተባለውን ቡድን አስከ አፍንጫው ድረስ አስታጠቀው ሆኖም ቡድኑ ከፍተኛ የሰው ሀይል እጥረት ስላነበረበት ኢሳያስ አፍወርቂ በጊዜያዊነት ከሚመራው ሰልፊ ነጻነት ጋር በጋራ ግንባር ለመስራት መነጋገር ጀመረ በውይይታቸው ወደ ስምምነት ተቃረቡ በዚህ መሀል ደግሞ ከጀብሃ ታጋዮች መካከል የማሪያ ጎሳ ተወላጆች የአቆርዳት አካባቢ ልጆች የሆኑት ጥቂት ሰዎች ሟብሃ ለቤኒ አምር ልጆች ያደላል በሚል ቂም ቋጥረው ኖሮ ከጀብሃ ተገንጥለው ወደ ሳሕል ወረዱና ከሰልፊ ነጻነት እና ህዝባዊ ኃይሊ ጋር የጋራ ግንባር ፈጠሩ ይህ የማሪያ ልጆች ቡድን ዑበል ይሰኛል ጀብሃ በ ድርጅታዊ ጉባኤ ጠራ የሁለቱ ዞኖች ዞን አንድ አና ዞን ሁለት ተወካዮች በጉባኤው ተገኙ ከግንባሩ የወጡት ሶስቱ ቡድኖች ግን በጉባኤው ላይ እንደማይገኙ አስታወቁ ጀብሃ ለጊዜው እነርሱን ችላ በማለት ጉባኤውን በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት አካሄደ በጉባኤው ፍጻሜ ላይ በርካታ ስርነቀል እርምጃዎች ተወሰዱ እስከ ዛሬ ድረስ የጀብሃ መለያ ሆኖ የሚታወቀው ሰውራዊ ባይቶ አብዮታዊ ምክር ቤት ማለት ነው በትግረ ቋንቋ የሚባለው የግንባሩ ላዕላይ ምከር ቤት በዚያ ጉባኤ ውሳኔ መሰረት ተፈጠረ እነ ህሩይ ተድላ ባይሩን የመሳሰሉ ታዋቂ ደገኛ ግለሰቦቸ ወደ አመራሩ መጡ ህሩይ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የጀብሃ ምከትል ፕሬዚዳንት ነው ተቀማጭነቱ ከሰላ ላይ የሆነው አብዮታዊ እዝ ቃኢዳ ሰውራ ህጋዊ ስለሆነ በዚያው ይቀጥል ተባለ ሆኖም አላግባብ ሰው ገድለዋል የተባሉ የጦር መሪዎች ከስልጣን ተባረው በአዳዲስ ሰዎች ተተኩ የጀብሃ መሪዎች ራሳቸውን እንዲህ ከቀያየሩ በኋላ በድርጅቱ ውስጥ የነበረው ችግር ሙሉ በሙሉ ተፈቷል ከዚህ በኋላ የሚያንገራግር ወይንም ቅሬታ አለኝ የሚል አካል ለኤርትራ ነጻነት አንቅፋት ነው የሚል አዋጅ አወጁ በተጨማሪም በብዙዎች አንደበት ተደጋግሞ የሚጠቀሰውን የኤርትራ መሬት ከአንድ ድርጅት በላይ አይቸልም የሚለውን የድርጅታቸውን መርህ በይፋ አሰሙ በዚህም መሰረት በጉባኤው ላይ ካልተሳተፉት ሶስት ቡድኖች መካከል ዑበል እና ህዝባዊ ኃይሊ በሚባሉት ላይ ጥቃት ለመከፈት ወሰኑ በሰልፊ ነጻነት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ግን ለጊዜው እንዲዘገይ ተወሰነ እንዲህ የተደረገው በሁለት ምከንያት ነው ይባላል አንደኛው ምክንያት አብርሃም ተወልደ የሚባለው የቡድኑ ዋነኛ ሰው ከጀብሃ ጋር ለመደራደር ፍላጎት እንዳለው በድብቅ መልዕከት ልኳል የሚል ነው ሁለተኛውና ዋነኛው ምከንያት ደግሞ ቡድኑ በአብዛኛው ከርስትያን የሆኑ ታጋዮችን ያቀፈ በመሆኑ ከባድ እርምጃ ከተወሰደበት ሟብሃ ጸረከርስቲያን ነው የሚለው ፕሮፓጋንዳ ይጠናከራል በማለት ስለተፈራ ነው ይባላል ሻዕቢያ ተወለደ ጀብሃ በአንደኛው ድርጅታዊ ጉባኤ በተወሰነው መሰረት አፈንጋጮቹን ለማጥፋት ሰራዊቱን ወደ ሳሕል በረሃ አዘመተ የዑበል እና ህዝባዊ ኃይሊ አባላት በሰፈሩበት ጎራ ላይ ጥቃት ተከፈተባቸው ሆኖም ቡድኖቹ ነቅተው ይጠብቁ ስለነበር አጥቂው ሀይል ሲመጣባቸው በሰሜን አቅጣጫ ወደ ሱዳን ሸሹ ይህንን ያየው የጀብሃ ሰራዊት ሰልፊ ነጻነት የሚባለውን ቡድን ሳይነካው ወደ ባርካ ተመለሰ ሰልፊ ነጻነት በበኩሉ የጀብሃን አርምጃ እኛን ለማታለል የተደረገ ነው በሚል ስለወሰደው ሰራዊቱን በመያዝ በፊት ወደ ነበረበት የዓላ በረሃ አከለ ጉዛይ አውራጃደቀምሐረ ወረዳ ተመለሰ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ከሳሕል የተባረሩት የዑበል እና ህዝባዊ ኃይሊ አባላት በዑስማን ሳልሕ ሳቤ መሪነት በቀይ ባህር አቋርጠው በደቡብ ኤርትራ እምባሶይራ በሚባለው ተራራ እንደመሸጉ ተሰማ የሰልፊ ነጻነት ቡድን አባላት ከቦታው ድረስ ሄደው ከተቀበሏቸው በኋላ በፊት የተጀመረው በጋራ ግንባር የመስራት ጥያቄ በአጭር ጊዜ መልስ እንዲያገኝ ጠየቋቸው የተቀሩት ቡድኖችም ጥያቄውን በደስታ በመቀበላቸው ቤይሩት ላይ ህብረቱ እንዲታወጅ ተወሰነ በዚህም መሰረት በ በቤይሩት ከተማ የጋራ ግንባሩን አወጁ ለአሰራር ያመቻል ስለተባለም ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ የሚለው የቀድሞው የድርጅታቸው ስም በነበረበት እንዲቀጥልና በስሙ ላይ ህዝባዊ ሓርነት ኃይልታት የሚል ቅጥያ እንዲጨመርበት ተወሰነ በእንግሊዝኛ ቭቨፐፍኋክ ከፎየቨዐክ ኮዮዐክቪ ከፎየቨክ ርርርፀ ተብሎ ነበር የሚጠራው ቡድኖቹ የግንባሩ አመራር ወደፊት እንዲመረጥም ነው የተስማሙት ኦሥማን ሳልሕ ሳቤ ግን የግንባሩ የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ሆኖ እንዲቀጥል በአንድ ድምጽ ወስነው ነበር ይህ ግንባር በታሪከ ምዕራፎች በአጭሩ ህዝባዊ ኃይልታት ተብሎ ነው የታወቀው ብዙዎች አርሱን የሚያውቁት ግን ሻዕቢያ በሚል የዐረብኛ ስሙ ነው ሻዕቢያ ህዝባዊ ማለት ነውበዐረብኛ ነገር ግን ይህ የመጀመሪያው ማዕቢያ አሁን ካለው ጣዕቢያ ይለያል ህዝባዊ ኃይልታት በሳሕልና በዓላ በረሃዎች እንቅስቃሴውን ሲጀምር ጀብሃ በከፍተኛ ሽብር ውስጥ ወደቀ ይህ አዲስ የበቀለው ግንባር በአንጭጩ ካልተቀጨ ለስልጣኔ ያሰጋኛል በሚል ደመደመ በተለይም የጀብሃ መሪዎች ዑስማን ሳልህ ሳቤ የግንባሩ የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ሆኖ መሰየሙን በዝምታ ሊያልፉት አልፈለጉም ስለዚህ የልባቸውን ለማድረስ ሰራዊታቸውን ወደ ሳሕል በረሃ አዘመቱት ሆኖም ጀብሃዎች በአዲሱ ግንባር ተሸነፉ እንደገና ጥቃት ቢሞከሩም አልተሳካላቸውም ዓመቱን በሙሉ ከህዝባዊ ሀይልታት ጋር ቢዋጉም ውጤቱ ሊቀየር አልቻለም ይባስ ብሎም በስተመጨረሻ በአዲሱ ግንባር ሙሉ በሙሉ በመሸነፋቸው ከሳሕል በረሃ ተጠራርገው ወደ ባርካ አውራጃ ገቡ አዲሱ ህዝባዊ ኃይልታት ጀብሃን እንዲህ ከመከተ በኋላ ግን አንድነቱን ማስጠበቅ አልቻለም ዑበል የተሰኘው ቡድን አባላት በግንባሩ ውስጥ ተሰሚነት የለንም በሌሎቹ ተውጠናል የሚል ቅሬታ ስለተፈጠረባቸው ከአንድነት ግንባሩ በመውጣት በባርካ አውራጃ የራሳቸውን የውጊያ ግንባር ለመከፈት ወደ ትውልድ መንደራቸው ሄዱ ሆኖም በመንገድ ላይ ባልተጠበቀ ሁኔታ በጀብሃ ሰራዊት ቀለበት ውስጥ ገቡ ጀብሃዎቹም አንዳቸውንም ሳያስተርፉ ፈጁአቸው በዚህም የዑበል እንቅስቃሴ ታሪክ አከተመ በህዝባዊ ኃይልታት ውስጥ የቀሩት ህዝባዊ ኃይሊ እና ሰልፊ ነጻነት ወደ ውህደት ለመሸጋገር ከጫፍ ላይ ደረሱ ሆኖም ሁለት ያልታሰቡ እንግዳ ከስተቶች ገፍተው ስለወጡ የውህደቱን አርምጃ ገቱት ታዲያ እነዚህ እንግዳ ነገሮች መሰረታቸውን የጣሉት ሶስቱ ቡድኖች ከጀብሃ በይፋ ተነጥለው ከመውጣታቸው በፊት ነው ከነዚህ ከስተቶች መካከል አንደኛው የኤርትራ ገዥ የነበሩት ልዑል ራስ አስራተ ካሳ ጀብሃን ለማጥፋት ከሰልፊ ነጻነት ጋር በስውር በተዋዋሉት መሰረት ኢሳያስ አፈወርቂን የመሳሰሉ የቡድኑ መሪዎች ጀብሃን እስከ መጨረሻው መደምሰስ አንጂ መታረቅ አይታሰብም የሚል አቋም ይዘው መገኘታቸው ነው ሁለተኛው አንግዳ ከስተት ደግሞ ሲአይኤ በ ከኢሳያስ አፍወርቂ ጋር በሚስጢር ተገናኝቶ የቀበረው ፈንጂ እየፈነዳ ማስቸገሩ ነው የዚህ የሲአይኤ ፈንጂ የአጭር ጊዜ ዓላማ በፍልስጥኡም ነጻ አውጪ ድርጅት ደጋፊነት የተጠረጠረውን ጀብሃን ማዳከም ነው የረጅም ጊዜ ዓላማው ኤርትራን አስገንጥሎ በአንድም ወቅት ከሌሎች ሀገራት ጋር በስምምነት መኖር የማትችል ሀገር ማድረግ ነው ስለራስ አስራተ ካሳ ሴራ እና በሲአይኤ ስለተቀበረው ፈንጂ የሴራው ተባባሪ በነበሩት አቶ ተስፋሚካኤል ጆርጆ የተጻፈው ጽሑፍ ወደፊት ትመጡበታላችሁ እነዚህ ሁለት ጎታች ድርጊቶች ሚስጢራዊ በሆነ መንገድ የተጫወቱት ሚና ህዝባዊ ኃይልታት ወደ አንድ ግንባር ለመለወጥ የተደረገውን ጥረት ገድለውታል በሌላ በኩል ግን በህዝባዊ ኃይልታት ኤርትራ ውስጥ የሚገኙት አንዳንድ ስም ያላቸው መሪዎች ከጀብሃ ጋር የሚደረገውን ጦርነት ለማስቆም ጥረታቸውን አጠናከረው ቀጥለዋል የአስመራ ከተማ ህዝብም እስከ መቼ በካራ ትተራረዳላችሁ። አላቸው ወደ ሙስሊሞቹ ተጠግቶም እነዚህ ከርስቲያኖች ሊያጠፏችሁ ተነስተዋል ከነርሱ ጋር አንዳትወግኑ በማለት መከራቸው ከሌሎች አውራጃዎች በመጡትም ላይ ተመሳሳይ ዘዴ በመጠቀም እንቅስቃሴው የአከለ ጉዛይ ልጆች በአውራጃዊነት ስሜት ያፈነዱት ነው ዓላማቸው ድርጅቱን ማጥፋት ነው ተብሎ እንዲወራ ተደረገ እነ ስብሐት ኤፍሬም እና ጴጥሮስ ሰለሞን የመሳሰሉትን የሐማሴን ልጆችን ደግሞ ኢሳያስ አፍወርቂ ራሱ አየተጠጋቸው መንካዕ የአከለ ጉዛይ ንቅናቄ ስለሆነ በቶሎ እጃችሁን አውጡ አላቸው የንቅናቄው መሪዎች ለእንዲህ ዓይነቱ ቅልበሳ አልተዘጋጁም ነበርና በአንድ ጊዜ የፕሮፓጋንዳ ሰለባ ሆኑ በርግጥም የሰልፊ ነጻነት አመራሮች አንዳሉት ሙሴ ተከለመድህን ዮሐንስ ስብሐቱ ሀብተ ሥላሜ ገብረመድህን ወዘተ የመሳሰሉት የመንካዕ መሪዎች የአከለ ጉዛይ ተወላጆች ነበሩ ስለዚህ መሪዎቹ ይህ የአከለ ጉዛይ ንቅናቄ ነው እያሉ ሲለፍፉ ተራ ታጋዮች በቀላሉ ተታለሉ አብዛኛው ታጋይ አውራጃዊነት የምትለው ነገር ስለረበሸትው ከንቅናቄው አፈገፈገ በተለይ የሰሜን ኤርትራ ተወላጆች ከንቅናቄው ሙሉ በሙሉ እጃቸውን አወጡ እነ ሙሴ ተክለ መድህን አና ዮሐንስ ስብሐቱ በድምጽ ማጉያ ጭምር እየታገዙ ንቅናቄው ከአውራጃዊነት የጸዳ መሆኑን ለማስረዳት ቢሞከሩም አንድም ተከታይ አላገኙም ታሕሳስ ላይ ሁሉም ነገር አበቃ የንቅናቄው መሪዎች በሙሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ እነ ጴጥሮስ ሰለሞን ስብሐት ኤፍሬም እና ኃይሌ ወልደ ትንሳኤም ከመንካዕ መሪዎች ጋር ታሰሩ አንድ ሺህ የሚሆኑ ሌሎች ታጋዮችም ተያዙ ህለዋ ሰውራ የሚባለው የሻዕቢያ የስለላ የምርመራ አና የእስረኞች ጉዳይ ጠቅላይ መምሪያ የመንካዕ መሪዎች ሂሳቸውን አንዲያወርዱ በሚል ለአንድ ዓመት ያህል በግርፋትና በልዩ ልዩ የምርመራ ዘዴዎች ሲያሰቃያቸው ሰነበተ አነ ስብሐት ኤፍሬም ፈጥነው ሂስ በማውረድ በታጋዩ ፊት መንካዕ የአከለ ጉዛይ ልጆች በአውራጃዊነት ስሜት ያካሄዱት ንቅናቄ ነው በማለታቸው ከእስሩና ከስቃዩ ነጻ ወጡ አንድ ሺህ ታጋዮች ደግሞ የስድስት ወራት የተሓድሶ ስልጠና ከተሰጣቸው በኋላ በውጊያ ግንባር እንዲሰለፉ ተደረገ ሙሴ ተስፋ ሚካኤል ዮሐንስ ስብሐቱ ሀብተሥላሜ ገብረ መድህን አፈወርቂ ተከሉ ደበሳይ ገብረ ሥላሜ ዶር ርዕሶም ወልዱ ደሀብ ተስፋጽዮን አበራሽ መልኬ የመሳሰሉት ግን አቋማችንን አንለውጥም ዛሬም ትከከለኞች ነን በማለታቸው ድርጅቱ ባቋቋመው ወታደራዊ ችሎት ፊት ቀረቡ ችሎቱም በሀለዋ ሰውራ ሲሰቃዩ በነበሩ ተራማጅ አብዮተኞች ላይ የሞት ፍርድ ፈረደባቸው ፍርዱ የሚጸድቀው በድርጅቱ የበላይ መሪዎች ስምምነት በመሆኑ ውሳኔው ለመሪዎቹ ቀረበ ከአምስቱ የድርጅቱ መሪዎች መካከል ተወልደ እዮብ እነዚህ ታጋዮች የዲሲፕሊን ጥፋት ነው ያጠፉት በዚያ ሊጠየቁ ይቸላሉ ሆኖም አንድም ወንጀል ሰላልሰሩ በሞት መቀጣት የለባቸውም በማለት አቋሙን ገለጸ እነ ሰለሞን ወልደማሪያምና ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ፍርዱ ትከከል ነው በማለት በድምጽ ብልጫ አጸደቁት በመሆኑም ከአስር የማያንሱ የመንካዕ መሪዎቹና በርካታ ተባባሪዎቻቸው በ መጀመሪያ ላይ በጥይት ተደብድበው ተረሽኑ ድድድቱቴቴ የመንካዕ ንቅናቄ ታሪከ በአጭሩ ይህንን ይመስላል ይህ ንቅናቄ የተቋጨበት መንገድ በየቦታው ሲሰማ እጅግ ከባድ የሆነ ነቀፌታና ውግዘት ገጥሞታል በተለይ በኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ ትልቅ ስም የነበረውና በ እንደ ሐበሻ አቆጣጠር በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ታሪከ ለመጀመሪያ ጊዜ ከትምህርት ገበታ ከተባረሩት ሰባት ተማሪዎች አንዱ የነበረው የዮሐንስ ስብሐቱ አሟሟት የብዙዎችን ልብ አቁስሏል የሚገርመው ታዲያ ይህ በአሳዛኝ ፍጻሜ የተቋጨው ንቅናቄ የተካሄደው የኢህአፓ መስራቾች በህዝባዊ ሓርነት ኃይልታት ቃል በተገባላቸው መሰረት ለወታደራዊ ስልጠና በኤርትራ ምድር በነበሩበት ወቅት ነው ከፍሉ ታደሰ እንደጻፈው የሰልፊ ነጻነት መሪዎች አንቅስቃሴውን የቀለበሱበት አካሄድና በተራማጅ አብዮተኞች ላይ የወሰዱት የቅጣት አርምጃ በስፍራው በነበሩት የኢህአፓ ታጋዮች ላይ የማይሽር የስነልቦና ቀውስ አድርሷል አንዳንድ ታዛቢዎች ደግሞ ለሽምቅ ውጊያ ጫካ የገቡ በርካታ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች ለውስጣዊ ተሃድሶ የሚታገሉ አብዮተኞችን አንጃ ፈጥራቸኋል አያሉ መጨፍለቅን የተማሩት ሻዕቢያሰልፊ ነጻነት የመንካዕ ንቅናቄን ከደመሰሰበት ስልት ነው ይላሉ የመንካዕ ንቅናቄ መሪዎች በተደመሰሱበት ስልት ላይ ፍርድ መስጠት አስቸጋሪ ነው ማርከሳዊ ርፅዮትን የሚከተሉ ፓርቲዎችና ነጻ አውጪ ድርጅቶች በሙሉ ውስጣዊ ንቅናቄንና የሃሳብ ልዩነትን በሀይል ሲጨፈልቁ መኖራቸው የሚታወቅ በመሆኑ የሻዕቢያ አርምጃ ከሌሎች የተለየ ሆኖ የሚታይበት ምከንያት ያለ አይመስለኝም በሀገራችንም ሆነ በአለማችን በደንብ አይተነዋል ሆኖም እንዲህ አይነት ንቅናቄ ከከሸፈ እና እንጀኞቸ ተብለው የተያዙት ከተገደሉ በኋላ የንቅናቄው መሪዎች ንጹሐን ነበሩ እየተባለ የሚነገረው ስላቅ በጣም ያበሸቃል አንዲህ እያሉ የሰውን ልብ የሚቆርጡት ደግሞ የውጪ ተመልካቾች ወይንም ንቅናቄው ሲካሄድ ድጋፍ የሰጡ ሰዎች እንዳይመስሏችሁ እነርሱማ የታሪከ ምስከርነት ነው የሰጡት እንጂ ምንም ጥፋት አላጠፉም ይህንን አናዳጅ ንግግር የሚናገሩት ንቅናቄውን በማዳፈን ሂደት ቀንደኛ ተጠቃሽ የነበሩ ግለሰቦች ናቸው ትላንት ሰውን የመሰለ ከቡር ነገር ሲቀጥፉ ይከርሙና ነገ ደግሞ የወሰድነው እርምጃ ህገወጥ ነው ስህተት ፈጽመናል እያሉ በተቃራኒው አቅጣጫ መቶ ሰማኒያ ዲግሪ ያህል ይገለበጣሉ ለዚህ ቀላሉ ምሳሌ የሻዕቢያው ሰለሞን ወልደማሪያም ነው ሰለሞን የመንካዕ መሪዎችን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ጭጭ ካሰኘ በኋላ እነዚያ ሰዎች ንጹሐን ነበሩ እያለ መደስኮሩ በታሪከ ተመዝግቧል ለመሆኑ የርሱ መጨረሻስ እንዴት ሆነ ወደፊት እናየዋለን በመጨረሻም አንድ የምለው ነገር አለ ይህ ጽሑፍ ታሪከን ከማሳወቅ ውጪ አንድም ዐይነት ፖለቲካዊ ዓላማ የለውም ሆኖም ሚዛናዊ ለመሆን እየሞከርኩኝ ወደ አንድ ጎን ያዘነበልኩ ሳልሆን አልቀረሁም ታዲያ ወደዚያ ያጋደልኩት ፈልጌ አንዳይመስላችሁ በጉዳዩ ዙሪያ ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ከፍተት ስላለ ነው ለምሳሌ የሻዕቢያ አባላትና ደጋፊዎች ስለመንካዕ ንቅናቄ በይፋ አይጽፉም በድርጅቱ የታተሙ መጻሕፍትም ሆነ በደጋፊዎቹ ባለቤትነት ስር ያሉ ድረገጾች ከውስጥ የተነሱ የነጻነትና የትግል ጸሮችን አስወግደናል ከማለት ውጪ ዝርዝር ታሪክ አይጽፉም በዚህም የተነሳ ፓርቲው የአሁኑ ህግዴፍ እና አመራሩ በዝርዝር ታሪኩ ላይ ያላቸውን አቋም ለማወቅ አልተቻለም ምናልባት ይህንን ጽሑፍ የምታነቡ ኤርትራዊያን ካላችሁ ሻዕቢያ በጉዳዩ ዙሪያ ያለውን አቋም ብታስረዱን በደስታ እንቀበላለን ኢትዮጵያዊያን የሆናችሁት ደግሞ ሻዕቢያ የሚለው ስም ስድብ አለመሆኑን ልብ በሉልኝ የሻዕቢያ ደጋፊዎች በዚህ ስም ይኮሩበታል እንጂ አያፍሩበትም የፓርቲው ኦፊሴላዊ ዌብሳይት ራሱ ከከዐየ ተብሎ ነው የሚጠራው ህዳር ድድድቱቴቴ ጀብሃ እና ሻዕቢያ ከፍል አምስት በትናንትናው ጽሑፌ ስለመንካዕ ንቅናቄ ታሪከ አውግቼአችሁ ነበር የዛሬው ጽሑፍ ደግሞ ከመንካዕ በኋላ በሻዕቢያ ውስጥ በታዩ ሁለት መለስተኛ ንቅናቄዎች ላይ ያተኩራል አነዚህ ንቅናቄዎች የመንካዕን ያህል ጥንካሬ አልነበራቸውም ሆኖም ከሻዕቢያ ጋር ሁሌ የሚጠቀሱ በመሆናቸው ልንዳስሳቸው ግድ ይለናልዬ የብጽኣይ እንቅስቃሴ በሻዕቢያ ውስጥ የፈነዳው የመንካዕ ንቅናቄ ከተዳፈነ በኋላ የድርጅቱ ታጋዮች ማጉረምረማቸውን አላቆሙም በተለይ የመንካዕ መሪዎችን የገጠማቸው ሰቆቃ የተመላበት አስርና የሞት ቅጣት ብዙዎቹን አስከፍቷል ሆኖም ታጋዩ አርስ በራሱ ይጠራጠር ስለነበር ድምጹን ከፍ አድርጎ አላሰማም በዕድሜው ጠና ያለ አንድ ታጋይ ግን ድርጅቱ ውስጣዊ ዲሞክራሲ እንዲኖረው አደርጋለሁ በማለት የበኩሉን ጥረት ለማድረግ ተነሳ ያ ታጋይ ገይቶም በርሄ ይባላል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ምሩቅ ነው ሻዕቢያን የተቀላቀለው በ ነው ይህ ሰው ከፍተኛ የሆነ የስነጽሑፍና የርፅዮተ ዓለም ትንታኔ ችሎታ ነበረው በዘመኑ አጅግ በጣም ይፈለጉ የነበሩትን ማርከሳዊና የዲያሌከቲከ ፍልስፍና መጻሕፍትን ከውጪ ቋንቋዎች ወደ ትግርኛ ተርጉሟል እርሱ ራሱ ከጻፋቸው ኦሪጂናል ጽሑፎች መካከል ደግሞ መን እዩ ብፅአዊ። የሚል ርዕስ ያለው ባለ ገጽ መጣጥፍ ከፍተኛ ተቀባይነት አንደነበረው የታሪከ ሰዎች ይናገራሉ ሻዕቢያ የርሱን ጽሑፎች ታጋዩን ለማስተማር ተጠቅሞባቸዋል ይህ ሰው በዕድሜውም ሆነ በተሰጥኦው አንቱታን ያገኘ ስለሆነ ሁሉም ታጋዮች ብጽአይ ጓድ በማለት ነበር የሚጠሩት ብጽአይ ጎይቶም በመንካዕ ንቅናቄ ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ አላደረገም ሆኖም ውጥረቱን አንዲሸመግሉ ከተመረጡ ሽማግሌዎች መካከል አንዱ ነበር እነ ኢሳያስ የመንካዕ መሪዎችን በከባድ ቅጣት ዝም ሲያሰቸው ግን የተሰጠው ፍርድ ኢፍትሓዊ ነው በሚል ተቃውሞ አሰምቷል በዚህም ከሃላፊነት አንዲወርድ ተደርጓል ታዲያ ብፅአይ ጎይቶም ስልጣኔን ተቀማሁ ብሎ ወደ ኩርፊያ አልሄደም ድምጹን አጥፍቶ በድርጅቱ ውስጥ ዲሞከራሲ የሚሰፍነበትን መንገድ ያውጠነጥን ነበር በ መጨረሻ ላይም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩ ጥቂት ጓዶች ግንባሩን ሲቀላቀሉ ከነርሱ ጋር መቀራረብ ጀመረ ከተማሪዎቹ ጋር ባደረገው ውይይትም ድርጅቱን ዲሞከራሲያዊ ማድረግ አለብን የሚል አጀንዳ አስታጠቃቸው አነዚያ ወጣቶቸም የርሱን ሀሳብ ማቀንቀን ጀመሩ በዚህ ነጥብ ዙሪያ ታጋዩን ማወያየትና ድጋፍ ማሰባሰብ ሞከሩ አንዳንዶች ወደነርሱ ተጠጉ ብዙዎቹ ግን የመንካዕ ትውስታ ከአዕምሮአቸው ያልጠፋ በመሆኑ ወደ ብጽአይ ጎይቶምና ጓዶቹ ለመጠጋት አልፈቀዱም እነ ብጽአይ ግን ጥረታቸውን ቀጠሉ በርካታ የቀድሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድጋፍ ሰጡአቸው ሆኖም ዓላማቸውን በሚያስፈጽመበት መንገድ ላይ በመምከር ላይ ሳሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ የስለላ መረቡን በሁሉም የሻዕቢያ ታጋዮች ላይ እንደ ሸረሪት ድር ያደራው የህላዋ ሰውራ አዳኞች በቀላሉ ቀጨም አደረጓቸው የንቅናቄው መሪዎችና ተባባሪዎች የተባሉት በሙሱ እየተፈለጉ ታሰሩ የሀለዋ ሰውራ ኃላፊዎች ብጽአይ ጎይቶምንና ጓዶቹን ለአራት ዓመታት በአስር ካቆዩአቸው በኋላ በ በሞት ቀጡአቸው ብጽአይ ጎይቶም የተረጎማቸው መጻሕፍትና በራሪ ወረቀቶችም ከያሉበት አየተሰበሰቡ ተቃጠሉ በጎይቶም ጽሑፎች የተበላሸውን የታጋይ አዕምሮ ለማደስ በሚልም ስታሊናዊ የሶሻሊዝም ፍልስፍና ድርሰቶች በብዛት አንዲተረጎሙ ተደረጉ የትርጉም ስራውን በዋናነት ያከናወነው በ ገደማ በኢትዮጵያ የኤርትራ አምባሳደር የነበረውና አሁን በሱዳን የተባበሩት መንግሥታት ልዩ መልዕከተኛ ሆኖ የሚያገለግለው ሀይሌ መንቆርዮስ አንደሆነ ይነገራል ድድድቱቴቴ ይህ ብዙ ሳይራመድ በአንጭጩ የተቀጨው ንቅናቄ ብፅአይ ምንቀስቓስ ይባላል የጓዱ አንቅስቃሴ ማለት ነው ጓድ ወይንም ብፅአይ ተብሎ የሚጠራው ጎይቶም በርሄ ነው ከርሱ ጋር በቅርበት ሆኖ እንቅስቃሴውን መርቷል የሚባለው ደግሞ ዓለም አብርሃ የተባለ ታጋይ ነው እነዚህ ጓዶች አንደ መንካዕ ንቅናቄ መሪዎች የድርጅቱ አመራር ከስልጣን ይውረድልን አላሉም በድርጅቱ ውስጥ ዲሞከራሲ እንዲሰፍን ለመጠየቅ ብቻ ነበር የተነሱት ሆኖም የሰልፊ ነጻነት መሪዎች በአንቅስቃሴው አልተደሰቱም እንዲያውም የድርጅቱን ህልውና የሚያናጋ መናፍቃዊ ንቅናቄ አድርገው ነው የወሰዱት ሻዕቢያዎች የብፅአይ ምንቅስቃስ መሪዎች የኤርትራ አብዮታዊ ፓርቲ በከኮ የተባለ ህገወጥ ፓርቲ በግንባሩ ውስጥ አቋቁመዋል የታወቀውን የግንባሩን ሶቪየት ቀመስ የርዕዮተ ዓለም አቅጣጫ በመቀልበስ የሊቀመንበር ማኦ ዜዱንግን መስመር ለማስፈን ሞከረዋል በመሆኑም የሞት ቅጣት መፈጸሙ በግንባሩ ህግ መሰረት ተገቢ ነው ይላሉ ሆኖም ይህ የኤርትራ አብዮታዊ ፓርቲ የተሰኘ ፓርቲ በግንባሩ ውስጥ ስለመፈጠሩ ለማረጋገጥ አልተቻለም በዚህ ንቅናቄ ጦስ ታስረው ህይወታቸው ካለፈው ታጋዮች መካከል ጎይቶም በርሄ ብፅአይገ ዓለም አብረሃ መሲህ ርፅሶም ተከላይ ገብረ ከርስቶስ ሚካኤል በረከተአብ ሀይሌ ዮሐንሶም ሳሙኤል ገብረ ድንግል በረከት ሀይሌ ሀይሌ ሀብተጽዮን እና ሌሎችም ይገኙባቸዋል ተወልደ እዮብ የሚባለው የቀድሞው የድርጅቱ ቁልፍ ሰውም ከነዚህ ሴረኞች ጋር አብረሃል በሚል በጥይት ተደብድቦ ተረሸኗል እነዚህ ታጋዮች የተረሸኑት በ ሳሕል በረሃ ውስጥ በሚገኘው አራግ በተሰኘ ቀበሌ ነው የኖማናዊ ቀኝ መንገደኞች እንቅስቃሴ ይህኛው እንቅስቃሴ የብጽዓይ ንቅናቄ ተከታይ ሆኖ ነው የፈነዳው ንቅናቄው የተካሄደው ሰልፊ ነጻነት እና ህዝባዊ ሀይሊ በይፋ ተዋህደው ህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ የተሰኘውን ግንባር መፍጠራቸው ከተነገረበት ጊዜ ትንሽ ቀደም ብሎ ነው በተጨማሪም በዚያ በወቅት በ ብዙዎቹ የኤርትራ ከተሞች ከመንግሥት እጅ በመውጣት በሻዕቢያ እና ጀብሃ ቁጥጥር ስር ገብተው ነበር በዚህ ንቅናቄ ገፍቶ የወጣው ዋነኛ ጥያቄ በግንባሩ ውስጥ እየተስፋፋ የመጣው ሙስናና ብልሹ አሰራር ይወገድ የሚል ነው ይሁንና የዚህ ንቅናቄ ጀማሪ ማን አንደሆነ በትከከል አይታወቅም በንቅናቄው ውስጥ ከተሳተፉት ግንባር ቀደም መሪዎች መካከል ዶር እዮብ ገብረልዑል መሓሪ ግርማጽዮን ገብረሚካኤል መሐራእዝጊ ህብረት ተስፋጋብር ኪዳኔ አቤቶ ፍሥሐዬ ኪዳኔ አርአያ ሰመረ አማኑኤል ፊላንሳ የተባሱት ይጠቀሳሉ ብዙዎቹ በአውሮጳ ሀገራት የተማሩ ናቸው የሻዕቢያ መሪዎች በንቅናቄው የተሳተፉ ታጋዮችን የቀይ መንገደኛነት ፈለግ ተከታዮች በማለት ይጠሯቸዋል እነዚያ የንቅናቄ መሪዎች ጥያቄዎቻቸውን ለሻዕቢያ አመራር ባቀረቡ ማግስት ነው የታሰሩት ታዲያ ንቅናቄው ከተዳፈነና ሻዕቢያ አንደኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን ካካሄደ በኋላ የቀድሞ የግንባሩ ቀንደኛ መሪ እና የሀለዋ ሰውራ ዋና ጸሓፊ የነበረው ሰለሞን ወልደማሪያምም ከንቅናቄው ጋር ንከኪ አለው ተብሎ በቁጥጥር ስር ውሏል የግንባሩ ዋነኛ መርማሪ የነበረው ሀይሌ ጀብሃም በዚያው ወቅት አንዲታሰር ተደርጓል ሀይሌ ጀብሃ የታሰረው በአስረኞች ላይ ከመጠኑ ያለፈ ኢሰብአዊ ሰቆቃ ይፈጽማል በሚል ምከንያት ነው በርግጥም በርካታ ኤርትራዊያን ስለርሱ ጭካኔና ገዳይነት በሰፊው ጽፈዋል ለምሳሌ እውቁ ኤርትራዊ ምሁር ዶር በረከት ሀብተስላሴ በቅርቡ ከአንድ ድረገጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሀይሌ ጀብሃ አንዱን አስረኛ በብትር ጭንቅላቱን እየቀጠቀጠ ሲመረምረው ማየታቸውን መስከረዋል ሰለሞን ወልደማሪያም የታሰረበት ምከንያት ግን ከዚህ የተለየ ነው ሰለሞን ወልደማሪያም በግንባሩ ውስጥ የነበረው ተፈላጊነት እየቀነሰ መምጣቱን የሚያሳዩ ምልከቶች የታዩት ቀደም ብለው ነው ለምሳሌ በ መጨረሻ ላይ ለህከምና ፖርት ሱዳን ደርሶ ከተመለሰ በኋላ ቁልፍ ከሆኑ የድርጅቱ የስልጣን ቦታዎች ተገፍቶ የካድሬ ትምህርት ቤት አሰልጣኝ እንዲሆን ተመድቧል የሀለዋ ሰውራ ዋና ጸሓፊነቱንም ከህዝባዊ ሀይሊ ለመጣው ዓሊ ሰዒድ አብደላ አስረከቧል አርሱ ግን የድርጅቱ ጉባኤ እስኪካሄድ ድረስ የግንባሩ መሪዎች ይከዱኛል የሚል ጥርጣሬ አልነበረውም ለሰለሞን ሁሉም ነገር ፍንትው ብሎ የታየው አባላት ያሉት የማዕከላዊ ኮሚቴ ምርጫ በተካሄደበት ወቅት ነው በዚያ ምርጫ ላይ ሰለሞን በአጩነት ሲጠቆም ካድሬው በከፍተኛ ጩኸት ተቃውሞውን እንደገለጸ ይወሳል አንዳንድ ካድሬዎች ከመቀመጫቸው እየተነሱ ህ ሰው የቀኝ መንገደኞቹ አንጃ መሪ ነው ለርሱ አስር ቤት እንጂ ስልጣን አይገባውም የሚል ሐሳብ መስጠታቸው ተመዝግቧል በዚህም ሳቢያ ከኢሳያስ አፈወርቂ በፊት ወደ ዓላ በረሃ ሄዶ ከጥቂት ወጣቶች ጋር ሰልፊ ነጻነት የተባለውን ቡድን የመሰረተው ሰለሞን ወልደማሪያም አዛዥ ናዛዥ ሆኖ ብዙዎችን ካንቀጠቀጠበት መንበረ ስልጣን ላይ ተገፍትሮ ወደታች ተወርውሯል ኢሳያስ አፈወርቂ ሰለሞንን ከስልጣኑ ያስነሳው ይህ ወጣት በድርጅቱ ውስጥ ቁልፍ የሆኑ ቦታዎችን በመዳፉ ጠቅልሎ በመያዙ ወደፊት ከሊቀመንበርነቴ ያባረኛል የሚል ስጋት ስለገባው መሆኑን ታሪኩን የሚያውቁ ምስከሮች ያስረዳሉ በርግጥም ሰለሞን በሰልፊ ነጻነት ውስጥ ፈላጭ ቆራጭ ሰው ነበር ኢሳያስ አፈወርቂ የቡድኑ መሪ ሆኖ ቢቀመጥም ድርጅቱን በቀጥታ የሚመራው ሰለሞን ወልደማሪያም ነበር በወቅቱ የድርጅቱ አባል የነበሩት አቶ አድሓኖም ፍትዊ የተባሉ ኤርትራዊ በጊዜው የነበረውን የስልጣን ከፍፍል ሲያስረዱ ሰለሞን ሁሉንም ነገር ነበር የሀለዋ ሰውራ ዋና ጸሐፊ ነው ወታደራዊ አዛዥም ነው የስልጠና ማዕከል ሀላፊም ነው የጠቅላይ እዙ የበላይ አዛዥም ነበር በግንባር ያለውን ጦር የሚያንቀሳቅሰው እርሱ ነው ኢሳያስ አፈወርቂ ለስም ብቻ ነው ሊቀመንበር ሆኖ የተቀመጠው በማለት አስረድተዋል ታዲያ ኢሳያስ ሰለሞንን ከስልጣን ያስነሳው ብልጠት በተመላበት ዘዴ ነው ሰለሞን ለረጅም ጊዜ የጉበት በሽተኛ እንደሆነ ስለሚታወቅ እስከዛሬ ድረስ ለኛ ስትል ደከመሃል አሁን ግን መታከም አለብህ ህከምና አያለ መሞት የለብህም ሱዳን ሄደህ ከፍተኛ ሐኪም መጎብኘት አለብህ አለው በተጨማሪም ኡሥማን ሳልህ ሳቤ የድርጅታችንን የእርዳታ መስመር ስለዘጋብን ወደ ውጪ ሄደህ እርሱንም ማስከፈት አለብህ ይህንን ማድረግ የምትቸለው አንተ ብቻ ነህ በማለት አከለበት ሰለሞን የኢሳያስን ምከር ሲሰማ በልቡ ኩራት ተሰማው ለካስ እንዲህ ዓይነት ትልቅና ተፈላጊ ሰው ኑሬአለሁ። ካላወቃቸኋችሁ እኝሁላችሁ ረመዳን መሐመድ ኑር ዋና ጸሓፊ ኢሳያስ አፈወርቂ ምከትል ዋና ጸሓፊ ዓሊ ሰዒድ አብደላ ዑቅበ አብረሃ ስብሐት ኤፍሬም ሀይሌ ወልደ ትንሳኤ ጴጥሮስ ሰለሞን ሙሐመድ ሰዒድ በርሄ መስፍን ሐጎስ ኢብራሂም አፋ አልአሚን መሀመድ ብርሃነ ገብረ እግዚአብሄር ማሕሙድ አሕመድ ሸሪፎ ናቸው ከዝርዝሩ አንደምታዩት ለፖሊት ቢሮ አባልነት ሰባት ደገኛ ከርስቲያኖች እና ስድስት ቆለኛ ሙስሊሞች ተመርጠዋል ከፖሊት ቢሮው በላይ ባለው የማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥም አስራ ዘጠኝ ደገኞች እና አስራ ስምንት ቆለኞች ነበሩ የግንባሩ ፖሊት ቢሮ የኤርትራ ህዝብን ሀይማኖታዊ ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ የተዋቀረ ይመስላል በኤርትራ የከርስትያኑና የሙስሊሙ ብዛት ተቀራራቢ ነው የግንባሩ አባላት ግን በአብዛኛው ከርስቲያኖች ነበሩ ነገሩን ያጠኑ ምሁራን እንደሚሉት በፖሊት ቢሮው ውስጥ የከርስቲያን እና የሙስሊሙን ቁጥር ማመጣጠን ያስፈለገው በልዩ ልዩ ምከንያቶች ነው ከነዚህም ምክንያቶች አንደኛው ጀብሃ ቆለኞቸን ብቻ በአመራር ላይ በመሰየም ደገኞችን አያስከፋ ሲፈጽመው የነበረውን ታሪካዊ ስህተት ላለመድገም በሚል ነው ሁለተኛው ደግሞ እነ ዑስማን ሳልህ ሳቤ ከጀብሃ ተገንጥለው ህዝባዊ ኃይልታትን ለመመስረት የተጫወቱትን ሚና ላለመርሳት ሲባል ነው ሶስተኛው ምከንያት የሻዕቢያ ህዝባዊ ግንባር ደጋፊ ከሆኑ የዐረብ ሀገራት በተለይ ሱዳን በግንባሩ ውስጥ የሙስሊሙ ውከልና አንሷል የሚል ጥያቄ አንዳይቀርብ ለመከላከል በሚል ነው የተወሰኑ ጸሐፍት ግን በዚህ የፖሊት ቢሮ አወቃቀር ላይ የተለየ አመለካከት አላቸው ለምሳሌ የተገንጣዮችና እና የሲአይኤ ግንኙነት የሚለውን ታሪካዊ ጽሑፍ የጻፉት አቶ ተስፋሚካኤል ጆርጆ በጽሁፋቸው ኢሳያስ ተንኮሉን አይተውምና በቡድኑ ውስጥ ደገኞች በብዛት አንዲመረጡ ያደረገው ድምጽ እንዲበዛለት ፈልጎ ነው ይላሉ የምጽዋ ስፖዚየም ጥር ገጽ ሆኖም ይህ የአቶ ተስፋሚካኤል እይታ ትከክል አልመሰለኝም ህዝባዊ ግንባር የሚባለው ድርጅት በጉባኤ ከታወጀበት ከ ጀምሮ ለኢሳያስ ከደገኞቹ ይልቅ ቆለኞች ናቸው የሚቀርቡበት እጅግ ጥብቅ የሆነ ታማኝነት በሚፈልጉ ቦታዎች ላይ የተቀመጡትም ቆለኞች ነበሩ ለምሳሌ ዓሊ ሰዒድ አብደላ ለረጅም ዓመታት ከ የሀለዋ ሰውራ ዋና ጸሐፊ ነበር ኢብራሂም አፋ ደግሞ የወታደራዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር ነው ከነዚህ የሻዕቢያ መሪዎች መካከል ሶስቱ በህይወት የሉም ሻዕቢያ የጀግኖች ጀግና እያለ የሚያሞካሸው ኢብራሂም አፋ በ ከረን አቅራቢያ በተደረገ አንድ ውጊያ ላይ ሞቷል ብዙዎች ኢሳያስ ራሱ ነው ያስገደለው በማለት ቢጽፉም ከነጻ ምንጭ ለማረጋገጥ አልተቻለም ዓሊ ሰዒድ አብደላ ደግሞ ከ እስከ ድረስ የኤርትራ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኖ ካገለገለ በኋላ ሞቷል መሐመድ ሰዒድ በርሄም የትራንስፖርት ሚኒስትር ሆኖ ካገለገለ በኋላ በ አርፏል ማሕሙድ አሕመድ ሸሪፎ ሀይሌ ወልደ ትንሳኤ ብርሃነ ገብረ እግዚአብሄር ጴጥሮስ ሰለሞን እና ዑቅበ አብርሃ ደግሞ ር የሚባለው ቡድን ቀንደኛ መሪዎች ናቸው ተብለው ከታሰሩ ዓመት ሆኖአቸዋል መስፍን ሐጎስ አንዳግጣሚ ውጪ ሀገር ስለነበር ከአስሩ አምልጧል ረመዳን መሐመድ ኑር ከፖለቲካው ዓለም ራሱን አግልሏል በአሁኑ ወቅት ከኢሳያስ ጋር በስልጣን ላይ ያሉት ስብሐት ኤፍሬም እና አልአሚን መሐመድ ብቻ ናቸው ስብሐት የመከላከያ ሚኒስትር አልአሚን የህግዴፍ ዋና ጸሐፊ ናቸው እነዚያ ታላላቅ የሻዕቢያ ሰዎች የሚባሉት ለእስር ሊዳረጉ የበቁት አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ የኤርትራን ህገመንግሥት በአስቸኳይ በስራ ላይ አንዲያውሉ ፔቲሽን በመፈራረም ስለጠየቁ ነው ፕሬዚዳንቱ ሁለት ጊዜ ያህል ተው አየተሳሳታቸሁ ነው እረፉ በማለት ከመለሰላቸው በኋላ በመስከረም ወር በቁጥጥር ስር እንዲዉሉ በማዘዝ ወደ እስር ቤት ወርውሮአቸዋል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያሉበት ሁኔታ በትከከል አይታወቅም ድድድቱቴቴ ሻዕቢያ የመጀመሪያ ጉባኤውን ያካሄደው በምስራቅና ሰሜን ኤርትራ የሚገኙትን ከረን ደቀምሐረ ጊንዳእ ሰንአፌ ሐሙሲት የመሳሰሉ ከተሞችን በተቆጣጠረ ማግስት ነው ሆኖም ከሁለት ዓመታት በኋላ ከናቅፋ በስተቀር ሁሉንም ከተሞች መልቀቅ ግድ ሆኖበታል ጀብሃም በወቅቱ በምዕራብ ኤርትራ የሚገኙትን መንደፈራ አዲኳላ ተሰነይ አቆርዳትና ባርካን ተቆጣጥሯል ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ጠንካራ ማጥቃት ሲሰነዝርበት ግን ከተሞቹን በሙሉ ለቅቋል ሻዕቢያ የደርግ ጦርን ጥንካሬ ከመዘነ በኋላ በጊዜው በነበረው አቅም የማይመልሰው መሆኑን ስለተረዳ የተፈጥሮ መከላከያው ወደሆነው የሳህል በረሃ ገብቶ መደበቅን ነው የመረጠው ጀብሃ ግን በጀብደኝነት ከደርግ ጦር ጋር ሲዋጋ ሀይሉን አስጨርሷል ብእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አንዲሉም የኔ ደጀን ነው ብሎ የተማመነበት የባርካ ቆላማ አውራጃም በደርግ ሰራዊት ተይዞበታል ስለዚህ ለጊዜው ማምለጫ ከሆነኝ በሚል የሻዕቢያ አምባ በሆነው የሳሕል ተራራ ውስጥ ራሱን ለመደበቅ ሞክሯል ሁለቱ ግንባሮች የርስ በርስ መተላለቁን በ በመጣባቸው የህዝብ ግፊት አቁመው ስለነበር ሻዕቢያ ከደርግ ሸሽቶ በመጣው የጀብሃ ሰራዊት ላይ ብረት አላነሳም እየዋለ ሲያድር ግን የድሮው ቂም አገረሸባቸው ሻዕቢያ ባርካን አስረከበህ ሳሕልን ልትይዝ መጣህ እንዴ። ርክካከፎየ የተሰኘው የፍልስጥኤም ነጻ አውጭ ድርጅት ቦህ ቡድን በየኤምባሲዎቻቸው የቦምብ ናዳ በማዝነብ ተቃውሞውን ይገልጽ ስለነበር አሥመራና ጉራዕ የሚገኙትን ጣቢያዎቻቸውን ያጠቃብናል የሚል ስጋት ነበረባቸው ሁኔታዎች በዚህ ደረጃ ላይ በነበሩበት ወቅት ነበር እነ ኢሳያስ አፈወርቂ ግኑኝነታቸውን ከአሜሪካኖች ጋር የጀመሩት በአንጻሩ ደግሞ በዚያን ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት የኤርትራን ከሀገር ችግር ለመፍታት የሚል ሙከራ በማድረግ ላይ ነበር እንዲያውም ጥቅምት ቀን ዓም በአሥመራ ውስጥ የኤርትራ ከሀገር መኳንንት የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎች በተገኙበት የኤርትራ ከሀገር የሰላም ጉባኤ በሚል ስያሜ አንድ ቋሚ ኮሚቴና ቋሚ ሊቀ መንበር ያለበት ቡድን ተቋቋመ ዓላማውም የኤርትራ ከሀገር ጉዳይ መፍትሔ እንዲያገኝ በመንግሥትና በተገንጣዮች መካከል የነበረውን የወታደራዊ እንቅስቃሴ ለማቆም በአመቺ ቦታና ጊዜ ተገናኝቶ ለመነጋገር ነበር ይህንንም ምከንያት በማድረግ የዚህ የተጠቀሰው ቋሚ ኮሚቴ ሊቀ መገበር የነበሩት ደጃዝማች ገብረዮሃንስ ተስፋማርያም የፈረሙበት የሰላም ጥሪ ደብዳቤ በዑመር ሐንገለና በሌሎች አማካይነት ለተገንጣዮች እንዲደርስ ተደረገ መልሱም ከተጋድሎ ሐርነት ኤርትራ መጠሐሠ ኤርትራ ከሜዳ በማለት በ ኢኤአ የተጻፈ ደብዳቤ ከልጆቻችሁ ሓሳብ ለሓሳብ ለመለዋወጥ ባስቸኳይ በፈለጋችሁበት ቀን ከቡርነትዎ በወሰኑት ቦታ በአከብሮት አንጠባበቃለን የሚል ደብዳቤ አብርሃም ተወልደና ሰሎሞን ወማርያም በተባሉት ግለሰቦች ተፈርሞ መጣ በዚህም መሠረት ከተገንጣይ ቡድን መሪዎች ጋር ለመነጋገርና ለመደራደር በደጃዝማች ገብረኪዳን ተሰማ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ ዳኛ ሰብሳቢነት ሌተና ኮሎኔል ገብረአግዚአብሔር መሐረና የኤርትራ ከፍለ ሀገር ፖሊስ ምከትል ኮሚሽነርና እኔ ራሴ ተስፋሚካኤል ጆርጆ በአባልነት ያለንበት ኮሚቴ ሕዳር ቀን ዓም ተቋቋመ አኔ በዚያን ወቅት የደቀመሐረ ወረዳ ገዢ ነበርኩ ይህ ኮሚቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ሕዳር ቀን ዓም ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ ታሕሳስ ቀን ዓም ተገንጣዮች ወደሚገኙበት ወደ ዓላ በረሃ ሄዶ ነበር ነገር ግን የተገንጣይ ቡድን መሪዎቹ በኋላቀር አስተሳሰብና በሥልጣን ሽሚያ ምክንያት በመለያየታቸው በአንድነት ጉዳያቸውን ለማቅረብ አልቻሉም በመሆኑም ኮሚቴው መገናኘትና መነጋገር የቻለው ከከርስቲያኑ ተገንጣይ ቡድን ጋር ብቻ ነበር ከኮሚቴው ጋር ቀርበው የተነጋገሩት የቡድኑ ቀንደኛ መሪዎችም አብርሃም ተወልደ ኢሳያስ አፈወርቂ ሰለሞን ወማርያም ሀብተስላሴ ገመድህን ወሚካኤል ሃይለ በራኺ ንጉሠና ሌሎቸም ነበሩ ያቀረቡትም ሐሳብ እኛ ከእስላሞች ተለያይተናልና እነሱን መውጋት አንድንቸል ከመንግሥት ማቴሪያላዊና ሞራላዊ እርዳታ ይሰጠን የሚል ነበር ኮሚቴውም መንግሥት በዜጎቹ መካከል የሃይማኖት ልዩነት አንደማይፈጥርና ጥያቄአቸውም ተቀባይነት እንደሌለው በመግለጽ በበኩላቸው አጃቸውን ለመስጠት ዝግጁ ከሆኑ ግን መንግሥት እንደሚቀበላቸው ገለጸላቸው ይህም በወንጀል መዝገብ ቁ መከላከያ ምስከር ሌኮሎኔል ገብረአግዚአብሔር መሐረና በሚለው በገጽ ላይ ሰፍረዋል ተገንጣዮቹም ቁጥራችን ከፍተኛ ስለሆነ ተሰባስበንና ተመካከረን አጃችንን እስከምንሰጥ የቀሩት እንደኛ የመሰሱት ወንድሞቻችን አደጋ ላይ እንዳይወድቁ የተነጋገርንባቸው ጉዳዮች ይዘትና የመገናኘቱም ጉዳይ በከፍተኛ ምስጢር አእንዲጠበቅልን ስላሉና ይህም ሀሳባቸው ተቀባይነት ስላገኘ የሚሰበሰቡበት ቦታና ጊዜ ተወሰነ ይሄም በወንጀል መዝገብ ቁ በደጃዝማች ተስፋዮሐንስ በርሄ ምአንደራሴ የቀረበ የመካላከል ምስከር በሚለው ገጽ ላይ ሰፍረዋል ኮሚቴው ይህንን ሁሉ እንደተለመደው ለመንግሥት አቀረበ ነገር ግን በምስጢር ይጠበቅልን ብለው ቃል ያስገቡን ጉዳይ ሊከበርላቸው አልቻለም ምከንያቱም በዚያን ጊዜ በአሜሪካና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ምሥጢራዊ መረጃዎችን በመለዋወጥ በኩል እርከካዩ ርዐክስርክ ከርቪጠበክ የነበረው ስምምነት ጠንካራ በመሆኑ ኮሚቴው በምስጢር ያቀረበው ሪፖርት ሁሉ አሜሪካኖቹ እጅ ወደቀ አነሱም አሜሪካኖች በበኩላቸው ከዚያ በኋላ ሰልፊ ነጻነት በሚል ስያሜ ተቋቋሞ የነበረውን የኢሳያስ ቡድን ለመገናኘት ለብቻቸው ሩጫ ጀመሩበዚህ ዓይነት አሜሪካኖቹ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊገናኙና ሊነጋገሩ የቻሉት ሀብተሥላሴ ገመድህን ከተባለውና ከሰልፊ ነጻነት ተገንጣይ ቡድን መሪዎች መካከል አንደኛው ከነበረው ግለሰብ ጋር ነበር ንግግሩም የተደረገው አኔ ራሴ በተገኘሁበት በቃኘው ጣቢያ ግቢ ውስጥ ሪቻርድ ኮፕላንድ ከሚባለው ችግኝ ተከላ ፕሮጀከት በሚል ሽፋን ከብዙ ሰዎች ጋር እየተገናኘ ስለላ በሰፊው ያካሄድ ከነበረው አሜሪካዊ ጋር ነበር ሪቻርድ ኮፕላንድ ከሀብተሥላሴ ጋር ባደረገው የሀሳብ ልውውጥ ተገንጣይ ቡድኖቹ በአሜሪካኖች ላይ የቱን ያህል ከፍ ያለ ጥላቻና ቅያሜ አንደነበራቸው መረዳት ቻለ አድሃሪውን የሃይለስላሴ መንግሥት አቅፈው በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ሕዝብ በተለይ በኤርትራ ከፍለ ሀገር ሕዝብ ላይ ያደርሱ የነበረውን ጭቆና በመዘርዘር የቱን ያህል እንዳስቆጣቸው ሀብተስላሴ በግልጽ አስረዳው ኮፕላንድ ይህ ሁኔታ አሜሪካኖቹ ከመጀመሪያ ጀምሮ ይፈሩት የነበረውን ቅዋሜና ወታደራዊ ጥቃት በቃኘሃውና በጉራዕ ጣቢያዎቻቸው ላይ ወደፊትም በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ባላቸው የረጅም ጊዜ ፖሊሲ ላይ ከፍተኛ ከስረት ሊያደርሱ የሚቸሉ መሆናቸውን ለመረዳት ቻሰ ስለሆነም ከተገንጣይ ቡድኖች ዋና ዋና መሪዎች ጋር እንዲያገናኘውና የጋራ ስምምነት ለመቀየስ አንዲቻል ያደርግ ዘንድ ሀብተሥላሴን ጠየቀ ከዚህ ውይይት በኋላ ሀብተሥላሴ ከቃኘው ጣቢያ ጓደኞቹ ወደነበሩበት ወደ ዓላ በረሃ ተመልሶ ሄደ ሃብተሥሳሌም የሰልፊ ነጻነት የበላይ መሪዎች ከነበሩት ከአብርሃ ተወልደና ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ስለ ጉዳዩ ከተወያየበት በኋላ ወደ ደቀምሐረ ከተማ ተመልሶ አሜሪካኖቹ ከዋና ዋናዎቹ የሠልፊ ነጻነት መሪዎች ጋር ሊነጋገሩ የሚችሉበትን አጀንዳ እንዲያዘጋጅ ታዘዘ ከአሜሪካኖቹ ጋርም የግንኙነት ቀጠሮ አደረገ በቀጠሮው መሠረትም ሪቻርድ ኮፕላንድ ደቀምሐረ ሲመጣ ጓደኛው የነበረውን ሪቻርድ ሲወልንና አንድ ትልቅ የጦር መሣሪያ ካታሎግ ይዞ መጣ በወቅቱ በተደረገው ውይይት አሜሪካኖቹ በመጀመሪያ ደረጃ ለማወቅ የፈለጉት ተገንጣዮቹ የጦር መሣሪያ የሚያገኙበትን ምንጭና የንቅናቄአቸውን የውጭ ደጋፊ ሃይላት ነበር ሀብተሥላሴንም በመጀመሪያ የጠየቁት ምን ዓይነት ጠመንጃና ሌላ መሣሪያ እንዳላቸው ነበር እሱ ደቀምሐረ ይዞት መጥቶ የነበረውንም ከላሽንኮቭ አውቶማቲከ መሣሪያ ተውሰው ቃኘው ጣቢያ ከወሰዱ በኋላ ፎቶግራፍ አንስተውና መርምረው መለሱለት አሜሪካውያኑ በተጨማሪም የተገንጣይ ቡድኑ ዋና ዋና መሪዎች ስለቡድናቸው አጠቃላይ ፖሊሲ ከጀብሃ ጋር ስላላቸው ቅራኔ ለጀብሃ ሶሻሊስት አገሮች በፍልስጥኤም ነፃ አውጪ ድርጅት በኩል በእጅ አዙር እርዳታ አንደሚሰጡና ሰልፊ ነጻነት ከአሜሪካ ጋር ለማድረግ የሚፈልገውን ግንኙነት የሚገልጽ ኦፊሴላዊ ደብዳቤ በጊዜው የቃኘው ጣቢያ አዛዥ ለነበረው ኮሎኔል ማሙዘር እንዲጽፉ ያደርግ ዘንድ ሀብተሥላሴን ጠየቁት በዚህ መሠረት ደብዳቤው በመሪዎቹ ተረቅቆና ተዘጋጅቶ በፖስታ ቤት እንዲላክ ተደረገ በደብዳቤው ውስጥ የሰፈሩት ዋና ዋና ነጥቦችም ኛ በዓላ በረሃ የሚገኙት ታጋዮች ከርስቲያን በመሆናቸው ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካና የመሣሪያ ርዳታ ከዓረብ መንግሥትና ከሶሻሊስት አገሮች በእጅ አዙር በሚያገኘው የጀብሐ ቡድን በየቀኑ የሚገደሉና የሚታረዱ መሆናቸውን ኛ ጀብሃ የያዘቸው ፖለቲካ ጭልጥ ያለ የሃይማኖት ይዘት ያለውና የአስራኤልና የአሜሪካ ዓይነተኛ ጠላት ከሆኑት የአረብ ሀገሮች ጋር ፖሊሲው የተዛመደ መሆኑን የሰልፊ ነጻነት ቡድን ዋና ዓላማ ግን ተራማጅና ዲሞከራቲከ እንቅስቃሴ ለማካሄድ መሆኑን የሚገልጽና አሜሪካም የሚያስፈልገውን አርዳታ አንድትሰጣቸው የሚማፀን ነበር ይህ ደብዳቤ በ ቁ ማህደር ቁ ሀሠ በእንግሊዝኛ ጽሑፍ ሰፍሮ ይገኛል በዚሁ ወቅት ይኸው ተገንጣይ ቡድን ተመሳሳይ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ቆንስልም በአስመራ የአሜሪካ ቆንስላ ጽቤት መሆኑ ነው ጽፎ ነበር የደብዳቤውም ዋና ይዘት ባጭሩ ጐሚኒስቶች እስላሞችን ስለሚረዱ እናንተ ምዕራባዊያን ደግሞ እኛን ልትረዱ ይገባል የሚል ነበር ይህ ደብዳቤ የተጻፈው እንደ አውሮጳ አቆጣጠር በ ሲሆን ቆንስላው ደብዳቤውን የኤርትራ ከሀገር ምከትል እንደራሴ ለነበሩት ለደጀተስፋዮሐንስ በርሄ ሚያዝያ ዓም አስረከበዋል ይህም በመዝገብ ቁሀ ደብዳቤ ቁጥር ሰኔ ቀን ዓም ተጠቅሶ ይገኛል በተጨማሪም መንግሥቱ ባይሩ ዑቅቢት በተባለው ግለሰብ አማካይነት ከሌላ ካልታወቀ የውጭ አገር ሃይል ተመሳሳይ ዕርዳታ ለነ አብርሃ ተወልደና ለነ ኢሳያስ አፈወርቂ የሚገኝበት መንገድ ተቀይሶ እንደነበረና ከተባሉትም የውጭ ሀገር ሰዎች ጋር አገናኝቷቸው እንደ ነበረ ሃብተሥላሴ ገብረመድህን ተማርኮ በነበረበት ጊዜ በሰጠው ቃል አረጋግጡዋል ይኸም በመዝገብ ቁ ሀሰዐ ደብዳቤ ቁ አሥመራ ሰኔ ዓም ተጠቅሶአል አሜሪካኖቹም በበኩላቸው የመጣላቸውን ደብዳቤ በደስታ ተቀበሉት ከዚያም በኋላ የቡድኑ መሪ የሆነው ኢሳያስ አፈወርቂ ራሱ መጥቶ ከአሜሪካኖቹ ጋር እንዲነጋገር ቀጠሮ ተደረገ በተባለውም ቀን እኔ ራሴ በማሽከረክረው የመንግሥት ላንድሮቨር መኪና ከደቀምሐረ ዓላ በረሃ ድረስ ሔጄ ኢሳያስን ወደ አሥመራ ይዥው መጣሁ በአሥመራ ከተማ ውስጥም ለሁለት ሰዓት ያህል በመኪናው ሳንሸራሽረው ቆይቼ በቀጠሮው ሰዓት ቃኘው ጣቢያ ወሰድሁት አሜሪካኖቹም የሴኩሪቲ ችግር እንዳይፈጠር ብለው ውይይቱ ሚስተር ቦውሊንግ በተባለው የቃኘው ጣቢያ ሴንትራል ኢንተሊጀንስ ዲፓርትመንት ባልደረባ መኖሪያ ቤት ማለትም ቅዱስ ፍራንሲስኮ ካቴድራል አጠገብ ተካሄደ በአሜሪካኖቹ በኩል ከሪቻርድ ኮፕሊንግ ጋር ሌሎች ሶስት የሚሆኑ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ነበሩ በንግግሩ ወቅት ኢሳያስ ካነሳቸው ነጥቦች መካከል የአሜሪካ መንግሥት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመመሳጠር የኤርትራን ዕድል በመወሰን ጉዳይ የሰፊውን የኤርትራ ሕዝብ ፍላጎት የማያሟላ የፌደሬሽን አቋም በመፍቀድዋ ፌደራላዊ መንግሥት ከተመሠረተ በኋላ ደግሞ የኤርትራን ሕዝብ ለማጥፋትና አንቅስቃሴውን ለመደምሰስ ስፍር ቁጥር የሌለው መሣሪያና አማካሪዎች ለኢትዮጵያ መንግሥት ማቅረቡዋ በነሱ ዘንድ የተወገዘ ድርጊት መሆኑን የዓረብ አገሮች ጀብሃን በመርዳት ቀይ ባህርን የዓረብ ግዛት ለማድረግ መወሰናቸውንና ተራማጅ ድርጅትና ዴሞክራሲያዊ መንግሥት ለመመስረት በሚደረገው ትግል ያለፈውን ድርጊታቸውን በማረምና በማስተካከል የሱን ቡድን እንዲተባበሩ ሙሉ እርዳታን የሚጠይቁ ይገኙባቸዋል አሜሪካዊያኑም ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በዓላ በረሃ ይደረግ የነበረውን ድርድርና የጀብሃንም አኳኋን በሚገባ ስለሚያውቁ ጀግኖቹ እንደተሰቃያችሁና እንደተገደላችሁ በይፋ የምናውቀው ነገር ነው ከነሱ መገንጠላችሁም የሚደገፍ ነው ካሉ በኋላ የፍልስጥኤም ቡድን አካል የሆነው ጨለማው መስከረም « ዩኮ። በማለት ጠየቀ አሜሪካኖቹም ፖለቲካ የቁማር ጨዋታ ስለሆነ ቁማር ተጫወት እናንተ የምትፈልጉት ነጻነት ነው አኛ ደግሞ የምንሻው የቀይ ባህር ይዞታችን እንዲጠናከር ስለሆነ ይኸው ዋስትናችን ነው ብለው መለሱለት ይህን አጠቃላይ ውይይት ካደረጉ በኋላ አሜሪካኖቹ ስለ ኤርትራና ስለ ኢትዮጵያ የወደፊት ህልውና ቀደም አርገው የዚህ ዓይነት የተራቀቀ ፖሊሲ ማውጣታቸው ያስደነቀው መሆኑን ኢሳያስ ገለጠላቸው ስለተለዋወጥዋቸው ሀሳቦች ግን በሰፊው ከበረሃ ጓደኞቹ ጋር ተወያይቶ የመጨረሻውን መልስ በተከታታይ እንደሚልከላቸው አስታውቆ ስብሰባው አበቃ አኛም ለአዳርና ለግብዣ ተመልሰን በቃኘው ጣቢያ በተለይ ተዘጋጅቶልን ወደነበረው የሚስተር ኮፕላንድ መኖሪያ ቤት ሔድን በማግሥቱ ኢሳያስን ወደ በረሃ ለመመለስ አሜሪካኖቹ ብዙ ዝግጅት ማድረግ አስፈለጋቸው ምከንያቱም በዚያን ወቅት በአሥመራ መውጫና መግቢያ በሮች ሁሉ የተሰማሩት ፀጥታ አስከባሪዎች ከባድ ፍተሻ ያካሔዱ ስለነበር ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ የግድ አስፈላጊ ነበር ስለሆነም ኮፕላንድ ራሱ ሾፌር ሆኖ የአሜሪካን ባንዴራ የሚውለበለብበትና የዲፕሎማቲከ ታርጋ ያለውን እንዲሁም የጧላው መስተዋት በመጋረጃ የተሸፈነ ካዲላከ መኪና በማዘጋጀት እኔንና ኢሳያስን ይዞ በምፅዋ መንገድ በኩል የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪ ወታደሮችን ሰላምታ እየተቀበልን ወደ ነፋሲት አመራገ ከነፋሲት ወደ ደቀምሐረ በሚወስደው መንገድ አስከማይሐባር አካባቢ ድረስ ኢሳያስን ይዘነው ሔድንና አዚያ ይጠብቁት ለነበሩት ጓደኞቹ አስረከበነው እኛ ደግሞ በደቀምሐረ በኩል ዞረን ወደ አሥመራ ተመለስን አሜሪካኖቹ ወዲያውኑ ይህን ስምምነት ተግባራዊ የሚያደርጉበትን ዝግጅት ተያያዙት ጨለማው መስከረም የተባለው የፍልስጥኤም ነጻ አውጭ ድርጅት ጥቃት ያደርስብናል በሚል ሽፋን ራስ አሥራተ ካሣን በማግባባት ከሀገራቸውና በፀጥታ አስከባሪዎች ከየቦታው ተቀብረው የተገኙትን እንደዚሁም በጦርነት የተማረኩትን አያሌ መሣሪያዎች በኤንትረ ከባድ መኪናዎች አስጭነውና ሸፋፍነው በማሰራጨት ከኤርትራ እስከ መሀል አገር ያሉት የአሜሪካ ደጋፊዎች በየቦታው አንዲጠናከሩ አደረጉ ወዲያውኑ በምስራቃዊና በምዕራባዊ የኤርትራ ቆላዎች ከበድ ያለ ወታደራዊ አንቅስቃሴ ለማካሄድ ከመሃል አገር ቁጥሩ በርከት ያለ ሠራዊት እንዲመጣ ተደረገ ምከንያቱም በኤርትራ ከሀገር ውስጥ ጦርነት ማቀጣጠል አንድ ስንኩል መንግሥት በማሃል ኢትዮጵያ ለመፍጠር ለታቀደው መፈንቅለ መንግሥት የመጀመሪያው ቅድመ ሁኔታ አንዲሆን ታቅዶ ነበር ይህ በአዚህ እንዳለ አነዚያ በቃኘው ጣቢያ ከሃብተስላሴ ገብረመድህንና ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የተካሄዱት ስብሰባዎች በድብቅ በቴፕና በፎቶግራፎች ተቀርጸው ስለነበር የካቲት ቀን ዓም ፍሬ ነገሩ በጽሑፍ ሰፍሮ ከነፎቶግራፎቹ በአሥመራ የአሥራተ ካሣ ሰላይ በነበረው በሚስተር ግለንቦየት በተባለ አሜሪካዊ ተደርሶበት ለአሥራተ ካሣ ቀረበ ለዚሁም ወንጀል መዝገብ ቁጥር ቀኛ ካሳሁን መከላከያ ምስከር ገጽ የሚለውን መመልከት ይቻላል በዚህ ምክንያት እኔም ከደቀምሐረ ባስቸኳይ ተጠርቸ ተጠየቅሁ ራስ አሥራተ ካሣም ኢሳያስ አፈወርቅና ጓደኞቹ ከአሜሪካኖቹ ጋር ለመገናኘታቸው እኔን በሃላፊነት ለመጠየቅ ሞከረ እኔ ግን በበኩሌ አሜሪካኖቹ እንደልባቸው በየገጠሩ ሁሉ እንዲዘዋወሩ በመንግሥት ስለተፈቀደላቸው ሰፊ ግንኙነት ማቋቋማቸውን ገልጨ ጉዳዩ የኔ ሃላፊነት አለመሆኑን አስረዳሁ አንደዚሁም እኔ የወረዳው ገዢ በመሆኔ ብቻ ሳይሆን መንግሥት የሰላም ጉባኤ በማለት ያቋቋመው ኮሚቴ ተወካይም ስለሆንኩ በዓላ በረሃ የሚካሄደውን እንቅስቃሴ በቀጥታ ለመከታተል ኃላፊነት እንደነበረብኝ በተጨማሪ አስረዳሁ ይህንን ከገለጽኩ በኋላ ሁኔታውን ወደፊት በምስጢር እየተከታተልኩ ዕለት በዕለት ሪፖርት አንዳቀርብ በአሥራተ ካሣ ትእዛዝ ተሰጠኝ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን የአሥራተ ካሣ የወደፊት ሴራ በየአቅጣጫው መወራት በመጀመሩ የተፈጠረውን ውዥንብር ለማርገብ እኔ እንድታሰርና በወንጀል እንድከሰስ ተደረገ ራስ አሥራተ ካሣም ስሙን ለመጠበቅ ሲል በምስጢር ይደራደራቸው የነበሩት የዓላ በረሃ ተገንጣይ ቡድን አባሎች በጦር ኃይል እንዲመለሱ ትእዛዝ አስተላለፈ ህዳር ጀብሃ እና ሻዕቢያ ከፍል ዘጠኝ አስከ አሁን ድረስ የሁለቱ የኤርትራ ግንባሮች ውስጣዊ እይታ ምን ይመስል እንደነበር በጥቂቱ ዳስሰናል አሁን ደግሞ በደርግ ዘመን የነበረውን የግንባሮቹን ወታደራዊ አንቅስቃሴ አንቃኛለን ከቀይ ኮከብ ዘመቻ በፊት ከፋ በነበረው ዘመን የኤርትራ ግንባሮች አርስ በርስ ሲገዳደሉ ከኢትዮጵያ መንግሥት ወታደሮች ጋር መዋጋቱን በአብዛኛው ረስተውት ነበር ለማለት ይቻላል በዚህም የተነሳ በወቅቱ በኤርትራ ምድር የነበረው ከ የሚበልጥ ጦር ከጦር ሰፈሩ ወጥቶ አንቅስቃሴ አላደረገም የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮት ከፈነዳ በኋላ ግን ግንባሮቹ ከህዝቡ በመጣባቸው ከፍተኛ ግፊት ምከንያት በጥቅምት የተኩስ አቁም አድርገዋል የተኩስ አቁሙ እርስ በርስ ባለመዋጋት ብቻ የተወሰነ አይደለም ጠላትን በጋራ መመከት አንደኛው የሌላኛውን ይዞታ ማከበር ለውጊያም ሆነ ለሌላ እንቅስቃሴ የሚሰማራን ሀይል የሻዕቢያና ጀብሃ በመንገድ ላይ አለማገት ወዘተ የመሳሰሉ ተጨማሪ ግዴታዎችም ነበሩት የተኩስ አቁሙ ግንባሮቹ በኤርትራ ምድር መጠነ ሰፊ ማጥቃት እንዲሰነዝሩ አስችሎአቸዋል በውጤቱም የጀብሃ ሰራዊት ተሰነይ አቆርዳት አሊጊደር ኡምሀጀር መንደፈራ እና አዲኳላ ከመሳሰሉ ከተሞች በተጨማሪ የባርካ አውራጃን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ ሻዕቢያ ደግሞ ከሳህል አና ሰንሒት አውራጃዎች በተጨማሪ ከረን ደቀምሐረ ጊንዳፅ ሰገነይቲ ነፋሲት የመሳሰሉትን ከተሞች በእጁ አስገባ በግንባሮቹ አጅ ያልገቡት አስመራ ምጽዋ እና ባሬንቱ ብቻ ነበሩ ከዚህ በተጨማሪ ግንባሮቹ አስመራን በ ኪሎሜትር ቀለበት ከበዋት ከዛሬ ነገ እንገባለን በሚል ተስፋ ይጠባበቁ ነበር በጥር ወር ሻዕቢያ አስመራን ለመያዝ ያደረገው አደገኛ ሙከራ አልተሳካለትም በወቅቱ ለአራት ተከታታይ ቀናት በተካሄደ ውጊያ ከሁለቱም ወገን ከፍተኛ እልቂት አስከትሏል በአንዳንድ ጋዜጠኞች ግምት ከሁለቱም ወገን ተዋጊዎች ሞተዋል በነዚህ ቀናት ሲቪሉ የአስመራ ነዋሪም የእልቂቱ ሰለባ ሆኗል ጦርነቱን ተከትሎ በተካሄደው የማጽዳት ዘመቻ ከሺህ የማያንሱ ሲቪሎች አንደሞቱ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶቹ ይፋ አድርገዋል በተለይም የደርግ መንግሥት ለአንድ ዓመት ያህል የኤርትራ አስተዳዳሪ እና የሁለተኛ ከፍለጦር አዛዥ የነበሩት ጄኔራል ጌታቸው ናደው ግንባሮቹ ለሚፈጽሙት ጥቃት ሲቪሎችን ተጠያቂ በማድረግ ጭፍጨፋ ያካሂዱ እንደነበር የተለያዩ ጸሓፊዎች ዘግበዋል ለምሳሌ ሚያዚያ ሻዕቢያ ጸሎት በተሰኘችው አነስተኛ መንደር ባካሄደው የደፈጣ ጥቃት በርካታ የመንግሥት ወታደሮችን ሲገድል ጄኔራል ጌታቸው ወደ አየር ሀይል መደብ ደውለው አሁኑኑ ተነስተህ ወደ ጸሎት ብረር ጸሎት ላይ የሚንቀሳቀስ ዛፍ አንዳላይ ከአስራ አምስት ደቂቃ በኋላ ስለ አፈጻጸሙ ሪፖርት እፈልጋለሁ የሚል የጀብደኝነትና የጭካኔ ትዕዛዝ ሲሰጡ መስማታቸውን በር የተሰኘውን መጽሐፍ የጻፉት ዘነበ ፈለቀ ገስሥ ተጫኔ ይመሰከራሉ መድድቋጽ በ በብዙ ጸሓፊዎችና ምሁራን የተተቸውና በአሳዛኝ ፍጻሜ የተደመደመው የራዛ ዘመቻ ተካሄደ ይህ ዘመቻ ለደርግ በማን እንደተወጠነ አይታወቅም አንዳንዶች ለምሳሌ ባቢሌ ቶላ የመኢሶን ውጥን ነው እያሉ ቢጽፉም መኢሶን ከጥንስሱ ጀምሮ የዘመቻው ተቃዋሚ እንደነበር የደርግ ሰዎች ራሳቸው መስከረዋል በርካታ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶችም ዘመቻው ይገታ በማለት ጮኸዋል የራዛ ዘመቻ ዓላማ የጀብሃና የሻዕቢያን ሀይል ከጎጃም ጎንደር ወሎ እና ትግራይ በተውጣጡ ገበሬዎች መምታት ነበር እነኛ ገበሬዎች በቂ ስልጠናና የዝግጅት ጊዜ ሳይወስዱ ነበር የዘመቱት ገበሬዎቹ የታጠቋቸው መሳሪያዎቹም አልቤን መውዜር ቹኮዝ ምንሽሸር ዲሞትፈር የመሳሰሉት ኋላቀር ጠመንጃዎች ነበሩ በቂ ጥይትም ሆነ የስንቅ አቅርቦት አልነበራቸውም ከሁሉም የሚያሳዝነው ደግሞ እነኝህ የውትድርና ልምድ ጨርሶ የሌላቸውን ገበሬዎች በደፈጣ ጥቃት በተካነው የጀብሃና ሻዕቢያ ሰራዊት ላይ ማዝመቱ ነበር እነዚህ ገበሬዎች ለዘመቻቸው እንዲነሳሱ ጀብሃ እና ሻዕቢያን አባርረው የማረኩት ንብረት በጠቅላላ የናንተ ይሆናል ወንበዴዎቹ የለቀቁት መሬትም የናንተ የግል ንብረት ስለሚሆን እንደሻቸሁ ትገለገሉበታላችሁ የሚል ቃል ተሰጥቶአቸው ነበር ዘማቾቹ በሶስት ግንባር ነው ወደ ኤርትራ የነጎዱት አንደኛው ቡድን ተነስቶ ተከዜን ተሻግሮ ከኡምሀጀር ጀምሮ ጀብሃን አየመታ ተሰነይ እንዲገባ ነበር የታሰበው ሁለተኛው ቡድን ከኢንቲጮ ተነስቶ መረብን በመሻገር ሻዕቢያን እየመታ እስከ ሰንአፌ እንዲደርስ ነበር የተፈለገው ሶስተኛው ቡድን ከሽሬ እንዳሥላሜ በመነሳት በጾረና በኩል ወደ መንደፈራ አንዲዘምት ታስቦ ነበር ሁለቱ ሽምቅ ተዋጊዎች ወደነርሱ የሚጎርፈውን የገበሬ ማዕበል ለመመለስ ምሸግ መቆፈር አላስፈለጋቸውም ቦታ ቦታ ጠብቆ በአርፒ ጂ ሮኬትና በመትረየስ መዎታት ብቻ በቂአቸው ነበር በዚህም አኳኋን ከሁመራ የተነሳው ዘማች ሀይል ገና ተከዜን አንደተሻገረ በኢንቲጮ በኩል የዘመተው ደግሞ ከትግራይ ድንበር ሳያልፍ በሮኬትና በመትረየስ ተደበደበ ይህ ቀረሽ የማይባል የኢትዮጵያዊያን እልቂት ተከሰተ ብዙዎቹ ተማረኩ ከእልቂትና ምርኮ የተፈረው መንገድ ጠፍቶት ሲዳከር በውሃ ጥም አለቀ ጥቂቶች በጥንካሬ ወደ ትግራይ ከተሞች ለመድረስ ቢችሉም ከደረሰው ውድቀት አንጻር ቁጥራቸው ይህ ነው አይባልም በሁለቱ ቡድኖች ላይ የደረሰውን አልቂት ያስተዋለው ወታደራዊ ደርግ ሶስተኛው ቡድን ከሽሬ ሳይንቀሳቀስ ወደመጣበት እንዲመለስ ሸኘው በዘመቻው ተሳትፈው በሰላም ለተመለሱ ገበሬዎች የያዙት ጠመንጃ በነጻ ተሰጥቶአቸዋል በ አዚህ ግባ የሚባል ወታደራዊ አንቅስቃሴ በኤርትራ ምድር አልተካሄደም የዚህም ምከንያት በሶሻሊስት ሀገራት አሳሳቢነት በግንባሮቹና በደርግ መንግሥት መካከል ሰላማዊ ድርድሮች መካሄድ መጀመራቸው ነው በዚህም መሰረት የቀድሞዋ ምስራቅ ጀርመን በህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ሻዕቢያ እና በደርግ መንግሥት መካከል የሚካሄደውን የሰላም ድርድር አመቻችታለች በውይይቱ ላይ የሻዕቢያው መሪ አሳያስ አፈወርቂ ተሳፏል በተጋድሎ ሓርነት ኤርትራና በደርግ መንግሥት መካከል የተካሄደውን ድርድር የሸመገለችው ደግሞ ሶቪየት ህብረት ነበረች አብደላ ኢድሪስ ጀብሃን በመወከል ሞስኮ ተገኝቷል ይሁንና ሁለቱም ውይይቶች ፍሬ አላፈሩም በሌላ በኩል በዚያ ዓመት በ የተጀመረው የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ደርግ ሙሉ ትኩረቱን በኦጋዴን ላይ ብቻ እንዲያደርግ ስላደረገው በኤርትራ ምድር የነበረውን ወታደራዊ ዘመቻ እንዲያቀዘቅዝ ምክንያት ሆኗል የሶማሊያው ጦርነት በ አጋማሽ ላይ በድል ሲጠናቀቅ የደርግ መንግሥት ከድል አድራጊው ጦር ግማሸ ያህሉን ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት በማለት አደራጀ ይህ ሺህ ያህል የሰው ሀይል ያቀፈ ትኩስ ሀይል የምስራቁ ድል በሰሜንም ይደገማል የሚል መፈክር በመጨበጥ ወደ ኤርትራ ምድር ተመመ የጦር ሰራዊቱ በአምስት ግብረሀይሎች ተከፋፍሎ ነበር ወደ ኤርትራ የዘመተው የግብረሀይሎቹ መነሻና ግብ አንደሚከተለው ነበር ሀ ኛ ግብረ ሀይልፁ ከሁመራ ተነስቶ በኡምሐጀር በማድረግ ተሰነይ ይገባል ለ ኛ ግብረ ሀይል ከሸሬ ተነስቶ በሸምበቆ አድርጎ ባሬንቱን ከጀብሃ ያስለቅቃል ከዚያም ከ ግብረኃይል ጋር ይጋጠምና ወደ አቆርዳት ይገባል ሐ ኛ ግብረ ሀይልሀ ከመረብ ድልድይ ተነስቶ አዲኳላን በማስለቀቅ አረዛ ከተማ ይገባል መ ኛ ግብረኃይልለፁ ከገርሁ ሰናይ ተነስቶ በጾረና በኩል በማድረግ ከዘላአምበሳ አስመራ የሚያደርሰውን ጎዳና ያጸዳል ሠ ኛ ግብረ ኃይል ከአስመራ ተነስቶ ኃይሉን በሶስት አቅጣጫ በማነቃነቅ በዙሪያው ያለውን የጠላት ኃይል ወደ ውጪ በመግፋት አረዛ ላይ ከኛሀ ደቀምሐረ ላይ ከሰ ከረን ላይ ከኛ ግብረኃይሎች ጋር መገናኘት ነበር ረ ኛ ግብረሀይል ምጽዋን ሙሉ በሙሉ ከጠላት ከበባ ካላቀቀ በኋላ ኃይሉን ለሁለት ከፍሎ አንዱ ወገን ዶጋሊን ተቆጣጥሮ ከምጽዋ አስመራ መንገድን ነጻ ማድረግ ሌላው ወገን ደግሞ በመርከብ ወደ መርሳ ጉልቡብ ተጉዞ አልጌናን መያዝና ከናቅፋ ጀርባ መግባት ነው በሁሉም ግንባሮች የዘመቱት ግብረሀይሎች የተሰጣቸውን ግዳጅ በከፍተኛ መስዋእትነት ፈጸሙ ሻዕቢያና ጀብሃም በጦር አውሮፕላኖች የተጠናከረውን የሁለተኛ አብዮታዊ ሰራዊት ጥቃት ለመመከት በብርቱ ሞከሩ በተለይ ኤላበረድ በምትባለው አነስተኛ ከተማ አቅራቢያ የሻዕቢያ ሀይሎች ከአብዮታዊ ሰራዊት ጋር ለሶስት ተከታታይ ቀናት የዘለቀ ከባድ ውጊያ አካሄዱ ሆኖም የጦር ሰራዊቱ ጥቃት ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ከረን የተሰኘችውን ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ከተማ ለመልቀቅ ተገደዱ የአብዮታዊ ሰራዊት ግብረሀይሎችም በአማጺያኑ የተያዙትን የኤርትራ ከተሞች ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠሩ ሆኖም የተሰጣቸውን የመጨረሻ ግብ ማሳካት አልቻሉም ሻዕቢያና ጀብሃን ከናቅፋ ማባረር እንዲህ በቀላሉ የሚደረስበት ሆኖ አልተገኘም ስለዚህ ሰራዊቱ በተጨማሪ ስልጠናና ትጥቅ እስኪደራጅ ድረስ ይዞታውን አያጠናከረ እንዲቆይ ተደረገ በ መጨረሻ ገደማ ሁለት አነስተኛ ዘመቻዎች ተደርገዋል በ አጋማሽ ላይ አብዮታዊ ሰራዊት ናቅፋን ከሻዕቢያ ለማስለቀቅ ከባድ ዘመቻ ከፈተ ሆኖም ሻዕቢያ በሰላዮቹ አማካኝነት ያገኘውን መረጃ በመጠቀም ተዋጊዎቹን በደፈጣ ስልት በማሰለፉ ከተቃጣበት ጥቃት ተረፈ ይባስ ብሎም አብዮታዊ ሰራዊቱ ተዘናግቶ በሰፈሩ ሲከትም ሻዕቢያ የተበታተነውን ሀይሉን በማሰባሰብ ድንገተኛ ጥቃት ከፈተበት በአብዮታዊ ሰራዊት ላይ ብርቱ ጉዳት ደረሰ የሰፈረበት የናቅፋ መሬት ለጥቃት አንዳጋለጠው ስለታመነ ወደ አፋበት አንዲያፈገፍግ ተደረገ ሻዕቢያም የሚያፈገፍገውን ጦር እየተከታተለ ወጋው ከሶማሊያ ወረራ ወዲህ ታላቅ የተባለውን የመጀመሪያ ድሉን ተጎናጸፈ በምዕራብ ኤርትራ የነበረው ሁኔታ ደግሞ ከዚህ ይለያል በከፍል ሰባት እንደገለጽኩት ጀብሃ በርሱ ላይ የዘመተውን ብዙ ሺህ ሰራዊት ከመሸሸ ይልቅ በመጋፈጡ ሀይሉን አስጨርሲሷል ለከፉ ቀን ይሆነኛል ብሎ የያዘው የባርካ ቆላ ሜዳማ በመሆኑ ከሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ጥቃት ሊያድነው አልቻለም ስለዚህ ያለው አማራጭ ልከ እንደ ሻዕቢያ ወደ ሳህል መሸሽ ነበር ከ ድረስ በነበሩት ዓመታት የተደረጉት ጦርነቶች አዚህ ግባ የሚባሉ አልነበሩም ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ሻዕቢያ ከናቅፋ ተራሮች አንዳይወርድ በማድረግ ብቻ ተወስኖ ነበር በሌላ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው በነኝህ ዓመታት ሻዕቢያና ጀብሃ በመካከላቸው የነበረውን ስምምነት አፍርሰው መተላለቅ በመጀመራቸው ሻዕቢያ ጀብሃን ከኤርትራ ምድር በማባረር ወደ ሱዳን እንዲገባ አድርጎታል ጀብሃን በመምታቱ ረገድ ህወሐትም ከሻዕቢያ ጋር በትብብር ሰርቷል ማጽጁቋቋ ህዳር ጀብሃ እና ሻዕቢያ ክፍል አስር በቀይ ኮከብ ዘመቻ የኤርትራ አማጺያንን ለማጥፋት ከተደረጉ ዘመቻዎች መካከል ብዙ የተባለለት ነው የቀይ ኮከብ ዘመቻ ታዋቂ የጦር ጠበብት እየደጋገሙ አውስተውታል በጋዜጣና በሬድዮ ብዙ ተለፍፎለታል አጀማመሩም ሆነ አፈጻጸሙ ትንግርተኛ መሆኑ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው ዘመቻው የተካሄደበት ለየት ያለ ድባብና በርሱ ሳቢያ የተፈጠረው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ኦሮማይ የተሰኘው ተወዳጅ ድርሰት እንዲጻፍ ምክንያት ሆኗል ያ ዘመቻ በኦፊሴል ጥቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመም ተብሎ ነበር የተሰየመው የዘመቻው ዓላማዎቸም ሁለት ናቸው አንደኛው ሻዕቢያን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መደምሰስ ነው ሁለተኛው በጦርነቱ የፈራረሱ መሰረተልማቶችን መገንባት ነው ለዘመቻው ቀይ ኮከብ የሚል ስም የተሰጠው ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም የአሜሪካ ባህር ሀይል ብሩህ ኮከብ ዌሼክር ሀኗ በሚል ስም በቀይ ባህር ላይ ላደረገው ወታደራዊ ልምምድ ምላሽ መሆን አለበት በማለት ባደረጉት ውሳኔ መሰረት እንደሆነ በወቅቱ የኤርትራ ከፍለሀገር ኢሠፓአኮ ተጠሪ የነበሩት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ቀይ እምባ ቪበ ፐፀ በተሰኘው መጽሐፋቸው ገልጸዋል የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻ ይፋ የተደረገው በሀገር አቀፍ ደረጃ በታወጀ ልዩ አዋጅ ነው ዘመቻውን በበላይነት የሚያስፈጽም ከፍተኛ ስልጣን የተሰጠው ሀገር አቀፍ ምከር ቤት ተቋቁሞለታል የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ሲሆኑ ዋና ጸሓፊው ኤርትራዊው አቶ አማኑኤል አምደሚካኤል ነበሩ የሀገሪቱ ምርጥ ምሁራን የተሳተፉበትና ድርጅታዊ ሀይሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሟላለት የምከር ቤቱ ጽሕፈት ቤትም አስመራ ላይ ተሰይሞም ነበር ለዘመቻው ማስፈጸሚያ ከሁለት ቢሊዮን ብር የሚበልጥ በዛሬው የምንዛሬ ተመን ወደ ሀያ ቢሊዮን ብር ያህል የሚሆን በጀት ተመድቦለታል ዘመቻውን ለማስፈጸም በሚልም ከሊቀመንበር መንግሥቱ ጀምሮ ሀገሪቷ ያሏት ከፍተኛ ወታደራዊና የሲቪል ባለስልጣናት አስመራ ላይ ከትመዋል የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻ በይፋ የተከፈተው ጥር ነበር የዘመቻውን መከፈት በሚያበስረው ጉባኤ ላይ ከሁሉም የኢትዮጵያ ከፍለ ሀገሮች የተወከሉ የሀገር ሽማግሌዎች ሙያተኞች መለዮ ለባሾች የገበሬ ተወካዮች ወዘተ ተሳትፈዋል ሊቀመንበር መንግሥቱ ጉባኤውን የከፈቱበት ንግግር በሬዲዮ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ በቀጥታ ተላልፏል የአስራ አራቱ ከፍለ ሀገራት ተወካዮችም በጉባኤው ላይ ንግግር አድርገዋል ጉባኤው ጥር ሲጠናቀቅ ሰባት ነጥቦች ያሉት የአስመራ ማኒፌስቶ በአቋም መግለጫ መልከ ይፋ ተደርጓል የቀይ ኮከብ ዘመቻ ጉባኤ በተከፈተበት ማግስት በቀይ ባህር ዳርቻ በምትገኘው ጉርጉሱም የተባለች ሰርጥ ላይ የተዘጋጀው የምጽዋ ኤክስፖ በሊቀመንበር መንግሥቱ ተመርቋል ዶጋሊ ላይ ሊገነባ ለታቀደው የራስ አሉላ መታሰቢያ ሀውልት የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጡትም ሊቀመንበር መንግሥቱ ነበሩ በምጽዋ ከተማ በሚገኘው አጹ ካሌብ አዳራሽ ታሪካዊው የምጽዋ ሲምፖዚየም ተካሂዷል በአስመራና በምጽዋ ከተሞች የሚገኙ በርካታ ፋብሪካዎችም ተጠግነው የማምረት ተግባራቸውን እንዲጀምሩ ተደርገዋል ከምጽዋአቆርዳት የተዘረጋው የባቡር መስመርም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ይህ ሁሉ ከተገባደደ በኋላ ነው ወታደራዊው ዘመቻ የተካሄደው አጽጁቋቋ የቀይ ኮከብ ወታደራዊ ዘመቻ በአራት ግንባሮች ነበር የተከናወነው በብርጋዴር ጄኔራል አበራ አበበ የሚታዘዘው ውቃው እዝ በአልጌና በኩል በሰሜናዊ ቀይ ባሕር ጠረፍ ከናቅፋ ጀርባ እንዲያጠቃ በብርጋዴር ጄኔራል ውበቱ ጸጋዬ የሚታዘዘው ናደው እዝ ከከረን ጀርባ ወደ ናቅፋ በር በከርከበት ግንባር ከናቅፋ ደቡባዊ ምሥራቅ በኩል እንዲያጠቃ በብርጋዴር ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ የሚታዘዘው መብረቅ አዝ በቃሮራ ግንባር ከናቅፋ ሰሜን ምዕራብ እንዲያጠቃና የሻዕቢያን መውጫ እንዲዘጋ በብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ጋሼ የሚታዘዘው መክከት እዝ የአስመራን ዙሪያ አንዲያጥር የሚል ትዕዛዝ ተቀብለው ለውጊያ ዝግጁ ሆኑ የካቲት ጎህ ከመቅደዱ በፊት በሁሉም ግንባሮች ወደ ናቅፋ የመጠጋት አንቅስቃሴ ተጀመረ የናቅፋ ተራሮች በቢኤም እና በሞርታር ተደበደቡ ከሰማይ በሚወርዱ የአውሮፕላን ቦንቦች ታረሱ ሮኬቶችና ካሊበሮች ተወናጨፉ ናቅፋ አሳተ ጎመራ የፈነዳባት መሰለች ሻዕቢያ መጥፊያው የተቃረበ መሆኑን ገምቶ ከናቅፋ ምሽጉ ሊወጣ ሲሰናዳ በሁሉም አቅጣጫዎች ዝግ ሆነበት ስለዚህ ተራሮቹን የሙጥኝ ብሎ መከላከሱን ቀጠሰ የእግረኛና ሜካናይዝድ ውጊያ እንዲጀምር የታዘዘው በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ የተሰለፈው መብረቅ እዝ ነበር ይሁን አንጂ እዙ በታቀደለት ሰዓት ባለመንቀሳቀሱ ሻዕቢያ በርቀት ያሉ ሀይሎቹን አንዲያሰባስብ ጊዜ ሰጠው በሌላ በኩል ለዚሁ የመብረቅ እዝ ግንባር ቀደም ሆኖ የማጥቃት ግዳጅ የተሰጠው ኛ ተራራ ከፍለጦር በብቃቱ አንደተጠበቀው ሆኖ አልተገኘም ከፍለጦሩ በተያዘለት እቅድ መሰረት ወደ ናቅፋ ተራሮች ምዕራባዊ ከፍል ተጠግቶ ሻዕቢያን ማባረር አቃተው ይባስ ብሎም ጠላት በሰራለት ቀለበት ውስጥ ገብቶ ተከበበ ሻዕቢያም ባለ በሌለ ኃይሉ ተረባረበበት የኛ ተራራ ከፍለ ጦርም ተፍረከረከ ሺዎች በሜዳ ላይ እንደ ቅጠል ረገፉ የውቃው እና የናደው እዞች ከፍተኛ ጀግንነት አሳይተው ከናቅፋ ስምንት ኪሎሜትር ርቀት ላይ ደረሱ ይሁንና ባልታወቀ ምከንያት በተሰጠ ትዕዛዝ እንቅስቃሴአቸው ተገታ ከዚያ በኋላ አንንቀሳቀስ ቢሉ የማይቻል ነገር ሆነ ሻዕቢያ ተዋጊዎቹን ከያሱበት አሰባስቦ ወደ ኋላ ይገፋቸው ጀመር ለሶስት ተከታታይ ቀናት ባደረገው መልሶ ማጥቃት በአፋቤት ከርከበት ግንባር በዘመተው ናደው እዝ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ ሺዎች ሙትና ቁስለኛ ሆኑ በትልቅ ሞራልና የድል ጉጉት የተጀመረው የቀይ ኮከብ ዘመቻም በከፍተኛ ሽንፈት ተፈጸመ ጽጽጽጽጽ የውቃውና የናደው እዞች ከናቅፋ አጠገብ ደርሰው ውጊያ አንዲያቆሙ የተደረገበት ምከንያት አስከዛሬ ድረስ በግልጽ አይታወቅም ሻለቃ ጌታቸው የሮም በጻፉት መፅሐፍ አንድ ከፍተኛ የኢሠፓ ባለስልጣን ሻዕቢያ እያዘናጋችሁ ሊፈጃችሁ ስለተዘጋጀ መቆም አለባችሁ የሚል ትዕዛዝ ስለሰጠ ነው ይላሉ ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው የጦር ሀይሎቹ መዋጋት ያቆሙት ናቅፋን የመያዙ ተግባር ሊቀመንበር መንግሥቱ ረጅም ዕድሜአቸውን ባሳለፉበት አንበሳው ሶስተኛ ከፍለ ጦር እንዲፈጸም ስለተፈለገ ነው በማለት ጽፈዋል ኮሎኔል መንግሥቱ ግን ይህንን አባባል በከፍተኛ ቁጣ አስተባብለዋል ከሁሉም ጦሮች ቀድሞ ናቅፋ የደረሰውና ያለቀው ሶስተኛ ከፍለ ጦር ነው በማለትም ተከራከረዋል ለዘመቻው አጠቃላይ ውድቀት መንስኤ የሆነው ምከንያትም በታሪከ ጸሐፊዎችና በወታደራዊ ጠበብቶች ስምምነት አልተደረገበትም ይሁንና አቶ ገስጥ ተጫኔ ዘነበ ፈለቀ በጻፉት ኀበር የተሰኘ መጽሐፋቸው ውስጥ የሰነዘሯቸው ነጥቦች ብዙዎችን የሚያስማሙ ይመስላሉ እነርሱም የመብረቅ እዝ በተሰጠው ሰዓት መሰረት ግዳጁን አለመፈጸሙ ለኤርትራ መሬት እንግዳና ባዳ የሆነውና በቅርብ ጊዜ ከማሰልጠኛ የወጡ ሀይሎች የተሰባሰቡበት ኛው ተራራ ከፍለ ጦር ግንባር ቀደም መቺ ሀይል ሆኖ ወደ ናቅፋ አንዲዘምት መደረጉ ሊቀመንበር መንግሥቱ ለድል በመቸኮላቸው የውጊያው እቅድ ሲከለስ ከወታደራዊ አዛች የተሰጡትን የእርማትና የማሻሻያ ሐሳቦች ጨርሶ ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆናቸው ለምሳሌ ጄኔራል አበራ አበበ ኛው ተራራ ከፍለ ጦር አስተማማኝ ባለመሆኑ ግዳጁ ለሌላ ጠንካራ ከፍለ ጦር አንዲሰጥ ያቀረቡትን ሐሳብ ጨርሶ ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆናቸውነ የእዞቹ አዛዥዞች በእቅዱ ሳያምኑበት ወደ ውጊያ የገቡ መሆናቸውና ሌሎችም ምከንያቶች ናቸው የቀይ ኮከብ ዘመቻ በውድቀት ከጨነገፈ በኋላ የውድቀቱ መንስኤ ተጠንቶ ለውሳኔ አንዲቀርብ ታዘዘ በዘመቻው የውጊያ ኢኒስፔክሽን መምሪያ ሃላፊ የሚመራ ቡድን የመብረቅ አዝ ወደ ሚገኝበት ቃሮራ ግንባር ተላከ ቡድኑ ማጣራቱን ካከናወነ በኋላ የሬፌኛው ተራራ ከፍለ ጦር አዛዥ የነበሩት ኮሎኔል ውብሸት ማሞ እና በከፍለ ጦሩ የኛው ብርጌድ አዛዥ የሆኑት ሌኮል ስለሺ አስፋው የውድቀቱ ተጠያቂዎች ናቸው ተባሉ ሁለቱ መኮንኖች በልዩ ትዕዛዝ በተቋቋመ የጦር ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው በተላለፈባቸው ፍርድ መሰረት ኮል ውብሸት ማሞ ተረሸኑ ሌኮል ስለሺ አስፋው ደግሞ ማዕረጋቸውን ተገፍፈው ወህኒ ወረዱ የመብረቅ አዝ ዋና አዛዥ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ወደ አስመራ ተጠርተው በቁም አስረኛነት ለረጅም ጊዜ ተቀመጡ መድድቋጽ አንድ ዓመት ሙሉ ዝግጅት የተደረገበት የቀይ ኮከብ ዘመቻ በዚሁ መልክ ነበር የተደመደመው ሁለት ቢሊዮን ብር በሁለት ወር ውስጥ እንደ ጉም ተንኖ ቀርቷል ታዲያ ሊቀመንበር መንግሥቱ የባሰ እልህ ይዞአቸው ቀይ ኮከብ ሁለት እና ቀይ ኮከብ ሶስት የተሰኙ ዘመቻዎችን ሞክረው ነበር ውጤቱ ግን ሊሰምርላቸው አልቻለም በርካታ ታዛቢዎች አንደሚሉት ዘመቻው እንዳበቃ የናደውና የውቃው እዞች የናቅፋን ዙሪያ አጥረው እንዲቆዩ ቢደረግና ኮል መንግሥቱም ሰኤርትራ ችግር ሰላማዊ መፍትሔ ወደ ማፈላለጉ ቢሄዱ ኖሮ ጥሩ ውጤት በተገኘ ነበር ምክንያቱም ዘመቻው ሻዕቢያንም ከፉኛ ያደከመ በመሆኑ አማጺው ሀይል ሰላማዊውን አማራጭ ይቀበል ነበር ተብሎ ይታሰብ ስለነበረ ነው የቀይ ኮከብ ዘመቻ በኢትዮጵያ ታሪከ ውስጥ ጥቁር ነጥብ ጥሎ ነው ያለፈው አብዮታዊ ሰራዊት በዘመቻው ማብቂያ ላይ ባጋጠመው ውድቀት ከፉኛ ተናግቷል የወታደሮቹ ስነ ልቦናም በጣም ተቃውሲል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም የጦር ሀይል ወደ ናቅፋ መጠጋት ይፈራ ነበር ዘማቾች ናቅፋ ከተባለ ሞት ብቻ ነበር የሚታያቸው በአንጻሩ ደግሞ የቀይ ኮከብ ዘመቻ ለሻዕቢያ ሀይሎች ከፍተኛ የሞራል ስንቅ ሆኖአቸዋል ግዐ ሆነን ከ የሚልቅ እጅግ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀና በአውሮፕላንና በቢኤም የተጠናከረ ግዙፍ ሰራዊት ድል አድርገናል በማለት አንዲኩራሩ አድርጎአቸዋል ናቅፋንም ምልከት ጽናትና የጽናታችን ምልከት በማለት እንዲጠሯት መንስኤ የሆናቸው ይኸው ነው ህዳር ብሃ እና ሻዕቢም ከፍል አስራ አንድ ድህረቀይ ኮከብ የቀይ ኮከብ ዘመቻ በሽንፈት ከተቋጨ በኋላ የዘመቻውን መጀመር በከፍተኛ ፕሮፓጋንዳ ያበሰሩት የመንግሥት ሚዲያና ፕሬሶች በዝምታ ተዋጡ በኤርትራ ምድር ስለሚካሄድ ወታደራዊም ሆነ ሰብዓዊ እንቅስቃሴ ደፍሮ የሚናገር ጠፋ የቀይ ኮከብ ዘመቻም ይፋዊ ባልሆነ መንገድ በሰኔ ተሰረዘ የዘመን አቆጣጠሩ እንደ አውሮጳ ቀመር መሆኑን አትርሱ አንዳንድ ጸሐፍት ዘመቻው አንደታቀደው በድል ቢደመደም ኖሮ ሻዕቢያ ከኤርትራ ምድር ይነቀልና ኤርትራም በማያሻማ ሁኔታ የኢትዮጵያ አካል መሆኗ ይረጋገጥ ነበር ይላሉ ሌሎች ግን ይህንን አባባል ይቃወማሉ የኤርትራ ቸግር በሰላማዊ መንገድ አስካልተፈታ ድረስ የሻዕቢያ መጥፋት ብቻውን የኤርትራን ኢትዮጵያዊነት አያረጋግጥም በማለትም ያከላሉ ታዲያ ለችግሩ ሰላማዊ መፍትሔ ለማስገኘት የተደረገው ጥረት በጣም አነስተኛ ነበር ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም ከወታደራዊ አርምጃ በስተቀር የሰላሙን መንገድ መከተልን አንደ አማራጭ አልወሰዱትም አንዳንድ ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ለችግሩ ሰላማዊ መፍትሔ ለማስገኘት በራስ ተነሳሽነት ያደረጉት ጥረት ከግብ ሳይደርስ የቀረው ሊቀመንበር መንግሥቱ ችግሩን በወታደራዊ መንገድ ብቻ ለመፍታት በመወሰናቸው እንደሆነ ይነገራል ለምሳሌ የቀድሞው የሀገርና ህዝብ ደህንነት ሚኒስትር ኮል ተስፋዬ ወልደሥላሜ በግላቸው ያደረጉት የሰላም ጥረት በሊቀመንበሩ ግትርነት አንደተሰናከለባቸው በምሬት ተናግረዋል ድድድቱቴቴ በመጋቢት ወር አንዳንዶች ጸጥተኛው ዘመቻ በማለት የሚጠሩት ወታደራዊ ኦፕሬሽን ተጀምሮ ነበር ዘመቻው ጸጥተኛ ተብሎ የተጠራው በህዝብ ሚዲያ ምንም ዓይነት ቅስቀሳ ስላልተደረገለት ነው በዚህ ዘመቻ የተካፈለው የወታደር ብዛት በቀይ ኮከብ ጊዜ ከነበረው በጣም ያንሳል የዘመቻው ትኩረትም ከከረን ከተማ በስተሰሜን ያለቸው ሐልሐል የተሰኘች ስትራቲጂካዊ መንደር ነበረች ሐልሐል በ የጀብሃ እውቅ ኮማንደር የነበረው ዑመር እዛዝ የሞተባት መንደር ናት በዘመቻው የአብዮታዊ ሰራዊት ሀይሎች የሻዕቢያ ተዋጊዎችን አሸንፈው ለማባረር ችለዋል ሆኖም በሻዕቢያ ላይ የደረሰው ሽንፈት የአማጺውን ቅስም ለመስበር የሚችል አልነበረም በ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰራዊት በታሪኩ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በከፍተኛ ቁጥር ጨምሮ ነበር የዚህም ምከንያት የብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት መታወጁ ነው በዚህ መሰረት የመጀመሪያው ዙር ዘማቾች በጥር ወር ወደ ማሰልጠኛ ጣቢያ ገብተዋል ታዲያ ሻዕቢያም አልሰነፈም መከላከልንና ማጥቃትን እያፈራረቀ የመንግሥት ሰራዊትን አስጨንቆ ይዞአል ይባስ ብሎም የአብዮታዊ ሰራዊት አዛች ባልጠበቁት መንገድ የውጊያ ቀጣናውን ፊት ወደማይታወቅበት የምዕራብ ኤርትራ ቆላማ መሬት አስፋፍቷል በቀድሞ ጊዜ በዚህ ግንባር ጀብሃ እንጂ ሻዕቢያ ተዋግቶ አያውቅም በተለይም በሱዳንና ኤርትራ ድንበር ላይ የምትገኘውን የተሰነይ ከተማን በመቆጣጠር የመንግሥት ሀይሎችን ስጋት ላይ ጥሷል አብዮታዊ ሰራዊት ከተማዋን በአውሮፕላን ደጋግሞ ቢደበድባትም ከሻዕቢያ ሊያስለቅቃት አልቻለም እንዲያውም በአንደኛው ድብደባ ላይ ከፍተኛ የአብራሪነት ልምድ ያካበቱትና በሰሜን አሜሪካ አሪዞና ስቴት የሰለጠኑት አውቁ አብራሪ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በሻዕቢያ አየር መቃወሚያ ተመትተው ለመማረከ በቅተዋል እኝህ ኮሎኔል በሻዕቢያ እጅ ለስድስት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደርግ መንግሥት ከስልጣን ሲወገድ በምህረት ተለቀዋል በ የኢትዮኤርትራ ጦርነት ሲቀሰቀስ እንደገና ዘምተው በአየር ላይ በመመታታቸው በድጋሚ በሻዕቢያ ተማርከዋል በሌላ በኩል በሀምሌ ወር ሻዕቢያ የጋሽና ሰቲት አውራጃ ዋና ከተማ የነበረችውን ባሬንቱን በመቆጣጠሩ ምዕራባዊው የኤርትራ ከፍል በአብዛኛው ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ ሆና ነበር ሻዕቢያ ምዕራብ ኤርትራን በመቆጣጠሩ በሱዳን ካሉት ደጋፊዎቹና ኤርትራዊያን ስደተኞች ጋር እንደ ልብ የሚገናኝበት ሁኔታ ተፈጥሮለታል በተለይ የኤርትራ አርዳታ ማህበር ቭየዩክ ቪዩቨር ላርቨክጀቪላ የተሰኘው ድርጅት ሻዕቢያ በሚቆጣጠራቸው ከልሎች ለሚኖሩትና በቱ ድርቅ ለተጎዱ ዜጎች አንዳሻው እርዳታ ማቅረብ የቻለው በተሰነይ በኩል ወደ ሱዳን የሚዘልቀው ጎዳና በሻዕቢያ ቁጥጥር ስር ስለዋለ ነው ከዚያ በፊት ላ ለእርዳታ አቅርቦቱ የሚጠቀመው ከፖርት ሱዳን ወደ ሰሜናዊ ኤርትራ የሚያመራውን ረጅም ጎዳና ነው እንደሚባለው ከሆነ የደርግ ሀይሎች ለኤርትራዊያን ዜጎች እርዳታ እንዳይደርስ አግደው ቆይተዋል እርዳታው በክላ በኩል እንዲደርስ የተፈለገው ለዚህ ነው ዘመቻ ባህረነጋሽ አብዮታዊው ሰራዊት ሻዕቢያን ከምዕራብ ኤርትራ ለማባረር በቂ ዝግጅት ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሐምሌ ወር ለመልሶ ማጥቃት ተዘጋጀ በአንደኛው ዙር የብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት የተመለመሉ ሺህ ዘማቾችን ጨምሮ ከመቶ ሀምሳ ሺህ የማያንስ የጦር ሰራዊት ለውጊያው ተሰለፈ የዘመቻው ፕላን በሶቭየት ህብረት ወታደራዊ ኤከስፐርቶች ተዘጋጀ ከሶስት መቶ የማያንሱ ታንኮችና ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች ዝግጁ ሆኑ ዘመቻውም ባህረ ነጋሽ ተብሎ ተሰየመ መቻ ባህረ ነጋሽ ሻዕቢያን ከምዕራብ ኤርትራ አባርሮ ወደ ሳሕል በረሃ የመመለስ እቅድ ነበረው የዘመቻው አቅድ በመገናኛ ብዙሃን በይፋ ባይታወጅም እንኳ ለዘመቻ በተሰለፈው የሰው ሀይልና በተመደበለት የጦር መሳሪያ ዓይነትና ብዛት ከቀይ ኮከብ ሁለገብ ዘመቻ ጋር ይስተካከላል ሀገሪቷ የነበሯት ምርጥ የጦር መኮንኖችም በአዛዥነት ተሰልፈዋል የዘመቻው የበላይ አዛዥ እውቁ የጦር ሰው ሜጀር ጄኔራል መርዕድ ንጉሜ ሲሆኑ በርሳቸው ስር ሜጄ ደምሴ ቡልቶ ሜጄ አበራ አበበና ሜጄ ረጋሳ ጅማ ተሰልፈው ነበር የአየር ሀይሉ ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይም ከምርጥ አብራሪዎች ጋር ተሰልፈዋል ዘመቻው በታቀደለት ፕሮግራም መሰረት በሰኔ ወር ተጀመረ ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት በከፍተኛ ወኔ ሻዕቢያን ከምዕራብ ኤርትራ እያባረረ በድል ገሰገሰ ሻዕቢያ በታሪኩ አይቶት የማያውቅ ሀያል ሰራዊት ገጠመው ከ እስከ የሚሆን ተዋጊ አለቀበት በዚህም የተነሳ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ባሬንቱና ተሰነይን ለመልቀቅ ተገደደ ለአስራ ስምንት ወራት የገነባው መከላከያ ስላልሰራለት በስልታዊ ማፈግፈግ ስም ወደ ሳህል በረሃ መሸሽ ግድ ሆነበት አብዮታዊ ሰራዊትም ማንንም ባስደነቀ ፍጥነት እየተጓዘ ከናቅፋ በር ላይ በድጋሚ ደረሰ ሆኖም በዚህኛውም ጊዜ በግልጽ ባልታወቀ ምከንያት ውጊያውን እንዲያቆም ታዘክዘ የዘመቻ ባህረ ነጋሽ አፈጻጸም ሲገመገም ውጤቱ ጥሩ ሆኖ በመገኘቱ ሊቀመንበር መንግሥቱ ቀጣይ ዘመቻዎችንም በተመሳሳይ ስልት ለማካሄድ ከውሳኔ ላይ አንዲደርሱ አድርጎአቸዋል ይሁን አንጂ በዘመቻው ከፍተኛ የሰው ሀይል መስዋእት ሆኖአል በተለይ ከአስር ሺህ የማያንሱ የአንደኛው ዙር ብሄራዊ ውትድርና ዘማቾች አልቀውበታል በዚህም የተነሳ በኢትዮጵያዊያን የጦር አዛኙች ልብ ውስጥ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል ጄኔራል ፋንታ በላይ እንደተናገሩት ሊቀመንበር መንግሥቱን ከአመራር ለማስወገድ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ማውጠንጠን የጀመሩት በዘመቻ ባህረ ነጋሽ ወቅት የተከሰተውን የወገን ጦር እልቂት ካዩ በኋላ ነው ጄኔራል ፋንታ ሁኔታውን ሲገልጹት እንዲህ ብለው ነበር ሊቀመንበር መንግሥቱ እኛ ያዘጋጀነውን የውጊያ አቅድ ትተው የኛን ወታደሮች አንደ ጭራሮ በሚቆጥሩት የሶቪየት አዛች የተዘጋጀውን የውጊያ እቅድ በመቀበል ከፍተኛ መስዋእትነት አንድንከፍል አስደረጉን መስዋዕትነት መከፈላችን ካልቀረም ውጊያውን በጀመርንበት ፍጥነት መቀጠል ሲገባን አለምንም ምከንያት እንድናቆም አዘዙን ዘነበ ፈለቀ ኀበር ቁጥር ሁለት ገጽ ድድድቱቴቴ ከዘመቻ ባህረ ነጋሽ ፍጻሜ በኋላ በነበሩት ሁለት ዓመታት በኤርትራ ምድር የሚደረገው ውጊያ ጋብ ብሏል በነዚያ ዓመታት ሁለቱም ተዋጊ ወገኖች አጣዳፊ ለሚሏቸው ጉዳዮች ቅድሚያ ሰጥተዋል በዚህም መሰረት የደርግ መንግሥት የመንደር ምስረታ እና ህገመንግሥት ማርቀቅን ለመሳሰሉ ጉዳዮች ቅድሚያ ሰጥቶ በነርሱ ላይ አተኩሯል ሻዕቢያ ደግሞ ሁለተኛውን ድርጅታዊ ጉባኤ በማዘጋጀቱ ላይ ነበር ያተኮረው ደርግ ያረቀቀው ህገመንግሥት በነሐሴ ወር ጸደቀ ኢህዲሪ የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊከ ተመሰረተ ሊቀመንበር መንግሥቱ በብሄራዊ ሸንጎ ምርጫ ፕሬዚዳንት ሆኑ አዲሱ ህገመንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሰኤርትራ ችግር ዘለቄታዊ መፍትሔ አንደሚሰጠውም ተገለጸ ሆኖም ቃል የተገባው ሁሉ የጉባኤ ላይ ልፈፋ ሆኖ ቀረ የጦርነት መንገድ የመንግሥቱ ብቸኛ ምርጫ መሆኑ ሳይውል ሳያድር ታወቀ ሆኖም የደርግ አካሄድ የሚያዛልቅ ሆኖ አልተገኘም ከደርግ ይልቅ መንገዱ ቀና ሆኖ የተገኘው በሚያዚያ ባካሄደው ጉባኤ ኢሳያስ አፈወርቂን በዋና ጸሓፊነት ለሰየመው ህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ሻዕቢያ ነው ለሰላሳ ዓመታት በዓላና ናቅፋ በረሃዎች ሲፋለሙ የቆዩት የኤርትራ አማጺያን ለመጨረሻው ግብ የሚያበቃቸውን ወታደራዊ ስልት በተግባር ላይ የሚያውሉበት ጊዜ ተቃርቦ ነበር ቀጣዮቹ ሶስት ዓመታትም የኢትዮጵያና ኤርትራን የታሪከ አቅጣጫ ከመሰረቱ የቀየሩ ታላላቅ ፍልሚያዎች የተካሄዱባቸው ነበሩ አነዚያ ታላላቅ ፍልሚያዎች ምን ይመስላሉ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

አስተያየቶች:


memezon

የማውረድ አማራጮች | ወደ ፒዲኤፍ ቀይር | የዕለቱ መጽሐፍ

© dirzon | የአገልግሎት ደንቦች | የግላዊነት መምሪያ | ስለ | አገልግሎቶች | መልእክት