Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ወ ዐዐፋ ከሃ ርፀከውሪ ፄ ቃ የማሳተም መብት ከጸሐፊው ወይም እርሱ በሕግ ከወከለው ሰው በስተቀር መጽሐፉን በምንም መልክ ለጥቅስ ካልሆነ በከፊል ወይም በሙሉ አባዝቶ እጥቅም ላይ ማዋል እንደሚያዳግታቸው የታወቀ ነው። በዕፅነት ተግባር ላይ ውሏል። ለዚህም ለውጥ በምክንያትነት የሚጠቀሰው የሶቭየት ኅብረት በዓለም ላይ የነበራትን ኃያልነት ማጣትዋ ነው። ለምሳሌ እስራኤልን ለዘመናት በመደገፍዋ ብዙ ጠላቶችን ማፍራትዋ በገሐድ የታወቀ ጉዳይ ነው። ሆኖም በኢኮኖሚዋ መውደቅ የተነሣ ፅቅዷን ማሳካት እንደማትችል ስለ ገመተች ወዳጅ የሆኑ አገሮች እንዲተባበሯት በመማጸን ላይ ብትሆንም ሁሉም የውስጥ ችግር ስላለበት የተሳትፎው መጠን ውስን መሆኑ በተግባር እየታየ ነው። ዕቅዱ ተግባራዊ ሆኖ ውጤት እስከሚያሳይ ድረስ ባለሙያ የሆነው የሰው ኃይል ሥራ ፍለጋ ወደ ሌላው ዓለም ይሰደድ ይሆናል የሚል ፍራቻ በመንግሥት ላይ አሳድሯል። በእነኝህና በሌሎች ምክንያቶች የተነሣ የሥራ ፈቱ ቁጥር ክመቼውም በላይ ጨምሯል። የጐዳና ተዳዳሪው ሕዝብም ካለወትሮው አድጎ መንግሥትን ለእኩለነት ታጋይ ድርጅቶችን የሕዝብ መብትና መሠረታዊ ፍላጎት አስከባሪ ተቋማ ትን ካልተጠበቀ ሥጋት ላይ በመጣሉ ችግሩ የሚቀረፍበትን ሐሳብ የሚያ መነጩ የመወያያ መድረኮች በየአቅጣጫው ለመከፈታቸው ምክንያት ሆኗል። በአገሪቱ ላይ የደረሰው ችግር ያስከተለው መዘዝ ተዝናንቶ ይኖር የነበ ረውን ሕዝብ የገቢ ምንጭ አድርቆ ኑሮውን ለማሸነፍ ከማይችልበት ደረጃ አድርሶታል። ከዚህም በተጨማሪ ከወህኒ ቤቶች እያመለጠ የሚወጣውን እሥረኛ አድኖ መያዝ ባለመቻሉ እሥረኛ ሲያመልጥ አደገ ኛነቱን ሕዝቡ እንዲያውቀው በማድረግ በየአካባቢው ሲዘዋወር በሚታ ይበት ጊዜ ለጸጥታ አስከባሪዎች ጥቆማ እንዲደረግ ወንጀለኛውን ሲረዳ የተገኘ በሕግ እንደሚጠየቅ በማስገንዘብ የአምላጮችን ፎቶግራፍ በየቦታው በግልጽ በሚታይ ሰሌዳ ላይ በመለጠፍ የሕዝብ ዕርዳታ ከመማጸን ደረጃ ላይ ተደርሷል። ከላይ የተጠቀሱት የጥበቃ ዘዴዎች በሥራ ላይ ውለውም ወንጀለ ኛውንና የአደንዛዥ ዕፅ አስተላላፊውን ለመግታት በማዳገቱ በአጐራባች አገሮች በኩል እያሳበረ ካለቪዛ ተደብቆ የሚገባውን የውጭ ዜጋ ለመቆጣጠር የድንበር ኬላ ጠባቂዎች ቁጥር ጨምሯል። የአገር ውስጥ የሕዝብ ደኅንነት ጥበቃው መጠናከር በኢትዮጵያውያን ላይ ምን ችግር አስከተለ። አዲስ የታወጁት የውጭ አገር ዜጎችን መቆጣጠሪያ ደንቦች በተለይ ዜግነታቸውን ላልለወጡ ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው በተጠቀሱት ምክንያቶች ችግር አስከትለዋል። አንደኛ አሸባሪዎች ካደረሱት ጥቃት በኋላ በተለያየ ምክንያት ወደ አሜሪካን የሚገቡ የአረብ አገር ተወላጆች በዓለም አቀፍ መግቢያ ኪላዎች ላይ ፎቶግራፍ እየተነሠና የጣት አሻራ እየሰጡ እንዲገቡ የሚል ሕግ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ መሥራት ወይም ምርጫ ውስጥ ገብቶ መምረጥም ሆነ መመረጥ የአሜሪካን ሕገ መንግሥት ይከለከላል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በተፈጥሮው ኩሩ ቢሆንም ችግር ሰለ ተጫነው ከአሜሪካን የሚመለሰው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ገንዘብ በገፍ ያለው እየመሰለው የቅርብ ዘመድ ብቻ ሳይሆን የሩቁም ሰው ዕርዳታ ጠያቂ ሆኖ እናገኘዋለን። ብሎ የሚጠይቀን ሰው አይኖርም። በተግባር እንዳየነው ከሆነ አሜሪካን ተሰድደን የመኖሪያ ፈቃድ ካገኘን ሙሉ ጤና ካለንና አኗኗሩን ካወቅንበት ፍላጎታችንን ለማሟላት ችግር አይገጥመንም። መሥራት ገንዘብ ማፍሪያ መሣሪያ ነው። የሁለቱም የመጨረሻ ዓላማቸው ደግሞ ገንዘብ ነው። ለቃላቱ የተሰጠው ትርጐም በመጽሐፉ ዐውደ ንባብ ርጠዌነ ባላቸው ፍቺ ላይ የተመሠረተ ነው። ለየቅል ለየብቻ ሎቲ የጆሮ ጌጥ ሕሊና አዕምሮ መማተር በሐሳብ መጐብኘት መፈለግ መርሐ ግብር እቅድ ፕላን መስፈርት መመዘኛ ነጥብ መለኪያ መሸንገል መደለል ማሞኘት ማታለል መተነኳኩል በነገር መነካካት መተንኩስ መቅበዝበዝ መንቀዥቀዥ መዘንጋት መርሳት መደብር ሱቅ መጸጸት መቆጨት ማዘን ሚና አስተዋፅኦ የሥራ ድርሻ ሚዶ ማበጠሪያ ማሟሸት ማስለመድ ለመጀመሪያ ጊዜ መሥራት መጠቀም ማስላት ሒሳብ ማውጣት ማሰብ ማዘንበል ማጋደል ማድላት ማዳገት ማስቸገር ምጣኔ ሀብት ኢኮኖሚ ሥርዓት ድስፕሊን ደንብ ወግ ባህል ደንብ ልምድ ዋልታ ቋሚ ምሰሶ ዋቢ ምንጭመረጃ ዐበይት ዋና ዋና ይዘት ርዕሰ ጉዳይ መልዕክት ጋርዮሽ ኅብረት ጋብ አለ በረድ ወይም ቀነስ ኣለ ጐላ ደመቀ ገዘፈ ጐተጐተ አጣደፈ አቻኩለ ደጀን ከለላ ዳዳ ከጀለ አሰኘ ቃጣ ድል ያለ ድግስ ትልቅ ድግስ ድብርት የአዕምሮ መሰላቸት ድኅረምረቃ ከመጀመሪያ ድግሪ ቀጣይ ትምህርት ጅምላ ጥቅል በነጠላ ያልሆነ ጥርቅም ስብስብ ጥንት ድሮ ቀድሞ ጸና ረጋ ቆመ በረታ ፈለሰፈ ፈጠረ ፈንጠዝያ ደስታ ቄ ፉርሽ ብላሽ የከሸፈ የተሳሳተ ፋይዳ ጠቀሜታ ፍቺ የትዳር መፍረስ ፍጆታ አላቂ ነገር የመጨረሻ ቃል ከአገራችን ንጹህ አየር በስተቀር በአሜሪካን እንደ ልብ ነው ሁሉም ነገር። ይህ መጽሐፍ በልዩ ልዩ ምክንያት በስደት አሜሪካን አገር በምንኖረው ኢት ዮጵያውያን ማኅበራዊ ኑሮና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል።
ኢትዮጵያን ስንቃኛት አጐራባች አገሮች ተራሮችና ወንዞች የተፈጥሮ ሀብት የሕዝብ ብዛትና ቋንቋ ርእሰ ከተማ ምጣኔ ሀብት መጠሪያ ስም ትምህርት የሕዝብ በዓላት የአየር ጠባይ ስደት » » » ስደት ወደ አሜሪካን »» ያላዩት አገር ይናፍቃል » አሜሪካን ከመምጣታችን በፊት አሜሪካን ከመጣን በኋላ የጸጥታ አስከባሪ ግብረ ኃይል ተንኩለኛን መቋቋም መፍትሔ ያልተገኘላቸው ችግሮች ስደተኛው ታሪከ ሠርቶ አልፏል። የኑሮ መጣጣም መገለጫ » » » ሥራ ፍለጋ በአሜሪካን የቢሮ ሥራ የጐልበት ሥራ አሠሪና የሥራ ጠባይ ምስጋና ቢስ ሥራ የክፍያ መጠንና ጊዜ። መግቢያ የኢትዮጵያውያን የስደት ኑሮ የተሰኘው ይህ መጽሐፍ የተዘጋጀው ባብዛኛው ደራሲው በአሜሪካን አገር የረጅም ጊዜ ቆይታው ካገኘው የአኗኗር ልምድ ላይ ተመሥርቶ ሲሆን እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት ወደ አሜሪካን አገር በስደት መጥተው የብዙ ዓመታት ቆይታ ያደረጉትን በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በማነጋገርና ተደጋጋሚ ቃለ ምልልስ በማድረግ ከተገኘ መረጃ ጭምር ነው። መጽሐፉ የሚያተኩረው በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ አሜሪካን አገር አመጣጥ ወደ አሜሪካን አገር እንዲስደዱ ባደረጓቸው ምክንያቶች በአሜሪካን አገር አኗኗራቸው በኑሮ ላይ ስለሚገጥሟቸው የአኗኗር ችግሮች በመካከላቸው ስለሚፈጠር ክፍፍልና ክፍፍሉን ለማጥበብ በተናጠልም ሆነ በቡድን በሚደረገው ጥረት ላይ ነው። ከተገኘው መረጃ በመነሣት ስደተኛው ወደ አሜሪካን ክመምጣቱ በፊት ስለ አሜሪካን አገር ኑሮ ጥሩነት ተጋንኖ ስለሚነገረው ወደ አሜሪካን አገር ለመምጣትና ለመኖር ያለው ጉጐጐት አጅግ ከፍተኛ መሆኑን ውስጡ ተገብቶ ኑሮው በተጨባጭ ሲታይ ግን የአኗኗር ሁኔታው እንደ ተሰማውና እንደ ተገመተው ሳይሆን መቅረቱን እየተረዳው መሄድ ጀምሯል ባጠቃላይ ኑሮው እስክሚለመድ ድረስ የሚያጋጥመው የግልና የማኅበራዊ ግንኙነት ችግር የአየሩ ጠባይ ያልተለመደ መሆን የአገር ናፍቆቱ ጭንቀት ላይ የሚጥልና ፍጹም የሚለመድ የማይመስል ከባድ ተጽዕኖ የሚያሳድር መሆኑ ሁኔታው በአንዳንድ ወገኖች ላይ የአዕምሮ መረበሽና የጤንነት መታወክ በማድረሱ ወደ አገር ቤት የተመለሱ በርካታ መሆናቸውን መረዳት ተችሏል። ይህ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለአንባብያን እንዲደርስ የተፈለገበት ምክንያት በርካታ ሲሆን ከምክንያቶቹ መካከል ጥቂቶቹን በዚህ አጋጣሚ እናነሣቸዋለንአንደኛደራሲው ለብዙ ጊዜያት የማኅበራዊ ጉዳዮችን በተመለክተ በተ ለያዩ ርእሶች ላይ ያተኮሩ የጥናት ጽሑፎችን እያዘጋጀ በውጭ አገር በሚታተሙ ጋዜጦችና መጽሔቶች ላይ ያሳትም ስለነበርና እነዚህ የሕት መት ውጤቶች በአሁኑ ጊዜ መታተማቸውን በማቋረጣቸው ጽሑፎቹ በጥናት ተደግፈው በመጽሐፍ መልክ ተቀነባብረው ታትመው በውጭው ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ኅብረተስብ እንዲደርስ ለማድረግ ሁለ ተኛ ወደ አሜሪካን አገር ካልሄድኩ ሞቼ እገኛለሁ እያለ አገር ቤት ሆኖ ሌት ተቀን የሚጸልየው ወገንዖየውጭው ዓለም ኑሮ ምን እንደሚመስል በቅድሚያ እንዲያውቀውና ለመምጣት ከወሰነም አካላዊም ሆነ ኣዕም ሮአዊ ዝግጅት አድርጎ እንዲመጣ ለማስገንዘብ ሦስተኛ ስደተኛው ኅብረ ተሰብ በኑሮ ውጣ ውረድ ያሳለፋቸው ጊዜያት ምን እንደሚመስሉ ነባር ኢትዮጵያውያን ወደ ኋላ መለስ ብለው ለማስታወስ ይረዳቸው ይሆናል ተብሎ ነው። በተለይ ስለ አሜሪካን ሕዝብ የአኗኗር ባሕርይ የተመለከትን እንደሆን ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጣ ጥርቅም ሕዝብ በመሆኑ አንድ ወጥ የሆነ ዝርያ የሌለው በኑሮውም በባህሉም በመልኩም በአቋሙም እንደ ሚለያይ ሁሉ ከትውልድ አገሩ ይዞ የመጣውን የአኗኗር ባህል ንብረቱን ስለ ረሳ ከጥቂት አክራሪ በቀር ከዓለም ኅብረተሰብ የተለየ ሕዝብ አድር ጎታል። በተጨማሪም ለመመረጥ ነጥብ ከሚያሰጣቸው የሥራ ክንዋኔዎች መካከል እንደ ምሳሌ የሚጠቀስው አንድ የአሜሪካን ዜጋ የሆነ ግለሰብ ከአገሩ ውጭ አንድ ነገር ቢደርስበት ያን ሰው ካጋጠመው ችግር አውጥቶ ወደ አገሩ ለመመለስ ወይም ባለበት አገር በሕይወት ለማቆየት አስፈላጊው ጥረት የሚደረግ መሆኑ ነው። ትምህርት ቤት የኢትዮጵያን ሕዝብ የትምህርት ፍላጎት ለማርካት በትምህርት ሚኒስቴር ሥር በመንግሥት በጀት የሚተዳደሩ የእንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና እንጋፋ ዩኒቨርሲቲዎች ሲኖሯት በአሁኑ ጊዜ በግል ባለቤትነት የሚተዳደሩ በርካታ ከፍተኛና መለስተኛ ኮሌጆች እንዲሁም ልዩ ልዩ የሙያ ማሠልጠኛ ማዕከላት በብዛት ተቋቀመዋል። ለስደተኛው ወደ አሜሪካን አገር መግባት ምክንያት ናቸው ተብለው ከፍ ብሎ ከተጠቀሱት ነጥቦች ሌላ የፖለቲካ ጥገኝነትን የማግኘት ፍላጎት የተለያዩ አገሮች ባለሥልጣናትና ምሁራን ከየአገራቸው መሪዎች ጋር የሐሰብ ልዩነትና አለመጣጣም ሲገጥማቸው በሰላምና በመግባባት መብ ታቸው ተጠብቆ መኖር ስለማይችሉ ወይም ያ አገር ክአሜሪካን መንግሥት ጋር ስምምነት ከሌለው መንግሥቱን ለመገልበጥ ተሳትፎ ያደረጉ ግለሰቦች አሜሪካን ገብተው ለመኖር ጥያቄ ሲያቀርቡ ያለምንም ማመንታት ቪዛ እየስጠች ገብተው መኖር እንዲችሉ ታደርጋለች። በተለይ አሜሪካን አገር የሚኖሩ የቅርብ ዘመዶች ካሉንና ደብዳቤ ከደረሰን የታየን ነገር ሁሉ እንደ እነርሱ አሜሪካን አገር ገብተን መኖር ብቻ ነበር። ይህ ባህላቸው ከእኛ አገር ባህል ጋር ፍጹም የማይጣጣም በመሆኑ ከአሜሪካን ሕዝብ ጋር በአጭር ጊዜ ቆይታ ተቀራርቦ ለመኖር ከባድ ሆኖ እግኝተነዋል። ይህንን በጐ ተግባር በሥራ ለመተርጐም የገቢ ምንጭ ያለው በገንዘቡ ጐልበት ያለው በጐልበቱ ሌላው የሐሳብ አስተዋጽኦ እያበረከተ ተሰባስቦ በአንድነት የሚጸልይበት ቤተ ክርስቲያን የእስላም መስጊድ የጸሎት ቤት ፍርድ ቤት የጸጥታ ማስከበሪያ ጣቢያ የስፖርት ክበብ ትምህርት ቤት መጻሕፍት ቤት ፖስታ ቤት ካኩማ እየተባለ የሚጠራ ወርሐዊ ጋዜጣ የመረዳጃ ማኅበር አቋቁሞ ስደተኛው ያለውን ልዩ ሙያ ጥበብና የሥራ ልምድ በመጠቀም በሚገባ ማስተዳደር ጀመረ። ከጥገኛው መካከል ገሚሱ ባደረበት ሕመም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ በአሁኑ ጊዜ በኬንያ ምድር በጥገኝነት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ቁጥር በግምት ወደ እንደሚጠጋ በቅርብ ጊዜ ከአካባቢው ወደ አሜሪካን አገር ዕድል ገጥሟቸው ከመጡ ግለሰቦች ለመረዳት ተችሏል። በስደት በሚኖርበት ጊዜ የሥራ ዕድል ማግኘት በግል ሥራ ላይ ተሰማርቶ ገንዘብ ለማፍራትና ራሱን ችሎ እንዲተዳደር የሱዳን መንግሥት ትብብር ስላልተለየው ኑሮው ከመሐል አገሩ ጥገኛ የተሻለ ነበር። እነኝህ ከላይ የተጠቀሱት የኑሮ መጣጣም መገለጫዎች ለአገሩ እንግዳ ለሰዉ ባዳ ለሆነ ማንኛውም እንግዳ መስጠት የሚገባቸው አስፈላጊ የኑሮ መለማመጃ ስለሆኑ በግል ጥረታችን ወደ አሜሪካን ለመጣነውም ቢሆን የሚቀበለን ግለሰብ ክላይ የተጠቀሱትን መሠረታዊ ትምህርቶች ቢያንስ ዋና ዋናዎቹን የማስተዋወቅ ማረፊያ ቤት የመስጠት ምግብ የማቅረብ የአካ ባቢውን መውጫ መግቢያ የማላየትና የመምራት ሕጋዊ ግዴታ ይኖር እንደ አውሮፓ ዘመን አቆጣጠር በሐምሌ ወር መግቢያ ላይ በአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ኦኤዩ ጽሕፈት ቤት በመሪዎች ትብብር የተቋቋመው የአፍሪቃ ኅብረት አፍሪቃ ዩኒየን የአውሮፓን ኅብረት የመሰለ ዓላማ ያለው ከሆነ የጐረቤት አገር ስደተኛን ተቀብሎ ከማስተናገድ ከኢኮኖሚከድንበርከማኅበራዊናቭሕ ፖለቲካ አመለካከት ልዩነቶች ነፃ የሆነ የትብብር ተቋም ሆኖ አባል አገሮችያላቸውን ጥሬ ሀብትና የሠለጠነ የሰው ኃይል በቅንጅት መጠቀም ከቻሉ ከመመጽወት ሊወጡ ይችላሉ የሚል ተስፋ አለ። የቢሮ ሥራ በሠራተኛ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት በኩል ሥራ አፈላልጎ ለመቀጠርና ሠርቶ ለማደር ዕድሜው የሚፈቅድ ማንኛውም የአሜሪካን ዜጋ መብቱ የተጠበቀ ነው የሚል ቋሚ ሕግ አለ። ከነበረበት መሥሪያ ቤት የሚሰጠው ምስክርነት አዲስ ቦታ ሄዶ ለመቀጠርና ሥራ እስከሚያገኝ ጊዜ ድረስ ከሠራተኛ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት የሚሰጠውን የሥራ ፈት የኑሮ መደጎ ሚያ ገንዘብ ለማግኘት ወሳኝ በመሆኑ ሠራተኛው በተቻለ መጠን ጥሩ ስም ይዞ በሰላም ክድርጅቱ ለመሰናበት ጥረት ማድረግ ይጠቅመዋል። እንዲሁም በአሠሪዎች ጠባይ ሳቢያ ከጥቂት የአገሬው ሠራተኛና ከውጭ አገር ዜጋ በቀር በአንድ ሥራ ላይ ለረጅም ጊዜ ጨክኖ ረግቶ የሚቆይ ሠራተኛ ጥቂት ነው። ከዚህ ለመዳን የበለጠ ገቢ ይገኝበታል ትምህርት ቤት ለጀመረ ለጥናት ያመቻል በሚል ግምት ወደ ታክሲ ሥራ የሚሰማራው አበሻ ብዛት ከፍተኛ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ የታከሲ ሥራ «መሸሻ» የሚል የቅጽል ስም ተሰጥቶታል። ይሁንና በልዩ ልዩ ምክንያት የአገር መኖሪያና የሥራ ፈቃድ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን በአብዛኛው በሰዓት የሚያገኙት ክፍያ መንግሥት ተምኖ ካወጣው የደሞዝ እርከን በታች ከመሆኑም በላይ ምንም ዓይነት የሥራ በደል ቢደርስባቸውና በሕጋዊ መንገድ ተቀጥረው ተመሳሳይ ሥራ ለሚሠሩ ሠራተኞች የሚሰጠውን ጥቅማ ጥቅም ለመጠየቅ አይችሉም። በዚህ ምክንያት በትምህርት ቤት በቀሰሙት ሙያ ተሰልፈው የሚተዳደሩ ወገኖች ቁጥር እጅግ በጣም አነስተኛ በመሆኑ «በሙያዬ በትምህርቴ በቀሰምኩት የሥራ ልምድ ሥራ ካላገኘሁ ተራ ሥራ አልሠራም» ወይም «አገሬ በሥልጣን ላይ የነበርኩ ሰው ይህንን አናሳ ሥራ ስሠራ የሚያውቀኝ ሰሙ ቢያየኝ ምን ይለኛል። የግል መኪና መኖር ቀን ተቀን ለምናካሂደው ማኅበራዊ ኑሮአችን ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን ለማግኘት የመገናኛ መስመር ለመክፈት የግል ጉዳዮችን በተፈለገ ጊዜ ሰዓት ቦታና አቅጣጫ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተዘዋውሮ ለማከናወን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል። ይሁንና በኢትዮጵያ ተወልደው ለአካለ መጠን ደርሰው ወደ አሜሪካን ተሰድደው ከሚኖሩት በስተቀር በአሜሪካን አገር የተወለዱትንም ሆነ በሕፃንነታቸው ወደ አሜሪካን የመጡትን ልጆች በአገራችን የልጆች አስተ ዳዳግ ባህል በማኅበራዊ ደንብና ሥነ ሥርዓት መሠረት ማሳደግን የአሜ ሪካን አገር ሕግ አይፈቅድልንም። የኢትዮጵያውያን ስደትና ኑሮ ለልጆች የሚሰጥ የኪስ ገንዘብ ባመቸ ጊዜ ለልጆች የኪስ ገንዘብ መስጠት በየትኛውም አገር የልጅ አስተዳደግ የተለመደ የወላጆች የፍቅር መግለጫና የትምህርት ማስተላለፊያ ስልት ነው። በቅርቡ የውጭ አገር ዜጎች የሆኑ ግለሰቦች ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጣ ዕፅ በቦሌ ዓለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ በኩል ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ጥረት ሲያደርጉ ተያዙ የሚል ዜና ተሰራጭቶ ነበር። በአሜሪካን አገር የሚኖር ማንኛውም ሠራተኛ በአንድ ሳምንት ውስጥ አምስት የሥራ ቀናት ብቻ ሠርቶ ድካሙን ለመወጣትና የግል ጉዳዩን ለማከናወን ሁለት ሙሉ ቀን የዕረፍት ጊዜ ማግኘት ሕጋዊ መብቱ ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ የዕረፍቱ አሰጣጥ ሁኔታ ቤተሰብ ላልመሠረቱ አገር ቤት ለሚኖሩ ደካማ ወላጆችና ዘመዶቻቸው ጠቀም ያለ ገንዘብ እየላኩ ለሚጦሩ በቋሚ ሥራቸው ላይ ድርጅት አቋቁመው ለሚያካሄዱ ጠቅላላ መጭ ችለው ዘመድ ከአገር ቤት ለማስመጣትና ጥሬ ገንዘብ ለማጠራቀም የረጅም ጊዜ ዕቅድ ላላቸው ኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ጥቅም በቀላሉ የሚገመት አይደለም። ይህ በመሆኑ ተቀጥሮ የሰው እጅ እየጠበቁ ከመኖር በግል ሥራ ብተዳደር ይሻላል ብሎ የመተዳደሪያ የሥራ መስክ የመረጠው የአገሩን ባህል ለማስተዋወቅ ምግብ ቤት የጌጣጌጥ ሱቁ የልብስና የጥራጥሬ እህል መሸጫ መደብር መጠነኛ ድርጅት ከፍቶ ራሱን ቤተሰቡንና አገር ቤት ያሉ ዘመዶቹን ይረዳል። ለኮምዩኒቲው ማኅበራዊ አገልግሎት ማበርከት »« በየአካባቢው ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ተጠሪ መሆን »« ቤት ለሌላቸው መኖሪያ ገቢ ለሌላቸው ሥራ ማፈላለግ « ሕመምተኛውን ማስታመም በሞት ለተለየው የቀብር ሥነ ሥርዓት ማስፈጸም አስፈላጊሆኖ ሲገኝ አስከሬን ወደ አገር ቤት እንዲላከ ማድረግ የትርጁማን አገልግሎት ማበርከት በአገር ቤት በረሃብ ለተጠቁ ወገኖች መርጃ የሚሆን የገንዘብ የምግብና የቁሳቁስ ረድዔት አሰባስቦ በዓለም አቀፍ ሰብአዊ ድርጅቶች አማካይነት እንዲደርሳቸው ማድረግ » በትምህርታቸው ታታሪ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በየዓመቱ የማበረታቻ ስጦታ መለገስ ፄ » ልዩ ሞያና ስጦታ ያላቸውን ወገኖች ከሕዝብ ጋር ማስተዋወቅ « ኮምዩኒቲውን በሚያገናኝ ወቅታዊ የስፖርታዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚወያዩ የአካባቢ ስብሰባዎችን ማካሄድ የሚሉት ናቸው። ከፍ ብለው በተጠቀሱትም ሆነ በሌላ ምክንያት ወደ አሜሪካን አገር ገብቶ ለመኖር በሚመለከተው የመንግሥት አካል ተወስኖ የተሰጠው ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ከማለቁ አስቀድሞ ወደ አገሩ ተመልሶ ቢገባ ከግል አመለካከቱ የተነሣ የአገሩ መንግሥት እንደሚያሥረው የደኅንነት አካላት ክትትል እንደሚያደርጉበት የመሸማቀቅ ኑሮ እንደሚደርስበት ወይም በሚከተለው ሃይማኖትና የፖለቲካ አቋም መብቱ እንደሚነፈገው የሚያረጋግጥ የጽሑፍ ማስረጃ ለኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት ሲያቀርብ ቅድመ ሁኔታ ያረፈበት ለአንድ ዓመት የሚያቆይ የሥራና የመኖሪያ ፈቃድ ይስሰጠዋል። በተወለደበት አገር በሚኖርበት ጊዜ በአገሩ መንግሥት ተቀባይነት በሌለው ሃይማኖት ወይም የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ በመላተፉ ባለው ግላዊ የፖለቲካ አመለካከት በሚከተለው ሃይማኖት ወይም በዘሩ በፆታው በጎሳውና በቋንቋው ሳቢያ የተገለለ ቅጣት የደረሰበት የተጉላላና ብሔራዊ መብት የተነፈገው በመሆኑ በጻፈው በተናገረው በሣለው ፎቶግራፍ ቀርጾ ለሕዝብ ባቀረባቸው መረጃዎች ምክንያት ማስፈራራት የገንዘብና ሌላ ቅጣት የደረሰበት በመሆኑ ፄ በተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ውስት በመካፈሉ ወይም ድጋፍ ሰጥቶ በመገኘቱ ወይም የአገሩን መንግሥት በሬዲዮ ወይም በቴሌቪዥን ቀርቦ በመቃወሙ ጉዳት ሊደርስብኝ ይችላል ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀ ግለስብ ባለው ልዩ ሙያ ቀጥሮ የሚያሠራው ድርጅት የኢሚግሬሽንን ጽሕፈት ቤት ጠይቆ የመኖሪያ ፈቃድ ሊያስጠው ይችላል። በአሁኑ ጊዜ ብዙ ኢትዮጵያውያን ይህንን ዘዴ በመጠቀም ከሚኖሩበት አገር ቪዛ እያገኙ አሜሪካን ገብተው መኖር ችለዋል። የቪዛ ሎተሪው ለግለስቡ ከወጣለት በኋላ በአሜሪካን አገር የሚኖርና ሊቀበለው የፈቀደ ግለሰብ የቪዛ ሎተሪው የወጣለት ሰው አሜሪካን ሲገባ ወጭውን ሸፍኖ ለማስተዳደር በቂ ገቢ ያለው ለመሆኑ ከመሥሪያ ቤቱ ማስረጃ በተጨማሪ በአሜሪካን በሚኖርበት ጊዜ በባንክ ያንቀሳቀሰውን የገንዘብ መጠን የሚገልጽ የባንክ ሰነድ የዲቪ ሎተሪ የወጣለት ሰው የሚኖርበት አገር ለሚገኘው የአሜሪካን ኤምባሲ በኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት በኩል ከተላከለትና የቀረቡት ሰነዶች አጥጋቢ ሆነው ከተገኙ አመልካቹ እስከነቤተሰቡ አሜሪካን ጠቅልሎ እንዲገባ ቪዛ ይሰጠዋል። ዜግነትን መለወጥ የአሜሪካንን ዜግነት ለማግኘት አስፈላጊው ቅጽ ተሞልቶ ለጉዳዩ ማስፈጸሚያ የሚጠየቀው ገንዘብ ተከፍሎ ለኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት ሲላክ ከዚህ በታች የተጠቀሱት የመስፈርት ነጥቦች ተሟልተው መቅረባቸው በዝርዝር ይታያል የአመልካቹ ዕድሜ አሥራ ስምንት ወይም ከዚያ በላይ መሆኑ ዕድሜው ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች ከሆነየአሜሪካንን ዜግነት ማግኘት የሚችለው በወላጆቹ ወይም በሕጋዊ አሳዳጊዎቹ አማካይነት መሆኑ ቅጹ በትክክል መሞላቱን ተገቢው ከክፍያ መፈጸሙን የቅርብ ጊዜ ሁለት ፎቶ ግራፍ መኖሩን የግሪን ካርድና የመታወቂያ ካርድ ፎቶ ኮፒ ተያይዞ መቅረቡን በአሜሪካን አገር አምስት ዓመት መኖሩ በወንጀል ድርጊት ስሙ ያልተመዘገበና በዚህ ውስን ጊዜ ውስጥ ከስድስት ወር በላይ ለሆነ ጊዜ ከአሜሪካን ውጭ ወጥቶ አለመኖሩ የአሜሪካንን ሕገ መንግሥት ለመደገፍ ፈቃደኝነት ያለው መሆኑ የእንግሊዝኛ ቋንቋ የመናገር የመጻፍና የማንበብ ችሎታ ያለው መሆኑ የአገሪቱን ታሪክና የሕገ መንግሥቱን አመራር ሂደት ማወቁ ዕድሜው ከአሥራ ስምንት እስከ ሃያ ስድስት ዓመት ክልል ከሆነ በብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ለመሳተፍ በፈቃደኝነት መመዝገቡ የፍርድ ቤት ቅጣት የተላለፈበት ከሆነቅጣቱን በትክከል ያጠናቀቀ መሆኑ በሥራ ላይ በተሰማራባቸው ጊዜያት የመንግሥት ታክስ መክፈሉ ሲረጋጥ ብቻ ነው። የአገሪቱን ፕረዚዳንት በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በሕዝብ የሚመረጡ ባለሥልጣናትን የመምረጥ ወይም ራሱ ዕጩ ሆኖ የመቅረብ ክአሜሪካን ውጭ ሄዶ በሚኖርበትና ጐብኝት በሚያደርግበት ወቅት በአገሪቱ ኤምባሲ አገልግሎት በነፃ የመጠቀም የአሜሪካንን ፓስፖርት የማግኘትና በፈለገው አገር ሄዶ የመኖር ከአሜሪካን መንግሥት ልዩ ደቃድ ከሌለው በቀር በውጪ አገር የውስጥ ጉዳይ ለመላተፍ ወይም በዚያ አገር የመንግሥት መሥሪያ ቤት መሥራት አይፈቀድለትም። ዛ ቪዛ የሚሰጠው በአሜሪካን አገር የሠራተኛ እጥረት ሲፈጠር ለተወሰነ ጊዜ ወደ አሜሪካን ገብተው ሠርተው ለሚወጡ ጊዜያዊ ሠራተኞች ነው። የተባለው ቪዛ በቪዛ ጠያቂው አገር ውስጥ ንብረትነቱ የአሜሪካን መንግሥት በሆነ መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ በከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት ላይ ለተወሰነ ጊዜ ካገለገለ በኋላ ወደ አሜሪካን አገር ተዛውሮ በተመሳሳይ የሥራ ዘርፍ ላይ ተመድቦ እንዲሠራ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘና ሙሉ ስምምነት ከተደረሰ ለተወሰነ ዓመት የሚሰጥ ነው። አንድ ሰው ወደ አሜሪካን አገር ሲገባ በአይሮፕላን ማረፊያዎች በአውራ መንገድ ኬላዎችና በባሕር በር ወደቦች ላይ በኢሚግሬሽን ጽሕፈት ቤት ወይም መንግሥት ለዚህ ተግባር መድቦ ባስቀመጣቸው ሠራተኞች አማካይነት የሚሰጠው የተባለው ካርድ መንገደኛው በሕጋዊ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ለመግባቱ የመለያ ወረቀቱ ሲሆን ግለሰቡ ከአገር በሚወጣበት ጊዜ ካርዱን የመመለስ ግዴታ አለበት። በአሜሪካን አገር የቤት ቃጠሎ በየቀኑ ሳይታሰብ የሚደርስ አደጋ በመሆኑ ሕዝቡ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ የሚወስድበት ጉዳይ ነው። አሜሪካን ከልዩ ልዩ አገሮች ተሰድዶ በመጣ ልዩ ልዩ ቋንቋ ዘር ባህል ሃይማኖት ባለው ጥቁር ነጭ ቀይ ጠይም ቢጫ የቆዳ ቀለም በተላበሰ ሕዝብ የተሞላች አገር ናት። በየጊዜው በተለያየ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብቶ ለመኖር ከውጭ የሚጐርፈውም ሆነ የአገር ውስጡ ነዋሪ ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመሄዱ የአገሪቱ ሕዝብ ብዛት ከፍተኛ የሆነ ዕድገት አሳይቷል። አራተኛአሸባሪዎች አሜሪካን አገር ገብተው ሊጠናከሩ የበቁት በቁጥጥር መላላት ምክንያት በመሆኑ የጸጥታ ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ፈርሶ ሥራው በግል ድርጅቶች ይካሄድ የሚለው ሐሳብ የመንግሥትን ዓይነልቦና ከሳበ ወዲህ አቤቱታዎች በአፋጣኝ መልስ ማግኘት በመጀመራቸው ጉዳያቸው በእንጥልጥል ላይ በመሆኑ ምክንያት ጭንቀት ላይ ለነበሩ ኢትዮጵያውያን አፋጣኝ መልስ የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል። የአኗኗር ችግሮች አገር ቤት ተመልሰን ለመኖር ዕቅድ ያለን ወገኖች በቅድሚያ ልናውቃቸው የሚገቡ አንዳንድ መሠረታዊ ጉዳዮች አሉ። ከአሜሪካን መንግሥት ልዩ ፈቃድ ካልተገኘ በቀር በውጭ አገር መንግሥት መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ መሥራት ወይም ምርጫ ውስጥ ገብቶ መምረጥም ሆነ መመረጥ የአሜሪካን ሕገ መንግሥት ይከለከላል። አሜሪካን አገር በምንኖርበት ጊዜ አብዛኛዎቻችን በአንድ አካባቢ ተሰባስበን እንደምንኖረው ወደ አገራችንም ስንመለስ ይህንኑ የአኗኗር ሥርዓት ከተከተልን በአሜሪካን አገር «ኢትዮጵያዊ አሜሪካኖች» ተብለን እንደምንጠራው ሁሉ በኢትዮጵያም «አሜሪካዊ ኢትዮጵያውያን» የሚል ቅጽል ስም እንደሚሰጠን አያጠራጥርም። ከችግር ነፃ የሆነ ምንም ነገር ባይኖርም ከሚያጋጥሙ የዘር የቀለም የአኗኗር ልዩነቶችና የማኅበራዊ ኑሮ ችግሮች አኳያ ሲታይ አሜሪካን አገር መኖር ብዙ ችግር አለበት።