Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የዉሀዐ ከበ ከሸ ቨ ርዐዞሃቦፀኮ ሃ የማሳተም መብት ስው በስተቀር ክጸሐፊው ወይም እርሱ በሕግ ከወከለው መጽሐፉን በምንም መልክ ለጥቅስ ካልሆነ በከፊል ወይም በሙሉ አባዝቶ እጥቅም ላይ ማዋል እንደሚያዳግታቸው የታወቀ ነው። በዕፅነት ተግባር ላይ ውሏል። ለዚህም ለውጥ በምከንያትነት የሚጠቀሰው የሶቭየት ኅብረት በዓለም ላይ የነበራትን ኃያልነት ማጣትዋ ነው። ለምሳሌ እሰራኤልን ለዘመናት በመደገፍዋ ብዙ ጠላቶችን ማፍራትዋ በገሐድ የታወቀ ጉዳይ ነው። ሆኖም በኢኮኖሚዋ መውደቅ የተነሣ ዕቅዷን ማሳካት እንደማትችል ስለ ገመተች ወዳጅ የሆኑ አገሮች እንዲተባበሯት በመማጸን ላይ ብትሆንም ሁሉም የውስጥ ችግር ሰላለበት የተሳትፎው መጠን ውሰን መሆኑ በተግባር እየታየ ነው። ዕቅዱ ተግባራዊ ሆኖ ውጤት እስከሚያሳይ ድረስ ባለሙያ የሆነው የሰው ኃይል ሥራ ፍለጋ ወደ ሌላው ዓለም ይሰደድ ይሆናል የሚል የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ መነገር በመቻሉ የአሜሪካን ሕዝብ ከወትሮው በበስጠ ሐሳብ ላይ ለመውደቅ በቅቶ የመኖር ትርጐሙ እየጠፋው በመሄድ ላይ ይገኛል። የአገር ውስጥ የሕዝብ ደኅንነት ጥበቃው መጠናከር በኢትዮጵያውያን ላይ ምን ችግር አስክተለ። አዲስ የታወጁት የውጭ አገር ዜጎችን መቆጣጠሪያ ደንቦች በተለይ ዜግነታቸውን ላልለወጡ ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው በተጠቀሱት ምክንያቶች ችግር አስከትለዋል። አንደኛ አሸባሪዎች ካደረሱት ጥቃት በኋላ በተለያየ ምክንያት ወደ አሜሪካን የሚገቡ የአረብ አገር ተወላጆች በዓለም አቀፍ መግቢያ ኬላዎች ላይ ፎቶግራፍ እየተነሠና የጣት አሻራ እየሰጡ እንዲገቡ የሚል ሕግ የኢሚግሬሽን መሥረያ ቤት አውጥቷል። አሸባሪዎችን ከአፍረቃ አገሮች ለማጥፋት አሜሪካን ለምታካሂደው ዘመቻ ሙሉ ትብብራቸውን ከገለጹ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ በመሆኗ የአገራችን የጸጥታ ኃይሎች ካለ ከፍያ ተጨማሪ ሥራ ተጭናባቸዋል። ይሁን አንጂ የሕዝቡ የነፃነት መገለጫ ከሆኑት ዐቢይ ጉዳዮች አንዱ የሆነው የአገሩን አመራር በበላይነት ይዘው የሚያስተዳድሩትን ባለሥልጣናት በመምረጥ ሂደት ውስጥ ተሳትፎ ማድረግ መቻላቸው ነው። ነፃነት ከሃይማኖት ተከታዮች አንፃር ሆነን ስናየው ደግሞ አንድ ስው ጐረቤቱን እንደ ወንድሙና እንደ እኅቱ አድርጎ መመልከት ያለውን ተካፍሎ መኖር በጠቅላላው በጐ ነገር ማድረግ መቻል ነው። ከስደተኛው ወገን ቆመን ነፃነትን ስናየው ካለምንም ፍርሐት በስላም እየኖረ ላቡን ጠብ አድርጎ እየሠራ በሚያፈራት ገንዘብ ራሱንና ቤተስቡን አስተዳድሮ የተረፈችውን አገር ቤት ላሉ ዘመዶቹ የኑሮ መደጎሚያ እየላከ ልጆቹን እያስተማረ በባፅድ አገር የኑሮ ውጣ ውረዱን ችሎ ፅድሜውን መግፋት ነው። አንኳን አኛ መጤዎቹ ቀርቶ በአገሪቱ ውስጥ ተወልዶ ጥርሱን ነቅሎ ያደገው ጥቁር ሕዝብ አንኳን ከፈል የኢኮኖሚ ነፃነት አግኝቶ ለመኖር በቅቶ አንደሆን አንጂ የፖለቲካ ነፃነቱን ለማሰከበር ገና በትግል ላይ መሆኑን በዓይናችን አየተመለከትን በጆሮአችን እየሰማንና የትግሉ ሰሜት ወኔአችንን እየቀሰቀሰው ነው። የነፃነት ደወል የነፃነት ሐውልት ኢትዮአሜሪካን በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች ከአገራቸው ወጥተው በባሕር ማዶ በፈረንጅ አገር ግማሽ ዕድሜያቸውን ያሳለፉ ኢትዮጵያውያን ሰደተኞችና ጥገኞች ከባዕድ አገር ኑሮ ወደ አገራቸው ተመልሰው የልጅነት ትዝታቸውንና ናፍቆታቸውን ተወልደው ባደጉበት አካባቢ ለመወጣት በገበዩት ዕውቀትና ባካበቱት የሥራ ልምድ አገራቸውን ለመርዳትና ለማልማት ያላቸው ምኞት ከፍተኛ ነው። በዚህም ምከንያት በውጭ አገር መንግሥት መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ መሥራት ወይም ምርጫ ውስጥ ገብቶ መምረጥም ሆነ መመረጥ የአሜሪካን ሕገ መንግሥት ይከለከላል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በተፈጥሮው ኩሩ ቢሆንም ችግር ሰለ ተጫነው ከአሜሪካን የሚመለሰው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ገንዘብ በገፍ ያለው እየመሰለው የቅርብ ዘመድ ብቻ ሳይሆን የሩቁም ሰው ዕርዳታ ጠያቂ ሆኖ እናገኘዋለን። ብሎ የሚጠይቀን ሰው አይኖርም። በተግባር አንዳየነው ክሆነ አሜሪካን ተሰድደን የመኖሪያ ፈቃድ ካገኘን ሙሉ ጤና ካለንና አኗኗሩን ካወቅንበት ፍላጎታችንን ለማሟላት ችግር አይገጥመንም። መሥራት ገንዘብ ማፍሪያ መሣሪያ ነው። የሁለቱም የመጨረሻ ዓላማቸው ደግሞ ገንዘብ ነው። ከችግር ነፃ የሆነ ምንም ነገር ባይኖርም ከሚያጋጥሙ የዘር የቀለም የአኗኗር ልዩነቶችና የማኅበራዊ ኑሮ ችግሮች አኳያ ሲታይ እሜሪካን አገር መኖር ብዙ ችግር እለበት። ለቃላቱ የተሰጠው ትርጐም በመጽሐፉ ፀውደ ንባብ ርበኦ ባሳቸው ፍቺ ላይ የተመሠረተ ነው። ለየቅል ለየብቻ ሎቲ የጆሮ ጌጥ ሕሊና አዕምሮ መማተር በሐሳብ መጐብኘት መፈለግ መርሐ ግብር እቅድ ፕላን መሰፈርት መመዘኛ ነጥብ መለኪያ መሸንገል መደለል ማሞኘት ማታለል መተነኳኩል በነገር መነካካት መተንኩስ መቅበዝበዝ መንቀዥቀዥ መዘንጋት መርሳት መደብር ሱቅ መጸጸት መቆጨት ማዘን ሚና አስተዋፅኦ የሥራ ድርሻ ሚዶ ማበጠሪያ ማሟሸት ማስለመድ ለመጀመሪያ ጊዜ መሥራት መጠቀም ማስላት ሒሳብ ማውጣት ማለብ ማዘንበል ማጋደል ማድላት ማዳገት ማስቸገር ምጣኔ ሀብት ኢኮኖሚ ሥርዓት ድስፕሊን ደንብ ወግ ባህል ደንብ ልምድ ዋልታ ቋሚ ምሰሶ ዋቢ ምንጭመረጃ ዐበይት ዋና ዋና ይዘት ርዕሰ ጉዳይ መልዕከት ጋርዮሽ ኅብረት ጋብ አለ በረድ ወይም ቀነስ አለ ጐላ ደመቀ ገዘፈ ጐተጐተ አጣደፈ አቻኩለ ደጀን ከለላ ዳዳ ከጀለ አስኘ ቃጣ ድል ያለ ድግስ ትልቅ ድግስ ድብርት የአዕምሮ መስላቸት ድኅረምረቃ ከመጀመሪያ ድግሪ ቀጣይ ትምህርት ጅምላ ጥቅል በነጠላ ያልሆነ ጥርቅም ስብስብ ጥንት ድሮ ቀድሞ ጸና ረጋ ቆመ በረታ ፈለስፈ ፈጠረ ፈንጠዝያ ደስታ ፉርሽ ብላሽ የከሸፈ የተሳሳተ ፋይዳ ጠቀሜታ ፍቺ የትዳር መፍረስ ፍጆታ አላቂ ነገር የመጨረሻ ቃል ከአገራችን ንጹህ አየር በስተቀር በአሜሪካን እንደ ልብ ነው ሁሉም ነገር። ይህ መጽሐፍ በልዩ ልዩ ምክንያት በስደት አሜሪካን አገር በምንኖረው ኢት ዮጵያውያን ማኅበራዊ ኑሮና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል።
ኢትዮጵያን ስንቃኛት ብ አጐራባች አገሮች ተራሮችና ወንዞች የተፈጥሮ ሀብት የሕዝብ ብዛትና ቋንቋ ርአስ ከተማ ምጣኔ ሀብት መጠሪያ ስም ትምህርት የሕዝብ በዓላት የአየር ጠባይ ስደት » » » » » » » » » ስደት ወደ አሜሪካን ያላዩት አገር ይናፍቃል አሜሪካን ከመምጣታችን በፊት አሜሪካን ከመጣን በኋላ ። ዔጢ ሥራ ፍለጋ በአሜሪካን የቢሮ ሥራ የጐልበት ሥራ አሠሪና የሥራ ጠባይ ምስጋና ቢስ ሥራ የክፍያ መጠንና ጊዜ። መግቢያ የኢትዮጵያውያን የስደት ኑሮ የተስኘው ይህ መጽሐፍ የተዘጋጀው ባብዛኛው ደራሲው በአሜሪካን አገር የረጅም ጊዜ ቆይታው ካገኘው የአኗኗር ልምድ ላይ ተመሥርቶ ሲሆን እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት ወደ አሜሪካን አገር በስደት መጥተው የብዙ ዓመታት ቆይታ ያደረጉትን በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በማነጋገርና ተደጋጋሚ ቃለ ምልልስ በማድረግ ክተገኘ መረጃ ጭምር ነው። መጽሐፉ የሚያተኩረው በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ አሜሪካን አገር አመጣጥ ወደ አሜሪካን አገር እንዲስደዱ ባደረጓቸው ምክንያቶች በአሜሪካን አገር አኗኗራቸው በኑሮ ላይ ስለሚገጥሟቸው የአኗኗር ችግሮች በመካክላቸው ስለሚፈጠር ክፍፍልና ክፍፍሉን ለማጥበብ በተናጠልም ሆነ በቡድን በሚደረገው ጥረት ላይ ነው። ክተገኘው መረጃ በመነሣት ስደተኛው ወደ አሜሪካን ክመምጣቱ በፊት ስለ አሜሪካን አገር ኑሮ ጥሩነት ተጋንኖ ስለሚነገረው ወደ አሜሪካን አገር ለመምጣትና ለመኖር ያለው ኾጐጐት አጅግ ከፍተኛ መሆኑን ውስጡ ተገብቶ ኑሮው በተጨባጭ ሲታይ ግን የአኗኗር ሁኔታው አንደ ተስማውና እንደ ተገመተው ሳይሆን መቅረቱን እየተረዳው መሄድ ጀምሯል ባጠቃላይ ኑሮው እስከሚስመድ ድረስ የሚያጋጥመው የግልና የማኅበራዊ ግንኙነት ችግር የአየሩ ጠባይ ያልተለመደ መሆን የአገር ናፍቆቱ ጭንቀት ላይ የሚጥልና ፍጹም የሚስመድ የማይመስል ከባድ ተጽዕኖ የሚያሳድር መሆኑ ሁኔታው በአንዳንድ ወገኖች ላይ የአዕምሮ መረበሽና የጤንነት መታወክ በማድረሱ ወደ አገር ቤት የተመለሱ በርካታ መሆናቸውን መረዳት ተችሏል። ይህ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለአንባብያን እንዲደርስ የተፈለገበት ምክንያት በርካታ ሲሆን ክምክንያቶቹ መካከል ጥቂቶቹን በዚህ አጋጣሚ አናነሣቸዋለንአንደኛ ደራሲው ለብዙ ጊዜያት የማኅበራዊ ጉዳዮችን በተመለክተ በተ ለያዩ ርአሶች ላይ ያተኮሩ የጥናት ጽሑፎችን አያዘጋጀ በውጭ አገር በሚታተሙ ጋዜጦችና መጽሔቶች ላይ ያሳትም ስስነበርና እነዚህ የሕት መት ውጤቶች በአሁኑ ጊዜ መታተማቸውን በማቋረጣቸው ጽሑፎቹ በጥናት ተደግፈው በመጽሐፍ መልከ ተቀነባብረው ታትመው በውጭው ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ኅብረተሰብ እንዲደርስ ለማድረግ ሁለ ተኛ ወደ አሜሪካን አገር ካልሄድኩ ሞቼ እገኛለሁ እያለ አገር ቤት ሆኖ ሌት ተቀን የሚጸልየው ወገን የውጭው ዓለም ኑሮ ምን አንደሚመስል በቅድሚያ እንዲያውቀውና ለመምጣት ከወስነም አካላዊም ሆነ አዕም ሮአዊ ዝግጅት አድርጎ አንዲመጣ ለማለገንዘብ ሦስተኛ ስደተኛው ኅብረ ተለብ በኑሮ ውጣ ውረድ ያሳለፋቸው ጊዜያት ምን እንደሚመስሉ ነባር ኢትዮጵያውያን ወደ ኋላ መለስ ብለው ለማስታወስ ይረዳቸው ይሆናል ተብሎ ነው። በተለይ ስለ አሜሪካን ሕዝብ የአኗኗር ባሕርይ የተመለከትን እንደሆን ክተለያየ ከፍለ ዓለም የመጣ ጥርቅም ሕዝብ በመሆኑ አንድ ወጥ የሆነ ዝርያ የሌለው በኑሮውም በባህሉም በመልኩም በእቋሙም አንደ ሚለያይ ሁሉ ከትውልድ አገሩ ይዞ የመጣውን የአኗኗር ባህል ንብረቱን ስለ ረሳ ከጥቂት አክራሪ በቀር ከዓለም ኅብረተሰብ የተለየ ሕዝብ አድር ጎታል። በተጨማሪም ለመመረጥ ነጥብ ከሚያሰጣቸው የሥራ ክንዋኔዎች መካከል እንደ ምሳሌ የሚጠቀሰው አንድ የአሜሪካን ዜጋ የሆነ ግለሰብ ክአገሩ ውጭ አንድ ነገር ቢደርስበት ያን ሰው ካጋጠመው ችግር አውጥቶ ወደ አገሩ ለመመለስ ወይም ባለበት አገር በሕይወት ለማቆየት አስፈላጊው ጥረት የሚደረግ መሆኑ ነው። በአሁኑ ጊዜ ቻይና የእስያና የተባበሩት የአውሮፓ አገሮች በጥቅል ሀብት በኢኮኖሚ በንግድ በፖለቲካና በወታደራዊ ተቋማት እየተፈታተኗት በመሆናቸው አሜሪካን በዓለም ላይ የነበራትን ዝና እንዳታጣ በእጅጉ ሥጋት ላይ ወድቃ ተ ም ታወቅባቸው የምርት ውጤቶችና የቴክኖሎጂ መራቀቅ ሮኒክስ በመገናኛ አው በአገልግሎት ሥራ በዓለም በጣም ያደገች አገር በመና አዜ ከፍተኛ የነፍስ ወከፍ ገቢ ያለውና ከዳበረ የኑሮ ደረጃ ላይ የደረስባት አገር ለመ በቅታለች። የሕዝብ ብዛትና ቋንቋ በቅርብ ጊዜ በወጣው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሠረት በአሁኑ ጊዜ ከ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በአገሪቱ ውስጥ ይኖራል። በሌላ በኩል በቅርብ ጊዜ አሜሪካን የገባው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ግን ራሱን አግልሎና ከሚያውቀው ሰው ጋር ብቻ ተወስኖ ስለሚኖር የአንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታውን ለማሻሻል ጊዜ ስለሚወስድበት ወደ መደበኛ ትምህርት ለመረማመድ አክል ይገጥመዋል። በተለይ አሜሪካን አገር የሚኖሩ የቅርብ ዘመዶች ካሉንና ደብዳቤ ከደረሰን የሚታየን ነገር ሁሉ እንደ እነርሱ አሜሪካን አገር ገብተን መኖር ብቻ ነበር። ይህ ባህላቸው ከእኛ አገር ባህል ጋር ፍጹም የማይጣጣም በመሆኑ ክአሜሬሪካን ሕዝብ ጋር በአጭር ጊዜ ቆይታ ተቀራርቦ ለመኖር ክባድ ሆኖ አግኝተነዋል። ይህንን በጐ ተግባር በሥራ ለመተርጐም የገቢ ምንጭ ያለው በገንዘቡ ጐልበት ያለው በጉልበቱ ሌላው የሐሳብ አስተዋጽኦ እያበረከተ ተሰባስቦ በአንድነት የሚጸልይበት ቤተ ክርስቲያን የአስላም መስጊድ የጸሎት ቤት ፍርድ ቤት የጸጥታ ማስከበሪያ ጣቢያ የስፖርት ክበብ ትምህርት ቤት መጻሕፍት ቤት ፖስታ ቤት ካኩማ አየተባለ የሚጠራ ወርሐዊ ጋዜጣ የመረዳጃ ማኅበር አቋቁሞ ስደተኛው ያለውን ልዩ ሙያ ጥበብና የሥራ ልምድ በመጠቀም በሚገባ ማስተዳደር ጀመረ። ስደተኛው በኬንያ የጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ስፍሮ በሚኖርበት ጊዜ ከላይ በተጠቀሱት ምከንያቶችና አንዳንድ የማኅበራዊ ኑሮ ግጭቶች ከመፈጠራቸው በቀር እያንዳንዱ ጥገኛ ካለ አንዳች የፖለቲካ ተጽዕኖ ፍጹም ዲሞከራሲ በሰፈነበት መንገድ ያለውን ተካፍሎና ማኅበራዊ ፍቅር ተላብሶ ለመኖር በቅቷል። በስደት በሚኖርበት ጊዜ የሥራ ዕድል ማግኘት በግል ሥራ ላይ ተሰማርቶ ገንዘብ ለማፍራትና ራሱን ችሎ አንዲተዳደር የሱዳን መንግሥት ትብብር ስላልተለየው ኑሮው ከመሐል አገሩ ጥገኛ የተሻለ ነበር። ይህም በመሆኑ በልዩ ልዩ የሥራ መስክ ተቀጥሮ በትዕግሥት በመሥራት የኑሮ መደጎሚያ የሚሆን ገንዘብ ለማፍራትና በተደረገሰትም ያልተቆጠበ ዕርዳታ ለመርካት በቅቷል። የኢትዮጵያውያን ስደትና ኑሮ የኑሮ መጣጣም መገለጫ በግብረ ሠናይ ድርጅቶች አማካይነት ዕርዳታ ተለግሰን አሜሪካን አገር ከገባን በኋላ ተገቢውን አቀባበል አድርገው ማንኛውንም ወጭ ሸፍነው ለተወሰነ ጊዜ ስለሚያስተናግዱን ለአገሩና ለባህሉ እንግዳ ከመሆን ሌላ ብዙም እንግልት አልደረሰብንም። የቢሮ ሥራ በሠራተኛ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት በኩል ሥራ አፈላልጎ ለመቀጠርና ሠርቶ ለማደር ዕድሜው የሚፈቅድ ማንኛውም የአሜሪካን ዜጋ መብቱ የተጠበቀ ነው የሚል ቋሚ ሕግ አለ። ከነበረበት መሥሪያ ቤት የሚሰጠው ምስክርነት አዲስ ቦታ ሄዶ ለመቀጠርና ሥራ እሰከሚያገኝ ጊዜ ድረሰ ከሠራተኛ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት የሚሰጠውን የሥራ ፈት የኑሮ መደጎ ሚያ ገንዘብ ለማግኘት ወሳኝ በመሆኑ ሠራተኛው በተቻለ መጠን ጥሩ ስም ይዞ በሰላም ከድርጅቱ ለመሰናበት ጥረት ማድረግ ይጠቅመዋል። ከዚህ ለመዳን የበለጠ ገቢ ይገኝበታል ትምህርት ቤት ለጀመረ ለጥናት ያመቻል በሚል ግምት ወደ ታከሲ ሥራ የሚስማራው አበሻ ብዛት ከፍተኛ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ የታክሲ ሥራ «መሸሻ» የሚል የቅጽል ስም ተስጥቶታል። ይሁንና በልዩ ልዩ ምክንያት የአገር መኖረያና የሥራ ፈቃድ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን በአብዛኛው በስዓት የሚያገኙት ከፍያ መንግሥት ተምኖ ካወጣው የደሞዝ እርከን በታች ከመሆኑም በላይ ምንም ዓይነት የሥራ በደል ቢደርስባቸውና በሕጋዊ መንገድ ተቀጥረው ተመሳሳይ ሥራ ለሚሠሩ ሠራተኞች የሚለጠውን ጥቅማ ጥቅም ለመጠየቅ አይችሉም። በዚህ ምክንያት በትምህርት ቤት በቀሰሙት ሙያ ተሰልፈው የሚተዳደሩ ወገኖች ቁጥር እጅግ በጣም አነሰተኛ በመሆኑ «በሙያዬ በትምህርቴ በቀሰምኩት የሥራ ልምድ ሥራ ካላገኘሁ ተራ ሥራ አልሠራም» ወይም «አገሬ በሥልጣን ላይ የነበርኩ ሰው ይህንን አናላ ሥራ ስሠራ የሚያውቀኝ ሰው ቢያየኝ ምን ይለኛል። የግል መኪና መኖር ቀን ተቀን ለምናካሂደው ማኅበራዊ ኑሮአችን ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን ለማግኘት የመገናኛ መስመር ስመከፈት የግል ጉዳዮችን በተፈለገ ጊዜ ስዓት ቦታና አቅጣጫ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተዘዋውሮለማከናወን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል። ይሁንና በኢትዮጵያ ተወልደው ለአካለ መጠን ደርሰው ወደ አሜሪካን ተስድደው ክሚኖሩት በስተቀር በአሜሪካን አገር የተወሰዱትንም ሆነ በሕፃንነታቸው ወደ አሜሪካን የመጡትን ልጆች በአገራችን የልጆች አስተ ዳዳግ ባህል በማኅበራዊ ደንብና ሥነ ሥርዓት መሠረት ማሳደግን የአሜ ሪካን አገር ሕግ አይፈቅድልንም። የኢትዮጵያውያን ስደትና ኑሮ ለልጆች የሚሰጥ የኪስ ገንዘብ ባመቸ ጊዜ ለልጆች የኪስ ገንዘብ መስጠት በየትኛውም አገር የልጅ አስተዳደግ የተለመደ የወላጆች የፍቅር መግለጫና የትምህርት ማስተላለፊያ ስልት ነው። በቅርቡ የውጭ አገር ዜጎች የሆኑ ግለስቦች ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጣ ዕፅ በቦሌ ዓለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ በኩል ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ጥረት ሲያደርጉ ተያዙ የሚል ዜና ተሰራጭቶ ነበር። በአሜረካን አገር የሚኖር ማንኛውም ሠራተኛ በአንድ ሳምንት ውስጥ አምስት የሥራ ቀናት ብቻ ሠርቶ ድካሙን ለመወጣትና የግል ጉዳዩን ለማከናወን ሁለት ሙሉ ቀን የዕረፍት ጊዜ ማግኘት ሕጋዊ መብቱ ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ የዕረፍቱ አሰጣጥ ሁኔታ ቤተሰብ ላልመሠረቱ እገር ቤት ለሚኖሩ ደካማ ወላጆችና ዘመዶቻቸው ጠቀም ያለ ገንዘብ እየላኩ ለሚጦሩ በቋሚ ሥራቸው ላይ ድርጅት አቋቁመው ለሚያካሄዱ ጠቅላላ መጭ ችለው ዘመድ ከአገር ቤት ለማስመጣትና ጥሬ ገንዘብ ለማጠራቀም የረጅም ጊዜ ዕቅድ ላላቸው ኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ጥቅም በቀላሉ የሚገመት አይደለም። ይህ በመሆኑ ተቀጥሮ የስው እጅ እየጠበቁ ከመኖር በግል ሥራ ብተዳደር ይሻላል ብሎ የመተዳደሪያ የሥራ መስከ የመረጠው የአገሩን ባህል ለማስተዋወቅ ምግብ ቤት የጌጣጌጥ ሱቁ የልብስና የጥራጥሬ እህል መሸጫ መደብር መጠነኛ ድርጅት ከፍቶ ራሱን ቤተስቡንና አገር ቤት ያሉ ዘመዶቹን ይረዳል። ለኮምዩኒቲው ማኅበራዊ አገልግሎት ማበርከት « በየአካባቢው ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ተጠረ መሆን « ቤት ለሌላቸው መኖሪያ ገቢ ለሌላቸው ሥራ ማፈላለግ ሕመምተኛውን ማስታመም በሞት ለተለየው የቀብር ሥነ ሥርዓት ማስፈጸም አስፈላጊሆኖ ሲገኝ አስከሬን ወደ አገር ቤት እንዲላክ ማድረግ « የትርጁማን አገልግሎት ማበርከት » በአገር ቤት በረሃብ ለትጠቁ ወገኖች መርጃ የሚሆን የገንዘብ የምግብና የቁሳቁስ ረድዔት አለባስቦ በዓለም አቀፍ ስብአዊ ድርጅቶች አማካይነት እንዲደርሳቸው ማድረግ » በትምህርታቸው ታታሪ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በየዓመቱ የማበረታቻ ስጦታ መለገስ » ልዩ ሞያና ስጦታ ያላቸውን ወገኖች ከሕዝብ ጋር ማስተዋወቅ » ኮምዩኒቲውን በሚያገናኝ ወቅታዊ የስፖርታዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚወያዩ የአካባቢ ስብስባዎችን ማካሄድ የሚሉት ናቸው። አሜሪካን አገር የመግባት ዕድል ያጋጠመው አብዛኛው የኢትዮጵያ ስደተኛ ለረጅም ጊዜ የጠበቃ ሲሳይ ሆኖ ቆይቷል። ከፍ ብለው በተጠቀሱትም ሆነ በሌሳ ምክንያት ወደ አሜሪካን አገር ገብቶ ለመኖር በሚመለከተው የመንግሥት አካል ተወሰኖ የተሰጠው ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ክማለቁ አስቀድሞ ወደ አገሩ ተመልሶ ቢገባ ከግል እመለካከቱ የተነሣ የአገሩ መንግሥት አንደሚያሥረው የደኅንነት አካላት ክትትል እንደሚያደርጉበት የመሸማቀቅ ኑሮ አንደሚደርስበት ወይም በሚከተለው ሃይማኖትና የፖለቲካ አቋም መብቱ እንደሚነፈገው የሚያረጋግጥ የጽሑፍ ማስረጃ ለኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት ሲያቀርብ ቅድመ ሁኔታ ያረፈበት ለአንድ ዓመት የሚያቆይ የሥራና የመኖሪያ ፈቃድ ይሰጠዋል። በተወለደበት አገር በሚኖርበት ጊዜ በአገሩ መንግሥት ተቀባይነት በሌለው ሃይማኖት ወይም የፖለቲካ ድርጅት ውሰጥ በመሳተፉ ባለው ግላዊ የፖለቲካ አመስካከት በሚከተለው ሃይማኖት ወይም በዘሩ በፆታው በጎላውና በቋንቋው ላቢያ የተገለለ ቅጣት የደረሰበት የተጉላላና ብሔራዊ መብት የተነፈገው በመሆኑ በጻፈው በተናገረው በሣለው ፎቶግራፍ ቀርጾ ለሕዝብ ባቀረባቸው መረጃዎች ምከንያት ማለፈራራት የገንዘብና ሌላ ቅጣት የደረሰበት በመሆኑ በተቃውሞ ስላማዊ ሰልፍ ውሰጥ በመካፈሉ ወይም ድጋፍ ስጥቶ በመገኘቱ ወይም የአገሩን መንግሥት በሬዲዮ ወይም በቴሌቪዥን ቀርቦ በመቃወሙ ጉዳት ሊደርስብኝ ይችላል ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀ ግለሰብ ባለው ልዩ ሙያ ቀጥሮ የሚያሠራው ድርጅት የኢሚግሬሽንን ጽሕፈት ቤት ጠይቆ የመኖሪያ ፈቃድ ሊያሰጠው ይችላል። በአሁኑ ጊዜ ብዙ ኢትዮጵያውያን ይህንን ዘዴ በመጠቀም ከሚኖሩበት አገር ቪዛ አያገኙ አሜሪካን ገብተው መኖር ችለዋል። ዜግነትን መለወጥ የአሜሪካንን ዜግነት ለማግኘት አስፈላጊው ቅጽ ተሞልቶ ለጉዳዩ ማስፈጸሚያ የሚጠየቀው ገንዘብ ተከፍሎ ለኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት ሊላክ ክዚህ በታች የተጠቀሱት የመስፈርት ነጥቦች ተሟልተው መቅረባቸው በዝርዝር ይታያል የአመልካቹ ዕድሜ አሥራ ስምንት ወይም ከዚያ በላይ መሆኑ ዕድሜውክአሥራ ስምንት ዓመት በታች ከሆነ የአሜሪካንን ዜግነት ማግኘት የሚችለው በወላጆቹ ወይም በሕጋዊ አሳዳጊዎቹ አማካይነት መሆኑ ሙን የቅርብ ጊዜ ቅጹ በትክክል መሞላቱን ተገቢው ክፍያ መፈጸ ሁለት ፎቶ ግራፍ መኖሩን የግሪን ካርድና የመታወቂያ ካርድ ፎቶ ኮፒ ተያይዞ መቅረቡን ታ በአሜሪካን አገር አምስት ዓመት መኖሩ በወንጀል ድርጊት ስሙ ያልተመዘገበና በዚህ ውስን ጊዜ ውስጥ ክስድስት ወር በላይ ለሆነ ጊዜ ክአሜሪካን ውጭ ወጥቶ አለመኖሩ የአሜሪካንን ሕገ መንግሥት ለመደገፍ ፈቃደኝነት ያለው መሆኑ የእንግሊዝኛ ቋንቋ የመናገር የመጻፍና የማንበብ ችሎታ ያለው መሆኑ የአገሪቱን ታሪክና የሕገ መንግሥቱን አመራር ሂደት ማወቁ ዕድሜው ክአሥራ ስምንት እስክ ሃያ ስድስት ዓመት ክልል ከሆነ በብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ለመላተፍ በፈቃደኝነት መመዝገቡ የፍርድ ቤት ቅጣት የተላለፈበት ከሆነቅጣቱን በትክክል ያጠናቀቀመሆኑ በሥራ ላይ በተሰማራባቸው ጊዜያት የመንግሥት ታክስ መክፈሉ ሲረጋጥ ብቻ ነው። የአገሪቱን ፕረዚዳንት በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በሕዝብ የሚመረጡ ባለሥልጣናትን የመምረጥ ወይም ራሱ ዕጩ ሆኖ የመቅረብ ከአሜሪካን ውጭ ሄዶ በሚኖርበትና ጉብኝት በሚያደርግበት ወቅት በአገሪቱ ኤምባሲ አገልግሎት በነፃ የመጠቀም የአሜሪካንን ፓሰፖርት የማግኘትና በፈለገው አገር ሄዶ የመኖር ከአሜሪካን መንግሥት ልዩ ፈቃድ ከሌለው በቀር በውጪ አገር የውሰጥ ጉዳይ ለመሳተፍ ወይም በዚያ አገር የመንግሥት መሥሪያ ቤት መሥራት አይፈቀድለትም። የቅርብ ዘመዶቹን ወደ አሜሪካን አሰገብቶ የማኖር በአሜሪካን በሚገኙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ተቀጥሮ የመሥራት ሠርቶ ለመኖር አቅመ ደካማና አካለ ሰንኩል መሆኑ ከተረጋገጠ ምግብ በቅናሽ ዋጋ የመግዛት ነፃ የሕከምና አገልግሎት የማግኘት መጠነኛ የቤት ኪራይ አየተከፈለለት የመኖር ወይም መንግሥት ለአቅመ ደካሞች መኖሪያ ብሎ በሚያሠራቸው ቤቶች ውሰጥ የመኖር ምንም ዓይነት ወንጀል ፈጽሞ ቢገኝ ከአገር አንዲወጣ ያለመገደድ «ማንም ሰው ለአገሩ ሰላይ ነው» በሚለው ብሔራዊ ጥሪ ተሳታፊ የመሆን። ዘ ቪዛ የሚሰጠው በአሜሪካን አገር የሠራተኛ እጥረት ሲፈጠር ለተወስነ ጊዜ ወደ አሜሪካን ገብተው ሠርተው ለሚወጡ ጊዜያዊ ሠራተኞች ነው። የተባለው ቪዛ በቪዛ ጠያቂው አገር ውስጥ ንብረትነቱ የአሜሪካን መንግሥት ስሆነ መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ በከፍተኛ የሥራ ኃላፈነት ላይ ለተወሰነ ጊዜ ካገለገለ በኋላ ወደ አሜሪካን አገር ተዛውሮ በተመሳላይ የሥራ ዘርፍ ሳይ ተመድቦ አንዲሠራ እስፈላጊ ሆኖ ከተገኘና ሙሉ ስምምነት ከተደረስ ለተወስነ ዓመት የሚስጥ ነው። አንድ ሰው ወደ አሜሪካን አገር ሲገባ በአይሮፕላን ማረፊያዎች በአውራ መንገድ ኬሳዎችና በባሕር በር ወደቦች ላይ በኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት ወይም መንግሥት ለዚህ ተግባር መድቦ ባሰቀመጣቸው ሠራተኞች አማካይነት የሚሰጠው የተባሰው ካርድ መንገደኛው በሕጋዊ መንገድ ወደ አገር ውሰጥ ለመግባቱ የመለያ ወረቀቱ ሲሆን ግለሰቡ ከአገር በሚወጣበት ጊዜ ካርዱን የመመለስ ግዴታ አለበት። በአሜረካን አገር የቤት ቃጠሎ በየቀኑ ሳይታሰብ የሚደርስ አደጋ በመሆኑ ሕዝቡ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ የሚወስድበት ጉዳይ ነው። አሜሪካን ከልዩ ልዩ አገሮች ተስድዶ በመጣ ልዩ ልዩ ቋንቋ ዘር ባህል ሃይማኖት ባለው ጥቁር ነጭ ቀይ ጠይም ቢጫ የቆዳ ቀለም በተላበሰ ሕዝብ የተሞላች አገር ናት። ከዚህም የተነሣ ሥራ ፈቱ ከመንግሥት ለተወሰነ ጊዜ የሚሰጠውን የኑሮ መደጎሚያ ተቀባይ ለመሆን በቅቷል። በየጊዜው በተለያየ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብቶ ለመኖር ከውጭ የሚጐርፈውም ሆነ የአገር ውስጡ ነዋሪ ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመሄዱ የአገሪቱ ሕዝብ ብዛት ከፍተኛ የሆነ ዕድገት እሳይቷል። አራተኞኛ አሸባሪዎች አሜሪካን አገር ገብተው ሊጠናከሩ የበቁት በቁጥጥር መላላት ምክንያት በመሆኑ የጸጥታ ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ፈርሶ ሥራው በግል ድርጅቶች ይካሄድ የሚለው ሐሳብ የመንግሥትን ዓይነልቦና ከሳበ ወዲህ አቤቱታዎች በአፋጣኝ መልስ ማግኘት በመጀመራቸው ጉዳያቸው በእንጥልጥል ላይ በመሆኑ ምከንያት ጭንቀት ላይ ለነበሩ ኢትዮጵያውያን አፋጣኝ መልስ የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ከአሜሪካን መንግሥት ልዩ ፈቃድ ካልተገኘ በቀር በውጭ አገር መንግሥት መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ መሥራት ወይም ምርጫ ውስጥ ገብቶ መምረጥም ሆነ መመረጥ የአሜሪካን ሕገ መንግሥት ይከለከላል። አሜሪካን አገር በምንኖርበት ጊዜ አብዛኛዎቻችን በአንድ አካባቢ ተስባስበን እንደምንኖረው ወደ አገራችንም ስንመለስ ይህንኑ የአኗኗር ሥርዓት ከተከተልን በአሜሪካን አገር «ኢትዮጵያዊ አሜሪካኖች» ተብለን እንደምንጠራው ሁሉ በኢትዮጵያም «አሜረካዊ ኢትዮጵያውያን» የሚል ቅጽል ስም እንደሚስጠን አያጠራጥርም።