Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • ወደ ፒዲኤፍ ቀይር
  • የንባብ ዝርዝር
  • አጠሬራ
  • ኦዲዮ መጽሐፍ
  • ፍለጋ
  • ይስቀሉ
  • የኔዞን
  • ይግቡ
  • ይመዝገቡ
English  አማርኛ  Français  العربية
የዕለቱ መጽሐፍ

70 የፆም አጀንዳዎች.pdf


  • የቃላት ደመና

70 የፆም አጀንዳዎች.pdf
  • የማውጣት አጠሬራ

  • Cosine ማጠቃለያ

ሂራ ህህ ራጋ ቃ ዕጨ ኃዱ መጋ ውሪ ዖሪህ በአማረኛ ቋንቋ ፆምን የሚመለከቱ ሰባ ጠቃሚ ነጥቦች ሸይኸ ሙሐመድ ሳሊህ አልሙነጂድ ያዘጋጄቸዉ የሆኑ ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነዉ እናመሰግነዋለን እገዛዉንም ምህረቱንም እንጠይቀዋለን ከነፍሶቻችን ከፋትና ከስራዎቻችን መጥፎ በአላህ እንጠበቃለን አላህ ቅኑን መንገድ የመራዉ ሊያጠመዉ የሚችል የለም አላህ ያጠመመዉ ደግሞ ትክክለኛዉን መንገድ ሊመራዉ የሚችል አካል የለም ከአላህ በስተቀር ሌላ በእዉነት የሚመለከ አምላከ አለመኖሩን እሱ አጋር የሌለዉ አንድ አምላከ መሆኑን እመሰከራለሁ ሙሐመድ የአላህ አገልጋይና መልዕከተኛ መሆናቸዉን እመሰክራለሁ አላህ መልካም ነገሮችን ባዘሉ ወራት ምክንያት ለባሮቹ ወደር የለሽ ፀጋን ለግሷል በነፒሂህ ወራት መልካም ስራዎች ምንዳቸዉ ይነባበራል ወንጀሎች ይታበሳሉ ደረጃዎች ይጨምራሉ ከነኝህ መልካም ነገሮችን ካዘሉ ወራት መካከል ትልቅ ግምት የሚሰጠዉ አላህ ጩ በባሮቹ ላይ ግዴታ ያደረገዉ የረመዷን ወር አንዱ ነዉ አንዲሁም በጉጉት እንዲጠቀሙበት አድርጓል ግዴታ ስላደረገዉም ያመሰግኑት ዘንድ አመላከቷል ይህ የረመዷን ኢባዳ ደረጃዉ ከፍ ያለ ስለሆነ ከዚህ ወር ጋር ትስስርነት ያላቸዉን ህጎች የፆም ህጎችን ስርዓቶችን እና መማር ግዴታ ይሆናል ይህ መልዕከት ሱናዎችን ጠቅለል ባለ መልኩ አቅፎ የያዘ መልዕከት ነዉ ፆም ማለት ምንዲን ነዉ ፆም በቋንቋ ደረጃ መከልከል ማለት ሲሆን ግን እንደኢስላም ህግ ሌሊቱ ከመንጋቱ በፊት ለመዖም ኒያ ሀሣብ በማድረግ አላህን በማምሰክ አላማ ጠዋት ሁለተኛዉ ጎህ ከቀደደበት ከወጣበት ጀምሮ እስከ ፀሐይ መጥለቅ ድረስ ፆምን ከሚያበላሽ ነገር መከልከል ነዉ የፆም ህግብይን የረመዷን ወር መፆም ግዴታ ለመሆኑና ምንም ምክንያት የሌለዉ ሰዉ በረመዷን ወር ካፈጠረ በርግጥ ትልቅ ወንጀል የፈፀመ ለመሆኑ ሙስሊሞች ተስማምተዋል የፆም ትሩፋት ከፆም ትሩፋቶች መካከል አላህ ፆምን ለራሱ መርጦ በሱ የተነባበረን ምንዳ የሚከፍል የፆመኛ ዱዓ የማይመለስ ፆመኛ ሰዉ ሁለት ደስታዎችን ማግኘቱ ፆም ለባሪያ የቂያማ ቀን መሸምገሉ የፆመኛ ሰዉ አፍ ጠረን አላህ ዘንድ ከሚስከ ሸታ የበለጠ መዓዛ ያለው መሆኑ ፆም ከገሀነም አሳት የሚጠብቅ መከላከያ ምሸግ እና ጋሻ መሆኑ ጂሃድ ላይ አንድ ቀን የዖመ በዚህ ቀን ምከንያት አላህ ፊቱን ከሳት የሰባ ዓመት ያህል የሚያርቀዉ መሆኑ በገነት ዉስጥ ከፆመኞች በስተቀር ማንም ሊገባበት የማይቸል የሆነ ረይያን የሚባል በር መኖሩ እነኝህ ለምሳሌ ያህል የቀረቡ የረመዷን ትሩፋቶች ናቸዉ የረመዷን ፆም ከኢስላም ማዕዘናት አንዱ ነዉ ቁርዓን የወረደበት ወር ነዉ የተላቀች ሌሊት ከአንድ ሺ ወራት የምትበልጥ የምትገኝበት ነዉ የረመዷን ወር ሲገባ የሰማይየጀነት በሮች ይከፈታሉ የገሀነም በሮች ይዘጋሉ ሰይጣኖችም በሰንሰለት ይታሰራሉ የረመዷን ፆም እንዴ አሥር ወሮች ይቆጠራል ይህን ለማብራራት አንድ በጎ ስራ አላህ ዘንድ አሥር እጥፍ ምንዳ አለዉ የረመዷን ፆም በአስር ወሮች ይቆጠራል ስድስት የሸዋል ቀናት ደግሞ በሁለት ወሮች ይቆጠራሉ ድምራቸዉ ወራት አንድ ዓመት ይሆናል በዚህ ዓይነት ፆሙ በየዓመቱ ከተደጋገመ ዕድሜ ልከ አእንደመፆም ይቆጠራል ማለት ነዉ ላህ አዕለም የፆም ጥቅሞችፋዒዳዎች ፆም ከተቅዋርአላህን ከመፍራት ጋር የተሳሰሩ ብዙ ጥቅሞችን ያዘለ ነዉ ፆም ሰይጣንን ለማሸነፍ ስሜትን ለመስበር የሰዉነትን ከፍል ለመቆጣጠር መንገድ ነዉ ከመጥፎ ስሜትና ወንጀል የመራቅ ፍላጎትን ያዳብራል እንዲሁም ከስርዓቶች ና ከቃል ኪዳን ጋር መላመድን ያስተምራል ይህ ወር የሙስሊሞች አንድነት የሚጀምርበት ወር ለመሆኑ አዋጅ ጥቆማ አለበት የፆም ስርዓቶችና ሱናዎች ግዴታ ወይም ተወዳጅ የሆነ አለ እሱም ለኩለ ሌሊት ምግብ ግምት መስጠትና ማዘግየት ፊጥር ማፋጠን ረሱል እንዲህ ብለዋልሰዎች በጎ ነገር ከመፈፀም አይወገዱም ፆማቸዉን ወቅቱ እንደገባ በአስቸኳይ እስካቆሙ እስካፋጠሩ ድረስ ረሱል ከመስገዳቸዉ በፊት በተምር እሸት ያፈጥሩ ነበር ይህን ካላገኙ በደረቅ ተምሮች ይህን ካላገኙ በዉሃ ያፈጥሩ ነበር ካፈጠሩ በኋላ ጥማቱ ሄደ ጅማቶችም ራሱ በአላህ ፍቃድም ምንዳዉ ፀና ይሉ ነበር ተገቢ ያልሆኑ መጥፎ ነገሮችንና ወንጀሎችን መራቅ መልካም ነገሮች አንዲወገዱና እንዲጠፉ እነዲሁም መጥፎ እንዲስፋፋና እንዲከሰት ከሚያደርጉት ጥቂቶቹ ለምሳሌ አፈ ታሪከ ተረቶች ሙሰልሰሎች ድራማ ኳስ ጨዋታ ከጥቅም ያገለለ የሆነ ስብሰባ ና መንገዶች ላይ በመዝናናት ጊዜን ማባከን ናቸዉ ምግብ መቀነስ ረሱል የአደም ልጅ ከዕቃዎች ሁሉ እንደ ሆድ ያለ መጥፎ ዕቃ አይሞላም ብለዋል በዕዉቀት በገንዘብ በስልጣን በአካልና በጥሩ ፀባይ ቸር መሆን ረሱል በእርግጥ በመልካም ነገር እንደሳቸዉ ቸር ማንም አልነበረም በተለይም ረመዷን ወር ላይ በተከበረዉ ወር ዉስጥ መሰራት ያለበት ነገር ነፍሶችን እና ሁኔታዎችን አላህን ለማምለከ ዝገጁ ማድረግበፍጥነት ወደ አላህ በመመለስ ተዉባህ ማድረግ ረመዷን በመግባቱ መደሰት ፆምን በሚገባ መፆም ተራዊህን በፍርሀት መስገድ መካከለኞቹ አሥር ቀናት ላይ አለመሰላቸት ለይለተል ቀድርን መጠባበቅ ምፅዋትሶደቃ ማብዛትናየመጨረሻ አሥር ቀናት እዕቲካፍ መቀጥ ለረመዷን ወር እንኳን በሰላም አደረሳችሁ ቢባል ችግር የለዉም ረሱል ረመዷን በመግባቱ ለሶሃቦች አንኳን ደስ አላችሁ ይሉ ነበር ትኩረት እንዲሰጡትም ቅስቀሳ ያደርጉ ነበር የፆም ህጎች ከፆም በተከታታይ መፆም ግዴታ የሆነ አለ ለምሳሌየረመዷን ፆም በስህተት ሰዉ የገደለ ማበሻከፍፋራፆም ሚስቱን እንደ አናቴ ጀርባ ነሸ ያለ የቅጣት ከፍያ ከፍፋራንዖም ረመዷን ዉስጥ ቀን ከሴት ጋር ግንኙነት የፈፀመ እንዲሁም በተከታታይ መፆም ግዴታ ያልሆነ አለለምሳሌየረመዷን ቀዷ ማረድ ያልቻለ ሐጃጅ የሚፆማቸዉ አሥር ቀናት ግዴታ ያልሆነ የፍላጎት ፆም ግዴታ የሆነን ፆም እንከን ይጠግናል ጁሙዓን ከቀናት ለይቶ መፆም ከልከል ነዉ እንዲሁም ቅዳሜን ግዴታ የሆነ ፆም ሲቀር እንዲሁም ዓመትን በሙሉ መፆም ፏ ያለፊጥርፀሀይ እንደገባች ሳይመገብና ሳይጠጣ ፆምን መቀጠልሁለቱን የዒድ ቀናት አና አይያመተሸሪቅም መፆም ሀራም ነዉ የረመዷን ወር መግባት የረመዷን ወር መግባት ጨረቃን በማየት ወይም የሸዕባን ወር ሰላሳ ቀን በመሙላት ይታወቃል ነገር ግን በካላንደር መጠቀም ቢድዓ ነዉ ፆም በማን ላይ ግዴታ ይሆናል ሙስሊም በሆነ ለአቅመ አዳም በደረሰ ጤናማ አዕምሮ ባለዉ መንገደኛ ባልሆነ ለመፆም በሚችል እና ፆምን ከሚከለከሉ ነገሮች ነፃ መሆን ለምሳሌከወር አበባና ከወሊድ ደም ዝ ሰባት ዓመት የሆነዉ ህፃን የሚችል ከሆነ አንዲዖም ይታዘዛል እንደዉም ከፊል ዑለማዎች አሥር ዓመት ላይ የማይዖም ከሆነ ለሶላት እንደሚገረፍ ሁሉ ለፆምም ይገረፋል ብለዋል ግማሽ ቀን ላይ ከሃዲካፊር የነበረ ቢያምን ወይም ህፃኑ ለአቅመ አዳም ቢደርስ ወይም የአዕምሮ በሽተኛ ቢሻለዉ ሁሉም የቀረዉን ቀን መከልከል ግዴታ ይሆንባቸዋል ግን ከወሩ ያመለጣቸዉ ቀዷ የለባቸዉም የአዕምሮ በሽተኛ ተጠያቂ አይደለም አንዳንድ ጊዜ የሚሻለዉ ሌላ ጊዜ የሚታመም ከሆነ በሽታዉ ሲያገልለትሲወገድለት መፆም ግዴታ ይሆንበታል በሚታመም ጊዜ ግን ግዴታ አይሆንበትም በሰይጣን ከመለከፉ የተነሳአዉድቅ የጣለዉ ሰዉ ካለፈው ህግ ጋር ተመሳሳይ ነዉ ረመዷን ወር ዉስጥ የሞተ ሟቹም ሆነ ዘመዶቹ በቀሩት ቀናት ተጠያቂ አይደሉም የረመዷን ፆም ግዴታ መሆኑን ያላወቀ እንዲሁም መመገብ እና ከሴት ጋር ግንኙነት መፈፀም ሀራም መሆኑን ያልተረዳ ሰዉ ይህን አንዲሁም ትከከለኛዉ አቋም ይህን ቀን ቀዷ ማዉጣት የለባቸዉም የሚለዉ ነዉ ተርጓሚው የአዕምሮ በሽተኛ መጀመሪያ ፆም ግዴታ ስላልሆነበት ቀዷ የለበትምተርጓሚው ነገር ግን ዐሊሞች ይህ ሰዉ የመፆም ግዴታ ስላለበት ቀዷ ግዴታ ይሆንበታል ብለዋል ተርጓሚው ቢፈፅም ያቀረበዉ ምክንያት ተቀባይነት ያለዉ ከሆነ በርካታዎቹ ዐሊሞች ተቀባይነት አለዉ ብለዋል ግን ሙስሊሞች መካከል የሚኖር ሆኖ መጠየቅና መማር እየቻለ ከሆነ ይህን የፈፀመዉ ያቀረበዉ ምከንያት ተቀባይነት የለዉም ጉዞ ላይ መፆም ጉዞ ላይ ማፍጠር መስፈርት አለዉ በርቀት ወይም ከሰዎች ልምድ አንፃር መንገድ መባል አለበት እንዲሁም የሚኖርበትን ሀገርና ከሀገሩ ጋር የተያያዙ አካባቢዎችን ያለፈ መሆን ዐሊሞች ጉዞዉ ወንጀል የሚሰራበት እንዳይሆን ይላሉ ተጨማሪም ጉዞዉን ምከኒያት በማድረግ ለማፍጠር ያሰበ መሆን የለበትም መንገደኛ ማፍጠር አንደሚችል ሙስሊሞች ተስማምተዉበታል ጠንካራ ቢሆንም ደካማ ጥግር ላይ የሚወድቅ ቢሆንም ባይሆንም በረመዷን ጉዞ የወሰነ እስከሚጓዝ ድረስ ለማፍጠር ኒያ ማድረግ የለበትም ከወጣ በኋላና የሚኖርበትን ሀገር አካባቢና ቤቶች ካለፈ በኋላ ቢኃን እንጄ ምድር ላይ እያለ ፀሀይ ከገባች በኋላ አፈጠረ ከዚያ አዉሮፕላኑ ጉዞ ቢቀጥልና ፀሀይ እንዳልገባች ቢረዳ በፆሙ ላይ መቀጠል ግዴታ አይሆንበትም ለምን ቢባልምድር ላይ እያለ ፆሙን በሙሉ ስላጠናቀቀ እሚጓዝበት ሀገር ከደረሰ በኋላ ከአራት ቀናት በላይ እንደሚቀመጥ ካሰበ በርካታዎቹ ዑለማዎች መፆም ግዴታ ይሆንበታል ብለዋል ሀገሩ እያለ ፆምን ቢጀምር እና ከቀኑ መካከል ላይ ጉዞ ቢቀጥል ማፍጠር ይችላል ምን ጊዜም ጉዞ ላይ ያለ የሚጠጋበት ሀገር ያለዉ ቢሆንም እንኳ ማፍጠር ይችላል ለምሳሌፖስታ ቤት ሰራተኛ ከአንድ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ተመላላሽ ሾፌሮች አዉሮፕላን አብራሪዎች እና አስተናጋጆች ጉዚቸዉ አለት በዕለት በየቀኑ ቢሆንም እንኳ ነገር ግን ቀዷ ማዉጣት አለባቸዉ እንዲሁም የብስ ላይ መኖሪያ ያለዉ የመርከብ ኮፌር ይህ ገደብ ምንም ዓይነት መረጃ የለዉም ትክክለኛዉ እሚሜጓዝበት ሀገር አንደደረሰ አቀመጣለሁ የሚል ዉሳኔ ከወሰነ የመፆም ግዴታ አለበት ነገር ግን መቀመጥን ካልወሰን ማፍጠር ይትላል የሚለዉ አስተያየት ነዉ ተረጓሚው ጉዞ ላይ የነበረ ከቀኑ መካከል ላይ አገሩ ቢገባ ጥንቃቄ ለማድረግ የወሩን ከብር ለመጠበቅ መከልከሉ ጥሩ ነዉ ነገር ግን ተከለከለም አልተከለከለም ቀዷ አለበት ሀገር ላይ እያለ ፆምን ቢጀምር ከዚህ በኋላ ወደ ሌላ ሀገር ቢጓዝ እነዚህ ሰዎች ፆምን የጀመሩት ከነሱ በፊት ወይም በኋላ ቢሆንም ይህ ሰዉ የሀገሩን ህግ ሳይሆን የነዚህን ሰዎች ህግ መከተል አለበት የበሽተኛ ፆም ማንኛዉም በሽታ የሰዉ ልጅን ጤነኛ ከመባል እንዲወጣ የሚያደርገዉ ከሆነ ማፍጠር ይቻላል ነገር ግን ቀላል ከሆነ ለምሳል ጉንፋን እና የራስ ምታት ይህን ምክንያት በማድረግ ማፍጠር አይፈቀድም በሐኪም ቢረጋገጥ ወይም አንድ ሰዉ ከተሞከሮዉ ከልምዱና ከጥርጣሬዉ አንፃር ፆም ቢፆም በሽታ አንደሚያመጣበት ወይም በሽታዉ እንደሚጨምርና እንደሚዘገይ ከተረዳ ማፍጠር ይችላል ይልቁንም መፆሙ ይጠላል መፆሙ ለአዉድቅ በሽታ የሚዳርገዉ ከሆነ ያፍጥር እና ቀዷ ያዉጣ ከቀኑ መካከል ላይ አዉድቁ ቢጥለዉ ፀሀይ ከመግባቷ በፊት ወይም ከገባች በኋላ በሽታዉ ቢሻለዉ ፆሙ ትከከል ነዉ ፆመኛ አስከሆነ ድረስ በሸታዉ የጀመረዉ ጎህ ከቀደደ ከወጣጀምሮ እስከ መግሪብ ድረስ ከሆነ በርካታዎቹ ዐሊሞች ፆሙ ተቀባይነት የለዉም ብለዋል አዉድቅ በሽታ የጣለዉ የፈለገዉን ያህል ቢቆይበትም በርካታዎቹ ዐሊምች ቀዷ ማዉጣት ግዴታ ይሆንበታል ይላሉ ገደብ ያለፈ ረሃብ ወይም ሀይለኛ የዉሃ ጥም ቢያደከመዉ በሕይወቱ ላይ ሞትን ከፈራ ወይም ከሰዉነቱ ከፍል ከፊሉ ከጥቅም ዉጭ ይሆናል የሚል ብዢታ ሳይሆን ጥርጣሬዉ ካመዘነ አፍጥሮ ቀዷ ያወጣ ከባድ በሆነ ሙያ ላይ የተሰማሩ ሰዎች ማፍጠር አይፈቀድላቸዉም ከቀኑ መካከል ላይ ስራዉን ቢያቆሙት ጉዳት የሚያመጣ እና በስራዉ ላይ ቢቀጥሉ በሕይወታቸዉ ላይ ሞትን የሚፈሩ ከሆነ ያፍጥሩ ቀዷ ያዉጡ የተማሪዎች ፈተና በረመዷን እንዲያፈጥሩ የሚያደርግ በቂ ምክንያት አይደለም በሽተኛዉ በሸታየ ይወገድልኛል ብሎ ተስፋ ካደረገ አስከሚድን ድረስ ትግስት ያድርግ ከዚያም ቀዷ ያዉጣ ድሆችን ማብላቱ በቂ አይደለም በሽተኛዉ በሽታየ ፈፅሞ አይወገድም የሚል እምነት ካለዉ እንዲሁም በዕድሜ የገፋ ሽማግሌ ሀገሩ ላይ ህዝቦች ከሚመገቡት በየቀኑ ላንዳንድ ድሃ የቁና ግማሸ ያብላ ታሞ የዳነ ቀዷ ለማዉጣት ጊዜ አያገኘ ቀዷሳያወጣ ቢሞት ከንብረቱ ለያንዳንዱ ቀን ለድሃ የሚሰጥ መመደብ አለበት ከዘመዶቹ አንዱ ቢዖምለት ፆሙ ተቀባይነት አለዉ የሽማግሌ የደካማና ያዛዉንት ፆም ሽማግሌ እና በዕድሜ መግፋት ምክንያት ጉልበቱ የደከመ አዛዉንት ፆም ግዴታ አይሆንባቸዉም መፆም የሚከብዳቸዉና የሚያንገላታቸዉ ከሆነ ማፍጠር ይትላሉ ለየቀኑ አንዳንድ ድሃ ማብላት አለባቸዉ ነገሮችን መለየት የማይችል እና ከቁጥጥር ዉጭ የሆነ አዛዉንት ግዴታ ስለሌለበት በሱም ላይ ሆነ በቤተሰቦቹ ምንም ነገር የለባቸዉም ከጥላት ጋር የሚፋለም ወይም ሀገሩ በጠላት የተከበበ መፆም ከመጋደልከመፋለም የሚያደከመዉ ከሆነ ጉዞ ላይ እንኳ ባይሆንም ማፍጠር ይችላል እንዲሁም ከግድያ በፊት ማፍጠር ካስፈለገዉም ማፍጠር ይችላል ለማፍጠር ምከንያት የሆነዉ ነገር በግልፅ የሚታይ ከሆነለምሳሌ በሽተኛ በግልፅ ማፍጠር ይችላል ግን ስዉር ከሆነ የወር አበባን ይመስል ሰዎች በመጥፎ ነገር እንዳይጠረጥሩት ተደብቆ ማፍጠሩ የተመረጠ ነዉ ለመፆም ኒያ ማድረግ ፈርድ ግዴታ በሆነ ፆም ላይ ኒያ ማድረግ መስፈርት ነዉ አንዲሁም ዋጂብማዴታ የሆነን ፆም ቀዷበሚወጣ ጊዜ እና የከፍፋራ ማበሻ ፆም በሚጾም ወቅት ኒያ መስፈርት ነዉ ሌሊት በማንኛዉም ሰዓት ኒያ ማድረግ ጎህ ከመቅደዱ በፊት በተወሰኑ ደቂቃዎች ልዩነት እንኳ ቢሆን ኒያ ማድረግ ይቻላል ኒያ ማለት ለመፆምለመተግበር እርግጠኛ በመሆን ሀሣብ ማሳደር ነዉ ባንደበት መናገር አዲስ ፈጠራቢድዓነዉ ረመዷንን የሚፆም ሌሊቶች በመጡ ቁጥር ኒያ ማደስ አያስፈልገዉም ይልቁንም ወሩ እንደገባ መጀመሪያ ላይ ኒያ ማድረጉ በቂ ነዉ ገደብ የሌለዉ ትርፍ ፆም ሌሊት ኒያ ማድረግ መስፈርት አይደለም ነገር ግን ገደብ የተደረገለት ትርፍ ፆም አህወጡጥንቃቄ ለማድረግ ሌሊት ኒያ ማድረግ በላጭ ነዉ ዋጂብግዴታ ፆምን ለመፆም የጀመረ ለምሳሌቀዷ ስለት አና ከፍፋራማበሻንመሙላት ግዴታ ይሆንበታል ያለ ምከንያት ማፍጠር አይቻልም ትርፍ ፆም ከሆነ ፆመኛዉ ራሱ ያዉቃል ከፈለገ ይፁም ከፈለገ ያፍጥር ምንም ምከንያት ባይኖረዉ እንኳ ረመዷን መግባቱን ጎህ ከቀደደ በኋላ እንጂ ያላወቀ ሰዉ ቀሪዉን ቀን መከልከል አለበት በርካታ ዐሊሞችም ቀዷ አለበት ብለዋል እስረኛ እና በሰዎች ቁጥጥር ስር የታገደ ራሱ ጨረቃን አይቶም ይሁን ታማኝ ሰዉ ነግሮት ወሩ መግባቱን ከተረዳ መፆም ግዴታ ይሆንበታል አልያም ትግል በማድረግ በግምት መጠቀም ይኖርበታል ማፍጠር እና መከልከል የፀሀይ ጨረር እንደገባ ፆመኛ ማፍጠር አለበት በአድማሱ ላይ የሚታየዉ ቀይ ነገር ግምት አይሰጠዉም ጎህ ከወጣ ፆመኛ አዛን ይስማም አይስማም በፍጥነት መከልከል አለበት ለጥንቃቄ እየተባለ ጎህ ከመዉጣቱ በፊት የአሥር ደቂቃና ሌላም ደቂቃ ይሁን ልዩነት እያለ መከልከል አዲስ ፈጠራ ቢድዓነዉ በሃያ አራት ሰዓት ዉስጥ ሌሊትና ቀን የሚገኙበት ማንኛዉም ሀገር ቀኑ ረጂም ቢሆንም የመፆም ግዴታ አለባቸዉ ፆምን የሚያበላሹ ነገሮች ብ ከወር አበባና ከወሊድ ደም ሌላ ፆምን የሚያበላሹ ነገሮች የዖመኛዉ ፆም ለመበላሸት ሶስት መስፈርቶች መሟላት አለባቸዉ ፆምን በሚያበላሸዉ ነገር መሃይም ሳይሆን እዉቀት ያለዉ መሆን እረስቶ ሳይሆን እያስታወሰ እና ተቸግሮና ተገዶ ሳይሆን በምርጫዉ መሆን አለበት ፆምን ከሚያበላሹ ነገሮችለምሳሌግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም አዉቆና ሆን ብሎ ማስታወክ የወር አበባ መታገምመመገብና መጠጣት ናቸዉ ምግብን እና ዉሃን የሚተኩ ነገሮች ፆምን ከሚያበላሹት ይመደባሉ ለምሳሴ መድኃኒቶች እና በአፍ የሚዋጡ ከኒኖች ግን ምግብንና ዉሃን ሊተኩ የማይችሉ ለመድኃኒት ብቻ የሚገለገሏቸዉ ከሆኑ ፆም ላይ ችግር አያመጡም እንዲሁም የኩላሊት በሽታ ያለበት አዚህ ላይ ትከከለኛዉ ከመረጃ አንጻር መታገም አያስፈጥርም በመታገሙ ምከንያት ስለደከመ የሚያፈጥር ከሆነ መታገም ሀራም ይሆናል ግን ከመፆም የማያደከመዉ ከሆነ ይጠላል እንጂ አያስፈጥርም የሚለዉ ነዉተረጓሚው ኩላሊቱን ቢያሳጥብ ፆሙ አይበላሽም በሰገራ መጠቀሚያ ላይ በመርፌ ምከንያት የሚገቡ መድኃኒቶች እንዲሁም የአይንና የጆሮ ጠብታ ጥርስ ማስወጣት እና ለቁስል መድሃኃቶች መጠቀም ፆም አያበላሽም ለሳምባ ነቀርሳ በሽታ መድኃኒት ማስረጨትም ለምርመራ ደም መስጠትመለገስ አያበላሽም ጣረ ሞት ላይ ለሆነ የሚሰጥ መድኃኒት አስካልዋጠዉ ድረስ አያበላሽም ለጥርሱ ማጠናከሪያ ያስጨመረ የዚህን ጣዕም ከጉሮሮዉ ላይ ቢያገኝ በፆሙ ላይ ችግር አያመጣም ያለምንም ምከንያት በረመዷን ቀን አዉቆና ሆን ብሎ የበላ ወይም የጠጣ ትልቅ ወንጀል ፈፅሟል ተዉባህ ማድረግና ቀዷ ማዉጣት አለበት ፆመኛ መሆኑን ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰዉ ፆሙን ያሟላ ያበላዉና ያጠጣዉ አላህ ነዉና ረስቶ የሚመገብን ፆመኛ ያየ ፆመኛ መሆኑን ያስታዉሰዉ የተከበረውን የሠዉ ልጅ ከሞት ለማዳን ማፍጠር ያስፈለገዉ ሰዉ ያፍጥር እና ቀዷ ያዉጣ መፆም ግዴታ የሆነበት ሰው በረመዷን ቀን አዉቆና ሆን ብሎ በምርጫዉ ግብረ ስጋ ግንኙነት ቢፈፅም ፆሙ ይበላሻልተዉባህ ማድረግ ግንኙነት የተፈፀመበትን ቀን በፆም ማጠናቀቅ በፆሙ ላይ መቀጠል ቀዷ እና ከፍፋራመቀጫ ግዴታ አለበት ይህ ህግ ዝሙትም ይሁን ግብረ ሰዶም እንዲሁም ድርጊቱ በእንስሳዎች ላይ ቢፈፀም ተመሳሳይ ነዉ ከባለቤቱ ጋር ግንኙነት ማድረግ ፈልጎ መጀመሪያ ምግብ በመብላት ፆሙን ቢያበላሽ ወንጀሉ በጣም የከበደ ይሆናል በአርግጥ በመብላቱና ግንኙነት በመፈፀሙ የወሩን ከብር ሁለት ጊዜ ተዳፍሯል የመቀጫ የሆነዉ ከፍፋራም በጣም የከበደ ይሆናል ፆመኛዉ ነፍሱን መቆጣጠር የሚችል ከሆነ ከሚስቱና ከባሪያዉ ጋር መሳሳም መነካካት መተቃቀፍመተሻሸት እና በተደጋጋሚ መመልከት ይቸላል ነገር ግን ስሜቱ ፈጣን ከመሆኑ አንፃር ነፍሱን መቆጣጠር የማይችል ከሆነ እነኝህን ነገሮች በሙሉ መራቅ አለበት ግንኙነት እያደረገ ጎህ ድንገት ቢወጣ በፍጥነት ግንኙነቱን ማቋረጥ ግዴታ ይሆንበታል ብልቱን ካወጣ በኋላ ፈሳሽ ቢወጣዉ እንኳ ፆሙ ትከከል ነዉ አይበላሽም ጎሁ አንደወጣ በግንኙነቱ ላይ ከቀጠለ ያፍጥር ተዉባህ ያድርግ ቀዷእና የመቀጫ ከፍፋራ አለበት ጀናባ ሆኖ እያለ ቢነጋ ፆሙ ላይ ችግር አያመጣበትም የጀናባ የወር አበባን እና የወሊድ ደም ትጥበት ከፈጅር በኋላ ወዳለዉ ጊዜ ማዘግየት ይቻላል ለሶላት ግን ግዴታ መታጠብ አለበት ፆመኛዉ እንደተኛ በህልሙ የዘር ፈሳሽ ቢፈሰዉ ፆሙ አእንደማይበላሽ ዐሊሞች ተስማምተዋል በፆሙ መቀጠል አለበት በረመዷን ቀን ሊጠነቀቀዉ በሚችለዉ ነገር ምከንያት ለምሳሌ ብልትን በእጅ በመነካካት እና በተደጋጋሚ በማየት የዘር ፈሳሽ እንዲወጣዉ ያደረገ ወደ አላህ መመለስ እና ቀሪዉን ቀን መከልከል ግዴታ ይሆንበታል ከዚያም ቀዷማዉጣት አለበት ፆመኛ ሆኖ ሳይፈልግ ያስታወከ ሰዉ ቀዷ የለበትም አዉቆና ሆን ብሎ ያስታወከ ሰዉ ቀዷማዉጣት አለበት ያስታወከዉ ከቁጥጥሩ ዉጭ ሆኖ እያለ ወደ ሆዱ ቢመለስ አያስፈጥረዉም የሚበጣጠስ ማስቲካ ወይም ጣፋጭ ነገር ማኘከ ሀራም ነዉ ግን ወደ ጉሮሮዉ የሆነ ነገር ከገባ ያስፈጥረዋል አከታ አና ንፍጥ ወደ አፉ ከመድረሳቸዉ በፊት ቢዉጣቸዉከጉሮሮዉ ላይ እያለ ቢመልሰዉ ፆሙ አይበላሽም ግን አፉ ከደረሱ በኋላ ወደ ሆዱ ከመለሳቸዉ ፆሙ ይበላሻል እንዲሁም አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ምግብን መቅመስ ይጠላል ፆመኛ በረመዷን ሙሉ ቀን ጥርሱን መፋቅ ሱና ነዉ ማንኛዉም ፆመኛ በምርጫዉ ሳይሆን በድንገት ጉሮሮዉ ዉስጥ አንድ ነገር ቢገባበት ለምሳሌነስር የቁስል ፈሳሽ ዉሃ አና ቤንዚን ፆሙ አይበላሽም እንዲሁም የሚያለቅስ ሰው እንባዉ ጉሮሮዉ ዉስጥ ቢገባ ፀጉሩን ወይም ከላኛዉ ከንፈሩ ላይ የሚገኘዉን ፀጉርቀድሞ ቀመስቅባት ቢቀባ እንዲሁም ሂናዕ ቢቀባና ጉሮሮዉ ዉስጥ ጣዕሙን ቢያገኝ አያስፈጥረዉም እንዲሁም ቁስል እንዳዘና እና ሰዉነትን ለማለስለስ የሚቀቡ ቅባቶች አያስፈጥሩም ሽቶ ማሸተት እና የጭስ ሽታ ችግር የለዉም ነገር ግን ጭሱ ጉሮሮዉ እንዳይገባ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ጥንቃቄ ለማድረግ ሲባል ፆመኛ አለመታገሙ ይመረጣል በዓሊሞች መካከልያለዉ ልዩነት ጠንካራ ስለሆነ ማጨስ ፆም ያጠፋልሀያበላሻል ፆምን ለመተዉ ሱስ በቂ ምክንያትም አይደለም ዉሃ ዉስጥ መዘፈቅ ወይም ሰዉነቱ እንዲቀዘቅዝ እርጥብ በሆነ ልብስ መጠቅለል ችግር የለዉም ሌሊቱ ገና ነዉ በሚል እምነት ቢመገብ ቢጠጣና ግንኙነት ቢፈፅም እናም ጎህ እንደቀደደአንደወጣግልፅ ቢሆንለት ምንም አይነት ተግር የለበትም አንድ ሰው ፀሀይ ገብታለች በሚል ግምት አፈጠረ ነገር ግን ካፈጠረ በኋላ ፀሀይ አለመግባቷ ከተረጋገጠ ኡለማዎች ቀዷ አለበት ይላሉ አፉ ዉስጥ ምግብ ወይም መጠጥ እያለ ጎህ ቢወጣ ከአፉ ማዉጣት እንዳለበትና ፆሙ ተቀባይነት እንዳለዉ ዐሊሞች ተስማምተዉበታል ሴቶችን የሚመለከቱ የፆም ህጎች ለአቅመ አዳም የደረሰች ሴት ሰዎችን ከመፍራቷ አንፃር ባትዖም ብታፈጥር ተዉባህ በማድረግ ቀዷ ከማዉጣት ጋር ሌላ ረመዷን እስከሚመጣ ድረስ ቀዷን ያዘገየች ከሆነ ለየቀኑ መቀጫ አንዳንድ ድሃ ማብላት አለባት እንዲሁም የወር አበባ በምታይበት ጊዜ ሰዎችን ከመፍራቷ አንፃር የፆመች ሴት ህግ ከዚህ ህግ ጋር ተመሳሳይነት አለዉ ሚስት ባለቤቷ እያለ በፍቃዱ ካልሆነ በስተቀር ከረመዷን ዉጭ ያለን ፆም መፆም አትችልም ነገር ግን ከተሳፈረ ትቸላለች የወር አበባ የምታይ ሴት ንፁህ መሆኗን የምታረጋግጥበት የሆነዉን ቀስሰተልበይዷዕ ካየች ሌሊት ኒያ በማድረግ ትፁም ንፁህ መሆኗን የምትለይበት ነገር ከሌላት በጥጥ ወይም በሌላ ነገር ብልቷን ትሸገዉ ያሸገችበት ነገር ንፁህ ሆኖ ከወጣ መፆም አለባት የወር አበባ ወይም የወሊድ ደም የምታይ ሴት ሌሊት ደሟ ቢቋረጥና ለመፆም ኒያ ብታደርግ ከዚያም ከመታጠቧ በፊት ጎህ ቢወጣ ፆሟ ትከክል ለመሆኑ የሁሉም ዑለማዎች እምነት ነዉ አዚህ ላይ ትከከለኛዉ ንግግር ቀዷየለበትም የሚለዉ ነዉተርጓሚው የወር አበባ ደም ሲቋረጥ ከመሀፀን የሚወጣ ነጭ ዉሃ ነዉ ከልምድ አንፃር ነገ የወር አበባ ይመጣብኛል ብላ የተረዳች ሴት ደም እስከምታይ ድረስ ማፍጠር አትችልም በኒያዋ እና በፆሟ ላይ ትቀጥል ሴትለፆም ብላ የወር አበባዋን የሚያዘገይ መድኃኒት በመዉሰድ ከማቋረጥ ይልቅ አላህ የሰጣትን በደስታ በመቀበል በተፈጥሮዋ ላይ መቀጠሏ መድኃኒት ሳትጠቀም በደረጃ ይበልጣል መፈጠር የጀመረን ፅንስ ያስወረደች ሴት ከወሊድ ደም ላይ ስለሆነች መፆም የለባትም ይህ ካልሆነ ግን የበሽታ ደም ስለሆነ የምትችል ከሆነች መፆም አለባት የወሊድ ደም የምታይ ሴት ከአርባ ቀን በፊት ደሟ ከተቋረጠ መፆም እንዲሁም ለሶላት ገላዋን መታጠብ አለባት ግን ደሟ ከአርባ ቀን የሚጨምር ከሆነ ለመፆም ኒያ ታድርግ እና ትፁም ገላዋንም ትታጠብ ከዚህ በኋላ ቀጣይ የሆነዉ ደም የበሽታ ደም ስለሆነ የበሽታ ደም በዖም ላይ ችግር አያመጣም የምትፈራ ነፍሰ ጡር እና አመጫት የምታጠባ ሴት ከበሽተኛ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸዉ መሆኑ ተቀባይነት ያለዉ አቋም ማፍጠር ይችላሉ ከዚያም ቀዷ እንጂ ሌላ የለባቸዉም የሚለው ሀሳብ ነው የሚፈሩት በራሳቸዉም ላይ ሆነ በልጆቻቸዉ ላይ የተሰጣቸዉ ህግ ተመሳሳይ ነዉ መፆም ግዴታ የሆነባት ሴት በረመዷን ቀን ፍቃደኛ ሆና ባለቤቷ ቢገናኛት ኢስላም ለባለቤቷ ያስቀመጠዉ ህግ እርሷንም ይመለከታታል ነገር ግን ፍቃደኛ ሳትሆን ግንኙነት ላለመፈጸም ትግል እያደረገች አስገድዶ ከሆነ የተገናኛት ከፍፋራ መቀጫ የለባትም በመጨረሻም ከፆም ጋር ትስስርነት ያላቸዉ ጠቃሚ ነጥቦች አላህ አንዲወሱ ያገራቸው የሆኑት ይህን ይመስላሉ ጌታችንን አላህን በብዛት እንድናወሳዉ እንዲሁም እንድናመሰግነዉና እርሱ በሚፈልገው ሁኔታ እንድናመልከዉም ያግዘን ዘንድ የረመዷንን ወርም የአላህን ምህረት ትከከለኛዉ ያፍጥሩ ለያንዳንዱ ቀን ድሃ ይመግቡ ቀዷማዉጣት የለባቸዉም የሚለዉ የኢብኑ አብባስ እና የኢብኑ ዑመር ንግግ የሆነዉ ይህ አቋም ነዉ ከፍፋራ መቀጫማለት አንድ ባሪያ ነፃ ማዉጣት ይህን ካላገኘ በተከታታይ ሁለት ወር መፆም ይህን ካልቻለ ስልሳ ድሃ ማብላት ነዉ በማግኘትና ከእሳት ነፃ በመዉጣት የምንጨርስ እንዲያደርገን አለምነዋለሁአማጸነዋለሁ የአላህ እዝነትና ሠላም ለአገልጋዩ እና ለመልፅከተኛዉ ለሙሐመድ እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸዉ እና ለባልደረቦቻቸዉ ሁሉ ይሁን ትርጉም አቡዘር ሀሰን ኢማም ሁሙ » ቶቅ ጋ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

አስተያየቶች:


memezon

የማውረድ አማራጮች | ወደ ፒዲኤፍ ቀይር | የዕለቱ መጽሐፍ

© dirzon | የአገልግሎት ደንቦች | የግላዊነት መምሪያ | ስለ | አገልግሎቶች | መልእክት