Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሃሃቨዘበሀፎ ፅሁፎችን በማንበብ የአፃፃፍ ክህሎትን ለማዳበርና የራስ ለማድረግ ወሳኝ ናቸው በተቻለ መጠን ልዩነት የሚያሰፍር ዳኛ ቢቻል ምጥን ባለ አገላለጽ ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር የማይስማማባቸው ነጥቦች አንዳሉ እና ነጥቦቹም ዘርዘር ብለው ቢገለጹ ይመረጣለል የአጻጻፍ አድማስ ተደጋግሞ እንደተገለፀው የአንድ ይግባኝ ሰሚ ፍቤት ዋና ተግባር በሥር ፍቤት የውሣኔ አሰጣጥ አና አካፄድ ላይ የተከሰቱ ስህተቶች በመከላከል ማረም ነው በዚህ ረገድ በሥር ፍቤቶች በርካታ ስህተቶች ተፈጽመው ሊገኙ ይችላሉ የተወሰኑት ተከራካሪ ወገን ላይ ጉዳት የማያደርሱ ሊሆኑ ይችላሉ ለምሣሌ ከሣሽ ዐዐዐዐ ብር ይገኛል በማለት የጠየቀውን ፍቤቱ ።
ሃሃቨዘበሀፎ ፅሁፎችን በማንበብ የአፃፃፍ ክህሎትን ለማዳበርና የራስ ለማድረግ ወሳኝ ናቸው በተቻለ መጠን ባለሙያዎች የሚሰጡት የውሳኔ ፅሁፎች ተነባቢ እና አሳማኝ ሊሆኑ ይገባል ይህ ካልሆነ ግን ለወቀሳ የተጋለጡ ናቸው የዚህ ምክንያትም የውሳኔው ይዘት አለዚያ ስነምግባር የጐደለው የአፃፃፍ ክህሎት ከመከተል የመነጨ ሊሆን ይችላል በአጠቃላይ የዚህ ፅሁፍ ዋና ዓላማ በውሳኔ አፃፃፍ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በማስወገድ የተሻለ የውሳኔ አፃፃፍ ስርዓት ይኖር ዘንደ እንደመነሻ ማገልገል ነው የቅድመ ክስ ዝግጅት ታሣቢ ነጥቦች የፖሊስ የምርመራ መዝገብ የደረሰው ማንኛውም ዐሕግ በወመሕሥሥቁጥር መሠረት ተገቢውን ከመወሰነ በፊት የቅድመ ውሳኔ ዝግጅቱን የተሟላ ለማድረግ የምመዝገቡን በጥንቃቄ መመርመርና ማጥናት ይኖርበታል በዚህ መሠረት በተለይ በሚከተለው ነጥቦች ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል የአሠራር ቅደም ተከተል ማውጣት ዐቃብያነ ሕግ በአጃቸው የሚገኙ የምመዛግብትን ሲያጠኑና ሲመረምሩ እስረኛ ላለበት እንዲሁም በሕዝብ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ መሆናቸው የሚታመንባቸው ከባድ ወንጀሎች የተፈጸሙበትን ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት አስፈላጊውን ተጨማሪ መመሪያ ወይም ውሳኔ መስጠት ይኖርባቸዋል ሀ በፖሊስ ምርመራ የተጣራበት ጉዳይ የወንጀል ተግባር መሆን አለመሆኑ ማለትም በወመሕቁ ድንጋጌ መሠረት ወንጀልን የሚያቋቁሙ ማለትም የህግ ሀጠበከ የድርጊት «በሸ ከዬፀበ እና የሃሳብ በ ፀፎቓዩከህ ባህሪያት ስለማሟላቱ ማረጋገጥ ለ በወመሕቁ መሠረት በምክንያትና በውጤት ርልሀ በ ሯቨፀር መካከል ግንኙነት መኖሩን በቅድሚያ ማረጋገጥ ሐ የኤግዚቪት መግለጫ የተያያዙ መሆኑን ማረጋገጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ ዐቃብያነ ሕግ የምመዝገቡን ሲመረምሩ የወንጀሉ ድርጊት በኤግዚቪት ማስረጃ የተደገፈ ስለመሆኑ የሚጠቁም ፍሬ ነገር ካለበት ስለዚሁ ጉዳይ የኤግዚቪት መግለጫው በአግባቡ የተያያዘ መሆኑን ማጣራት ያስፈልጋል የቀድሞ የጥፋተኛነት ሪኮርድ መግለጫ መያያዝ የቀድሞ የጥፋተኝነት ሪኮርድ ለቅጣት ውሣኔ አሰጣጥ አስፈላጊ ማስረጃ ሆኖ የሚቀረብ ስለሚሆን ዐቃቤ ሕግ ከያዘው የምመዝገብ አንፃር ተፈፅሟል የተባለው ወንጀል የሚያስከስስ መሆኑን የሚያስረዳ ማስረጃ ካለ ከመዝገቡ ጋር የቀድሞ የጥፋተኝነት ሪኮርድ መግለጫ መኖር አለመኖሩ መጣራት ይገባዋል የማስረጃዎችን ይዘት መመርመር ዐቃብያነ ሕግ ከተገቢው ውሣኔ በፊት የምርመራ መዝገቡን ሲመረምሩ በማስረጃነት የተቆጠሩት ምስክሮች የሚሰጡት የምስክርነት ቃል ተመሣሣይ እና እርስ በርስ የሚደጋገፍ ይሁን ወይም ደግሞ አንዱ ሌላውን የሚያፈርስ መሆን አለመሆኑን አንዲሁም ተፈፅሟል የተባለው ወንጀል በሰነድ ማስረጃም ጭምር የተደገፈ ከሆነ የምስክሮች ቃል እና የሠነድ ማስረጃው ይዘት የሚጣጣም መሆኑን ወይም ደግሞ በርካታ የሠነድ ማስረጃዎች ያሉበት ከሆነ በአከራካሪው ጭብጥ ላይ እነዚህ የሠነድ ማስረጃዎች ያላቸው የአስረጂነት ብቃት በጥልቀት መፈተሽ ይገባዋልበመሆኑም ዐቃብያነ ሕግ ከማናቸውም የወንጀል ምርመራ ክፍል የተላለፈላቸውን የምመዝገብ በማጥናት ከዚህ በላይ የተገለፁትንና ሌሎችንም አግባብነት ያላቸውን የቅድመ ውሣኔ መሰናዶዎች ካጠናቀቁ በኋላ ተከሣሹን በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ለማሰኘት የሚያስችል በቂ ማስረጃ መኖሩ ከታመነበትና ተጨማሪ ምርመራ እንዲደረግ መመሪያ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ካልተገኘ የዐቃብያነ ሕግ ቀጣይ ተግባር የወንጀል ክስ ማመልከቻ ማዘጋጀት ይሆናል በፍርድ ቤት ቀርቦ የሚታይ የማናቸውም የወንጀል ጉዳይ መሠረት የክስ ማመልከቻ ነው ጉዳዩ ሊሰማ ቀጠሮ ከተያዘበት ቀን ጀምሮ ክርክሩ በመጨረሻ ፍርድ እስኪቋጭ ድረስ በከሣሽና በተከሣሽ መካከል በደረጃው መራራ የሙግት ፍልሚያ የሚሜካሄፄድበት የምስክሮችን ትኩረት አሰባስቦ በአውነታም ሆነ በአሉታ በሚሰጡት ቃላቸው የሚፋጠጡበት ማዕከል የዐሕግ የክስ ማመልከቻ ነው በመሆኑም ፍርድ ቤት በሚቀርብ ጉዳይ ላይ ብርቱ ጥንቃቄን የሚጠይቀው ዋና ሥራ መከናወን ያለበት የወንጀል ክስ ከመዘጋጀቱ በፊትና በሚዘጋጅበት ወቅት ነው ዐቃብያነ ሕግ የክስ ማመልከቻውን ረቂቅ አዘጋጅተው እንዳጠናቀቁ በክሱ ላይ የሚጨመር ወይም የሚቀነስ ነገር መኖሩን ለማረጋገጥ የክስ ማመልከቻውን ደጋግመው ሊያነቡት ይገባል የክስ ማመልከቻው ረቂቅ ዝግጅት እንደተጠናቀቀም ክሱ ሊያስነሳ የሚችለው ታሳቢ የመቃወሚያ ነጥቦች ያሉ መሆን አለመሆኑን ከወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነሥርዓት ቁጥር አኳያ በማንሳት ክሱ ተቃውሞውን ማለፍ መቻሉን ዐቃብያነ ሕግ እርግጠኛ መሆን አለባቸውየክስ ማመልከቻው የሥነሥርዓት ሕግ በሚጠይቀው ፎርማት መሠረት መዘጋጀቱንና ማናቸውንም አስፈላጊ መረጃዎች አሟልቶ መያዙን ዐቃብያነ ሕግ በማያጠራጥር አኳጊን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል ዐቃቤሕጉ ያዘጋጀው የክስ ማመልከቻ የመጀመሪያ ደረጃ ተቃውሞዎችን ማለፍ የማይችል የይዘትና የቅርፅ ድክመት ያለበት መሆኑ እየታወቀ ለፍርድ ቤት ማስተላለፍ ተገቢ አይሆንምለወንጀል ድርጊቱ ከሚስማማ ተገቢ የሕግ ድንጋጌ ጋር ያልተዛመደ እና የወንጀሉን ዝርዝር ፍሬ ነገር በትክክል የማያመለክት የክስ ማመልከቻ ወደ ችሎት ይዞ በመቅረብ ተከሣሽን ለመርታት ክርክር መግጠም ከፍትሕ መስመር የወጣ እና ከዐቃብያነ ሕግ የሚጠበቀውን በገለልተኝነት ሙያዊ ኃላፊነትን የመወጣት መንፈስ የሚያደፈርስ የተከሣሹን የመከላከል መብት የሚያጣብብ የሀብት ብክነት የሚያስከትል እና በአጠቃላይ የማይመለስ ዘርፈ ብዙ ጉዳት የሚያስከትል ስለሚሆን የወንጀል ክስ ሲዘጋጅ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ከማናቸውም የወንጀል ምርመራ ክፍል ለዐሕግ መሥሪያ ቤት የተላከው የምመዝገብ በወንጀል የሚያስከስስ ሆኖ ሲገኝ ዐቃብያነ ሕግ የክስ ማመልከቻውን አዘጋጅተው ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ማቅረብ የሚገባው የምመዝገቡ በደረሰ በአስራ አምስት ቀን ጊዜ ውስጥ እንደሆነ የወመሕሥሥቁ ይደነግጋልየደንብ መተላለፍን የሚመለከት ካልሆነ በስተቀር ማናቸውም የወንጀል ጉዳይ በሥነሥርዓት ሕጉ መሠረት የተዘጋጀ የፅሑፍ የክስ ማመልከቻ ሳይቀርብ በፍርድ ቤት ሊሰማ አይችልምበፍርድ ቤት ሳይፈቀድ አካለ መጠን ባላደረሱት ላይ የወንጀል ክስ አይቀርብም ነገር ግን ፍርድ ቤቱ የፈቀደ እንደሆነ አካለመጠን ባላደረሱት አጥፊዎች ላይ የሚቀርበው የክስ ማመልከቻ አካለመጠን ባደረሱ ተከሣሾች ላይ እንደሚቀርበው ዓይነት ይሆናል የወመስስቁጥር መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል በክስ ዝግጅች ሂደት ዐቃቤያነ ሕግ አስቀድመው ሊያውቋቸው እና ሊያረጋግጡ የሚገቧቸው የመቃወሚያ ነጥቦች ከወንጀል ክስ አዘገጃጀት በፊትም ሆነ የክስ ማመልከቻው በሚዘጋጅበት ወቅት ከዚህ በላይ ከተገለፁት በተጨማሪ ትኩረት የሚሹ ሌሎችም ነጥቦች መኖራቸውን መገንዘብ የግድ ይላል ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው ፍርድ ቤቱ ክሱን ሰምቶ ለመወሰን ተገቢው የሥረ ነገር እና የአካባቢ ሥልጣን ያለው መሆኑን ማረጋገጥ ሀ ዐቃብያነ ሕግ የወንጀል ክስ ማመልከቻ አዘጋጅተው የሚያቀርቡት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት በአድራሻ ሲሆን ዐቃቤሕግ የወንጀሉን ክስ የሚያቀርብለት ፍርድ ቤት የሥረ ነገር አና የአካባቢ ጣምራ ሥልጣን እንዳለው ሳይረጋገጥ ክስ ተዘጋጅቶ የቀረበለት ከሆነ በወመሕሥሥቁጥር መሠረት ፍርድ ቤቱ የክስ ማመልከቻውን ባለመቀበል ስለሚመልሰው በዚህ ሂደት በሚከተለው የጊዜ ብክነት የመብት ጥሰት እና ሌሎችም አላስፈላጊ ችግሮች እንዳይከሰቱ ጥንቃቄ ማድረግ ያሻል ሌላ ተመሣሣይ ክስ በሌላ ፍርድ ቤት አለመኖሩን ማረጋገጥ በወመሕሥሥቁጥር ሀ ላይ እንደተመለከተው በወንጀሉ ዓይነት በሌላ ፍርድ ቤት ተመሣሣይ ክስ ቀርቦ በመታየት ላይ ባለበት ጉዳይ የሚቀርብ ማንኛውም ክስ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያን ስለሚያስከትል ዐሕግ በጉዳዩ ላይ ለባለመብቱ ፍርድ ቤት ክስ ከማቅረቡ በፊት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል ጉዳዩ ቀደም ሲል በፍርድ ቤት ውሣኔ ያልተሰጠው መሆኑን ማረጋገጥ በአንድ ወንጀል ድጋሚ ቅጣት ስለመከልከሉ የኢፌዲሪ ሕገመንግስት አንቀፅ በግልጽ ሲደነግግ ማንኛውም ሰው በወንጀል ሕግና ሥነሥርዓት መሠረት ተከሶ የመጨረሻ በሆነ ውሳኔ ጥፋተኛነቱ በተረጋገጠበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንደል እንደገና አይከሰስም ወይም አይቀጣም ይላልየኢፌዲሪ የወንጀል ሕግም እንዲሁ ስለሕጋዊነት መርህ ባሰፈረበት አንቀፅ ላይ በግልፅ እንደሚያረጋግጠው ማንም ሰው በሕግ መሠረት የመጨረሻ በሆነ ውሣኔ ጥፋተኛነቱ ተረጋግጦ ከዚህ ቀደም በተቀጣበት ወይም ሌላ ሕጋዊ እርምጃ በተወሰደበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና እንደማይከሰስ ወይም እንደማይቀጣ በማያሻማ አኳን ደንግጓል በዚህም መሠረት በወመሕሥሥቁጥር ለ መሠረት በዚያው ወንጀል ቀደም ሲል ተከሶ ነፃ የወጣ ወይም የጥፋተኛነት ውሣኔ የተሰጠው ግለሰብ ላይ የሚቀርብ የክስ ማመልከቻ ተቃውሞ ሊቀርብበት ስለሚችል ዐሕግ የምርመራ መዝገቡን ጥናት አጠናቆ ወደ ክስ ከማምራቱ በፊት ተከሣሽ በጉዳዩ ቀደም ሲል ተከሶ የተቀጣ ወይም በነፃ የተለቀቀ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል ክሱ በይርጋ ሕግ ያልታገደ መሆኑን ማረጋገጥ በመሠረቱ አንድ ጉዳይ በይርጋ ሕግ የታገደ ነው ወይስ አልታገደም የሚለውን ለመወሰን የይርጋውን ዘመን በትክክል ማሰላት ይገባልዐሕግ ክሱን ካቀረበ በኋላ አልፎ አልፎ በተከሣሽ በኩል በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነሥርዓት ሐ መሠረት የሚቀርብ ተቃውሞ የይርጋውን ዘመን ጊዜ በትክክል ካለማስላት የተነሳ ስለሚሆን የይርጋን ዘመን ጊዜ በጥንቃቄ ማስላት ያስፈልጋል በመሠረቱ ስለይርጋ ዘመን አቆጣጠር ስለይርጋ መታገድ ወይም መቋረጥ በወንጀል ሕጉ ከአንቀጽ እስከ ድረስ ባሉት ድንጋጌዎች ላይ የተመለከተውን መርህ ዐቃብያነ ሕግ በጥንቃቄ ማንበብ እና መገንዘብ ይኖርባቸዋልበዚህም መሠረት በሕግ በሌላ አኳን ካልተደነገገ በስተቀር ከዚህ በላይ የተመለከተው የይርጋ ዘመን ካለፈ በኋላ በማናቸውም ወንጀል የግል አቤቱታን ወይም የወንጀል ክስን መቀበልና ጉዳዩን በዳኝነት ማየት አይቻልም የክስ ተነጥሎ አለመቅረብ በተከሣሽ ላይ ጉዳት የማያስከትል መሆኑን ማረጋገጥ በመሠረቱ ዐቃቤሕግ የሚያዘጋጀው የክስ ማመልከቻ አንድ ተከሣሽ ብቻውን በፈፀመው አንድ ወንጀል ወይም አያሌ ተከሣሾች በዋናው ወንጀል አድራጊነት በግብረአብርነት በአባሪነት ወይም በአነሳሸነት ደረጃ በጋራ በፈፀሙበት አንድ ወንጀል ምክንያት አንድ ክስ የያዘ ሊሆን ይችላል ከዚህም በቀር የክስ ማመልከቻው ከአንድ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዙ ወይም ባልተያያዙ ሌሎች ከአንድ የበለጡ ተከሣሾችን የሚመለከቱ ብዙ ክሶች ሊይዝ ይችላልጉዳዩ በአንድ የምርመር መዝገብ የተጣራ እስከሆነ ድረስ አንድ ወንጀል ወይም ብዙ የተለያዩ ወንጀሎች የፈፀሙ ተከሣሾችን በአንድ የክስ ማመልከቻ ውስጥ በማጠቃለል አንድ ክስ ወይም ከአንድ የበለጡ ክሶችን አቅርቦ ማስረጃ ማሰማት ለዐቃቤሕጉ ይቀለዋልይህም ሲሆን ምስክሮቹ በሆነ ባልሆነው አንዳይመላለሱና ከዕለት ስራቸው እንደይፈናቀሉ ያደርጋቸዋል በሌላ በኩል ግን በተለይ ብዙ ተከሣሾች በተለያዩ ወንጀሉችና ክሶች በአንድ የክስ ማመልከቻ አማካኝነት ክስ ሲቀርብባቸው ከመካከላቸው በአንዳንዶቹ ላይ ጉዳት ሊደርስ ይችላል ጉዳቱም አንዳንድ ተከሣሾች በአጭር ጊዜ የሚያቀርቡት መከላከያ ጥንካሬ ወዲያውኑ በነፃ የሚያስለቅቅ ጉዳይ ሲኖራቸውአንዳንዶቹ ደግሞ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የራሳቸውን ጉዳይ ቶሎ ውሣኔ እንዳያገኝ የሚያጓትቱበት ሁኔታ ይፈጥራሉ ፍርድ ቤት በሁሉም ጉዳዮች ላይ ውሣኔ የሚሰጠው አንድ ጊዜ ስለሚሆን ጉዳያቸው ውሣኔ እንዳያገኝ የሚያጓትቱ ተከሣሾች የሚጎዱት ከሁሉም በላይ አስቸኳይ ውሣኔ የሚያስገኝ ጉዳይ ያላቸውን ሌሎች ተከሣሾች ይሆናልዐቃቤሕግ እንዲህ ዓይነት ሁኔታን ሊፈጥሩ የሚችሉ ጉዳዮችና ተከሣሾች የሚኖሩ መሆናቸውን የምርመራ መዝገቡን በሚያጠናበት ጊዜ የሚረዳ ከሆነ ችግሩን የሚያስወግድበትን ወይም የሚያቃልልበትን ሁኔታ መፍጠር ይኖርበታል በመሠረቱ በአንድ የክስ ማመልከቻ የግድ መከሰስ የሚኖርባቸው ካልሆነ በቀር ዐቃቤሕግ በመነጣጠል ክሶችን ቢያቀርብም ችግሩ ሊወገድ ይችላል ዐቃቤሕግ በራሱ አነሳሽነት ይህን ማድረግ ባይፈልግ ማንኛውም ተከሣሽ በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት ቁጥር መ መሠረት ከሌሎች ተከሣሾች ጋር መከሰሱ የሚጎዳው በመሆኑ ክሱ ከሌሎች ተከሣሾች ተነጥሎ ለብቻው እንዲቀርብበት እንዲደረግለት ተቃውሞ ማቅረብ ይቻላል ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕጉን መልስ ከሰማ በጊላ እንደነገሩ ሁኔታ ተቃውሞውን በመቀበል ወይም ውድቅ በማድረግ አስፈላጊውን ብይን ይሰጣል ክስ ለማቅረብ ፈቃድ የተሰጠ መሆኑን ማረጋገጥ አንዳንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ወይም የሕዝብ ተመራጮች የተመረጡበትን ተግባር ወይም የተጣለባቸውን የሥራ ኃላፊነትና ሥልጣን በአግባቡ እንዲወጡ ለማስቻል ሲባል የተሻለ የሕግ ጥበቃ ሊደርግላቸው እንደሚገባ በሕገመንግሥቱም ሆነ በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ ላይ በግልፅ ተመልክቷል በዚህም መሠረት እነዚህ አካላት ከባድ ወንጀል ሲፈፅሙ እጅ ከፍንጅ ካልተገኙ በስተቀር የመያዝም ሆነ ክስ የማቅረብ ሥነሥርዓት ሊፈፀም እንደማይገባ በሕጉ ተገልዷጺል ዐሕግ የደረሰውን የፖሊስ ምርመራ መዘገብ አጥንቶ ወደ ክስ ዝግጅት ከማምራቱ በፊት ከተከሣሹ ሥራ አንፃር ከሚመለከተው የመንግስት አካል በተለይ ፈቃድ የተሰጠ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል ይህ ካለሆነ ግን በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት ሠ መሠረት በሕጉ መሠረት ፈቃድ ያልተገኘበት ክስ በተከሣሽ በኩል የመጀመሪያ ደረጃ ተቃውሞ የሚቀርብበት ነው የወንጀል ክስ ማመልከቻ አጠቃላይ ይዘት ዐቃቤሕግ የምርመራ መዝገብ ወይም የቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍቤት መዝገብ ከደረሰው በኋላ ጉዳዩን መርምሮ የሚያስከስስ ሆኖ ከተገኘ በ ቀን ውስጥ ተገቢውን ክስ አዘጋጅቶ ለሚመለከተው ፍቤት ማቅረብ እንዳለበት የወመሕሥሥቁ ይደነግጋል የሥራ ብዛትና የባለሙያ ዕጥረት የወንጀሉ ውስብስብነት የተከሣሾችና የምስክሮች ቁጥር በርካታ መሆን ጉዳዩን ለመመርመር ረዥም ጊዜ የሚጠይቅ ሊያደርገው ይችላል ይልቁንም የክስ ማመልከቻው ብዙ ወንጀሎችን የሚመለከትና በርካታ ክሶችን የሚያጣምር ሲሆን ሰፊ ጊዜ መጠየቁ የማይቀር ነው በመሆኑም በሕጉ ላይ የተወሰነው የ ቀን ጊዜ ገደብ አልፎ አልፎ በቂ እንደማይሆን መገንዘብ አያዳግትምይሁን እንጂ አሰራራችንን ቀልጣፋ በማድረግ የተፋጠነ ውሣኔ መስጠት የደንበኞችን ፍላጐት ከማርካት አንፃር ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነውየሚያዘጋጀው የክስ ማመልከቻ በወመሕሥሥቁ እና ቁጥር የተገለፁትን ሁኔታዎች የሚያሟላና ከወንጀለኛ መቅጫ ሥነሥርዓት ሕግ ጋር በተያያዘው ኛ ሠንጠረዥ በምሳሌነት ከሰፈረው የክስ አዘገጃጀት ጋር የተቀራረበ መሆን ይገባዋል ከፍ ሲል በተገለፀው መሠረት የክሱ ማመልከቻ ክሱ የሚቀርብለትን ፍቤት ሥምና አድራሻ ክስ የተዘጋጀበትን ቀን እና ቁጥር የዐቃቤ ሕጉን እና የፖሊሱን መዝገብ ቁጥር ከሳሽ ዐቃቤ ህግ የተከሳሽ ስምዕድሜአድራሻና ዜግነት የምስክሮች ስም ዝርዝርና አድራሻ የዐቃቤ ህጉ ፊርማ ይኖራል የተጣሰውን የሕግ አንቀጽ የወንጀሉን ዝርዝርማለትም ወንጀሉ የተፈፀመበት ጊዜና ቦታ ተበዳዩንና ወንጀል የተፈፀመበትን ንብረት ወይም መብት የወንጀሉን አፈፃፀም ሁኔታ ከሕጉ ጋር በማገናዘብ መግለጽ ይኖርበታል ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ወንጀሎች የተፈፀሙ ሲሆንኛኛኛ ክስ እየተባለ በርዕሰ ተለይቶ እያንዳንዱ ክስ ከላይ በተገለፀው መሠረት መዘጋጀት ይገባዋልበቀረበው የምርመራ ውጤት መሠረት ወንጀል መፈፀሙ በዐቃቤሕጉ ታምናበት ነገር ግን የተጣሰው የሕግ አንቀጽ የትኛው እንደሆነ ለመወሰን ሁኔታው አሻሚ የሚሆንበት ጊዜ ሊያጋጥም ይችላል በዚህን ጊዜ ዐቃቤሕገጉ በወመሕሥሥቁ መሠረት በይበልጥ ተጥሷል ብሎ የሚያምንበትን ድንጋጌ በመጥቀስ ክስ ካዘጋጀ በኋላ በተጨማሪም ሌላውን አማራጭ የሕግ አንቀጽ በመጥቀስ ተተኪ ክስ ማቅረብ ይችላል በሌላ በኩል ተከሣሹ ደጋጋሚ ወንጀለኛ በመሆኑ ምክንያት በመጨረሻ የፈፀመው ወንጀል በሚከብድበት ጊዜወንጀሉ ባይከብድ ኖሮ መጥቀስ ያለበት የሕግ ድንጋጌ ጠቅሶ ክስ ማቅረብ አለበት ፍቤት በቀረበው መሠረት በተከሳሹ ላይ የጥፋተኛነት ውሣኔ የሰጠ ከሆነ ዐሕጉ የጥፋተኛነት ውሣኔው ወደ ከባዱ የሕግ አንቀጽ እንዲለወጥለት ያመለክታል ፍቤቱም በዚሁ መሠረት በከባዱ የሕግ አንቀጽ የጥፋተኛነት ውሣኔ አሳልፎ ተገቢውን ቅጣት ይፈርዳልክስ በሚዘጋጅበት ጊዜ ስህተት ሊከሰት ይችላል ስህተቱ ቀላልና ጉዳት የማያስከትል ወይም መሠረታዊና ተከሣሹን የሚጎዳ ሊሆን ይችላል ስህተቱ ቀላል ከሆነ የክስ ማመልከቻው ለውጥ የሚያስፈልገው አይሆንምነገር ግን ስህተቱ ከባድና ተከሣሹን የሚጎዳ ከሆነ በወመሕሥቁ መሠረት ፍቤቱ በራሱ አነሳሽነት ወይም ጥያቄ ሲቀርብለት ክሱ እንዲሻሻል ትዕዛዝ ለመስጠት ሀ ይችላልበመሆኑም በወመሕሥሥቁ መሠረት ምስክሮቹ ቃላቸውን እንዲሰጡ ያደርጋል ዐቃቤሕግ ክስ ካቀረበ በኋላ ክሱን ለመተው ወይም ለማንሳት የሚፈለግበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል ለምሳሌ ጉዳዩን በተመለከተ አስፈላጊ የሆነው ዋና ማስረጃ ሲጠፋ ክሱን መቀጠል የማይችልበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል። በዐሕግ የክስ አዘገጃጀት ረገድ በርካታ ችግሮች የሚያጋጥሙ እንደሆነ ይታወቃል በየደረጃው የሚሰሩ ዐቃብያነ ሕግ የወንጀል ሥነሥረዓት ሕጉን ያልተከተለ ልዩ ልዩ ግድፈቶች የሚታዩበትን ክስ በማዘጋጀት ወደ ፍርድ ቤት የሚያቀርቡበት አሠራር የዐቃቤሕግን የማስቀጣት አቅም በእጅጉ አያሳነሰው ሕብረተሰቡ በፍትሕ ሥርዓቱ እና በፍትሕ አስተዳደር አካላቱ ላይ ያለው አመኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መምጣቱ ይስተዋላልበወንጀል ክስ ዝግጅት ሂደት የሚከሰቱ ችግሮችን ሙሉ በሙሉ መዘርዘር አዳጋች ቢሆንም የሚከተሉትን እንደአብነት መጥቀስ ይቻላል ለክሱ አግባብነት ያለው የሕግ አንቀፅ ለይቶ አለመጥቀስ ግልፅና የተሟላ የክስ ማመልከቻ አለማዘጋጀት ይህም ማለት ሀ በቂ ማስረጃ በሌለው ጉዳይ ክስ ማዘጋጀት ለ መከሰስ የማይገባቸውን ሰዎች በክሱ ውሰጥ ማካተት አንዲሁም በተቃራኒው መከሰስ የሚገባቸውን ሰዎች በክሱ አለማካተት ሐ በተከሣሹ ላይ ከአንድ በላይ ክስ ማቅረብ ሲገባ አንድ ክስ ብቻ ማቅረብና ከአንድ በላይ ክስ በቀረበ ጊዜም የትኛው ማስረጃ የትኛውን ክስ እንደሚያስረዳ ለይቶ በግልፅ አለማመልከት መ የተከሣሽንም ሆነ የምስክሮችን አድራሻ በትክክል አለመመዝገብ የታይፕ ግድፈቶችን ሳያርሙ ወደ ፍርድ ቤት መላክ አልፎ አልፎም ቢሆን በክስ ቻርጅ ላይ ዐህግ ሳይፈርም ወይም ማህተም ሳይደረግበት ወደ ፍርድ ቤት መላክ ሠ ወንጀሉ የተፈፀመበትን ጊዜና ቦታ በክስ ማመልከቻው ላይ አለመግለፅ ረ በይርጋ የታገዱ ጉዳዮች ላይ ክስ መመስረት ሰ የግል ተበዳይና ተከሣሹ በሰጡት ቃል ላይ ብቻ ተመስርቶ ክስ ማዘጋጀት ሸ አግባብነት ያለውን አዋጅደንብ ወይም መመሪያ በትክክል ለይቶ አለማወቅ ቀ ኢግዚቢት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ኢግዚቢት መኖሩን በክሱ ቻርጅ ላይ አለማመልከት በ የምስክሮችን ቃል መሠረት አድርጎ ክስ ከማዘጋጀት ይልቅ ፖሊስ በምርመራ መዝገቡ መቅድም ላይ የጠቀሰውን የወንጀል ዓይነት ጠቅሶ ከማስረጃው ጋር የማይጣጣም ክስ ማዘጋጀት በዋነኛነት የሚጠቀሱ ችግሮች ናቸው በክስ አዘገጃደት ረገድ የሚታዩ ችግሮችን አስመልክቶ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩት ችግሮች አዘውትረው የሚከሰቱ መሆናቸው ስለተረጋገጠ እነዚህ ችግሮች ያሉበት ክስ ተዘጋጅቶ ፍቤት ሲቀርብ ውጤት አልባ ከመሆኑም በላይ በተከሣሽ እና በምስክሮች ላይም አላስፈላጊ የሆነ መጉላላትን በማስከተል ሊካስ የማይችል ጉዳት ያደርስባቸዋል እንዲሁም በዐቃቤ ሕግና በፍቤት ላይ ያለአግባብ የሥራ ጫናና የማቴሪያል ብክነት ያስከትላል ይህም በመሆነ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደሩ ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተጽእኖ ይኖረዋል በመሆኑም አሁን የተጀመረውን ኮክቨ ስራን መልሶ የማደራጀት ጥናት መሠረት የተቀየሱ የለውጥ አቅጣጫዎችን መሠረት በማድረግና አብረው የወረዱ የክስ አዘገጃጀት ፎርሞችን በመነሻነት በመጠቀም ለጥሩ ውጤት መስራት ካልተቻለ በኀብረተሰቡ ውስጥ ፍትሕን ማስፈን ቀርቶ አላማውን የሣተ ተግባር በማከናወን በውጤቱ ኀብረተሰቡ በአጠቃላይ በፍትህ አካላት ላይ አመኔታ አንዲያጣ ሊያደርግ ይችላል ለምሳሌ የሚከተለውን ጉዳይ እንመልከት ጉዳይ ል ከሣሽ ዐቃቤ ሕግ ተከሣሽ ወርቁ በላይ የመዝገብ ቁጥር ዐቃቤ ሕግ ለክሱ የጠቀሰው የወሕቁ ሲሆን ተከሣሹ ፈጸመ የተባለው እና ምርመራ የተጣራበት የወንጀል ተግባር የግል ተበዳይ አልማዝ በኃይሉን መንገድ ላይ እየፄደች ሣለ አድርጋው የነበረውን ግራም የአንገት ሐብል ወርቅ ከአንገቷ ላይ በጥሶ በመሮጥ ለማምለጥ ሲሞከር እጅ ከፍንጅ ተይዚል በሚል ነው በዚህ ጉዳይ ላይ የተዘጋጀው ክስ ፍቤት ከቀረበ በኋላ ተከሣሹ የእምነት ክህደት ቃሉን ተጠይቆ ባለሙያ አማክሬ እቀርባለሁ በማለቱ ፍቤት ለሌላ ጊዜ ቀጥሮ ችሎቹ ከአበቃ በኋላ የችሎቱ ዐቃቤ ሕግ በጻፈው አስተያየት ተከሣሽ ወንጀሉን በፈጸመበት ወቅት ኃይል መጠቀሙን የሚያስረዳ ነገር ስለሌለ ክሱ መቅረብ የሚገባው በወመሕቁ መሠረት በውንብድና ሣይሆን በወመሕቁ መሠረት በስርቆት ወንጀል መሆን ይገባዋል የሚል እምነት አለኝ በማለት ለችሎት ኃላፊው ማስታወሻ አቀረበ የውይይት ነጥቦች በተጠቀሰው ጉዳይ ላይ ዐቃቤ ሕግ በውንብድና የመሠረተው ክስ አግባብነት አለው የሚል አመለካከት አለዎት። ጉዳይ ርል ተከሣሽ አቶ በልሁ የግል ተበዳይ አቶ አናጋውን በቦክስ አፉ ላይ በመምታት ሶስት ጥርሶቱን አነቃንቆ ከኪሱ ዐ ብር በመውሰዱ በከተማ ፖሊስ መምሪያ በፖሊስ የምርመራ መዝገብ ቁጥር ምርመራ ተጣርቶበት መዝገቡ ለወረዳ ለዐቃቤ ሕግ ተልኮ መዝገቡ የተመራለት ዐቃቤ ሕግ በተከሣሹ ላይ በኛ ክስ የወሕ በመጥቀስ በሰው አካል ላይ ቀላል ጉዳት በማድረስ ወንጀል እንዲሁም በኛ ክስ የወሕክንቀጽ በመጥቀስ በሥርቆት ወንጀል ክስ አዘጋጅቶበት ፍቤት ከቀረበ በኋላ ፍቤቱ ጉዳዩን ተመልክቶ የተፈጸመው ወንጀል የውንብድና ወንጀል በመሆኑ ጉዳዩን የማየት ሥልጣን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው በማለት ክሱን በዐዐዐ ስላቋረጠው መዝገቡ ለዞን ዐቃቤ ሕግ ተልኳልከዚህ ጉዳይ የምንረዳው ክሱን ያዘጋጀው ዐቃቤ ሕግ በቂ የሆነ ስልጠና ወይም ልምድ ማያገኝ በቀጥታ በምርመራ መዛግብት ላይ ውሣኔ እንዲሰጥ መደረጉን እና ውሣኔውም በቅርብ አለቃው ወይም ልምድ ባለው ዐቃቤ ሕግ ሣይታይ ወደ ፍርድ ቤት የተላከ መሆኑ ነው በዚህ ዓይነቱ የአሰራር ግድፈት በርካታ ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ማሣያ ነው ተመሳሳይ በተግባር ያጋጠሙ ችግሮችን በማንሳት ተወያዩበት። የአያስከስስም ውሣኔ በሚሰጥባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የሚታዩ ችግሮች የአያስከስስም ውሣኔ የሚሰጥባቸው ሁኔታዎች በወመሕሥሥቁ እና ሥር በዝርዝር የተደነገገ ሲሆን በተለይ በቁጥር ሀ እና ለ ሥር የተቀመጡት የአያስከስስም ውሣኔ መስጫ ምክንያቶች ግልጽነት የሌላቸው በመሆናቸው ዐቃቤያነ ሕግ በተመሣሣይ ጉዳዮች ላይ የሚሰጧቸው ውሣኔዎች ወጥነት የሌላቸው አና የሚቃረኑ እንዲሆኑ ስለማድረጉ በተግባር ከሚታየው የዕለት ተዕለት አፈጻጸም ለመረዳት ይቻላል በቁጥር ሀ መሠረት በቂ ማስረጃ የለም የሚለው የማስረጃ ምዘና ግላዊ ወይም ሣብጀክቲቭ መሆኑ እያንዳንዱ ዐቃቤ ሕግ የራሱን የምዘና አቅም በመጠቀም የሚሰጠው ውሣኔ የተለያየ ነው ከዚህም የተነሣ አንዱ ዐቃቤ ሕግ ክስ የሚመሰርበትን ጉዳይ ሌላው ዐቃቤ ሕግ በቁጥር ሀ መሠረት ሲዘጋው ማየት የተለመደ ተግባር ነውእንዲሁም በቁጥር ለ መሠት ተከሣሹ ካልተገኘ ወይም የማይገኝ ከሆነ መዝገቡን ለመዝጋት የተቀመጠው መመዘኛም አሻሚ የሚሆንበት አጋጣሚ እንዳለ ከተሞክሮ ለማወቅ ተችሏል ተከሣሹን ለማግኘት የማይቻል እንደሆነ ክሱ አይቀርብም ሲባል እስከ አሁን ባለው አሰራር ዐቃብያነ ሕግ ከፖሊስ የተላከላቸውን የምርመራ መዝገብ በማየት የተከሣሽ ስምና አድራሻ ስለመኖሩ እንዲሁም የዋስትና ፎርም ሞልቶ በዋስ መለቀቁን ከማየት ውጭ ክሱ ከተመሠረተ በኋላ ተከሣሽ በአድራሻው ስለመገኘቱ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ መንገድ የላቸውም በዚህ ሁኔታ ማስረጃው የተሟላ ነው የሚል እምነት ያለው ዐቃቤ ሕግ ክስ ይመሰረታል ተከሣሽ የማይገኝ መሆኑ የሚታወቀውም በፍቤት መጥሪያ ተልኮለት ሣይቀርብ በቀረ ጊዜ ነው ከዚህ ፅሁፍ ጋር የተያያዘውን የ ሀ ውሳኔ ይዘት ለመረዳት አንደሚቻለው በአድራሻ ለፖሊስ የሚፃፍ ሲሆን » ቀንና ቁጥር ይኖረዋል » የፍትህ ጽቤት መዝገብ ቁጥር ሩ የፓሊስ የምርመራ መዝገብ ቁጥር ሩ ሉ ፓሊስ ኮሚሽን ቤት ቀ የክስ ፍሬ ነገር ቀ የተከሳሾች ቃል ሩ የምስክሮች ቃል ባጭሩ ህጋዊ አስተያየትና ውሳኔየሚሉ ሀሳቦችን የያዘ ሲሆን በመጨረሻም የዐቃቤ ህጉ ፊርማ ይኖርበታል ጉዳይ እነ አቶ ቦጋለ ሰዎች የቀበሌ ተመራጮች በመሆን ሲሠሩ የወሮ ዘርፌ የይዞታ የገጠር መሬት በቆሎ ከተዘራበት በኋላ መንገድ እንዲወጣበት አድርገዋልየሚል የምርመራ መዝገብ ደርሶፃል በጉዳይ ላይ የሰው እና የጽሁፍ ማስረጃ ቀርቧል ኛኛኛ ምስክሮት አዲስ መንግድ አልተከፈተም በማለት መስክረዋል ኛ ምስክር መንገድ በተከሳሾች ሲከፈት አላየሁም ብሏል ኛ እና ኛ ምስክሮቹ በበኩላቸው በወሮ ዘርፌ መሬት ላይ ተከሳሾች በክሱ መሠረት መንገድ ሲከፍቱ ተመልክቻለሁ በማለት አስረድቷል በሌላ በኩል የቀረበው የሰነድ ማስረጃ ከዚህ ቀበሌ የተገኘ የሰነድ ማስረጃ ሲሆን የተባለው መንገድ በአሁን ተከሳሾች የተከፈተ ሳይሆን ክስ ከመመስረቱ በፊት በ አንስቶ የነበረ መንገድ ነው በማለት ያስረዳል ከላይ የቀረቡትን ሁኔታዎች ግምት ውስጥ በማስገባት በጉዳዩ ላይ የመሠለህን የውሳኔ ሀሳብ በፅሁፋ አስፍር አቶ በድሉ የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ ለሆነው አቶ ኺኮ ጉቦ ለመስጠት በማሰብ አቶ በድሉ በጉን መግዛቱን በራሱ ግቢ ውስጥ አስሮ ማስቀመጡን አምኗል ድርጊቱ በ ዓም በ በወረዳ ቀበሌ አስተዳደር ውስጥ የተፈፀመ ነውበጉዳዩ ላይ ተጣርቶ ለደረሰው የምርመራ መዝገብ የአያስጠይቅም ውሳኔ ስጥጭድርጊቱ የሚያስጠይቅ ከመሠለህ ክስ መስርትች ተከሣሾች ኛ አቶ ሙራድ ኛ አቶ ቢምረው ተከሣሾች የተከሰሱበት ሰኔ ቀን ዐዐ ዓም በግምት ሠዓት ሲሆን ወልባ ወረዳ ኩሙ ቀበሌ ባህር ጐጥ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ ከዱር ውስጥ አድፍጠው በመጠበቅ ሟች አቶ ኖህ የተባለው ከወሮ ሚዛን ለቅሶ ቤት ውሎ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲመለስ ተከሣሾች በያዙት ዱላ የሟችን አናት ደጋግመው በመምታት ገድለውታል የሚሜል ሲሆን ሁለት የሰው ምስክር ቀርበው በተመሣሣይ ቃል ኛ ተከሣሽ ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ስፍራ ሟችን በያዘው ዱላ ደጋግሞ አናቱን የመታው ሲሆን ኛ ተከሣሽ ለመገላገል ሲሞክር ያዩት መሆኑን እንጅ ሟችን ሲደበድበው ያላዩ መሆኑን መስክረዋል የቀረበው የሀኪም ማስረጃ ሟች ጭንቅላት ላይ በመፈንከቱ ርበ ጥልቀት የሚታይና በዚሁ ምክንያት መሞቱን ያሣያል በቀረበው ማስረጃ ላይ ተመርኩዘህ ተገቢ ነው የምትሉትን ውሣኔ በፅሁፍ አስፍር የፍርድ አሰጣጥንና አፃፃፍን ከሌሎች ሰነዶች አፃፃፍ ልዩ የሚዳርጉት ባህርያት ቀሩ ሥራው ፍሬነገርንና ማስረጃን ከሕግ ጋር አስማምቶ በሚያሳምን መልኩ መጻፍን የሚጠይቅ መሆኑ ቀሩ የፍሬ ነገር ማስረጃና ሕግ የውስብስብነት ባህርይ ያላቸው መሆናቸውንና ክርክሮች የሚቀርቡበት በተቃራኒና በተደበላለቀ መልኩ በመሆኑና ከውሳኔ በፊት ስንዴውን ከገለባው የመለየትን እውቀትና ክህሎት ስለሚጠይቅ ሩ አለመግባባቶችን ሀሀፀሀ መፍትሔ መስጫ የመጨረሻ መንገድ መሆኑና አሸናፊና ተሸናፊ ረቺና ተረቺ የሚታይበት መሆኑ ቀሩ የክርክሩ ጉዳይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሚመለከታቸው ወገኖች ወይም ባለድርሻዎች በአንፃራዊ መልኩ አሳማኝ ዐህ መሆን ስለሚገባው ሩዳኞች ነፃ የሆነውን ሙያዊ የዳኝነት ሥልጣናቸውን ህዐር ሀከበ ተጠቅመው የሚያከናውኑት ሥራ በመሆኑና በባህሪይው አነስተኛ ቁጥጥር ርበከ ያለበት በመሆኑ ሩሥራው ቴክኒካል ብቻ ሳይሆን ዕውቀትንክህሎትንጥበብንጥንቃቄንመልካም ሥነምግባርንና ታማኝነትን የሚጠይቅ መሆኑ ሩ በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ጉዳዮች የሚሰጡት የዳኝነት ውሳኔዎች የሰዎችን መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች የሚመለከቱ መሆኑ ሩፍርድ የፍቤቶች የመጨረሻ የሥራቸው ውጤት ከመሆኑ አንፃር ጥንቃቄን የሚሻ መሆኑ ሩ ፍርድ በይግባኝ አስካልተሻረ ድረስ በማንም ላይ የአስገዳጅነትና ተፈጻሚነት ኃይል ያለው በመሆኑ ሩ ሰውኛ ባህርይው ዖህጋገዌገወዕር ለደፈያወ የጐላ በመሆኑና ሰዎች ኀብረተሰቡ ለፍርድ ካላቸው ከፍተኛ ከበሬታና አመኔታ አንፃር ትልቅ ክብደት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑ የሚሉት ዋና ዋነዎቹ ሲሆኑ ከተሳታፊዎችም ተመሳሳይ ነጥቦችን ማሰብና መጨመር ይጠበቃል የፍርድ አሰጣጥና አፃፃፍ ተግባር በዳኛው ከፍተኛ የመጨረሻውን ጥንቃቄ እንደሚያስፈልገው ለማመልከት የአሜሪካን የሕግ ባለሙያዎች የዳኝነት ውሳኔ ስትሰጥም ሆነ ሌላውን ሰው ወክለህ ስትከራከር ራስህን በባለ ጉዳዩበተከራካሪውእግር ተክተህ አስብ የሚሉት ተጠቃሽ ነው በተለይ ደግሞ ዳኛ በውሳኔው በአብዛኛው ከአንድ በላይ የሆነ ተከራካሪ ወገኖችን መብት አስመልክቶ አልባት የሚሰጥ ከመሆኑ አንፃር ሁሉንም ለማሳመንና ፍትሕ ለመስጠት የቱን ያህል ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅበት ማሰብ ይቻላልለዚህም ይመስላል ዳኛ የዳኝነት አካል ወይም የፍትሕ ባለሥልጣንርዐሀበ ዐየ ህህር ቨር ለመባል የሚያበቃው ዋናው ምክንያት የፍርድ አሰጣጥና አፃፃፍ ቅድመ ባህርይና ዓላማው የፍርድ አሰጣጥና አጻጻፍ ሥራ ብዕርን በወረቀት ላይ በማሳረፍ የሚጀምር ክንውን ሳይሆን መሠረታዊ የሆኑ ቅድመ ፍርድ ፃደቶች አሉትፍርድ የሚሰጥበትና የሚጻፍበትም ምክንያት እንደየ ጉዳዩ ዓይነት የሚመዝን ዓላማና ግብ ያለው ነው ቅድመ ፍርድ ሄደቶች ክንውኖች ከመሠረታዊ ቅድመ ፍርድ ሂደቶች መካከል የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው ቀሩ ዳኛው ፍርዱን ለማን እንደሚሰጥና እንደሚጽፈው ራሱን መጠየቅ አለበት የፍርዱ ተጠቃሚ አንባቢ ማን አንደሆነ ማሰብና መለየት ይጠበቅበታል ሩ ፍርድ የሚሰጥበትን ጉዳይ ፍሬ ነገርና ማስረጃ ጠንቅቆ ማጥናትና መሠረታዊ ግንዛቤ መያዝ አከራካሪውን ጉዳይ መለየትና በተገቢው መግለጽ መቻል » በአከራካሪው ጉዳይ ላይ ተከራካሪ ወገኖች የሚሉትን አቤቱታቸውን ሁሉ የቃል ከርክራቸውን ጭምር መስማት ምክንያቱም የሕግ ሊቃውንቱ አንደሚሉት ጽሑፍ የቀረበን ቃል ሕይወት ባለው መልኩ ማስረዳት የሚቻለውና የባለ ጉዳዩን ችግሮች በተግባር መረዳት የሚቻለው በቃል ጭምር ሲሰማ ነው ባለጉዳዩም በፍትሕ ሂደቱ ሥርዓት ላይ አመኔታ እንዲኖረው ይረዳል ሐኪም ለበሽተኛው መድኃኒት የሚያዝለት የሚሰማውን ሰሜት ሁሉ በቃል ሰምቶ መርምሮ እንደመሆኑ ዳኞችም ፍትሕ ቸግሮት የፍትህ በሽተኛሆኖ የቀረበን ባለጉዳይ ከጽሑፍ አቤቱታው ባሻገር ጽሑፉ በሌላ ሰው የተጻፈም ሊሆን መቻሉ ግምት ይወስድበታል አቤቱታውን በቃል መስማቱና ማከራከሩ ለፍርድ አሰጣጥ ጠቀሜታው ቀላል አይሆንም » የታመኑትንና የተካዱትን ፍሬ ነገሮች መለየትና ጉዳዩን መተንተን አስፈላጊ ነው ሩ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን ክርክሮች መርምሮ ከዋናው ክርክር ሂደት በፊት ውሳኔ መስጠት የማይታለፍ ተግባር መሆኑ ሩ ማሰረጃዎችን በተመለከተ የሚሰጡትን ትዕዛዞች የማረጃ አግባብነትና ተቀባይነትን የተጨማሪ ማስረጃ አስፈላጊነት በጥንቃቄና በወቅቱ መስጠት ለጉዳዩ አግባብነት ያለውን ሕግ መለየትና ማጥናት ሩ የዳኝነት ውሳኔው የሚያሳምን መሆኑን መመዘንና ወደ ፍርድ ሥራ መሄድ ናቸው የፍርድ መስጠትና መፃፍ ዓላማና ግቦች የፍርድ መስጠትና የፍርድ መፃፍ የራሱ ዓላማና ግብ አለው ከአነዚህም መካከል የሚተሉት ይገኙበታል ጅ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቶች የፍሬ ነገር የማሰረጃና የሕግ ክርክሮችን መርምሮ የፍቤቱን መልስ የዳኝነት ውሳኔ መፍትሔ መግለጫ መገናኛ መንገድ ነውለይግባኝ ፍቤቶችም ይግባኝ የቀረበበትን የስህተት ነጥቦች አሰመልክቶ ለማረም የሕግ ትንተና ምክንያት የሚቀርብበት መንገድ ነው ውጅ ለተከራካሪ ወገኖች አለመግባባት ክርክርነ መፍትሔ መስጫና ውሳኔውንም ለማስፈፀም አንዲችሉ ወይም የይግባኝ መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ በምን ምክንያት ረቺና ተረቺ እንደሆኑ ፍቤቱ የሚገልጽበትና የሚያሳምንበት መንገድ ነው የፍቤቱን መደምደሚያ ማሳወቂያ መንገድ ነው ለምርምርለማስተማሪያና የትችት ጽሑፎችን ለማዘጋጀት ሊጠቅም ይችላል አዳዲስ ሕጐችን ለማውጣትና ነባር ሕጐችን ለማሻሻል የሕጉን አተገባበር ከነባራዊ የኀብረተሰቡ ሕይወት ጋር የሚሄድ መሆኑን ለመገምገምና ለመረዳት ይጠቅማል በፍቤቶች ሕግን ለመተርጐምና በፍትህ ሥርዓቱ የድርሻቸውን ግዴታ ለመወጣት የቅልጥፍናቸውንና የተገማችነታቸው መለኪያ በመሆንም ሊያገለግል ይችላል የሰበር ችሎት ውሳኔ ከሆነ ደግሞ የሕግ አተረጓጐምን ዘዴ ተመሳሳይነት ለማስጠበቅ እንደሕግ ሆኖ ገዥ በመሆን ሊያገለግል ይችላል ለሕግ ሳይንስና ሙያ ዕድገት ህፀዐጠፀበ። ርቬ በክህፀከርበ ህሀር ሃሃቨከበኡ ፍቤቶች በሀገሪቱ ሕገመንግሥትና በሌሎች ኅጎች በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት ህግን መተርጐም መቻላቸው ዳኞች ስለሚኖራቸው ሚናና ሥልጣናቸው ያላቸው እይታ ኀብረተሰቡ ስለ ዳኞች ሚና ያለው ግምትና ሚዛንየዳኞች የሙያና የትምህርት ደረጃ እንዲሁም ያላቸው የዳኝነት ልምድ የዳኞች የዳኝነት ውሳኔ አሰጣጥና አጻጻፍ ክህሎትና ጥበብ የዳኞች ነፃነት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ከሙስና ከዘር እና ከመሳሰሉት ወገንተኝነት ነፃ መሆን ጠሀፀጠህዖ ጅ አንድ ሀገር የምትከተለው የሕግ ሥርዓት ፐጨዐዘበ ባህርይ የአገሪቷ የሕግ ትምህርት ሥርዓት በተግባርና ክህሎት ነክ ትምህርቶች ላይ ትኩረት የሰጠ መሆንና አለመሆን ጅሙ ዳኞች ዳኝነትን በሙሉ ፍላጐትና ፍቅር ቋሚና ዘላቂ ሙያ አድርገው ለመቆየት ያላቸው ዝንባሌ ቁርጠኝነትና መስዋዕትነት የፍቤቶች ተቋማዊ አስተዳደራዊ የገንዘብና የቁሳቁስ ጥንካሬና ብቃት በተዘዋዋሪ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ተሳታፊዎችም ሌሎች ምክንያቶችን መጨመር ይችላሉ የዳኝነት ውሳኔ አፃፃፍ መመዘኛዎች የዳኝነት ዓይነቶች ፍቤቶች በሚመለከቷቸው ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ዓይነት ውጤቶችን ይጽፋል እነዚህ ውጤቶች ጊዜያዊ በዌጩዘዐርህዐዓ እና የመጨረቫ ተብለው ሊከፋፈሉ ይችላሉ ጊዜያዊ ትዕዛዞቹ የመጨረሻ ውሳኔውን ፍርዱን ለማመቻቸት የሚያግዙ ናቸው ለምሳሌ ንብረት እንዳይሸጥ ማገድ በራሱ ውጤት ያለው ሳይሆን የመጨረሻ ፍርዱን ለማስፈጸም የሚረዳ ነው የመጨረሻ ፍርድ ግን የፍርድ ባለዕዳነትንና ባለመብትነትን የሚያስከትል በመሆኑ በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ጉዳይ እንደ አግቦብነቱ መፈጸምን ወይም ይግባኝ መጠየቅን ውጤት ያስከትላል በኢትዮጵያ የፍብሥሥሕግ መሠረት ሦስት ዓይነት የዳኝነት ዓይነቶች አሉእነዚህም ውሳኔ ትፅዛዝ ዐርዌ እና ፍርድ ህህዐጠፀበህ ተብለው ተቀምጠዋል እንዲሁም የሥነ ሥርዓት ሕጉ ትርጓሜ ያልሰጠውና በዝርዝር ድንጋጌዎች አተገባበርም ላይ መቼ አግባብነት አንደሚኖረው ያልተገለጸ ብይን የሚባል የትዕዛዝ ዓይነት እንዳለ ያመለክታል በልምድም ኮርር አንዳንድ ጊዜ በትዕዛዝ ሊወጡ የሚገባቸው ጉዳዮች ብይን በሚል ሲወጡ ይታያሉ ስለዚህ ከሕጉና ከልምዱ አንጻር ሲታይ በአሁነ ጊዜ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ዳኝነት የሚሰጡባቸው መንገዶች ትዕዛዝብይንውሳኔ እና ፍርድ ናቸው ከልምዱ ሲታይ ፍርድና ውሳኔ በተለዋዋጭነት በሥራ ላይ ሲውሉ የሚታይ ሲሆን ውሳኔ ግን ተፈጻሚው የፍርድ የመጨረሻው አካል መሆኑን ለመረዳት ይቻላል ብይንና ትዕዛዝ ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው ዳኝነት የሚሰጥባቸው ስያሜዎች አርፅስት ናቸው የትፅዛዝ ውሳኔና ፍርድ ትርጉሞች በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ የተመለከተ ሲሆን በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕጉ ግን ስለትርጉማቸው « ሆነ ስለአገልግሎታቸው የተገለጸ ነገር የለምየትፅዛዝና የውሳኔ ልዩነት በግልጽ አልተመለከተምይህም በመሆኑ ይመስላል አንዳንድ ጊዜ ፍቤቶች በማቀያየር ሲጠቀሙባቸው የሚታየው በኢትዮጵያ የፍሥሥሕግ መሠረት የሚሰጡት ትዕዛዞች በአምስት ከፍለን ልናያቸው እንኝላለን ሀ ክስን የመሰረዝ ባህሪ ያለው በመሆነ ይግባኝ የሚባልበት ትዕዛዝለምሳሌ ክሱ በይርጋ ወይም የክስ ምክንያት የለውም ተብሎ በትዕዛዝ ቢዘጋ ቢሠረዝ ወይም ይግባኙ መልስ ሰጭን አያስቀርብም ተበሎ ቢዘጋ ለ ክሱን የመሰረዝ ውጤት የሌለው ግን ይግባኝ የሚባልበት ትዕዛዝ ለምሳሌ ንብረት ከእጅ እንዲወጣ የሚሰጥ ትዕዛዝ ወይም የእሥራት ትዕዛዝ ሲሰጥ አንቀጽ ሐ ክሱ ተከፍቶ አስኪጠናቀቅ ድረስ በማናቸውም ጊዜ ቢሰጥም ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ለይግባኝ ምክንያት ሊሆን የሚችል ትፅዛዝ አንቀጽ ለምሳሌ የይርጋን መቃወሚያ ባለመቀበል በሚሰጥ ትዕዛዝ መ በከፊል የይግባኝ ምክንያት ሊሆን የሚችል ትዕዛዝ ለምሳሌ በአንቀጽ መሠረት የሚሰጥ ትዕዛዝ ሠ ፈጽሞ ይግባኝ ሊባልበት ወይም ለይግባኝ ምክንያት ሊሆን የማይችል ትዕዛዝ በአንቀጽ መሠረት ዳኝነቱ እንደገና ሊታይ ይገባዋል ወይም አይገባውም ሲል ፍቤቱ በሚሰጠው ውሳኔ ላይ ይግባኝ ለማቅረብ አይችልም ለምሳሌ የቀጠሮ መለወጫ ትዕዛዝ መስጠት ይመለከታል የመጨረሻ ውሣኔዎች ይዘት በመጀመሪያ ደረጃ በሚታዩ ጉዳዮች ላይ የሚሰጥ ውሳኔ ፍርድ የሚከተሉትን ነጥቦች ይሸፍናል የጉዳዩ ባህርይ አህጩዌ ሀር ካ ልርከበ ከሳሽተከሳሽ የሚጠይቁት መፍትሔ ዓይነትና የተከራካሪዎቹ ሚና የጉዳዩ አቀራረብ ታሪክ ወደ ፍቤት እንዴትና በማን እንደረበ የሚናገር ክፍል ነው ዝርዝር ፍሬ ነገሮች ዞኮጸር ከሳሸና ተከሳሽ ያቀረቧቸው ዝርዝር ፍሬ ነገርና የማስረጃ ክርክሮችና ዓይነቶቻቸው ለጭብጡ አመሠራረትና ለጉዳዩ አመራርና አወሳሰን የሚጠቅሙትን አግባብነት የክርክሩ ነጥብ ከፍቤቱ ምላሽ የሚፈልገውን ጉዳይ የሚይዝ ነው ጭብጥ ሀ ከሳሸና ተከሳሽ ያልተግባቡት የክርክሩ ነጥብ ከፍቤቱ ምላሽ የሚፈልገውን ጉዳይ የሚይዝ ነው ሕግና አስተያየት ዉእ በዐ በበ ፍቤቱ ለክርክሩ መደምደሚያ የሚጠቀምበት የሕግ ድጋፍና ምክንያት ነው ውሳኔ ፀበ ዐ ርበርህዌበ በጉዳዩ ረቺውና ተረውን ለይቶ ተፈጻሚ የሚሆነውን የፍቤቱን ድምዳሜ ማጠቃለያ የሚይዘው ክፍል ነው በተመሳሳይ ሁኔታ በይግባኝና በሰበር የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የሚሰጥ ፍርድ ብዙም ልዩነት በሌለው ሁኔታ መልኩ የሚከተሉትን ነጥቦች ይሸፍናል የጉዳዩ ባህሪይ አክጸኋህጩ ዐ ከ ልርበዐበ ጭብጦች በፀ ኗክፀበበበ። ዐ ቀን ብር ዐዐዐዐዐ አንድ ሺህ ብር በአጠቃላይ ዐዐዐ የጉዳት ካሣ ከበቂ ኪሣራና ወጭ እንዲሁም ወለድ ታስቦ ይከፈለኝ በማለት ክስ አቅርቧል በማስረጃነትም የባጃጁ ሊብሬ ከኮሌጅ ጋር ስምምነት የወሰደበት ውል ዋናውና ኮፒው ተያይዚል አደጋው የደረሰው በአቶ ከበደ በአይሱዙ መኪና ምክንያት መሆኑን የሚያሣይ የቴክኒክ ማስረጃ ተያይዛል አደጋው ሲፈጸም የተመለከቱ ሶስት ምስክሮች ቀርበው መስክረዋል የተለያዩ ገንዘብ የተከፈለባቸው ደረሰኞች ተያይክዘዋል የተከሣሽ መልስ አቶ ከበደ አደጋው መድረሱን አምኗል ሆኖም በመከራከሪያነት ያቀረባቸው ነጥቦችም ለማስጠገኛ ወጣ የተባለው ወጭ የተጋነነ ነው በከሣሽ የቀረበው የውል ሠነድ ህጋዊነትን የጠበቀ አይደለም አደጋው ከመድረሱ ከአንድ ሣምንት በፊት መኪናዬ ባልታወቀ ሰው ተሰርቆ ስለነበር ለደረሰው ጉዳት ጥፋትና ኃላፊነት የለብኝም ብሏል በማስረጃነት ተከሣሹ ለፎገራ ወረዳ ፖሊስ መኪናው ካቆመበት የጠፋ ስለመሆኑ ያመለከተበት ማስረጃ በቁጥር በቀን የተፃፈ ተያይዛል የመኪናው ሊብሬ ባለቤትነት ደብተር ኮፒው ቀርቧል መወያያ ጥያቄ ከላይ የቀረበውን ክስና መልስ እንዲሁም ማስረጃዎችን በመመርመር አንድ ፍርድ መያዝ ያለበትን ቅርጽና ይዘት ግምት ውስጥ በማስገባት ፍርድ ውሣኔ ሰጡ የውሣኔ አፃፃፍ በፍርድ ቤቶች ደረጃ አስቀድመን ለመመልከት እንደሞከርነው የውሣኔ አፃፃባፍ ይዘት በጥቅሉ የተመሣሰለ ቢሆንም ከጉዳይ ጉዳይ ግን ይለያያል በወንጀል ጉዳይ የሚፃፈው ውሣኔ በይዘቱ እና በቅርፁ በፍትሐብሄር ጉዳይ ከሚፃፈው ይለያል በፍታብሔር ጉዳይም በተፋጠነ ሥነ ሥርዓት የሚቀርበው በመደበኛው ሥርዓት ከሚቀርበው እንዲሁም በመደኛ ከሚቀርበው ውስጥ አከራካሪ ጉዳይ ያለው እና ጭብጥ የሌለው ልዩነት አላቸው ጭብጥ በሌላቸው ውስጥም ቢሆን የውሣኔ አፃፃፍ በተለይ በውሣኔ ሰጭ ጥራት እና ትጋት ሊለያይ ይቻላል ልዩነቱ ማቆሚያ አይኖረውምበዚህ ርዕስ ላይ የምንመለከተው በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች መሐከል ሊኖር የሚችለውን የውሣኔ አፃፃፍ ቅርጽ እና ይዘት ነው በዚህ መልኩ ውይይት የሚደረግበት የውሣኔ ጽሑፍ ልዩነት ሣይደረግበት ለሁሉም ጉዳዩች ነው የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ውሣኔ አፃፃፍ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቶች በተለይ የማስረጃ እና የፍሬ ነገር ክርክር በስፋት የሚካፄድባቸው እና የሚመዘገብባቸው ናቸው በዚህ ደረጃ በሚሰጡ ውሣኔዎች የፍርድ ቤቱ ውሣኔ አልፎ አልፎ መንደርደሪያ ላይ ሰፍሮ ይገኛል ከሣሽ በክሱ ላይ ክሱ የቀረበው ያህል ገንዘብ ለማስከፈል ነው በማለት ጥያቄውን በግልጽ በመንደርደሪያው ላይ እንደሚገልጸው ሁሉ በመጀመሪያ ደረጃ ፍቤትም በዚሁ አገላለጽ የተከሣሽን ክስ መሰረዙን ወይም በተከሣሽ ላይ የኃላፊነት ውሣኔ መሰጠቱን ገልፆ ሊጀምር ይችላል በመጀመሪያ ደረጃ ለሚፃፉ ውሣኔዎች በይዘታቸው እንደቅደም ተከተሉ የጉዳዩ ዓይነት ፍሬ ነገሮችን ጭብጥ ጭብጦችን ሕግ ብያኔ እና መደምደሚያ ማጠቃለያ ፍርድ ሊይዙ ይገባል በዝርዝር ስንመልከታቸውም የጉዳዩ ዓይነት ይህ የውሣኔ ክፍል ፍርድ አየተባለ ርዕስ ተሰጥቶት ከሚዛፈው ሥር በመጀመሪያ የሚሰፍረው ነው ጉዳዩ የምን እንደሆነ ያለፈበት አስፈላጊ ታሪክ በጉዳዩ ላይ ፍቤት ያለው ሥልጣንና በፍቤቱ ሊወሰን የሚገባው ጉዳይ የሚጠየቅበትን የሚይዝ ነው ለምሣኔ ጉዳዩ የመሬት ክርክርን የሚመለከት መሆኑበጉዳዩ ላይ የመሬት አስታራቂ አስማሚ ሽማግሌዎች ያደረጉት የማስታረቅ የማስማማት ጥረት ውጤት አለማስገኘትን ጉዳዩ በሕግ መሠረት በፍርድ ማለቅ የሚገባው ስለሆነ ከሣሸ መሬቱን ለመረከብ ጥያቄ ማቅረቡ ይገለጽበታል እንደ ርዕስ ሊጠቀስ የሚባውም ነው ፍሬ ነገር ፍሬ ነገር ስንል በተከራካሪ ወገን ማስረጃ ሊረጋገጡ ወይም ሊፈርሱ የሚችሉ ሕግ ነክ ያልሆኑ ክርክሮች ማለታችን ነው በሲቪል ሎው ሕግ ፊት ውሣኔ አሰጣጥ በአንድ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ውሣኔ ውስጥ ፍሬ ነገሮች ምን ጊዜም መካተት ይገባቸዋል በጉዳዩ አስፈላጊ የሆኑት ብቻ በትረካ መልክ ሊካተቱ ይገባል ዳኛው ተገቢ የሆኑትን የፍሬ ነገር ክርክሮች ብቻ መርጦ መመዝገብ ይኖርበታል ውሣፄውን ለመረዳት የሚያነብ ሰው ወሣኝ የሚለውና ውሣኔውን ለመረዳት የሚያግዙት ፍሬ ነገሮች ብቻ ይካትታሉ ተከራካሪ ወገን እና አንባቢ በውሣኔው ተስቦ በቀላሉ እንዲያነበው እና እንዲረዳው ፍሬ ነገሮችን በተቻለ መጠን ይገለፃል ጊዜን መጥቀስ አስፈላጊ ቢሆንም ፍሬ ነገሮች እንደቀደም ተከተላቸው ቢገለፁ ይመረጣል የውሣኔው ፀሐፊ ተከራካሪ ወገን እና ወይም ሌላው አንባቢ ከፍሬ ነገሩ በይበልጥ የሚፈለገውን በሚያካትት መልኩ መፃፍ ይኖርበታል ለምሣሌ በመሬት ጉዳይ ከፍቤት ክርክር አስቀድሞ በአርቅ ጉዳዩ መፈታት አለመቻሉ ቢገለፁ በቂ ሲሆን በውል ክርክር ጊዜ ውሉ የተፈፀመበት የፈረሰበት ጊዜ ወዘተ አንደ ቅደም ተከተል እየጐላ መጠቀስ ያስፈልገዋል የጊዜ ቅደም ተከተል ያለባቸው ጉዳዮች በሐተታ መልክ ወይም በመዘርዘር ሊገለጽ ይችላሉለምሣሌኀዳር ዐዐዐ የተፈረመውን ውል ባለማክበር በውሉ ላይ የተመለከተውን እንቁላል ጥር አጋማሽ ዐዐዐ አላስረክበኝምብሉ መፃፍ እንደሚቻለው ሁሉ ኀዳር ዐዐዐ ውል ተፈፀመ በጥር አጋማሽ ዐዐዐ ውሉ ፈረሰተብሉ ሊቀመጥ ይቻላል ዳኞች ፍሬ ነገርን በውሣኔያቸው ውስጥ በሚያሰፍሩበት ጊዜ የይዘት ለውጥ እንዳይኖረው ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል በተቻለ መጠን በክርክሩ ቋንቋ መቀመጥ ይገባዋል ዳኞች ፍሬ ነገርን የመተርጐም ሥልጣን የላቸውም ሕግን ለመተርጐም የተሰጣቸው ሥልጣን ለፍሬ ነገር መመዝገብ ብቻ ተደርጐ መታየት ይኖርበታል ከሣሽ ጥር አጋማሽ ውሉ ፈረሰ ቢል ውሣኔ ሲፃፍ ጥር ዐዐዐ ተብሎ መጠቀስ አይኖርበትም ፍሬ ነገርን መተርጐም አንባቢን የማሣመን ኃይልን መቀነስ ከመሆኑም በላይ ፍሬ ነገርን የመመርመር ስልጣናቸው ኃላፊነታቸው እየቀነሱ የሚመጡ የበላይ ፍቤቶችም በጉዳዩ ላይ የተዛባ ውሣኔ አንዲያሣርፍ በር የሚከፍት ስለሆነ በጥንቃቄ መፃፍ ይኖርበታል ፍሬ ነገር በጥንቃቄ መፃፍ አለበት ሲባል የተከራካሪ ወገን የፍሬ ነገር ክርክር እንዳለ መስፈር አለበት ማለት አይደለም ለምሣሌ የልጅነት ይረጋገጥልኝ የሚል አቤቱታ ከቀረበ መስፈር ያለበት አባትነትን ሊያረጋግጡ የሚችሉ ፍሬ ነገሮች እንጅ አባት የተባለው ሰው የዘር ግንድ ተዘርዝሮ መስፈር አለበት ማለት አይደለም አግባብ ያለውን ፍሬ ነገር መምረጥ ከፍተኛ ጥበብንአእውቀትንና ልምድን ይጠይቃል ፍሬ ነገርን መርጦ ድምዳሜ ላይ መድረስም በተመሣሣይ መልኩ ጥንቃቄን የሚጠይቁ በሀገራችን የዳኛ ብቻ የሆነ ሥራ ነው እዚህ ድምዳሜ ላይ ለመድረስም መነሻው ማስረጃ ብቻ ነው ለምሣሌ አባትነትን ለማስረዳት ከቀረበው ማስረጃ ውስጥ ፍቤቱ ተከሣሽ አባት የተባለው ከወሮእናት ጋር ጋብቻውን ከዐ መፈጸሙ ተረጋግጧል የሚል የፍሬ ነገር መደምደሚያ ላይ ይደረሣል ይህ የፍሬ ነገር መደምደሚያ በራሱ ትርጉም የሌለው በመሆኑ ወደ ሕግ መደምደሚያ መቀየር ይኖርበታል በዚህም መሠረት ፍሬ ነገር በጉዳዩ ላይ ለተያዘው ጭብጥ አልባት የሚያሰጥ ይሆናል ስለሆነም በተያዘው ጉዳይ ላይ ጭብጥ ከሌለ ፍሬ ነገርና መደምደሚያ ላይኖር ይችላል ማለት ነው በርካታ ፍሬ ነገሮች ይኖራሉ ይህ ማለት ግን በፍሬ ነገር እና መደምደሚያ መኖር ሁል ጊዜ ጭብጥ ያስፈልጋል ማለት አለመሆኑን ማስታወስም ይገባልፍሬ ነገሮች መረጃ የሚሰጡ የታመኑ ወይም በማስረጃ ላይ የተመለከቱ ጭብጥ ሊሆን የሚችል ክስ ላይ የተመለከተወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ ክስ የተመሠረተበት ቀን የከሣሽ ቀበሌ የከሣሽ ችሎታ በእነዚህ ዝርዝር ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው እነዚህ ፍሬ ነገሮች ውሣኔ እስከተደመደመ ድረስ ሊጠቀሱ የሚችሉ ሲሆን አስፈላጊ ካልሆኑና አግባብነት ከሌላቸው ፍሬ ነገሮች መለየት ያለባቸው ናቸውበአጠቃላይ ከጭብጥ በፊት እንዲሁም ከጭብጥ በጊላ ከጭብጡ ጋር የተያያዙ ፍሬ ነገሮች ሊገለፁ ይችላሉ የሚፃፉ ፍሬ ነገሮች በማስረጃ ክርክሩ ቃል የተቀመጡ የተመረጡ አስፈላጊ ብቻ የሆኑት በቅደም ተከተላቸው የተቀመጡ መሆን ይኖርባቸዋል ጭብጥ ጭብጥ ከዚህ በፊት እንደተገለጸው ተከራካሪ ወገኖች ያልተስማሙበት የፍርድ ቤቱን ውሣኔ የሚጠይቅ ነጥብ ነው የፍሬ ነገር ወይም የሕግ አለዚያም የሁለቱም ጥያቄ ሆኖ የሕግ ምላሽ የሚጠይቅ ነው እንደ ሌሎች ጽሑፎች ሁሉ ጭብጥም በግልጽ ቋንቋ መቀመጥ ይኖርበታል ጭብጥ በፍርድ ቤቱ አገላለጽ የሚቀመጥ ሆኖ በጥያቄ መልክ ወይም ስለመሆን አለመሆነን ስለመኖር አለመኖሩ ወዘተበሚል አረፍተ ነገር ሊቀመጥ ይችላልለምሣሌ በፍቤቱ ሊመረመር የሚገባው ጭብጥ ነጥብ አከራካሪ ጉዳይ የከሣሽ ክርክር በይርጋ ቀሪ ሊሆን ይገባል። አየተባለ ሊቀመጥ ይችላል እያንዳንዱ ጭብጥ ዋና እና ንዑስ ጭብጦችን የያዘ ነው እንደሁኔታው ሁሉም ምላሽ ላያስፈልጋቸው ይችላል ከሣሽ እና ተከሣሽ የፀና ጋብቻ የላቸውም የሚል መደምደሚያ ላይ ፍቤቱ ከደረሰ ቀሪ ጭብጦችን በመተቸት በውሣኔ ላይ መፃፍ አያስፈልግም የጭብጥ አቀማመጡም ቅደም ተከተል ይህንና ጊዜን መሠረት ማድረግ ይኖርበታል የሕግ ጭብጦች በመጀመር ምላሽ ቢያገኙም ይመረጣል ሕግ እና ምክንያት በውሣኔ ላይ ጭብጥ ከተገለጸ በኋላ የሚከተለው ለጭብጡ ምላሽ ለመስጠት አግባብ ያለው ሕግ አና ሕጉ ከጭብጡ ጋር ያለው ግንኙነት ነው ሕጉን እንዳለ መገልበጥ ሁልጊዜ አያስፈልግም ለምሣሌ የኢትዩጵያ ሕግ ክርክሩ በ ሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ ቀሪ ይሆናል በማለት ይደነግጋል ተብሎ ሊገለጽ ይችላል የሚጠቀሰው ሕግ የተሻረ ካልሆነ በስተቀር ሕግ ምንጊዜም በአሁን ጊዜ መገለጽ አለበት ሕጉ ግልጽ በሆነ ጊዜ ይኸው ሕግ ግልጽ ለሆነው ፍሬ ነገር ተፈጻሚ ይደረጋል ሕጉም ሆነ ፍሬ ነገሩ ሁለቱም ግልጽ ባልሆኑ ጊዜ በውሣኔው ላይ በፍሬ ነገሩ የተሰጠው ክብደት ተመዝኖ ከተቀመጠ በኋላ ሕጉ በምን መልኩ ተፈጻሚ ሊሆን አንደሚገባው ይዛፃፋል ፍሬ ነገሩ ብቻ ግልጽ ካልሆነ ይህንኑ በምዘና ወስኖ ግልጹን ሕግ ተፈጻሚ ማድረግ ነው ሁልጊዜ ግልጽ ላልሆነው ነገር ምላሽ መስጠትን ማስቀደም እና መቋጫውን ግልጽ ከሆነው ነገር ጋር ማገናኘት አፃፃፉን ይበልጥ ተነባቢ ያደርጋዋል ከፍ ሲል ለመግለጽ እንደተሞረው በሕግ ጥያቄ የሚደረስበት መደምደሚያ የፍሬ ነገርን መደምደሚያ መሠረት ያደረገ ነው በፍሬ ነገር ላይ የሚደረስበት ድምዳሜ በዳኝነት ነፃነት ላይ የተመሠረተ ሣይሆን የቀረበን ማስረጃ መሠረት ያደረገ ነው ይህ በራሱ የመጨረሻ የሚሆን ሣይሆን ለሕግ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት መነሻ ነው የሕግ ጥያቄ ምላሽ በሚሰጥበት ጊዜ የተባለውን ሕግ ሙሉ ቁጥር አንቀጽ መገልበጥ ላያስፈልግ ይችላል ልዩ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በዚህ መልኩ ሕጉ ባይገለበጥ ይመረጣል ፍሬ ነገር ጥያቄ ትርጉም ያለው የሕግ ውጤት የሚኖረው በዚህ ጊዜ ነው የተከራካሪ መገኖች መብት ውሣኔ የሚያገኝበት በመሆኑ ከፍሬ ነገር ጋር ትስስሩ በግልጽ ተመልክቶ ነገር ግን በአንድ ዓርፍተ ነገር ከፍሬ ነገር በነፃ መልኩ መቀመጥ ይኖርበታል ለምሣሌ ፍሬ ነገር መደምደም «ተከሣሽ የውሉን እንቁላል በጥር አጋማሽዐዐዐ አላስረከበም ሚሲንሲሲኑ የህግ መደምደሚያ «ዋርአጋማሽ ዐዐዐ ባለማስረከቡ ውል አፍርሷል ፍቤቱ የሕግ መደምደሚያ ላይ ሲደርስ ፍሬ ነገሩን መሠረት በማድረግ አይገባም ያለውን ሕግ የመፈለግ ለጉዳዩ በጥቅሉ እና ለያዘው ጉዳይ በተለይ የሚፈጸም መሆኑን መርምሮ ነው ይህም በፍቤቱ የተለየውን ጭብጥ አገላለፁ እና የማስረዳት ሸክሙን መወጣት ያለበት ወገንን ማስረጃ በተከተለ ሁኔታ ይገለፃል ይፃፋልየሕግ እና ምክንያት ትንተና ከተቋጩ በላ የፍርድ ቤቱ ውሣኔ ይገለፃል ይህን ውሣኔ በተቻለ መጠን አጭር እና ለአፈጻጸም የሚመች መሆን አለበት ግልጽ አጭር ምጥን ቃል መሆንና ሁሉም ወገኖች የሚገባቸውን የማይገባቸውን በቀጥታ የሚናገር መሆን አለበት ለምሣሌ ከፍ ሲል በተገለጸው መሠረት ከሣሽ ክሱን ያቀረበው ውሉ ከፈረሰ ከሁለት ዓመት በኋላ በመሆኑ ክስ የማቅረብ መብት የለውም ተብሎ ሊፃፍ ይችላል የበለጠ የሚገለፀውም ከሆነ ሩ ክሱ በይርጋ ቀሪ ይሆናል ሊባል ይችላል ከውሣኔው ጋርም ተያይዞ ተፈፃሚ መሆን የሚገባቸው ጉዳዩች ሊካተቱ ይችላሉ ለምሣሌ ከሣሽ አላግባብ ክስ በማቅረቡ ተከሣሽን ለወጭ እና ለኪሣራ ለዳረገበት ካሣ ይከፈል በዚህ ውሣኔ ቅር የተሰኘ የይግባኝ መብቱ የተጠበቀ በሕግ ነው መዝገቡ የተዘጋ በመሆኑ በቋሚነት ስለሚቀመጥበት ቦታ ሊወሰን ይችላል ይህ ውሣኔ ብዙውን ጊዜ ትዕዛዝ በሚል ርዕስ ስር ሲቀመጥ እንመልከታለን የወንጀል ጉዳይ የውሳኔ አሰጣጥ ህጉ በየቀጠሮው የሚሠጥ ውሳኔ ትዕዛዝፍርድ ይዘት ምን መምሰል እንዳለበት በዝርዝር በግልፅ አያስቀምጥም ይሁን እንጅ የወመስስህግ ከአንቀጽ የማስረጃ ስርዐትና የፍርድ አሰጣጥ ሁኔታ ይደነግጋል ጅ የመዝገብ ቁጥር ጅ ጉዳዩ የታየበት ቀን አና ሠዓት ጅ የዐህግ የተከሳሽ ጠበቃስም የዳኞች ስም ጅ የጉዳዩ መሰማት የተቆረጠበትን እና የተቀጠረበትን ቀን ቁ በፅሑፍ መያዝ አለበት መ በተቃውሞ ላይ የሚሠጥ ውሳኔ ያለ ቀጠሮ ወዲያውነ መሠጠት ያለበት ሲሆን ሌሎች ክርክር የተደረገባቸው የህግ ጉዳዮችም ያሉ እንደሆኑ ክርክሩ በተነሳበት ቀን መዛፍ አለባቸው ወ ውሳኔዎች እና ትዕዛዞች በተለይ የሚፈፀሙ በመሆናቸው ግልፅ ሆነው መፃፍ አለባቸው ከምንል በቀር በህጉ ላይ እያንዳንዱ ውሳኔ ትዕዛዝ ሲፃፍ ሊከተለው ስለሚገባው ሊይዘው ስለሚገባቅርፅ የተገለፀ ነገር የለም ይሁን እንጅ በወመህስስቁጥር መሠረት የሚሠጥ ፍርድ በቅርፅ ደረጃ ሲታይ የሚከለውን ይመስላል ፍርድ ውሳኔየቅጣት ትዕዛዝአፈፃፀምሊይዝ የሚችል መሆኑን ስንመለከት በይዘቱም » ፍርድ የተሰጠበት ቀን የዳኛ ፊርማ » የማስረጃ አጭር መግለጫ » ማስረጃ ተቀባይነት ያገኘበት ምክንያት » ማስረጃው ተቀባይነት ያላገኘበት ምክንያት » ፍርዱ መሠረት ያደረገው የህግ ቁጥር ጥፋተኛ ያሰኘው ህግ » ቅጣትን ለማክበድ እና ለማቅለል የተሰጡ አስተያየቶች » ይህን ለማስረዳት የቀረበ ማስረጃ ስለ ጠባዩ የይግባኝ መብት ያለ መሆኑን ስለ መናገር መፃፍ እንዳለበት የወመስስ ህግ ቁጥር መረዳት ይቻላል በወንጀል ጉዳይ የሚሠጥ ፍርድ ላይ መገለፅ አንዳለበት በህጉ ላይ የተመለከተ ሲሆን የፍቤቱ ስም ፍርድ ቤቱ ያስቻለበት ቦታ የተከሳሽ ማንነት አድራሻ ወንጀሉ የተፈፀመበት ቦታና ጊዜ የተላለፈው የህግ አንቀጽ ተከሳሹ አምኖ መከራከሩን ጭብጥ ተከሳሽ ያቀረበው የክስ ተቃውሞ ካለ ውሳኔው መኖሩ በአጭሩ የተገለፅ ሠለክሱ የቀረቡ ማስረጃዎች አይነት እና ዝርዝር መከላከያ ማስረጃ ቀርቦ ከሆነ በተመሳሳይ መልኩ አይነቱንብዛቱን የሚያስረዳውንጭብጥ ተቀባይነት ያገኘበትን ያጣበትን ምክንያት ክርክር የተደረገባቸው ሌሎች ጉዳዮች ምሳሌ ፅድሜ ጤናካሉ ክርክራቸውና ውሳኔው በጥቅሉ በአግባቡ መገለጽ ይኖርበታልከዚህ በላይ የተጠቀሱት ጉዳዮች በህግ እና በልምድ ተቀባይነት ያላቸው አሰራሮች ናቸው አንዳንዶቹ ነጥቦች በውሳኔው ላይ በግልፅ መቀመጥ ያለባቸው ለይግባኝ ሰሚ ፍቤት ለተከራካሪ ወገንና ለህብረተሰቡ መገለፅ ስላለባቸው ነውክርክሩ ሁሉ ተገቢውን ሚዛንና ክብደት የተሰጠው መሆኑን ለማስረዳትና የወንጀል ፍርድ የማስተማር አላማ ያለው በመሆነ ለአስተማሪነቱም ጭምር ነው ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በፍቤቶች አወቃቀር የበላይ የሆነ ፍቤቶች ዋነኛ ተግባራቸው በሥር ፍቤት የታዩ ጉዳዮችን በይግባኝ መመልከት ነው የሀገራችን ፍቤቶች አወቃቀር ከዚህ አምብዛም የተለየ አይደለም በወረዳ ፍቤቶች የቀጥታ ክስ ክርክሮች የሚበዙ ሲሆን በበላይ በከፍተኛ እና ጠቅላይ ፍቤቶች በይግባኝ የሚታዩት ጉዳዩች እየበዙ ይመጣሉ ይህ ማለት ግን በወረዳ ፍቤት ይግባኝ አይታይም ሀ በጠቅላይ ፍቤቶች ደግሞ ቀጥታ ክስ አይኖርም ማለት አይደለም መጠኑ እና የሚጠበቀው ውጤት ይለያያል እንጅ በሁሉም ፍቤቶች ይግባኝ ይታያል ስለሆነም የሚከተለው ውይይትም እንደአግባቡ ለፍቤቶች ሁሉ ያገለግላልይግባኝ ሰሚ ፍቤት አንድን ጉዳይ በይግባኝ በሚመለከቱበት ጊዜ በዋነኛነት የክለሣ ተግባር ያከናውናል የሥር ፍቤት የሥነ ሥርዓት ሕጉን በአግባቡ ለመፈጸሙ መሠረታዊ ሕጐች አለመጣሣቸው ማስረጃ በአግባቡ መመዘኑን እና የመሣሠሉ ተግባራት በፍትህዊነት መፈጸማቸውን ያረጋገጣል ይግባኝ ሰሚው ፍቤት የመጨረሻው በሆነ ጊዜ የሕግ ስህተት አለመፈጸሙን ያረጋግጣሉ ይግባኝ ሰሚው ፍቤት የመጨረሻው በሆነ ጊዜ አትኩረቱ በሕግ ጥያቄዎች ላይ ሆኖ ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች አለመጣሣቸውን ፖሊሲዎች እና ሌሎች ሕጐችም በመሠረታዊነት አለመጣሣቸውን በማረጋገጥ በክልሉ ወይም በሀገሪቱ ተመሣሣይ እና ተገማች የሆነ የሕግ ሥርዓት መኖሩን የሚረጋገጥ ተጨማሪ ከባድ ኃላፊነት አለባቸው የይግባኝ ሰሚ ፍቤት ከመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በተለይ የሚለየው ጉዳይን በይግባኝ በክለሣ መመልከቱ ብቻ አይደለም ይህንን ለመፈጸም በአብዛኛው የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤትን የመዝገብ ግልባጭ ይመረምራል ከታች የመጡትን የመዝገብ ግጭባጭ ከመረመረ በላ የሥር ፍቤትን ውሣኔ የማጽናት የመሻር የማሻሻል ጉዳዩ እንደገና እንዲወሰን ወይም ተጣርቶ እንዲመለስለት የመወሰን ሥልጣን አለው የበላይ ፍቤት ይህንን ሥልጣን ከሥር በተለየ መልኩ በኀብረት በሚሠራ የዳኝነት ተግባር ያከናውናል ዳኝነት በቡድን በኀብረት የሚሠራ በመሆኑ የውይይት ተግባር በስፋት የሚከናወንበትና አብዛኛው የተስማማበት የፍቤቱ ውሣኔ የሚሆንበት ነው በአብዛኛው ሃሣብ ያልተስማማ የራሱን ፃሣብ ያስፍራል በአንድ ጉዳይ አነስተኛ ድምጽ ያለው በሌላው በአብዛኛው ድምጽ ውስጥ ሊካተት ይችላልይግባኝ ሰሚ ፍቤት የዳኝነት ተግባሩን በአብዛኛው በኀብረት የሚከናወን ይሁን እንጅ በሀገራችን የውሣኔ አፃፃፍ ሥርዓት የፍቤት ውሣኔ የምንለው በአንድ ዳኛ ተጽፎ በሁሉም የሚፈረምበት ነው ውሣኔውን የሚጽፈው ዳኛ የራሱን ብቻ ሣይሆን የሥራ ባልደረቦቹ ሊያደርጉ የሚፈልጉትን ጥንቃቄ መረዳት ይኖርበታል ጽሑፍ የአንድ ዳኛ ውሣኔ ሣይሆን ከፍሬ ነገርም ይሁን ከሕግ የተጨመቀ የጋራ የአእምሮ ውጤት መሆኑን ማሣየት ይገባዋል በንብረት በሚከናወን ተግባር ውስጥ ልዩነትን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት አይችልም በሌላ በኩልም በውሣኔው የሚስማማ ነገር ግን የተለየ ምክንያት መቀመጥ ይገባዋል የሚል ፃሣብ ሊኖረው ይችላል የእነዚህ ልዩነቶች መፃፍ በዳኝነት ሥርዓቱ አቋም መጠናከር አስፈላጊ ሲሆን ቢፃፍ ይመረጣል ሲፃፍም አብዛኛውን ዳኛ በግል የሚመለከቱ ሁነው ሣይሆን የችሎት ውሣኔ የተባለውን ብቻ በሚመለከት ይሆናሉ ትችት እና ወቀሣ ያዘሉም መሆን የማይገባቸው ሆኖ በክርክሩ ላይ የተስማማውን ጭብጥ ብቻ ማዕከል ያደረጉ ይሆናሉ በተቻለ መጠን ልዩነት የሚያሰፍር ዳኛ ቢቻል ምጥን ባለ አገላለጽ ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር የማይስማማባቸው ነጥቦች አንዳሉ እና ነጥቦቹም ዘርዘር ብለው ቢገለጹ ይመረጣለል የአጻጻፍ አድማስ ተደጋግሞ እንደተገለፀው የአንድ ይግባኝ ሰሚ ፍቤት ዋና ተግባር በሥር ፍቤት የውሣኔ አሰጣጥ አና አካፄድ ላይ የተከሰቱ ስህተቶች በመከላከል ማረም ነው በዚህ ረገድ በሥር ፍቤቶች በርካታ ስህተቶች ተፈጽመው ሊገኙ ይችላሉ የተወሰኑት ተከራካሪ ወገን ላይ ጉዳት የማያደርሱ ሊሆኑ ይችላሉ ለምሣሌ ከሣሽ ዐዐዐዐ ብር ይገኛል በማለት የጠየቀውን ፍቤቱ ። ዐዐዐ ብር ይገባዋል ብሎ ቢወስን እንደማለት ነው የዚህ ዓይነት ስህተቶች በተለይ ከሀገራችን የሙግት መብዛት ጋር ተያይዞ ፍትህን የሚያዛቡ ሊሆነ ስለማይችሉ በይግባኝ ላይታረሙ ይችላሉ ስህተት ግልጽ እና አንድ ፍቤት በመሠረቱ ሊከተለው የሚገባውን አቅጣጫ የሣተ ሆኖ ሲገኝ መታረም ግድ ይለዋል ስህተት አልተፈጸመም ስህተት ቢፈጸምም ጉጅ አይደለም እንዲሁም ስህተቱ መታረም አለበት በማለት የይግባኝ ሰሚ ፍቤት የሚይዘው አቋም የሚገለጽበት ጽሑፍም ይለያያል የውሣኔው ይዘት ከፀሐፊ ፀሐፊ ሊለያይ ቢችልም በጥቅሉ የሚከተለውን ይመስላል የጉዳዩ ዓይነት ጭብጥ ፍሬ ነገር የተገኘው ስህተት ሕግ ትንታኔምክንያት ማጠቃለያ አንድ ውሣኔ ማጠቃለያ ይኖረዋል ከተራ ቁጥር ድረስ የተመለከቱት ነጥቦች በመሠረቱ ከዚህ ቀደም በነበረው ክፍል የተመለከትናቸው ሲሆኑ ልዩ ሁኔታዎች በውይይት የሚታይ ሆነው በዚህ ክፍል ውይይት በተራ ቁጥር ሥር የተመለከተውን ብቻ እናያለንየፍሥሥሕግ በቁጥር ላይ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በይግባኝ የቀረበለትን ውሣኔ ለማጽናት ለማሻሻል ለመለወጥ ወይም ለመሻር ይችላል በማለት ይደነግጋል በቁጥር እና መሠረትም ጭብጥ አስተካክሎ ወይም ክርክር ተደርጐ ውሣኔ እንዲሰጥ ጉዳዩን ለበታች ፍቤት መመለስ ይችላል በተመሣሣይ መልኩ የወንጀል ይግባኝ ሰሚ ፍቤት በወመህሥሥቁጥር መሠረት ይግባኙን የማጽናትጉዳዩን ሌላ ፍርድ ቤት እንዲምለከተው ማዘዝ ውሣኔውን ሙሉ « በሙሉ የመሻር ቅጣትን የመጨመርየማጽናትየመቀነስ ሥልጣን አለው ይህ ሥልጣን በተራ ቁጥር ሥር የተቀመጠው የይግባኝ ሰሚ ፍቤት ይግባኙን ከመረመረ በላ አቋሙን የሚገልጽበት ማጠቃለያው ነው ማጽናት ይግባኝ ሰሚ ፍቤት የሥር ፍቤትን የመዝገብ ግልባጭ መዝገብ ከመረመረ በኋላ በክሱ ውስጥ የሚያስገባው ስህተት አለመፈጸሙን ከተረዳ ይህንነ በመግለጽ ብቻ ብዙ ሣያስፈልገው ውሣኔውን በጹሑፍ ማስፈር ይችላል የፍሥሥሕቁጥር እና የወመህሥሥቁጥር ይህንኑ ያሰምሩበታል በዚህ መሠረት የይግባኝ ሰሚው ፍቤት ይግባኝ ባይ ያቀረበው ቅሬታ ተቀባይነት ስለሌለው የሥር ፍቤት ውሣኔ ፀንቷል በማለት ውሣኔን መፃፍ ይቻላል ማለት ነው በሀገራችን የውሣኔ አፃባፍ ሥርዓት ውስጥ ይግባኝ ሰሚ ፍቤቶች የሥር ፍቤት ውሣኔ ሲያፀኑ የይግባኝ ባይን ቅሬታ ከሥር ፍቤት የመዝገብ ግጭባጭ ጋር አገናዝበን እንደመረመርነው በሥር ፍቤት የተፈጸመ የሕግም ሆነ የፍፊ ነገር ስህተት ያላገኘን በመሆኑ ይግባኙን በፍሥሥሕቁጥር በወመህሥሥቁጥር መሠረት ሠርዘናል መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የሚል አጭር ትዕዛዝ መስጠታቸው በጣም የተለመደ ነው ይህንን አፃፃፍ በተመለከተ አንዳንድ ፀሐፊዎች የይግባኝ ባይ ቅሬታ ለምን ተቀባይነት እንዳላገኘ የማይገልፁ በመሆኑ ትክክለኛ አፃፃፍ አይደለም በማለት ሲተቹ ይሰማሉ የመወያያ ጥያቄ በፍሥሥሕግ እና ሌሎች ሥልጠናዎች ውስጥ ከተመለከትካቸው ውሣኔዎች ውስጥ የሰበር መቁጥር በዐዐዐ የተሰጠውን ትዕዛዝ « በመቁጥር ዐ በዐዐዐ የተሰጠውን ትዕዛዝ ተመልክተህ በውሣኔ አፃፃባፋቸው ላይ ያለህን አስተያየት አስቀምጥጭ ሁሉንም ትዕዛዞች አግባብ ነው ባልከው ሸው አፃዓፃዛፍ አስፍር ውሣኔ አፃፃፍ እና ሥነ ምግባር ውድ ሰልጣኞች ከዚህ ቀደም የሥነ ምግባር ኮርሶችን ወስዳችኋል ተብሎ ይገመታል ውሣኔ ሰጭዎች ሥነ ምግባራቸውን ሊጠብቁ የሚገባው ለፍቤትመቤታቸው እና ከፍርድ ቤት ውጭ በንግግራቸው በአኳሏናቸው እና በጽሑፋቸው ነው በሁሉም ረገድ ምን ዓይነት ሥነ ምግባር ሊከተል እንደሚገባ ከዚህ ቀደም የተመለከትነው ስለሆነ ተመልሰን በድጋሜ አንመለከተውም ይልቁንም ውሣኔ ሰጭዎች በጽሑፋቸው ምን ዓይነት ሥነ ምግባር ሊከተሉ እንደሚገባቸው ለይተን ብቻ በጥቅሉ እንመለከታለንበሀገራችን የፍትህ ሥርዓት ክርክሮች እና አለመግባባቶች በፍቤት ሲቋጩ በጽሑፍ መሆን እንዳለባቸው ህጐቻችን በአስገዳጅነት ደንግገዋል የዳኞች የመጨረሻ ተግባር አለመግባባትን በውሣኔ መቋጨት ነው ውሣኔው የተለያየ ስያሜ እየያዘ በጹሑፍ ይሰፍራል ከውሣኔ በፊት ዳኞች ያላቸው የፍቤት አመራር ችሎታ እና በሕብረተሰቡ በተለይ በተከራካሪ ወገኖች ብቻ ምስክርነት የሚያገኝ ነው በፍቤት ያለ አብዛኛው ታዳሚ ለራሱ ጉዳይ ብቻ የተለየ ትኩረት የሚሰጥ ነው ዳኛው ለሁሉም አግባብ ከባለጉዳይ ጋር የሚገናኘውም በዚሁ በራሱ ጉዳይ ነው የፍቤት ውሣኔ በጹሑፍ መስፈር ግን የግንኙነት አድማሱ ከሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር የሚሆንበት ዕድል ይሰፋል በሁሉም ግንኙነቶች የዳኞች ውሣኔ አስተያየት ባለጉዳይ እንዲሁም ሕብረተሰቡ ላይ ተፅዕኖ የሚያሣድረው ለተደረሰበት መደምደሚያ ብቻ ሣይሆን ውሣኔዎች እንዴት እንደተፃፉም ጭምር ነው ከፍቤት ውጭ ታዳሚ ዳኞችን የሚዳኘው በውሣኔያቸው ላይ በሚያሰፍሩት በዚሁ ፀሑፍ ነው ሕብረተሰቡ በፍቤት ላይ እምነት የሚጥለውም በተለይ በዚሁ ውሣኔ ነው ጽሑፍ ችሎታ ይለካበታል ይግባኝ ላይ ወሣኝ ሚና ይኖረዋል የሕብረተሰቡን ማኀበራዊ ግንኙነት የሚኖረውን ይዘት ይወስናል ተጠያቂነትን ያስከትላሉ ለሕግ ትምህርት እና ምርምር መሠረት ይሆናሉ የታሪክ ሰነድ ነውና ስለሆነም የሚፃፍ ውሣኔ ሊታመን የሚችል ገለልተኛ ቶን ያለው ክብሩን የጠበቀጉዳዮ ከሚፈጥረው ስሜት የራቀ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባልበእርግጥ በሥነ ምግባር መርሆዎች ውስጥ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ከመግለጽ ከመዘርዘር ይልቅ ምን መደረግ የለባቸውም የሚባሉትን መዘርዘሩ ቀላል ነው በውሣኔ አፃፃፍ ውስጥም ስድብ መግባት የለበትም የተገለበጠ የተዘበራረቀ መሆን የለበትም ከፍሬ ነገር የወጣ መሆን የለበትም ወዘተ የሚሉትን መዘርዘሩ ምን መካተት አለበት የሚለውን ከመዘርዘር ይቀላልጥሩ የውሣኔ ጽሑፍ የሚባለው የተከለከሉትንም የተፈቀዱትና በአግባቡ ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው በጥሩ ሥነ ምግባር የታነፀ ዳኛ ጥሩ ውሣኔ ሊጽፍ ይችላል ይህ ማለት ግን ጥሩ ስነ ምግባር ያለው ዳኛ ሁልጊዜ ጥሩ ውሣኔ ይጽፋል ማለት አይደለም ጥሩ ውሣኔ ለመፃፍ ከሚያስፈልጉ ቁምነገሮች ውስጥ አንዱ የሥነ ምግባር ደንቦች በውሣኔ በጽሑፍ ውስጥ በአግባቡ መጠበቃቸውን ማረጋገጥ ነው የዳኝነት የውሳኔ ፅሁፋ ታዳሚ መለየት ዳኞች ውሣኔ ሲጽፍ ውሣኔውን በማንበብ የሚታደሙ በርካታ እና የተለያየ የሕብረተሰብ ክፍል እንደሆነ ልብ ማለት ይገባቸዋል የአንድ ውሣኔ ታዳሚ ሊሆኑ ከሚችሉት ውስጥ ውሣኔውን የሚጽፈው ዳኛ ራሱ የሥራ ባልደረባ ዳኛ ዳኞች የውሣኔው ፈራሚ ዳኞች የሙያ የሕግ ማኅኀበር የሕግ ትምህርት ቤቶች ሥልጠና ማዕከላት በጉዳዩ ላይ ያገባናል የሚሉ ወገኖች ለምሣሌ ሴቶች ማኅበር ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ሕግ አውጭውና የመንግስት አካላት ዓለም አቀፍ አገር አቀፍ ድርጅቶች ሚዲያ ኢምባሲዎች የመላው ዓለም በኢንተርኒት ዌብ ሣይት ወዘተ የሚገኝበት መሆኑን ማስተዋል ተገቢ ነውውሣኔው ሲፃዓፍም በተለይ የሚመለከተው ታዳሚ እና የውሣኔው ግብ መለየት አለበት ተከራካሪ ወገኖች በተለይ በሕግ አሣማኝ የሆነ አስገዳጅ ውሣኔ የማግኘት መብት አንዳላቸውና ይህን መብት የማክበር ግዴታ ደግሞ የውሣኔ ሰጭው አካል ይሆናል ውሣኔ ሰጭዎች ሕግን የመተርጉም ሕግን የመፈጸም ተግባራቸውን ገለልተኛ ፍትሐዊ እና ግልጽ በሆነ መንገድ መውጣታቸውን በሕግ አውጭው እና በሕብርተሰቡ ያለባቸውን ተጠያቂነት ከሚወጡበት መንገድ አንዱ በአሣማኝ ምክንያት ላይ የተደገፈ ውሣኔ በመፃፍ ነው ውሣኔ በሚፃፍበት ጊዜም ከላይ ከተመለከቱት አና መሰል ታዳሚዎች መሐከል ሩ ውሣኔውን ማን ሊያነበው እንደሚችል ሩ አንባቢው ምን ማድረግ እንዳለበት ሩ ውሣኔው የሚገለጽበት አግባብ እና ቃል ከአንባቢው ጋር ያለው ግንኙነት ምን ሊሆን እንደሚችል አስቀድሞ በአአምሮ ማሰብ ይኖርበታል ውሣኔ በሚፃፍበት ጊዜ በውሣኔው ሊስማማ የማይችል አካል ሊኖር ይችላል በክርክሩ የተሸነፈ ጠበቃ የጠበቃ ማኀበርተከራካሪ ወገን ሌላ ዳኛ የበታች ወይም የበላይ ፍቤት ወዘተ በተሰጠው ውሣኔ ላይ ላይስማሙ ይችላሉ ክርክሩን በሽንፈት ያጣ ተከራካሪ ወገን በተለይ በውሣኔው እንዲስማማ ለማድረግ አግባብ ያለው የፍሬ ነገር ክርክር ሣይዛባ በታማኝነት ማስፈር የሚያስፈልግ ሲሆን ቢቻል ከፍሬ ነገሮች ውስጥ ፍርድ ቤቱ የተስማማባቸው ነጥቦች የተወኑትን በዚሁ ቃላት መገለጽ ጥሩ ይሆናል ይህም ፍቤቱ ውሣኔ ሲሰጥ ለተከራከሪ ወገኖች ክርክር እኩል ክብደት የሰጠ ታማኝ መሆኑን ለማሣየት ይጠቅማል ለተከራካሪ ወገኖች ክርክር ታማኝ መሆን ማለት ግን ተከራካሪ ያቀረበውን ክርክር ሙሉ በሙሉ በውሣኔ ላይ ገልብጦ ማስፈር ማለት አይደለምበአጠቃላይ ውሣኔ በሚፃፍበት ጊዜ ከሙያው የሚጠበቀው ሥነ ምግባር በአጠቃላይ መጠበቁን ማረጋገጥ ይገባል ለአብነት ገለልተኝነት ማሣየት ዲዩ ኘሮሶስ መጠበቁን ውሣኔ የመስጠት ብቃት ያለ መሆኑን የታዳሚ ክብርና ሙገሣ ሊቸረው የሚገባ የፍቤትን ክብር የጠበቀ መሆኑን እና የመሣሠሉትን የሥነ ምግባር መርሆዎች ያከበረ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል የመወያያ ጥያቄ ሥነ ምግባር እና የውሣኔ አፃፃፍ ያላቸውን ግንኙነት አብራራ ሪ ከዚህ በታች ያሉትን ጉዳዩች ተመልክተህሽ የውሣኔውን ግብ እና ታዳሚ ላይ አቶ ሀ ለልጅ ልጁ ሞግዚት እንዲሆን ጥያቄ አቅርቧል በሌላ በኩልሀ ልጅ ለራሷ ልጅ ሞግዚት መሆን ይገባኛል በማለት ተቃውማለች አቶ ሀ ሞግዚት ሊሆን ይገባል በማለት ትዕዛዝ ሰጥተፃል አቶ ለ ጠበቃ ለያዘው ክርክር የጠየቀው ክፍያ የተጋነነ ስለሆነ ሊቀነስ ይገባል በማለት ወሮ መ ጠይቀዋል ክፍያው የተጋነነ በመሆኑ የሙያ ሥነ ምግባሩን ባለመጠበቁ ሊቀነስ ይገባዋል በማለት ትዕዛዝ ሰጥተሃል አቶረ ስሜ ይቀየርልኝና ውሣኔው ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይላክልኝ በማለት ጠይቋል ስሙ እንዲቀየርለት ትዕዛዝ ሰጥተዛሣል በከተማ የሚሠራ የግንድ ባንክ ሠራተኛ ከባንኩ ደንብ ውጭ ለ ዓመት በቦታው እየሠራሁ ስለሆነ የ ዓመት ውሎ አበል ይከፈለኝ በማለት ጠይቋል የ ዓመት አበል እንዲከፈለው ውሣኔ ሰጥተሃል የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቶ መ የተባለው ሠራተኛ ያለው ባህሪ በዓለም አቀፍ ውድድር ውስጥ የማያስቀጥለው በመሆኑ ከሥራ አሰናብቶታል አቶ መ ወደ ሥራ እንዲመለስ ጠይቋል በአማራጭ በቂ ካሣ ተከፍሎት እንዲሰናበት የቀረበውን ጥያቄ ተቀብለህ አቶ መ ወደ ሥራ እንዳይመለስ ወስነሃል ሮፃ የተባለ ድርጅት ለመንገድ ሥራ ያከማቸው ድማሚት በአቶ በድሉ ይዞታ ላይ ሁከት የፈጠረ በመሆኑ በአስኳይ የተባለው ድማሚት በባለሙያ እንዲነሣ ወስነፃል ጊዜ ቢጠይቅም ይህ ጊዜ መግዣ ብቻ ነው በማለት በአስቸኳይ እንዲነሣ ወስነሃል አጠቃላይ የፍርድ አሰጣጥና አፃፃፍ ዘዴ ጉድለት ውጤት ፍርድ የፍቤቶች ዋናውና የመጨረሻው የሥራቸው ውጤት መለኪያ በመሆኑ ገድለቱ ዘርፈ ብዙ አሉታዊ ውጤት የሚያስከትል ስለሆነ በተቻለ መጠን በጥንቃቄ መታየት ይኖርበታልበመሆኑም ዋና ዋናዎቹን በምሳሌነት ለማየት ያህል በሚከተለው መልኩ ቀርቧል የፍትህ መዘግየትንና መንፈግን ያስከትላል በፍቤቱም ሆነ በተከራካሪ ወገኖች ላይ አላስፈላጊ የገንዘብ የቁሳቁስ የሰው ሃይልና የጊዜ ብክነትን ያስከትላል አላስፈላጊ ይግባኝ እና ሰበር አቤቱታና ክርክር እንዲበዛ ያደርጋል ባለጉዳዮች እንዲሁም ኀብረተሰቡ በፍቤቶችና በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ አመኔታ እንዲያጣ ያደርገዋል በመሆኑም በማኀበራዊበኢኮኖሚየዊ ፖለቲካዊና ባህላዊ ሥርዓቱ ላይ አሉታዊ ውጤት ይኖረዋል ተሳታፊዎች እስቲ ራሳችሁን በምሳሌነት ውሰዱና ለአፍታ ሁለት ደቂቃዎች ወስዳችሁ እንደባለጉዳይ ወይም እንደከሳሽተከሳሽ ወይም ይግባኝ ባይና መልስ ሰጪ አስቡና ከመደምደሚያ ድረሱ ለመሆኑ በፍቤቶቻችን አሠራር ፍርድ አሰጣጥና በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የአመኔታችሁ መጠን ስንት ፐርሰንት ይሆናል።