Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ፅ ፅፅርፅዐበን ናቸው በአጠቃላይ አሁን እየተሠራባቸው ያሉ የውርስ ህግጋት የሟች የሚንቀሣቀሥ እና የማይንቀሣቀሥ ንብረት ገንዘብና ከሌሎች ሰዎች የሚሰበሰብ ብድር ወይም ተከፋይ ገንዘብ የአክስዮን ድርሻና ሌሉች በሟች መሞት ምክንያት የማይቋረጡ የሟች መብትና ግዴታዎች ሊኖረው የሚችለው ከተወለደበት ቀን አንስቶ እስከሞተበት ቀን ድረስ ያለው ጊዜ ሲሰላ ከ ዓመት በላይ በመሆኑ በህጉ ቁጥር መሠረት ግልጽ ሀራጅ የሚያወጣው ዋጋ መሠረት ለማስቀረት የሚስማሙ ከሆነ በስምምነታቸው መሠረት መፈፀም አለበት አመልካች አና ተጠሪዎች ቤቱንና ቦታውን እኩል ይካፈሉ ብለናል ንብረቱ ለመከፋፈል የማይቻል ካልሆነና አመልካችና ተጠሪዎች በገበያ ዋጋ አንዳቸው የሌላውን ድርሻ ከፍለው ንብረቱን ለማስቀረት ያልተስማሙ እንደሆነ ንብረቱ በሀራጅ ተሸጦ የንብረቱን ዋጋ ግማሽ አመልካች ቀሪውን ግማሽ ደግሞ ተጠሪዎች ይውሰዱ ብለናል በዚህ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ፀጋዬ አስማማው አቶ አልማው ወሌ አመልካች ወሮ አቦነሽ ምትኩ ቀረቡ ተጠሪ እነ አቶ አዳነ ፎላ ምስት ሠዎች አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዮ የተጀመረው በአለታ ወንዶ ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን ቁጥሩ የሆነውን ቤት ተጠሪዎች ይዘው የሚጠቀሙበት ለመሆኑ ለቀው እንዲያስረክቡ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል የአመልካች አቤቱታ ተመርምሮ ተጠሪዎችን ያስቀርባል ተብሎ ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ የመልስ መልስ ሠጥተዋል የጉዳዮ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን ችሎቱም ይህንኑ አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መርምሮታል አንደመረመረውም የአመልካች ክስ የፍሕቁ ተጠቅሶ ውድቅ መደረጉ ባግባቡ ነው።
የሚሉትና ሌሉች በርካታ ጥያቄዎች ይነሣሉ አንድ ነገር በእርግጠኝነት ለመናገር የሚቻለው የእኛ አገር የውርስ ሕግ ብቻ ሣይሆን የብዙ አገሮች የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች የኑዛዜ ፎርሞች ጥብቅና አስገዳጅ እንዲሆኑ የሚያደርጉት ሟች ኑዛዜ የማድረግ ሀሣብ ኖሮትና የሚፈጽመውን ኑዛዜ ይዘት ተረድቶና አውቆት መሆኑ ለማረጋገጥ ጥብቅ የኑዛዜ አፈጻጸም ስርዓት አስቀምጦ ፎርማሊቲዎቹ መሟላታቸው ከመቆጣጠር ውጭ ሌላ መንገድ ስለሌላቸው ነው ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ ሕግም በሕጉ ከተቀመጠው አንዱ ካልተሟላ ኑዛዜው ፈራሽ እንደሚሆን ማስቀመጡ ተገቢነት ያለው ነው ለ በተናዛ ጽሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ በእኛ የውርስ ሕግ አንድ ሰው በራሱ የአጅ ጽሑፍ ነዛዜ እንዲፈጽም ይፈቅዳል ተናዛዙ በራሱ አጅ ጽሑፍ ያደረገው ኑዛዜ ሕጋዊ ውጤት የሚኖረው ተናዛ ኑዛዜው ሙሉ በሙሉ በራሱ የአጅ ጽሁፍ የጻፈው እንደሆነ ተናዛ የጻፈው ጽሑፍ ኑዛዜ መሆኑን በግልጽ ያመለከተ አእንደሆነ ኑዛዜው ከአንድ ገጽ በላይ ከሆነ ተናዛዙ እያንዳንዱ ገጽ ላይ ከፈረመበትና ቀን የጻፈበት አንደሆነ መሆኑን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል ከዚህ በተጨማሪ ተናዛ ያደረገውን ኑዛዜ ራሱ በመኪና ጽፎት እንደሆነና በእያንዳንዱ ቅጠል ራሱ በመኪና የጻፈው መሆኑን በእጅ ጽሑፍ ካመለከተ ውጤት እንደሚኖረውና ይህንን ካላደረገ ግን ፈራሽ እንደሚሆን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል እንደዚሁም በተናዛ አጅ ጽሑፍ የሆነው ኑዛዜ ተናዛ ያልተማረ ማህይም በመሆኑ ወይም ኑዛዜውን የተጻፈበትን ቋንቋ ካላወቀው ወይም ፍቻቸውን በማያውቃቸው ፊደሎች ጽፎ ቢገኝ ፈራሽ እነደሚሆንና ኑዛዜው የተደረገበትን ቀን ወርና ዓመት ምህረት ማመልከት እንደማገባው ይደነግጋል ሐ በቃል የሚደረግ ኑዛዜ አንድ ሰው የሞቱ መቃረብ ተሰምቶት የመጨረሻ ፈቃድ ቃሎቹን በሁለት ምስክሮች ፊት ሊሰጥ እንደሚችልና ይኸም የቃል ኑዛዜ በመባል እንደሚታወቅ የቃል ኑዛዜ በሕግ ውጤት እንዲኖረው የሚከተሉትን ሁኔታዎች ማሟላት እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል ኑዛዜው ያደረገው የመሞቻ ጊዜው መቃረቡን ተሰምቶት መሆን ይገባዋል ይኸ ማለት ምንም አይነት የሕመም ስሜት ወይም አደጋ ሣይገጥመው ሟች እኔ ስሞት እከሌ ይህንን ይወስዳል በማለት የሚያወራው ወሬ ሁሉ የቃል ኑዛዜ ነው ተብሎ እንደማይወሰድ የመሞቻ ጊዜው መቃረቡ ተሰምቶት የሚለው የሕጉ ድንጋጌ ሀረግ ያመለክታል ኑዛዜውን ያደረገው ቢያንስ ሁለት ምስክሮች ባሉበት መሆን አለበት እንደዚሁም ምስክሮቹ አካለ መጠን ያደረሱ በፍርድ ወይም በሕግ ያልተከለከሉ መሆን አለባቸው ከዚህ በተጨማሪ በቃል ኙዛዜ ሊደረግባቸው የሚችሉት ጉዳዮች ምን እንደሆኑ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል ከዚህ ላይ ግንዛቤ ሊያዝበት የሚገባው ነገር ሟች በግልጽ በሚደረግ ኑዛዜ ወይም በራሱ እጅ ጽሑፍ ባደረገው ኑዛዜ በርካታ ጉዳዮች አንዲፈፀሙለት መመሪያ ሊሰጥ ይችላል ይኸም ማለት ጠቅላላ የኑዛዜ ወራሽ መሾም ከፍተኛ የዋጋ ግምት ያለውን ንብረቱን በልዩ የነዛዜ ስጦታ መስጠት ከወራሾቹ አንዱን ወይም ሁሉንም ከውርስ መንቀል እና ሌሎች ጉዳዮችን አስመልክቶ ኑዛዜ መተው ይችላል በቃል ኑዛዜ ሊያካትታቸው የሚገባቸው ጉዳዮች ግን በሕግ ገደብ ተደርገበታል ሟች በሚያደርገው የቃል ኑዛዜ ስለ ቀብሩ ሥነ ሥርዓት መመሪያ መስጠት የእያንዳንዱ የስጦታ ዋጋ ከብር ለመብለጥ ሣይችል ልዩ የኑዛዜ ስጦታ ማድረግ አካለ መጠን ላላደረሰ« ልጆች ሞግዚት ወይም አስተዳዳሪ መሾም እንደሚችል የሕጉ ድንጋጌ ያሣያል ሟች በቃል ኑዛዜ ከነዚህ ውጭ የሆነ ነገር ቢናገር ለምሣሌ ጠቅላላ የኑዛዜ ወራሽ ቢሾም ወይም ከወራሾቹ አንዱ ከውርስ እንዲነቀል ቢናዘዝ ውጤት እንደማይኖረው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የሚደነግግ ሲሆን ሟች በቃል ኑዛዜ ግምቱ ብር በላይ የሆነ ስጦታ ቢሰጥ ከዚህ በላይ ያለው ነገር እንደሚቀንስ በፍትሐበሔር ሕግ ቁጥር ተደንግጓል በአጠቃላይ በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ሟች ሁለት ምስክሮቹ ባለበት ከሞተ በጐላ ስለሚፈፀሙ ነገሮች የሰጠውን ቃል የሚመለከቱ በመሆናቸው ከሟች ቃል ሊረሣ ወይም ሊጨመርበት የሚችሉበት አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ሕጉ በቃል ኑዛዜ ሊካተቱ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ገደብ በመጣል በዚህ በኩል ሊመጣ የሚችለውን ችግር ለመቀነስ ጥንቃቄ አድርጓል በኢትዮጵያ የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች ከሶስቱ በአንደኛ ፎርም የሚጠይቀውን ሁኔታ ሣያሟላ የተፈፀመ ኑዛዜ አውቅና የማይሰጥና ኑዛዜውም ዋጋ እንደማይኖረው በኑዛዜ ፎርም ጥብቅና አስገዳድ መሆኑን ፎርሙን አለማሟላት ኑዛዜውን ፈራሽ ሊያደርገው አንደሚችል መገንዘብ ያስፈልጋል ስለ ኑዛዜ የተደነገጉት የውርስ ሕግ የሕግ ድንጋጌዎች በፍርድ ቤቶች የሚሰጣቸውን ትርጓሜ ፍርድ ቤቶች ከሰጧቸው ውሣኔ አንጻር መመልከቱ ጠቀሜታ ይኖረዋል ከበርካታ ውርስ ውሳኔዎች መረዳት የሚቻለው ኑዛዜን አስመልክቶ የሚነሱ ክርክሮች አብዛኛዎቹ ኑዛዜው የሟች አይደለም ኑዛዜው ላይ ያለው ጽሑፍ ወይም ፊርማ የሟች አይደለም የሚሉ የክህደት ክርክሮች ከሟች የስጋ ወራሾች በኩል እንደሚቀርቡና ፍርድ ቤቶችም የእጅ ጽሑፍ ወይም ፊርማው የሟች መሆኑን ለማረጋገጥ ለፖሊስ የቴክኒክ ምርመራ ክፍል በመላክ ይኸ የማይቻል ከሆነ ደግሞ ነዛዜው ሲደረግ ምስክር የሆኑ ሰዎችን ቃል በመስማት ውሣኔ እንደሚሰጡ በርካታ አብነቶችን በማንሣት ለማየት ይቻላል ይኸም ኑዛዜው የሟች አይደለም ወይም ኑዛዜው ጽሑፍ ወይም ፊርማ የሟች አይደለም የሚል ክርክር በሚቀርብ ጊዜ ነዛዜው ላይ ያለው ፊርማ የሟች መሆኑን ለማረጋገጥ ምን አይነት ማስረጃ ነው መቅረብ ያለበት የሚለውን ነጥብ ለመገንዘብ የሚረዳ ይሆናል ይህንን አስመልክቶ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ይግባኝ መዝገብ ቁጥር ጥቅምት ቀን ዓም በይግባኝ ባይ በወሮ ደመቀች ልባሴ እአና በመልስ ሰጭዎች በእነ ሻንበል ባሻ ተዘራሽ ሙሉነህ መካከል የነበረውን የይግባኝ ክርክር አይቶ የሰጠው ውሣኔ በአጭሩ ማየቱ ይጠቅማል የክርክሩ መነሻ የሆነው የሟች ሙሉነህ ተክለወልድ ሚስት ነኝ የምትለው ይግባኝ ባይ ወሮ ደመቀች ሰኔ ቀን ዓም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ባለቤቱ ነዛዜ የተወልኝ ሰለሆነ የኑዛዜ ወራሽ መሆፄ ይጽናልኝ በማለት ጉዳዩን በመጀመሪያ ለሚያየው ፍርድ ቤት ያቀረበችው ማመልከቻ ሲሆን መልስ ሰጭዎች በተቃዋሚነት ቀርበው አባታችን ዓም ጀምሮ ማየት ስለማይችል ኑዛዜ ይጸናልኝ በማለት ያቀረበችው ሰነድ የሀሰት ሰነድ ነው በኑዛዜው ላይ ያለው ፊርማ የአባታችን ስላልሆነ ይመረመርልን በማለት ክርክራቸውን አቅርበዋል ጉዳዮን በመጀመሪያ ያየው የአራዳ አውራጃ ፍርድ ቤት ኑዛዜው ላይ ያለው ፊርማ የሟች ፊርማ ስለመሆኑ ተመርምሮ ውጤቱ እንዲቀርብ ለፖሊስ ቴክኒክ ምርመራ ክፍል ታዞ የፖሊስ ቴክኒክ ምርመራ ክፍልም ኑዛዜው ላይ ያለው ፊርማም ሆነ ለማመሣከሪያ የተላከው ፊርማ የተበላሸ ስለሆነ ፊርማው የእገሌ ነው ብለው ለመለየትና ለማረጋገጥ አልቻልንም በማለት ምላሽ ሰጥቷል የአውራጃው ፍርድ ቤት ወሮ ደመቀች የሟች ሚስት ስለመሆኗና ሟች ኑዛዜ ያደረገላት ስለመሆኑ አራት ምስከሮችን ከሰማ በኋላ የሟች ሚስት መሆኗን በኑዛዜ ካረጋገጠ በኋላ ኑዛዜውን በተመለከተ ሟች የፈረመበት ስለመሆኑ ግልጽ ሆኖ በቴክኒክ ምርመራ ያልቀረበ ስለሆነ ወሮ ደመቀች የሟች የኑዛዜ ወራሽ አይደለችም በማለት ወስኗል ይግባኝ ባይ በዚህ ውሣኔ ይግባኝ ብላ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኙን ብታቀርብም የከፍተኛው ፍርድ ቤት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር እና የሚቃረን በመሆኑ ይግባኙን አልተቀበልነውም በማለት የአውራጃው ፍርድ ቤት በውሣኔው ከሰጠው የተለየ የሕግ ምክንያት በመጥቀስ የይግባኝ ባይን ይግባኝ ውድቅ አድርጉታል ይግባኝ ባይ የከፍተኛው ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሣኔ ባለመቀበል ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርባለች ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተለያየ ምክንያት በመስጠት የአውራጃው እና የከፍተኛው ፍርድ ቤት የሰጡትን ውሣኔ የሚከተለውን ትችት በመስጠት ሽሮታል ከመዝገቡ ለመረዳት እንደቻልነው የፖሊስ የቴክኒክ የምርመራ ውጤት ፊርማው የሟቹ ነው አይደለም ለማለት አንችልም ከማለት ውጭ በግልጽ ያስቀመጠው ነገር የለም ይህም በመሆኑ ሟች ኑዛዜው ላይ ሲፈረሙ የነበሩና በኑዛዜው ላይ በምስክርነት የተጠቀሱት ምስክሮች ቀርበው በኑዛዜው ላይ ሟች መፈረማቸውን አረጋግጠዋል በመሆኑም ፊርማው የሟች ለመሆኑ በቴክኒክ ምርመራ ለማረጋገጥ ባይቻልም በኑዛዜው ወቅት ነበርን የሚሉ ምስክሮች የሰጡት ቃል ሲመዘን ዋጋ ያለው ሆኖ በመገኘቱና ማስተባበያ ማስረጃም ያልቀረበበት ስለሆነ ነዛዜው የሟች ኑዛዜ ነው ለማለት ተችሏል በመሆኑም የስር ፍርድ ቤት የይግባኝ ባይ የኑዛዜ የጽደቅልኝ ጥያቄ ኑዛዜው ን ሕገ ወጥ ነው በማለት ውድቅ ማድረጉ አግባቡ ስላልሆነ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት ሽረነዋል በማለት ውሣኔ ሰጥቷል በዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ አስተያየት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሣኔ ተገቢነት ያለው ነው ኑዛዜን አስመልክቶ የሚነሱ ክርክሮች ሟች ከሞተ በኋላ የሚቀርቡ በመሆናቸው የሟች የስጋ ዘመዶችና የሕግ ወራሾች የተለያየ ምክንያት እየፈጠሩ የሟችን ኑዛዜ በመቃወም ሙሉ ውርሱን ለመውሰድ ይጥራሉ አንዳንድ ጊዜ የሟች የማመሣከሪያ ፊርማዎች አንዳይገኙ ለማድረግ ሰነዶችን ሆነ ብለው በመቅደድ በማቃጠልና በማበላሸት ለቴክኒክ ምርመራ አስፈላጊ የሆነውን የማመሣከሪያ ፊርማ የሚያጠፉበት ወይም የሚያበላሹበት ሁኔታ ያጋጥማል እንደዚሁ አይነት ሁኔታ ሲያጋጥም በነዛዜው ለይ ስማቸውና ፊርማቸው በምስክርነት የተገለጹት ሰዎች ሟች በኑዛዜ ሰነዱ ላይ ፊርማ የፈረመ ስለመሆነ በአጥጋቢ ሁኔታ ካስረዱ የሟችን ኑዛዜ ውድቅ ማድረግ ሟቹ ከሞተ በላ ንብረቱን ለማስተላለፍ አስቦ የፈፀመውን ተግባር ያለ ምክንያት ህጋዊ ውጤት እንዳያገኝ ማድረግና የሟች የሕግ ወራሾች የሟችን የኑዛዜ ጽሑፍና ፊርማ ወይም ለማመሣከሪያ የሚሆኑ ሰነዶችን ሆነ ብለው አያጠፉ እና እያበላሹ የሕግ ወጥ ተግባራቸው ፍሬ እንዲሰበሰቡ መፍቃድ ጭምር ሆኗል በመሆኑም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ማስረጃውን የመዘነበትና የተቀበለበት አግባብ የሟችን ነዛዜ አና ፍቃድ ከማስፈፀም አንጻር ፍርዱ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል ሌላው በኑዛዜ ዙሪያ የሚደረጉ ክርክሮች የኑዛዜ ፎርሞችን መነሻ ያደረጉ ናቸው ከዚህ በፊት እንዳየነው ሟች ኑዛዜው በሕግ ፊት ውጤት እንዲኖረው ከፈለገ በሕጉ መሟላት አለባቸው የተባሉ ፎርሞችን በሟሟላት ኑዛዜውን ማድረግ አለበት እዚህ ላይ የሚነሣው ጥያቄ ሟች በሕጉ ከተገለፀው ፎርም አንዲን እንኳን መስፈርት ባያሟላ ምን ይሆናል የሚለው ነጥብ ነው በዚህ ዙሪያ የሚነሱ ክርክሮችንና የሚሰጡ ውሣኔዎችን ለመረዳት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ይግባኝ መዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም በይግባኝ ባዩ በአቶ ገብረየስ አርፍቶ አና በመልስ ሰጭ አፀደ ተፈራ መካከል የቀረበውን ክርክር ሰምቶ የሰጠውን ውሣኔ ማየቱ ለግንዛቤ ይረዳል ክርክሩ የተነሣው ይግባኝ ባይ ሟች እናቴ ወሮ ለተየሰ መካሻ መሆኔ ይረጋገጥ በማለት በወቀቱ ለነበረው ለአውራጃው ፍርድ ቤት በማመልከቱ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ተቃዋሚ ስላልቀረበ ምስክሮችን ሰምቶ ኑዛዜውን አጽድቋል በዚህ በኋእላ መልሰ ሰጭ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት ውሣኔው ላይ ሟች የተናዘዘችበት ንብረት የሟች ሣይሆን የእኔ አባት ቤት ስለሆነ ውሣኔው ይሠረዝልኝ በማለት ውሣኔውን ለሰጠው ፍርድ ቤት በማመልከቷ የአውራጃው ፍርድ ቤት ሟች የተናዘዘችበት ቤት የተቃዋሚዋ መልስ ሰጭ አባት ቤት ስለሆነ መጀመሪያ የሰጠሁትን ውሣኔ ሽሬዋለሁ በማለት ወስኗል የአሁን ይግባኝ ባይ የአውራጃው ፍርድ ቤት ጉዳዮን በድጋሚ አይቶ በሰጠው ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦ የፊተኛው ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ የቀረበው ኑዛዜ በሟች የአጅ ጽሑፍ የተደረገ ኑዛዜ ሣይሆን በግልጽ የተደረገ ኑዛዜ ነው ሆኖም ኑዛዜው የተደረገው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር በሚደነግገው መሠረት በአራት ምስክሮች ፊት ሣይሆን በሶስት ምስክሮች ፊት ስለሆነ በሕጉ የተቀመጠውን ፎርማሊቲ አላሟላም በማለት የአውራጃው ፍርድ ቤት የሰጠውን ምክንያት ለውጦ ኑዛዜው አይፀናም የሚለውን የስር ፍርድ ቤት ወሣኔ አጽንቶታል ይግባኝ ባዩ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሣኔ ቅር በመሰኘት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኙን አቅርቧል ፍርድ ቤቱም የይግባኝ ባይንና የመልስ ሰጭን ክርክር ከሰማ በኋላ በሰጠው ውሣኔ ይህ ፍርድ ቤት መዝገቡን ከሕጉ ጋር መርምሯል ይህንን ጉዳይ ለመወሰን መልስ ማግኘት የሚገባው ጭብጥ ኑዛዜው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ፈራሽ ነው መባል ይገባዋል ወይስ አይገባውም የሚለው ነው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር እና እንደተመለከተው ተናዛ እየተናገረ ማናቸውም ሌላ ሰው በተናዛና በአራት መስክሮች ፊት ካልተነበበና ይኸው ስርዓት ፎርማሊቲ መፈፀምንና የተፈፀመበትን ቀን የሚያመለከት ካልሆነ በቀር ፈራሽ ነው ወደዚህ ጉዳይ ስንመለስ ኑዛዜው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የተመለከተውን ፎርም አላሟላም ኑዛዜው የተደረገው በአራት ምስክሮች ፊት ነው የሚል ክርክር በይግባኝ ባይ በኩል አልቀረበም በነዛዜው ላይ በምስክረነት የተጠቀሱት ሶስት ሰዎች ናቸው ሰለዚህ ኑዛዜው በአራት ምስክሮች ፊት ነው የሚል ክርክር በይግባኝ ባይ በኩል አልቀረበም በኑዛዜው ላይ የምስከርነት የተጠቀሱት ሶስት ሰዎች ናቸው ስለዚህ ኑዛዜው በአራት ምስክሮች ፊት አለመደረጉ አላከራከረም ይህ ማለት ኑዛዜው የተደረገው በአራት ምስክሮች ፊት ሣይሆን በሶስት ምስክሮች ፊት ነው ማለት ነው ይህ ከሆነ ዘንዳ የተጠቀሰው ኑዛዜ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ፈራሽ ነው ተብሎ መወሰኑ የሚነቀፍ ስላለሆነ ይግባኝ የቀረበበት ውሣኔ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት ፀንቷል በማለት ወስኗል እዚህ ላይ የአንድ ምስክር ነዛዜው ሲደረግ አለመኖር የነዛዜውን ፈራሸነት ማስከተሉ ምን ያህል ሚዛናዊና ፍትሐዊ ነው የሚለውን ክርክር የሚያነሠ ሰዎች አሉ ሆኖም ዳኞች በሕጉ በግልጽ ፊን የተቀመጠውን ድንጋጌ ሥራ ላይ የማዋል ኃላፊነት አለባቸው ዳኞች ሕግ የሚተረጉሙት የሕጉ ድንጋጌ ግልጽ ካልሆነ ወይም ክፍተት ያለበት ሲሆን እንጅ በሕግ የተገለፀውን ሁኔታ በርትዕና ሚዛናዊነት ሰበብ ሊጋፉት አይገባም በአጭሩ ዳኞች ሕግ ሊተረጉሙ እንጅ በሕግ መተርጐም ሰበብ ሕግ እንዲያወጡና ሕግ አውጭው በግልጽ ያስቀመጠውን የሕግ ድንጋጌ እንዲሽሩ አይፈቅድላቸውም በሌላ በኩል የነዛዜ ፎርሞች አለመሟላት ጥብቅ የሆነ አፍራሽ ውጤት እንደሚያሰከትሉ በሕጉ በግልጽ ተቀምጧል ስለዚህ ሟች ኑዛዜው ዋጋ እንዲኖረው ከፈለገ በሕጉ የተቀመጠውን ጥብቅ ስርዓት አሟልቶ ኑዛዜውን መተው አለበት በመሆኑም የፍትሐበሔር ሕግ ቁጥር አለመሟላት ምክንያት በማድረግ በከፍተኛው ና በጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰጠው ውሣኔ የኑዛዜ ፎርም የሚደነግጉ ድንጋጌዎች አስገዳጅና ጥብቅ መሆናቸውን በሚያረጋግጥ መልኩ የተሰጡ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ሌላውን በትኩረት መታየት ያለበት የኑዛዜ ፎርም አለመሟላት አስመልክቶ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍመቁ የካቲት ቀን ዓም ይግባኝ ባይ በአቶ አፍወርቅ ደምሴና መልስ ሰጭ በወት እጅግአየሁ ደምሴ መካከል የሰጠውን ውሣኔ ማየቱ የኑዛዜ ፎርም መሟላት ጉዳይ ኑዛዜውን በሕግ ፊት ዋጋ አንዲኖረው ለማድረግ አስፈላጊና አስገዳጅ አንደሆነ ለመገንዘብ ይጠቅማል ተከራካሪዎቹ የሚከራከሩት በሁለት መሠረታዊ ጉዳዮች ነው የመጀመሪያው በውርስ ንብረት ክፍፍል ሲሆን ሁለተኛው አቶ አፈወረቅ ደምሴ ሟች እናቴ ወሮ ዘነበች ቦጋለ ቤቱንና የቤቱን አቃ እኔ እንድጠቀምበት በግልጽ ኑዛዜ አውርሣኛለች በማለት ያቀረበው ክርክርና ማስረጃ ነው ጉዳዮን በመጀመሪያ ያየው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ባይና መልስ ሰጭ የሟችን ንብረት አኩል እንዲካፈል ሲወስን ይግባኝ ባይ የሟች የኑዛዜ ተጠቃሚ ነኝ በማለት ያቀረበውን ክርክር ውድቅ አድርጉበታል ይግባኝ ባይ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ሟች ለአኔ ኑዛዜ የተውልኝ ስለመሆኑ የሰነድ ማስረጃውን ሣይመረምርና ምስክሮችን ሣይሰማ መወሰኑ ተገቢ አይደለም በሚልና በንብረት ክፍፍሉ በተሰጠው ትዕዛዝ ቅር በመሰኘት ይግባኙን በጠቅላይ ፍርድ ቤት በማቅረቡ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ ኑዛዜውን በተመለከተ የይግባኝ ባዩን ሁለት ምስክሮች በማስቀረብ ሰምቷል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ምስክሮችን ሲሰማ ከምስክሮቹ አንደኛው አቶ ታደሠ በርቄ የተባለው ሟች ኑዛዜ ስታደረግ በቦታው የነበረው መሆኑን ገልጾ ነገር ግን በኑዛዜው ላይ እንዳልፈረመና በአሱ ስም ፊት ለፊት ያለው ፊርማ የእሱ እንዳልሆነ እሱ በጣት አሻራ ካልሆነ በስተቀር ማንበብና መጻፍና ስለማይችል በጽሑና መፈረም እንደማይችል አስረድቷል ጉዳዮን ካዩት ሁለት ዳኞችም ይህ የሟች ኑዛዜ የተባለው በሕግ ፊት የፀና እንዲሆን ሕጉ የሚለውን አሟልቶ መገኘት ይኖርበታል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት በኑዛዜው ሰነድ ላይ የሟችና የአራት ምስክሮች ፊርማ መኖር አለበት በኑዛዜው ላይ የአራት ምስክሮች ስምና ፊርማ በግልጽ ይታያል ይሆን እንጅ በኑዛዜው ላይ ስማቸው በአራተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት አቶ ታደሰ ብርቄ ኑዛዜውን ተመልክተው በስማቸው ፊት ለፊት ያለው ፊርማ የአሣቸው አለመሆኑን በዕለቱም በኑዛዜው ላይ አለመፈረማቸውን መጻፍም ሆነ ማንበብ አለመቻላቸውን ገልፀው የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል ምስክሩ ፍርድ ቤት ቀርበው በዚህ መልክ እያስረዱ ፊርማው የምስክሩ ፊርማ ነው ተብሎ የሚወሰድበት ምክንያት የለም ሰለዚህ ይግባኝ ባይ የሟች ኑዛዜ ነው በማለት በማስረጃነት ያቀረቡት በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ፎርማቱን ጠብቆ ያልተዘጋጀ መሆኑ ስለተረጋገጠ የስር ፍርድ ቤት ኑዛዜው ፈራሽ ነው በማለት የሰጠው ውሣኔ የሚነቀፍ ሆኖ አልተገኘም በማለት የወሰኑ ሲሆን ሶስተኛው ዳኛ በበኩላቸው በውሣኔው ባስቀመጡት የሐሣብ ልዩነት ግራ ቀኙን እያከራከረ ያለው የወሐሮ ዘነበች ቦጋለ ኑዛዜ ሕጉ የሚጠይቀውን መሰፈርት ያሟላ መሆን አለመሆኑን አስመልክቶ ሲመረመር አንዱ ምስክር ያልፈረመበት መሆኑን የመሠከረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በቦታው ተገኝቶ ኑዛዜ ሲደረግ የሰማ መሆኑን መስከሯል የኑዛዜውን ይዘትና የተናዘዙበትን ሁኔታ አስመልክቶ ከሌሎች ምስክሮች ጋር የሚስማማ መልኩ መስክራል የምስክሮች ቃል ከኑዛዜው ጋር በይዘቱ የተስማማ ነው ነገር ግን የቀረበው ኑዛዜ ተናዛዥዋ ያአውራጣት ምልክታቸውን አድርገውበታል ተብሎ የቀረበ ቢሆንም ያውራጣት ምልክት ነው ተብሎ የተቀመጠው ምልክት በእስክርቢቶ የተሞጫጨረ እንጂ በአርግጥም የጣት አሻራ አለመሆኑን በአይን ስመለከተው በግልጽ ለይቸዋለሁ ስለዚህ አእንደብዙሀኑ ድምጽ ምስክረ አልፈረመበትም በሚል ብቻ ሣይሆን ተናዛዥዋ የአውራጣት ምልክታቸውን ያላደረጉበትም በመሆኑ ጭምር ኑዛዜው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ላይ የተመለከተውን መስፈርት ስላላሟላ ከብዙሀኑ ደምጽ በአካሄድ ብቻ በሐሣብ ተለይቻለሁ በማለት ወስነዋል ከላይ ካነሣናቸው በፍርድ ቤት ታይተው ከተወሰኑ ጉዳዮች የምንረዳው አንድ ነዛዜ በሕግ ማሟላት የሚገባውን ፎርማሊቲ በተሟላ ሁኔታ ካላሟላ ፈራሽ እንደሚሆን ነው ምከነየቱም ሕጉ የኑዛዜ ፎርም አስመልክቶ ያስቀመጣቸው ድንጋጌዎች እጅግ ጥበቅና ተናዛዥ በሕይወት ዘመኑ የሚያደርገው ኑዛዜ ከሞተ በኋላ ውጤት እንዲኖረው ከፈለገ ሊከተላቸው የሚገቡ አስገዳጅ ድንጋጌዎች ናቸው ተናዛ ሕጉ ካስቀመጠው ፎርም አንዷን ሣያሟላ የሚተወው ኑዛዜ ፈራሽ አንደሚሆን አውቆም ሆነ ሳያውቅ የሕጉን ፎርማሊቲ አንዲን እንኳን ሣያሟላ ነዛዜ ጥሎ ካለፈና በዙዛዜው ተፈጻሚነት ክርክር ከተነሣ ነዛዜው ፈራሽ ይሆንበታል ሰለዚህ የኑዛዜ ፎርም ለነዛዜ በሕግ ፊት ዋጋ መኖር አጅግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን መገንዘብ ይገባናል ኑዛዜው ያልተሻረ ወይም ውድቅ ያልሆነ መሆኑ አንድ ኑዛዜ በሕገ የተደነገጉትን የሥረ ነገር ሁኔታዎች አሟልቶ መገኘቱና በሕጉ በተደነገገው ፎርም መሠረት መፈፀሙ ብቻውን ሟች በሞተ ጊዜ ኑዛዜውን ውጤት ለማሰጠትና ለማስፈፀም አያስችልም በሕጉ የተደነገጉትን የሥረ ነገር ሁኔታዎች በሟሟላት ሕጉ በሚደነግገው ፎርም መሠረት የተፈፀሙ ኑዛዜ ዋጋ የሚኖረው ሟች ኑዛዜውን ያልሻረው ወይም ኑዛዜው ውድቅ ያልሆነ እንደሆነ ነው እዚህ ላይ መታየት ያለበት የኑዛዜ መሻር እና የኑዛዜ ውድቅ መሆን አንድና ተመሣሣይ አለመሆናቸው ነው የኑዛዜ መሻርና ቬጩህዐርልከበ ዐ ህዚ የኑዛዜ ውድቅ መሆን ዐ ህ በተለይ በኢትዮጵያ የውርስ ሕግ ውስጥ የተለያዩ ጽንሰ ሀሣቦች ናቸው የኑዛዜ መሻር የሃዐርከርበ ዐ ነኣ የነዛዜ መሻር የሚለውን ጽንሰ ሀሣብ ብዙ የሕግ ሙሁራን በብዙ መንገድ ይተረጉሙታል የኑዛዜ መሻር የሚለው ጸንስ ሀሣብ ተናዛዥ ኑዛዜውን ካደረገ በጐላ ያደረገው ኑዛዜ ውጤት እንዳይኖረው አስቦ የሚፈጽመውን ማናቸውንም ድርጊት አጠቃለን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ቃል ነው ለግንዛቤአችን ይረዳን ዘንድ በከር ዉ በርከርበፌቫዥ የተሰጠውን ትርጉም ብንመለከት ክፀህሃርከበዕበ ዐ ህ ርባ በከበህበ ዕ በበቨበ በፀሃፀ ልበ እበ ነኣ ሀሃ ጠፅ ሀህባሀህበ። የሚሉትን ነጥቦች መዳሰሱ አስፈላጊ ነው ከዚህ ምዕራፍ ውስጥ ትኩረት የሚሰጠው በተለይ የሟች ውርስ ከተከፈተ በጊላ ሊቀርቡ የሚችሉ ክርክሮችን አስመልክቶ በሕጉ የተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች እና በአፈጻጸምና በአተረጓጐም ላይ ያለው ችግር ላይ ነው ኩዛዜን ስለመቃወም የተቀመጠ የጊዜ ገደብ በመጀመሪያ የውርሱ አጣሪ የሟችን ኑዛዜ የማፈላለግ ግዴታ እንዳለበት እና የሟችን ኑዛዜ ባገኘ ጊዜ ሟች በሞተ በአርባ ቀን ውስጥ የሟች ያለኑዛዜ ወራሾች አንደሚናገርና ኑዛዜው የሟች ያለኑዛዘ ወራሾች ባሉበት እንደሚነበብ እንደዚሁም የኑዛዜው ፎርምና ኑዛዜው ዋጋ ያለው መሆኑ አእንደሚመረመር በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር እና በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋሉ እንደዚሁም ሟች ኑዛዜ ያልተወ እንደሆነ የውርሱን አደራረግ እና የአከፋፈል ዓይነት እንዴት ሊፈፅም እንዳቀደ ውርስ አጣሪ ለሟች ያለ ነዛዜ ወራሾች ሟች ከሞተ ከአርባ ቀን በኋላ ማሳወቅ እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋልኑዛዜው ሲነበብ የነበሩ ወይም በአግባቡ የተወከሉ ሰዎች ኑዛዜው በጠቅላላ አይፀናም ወይም በኑዛዜው ከተነገረው ቃል ውስጥ አንዱ አይፀናም በማለት ክስ ለማቅረብ ያላቸውን የኃሣብ መግለጫ ወይም ስለክፍያው በሒሣብ አጣሪው ያቀረበውን ድልድል አመዳደብ ኃሣብ ለመቃወም ነዛዜው ከተነበበበለት ቀን አንስቶ የአሥራ አምሥት ቀን ጊዜ እንዳላቸው ይህ መግለጫ በፅሑፍ ካልሆነና ለአጣሪው ወይም ለዳኞች ካልደረሰ በርቀት እንደማይፀና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር እና ይደነግጋሉበእነዚህ የሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ነዛዜው ሲፈስ ሲነበብ ወራሹ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ የነበረ ሰው የሟች ኑዛዜ ነው ብሎ ውርስ አጣሪው በያዘው ኑዛዜ ላይ መቃወሚያና ክርክር ማቅረብ ከፈለገ ይህንኑ ኃሣቡን በፅሑፍ ለውርስ አጣሪው ለዳኞች ወይም የወራሹን ጉዳይ ለማየት የተሰየሙ የሽማግሌ ዳኞች ካሉ በአሥራ አምሥት ቀን ውስጥ የጽሑፍ መግለጫ መስጠት እንዳለበት ይደነግጋል ሕጉ የሚለው መቃወሚያውን ኃሣብ ያለው መሆኑን ማሳወቅ አለትፊ ወራሹ በአሥራ አምሥት ቀን ውስጥ የፅሑፍ መግለጫውን ባያቀርብ ምን ይሆናል የሚለውን ጥያቄ ስናነሳ በአሥራ አምሥት ቀን ውስጥ ለመቃወም ያለውን የኃሣብ መግለጫ ካላቀረበ በኑዛዜው ወይም የውርሱ አጣሪ ያቀረበውን የድልድል ኃሣብ እንደተቀበለ እንደሚቆጠር ከሕጉ ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል አዚህ ላይ ስለክፍያው በሒሣብ አጣሪው የቀረበውን ድልድልን አመዳደብ ኃሳብ በመቃወም የሚለው ሐረግ የውርሱ ኃብት በወራሾች መካከል የሚደረገውን አከፋፈል ማለት እንዳልሆነ መገንዘብ ይገባል ውርስ አጣሪው ውርሱ ከመዘጋቱ በፊት የሟች የመክፈያ ጊዜ የደረሰ ዕዳ እና የመክፈያ ጊዜ ያልደረሰ ዕዳ የሟችን ልዩ የኑዛዜ ስጦታ እና የውርሱን ዕዳ አንዴት ሊከፍል አንዳለበት የሚያቀርበውን የክፍያና የድልድል ኃሣብ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ በአሥራ አምሥት ቀን ውስጥ መግለጫቸውን ማቅረብ አለባቸው በማለት ታስቦ የተደነገገ ድንጋጌ ነው ምክንያቱም ውርሱ ከተዘጋ በኋላ ወራሾች ውርሱን የሚከፋፈሉት በመካከላቸው የሚያደርጉት ሥምምነት በሚች ኑዛዜ ውስጥ በተቀመጠ የክፍያ ደንብ ወይም ዳኞች በሚሰጡት ትዕዛዝ መሠረት መሆኑን በምዕራፍ ስድስት በሰፊው ያየነው በመሆኑ ነውነዛዜው ሲነበብ የነበሩ ወይም በሕጋዊ ወኪላቸው የተወከሉ ሰዎች ኑዛዜው አይፀናም ወይም በውርስ አጣሪው የቀረበው የክፍያና የድልድል ኃሣብ ተገቢ ዓይደለም የሚለውን መቃዎሚያ በፅሑፍ በአሥራ አምሥት ቀን ውስጥ ካሣወቁ በላ መግለጫውን ካቀረቡበት ቀን ጀምሮ እስከ ሶስት ወር ድረስ ክሱን ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ወይም በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ለተሰየመው የሽምግልና ዳኞች ክስ ካላቀረበ በስተቀር በሌላ ጊዜ መቃወሚያውን ማቅረብ አንደማይችል እና ጥያቄው በይርጋ እንደሚታገድ የፍትሐብሐር ሕግ ቁጥር ይደነግጋልኑዛዜው ሲነበብና ሲፈፀም ያልነበሩ ወይም ሕጋዊ ወኪል ያልነበራቸው ሰዎች የውርሱ አጣሪ ስለኑዛዜው እና ክፍያና ድልድል አመዳደብ ኑዛዜው ሲነበብ ላልነበረው ሰው ከነገረው በአሥራ አምሥት ቀን ውስጥ የመቃወሚያውን የፅሑፍ መግለጫ ማቅረብ ያለበት መሆኑንና መግለጫ ካቀረበበት ቀን ጀምሮ እስከ ሶስት ወር ድረስ ክሱን ለዳኞች ማቅረብ እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋልኑዛዜው ሲነብና ሲፈርስ ራሣቸው ወይም ወኪላቸው ያልነበሩ ሰዎችና ከዚያም በጊላ ውርስ አጣሪው አግኝቶ ስለኑዛዜው ያልነገራቸው ሰዎች ኑዛዜው ከፈሰሰበት ጊዜ ከአምሥት ዓመት በላ ወይም ኑዛዜ የሌለ ከሆነ ሟች ከሞተ ከአምሥት ዓመት በላ በኑዛዜው መፅናት ስለከፍያው አመዳደብ አጣሪው ያቀረበውን ኃሣብ በማናቸውም አስተያዬት ቢሆን መቃወሚያ ሊያቀርብበት እንደማይችል እና ጥያቄው በይርጋ አንደሚታገድ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል ከላይ ያነሳናቸው የሕግ ድንጋጌዎች በውርስ አጣሪው አፈላልጐ ባቀረበው ኑዛዜና ባቀረበው የክፍያና የድልድል ኃሣብ ላይ ያለ ኑዛዜ ወራሾች በስንት ጊዜ ውስጥና እንዴት መቃወሚያቸውን ማቅረብ አንደሚችሉ የሚደነግጉ ናቸው እነዚህን የሕግ ድንጋጌዎች በሌላ ክፍል ስለ ውርስ ይርጋ ከተደነገጉት ጋር በማገናዘብ ማየት ይገባል የወራሽነት ጥያቄ ለማቅረብ የተቀመጠ የጌዜ ገደብ ወራሽ የሆነ ሰው ለሟቹ ወራሽ መሆኑና ከውርሱ ላይ ያገኘውን ድርሻ የሚያመለክት የወራሽነት የምሥክር ወረቀት እንዳጡት ዳኞችን ለመጠየቅ እንደሚችል የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል ይኸ ድንጋጌ ከፍርድ ቤት የወራሽነት የምሥክርነት ወረቀት መያዝ በወራሹ ሲፈልግ የሚጠይቀው እንጅ ሕጉ ሟችን ለመውረስ የግድ ከፍርድ ቤት የወራሽነት ማስረጃ ማውጣት አንዳለበት እንደሚያስገድደው ውርሱን አስመልክቶ ለመወሰን ከተሰየሙ የሽምግልና ዳኞች በውርሱ አጣሪ እና ወራሾች በመካከላቸው በሚያደርጉት ሥምምነት ወራሽነቱ እና ከውርሱ ስለደረሰው ድርሻ ማስረጃ ሊሰጠው አንደሚችል ይታያል ያም ሆነ ስመንብረት ለማዛወር እና ከሌሎች የሟች መብቶች ለመጠቀምና ለመሥራት የፍርድ ቤት የወራሽነት የምሥክር ወረቀት መጠየቁ የተለመደ ስለሆነ የወራሽነት የምሥክር ወረቀት መጠየቅ ይችላልእንደዚኪዚሁም ወራሽ አለመሆኑን በግልፅ የሚያሣይ ማስረጃና መቃወሚያ በቀረበ ጊዜ የተሰጠው የወራሽነት ማስረጃ አንደሚሰረዝና ዳኞች የወራሽነት ማስረጃ በሚሰጡበት ጊዜ አስፈላጊ መስሎ ከታያቸው ማናቸውንም የማረጋገጫ ዋስትና አንዲሰጥ ሊያስገድዱት አንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር እና ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል ከዚህ በመነሳት አንድ ሰው ዋጋ ያለው የወራሽነት ማስረጃ ሳይኖረው ውርሱን ወይም ከውርሱ አንዱን ክፍል በአጁ ያደረገ አንደሆነ እውነተኛው ወራሽ ወራሽነቱ አንዲታወቅለትና የተወሰደው የውርስ ንብረቶች እንዲመለስለት መጠየቅ አንደሚችል የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የሚደነግግ ሲሆን ጥያቄውን ማቅረብ ያለበትን ጊዜ አስመልክቶ ከሣሽ መብቱንና የውርሱ ንብረቶች በተከሣሹ መያዛቸውን ካወቀ ሦሥት ዓመት ካለፈ በላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚያቀርበው ክስ ተቀባይነት ማግኘት አንደማይችል የፍትሐብሔር ሕጋችን ዐዐ ይደነግጋልአዚህ ላይ መታየት ያለበት አንድ ሰው የሟች ኑዛዜ ተጠቃሚ መሆን የሚችል ነዛዜ በእጁ እንደሚገኝ ለውርስ አጣሪው አቅርቦ ውርስ አጣሪወ ኑዛዘውን በሚያነብበት ሰዓት ራሱ ወይም ወኪሉ ካንልነበረ ወራሽ ኑዛዜው ከፈሰሰበት ቀን አንስቶ በአምሥት ዓመት ውስጥ መቃወሚያ ካልቀረበ ከዚያ በኋላ ሊቀርብ እንደማይችል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የተደነገገው ድንጋጌ ከፍትሐበሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ድንጋጌ ጋር እንዴት ነው ተጣጥመው ተግባራዊ የሚሆኑት የሚለው ሲሆን በሌላ በኩል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ እና በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ አተረጓጐምና አፈጻጸም እንዴት መሆን አለበት የሚለው ጥያቄም መነሳት ያለበት ነው ምክንያቱም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ሟች ከሞተበት ወይም ከሣሹ በመብቱ ለመሥራት ከቻለበት ቀን አንስቶ አሥራ አምሥት ዓመት ካለፈ በላ በዘር የወረደ ርስት ካልሆነ በስተቀር የተባለው የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን ተቀባይነት አይኖረውም በማለት የሚደነግግ በመሆኑ ነውይህንን አስመልክቶ በውርስ ሕግ ዙሪያ የተደነገጉ የይርጋ ጊዜ ገደቦች አተረጓጐምና አፈጻጸም በፍርድ ቤቶች የተለያዩ ትርጉሞችና ውሣኔዎች መስጠት ምከንያት እንዲሆኑና እስካሁን ድረስ ችግሩ አንዳልተቃለለ አሁንም ይኸ ነው ትክክለኛው አተረጓጉም እና አፈጻጸም ብሎ ለመናገርም ሆነ ለመጻፍ አስቸጋሪ መሆኑን መገንዘብ ይገባል ሆኖም እስካሁን የሰጡ አንድ አንድ አተረጓጐሞችን በማሳየት ተማሪዎች የበለጠ እንዲከራከሩና እንዲወያዩ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ አንድ አንድ ነጥቦችን ለማንሣት አሞክራለሁ የመጀመሪያው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ተፈጻሚ የሚሆነው የሟችን ውርስ የሚያጣራ በሕግ በሟች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት የተሾመ የውርስ አጣሪ ሟች አድርጐታል የተባለው ኑዛዜ አግኝቶ የነዛዜውን ፎርምና የነዛዘውን ዋጋ መኖር የሟች ያለነዛዜ ወራሾች ወይም አራት አካለመጠን ያደረሱ ሰዎች ባሉበት በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር በተመረመረበት ሁኔታ ነው ሆኖም ኑዛዜ ያለ መሆኑን ለውርስ አጣሪው ሣያሳውቅ ቀጥታ የነዛዜ ወራሽ መሆነ እንዲታወቅለት ለፍርድ ቤት አመልክቶ የወራሽነት የምሥክርነት ወረቀት በመውሰድ የሟችን ንብረት በእጁ ካስገባ ሰው ወይም በሐሰት የሟች ያለኑዛዜ ወራሽ ነኝ ብሎ የሟችን ንብረት ከወሰደ ሰው ለማስመለስ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ሣይሆን በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ የተመለከተው ተፈጻሚነት ሊኖረው ይገባል የሚል ነው ሁለተኛው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ እና ዐዐዐ አስመልክቶ የሚታየው አተረጓጉም ልዩነት ሲሆን በአንድ በኩል የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ የማይነቀሣቀስ የሟችን ንብረት ለማስመለስ ሊቀርብ የሚችለው ክስ በምን ያህል ጊዜ መቅረብ እንደሚገባው የሚወሰን ሲሆን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዝዐዐዐ ግን የማይንቀሣቀስ ንብረትን ለማስመለስ የሚቀርብን ክስ የይርጋ ጊዜ የሚመለከት ነው በማለት በመተርጐም ፍርድ የሰጡ ዳኞች ያሉ ሲሆንበሌላ በኩል የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ከዘር የወረደ ርስት ወይም የማይንቀሣቀስ ንብረት በማስመለስ ከአሥራ አምሥት ዓመት በላም ክስ ለማቅረብ እንደሚፈቀድ ሟች ከሞተበት ወይም ከሣሹ በመብቱ ሊሰራበት ከቻለበት ቀን አንስቶ አሥራ አምሥት ዓመት ካለፈ በላ ከዘር የወረደ እርስት ካልሆነ በቀር የተባለው የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸወም አስተያዬት ቢሆን ተቀባይነት አያገኝም የሚለው ድንጋጌ ያስረዳል ስለዚህ ንብረቱ የሚንቀሣቀስ እና የማይንቀሣቀስ ሲሆን በማለት ለመለየት መሞከሩ የሕጉን ይዘት መንፈስና መልዕክት የሚያንፀባርቅ አይደለም የሚል ትችት ሲሰጡ ይስተዋላሉ በመሆኑም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ምን ጊዜም ተፈጻሚነቱ የሚንቀሣቀሱ ንብረቶችን ለማስመለስ ቢሆንም ንብረቶቹን የያዛቸው ዋጋ ያለው የወራሽነት ማስረጃ ሳይኖረው የውርሱን ንብረት በያዘው ሰው ላይ ክስ የማቅረቢያ ጊዜን የሚወስን ነው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ደግሞ ዋጋ ያለው የወራሽነት ማስረጃ ኖሮት ነገር ግን የውርሱ ኃብት ለአሱ ብቻ የማይገባ በሆነ ጊዜ ሌላኛው ወራሽ ከውርሱ ድርሻውን እንዲያካፍለው ሊጠይቅ የሚችልበት የጊዜ ገደብ ነው ምከንያቱም በወራሾች መካከል የመተማመን ሁኔታ ሊኖር ስለሚችል በሶስት ዓመት ውስጥ ወንድሙ ከአባታቸው ያገኘውን የውርስ ኃብት እንዲያካፍለው ካልጠየቀ ጥያቄውን በይርጋ ለመገደብ አስቦ አይደለም ሕግ አውጭው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ የደነገገውበመሆነም ሕጉ ወራሾች ወራሽ ያልሆነ ባዕድ ሰው የውርሱን ንብረት መያዙን ባወቁ በአጭር ጊዜ ውስጥ መብታቸውን እንዲያስከብሩ የሚገፋፋ ሲሆን የሟች ወራሽ የሆነ ሰው የውርሱን ንብረት ጠቅልሎ በያዘበት ሁኔታ ግን የወራሽነታቸውን መብት ካረጋገጡ ወይም ሟች ከሞተ እስከ አሥራ አምሥት ዓመት ባለው የጊዜ ገደብ ውስጥ ድርሻቸውን እንዲያካፍላቸው መጠየቅ ይኖርባቸዋል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ መተርጐም ያለበት በዚህ መልኩ ነው በማለት ትርጉም የሚሰጡ አሉ ከዘር የወረደ ርስትን አስመልክቶ የፍትሐብሔር ሕጉ በወጣበት ጊዜ የነበረው የመሬት ሥሪት ዘር አየተቆጠረ ከአንዱ ወደ ሌላው እንዲተላለፍ ይፈቀድ የነበረ በመሆኑ ሕግ አውጭው የሟች ርስት ለኔ ይገባኛል የሚለውን ጥያቄ የጊዜ ገደብ ሊያደርግበት አልፈለገም ሆኖም ርስት ማለት ከመሬት ውጭ ሌሎች የማይንቀሣቀሱ ንብረቶችን ለምሣሌ ቤትን ይጨምራል ወይስ አይጨምርም የሚለው ነጥብ በትኩረት መታየት አለበት የሚል አስተያየትና ትችት የሚሰጡ አሉከላይ አንዳነሳነው የውርስ ሕግ የይርጋ ጊዜ ድንጋጌዎች አጅግ በጣም አከራካሪና ውስብስብ ናቸው በመሆኑም የፅርቀት ትምህርት ተማሪዎች እነዚህን እና ሌሎች የይርጋ ጊዜ ድንጋጌዎች ዙሪያ የሚነሱትን ጥያቄዎች በቴቶሪያል ክፍል በሚገናኙበት ጊዜ አንስተው መወያየትና መከራከር ይጠበቅባቸዋል በፍርድ ቤቶች የሚሰጠውን ትርጉም ለመረዳት በፍርድ ቤቶች እየተሰጡ ያለ የተለያዩ አተረጓጐሞችንና ተከራካሪዎች የሚያቀርቧቸውን ሙግቶች ማየት ጠቀሜታ ይኖረዋልበውርስ ጉዳይ የይርጋ ክርክር አስቸጋሪነትና የይርጋ ሕግ ድንጋጌዎችን አተረጓጉም ላይ የሚታየውን ልዩነት ለመረዳት ከዚህ በታች በተሰጠቀሱት ሶስት ጉዳዮች የቀረበውን ክርክርክና የተሰጠውን ትርጉም ዋና ዋና ነጥቦች መመልከቱ አስፈላጊ ነው የመጀመሪያው ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ይግባኝ መዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም በይግባኝ ባዮች በእነ ወሮ እየሩሣሌም ታደሰ ሶስት ሰዎች እና በመልስ ሰጭዎች በሆኑትና የወሮ አሸቴ የሱፍ ወራሾች በሆኑት እነ ወሮ አበባየ ወሚካኤል ስድስት ሰዎች መካከል በሰጠው ውሣኔ ላይ የቀረበውን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ድንጋጌዎች አተረጓጐም ላይ የቀረበውን የመከራከሪያ ሀሣብ ነውየጉዳዩ መነሻ ግምቱ ብር ዐዐዐዐ አስር ሺ ብር የሆነ በቀድሞው አሠራር ጉለሌ አወራጃ እየተባለ ይጠራ በነበረው በቀበሌ ዐ ውስጥ የሚገኘው ቁጥር የሆነው ቤት ነው የዚህ ክርክር መነሻ የሆነው ቤትም የጥንት ባለቤት ወሮ ሰናይት ኃይለየሱስ የተባሉት ሴት ሲሆኑ ወሮ ሰናይት ጥር ቀን ዓም ቤቱን ቦታና መሬቱን ለሚመለከት የጽሑፍ ኑዛዜ አድርገው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋልወሮ ሰናይት የተናዘዙት በወቅቱ በህይወት ለነበሩት ልጃቸው ለወሮ ማርትሬዛያ ወሚካኤል ሲሆን ኑዛዜው ለፍርድ ቤት ከቀረበ በኋላ ተቃውሞ ስለገጠመው በፍርድ ቤት የፀና መሆኑን ከፍተኛው ፍርድ ቤት መጋቢት ቀን የሰጠው ፍርድ ቤት በማስረጃነት ቀርቦ ተያይዚል የወሮ ሰናይት ወራሽ የሆነችው ወሮ ማርትሪዘያ ወሚካኤል መጋቢት ቀን ዓም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን ይግባኝ ባዮች የሟች ወሮ ማርትሪዘዚያ ወራሽ መሆናቸውን ለፍርድ ቤት አቅርበው ያረጋገጡት ከፃያ ሁለት ዓመት በላ ጥቅምት ቀን ዓም ነው ይግባኝ ባዮች መጋቢት ቀን ዓም ለአዲስ አበባ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጽፈው ባቀረቡት ማመልከቻ ከላይ የተጠቀሰውን ቤትና ቦታ እናታቸው ወሮ ማርትሪዘያ ከእናቷ ከወሮ ሰናይት የወረሰችውና በዓም እናታቸው ቢሞቱም እስከ ዓም የአብዮት ለውጥ ድረት በቤትና በቦታው ይኖሩ እንደነበር ገልፀው ከዚያ በኋላ እኛ በማናውቀው መንገድ ወሮ አሸቴ የሱፍ የቤትና የቦታውን የባለቤትነት ስም በስሟ አዛውራና ወሮ እሸቴ የሱፍ በዓም ስትሞት የወሮ እሸቴ የሱፍ ወራሾች የሆኑት ከአንደኛ አስከ አራተኛ ተራ ቁጥር ድረስ ስማቸው ለተጠቀሰው መልስ ሰጭዎች ተላልፎ የወሮ እሸቴ ወራሾች ቤቱንና ቦታውን ለአምስተኛ እና ለስድስተኛ መልስ ሰጭዎች ሸጠውላቸው ስመ ንብረቱ በአምስተኛና በስድስተኛ መልስ ሰጭዎች ስም ተዛውራል በመሆኑም ቤቱና ቦታው ከአያታችን በውርስ የወረደልን ርዕስት ስለሆነ ያለምንም ሕጋዊ መብት ቤቱንና ቦታውን የሸጡት የሟች ወሮ አሸቴ ወራሾችና አምስተኛና ስድስተኛ መልስ ሰጭዎች የውርሱን ንብረት ሊያስረክቡን ይገባል በማለት ይግባኝ ባዮች ክስ አቅርበዋልመልስ ሰጭዎች በበኩላቸው የቤቱ ግምት ብር ዐዐዐዐ አስር ሺ ብር ስለሆነ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ አከራክሮ የመወሰን ስልጣን የለውም ከዚህ በተጨማሪ ክሱ የቀረበው የይግባኝ ባይ አውራሽ ወሮ ማርትሪዚያ ከሞቱ ከፃያ ዓመት በኋላ በመሆኑ ክሱ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ድንጋጌዎች መሠረት በይርጋ ይታገዳል በማለት ክስ አቅርበዋል ይግባኝ ባዮች በበኩላቸው ቤቱ ከእናታቸውና ከአያታቸው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የውርስ ንብረት ስለሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ላይ የተጠቀሰው የሶስት ዓመትም ሆነ የአስራ አምስት ዓመት ይርጋ ሕግ ቀሪ አይሆንም እንደዚህ አይነቱ የውርስ ንብረት በሚመለከት የሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ሊሆን አይችልም በማለት ተከራክረዋል የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፍርድ ቤቱን ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ አከራክሮ ለመወሰን የሚያስችል የሥረ ነገር ስልጣን የለውም በሚለው የመልስ ሰጭዎችየሥር ተከሣሾች መቃወሚያ ላይ ብይን ሣይሰጥ የግራ ቀኙን የጽሑፍ ክርክር ካለቀ በኋላ ተከሣሾች መልስ ሰጭዎች የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ጠቅሰው ያቀረቡትን የመጀመሪያ ደረጃ የይርጋ መቃወሚያ ክርክር መሠረት በማድረግ ከሣሾች ይግባኝ ባዮች በውርስ ከእናታችን ሊተላለፍልን የሚገባ ነው የሚሉት ቤት ጉዳይ አናታቸው ከሞቱበት ዓም ጀምሮ ክሱ እስከቀረበበት መጋቢት ወር ዓም ድረስ ፃያ አምስት ዓመት በላይ ስለሆነው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ላይ በተመለከተው የአስራ አምስት ዓመት ይርጋ ሕግ ቀሪ ይሆናል በማለት የካቲት ዐ ቀን ዐዓም ውሣኔ ሰጥቷል ይግባኝ ባዮች ይህንን የከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠውን የይርጋ ሕግ ድንጋጌ በተለይም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ አተረጓጐም በመቃወም ይግባኝ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ሲያቀርቡ የሕጉ ድንጋጌ ሟች ከሞተበት ወይም ተከሣሹ በመብቱ ለመስራት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት ዓመት ካለፈ በኋላ ከዘር የወረደ ርዕስት ካልሆነ በቀር የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን ተቀባይነት አያገኝም በማለት ይደነግጋል አሁን ክስ ያቀረብንበት ቤት ከአያታችን ጀምሮ በዘር የወረደልን ርዕፅስት በመሆኑ የዚህ አይነት ጥያቄ በይርጋ የጊዜ ገደብ ቀሪ አይሆንም በመሆኑም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የከፍተኛው ፍርድ ቤት የፈፀመውን የሕግ አተረጓጐም ስህተት በማረም ውሣኔውን እንዲሽረው በማለት ያመለከቱ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይግባኙን ያስቀርባል ብሎ መልስ ሰጭዎች ክርክራቸውን እንዲያቀርቡ ካደረገ በኋላ አወዛጋቢ ስለሆነው የይርጋ ክርክር ምንም አይነት የወራሽነት ክርክር ወራሾች በሶስተኛ ወገኖች ላይ ሊያቀርቡ እንደማይችሉና ከአስራ አምስት ዓመት በላ ክስ ቢያቀርቡ ተከሣሾች የይርጋ ጥያቄ ካነሱ ክሱ በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን የሰጠው መደምደሚያ ነው ሁለተኛው ይግባኝ ባይዮች የዚህ አይነት አተረጓጐም ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ድንጋጌ መንፈስ ውጭ መሆኑን በመጥቀስ ንብረቱ ከዘር የወረደ ርዕስት ከሆነ ወራሾች ምንም አይነት የይርጋ የጊዜ ገደብ ሣይኖርባቸው ከሃምሣ ዓመት ከሰማንያ ዓመት ከዚያም በላይ ቆይተው ክስ ማቅረብ የሚከለከሉበት የሕግ ድንጋጌ የለም በማለት ከዘር የወረደ ርዕስትን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ ምንም አይነት የጊዜ ገደብ አልተጣለበትም የሚለውን ጽንፍ የሚያሣየው ይግባኝ ባዮች ለፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ የሰጡት ትርጓሜና ያቀረቡት የመከራከሪያ ሀሣብ ነውበመሆኑም የሚከተሉትን ነጥቦች በትኩረት ማየት ያስፈልጋል ርዕስት የሚለው ቃል የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የካቲት ዓም ባሣተመው የአማርኛ መዝገበ ቃላት የተሰጠው ትርጉም ርዕስት ማለት ቤተዘመድ የሆነ እያረሰ የሚጠቀምበትና ለተወላጅ በውርስ የሚተላለፍ መሬት ማለት እንደሆነ ተገልጺል ይህንን የመዝገበ ቃላት ትርጉም እንዳለ ከወሰድነው ሕጉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ከመሬት ውጭ ሌሎች የማይንቀሣቀሱ ንብረቶችን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ የይርጋ የጊዜ ገደብ አንዳይኖረው ታስቦ የተቀረፀ ነው ወይ ብለን ስንጠይቅ በእንግሊዝኛው ቅጅ ርከኪ የ ከኛ በሚለውና በአማርኛው ርዕስት በሚለው ቃል መካከል ልዩነት እንዳለ እናያለን ይግባኝ ባዮች እንዳቀረቡት በውርስ ከዘር የሚተላለፍ የማይንቀሣቀስ ንብረት አስመልክቶ የሚቀርበው ጥያቄ የጊዜ ገደብ የማይኖረው ከሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለ እጅ ባለይዞታ የሆነ ሰው የዚህኑ ንብረት ግብር ሣያቋርጥ በስሙ ከከፈለ የዚሁ ሀብት ባለቤት ይሆናል በማለት ስለሚደነግግ ይግባኝ ባዮች ያቀረቡት አተረጓጐም እንዴት ከዚህ የሕግ ድንጋጌ ጋር የሚጣጣም ይሆናል የሚለውን ነጥብ መመልከት ያስፈልጋል ሌላው በትኩረት መታየት ያለቡት ነጥብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ ቁጥር ውስጥ በሁለተኛው ሀረግ ላይ በልዩ ሁኔታ የተቀመጠው መሠረተ ሀሣብ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐዐዐ ከዘር የወረደ ርዕስት ካልሆነ በስተቀር የሚለውን ለመረዳትና ለማገናዘብ ብንጠቀምበት መዝገቡን ለመፍታት የሚረዳ አይሆንም ወይ። የሚለውንና የፍታብሔር ሕግ ቁጥር ድንጋጌ የተፈፃሚነት ወሰን በምን መልኩ መታየት አለበት የሚለውን ጭብጥ መርምራል የመጀመሪያውን ነጥብ በተመለከተ በአገራችን የውርስ ሕግ መሠረት የሟች ውርስ ሙሉ በሙሉ በኑዛዜ ሙሉ በሙሉ ያለኑዛዜ ወይም በከፊል በኑዛዜና በከፊል ያለነዛዜ ሊፈፀም የሚች መሆኑ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ተደንግጓል በያዝነው ጉዳይ የአመልካች ልጅ የሆነችው ሟች ይታይሽ አለልኝ በሕግ የሚፀና ኑዛዜ ያልተወች በመሆኑ የሟች አለልኝ ይታይሽ ውርስ የሚፈፀመው የፍትሐብሔር ሕጉ ያለኑዛዜ የሞተ ሰው ውርስ ለማስፈፀም በደነገጋቸው ድንጋጌዎች መሠረት ነው አንድ ሰው በሕግ የሚፀና ኑዛዜ ካልተወ በመጀመሪያ ወራሽነት የሚጠሩት ልጆቹ ናቸው ሟች ይታይሽ አለልኝ ልጅ ወይም ሌሎች ተወላጆች የሏትም ስለሆነም በሁለተኛ ደረጃ በወራሽነት የሚጠሩት እናት አባቷ አንደሆኑ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ይደነግጋል አመልካች የሟች አባት በመሆኑ በወራሽነት የቀረበች ሲሆን የሟች አናት የሟች ውርስ ሲከፈት በሕይወት ያልነበረች በመሆኑ ሟችን የመውረስ መብት የላትም ከዚህ በተጨማሪ የሟች ይታይሽ አለልኝ እናት ከእሷ ሌላ ልጅ ወይም ሌሎች ተወላጆች ቢኖሯት ኖሮ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት የእናቷ ተተኪዎች ከአመልካች ጋር በሟች ይታይሽ አለልኝ ውርስ ተካፋይ ይሆኑ ነበር የሟች ይታይሽ አለልኝ እናት ግን ከእሷ ውጭ ሌላ ልጅም ሆነ ተወላጅ አንደሌላት በግራ ቀኙ መካከል ከተደረገው ክርክር ለመረዳት ይቻላል በመሆኑም ሟች በሁለተኛ ደረጃ በወራሽነት ከተጠሩት አባትና እናቷ መካከል አባቷ በወራሽነት ሲቀርብ አናቷ ወይም እናቷን ተክተው በውርሱ ሊካፈሉ የሚችሉ ወራሾች የሏትም የዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲፈጠር የውርስ ሕጋችን በእናት ወገን ያሉ ሶስተኛ ደረጃ ወራሾች ወይም የእነርሥ ተተኪዎች በወራሽነት እንዲቀርቡ የሚፈቅድ አይደለም ይህንንም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ ከእነዚህ መስመሮች በአንዱ መስመር ያለው ወራሽ ቢታጣ ውርሱ በሙሉ በሌላ መስመር ላለው ወራሽ ይሰጣል በማለት በግልጽ ይደነግጋል ስለሆነም በሁለተኛ ደረጃ ወራሽነት ከተጠሩት የሟች ይታይሽ አለልኝ እናትና አባት መስመር አናቷ ወይም እናቷን ተክተው ሊወርሱ የሚችሉ ተተኪ ወራሾች የሌሉ በመሆነ የሟች ውርስ ሙሉ በሙሉ ለሟች አባት ማለትም ለአመልካቹ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት መሰጠት ይኖርበታል ሁለተኛውን ነጥብ በተመለከተ የእናትን ለእናት ወገን የአባትን ለአባት ወገን የሚለው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ደንብ የተፈፃሚነት ወሰን እና ይህ ደንብ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር እና ከፍትታብሔር ሕግ ቁጥር ድንጋጌዎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት ስንመለከት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ድንጋጌዎች በመጥቀስ ከአናት ወይም ከአባት ወገን የመጣ የማይንቀሣቀስ ንብረት በሙሉ ባለቤትነት ከሌላው ወገን ለመጣ ወራሽ ሊተላለፍልን አይገባም የሚለውን መከራከሪያ ማቅረብ የሚችሉት ማናቸውም የሟች ዘመድ የሆነ ሰው ሣይሆን ሟችን ለመውረስ በሕግ መብት ያለው ሰው ነው ይህንንም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር በአባት መስመር ወገን ወይም በእናት መስመር ወገን ወራሾች ከሌሉ ከዚህ በላይ በተፃፉት በሁለቱ ቁጥሮች ማለትም የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር አና የፍታብሔር ሕግ ቁጥር ዐ ድንጋጌዎች ተፈፃሚነት የላቸውም በማለት ይደነግጋል ስለሆነም በያዝነው ጉዳይ ተጠሪዎች የሟች ይታይሽ አለልኝ የሥጋ ዘመዶች ማለት አክስትና አጎት ናቸው እንጅ የሟች ወራሾች አይደሉም በሟች ውርስ እናቷ በወራሽነት ተጠርታ በሕይወት የሌለች ወይም በተተኪነት የሚወርስ ተወላጆች የሌሏት በመሆኑ ሟች ይታይሽ አለልኝ በሁለተኛ ደረጃ ወራሽነት ቀርቦ በውርስ የሚካፈል ከእናቷ መስመር ወራሽ የላትም ይኸም በመሆኑ አባቷ ማለትም አመልካቹ የሟች ንብረት ወራሽ እንደሚሆን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል ከዚህ በተጨማሪ የእናትን ለእናት ወገን የአባትን ለአባት ወገን የሚለው ደንብ የውርስ ንብረት በሚከፈልበት ጊዜ ተግባራዊ የሚሆን እንጅ በሕግ ወራሽ ያልሆኑ ሰዎች በሟች ውርስ ቀርበው ተካፋይ እንዲሆኑ የሚያደርግ እንዳልሆነ ከላይ የተገለፁትን ድንጋጌዎች ብቻ ሣይሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ዐ ከተደነገጉት የውርስ ንብረት ክፍያና የድልድል ደንቦች ለመረዳት ይቻላል በመሆኑም አመልካች የሟች ይታይሽ አለልኝ ብቸኛ ወራሽ በመሆኑ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ደንብ በዚህ ጉዳይ አግባብነት የሌለው በመሆኑ የአመልካችን የሟችን የውርስ ሀብት የሚንቀሣቀስም ሆነ የማይንቀሣቀስ ንብረት የመካፈል ሕጋዊ መብት አለው በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ሚያዚያ ቀን የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ተሽሯል ግልባጩ ይተላለፍ የሟች ይታይሽ አለልኝ የሚንቀሣቀስና የማይንቀሣቀስ ንብረት በውርስ አጣሪ ተጣርቶ አመልካች ሟችን የመውረስ ያልተገደበና ሙሉ መብት አላቸው ብለናል ይህንን ያስፈጽም ዘንድ ለሚመለከተው ክፍል የፍርዱ ግልባጭ ከመሸኛ ደብዳቤ ጋር ይላክ ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ በተመለከተ በየራሣቸው ይቻሉ ይህ ፍርድ በፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሉት በአዳሪ ተሰርቶ ግንቦት ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ተገኔ ጌታነህ መድሕን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም አመልካች አቶ ጌታቸው ደመቀ ቀረቡ ተጠሪዎች እነ ወሮ ባዩሽ ደብርነህ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረው በሐረሪ ክልል ከፍቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ግንቦት ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ እህቴ ወሮ ቀለሟ ደመቀ ታህሳስ ቀን ዓም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች አባትና እናቷ አስቀድመው የሞቱ በመሆኑና ልጅም ባለመውለድዋ የመውረስ መብት ያለኝ እኔው ነኝ በዚሁ መሰረትም ወራሽነቴን አሳውጃለሁ ሆኖም ተከሳሾች አየተጠቀሙበት የሚገኙትን በሐረር ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥሩ የሆነውን የሟች ቤት እንዲያስረክቡኝ ስጠይቃቸው ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ቤቱን እንዲያስረክቡኝ ቤቱ ሊከራይ የሚችልበትን በወር ሒሳብ ቤቱን ከያዙበት ጀምሮ እአስከሚያስረክቡኝ ጊዜ ድረስ ተሰልቶ እንዲከፍሉን እንዲወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል የአሁኑ ተጠሪዎች የሥር ተከሳሾች ደግሞ ሰኔ ቀን ዓም አዘጋጅተው ባቀረቡት መልስ ክሱ በፍብሕቁ መሰረት በይርጋ ቀሪ ይሆናል የሟች ቤት የቤት ቁጥር እንጂ ባለመሆኑ ከሣሽ በቤቱ ላይ ክስ የመመስረት መብት የላቸውም ሟች ቤቱን ከእናቷ በውርስ ያገኘችው በመሆኑ ለአባት ወገን የሚተላለፍ አይደለም በእናቷ በኩል ያለነው ወራሾች እኛ በመሆናችን ወራሽነታችንን አሳውጀናል በመሆኑም የቀረበው ውድቅ ሊሆን የሚገባው ነው በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ ክሱ በፍብሕቁ መሰረት በይርጋ ቀሪ ሊሆን አይችልም ሲል ብይን ሰጥቷል በመቀጠልም ክርክር ያስነሳው ቤት ዋናው መለያው በሟች ስም መመዝገቡን እንጂ ቁጥሩ ባለመሆኑ የቤት ቁጥሩ በዚሁ ሊስተካከል የሚችል ነው በማለት አልፎታል ወራሽ ሊሆን የሚገባውን ወገን በተመለከተ ደግሞ ክርክር ያስነሳው ቤት የወሮ ማሚቴ ደብርነህ መሆኑን እሳቸው ከሞቱ በላ ደግሞ ወሮ ቀለሟ ደመቀ ብቸኛ ወራሽ በመሆናቸው ይህ በሐረር ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥሩ የሆነውን ቤት የባለቤትነት መብት የተዛወረላቸው መሆኑን ቤቱም የሟች እናት የሆኑት ወሮ ማሚቴ ደብርነህ የሰሩት አንጂ በዘር ሐረግ በትውልድ የመጣላቸው ያለመሆኑን ማስረጃው ያሳያል በእናት ወገን ያሉት ወራሾች በሶስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙው በመሆኑና ከሳሽ ደግሞ በአባት በኩል በኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወራሾች በመሆናቸው ሟችን የመውረስ መብት ያላቸው ከሣሽ ብቻ ናቸው በማለት ተከሳሾች የሟችን ቤት ለከሳሽ ያስረክቡ ኪራዩን በተመለከተም ተከሳሾች ያቀረቡት መቃወሚያ ባለመኖሩ የ ወር ኪራይ በብር ሒሳብ ተሰልቶ ለከሣሽ እንዲከፍሉ ተከሳሾች ቀደም ብሎ ያገኙት የወራሽነት የምስክር ወረቀትም እንዲሰረዝ በማለት ወስኗል የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ደግሞ የአሁኑ ተጠሪዎች ያቀረቡት ይግባኝ ተቀብሉ ግራ ቀኙን ካከራከረ በጊላ ክርክር የተነሳበት ቤት ወሮ ቀለሟ ደመቀ ከእናቷ በውርስ ያገኘችው በመሆኑ የአሁኑ አመልካች ደግሞ የሟች በአባት በኩል ወንድም በመሆናቸውና የአሁኑ ተጠሪዎች ለሟች በእናት በኩል አክስትና የኛ ደረጃ ወራሾች በመሆናቸው የአሁኑ አመልካች በፍብሕቁ መሰረት ሟች በእናታቸው በኩል በውርስ ያገኙትን የማይንቀሳቀስ ንብረት ሊወርሱ አይችሉም በማለት የከፍተኛ ፍቤቱ የሰጠውን ውሳኔ ሽሮታል አመልካች ለዚህ ፌጠፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረቡት አቤቱታም በሐረሪ ክልል ጠፍቤት የተሰጠውን ውሳኔ በመቃመዋ ነው የቅሬታ ነጥቦቹም ሟች እህቴ ቀለሟ ደመቀ ወደ ላይ የሚቆጠር እንደዚሁም ወደታች የሚቆጠር ወራሽ የላትም አንደዚሁም ከአኔው በስተቀር አህት ወይም ወንድም የላትም እኔ አባቴን ተክቼ አህቴን የመውረስ መብት አለኝ የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍቤት እኔ ኛ ደረጃ ወራሽ አያለሁና ቤቱም በዘር ሐረግ ከትውልድ የተላለፈ መሆኑ ሳይረጋገጥ የአባት ላአባት የአናት ለአናት በሚለው ውርስ መሰረት ቤቱ ለተጠሪዎች ሊሰጥ ይገባል አንተ ልትወርስ አይገባም በማለት የከፍተኛ ፍቤትን ውሳኔ መሻሩ አግባብ አይደለም ውሳኔው መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትና ሊታረም የሚገባው በመሆኑ የሐረሪ ጠቅላይ ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ እንዲሻርልኝ የሚል ነው የፌጠፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም አቤቱታውን በመረመረበት ጊዜ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ግራ ቀኙ ለሚከራከሩበት ቤት አግባባነት ያለው መሆን ያለመሆኑን ለማጣራት አቤቱታው ያስቀርባል ሲል ትእዛዝ ሰጥቷል በዚሁ መሰረት ተጠሪዎች ሕዳር ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት መልስ ክርክር ያስነሳው ቤት ሟች ወሮ ቀለሟ ደመቀ ከእናቷ ወሮ ማሚቴ ደብርነህ በውርስ ያገኘችው በመሆኑ ቤቱ በእናት በኩል ከዘር የተላለፈ ነው ሟች ወላጆቿ ስለሌሉ ከላይ የሚቆጠር ወራሽ የላትም የሞተችው ሳትወልድ በመሆኑም ወደታች የሚቆጠር ወራሽ የላትም ሟችን መውረስ የምንችለው የሟች አያቶች የሆኑት ወላጆቻችንን በመተካት አኛው ነን አመልካች በአባት ወገን የመጣ በመሆኑ ከእናት ወገን በዘር የተላለፈውን ቤት የመውረስ ሕጋዊ መብት የለውም በመሆኑም የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍቤት የሰጠው ውሳኔ ተገቢና መሰረታዊ የሕግ ስህተት የሌለበት መሆኑ ውሳኔ ሊፀዐፀናልን ይገባል በማለት ተከራክረዋል በበኩላችን ደግሞ በሕጉ መሰረት ሟች ወሮ ቀለሟ ደመቀን የመውረስ መብት ያላቸው አመልካች ናቸው ወይስ ተጠሪዎች። በሚለው ነጥብ ላይ ጉዳዩ የተወሰነ ነው ይህንንም በሚመለከት የከፍተኛው ፍቤት ምንም አንኳ አመልካችና ሟች አብረው ባልና ሚስት ሆነው አብረው ሲኖሩ አናውቃለን በማለት ያረጋገጡ ቢሆንም ሲጋቡና የጋብቻው ሥርዓት ሲፈፀም ነበርን እናውቃለን በማለት ያላስረዱ ስለሆነ በፍብሕቁ እንደሚደነግገው ሚስትነቷን በጋብቻ ሁኔታ አስረድተዋል ማለት አይቻልም በማለት የሰጠው ድምዳሜ ይህንን ለጉዳዩ አግባብነት ያለውን ድንጋጌ በመተርጎም ረገድ መሠረታዊ የሕግ ስህተት መፈፀሙን ተገንዝበናል የፍብሕቁ የጋብቻ ጽሑፍ በሌላ ጊዜ ጋብቻ መኖሩን ለማስረዳት የሚቻለው የባልና ሚስትነት ሁኔታ መኖሩን በማስረዳት ነው ሲል ከደነገገ በኋላ ሁለት ሰዎች የባልና ሚስትነት ሁኔታ አላቸው የሚባለው ባልና ሚስት ነን እየተባባሉ አብረው የሚኖሩ እንደሆነና ቤተዘመዶቻቸውና ሌሎችም ሰዎች በዚሁ ሁፄታ መኖራቸውን ሲያረጋግጡላቸው ነው በማለት ለይቶ አስቀምጧል በመሠረቱ ይኸው ድንጋጌ ግልጽ ነው ሕግ ግልጽ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ደግሞ የሕግ ትርጉም ሥራ እንደሚያስፈልግ የሕግ አተረጓጎም ዘዴ ያስገነዝባል በግልጽ በሕግ በተመለከተው አኳቷን አመልካች በማስረጃ ያረጋገጠች ለመሆኑ እራሱ ይግባኝ ሰሚው ፍቤት የተቀበለው ጉዳይ ነው ነገር ግን ወደ ትርጉም ሥራ እንዲገባ ምክንያት የሆነው በዚህ ድንጋጌ ቁጥር የተመለከተው በተለያዩ ሁኔታ ካልታየ በቀር በፍብሕቁ ከተመለከተው ከጋብቻ ውጭ በግብረ ሥጋ ግንኙነት መኖር ከሚለው በምን ሊለይ ይችላል የሚለውን በመያዝ ነው ይሁን እንጂ በፍሥሥሕቁ አለ የተባለው ግነኙነት የሚመለከት ሁኔታ ሳይሆን በፍብሕቁ ዐ የተጠቀሰውን የሚመለከት ነው የሚባል ከሆነ ይህንን የማሳየት አና የመከላከል ተግባር የሚለየው ተከራካሪ ወገን ተግባርና ግዴታ ነው በዚሁም ነው በፍብሕቁ ዐዐ የባልና ሚስትነት ሁኔታ አለመኖሩንን ለመከራከር የሚቻለው የተከራካሪዎች ዘመዶች የሆኑ ወይም ያልሆኑ አራት የመከላከያ ምስክሮችን በማስመስከር ነው የሚለው መደንገግ ያስፈለገው ስለሆነም አመልካች የአሁን በፍብሕቁ ለሚደነግገው ሁኔታ የሟች የመአለቃ መኮንን ለማ ሚስት ለመሆኗ በበቂ ሁኔታ ማረጋገጧ እየታወቀ ከላይ እንደተገለፀው አግባብነት ያለውን ድንጋጌ በትክክል ካለመረዳት የተነሣ የሟች ሚስት መሆኗን አላረጋገጠችም ማስረጃው አግባብነት እንደሌለው ተደርጎ ሚስት አይደለችም በማለት የተሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት መፈፀሙን ተገንዝበናል ውሣኔ አመልካች ወሮ አስረስ መስፍን የሟች መአለቃ መኮንን ለማ ሚስት ናቸው አንዲሁም ይኸው ፍርድ በውጤት ደረጃ መልስ ሰጭም የሟች ሚስት መሆናቸውን አረጋጋጭ ነው ብለናል የአማብሕክል መንግሥት ጠቅላይ ፍቤት በፍብይመቁ ዐ በዐዐ እንዲሁም የከፍተኛው ፍቤት በቁጥር ዐዐ በዐዐ የሰጠውን ውሣኔ በፍብሥሥሃቁ መሠረት ተሻሽሏል ይፃባዛ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ኀዳር ዐዐዐ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ መስፍን እቁበዮናስ አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አመልካች ወት አይናለም አበበ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ደገፋ ጉርሙ ጠበቃ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው አመልካች ሰኔ ቀን ዓም የተፃፈ ማመልከቻ በማቅረቧ መነሻነት ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተጀመረ ክርክር ሲሆን ፍሬ ነገሩም ያሁኑ ተጠሪ የሥር ከሣሽ በመሆን በሥር ኛ በመቃወም ተጠሪ ወሮ ደስታ ይመር በዚህ መዝገብ የሌሉበት እና ባሁኗ አመልካች የሥር ኛ በመቃወም ተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ሟች ወንድማቸው አቶ አበበ ጉርሙ ልጅ አለመውለዱ እየታቀ አመልካች የሟች ልጅ ናት ተብሉ ወራሽነቱ የተረጋገጠው ባግባቡ ስላልሆነ ውሣኔው ይሻር የሚል ነው ለክሱም ኛ የመቃወም ተጠሪ በርግጥ አመልካች ከኔም ሆነ ከሟች አትወለድም ልጄ ነች ብዬ ውሣኔ ያሰጠሁት ከሕፃንነቷ ጀምሮ ስላሳደኳትና እንደ ልጅ ስለምቆጥራት ነው ሲሉ አመልካችም በበኩሏ ተጠሪ ሕፃን ሆቼፄ ውሣኔ ሲሰጥ ቀርበው መቃወም ሲችሉ ከ ዓመት በኋላ መቅረባቸው በፍብሕቁ ዐዐዐ መሠረት ተቀባይነት የለውም በማለት በየበኩላቸው መልስ ሰጥተዋል ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከሰማ በላ የፍብሕቁ ዐዐዐ የሚሠራው የፈረሰ ንብረት ይገባኛል ለሚል ክርክር እንጂ ወራሽ ናት አይደለችም ለሜል ክርክር አይደለም በሚል የይርጋ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎ አመልካች ከሟች የማትወለው በመሆኑ ስለ ኑዛዜ ወራሽ ልትሆን አትችልም በማለት ወስኗል ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለት የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤትም በበኩሉ የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ሟችና ኛ የመቃወም ተጠሪ ከቤተሰብ ሕግ አንቀጽ ሠሥ መሠረት አመልካችን ወደ ቤት በመውሰድ በማንከባከብና በማስተማር አንደ አባት በመሆን የተሣተፉ በመሆኑ አመልካች የሟች ልጅና የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ ነች በማለት ወስኗል ያሁኑ ተጠሪ በዚህ ውሣኔ ቅር ተሰኝተው ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርበው ፍርድ ቤቱም የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሣኔ ሽሮ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትን ውሣኔ አጽንቷል አመልካች ይህን የሰበር አቤቱታ ያቀረቡት በዚህ መነሻነት ሲሆን ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን መርምሮ ተጠሪን በማስቀረብ ግራ ቀኙን አከራክሯል ክርክሩንም ከሕጉ ጋር በማገናዘብ መርምራሯል በዚህም መሠረት አመልካች ኀዳር ቀን ዓም የወራሽነት ማስረጃ ካገኙ በኋላ የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ መሆናቸውን በመግለጽ በቤቱ ላይ ያገኙት የጋራ ባለሀብትነት ከሥር ኛ የመቃወም ተጠሪ ጋር ተቀባይነት ያጣው ባግባቡ መሆን አለመሆኑን ፍርድ ቤቱ እንደሚከተለው ተመልክቷል አመልካች በሥር ፍርድ ቤቶች ያቀረቡት ክርክር ባንድ በኩል የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ መሆናቸውን በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ ከዐ ዓመት በላይ ቆይተው በቤቱ ላይ አለኝ የሚሉት የወራሽነት መብት በፍብሕቁ ዐዐዐ መሠረት የሚታገድ ነው የሚል ሲሆን የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የጠቀሱት የፍብሕቁ ዐዐዐ የሚሠራው የውርስ ንብረት ይገባኛል ይሰጠኝ ለሜል ክርክር እንጂ ወራሽ ናት አይደለምችም ለሜል ክርክር ተፈፃሚነት ያለው አይደለም በማለት የሰጠውን ውሣኔ እንደተመለከትነው ድንጋጌው ባግባቡ አለመፈጸሙን ተረድተናል ያሁኑ ተጠሪ በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ በራሱም ሲታይ ይዘቱ ወንድሜ ልጅ አለመውለዱ እየታወቀ አመልካች በሐሰት ልጅ ነኝ ብላ የወራሽነት ማስረጃ የወሰደች ስለሆነ ትመልስ በቤቱ ላይ ያለው የሟች ድርሻ ለኔ ይሰጠኝ የሚል ሲሆን አመልካችም በበኩሏ የሟች ልጅ መሆኗን እና ንብረቱም እንደሚገባት መከራከራቸው ታይቷል ክርክሩ ትክክለኛ ገጽ ይህ ሁኖ እያለ የሥር ፍርድ ቤት አመልካች ክሱን ያመነኑ ይመስል ገና ከጅምሩ ድንጋጌውን አጥብቦ በመተርጎም በልጅነት ጥያቄ ቢነሣ ድንጋጌው ተፈፃሚነት የለውም ማለቱ ቀጣይ ሆኖ አልተገኘም ይህ ድንጋጌ መገኛው አንቀጽ ሆኖ እውነተኛ ወራሽ እፄ ነኝ ከሚል ጥያቄ ጀምሮ የውርስ ንብረት ያላግባብ ተወስዲልና ይመለስልኝ በማለት የሚቀርቡትን ክሶች ጥያቄዎች የሚያካትት ለመሆኑ አንቀጽ መመልከቱ ይበቃል በዚህ ረገድ አመልካች ክርክሩን ባስነሳው ቤት ላይ ከዐ ዓመት በላይ የቁቀየ የባለሀብትነት ድርሻ ማግኘታቸው አየተመለከተም ተጠሪም ድርሻቸውን ለመጠየቅ ከሚያስችላቸው ጊዜ በላይ ቆይተው ክስ ለማቅረባቸው አመልካች ያቀረቡት የይርጋ ክርክር ተቀባይነት ያጣው ድንጋጌውን በጠባቡ በሥር ፍርድ ቤት በሚተረጎመሙ ሳቢያ መሆኑን ይህ ፍቤት ተገንዝቧል በመሆኑም የመጨረሻ ውሣኔ የሰጠው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይርጋውን ነጥብ አልፎ ውሣኔ መስጠቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል የከፍተኛው ፍርድ ቤት ምንም እንኳ የአመልካችን ልጅነት ተቀብሎ የሥር ፍቤት ውሣኔ የሻረ ቢሆንም ፍቤቱ በቅድሚያ በይርጋው ጥያቄ በቅድሚያ ለይርጋው ጥያቄ በቅድሚያ ምላሽ ቢሰጥ ኖሮ ወደዚህ ነጥብ መግባት ያስፈለገው እንዳልነበር ተገንዝበናል ስለሆነም ክሱ በይርጋ ታግዲል ብለናል ውሣኔ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ዐ ጥር ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ የከፍተኛ ፍርድ ቤት መቁ በመጣበት አኳን በመሸኛ ተመልሶ ይላክ መዝገቡ ተዘግቷል ክሱ በይርጋ ይታገዳል ተብሏል መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ርዘርዩ ዘፀየፎ ሀፀ ዩ ። ፍ ውሣኔ የመጀመሪያው ደረጃ ፍቤት በመቁ ዐዐ በ የሰጠው ብይን እና ይህም ብይን ጉድለት አልተገኘበትም በማለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ በ የሰጠው ትእዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽሯል ይህ ክርክር ስለተወሰ ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሣቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ጎዳር ዐዐዐ ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ ሐጎስ ወልዱ ወት ሒሩት መለሠ አቶ ታፈሰ ይርጋ አመልካች እነ ወሮ ዋጋዬ ገብሬ ጠበቃ አዝመራ ነጋሽ ተጠሪ አቶ ደመላሽ ታምሩ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው ለተጠሪ የተሰጠው የወራሽነት ማስረጃ በአግባቡ ስላልሆነ ውሣኔው ይሰረዝልን በማለት አመልካቾች ለአዲስ አበባ ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ያቀረቡት አቤቱታ በየደረጃው ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት ቅሬታ በማቅረባቸው ነው የጉዳዩ ይዘትም ባጭሩ ሲታይ ተጠሪ ሟች እናቴ ወሮ እታገኝ ገብሬ ስለሞቱ ወራሽነቴ ተረጋግጦ ማስረጃ ይሰጠኝ በማለት ለአዲስ አበባ ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደፍቤት አቤቱታ አቅርቦ ፍቤቱም የአመልካችን ምስክሮች ሰምቶ የሟች ወሮ እታገኝ ገብሬ ወራሽ ነው በማለት ውሣኔ ከሰጠ በላ የአሁን አመልካቾች ሟች ወር እታገኝ ገብሬ እህታቸው እንደሆኑና ልጅም ያልወለዱ መካን የነበሩ መሆናቸውን ገልጸው ተጠሪ የሟች እህታችን ወራሽ ነው ተብሎ ማስረጃ እንዲያገኝ የተሰጠው ውሣኔ መብታችንን የነካ ስለሆነ ይፄው ውሣኔ ሊሰረዝልን ይገባል በማለት ውሣኔውን ለሰጠው ፍቤት በፍብሕሥሥቁ መሠረት መቃወሚያ አቅርበዋል ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ ተጠሪ ቀደም ሲል የሟች ወራሽነቱን ባረጋገጠ ጊዜ የተሰሙትን ምስክሮች በድጋሚ አስቀርቦ የምስክርነት ቃላቸውን ከሰማ በኋላ አመልካች የአሁን ተጠሪ ሟች ወሮ እታገኝ ገብሬ የወለዱት ልጅ ወይንም የጉዲፈቻ ልጅ ስለመሆኑ በምስክሮች ስላልተገለጸ ልጅ ነው አይደለም የሚለው ጭብጥ የፍቤቱ ሥልጣን ሰላልሆነ አመልካቾች በቅድሚያ በዚህ ነጥብ ላይ በፌዴራል መደፍቤት አቤቱታ አቅርበው አረጋግጠው ሲመጡ ወራሽነትን አስመልክቶ የቀረበው አቤቱታ የሚታይ ነው በማለት ሳይቀበለው ቀርቷል ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የከተማው አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍቤት ይግባኙን ያልተቀበለው ሲሆን ሰበር ሰሚ ችሎቱም መሠረታዊ የሕግ ስህተት አልተፈጸመም በማለት አቤቱታውን ሳይቀበለው ቀርቷል ይህ የሰበር ችሎትም የቀረበው አቤቱታ መርምሮ አመልካቾች የተጠሪ ወራሽነት የተረጋገጠበትን ውሣኔ በመቃወም ባቀረቡት አቤቱታ ላይ የአአ ከተማ ነክ ፍቤት የሰጠውና በይግባኝ የጸናው ትዕዛዝ ከፍብሕሥሥቁ አኳያ ለሰበር ቀርቦ የሚጣራ ሆኖ በማግኘቱ ግራ ቀኙን አከራክራል በአጠቃላይ የክርክሩ ነጥብ ከላይ አንደተመለከተው ሲሆን የሰበር አቤቱታውም እንደሚከተለው ተመርምራል ተጠሪ የሟች ወሮ እታገኝ ገብሬ ልጅ ስለሆንኩ የወራሽነት ማስረጃ ይሰጠኝ በማለት ለከተማ ነክ የመደፍቤት ባመለከተው መሠረት ፍቤቱ ለተጠሪ የወራሽነት ማስረጃ ሠጥቷል ከዚህ በኋላም የአሁን አመልካቾች ተጠሪ የሟች እህታችን እታገኝ ገብሬ ልጅ አይደለም ሟችም ልጅ ያልወለደችና መሃፃን ስለነበረች ፍቤቱ ተጠሪ የሟች ወራሽ ነው በማለት ማስረጃ እንዲሰጠው የሰጠው ውሣኔ መብታችንን የነካ ስለሆነ ይሄው ውሣኔ ሊሰረዝ ይገባል በማለት በፍብሕሥቁ መሠረት መቃወሚያ አቅርቧል በአንድ ክርክር ውስጥ ተካፋይ መሆን የሚገባው ወይም በክርክሩ ውስጥ ለመግባት የሚችልና እንደዚሁም ተካፋይ ባልሆነበት ክርክር የተሰጠው ፍርድ መብቱን የሚነካበት ማናቸውም ሰው መቃወሚያ ማቅረብ እንደሚችል በተጠቀሰው የፍብሕሥሥቁ ላይ ተመልክቷል የዚህ ዓይነት አቤቱታ ለፍቤት በቀረበ ጊዜም ፍቤቱ ሊይዘው የሚገባ የክርክር ጭብጥ አስቀድሞ የተሰጠው ውሣኔ ሊሰረዝ ይገባል ወይንስ አይገባም የሚለውን ነው በዚህም መሠረት የአአበባ ከተማ ነክ የመደፍቤት ይህንኑ ጭብጥ ይዞ በአንድ በኩል ተጠሪ የሟች ልጅ ስለመሆኑ ያቀረበው ማስረጃ በሌላም በኩል አመልካቾች ተጠሪ የሟች ልጅ ስላለመሆኑ በበኩላቸው ያቀረቡትን ማስረጃ መዝኖ በጭብጥ በተያዘው ላይ ዕልባት መስጠት ሲገባው በልጅነት ጉዳይ ላይ ውሣኔ መስጠት ከፍቤቱ የሥረነገር ሥልጣን ውጪ ስለሆነ አመልካቾች በቅድሚያ በልጅነት ክርክሩ ላይ ሥልጣን ባለው የፌመደፍቤት አስወስነው መቅረብ አለባቸው በማለት ለጉዳዩ አልባት ሳይሰጥ መቅረቱ እንደዚሁም ይግባኝ ሰሚው ፍቤትና ሰበር ችሎቱ ይህንኑ ጉልህ የሆነ የሥነ ሥርዓት ግድፈት ሳያርሙ መቅረታቸው በአግባቡ ሆኖ አልተገኘም ውሣኔ የአአበባ ከተማ ነክ የመደፍቤት በመቁ በዐ የሰጠው ትዕዛዝ የከተማ ነክ ይግባኝ ሰሚ ፍቤት በመቁ ዐ በዐ የሰጠው ውሣኔና ሰበር ችሉቱ በመቁ ዐዐ በ የሰጠው ትፅዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለተገኘ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል አመልካቾች ያቀረቡት መቃወሚያ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ተመርምሮ ውሣኔ ሊሰጥበት የሚገባ ስለሆነ የአአ ከተማ ነክ የመደፍቤት በዚሁ መሠረት መርምሮ አንዲወስን ተመልሶለታል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ የሰመቁጥር ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ መስፍን እቁበዮስ አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አመልካች ወሮ ዕቁባይ በላይ መልስ ሰጪዎች ህፃን ናሆም ገሕይወት መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ውሣኔ ተሰጥቷል ውሣኔ ለዚህ ችሎት ኅዳር ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ የቀረበው የሰበር አቤቱታ ለመልስ ሰጭ ደርሶ ሰኔ ቀን ዓም የተፃፈ የመልስ ማመልከቻ ቀርቧል የግራ ቀኙን ክርክር አቤቱታው ከቀረበበት ውሣኔ መደምደሚያና ለዚህም መሠረት ከሆነው የሕግ ትንታኔ አንፃር ተመርምሮ ውሣኔው ጉድለት ያለበት ሆኖ ስላልተገኘ በትግራይ ብክመጠፍቤት በመዝገብ ቁጥር በመስከረም ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ መሠረት ፀንቷል ይፃፍ ግራ ቀኙ ኪሣራቸውን ለየራሣቸው ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ዐ ኀዳር ዐዐዐ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አቶ አብዱራሂም አህመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ወሮ የኔነሽ ከበደ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ዮሐንስ ከበደ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው አመልካች ጥር ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት ማመልከቻ መነሻነት ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ የአሁኑ አመልካች የሥር ተከሣሽ በሆነበት መዝገብ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ የሟች አባታቸው የደጅአዝማች ከበደ ወዮሐንስ የሆነውን ቁጥሩ ቤት አመልካች የያዙ መሆኑን ገልፀው የአመልካችን ድርሻ ኛ አስይዘው ቤቱን እንዲረከቡ ይህ ካልሆነም ቤቱ በሐራጅ ተሸጦ እንዲከፋፈሉ የሚል ሲሆን አመልካችም በበኩላቸው ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው ጉዳዩ ቀደም ሲል የመጨረሻ ውሣኔ ያገኘ ጉዳይ ነው ተጠሪ ቤቱ የሟች ለመሆኑ ማስረጃ አላቀረቡም በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩን ያስተናገደው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም ያቀረበው የይርጋ ተቃውሞ በወራሽና ያለ ማስረጃ ንብረት በያዘ ወራሽ ባልሆነ ሰው ላይ ተፈፃሚነት ከሚኖረው በስተቀር ለዚህ ጉዳይ አግባብነት የለውም የፍብሕቁ ደግሞ በውል ላይ ለተመሠረተ ግንኙነት የሚጠቀስ እንጂ በወራሾች መካከል የሚጠቀስ በመሆነ በክርክሩ አግባብነት የለውም ጉዳዩ ቀደም ብሎ የመጨረሻ ውሣኔ አግኝቷል የተባለውን ሌሎች ወራሽ ያልሆኑ ተከሣሾች ቤቱን እንዲያስረክቡ የተወሰነ ከመሆኑ ውጭ በተመሣሣይ ጭብጥ ላይ የተሰጠ ውሣኔ አይደለም በማለት ያቀረቡትን ተቃውሞዎች ውድቅ ካደረገ በኋላ ቤቱ የአውራሻቸው ለመሆኑ ካርታው በማስረጃዎች መቅረቡን ገልፆ ክስ የቀረበበትን ቤት ግራ ቀኙ ከተስማሙ አንዳቸው ለአንዳቸው ከፍለው ቤቱን እንዲያስቀሩ ይህ ካልተቻለ ቤቱ በሐራጅ ተሸጦ የየድርሻቸውን እንዲወስኑ በማለት ወስኗል ውሣኔው በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በይግባኝ ፀንቷል አመልካች ይህን የሰበር አቤቱታ ያቀረቡት በዚህ መነሻነት ሲሆን አቤቱታው ከተመረመረ በላ ተጠሪን በማስቀረብ ግራ ቀኙ እንዲከራከሩ ተደርጓ ክርክርራቸውም ከሕግ ጋር ተገናዝቦ ተመርምሯል በዚህም መሠረት የሥር ፍቤቶች በፍብሕቁ ዐዐዐ ላይ የተመለከተው የይርጋ መቃወሚያ ለጉዳዩ አግባብነት የለውም በማለቱ ውድቅ ማድረጋቸው ባግባቡ መሆን አለመሆኑን ተመልክተናል የፍብሕቁ ዐዐዐ ለጉዳዩ አግባብነት የለውም በሚል በሥር ፍርድ ቤት የተሰጠው ምክንያት ድንጋጌው በወራሽ እአና ወራሽ ሣይሆን ማስረጃ ሣይኖረው ንብረት በያዘ ሰው ላይ ለሚቀርብ ክስ የሚነሣ እንጂ አሁን በወራሾች መካከል ለተነሣው ክርክር ተጠቃሽ አይሆንም የሚል ነው ሆኖም ይህ የሰበር ሰሚ ችሎት በአመልካች በወሮ ድንቄ ተድላና በተጠሪዎች እነ አቶ አባተ ጫኔ መካከል በነበረው የውርስ ክርክር በፍብሕቁ ዐዐዐ እና ላይ የሰፈረው የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ የሚሆነው አንድ ወራሽ በሌላ በወራሽነት የውርስ ሀብት በያዘ ሰው ላይ ክስ ሲያቀረብ ነው በማለት የሰጠውን ውሣኔ ያልተከተለ በመሆኑ የሥር ፍቤት ለድንጋጌው የሰጠው ትርጉም መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ተገኝቷል ከዚህ አንፃር አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት የይርጋ ክርክር ተቀባይነት ሊኖረው ይገባ ነበር ከተባለ ባጠቃላይ ክርክሩ ላይ ለውጥ ያመጣ ወይም አያመጣ እንደሆነ መመልከቱ አስፈላጊ ነው ተጠሪ በንብረት ጥያቄው ላይ ክስ ያቀረበው ዐ ዓመት ካለፈው በኋላ ነው በማለት የይርጋ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል ሆኖም ክስ በቀረበለት ቤት ላይ ቀደም ሲል በሌላ መዝገብ ክስ አቅርበው ጉዳዩ እስከ ሰበር ደርሶ ከተወሰነላቸው በላ የአፈፃፀም መዝገብ ከፍተው ታህሣሥ ቀን ዓም ቤቱ እንዲረከቡ የአፈፃፀም ትዕዛዝ የተሰጠላቸው መሆኑን በሰበር ማመልከቻቸው ላይ ገልፀዋል በሌላም በኩል ያሁኑ ተጠሪ የስር ከሣሽ በመሆን በመልካች ላይ ቤቱን በተመለተ ክስ ያቀረቡት ግንቦት ቀን ዓም መሆኑ ከሥር ፍርድ ቤት መዝገብ ተረጋግጧል ከዚህ አኳያ አመልካች ክስ የቀረበበትን ቤት በፍርድ ቤት ውሣኔ በይዞታቸው ሥር በማድረግ የተረከቡት ታህሣሥ ቀን ዓም ነው ቢባል እንኳ ተጠሪ በበኩላቸው ክስ ያቀረቡባቸው አንድ ዓመት ተኩል በማይሞላ ጊዜ ውሰጥ መሆኑ ታይቷል በፍብሕቁ ዐዐዐ እና ላይ የተመለከቱት የይርጋ ጊዜዎች በ እና ዓመት የተካፄዱ በመሆናቸው አመልካች ያቀረቡት የይርጋ ጥያቄ ሁለቱንም ያላሟላ ነው ስለዚህ የይርጋ ተጠቃሚ የሚሆነበት ምክንያት አልተገኘም ውሣኔ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የከፍተኛው ፍቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔ በተለየ ምክንያት ፀንቷል ይፃፍ ግራ ቀኙ ወጪያቸውን ይቻቻሉ በትፅዛዝ የመጣው የፌዴራል የመጀመሪያ ደርጃ ፍርድ ቤት መቁ የተፈለገበት ምክንያት ስላለቀ ወደመጣበት በሸፒ ደብዳቤ ተመልሶ ይላክ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ዐ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ አብዱልቃድር መሐመድ አብዱራሂም አህመድ ታፈሰ ይርጋ አመልካች እነ ሣሙኤል ውብሸት ቀረቡ ተጠሪ ብዙነህ በላይነህ አልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀረብ የቻለው አመልካቾች ተጠሪ በይዞታችን ላይ የፈጠረው ሁከት ይወገድልን የሚል አቤቱታ ለጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ ተጠሪ በአመልካቾች ላይ የፈጠረው ሁከት ሊወገድ ይገባል በማለት ውሣኔ ሰጥቶ ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት የክፍተኛ ፍቤቱን ውሣኔ በመሻር ሁከት የለም በማለት ውሣኔ በመስጠቱ አመልካቾች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት ቅሬታ በማቅረባቸው ነው ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀረብ በተሰጠው ትአዛዝ ተጠሪ የአመልካቾች አቤቱታ ደርሷቸው መልስ የሰጡ ሲሆን አመልካቾችም የመመልስ በመስጠት አቤቱታቸውን አጠናክረው ተከራክረዋል የጉዳዩ አመጣጥም ባጭሩ ሲታይ አመልካቾች በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረቡት ክስ በጅጅጋ ከተማ ቀበሌ ዐ የሚገኝና የምንኖርበት ቤት በአዋጅ ቁጥር ተወርሶ ቀበሌው የሚያስተዳድረውና ላለፉት ዐ ዓመታት በተከራይነት ኖረንበታል የሁን አንጂ ተከሣሽ ይፄው ቤት የአውራሼ የሟች ወሮ ተዋበች ዘርፉ ነው በማለት አኛ በሌለንበት ይህንኑ ከቀበሌው አስተዳደር በኪራይ የያዝነውን ቤት እየተገለገለበት ሰለሆነ የተፈጠረው ሁከት ይወገድልን በማለት ጠይቀዋል ተጠሪም በበኩሉ በሰጠው መልስ ለክሱ መነሻ ምክንያት የሆነው ቤት ከአክስቱ በውረስ የተላለፈለት ንብረት መሆኑን በመግለጽ አቤቱታው ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክራል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት ለክርክሩ ምክንያት የሆኑት ቤቶች የጅጅጋ ከተማ አስተዳደር መሆናቸውን ከሣሾችም በእነዚሁ ቤቶች በሕጋዊ መንገድ እየኖሩ እንደሆነ ከቀረበው ማስረጃ ማረጋገጥ የተቻለ ስለሆነ በተከሣሽ በኩል የተፈጠረው ሁከት በፍብሕቁጥር መሠረት እንዲወገድ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል ክርክሩን በይግባኝ የተመለከተውም የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ ለክርክሩ ምክንያት የሆኑት ቤቶች በአዋጅ ያልተወረሱ ስለመሆናቸው የሚመለከተው የቀበሌ አስተዳደር ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ይግባኝ ባይ ተጠሪ የቤቱ ባለንብረት የነበሩት ግለሰብ ወራሽ መሆናቸው ባቀረቡት ማስረጃ ስለተረጋገጠ የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት በተጠሪ በኩል የተፈጠረው ሁከት ሊወገድ ይገባል በማለት የሰጠው ውሣኔ ከጭብጡ ያፈነገጠ ነው በማለት ሽራል ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም አቤቱታው ለሰበር ቀረቦ መታየት አለበት በማለት ትአዛዝ የሰጠው ለክርከሩ ምክንያት የሆነውን ቤት የቀበሌው አስተዳደር እያከራየ ገቢ ይሰበስብ ነበር ከተባለ በአዋጅ አልተወረሰም በሚል የተጠሪ የውረስ ሀብት ነው መባሉ አግባብነቱን ለማጣራት ሲሆን ከዚሁ አኳያም አቤቱታው አንደሚከተለው ተመርምራሯል አመልካቾች በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በተጠሪ ላይ ክስ የመሠረቱት ከጅጅጋ ከተማ ቀበሌ አስተዳደር በተከራይነት የምንኖርበትን ቤት ተጠሪ ወራሽ ነኝ በማለት ያለአግባብ ይዘው የሚገኙ ስለሆነ የተፈጠረው ሁከት ይወገድልን በማለት ነው ሁከት ይወገድልኝ የሚል አቤቱታ የሚያቀረብ ወገን በንብረቱ ላይ የይዞታ መብት እንዳለውና በአርግጥም የሚያዝበት ስለመሆኑ ማረጋገጥ እንደሚገባው ከፍብሕቁዐ ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል በተያዘው ጉዳይ አመልካቾች ሁከት ተፈጥሮብናል በሚሉት ቤት ላይ በኪራይ ውል መነሻነት ቤቱን ይዘው እንደሚገኙና የይዞታ መብት እንዳላቸው በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ክርክር ሲደረግ በማስረጃ አረጋግጠዋል የአመልካቾች አቤቱታ ሁከት ይወገድልን የሚል ከሆነ ክርክሩ የይዞታ መብትን ሀ ቪበ የሚመለከት በመሆኑ በጭብጥ ተይዞ ዕልባት ሊሰጠው የሚገባው ነጥብ ሁከት ተፈጥሯል ወይስ አልተፈጠረም የሚለው ነው ይሁንና ተጠሪ በዞኑ ከፍተኛ ፍቤት ያቀረቡት ክርክር ለክሱ ምክንያት የሆነው ቤት በውርስ የተላለፈልኝ የግል ቤቴ ሰለሆነ የአመልካቾች አቤቱታ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት እንጂ ሁከት አልፈጠርኩም በማለት አይደለም ተጠሪ በባለቤትነት ረገድ የሚያነሱት ክርክር ሁከት ተፈጥራል ወይስ አልተፈጠረም ተብሎ ለሚያዘው ጭብጥ ተገቢነት የሌውና አራሱን የቻለ ባለቤትነትና የመፋለም ክስ ዐቨቫሃ ቪከበ በሚመለከተው ላይ አቅርበው ከሚታይ በስተቀር ሁከት እንዲወገድ በቀረበ ክስ የባለቤትነት ክርክር ማንሣት አግባብነት አየኖረውም ስለሆነም የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በተጠሪ በኩል ባለቤትነትን የመፋለም ክስ ባልቀረበበትና አመልካቾች ሁከት ይወገድልን በማለት ባቀረቡት ክስ ተጠሪ የቤቱ ባለቤት ናቸው በማለት ውሣኔ መስጠቱ መሠረታዊ የሕግ ሰህተት ያለበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ በ ተጠሪ በአመልካቾች ላይ የፈፀመው ሁከት ይወገድ በማለት የሰጠው ውሣኔ በማጽናት የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ዐ በዮ ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለበት በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽራል ይፃፍ ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማየነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ አሰግድ ጋሻው አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ወሮ እናትነሽ ከተማ ጠበቃ አቶ መኮንን አምቦ ቀረቡ መልስ ሰጭ ወሮ ፋንታዬ መሐመድ አልቀረቡም መዝገቡን መርምረን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የአማብሔክልላዊ መንግሥት ጠፍቤት በይግባኝ ሥልጣኑ ተመልክቶ በሰጠው ውሣኔነ ላይ ነው የነገሩም መነሻ የአሁን መልስ ሰጭ ሚስትነታቸው እና የልጆች የአሁኑን አመልካችን ጨምሮ ሞግዚትነት ሥልጣን ማስረጃ እንዲሰጣቸው ለወረዳው ናዒባ ፍቤት አቤቱታ በማቅረባቸው ጉዳዩ ታይቶ በፍብሕቁ ሐምሌ ቀን ዓም ማስረጃው ተሰጥቷቸዋል ከዚህ በኋላ የአሁን አመልካች ኛ እኔ በሌለሁበት በውጭ አገር የተሰጠ ማስረጃ በመሆኑ ሁለተኛ ጉዳዩ በሀይማኖታዊ ፍቤት ቀርቦ የታየ ሲሆን በማስረጃው ላይ የፍብሕቁ መጠቀሱ አግባብነት የለውም በሚል ለቃዲ ፍቤት የይግባኝ አቤቱታ አቅርባለች የቃዲው ፍቤትም ለውሣኔው መሠረት የሆነው ህግ ከቅዱስ ቁርዓን ውጭ የተጠቀሰ በመሆነ የናዒባው ፍቤት አስተካክሎ ይወስን ዘንድ መልሶታል በዚሁ መሠረት የናዒባው ፍቤት ጉዳዩን አያየው እያለ የአሁን መልስ ሰጭ ጉዳዩ በመደበኛ ፍቤት ሊታይ ይገባዋል በሚል ሲከራከሩ አመልካች በበኩሏ በሸሪዓ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ያለው ይኸው ፃይማኖታዊው ፍቤት ነው በማለት ተከራክራለች የናዒባው ፍቤትም ይህንን የአመልካችን ክርክር ተቀበሉ አስቀድሞ በአሁን መልስ ሰጭ ጠያቂነት በናዒባው ፍቤት የታየ ጉዳይ አስከሆነ ድረስ በተጀመረው በቅዱስ ቁርዓን ህግ መሠረት ሊታይ ይገባዋል አንጂ በመደበኛ ፍቤት ሊታይ የሚችል አይደለም በማለት በቅዱስ ቁርዓን ህግ መሠረት መልስ ሰጭ አንድ ስምንተኛ ንብረት ይወስዳሉ ሲል መጋቢት ዐ ቀን ዓም ወስኗል በዚህ ውሣኔ ላይ የአሁን መልስ ሰጪ ለቃዲው ፍቤት አቤቱታ በማቅረባቸው የቃዲ ፍቤት ጉዳዩን በሃይማኖታዊ ፍቤት ለማየት የሁለቱ ተከራካሪ ወገኖች ፈቃድ ያስፈልጋል መልስ ሰጭ በዚሁ መሠረት ጉዳዩ በናዒባው ፍቤት አንዲታይ ፈቃድ የላቸውም ስለሆነም ጉዳዩ ሊታይ የሚገባው በመደበኛው ፍቤት ነው ሲል ዳኝነት ሰጥቷል በዚሁ የቃዲ ፍቤት ውሣኔ መሠረት መልስ ሰጭ ሚስትነታቸው እና የልጆቻቸው ሞግዚትነት ተረጋግጦ ማስረጃ እንዲሰጣቸው ለዳንግላ ወረዳ ፍቤት አቤቱታ አቅርበዋል ይኸው ፍቤትም ጉዳዩን ተመልክቶ በሥፋመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሚስትነትና የልጆች ወራሽነትን ማስረጃ ሰጥቷቸዋል አመልካችም ከላይ ከፍ ሲል እንደተገለፀው የቃዲው ፍቤት ጉዳዩ በመደበኛ ፍቤት አንጂ በሸሪዓ ህግ መሠረት ሊዳኝ አይገባውም ሲል በሰጠው ውሣኔ የይግባኝ አቤቱታ ለአማራ ክልል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍቤት ይግባኝ አቅርበው ይኸው ጠቅላይ ሸሪዓ ፍቤት ጉዳዩን ተመልክቶ በመቁ ሰኔ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የዳንግላ ወረዳ ናዒባ ፍቤት የሰጠውን ውሣኔ በማጽናት ወስኗል ከዚህም ሌላ የዳንግላ ወረዳ ፍቤት በሥፋመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የመልስ ሰጭን ሚስትነትና የልጆችን ወራሽነት በማረጋገጥ የሰጠው «ውሣኔ» ይሰረዝለት ዘንድ አመልካች በፍብሥሥሃሕቁጥር መሠረት አቤቱታ አቅርባለች የወረዳው ፍቤትም በዚሁ ነጥብ ላይ ካከራከረ በኋላ መልስ ሰጭ ባቀረቡት አቤቱታ መነሻ የናዒባ ፍቤቱ ሐምሌ ቀን ዓም ሚስትነታቸውን አረጋግጦ ውሣኔ ከሰጣቸው በኋላ ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ለሁለተኛ ጊዜ ለዳንግላ ወረዳ ፍቤት አቤቱታ በማቅረባቸው በፍትመቁ ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት በድጋሚ የሚስትነት ውሣኔ የሰጠበት መሆኑን ተረድቻለሁ ስለሆነም ይህ ለሁለተኛ ጊዜ በመደበኛው ፍቤት የተሰጠው የሚስትነት ማስረጃ ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ሊሰረዝ ይገባዋል በማለት ውሣኔ ሰጥተበታል ለዚህ የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነውም ይኸው ውሣኔ ነው የአሁን መልስ ሰጭ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት የይግባኝ አቤቱታ ለአዊ ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው ቀደም ሲል በዳንግል ወረዳ ፍቤት በሥፋመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ መሰረዙ ተገቢ ነው ወይስ አይደለም በሚለው ነጥብ ላይ ግራ ቀኙ ተከራክረዋል የከፍተኛው ፍቤትም ይግባኙን ከመረመረ በኋላ ቀደም ሲል የዳንግላ ወረዳ ፍቤት በጉዳዩ ላይ ውሣኔ የሰጠው ሐምሌ ቀን ዓም ነው ይሁን እንጂ የአሁን አመልካች ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ገብቼ እንድከራከር ይፈቀድልኝ በማለት መጠየቁን ተረድተናል እንዲሁም ውሣኔ ከመሰጠቱ በፊት በአስተዳደራዊ ሁኔታ አቤቱታ አቅርበው የክልሉ ጠፍቤት አንድ ጉዳይ በሁለት የተለያዩ ፍቤቶች ሊታይ አይገባውም ስለሆነም ክርክሩ ሊቆም ይገባዋል ሲል የዛፈ መሆኑንም ካቀረባቸው ማስረጃ ተረድተናል ይህም ከሆነ የወረዳው ፍቤት በጉዳዩ ላይ ውሣኔ ከመስጠቱ በፊት አመልካች በወረዳው ፍቤት ጉዳዩ እንደነበረ ታውቃለች የፍብሥሥሕቁ ክርክር መደረጉን ለማያውቅ ወገን እንጂ እንደ አመልካች አቤቱታ ያለውን ሊሸፍን አይችልም አመልካች ያለአግባብ ጣልቃ ልትገቢ አይገባም ተብላ ከሆነ በየደረጃው በይግባኝ እንዲስተካከል ማድረግ ከምትችል በቀር በፍብሥሥሕቁ መሠረት አቤቱታ ማቅረብ አትችልም አንዲሁም የአሁን መልስ ሰጭ ያቀረበችው አቤቱታ የሚስትነት መብትን ለማረጋገጥ በመሆኑ ከጉዳዩ ይዘት አንፃር የክርክር ተካፋይ የግድ ይኖራል ማለት አይደለም በፍብሥሥሕቁ አቤቱታ ማቅረብ የሚችለው ደግሞ የክርክር ተካፋይ መሆን እየቻለ ተካፋይ ሳይሆን ውሣኔ ተሰጥቶ ከሆነ ነው በዚህ ጉዳይ አመልካች የግድ የክርክር ተካፋይ ናት ማለት አይቻልም የሚሉትን ሁለት ምክንያቶች መሠረት አድርጐ የወረዳው ፍቤት ቀደም ሲል የሰጠውን ውሣኔ መሻሩ ተገቢ አይደለም በማለት ሽሮ ወስኗል የአሁን አመልካች ለጠፍቤቱ ባቀረበችው የይግባኝ አቤቱታ መነሻ ይኸው ፍቤት ሁለቱንም ወገኖች አከራክሮ በተመሳሳይ ምክንያት የከፍተኛውን ፍቤት ውሣኔ አጽንቶታል አመልካች ይህ በከፍተኛው ፍቤት እና በጠፍቤት የተሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ ሊታረምልኝ ይገባል በማለት ነው የሰበር አቤቱታ ያቀረበችው የሰበር አቤቱታው ይዘት በሥር ፍቤቶች ከቀረበው የተለየ አይደለም በዚህም ሰበር ችሎት ግራ ቀኙ የቃል ክርክራቸውን አሰምተዋል በሥር ፍቤቶች የተነሳውን ክርክር በየፊናቸው በማጠናከር የተከራከሩ ከመሆኑ በቀር በአዲስ መልክ የተጠቀሰ ክርክር የለውም አኛም ጉዳዩን ተመልክተናል የመዝገቡ ግልባጭ እንደሚያስረዳው መልስ ሰጭ የሟች ከተማ ኢብራሂም ሚስት ናት ወይስ አይደለችም። የሚለው ነው ይህንኑ ጭብጥ በመያዝም አቤቱታው ከሕጉ ጋር ተገናዝቦ ተመርምራሯል ወራሽ የሆነ ሰው ለሟቹ ወራሽ መሆኑና ከውርሱ ላይ የሚያገኘውን ድርሻ የሚያመለከት የወራሽነት የምስክር ወረቀት አንዲሰጠው ለፍቤት አቤቱታ ማቅረብ አንደሚችል በፍብሕቁ ላይ የተመለከተ ሲሆን ከፍቤት ለአመልካቹ የምስክር ወረቀት ከተሰጠ በኋላም ይህ የምስክር ወረቀት አስካልተሰረዘ ድረስ በተሰጠው የወራሽነት የምስክር ወረቀት መሠረት ወራሽ ሆኖ እንደሚገመት ቀጥሎ በሚገኘው የፍብሕቁ ላይ ተመልክቷል በዚህ ሁኔታ የወራሽነት የምስክር ወረቀት ከተሰጠ በኋላ አውነተኛ ወራሽ የሆነ ሰው መጥቶ አስቀድሞ ለሌላ ሰው የተሰጠው የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰረዝለት ካመለከተ ዳኞች አስቀድሞ የተሰጠውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት መሰረዝ እንደሚችሉና በዚህ መልኩ ተወስዶ የነበረው የምስክር ወረቀት መመለስ እንዳለበት በቁጥር እና ላይ ተመልክቷል ከዚህ በኋላ የውርስ ንብረቱ በሚጸና የወራሽነት ማስረጃ በሌለው ሰው ተይዞ የሚገኝ ከሆነ እውነተኛው ወራሽ በክስ መጠየቅ እንደሚችል ይህንንም አቤቱታውን ንብረቶቹ የሚጸና የወራሽነት ማስረጃ በሌለው ሰው መያዙን ባወቀ በሶስት ዓመት ጊዜ ማቅረብ እንደሚጠበቅበት በቁጥር እና ላይ ተደንግጓል ከእነዚህ የሕጉ ድንጋጌዎች በግልጽ መረዳት የሚቻለው የድንጋጌዎቹ የተፈጻሚነት ወሰን በወራሾች መካከል ሆኖ የሚጸና የወራሽነት ማስረጃ ባለውና በሌለው ወገን ላይ እንደሆነ ነው በተያዘው ጉዳይ አመልካችና ተጠሪ የሟች ልጆች ስለመሆናቸው ክርክር ያላስነሳ በመሆኑ በሁለቱ ወራሾች መካከል የተነሳው የወራሽነት ክርክር ከላይ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች መሠረት ይሸፈናል ማለት ነው ተጠሪም በሥር ፍቤት በአመልካች ላይ ክስ ያቀረቡት የጋራ የሆነውን የውርስ ሀብት ይዛ ስለምትገኝ ድርሻዬን ታካፍለኝ በማለት ነው የአመልካችና የተጠሪ አባት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል የተባለው የካቲት ቀን ዓም ሲሆን ተጠሪ የውርስ ንብረቱን ለመካፈል በአመልካች ላይ ክስ የመሰረቱት ደግሞ ታህሳስ ቀን ዓም ነው በፍትሐብሔር ሕቁ መሠረትም እውነተኛ ወራሽ የሆነው ወገን እውነተኛ ወራሽ ባልሆነው በሌላው ወገን ላይ ክስ ማቀረብ የሚገባው ከላይ እንደተጠቀሰው የንብረቱን አውነተኛ የወራሽነት ማስረጃ በሌለው ወገን መያዙን ባወቀ በ ሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ነው አመልካች ክስ ከቀረበበት ንብረት የግማሹ ባለቤት ስለሆኑ በዚሁ ልክ አውነተኛ ወራሽ ሊባሉ የሚችሉ ሲሆን ለቀሪው ግማሽ ንብረት ደግሞ እውነተኛ ወራሽ አይደሉም ማለት ነው ይሁንና ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ ጠቅላላ የውርሱ ሀብት በአመልካች እጅ እንደሚገኝ ተጠሪ ያውቃሉ ተብሎ ስለሚገመት ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ በ ሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠሪ ክሱን ማቅረብ ሲገባቸው ይህ ጊዜ ካለፈ በኋላ ክሱን ያቀረቡ በመሆኑ የሥር ፍቤቶች ለድንጋጌው የተሳሳተ ትርጉም በመስጠት ክሱ በይርጋ ቀሪ አልሆነም በማለት በፍሬ ጉዳይ ረገድ የቀረበውን ክርክር መርምረው ውሣኔ መስጠታቸው የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔነ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የቀይት ወረዳ ፍቤት በመቁ የካቲት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ አንደዚሁም የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ስለተገኘ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል ተጠሪ የውርስ ንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ በአመልካች ላይ ያቀረቡት ክስ በፍብሕቁ መሠረት በ ዓመት ጊዜ ውስጥ ያልቀረበ ስለሆነ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ተብሎ ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ የሰመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ጌታቸው ምህረቱ አቶ አሰግድ ጋሻው ወት ሒሩት መለሰ አቶ አብዱራሂም አህመድ አመልካች አቶ መላኩ ማሞ ተጠሪዎች እነ ወሮ ፈለቀች ማሞ ሰዎች ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበው በመጀመሪያ ደረጃ በሚቀርብ መቃወሚያ ላይ የተሰጠ ውሳኔ ላይ ከስረነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ የማቅረብ መብትን የሚመለከት ጉዳይ ነው ጉዳዩ የጀመረው በሰሸዋ መዞን ከፍተኛ ፍቤት ነው የአሁኑ ተጠሪዎች ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ ከአክስታቸው በውርስ የተላለፈላቸው ቤት የአሁኑ አመልካች ለብቻው ይዞ ሊያካፍላቸው ፈቃደኛ ባለመሆኑ ቤቱን እንዲያካፍላቸው ጠይቀዋል አመልካቹ በሰጡት መልስ የነዛዜ ወራሽነታቸውን ቀደም ሲል በወረዳ ፍቤት አረጋግጠው የጨረሱ በመሆኑ ድጋሚ ክስ ሊቀርብ እንደማይገባው ክሱም ቢሆን በይርጋ የሚቋረጥ በሆኑት አንዲሁም የቤቱ ግምት የተጋነነ መሆኑን በመግለጽ ተከራክርዋል ፍቤቱም ኑዛዜው በህጉ የተቀመጠውን ፎርማሊቲ አያሟላም ክሱም በይርጋ አይቋረጥም በማለት መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎ ቤቱ በባለሙያ እንዲገመት ትእዛዝ ሰጥቶ ውጤቱን ለመጠባበቅ ቀጠሮ ሰጥቷል በዚህ ብይን ላይ አመልካች ለአማራ ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ አቅርበው ፍቤቱ መልስ ሰጪዎችን ሳይጠራ የይግባኝ ቅሬታውን በፍሥሥህቁ መሰረት ዘግቶታል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ ውሳኔ ላይ ነው ይህ ችሎትም ኑዛዜው መፍረሱ እና የይርጋው መቃወሚያም ውድቅ መደረጉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ቀርቦ እንዲታይ አድርጓል ግራ ቀኙም ክርክራቸውን በጽሁፍ አቅረበዋል ይህ ችሎትም ጉዳዩን ምርምሯል ከፍ ሲል እንደተመለከተው ተጠሪዎች ላቀረቡት ክስ አመልካች የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል ፍቤቱም መቃወሚያዎቹን ውድቅ በማድረግ ቤቱ እንዲገመት ቀጠሮ ሰጥቷል በስረነገሩ ላይ የመጨረሻ ፍርድ ገና አልሰጠም በፍሥሥሕቁ መሰረት በመጀመሪያ ደረጃ በሚቀርብ መቃወሚያ ላይ ፍቤቱ ተገቢ መስሎ የታየውን ውሳኔ ሲሰጥ ከስረነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ማለት እንደማይፈቀድ እና ይግባኝ ማለት የሚቻለው የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ መሆኑ ተመልክቷል በተያዘውም ጉዳይ አመልካች ባቀረቡት የመጀመሪያ መቃወሚያ ላይ ዋፍቤቱ የመሰለውን ብይን ከሰጠ በላ በስረነገሩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ያልሰጠ መሆኑ ከፍ ሲል በተጠቀሰው የስስርአት ህግ መሰረት በብይኑ ላይ ይግባኝ ሊልበት እይችልም አመልካች በዚህ ብይን ላይ ያላቸውን ቅሬታ ይግባኝ ሊያቀርቡበት የሚችሉት ናቤቱ በስረነገሩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ከሰጠ በላ ነው በመሆኑም የመጨረሻ ውሳኔ ሳይሰጥ የቀረበው ይግባኝም ሆነ የሰበር አቤቱታ የስስርአት ህጉን ያልተከተለ በመሆኑ አመልካች ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት የለውም የሰሸዋ ከፍተኛ ፍቤትም ጉዳዩ ይግባኝ የማይባልበት መሆኑን ገልጾ አቤቱታውን ውድቅ ከማድረግ ፋንታ ይግባኙን በፍሥሥሕቁ መዝጋቱ ተገቢ አልነበረም ውሳኔ በስረነገሩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ሳይሰጥ በመቃወሚያው ላይ ይግባኝም ሆነ የሰበር አቤቱታ ሊቀረብ አይችልም የሰሸዋ ከፍተኛ ፍቤት በመቁ መጋቢት ዓም ይግባኙ በፍሥሥሕቁ በመዝጋት የሰጠው ትዕዛዝ ተሽሯራል ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዐዐዐ ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ መስፍን ዕቁበዮናስ ተሻገር ገሥላሴ ብርሃኑ አመነው አመልካች ወት ፀዳለ ደምሴ ቀረበች ተጠሪ አቶ ክፍሌ ደምሴ አልቀረበም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ መዝገቡ ለሰበር ችሎቱ ሊቀርብ የቻለው የአሁኗ አመልካች የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍቤት በሰጠው ውሣኔ ባቀረበችው የሰበር ቅሬታ ማመልከቻ መነሻነት ነው የአሁኑ ተጠሪ በቦንጋ ዙሪያ ወረዳ ፍቤት የሕፃን ቢኒያም ክፍሌ ወላጅ አባት ስለሆንኩ ፍቤቱ ለሕፃኑ ሞግዚትና አስተዳዳሪ አድርጎ ይሹመኝ በማለት የቀረበውን አቤቱታ ፍቤቱ መርምሮ የሕፃኑን ሞግዚትና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሞታል የአሁኗ አመልካች በፍሕሥሥቁ መሠረት ባቀረበችው የተቃውሞ አቤቱታ የአሁኑ ተጠሪ ሕፃኑን ከመውለዱ በስተቀር ምንም ዓይነት እርዳታ እንዳላደረገም ተንከባክቦም ዓላሣደገም አሁን ሕፃኑ ከአናቱ የሚወርሰውን ሐብት እና ንብረት ፍለጋ እንጂ ለሕፃኑ ጥቅም ብሎ ስላልሆነ ተጠሪ ሞግዚት እንዲሆን የተላለፈው ውሣኔ ተሽሮ በምትኩ እኔ አክስቱ ላለፉት ዓመታት ተንከባክቤ ያሣደኩት ሞግዚት ሆኝ እንድሾም ይወሰንልኝ በማለት ያቀረበችው መቃወሚያ የወረዳው ፍቤት መርምሮ አባት ላለው ልጅ አመልካች የሞግዚትነት ጥያቄ ማቅረብ አትችልም በማለት መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎ መዝገቡን ዘግቷል ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለት የከፋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት የአሁኑ ተጠሪ ሕፃኑን እስከዛሬ ድረስ ሣያሣድግ አሁን እናቱ ስትሞት ላሣድግ ማለቱ ሀብትና ንብረት ፍለጋ ሊሆን አንደሚችል ለመገመት የሚያዳግት ቢሆንም የደቡብ ብብሕክመንግሥት የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ከወላጆቹ አንዱ በሞት የተለየው ሕፃን በሕይወት ያለው ወላጅ ሞግዚትና አስተዳዳሪ እንደሚሆንለት ስለሚደነግግ የወረዳው ፍቤት የአመልካችን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ተገቢ ነው በማለት መልስ ሰጭን አስቀረቦ ሣያከራከር በፍሕሥሥቁ መሠረት መዝገቡን ዘግቶታል የክልሉ ጠቅላይ ፍቤትም የተፈፀመ መሠረታዊ የሕግ ሥህተት የለም በማለት ውድቅ አድርጎታል የሰበር ቅሬታ ማመልከቻው የቀረበው ይህንን ውሣኔ ለማስለወጥ ሲሆን ይህ ችሎት መጋቢት ቀን በዋለው ችሎት በዚህ ጉዳይ የሕፃን ቢንያም ክፍሌ አክስት የሆነችው የአሁኗ አመልካች ሞግዚት ለመሆን ያቀረበችውን ጥያቄ የሥር ፍቤቱ ውድቅ ያደረገበትን የሕግ አግባብ ለመመርመር ሲባል መዝገቡ ለሰበር እንዲቀርብ ትአዛዝ ተሰጥቷል መልስ ሰጭም መጥሪያ ደርሶት መልሱን ባለማቅረቡ የጽሁፍ መልስ የማቅረብ መብቱ ታልፏል ይህ ችሎት የሰበር ቅሬታ ማመልከቻውን ከሥር ፍቤት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር በማገናዘብ መርምሯል የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ስለ ሕፃናት መብት ደንግጓል በዚሁ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ መሠረት ሕፃናትን የሚመለከቱ አርምጃዎች በሚወስዱበት ጊዜ ሁሉ የመንግሥታዊ ወይም የበጎ አድራጎት ተቋማት እንዲሁም ፍርድ ቤቶችና የአስተዳደር ባለሥልጣናት ወይም የሕግ አውጭው አካላት የሕፃናትን ደህንነት በቀደምትነት እንዲያስቡ በአስገዳጅነት ተመልክቷል ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ ካፀደቀቻቸው የአለም አቀፍ ስምምነቶች መካከል የሕፃናትን መብት በሚመለከት ዓም የፀደቀውና በሕገመንግሥቱ አንቀጽ መሠረት የሀገሪቱ የሕግ አካል የሆነው የሕፃናት መብት ኮንቬንሽን አንቀጽ ፍርድ ቤቶችም ሆኑ ሌሎች አካላት ሕፃናትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ውሣኔዎች ሲሰጡ የሕፃናቱን ጥቅምና ደህንነት በዋነኛነት መመልከት እንደሚገባቸው ተመልክቷል እንደሚታወቀው የልጆቻቸው መብትና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ከወላጆቻቸው የበለጠ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ሰው ሊኖር ስለማይችል ሕግ አውጭው በመርህ ደረጃ የተቀበለው በመሆነ በሕይወት ያለው አባት ወይም እናት የሕፃን ልጁ ሞግዚት እና አስተዳዳሪ አድርጎ የመሾሙ አሰራር ሐገራችንን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ተሞክሮ መሆኑ ይታወቃል በዚህ መሠረት በፌዴራልም ሆነ በክልል የቤተሰብ ሕጎች ውስጥ ወላጆች ለሕፃናት ልጆቻቸው ሞግዚትና አስተዳዳሪ ስለመሆናቸው በግልጽ የተመለከቱ ድንጋጌዎች ያሉ ቢሆንም እነዚህ ድንጋጌዎች ተፈፃሚት የሚኖራቸው ሞግዚት ወይም አስተዳዳሪ የተባለው ወላጅ በሕገ መንግሥቱ እንደተመለከተው ለሕፃኑ ጥቅምና ደህንነት አስከሰሩ ጊዜ ድረስ ብቻ እንደሆነ ሊስተዋል የሚገባ ጉዳይ ነው በሌላ አነገጋገር በአባት ወይም በአናት የሞግዚትነት ሽፋን የሕባናትን መብትና ደህንነት የሚጎዱ ወይም ሊጎዱ የሚችሉ ስራዎች ሁሉ በዳኞች ቀሪ እና ፈራሽ ሊሆኑ የሚችሉበት አግባብ በሕጉ የተለያዩ ክፍሎች መገኘቱ ይህንኑ የሕፃኑን መብትና ጥቅም በዋነኛነት ለማስከበር የተደነገገ ነው በዚህ ረገድ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙ ዳኞች ሕፃናትን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ሲመረምሩ ከዝርዝር ሕጎቹ በተጨማሪ በሕገመንግሥት አንቀጽ በአስገዳጅነት የተቀመጠውን የሕፃናትን ደህንነት ከግምት ውስጥ ያስገባ ውሣኔ ላይ እንዲደርሱ የግድ ይላል ይህን በመተላለፍ የሚሰጡ ማናቸውም ውሣኔዎችና ልማዳዊ አሰራሮች የሕገ መንግሥቱን ኃይለቃል የሚቃረኑ ስለሚሆኑ ፈራሽነታቸው የሚያጠራጥር ነው ወደያዝነው ጉዳይ ስናመራ የክልሉ ፍርድ ቤቶች የሕፃን ቢንያም ክፍሌን ሞግዚትነት አስመልክቶ የቀረበላቸው ጉዳይ ሲመረምሩ ከሕጎቹ ግልጽ ድንጋጌዎች ባሻገር ሕገመንግሥቱ ያስቀመጠውን የሕፃኑን ደህንነትና ጥቅም የማስከበር መርህ ተግባራዊ ማድረግ ሲገባቸው በተለይ የአሁኑ ተጠሪ በዚህ ደረጃ የሞግዚትነት ጥያቄ ያነሣው ሕፃኑ ልጅ ከእናቱ በውርስ ከሚያገኘው ንብረትና ሀብት ላይ ተካፋይ ለመሆን አስቦ ስለመሆኑ» የከፍተኛው ፍቤት በውሣኔው ላይ ገልጾ ሕባኑን ከመውለድ ውጭ ከዓስር ዓመታት በላይ ዞር ብሎ ያላየውን ያልተንከባከበውን ያላሣደገውን እንዲሁም ፍላጎቱን አንኳን ያልጠየቁትን ሕፃን በሰላምና በእንክብካቤ ካደገበት ቤት ወጥቶ በአሁኑ ተጠሪ ሞግዚትነት ሥር ይተዳደር ብሎ የተደረሰበት መደምደሚያ የሕፃኑን ደህንነትና ጥቅም ያላገናዘበ ነው የሥር ፍቤቶች ከሕጎቹ ግልጽ ቃላት ባሻገር የሕጎቹን አላማና መንፈስ በቅጡ ሣያጤኑ የአንቀጾቹን ግርድፍ ቃላት ብቻ በመውሰድ ሕገመንግሥቱን በሚጋፋና የሕፃኑን መብትና ደህንነት በሚጎዳ አኳኋን የሰጡት የሞግዚትነት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው ብለናል ውሣኔ የደብብሕክመ ከፋ ዞን የቦንጋ ዙሪያ ወረዳ ፍቤት ታህሣሥ ቀን በመዝገብ ቁጥር እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ ፍቤት በዐ በመቁ ዐዐዐ በተጨማሪ የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ የሰጡዋቸው ውሣኔዎችና ትእዛዞች ተሽረዋል የአሁኗ ተጠሪ ወሮ ፀዳለ ደምሴ የሕፃን ቢንያም ክፍሌ ሞግዚትና አስተዳዳሪ ሆና ሕፃኑ ከሟች ወላጅ እናቱ ከወሮ ፋንታዬ ኃሚካኤል የሚያገኘውን ማናቸውም የውርስ ሀብት ተረክባ ሕፃኑን በመልካም አስተዳደግና ደህንነነት ተንከባክባ እንድታሣድገው ተሹማለች መዝገቡ ያለቀለት ስለሆነ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መዝገብ ቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ዳሼ መላኩ መስፍን ዑቁበዮናስ አመልካች ጠንክር ድምድ ተጠሪዎች ባበንጋ አሮሬ ወሮ በርጫት ፃብቴ በዚህ መዝገብ የቀረበውን ጉዳይ መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለአቤቱታው መነሻ የሆነው ክርክር የተጀመረው በደቡብ ብብሕክልል በጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ነው ከሣሽ የነበረው የአሁኑ አመልካች ሲሆን በአሁኖቹ ተጠሪዎች ላይ ክስ የመሠረተው ከእናቴ በውርስ ላገኘው የሚገባኝን ንብረት ተከሣሾች በሕገወጥ መንገድ ይዘው ሲጠቀሙበት ቆይተዋል በመሆኑም ንብረቱን እንዲለቁልኝ አንዲሁም የንብረቱን ግምት እንዲከፍሉኝ ይወሰንባቸው በማለት ነው ተጠሪዎቹ ደግሞ ለክሱ መነሻ የሆነው መሬት ከአፄ ሃይለስላሴ ዘመነ መንግስት ጀምሮ በይዞታችን ስር የቆየ ነው በ ዓም አንደገና የመሬት ድልድል ሲደገግም ለኛ ተሰጥቶአል በዚህ መሠረትም ያለማቁረጥ ግብር እየከፈልን የምንጠቀምበት ከመሆኑ ውጪ የሌላ ሰው ይዞታ ሆኖ አያውቅም ከሣሽ እኛን ለመክሰስ ምንም ምክንያት የለውም በማለት እንደተከራከሩ ከመዝገቡ ተመልክተናል ክሱ የቀረበለት ፍቤትም የሁለቱን ወገኖች ክርክር እና ማስረጃ ከሰማ በጊላከሣሽ ክስ በመሠረተበት መሬት ላይ ምንም አይነት መብት የለውም በማለት ክሱን ውድቅ ያደገረ ሲሆን በዚህ ፍቤት ውሳኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የክልሉ ጠፍቤትም የስር ፍቤት ውሳኔ ጉድለት የለበትም የሚል ምክንያት በመስጠት ይግባኙን ሳይቀበለው ቀርቶአል አቤቱታው የቀረበውም በዚህ ላይ ነው አኛም አመልካች በ ዓም በጻፈው ማመልከቻ ያቀረበውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ተጠሪዎቹን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል ከስር ጀምሮ እስከዚህ ሰበር ችሎት ድረስ ከተደረገው ክርክር እና የሥር ፍቤቶች ከሰጡት ውሳፄ መገንዘብ አንደቻልነው አመልካች ያለ አግባብብ ተወሰደብኝ የሚለው ንብረት የእርሻ መሬት በላዩ ላይ አሉ የተባሉት አትክልቶች እና የሳር ክዳን ቤትን ያጠቃልላል የተባለው ነው ይህ ንብረትም የእናቱ የነበረ አና በኋላ ግን በተጠሪዎች እና በአመልካቹ እናት መካከል በተደረገው ውል መሠረት በተጠሪዎች እጅ መግባቱንም በክስ ማመልከቻው ላይ ተመልክቶአል ክሱ የመሠረተው ሐምሌ ቀን ዓም ሲሆን አናቴ ከዚህ ዓለም ተለየች ያለው ደግሞ ታሕሳስ ዐ ቀን ዓም ነው በዚህ አይነት ለቀረበው ክስ ከተጠሪዎች የተሰጠ የመከላከያ ክርክር ደግሞ ከላይ ያየነው ክርክሩን በመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣነ ያስተናገደው የከፍተኛ ፍቤት የአመልካችን ክስ ውድቅ ያደረገው ክሱ በምንም አይነት ማስረጃ አልተደገፈም ይልቁንም ተከሣሾች በመሬቱ ላይ ለብዙ ዓመታት የቆየ ሕጋዊ የዞታ እንዳላቸው ባቀረቡት ማስረጃ አስረድተዋል በማለት ነው እንደምንመለከተው ፍቤቱ ከግራቀኝ ተከራካሪ ወገኖች የቀረበውን ክርክር ከማስረጃዎቻቸው ጋር አገናዝቦ መርምሮአል በዚህም አመልካች እንደክሱ ማስረዳት አለመቻሉን ሲያረጋግጥ ተጠሪዎች ግን ዓም ጀምሮ በይዞታቸው ስር አድርገው አና ተገቢውን ግብር እየከፈሉ ሲጠቀሙበት መቆየታቸውን አረጋግጦአል ከዚህ ውጪም በአመልካች እናት እና በተጠሪዎች መካከል የተደገረ ውል አላገኘም ስለዚህም በዚህ ረገድ የፈፀመውን የሕግ ስህተት የለም ውሳኔ በጉራጌ ዞን ከፈተኛ ፍቤት የፍብቁጥር በሆነው መዝገብ ግንቦት ዐ ቀን የተሰጠውና የክልሉ ጠፍቤት በመቁ በ ዓም ያፀናው ውሳኔ በዚህ ሰበር ችሎትም ፀንቶአል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች ይቻቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ወፈ የሰመቁ ጥቅምት ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድ መሐመድ አቶ ሐጐስ መልዱ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አቶ ተሻገር ገስላሴ አቶ ብርሃኑ አመነው አመልካች ወሮ ስንልሽ ማዘንጊያ ጠበቃ ቀረበ ተጠሪ እነ አቶ ተስፋ ማዘንጊያ ቀርበዋል መዝገቡን መርምረን የሚተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ ጉዳይ የአሁኖቹ ተጠሪዎች በአመልካች ላይ ህዳር ቀን ዓም ባቀረቡት ክስየአሁኗ አመልካች ግምቱ ብር የሆነና ከአውራሻችን ከወሮ የንጉሜ ማዘንጊያ የሚደርሰንን የውርስ ንብረት የያዘች ስለሆነ የውርስ ንብረት ታካፍለን የሜል ነው የአሁን አመልካች ለክሱ ከሰጠችው መልሶች መካከልአሁን የተጠየቀውን የውርስ ንብረት ወራሽ መሆኔ በፍቤት ተረጋግጦ ላለፉት አመታት በእጄ የቆየ ስለሆነ ተጠሪዎች በይርጋ ቀሪ የሆነን ጉዳይ አንስተው ሊጠይቁኝ አይገባም የሚል ይገኝበታል አቤቱታ የቀረበለት የሰሜን ጎንደር መስተዳደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት የአሁኗል አመልካች የይርጋ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ የውርስ ንብረቱን ከሳሽና ተከሳሾች አኩል ይካፈሉ ብሏል ጉዳዩን በይግባኝ የቀረበለት የአብክመጠቅላይ ፍቤት ይግባኙን በፍሕሥሥቁ ውድቅ በማድረግ መዝገቡን ዘግቶታል የሰበር አቤቱታው በዚህ ላይ የቀረበ ሲሆን ይህ ችሉት የካቲት ቀን በዋለው ችሉት የሥር ፍቤት የይርጋ ጥያቄውን ያለፈው በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ሲባል መዝገቡ ለሠበር እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቶ የግራ ቀኙን የቃል ክርክር ሰኔ ቀን ሰምቷል በዚህ ጉዳይ የሥር ፍቤት የይርጋው ጥያቄ ውድቅ ያደረገበት ዋንኛ ምክንያት የአሁኗ አመልካች ለክርክሩ ምክንያት የሆኑትን የውርስ ንብረቶች የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር በሚደነግገው መሠረት ከ ዓመት በላይ በይዞታዋ ስር ስላላደረገች ክሱ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በሚል ነው በመሠረቱ አውራሽ የተባሉት ወሮ ንጉሜጫ ማዘንጊያ መጋቢት ቀን ዓም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ መሆኑ ታውቋል የአሁኗ አመልካች ግንቦት ቀን ዓም የሟች ሕጋዊ ወራሽ መሆኗ ተረጋግጦ ንብረቱን ይዛ ስትገለገልበት ስለመቆየቷም ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ መረዳት ተችሏል የአሁኖቹ ተጠሪዎች ደግሞ በዚሁ ከተማ እየኖሩ ላለፉት ዓመታት በተከሳሽ የተያዙትን የውርስ ንብረቶች ሳይጠይቁ መቆየታቸው ታውቋል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ከሳሽ መብቱንና የውርስ ንብረቶች በተከሳሹ መያዛቸውን ካወቀ ሦስት ዓመት በኋላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ለማግኘት አይችልም በሚል ተደንግጓል የሥር ፍቤት የኸን መሠረታዊ የይርጋ ሕግ ወደ ጐን በመተው ግራ ቀኙ እየተከራከሩበት ያለው የውርስ ንብረት ከዘር የወረደ ርስት እንደሆነ በመቁጠር ለጉዳዩ አግባብ ያልሆን ሕግ ጠቅሶ የይርጋ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ መሠታዊ የሕግ ስህተት ነው ብለናል ውሣኔ የተጠሪዎች የውርስ ንብረት ጥያቄ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ብለናል የአብክመ የሰሜን ጎንደር መዞን ከፍተኛ ፍቤት ሰኔ ቀን ቁጥር በሆነ መዝገብ የሰጠው ውሳኔ አና የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በፍይመቁ በ የሰጡት ትዕዛዝ ተሽራል የቪህን ፍቤት ወጭና ኪሳራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ያለቀለት ስለሆነ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ ፀጋዬ አስማማው ዓሊ መሐመድ አልማው ወሌ አመልካች የወሮ አመለወርቅ እየሱስ ወራሽ ጠበቃ ሰለመን ገመቀል ቀረቡ ተጠሪዎቹ አቶ መስፍን አስፋው ወሮ አልማዝ አስፋው ጠበቃ መልካም ዓለማየሁ ቀረቡ ቱቱ አስፋው ሶስና አስፋው መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዮ የቀረበው አመልካች የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ትአዛዝ መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ጥር ቀን ዓም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ ስለጠየቁ ነው የክርክሩ ፍሬ ጉዳይ ከመዝገቡ ለመረዳት አንደሚቻለው በመጀመሪያ የአሁን ተጠሪዎች በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በከሳሽነት ቀርበው እህታችን ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው በ ዓም በሞት ተለይታለች እህታችን ልጅ ወይም ተወላጅ የሌላት መሆኑና እኛ ወራሾቿ መሆናችንን በፍርድ አረጋግጠናል ሟች እህታችን ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው ከወደ ውጭ አገር ለህክምና ስትፄድ ቤቷንና ንብረቷን ለአቶ ፈንታይ ወልደዮሐንስ እና ወሮ የሺመቤት ሀብተሚካኤል ሰጥታ ሄዳለች ሆኖም አደራ ተቀባዮች የሆኑት እነ አቶ ፋንታዬ የውርሱን ንብረት እንዲያስረክቡን ስንጠይቅ ለማስረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ቁጥሩ የሆነውን ቤትና በክሱ የተዘረዘሩ ንብረቶች አንዲያስረክቡ ውሣኔ ይሰጥልን በማለት ክስ አቅርበዋል ተጠሪዎች የውርስ ንብረቱን ይዘዋል ከሚሏቸው ከእነ አቶ ፈንታዬ ወልደዮሐነስና ወሮ የሺመቤት ሀብተሚካኤል ጋር እየተከራከሩ እያሉ ወሮ አመለወርቅ አየሱስ ቀርበው ሟች ጥሩወርቅ አስፋው የሟች አቶ አበበ ከበደ ሚስት ነበሩ እኔ የአቶ አበበ ከበደ ሚስት መሆኔን በፍርድ ቤት አረጋጋጫለሁ ክርክር እየተካሄደበት ያለው ንብረት የሟች አበበ ከበደ የጋራ ሀብት በመሆኑ በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ በማለት ያመለከተች ሲሆን ፍርድ ቤቱም የአመልካችን ማመልከቻ እና ማስረጃ ከመዘነ በኋላ ወደ ክርክሩ በጣልቃ ገብነት እንድትገባ ወስኗል የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የተጠሪዎችን ክስ የአመልካች አውራሽ የሆነችው አመለወርቅ እየሱስ በጣልቃ ገብነት ያቀረበችውን ማስረጃና የእነ ፈንታዬ ወልደዮሐንስን መልስና ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተጠሪዎች የቀረበባቸውን ክስ ኛ ተጠሪ ያልካዱና ክሱን ስለአመኑ የፍታብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት በዝርዝር የተያዘው ንብረት በራሱ ላይ ተዘርዝሮ የቀረበው ንብረት ለአመልካቾችና ለጣልቃ ገብ እንዲያስረክቡ ሁለተኛ ተጠሪ የአንደኛ ተጠሪ ባለቤት ሲሆን ባለቤታቻው ለህክምና ወደ ውጭ እንደፄዱና ሲመለሱ እንደሚፈጽሙ በመግለጽ ለጊዜው ከነገር ለመሸሽ እኔ ንብረቱን አልተረከብኩም በዝርዝር ላይም አልፈረምኩም ይበሉ እንጂ ክሱን በግልበጽ ስላልካዱ በነገሩ የመሸሽ የተሰጠ መልስ ክሱን እንደመካድ ስለማያስቆጥር ክስ በቀረበበት ንብረት ላይ አንደኛ ተጠሪ ጋር በጋራ ሀላፊ ናቸው ብለን ወስነናል ጣልቃ ገብም ተካፋይ ናቸው ብለናል በማለት ወስኗል የፌዴራልና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከክሱ ጋር በዝርዝር የተያዘው ንብረት በክሱ ላይ የተመለከተው ወይም የሟች የውርስ ንብረት ተጣርቶ ክፍፍሉን እንዲያስፈጽሙ አቶ ቸርነት ተገኝን ሹሟል ከዚህ በኋላ ውርስ አጣሪው በተጠሪዎችና አመልካች የግልና የሚስቱ የጋራ ሀብት ነው በሚሉት ጉዳይ ላይ ክርክርና ማስረጃ ከሰማ በኋላ አመልካች የፍታብሔር ህግ ቁጥር በተደነገገው መሠረት መብታቸውን ያልጠየቁ ስለሆነና በአዲስ አበባ አስተዳደር በየካ ክፍለ ከተማ በቀበሌ ቁጥሩ የሆነው ቤት ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው የተመዘገበ ስለሆነ የእሷ የግል ንብረት የሚልና ሌሎች ንብረቶችም ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው የግል ሀብት ናቸው በማለት ወስኖ ይህንን ሪፖርት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቅርቧል ፍርድ ቤቱም የውርስ አጣሪው ሰኔ ቀን ከተፃፈ መሸኛ ጋር የቀረበለትን ሪፖርት ህግና ሞራልን የማይቃረን በመሆኑና ተከራካሪዎቹ ትክክለኛነቱን ቀርበው ስላረጋገጡ የፍርድ ቤቱ የውሣኔ አካል አድርጐ መዝግቦታል በማለት ትዕዛዝ ሰጥቷል አመልካች በዚህ ወሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርባ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኙን በፍታብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ሰርዞታል አመልካች የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የውርስ አጣሪውን ሪፖርት በማጽደቅ የሰጠውና ትእዛዝና የከፍተኛው ፍርድ ቤት ያቀረብኩትን ይግባኝ ለመሰረዝ የሰጠው ትእዛዝ መሠረታዊ የህግ ስህተት አለበት በማለት ባቀረቡት አቤቱታ ፍርድ ቤቱ የሾማቸው የውርስ አጣሪ ከእኛ በኩል ያቀረበውን ማስረጃ ተቀብለው አልመረመሩም ፍርድ ቤቱ የውርስ ከጣሪው ባቀረበው ሪፖርት ላይ በጽሑፍ መቃወሚያ ብይን ሣይሰጥ የውርስ አጣሪውን ሪፖርት ማጽደቅ መሠረታዊ የህግ ስህተት አለበት ከሁሉም በላይ በጣልቃ ገብ ተከራካሪነት ቀርበን ባቀረብነው ክስና ማስረጃ መሠረት በክርክር የተያዘው ሀብት የወሮ ጥሩወርቅ አስፋውና የአቶ አበበ ከበደ የጋራ ንብረት እንደሆነ በማረጋገጥ ፍርድ ቤቱ ንብረቱን በአደራ የያዙትና በሥር ፍርድ ቤት ተከሳሽ የነበሩት እነ ፈንታዬ ወዮሐንስ ንብረቱን ለከሳሾች ተጠሪዎች እና ለጣልቃ ገብ ያስረክቡ ጣልቃ ገብ ተከፋይ ናቸው በማለት ውሣኔ የሰጠበትን ጉዳይ የውርስ አጣሪው ከተሰጠው ስልጣን ውጭ በማከራከር ውሣኔ መስጠቱና ፍርድ ቤቱም ተቀብሎ ማጽደቁ መሠረታዊ የህግ ስህተት በመሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት አመልክተዋል ተጠሪዎች በበኩላቸው የባልና የሚስቱ ግንኙነት ከተቋረጠ ሰላሣ አመት የሆነው በመሆኑ አቶ አበበ ከበደ ከዚህ በፊት የመጥፋት ውሣኔ የተሰጠባቸው በመሆኑ የውርስ አጣሪው ንብረቱ የግል ነው ወይስ የጋራ የሚለውን አጣርቶ አንዲወሰን የተሾው በመሆኑና ይህንንም ያደረገው ፍርድ ቤቱ በሰጠው ስልጣን መሠረት በመሆኑ በአጠቃላይ በውርስ አጣሪውም ሆነ በሥር ፍርድ ቤት የተፈፀመ የህግ ስህተት የሌለ በመሆኑ የአመልካች አቤቱታ ውድቅ ይደረግልን በማለት ሀምሌ ቀን ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበዋል አመልካች በበኩላቸው ሟች አበበ ከበደ በህይወት አለመኖራቸው የተረጋገጠው ዓም በመሆኑ ከዚህ ጊዜ በፊት የተፈራው ሀብት የጋራ ሀብት ነው የቤቱ ፕላንና ሥራው የተፈቀደው ከአቶ አበበ ከበደ በመሆኑ ቤቱ የጋራ ንብረት ስለመሆኑ የሚያከራክር አይደለም ሌሎች ንብረቶች መኪና በባንክ የተያዘው ገንዘብ እና ልዩ ልዩ ጌጣጌጦች የጋራ ሀብት ናቸው የውርስ አጣሪው ከማጣራት ተግባር ወጥተው ህግ የመተርጐም ሥራ የሠሩ በመሆናቸውና ፍርድ ቤቱም ይህንኑ ተቀብሎ የፀደቀ በመሆኑ መሠረታዊ የህግ ስህተት በሥር ፍርድ ቤቶች በኩል ተሰርቷል በማለት የመልስ መልስ አቅርበዋል ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር ደረጃ ግራ ቀኙ በኩል የቀረበው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው ኛ ተጠሪዎች የሟች የወሮ ጥሩወርቅ አስፋው ንብረት ነው በማለት ዘርዝረው በእነ አቶ ፈንታዬ ወልደዮሐንስ ላይ ክስ አቅርበው ሲከራከሩበት የነበረው ንብረት የአመልካች አውራሽ የአቶ አበበ ከበደ የጋራ ሀብት መሆኑ በፍርድ ተወስኗል ወይስ አልተወሰነም። የሚለውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም የውርስ አጣሪው ለፍቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት ቁጥሩ የሆነው ቤት አዋጅ ቁጥር ከመውጣቱ በፊት ሟች ወሮ ደጊቱ ደንጓሬ ለወሮ አሰለፈች ወርዶፋ በስጦታ የሰጡዋቸው በመሆኑ የውርስ ሐብት አይደለም በማለት ወስኛለሁ ቁጥሩ የሆነው ቤትም የወሮ አስናቀች ወርዶፋ የኑዛዜ ድርሻ ነው አመልካች ስጦታዎቹ ፈራሽ ናቸው በማለት ቢከራከሩም የሚፈርስበትን ምክንያት አልገለፀም ስጦታው እንዲፈርስ በፍርድ ቤት ጠይቀው ያስፈረሱበትን የፍቤት ውሳኔ አላቀረቡም በማለት ያሰፈሩዋቸው ድምዳሜዎች ንብረቶቹን የማከፋፈል ዓይነት ሥራ ያከናወኑ መሆኑን እንደሚጠቁሙ ለመረዳት ችለናል በፍብሕቁ እንደተደነገገው የአጣሪው ሥራ ሟቹ አንድ ኑዛዜ ትቶ አንደሆነ መፈለግና በመጨረሻው ውርሱ የሜደርሳቸው ሰዎች እነማን እንደሆኑ ማረጋገጥ የውርሱን ሃብት ማስተዳደር መክፈያቸው የደረሰውን የውርስ አዳዎች መክፈል እና ሟቹ በኑዛዜ ያደረጋቸውን ስጦታዎች መክፈልና የኑዛዜውን ቃል ለመፈፀም ማንኛቸውም ሌሎች አስፈላጊ ጥንቃቄዎች ማድረግ ነው እነዚህ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት በሚያከናውንበት ጊዜ ደግሞ በኑዛዜው የውርስ ንብረት መሆናቸው ተጠቅሶ የክፍፍል ስርአትም የተቀመጠላቸውና ወራሾች በሙሉ የተስማሙባቸው ንብረቶችና መክፈያቸው የደረሰው የውርስ አዳዎች ሲኖሩ በወራሾቹ ስምምነት መሰረት ንብረቶቹን ሊያከፋፍል አዳዎችንም ሊከፍል ይችላል በነዛዜው ላይ በተጠቀሱትና ባልተጠቀሱት ንብረቶች የውርስ ዛብት መሆን ያለመሆኑ ላይ ወራሾቹ ያልተስማሙና ክርክር ያስነሱ ከሆነ ግን የአጣሪው ሥራና ሐላፊነት ወራሾች የተስማሙባቸውን ንብረቶች የውርስ ሃብት መሆናቸው መመዝገብ ወራሾች ያልተስማሙባቸው ንብረቶችና እዳዎች ካሉ ደግሞ ማስረጃ በመሰማት ማስረጃው ምን እንደሚያስረዳ ሪፖርቱ ላይ በማስፈር እንዲያጣራ ላዘዘው ፍቤት ማቅረብ እንጅ ንብረት አጣሪው ይህ ንብረት የውርስ ሐብት አይደለም የሚሉ ወራሾች ቢኖሩም ማስረጃ በመስማት የውርስ ሃብት መሆኑን ስለተገነዘብኩኝ ንብረቱ የውርስ ህብት ነው በማለት ወስኛለሁ ወይም ደግሞ ማስረጃውን እንደተመለከትኩት ንብረቱ የውርስ ሐብት ያለመሆኑን ስላረጋገጥኩኝ የውርስ ሐብት አይደለም በማለት ወስኛለሁ ለማለት የሚያስችለው ሥልጣን የለውም በዚህ ጉዳይ የውርስ አጣሪው ያደረጉትን የማጣራት ሥራ ስንመለከተው ወራሾቹ የውርስ ሐብት ናቸው በሚሉዋቸው ሁለቱም ቤቶች ላይ ገና ከጅምሩ አንስቶ ያልተስማሙና ክርክር ያነሱ በመሆኑ አጣሪው ማስረጃ መስማታቸው በአግባቡ ነው ሁኖም አጣሪው በወራሾች መካከል የተደረገው ክርክር ምን እንደነበረ የኑዛዜ ወራሾችና የሕግ ወራሾች እነማን እንደሆኑ የግራ ቀኙ ማስረጃ ምን አንደሚመልስ ወራሾች የተማመኑባቸውና ያልተማመኑባቸው የውርስ ንብረቶችና እዳዎቹ ምን ምን እንደሆኑ በመዘርዘር ሪፖርት ማዘጋጀት ሲኖርባቸው ከዚህ አልፈው ወራሾችን አከራከረው ማስረጃ ከሰሙ በጊላ ክርክሩን ማስረጃውን ከሕግ ጋር በማገናዘብ ይህ ንብረት የእገሌ እንጅ የአገሌ አይደለም በማለት መወሰናቸው ከተሰጣቸው የውርስ አጣሪነት ሥልጣን በላይ በመሄድ መደመኛ ፍቤት የሚያከናውነውን የዳኝነት ሥራ ውስጥ መግባታቸው ተገቢ ያለመሆኑን ተገንዝበናል ውርስ አጣሪው አዘጋጅተው ያቀረቡት ሪፖርት ውሳኔም ጭምር ያዘለ በመሆኑ ሪፖርቱ በቀረበለት ፌመደፍቤት መጽደቁ ደግሞ በአጣሪው የተወሰነው ነገር በፍቤት ተቀባይነት አግኝቶ የፀደቀ ተደርጐ ስለሚወሰድ አመልካች አዲስ ክስ አቅርበው የውርስ ድርሻቸውን ሊያገኙ የሚያስችላቸው መብት የሚያጣብብ ነው የሚሆነው በመሆኑም ፏ የፌመደፍቤት ሪፖርቱን መርምሮ ያለበትን ጉድለት እንዲያስተካክል ማድረግ ሲገባው አንዳለ ተቀብሎ ማጽደቁ ተገቢ ሆኖ አልተገኘም ስለዚህ የውርስ ንብረት አጣሪው ያቀረቡት ሪፖርት የአጣሪንና የመደበኛ ፍቤትን ሥራ አጠቃሎ የያዘ በመሆኑ ሪፖርቱ በአግባቡ የተዘጋጀ ባለመሆኑና የፌመደፍቤት ሪፖርቱን ያፀደቀበትና የፌከፍቤት ደግሞ የቀረበለትን ይግባኝ የሰረዘበት ትአዛዝ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለተገኘ የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ የፌመደፍቤት በመቁ ጥር ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝና የፌከፍቤት በመቁ ሕዳር ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽረዋል የሥር ፍቤት የውርስ ማጣራት ሪፖርቱን ያፀደቀው ከነጉድለቱ ጭምር በመሆኑ መጽደቅ አልነበረበትም ብለናል በመሆኑም የሥር ፍቤት እንደገና አጣሪ ሾሞ የውርስ ማጣራቱን ሥራ በፍብሕቁ መሰረት እንዲጣራ በማስደረግ ሪፖርቱ በአግባቡ የቀረበ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ በሕጉ መሰረት አስፈላጊውን እንዲፈጽም በማለት ወስነናል ይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን እንዲችሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መለሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ መድንን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም አመልካች ወሮ አየለች አልታዬ ቀረቡ ተጠሪ ወሮ አስናቀች አየለ ቀረቡ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ በሰበር የቀረበው የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እና ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የፌዴራል የከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ስላለበት በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ሰኔ ቀን ዓም ባቀረበችው አቤቱታ ስለጠየቀች ነው የክርክሩ መነሻ አመልካች የሕፃን ዮናስ ወንድሙና የያሬድ ወንድሙ ወላጅ አናት እና ሞግዚት መሆኗን ገልፆ የሞግዚት አድራጊዎች ወላጅ አባት አቶ ወንድሙ ገብረየስ መጋቢት ቀን ዓም በሞት ተለይተዋል ሟች አቶ ወንድሙ ከተከሣሽ ከተጠሪ ጋር በባልና ሚስትነት እያሉ በአዲስ አበባ ከተማ ወረዳ ቀበሌ ቁጥሩ የሆነ መኖሪያ ቤት ሠርተዋል ስለዚህ የመኖሪያ ቤቱን ግምትና ቤቱን ለሱቅና ለሆቴል እያከራየች የምታገኘው ገንዘብ ጭምር የሕፃኖቹ ወላጅ አባት የጋራ ሀብት በመሆኑና የውርስ ሀብት ክፍል እንድታካፍለኝ ውሣኔ ይሰጥልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል ተጠሪ የውርስ ንብረት ክፍል ነው የተባለውን ሀብት አስመልክቶ የተለያየ ክርክርና ማስረጃ ያቀረበች ሲሆን ወሮ ጥሩወርቅ ወንድሙ የተባለች ሴት በበኩሏ የሟች ወንድሙ ገብረየስ ወራሽ እና ልጅ ነኝ በማለት የወራሽነት ማስረጃዋን በማያያዝ በክርክሩ ጣልቃ ገብታለች ፍርድ ቤቱ ቤቱና ሌሎች ንብረቶች ተገምተው እንዲቀርቡለት ትእዛዝ ሰጥቶ የፍርድ አፈፃፀም መምሪያ መሀዲስ የቤቱ ጠቅላላ ዋጋ ብር አስራ ዘጠኝ ሺ ስምንት መቶ ፃያ ሶስት ብር ከአርባ ሰባት ሣንቲም ነው በማለት አስተያየት አቅርቧል ከዚህ በኋላ የቤቱ ግማሽ ባለቤትነት የተጠሪ የቤቱ ግማሽ ባለቤትነት ደግሞ የአመልካች ሞግዚት አድራጊዎችና የወሮ ጥሩወርቅ ወንድሙ መሆኑን ከዘረዘረ በኋላ ተጠሪና ወሮ ጥሩወርቅ ወንድሙ ለአመልካች ብር አምስት ሺ አምስት መቶ ፃምሣ አንድ ብር ከፃያ አንድ ሣንቲም በመክፈል ቤቱን በጋራ እንዲያስቀሩ ይህንን ማድረግ ካልቻሉ በሀራጅ እንዲሸጥ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርባ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሣኔ አጽንቷል አመልካች ልጆቹን ማሣደጊያ ቤት የለኝም ንብረቱ በአይነት መካፈል እየተቻለ ተጠሪ ትጠቅልለው መባሉ ተገቢ አይደለም ንብረቱም መሸጥ ካለበት መሀዲሱ ባቀረበው ግምት ሣይሆን በሀራጅ መሆን ይገባዋል የዳኝነት በጋራ ክፈሉ መባሉ ተገቢ አይደለም በአጠቃላይ የሥር ፍርድ ቤቶች ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለበት በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ያመለከተች ሲሆን ተጠሪ በበኩሏ ቤቱ አመልካችና ተጠሪ ባሉበት በመሐንዲስ የተገመተ በመሆኑ እአና በአይነት ሊከፈል የማይችል በመሆኑ አመልካች ያቀረበችው አቤቱታ ሕጋዊ መሠረት የለውም የሚል መልስ የሰጠች ሲሆን አመልካች የመልስ መልስ አቅርባለች ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር የተደረገው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን አኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው የክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት ሟች ወንድሙ ገብረየስ እና ተጠሪ በባልና ሚስትነት ሲኖሩ በጋራ የሰሩት ቤትና የጋራ ንብረት መሆኑ አልተካደም ሟች ወንድሙ የሞተ በመሆኑ አሱ በቤቱ ላይ ያለው የጋራ ባለቤትነት መብት ለወራሾቹ ዮናስ ወንድሙ ያሬድ ወንድሙና ወርቅነሽ ወንድሙ በፍትሐብሔር ሕግ ቀጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይተላለፋል ስለሆነም የቤቱ የጋራ ባለንብረቶች የሟች ወንድሙ ገብረየስ ወራሾች እና ተጠሪ ናቸው የማይንቀሣቀስም ንብረት የጋራ ባለቤት የሆኑ ሰዎች የማይንቀሣቀሰውን ንብርት በአይነት ለመከፋፈል የሚችሉ ከሆነ በአይነት መከፋፈል እንደሚችሉ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የተደነገገ ሲሆን ንብረቱ በአይነት መከፋፈል የማይቻል ሲሆን በሀራጅ ተሸጦ ገንዘቡን እንደሚከፋፈሉ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ተደንግጓል ከዚህ አንፃር ንብረቱ በአይነት ለመከፋፈል የሚችል ከሆነ የሟች ወራሾች እና ተጠሪ ንብረቱን እኩል መከፋፈልና የሟች ወራሾች ድርሻቸውን በስምምነት የሚከፋፈሉበት ዕድል ሊሰጣቸው ይገባል ስለሆነም ቤቱ በአይነት ለመከፋፈል የሜቻል ሲሆን አመልካችና ተጠሪ ቤቱን በአይነት እንዲካፈሉ ትአዛዝ መስጠት ሲገባቸው አላግባብ ያለፉት በመሆኑ ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል ከላይ በተገለፀው መንገድ ቤቱ በአይነት ለመከፋፈል የሚችል ካልሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ግልጽ ሀራጅ ወጥቶ መሸጥ ይገባዋል ተጠሪም ሆነች አመልካች የቤቱን ዋጋ በመክፈል የቅድሚያ ግዥ መብታቸው የሚጠበቀው ቤቱ በግልጽ ጨረታ ያወጣውን ከፍተኛ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዝግጁ ሆነው ሲገኙ እንጅ መሀዲሱ ገምቶ ያቀረበውን ዋጋ ገቢ በማድረግ አይደለም ስለሆነም አመልካችና ተጠሪ ቤቱ በግልጽ ሀራጅ የሚያወጣው ዋጋ መሠረት ለማስቀረት የሚስማሙ ከሆነ በስምምነታቸው መሠረት መፈፀም አለበት አመልካች አና ተጠሪ የማይስማሙ ከሆነ ግን ቤቱ በግልጽ ሐራጅ ተሸጦ የሟች ወራሽ የሆኑት ሶስት ልጆች ግማሹን ለሶስት እኩል እንዲካፈሉ ተጠሪ ደግሞ የቤቱን ግማሽ ዋጋ እንድትወስድ መደረግ ይገባዋል ከዚህ በተጨማሪ አመልካች በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ባቀረበችው ክስ መሠረት በክርክሩ ፊት ሆና እያለ ከተጠሪ ጋር ዳኝነት በጋራ እንድትከፍል የሰጠው ውሣኔ ተገቢነት የሌለውና መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሚያዚያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ አመልካችና ተጠሪ የሚቻል ከሆነ ቤቱንና ቦታውን በአይነት እንዲከፋፈሉ ቤቱን በአይነት ለመከፋፈል የማይችሉ ከሆነ በግልጽ ጨረታ በሀራጅ ተሸጦ ግማሹን ተጠሪ እንዲወስዱ ግማሹን የሟች አቶ ወንድሙ ወራሾች ለሶስት አኩል እንዲካፈሉ በማለት ወስነናል በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዳኝነት ወጭ ተጠሪ ብቻዋን መሸፈን አለባት ብለናል በዚህ ፍርድ ቤት ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ለየራሣቸው ይቻቻሉ ይህ ፍርድ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ቀን ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ሐጐስ ወልዱ አቶ ታፈሰ ይርጋ አቶ መድሕን ኪሮስ አቶ ሱልጣን አባተማም አመልካች ወት ዘላለም ታምራት መልስ ሰጭ ወት ቤቴልፄም ዑመር መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ውሳኔ ተሰጥቷል ውሣኔ ለዚህ ችሎት ታህሣሥ ቀን ዓም በተጻፈ ማመልከቻ የቀረበው የሰበር አቤቱታ ለመልስ ሰጭ ደርሶ ሰኔ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የግራ ቀኙን ተከራካሪ ወገኖች የቃል ክርክር ችሎቱ አድምጧል የግራ ቀኙን ክርክር አቤቱታው ከቀረበበት ውሣኔ መደምደሚያና ለዚህም መሠረት ከሆነው የሕግ ትንታኔ አንጻር ተመርምሮ ውሣኔው ጉድለት ያለበት ሆኖ ስላልተገኘ በደክጠፍሰበር ፍቤት በመዝገብ ቁጥር በ ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ መሠረት ፀንቷል ይጻፍ ግራ ቀኙ ኪሣራቸውን ለየራሣቸው ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የካቲት ቀን ዓም የተሰጠው የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ይፃፍ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ዙዘ የሰመቁ ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ብርፃኑ አመነው አቶ መድሕን ኪሮስ አቶ ዓሊ መሐመድ አቶ ሱልጣን አባተማም አመልካችኹ እማሆይ ወይንሸት አድማሱ ተጠሪ እነ ወሮ ክብነሽ ስዩም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የተጀመረው በፌመደፍቤት ሲሆን አመጣጡም የአሁኑ ተጠሪዎች ታህሳስ ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት የክስ ማመልከቻ ሟች አቶ ስዩም አየለ በወረዳ ቀበሌ ቁጥሩ የሆነውን ቤት አኩል እንድንካፈለው ለኛና ለተከሳሾች ተናዝዘውልናል ስለቤቱ አጠቃቀም ውርሱን በማጣራትና በመለየት ቤቱን አስከምንከፋፈል በኪራይም ይሁን በኮንትራት የሚገኘውን ገቢ እየተከፋፈልን እንድቆይ ተስማምተናል ሆኖም ተከሳሾች ቤቱን አከራይተው ያገኙትን ገቢ ሊያካፈሉን ፈቃደኞች ባለመሆናቸው በኪራይ ያገኙትን ገንዘብ እንዲያካፍሉን ቤቱም ተሽጦ እንድንከፋፈል ይወሰንልን በማለት ክስ አቅርበዋል የአሁን አመልካቾች የሥር ተከሳሾች ደግሞ ለቀረበባቸው ክስ በሰጡት መልስ ያደረግነው ስምምነት ኑዛዜውን የሚተካና ወሳኝነት ያለው አይደለም ክርክር ያስነሳው ቤትም የምንኖርበት አንጅ የሚከራይ አይደለም ለተወሰነ ጊዜ ተከራይቶ በነበረበት ጊዜ የተገኘው ገቢም ብር ነው ከዚሁ ገንዘብ የቤት ባለቤትነት ደብተር ለማስወጣት ከፍለንበታል ቀሪውን ገንዘብ ተሳስበን ለመክፈል ዝግጁነን የቤቱን መከፋፈል ግን የሚደረገው በኑዛዜው መሰረት ከኛ ተከሳሽ የህይወት ፍፃሜ በላ ነው በመሆኑም ከሣሾች ያቀረቡት ክስ ኑዛዜውን መሰረት ያላደረገ መሆነ ውድቅ ሊሆን ይገባል በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም ግራ ቀኙን ካከራከረና ማስረጃ ከተማ በኋላ ተከሳሾች ቤቱን በማከራየት ካገኙት ገቢ ውስጥ የከሳሾች ድርሻ የሆነውን ብር ለከሳሾች እንዲከፍሉ ቤቱም በሐራጅ ተሸጦ ለወራሾች እንዲከፋፈል በማለት ወስነናል ከፍተኛው ፍቤት የቀረበለትን ይግባኝ መሰረት በማድረግ ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ የሥር ፍቤቱን ውሳኔ አጽንቶታል አመልካቾች የሰበር አቤቱታው ያቀረቡት በሥር ፍቤቶቹ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ሲሆን ቅሬታቸውም ሟች የተናዘዙት ክርክር ያስነሳውን ቤት ኛ ተጠሪ ከሌሎቻችን መራሾች ጋር በመሆን እንዲገለገሉበት ለሌሎቻችን ወራሾች ሊከፋፈል የሚችለው አሳቸው ከዚህ ዓለም በሞት በሚለዩበት ጊዜ መሆኑን ነው ኛ አመልካች በህይወት እያለ ቤቱን መሸጥና መከፋፈል አይቻልም እንደዚሁም መራሾች በሙሉ ተሰብስበን ኛ አመልካችም ጭምር ቤቱ ሳይከፋፈል ከሚያስገኘው ጥቅም እኩል እየተጠቀምን መቆየት እንዳለብን የተስማማንና የተዋዋልን በመሆኑ ተጠሪዎች ቤቱን ለመካፈል ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለውም የፌመደፍቤትና የፌከፍቤትም ቤቱ በሐራጅ ተሽጦ ገንዘቡን ወራሾች እንዲከፋፈሉት በማለት የሰጡት ውሳኔ የአውራሻችን ኑዛዜና ከዚያም በኋላ ወራሾች ያደረግነውን ውል ያላገናዘበና መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ውሳኔው ሊሻርልን ይገባል የሚል ነው የሰበር ችሎቱም አቤቱታውን ከመረመረ በኋላ ክርክር የተነሳበት ቤት በአጠቃላይ በሐራጅ እንዲሸጥ በማለት የተሰጠው ውሳኔ የሟችን የኑዛዜ ቃል የተከተለ መሆን አለመሆኑን መመርመር አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘው አቤቱታው ያስቀርባል ሲል ትእዛዝ ሰጥቷል ተጠሪዎችም ሐምሌ ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት መልስ ኛ አመልካች በቤቱ ላይ የጋራ መብት የላቸውም ከኑዛዜው በላ ጥር ቀን ዓም በተባፈው የወራሾች የጋራ የስምምነት ውል ኛ አመልካች ቤቱ የማይመለከታቸው መሆኑን ተወስኗል ቤቱ የወራሾች የጋራ ንብረት በመሆኑ ተሽጦ እንድንከፋፈለው እንዲወሰንልን ክስ ማቅረባችን በአግባቡ ነው ኛ እና ኛ አመልካቾች በኑዛዜ ያገኘነውን ቤት ክርክር ካስነሳው ቤት ጋራ በሐራጅ እአዲሸጥ ተወሰነብን በማለት ያቀረቡት ክርክር በስር ፍቤት ያላነሱት በመሆኑ ተቀባይነት የለውም የስር ፍቤቶች ቤቱ በሐራጅ ተሽጦ ገንዘቡን ወራሾች እንዲከፋፈሉት በማለት የሰጡት ውሳኔም አንዳችም የሕግ ስህተት የለበትም በመሆኑም ውሳኔው እንዲፀናልን በማለት ተከራክረዋል አመልካቾች ያቀረቡት የመልስ መልስ ከመዝገቡ ጋር ተያይዛል በበኩላችን ደግሞ ክርክር ያስነሳው ቤት ኛ አመልካች በህይወት እያሉ በሐራጅ ተሽጦ ወራሾቹ ሊከፋፈሉት ይገባል ወይስ አይገባም። የሚለውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም የወራሾቹ አውራሽ የሆኑት ሟች አቶ ስዩም አየለ ነሐሴ ቀን ዓም በሰጡት ኑዛዜ ወሮ ወይንሸት አድማሱ ክርክር ባስነሳው ቤት ውስጥ ከሌሎቹ ወራሾች ጋር አብረው እንዲኖሩ የፈቀዱና እሳቸው በህይወት እያሉም ቤቱን ሸጨ ድርሻዬን እወስዳለሁ የሚል ካለ ያገዱት መሆኑን ተገንዝበናል ተናዛዝ ወራሾችን ወይም በኑዛዜ ስጦታ የተሰጣቸውን ሰዎች ከሚደርሳቸው ዛብት ላይ በተለየ ለአንድ ወይም ለብዙ ሰዎች አንድ አገልግሎት እንዲሰጡ ግድ እንዲሆንባቸው በኑዛዜው ለመወሰን እንደሚቻል በፍብሕቁ ተደንግጓል የአመልካቾችና የተጠሪዎች አውራሽ የሆኑት አቶ ስዩም አየለ በኑዛዜያቸው ያስቀመጡት የኛ አመልካች ቤቱን የመጠቀም መብትም ወራሾች እንዲፈጽሙት የሚያስገድዳቸው ነው በኑዛዜው ግዴታ የተገባላቸው ኛ አመልካችም በፍብሕቁ መሰረት የታዘዘላቸውን እንዲፈጽሙላቸው ወራሾችን ለማስገደድ ይችላሉ ወራሾቹ ተሰብስበው በውርስ ስለተሰጣቸው ቤት አጠቃቀም ለመወሰን ጥር ቀን ዓም የደረሱበት ስምምነትም የአውራሹን ኑዛዜ የሚያስቀይር ይዘት ስለሌለው ተጠሪዎቹ ላቀረቡት ክስ በምክንያትነት ሊጠቀስ የሚገባው አይሆንም ኛ እና ኛ አመልካቾች በነዛዜ አገኘነው ያሉትን ቤት በተመለከተ ደግሞ የአሁኑ ተጠሪዎች ባቀረቡት ክስ ተለይቶ ክስ ያልቀረበበትና የሥር ፍቤትም ይህን አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ ባለመኖሩ በግራ ቀኙ የተደገው ክርክር አግባብነት የለውም በመሆኑም ኛ አመልካች በህይወት ዘመናቸው ክርክር ያስነሳውን ቤት የመገልገል በኑዛዜ የተሰጣቸውን መብት ወራሾች ሊያሳጡዋቸው የሚችሉበት ምክንያት ባለመኖሩ ተጠሪዎች የውርስ ንብረት የሆነው ቤት ተሽጦ ገንዘቡን ወራሾች እንድንከፋፈለው በማለት ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለውም የሥር ፍቤቶች የሰጡት ቤቱ ተሽጦ ገንዘቡ ወራሾች እንዲከፋፈሉት የሚለው ውሳኔም የኛ አመልካችን በቤቱ የመገልገል መብትና የወራሾቹን ኛ አመልካች በህይወት እያሉ ቤቱን ያለመሸጥ ግዴታ የጣሰና መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ስለተገኘ የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ የፌመደፍቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔና የፌከፍቤት በመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽረዋል አቶ ስዩም አየለ ኛ አመልካች በቤቱ ውስጥ መኖር አንዳይከላከሉ አሳቸው በህይወት እያሉ ቤቱ ሸጨ ልካፈል ማለት አይቻልም በማለት የተናዘዙ በመሆኑ በወረዳ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥሩ የሆነው ቤት አማሆይ ወይንሸት አድማሱ በህይወት እያሉ መሸጥ የለበትም በማለት ወስነናልይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ ዐ ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም አመልካች ተስፋዬ አርጋው ጠበቃ አቶ ጎበና እጅጉ ቀረቡ ተጠሪዎች ጠጅቱ አርጋው ቀረቡ በለጠ አርጋው ቀረቡ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ ለሰበር የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ዐ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት ሐምሌ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው አቤቱታ ስለጠየቀ ነው ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው በምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛው ፍርድ ቤት አመልካች በከሳሽነት ቀርቦ አባታችን አቶ አራጋው ሀብቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል አባቴ በሕይወት እያለ ግንቦት ዐ ቀን ኑዛዜ ያደረገ ስለመሆን ኑዛዜውም ግንቦት ቀን ዐ ዓም በመናገሻ አውራጃ ፍርድ ቤት ፀድቋል አባቴ ለእኔ በኑዛኔ የሰጠኝ ንብረት በተከሣሾች እና ለእኔ ደግሞ እንጀራ እናቴ የሆነችው ወሮ አስካለ ኃይለማርያም ጋር የጋራ ንብረት በመሆኑ የእኔና የጌታቸው አራጋው ድርሻ ንብረቱ ለሶስት ተከፍሉ እንዲያካፍሉኝ እና በገንዘብ ያገኙትን ጥቅም እንዲከፍሉ ውሣኔ ይሰጥልኝ በማለት በተጠሪዎች ላይ ክስ አቅርቧል ተጠሪዎች በበኩላቸው የወሮ አስካለ ሀይለማርያም ልጆች መሆናቸውን ገልፀው ቤቱን በማከራየት ያገኘነው ጥቅም የለም ቤቱ በባለሙያ ይገመት የሚሉና ሌሎች የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ አቅርበው ተከራክረዋል ፍርድ ቤቱ በአዲስ አለም ከተማ ቁጥሩ ዐ የሆነው ቤት እንዲገመት ትእዛዝ ሰጥቶ የቤቱ ግምት ሀምሣ አንድ ሺ ስምንት መቶ አርባ ስድስት ብር ከሰባ አራት ሣንቲም መሆኑን የባለሙያ አስተያየት ቀርቧል ፍርድ ቤቱም የአሁን አመልካች ውርሱ ለሶስት ተከፍሉ የአሱንና የወንድሙ ጌታቸው አራጋው ድርሻ እንደሚወስድና የተጠሪዎች ድርሻ ብር አስራ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ሰማኒያ ሁለት ብር ከአስራ ስድስት ሣንቲም በመክፈል ቤቱን በኑዛዜው መሠረት በግሉ እንዲያደርግ በማለት ወስኗል በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ተጠሪዎች ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ አቅርበው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የአመልካችንና የተጠሪዎችን የይግባኝ ክርክር ከሰማ በሏላ ተጠሪዎች የንብረቱ ግማሽ ዋጋ ማለት ሀያ አምስት ሺ ዘጠኝ መቶ ፃያ ሶስት ከፃያ አራት ሣንቲም መሆኑን ከገለፀ በኋላ ተጠሪዎች የአመልካችን ድርሻ ብር ፃያ አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ፃያ ሦስት ብር ከአርባ ሳንቲም ከፍለው ቤቱን እንዲያስቀሩ ተጠሪዎች ካልቻሉ አመልካች የእነርሱን ድርሻ ከፍሉ እንዲያስቀር ይህ ካልሆነ በጨረታ ተሸጦ ግማሹን አመልካች ግማሹን ተጠሪዎች እንዲወስዱ በማለት የከፍተኛው ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሣኔ በማሻሻል ውሣኔ ሰጥቷል አመልካች ይህንን ፍርድ በመቃወም ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበ ቢሆንም መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለም ተብሎ አቤቱታው በሰበር ችሎቱ ውድቅ ሆኗል አመልካች ይህ ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት ቤቱና ቦታው በአይነት ለመከፋፈል የሚችል ንብረት በመሆኑ በአይነት እንድንከፋፈል እንዲወስንልን ይህ የማይሆን ከሆነ በሀራጅ ተሸጦ እንድንከፋፈል መወሰን ሲገባው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት የቤቱ ግምት ግማሽ ዋጋ ብቻ ተጠሪዎች ከፍለው ቤቱን እንዲወስዱ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ ይታረምልኝ በማለት ያመለከተ ሲሆን ተጠሪዎች በበኩላችን በቤቱ ላይ ወጭ አውጥተናል ቤቱን በአይነት መካፈል አይቻልም ቤቱን የያዝነው አኛ ስለሆንን ለአኛ ቅድሚያ መስጠቱ ተገቢ ነው የሚል መልስ የሰጡ ሲሆን አመልካች የመልስ መልስ አቅርበዋል ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር የተደረገው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም ጉዳዩን መርምረናል ጉዳዩን እንደመረመርነው ክርክር የተነሣበት ንብረት የሟች አቶ አራጋው ሀብቱና የሟች የወሮ አስካለ ሀይለማርያም በባልና ሚስትነት ያፈሩት የጋራ ሀብት እንደሆነ አመልካችና ተጠሪዎች አልተካካዱም እንደዚሁም የሟች አቶ አራጋው ወራሽ አመልካቿ የሟች የወሮ አስካለ ወራሾች ደግሞ ተጠሪዎች መሆናቸው በግራ ቀኙ የታመነ ጉዳይ ነው ስለሆነም ሟች አቶ አራጋው በቤቱ ላይ ያላቸው የጋራ ባለቤትነት መብት ለአመልካች ሟች ወሮ አስካለ በቤቱ ላይ ያላት የጋራ ባለቤትነት መብት ደግሞ ለተጠሪዎች በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይተላለፋል ከላይ ከተጠቀሰው የሕግ ድንጋጌ መሠረትም አመልካችና ተጠሪዎች የቤቱ የጋራ ባለሀብቶች ናቸው የጋራ ሀብት የሆነ ንብረት በአይነት መከፋፈል የሚቻል በሆነ ጊዜ የጋራ ባለሀብቶቹ በአይነት ሊከፋፈሉት አንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የሚደነግግ በመሆኑ የመጀመሪያው አማራጭ ንብረቷ በአይነት የሚከፋፈል ከሆነ አመልካች አና ተጠሪዎች ቤቱንና ቦታውን እኩል ለሁለት እንዲከፋፈሉት ማድረግ ነው በዚህ አንፃር የሥር ፍርድ ቤቶች ይህንን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚችል አማራጭ ያለፉ በመሆኑ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሰርተዋል ንብረቱ በአይነት ለመከፋፈል የሚያስቸግር ከሆነ በግልጽ ጨረታ ወጥቶ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሸጥና አመልካችና ተጠሪዎች እኩል መካፈል ይገባቸዋል የቤቱን ዋጋ ክፍያ አስቀራለሁ የሚል ወገን ካለ መክፈል የሚገባው ቤቱ በሀራጅ ያወጣውን የገበያ ዋጋ ግምት እንጂ በመሐንዲስ የተገመተውን ዋጋ አይደለም ስለሆነም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ከላይ የተገለጹትን ግልጽ የሕግ ድንጋጌዎች በመተላለፍ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሻሽሏል ይፃፍ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉሎት በመዝገብ ቁጥር ዐ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ ክርክር የተነሳበት ቤት በአይነት ለመከፋፈል የማይቻል ከሆነ አመልካችና ተጠሪዎች ንብረቱንና ቦታውን እኩል ይካፈሉ ብለናል ንብረቱ ለመከፋፈል የማይቻል ካልሆነና አመልካችና ተጠሪዎች በገበያ ዋጋ አንዳቸው የሌላውን ድርሻ ከፍለው ንብረቱን ለማስቀረት ያልተስማሙ እንደሆነ ንብረቱ በሀራጅ ተሸጦ የንብረቱን ዋጋ ግማሽ አመልካች ቀሪውን ግማሽ ደግሞ ተጠሪዎች ይውሰዱ ብለናል በዚህ ፍርድ ቤት ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል ይህ ፍርድ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ሠልጣን አባተማም አመልካች ወሮ ባዮሽ ደጀኔ ከጠበቃ ዳኛቸው ተስፋዬ ጋር ቀረበች ተጠሪዎች ወሮ ፃሳብ ከፋይ ጌራወርቅ ቀረበች ደረጀ ጌራወርቅ አልቀረበም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ ኑዛዜን መሠረት በማድረግ የቀረበውን ክርክር የሚመለከት ነው ከመዝገቡ እንደሚታየው ክርክሩ በተጀመረበት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመጀመያ ደረጃ ፍቤት የአሁንዋ አመልካች ሟች አቶ ጌራወርቅ ህሩይ ባለቤትዋ አድርገውት ያለፉት ኑዛዜ መሠረት ተደርጐ የወራሽነት ማስረጃ ይሰጣት ዘንድ በመጠየቅዋ ፍቤቱም ጥያቄዋን በመቀጠል የኑዛዜ ወራሽነት በማለት ማስረጃውን ሰጥቶአት ነበር በሌላ በኩል ደግሞ የአሁኖቹ ተጠሪዎች ማስረጃው መሰጠት አልነበረበትም በማለት መቃወሚያ በማቅረባቸው ናቤቱ ጉዳዮን በድጋሚ ያየ ሲሆን በመጨረሻም ሟች አድርገውታል የተባለውን ኑዛዜ ከፊሉን በመሻር የተወሰነውን ክፍሉን ደግሞ በማጽደቅ ወስኖአል በዚህ ላይ ከአሁንዋ አመልካች ይግባኝ የቀረበላቸው ይግባኝ ሰሚ ፍቤቶችም ውሳኔው ጉድለት የለውም ብለዋል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው አኛም አመልካች ነሐሴ ቀን ዓም በጻፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ጉዳዮን ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሳኔ አና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከላይ እደተመለከተው ክርክሩ ሊነሳ የቻለው ሟች አደረገው የተባለው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል የሚል ክስ በመቅረቡ ሳይሆን የፍብ ሕግ ቁ ኑዛዜውን መሠረት በማድረግ የወራሽነት ማስረጃ የምስክር ወረቀት ይሰጠኝ የፍብሕግ ቁ በማለት አመልካች ጥያቄ በማቅረብዋ ነው በፍትሐብሔር ሕጉ በግልጽ እንደተመለከተው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል በሚል የሚቀርበው ክስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ከሚቀርበው ጥያቄ አቤቱታ የተለየ ነው ጥያቄዎቹ የተለያዩ በመሆናቸውም የተለያዩ ውጤት ነው ያላቸው በፍሥሥሕግ ቁ እንደተደነገገው ወራሽነኝ የሚል ማንኛውም ሰው የወራሽነት ምስክር ወረቀት ይሰጠው ዘንድ ለፍቤት ሊያመለክት ይችላል ፍቤቱም ጥያቄውን ከመቀበሉ በፊት ጠያቂው ማስረጃዎቹን ሁሉ እንዲያቀርብ በማድረግ እና አስፈላጊ መስሎ የታየውን ዋስትና እንዲሰጥ በማስገደድ ጭምር ዋስትናውን ካገኘ በኋላ የተጠየቀውን የምስክር ወረቀት ሊሰጥ እንደሚችል በፍብሕግ ቁ ተመልክቶአል በሌላ በኩል ደግሞ ፍቤቱ የአመልካቹን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ሰጥቶት የነበረው የወራሽነት የምስክር ወረቀት ሊሰረዝው እንደሚችል በፍብሕግ ቁ የተቀመጠው ድንጋጌ ያመለክታል ከዚህ አንግዲህ መገንዘብ እንደሚቻለው የምስክር ወረቀቱ በጠያቂው አቤቱታ መነሻነት የሚሰጥ ቢሆንም የተሰጠው ያለአግባብ ነው የሚል መቃወሚያ ሊቀርብ የሚችልበት ሁፄታ መኖሩንና መቃወሚያው ተገቢ ሆኖ ከተገኘም የምስክር ወረቀቱ የሚሰረዝ መሆኑን ነው ወደ ያዝነው ጉዳይ ስንመለስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት አንዲሰጥ ጥያቄ የቀረበበት ፍቤት ጥያቄውን ተቀብሎ የምስክር ወረቀቱን ሰጥቶ እንደነበር አእንመለከታለን ይህም በፍብሕግ ቁ የተመለከተውን ድንጋጌ ተከትሎ የተፈጸመ በመሆኑ ትክክል ነው ሌላው ቀጥለን የምናየው ተጠሪዎች የተሰጠውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት በመቃወም መቅረባቸው ሲሆን ፍቤቱም መቃወሚያውን መሠረት በማድረግ ለምስክር ወረቀቱ መሰጠት መሠረት የሆነውን ኑዛዜ ይዘት እና ሕጋዊነትን መርምሮአል በመጨረሻም ኑዛዜውን በከፊል በመሻር በከፊል ደግሞ አጽድቄአለሁ ብሎአል በበኩላችን ትክክለኛ አካፄድ ሆኖ ያላገኘነውም ይኸው ነው በመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቱ በሕጉ የተቀመጠውን ድንጋጌ መሠረት በማድረግ ኑዛዜው ፈራሽ ነው እንዲባል ክስ አልቀረበለትም የፍቤቱ የዳኝነት ስልጣን የተወሰነ በመሆኑ በስልጣን ክልሉ ስር የሚወድቀውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ነው ጥያቄ የቀረበለት ይህን ጥያቄ ተቀብሎ ሰጥቶት የነበረው የምስክር ወረቀት ተጠሪዎች ካቀረቡለት መቃወሚያ አንጻር ሲመዝነው ተገቢ አልነበረም የሚል ድምዳሜ ከደረሰም በፍብሕግ ቁ በተደነገገው መሠረት መሠረዝ ነው የነበረበት ከዚህ አልፎ ኑዛዜው ፈራሽ ይባል በሚል ክስ በቀረበ ጊዜ ሊደረግ አንደሚችለው ሁሉ ኑዛዜውን በከፊል ሽሬአለሁ ማለቱ ትክክል አይደለም የሕግ መሠረትም የለውም ከሁሉ በላይ ደግሞ ፍቤቱ ወደ ኑዛዜው ይዘት እአና ሕጋዊነት ሁኔታ ገብቶ ውሳኔ መስጠት የሚችልበት ሕጋዊ መንገድ አልነበረውም እንጂ ሕጋዊ መንገድ ነበረው ተብሉም ቢሆን ኖሮ የደረሰበት መደምደሚያ የኑዛዜ ፎርም አና ማስረጃ ከሚመለከተው ሕግ አንፃር ሊታይ ፍጹም የተሳሳተ ነው ለክርክሩ መነሻ የሆነው ነዛዜ በግልጽ የተደረገ ነዛዜ እንደሆነ በፍቤቱ ውሳኔ ተመልክቶአል በግልጽ የተደረገ ኑዛዜ ሊያሟላቸው የሚገቡ በፍብሕግቁ የተመለከቱት መስፈርቶች ያሟላ እንደሆነም ፍቤቱ ማረጋገጡን በውሳኔው ላይ አመልክቶአል ይህን ሁሉ ካረጋገጠ በኋላ በከፊል ሽሬዋለሁ ያለው ሟች ንብረቱ ባልሆነው ንብረት ላይ ጭምር ተናኮዞአል በሚለት እንደሆነ ከውሳኔው ይዘት ለመገንዘብ ችለናል በሕጉ በግልጽ እንደተመለከተው በግልጽ የተደረገው ኑዛዜ በሕጉ መሠረት አልተደረገም ተብሉ ሊነቀና የሚችለው በፍብሕግቁ የተቀመጡትን መስፈርቶች ያላሟላ ሆኖ ሲገኝ ነው የስር ፍቤት ኑዛዜውን ለመንቀፍ ምክንያት ያደገው ነጥብ የነዛዜውን ሕጋዊነት በተመለከተ አግባብነት የለውም ተናዛዝ የሱባልሆነው ንብረት ተናዞአል የሚባል ቢሆን የንብረት ክርክር ሲቀርብ እራሱን ችሉ የሚታይ ነው ፍቤቱ ይህን ነጥብ በማድረግ የኑዛዜውን ሕጋዊነት ፎርም መንቀፍ ተገቢ አይደለም የምንለውም በዚህ ምክንያት ነው ሲጠቃለል የስር ፍቤቶች የተጠሪዎችን መቃወሚያ መሠረት በማድረግ የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለት ሆኖ አግኝተነዋል ውሳኔ አቤቱታ የቀረበበት በድሬዳዋ ጊዜያዊ አስተዳደር የድሬዳዋ ከተማ የመጀመያ ደረጃ ፍቤት በመቁ የካቲት ቀን ዓም ተሰጥቶ በይባኝ ሰሚሜው ፍቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም በተሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሳኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽሮአል ቀደም ሲል ለአመልካች የተሰጠው የወራሽነት የምሰክር ወረቀት የሚሰረዝበት የሕግ ምከንያት የለም ብለናል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኙ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ፀመ የሰበር መቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አቶ ዓሊ መሐመድ አቶ ፀጋዬ አስማማው አቶ አልማው ወሌ አመልካች ወሮ አቦነሽ ምትኩ ቀረቡ ተጠሪ እነ አቶ አዳነ ፎላ ምስት ሠዎች አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዮ የተጀመረው በአለታ ወንዶ ወረዳ ፍቤት ሲሆን የአሁኗ አመልካች በዚህ ፍቤት የአቶ ንጋቱ ምትኩ ወራሽነት ተረጋግጦ ማስረጃ እንዲሠጣቸው አመልክተው ተቃዋሚ ካለ እንዲቀርብ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጐ የአሁኑ ተጠሪዎች ቀርበው አለን ያሉትን የተቃውሞ ክርክር ከአቀረቡ በላ ፍቤቱ አመልካች የሟች ወንድሟ ወራሽ መሆናቸውን በማረጋገጥ ማስረጃ ሠጥቷቸዋል ይህ የአመልካች የወራሽነት ማስረጃ የተሠጣቸው መስከረም ቀን ዓም ሲሆን ይህንኑ ማስረጃ አመልካች ከያዙ በኋላ ተጠሪዎች ላይ ህዳር ቀን ዓም ክስ መስርተዋል የክሱ ይዘትም ንብረትነቱ የሟች ወንድሜ የአቶ ንጋቱ ምትኩ የሆነውንና በአለታ ወንዶ ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን ቁጥሩ የሆነውን ቤት ተጠሪዎች ይዘው የሚጠቀሙበት ለመሆኑ ለቀው እንዲያስረክቡ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን ያሣያል የአሁነ ተጠሪዎችም በተከሣሽነታቸው ቀርበው ጥር ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ የመከላከያ መልሣቸውን አቅርበዋል ይዘቱም በአጭሩ የከሣሽ ክስ በፍሕቁ መሠረት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ንብረቱ በሟች እናት በኩል የመጣ በመሆነ ከሣሽ ከፍሕቁ ለ አኳያ የመውረስ መብት እንደሌላቸው ቤቱ ለሟች ንጋቱ ምትኩ እናት የሆኑት ወሮ የሺ ወንድሙ የተከሣሾች እናት ለሆኑት እህታቸው ለወሮ ፀሐይ ገኪዳን በስጦታ አስተላልፈው ሰጥተው ስጦታ ተቀባይ እስከ ዓም ድረስ በእጃቸው አድርገው ሲጠቀሙበት ቆይተው ከዚህ አለም በሞት ሲለዮ የአሁነ ኛ ተጠሪ የወሮ ፀሐይ ገኪዳን ወራሽነታቸውን በማረጋገጥ ቤቱን በእጃቸው ማድረጋቸውንና ከሣሽ በቤቱ ላይ አንዳችም መብት የሌላቸው መሆኑን በመዘርዘር ክሱ ውድቅ ሊሆን ይገባል በማለት መከራከራቸውን የሚያሣይ ነው ጉዳዮን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው የወረዳ ፍቤትም የይርጋ ክርክሩን በተመለከተ ከሣሽ እንዲለቀቅላት የጠየቀችው በዘር የመጣውን የውርስ ንብረት ስለሆነ የመብት ጥያቄዋ በፍሕቁ መሠረት በይርጋ አይታገድም ንብረቱ በእናት በኩል የመጣ ስላልሆነ መውረስ አትችልም የተባለውን በተመለከተም ወራሽነቷን አረጋግጣ መብት የላትም ተብሎ የተወሰነ በመሆኑና የቀረበ ተቃውሞም ስለሌለ ተቀባይነት የለውም በማለት የውርስ ንብረቱ እንዲጣራ ሲል ወስኗል በዚህ የፍቤቱ ውሣኔ የአሁኑ ተጠሪዎች ባለመስማማት ይግባኛቸውን ለሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው ፍቤቱም ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ ለጉዳዮ አግባብነት ያለው የፍሕቁ ስር የተመለከተው የይርጋ ጊዜ መሆኑን በመጥቀስ የአመልካች አቤቱታ የወራሽነት ማስረጃውን ከያዙ አምስት ዓመታት ያህል ቆይቶ የቀረበ በመሆነ በፍሕቁ ስር በተመለከተው የሦስት ዓመት ይርጋ ቀሪ ሊሆን የሚገባው ነው በማለት የወረዳውን ፍቤት ውሣኔ ሽሮታል የአሁኗ አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ለክልሉ ጠፍቤት ይግባኝ እና ሠበር ሠሚ ችሎቶች ቅሬታቸውን ቢያቀርቡም ተቀባይነት ሣያገኙ ቀርተዋል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ የበታች ፍቤቶች ውሣኔ ባለመስማማት ለማስለወጥ ነው አመልካች ታህሣስ ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት ሦስት ገጽ የሠበር አቤቱታ ጉዳዮ የመፋለም ክስ ሆኖ እያለ እና ከውርስ ክርክር ጋር የሚያገናኘው ነገር ሣይኖር በጉዳዮ ላይ የቀረበውን ክርክርና ማስረጃ ባላገናዘበ መልኩ አግባብነት የሌለውን ድንጋጌ በመጥቀስ ውሣኔ መስጠቱ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ይኸው ታርሞ ተጠሪዎች ቤቱን እንዲያስረክቡ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል የአመልካች አቤቱታ ተመርምሮ ተጠሪዎችን ያስቀርባል ተብሎ ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ መልሣቸውን አቅርበዋል አመልካችም በዚህ የተጠሪዎች መልስ ነሐሴ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ የመልስ መልስ ሠጥተዋል የጉዳዮ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን ችሎቱም ይህንኑ አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መርምሮታል አንደመረመረውም የአመልካች ክስ የፍሕቁ ተጠቅሶ ውድቅ መደረጉ ባግባቡ ነው። የሚለውን ጭብጥ የስር ፍቤት ሊወስነው የሚገባ በመሆኑ በዚሁ ነጥብ ጉዳዮ ሊመለስለት የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል ሲጠቃለልም ከላይ የተገለፁት ምክንያቶች መሠረት የሚከተለው ተወስኗል ውሳኔ የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በፍመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሠጠውን ውሳኔ የደብብሕ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍቤት በፍይመቁ ጥር ቀን ዓም የሠጠውን ትአዛዝ የጠቅላይ ፍቤቱ ሠበር ሠሚ ችሎት በመቁ ህዳር ቀን ዓም የሠጠውን ውሣኔ በፍሥሥሕቁ መሠረት ሽረነዋል የአለታ ወንዶ ፍቤት የሠጠውን የይርጋንና የውርስ ማጣራት ብይን በተለወጠ ምክንያት በአብላጫ ድምጽ ሽረነዋል ለጉዳዮ ተፈፃሚነት ያለው የይርጋ ገደብ በፍሕቁ ስር የተመለከተው የክስር ዓመት ጊዜ በመሆኑ የአመልካች ጥያቄ በይርጋ ቀሪ አይሆንም ብለናል ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት የማን እንደሆነ የግራ ቀኙን ማስረጃዎችን በመመርመር ተገቢውን ውሣኔ ይሰጥበት ዘንድ ለአለታ ወንዶ ወረዳ ፍቤት በፍብሥሥሕቁ መሠረት መልሰንለታል ይፃፍ ወጪና ኪሣራ የየራሣቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መቤት ይመለስ የማይነበብ የአራት ዳኞች ፊርማ አለበት የሀሳብ ልዮነት አኔ ስሜ በሶስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰው ዳኛ አብላጫው ድምጽ በደረሰበት መደምደሚያ ላይ የምስማማ ቢሆንም አብላጫው ድምጽ የፍታብሔር ህግ ቁጥር የይርጋ ድንጋጌ በሁለት ወራሾች መካከል ያለን ክርክር ለመፍታት ነው የሚያገለግለው በሚለው የህግ አተረጓጐም ተገቢ አይደለም የሚል ሀሳብ ስላለኝ ይህንን ልዮነት ለመፃፍ ተገድጃለሁ የፍታብሔር ሕግ ቁጥር የይርጋ ድንጋጌ በወራሾች መካከል ለሚደረግ ክርክር ሣይሆን አውነተኛ የሟች ወራሽ በሆነ ሰውና የሟች ወራሽ ባልሆነ ሰው መካከል የሚያገለግል ስለመሆኑ ከፍታብሔር ህግ ቁጥር እስከ ፍታብሔር ህግ ቁጥር ድንጋጌዎች አቀራረጽና ይዘት በማየት ለመረዳት ይቻላል ህግ አውጭ የሟች የኑዛዜ ወይም ያለ ኑዛዜ ወራሽነኝ በማለት በፍታብሔር ህግ ቁጥር መሠረት የወራሽነት የምስክር ወረቀት ያወጣ ሰው እውነተኛው የሟች ወራሽ የወራሽነት ጥያቄ ሲያቀርብ የተሰጠው የወራሽነት የምስክር ወረቀት ፍርድ ቤቱ ለመሰረዝ አንደሚችል የፍታብሔር ህግ ቁጥር ይደነግጋል የወራሽነት ጥያቄ በማንና እንዴት ሊቀርብ እንደሚችል የተደነገገው ፍታብሔር ሕህ ቁጥር ነው ስለዚህ አንድ ሰው አውነተኛ የሟች ወራሽ ሣይሆን የወራሽነት ሰርተፍኬት በመያዝ የሟችን ንብረት ከወሰደ አውነተኛው ወራሽ የአሱን ወራሽነት እንደታወቀለትና የውርስ ንብረቱም አንዲመለስለት የሚያቀርበው ክስና የክሱ ማቅረቢያ ጊዜ በፍታብሔር ህግ ቁጥር እና ከፍታብሔር ህግ ቁጥር ተደንግጓል አውነተኛ ወራሽ በሆነው ሰውና አውነተኛ ወራሽ ባልሆነ ሰው መካከል የሚደረግ ክርክር በሟች ወራሾችና ወራሽ ባልሆነ ሌላ ሰው መካከል የሚደረግ ክርክር ነው ስለሆነም የፍታብሔር ህግ ቁጥር የሚያገለግለው በሟች ወራሾች መካከል ለሚደረግ ክርክር የሚሠራ አይደለም የሟች ወራሽ ለመሆን የግድ የወራሽነት ሰርተፍኬት መያዝ አያስፈልግም የሟች የኑዛዜ ወይም የህግ ወራሽ መሆኑን ቢውርስ አጣሪ በኩል ለማረጋገጥ አንደሚቻል የውርስ ህግ ድንጋጌዎችን ለማየት ለመረዳት ይቻላል በወራሽነት መካከል የሚነሣው ክርክር የድርሻ ጉዳይ ሲሆን አሱም በፍታብሔር ህግ ቁጥር መሠረት የሚታይ ነው ስለዚህ የፍታብሔር ህግ ቁጥር በወራሾሽ መካከል ላይ ክርክር ነው የሚለው አተረጓጐም ካለመስማማት ይህንን የሀሳብ ልዮነት ጽፌአለሁ የማይነበብ የአንድ ዳኛ ፊርማ አለበት ፀመ የሰመቁ ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ አመልካች ወሮ ዘነበወርቅ ወልዱ ፀጋ ወኪል አስክንድር ወልዱ ቀረቡ ተጠሪዎች እማሆይ ድብቅነሽ ግዛው ወሮ አዳነች ወልዱ ፀጋ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ በውርስ ንብረት ክፍፍል ላይ የተነሳውን ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ ሲጀመር ከሳሽ የነበረችው የአሁንዋ አመልካች ስትሆን በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሰረተችው ይዘውት ከሚገኘው የውርስ ንብረት ላይ ድርሻዋን እንዲያካፍሉአት ነው የውርስ ንብረት የተባሉት በአዲስ አበባ ከተማ እና በደሴ የሚገኙ ሁለት ቤቶች እንደሆኑም ተገልፆአል ክሱ የቀረበለት የደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤትም ወደ ክሱ ስረ ነገር ከመግባቱ በፊት አዲስ አበባ ከተማ ይገኛል በተባለው ቤት ላይ የዳኝነት ስልጣን የለኝም ማስተናገድ የምችለው ደሴ ከተማ ውስጥ የሚገኘውን ቤት በሚመለከት የሚቀርበውን ክስ ነው በማለት መዝገቡን ዘግቶአል በዚህ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የአማራ ብክመጠፍቤትም የግዛት ክልል ስልጣን የለኝም በሚል በሚሰጥ ትአዛዝ ላይ ይግባኝ ሊቀርብ አይችልም የሚል ምክንያት በመስጠት ይግባኙን ሳያስተናግድ ቀርቶአል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው አኛም አመልካች ሕዳር ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሰረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው ለሰበር ችሎት አንዲቀርብ የተወሰነው አመልካች ለደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ያቀረበችው የውርስ ንብረት ክፍፍል የሚመለከተው ክስ በግዛት ክልል የዳኝነት ስልጣን ምክንያት አይስተናገድም የመባሉን አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሰረትም ይህን ነጥብ ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክርአቤቱታ ከቀረበበት ትእዛዝ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር መገዝብ እንደቻልነው አመልካች እና ኛ ተጠሪ የሟች አቶ ወልዱ ፀጋ ልጆች ሲሆኑ ኛ ተጠሪ ደግሞ የሟቹ ሚስት ናቸው ሟች ይኖሩ የነበሩት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን አንደሆነና የሞቱትም በዚሁ ቦታ ስለመሆኑ በክርክሩ ተመልክቶአል ከዚህም በተጨማሪ ተጠሪዎች ሟች በኖሩበትና በሞቱበት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን በደሴ ወረዳ ፍቤት የውርስ ንብረት ክፍፍል ጥያቄ ማቅረባቸውን ከቀረበው ክርክር ተመልክተናል እንደምናየው ጉዳዩ የውርስ ንብረት ክፍፍል የሚመለከት ነው አመልካች በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሰረተችው የውርስ ሃብት ነው ከተባለው ንብረት ላይ ድርሻዋን ለማግኘት ነው በአጠቃላይ ክርክሩ የፍትሐብሔር እንደመሆኑ የሚመራው በፍትሐብሔር ስነ ስርአት ሕግ መሰረት ነው በግዛት ክልል ስለሚወሰን የዳኝነት ስልጣን በተመለከተ በስነ ስርዓት ሕጉ አንደኛ መጽሐፍ በምአራፍ ስር ካሉት ድንጋጌዎች ውስጥ በቁ የተመለከተውም ለጉዳዩ አወሳሰን ተገቢነት ያለው ነው ይህ ድንጋጌ በውርስ ምክንያት የሚቀርብን ክስ የሚታይበትን ቦታ የሚወሰን ነው ክሱ መቅረብ ያለበት ወይም የሚቀርበው የውርሱ ክፍያ በተጀመረበት ቦታ ለሚገኘው ፍናቤት እንደሆነም ያመለክታል ሕጉ ይህን ያህል ግልጽ ከሆነ ደግሞ የውርስ ፃብት የሆኑ ንብርቶች በተለያዩ ቦታዎች የሚኖራቸው ጉዳይ እግምት ውጥስ የሚገባ አይደለም አቤቱታ የቀረበበት ትእዛዝ ከዚህ አንጽር ሲታይም የሕግ መሰረት ያለው አይደለም ይልቁንም መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ነው ያገኘነው ስለዚህም የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በአማራ ብሔራዊ ክመደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም ተሰጥቶ የክልሉ ጠፍቤት በመቁ መስከረም ቀን ዓም በሰጠው ትአዛዝ ይግባኝ አይባልበትም የተባለው ትእዛዝ በፍብሥሥሕግ ቁ መሰረት ተሽሮአል አመልካች ያረበችው የውርስ ክፍፍል ክስ መታየት ያለበት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ፍቤት በመሆኑ ፍቤቱ ክሱን በማስተናገድ በበኩሉ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ ይስጥበት ብለናል ጉዳዩ ይመለስለት ይፃዓና ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መ ቁ ጥቅምት ቀን ዒም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጉስ ወልዱ መስፍን ዕቁበዮናስ ሂሩት መለሰ አመልካች ወሮ የኋላሸት ተካ ወኪል የ አለቃ ፈጠነ ካሣሁን ቀረቡ ተጠሪ የለም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ነው ጉዳዩ ሊጀመር የቻለው የአሁንዋ አመልካች የወራሽነት የምስክር ወረቀት ይሰጣት ዘንድ በመጠየቅዋ ነው ጥያቄው የቀረበለት ፍቤት የወራሽነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ይሰጥ ዘንድ ጥያቄው መቅረብ ያለበት አውራሽ ነው በተባለው ሰው የመኖሪያ አድራሻ ለሚገ ው ፍቤት ነው የሟች የመኖሪያ አድራሻ አዲሰ አበባ ባለመሆኑም ፍቤቱ ጥያቄውን ማስተናገድ አይችልም በማለት ጥያቄውን ውድቅ አድርጉአል የከተማው አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍቤት እና የሰበር ችሉትም የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቱ የሰጠውን ውሣኔ አጽንተዋል አቤቱታው የቀረበውም በዚሁ ላይ ነው እኛም አመልካች መጋቢት ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችው አቤቱታ የስር ፍቤቶች ከሰጡት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል አመልካች ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ያመለከተችው የወላጅ አባትዋ ተካ ግዛው ወራሽ መሆንዋ ተረጋግጦ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጣት ነው በማመልከቻዋ ላይም የአባትዋ መኖሪያ ስፍራ የነበረው አዲስ አበባ መሆኑ ብትገልጽም በዚህ ረገድ ያቀረበቻቸው ምስክርችዋ ግን ሟች ይኖር የነበረው ከአዲስ አበባ ውጪ አላባ በተባለ ሥፍራ እንደሆነ ነው ያስረዱት ጥያቄው የቀረበለት ፍቤትም ይህንኑ ሁኔታ በፍብሕግ ቁ ከተመለከተው ድንጋጌ ጋር በማገናዘብ ውሣኔ ሰጥቶአል ፍቤቱ ለውሣኔው መሠረት ያደረገው የፍብሕግ ቁፋ የማገው በፍትሐብሔር ሕጉ በሁለተኛው መጽሐፍ« ስለውርስስለአወራረስ» በሚለው በአንቀጽ አምስት ሥር ነው የተያዘው ጉዳይም ውርስን ወይም አወራረስን የሚመለከት ነው ቁ በግልጽ የሚያመለክተው አንድ ሰው የሞተ እንደሆነ በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ በሆነበት ቦታ ውርሱ እንደሜከፈት ነው ይህ ድንጋጌ በመሠረታዊው ሕግ በከፎ ህህ ውሰጥ የሚገኝ ሲሆን ኛ የፍትሐብሔር ክርክሮች የሚመሩበትን የሥነ ሥርዓት ደንቦች በያዘው የፍትሐብሔር ሕግ ውስጥ የሚገ ው ቁም እንደዚሁ ተመሣሣይ ነገር ነው የሚሜናገረው ድንጋጌው በውርስ ምክንያት ስለሚቀርብ ክስ የሚል ርእስ ያለው ሆኖ ክሱ የሚቀርበው የውርሱ ክፍያ በተጀመረበት ቦታ ለማገ ው ፍቤት እንደሆነ ያመለክታል ከፍ ሲል እንደተገለፀውም የውርሱ ክፍያ የሚጀመረው ሟች በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ በሆነበት ቦታ ነው የአመልካች አባት በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ አዲስ አበባ አልነበረም ከዚህ የተነሣም ፍቤቱ ጥያቄው መቅረብ ያለበት ሟች በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ በሆነበት ቦታ ላለው ፍቤት ነው በማለት ወስኖአል በበኩላችንም እንደምናየው ፍቤቱ በዚህ ረገድ የፈፀመው መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለም ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት የሥር ፍቤቶች ውሣኔ ፀንቶአል ጉዳዩ የተወሰነ በመሆኑ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ኸወ የሰመቁ ግንቦት ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ሐጐስ ወልዱ ወት ሂሩት መለሰ አቶ መድሕን ኪሮስ አቶ ሱልጣን አባተማም አመልካች ወሮ አልማዝ ታፈሰ ጠበቃዋ ቀርቧል ተጠሪ ወሮ የሺመቤት ትኩ አልቀረበችም ፍርድ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ጉዳይ የጀመረው በይርጋ አለም ከተማ መደረጃ ፍቤት ነው የአሁኗ አመልካች ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ የአባታቸው ወራሽ በመሆናቸው ንብረት ተጣርቶ ድርሻቸውን ተጠሪ እንዲያካፈሏቸው ጠይቀዋል ተጠሪም ለክሱ በሰጡት መልስ ክሱ በይርጋ ይታገዳል የሚልና ሌሎችም የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ካቀረቡ በኋላ ለጉዳዩ ሙሉ መልስ ሰጥተዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ ያየው ፍቤትም አመልካች ወራሽ መሆናቸውን ካወቁበት ጊዜ ጀምሮ ክስ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ አመት ያለፈው በመሆኑ ክሱ በፍህቁ መሰረት በይርጋ ይታገዳል በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ከዛም ለደብብሕክመጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት አቤቱታ አቅርበው ፍቤቶቹ ይግባኛቸውን ሣይቀበሏቸው ቀርተዋል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ሲሆን ችሎቱ የአመልካች ጥያቄ በፍህቁ መሰረት በይርጋ ይታገዳል መባሉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ አድርጓል ተጠሪም ቀርበው መልስ እንዲሰጡ መጥሪያ ደርሷቸው ባለመቅረባቸው የጽሁፍ መልስ የመስጠት መብታቸው ታልፎ ችሉቱ ጉዳዩን መርምራሯል ከመዝገቡ እና ከክርክሩ እንደተረዳነው የአመልካች አባትና ተጠሪዋ ባልና ሚስት የነበሩ ሲሆን የአመልካች አባት በመሞታቸው ምክንያት አመልካች በወራሽነታቸው የሚገባቸውን የአባታቸውን ድርሻ ተጠሪ እንዲያካፍሏቸው ጠይቀዋል ተጠሪም የአመልካች አባት የሞቱት ሰኔ ሲሆን ክሱ የቀረበው ግን ሐምሌ ቀን ዓም በመሆኑ በፍህቁ መሰረት ክሱ በይርጋ ይታገዳል በማለት ተከራክረዋል በመሆኑም ይህ ተጠሪዋ የሚከራከሩበት ድንጋጌ ለተያዘው ጉዳይ ተፈፃሚነት አለው ወይ። የሜለው ሆኖ ተገኝቷል መልስ ሰጭ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በአቀረበው አቤቱታ የጠየቀው የአባቱ የአቶ ኃይሌ ኃይለማርያም አባት የሆኑት የመምሬ ኃይለማርያም አጉናቸው የውርስ ንብረት ይጣራ ዘንድ የውርስ አጣሪ እንዲቋቋምለት ነው በስር ፍቤቶች የተረጋገጠው የጉዳዩ ፍሬ ነገር በመልስ ሰጭ አባት ከሣሽነት በከፍተኛ ፍቤት ተከፍቶ በነበረው የመቁ ከሣሹ ኃይሌ ኃማርያም የአባት እና የእናቱን ንብረት ከሌሉች እህትና ወንድሞቹ ጋር እንዲከፋፈል ሰኔ ቀን ዓም ተወስኖ እንደነበር ያሳያል እንዲሁም መልስ ሰጭ የአባቱ የኃይሌ ኃማርያም ወራሽ መሆኑን ጥቅምት ዒም በተሰጠ ውሳኔ ማረጋገጡ በውሳኔዎቹ ተመልክቷል አመልካቹ በመዝገብ ቁ ሰኔ ዒም የመምሬ ኃማርያም አጉናቸው ወራሾችተወላጆች ንብረታቸውን እንዲከፋፈሉ የተወሰነ መሆኑን በመጥቀስ ጉዳዩ ፍርድ ያረፈበት ነውና አሁን ውርስ አጣሪ ይሾምልኝ ሊባል አይችልም ሲል ያቀረበው ክርክር በስር ፍርድ ቤቶች ውድቅ የተደረገው ፍርዱ ተወላጆቹ ንብረቱን ለመከፋፈል መብት እንዳላቸው ከሜገልጽ ውጭ ዝርዝር ድርሻቸውን የሚያሳይ አይደለም ንብረቱ በውርስ አጣሪ ተጣርቶ የማይከፋፈልበት ምክንያት አይኖርም በማል ነው በመሰረቱ መልስ ሰጭ የአያቱን የመምሬ ኃይለማርያም አጉናቸውን ንብረት የሚወርሰው አባቱን ተክቶ እንደሆነ ግልጽ ነው አባቱ ኃይሌ ኃማርያም የአባቱን ንብረት ከሌሉቹ ወንድምና እህቶቹ ጋር እንዲከፋፈል በመቁ ሰኔ ዓም የተወሰነለት እንደመሆኑ መልስ ሰጭም በአባቱ ምትክ ለተጠቀሰው ውሳኔ ባለመብት መሆኑ አያከራክርም የአንድ ውሳኔ ባለመብት የሆነ ሰው በፍብሥሥሕጉ መሰረት ያለው መብት ደግሞ ፍርዱ ከተሰጠበት ቀንና ዓመተ ምህረት ጀምሮ በሜቆጠር የአስር ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደፍርዱ እንዲፈፀምለት የመጠየቅ እንደሆነ ከተጠቀሰው ሕግ አንቀጽ ሀ ላይ መረዳት የማቻል ነው በተያዘው ጉዳይ መልስ ሰጭ በሕግ የተወሰነውን የአስር አመት ጊዜ ጠብቆ ሊደርሰኝ የሜገባው የውርስ ንብረት ይኸ ነው ሲል የአፈፃፀም አቤቱታ አላቀረበም ውሳኔው የውርሱን ንብረት ወራሾች እንዴት እንደሜከፋፈሉት ያልዘረዘረ ስለሆነ ግልጽነት ይጉድለዋል መባሉ በዚህ ችሉት እምነት ውሳኔውን ውጤት አልባ የሜያደርገው አይደለም በይግባኝ ሰሚ ፍቤት ያልተሻረ ወይም ያልተሻሻለ ውሳኔ እንደመሆኑ በአለበት ሁኔታ ሊፈፀም የሚገባው ነው ይሁን እንጂ መልስ ሰጭው የውሳኔውን አፈፃፀም በመጠየቅ አቤቱታውን በጊዜው በማቅረብ ፋንታ ለዚህ ክርክር መነሻ የሆነውን የውርስ አጣሪ ይሾምልኝ ጥያቄ አቅርቧል አቤቱታው የቀረበለት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤትም ጉዳዩን ከፍብሥሥሕቁለ እና አኳያ አገናዝቦ ክሱን በመዝጋት ተከራካሪዎቹን ማሰናበት ሲገባው የውርስ አጣሪው እንዲሾም ወስኗል የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ውሳኔውን በተመሳሳይ ምክንያት አጽንቶታል ከፍ ሲል እንደተገለፀው መልስ ሰጭ የውርስ አጣሪ እንዲሾምለት የጠየቀው አስቀድሞ በፍርድ ተወስኖ በአለቀ ጉዳይ ላይ በመሆኑ ክርክሩ ተቀባይነት ሊያገኝ የሚገባው ሆኖ አላገ ነውም ስለሆነም ይህ ችሉት የስር ፍቤቶችን ውሳኔ በፍብሥሥሕ ቁ መሰረት በመሻር የውርስ አጣሪው ሊቋቋም አይገባም በማለት ወስኗል ይፃፍ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ባአ የሰ መ ቁ የካቲት ቀን ዓም ዳኞች አቶ ከማል በድሪ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አመልካች አቶ ህይወት በፍቃዱ ከጠበቃ አቶ በኃይሉ ነገዎ ጋር ቀረቡ መለስ ሰጭ የለውም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ውሣኔ ሰጥተናል ውሣኔ ይህ መዝገብ ተከፍቶ ለዚህ ችሉት የቀረበው የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በይ መ ቁፏ ላይ ጠዓዒጨም በሰጠው ትዕዛዝ አመልካች ቅር በመሰ ቱ የሰበር አቤቱታ ስላቀረበ ነው የሥር አመልካችና የፌ መደ ፍቤት ባቀረቡት ማመልከቻ ሟች እማሆይ ወርቅነሽ ወኪሮስ ማለትም የሥር አንደኛ አመልካች እናት እና የሥር ሁለተኛ አመልካች የነበረው የአሁን አመልካች አያት ባደረጉት ኑዛዜ መሠረት የሟች ወራሾች ነን በማለት በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽቤት በቁ የተመዘገበ ኑዛዜ ፎቶ ኮፒና የሁለት ምስክሮችን ስም ዝርዝር በማቅረብ ኑዛዜው ፀድቆ ማስረጃ ይሰጠኝ በማለት ጠይቀዋል ፍቤቱም ምስክሮች በአቤቱታቸው የገለፁት በሙሉ እውነት እንደሆነ ኑዛዜው በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽቤት በዓም የተደረገ መሆኑንና ሟችም ሲናዘዙ አእምርአቸው ጤነኛ እንደነበረ በመግለጽ ያስረዱትን ከሰማ በኋላ በሰጠው ውሣኔ ሟች አደረጉት የተባለው ኑዛዜ ግልፅ ኑዛዜ ነው ግልፅ ኑዛዜ ከሆነ ደግሞ በፍ ብህ ቁ መሠረት ከምስክርቹ መካከል አንዱ ዳኛ ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሆኖ ኑዛዜውም የተደረገው ከእነዚህ አንደኛው ሥራውን በሜያካድበት ክፍል ውስጥ ከሆነ ለኑዛዜው ዋጋ ማግ ት ሁለት ምስክሮች ብቻ በቂ ናቸው ሟች ተናዘዙ የተባለው ውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽቤት ነው በመሆኑም ከምስክሮቹ መካከል አንዱ ውል የማዋዋል ስልጣን ካለው ሁለት ምስክር በቂ ነው ይሁን እንጂ በያዝነው ጉ ዳይ በምስክርነት የፈረሙት ምስክርች ብዛት ሁለት ሲሆን ሁለቱም ውል የማዋዋልም ሆነ የዳኝነት ስልጣን የላቸውም በፍ ብህ ቁ መሠረት ተናዛኙና ሁለቱም ምስክርች በኑዛዜው ላይ ወድያውኑ ፊርማቸውን ወይም ያውራ ጣት ምልክታቸውን ካላደረጉበት በቀር ፈራሽ ነው ሟች በ አደረጉት በተባለው የኑዛዜ ሰነድ ላይ የሁለት ምስክርች ፊርማ በቂ የሚሆነው ውል የማዋዋል ስልጣን ያለው ሰው ፊርማውን አስቀምጦ ቢሆን ነበር በመሆኑም ሟች አደረጉት የተባለው ኑዛዜ ፈራሽ ነው በሌላ በኩል አንደኛ አመልካች የሟች ልጅ መሆናቸው በምስክሮች ቃል ስለተረጋገጠ በፍብህ ቁ መሠረት የሟች እናታቸው የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ ሲሆኑ የአሁኑ አመልካች ግን እናቱ የስር አንደኛ አመልካች ወር ሰፈፍየለሽ ደሣለኝ በህይወት መኖራቸው ስለተረጋገጠና ከእሱ ቀድመው የወራሽነት መብት ስላላቸው ሕጋዊ ወራሽነነቴ ይረጋገጥልኝ የሚለውን አቤቱታውን አልተቀበልነውም ብሏል የአሁን አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰ ት በፌከፍቤት ይግባኝ ያለ ሲሆን ፍቤቱ ግን የሥር ፍቤት የሰጠው ውሣኔ ጉድለት የለበትም በማለት አመልካች ያቀረበውን ይግባኝ ውድቅ በማድረግ ትዕዛዝ ሰጥቷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም አመልካች በዚህ ትዕዛዝ ቅር በመሰ ት ሲሆን የአቤቱታው ፍሬ ነገር የስር ፍቤት ለሰጠው ውሣኔ ምክንያት ያደረገው ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው በምስክርነት በኑዛዜው ላይ ፊርማውን አላስቀመጠም የሜለውን ነጥብ ነው በፍ ብህ ቁ ላይ እንደተመለከተው ሕጉ በኑዛዜ ላይ ጠንካራ ጥበቃ ያደረገው የተናዛፐች ፈቃድ እንዲከበርና ከማናቸውም የተንኮል ሥራ የፀዳ እንዲሆን ነው ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ሰው ሥራ በሜካሄድበት ክፍል ውስጥ እንዲደረግና ኑዛዜው ዋጋ እንዲኖረው ሁለት ምስክሮች በቂ ናቸው ብሉ ሕጉ የፈቀደው ውል ለማዋዋል ሥልጣን የተሰጠው ባለሥልጣን ተዓማንኒት እንደሚኖረው በመገንዘብ እንደሆነ ይታመናል በተያዘው ጉዳይም ኑዛዜውን ያስፈጸመው ባለሥልጣን በኑዛዜው ጽሁፍ ላይ በምስክርነት ፊርማው ባይኖርም እንኳ የኑዛዜው ጽሁፍ ሙሉ በሙሉ የተናዛኙን ፈቃድ የሚገልጽ መሆኑ አያጠራጥርም ነገር ግን የሥር ፍቤት ኑዛዜው በውል አዋዋዩ ዘንድ የተደረገሻ በፊርማና በማህተም የተረጋገጠ እንደመሆኑ ለኑዛዜው ዋጋ ማግ ት ሁለት ምስክሮች በኑዛዜው ሰነድ ላይ መመልከታቸውና በፊርማም መረጋገጡ በቂ ነው የማለውን የፍብህቁ ድንጋጌ የሥር ፍቤት በአግባቡ ባለመገንዘብ ኑዛዜው በአራት ምስክርች ካልተረጋገጠ በቀር ፈራሽ ነው ያለው ህጋዊነት የጎደለው ነው የኑዛዜው ጽሁፍ በውልና ማስረጃ ጽቤት በቁ ተመዝግቦ የሚገኝና በፍብህ ቁ መሠረት የማስረጃ ነቱ ብቃት በሕግ ተቀባይነት ሊያገኝ ሲገባው ኑዛዜው ፈራሽ ነው መባሉና ይህም በፌከፍቤት መፅናቱ በሥር ፍቤቶች የተሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስሀተት የተፈጸመበት በመሆኑ በዚህ ችሉት ስህተቱ ታርሞ ውሣኔ ይሰጥልኝ የሜል ነው እኛም መዝገቡን መርምረናል እንደመረመርነውም አመልካች ያቀረበው ኑዛዜ ሁለት ምስክሮች የፈረሙበትና በውልና ማስረጃ ጽቤትም የተመዘገበ ሆኖ እያለ ከምስክርቹ አንዱ ውል ለማዋዋል ሥልጣን ያለው ካለሆነ ኑዛዜው ተቀባይነት የለውም መባሉ ተገቢ መሆን አለመሆኑ በጭብጥነት ተይዞ ሊጣራ የማሜገባው ነጥብ ሆኖ አግኝተነዋል በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ ላይ ምስክርች ከሆኑት አንዱ ዳኛ ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን የተሰጠው አካል ከሆኑና ኑዛዜውም የተደረገው እነዚህ ኃላፊዎች ሥራቸውን በሚያከናውኑት ቦታ ከሆነ ኑዛዜው ዋጋ ያገኝ ዘንድ ሁለት ምስክርች ብቻ በቂ እንደሚሆኑ በፍ ብ ሕ ቁ ላይ ተደንግጓል በተያዘው ጉዳይ ሟች እማሆይ ወርቅነሽ ወኪሮስ ጥቅምት ዔም ያደረጉት ኑዛዜ በውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽቤት ተደርጉ በዋና ክፍል ኃላፊ የተፈረመበት እና በማሕተምም የተረጋገጠ መሆኑን እንዲሁም ሌሉቹ ሁለት ምስክርች ሟች ሲናዘዙ አይተውና ኑዛዜውም ተነቦላቸው መፈረማቸውን ጠቅሰው ፊርማቸውን ማኖራቸውን ከጉዳዩ ፍሬ ነገር መረዳት የሜቻል ነው እንዲህ ከሆነ ደግሞ የውል ምዝገባ ዋና ክፍል ኃላፊው ስም በኑዛዜው ላይ በእማኝነት የተጠቀሰ ባይሆንም እማኞቹ እንዳደረጉት ሁሉ የኑዛዜውን መፈጸም በፊርማው አረጋግጧልና እንደ ምስክር ጭምር የማይቆጠርበት ምክንያት አይታይም በዚህ ምክንያት ውል ለማዋዋል ስልጣን የተሰጠው ሰው በምስክርነት ፊርማውን አላስቀመጠምና ኑዛዜው ፈራሽ ሊሆን ይገባዋል በሚል የተሰጠው የስር ፍቤት ውሣኔ ተገቢነት የሌለው ነው በሟች እማሆይ ወርቅነሽ ወኪሮስ የተደረገው ኑዛዜ በፍ ብ ሕ ቁ የተደገፈ በመሆኑም ይህ ችሉት ኑዛዜው ሊፀና ይገባዋል በማለት ወስኗል በዚህም የስር ፍቤቶችን ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ሽርታል ይጻፍ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ኤገ የሰ መ ቁ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ሐጎስ ወልዱ አቶ ተገኔ ጌታነህ አቶ መስፍን እቁበዮናስ ወት ሒሩት መለሠ አመልካቾች እነ ወር ሉልአደይ ገመድኀን ሰዎች ተጠሪ አቶ አለማየሁ እሸቴ ፍርድ ይህ የሠበር አቤቱታ የቀረበው የሥር ፍቤቶች ሟች አቶ ገዛኸን ጌታቸው ያደረጉት ኑዛዜ በሜበቃ አኳኋን ተጠቃሚውን ወይም ጉዳዩን የሚያመለክት በመሆኑ ፈራሽ ነው ነገር ግን የተጠሪ በቤቱ የመኖር መብት ከኑዛዜው ቃል በመነሣት ተረጋግጧል በማለት የሰጡትን ውሣኔ በመቃወም ነው ተጠሪ በፌመደረጃ ፍቤት ባቀረቡት አቤቱታ ሟች ወንድማቸው አቶ ገዛኸኝ ጌታቸው በተውት ኒዛዜ በአዲስ አበባ ከተማ ወረዳ ቀበሌ ክልል በሚገ ው የቤቁ በሆነው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ካለው ሠርቪስ ቤት አንዱን ክፍል እያደሱ እንዲኖሩ የተናዘዙላቸው በመሆኑ የኑዛዜው ወራሽ መሆናቸው ተረጋግጦ ማስረጃ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል ፍቤቱም የኑዛዜው ይዘት እርስ በርሱ የሚጋጭና ለአፈፃፀም የሚያስቸግር በመሆኑ ፈራሽ ስለሆነ ተጠሪ የኑዛዜ ወራሽ በመሆናቸው ማስረጃ እንዲሠጣቸው ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት የለውም በቤቱ የመኖር መብታቸውን ግን ከኑዛዜው ቃል በመነሣት ፍቤቱ አረጋግጧል በማለት ወስኗል የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤቱም ይህንኑ ኑዛዜ አጽድቋል የአሁኑ የሠበር አቤቱታ የቀረበውም ይህ ውሣኔ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ ሊሻር ይገባዋል በሚሜል ነው ይህ ችሉትም ኑዛዜው ፈራሽ ከሆነ በኋላ የተጠሪን በቤቱ የመኖር መብት በመጠበቅ የሠጠውን ውሣኔ ሕጋዊነት ለመመርመር አቤቱታው ለሠበር እንዲቀርብ በማድረግ የግራ ቀ ን የቃል ክርክር ሠምቷል ከላይ እንደተመለከተው ተጠሪ በሥር ፍቤት ባቀረቡት አቤቱታ ሟች ወንድማቸው በተውት ኑዛዜ ላይ የሟቹ መኖሪያ ቤት አካል በሆነው ሠርቪስ ቤት ውስጥ ቤቱን እያደሱ እንዲኖሩ ስለተናዘዙላቸው የኑዛዜ ወራሽነታቸው እንዲረጋገጥ አመልክተዋል ፍቤቶቹም የቀረበላቸውን የኑዛዜ ሰነድ መርምረው የኑዛዜው ቃል ተጠቃሜውን ግልጽ በሆነ ሁኔታ የሚያመለክት እና ኑዛዜው ያረፈበትም ጉዳይ በበቂ ሁኔታ የማያመለክት በመሆኑ በተለይም ደግሞ ከኑዛዜው ቃል ግልጽ አለመሆን የተነሣ በኑዛዜው መሠረት መፈፀም የማይችል በመሆኑ ኑዛዜው ፈራሽ እንዲሆን ወስነዋል ተጠሪ ኑዛዜው ፈራሽ ነው ተብሎ በተሰጠው ውሣኔ ላይ ይግባኝ አቅርበው ውሣኔውን አላሻሩም ወይም አላስለወጡም ኑዛዜው ፈራሽ መሆኑ ከተወሰነ ደግሞ የኑዛዜ ሠነዱ ዋጋ ወይም ውጤት የለውም ማለት ነው ዋጋ በሌለው ወይም ውጤት በሌለው የኑዛዜ ሠነድ መሠረት የተገ ውም መብት በተመሣሣይ ዋጋ አይኖረውም ምክንያቱም ለመብቱ መገ ት መሠረት የሆነው የኑዛዜ ሠነድ ራሱ ውጤት አልባ ሆኗልና ነውፁ በመሆኑም ፍቤቶቹ ለተጠሪው በቤቱ የመኖር መብት የሰጠው ኑዛዜ ፈራሽ ሆኗል ውጤት የለውም በማለት ከወሰኑ በኋላ በዚህ ፈራሽ በሆነው ኑዛዜ መሠረት የተገ ውን የተጠሪን በቤቱ የመኖር መብት ማረጋገጣቸው እርስ በርሱ የሚቃረን መሆኑን ተረድተናል በመሆኑም ሕጋዊ ውጤት በሌለው ሠነድ የተገ ን መብት ሕጋዊ ውጤት እንዲኖረው የተሰጠው ውሣኔ የሕግ ግድፈት ያለበት ነው ውሣኔ የፌመደረጃ ፍቤት በመቁ በ እንዲሁም የፌከፍተኛ ፍቤት በመቁ በ የሰጡት ውሣኔ ተሽሯል ሟች አቶ ገዛኸኝ ጌታቸው የተውት ኑዛዜ ፈራሽ በመሆኑ ተጠሪ በሰርሺስ ቤቱ እንዲኖሩ በኑዛዜው የተሰጣቸው መብት ሕጋዊ ውጤት የለውም በመሆኑም የተጠሪ ክስ ተቀባይነት የለውም ወጪና ኪሣራ ግራ ቀ ይቻቻሉ። የሚሉትን ጭብጦች በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን አንደመረመርነውም ወራሸነትን ለማረጋገጥ በተደረገው ክርክር አመልካች የሟች የወሮ ቀለሟ ደመቀ ወንድም ስለመሆናቸው የታወቀ በመሆኑ ወራሽነታቸው አጠራጣሪ አይደለም አመልካችና ተጠሪዎች ያላቸውን የወራሽነት ደረጃ ደግሞ አመልካች አባታቸውን ተክተው የሚመጡ በመሆኑ ወራሽነታቸው በሁለትኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ተጠሪዎች የሚመጡት የሟች በእናት በኩል አያቶች የሆኑትን ወራሾች በመተካት በመሆኑ ተጠሪዎቹ በሶስተኛ ደረጃ ወራሽነት ላይ ያሉ ናቸው ይህን መሰረት በማድረግ ቅደም ተከተሉን ስንመለከተውም አመልካች የወራሽነት ቀደምትነት ያላቸው መሆኑን ተገንዝበናል ሁለተኛውን ጭብጥ በተመለከተ ደግሞ የአባትን ለአባት ወገን የእናተን ለአናት ወገን መስጠት ደንብ ስለመሆኑ በፍብሕቁ ሥር የተደነገገ ነው ቁምነገር መታየት ያለበት በየደረጃው ካሉት ወራሾች የወራሽነት ደረጃ ጋር ተገናዝቦ እንጂ በዚህ የሕግ አንቀጽ ሥር የተጠቀሰነው ብቻ ነጥሎ በመውሰድ አይደለም የእናትን ለእናት ወገን የአባትን ለአባት ወገን የሚፈፀመው ደንብ በተመሳሳይ የወራሽነት ደረጃ ላይ ባሉት ወራሾች እንጂ በተለያየ የወራሸነት ደረጃ ላይ ባሉት ወራሾች መካከል አይደለም ይህ ማለትም ወራሻቹ የመጀመሪያ ደረጃ የወራሸነት መብት ያላቸው እንደሆነ ደንቡ ተፈፃሚነት የሚኖረው በእነሱ መካከል ነው ወራሾቹ ሁለተኛ ደረጃ የወራሽነት መብት ያላቸው እንደሆነም ደንቡ የሚፈፀመው በእነሱ መካከል ብቻ ነው የወራሽነት ቀደምትነት ያለው አንደኛ ደረጃ ወራሽ እያለ ሁለተኛ ደረጃ የወራሽነት መብት ያላቸው ሰዎች ይህን የአባትን ለአባት ወገን የእናትን ለእናት ወገን የሚለውን ደንብ ለማስፈፀም የሚችሉበት የህግ ምክንያት የለም እንደዚሁም ሦስተኛ ደረጃ ወራሾች ከሁለተኛ ደረጃ ወራሾች አራተኛ ደረጃ ወራሾችም ከሶስተኛ ደረጃ ወራሾች ጋር በመሆን ይህንን ደንብ የሚያስፈጽሙበት የሕግ ምክንያት የለም ምክንያቱም የሁለተኛ ደረጃ ወራሽነትን መሰረት አድርገን ጉዳዩን ብንመለከትው ከአባት ከእናት አስቀድሞ የሞተ ቢኖር የሱን ፋንታ ልጆቹ ወይም ሌሎች ወደታች የሚቆጠሩ ተወላጆች በሱ ተተክተው ይወርሳሉ ተብሎ በፍብሕቁ የተደነገገው ልጆች የአባትና አናት ወይም የአንዳቸው ልጆች በሞቱ ግዜ አባት ወይም አናታቸውን ተክተው ለመውረስ እንዲችሉ ነው ከእነዚህ መስመሮች በአንዱ መስመር ያለው ወራሽ ቢታጣ ውርሱ በሙሉ በሌላው መስመር ላለው ወራሽ ይሰጣል ተብሉ በፍብሕቁ የተደነገገውም የአባትና የእናት ልጅ ሳይሆ የአባት ወይም የእናት ልጅ የሆነ ወንድም ወይም እህት ያለው ሰው በሞተ ጊዜ ሟችን የሚወርሰው የአባት ወይም የእናት ልጅ ብቻ በሆነ ጊዜና በአባት ወይም በአናት መስመር ልክ እንደርሱ የሁለተኛ ደረጃ ወራሽነት መብት ያለው ሰው ባልተገኘ ጊዜ ውርሱ በአባት ወይም በእናት መስመር ላለው የሁለተኛ ደረጃ የወራሽነት መብት ላለው ሰው መስጠት ተገቢ በመሆኑ ነው የማይንቀሳቀስ ንብረቱ ከሟች እናት መስመር በዘር የተላለፈም ቢሆን የአባትን ለአባት ወገን የእናትን ለእናት ወገን የሚለውን የመብት ጥያቄ ማንሳት የሚችሉት በተመሳሳይ የወራሽነት ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎች እንጂ ከዚህ ውጭ የሆነ የዝምድና ደረጃ ያላቸው ሰዎች ይህን ጥያቄ እንዲያነሱ ሕጉ መብት አይሰጣቸውም ወደ ያዝነው ጉዳይ ስንመለስም ሟች ወሮ ቀለሟ ደመቀ ወደ ላይና ወደታች የሚቆጠሩ ቀጥታ ወራሾች ስለሌሉዋቸው ቀጥለው የሚመጡት ወራሾች ወንድምና እህቶቻቸው ናቸው የእናታቸው የወሮ ማሚቴ ደብርነህ ልጆች የሆኑ እህትም ወንድምም የላቸውም ያሉዋቸው እንደ ወራሽ የአባታቸው ልጅ የሆኑት ወንድማቸው አመልካች ብቻ ናቸው የእናታቸው ልጅ የሆነ እንደየአባታቸው ልጅ ማለት አንዱ አመልካች ሆኖ በሁለተኛ ደረጃ ወራሽነት ላይ የሚገኝ ወራሽ በሌለበት ግዜ የእናትን ለአናት ወገን የሚለውን ደንብ መሰረት በማድረግ ተጠሪዎች የሟች ቤት ይገባናል ለማለት የሚችሉበት የሕግ መሰረት የለም ይህ ክርክር ሊነሳ ይችል የነበረው ሟች የእናታቸው ልጆች የሆኑት ወራሶች ቢኖሩዋቸው ብቻ ነው በአናት መስመር ወገን ወራሾች ከሌሉ በፍብሕቁ እና የተነገሩት ድንጋጌዎች ተፈፃሚዎች አይሆኑም ተብሎ አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ በፍብሕቁ የተደነገገውም ጥያቄው በዝምድና ደረጃ መሰረት የወራሸነት ቀደምትነት በሌላቸው ወገኖች ሲነሳ ደንቡ ተፈፃሚ እንዳይሆን ለመከልከል ታስቦ ነው በመሆኑም ተጠሪዎች ሶስተኛ ደረጃ ወራሾች ሆነው ሳለ ሟች ክርክር ያስነሳውን ቤት ያገኘችው በእናትዋ መስመር በመሆነ የአባቷ ልጅ ለሆነው ወንድሟ በውርስ ሊሰጠው አይገባም በማለት ያቀረቡት ክርክር ከአመልካች ጋር ተመሳሳይ የሆነ የመውረስ ደረጃ ሳይኖራቸው በመሆኑ ክርክራቸው ተቀባይነት ያለው ሆኖ አልተገኘም ይህን መሰረት በማድረግ የሐረሪ ክልል ጠፍቤት የሰጠውን ውሳኔ ስንመለከተውም የፍብሕቁ ከፍብሕቁ እና ጋር አገናዝቦ ያልተወሰነና ለተጠሪዎች የሌላቸውን መብት ያጐናፀፈ በመሆኑ ውሳኔው መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትና መታረም የሚገባው መሆኑ ተገንዝበናል ውሳኔ የሐረሪ ክልል ጠፍቤት በመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠውን ውሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሰረት በመሻር የሐረሪ ከልል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠውን ውሳኔ አጽንተናል ይፃፍ ሟች ወሮ ቀለሟ ደመቀ የአናት ልጅ የሆነ ወራሽ ስለሌላቸው ከአናታቸው በውርስ አገኙት የተባለው ቤት ውርስ ለአመልካች ሊሰጥ ይገባል ተጠሪዎች የያዙትን ክርክር ያስነሳው ቤት ለአመልካች ያስረክቡ የቤቱ ኪራይም የሐረሪ ክልል ከፍቤት በሰጠው ውሳኔ መሰረት ለአመልካች ይክፈሉ ብለናል ይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለን መዝገቡን በመዝጋት ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል ነሐሴ ቀን ዓም በሐረሪ ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ክልል በሚገኘው ቁጥሩ በሆነው መኖርያ ቤት ተሰጥቶ የነበረው እግድ ተነስቷል ይፃፍ ቤኃ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ኀዳር ዐዐዐ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ መስፍን እቁበዮናስ አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አመልካች ወት አይናለም አበበ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ደገፋ ጉርሙ ጠበቃ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው አመልካች ሰኔ ቀን ዓም የተፃፈ ማመልከቻ በማቅረቧ መነሻነት ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተጀመረ ክርክር ሲሆን ፍሬ ነገሩም ያሁኑ ተጠሪ የሥር ከሣሽ በመሆን በሥር ኛ በመቃወም ተጠሪ ወሮ ደስታ ይመር በዚህ መዝገብ የሌሉበት እና ባሁኗ አመልካች የሥር ኛ በመቃወም ተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ሟች ወንድማቸው አቶ አበበ ጉርሙ ልጅ አለመውለዱ እየታቀ አመልካች የሟች ልጅ ናት ተብሉ ወራሽነቱ የተረጋገጠው ባግባቡ ስላልሆነ ውሣኔው ይሻር የሚል ነው ለክሱም ኛ የመቃወም ተጠሪ በርግጥ አመልካች ከኔም ሆነ ከሟች አትወለድም ልጄ ነች ብዬ ውሣኔ ያሰጠሁት ከሕፃንነቷ ጀምሮ ስላሳደኳትና እንደ ልጅ ስለምቆጥራት ነው ሲሉ አመልካችም በበኩሏ ተጠሪ ሕፃን ሆቼፄ ውሣኔ ሲሰጥ ቀርበው መቃወም ሲችሉ ከ ዓመት በኋላ መቅረባቸው በፍብሕቁ ዐዐዐ መሠረት ተቀባይነት የለውም በማለት በየበኩላቸው መልስ ሰጥተዋል ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከሰማ በላ የፍብሕቁ ዐዐዐ የሚሠራው የፈረሰ ንብረት ይገባኛል ለሚል ክርክር እንጂ ወራሽ ናት አይደለችም ለሜል ክርክር አይደለም በሚል የይርጋ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎ አመልካች ከሟች የማትወለው በመሆኑ ስለ ኑዛዜ ወራሽ ልትሆን አትችልም በማለት ወስኗል ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለት የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤትም በበኩሉ የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ሟችና ኛ የመቃወም ተጠሪ ከቤተሰብ ሕግ አንቀጽ ሠሥ መሠረት አመልካችን ወደ ቤት በመውሰድ በማንከባከብና በማስተማር አንደ አባት በመሆን የተሣተፉ በመሆኑ አመልካች የሟች ልጅና የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ ነች በማለት ወስኗል ያሁኑ ተጠሪ በዚህ ውሣኔ ቅር ተሰኝተው ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርበው ፍርድ ቤቱም የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሣኔ ሽሮ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትን ውሣኔ አጽንቷል አመልካች ይህን የሰበር አቤቱታ ያቀረቡት በዚህ መነሻነት ሲሆን ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን መርምሮ ተጠሪን በማስቀረብ ግራ ቀኙን አከራክሯል ክርክሩንም ከሕጉ ጋር በማገናዘብ መርምራሯል በዚህም መሠረት አመልካች ኀዳር ቀን ዓም የወራሽነት ማስረጃ ካገኙ በኋላ የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ መሆናቸውን በመግለጽ በቤቱ ላይ ያገኙት የጋራ ባለሀብትነት ከሥር ኛ የመቃወም ተጠሪ ጋር ተቀባይነት ያጣው ባግባቡ መሆን አለመሆኑን ፍርድ ቤቱ እንደሚከተለው ተመልክቷል አመልካች በሥር ፍርድ ቤቶች ያቀረቡት ክርክር ባንድ በኩል የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ መሆናቸውን በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ ከዐ ዓመት በላይ ቆይተው በቤቱ ላይ አለኝ የሚሉት የወራሽነት መብት በፍብሕቁ ዐዐዐ መሠረት የሚታገድ ነው የሚል ሲሆን የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የጠቀሱት የፍብሕቁ ዐዐዐ የሚሠራው የውርስ ንብረት ይገባኛል ይሰጠኝ ለሜል ክርክር እንጂ ወራሽ ናት አይደለምችም ለሜል ክርክር ተፈፃሚነት ያለው አይደለም በማለት የሰጠውን ውሣኔ እንደተመለከትነው ድንጋጌው ባግባቡ አለመፈጸሙን ተረድተናል ያሁኑ ተጠሪ በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ በራሱም ሲታይ ይዘቱ ወንድሜ ልጅ አለመውለዱ እየታወቀ አመልካች በሐሰት ልጅ ነኝ ብላ የወራሽነት ማስረጃ የወሰደች ስለሆነ ትመልስ በቤቱ ላይ ያለው የሟች ድርሻ ለኔ ይሰጠኝ የሚል ሲሆን አመልካችም በበኩሏ የሟች ልጅ መሆኗን እና ንብረቱም እንደሚገባት መከራከራቸው ታይቷል ክርክሩ ትክክለኛ ገጽ ይህ ሁኖ እያለ የሥር ፍርድ ቤት አመልካች ክሱን ያመነኑ ይመስል ገና ከጅምሩ ድንጋጌውን አጥብቦ በመተርጎም በልጅነት ጥያቄ ቢነሣ ድንጋጌው ተፈፃሚነት የለውም ማለቱ ቀጣይ ሆኖ አልተገኘም ይህ ድንጋጌ መገኛው አንቀጽ ሆኖ እውነተኛ ወራሽ እፄ ነኝ ከሚል ጥያቄ ጀምሮ የውርስ ንብረት ያላግባብ ተወስዲልና ይመለስልኝ በማለት የሚቀርቡትን ክሶች ጥያቄዎች የሚያካትት ለመሆኑ አንቀጽ መመልከቱ ይበቃል በዚህ ረገድ አመልካች ክርክሩን ባስነሳው ቤት ላይ ከዐ ዓመት በላይ የቁቀየ የባለሀብትነት ድርሻ ማግኘታቸው አየተመለከተም ተጠሪም ድርሻቸውን ለመጠየቅ ከሚያስችላቸው ጊዜ በላይ ቆይተው ክስ ለማቅረባቸው አመልካች ያቀረቡት የይርጋ ክርክር ተቀባይነት ያጣው ድንጋጌውን በጠባቡ በሥር ፍርድ ቤት በሚተረጎመሙ ሳቢያ መሆኑን ይህ ፍቤት ተገንዝቧል በመሆኑም የመጨረሻ ውሣኔ የሰጠው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይርጋውን ነጥብ አልፎ ውሣኔ መስጠቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል የከፍተኛው ፍርድ ቤት ምንም እንኳ የአመልካችን ልጅነት ተቀብሎ የሥር ፍቤት ውሣኔ የሻረ ቢሆንም ፍቤቱ በቅድሚያ በይርጋው ጥያቄ በቅድሚያ ለይርጋው ጥያቄ በቅድሚያ ምላሽ ቢሰጥ ኖሮ ወደዚህ ነጥብ መግባት ያስፈለገው እንዳልነበር ተገንዝበናል ስለሆነም ክሱ በይርጋ ታግዲል ብለናል ውሣኔ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ዐ ጥር ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ የከፍተኛ ፍርድ ቤት መቁ በመጣበት አኳን በመሸኛ ተመልሶ ይላክ መዝገቡ ተዘግቷል ክሱ በይርጋ ይታገዳል ተብሏል መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ዐ ኀዳር ዐዐዐ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አቶ አብዱራሂም አህመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ወሮ የኔነሽ ከበደ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ዮሐንስ ከበደ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው አመልካች ጥር ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት ማመልከቻ መነሻነት ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ የአሁኑ አመልካች የሥር ተከሣሽ በሆነበት መዝገብ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ የሟች አባታቸው የደጅአዝማች ከበደ ወዮሐንስ የሆነውን ቁጥሩ ቤት አመልካች የያዙ መሆኑን ገልፀው የአመልካችን ድርሻ ኛ አስይዘው ቤቱን እንዲረከቡ ይህ ካልሆነም ቤቱ በሐራጅ ተሸጦ እንዲከፋፈሉ የሚል ሲሆን አመልካችም በበኩላቸው ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው ጉዳዩ ቀደም ሲል የመጨረሻ ውሣኔ ያገኘ ጉዳይ ነው ተጠሪ ቤቱ የሟች ለመሆኑ ማስረጃ አላቀረቡም በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩን ያስተናገደው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም ያቀረበው የይርጋ ተቃውሞ በወራሽና ያለ ማስረጃ ንብረት በያዘ ወራሽ ባልሆነ ሰው ላይ ተፈፃሚነት ከሚኖረው በስተቀር ለዚህ ጉዳይ አግባብነት የለውም የፍብሕቁ ደግሞ በውል ላይ ለተመሠረተ ግንኙነት የሚጠቀስ እንጂ በወራሾች መካከል የሚጠቀስ በመሆነ በክርክሩ አግባብነት የለውም ጉዳዩ ቀደም ብሎ የመጨረሻ ውሣኔ አግኝቷል የተባለውን ሌሎች ወራሽ ያልሆኑ ተከሣሾች ቤቱን እንዲያስረክቡ የተወሰነ ከመሆኑ ውጭ በተመሣሣይ ጭብጥ ላይ የተሰጠ ውሣኔ አይደለም በማለት ያቀረቡትን ተቃውሞዎች ውድቅ ካደረገ በኋላ ቤቱ የአውራሻቸው ለመሆኑ ካርታው በማስረጃዎች መቅረቡን ገልፆ ክስ የቀረበበትን ቤት ግራ ቀኙ ከተስማሙ አንዳቸው ለአንዳቸው ከፍለው ቤቱን እንዲያስቀሩ ይህ ካልተቻለ ቤቱ በሐራጅ ተሸጦ የየድርሻቸውን እንዲወስኑ በማለት ወስኗል ውሣኔው በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በይግባኝ ፀንቷል አመልካች ይህን የሰበር አቤቱታ ያቀረቡት በዚህ መነሻነት ሲሆን አቤቱታው ከተመረመረ በላ ተጠሪን በማስቀረብ ግራ ቀኙ እንዲከራከሩ ተደርጓ ክርክርራቸውም ከሕግ ጋር ተገናዝቦ ተመርምሯል በዚህም መሠረት የሥር ፍቤቶች በፍብሕቁ ዐዐዐ ላይ የተመለከተው የይርጋ መቃወሚያ ለጉዳዩ አግባብነት የለውም በማለቱ ውድቅ ማድረጋቸው ባግባቡ መሆን አለመሆኑን ተመልክተናል የፍብሕቁ ዐዐዐ ለጉዳዩ አግባብነት የለውም በሚል በሥር ፍርድ ቤት የተሰጠው ምክንያት ድንጋጌው በወራሽ እአና ወራሽ ሣይሆን ማስረጃ ሣይኖረው ንብረት በያዘ ሰው ላይ ለሚቀርብ ክስ የሚነሣ እንጂ አሁን በወራሾች መካከል ለተነሣው ክርክር ተጠቃሽ አይሆንም የሚል ነው ሆኖም ይህ የሰበር ሰሚ ችሎት በአመልካች በወሮ ድንቄ ተድላና በተጠሪዎች እነ አቶ አባተ ጫኔ መካከል በነበረው የውርስ ክርክር በፍብሕቁ ዐዐዐ እና ላይ የሰፈረው የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ የሚሆነው አንድ ወራሽ በሌላ በወራሽነት የውርስ ሀብት በያዘ ሰው ላይ ክስ ሲያቀረብ ነው በማለት የሰጠውን ውሣኔ ያልተከተለ በመሆኑ የሥር ፍቤት ለድንጋጌው የሰጠው ትርጉም መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ተገኝቷል ከዚህ አንፃር አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት የይርጋ ክርክር ተቀባይነት ሊኖረው ይገባ ነበር ከተባለ ባጠቃላይ ክርክሩ ላይ ለውጥ ያመጣ ወይም አያመጣ እንደሆነ መመልከቱ አስፈላጊ ነው ተጠሪ በንብረት ጥያቄው ላይ ክስ ያቀረበው ዐ ዓመት ካለፈው በኋላ ነው በማለት የይርጋ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል ሆኖም ክስ በቀረበለት ቤት ላይ ቀደም ሲል በሌላ መዝገብ ክስ አቅርበው ጉዳዩ እስከ ሰበር ደርሶ ከተወሰነላቸው በላ የአፈፃፀም መዝገብ ከፍተው ታህሣሥ ቀን ዓም ቤቱ እንዲረከቡ የአፈፃፀም ትዕዛዝ የተሰጠላቸው መሆኑን በሰበር ማመልከቻቸው ላይ ገልፀዋል በሌላም በኩል ያሁኑ ተጠሪ የስር ከሣሽ በመሆን በመልካች ላይ ቤቱን በተመለተ ክስ ያቀረቡት ግንቦት ቀን ዓም መሆኑ ከሥር ፍርድ ቤት መዝገብ ተረጋግጧል ከዚህ አኳያ አመልካች ክስ የቀረበበትን ቤት በፍርድ ቤት ውሣኔ በይዞታቸው ሥር በማድረግ የተረከቡት ታህሣሥ ቀን ዓም ነው ቢባል እንኳ ተጠሪ በበኩላቸው ክስ ያቀረቡባቸው አንድ ዓመት ተኩል በማይሞላ ጊዜ ውሰጥ መሆኑ ታይቷል በፍብሕቁ ዐዐዐ እና ላይ የተመለከቱት የይርጋ ጊዜዎች በ እና ዓመት የተካፄዱ በመሆናቸው አመልካች ያቀረቡት የይርጋ ጥያቄ ሁለቱንም ያላሟላ ነው ስለዚህ የይርጋ ተጠቃሚ የሚሆነበት ምክንያት አልተገኘም ውሣኔ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የከፍተኛው ፍቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔ በተለየ ምክንያት ፀንቷል ይፃፍ ግራ ቀኙ ወጪያቸውን ይቻቻሉ በትፅዛዝ የመጣው የፌዴራል የመጀመሪያ ደርጃ ፍርድ ቤት መቁ የተፈለገበት ምክንያት ስላለቀ ወደመጣበት በሸፒ ደብዳቤ ተመልሶ ይላክ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ አሰግድ ጋሻው አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ወሮ እናትነሽ ከተማ ጠበቃ አቶ መኮንን አምቦ ቀረቡ መልስ ሰጭ ወሮ ፋንታዬ መሐመድ አልቀረቡም መዝገቡን መርምረን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የአማብሔክልላዊ መንግሥት ጠፍቤት በይግባኝ ሥልጣኑ ተመልክቶ በሰጠው ውሣኔነ ላይ ነው የነገሩም መነሻ የአሁን መልስ ሰጭ ሚስትነታቸው እና የልጆች የአሁኑን አመልካችን ጨምሮ ሞግዚትነት ሥልጣን ማስረጃ እንዲሰጣቸው ለወረዳው ናዒባ ፍቤት አቤቱታ በማቅረባቸው ጉዳዩ ታይቶ በፍብሕቁ ሐምሌ ቀን ዓም ማስረጃው ተሰጥቷቸዋል ከዚህ በኋላ የአሁን አመልካች ኛ እኔ በሌለሁበት በውጭ አገር የተሰጠ ማስረጃ በመሆኑ ሁለተኛ ጉዳዩ በሀይማኖታዊ ፍቤት ቀርቦ የታየ ሲሆን በማስረጃው ላይ የፍብሕቁ መጠቀሱ አግባብነት የለውም በሚል ለቃዲ ፍቤት የይግባኝ አቤቱታ አቅርባለች የቃዲው ፍቤትም ለውሣኔው መሠረት የሆነው ህግ ከቅዱስ ቁርዓን ውጭ የተጠቀሰ በመሆነ የናዒባው ፍቤት አስተካክሎ ይወስን ዘንድ መልሶታል በዚሁ መሠረት የናዒባው ፍቤት ጉዳዩን አያየው እያለ የአሁን መልስ ሰጭ ጉዳዩ በመደበኛ ፍቤት ሊታይ ይገባዋል በሚል ሲከራከሩ አመልካች በበኩሏ በሸሪዓ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ያለው ይኸው ፃይማኖታዊው ፍቤት ነው በማለት ተከራክራለች የናዒባው ፍቤትም ይህንን የአመልካችን ክርክር ተቀበሉ አስቀድሞ በአሁን መልስ ሰጭ ጠያቂነት በናዒባው ፍቤት የታየ ጉዳይ አስከሆነ ድረስ በተጀመረው በቅዱስ ቁርዓን ህግ መሠረት ሊታይ ይገባዋል አንጂ በመደበኛ ፍቤት ሊታይ የሚችል አይደለም በማለት በቅዱስ ቁርዓን ህግ መሠረት መልስ ሰጭ አንድ ስምንተኛ ንብረት ይወስዳሉ ሲል መጋቢት ዐ ቀን ዓም ወስኗል በዚህ ውሣኔ ላይ የአሁን መልስ ሰጪ ለቃዲው ፍቤት አቤቱታ በማቅረባቸው የቃዲ ፍቤት ጉዳዩን በሃይማኖታዊ ፍቤት ለማየት የሁለቱ ተከራካሪ ወገኖች ፈቃድ ያስፈልጋል መልስ ሰጭ በዚሁ መሠረት ጉዳዩ በናዒባው ፍቤት አንዲታይ ፈቃድ የላቸውም ስለሆነም ጉዳዩ ሊታይ የሚገባው በመደበኛው ፍቤት ነው ሲል ዳኝነት ሰጥቷል በዚሁ የቃዲ ፍቤት ውሣኔ መሠረት መልስ ሰጭ ሚስትነታቸው እና የልጆቻቸው ሞግዚትነት ተረጋግጦ ማስረጃ እንዲሰጣቸው ለዳንግላ ወረዳ ፍቤት አቤቱታ አቅርበዋል ይኸው ፍቤትም ጉዳዩን ተመልክቶ በሥፋመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሚስትነትና የልጆች ወራሽነትን ማስረጃ ሰጥቷቸዋል አመልካችም ከላይ ከፍ ሲል እንደተገለፀው የቃዲው ፍቤት ጉዳዩ በመደበኛ ፍቤት አንጂ በሸሪዓ ህግ መሠረት ሊዳኝ አይገባውም ሲል በሰጠው ውሣኔ የይግባኝ አቤቱታ ለአማራ ክልል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍቤት ይግባኝ አቅርበው ይኸው ጠቅላይ ሸሪዓ ፍቤት ጉዳዩን ተመልክቶ በመቁ ሰኔ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የዳንግላ ወረዳ ናዒባ ፍቤት የሰጠውን ውሣኔ በማጽናት ወስኗል ከዚህም ሌላ የዳንግላ ወረዳ ፍቤት በሥፋመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የመልስ ሰጭን ሚስትነትና የልጆችን ወራሽነት በማረጋገጥ የሰጠው «ውሣኔ» ይሰረዝለት ዘንድ አመልካች በፍብሥሥሃሕቁጥር መሠረት አቤቱታ አቅርባለች የወረዳው ፍቤትም በዚሁ ነጥብ ላይ ካከራከረ በኋላ መልስ ሰጭ ባቀረቡት አቤቱታ መነሻ የናዒባ ፍቤቱ ሐምሌ ቀን ዓም ሚስትነታቸውን አረጋግጦ ውሣኔ ከሰጣቸው በኋላ ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ለሁለተኛ ጊዜ ለዳንግላ ወረዳ ፍቤት አቤቱታ በማቅረባቸው በፍትመቁ ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት በድጋሚ የሚስትነት ውሣኔ የሰጠበት መሆኑን ተረድቻለሁ ስለሆነም ይህ ለሁለተኛ ጊዜ በመደበኛው ፍቤት የተሰጠው የሚስትነት ማስረጃ ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ሊሰረዝ ይገባዋል በማለት ውሣኔ ሰጥተበታል ለዚህ የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነውም ይኸው ውሣኔ ነው የአሁን መልስ ሰጭ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት የይግባኝ አቤቱታ ለአዊ ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው ቀደም ሲል በዳንግል ወረዳ ፍቤት በሥፋመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ መሰረዙ ተገቢ ነው ወይስ አይደለም በሚለው ነጥብ ላይ ግራ ቀኙ ተከራክረዋል የከፍተኛው ፍቤትም ይግባኙን ከመረመረ በኋላ ቀደም ሲል የዳንግላ ወረዳ ፍቤት በጉዳዩ ላይ ውሣኔ የሰጠው ሐምሌ ቀን ዓም ነው ይሁን እንጂ የአሁን አመልካች ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ገብቼ እንድከራከር ይፈቀድልኝ በማለት መጠየቁን ተረድተናል እንዲሁም ውሣኔ ከመሰጠቱ በፊት በአስተዳደራዊ ሁኔታ አቤቱታ አቅርበው የክልሉ ጠፍቤት አንድ ጉዳይ በሁለት የተለያዩ ፍቤቶች ሊታይ አይገባውም ስለሆነም ክርክሩ ሊቆም ይገባዋል ሲል የዛፈ መሆኑንም ካቀረባቸው ማስረጃ ተረድተናል ይህም ከሆነ የወረዳው ፍቤት በጉዳዩ ላይ ውሣኔ ከመስጠቱ በፊት አመልካች በወረዳው ፍቤት ጉዳዩ እንደነበረ ታውቃለች የፍብሥሥሕቁ ክርክር መደረጉን ለማያውቅ ወገን እንጂ እንደ አመልካች አቤቱታ ያለውን ሊሸፍን አይችልም አመልካች ያለአግባብ ጣልቃ ልትገቢ አይገባም ተብላ ከሆነ በየደረጃው በይግባኝ እንዲስተካከል ማድረግ ከምትችል በቀር በፍብሥሥሕቁ መሠረት አቤቱታ ማቅረብ አትችልም አንዲሁም የአሁን መልስ ሰጭ ያቀረበችው አቤቱታ የሚስትነት መብትን ለማረጋገጥ በመሆኑ ከጉዳዩ ይዘት አንፃር የክርክር ተካፋይ የግድ ይኖራል ማለት አይደለም በፍብሥሥሕቁ አቤቱታ ማቅረብ የሚችለው ደግሞ የክርክር ተካፋይ መሆን እየቻለ ተካፋይ ሳይሆን ውሣኔ ተሰጥቶ ከሆነ ነው በዚህ ጉዳይ አመልካች የግድ የክርክር ተካፋይ ናት ማለት አይቻልም የሚሉትን ሁለት ምክንያቶች መሠረት አድርጐ የወረዳው ፍቤት ቀደም ሲል የሰጠውን ውሣኔ መሻሩ ተገቢ አይደለም በማለት ሽሮ ወስኗል የአሁን አመልካች ለጠፍቤቱ ባቀረበችው የይግባኝ አቤቱታ መነሻ ይኸው ፍቤት ሁለቱንም ወገኖች አከራክሮ በተመሳሳይ ምክንያት የከፍተኛውን ፍቤት ውሣኔ አጽንቶታል አመልካች ይህ በከፍተኛው ፍቤት እና በጠፍቤት የተሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ ሊታረምልኝ ይገባል በማለት ነው የሰበር አቤቱታ ያቀረበችው የሰበር አቤቱታው ይዘት በሥር ፍቤቶች ከቀረበው የተለየ አይደለም በዚህም ሰበር ችሎት ግራ ቀኙ የቃል ክርክራቸውን አሰምተዋል በሥር ፍቤቶች የተነሳውን ክርክር በየፊናቸው በማጠናከር የተከራከሩ ከመሆኑ በቀር በአዲስ መልክ የተጠቀሰ ክርክር የለውም አኛም ጉዳዩን ተመልክተናል የመዝገቡ ግልባጭ እንደሚያስረዳው መልስ ሰጭ የሟች ከተማ ኢብራሂም ሚስት ናት ወይስ አይደለችም። የሚለውን ጭብጥ ይዞ ኑዛዜ ላይ የነበረውን ምስክሮች ቃል ከሠማ በላ ምስክሮቹ ኑዛዜውን ሲያናዝዙ የነበሩና የሠሙ መሆኑን ስላስረዱና ኑዛዜው ላይም ኑዛዜውን ሲናዘዙ የነበርንና የሠማን ስለሆነ መስማማታችንን በተለመደው ፊርማችን እናረጋግጣለን በማለት ስለተገለፀ ኑዛዜው ሊፀና ይግባል በማለት የመጀመሪያውን ውሣኔ አጽንቷል አመልካች በዚህ ውሣኔ ላይ የይግባኝ ቅሬታቸውን ለፌጠቅላይ ፍቤት ያቀረቡ ቢሆንም ቅሬታቸው ተቀባይነት አላገኘም የአሁን የሠበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ነው ይህ ችሎት ኑዛዜው በምስክሮች ፊት የተነበበ መሆኑ የተገለፀው ከምስክሮቹ ፊርማ በላ ሆኖ ሣለ ኑዛዜው ይፀድቃል መባሉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት ቀርቦ አንዲታይ አድርጓል ግራ ቀኙም ክርክራቸውን በጽሁፍ አቅርበዋል ይህ ችሎትም መዝገቡን እንደሚከተለው መርምራል ከመዝገቡ እንደተረዳነው ተጠሪ ሚሟች ያደረጉላቸው ኑዛዜ እንዲፀድቅላቸው ጠይቀዋል የሥር ፍቤት ኑዛዜው ግልጽ ኑዛዜ በመሆኑ በፍሕቁ መነበቡንና ይህም ፎርማሊቲ መፈፀሙን ስላልተመለከተ ፈራሽ ነው በማለት ወስኗል የፌከፍተኛ ፍቤት ኑዛዜው ሊፀድቅ ይገባል በማለት የሥር ፍቤትን ውሣኔ የሻረው አንደኛ ነዛዜው በምስክሮች ፊት ለመነበቡ በነዛዜው ላይ ተገልዷል ሁለተኛ ደግሞ ምስክሮቹ ቀርበው ኑዛዜው ሲደረግ የነበሩና የተነበበላቸው መሆኑን አስረድተዋለ በማለት ነው ነገረ ግን እኛ የኑዛዜውን ሠነድ እንደተመለከትነው ምስክሮቹ ኑዛዜው ሲደረግ የነበሩና የሠሙ ስለመሆኑ የተገለፀው ከተናዛዢና ከምስክሮቹ ፊርማ ሥር ነው በፍሕቁ ዐ ሥር ደግሞ አንድ ግልጽ የሆነ ኑዛዜ በጽሁፍ ህዳግ ላይ ወይም በመስመሮቹ መካከል ወይም ከምስክሮች ፊርማ በኋላ ተጨማሪ ነገሮች ያሉበት ሲሆን ፊራሽ አንደሚሆኑ ተመልክቷል በመሆኑም በተያዘው ጉዳይ በኑዛዜው ላይ ኑዛዜው በምስክሮች ፊት በመነበቡ የሚገልፀው ጽሁፍ ከምስክሮቹ ፊርማ በኋላ የተጨመረ መሆኑ በግልጽ እየታየ ኑዛዜው እንዲፀድቅ መደረጉ ከፍ ሲል የተመለከተውን ሕግ ያላገናዘበ ነው ከዚህ በተጨማሪ የኑዛዜ ሰነዱ ቀርቦ እያለ በኑዛዜው ላይ የተመለከቱትን ምስክሮች ሠምቶ ኑዛዜው እንዲፀድቅ መደረጉ በፍሕቁ ዐዐን የሚቃረን ነው ምንም እንኳን ይህ ድንጋጌ ቀጥተኛ ተፈፃሚነቱ ለውል ግነኙነቶች ቢሆንም ግዴታዎቹ ከውል የተገኙ ባይሆንም ስለ ውል በጠቅላላው የተደነገጉት ደንቦች ተፈፃሚ እንደሚሆኑ በፍሕቁ ሥር ስለተመለከተ ይኸው የፍሕጉ ቁጥር ዐዐም ለኑዛዜ ተፈፃሚ ሊሆን ይችላል ስለሆነም በኑዛዜው ላይ ስለተፃፈው ነገር የሰው ምስክሮችም ሆነ የሕሊና ግምት ማስረጃ ሊቀርብ ስለማይገባ ፍቤቱ ምስክቹን ሠምቶ መወሠኑም ሕጋዊ አልነበረም በአጠቃላይ የክርክር ምክንያት የሆነው ኑዛዜ እንዲፀድቅ መደረጉ የሕግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የፌከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐ በ የሰጠው ውሣኔና የፌጠፍቤት በመቁ በዐዐ የሠጠው ትዕዛዝ ተሽሯል የፌመደረጃ ፍቤት በመቁ በ የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ጥቅምት ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድ መሐመድ አቶ ሐጐስ መልዱ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አቶ ተሻገር ገስላሴ አቶ ብርሃኑ አመነው አመልካች ወሮ ስንልሽ ማዘንጊያ ጠበቃ ቀረበ ተጠሪ እነ አቶ ተስፋ ማዘንጊያ ቀርበዋል መዝገቡን መርምረን የሚተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ ጉዳይ የአሁኖቹ ተጠሪዎች በአመልካች ላይ ህዳር ቀን ዓም ባቀረቡት ክስየአሁኗ አመልካች ግምቱ ብር የሆነና ከአውራሻችን ከወሮ የንጉሜ ማዘንጊያ የሚደርሰንን የውርስ ንብረት የያዘች ስለሆነ የውርስ ንብረት ታካፍለን የሜል ነው የአሁን አመልካች ለክሱ ከሰጠችው መልሶች መካከልአሁን የተጠየቀውን የውርስ ንብረት ወራሽ መሆኔ በፍቤት ተረጋግጦ ላለፉት አመታት በእጄ የቆየ ስለሆነ ተጠሪዎች በይርጋ ቀሪ የሆነን ጉዳይ አንስተው ሊጠይቁኝ አይገባም የሚል ይገኝበታል አቤቱታ የቀረበለት የሰሜን ጎንደር መስተዳደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት የአሁኗል አመልካች የይርጋ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ የውርስ ንብረቱን ከሳሽና ተከሳሾች አኩል ይካፈሉ ብሏል ጉዳዩን በይግባኝ የቀረበለት የአብክመጠቅላይ ፍቤት ይግባኙን በፍሕሥሥቁ ውድቅ በማድረግ መዝገቡን ዘግቶታል የሰበር አቤቱታው በዚህ ላይ የቀረበ ሲሆን ይህ ችሉት የካቲት ቀን በዋለው ችሉት የሥር ፍቤት የይርጋ ጥያቄውን ያለፈው በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ሲባል መዝገቡ ለሠበር እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቶ የግራ ቀኙን የቃል ክርክር ሰኔ ቀን ሰምቷል በዚህ ጉዳይ የሥር ፍቤት የይርጋው ጥያቄ ውድቅ ያደረገበት ዋንኛ ምክንያት የአሁኗ አመልካች ለክርክሩ ምክንያት የሆኑትን የውርስ ንብረቶች የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር በሚደነግገው መሠረት ከ ዓመት በላይ በይዞታዋ ስር ስላላደረገች ክሱ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በሚል ነው በመሠረቱ አውራሽ የተባሉት ወሮ ንጉሜጫ ማዘንጊያ መጋቢት ቀን ዓም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ መሆኑ ታውቋል የአሁኗ አመልካች ግንቦት ቀን ዓም የሟች ሕጋዊ ወራሽ መሆኗ ተረጋግጦ ንብረቱን ይዛ ስትገለገልበት ስለመቆየቷም ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ መረዳት ተችሏል የአሁኖቹ ተጠሪዎች ደግሞ በዚሁ ከተማ እየኖሩ ላለፉት ዓመታት በተከሳሽ የተያዙትን የውርስ ንብረቶች ሳይጠይቁ መቆየታቸው ታውቋል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ከሳሽ መብቱንና የውርስ ንብረቶች በተከሳሹ መያዛቸውን ካወቀ ሦስት ዓመት በኋላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ለማግኘት አይችልም በሚል ተደንግጓል የሥር ፍቤት የኸን መሠረታዊ የይርጋ ሕግ ወደ ጐን በመተው ግራ ቀኙ እየተከራከሩበት ያለው የውርስ ንብረት ከዘር የወረደ ርስት እንደሆነ በመቁጠር ለጉዳዩ አግባብ ያልሆን ሕግ ጠቅሶ የይርጋ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ መሠታዊ የሕግ ስህተት ነው ብለናል ውሣኔ የተጠሪዎች የውርስ ንብረት ጥያቄ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ብለናል የአብክመ የሰሜን ጎንደር መዞን ከፍተኛ ፍቤት ሰኔ ቀን ቁጥር በሆነ መዝገብ የሰጠው ውሳኔ አና የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በፍይመቁ በ የሰጡት ትዕዛዝ ተሽራል የቪህን ፍቤት ወጭና ኪሳራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ያለቀለት ስለሆነ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ ፀጋዬ አስማማው ዓሊ መሐመድ አልማው ወሌ አመልካች የወሮ አመለወርቅ እየሱስ ወራሽ ጠበቃ ሰለመን ገመቀል ቀረቡ ተጠሪዎቹ አቶ መስፍን አስፋው ወሮ አልማዝ አስፋው ጠበቃ መልካም ዓለማየሁ ቀረቡ ቱቱ አስፋው ሶስና አስፋው መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዮ የቀረበው አመልካች የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ትአዛዝ መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ጥር ቀን ዓም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ ስለጠየቁ ነው የክርክሩ ፍሬ ጉዳይ ከመዝገቡ ለመረዳት አንደሚቻለው በመጀመሪያ የአሁን ተጠሪዎች በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በከሳሽነት ቀርበው እህታችን ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው በ ዓም በሞት ተለይታለች እህታችን ልጅ ወይም ተወላጅ የሌላት መሆኑና እኛ ወራሾቿ መሆናችንን በፍርድ አረጋግጠናል ሟች እህታችን ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው ከወደ ውጭ አገር ለህክምና ስትፄድ ቤቷንና ንብረቷን ለአቶ ፈንታይ ወልደዮሐንስ እና ወሮ የሺመቤት ሀብተሚካኤል ሰጥታ ሄዳለች ሆኖም አደራ ተቀባዮች የሆኑት እነ አቶ ፋንታዬ የውርሱን ንብረት እንዲያስረክቡን ስንጠይቅ ለማስረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ቁጥሩ የሆነውን ቤትና በክሱ የተዘረዘሩ ንብረቶች አንዲያስረክቡ ውሣኔ ይሰጥልን በማለት ክስ አቅርበዋል ተጠሪዎች የውርስ ንብረቱን ይዘዋል ከሚሏቸው ከእነ አቶ ፈንታዬ ወልደዮሐነስና ወሮ የሺመቤት ሀብተሚካኤል ጋር እየተከራከሩ እያሉ ወሮ አመለወርቅ አየሱስ ቀርበው ሟች ጥሩወርቅ አስፋው የሟች አቶ አበበ ከበደ ሚስት ነበሩ እኔ የአቶ አበበ ከበደ ሚስት መሆኔን በፍርድ ቤት አረጋጋጫለሁ ክርክር እየተካሄደበት ያለው ንብረት የሟች አበበ ከበደ የጋራ ሀብት በመሆኑ በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ በማለት ያመለከተች ሲሆን ፍርድ ቤቱም የአመልካችን ማመልከቻ እና ማስረጃ ከመዘነ በኋላ ወደ ክርክሩ በጣልቃ ገብነት እንድትገባ ወስኗል የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የተጠሪዎችን ክስ የአመልካች አውራሽ የሆነችው አመለወርቅ እየሱስ በጣልቃ ገብነት ያቀረበችውን ማስረጃና የእነ ፈንታዬ ወልደዮሐንስን መልስና ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተጠሪዎች የቀረበባቸውን ክስ ኛ ተጠሪ ያልካዱና ክሱን ስለአመኑ የፍታብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት በዝርዝር የተያዘው ንብረት በራሱ ላይ ተዘርዝሮ የቀረበው ንብረት ለአመልካቾችና ለጣልቃ ገብ እንዲያስረክቡ ሁለተኛ ተጠሪ የአንደኛ ተጠሪ ባለቤት ሲሆን ባለቤታቻው ለህክምና ወደ ውጭ እንደፄዱና ሲመለሱ እንደሚፈጽሙ በመግለጽ ለጊዜው ከነገር ለመሸሽ እኔ ንብረቱን አልተረከብኩም በዝርዝር ላይም አልፈረምኩም ይበሉ እንጂ ክሱን በግልበጽ ስላልካዱ በነገሩ የመሸሽ የተሰጠ መልስ ክሱን እንደመካድ ስለማያስቆጥር ክስ በቀረበበት ንብረት ላይ አንደኛ ተጠሪ ጋር በጋራ ሀላፊ ናቸው ብለን ወስነናል ጣልቃ ገብም ተካፋይ ናቸው ብለናል በማለት ወስኗል የፌዴራልና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከክሱ ጋር በዝርዝር የተያዘው ንብረት በክሱ ላይ የተመለከተው ወይም የሟች የውርስ ንብረት ተጣርቶ ክፍፍሉን እንዲያስፈጽሙ አቶ ቸርነት ተገኝን ሹሟል ከዚህ በኋላ ውርስ አጣሪው በተጠሪዎችና አመልካች የግልና የሚስቱ የጋራ ሀብት ነው በሚሉት ጉዳይ ላይ ክርክርና ማስረጃ ከሰማ በኋላ አመልካች የፍታብሔር ህግ ቁጥር በተደነገገው መሠረት መብታቸውን ያልጠየቁ ስለሆነና በአዲስ አበባ አስተዳደር በየካ ክፍለ ከተማ በቀበሌ ቁጥሩ የሆነው ቤት ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው የተመዘገበ ስለሆነ የእሷ የግል ንብረት የሚልና ሌሎች ንብረቶችም ወሮ ጥሩወርቅ አስፋው የግል ሀብት ናቸው በማለት ወስኖ ይህንን ሪፖርት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቅርቧል ፍርድ ቤቱም የውርስ አጣሪው ሰኔ ቀን ከተፃፈ መሸኛ ጋር የቀረበለትን ሪፖርት ህግና ሞራልን የማይቃረን በመሆኑና ተከራካሪዎቹ ትክክለኛነቱን ቀርበው ስላረጋገጡ የፍርድ ቤቱ የውሣኔ አካል አድርጐ መዝግቦታል በማለት ትዕዛዝ ሰጥቷል አመልካች በዚህ ወሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርባ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኙን በፍታብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ሰርዞታል አመልካች የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የውርስ አጣሪውን ሪፖርት በማጽደቅ የሰጠውና ትእዛዝና የከፍተኛው ፍርድ ቤት ያቀረብኩትን ይግባኝ ለመሰረዝ የሰጠው ትእዛዝ መሠረታዊ የህግ ስህተት አለበት በማለት ባቀረቡት አቤቱታ ፍርድ ቤቱ የሾማቸው የውርስ አጣሪ ከእኛ በኩል ያቀረበውን ማስረጃ ተቀብለው አልመረመሩም ፍርድ ቤቱ የውርስ ከጣሪው ባቀረበው ሪፖርት ላይ በጽሑፍ መቃወሚያ ብይን ሣይሰጥ የውርስ አጣሪውን ሪፖርት ማጽደቅ መሠረታዊ የህግ ስህተት አለበት ከሁሉም በላይ በጣልቃ ገብ ተከራካሪነት ቀርበን ባቀረብነው ክስና ማስረጃ መሠረት በክርክር የተያዘው ሀብት የወሮ ጥሩወርቅ አስፋውና የአቶ አበበ ከበደ የጋራ ንብረት እንደሆነ በማረጋገጥ ፍርድ ቤቱ ንብረቱን በአደራ የያዙትና በሥር ፍርድ ቤት ተከሳሽ የነበሩት እነ ፈንታዬ ወዮሐንስ ንብረቱን ለከሳሾች ተጠሪዎች እና ለጣልቃ ገብ ያስረክቡ ጣልቃ ገብ ተከፋይ ናቸው በማለት ውሣኔ የሰጠበትን ጉዳይ የውርስ አጣሪው ከተሰጠው ስልጣን ውጭ በማከራከር ውሣኔ መስጠቱና ፍርድ ቤቱም ተቀብሎ ማጽደቁ መሠረታዊ የህግ ስህተት በመሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት አመልክተዋል ተጠሪዎች በበኩላቸው የባልና የሚስቱ ግንኙነት ከተቋረጠ ሰላሣ አመት የሆነው በመሆኑ አቶ አበበ ከበደ ከዚህ በፊት የመጥፋት ውሣኔ የተሰጠባቸው በመሆኑ የውርስ አጣሪው ንብረቱ የግል ነው ወይስ የጋራ የሚለውን አጣርቶ አንዲወሰን የተሾው በመሆኑና ይህንንም ያደረገው ፍርድ ቤቱ በሰጠው ስልጣን መሠረት በመሆኑ በአጠቃላይ በውርስ አጣሪውም ሆነ በሥር ፍርድ ቤት የተፈፀመ የህግ ስህተት የሌለ በመሆኑ የአመልካች አቤቱታ ውድቅ ይደረግልን በማለት ሀምሌ ቀን ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበዋል አመልካች በበኩላቸው ሟች አበበ ከበደ በህይወት አለመኖራቸው የተረጋገጠው ዓም በመሆኑ ከዚህ ጊዜ በፊት የተፈራው ሀብት የጋራ ሀብት ነው የቤቱ ፕላንና ሥራው የተፈቀደው ከአቶ አበበ ከበደ በመሆኑ ቤቱ የጋራ ንብረት ስለመሆኑ የሚያከራክር አይደለም ሌሎች ንብረቶች መኪና በባንክ የተያዘው ገንዘብ እና ልዩ ልዩ ጌጣጌጦች የጋራ ሀብት ናቸው የውርስ አጣሪው ከማጣራት ተግባር ወጥተው ህግ የመተርጐም ሥራ የሠሩ በመሆናቸውና ፍርድ ቤቱም ይህንኑ ተቀብሎ የፀደቀ በመሆኑ መሠረታዊ የህግ ስህተት በሥር ፍርድ ቤቶች በኩል ተሰርቷል በማለት የመልስ መልስ አቅርበዋል ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር ደረጃ ግራ ቀኙ በኩል የቀረበው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው ኛ ተጠሪዎች የሟች የወሮ ጥሩወርቅ አስፋው ንብረት ነው በማለት ዘርዝረው በእነ አቶ ፈንታዬ ወልደዮሐንስ ላይ ክስ አቅርበው ሲከራከሩበት የነበረው ንብረት የአመልካች አውራሽ የአቶ አበበ ከበደ የጋራ ሀብት መሆኑ በፍርድ ተወስኗል ወይስ አልተወሰነም። የሚለውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም የውርስ አጣሪው ለፍቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት ቁጥሩ የሆነው ቤት አዋጅ ቁጥር ከመውጣቱ በፊት ሟች ወሮ ደጊቱ ደንጓሬ ለወሮ አሰለፈች ወርዶፋ በስጦታ የሰጡዋቸው በመሆኑ የውርስ ሐብት አይደለም በማለት ወስኛለሁ ቁጥሩ የሆነው ቤትም የወሮ አስናቀች ወርዶፋ የኑዛዜ ድርሻ ነው አመልካች ስጦታዎቹ ፈራሽ ናቸው በማለት ቢከራከሩም የሚፈርስበትን ምክንያት አልገለፀም ስጦታው እንዲፈርስ በፍርድ ቤት ጠይቀው ያስፈረሱበትን የፍቤት ውሳኔ አላቀረቡም በማለት ያሰፈሩዋቸው ድምዳሜዎች ንብረቶቹን የማከፋፈል ዓይነት ሥራ ያከናወኑ መሆኑን እንደሚጠቁሙ ለመረዳት ችለናል በፍብሕቁ እንደተደነገገው የአጣሪው ሥራ ሟቹ አንድ ኑዛዜ ትቶ አንደሆነ መፈለግና በመጨረሻው ውርሱ የሜደርሳቸው ሰዎች እነማን እንደሆኑ ማረጋገጥ የውርሱን ሃብት ማስተዳደር መክፈያቸው የደረሰውን የውርስ አዳዎች መክፈል እና ሟቹ በኑዛዜ ያደረጋቸውን ስጦታዎች መክፈልና የኑዛዜውን ቃል ለመፈፀም ማንኛቸውም ሌሎች አስፈላጊ ጥንቃቄዎች ማድረግ ነው እነዚህ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት በሚያከናውንበት ጊዜ ደግሞ በኑዛዜው የውርስ ንብረት መሆናቸው ተጠቅሶ የክፍፍል ስርአትም የተቀመጠላቸውና ወራሾች በሙሉ የተስማሙባቸው ንብረቶችና መክፈያቸው የደረሰው የውርስ አዳዎች ሲኖሩ በወራሾቹ ስምምነት መሰረት ንብረቶቹን ሊያከፋፍል አዳዎችንም ሊከፍል ይችላል በነዛዜው ላይ በተጠቀሱትና ባልተጠቀሱት ንብረቶች የውርስ ዛብት መሆን ያለመሆኑ ላይ ወራሾቹ ያልተስማሙና ክርክር ያስነሱ ከሆነ ግን የአጣሪው ሥራና ሐላፊነት ወራሾች የተስማሙባቸውን ንብረቶች የውርስ ሃብት መሆናቸው መመዝገብ ወራሾች ያልተስማሙባቸው ንብረቶችና እዳዎች ካሉ ደግሞ ማስረጃ በመሰማት ማስረጃው ምን እንደሚያስረዳ ሪፖርቱ ላይ በማስፈር እንዲያጣራ ላዘዘው ፍቤት ማቅረብ እንጅ ንብረት አጣሪው ይህ ንብረት የውርስ ሐብት አይደለም የሚሉ ወራሾች ቢኖሩም ማስረጃ በመስማት የውርስ ሃብት መሆኑን ስለተገነዘብኩኝ ንብረቱ የውርስ ህብት ነው በማለት ወስኛለሁ ወይም ደግሞ ማስረጃውን እንደተመለከትኩት ንብረቱ የውርስ ሐብት ያለመሆኑን ስላረጋገጥኩኝ የውርስ ሐብት አይደለም በማለት ወስኛለሁ ለማለት የሚያስችለው ሥልጣን የለውም በዚህ ጉዳይ የውርስ አጣሪው ያደረጉትን የማጣራት ሥራ ስንመለከተው ወራሾቹ የውርስ ሐብት ናቸው በሚሉዋቸው ሁለቱም ቤቶች ላይ ገና ከጅምሩ አንስቶ ያልተስማሙና ክርክር ያነሱ በመሆኑ አጣሪው ማስረጃ መስማታቸው በአግባቡ ነው ሁኖም አጣሪው በወራሾች መካከል የተደረገው ክርክር ምን እንደነበረ የኑዛዜ ወራሾችና የሕግ ወራሾች እነማን እንደሆኑ የግራ ቀኙ ማስረጃ ምን አንደሚመልስ ወራሾች የተማመኑባቸውና ያልተማመኑባቸው የውርስ ንብረቶችና እዳዎቹ ምን ምን እንደሆኑ በመዘርዘር ሪፖርት ማዘጋጀት ሲኖርባቸው ከዚህ አልፈው ወራሾችን አከራከረው ማስረጃ ከሰሙ በጊላ ክርክሩን ማስረጃውን ከሕግ ጋር በማገናዘብ ይህ ንብረት የእገሌ እንጅ የአገሌ አይደለም በማለት መወሰናቸው ከተሰጣቸው የውርስ አጣሪነት ሥልጣን በላይ በመሄድ መደመኛ ፍቤት የሚያከናውነውን የዳኝነት ሥራ ውስጥ መግባታቸው ተገቢ ያለመሆኑን ተገንዝበናል ውርስ አጣሪው አዘጋጅተው ያቀረቡት ሪፖርት ውሳኔም ጭምር ያዘለ በመሆኑ ሪፖርቱ በቀረበለት ፌመደፍቤት መጽደቁ ደግሞ በአጣሪው የተወሰነው ነገር በፍቤት ተቀባይነት አግኝቶ የፀደቀ ተደርጐ ስለሚወሰድ አመልካች አዲስ ክስ አቅርበው የውርስ ድርሻቸውን ሊያገኙ የሚያስችላቸው መብት የሚያጣብብ ነው የሚሆነው በመሆኑም ፏ የፌመደፍቤት ሪፖርቱን መርምሮ ያለበትን ጉድለት እንዲያስተካክል ማድረግ ሲገባው አንዳለ ተቀብሎ ማጽደቁ ተገቢ ሆኖ አልተገኘም ስለዚህ የውርስ ንብረት አጣሪው ያቀረቡት ሪፖርት የአጣሪንና የመደበኛ ፍቤትን ሥራ አጠቃሎ የያዘ በመሆኑ ሪፖርቱ በአግባቡ የተዘጋጀ ባለመሆኑና የፌመደፍቤት ሪፖርቱን ያፀደቀበትና የፌከፍቤት ደግሞ የቀረበለትን ይግባኝ የሰረዘበት ትአዛዝ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለተገኘ የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ የፌመደፍቤት በመቁ ጥር ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝና የፌከፍቤት በመቁ ሕዳር ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽረዋል የሥር ፍቤት የውርስ ማጣራት ሪፖርቱን ያፀደቀው ከነጉድለቱ ጭምር በመሆኑ መጽደቅ አልነበረበትም ብለናል በመሆኑም የሥር ፍቤት እንደገና አጣሪ ሾሞ የውርስ ማጣራቱን ሥራ በፍብሕቁ መሰረት እንዲጣራ በማስደረግ ሪፖርቱ በአግባቡ የቀረበ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ በሕጉ መሰረት አስፈላጊውን እንዲፈጽም በማለት ወስነናል ይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን እንዲችሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መለሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ መድንን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም አመልካች ወሮ አየለች አልታዬ ቀረቡ ተጠሪ ወሮ አስናቀች አየለ ቀረቡ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ በሰበር የቀረበው የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እና ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የፌዴራል የከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ስላለበት በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ሰኔ ቀን ዓም ባቀረበችው አቤቱታ ስለጠየቀች ነው የክርክሩ መነሻ አመልካች የሕፃን ዮናስ ወንድሙና የያሬድ ወንድሙ ወላጅ አናት እና ሞግዚት መሆኗን ገልፆ የሞግዚት አድራጊዎች ወላጅ አባት አቶ ወንድሙ ገብረየስ መጋቢት ቀን ዓም በሞት ተለይተዋል ሟች አቶ ወንድሙ ከተከሣሽ ከተጠሪ ጋር በባልና ሚስትነት እያሉ በአዲስ አበባ ከተማ ወረዳ ቀበሌ ቁጥሩ የሆነ መኖሪያ ቤት ሠርተዋል ስለዚህ የመኖሪያ ቤቱን ግምትና ቤቱን ለሱቅና ለሆቴል እያከራየች የምታገኘው ገንዘብ ጭምር የሕፃኖቹ ወላጅ አባት የጋራ ሀብት በመሆኑና የውርስ ሀብት ክፍል እንድታካፍለኝ ውሣኔ ይሰጥልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል ተጠሪ የውርስ ንብረት ክፍል ነው የተባለውን ሀብት አስመልክቶ የተለያየ ክርክርና ማስረጃ ያቀረበች ሲሆን ወሮ ጥሩወርቅ ወንድሙ የተባለች ሴት በበኩሏ የሟች ወንድሙ ገብረየስ ወራሽ እና ልጅ ነኝ በማለት የወራሽነት ማስረጃዋን በማያያዝ በክርክሩ ጣልቃ ገብታለች ፍርድ ቤቱ ቤቱና ሌሎች ንብረቶች ተገምተው እንዲቀርቡለት ትእዛዝ ሰጥቶ የፍርድ አፈፃፀም መምሪያ መሀዲስ የቤቱ ጠቅላላ ዋጋ ብር አስራ ዘጠኝ ሺ ስምንት መቶ ፃያ ሶስት ብር ከአርባ ሰባት ሣንቲም ነው በማለት አስተያየት አቅርቧል ከዚህ በኋላ የቤቱ ግማሽ ባለቤትነት የተጠሪ የቤቱ ግማሽ ባለቤትነት ደግሞ የአመልካች ሞግዚት አድራጊዎችና የወሮ ጥሩወርቅ ወንድሙ መሆኑን ከዘረዘረ በኋላ ተጠሪና ወሮ ጥሩወርቅ ወንድሙ ለአመልካች ብር አምስት ሺ አምስት መቶ ፃምሣ አንድ ብር ከፃያ አንድ ሣንቲም በመክፈል ቤቱን በጋራ እንዲያስቀሩ ይህንን ማድረግ ካልቻሉ በሀራጅ እንዲሸጥ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርባ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሣኔ አጽንቷል አመልካች ልጆቹን ማሣደጊያ ቤት የለኝም ንብረቱ በአይነት መካፈል እየተቻለ ተጠሪ ትጠቅልለው መባሉ ተገቢ አይደለም ንብረቱም መሸጥ ካለበት መሀዲሱ ባቀረበው ግምት ሣይሆን በሀራጅ መሆን ይገባዋል የዳኝነት በጋራ ክፈሉ መባሉ ተገቢ አይደለም በአጠቃላይ የሥር ፍርድ ቤቶች ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለበት በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ያመለከተች ሲሆን ተጠሪ በበኩሏ ቤቱ አመልካችና ተጠሪ ባሉበት በመሐንዲስ የተገመተ በመሆኑ እአና በአይነት ሊከፈል የማይችል በመሆኑ አመልካች ያቀረበችው አቤቱታ ሕጋዊ መሠረት የለውም የሚል መልስ የሰጠች ሲሆን አመልካች የመልስ መልስ አቅርባለች ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር የተደረገው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን አኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው የክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት ሟች ወንድሙ ገብረየስ እና ተጠሪ በባልና ሚስትነት ሲኖሩ በጋራ የሰሩት ቤትና የጋራ ንብረት መሆኑ አልተካደም ሟች ወንድሙ የሞተ በመሆኑ አሱ በቤቱ ላይ ያለው የጋራ ባለቤትነት መብት ለወራሾቹ ዮናስ ወንድሙ ያሬድ ወንድሙና ወርቅነሽ ወንድሙ በፍትሐብሔር ሕግ ቀጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይተላለፋል ስለሆነም የቤቱ የጋራ ባለንብረቶች የሟች ወንድሙ ገብረየስ ወራሾች እና ተጠሪ ናቸው የማይንቀሣቀስም ንብረት የጋራ ባለቤት የሆኑ ሰዎች የማይንቀሣቀሰውን ንብርት በአይነት ለመከፋፈል የሚችሉ ከሆነ በአይነት መከፋፈል እንደሚችሉ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የተደነገገ ሲሆን ንብረቱ በአይነት መከፋፈል የማይቻል ሲሆን በሀራጅ ተሸጦ ገንዘቡን እንደሚከፋፈሉ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ተደንግጓል ከዚህ አንፃር ንብረቱ በአይነት ለመከፋፈል የሚችል ከሆነ የሟች ወራሾች እና ተጠሪ ንብረቱን እኩል መከፋፈልና የሟች ወራሾች ድርሻቸውን በስምምነት የሚከፋፈሉበት ዕድል ሊሰጣቸው ይገባል ስለሆነም ቤቱ በአይነት ለመከፋፈል የሜቻል ሲሆን አመልካችና ተጠሪ ቤቱን በአይነት እንዲካፈሉ ትአዛዝ መስጠት ሲገባቸው አላግባብ ያለፉት በመሆኑ ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል ከላይ በተገለፀው መንገድ ቤቱ በአይነት ለመከፋፈል የሚችል ካልሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት ግልጽ ሀራጅ ወጥቶ መሸጥ ይገባዋል ተጠሪም ሆነች አመልካች የቤቱን ዋጋ በመክፈል የቅድሚያ ግዥ መብታቸው የሚጠበቀው ቤቱ በግልጽ ጨረታ ያወጣውን ከፍተኛ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዝግጁ ሆነው ሲገኙ እንጅ መሀዲሱ ገምቶ ያቀረበውን ዋጋ ገቢ በማድረግ አይደለም ስለሆነም አመልካችና ተጠሪ ቤቱ በግልጽ ሀራጅ የሚያወጣው ዋጋ መሠረት ለማስቀረት የሚስማሙ ከሆነ በስምምነታቸው መሠረት መፈፀም አለበት አመልካች አና ተጠሪ የማይስማሙ ከሆነ ግን ቤቱ በግልጽ ሐራጅ ተሸጦ የሟች ወራሽ የሆኑት ሶስት ልጆች ግማሹን ለሶስት እኩል እንዲካፈሉ ተጠሪ ደግሞ የቤቱን ግማሽ ዋጋ እንድትወስድ መደረግ ይገባዋል ከዚህ በተጨማሪ አመልካች በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ባቀረበችው ክስ መሠረት በክርክሩ ፊት ሆና እያለ ከተጠሪ ጋር ዳኝነት በጋራ እንድትከፍል የሰጠው ውሣኔ ተገቢነት የሌለውና መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሚያዚያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ አመልካችና ተጠሪ የሚቻል ከሆነ ቤቱንና ቦታውን በአይነት እንዲከፋፈሉ ቤቱን በአይነት ለመከፋፈል የማይችሉ ከሆነ በግልጽ ጨረታ በሀራጅ ተሸጦ ግማሹን ተጠሪ እንዲወስዱ ግማሹን የሟች አቶ ወንድሙ ወራሾች ለሶስት አኩል እንዲካፈሉ በማለት ወስነናል በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዳኝነት ወጭ ተጠሪ ብቻዋን መሸፈን አለባት ብለናል በዚህ ፍርድ ቤት ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ለየራሣቸው ይቻቻሉ ይህ ፍርድ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ዐ ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም አመልካች ተስፋዬ አርጋው ጠበቃ አቶ ጎበና እጅጉ ቀረቡ ተጠሪዎች ጠጅቱ አርጋው ቀረቡ በለጠ አርጋው ቀረቡ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ ለሰበር የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ዐ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት ሐምሌ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው አቤቱታ ስለጠየቀ ነው ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው በምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛው ፍርድ ቤት አመልካች በከሳሽነት ቀርቦ አባታችን አቶ አራጋው ሀብቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል አባቴ በሕይወት እያለ ግንቦት ዐ ቀን ኑዛዜ ያደረገ ስለመሆን ኑዛዜውም ግንቦት ቀን ዐ ዓም በመናገሻ አውራጃ ፍርድ ቤት ፀድቋል አባቴ ለእኔ በኑዛኔ የሰጠኝ ንብረት በተከሣሾች እና ለእኔ ደግሞ እንጀራ እናቴ የሆነችው ወሮ አስካለ ኃይለማርያም ጋር የጋራ ንብረት በመሆኑ የእኔና የጌታቸው አራጋው ድርሻ ንብረቱ ለሶስት ተከፍሉ እንዲያካፍሉኝ እና በገንዘብ ያገኙትን ጥቅም እንዲከፍሉ ውሣኔ ይሰጥልኝ በማለት በተጠሪዎች ላይ ክስ አቅርቧል ተጠሪዎች በበኩላቸው የወሮ አስካለ ሀይለማርያም ልጆች መሆናቸውን ገልፀው ቤቱን በማከራየት ያገኘነው ጥቅም የለም ቤቱ በባለሙያ ይገመት የሚሉና ሌሎች የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ አቅርበው ተከራክረዋል ፍርድ ቤቱ በአዲስ አለም ከተማ ቁጥሩ ዐ የሆነው ቤት እንዲገመት ትእዛዝ ሰጥቶ የቤቱ ግምት ሀምሣ አንድ ሺ ስምንት መቶ አርባ ስድስት ብር ከሰባ አራት ሣንቲም መሆኑን የባለሙያ አስተያየት ቀርቧል ፍርድ ቤቱም የአሁን አመልካች ውርሱ ለሶስት ተከፍሉ የአሱንና የወንድሙ ጌታቸው አራጋው ድርሻ እንደሚወስድና የተጠሪዎች ድርሻ ብር አስራ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ሰማኒያ ሁለት ብር ከአስራ ስድስት ሣንቲም በመክፈል ቤቱን በኑዛዜው መሠረት በግሉ እንዲያደርግ በማለት ወስኗል በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ተጠሪዎች ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ አቅርበው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የአመልካችንና የተጠሪዎችን የይግባኝ ክርክር ከሰማ በሏላ ተጠሪዎች የንብረቱ ግማሽ ዋጋ ማለት ሀያ አምስት ሺ ዘጠኝ መቶ ፃያ ሶስት ከፃያ አራት ሣንቲም መሆኑን ከገለፀ በኋላ ተጠሪዎች የአመልካችን ድርሻ ብር ፃያ አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ፃያ ሦስት ብር ከአርባ ሳንቲም ከፍለው ቤቱን እንዲያስቀሩ ተጠሪዎች ካልቻሉ አመልካች የእነርሱን ድርሻ ከፍሉ እንዲያስቀር ይህ ካልሆነ በጨረታ ተሸጦ ግማሹን አመልካች ግማሹን ተጠሪዎች እንዲወስዱ በማለት የከፍተኛው ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሣኔ በማሻሻል ውሣኔ ሰጥቷል አመልካች ይህንን ፍርድ በመቃወም ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበ ቢሆንም መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለም ተብሎ አቤቱታው በሰበር ችሎቱ ውድቅ ሆኗል አመልካች ይህ ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት ቤቱና ቦታው በአይነት ለመከፋፈል የሚችል ንብረት በመሆኑ በአይነት እንድንከፋፈል እንዲወስንልን ይህ የማይሆን ከሆነ በሀራጅ ተሸጦ እንድንከፋፈል መወሰን ሲገባው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት የቤቱ ግምት ግማሽ ዋጋ ብቻ ተጠሪዎች ከፍለው ቤቱን እንዲወስዱ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ ይታረምልኝ በማለት ያመለከተ ሲሆን ተጠሪዎች በበኩላችን በቤቱ ላይ ወጭ አውጥተናል ቤቱን በአይነት መካፈል አይቻልም ቤቱን የያዝነው አኛ ስለሆንን ለአኛ ቅድሚያ መስጠቱ ተገቢ ነው የሚል መልስ የሰጡ ሲሆን አመልካች የመልስ መልስ አቅርበዋል ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር የተደረገው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም ጉዳዩን መርምረናል ጉዳዩን እንደመረመርነው ክርክር የተነሣበት ንብረት የሟች አቶ አራጋው ሀብቱና የሟች የወሮ አስካለ ሀይለማርያም በባልና ሚስትነት ያፈሩት የጋራ ሀብት እንደሆነ አመልካችና ተጠሪዎች አልተካካዱም እንደዚሁም የሟች አቶ አራጋው ወራሽ አመልካቿ የሟች የወሮ አስካለ ወራሾች ደግሞ ተጠሪዎች መሆናቸው በግራ ቀኙ የታመነ ጉዳይ ነው ስለሆነም ሟች አቶ አራጋው በቤቱ ላይ ያላቸው የጋራ ባለቤትነት መብት ለአመልካች ሟች ወሮ አስካለ በቤቱ ላይ ያላት የጋራ ባለቤትነት መብት ደግሞ ለተጠሪዎች በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይተላለፋል ከላይ ከተጠቀሰው የሕግ ድንጋጌ መሠረትም አመልካችና ተጠሪዎች የቤቱ የጋራ ባለሀብቶች ናቸው የጋራ ሀብት የሆነ ንብረት በአይነት መከፋፈል የሚቻል በሆነ ጊዜ የጋራ ባለሀብቶቹ በአይነት ሊከፋፈሉት አንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የሚደነግግ በመሆኑ የመጀመሪያው አማራጭ ንብረቷ በአይነት የሚከፋፈል ከሆነ አመልካች አና ተጠሪዎች ቤቱንና ቦታውን እኩል ለሁለት እንዲከፋፈሉት ማድረግ ነው በዚህ አንፃር የሥር ፍርድ ቤቶች ይህንን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚችል አማራጭ ያለፉ በመሆኑ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሰርተዋል ንብረቱ በአይነት ለመከፋፈል የሚያስቸግር ከሆነ በግልጽ ጨረታ ወጥቶ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሸጥና አመልካችና ተጠሪዎች እኩል መካፈል ይገባቸዋል የቤቱን ዋጋ ክፍያ አስቀራለሁ የሚል ወገን ካለ መክፈል የሚገባው ቤቱ በሀራጅ ያወጣውን የገበያ ዋጋ ግምት እንጂ በመሐንዲስ የተገመተውን ዋጋ አይደለም ስለሆነም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ከላይ የተገለጹትን ግልጽ የሕግ ድንጋጌዎች በመተላለፍ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሻሽሏል ይፃፍ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉሎት በመዝገብ ቁጥር ዐ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ይፃፍ ክርክር የተነሳበት ቤት በአይነት ለመከፋፈል የማይቻል ከሆነ አመልካችና ተጠሪዎች ንብረቱንና ቦታውን እኩል ይካፈሉ ብለናል ንብረቱ ለመከፋፈል የማይቻል ካልሆነና አመልካችና ተጠሪዎች በገበያ ዋጋ አንዳቸው የሌላውን ድርሻ ከፍለው ንብረቱን ለማስቀረት ያልተስማሙ እንደሆነ ንብረቱ በሀራጅ ተሸጦ የንብረቱን ዋጋ ግማሽ አመልካች ቀሪውን ግማሽ ደግሞ ተጠሪዎች ይውሰዱ ብለናል በዚህ ፍርድ ቤት ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል ይህ ፍርድ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሰኔ ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ሠልጣን አባተማም አመልካች ወሮ ባዮሽ ደጀኔ ከጠበቃ ዳኛቸው ተስፋዬ ጋር ቀረበች ተጠሪዎች ወሮ ፃሳብ ከፋይ ጌራወርቅ ቀረበች ደረጀ ጌራወርቅ አልቀረበም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ ኑዛዜን መሠረት በማድረግ የቀረበውን ክርክር የሚመለከት ነው ከመዝገቡ እንደሚታየው ክርክሩ በተጀመረበት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመጀመያ ደረጃ ፍቤት የአሁንዋ አመልካች ሟች አቶ ጌራወርቅ ህሩይ ባለቤትዋ አድርገውት ያለፉት ኑዛዜ መሠረት ተደርጐ የወራሽነት ማስረጃ ይሰጣት ዘንድ በመጠየቅዋ ፍቤቱም ጥያቄዋን በመቀጠል የኑዛዜ ወራሽነት በማለት ማስረጃውን ሰጥቶአት ነበር በሌላ በኩል ደግሞ የአሁኖቹ ተጠሪዎች ማስረጃው መሰጠት አልነበረበትም በማለት መቃወሚያ በማቅረባቸው ናቤቱ ጉዳዮን በድጋሚ ያየ ሲሆን በመጨረሻም ሟች አድርገውታል የተባለውን ኑዛዜ ከፊሉን በመሻር የተወሰነውን ክፍሉን ደግሞ በማጽደቅ ወስኖአል በዚህ ላይ ከአሁንዋ አመልካች ይግባኝ የቀረበላቸው ይግባኝ ሰሚ ፍቤቶችም ውሳኔው ጉድለት የለውም ብለዋል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው አኛም አመልካች ነሐሴ ቀን ዓም በጻፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ጉዳዮን ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሳኔ አና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከላይ እደተመለከተው ክርክሩ ሊነሳ የቻለው ሟች አደረገው የተባለው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል የሚል ክስ በመቅረቡ ሳይሆን የፍብ ሕግ ቁ ኑዛዜውን መሠረት በማድረግ የወራሽነት ማስረጃ የምስክር ወረቀት ይሰጠኝ የፍብሕግ ቁ በማለት አመልካች ጥያቄ በማቅረብዋ ነው በፍትሐብሔር ሕጉ በግልጽ እንደተመለከተው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል በሚል የሚቀርበው ክስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ከሚቀርበው ጥያቄ አቤቱታ የተለየ ነው ጥያቄዎቹ የተለያዩ በመሆናቸውም የተለያዩ ውጤት ነው ያላቸው በፍሥሥሕግ ቁ እንደተደነገገው ወራሽነኝ የሚል ማንኛውም ሰው የወራሽነት ምስክር ወረቀት ይሰጠው ዘንድ ለፍቤት ሊያመለክት ይችላል ፍቤቱም ጥያቄውን ከመቀበሉ በፊት ጠያቂው ማስረጃዎቹን ሁሉ እንዲያቀርብ በማድረግ እና አስፈላጊ መስሎ የታየውን ዋስትና እንዲሰጥ በማስገደድ ጭምር ዋስትናውን ካገኘ በኋላ የተጠየቀውን የምስክር ወረቀት ሊሰጥ እንደሚችል በፍብሕግ ቁ ተመልክቶአል በሌላ በኩል ደግሞ ፍቤቱ የአመልካቹን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ሰጥቶት የነበረው የወራሽነት የምስክር ወረቀት ሊሰረዝው እንደሚችል በፍብሕግ ቁ የተቀመጠው ድንጋጌ ያመለክታል ከዚህ አንግዲህ መገንዘብ እንደሚቻለው የምስክር ወረቀቱ በጠያቂው አቤቱታ መነሻነት የሚሰጥ ቢሆንም የተሰጠው ያለአግባብ ነው የሚል መቃወሚያ ሊቀርብ የሚችልበት ሁፄታ መኖሩንና መቃወሚያው ተገቢ ሆኖ ከተገኘም የምስክር ወረቀቱ የሚሰረዝ መሆኑን ነው ወደ ያዝነው ጉዳይ ስንመለስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት አንዲሰጥ ጥያቄ የቀረበበት ፍቤት ጥያቄውን ተቀብሎ የምስክር ወረቀቱን ሰጥቶ እንደነበር አእንመለከታለን ይህም በፍብሕግ ቁ የተመለከተውን ድንጋጌ ተከትሎ የተፈጸመ በመሆኑ ትክክል ነው ሌላው ቀጥለን የምናየው ተጠሪዎች የተሰጠውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት በመቃወም መቅረባቸው ሲሆን ፍቤቱም መቃወሚያውን መሠረት በማድረግ ለምስክር ወረቀቱ መሰጠት መሠረት የሆነውን ኑዛዜ ይዘት እና ሕጋዊነትን መርምሮአል በመጨረሻም ኑዛዜውን በከፊል በመሻር በከፊል ደግሞ አጽድቄአለሁ ብሎአል በበኩላችን ትክክለኛ አካፄድ ሆኖ ያላገኘነውም ይኸው ነው በመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቱ በሕጉ የተቀመጠውን ድንጋጌ መሠረት በማድረግ ኑዛዜው ፈራሽ ነው እንዲባል ክስ አልቀረበለትም የፍቤቱ የዳኝነት ስልጣን የተወሰነ በመሆኑ በስልጣን ክልሉ ስር የሚወድቀውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ነው ጥያቄ የቀረበለት ይህን ጥያቄ ተቀብሎ ሰጥቶት የነበረው የምስክር ወረቀት ተጠሪዎች ካቀረቡለት መቃወሚያ አንጻር ሲመዝነው ተገቢ አልነበረም የሚል ድምዳሜ ከደረሰም በፍብሕግ ቁ በተደነገገው መሠረት መሠረዝ ነው የነበረበት ከዚህ አልፎ ኑዛዜው ፈራሽ ይባል በሚል ክስ በቀረበ ጊዜ ሊደረግ አንደሚችለው ሁሉ ኑዛዜውን በከፊል ሽሬአለሁ ማለቱ ትክክል አይደለም የሕግ መሠረትም የለውም ከሁሉ በላይ ደግሞ ፍቤቱ ወደ ኑዛዜው ይዘት እአና ሕጋዊነት ሁኔታ ገብቶ ውሳኔ መስጠት የሚችልበት ሕጋዊ መንገድ አልነበረውም እንጂ ሕጋዊ መንገድ ነበረው ተብሉም ቢሆን ኖሮ የደረሰበት መደምደሚያ የኑዛዜ ፎርም አና ማስረጃ ከሚመለከተው ሕግ አንፃር ሊታይ ፍጹም የተሳሳተ ነው ለክርክሩ መነሻ የሆነው ነዛዜ በግልጽ የተደረገ ነዛዜ እንደሆነ በፍቤቱ ውሳኔ ተመልክቶአል በግልጽ የተደረገ ኑዛዜ ሊያሟላቸው የሚገቡ በፍብሕግቁ የተመለከቱት መስፈርቶች ያሟላ እንደሆነም ፍቤቱ ማረጋገጡን በውሳኔው ላይ አመልክቶአል ይህን ሁሉ ካረጋገጠ በኋላ በከፊል ሽሬዋለሁ ያለው ሟች ንብረቱ ባልሆነው ንብረት ላይ ጭምር ተናኮዞአል በሚለት እንደሆነ ከውሳኔው ይዘት ለመገንዘብ ችለናል በሕጉ በግልጽ እንደተመለከተው በግልጽ የተደረገው ኑዛዜ በሕጉ መሠረት አልተደረገም ተብሉ ሊነቀና የሚችለው በፍብሕግቁ የተቀመጡትን መስፈርቶች ያላሟላ ሆኖ ሲገኝ ነው የስር ፍቤት ኑዛዜውን ለመንቀፍ ምክንያት ያደገው ነጥብ የነዛዜውን ሕጋዊነት በተመለከተ አግባብነት የለውም ተናዛዝ የሱባልሆነው ንብረት ተናዞአል የሚባል ቢሆን የንብረት ክርክር ሲቀርብ እራሱን ችሉ የሚታይ ነው ፍቤቱ ይህን ነጥብ በማድረግ የኑዛዜውን ሕጋዊነት ፎርም መንቀፍ ተገቢ አይደለም የምንለውም በዚህ ምክንያት ነው ሲጠቃለል የስር ፍቤቶች የተጠሪዎችን መቃወሚያ መሠረት በማድረግ የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለት ሆኖ አግኝተነዋል ውሳኔ አቤቱታ የቀረበበት በድሬዳዋ ጊዜያዊ አስተዳደር የድሬዳዋ ከተማ የመጀመያ ደረጃ ፍቤት በመቁ የካቲት ቀን ዓም ተሰጥቶ በይባኝ ሰሚሜው ፍቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም በተሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሳኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽሮአል ቀደም ሲል ለአመልካች የተሰጠው የወራሽነት የምሰክር ወረቀት የሚሰረዝበት የሕግ ምከንያት የለም ብለናል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኙ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ፀመ የሰበር መቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አቶ ዓሊ መሐመድ አቶ ፀጋዬ አስማማው አቶ አልማው ወሌ አመልካች ወሮ አቦነሽ ምትኩ ቀረቡ ተጠሪ እነ አቶ አዳነ ፎላ ምስት ሠዎች አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዮ የተጀመረው በአለታ ወንዶ ወረዳ ፍቤት ሲሆን የአሁኗ አመልካች በዚህ ፍቤት የአቶ ንጋቱ ምትኩ ወራሽነት ተረጋግጦ ማስረጃ እንዲሠጣቸው አመልክተው ተቃዋሚ ካለ እንዲቀርብ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጐ የአሁኑ ተጠሪዎች ቀርበው አለን ያሉትን የተቃውሞ ክርክር ከአቀረቡ በላ ፍቤቱ አመልካች የሟች ወንድሟ ወራሽ መሆናቸውን በማረጋገጥ ማስረጃ ሠጥቷቸዋል ይህ የአመልካች የወራሽነት ማስረጃ የተሠጣቸው መስከረም ቀን ዓም ሲሆን ይህንኑ ማስረጃ አመልካች ከያዙ በኋላ ተጠሪዎች ላይ ህዳር ቀን ዓም ክስ መስርተዋል የክሱ ይዘትም ንብረትነቱ የሟች ወንድሜ የአቶ ንጋቱ ምትኩ የሆነውንና በአለታ ወንዶ ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን ቁጥሩ የሆነውን ቤት ተጠሪዎች ይዘው የሚጠቀሙበት ለመሆኑ ለቀው እንዲያስረክቡ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን ያሣያል የአሁነ ተጠሪዎችም በተከሣሽነታቸው ቀርበው ጥር ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ የመከላከያ መልሣቸውን አቅርበዋል ይዘቱም በአጭሩ የከሣሽ ክስ በፍሕቁ መሠረት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ንብረቱ በሟች እናት በኩል የመጣ በመሆነ ከሣሽ ከፍሕቁ ለ አኳያ የመውረስ መብት እንደሌላቸው ቤቱ ለሟች ንጋቱ ምትኩ እናት የሆኑት ወሮ የሺ ወንድሙ የተከሣሾች እናት ለሆኑት እህታቸው ለወሮ ፀሐይ ገኪዳን በስጦታ አስተላልፈው ሰጥተው ስጦታ ተቀባይ እስከ ዓም ድረስ በእጃቸው አድርገው ሲጠቀሙበት ቆይተው ከዚህ አለም በሞት ሲለዮ የአሁነ ኛ ተጠሪ የወሮ ፀሐይ ገኪዳን ወራሽነታቸውን በማረጋገጥ ቤቱን በእጃቸው ማድረጋቸውንና ከሣሽ በቤቱ ላይ አንዳችም መብት የሌላቸው መሆኑን በመዘርዘር ክሱ ውድቅ ሊሆን ይገባል በማለት መከራከራቸውን የሚያሣይ ነው ጉዳዮን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው የወረዳ ፍቤትም የይርጋ ክርክሩን በተመለከተ ከሣሽ እንዲለቀቅላት የጠየቀችው በዘር የመጣውን የውርስ ንብረት ስለሆነ የመብት ጥያቄዋ በፍሕቁ መሠረት በይርጋ አይታገድም ንብረቱ በእናት በኩል የመጣ ስላልሆነ መውረስ አትችልም የተባለውን በተመለከተም ወራሽነቷን አረጋግጣ መብት የላትም ተብሎ የተወሰነ በመሆኑና የቀረበ ተቃውሞም ስለሌለ ተቀባይነት የለውም በማለት የውርስ ንብረቱ እንዲጣራ ሲል ወስኗል በዚህ የፍቤቱ ውሣኔ የአሁኑ ተጠሪዎች ባለመስማማት ይግባኛቸውን ለሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው ፍቤቱም ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ ለጉዳዮ አግባብነት ያለው የፍሕቁ ስር የተመለከተው የይርጋ ጊዜ መሆኑን በመጥቀስ የአመልካች አቤቱታ የወራሽነት ማስረጃውን ከያዙ አምስት ዓመታት ያህል ቆይቶ የቀረበ በመሆነ በፍሕቁ ስር በተመለከተው የሦስት ዓመት ይርጋ ቀሪ ሊሆን የሚገባው ነው በማለት የወረዳውን ፍቤት ውሣኔ ሽሮታል የአሁኗ አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ለክልሉ ጠፍቤት ይግባኝ እና ሠበር ሠሚ ችሎቶች ቅሬታቸውን ቢያቀርቡም ተቀባይነት ሣያገኙ ቀርተዋል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ የበታች ፍቤቶች ውሣኔ ባለመስማማት ለማስለወጥ ነው አመልካች ታህሣስ ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት ሦስት ገጽ የሠበር አቤቱታ ጉዳዮ የመፋለም ክስ ሆኖ እያለ እና ከውርስ ክርክር ጋር የሚያገናኘው ነገር ሣይኖር በጉዳዮ ላይ የቀረበውን ክርክርና ማስረጃ ባላገናዘበ መልኩ አግባብነት የሌለውን ድንጋጌ በመጥቀስ ውሣኔ መስጠቱ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ይኸው ታርሞ ተጠሪዎች ቤቱን እንዲያስረክቡ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል የአመልካች አቤቱታ ተመርምሮ ተጠሪዎችን ያስቀርባል ተብሎ ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ መልሣቸውን አቅርበዋል አመልካችም በዚህ የተጠሪዎች መልስ ነሐሴ ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ የመልስ መልስ ሠጥተዋል የጉዳዮ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን ችሎቱም ይህንኑ አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መርምሮታል አንደመረመረውም የአመልካች ክስ የፍሕቁ ተጠቅሶ ውድቅ መደረጉ ባግባቡ ነው። የሚለውን ጭብጥ የስር ፍቤት ሊወስነው የሚገባ በመሆኑ በዚሁ ነጥብ ጉዳዮ ሊመለስለት የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል ሲጠቃለልም ከላይ የተገለፁት ምክንያቶች መሠረት የሚከተለው ተወስኗል ውሳኔ የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በፍመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሠጠውን ውሳኔ የደብብሕ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍቤት በፍይመቁ ጥር ቀን ዓም የሠጠውን ትአዛዝ የጠቅላይ ፍቤቱ ሠበር ሠሚ ችሎት በመቁ ህዳር ቀን ዓም የሠጠውን ውሣኔ በፍሥሥሕቁ መሠረት ሽረነዋል የአለታ ወንዶ ፍቤት የሠጠውን የይርጋንና የውርስ ማጣራት ብይን በተለወጠ ምክንያት በአብላጫ ድምጽ ሽረነዋል ለጉዳዮ ተፈፃሚነት ያለው የይርጋ ገደብ በፍሕቁ ስር የተመለከተው የክስር ዓመት ጊዜ በመሆኑ የአመልካች ጥያቄ በይርጋ ቀሪ አይሆንም ብለናል ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት የማን እንደሆነ የግራ ቀኙን ማስረጃዎችን በመመርመር ተገቢውን ውሣኔ ይሰጥበት ዘንድ ለአለታ ወንዶ ወረዳ ፍቤት በፍብሥሥሕቁ መሠረት መልሰንለታል ይፃፍ ወጪና ኪሣራ የየራሣቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መቤት ይመለስ የማይነበብ የአራት ዳኞች ፊርማ አለበት የሀሳብ ልዮነት አኔ ስሜ በሶስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰው ዳኛ አብላጫው ድምጽ በደረሰበት መደምደሚያ ላይ የምስማማ ቢሆንም አብላጫው ድምጽ የፍታብሔር ህግ ቁጥር የይርጋ ድንጋጌ በሁለት ወራሾች መካከል ያለን ክርክር ለመፍታት ነው የሚያገለግለው በሚለው የህግ አተረጓጐም ተገቢ አይደለም የሚል ሀሳብ ስላለኝ ይህንን ልዮነት ለመፃፍ ተገድጃለሁ የፍታብሔር ሕግ ቁጥር የይርጋ ድንጋጌ በወራሾች መካከል ለሚደረግ ክርክር ሣይሆን አውነተኛ የሟች ወራሽ በሆነ ሰውና የሟች ወራሽ ባልሆነ ሰው መካከል የሚያገለግል ስለመሆኑ ከፍታብሔር ህግ ቁጥር እስከ ፍታብሔር ህግ ቁጥር ድንጋጌዎች አቀራረጽና ይዘት በማየት ለመረዳት ይቻላል ህግ አውጭ የሟች የኑዛዜ ወይም ያለ ኑዛዜ ወራሽነኝ በማለት በፍታብሔር ህግ ቁጥር መሠረት የወራሽነት የምስክር ወረቀት ያወጣ ሰው እውነተኛው የሟች ወራሽ የወራሽነት ጥያቄ ሲያቀርብ የተሰጠው የወራሽነት የምስክር ወረቀት ፍርድ ቤቱ ለመሰረዝ አንደሚችል የፍታብሔር ህግ ቁጥር ይደነግጋል የወራሽነት ጥያቄ በማንና እንዴት ሊቀርብ እንደሚችል የተደነገገው ፍታብሔር ሕህ ቁጥር ነው ስለዚህ አንድ ሰው አውነተኛ የሟች ወራሽ ሣይሆን የወራሽነት ሰርተፍኬት በመያዝ የሟችን ንብረት ከወሰደ አውነተኛው ወራሽ የአሱን ወራሽነት እንደታወቀለትና የውርስ ንብረቱም አንዲመለስለት የሚያቀርበው ክስና የክሱ ማቅረቢያ ጊዜ በፍታብሔር ህግ ቁጥር እና ከፍታብሔር ህግ ቁጥር ተደንግጓል አውነተኛ ወራሽ በሆነው ሰውና አውነተኛ ወራሽ ባልሆነ ሰው መካከል የሚደረግ ክርክር በሟች ወራሾችና ወራሽ ባልሆነ ሌላ ሰው መካከል የሚደረግ ክርክር ነው ስለሆነም የፍታብሔር ህግ ቁጥር የሚያገለግለው በሟች ወራሾች መካከል ለሚደረግ ክርክር የሚሠራ አይደለም የሟች ወራሽ ለመሆን የግድ የወራሽነት ሰርተፍኬት መያዝ አያስፈልግም የሟች የኑዛዜ ወይም የህግ ወራሽ መሆኑን ቢውርስ አጣሪ በኩል ለማረጋገጥ አንደሚቻል የውርስ ህግ ድንጋጌዎችን ለማየት ለመረዳት ይቻላል በወራሽነት መካከል የሚነሣው ክርክር የድርሻ ጉዳይ ሲሆን አሱም በፍታብሔር ህግ ቁጥር መሠረት የሚታይ ነው ስለዚህ የፍታብሔር ህግ ቁጥር በወራሾሽ መካከል ላይ ክርክር ነው የሚለው አተረጓጐም ካለመስማማት ይህንን የሀሳብ ልዮነት ጽፌአለሁ የማይነበብ የአንድ ዳኛ ፊርማ አለበት ፀመ የሰበር መ ቁ ጥቅምት ቀን ዒም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጉስ ወልዱ መስፍን ዕቁበዮናስ ሂሩት መለሰ አመልካች ወሮ የኋላሸት ተካ ወኪል የ አለቃ ፈጠነ ካሣሁን ቀረቡ ተጠሪ የለም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ነው ጉዳዩ ሊጀመር የቻለው የአሁንዋ አመልካች የወራሽነት የምስክር ወረቀት ይሰጣት ዘንድ በመጠየቅዋ ነው ጥያቄው የቀረበለት ፍቤት የወራሽነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ይሰጥ ዘንድ ጥያቄው መቅረብ ያለበት አውራሽ ነው በተባለው ሰው የመኖሪያ አድራሻ ለሚገ ው ፍቤት ነው የሟች የመኖሪያ አድራሻ አዲሰ አበባ ባለመሆኑም ፍቤቱ ጥያቄውን ማስተናገድ አይችልም በማለት ጥያቄውን ውድቅ አድርጉአል የከተማው አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍቤት እና የሰበር ችሉትም የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቱ የሰጠውን ውሣኔ አጽንተዋል አቤቱታው የቀረበውም በዚሁ ላይ ነው እኛም አመልካች መጋቢት ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችው አቤቱታ የስር ፍቤቶች ከሰጡት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል አመልካች ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ያመለከተችው የወላጅ አባትዋ ተካ ግዛው ወራሽ መሆንዋ ተረጋግጦ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጣት ነው በማመልከቻዋ ላይም የአባትዋ መኖሪያ ስፍራ የነበረው አዲስ አበባ መሆኑ ብትገልጽም በዚህ ረገድ ያቀረበቻቸው ምስክርችዋ ግን ሟች ይኖር የነበረው ከአዲስ አበባ ውጪ አላባ በተባለ ሥፍራ እንደሆነ ነው ያስረዱት ጥያቄው የቀረበለት ፍቤትም ይህንኑ ሁኔታ በፍብሕግ ቁ ከተመለከተው ድንጋጌ ጋር በማገናዘብ ውሣኔ ሰጥቶአል ፍቤቱ ለውሣኔው መሠረት ያደረገው የፍብሕግ ቁፋ የማገው በፍትሐብሔር ሕጉ በሁለተኛው መጽሐፍ« ስለውርስስለአወራረስ» በሚለው በአንቀጽ አምስት ሥር ነው የተያዘው ጉዳይም ውርስን ወይም አወራረስን የሚመለከት ነው ቁ በግልጽ የሚያመለክተው አንድ ሰው የሞተ እንደሆነ በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ በሆነበት ቦታ ውርሱ እንደሜከፈት ነው ይህ ድንጋጌ በመሠረታዊው ሕግ በከፎ ህህ ውሰጥ የሚገኝ ሲሆን ኛ የፍትሐብሔር ክርክሮች የሚመሩበትን የሥነ ሥርዓት ደንቦች በያዘው የፍትሐብሔር ሕግ ውስጥ የሚገ ው ቁም እንደዚሁ ተመሣሣይ ነገር ነው የሚሜናገረው ድንጋጌው በውርስ ምክንያት ስለሚቀርብ ክስ የሚል ርእስ ያለው ሆኖ ክሱ የሚቀርበው የውርሱ ክፍያ በተጀመረበት ቦታ ለማገ ው ፍቤት እንደሆነ ያመለክታል ከፍ ሲል እንደተገለፀውም የውርሱ ክፍያ የሚጀመረው ሟች በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ በሆነበት ቦታ ነው የአመልካች አባት በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ አዲስ አበባ አልነበረም ከዚህ የተነሣም ፍቤቱ ጥያቄው መቅረብ ያለበት ሟች በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው ሥፍራ በሆነበት ቦታ ላለው ፍቤት ነው በማለት ወስኖአል በበኩላችንም እንደምናየው ፍቤቱ በዚህ ረገድ የፈፀመው መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለም ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት የሥር ፍቤቶች ውሣኔ ፀንቶአል ጉዳዩ የተወሰነ በመሆኑ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ኸወ የሰመቁ ግንቦት ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ሐጐስ ወልዱ ወት ሂሩት መለሰ አቶ መድሕን ኪሮስ አቶ ሱልጣን አባተማም አመልካች ወሮ አልማዝ ታፈሰ ጠበቃዋ ቀርቧል ተጠሪ ወሮ የሺመቤት ትኩ አልቀረበችም ፍርድ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ጉዳይ የጀመረው በይርጋ አለም ከተማ መደረጃ ፍቤት ነው የአሁኗ አመልካች ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ የአባታቸው ወራሽ በመሆናቸው ንብረት ተጣርቶ ድርሻቸውን ተጠሪ እንዲያካፈሏቸው ጠይቀዋል ተጠሪም ለክሱ በሰጡት መልስ ክሱ በይርጋ ይታገዳል የሚልና ሌሎችም የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ካቀረቡ በኋላ ለጉዳዩ ሙሉ መልስ ሰጥተዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ ያየው ፍቤትም አመልካች ወራሽ መሆናቸውን ካወቁበት ጊዜ ጀምሮ ክስ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ አመት ያለፈው በመሆኑ ክሱ በፍህቁ መሰረት በይርጋ ይታገዳል በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ከዛም ለደብብሕክመጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት አቤቱታ አቅርበው ፍቤቶቹ ይግባኛቸውን ሣይቀበሏቸው ቀርተዋል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ሲሆን ችሎቱ የአመልካች ጥያቄ በፍህቁ መሰረት በይርጋ ይታገዳል መባሉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ አድርጓል ተጠሪም ቀርበው መልስ እንዲሰጡ መጥሪያ ደርሷቸው ባለመቅረባቸው የጽሁፍ መልስ የመስጠት መብታቸው ታልፎ ችሉቱ ጉዳዩን መርምራሯል ከመዝገቡ እና ከክርክሩ እንደተረዳነው የአመልካች አባትና ተጠሪዋ ባልና ሚስት የነበሩ ሲሆን የአመልካች አባት በመሞታቸው ምክንያት አመልካች በወራሽነታቸው የሚገባቸውን የአባታቸውን ድርሻ ተጠሪ እንዲያካፍሏቸው ጠይቀዋል ተጠሪም የአመልካች አባት የሞቱት ሰኔ ሲሆን ክሱ የቀረበው ግን ሐምሌ ቀን ዓም በመሆኑ በፍህቁ መሰረት ክሱ በይርጋ ይታገዳል በማለት ተከራክረዋል በመሆኑም ይህ ተጠሪዋ የሚከራከሩበት ድንጋጌ ለተያዘው ጉዳይ ተፈፃሚነት አለው ወይ።