Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የሚል ቃል ለአልጋወራሹ ላኩና በዚህ ተስማሙ እነዚህን የመሰሉ ንግግሮች የሚያደርጉት በጊቢያቸው ውስጥ ይንሸራሸሩ በነበረበት ጊዜ መሆኑን መንግስቱ ያስታውሣሉ ጃንሆይ እንዲህ ያለው ተግባር በጦሩ ፊት በተግባር መፈፀሙ ደግሞ የጦሩን ሰሜት የሚጎዳና ሞራሉንም የሚነካ መሆኑ አያጠያይቅም በአፋቤት ጦርነት ሺህ የደርግ ሠራዊት በአንድ ጊዜ ፀጥ ረጭ እለ በአስመራ ራሳቸው ይመሩት በነበረው ሠራዊት የተረሸኑት የሚከተሉት ናቸው ሜጀል ደምሴ ቡልቶ የሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት መምሪያ ሻምበል ጌታሁን ግርማ ሁለተኛው አብዮታዊ መራዊት መምሪያ በዚህ እልቂት ሻዕቢያና ወያኔ በከፍተኛ የደስታ ስሜት ተጥለቀለቁ በሣቅ እያሽካኩም አላገጡ የአስመራው ሁኔታ ባየነው መልኩ ፈጣን ግድያ ተከናውኖ ተደመደመ የአዲስ አበባዎቹን ጄኔራሎች ስም ዝርዝር ተመዝግበ መውደቅ እንዳለባቸው ታምኖበት ተወሰኗል በዚያ ወቅት አሜሪካ ከፍተኛ የቤት ስራዋ ይሄ የነበረ ከመሆኑም በላይ ወዴ ተግባር ለመለወጥ ቀሳል ስራዋ ነበር ስራው የከበደው የማንም እጅ እንደሌለበት ለማሳመን የሚደረጉ የረቀቁ አሰራሮችን መቀመር የግድ በመሆኑ ምክንያት ብቻ ነው ለዚህ ሽፋንነት ይረዱ ዘንድም አሜሪካ ሠላማዊ አደራዳሪ መስላ መታየት ግዴታዋ ነበር የአፍሪካ የእስያና የአውሮፓ ኮሚኒስት አገዛዞች በጋራ ሲወድቁም በተጠቀሱት አገራት ሀዝቦች ዘንድ የአሜሪካ ስም እንዳይነሳ ልዩ ጥንቃቄ አድርጋለች እንግሊዝም ጭምር የደርግ መንግስት ምንም አይነት ተቃዋሚ ባይኖረውና ሻዕቢያ ወያኔ ገለመሌ ባይኖሩ ኖሮም የግድ መውደቅ ግን ነበረበት በአዲሱ የአሜሪካ ርፅዮት እመራለሁ ተውኝ ቢል እንኳ የቀድሞ መሪ ስለሆነ ብቻ ተቀባይነት አያገኝም ነበር ጓድ መንግሰቱ ያካሄድነውኮ አብዮት ነው። እያሉ ብዙዎች እጃቸው እስኪዘነጠል አጨብጭበውላቸዋል ዛሬ ግን ተነሰ። ዓም ቁጥር ዓም ክፍሉ ታደሰ ያ ቀጐውልድያ ዖሏሊቶዶታያ ሀኛ ለዳዝዶታዊ ፓሮጵ ታሪፅዕያ ክፍል እና ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ እና ኢትዮጵያ ተስፋዬ መኮንንይድረዕ ያፏፖሪ ዓም ኢዮብ አባተ እንዳለ ሻምበል ጀዕራሎቻ ዓም ትስፋዬ ሐብተማርያምያጦረ ማዳ ውሐ ዓም እፎይታ መጽሔት ኛ ዓመት ቁጥር ዓም አዲስ ዘመን የካቲት ቀን ዓም ክሯፎየፎክቨፎአርጅ።በ።
የጉልበት ብዝበዛ እንዲቀነስ እዋጅ እስከማውጣት ደርሷልይህን አይነት ያልተለመደ እቅድ ለማሳካት የተጠቀመበት ዘዴ ግን ጠልፎ ሲጥለው እናያለን ልጅ እያሠ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ነገስታት ለየት ያለ ተግባር ሲፈፅም የሚያስገኘውን አገራዊ ጥቅምና የሚፈጠረውን አንድነት አስቦ ከመደገፍ ይልቅ ወግ ጣሰ የሚለውን ቁጭት ነበር አግንነው የሚያስተጋቡበት ለክርስቲያኑ ቤተክርስቲያን ሲያሰራ ለሙስሊሞችም መስጊድ አሰራይህ ተግባሩ ብዙ ሹማምንትን አሳዘነበዘመኑ ስለእሱ የሚወራው ለሙስሊሞች ያሰራው መስጊድ እንጂ ለክርስቲያኖች ያሰራው ቤተክርስቲያን አልነበረም ሆኖም የአዲስ አበባውን ቀጨኔ መድሐኒዓለምና የሐረር መድሐኒዓለምን ቤተክርስቲያን አሰርቷል በአሁኑ ጊዜ የቀጨኔ መድሃኒዓለም የቤተክህነቱ የገንዘብ ቤት ሆኖ የሚያገለግለው መቃብር ቤት ከሌላ እናት የሚወለዱ እሀቶቹና የሌሎች ቤተሰቦች መቃብር የነበረ ሲሆንየእህቱ የወሮ ስሂን ሚካኤልዛየልዕልት እጅጋየሁ አስፋወሰን የእመቤት ሆይ ዓለም ፀሐይ እያሠሸወሮ እስከዳር ገህይወት ሚካኤልና የሌሎች አዕም ይገኝበታል አፄ ኃይለስላሴም በዘመናቸው ሄደውበት የሚያውቁት ብቸኛ ቤተክርስቲያን ይሄው ቀጨኔ መድሓኒዓለም ነበር እናም በዚህ ተግባር ሰልሟል ብሎ ለመክሰስ የሚያስችለው መንገድ ተያዘይህ በእንዲህ እንዳለም ቀደም ሲል የተጠቀሰው ብዙ ሚስት የማግባቱና እቄባቶቹን የማበርከቱ ጉዳይ ሃይማኖታዊ ቅርፁን እያጎሳው ሄደልጅ እያሠ ከሙስሊም ባላባቶች ጋር ጥብቅ ወዳጅነቱን አጠናክሮ ከመቀጠል ጎን ለጎን የአፋሩን ባላባት የደጃዝማች ኣቡበከርን ልጅ አፍቅሮ አገባትወደ አፋር እየሄደም ጥሩ የፍቅር ጊዜ አሳልፏል ቀደም ባለው ጊዜ የአፄ ዮሐንስን የልጅ ልጅ አግብቶ እንደነበርም አይተናል እንደገና ከጎጃም ባላባት የተወለደችውን ሰብለወንጌልን አገባከዚያም የጅማውን የአባ ጅፋርን ልጅ አገባእንደገና የሐረሩን አሚር የአብዱላሂን ልጅ ኣገባዙሪያውን ለማጠር የፈለገ ይመስል ሰሜንደቡብምስራቅምዕራብና መሐል ላይ ጎጆ ቀለሰይህን መሰሉን ጋብቻ ጥቂት ፀሐፍት ከሁሉም ጎሣ በመውለድ አንድነትን ለማጠንከር ሲል የፈፀመው ነው ይሉታል ምንም ቢባል እያሠ ላይ ገኖ ተወራ እንጂ በይፋዊ ጋብቻ ባይሆንም ቀደምት ነገሰታት የጭን ገረድቅምጥእቁባትነውሽማ ወዘተ በሚሉ ተመሳሳይ ስሞች በገሃድ ፈፅመውታልእንደነዘርዓያዕቆብ ያሉ ገናና ነገስታት የግራ ባህልቲትዛኖቀኝ ባህልቲት እያሉ በርከት ያሉ ሚስቶች ያገቡ የነበረ ሲሆንነገር ግን ሙስሊሟን ሴት ክርስትና አስነስተው ነበር የሚፈፅሙትይህም የሆነው ሳይወዱ በግድ በዚያ ዘመን የነበረውን ጦርነት ለማርገብ ሲሉ ነበር ልጅ እያሥ ይሀን ሲያደርግ ግን የነበረው ሳላም ዘሳቂ ሆኖ እንዲቀጥል በማሰብ ይመስላልይህ የልጅነት አስተሳሰቡ ከጥቅሙ ጉዳቱ እንደሚብስ ግን ማመዛዘን አልቻለም በዚያ ዘመን ደግሞ ትኩረት በተነፈጉት መኳንንት ዘንድ መስጊድ ከማሰራትና ሙስሊሲም ከማግባት የከፋ መኮነኛ አልነበረም ጌዱ ልጅ እያ የመኳንንቱን ክስ ቁብ ሳይሰጠው በምስራቃዊው የኢትዮጵያ ድንበር ላይ የሙጥኝ ብሎ ቀረ ዘረፋ በመፈፀም ብቻ ኑሮአቸውን መስርተው የነበሩትን ሱማሌዎችን ልጅ እያሠ ልዩ ትኩረት እንክብካቤና አክብሮት በመስጠት ወዳጅ አደረጋቸው በአካባቢው የጎሣ መሪ የነበረውን አብደላ ሰዴቅን የኦጋዴን ገዥ አድርጎ ሾመው ይህም በአካባቢው ለነበሩ ቅኝ ገዥዎች ትኩረት የሚስብ ሆነ ይባስ ብሎ ቅኝ ገዥነታቸውን ካወጁበት ጊዜ ጀምሮ በእንግሊዞችና በጣሊያኖች ላይ ለ ዓመታት ያህል ብሔራዊ ጦርነት አውጆ የተካፈሏትን ሱማሌ ነፃ ለማውጣት ሲንቀሳቀስ ለነበረው የሱማሌ መሪ ለሰይድ ሙሐመድ አብደሳ ሀሰን ልጅ እያ የገንዘብዛመሳሪያና የስንቅ ድጋፍ ሲያደርግለት የአውሮፓውያኑ ትልቅ የቤት ስራ እያሠን ከስልጣን ማስወገድ የሚለው ሆነ አቤቶ እያሠ ምንም እንኳ እቅዱ ባይሰምርና ባይሳካለትም ሁሉን የኢትዮጵያን ጎሳ በማስተባበር ኤርትራንጅቡቲንየበርበራንና የሞቃዲሾ ሶማሌን የማስመለስ ዕቅድ ነበረው ከዚህም የተነሳ አቤቶ እያሙ ሺ ጦር ለማሰናዳት ለየደጃዝማቾቹ በየግላቸው የሚያዘጋጁትን የጦር ሠራዊት ብዛት በመንገር የራሱንም ወስኖ ፈረሴ ከቀይ ባህር ውሃ ሳይጠጣ ዘውድ አልጭንም እያለ ይፎክር የነበረ ልዑል ነው ከዚህ አንፃር ለአካባቢው ነዋሪዎች ድጋፍ ማድረጉበጋብቻ መጣመሩም ሆነ መስጊድ ማሰራቱእንደአፋሮች መፋቂያ መያዙበየተጋበዘበት ቤት እንደእነሱ ለብሶ መታየቱወዘተ በአገር ውስጥ ባለሥልጣናት ዘንድ መናፍቅ ቢያሰኘውምበእያሱ አገዛዝ ክፉኛ ቢበሳጩምእንዴት አድርገውና በምን አይነት ዘዴ ከስልጣን እንደሚያስሰወግዱትጥፋቱን በማስረጃ ደግፈው ለህዝቡ እንዴት ማሳመን እንዳለባቸው የአገር ውስጥ ተቃዋሚዎቹ አልተረዱም ጎበርስለዚህ ኢትዮጵያውያኑ የልጅ እያሠን አካሄድ አለማማር መሠረት አድርገው ሲቃወሙትአውሮፓውያኑ ግን የልጅ እያ አካሄድ ሳይሆን አካሂዱ የሚያስከትለውን ውጤት አስበው ተቃወሙትእናም ኢትዮጵያውያኑ የጠፋባቸውን የማባረሪያ ዘዴ አውሮፓውያኑ በልግስና ሊሰጧቸው የሰራ እቅድ ወጣ ልጅ እያመ ምንም የሰልጣን ዘመኑ ቢያጥር ምኒልክ የጀመሩትን የአውሮፓ ስልጣኔ ወደአገር ውስጥ ለማስገባትና ኢትዮጵያም ስልጡን አገር እንድትሆን መጣሩን ቢገፋበትም ብዙዎች ሲረዱት አለመቻላቸው ይታወቃል ይህ ሲባል ግን የዘመኑ ጥቂት ምሁራን ከጎኑ ሆነው ድጋፋቸውን ይሰጡት እንደነበር አይዘነጋም ልዑሉ በዳግማዊ ምኒልክ ትቤት ለ ዓመታት ያሀል ስሰለተማረም ፈረንሣይኛ ቋንቋን በጥቂቱ ለምዶ ነበርና ከውጭ አገር ሰዎች ጋር መግባባት ጀምሮ ነበር ጥልቀት ያለው ውይይት ከውጭ ዜጎች ጋር የሚያደርግ ከሆነም በአስተርጓሚው በፊታውራሪ ተክለሃዋርያት ተከለማርያም በኩል ይወያይ ነበር ስለዓለም አቀፍ ፖለቲካዊ ጉዳዮችም እንዴ አንድ አገር መሪ ግንዛቤው ነባበረው ስለዚህም በኢትዮጵያ ድንበሮች ባሉ ጎረቤት አገሮች ቅኝ ገዥነታቸውን ተክለው ያሉ አገራት አልችል ብለው እንጂ ኢትዮጵያንም ቅኝ ማድረግ እንደሚሹ ለልጅ እያም ሆነ ለማንም ኢትዮጵያዊ ግልዕ ነውና ይህን ስጋት ለመቅረፍ የሚያስችል መንገድ ከተገኘ ማንኛውም አካል ይሄድበታል እያራም የተከተለው ይሄንኑ ነው ፈረንሣይ እንግሊዝና ጣሊያን በሱማሌ ግዛት ተካፍለው ለኢትዮጵያም መሣሪያም ሆነ ሌላ ነገር ሊገባ ሲል ወደቡ የነሱ ነውና የመከልከል አንዳንዴም መጥኖ የማሳለፍ ስልጣንን ይተገብሩ ነበር በተጨማሪም ኢጣሊያ ኤርትራን ከነወደቧ ወስዳለች የልጅ እያ የፈረሱ የቀይባህርን ውሃ የመጠጣት ጉዳይና የኦጋዴንና የአካባቢው አልፎም ሱማሌን የመጠቅለል ፍላጎት ግልፅ ግጭት እንደሚክከስት ስለሚታወቅ ልጅ እያሠ እነዚህን ጠላቶቹን ለማባረር ይረዳው ዘንድ የእነሱን ተፃራሪ ቡድን መቀላቀልና ድጋፍ አድርጎ መጠቀምን መምረጡ አያስነቅፈውም በዚያን ጊዜ ቱርክ የስዊዝ ካናልን ለመቆጣጠር በመፈለግ በሜዲትራኒያን በኩል ሞክራ ስለከሸፈባት አካሄዷን በመለወጥ የቦሶማሌን የኢትዮጵያንና የሱዳንን መንግስት ከግብፅ ጋር በማስተባበር እንግሊዝንና ፈረንሣይን ከስዊዝ ካናል ለማባረር ስትል በቆይ ባህር በኩል ጦርነት እንዲከፍቱ ትገፋፋ ነበር ልጅ እያሠ በበኩሉ የሶማሌ ግዛቶችን ለመጠቅለል ይፈልግ ነበርና ለአራት ቀን ጅቡቲን ጎብኝቶ በነበረበት ጊዜ ዘንጉን ወደቡ ላይ ተከሎ እስከዚህ ድረስ ግዛቴ ነው ብሎ ተመለሰ ወዲያውም ለቱርክ አምባሳደር አንድ ለሶማሌ ባለባቶች የኢትዮጵያ ባንዲራዎች ላይ ላ ኢላ ሐ ኢለላ የሚል ፅሁፍ አፅፎ ላከላቸው ይሀን በማድረጉም ክርስቲያንና ሙስሊሙን በእኩልነት የሚያስተዳድር ንጉስ መጣልን በማለት ቱ የሱማሊ ጎሳዎች በደስታ ለልጅ እያሠ ገቡለት ቱርክም የልጅ እያሠን ወዳጅነት በአዎንታ ተቀበለች እያሠ ጅቡቲን በጎበኘበት ጊዜ ተቀብሎ ላነጋገረው ለጅቡቲ ዋና አስተዳዳሪ በግልፅና በድፍረት በፈረንሣይ እዚህ መኖር ደስተኛ አይደለሁም አንተም ወዳገርህ ግባ በእኛ አገር ውስጥ እንድትቀመጥ አስፈላጊ አይደለም ቢለውም አስተርጓሚው ፊታውራሪ ተክለሃዋርያት ሌላውን ንግግር ሁሌ ተርጉመው ይህንን ግን ለዲፕሎማሲው ሰግቼ ተርጉሜ ጳልነግረው ቀረሁ ይሉናል ገ በዚህም ላይ የአንደኛው የዓለም ጦርነት እየተካሄደ ነበርና የእያ የውጭ ፖሊሲ ለእንግሊዝና ለፈረንሣይ ክፉ ራስ ምታት ሆነ ሁለቱ አገሮች ይህን ሁኔታ ሲረዱና አቤቶ እያሠ ከጀርመኑ ንጉስ ከዳግማዊ ዊሊያምና ከቱርክ መሪ ከሱልጣን መሐመድ ኛ ጋር መወዳጀቱን እንዳዩ በየቆንሲሎቻቸው በኩል የተቻላቸውን ሴራ በመሸረብ ውድቀቱን ማፋጠን የሜል አቋም ወሰዱ ልጁ እያሠ ከጀርመንና ከቱርክ ጋር የማበር አዝማሚያ ያሳየው ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ የነበረ ሲሆን ከጀርመናዊቷ ኦስትሪያ መሣሪያ ለመግዛትም ተዋውሷል ከዚህም ባለፈፊ ጀርመንን ለማገዝ ወደቀድሞዋ ታንጋኒካ የአሁኗ ታንዛኒያ ወታደር ልኳል እነዚህ ወታደሮች አሩሻ በተባለው ግዛት ስለቀሩ ከአካባቢው ህዝብ ጋር በጋብቻ ተሳስረው በአሁኑ ወቅት የልጅ ልጆቻቸው ወደ ቤተሰብ የሚሆኑት እዚያው ገበሬ ሆነው ቀርተዋል ታንዛኒያ ነፃ ከወጣች ጊዜ አንስቶ የእነዚህ ሰዎች ዜግነት ጉዳይ ሲያነጋግር ቆይቷል አቤቶ እያሠን ከስልጣን የማውረዱ ሴራ ሲጀመር ሐረር የነበረው የእንግሊዝ ቆንሲል ከሥልጣኑ እንዲለቅ ተደረገና በምትኩ ዓረቦችን ቀላቅሶ በቱርኮች ላይ እንዲነሱና ቱርኮች ይዞታቸውን እንዲለቁ ያስደረገው የእንግሊዝ ሰላይ የጦር መኮንን የሆነው ቫለቃ ቲኢ ሎውሬንስ ወደ ሐረር መጣሎውሬንስ ኦፍ ዓረቢያ እየተባለ የሚጠራው ይህ የእንግሊዝ ባለሥልጣን ሐረር ገብቶ እያሠን ከስልጣን ለማውረድ የሚያስችለውን ስራ መጀመር ብቻ ሳይሆን ተተኪውን ገዥም እስከመምረጥ ደረሰለዚህም ሲል የእያሠውን የአገር ውስጥ ተቃዋሚ መኳንንቶችን ድክመትኖ ብርታችአጠቃላይ የኢትዮጵያን ሁኔታ ባህልወግአስተሳሰብ ሳይቀር በሚሲዮኖችኖ ኢትዮጵያ ውሰጥ በሚኖሩ የውጭ ዜጎች አስጠንቶ በዙሪያው ካሉ መሰሎቹ ጋር መክሮ የሚከተለውን የስራ እቅድ ወደተግባር ለወጠው ኛ ለየመኳንንቱ ልጅ እያሠ መስለሙን ማስተጋባትነ ኛ ለዚህ ተግባር ሙሴ ሊዮን የተባለውን አርመናዊ ታዋቂ ፎቶግራፍ አንሺ የልጅ እያን መልክ በፎቶግራፍ ጥበብ የሙስሊም ልብስ የለበሰ አሰመስሎ ሺ ኮፒ በግብፅ አገር አሳትሞ በማስመጣት በገብረህይወት ባይከዳኝ አማካኝነት እንዲበተንበዚህ መሠረት ልጅ እያሠን ሣይማኖት በመለወጥ በሚል ክስ ወንጅለው ማስረጃው ፎቶ ግራፍ ሆኖ በተጨማሪም ወሬውን በድፍን ኢትዮጵያ እንዲሰራጭ በማድረግከዚህም ባለፈ በአማርኛና በፈረንሣይኛ ፅሁፎች በድሬዳዋ ማተሚያ ቤት እያሳተሙ በማሰራጨት ሹማምንቱንምካህናቱንምትተራውንም ህዝብ አሳመነት የ ቴቲ ኢ ሎዎሬንስ እቅድም በትክክል ሰራ ። ለት እምቡር ገበያ ላይ ነጋሪት እየነሰሙ እንግዳእቨትን መልዓከፀሐይ ጉሰ ነገስት አሰኝተው አውጀው ነበርበዚህ ጊዜ አርበኛው ሁሉ ያሎ ተሰባሰበና ሹመት ተካሄደበወቅቱ በርካታ ጦር ሠራዊት አስ ጉሎ የመጣው ባላምባራስ አበበ አረጋይ ራስ ትብሎ የጦር አበጋዝ መው በዚህ ጊዜ ነበር መልዓከፀሐይ እያሥ በ ዓም መስከረም ቀን ብዙ አርበኞች ከነወታደሮቻቸው መጥትው በተስበሰቡበት ቦታ ሆኖ የመሰቀል በዓል ሲያከብር እንደቀድሞው ንጉሣዊ ስርዓት ጠላት አገሪቱ ለይ ያልነበረ በሚመስል ሁኔታ ግብር ያበላ ሲሆን በእለቱም ለ ት የቆየ የወታደር ሰልፍ ተመልክቶዋል በዚሁ ዕለት መልዓከፀሐይ እያ ታመመና በቃሬዛ ወደ መምቻ ከተማ ተወስዶ መዳን ስላልቻለ መስከረም ቀን ህይወቱ ያልፍና በከፍተኛ የቀብር ስነስርዓት በቆቦ ማርያም እንደተቀበረ አርበኞች ታሪክ የሚለው መፅሐፍ ላይ ተገልጂል በነገሰ በኛ ወሩ የሞተውን ንጉስም በዚያች እለት ከጅቡቲ የመጡ መነኩሴ መርዘው እንደገደሉት ይነገራልየመነኩሴው ምክንያትና የላከውም ማን እንደሆነ ባይታወቅም ዴጃሃግቻ ዶኃፅ ጳጴዖቦሥያ ዮሐንሰ በወረራው ጊዜ በአርበኝነት ሲዋጋ ቆይቶ ንጉ ከስደት ሲመለሱ እንደሌሎች አርበኞች በስሩ ያሉትን ወታደሮች አሰልፎ ንጉመን የተቀበለ ነው ሆኖም የጎንደር እርበኞች ሣጥሸሸ ንጉስ አይነግስምያፈረሰ ቄስ አይቀድስም በማለት ንጉሠን አናስገባም ብለው ስለነበረኖበዚያም ጊዜ ደጃዝማች ዮሐንስ እያሠ የመንገስ ፍላጎት አሳይቶ ስለነበር ጃንሆይ ከ ዓመቱ የአርበኝነት ዘመን በኋላ በግዞት ወደ ከፋ ልከውታልበ ዓም የመንግስት ለውጥ ሲደረግ ተፊቶ ጅማ ሂዶ ሲኖር ታሞ ሞተ ደጃዝማች ዮሐንስ ሌላው በጃንሆይ ጥርስ እንዲገባ ያደረገው ንኮሠ በስደት ለይ ሳሉ ከአርበኞች ጋር ደብዳቤ ይፃፃፉ ነበርና ሌሎች ሁሉ ከጽሁፋቸው ሰር ባሪያዎ ወይም አገልጋይዎ እያሉ ሲፅፉ እሱ ግን ኣክባሪዎ እያለ ይፅፍ ስለነበር ነው ከደጃች ዮሐንስ እያሙ ልጆች ውስጥ ጀርመን አገር የሚኖሩት ፕር ግርማ ዮሐንስ አንዱ ናቸው ዎድሮዕ ጳያሠ ስለቴዎድሮስ የሚታወቀው ታሪክ ጋምቤላ ውስጥ ሸፍቶ ሲዋጋ መኖሩና በኋላ ላይ ናዝሬት ውስጥ ታስሮ እንደነበር ነው ምዕ ዳጳሯያመያ አፋር ውስጥ የተወለደው ምኒልክ እያሠ ፖለቲካ ውስጥ ባይገባም ከእያሠ በመወለዱ ብቻ አፍንጮ በር እስር ቤት ከ ዓመታት በላይ ታስሮ የነበረና በመጨረሻ በነፃ የተለቀቀ ነው ያለአንዳች ጥፋት ለረጅም አመታት የተንገላታው ምኒልክ ከተፈታ በኋላ እንኳ አገሩን ለመርዳት በተጠየቀ ጊዜ ፈቃደኛ ሆኖ የተቻለውን የሰራ ነው ምኒልክ የኢሣ ተወላጅ የሆነችውን ወሮ መሪማ አብዱራህማንን አግብቶ ድሬዳዋ ሱማሌ መንደር ሲኖር ቆይቶ ልጅ ሳይወልድ ነው የሞተው የጅቡቲ የነፃነት ጉዳይ በተቀጣጠለበት ጊዜ የጅቡቲው የበላይ ባላባት አልአሪፍ ከምኒልክ እያሠ ጋር የአንድ ኣያት ልጆች ስለነበሩ ለማግባባት የተቻለውን ጥሯል አልአሪፍ ጃንሆይን ፕአክስቴን ባል የገደለ ነው እያለ ይጠላቸው ስለነበርና ሊያኖግራቸውም ፈቃደኛ ስላልነበር ስለ እነዚሀ አይነት ጉዳዮች የሚወያየው ምኒልክ ነበር ልጅ ምኒልክ በደርግ ጊዜም የጅቡቲ መሪዎችን ለማግባባት ሞክሯል ልጆ መፅዕፍ ጴዲዖሠያ ልጅ መስፍን ዋልድባ ገዳም ተደብቆና ስሙንም መኮንን አንደልካቸው ብሎ ቀይሮ የቆየና በ ዓም የቀድሞ ስሙን መልሶ መስፍን እያሠ በሚል በጋዜጣ አሳውጂል ልጅ መሰፍን የቤተክህነት ሰው በመሆኑም በፓትሪያሪኩ በአቡነ ተክለሐይማኖት ዙ ጭጅ እርዳታ ተደርጎለት ከብት በማርባት ይተዳደር ነበር ኢህአዴግ ሲገባ ደርግ ዘግቶት የነበረውን ወደመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን የሚወስደውን መንገድ ያስከፈተና ከማዘጋጃ ቤቱ ፈቃድ ውጪ የአፄ ምኒልክን ሐውልት ብርማ ቀለም ያስቀባ ነው ሐውልቱ በነሐስ ስለተሰራ መወልወል እንጂ መቀባት ባይኖርበትም በተጨማሪም በእሣት አደጋ መከላከያ መስሪያ ቤት በኩል ያለውንና በብረት ሰንሰለት የተዘጋውን የአራዳ ጊዮርጊስ ቅጥር ጊቢ በር ከባህታዊ ገብረመስቀል ጋር በመጋዝ ቆርጠው አስከፍተዋል በዚህም ተከሰው ነበር ለፃ ዶሐዕ ጳያሥ ወልደታቷድድ አባ ዮሐንስ የካቶሊክ መነኩሴ ሆኖ በሐረር ይኖር ነበር የአባቱን ስም መወልደነጎድጓድ አሰኝቶ ሲኖርም መልኩ ቁርጥ እያሠን ይመስል ስለነበር እንዳይጠረጥሩት ቅን ቡን እያላጨ መልኩን ይለዋውጥ ነበር ዋይኋይ ጳሕዖሠያ ሽዋዐሕይ የልጅ እያ የመጀመሪያ ልጅ እንደሆነችና እያሠ ሲሞትም ለቅሶ የተደረሰው እሷ ቤት እንደነበር ተገልዷል ጳመቤምቶት ምኃዕይ ጳያሥ እመቤት ዓለምፀሐይ ከራስ ኃይሉ ተክለሐይማኖት ልጅ ከወሮ ሰብለወንጌል የተወለደችና ከመጀመሪያው ጅምሮ በቅርቡ በሞት እስከተለየችበት ጊዜ ድረስ በይፋ የምትታወቅ ልጅ ነበረች ሌላው ከልጅ እያሠ ታሪክ ጋር ተያይዞ የሚገለፀው የእሱም ሆነ የአባቱ የዘር ሐረግ በአባት በኩል ሲቆጠር ከነብዩ መሐመድ ጋር መገናኘቱ ነው ይህን ጉዳይ በሚመለከት ብርሃኑ ድንቁ አጭር የኢትዮጵያ ታሪክ በሚለው መፅሀፋቸው ያሰፈሩትን ስናይ ሥ ሁሴን ነብዩ መሐመድ ፋጡማ አሳብ ዓሊ ሚስት አንገቱን የተቀሳው ዘኖ ሳባዲን ሞሐመድ አልባጂር አብደላህ ሙሳ አልካዲን ዑመር ታጅ አላሀ ያህያ ኢስማኤል ኑር አሀመድ ከሊል ኢብራሂም ሞሐመድ ታማም ታጅ አዲን ሞሐመድ ያጉት ያኩብ ኢማም ኑር ሳኒ አሳህ ኢሳ አይሻ ዛኒ ኤልኬር ኑር ሁሴን ሻምስ አዲን ኑር አዲን ዲሞ አዲን ፓፔ ኢማም ዓሊ ወደ ኢትዮጵያ መጡ ኢማም መሐመድ ኢማም አህመድ ኢማም ሙሐመድ ኢማም ሊሃን ኢማም ዓሊ ሜካኤል አባት መሐመድ ዓሊ ገጉስ ሚካኤል አቤቶ እያ ያንጉስ ን ሚካኤል አባት ኢማም ዓሲ የነብዩ መሐመድ ኛ ትውልድ በመሆናቸው ወይም ነበሩ ተብሎ ስለሚታመን ልጅ እያሠ የነብዩ መሐመድ ኛ ትውልድ ሆኖ ይቆጠራል ልጅ ኢያሥ ባየነው ዓይነት በውጣ ውረድና በአወዛጋቢ ፈው የተሞላ የስልጣን ዘመኑንና ን ፈፅሞ በ ዓመቱ ማ የመ ተዘመረለት እያሠ ተብሎ የተጀመረውን ይህን ምዕራፍ ከመቋጨታችን በፊትም ለምን እንዳልተዘመረለት የሚጠቁሙ ጥቂት ካስፈለጉን ተን አትዮጵያ ታሪክ መፃህፍቶች በዘመናዊ መልክ በማተሚያ ቤት መታተም የጀመሩት ልጅ እያሠ በኩዴታ ከስልጣን ከተወገደ በኋሳ ከ ይ ዓመታት ነው በ ንግስት ውዲቱም ሆኑ አፄ ኃይለስሳሴ ስለልጅ እያሙ መልካም ስራ ሆን እንዲነሳ አይፈልጉም በርም አያው ከስልጣን ከተወገደ በኋላ ንጉሣዊ አገዛዙ ለ ዓመታት ያህል የዘለቀው ልጅ እያን ከስልጣን ባስወገዱት አካላት እጅ ነው በርካታ የታሪክ ፀሐፍት የታሪክ መፃህፍቶቻቸውን መፃፍና ማሣተም የጀመሩትም ከተጠቀሰው ጊዜ ጀምሮ ባሉት ጊዜያቶች ስሰነበርናበዚህም ስለ ልጅ እያሠ የተሻለ ገፅታ ማካተት ወቅቱ ስለማይፈቅድ ለረጅም ዓመታት የእያ ክፉ ገፅታ ብቻውን እየመራ እስከቅርብ ጊዜ ሊደርስ ግድ ነበርከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የተቀበሩ በጎ ገፅታዎች እንደነበሩትም የሚገልፁ እውነታዎች መውጣት ጀመሩእነዚሀም ከግማሽ ምዕተዓመታት በላይ የተብጠለጠለበትን ፅሑፍ ያህል ያልበረከቱ ናቸው ስለዚህ ያልተዘመረለት ሲባል ጥሩ ገፅታውን በክፉ ገፅታው ለውጠው ታሪኩን በሐሰት ቀበሩት ማለት ሳይሆንጥፋቱንም ልማቱንም እኩል ማንሳት ሲገባ ጥፋቱ ብቻ ጎልቶ የተተረከለት ነገር ግን ተራማጅነቱ ያልታየለት ልዑል እንደነበር ለመግለፅ የተጠቀምኩበት ቃል ነው ያልተዘመረለት ምዕራፍ ዖጋግዕዙ ቆ»ሷታምት ያዕውዳዴቱ ያመ ኑትመዕት ጻም በ ዓም ዘውዲቱ ንግስተ ነገስታት ተፈሪ መኮንን ራስ ተብለው አልጋ ወራሽ ሲሆኑ ክንውኑ ያልተለመደ እይነት ነበር በኢትዮጵያ ታሪክ የተለመደው ወግና ስርዓት ንጉሠ ነገስት ከተሾመ በኋላ ቆይቶ በተቪሚው ንጉሠ ነገስት ፍላጎትና ምርጫ ነበር አልጋወራሻ የሚሰየመው የዘውዲቱና የተፈሪ ግን በሀዝቡ ምርጫ በሚል የሁለቱም ሹመት በሌሎች ምርጫ በአንድ ቀን የተከናወነ ነበር ይህ የሆነበት ምክንያት ልጅ እያ ሲሻር በሁለት ጎራዎች ይሁንታ የነበረ በመሆኑና ቀጣይ ተጀሚሜው ሳይም እነዚያ ሁለቱ ጎራዎች መሳተፍ ስለነበረባቸው ነው ስለዚሀ ራስ ተፈሪ በነበራቸው አውሮፓ ቀመስ ትምህርትና በተራማጅነታቸው የአውሮፓውያኑ ምርጫ ሲሆኑ ዘውዲቱ ደግሞ የኢትዮጵያውያኑ ወግ አጥባቂ የመኳንንት ቡድን ምርጫ ነበሩ ይህ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ ብቻ የተተገበረና ያልተለመደ የሁለት ባንድ የአሺጀም ዘዴ የዘውዲቱን የአስተዳደር ጊዜ ያልተለመደ አድርጎት ሲቀጥል እናያለን ዘውዲቱን ለሥልጣን ያበቃቸው ብቸኛ መመዘኛ የአፄ ምኒልክ ቀጥተኛ ልጅ መሆናቸው ነው የሸዋ መኳንንት ምርጫ የሆኑትም የቀድሞውን የምኒልክን ወግና ስርዓት እንደማይጥሱትና እንደ እያ የተለየ ጎዳና እንደማይከተሉ እምነት ስለጣሉባቸው ነው ራስ ተፈሪም የንጉስ ሳህለሥላሴ ዝርያ ያላቸውና የአፄ ምኒልክ የአክስታቸው የልጅ ልጅ ስለሆኑ በዘር ሐረግ ረገድ ለዘውዱ የልጅን ያህል ባይሆንም የማይተናነስ ቅርበት ነበራቸው ነገር ግን የአልጋወራሸነቱን ስልጣን ያገኙት በዘር ቆጠራ ብቻ ሳይሆን እንደተባለው የአውሮፓውያንን ቋንቋ ስለሚናገሩና በዘመኖዊ አስተዳደግ ስላደጉ እንዲሁም የቆንሲሎች ወዳጅ ስለነበሩ ነው ቀስ በቀስም ከአልጋወራሽነት ወደ ባለሙሱ ስልጣን እንደራሴነት ሲቀጥሉም ባልተለመደ አኳኋን ወደፊት እንደምናየው የአዲስ አበባ ንጉስ እያሉ በመጨረሻ ንጉሠነገስት ሆነዋል በዚህ አካሄዳቸውም የዘውዲቱን ስልጣን በእርጋታ ከላያቸው ላይ እየገፈፉ እየገፈፉ ስልጣን አልባ ባለሥልጣን ሊያደርጓቸው ችለዋልይሀም ሲሆን ዘውዲቱ የአስተዳደር ልምድም ሆነ ከቄስ ትምህርት ያለፈ የዘመናዊ ትምህርት እውቀት ስላልነበራቸው በጥቂት ዓለማዊ ስራዎችና በብዙ መንፈሣዊ ስራቸው ተወስነው ስናይ አጠቃላይ ፖለቲካዊ ጉዳዮችንና የአገሪቱን የውጭ ፖሊሲም ሆነ የአስተዳደሩን ስራ ግን አልጋወራሽ ራስ ተፈሪ ከደጋፊዎቻቸው ጋር ሲያከናውኑት እንመለከታለንይህ አካሄዳቸውም ነው የዘውዲቱን ስልጣን ለመገዝገዝ የረዳቸው በዚህ መሠረት የንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግስት ተብሎ በተመደበው ጊዜ ውስጥ ዘውዲቱ በዘመናቸው ከፈፀሟቸው ስራዎች የበለጠ በዘመናቸው የተፈፀሙ ስራዎች መበርከታቸውን ከወዲሁ ተገንዝበን የዘውዲቱንና ያልጋወራሹን የጋራ የስልጣን ዘመን በጥምረት እናያለን ዘውዲቱ ከአባታቸው ከዳግማዊ ምኒልክና ከእናታቸው ከወሮ አብችው በያን ሚያዚያ ቀን ዓም በእነዋሪ ከተማ ነበር የተወለዱት እናታቸው ወሮ አብችው በያን ከወረኢሉ ባላባት የተወለዱ ናቸው አፄ ምኒልክ ቀደም ባለው ጊዜ ወሮ ሸዋረጋንና ልጅ አስፋወሰንን ሠልደው ስለነበር ዘውዲቱ ሦስተኛ ልጃቸው ነበሩ ሁለቱ ልጆች ምኒልክ በህይወት እያሉ ስለሞቱ የቀሩት ልጃቸው ዘውዲቱ ብቻ ነበሩ ዘውዲቱ ጥቅምት ቀን ዓም ገና የ ዓመት ተኩል ልጅ ሳሉ ለአፄ ዮሐንስ ልጅ ለራስ አርአያ ዮሐንስ ተድረው ወደ ትግራይ ግዛት ሄሂዱ የባለቤታቸው የራስ አርአያ እድሜም ዓመት ነበር ጋብቻውም የንጉሠነገስት ዮሐንስንና የንጉስ ምኒልክን ስምምነት ለማጠንከር ታስቦ የተደረገ ነው ይህ ከሆነ ከ ዓመት በኋላ ባለቤታቸው ራስ አርአያ ታሞ ስለሞት ዘውዲቱ ወደአባታቸው ወደ ሽዋ ትመልሰው መጡ በ ዓም ደጃዝማች ውቤ እጥናኣሠገድን አግብተው ኣራዳ በሚገኘው በደጃች ውቤ ቤት መኖር ጀመሩ በወቅቱ የፊታውራሪነት ማዕረግ የነበራቸው ውቤ ከዓመታት በኋላ ከባለቤታቸው ከዘውዲቱ ጋር ይጋጩና በጥፊ ይማታሉ ዘውዲቱም በንዴት በጠዋት አምልጠው ወዶ ቤተመንግስት ሄዴው መመታታቸውን ለምኒልክ ሲነግሩ እምየ ምኒልክ ውቤን ያስጠሩና ምነው በጥፊ መታኸኝ ብለው ጠየቋቸው ደጃች ውቤ መልስ አጥተው አቀርቅረው ሳለ ምኒልክ በጥፊ ያጮሏቸውና ወደቤታቸው በሰላም ይሸኙዋቸዋል ወሮ ዘውዲቱ ወደቤታቸው መመለስ ስሳልፈለጉ በዚያው ጊዜ ተፋቱ ቀጥሎ በ ዓም የጎንደር ገዥ የነበሩትንኖ የእቴጌ ጣይቱ የወንድም ልጅ የሆኑትን ራሳ ጉግሣ ወሌን አግብተው በኡራኤል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ በሚገሃው የአሁኑ የአዲሰ አበባ ከተማ እስተዳደር የጤና ጥበቃ ቢሮ ያለበት ቦታ ላይ ይኖሩ ጀመር ለቪህም ነው ሰፈሩ የንግስት ሰፈር እየተባለ የሚጠራው ምኒልክ ሲታመሙ ዘውዲቱ ከቤታቸው ወደ ቤተመንግስት በመሄድ ከእንጀራ እናታቸው ከእቴጌ ጣይቱ ጋር አባታቸውን ሲያስታምሙ ቆ ቆዩከምኒልክ ማለፍ በኋላ ጣይቱ ከቤተመንግስት እ ወዴ እንጦጦ እንዲሄዱ ሲደረግ በተመሳሳይ ከደና ስሁቸው ወዳለበት ፋሌ ወደሚባል ቦታ ተሳላኩየምኒልክ ተወላጅ ልጅ እያሠ ከስልጣን በኃይል መውረዱን ህዝቡ እንዳይቃወም በሚል መነሻና ቀደም ሲል በተጠቃቀሱት ምክንያቶች መነሻነትም ዘውዲቱን ማንገስ የውዴታ ግዴታ ነበርና ከነበሩበት ከፋሌ ሠላሌ አስመጥተው አነገሷቸው መስከረም ቀን ዓም ወሮ ዘውዲቱ ንግሉሱ ተብለው በአባታቸው ዙፋን ሲቀመጡ እድሜያቸው ሞልቶ ነብር ም ኖን ምክክር ባለቤታቸውን ራስ ጉግሳ ወሊን ው ታቸውን ሃ ግ እንዲርቱ አረጓ ው ጎንደርን እንደገና ሾመው ከቤተመንግስቱ የካቲት ቀን ዓም በአራዳ ቅዱ ክርስቲያን ሰርዓተ ንግስ ተደርጎላቸው ንግስተ ነገሰታት ዝሁዲቱ ወለተ ለዳግማዊ ምኒልክ ስይምተ እግዚአብሔር ተብለው በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዓ መንግስት ተቀብተው ዘውድ ሲጭኑየሐረር ገዥ የነበሩት የራስ መኮንን ልጅ ተፈሪ ደግሞ አባታቸው ሰጥተዋቸው የነበረው የደጃዝማችነት ማዕረግ ከፍ ብሎ ራስ ተፈሪ ተባሉና ታላቁን የሰለሞን ኒሻን ተሸልመው ለአልጋ ወራሽነት የሚገባው ክብርና ስርዓተ ፀሎት ተደርጎ ልዑል አልጋ ወራሽ ተብለው ተሰየሙበዚህ እለት ከቤተ መንግስት አልፎ የማያውቀው የኤሌክትሪክ መብራት ከቤተመንግስት እስከ አራዳ ጊዮርጊስ ተዘርግቶ በአውሮፓውያኑ ድጋፍ የአዲስ አባባ ህዝብ ልዩ ነገር እንዲያይ ሆነበንግስት ዘውዲቱ የሸዋ መኳንንት ደሰ ሲሰኙ በራስ ተፈሪ አልጋወራሽነትም አውሮፓውያን ቆንስሎች ተደሰቱየንግስ በዓሉም በደማቅ ሁኔታ አለፈ ይህ በሆነ በሳምንቱ ግርማዊት ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ የከፋ ገዥ ለነበሩትና የአክስታቸው ልጅ ለሆኑት ለራስ ወልደጊዮርጊስ የንጉስነት ዘውድ ሰጥተው የበጌምድርና የሰሜን ንጉስ አድርገው ሾሟቸውንግስት ዘውዲቱ ሃይማኖታቸውን ወዳጅዛበጾም በፀሎት የተጉና የህይወታቸው ሚዛን ወደመንፈሳዊነቱ ያዘነበለ ነበር የቀድሞዎቹ የነገስታት ሚስቶች እቱጌዎች እንኳ የዘውዲቱን አይነት ሙሉ የንግስና ስልጣን ዕድል ሳያገኙ በእቴጌነታቸው ብቻ ምን ያህል ለፖለቲካው ልዩ ትኩረት ያደርጉ እንደነበርና ተሳትፏቸው ከነገስታቱ የበሰጠ እንደሆነ በቁጥር አንዱ መፅሐፍ ያየነው ነው ንግስት ዘውዲቱ ግን ካለፉት ሴት ባለሥልጣናት ፍፁም የተለዩ ነበሩ ሌላው ቀርቶ ፊት ለፊት የመጣባቸውን ጠላት እንኳ በአግባቡ የተጋፈጡበት አጋጣሚ የለምለዚህም ነው ጥቂት ፀሐፍት ምስኪኗ ዘውዲቴ እያሉ የሚጠሯቸውማንም ሹም ያለሥልጣኑ ያሻውን ሲፈፅም ለአገር ከጠቀመ ይሁን ብያለሁ ማለትን እንጂ እንዴት ያለሥልጣኑና ያለእኔ ፈቃድ ማለትን አያውቁበትም ፖለቲካዊ ጉዳዩን ሙሱ በሙሉ ለመምራትና የአውሮፓን ስልጣኔ በኢትዮጵያ ለማስፋፋት በሚል ራስ ተፈሪ ያደርጉት ለነበረው ጥረት ሁሉ ዘውዲቱ እንቅፋት ሆነውምእኔ እያለሁ እንዴት። ብለውም አያውቁምይሀን ማድረጋቸው ተገቢ ቢሆንምገደብ ያለፈው የዋህነታቸው በስተመጨረሻ ሳይጎዳቸው አልቀረም እርስዎ በፀሎትዎ ይርዱኝእኔ እፈፅማለሁይሉ ነበር አልጋወራሹ የሚያገኙት መልስ እሸ የሚል ነው ንግስት ዘውዲቱ እንደነገ የነገስታት ደንብ ነውና በወቅቱ የነበረው መገበያያ ገንዘብ በምኒልክ ምስልና ስም የታተመውና የተቀረፀው ስለነበር እሱ ቀርቶ በዘውዲቱ ስምና ምስል ሊቀረፅ ታስቦ በብር በአላድ በሩብ በመሐለቅ ተከፋፍሎ ከተዘጋጀ በኋላ የገንዘብ ሚኒሰትሩ አይተው ፈቃዳቸውን እንዲሰጡኖ እንዲታተም ሲጠይቋቸው እኔን የኢትዮጵያ ህዝብ መርጦ ያነገሰኝ የዋልኩለት ውለታ ኖሮ ሳይሆን የአባቴን ውለታ አስቦ ስለሆነ እኔም በበኩሴ የአባቴ ሰም የሚጠራበትን ማሰብ ስላለብኝ በአባቴ ስም የታተመው ገንዘብ ተሰርዞ በእኔ ስም የታተመ ገንዘብ እንዲተካ አልፈቅድምና በዚያ ይቀጥል በእኔ ሰም ሊታተም የተሰናዳው የመታሰቢያ ስጦታ ብቻ ይታተምበት ስላሉ በምኒልክ ስም የሚታተመው ገንዘብ እንዲቀጥል ሆኗል ንግስት ዘውዲቱ ከ ዓም ድረስ በነበረው የስልጣን ዘመናቸው ምንም እንኳ በአንኳር አንኳር ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ባያደርጉም በዘመናቸው ሰርተዋቸው ያለፉ ስራዎች ቀላል አልነበሩም ከእነዚህም ውስጥ ዛሬም ድረስ ኣገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የንግስተ ነባስታት ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል አንዱና ግንባር ቀደሙ ነው ሐኪም ቤቱን በዘመናቸው ሲያቋቁሙትም ለሴቶች ማዋለጃ እንዲሆን በሚል ነበር አባታችው የጀመሩትን አገር የማዘመን ጅምርም እንዲቀጥል ይፈልጉ ነበርና ለዚህም ዘመናዊ ትምሀርት ወሣኝ መሆኑን በመረዳት የአዲስ አበባውን ቅዱስ ጊዮርጊስ ትምህርት ቤት አሰርተው አገልግሎት እንዲሰጥ አድርገዋል በተጨማሪም በ ዓም የተቋቋመው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትም የዘመናቸው ውጤት ነው ትምህርትን በሚመለከት ያወጁት አዋጅም ለዘርፉ የነበራቸውን ጠንካራ አቋም የሚያረጋግጥ ነው ልጅ ያለው ሰው ሁሉ ልጁን ስጋዊና መንፈሣዊ የሆነ ትምህርት እንዲያስተምር የሚያስገድድ አዋጅ ልጅ ያለው ልጁ ክፉንና በጎን የሚለይበትን ንጉሱንና ፈጣሪውን የሚፈራበትን እውቀትን ለማግኘት የንባብና የጽህፈት ትምህርት ያላስተማረ መቀጫውን ሃምሳ ሃምሳ ብር እየከፈለ የመቀጫው ገንዘብ ወደ ቤተቭርስቲያን እየገባ ለነዳይን ምግብና ልብስ ይሆናል የንሰሃ አባትም የሆንክ ቄስ ሁሉ የንስሃ ልጆችህ ልጆቻቸውን አስተምሩ ብለህ ከመከርክ በኋላ ምክርህን የማይቀበሱ ቢሆኑ ግን አዋጅ አፍራሾች መሆናቸውን ለአገሩ ሹም አሰታውቅ የገጠር መሪጌታም የሆንክ በቤተክርስቲያኑ ከሌላው ግብርህ ጋር ቀላቅለህ የሰበካውን ሰዎች ልጆች የንባብና የፅህፈት ትምሀርት አስተምር የደብርም አለቃ የሆንክ ሰው ፈጣሪውን አውቆ የሚጠቅምበትን በደብርህ መንፈሣዊ እውቀት ለምዕመናን በሚገባው ልክ የስብከት ትምሀርት በየደብርህ አስተምር ሳታስተምር የቀረህ እንደሆነ ግን በሹመትህ ትቀጣሰለህ ደግሞ ልጅ ያለህ ሰው ሁሉ ልጅሀ የንባብና የፅህፈት ትምህርት ከተማረ በኋሳ ለህይወቱና ለኑሮው የሚያሻውን ገንዘብ ለማግኘት አንዳይቸገር ባገራችን ካለው የእጅ ስራ ልብሀ የሚወደውን አንዳንድ የእጅ ስራ እንዲማር አድርግ ለትዳሩ የሚሆን የእጅ ስራ ሳታስተምረው የቀረህ እንደሆነ ግን በአካል ጉዳይ ካሣ ግማሽ ወደ ድሆች ተማሪ ቤት የሚገባ መቀጫ ሃምሳ ሃምሳ ብር ትከፍላለህ ይኸንንም የተቆጠረውን ትምህርት ይማር የተባለው ልጅ እድሜው ከ ዓመት እስከ ዓመት ድረስ ያለውን ነውና ከዚህ በላይ ላለው የትምህርት ዕድሜ በተላለፈው ልጁ አባቱ አላስተማርህም ተብሎ አይቀጣም ጥቅምት ቀን ዓም ዝክረነገር ዓም ይህ አዋጅ ተግባር ላይ በመዋሉም በተለይ በአዲስ አበባ አካባቢ በርካቶች ልጆቻቸውን ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲማሩ አድርገዋል ቶ ንግስት ዘውዲቱ የአባታቸውን የምኒልክን ሰራና ተግባር ቀጣዩ ትውልድ ያስበው ዘንድም በቅዱስ ጊዮርጊስ አቅራቢያ የሚገኘውን የምኒልክ ሐውልት አሰርተውላቸዋል የዳግማዊ ምኒልክ አደባባይ በሚባለው ቦታ ላይ የቆመውን ሕውልት ዘጀርመናዊው መሐንዲስ በሙሴ ሄርትል አስጠንተው ሐውልቱ በጀርመን አገር በነሃስ ተሰርቶ እንዲመጣ አዘዙ አውልቱ መጥቶ የተመደበለት ቦታ ተደልድሎ ከተዘጋጀ በኋላ ገና ሳይተከል ዘውዲቱ ስላረፉ አልጋወራሹ ጥቅምት ቀን ዓም በታላቅ ክብረበዓል እንዲተከል አድርገዋል ወደ መንፈሳዊ ተግባራቸው ስናልፍምለብዙ መቶ ዓመታት ፀንቶ የቆየው ኢትዮጵያውያን ከሊቃውንቶቻቸው ውስጥ ጳጳስ መሾም አይችሉም የሚለው ግብጾች በአንቀፅ ያካተቱት ሕግ ቀርቶ ለመጀመሪያ ጊዜ በንግስት ዘውዲቱ የጥረት ውጤት ግንቦት ተን ዓም አራት ኢትዮጵያውያን ጵጵስና ሹመት ሊያገኙ ችለዋል የእስክንድርያው ፓትሪያሪክ አቡነ ዮሐንስም ኢትዮጵያ ድረስ መጥተው የኢትዮጵያን ተወላጅ ጳጳስ አድርገው አዲስ አበባ ላይ ሶመውና ባርከው ተመልሰዋል ይህን ጉዳይ በሚመለከት የንጉስ ላሊበላ ወንድም ቅዱስ ሃርቤይ ሞክሮት እንደነበረና ሳይሳካለት እንደቀረ ይልቁንም በዘመኑ ብዙ ሁከት እንዳስነሳበት በእሱ ታሪክ ውስጥ ያየነው ነው በተጨማሪም በአፄ ዮሐንስ ኛ ተሞክሮ ሳይሳካ ቀርቶ የነበረና በዘውዲቱ ጊዜ እውን የሆነ የኢትዮጵያውያን ክርስቲያን ነገሰታት የዘመናት ህልም ሆኖ የቆየ ጉዳይ ነበር ስለዚህ በዘውዲቱ ጊዜ ኢትዮጵያ የራሷ ቋጳስ ኖሯት ቆየችና በ ዓም ደግሞ የራሷ ሊቃነጳጳሳት መሾም የሚችል በማግኘቷ ከእስክንድሪያ ማስመጭቱ ተረ ንግሰት ዘውዲቱ በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውህጪ በሚገኙ ከተሞች በርከት ያሌ አብያተክርስቲያናትን አሳንፀዋልያረጁና የፈራረሱትንም አሳድሰዋል በ ዓም ተመስርቶ ከ ዓመት በኋላ የተፈፀመው የበዓታ ገዳምን በማሰራትና ሙሉ መተዳደሪያ በመስጠት በዐሎት ቤታቸው ተቀምጦ የነበረውን የአፄ ምኒልክ አዕም እንዲያርፍበትና እንዲቀደስበት አድረገዋል የአዲስ አበባ ጴጥሮስ ወጳውሎስን የአዲስ አበባ ደብረነገስት ቁስቋምን የአዲስ አበባ ቅዱስ ዮሴናን ደብረ አሜን ተክለሐይማኖትንነ ቅዱስ ቂርቆስን የአዲስ አበባ ደብረሠላም እስጢፋኖስን በዘመናቸው አሰርተዋል ያእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያንን ካሰሩ በኋሳ በታላቅ ሰልፍ ታቦት ዛመመይጩመክዐ ጅ እንዲገባ ያደረጉትም ጥቅምት ቀን ዓም የሠገሌው ጦርነት ድል በእለተ እስጢፋኖስ ስለተገኘ በሚል ነበር የአዲስ አበባ ደብረፅጌ ዑራኤል ትክሉ በምኒልክ የነበረ ቢሆንም ስላረጀ አስፈርሰው አሁን ያለውን ሀንፃ ያሰሩት ዘውዲቱ ናቸው የአዲስ አበባ ፅርሐአርያም ቅዱስ ሩፋኤልን አፄ ምኒልክ በጭቃና በሣር ክዳን አሰርተውት የነበረ ሲሆን ዘውዲቱ እስፈርሰው ያሁኑን ሀንፃ አሳነፁ የአቃቂ ቀራንዮ መድሐኒዓለም ትክሉ የንጉስ ሳህለሥላሴ የአፄ ምኒልክ አያት የነበረና በምኒልክ ጊዜ የታደሰ የነበረ ቢሆንም አርጅቶ የሚፈርስ ስለሆነ የአሁኑን ህንፃ በአዲስ መልክ እሠርተዋል የእንጦጦ ማርያም ቤተክርስቲያን በእቴጌ ጣይቱ ሰም ሆኖ ቀደም ሲል በምኒልክ ዘመን የተሰራው በጭቃ ስለነበርና ዕድሜ ስለሌለው ንግስት ዘውዲቱ አሁን ያለውን ህንፃ አሠሩት ልጅ እያሠ ያሰራውን የቀጨኔ መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያንንም አሳድሰዋል ጠራ የደብረ በግዕ አቡነ ሞአን ገዳምንም ቤተክርስቲያን በአዲስ መልክ ያሰሩት ዘውዲቱ ነበሩ ይህ ቤተክርስቲያን የንጉስ ሳህለስላሴ ልጅ የሆኑት የአፄ ምኒልክ አባት የንጉስ ኃይለመለኩት መቃብር ያለበት ስለሆነ ዘውዲቱ ከመንገሣቸው በፊት ከነበረው ጊዜ ጀምሮ እስከዘመናቸው ፍፃሜ ድረስ አስፈላጊው ድግስ እየተዘጋጀ ሳይቋረጥ በየዓመቱ በፍትሐት የሸዋው ንጉስ የኃይለመለኮት ሰም ሲጠራበት በር መች ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ ከተሞች በንግስት ዘውዲቱ የተሰሩ አብያተከርስቲያናትም የመናገሻ ማርያም ቤተክርስቲያን የፋሴ መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን ሜታ የወረብ ማርያም ቤተክርስቲያን የአዋሸ ማርያም ቤተክርስቲያን የኤጀርሣ ለፎ ቅዱስ ገብርኤል ቤተከርስቲያን የየረር ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን የአድአ በርጋ አቡነ ተክለሐይማኖት ቤተክርስቲያን ናቸው በተጨማሪም በኢየሩሳሌም በሚገኘው ቦታ የኢትዮጵያ ቤት ተብሎ የሚጠራውን ከዘጠና በላይ ክፍል ያለውን ትልቅ ፎቅ ቤት አሰርተው ከኪራዩ ገቢ እሩቡ በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ መናንያን መርጃ እንዲውልና ቀሪው ለመንግስት ጉዳይ እንዲሆን አድርገዋል ንግስት ዘውዲቱ በዚህ መሰሉ መንፈሣዊ ተግባራት ላይ ትኩረታቸውን አድርገው ሲሰሩልዑል አልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ ደግሞ በእነዚህ ዓመታት በአውሮፓውያኑ ድጋፍና በኢትዮጵያውያን ምሁራን ረዳቶቻቸው እየታገዙ ግዙፍ ግዙፍ ተግባራትን እየከወኑ ኢትዮጵያን የማዘመንና የማሰልጠን ሂደታቸውን ቀጥለዋል ራስ ተፈሪ በዘውዲቱ ዘመን የሰሯቸው ስራዎቻቸውም በሀዝቡ ዘንድ ልዩ አድኖቆት ሲያስገኝላቸውበአገር ውስጥ ተራማጅ ሹማምንት ዘንድ ደግሞ ተቀባይነታቸውን አጉልቶላቸዋልበአውሮፓውያኑ ዓይን ደግሞ ወደርየለሽና በታሪክ ታይተው የማይታወቁ የኢትዮጵያ ተስፋ ተብለው ታዩከሁሉም በላይ ግን የሰራቸው ውጤት ያስገኘላቸው ትርፍ የደጋፊዎቻቸው መበርከትን ሲሆን ይህም አንደኛውና ዋናው ግባቸው የነበረ ጉዳይ ነውምክንያቱም በየጊዜው ይነሳባቸው የነበረውን አድማ ዝቅ ብለን እንደምናየው በቀላሉ ማክሸፍ የቻሉትም ሆነ የዘውዲቱን ሰልጣን እየሸረሸሩ ባዶ ለማስቀረት ቀላል የሆነላቸው የደጋፊዎቻቸውንና የሰላዮቻቸውን ቁጥር በማበርከታቸው ነውለዚህ ተግባር ሲሌም በስራ ውጤት ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ገንዘብ መድበው መቸርንም ተጠቅመውበታል ጥቂት ምሁራንን ከጎናቸው አሰልፈው የአስተዳደር እንቅስቃሴውን የገፉበት ልዑል አልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ ከ ዓም ካከናወኗቸው ተግባራቶች ውስጥ ኢትዮጵያን የመንግስታቱ ማኅበር አባል ማድረጋቸው ይጠቀሳል በ ዓም ኢትዮጵያ የአባልነት ማመልከቻዋን ስታስገባም ጠንከር ያለ ተቃውሞ ገጥሟት ነበር በውስጧ የባሪያ አዝዛዝ አለ ግድያና ዝርፊያ አለ የግዛቷ ወሰን በደንብ የተከለለ አይደለም በግዛቷ ላይ የመንግስታቱ ማኀበር የሚያዘውን ሕግ ልታስፈፅም አትችልም የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ነበሩ ሆኖም የአልጋወራሹን የአሰተዳደር ስራ ያዩ አገራት ድጋፋቸውን ሰጡ አልጋወራሹም የባሪያ አገዛዝ በሕግ እንደተሻረና አገራቸውም ሠላም መሆኗን አስረድተው በ ዓም በሚያዚያ ወር ኢትዮጵያ የመንግስታቁ ማኅበር አባል አገር ልትሆን ቻለች ዋኖ ደጋፊዎቹም እንግሊዝ ፈረንሣይኖ ጣሊያን ነበሩ በመጀመሪያ የተቃወሙትም እነሱው ነበሩ እነዚህ አገሮች ወዳጅ መሰለው አባል አድርገው መልሰው ደግሞ ትወረር ብለው በኢጣሊያ የዳግም ወረራ ጊዜ እውቅና ሰጥተዋል የሆነ ሆኖ ኢትዮጵያ በልዑል አልጋወራሹ ጥረት በ ዓም አባል አገር ሆናለች ይህም በወቅቱ ለኢትዮጵያ የማይገኝ እድል ተደርጎ የተወሰደና ልዑል አኣልጋወራሹም በከፍተኛ ደረጃ የተወደሱበት ትልቅ ተግባራቸው ንነበር ኢትዮጵያ አባል ከሆነች በኋላ ወዲያው በሚያዚያ ወር አልጋ ወራሹ መኳንንቱን አስከትለው በተመቻቸላቸው የጉብኝት ፕሮግራም ቆ» ንሣይን ልጂየምን የስዊዲንን የኢጣሲያን የእንግሊዝን የወን ዋፍ ከተሞች ተዘዋውረው እየጎበኙና ከየአገራቱ መሪዎች ጋር እየተወያዩ ደፕሎማሲያዊ ግንኙነቱን አጠናከሩት» የመንግስታቱ «ተመጫ ጄኔቭንም ጎበኙ ግሓ የመመመፈያው አውሮፓን የጎበኙ አልጋወራሽ ናቸውና በምሁራት ዘንድ ልዩ አድናቆት ተቸራቸውጉብኝቱ ለኢትዮጵያውያኑ ልዐካን ቡድንም ብዙ ነገርን ያስገነዘበ ነበርከወራት በኋላ ነሐሴ ቀን ዓም ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወዴ አዲስ አበባ ሲመለሱ ደማቅ አቀ ጠበቃቸውተመልሰውም በጉብኝታቸው ወቅት ያዩትን ስልጣኔ ኢ ዮኮ ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ረውን ቀጠሉ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው ች በስፋት መሰራ መሩት አዳዳሶ በለንደን ቆይታቸው በአፄ ቴዎድሮስ ጊዜ ከመቅደሳ ተወስዶ ከነበረው ህልቁ መሣፍርት ከሌስው ቅርስ ውስጥ አንድ የወርት ዘውድ ከእንግሊዝ ንጉስ ከጆርጅ ኛ የይመለሳል ቃል ተገብቶላ ው ኒ ና ሐምሌ ቀን ዓም ተመልሶ ንግስት ዘውዲቱ ተረክበዋል ከው አገር ነገስታትም በየጊዜው የአድናቆት መልዕክት ይደርሳቸው ጀመር ይህን ወዳጅነት መሠረት በማድረግም ራስ ተፈሪ ሯ ርሳታ ኢትዮጵያውያንን እየመለመሉ ለትምህርት ወደ አውሮፓ መላክ ጀመሩ ትምህርት ቤቶችም በአዲስ አበባና በየጠቅላይ ግዛቱ እንዲከፈቱ አደረጉ በጥቅሉ በአልጋ ወራሽነታቸው ዘመን ካሬም ድረስ ግልጋሎት የ ው ያሌ ተቋማትንና ልዬ ልዩ የመሠረተ ልማት እውታሮችን ለመገ መሠረት የጣሉበት ወቅት ሆነ ጎን ለጎንም የስልጣናቸውን መንገ ይ ዓም ለመጀመሪያ ጊዜ አውሮፕላን አስመጥተዋል ይህንንም ለዚያው ለመከረኛው ስልጣን ቦንብ ሲያዘንቡበት ወደፊት እናያለን» በተጨማሪም ከአውሮፓውያኑ ጋር የተለያዩ የሞ ፖል ውሎችን ሙሉ ኃላፊነት ወስደው ይፈራረሙ የነበሩት ራሳቸው ራ ባሩ በንግስተነገስት ዘውዲቱ ዘመነመንግስት እነዚህንና እነዚህን የመሣሠሉ ተግባራት ሲከናወኑ ኣገሪቱ ሠላም የሠፈነባትና ን የስልጣን ዘመንም የተረጋጋ የነበረ ሊመስለን ይችላልነገር ግይ ከመቸውም ጊዜ የበለጠ አደገኛ የስልጣን ትግልና ከቦት የነበረበትበየጊዜው በአልጋ ወራሹ ላይ የሚነሱ አድማዎች የበረ ቱበት ሹማምንቱ ጎራ ለይተው የተኖቆሩበትበወሬበሐሜትና በአሌባል ታ ብዙዎች የተቀጡበትዘውድ የጫኑት ንግሥት የተካለቡና የተየ ቡበት በሁለት ቤተመንግስት ግብር የተበላበትየንግስትና ያልጋወራ ስልጣን ማን አዛዥ ማን ታዛዥ እንደሆነ ያልተለየበትብዙ አወዛጋቢ ዳዱ የተስተናገደበት ዘመን ነበር ስለዚህም የተባሉትን ሁነቶች በአጭሩ አብራርቶ ለማስቀመጥ ከስረ መሠረቱ መጀመርና ልጅ እያሠ ስልጣኑን ካጣበት ጊዜ ጀምሮ መዳሰሱ ተመራጭ ነው ልጅ እያሠ ከስልጣን መሻሩ በቤተመንግስቱ አደባባይ በአዋጅ ሲነገር በአዲስ አባባ መጠነኛ የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ከ ሰዎች በሳይ ሞተዋል ደጃዝማች አብርሃም አርአያም በልጅ እያ መሻር ተበሳጭተው ጊቢ ገብተው ለማስቸገር ሞክረው የነበረ ሲሆን እንደማያዋጣቸው አውቀው እጅ ሰጥተዋል ከዚያ በኋላም የእያ ደጋፊዎች ያደረጓቸው ጦርነቶች ሁሌ ሳይሳኩ ቀርተዋል እነዚያ ሁሉ የፊት ለፊት ፍልሚያዎች አልፈው አዲሱ ሹም ሽር ከተከናወነበት ጊዜ ጀምሮ ደግሞ ትግሉ በሁለቱ ተጀሚዎች በንግስት ዘውዲቱና በራስ ተፈሪ መካከል ሆነ ይሀም ሲባል ሁለቱ ባለሥልጣናት በግልፅ ባይፋጠጡም የሁለቱ ጎራ ደጋፊዎች ትግል እየበረታ ሄደ ባንድ ወገን በራስ ተፈሪና በደጋፊዎቹ ምሁራንና መኳንንት በሌላ በኩል ደግሞ የቀድሞው ወግና ስርዓት የመቀጠል አለኝታ ምልክት አድርገው ዘውዲቱን በሚያዩ ወግ አጥባቂ መኳንንት መካከል የተደረገ ፍጥጫ ነው ከወግ አጥባቂው በኩል የአቡኑና የእጨጌው መንፈሣዊ ድጋፍ የማይለያቸው ፊታውራሪ ሐብተጊዮርጊስ ግንባር ቀደምትነቱን ይይዛሉ በሁለቱ ወገኖች መካከል የነበረውን ፍጥጫ ባህሩ ዘውዴ ሲገልፁት በወግ አጥባቂዎቹና በተፈሪ መካከል የነበረው ልዩነት ባጥቅሉ ሲታይኢትዮጵያ በነፃነት ባለችበት ቆማ ትቅር ወይስ የውጭ ኃያላንን ተጠግታ ወደፊት ትራመድ በሜለው አማራጭ ላይ የሚሽከረከር ነበር ይሉታልየምሁራኑ ራስ ተፈሪን መደገፍም ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሚታይ ነው በምሂልክ ዘመን የተሾሙት ሚኒስትሮች በእያሱ ጊዜም እንደቀጠሉ ነበሩ ስልጣናቸው ስር የሰደዴ መሆኑ ይታወቃልብዙዎችም ከተፈሪ ይልቅ ለዘውዲቱ አክብሮት ነበራቸውለዚህም ይመስሳል የመጀመሪያው አድማ ሚኒሰትሮች ይሻሩ በሚል መነሻ የተጀመረውበዚህ በመጀመሪያው አድማ ላይ የራስ ተፈሪ ተሳትፎ እምን ድረስ እንደነበር በውል አይታወቅምነገር ግን በቀጥታም ባይሳተፉበት በተዛዋሪ በደጋፊዎቻቸው ኣማካኝነት የተቀሰቀሰ አድማ እንደሆነ የብዙ ፀሐፍት ግምት ነውአድማው ህዝባዊ ገፅታ ያለው ይምሰል እንጂ አንቀሳቃሾች መሀል ሰፋሪዎች ነበሩ መሐል ሰፋሪ ተብሎ የሚጠራው ጦር ንጉሠ ነገሰቱ በሚቀመጥበት ከተማ ከየምድቡ እየተውጣጣ በወር ተራ እየገባ በቅርብ ሆኖ ከተማዋንና የመንግስትን ንብረት የሚጠብቅ የታጠቀ ሠራዊት ነው በዚህ ኣድማ ሙ ቆቆዓ የራስ ተፈሪ ሜና እንደነበረው የሚያስጠረጥረው የአድማው ቃል ላይ ገና አልጋወራሽ በሆኑ በኛ ዓመታቸው ከሳሾቹ የተፈሪን ስም እያሞገሱአስተዳደራቸውን እያጋነኑ ከአቤቱታቸው ጋር ማቅረባቸው ነው መጋቢት ቀን ዓም በመሀል ሰፋሪው አነሳሽነት ተጀምሮ ወዲያው ህዝባዊ ድጋፍ የተላበሰው የሚኒስትሮች ይሻሩ ጥያቄ ለራስ ተፈሪ እጅግ ጠቃሚ መሆኑ ግልፅ ሲሆንነገር ግን ሁለት ስጋቶች ነበሩሑአንደኛው ሜኒሰትሮች የከፍተኛ ስልጣን ባለቤትና በሹም ሽር ጉዳይ የሚመክሩ የየራሳቸው ብዙ ወታሮች የነበሯቸው ናቸውና አሜን ብለው መሻር ባይፈልጉ አመፁ ሲፈራበሌላ በኩል ደግሞ ህዝቡ የመሀል ሰፋሪው አነሳስ ተገቢ ነው ብሎ በአደባባይ መሰብሰቡና በዚህ ኣይነት ጉዳይ ቀጥታ የሀዝብ ተሳትፎ መኖሩ የራስ ተፈሪ ስጋት ነበር በሚገርም ሁኔታ ግን አንዱ ስጋታቸው በሌላኛው ሰጋት መቀረፍ መቻሉ ነውበሌላ አገላለዕ ራስ ተፈሪ ያልጠበቁት የህዝብ አመፅ ቢያሰጋቸውና ባይወዱትም ሚኒስትሮችን ግን አንለቅም ብለው እንዳያውኩ አግዶላቸዋል በየጊዜው እያደገ የሄደውን ይህን አድማ አስመልክቶ የህዝቡን የክስ ቃልየመሀል ሰፋሪውን የተቃውሞ ድምዕና ከአልጋ ወራሹ የተሰጠውን ምላሽ ለአንባብያን ማድረሱ ጠቃሚ ነውና በደጃዝማች ከበደ ተሰማ ተፅፎ በ ዓም ዋታሪክ ማስታወሻ በሚል ርዕስ የታተመውን መፅሐፍ ጠቅሼ በሚካተለው መልኩ አካትቸዋለሁ በጉዳዬ ላይ ህዝቡ ተሰብስቦ በሚዶልትበት ጊዜ የተሰበሰበውን ህዝብ የሚያስፈርድ አጋፋሪ ተሹሞ ስለበር እያስነሳ ይጠይቃል በዚህ ጊዜ አንዱ ሜታችን እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ዓለም ፈጥሮ ሐዋርያትን አገር ከፍሎ እንዲያስተምሩ ያሰማራቸውን ለመምሰል ላገሩና ለመንግስቱ ልማት በውነት እንዲመክሩና እንዳሰሩ ቱን ሚኒስትሮች ደጉ ጌታችን አፄ ምኒልክ መርጠው ቢሾሟቸው ለአገር ልማት ለህዝብ አንድነት በመምከር ፈንታ አንዱ ላንዱ ለየራሳቸው ጥቅም በመመልከት አገሩን አበላሹት እንጂ ስለመንግስት የጠቀሙትና የሰሩት ጉዳይ የለም ቱን ሐዋርያት በማየት የተሾሙት ሚኒስትሮች አጋንንት ስለሆኑ እንዲሻሩ ያስፈልጋል ለምሳሌ የስራ ሚኒስቴር ተብሎ የተሾመው የራሱን ቤት ለመስራት በቤት ላይ ቤት እየቀጠለ ወደሰማይ ለመውጣት ይገዓሰግሳል እንደዚሁም የግቢ ሜኒስቴር የተባለው የራሱን ሐብት ብቻ በማደራጀቱ ከምኒልክ ቤት ለግብር የሚሆን መሰናዶ ታጥቶ ባለፈው ሰሞን ከእርሱ ቤት ዱቄት ተግዞ ተሰናዳ ይህ ምን ያሳያል። ትልቅ ጅማሮ ነው እነዚህ እንደራሴዎች በፊት በመሳናንቱ ይሁንታ የሚመረጡ የነበሩ ሲሆን ከ ዓም በኋላ ግን በህዝብ መመረጥ ጀምረዋል ሀዝባዊ ምርጫ በ ዓም ከተጀመረ በኋላም ለዙር በየ ዓመቱ ምርጫ ተካሂዷልተመራጮች እንደዛሬው ኣይሁን እንጂ ቅስቀሳ ያደርጉ ነበር የመወዳደሪያ ምልክትም ነበራቸውከተሻሻለው ሕገዓ መንግስት ጋር ተያይዞም ሰባት የነበሩት የሰራ ክፍፍሎች ወደ አድገዋል ከየግዛቱ ተመርጠው የሚመጡ እንደራሴዎችም ቀደም ሲል አነስተኛ ቁጥር ይኑራቸው እንጂ ወደኋላ ደርሰዋልደሞዙ በ ብር ተጀምሮ በየጊዜው እያደገ ሺ ብር ደርሶ ነበር በርከት ያሉ ሴት ተመራጮች የፓርላማው አባል ነበሩከሰኞ እስከ አርብ ፓርላማው ስራ ላይ ነው ሰኔ ለእረፍት ይዘጋል ጥቅምት ስራ ይጀምራል ንጉሠ በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ ይገኛሉ በመዝጊያና በመክፈቻ እለት ብቻ ንግግር ያደርጋሉ የመወሰኛ ምክር ቤቱ አባላት ብዛትም ደርሶ ነበር በአጠቃላይ ይዘትና ቅርፁ ከአሁኑ ብዙ የተለዬ እንዳልነበር በህይወት ያሉ የቀድሞው አባላት ይገልፃሉ አፄ ኃይለስላሴ ምክር ቤቶችን ካቋቋሙና ሕገመንግስቱን ካፀደቁ በኋላ ግን ብዙሃኑ ተስማምቶ ለሕገመንግስቱ ተገዥነቱን ያረጋግጥ እንጂጥቂቶች እውቅና ነፍገው ነበር እንግዲህ በዚህ ሕገመንግስት መሠረት በርካታ የአስተዳደር ለውጦች የተፈጠሩ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የርስት ውርስ መብት አንዱ ነው በዚህም ንጉሠ ነገስቱ ይሾማል እንጂ ያባቴ ግዛት የሚባል ነገር የለም ይህን ህግ በመቃወም የጎጃሙ የንጉስ ተክለሐይማኖት ልጅ ራስ ኃይሉ ተክለሐይማኖት የጎጃም ገዢ ሆኖ ለ ዓመታት ያሀል የቆየ ነበርና አልገዛም አለ ይባስ ብሉ» ልጅ እያሠ ታስሮ ከነበረበት ከፍቼ እስር ቤት ሊያስመልጥ ሲል ተገኝቶ ለፍርድ ቀርቦ ሞት ቢፈረድበትም ንጉሥ ሀብቱ ተወርሶ እንዲታሰር አደረጉ ጎጃም ላይ የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ እምሩ ኃይለስላሴን በ ዓም ሾሙ ከዚያም አፄ ኃይለስላሴ ፊታቸውን ወደጅማ በማዞር በቀዳማዊ እባቿፋርና በዳግማዊ አባጅፋር ጊዜ ለአፄ ምኒልክ በሰላም ከገበረች ጊዜ ጀምሮ ነፃ የውስጥ አስተዳደር የነበራት ጅማ በማእከላዊው መንግስት ቁጥጥር ሰር ሆነች ሌሎችም በተመሳሳይ ተጠቀለሉ በቀጥተኛው አስተደደራዊ ቁጥጥር ስር ማዋል ከባድ ሆኖ የታየው የትግራይ ግዛት ብቻ ነበርና የአፄ ዮሐንስ የልጅ ልጅ የሆኑት ራስ ስዩም መንገሻና ራስ ጉግሳ አርአያ ምዕራብና ምስራቅ ትግራይን ያስተዳድሩ ስለነበር እነሱን በቅርብ ዘመድ ጋብቻ ጠልፈው ጠቀለሉ መንግስት በየግዛቱ ላይ የበላይነቱ እያየለ ሲሄድ ምንም እንኳ የቀድሞው ባሀሪውን የለወጠ ባይመስልም ንጉሠ ነገስቱ ግን በግዛቱ ብቻ ሳይሆን በሠራዊቱ ላይም ማዘዝ የሚችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል ባየነው መልኩ የአፄ ኃይለስላሴ ስልጣን በጽኑ መሠረት የተገነባ መሰለ የኢትዮጵያ የዘመናዊነት ጉዞም ፍጥነቱን ጨመረ ታማኝ ምሁራንም በተቋቋሙት ዘመናዊ የመንግስት ድርጅቶችና መስሪያ ቤቶች እየተመደቡ በሕግ በተሰጣቸው ሰልጣን ዘመናዊ አሰራራቸውን ገፉበት ቀደም ባለው ጊዜ ከውጭ አገር የመጡ አማካሪዎችና የልዩ ልዩ ሙያ ባለቤቶች የተባሉትም አንዳንድ አገር የማዘመን ሰስራ ለመስራት እንቅስቃሴ ጀመሩ ለምሳሌ ዘመናዊ ጦር የማሰልጠንና ሌሎች ከዚህ ቀደም ያልነበሩ ስራዎች ተጀመሩ የተጀመሩትም ተጠናክረው ቀጠሉ በጥቅሉ ከአልጋወራሽነታቸው ዘመን ጀምሮ የታቀዱ ስራዎች ሁሉም መልክ እንዲኖራቸው ሆነ ሕጉመንግስቱን መሠረት በማድረግም የመንግስትን የገቢና የወጪ ስርዓት ቅርፅ እንዲይዝ አደረጉት ለቤተ መንግስት ለቤተካክርስቲያን ለጦርና ለጉልተኛ ሹማምንት የገባሪዎች የጉልበት አገልግሎት የምግብ ግብር የምርት ስፍር የአስራት መዋጮ የመንግስት የግብርኖ እና የበጀት መሰረቶች ነበሩ ከሕገመንግስቱ መፅደቅ በኋላ ግን የመንግስት ገቢ ለመጀመሪያ ጊዜ በገንዘብ ግብር ላይ እንዲመሠረት ደነገጉ ምንም እንኳ ወደፊት እንደምናገኘው ዘመናዊ የሆነ የበጀት ስርዓት ነበር ባይባልም መሠረቱ የተጣለው ከወዲሁ ነበር እናም የቱ ሕጉመንግስት ለዘመናዊት ኢትዮጵያ ጅምር አንቅስቃሴ ሰፊ ሚና ነበረው አገር የማሰልጠን ሂደቱ በቀጠለበት ሁኔታ ግን ብዙ ሳይቆይ ከ ዓመት በኋላ ወረራው ተከተለ ከጣሊያን ወረራ እስከ ነፃነት የኢጣሊያ ዓድዋ ላይ መሸነፍ የሱዋ ብቻ ሳይሆን የመላው ቅኝ ገዥ ኃይል ሽንፈት ነበርና በቂ ዝግጅት ተደርጎ ሽንፈቱ በድል መለወጥ ነበረበት ይህ የሀያላኑ ግልፅ መሻት ነው አውሮፓውያን በጥቁር ህዝቦች ድል ከተደረጉ የሌላውም አገር ጥቁር ለነፃነቱ መነሳቱ አይቀሬ ጭና ሽንፈት ብቻ ሳይሆን ስጋትም ጭምር ነበር በመሆኑም ዳግም ወረራው እንደማይቀር አሳምረው ያውቁታል ኢጣሊያ ያቦካችውን እራቧ መጋገር እንዳለባትም እንዲሁ ስለዚህ ፈረንግይና እንግሊዝ የኢጣሊያ መንግስት ኢትዮጵያን ዳግም ወርሮ ሽንፈቱን በድል አንዲለውጥ ይፈልጋሉና ከፍተኛ ግፊትና ማበረታታት ቢያሳዩ አይደንቅም የዳግም ወረራው ጥንስስ ከዓድዋው ድል ማግስት የጀመረ ነው ጣልያኖች ከአድዋው ሽንፈታቸው በኋላ ከአፄ ምኒልክ ጋር ወዲያው ነበር ዣ የድንበር ስምምነት ያደረጉት በዚያው ጊዜም ቺኮዲኮላን የተባለው ቆንሲል ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሰላለው ቀጥኋሏል በጥቅምት ወር ዓም ፈረንሣይእንግሊዝና ኢጣሊያ የተፈራረሙት ውልም ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም ጋር ብቻ የተያያዘ ይምሰል እንጂ ኢጣሊያ በኢትዮጵያ ለሚኖራት ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ የወደፊት ወረራዋን የሚያመቻች ነበር በኛው የዓለም ጦርነት ጀርመን ኢጣሲያን የጦር ጓደኛዋ እንድትሆን ጥያቄ ስታቀርብላት ደግሞ ፈረንሣይና እንግሊዝ ኢጣሲያን መልቀቅ አልፈለጉምና ኢጣሊያ ከእነሱ ጋር ሆና ፀረጀርመን አቋም መያዝ እንዳለባትና ከድል በኋሳ ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛቷ እንድታደርግ አስፈላጊውን ትብብር ሁሉ እንደሚያደርጉላት ቃል ገቡ ኢጣሊያም ከቅኝ ግዛት ድንበረተኞቿ ጎን ብትሰለፍ እንደሚሻል መረጠች በዚህም ላይ ከድል በኋላ የጀርመንንና የቱርክን ግዛቶች መካፈል ይችሌ ነበርና ኢጣሊያ በተለይ የሰሜን አፍሪካን የቱርክ ግዛቶች ፈለገች እንደነሲቢያ ያሉትን ጓደኞቿ እንደማይሻሟት ቃል ገቡላት የኢጣሊያ እያንዳንዷ እንቅስቃሴም ኢትዮጵያን ዳግም በእጂ ከማስገባትጋር የተያያዘ ነው በ ዓም ኢትዮጵያ የመንግስታቱ ማኅበር አባል ስትሆንም የይስሙላ ተቃውሞ ከእንግሊዝ በኩል የተሰነዘረ ቢመስልም ኢጣሊያ ድጋፏን አሳይታለች ራስ ተፈሪ አውሮፓን በጎበኙ ጊዜ የኢጣሊያ አቀባበል ከሁሉም የተለየ ሆኖ ቪሻ ኢትዮጵያ እያሉ በይስሙላ አድናቆት እንዲቀበሏቸው ተደርጓል የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ፍቅር በደንብ መጠንከሩን ለማሳየት ደግሞ ሐምሌ ቀን ዓም ለ ዓመት የሚዘልቅ የወዳጅነትና የሠላም ውል ተፈራረሙ ከዚሁ ጋርም አሰብንና ደሴን የሚያገናኝ የመኪና መንገድ ለመስራት ተስማምተው ነበር በዚህ ሁኔታ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ስታዘናጋና ስታሰልል ከረመች ጎን ለጎንም ከፍተኛ የጦር ዝግጅት እያደረገች ቆየች ኢትዮጵያ የጦር መሣሪያም ሆነ ሌላ ነገር ገዝታም ሆነ በእርዳታ ሰማስገባት ብትፈልግ እንኳ ወደቦቿ ሁሉ በሦስቱ አገሮች ቁጥጥር ስር ነበሩና በተለያዩ ምክንያቶች ሲዘጉባትለማስመሰል ጥቂት ነገሮችን ሲለቁላት ቆዩ። ቢባል ይሻሳል የእንግሊዝ ውለታ ተገቢ ከብር ቢሰጠውም የራሠዋን ጥቅም ማእከል አድርጋ ማገዙዋ መዘንጋት የለበትምየሦሆነው ሆኖ ይህች በአምላክ እርዳታ ነፃ ሆናለች ሲያልፍ ሴረኞቹ በስምምነት አስያዚት ሲጣሉ አሰለቀቋት መቼም የኢትዮጵያ አምላክ ሒትለርን አስነሳላት አንልም ግን ይገርማልዲምትሪ የፍሞቭ የተባለ ሩሲያዊ ኛው የዓለም ጦርነትና የእስያና የአፍሪካ ህዝቦች ዕጣ በሚለው መፅሐፉ በዚያ የዳግም ወረራ ጊዜ ያለቁትን ኢትዮጵያውያን ሺ መሆናቸውን ፅፏል ሌሎችም ተመሳሳይ ኣሀዝ ያስቀምጣሉየኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ወርቅነህ ተገኘ በገለፁልኝ መሠረት ደግሞ ሚሊዮን ዜጎች አልቀዋልበመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ተቃጥለዋል በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶሮፍየልበግከብት አህያ ወዘተ አልቀዋልያውም በአሰቃቂ ሁኔታስለዚህ የኢትዮጵያ ነፃነት በደም የተዝዛ ነፃነት ነውሚያዚያ ቀን ብሔራዊ እለት ሆኖ የታወጀውም ለነዚሁ ጀግኖች ነውእኛም በዚሁ አጋጣሚ አመስግነናቸው እናልፋለን ጽ ቂልን ቁ በድል አድራጊነት ኣዲስ አበባ ሲገቡ ኛው የዓለም ጦርነትን የጀርመን ናዚዝም የኢጣሊያ ፋሺዝም የጃፓን ሚሊታሪዝም ተባብረው እሰከመጨረሻው ሊገፉበት ቢሞክሩም የቃልኪዳኑ የአሜሪካ የሶቭየት ኅብረት የፈረንሣይና የእንግሊዝ ጦር በስተመጨረሻ ድል አርጓቸዋል ከዚሁ ጋር ተያይዞም በተለይ የኢጣሊያ የአፍሪካ ግዛቶች ከፊል ሶማሊያ ኤርትራና ሊቢያ ከኢጣሊያ ተገዥነት ነፃ ወጥተዋል ሆኖም ድል አድራጊዎቹ የቃልኪዳኑ አገራት አንድ የጋራ ውሣኔ እስኪያሳልፉ ድረስ ነፃ የወጡ አገሮች በእንግሊዝ ሞግዚትነት መቆየት ነበረባቸው እንግሊዝም ከጠላት የነጠቅናቸው አገራት ናቸው አለች እንጂ ኝፃ አወጣናችሁ አላለችም ነበር የእንግሊዝ የበላይነት የእንግሊዝ ወታደሮችና የኢትዮጵያ አርበኞች በኅብረት ፋሽስቶችን በአጭር ጊዜ ድል አድርገዋል የቀድሞው የኢጣሊያ ሶማሌላንድን ወደራሳቸው የሶማሊያ ግዛት መቀላቀል የቻሉትም ሆነ ኤርትራንም ደርበው የያዙት በጦር ኃይል የተያዙ የጠሳት ግዛቶች ናቸው በሚል ነው ነገር ግን የኢትዮጵያ ግዛት የሆነውን ኦጋዴንን ቀደም ሲል ኢጣሊያ ከቀድሞው ግዛቷ ከኢጣሊያ ሶማሌላንድ ጋር ቀላቅላው ስለነበር አሁንም እንግሊዞች አብረው ሊወርሱት ፈለጉ የእንግሊዝ ጦር ባለስልጣኖች የኢትዮጵያን ነፃነት እውቅና ቢሰጡትም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረጉት ለ ዓመት የሚቆይ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ውል አማካኝነት የእጅአዙር ቅኝ ግዛታቸውን ለመቀጠል ሞከሩይህ ውል ጥቂት ለኢትዮጵያ የሚያስፈልጉ አንቀጸችን በማካተት የቀሩት የእንግሊዝን የበላይነት የሚያረጋግጡ ነበሩሆናም ለክፉ የሚሰጥ ውል አለነበረምንጉሱ ውለታ ስላለባቸው ብቻም ሳይሆን አንዳንድ ጠቃሚ ነዝሮች ስለነበሩበትና ለ ዓመት ብቻ ስለሆነ ፈረሙበትየታሪክ አጥኝው ፕር ላሏሶ ዲሌቦ ካካተቷቸው ጥቂቶችን ስናይ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ከሌሎች የውጭ መንግስታት ተወካዮች የቅድሚያ ክብር ይሰጠዋል የእንግሊዝ ዜጎች የጦር መኮንኖችና ባለስልጣኖች ለኢትዮጵያ መንግስት የፖለቲካ እና የሕግ አማካሪዎች ሆነው ይሰራሉ ለእንግሊዝ መንግስት በቅድሚያ ሳያሳውቅ የኢትዮጵያ መንግስት ሌላ የውጭ ኣገር አማካሪዎችንና ሰራተኞችን ለመቅጠር አይችልም በአራት ተከታታይ አመታት ውስጥ የእንግሊዝ መንግስት ስኢትዮጵያ መንግስት የ ሚሊዮን ሺ ፓውንድ ስተርሊንግ በእርዳታ ሊሰጥ ተስማምቷል የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ ለእንግሊዝ የጦር ኃይሎች አገልግሎት የሚያስፈልጉ የማይንቀሳቀስ ሐብትና ንብረት ማለትም የመሬት አገልግሎት ያለክፍያ ለመስጠት ተስማምቷል የኢትዮጵያ የውጭ ንግድና የገንዘብ ፖሊሲ የሚካሄደው በእንግሊዝ መንግስት የስራ መመሪያና ፈቃድ ይሆናል የፋሽስት ጦር እስረኞችና የእንግሊዝ ዜጎች በኢትዮጵያ ሕግኖ ዳኞች አይከሰሱም ከእንግሊዝ አየር መንገድ በስተቀር ሌላ የውጭ አገር አየር ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ተወስኗል በምስራቅ አፍሪካ የእንግሊዝ ጦር ጠቅላይ አዛዥ ሳይፈቅድ ያኢትዮጵያ መንግስት በወታደራዊ ጉዳይ ከሌላ የውጭ አገር መንግስት ጋር ምንም አይነት ስምምነት ለማድረግ አይችልም አንድ የእንግሊዝ ወታደራዊ ቡድን ከምስራቅ አፍሪካ የእንግሊዝ ጦር ጠቅላይ አዛዥ በሚሰጠው የስራ መመሪያ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ይቋቋማል በሚሉና የባቡር መሰመር ሐዲዱን ሳይቀር የበላይ የሚሆኑበትን ውል በጥር ወር ዓም አስፈረሟቸው በዚህም ኢትዮጵያን ለ ዓመት ያሀል በወታደራዊ ሕግ በጥገኝነት ይዘው ቆዩ የእንግሊዝ ጦር ባለስልጣኖች በሁለት ዓመት የጥገኝነት አዝካዛቸው ወቅት በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ወታደራዊ ተልዕኮ የሚባል ቡድን በማቋቋም የአገሪቱን የመከላከያ አቋም በዘመናዊ መልክ ለማደራጀት ተስማምተው እንቅሰቃሴያቸውን ጀመሩ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የበላይ ተቆጣጣሪ ሆኑ የኢጣሊያ ጦር ይጠቀምባቸው የነበሩትን ልዩ ልዩ ማቴሪያሎች ከአገር አወጡ በአንድ በኩል የንጉሠ የፖለቲካና የጦር አማካሪ ሆነው እየሰሩ በሌሳ በኩል በድብቅ ህዝቡን ማጋጨት አርበኛውን ከስደተኛ ስደተኛውን ከአርበኛ በዘዴ እያፋጩ ከውል ውጭ በሆነ መንገድ ኦጋዴንን በቁጥጥራቸው ስር አደረጉ ኤርትራ ከ ዓም ጀምሮ በኢጣሊያ ስር ስለነበረችና አሁን እንግሊዞች ስላስለቀቋት ከሌሎች የአፍሪካ ቅኝ ግዛት አገሮች ጋር እጣዋ እስኪወሰን በሞግዚትነት መያዛቸው አግባብነት ቢኖረው እንኳ ኦጋዴን ግን እስከ ዓም ድረስ ተነጥሎ ስለማያውቅ እንግሊዞች በአዲሱ የኢጣሊያ ክለላ መሰረት አድርገው ወደ ቅኝ ግዛታቸው መቀላቀላቸው ሕጉወጥ ነበር የእንግሊዝ ጦር ባለሰልጣኖች በዚህ ሳይወሰኑ የኤርትራን ህዝብም በዘር በሃይማኖት በጎሳ እየከፋፈሉ ወደፊት ከእናት አገሩ ከኢትዮጵያ ጋር እንዳይቀላቀልና ለነፃነት እንዳይነሳ ያመቻቹት ነበር ንጉሱ ኤርትራ ለኢትዮጵያ መሰጠት አለባት ብለው እየተከራከሩ ጭራሽ ኦጋዴንን ሊነጥቋቸው በመሞከራቸው ሊታገሱት እልቻሉም የእንግሊዝ አካሄድ መጥፎ አቅጣጫ እየያዘ ሲሄድ ሌላ ረዳት ፍለጋ ማማተር ነበረባቸው የሁለት ዓመቱ ውል አልቆ በታህሳስ ወር ዓም ሌላ ውል ሲፈራረሙ የኦጋዴንን ጉዳይ ቢያነሱትም እንግሊዞች መልቀቅ አልፈለጉም ለ ዓመት የዘለቁት ውሎች በሁለተኛው ውል አማካኝነት ቢሻሩም የኦጋዴን ጉዳይ አልተመለሰም ነበር በተረፈ የቱ ውል የባቡር መስመር ሐዲዱን ለኢትዮጵያ ያስመለሰ የአምባሳደሩን የበላይነት ያስቀረ ኢትዮጵያ ከየትኛውም አገር ጋር በነፃነት በአማካሪነትም ሆነ በቅጥረኝነት እንዲሁም በማናቸውም ኣይነት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥታ ማድረግ የምትችል በአጠቃላይ ሙሉ ለሙሉ ለማለት በሚያስችል ሁኔታ ነየነቷን የመለሰ ውል ነበር ከዚህኛው ውል በኋላም ነው ንጉሠ ከሌሎች ኃያላን አገራት ጋር ጥብቅ ትስስር ለመፍጠር እንቅስቃሴ የጀመሩት የኦጋዴን ጉዳይ ግን እስከ ዓም ድረስ በጅጅጋ ማዕከልነት በእንግሊዞች እጅ ቆይቶ በ ከፊሉን የኦጋዴን ድንበር ማለትም ከእንግሊዝ ሶማሌላንድ ጋር የሚዋሰነውን ሀውድን ቆርሳ ወደራሷ ከቀላቀለች በኋላ ግተከለለ ድንበር ብላ ወስና ከፊሉን ለኢትዮጵያ መለሰች በመጨረሻ በ ዓም ደግሞ እሱንም መልሳ ለቃ ወጣች ካባ ሁጤት ን ያ ሚንግለት ሙግትና ክርክር ብቻውን ያስገኘው ነ ም ፍ ይዘት ያለውን መፍረክረክን ተከትሎ የመጣ ነው የኦጋዴን ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ደግሞ ከሶማሊያዎች ነፃ መውጣት በኋላ የይገባናል ክርክር አስነስቶ ነበር በመጨረሻ ግን የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ከተቋቋመ በኋላ በቅኝ አቁብህ የተከለሱ ድንበሮች ሁሉ በዚያው መፅናት ኣለባቸው የሚል ው ምምነት ላይ ተደርሶ ኦጋዴን በትክክለኛ አላኔ ስምፖሥነት ላ ታሪኩ የኢትዮጵያ ሆኖ የእንግሊዝ የበላይነት ቆይታ ምንም እንኳ የንጉሠ መንግስት አስተዳደር ባይጋፋም ሴራ የተቀላቀለበት ችሮታ መሆኑ ንልፅ ነው የኢትዮጵያ መንግስት በእነዚያ ጊዜያቶች የድንበር ይገባኛል ጥያቄውንም የአዲስ የአስተዳደር ሰራውንም ሕጎችን በማውጣት አዋጆችንና ድንጋጌዎችን በማፅደቅ ወዘተ ተጠምዶ ነው የቆየው ምንም እንኳ የኦጋዴን ጉዳይ የኃያላን አገራቱን ትኩረት መሳብ ቢሳነውና እንግሊዝ በራሷ የውስጥ ፖለቲካ ችግር ለመልቀቅ ብትገደድም የኤርትራ ጉዳይ ግን በደንብ መገላበጥ ነበረበት ንጉመም ለኤርትራና ለኦጋዴን መመለስ የጣሩት ጥረት አጅግ ከፍተኛና የሚያስደንቃቸው ነው ነገር ግን ይህች ዓለም ጥኔ ተብላ የምትወሰንና እንደልብ የሚያደርጓት የየግል ግዛት ያላቸው መንግስታት የተካፈሏት ፈለክ ትሁን እንጂ የአንድ ወይም የጥቂት ልእለ ኃያላን ብቻ ንብረት ናት ጥንትም ዛሬም ያው ነው የዘመንና የአገዛዙ አይነት ብቻ ይለያያል እንግሊዝ በኦጋዴን ተክሳው የሄደችው እሾሃማ ችግኝ በዎቹና በዎቹ የሱማሊያንና የኢትዮጵያን ልጆች እያዋጋ አፋጅቷቸዋል አውሮፓውያን ኢምፔሪያሊስቶች ምንም እንኳ ሳይወዱ በግድ አፍሪካን ለቀው ቢሄዱም ለዘመናት ስንናጭ እንድንኖር የሚያደርገውን የቤት ስራቸውን አጠናቀው ነው የሄዱት ፈፅሞ የአፍሪካን ሰላም አይፈልጉም ነበር አሁንም ወደፊትም አይፈልጉም የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም ቢሆን የጥቂት ኃያላን ማሳኪያ እንጂ ሐቀኛ ድርጅት አለመሆኑ ጥንትም ዛሬም ግልቱ ተላ ኋያላኑ እርስ በርስ የተጣሉ ቢመስለንም አፍሪካን በማተራመስ ረገድ አቋማቸው አንድ ነው ልዩነቱ አንድ ኃያል አገር ስትከሰት ሰፊውን የአፍሪካ ክፍል የመቆጣጠር እድሷ መስፋቱ ብቻ ነው አንድ ግልፅ ነገር አለ ይረዱናል መልሰውም ያርዱናል እንግሊዝ ለቃ የወጣችው በተባበሩት መንግሰታት ውሣኔ ይሁን እንጂ ለአሜሪካ መልቀቅ ስለነበረባት ነው አሜሪካ በአልበርት አንስታይን ምክር የአቶሚክ ቦምብ ባለቤት ሆኖ በጃፓን ሁለት አውራጃዎች የፈፀመችው ከፍተኛ ግፍ የበላይነቷን አረጋግጧል እግረመንገዷንም በአለም ላይ የምትከተለውን ሙ ት ጻ ትሁ ት ነው ፖሊሲ ማመሳላከቷ ነው ጉዳዩ እኔ ነኝ የማዋጣችሁ አይነ እንዳለችውም ከኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ብቸኛዋ የሶቪየት ኅብረት ተፎካካሪ ሆናለች ኤርትራ ጉዳይ ደ ኛው የዓለም ጦርነት በኃያላኑ ትብብር በአሜሪካ በሶቭየት ና በእንግሊዝ የበላይነት ከተጠናቀቀ በኋላ የኤርትራ ጉዳይ ውይይት እየተካሄደበት ነበርና የእንግሊዝ ሞግዚትነት ቀጥሷል ኤርትራን ከ ዓም ጀምሮ ኢጣሊያ በጉልበት ወሰዳ እስከ ዓም ድረስ ስትገዛት ኖራለች የኢጣሊያ ጦር ከምስራቅ አፍሪካ እንዲለቅ ከተገደደ በኋላም የእንግሊዝ ጦር ባለስልጣኖች ይዘው ቀደም ሲል እንዳየነው የኤርትራን ህዝብ የመከፋፈል አላማቸውን ው ኢጣሊያ መልቀቅ ጀምሮ በኤርትራ የተለያዩ ቡድኖች ተፈጠሩ በመጀመሪያ ማኅበረ አገር ፍህሪ በሚል የአንድነት ቡድን ተመሠረተ ከዚህ ቡድን ተቃራኒ የሆኑ ሌሎች ቡድኖችም ተመሰረቱና የነፃነትእና የአንድነት ቡድኖች ሆኑ የአንድነት ቡድኑ ሰፊ ሀዝባዊ መሠረት የነበረውና ከኢትዮጵያ መንግስትም ድጋፍ ይደረግለት የነበረ ሲሆን ዓላማው ኤርትራን ከእናት አገሯ ከኢትዮጵያ ጋር ማዋሐድ ው ል አት ቡድኑ ድግሞ በእንግሊዞች አማካኝነት ተወልዶ ከሁለት ተከፈለና አንዱ የሙስሊም ሊግ ራቢጣ አል ዓረቢያ በሚል ስያሜው መሠረቱን በቆላማው የኤርትራ ክፍል አድርጎ ሲንቀሳቀስ ሌላው ሊበራል ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ በሚል ስያሜው መሠረቱን በደጋማው የኤርትራ ጎ መንቀሳቀስ ጀመሩረ ክል የስለም ሊጉ ራቢጣ አል ዓረቢያ ዓላማው በምዕራባዊ ቆላ የሚኖረው ህዝብ በቋንቋ በሐይማኖትና በባህል ከሱዳን ጋር ስለሚመሳሰል ተገንጥሎ ከሱዳን ጋር ይዋሐ ው ከ በራል ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ ደግሞ ዓላማው ከሙስሊም ሊሲጉ ሳይቃረን ደጋማውና ትግርኛ ተናጋሪውን ክፍል ከመረብ ማዶ ከሚገኘው ወባኑ ጋር አዋህዶ ነፃ መንግስት ለማቋቋም ነበር የኤርትራ ትግርኛ ተናጋሪዎችን ከትግራይ ጋር ቀላቅሎ ነፃ አገር ለመመስረት መሆኑ ነው ሌላው ደግሞ የኢጣሊያ ክልሶችና የቀድሞው ወታደሮች እንዲሁም የኢጣሊያ ወዳጆች ተደራጅተው የመሠረቱት አፍቃሬ ኢጣሊያ ፓርቲ ሲሆን ዓላማው በነፃነት ሻፋን የኢጣሊያ የበላይነት በሞግዚትነት እንዲቀጥል የሚፈልግ ነው ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍም ከኢጣሊያ በኩል ይደረግለት ነበር ሙስሊም ሊጉም በዓረቦች ይደገፍ ነበር እንግሊዝ የወለደችው ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ ደግሞ በእንግሊዝ ይደገፍ ነበር እንደሚታወቀው እንግሊዝ በወቅቱ ሱዳን ግዛትዋ ስለነበረች የኤርትራን ግዛት ከሱዳን አጣምራ መያዝ ትፈልግ ነበርኖ ፕሮግሬሲሹኩን ፈጥራ ማሳደግ ነበረባት። ግርማዊ ሆይ ኤርትራ ግዛትዎ በፋሽስቶች ተወርራ ከእናትዋ ኢትዮጵያ ተነጥሳጥንታዊ ክብሯን አጥታ በጠላት አገዛዝ ስር ወድቃ የግርማዊነትዎ አርቆ ተመልካችነት የወጠኑት ተስፋ ባለማቋረጥ እነሆ ጽኑ በሆነ መሠረት ላይ የጣሉት ተስፋ ተፈፅሞ ኤርትራን ከጠላት መንጋጋ ፈልቅቀው ነፃነቷን አልብሰው መታየቷ ግርማዊነትዎ ከፈፀሟቸው እጅግ ሰፊና ታላላቅ ከሆኑት ታሪካዊ የድካም ፍሬዎች አንዱን ምዕራፍ ይዞ የሚገኘው የኤርትራ ከእናትዋ ከኢትዮጵያ ጋር መዋሃድ ነው ግርማዊ ሆይ እኛ ኤርትራውያን ሀዝቦችዎን ከጠላት አገዝ ነፃ ለማውጣት ልዑል እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ በዘመናችን ግርማዊነትዎን ስለሰጠን ከሙሱ ጤንነት ጋር እድሜን እንዲሰጥልን ፈጣሪን ከመለመን በቀር ግርማዊነትዎ ለእኛ ለህዝቦችዎ የፈፀሟቸውን ታሪካዊ ስራዎች ይህን ያሀሳል ወይም ይሀን ይመስላል ብሎ ለመተንተን ችሎታዬ ስለማይፈቅድልኝ ንግግሬን ባጭሩ አቆማለሁ ኔ ማዞ ጃንሆይና አዲሱ የመንግስት አወቃቀር አፄ ኃይለስላሴ ከስደት ከተመለሱበት ከሚያዚያ ቀን ዓም ጀምሮ እስከ ዓም ያስ እረፍት ይችን አገር ለመገንባት በተቻላቸው ሁሉ ጥረዋል ከሰደት እንደተመለሱና ኢትዮጵያም በእንግሊዞች የበላይነት ከነበረችበት ጊዜ ጀምሮ በውስጥ አስተዳደራቸው ጣልቃ ስላልገባች ሕጎችን ሲያወጡ አዋጆችን ሲያውጁ ድንጋጌዎችን ሲደነግጉ ነው ያሳለፉት ነፃነት በተመለሰ ማግስት የአገሪቱ ታላላቅ ሰዎች በሦስት ተከፈሉ ስደተኛ አርበኛ ባንዳ በማሚል ባንዶችን በተመለከተ ወንጀላቸውን የሚያጣራ ልዩ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ተደረገ በስደተኞችና በአርበኞች መካከል ግን ከረር ያለ ውዝግብ ተፈጠረ በዚህ ላይ አንዱ የአንዱን ስም በከንቱ እያነሳ መወንጀል የግል ቂም በቀልን ለመወጣት በሐሰት ስም ማጥፋት ሹመት ለማግኘት ያልነበሩትን በርን ማለትና የመሳሰሉት ጉዳዮች ለፍርድ የማይመች ሁኔታን ፈጠሩ ንጉጮ ስደተኞችን ማስከፋት አልፈለጉም ራሳቸውም ስደተኛ ናቸውና አርበኞችን ማግለል አይችሉም ከሃዲ መባልን ይፈራሉና ባንዶችንም በሙሉ ማጥፋት እይችሉም አገር ምድሩ ባንዳ ነበርና በዚህ ውዝግብ አረበኞች ተሸነፉ ሰደተኞች ትልልቁን ስልጣን ያዙ እዚህ ላይ ፍትሐዊ የስልጣን ክፍፍል አለመደረጉ ብዙዎችን አሳዝኗል ለተሺሚዎችም ሰፋፊ መሬት ተሰጣቸው ንጉሠ ከስደት መልስ የመጀመሪያ ስራቸው ያደረጉት የሚኒስትሮች ምክር ቤት አዲስ ሹመትን ማፅደቅ ነበር ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ማለትም ከ ዓም በኋላ ባሉት ተከታታይ ዓመታት አዳዲስ ሕግና ደንቦች እየቆሙ የነበሩት እየተሻሻሉ አዲስ አስተዳደራዊ መዋቅር ለመዘርጋት ተቻለ ለምሳሌ በቱ የአገር ግዛት ደንብ መሠረት ኢትዮጵያን በ የሸዋ አርሲ የሐረርጌ የሲዳሞ የጋሞጎፋ የከፋ የኢሊባቡር የወለጋ የጎጃም የበጌምድር የወሎ የትግራይ ተብለው ተከፈሉ አውራጃ ግዛት ተብለው ተከፍለው የነበረ ቢሆንም በኋላ በ ጠቅላይ ግዛት ተሰኙና ለግብር አሰባሰብ ምቹ እንዲሆኑ ተደረገ ከዚያ በኋላ ነው ኤርትራ ስትጨመር በሐረርጌ ግዛት ሰር የነበረው ባሌ ራሱን ሲችል የሆነው አዲስ አበባም እምብርት ተብላ በ የጠቅላይ ግዛት ማዕረግ ተሰጣት በመጀመሪያው ሹመት የአገር ግዛት የፅህፈት የውጭ ጉዳይነ የትምሀርት የፍርድ የንግድና ኢንዱስትሪ የፖሰታ የቴሴግራፍና የቴሌፎን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንደ አዲስ ተዋቀሩ በየጊዜውም እየበዙ እየሰፉ ሄደዋል በዚህ መሰሉ የማዕከልና የክፍለ አገር ክፍፍል መሠረት አዲሱ የአገር ግዛት ደንብ ተግባራዊ ሆነና ዋናውን ስልጣንና ሰፊውን ስራ የአገር ግዛት ሚኒስቴር የሚሰራው ሆነ አዲስ የተቋቋመው የሚንስትሮች ካቢኔ ከንጉጮ የሚመነጨውና በማዕከል ከሚኒስትሩ ቢሮ ወደታች የሚተላለፈውን የስራ አመራር በክፍለ አገር ደረጃ በተግባር ላይ የሚያውሉ የአገር ግዛት ሚኒሰትር ባለሥልጣናትኖ ሠራተኞች ጠቅላይ አገር ገዢርዎች ዳይሬክተሮች ፀሐፊዎች የአውራጃ የወረዳና የምክትል ወረዳ ገዢዎች ዳኞች የኃይል አዛዞች ወታደሮች የፖሊስና የፀጥታ ተወካዮች ሌላ አግባብ ያሳቸው ለምሳሌ የገንዘብና የጤና ሚኒስቴር መስሪያቤቶች ተወካዮች ናቸው የአገር ግዛት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሁለት ዋና ተግባራት አሌት በአንድ በኩል በፀጥታ በፖሊስ በወህኒ ቤት በጠረፍ ጥበቃና በኢሚግሬሽን ክፍሎች አማካኝነት የመንግስትን ደህንነትና ፀጥታ መጠበቅ በሌላ በኩል በልዩ ልዩ የግብር የቀረጥና የብድር ምንጮች የመንግስትን የገንዘብ ገቢ መጠን ማሳደግ ናቸው በአዲሱ መንግስታዊ አወቃቀር ላይ ታማኝ ባለሥልጣናትን እየሾሙ የሁሉም የበላይ ንጉሠ ነገሰቱ ሆነው ሚኒስትሮች አስከ ቀበሌ ድረስ ስራው በተዋረድ እንዲቀጥል እያደረጉ በደሞዝ መስራት ጀመሩእንደተባለውም የመንግስት ገቢ በግብርዛቀረጥበአገልግሎት ክፍያዎች ላይ ተመሰረተየገቢ አሰባሰብን በተመለከተም በተለያዩ ጊዜያት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች እየወጡ ተግባራዊ ተደረጉ ከ የነበረው የፋሽስቶች ቆይታ የንጉሠን ስልጣን ለማጠናከር ረድቷል ለአብነት ያህል አንዳንድ ተቃዋሚዎቻቸው ተደምስሰዋል የየመኳንንቱና መሳፍንቱ የግል ጦር ፈርሷል ምንም እንኳን ጣሊያን ዝሙትን አስፋፍቶ ባህልን በርዞ አንድ ህዝቦችን ለራሱ ገ በሚያመች መንገድ በብሔር በጎሳ በሃይማኖት ለመከፋፈል የሸረበው ሴራ ባይዘነጋም አንዳንድ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎቹን ለራሱ መጠቀሚያ ሲል ለማከናወን እንቅስቃሴ ጀምሯል በሕግ ሽረው ያልሻሩትን የባሪያ ስርዓት ሙሉ ሰሙሱ እንዲደመሰሰ አስችሏልበዚህም በገንዘብ ተቀጥረው የሚሰሩ ሰዎች በመበርከታቸው ጅምሩን ካፒታሲዝም አጠናክረው እንዲቀጥሉበት ረድቷል ከጦርነቱ በኋላ በእንግሊዝ ተፅዕኖ ስር ቢሆንም በትምህርት በአስተዳደር በጦር በፖሊስ በፀጥታ በቢሮክራሲ በመንገድ በመገናኛ በንግድና በገንዘብ ስራዎች ድርጅቶችን መልሶ ለመገንባት በተወሰዱ እርምጃዎችና ኤርትራ ወደ እናት አገሯ የመቀሳቀሏ ጉዳይ ተደማምረው የጃንሆይን ስልጣን የበለጠ ሲያጠነክሩ በሌላ በኩልም የካፒታሊዝሙ ስርዓት የበለጠ እያደገ እንዲሄድ በር ከፍቷል ንጉሠ ከእንግሊዝ በኋላ በአሜሪካ በስዊድን በስዊዝ በፈረንሣይ በህንድ በዩጎዝላቪያና በቫፓን አሰልጣኞችና አማካሪዎች እንዲሁም እርዳታና እገዛ እየተደገፉ ሁሉንም ነገር በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ ችለዋል የጃንሆይ መንግስት ቢሮክራሲ ላዕላይ መዋቅሩ በተለያዩ በአዋጅ በሚቋቋሙ መስሪያ ቤቶች እየደረጀና ሕግ እየወጣለት ሲቀጥል ታህታይ መዋቅሩ በልዩ ልዩ የገቢ አሰባሰብ መሰረቱን ጥሎ በየእለቱ እየዘሙነና እየጠነከረ እንዲቀጥል ሆነ በወቅቱ የእንግሊዝ የበላይነት ጠንከር ያለ ነበርና የገንዘብና የወጪ ንግድ ቁጥጥሩ በእንግሊኮዞች የበላይነት ስር ነበር ኢትዮጵያም የራሷ የሆነ የመገበያያ የወረቀት ገንዘብ አላሳተመችም የእንግሊዝ የሁለት ዓመት ውል ካበቃ በኋላ ግን ነገሮች መልካቸውን ቀየሩ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቦች የማሪያ ትሬዛ የኢጣሊያ ሊሬ የእንግሊዝ ፓውንድ ስተርሊንግና የምሰራቅ አፍሪካ ሽልንጎች ነበሩ የገንዘብ ቦርዱም በእንግሊዝ ለንደን የነበረ ሲሆን ከሦስቱ የቦርድ አባላት ሁለቱ እንግሊዛውያን አንዱ ኢትዮጵያዊ ናቸው በ ዓም ኢትዮጵያ የራሷን ፕኢትዮጵያ ብር አሳተመች ስርዓት ያልነበረው የኢኮኖሚ መዋቅር ዘመናዊ እየሆነ ሄደ እጅግ ዘመናዊ የተባለው የግብር አሰባሰብና አጠቃላይ የበጀት ስርዓቱ ተግባራዊ መሆን የጀመረው በ ይሁን እንጂ ከነፃነት በኋላ ዘመናዊ የበጀት ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ ተችሏል ከነፃነት በኋላ ንጉራሙራ ኢትዮጵያዊ ምሁራንን ያሰማሩት በአምባሳደርነት እየሾሙ ነበር አባር ውስጥም በትልልቅ የመንግስት ተቋማት ታማኛቸው የሆኑ ምሁራንን መድበዋል የእንግሊዞች የበላይነት በነበረ ጊዜ የውጭ ግንኙነቱን በአምባሳደሮቻቸው አማካይነት እንዲከናወን ጊሩ አድርገዋል በዚህም ጥረት ለምሳሌ በሰኔ ወር ዓም ቁጥራቸው ከ በላይ የሆኑ አሜሪካውያን የልዩ ልዩ ሙያ ባለቤቶች በፍራንክሊን ሩዝቬልት መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል እነዚህም በሲቪሉ ዘርፍ እንጂ ባፖለቲካው ጣልቃ ገብነት አልነበራቸውም ኢንጅነሮች የቴክኒክ አማካሪዎች ነርሶች ዶክተሮች መምሀራን አናዎችና የልዩ ልዩ ዕደጥበብ ባለሙያዎች ነበሩ ከ በኋላ ግን ንጉሠ በነፃነት ከተለያዩ ስልጡን አገራት መንግስታት ጋር ግንኙነት በመመስረት አገር ግንባታውን በኢኮኖሚ በጦር በፖለቲካ ወዘተ በሰፋት ተያያዙት ወደፊት እንደምናገኘው ሰፋ ያለው እገዛ ከአሜሪካ ነበር የተገኘው የሚገርመው ግን ጃንሆይ እገር አይመርጡም። ገማች ኮሚቴዎች ማዳላት ጀመሩና አበላሹትጉ ምንም እንኳ ሰፊው መሬት ለግብርና ምቹ ሆኖ ቢገኝም በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ሲመጣ አልቻለም ለዚህ ደግሞ ዋናው ችግር ዘመናዊ የማምረቻ ግብአት አለመኖር ነው ስለዚህ በውጭ ንግድ ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የትራክተር እርሻ ተመራጭ ነበርና እሱኑ ተግባራዊ አስደረጉ ጊ የዚህ ተሳታፊዎች መንግስት የውጭ ባለሃብቶችና የአገር ውስጥ ባለሃብቶች ናቸው ባለመሬቶች የራሳቸውን መሬት ሲያርሱና ሲያሳርሱ ሌሎች መሬት ተከራይተው ማረስ ጀመሩ እነዚሀ በሰፊ የእርሻ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች በዋናነት በደቡብ ሸዋና በሁመራ አካባቢ ነበር ለአብነትም በእንግሊዛዊው ሜቼል ኮትስ ኩባንያ የተቋቋመው የተንዳሆ የጥጥ እርሻ ልማት በአዋሽ ሸለቆ በኤርትራ የጣሊያን ከበርቴዎች ያቋቋሙት የኤላበረድ እርሻነ በመንግስት በኩል በ በአዋሽ ሽለቆ ባለስልጣን አማካኝነት የእርሻ የአግሮ ኢንደስትሪና የሐይድሮ ኤሌክትሪክ እንቅስቃሴዎች ይካሄዱ ነበር ለተራው ገበሬም ሁለገብ የእርሻ ልማት በተሰኘ ፕሮግራም ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በማደል ግብርናውን ሰማሳደግ ተሞክሯል ይህም የእርሻ ዘዴኖ ጥቅም ማስፋፊያ በሚባለው የመንግስት ተቋም አማካይነት ይከናወን ነበር ከዓለም ባንክ በተገኘ እርዳታ የተቋቋመው የወላይታ እርሻ ድርጅት ዋዱ በሰፈራ ፕሮግራሙ አማካይነት የመሬት መጣበብን ለማቃለል በመቻሉ ደሃውን ገበሬ በማገዝ ውጤታማ ነበር የስዊድን ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት ሲዳ ገበሬውን በልማት ሊያግዝ ቢቋቋምም ሐብታም ባለመሬቶች እነሱን የሚያግደውን ሕግ ጥሰው ዋና ተጠቃሚዎች ሆኑበት ይህም የጭላሎ እርሻ ልማት ጫጣዱ በመባል የሚታወቀው ነው ድሆችን ሊረዳ ተቋቁሞ ማናለብኞች ተሻሙት ማለት ነው ይሄው ነው ፍትሀ ከሌለ እርሻ ብቻ ሳይሆን መናም ቢወርድ አይሳካልንም የትራክተር እርሻ በተስፋፋበት ጊዜ ለበርካታ ጭሰኞች መፈናቀል ምክንያት ሆነ ምከንያቱም ባለመሬቶች በጭሰኛ ከማሳረስ ይልቅ መሬት ማከራየቱን አዋጭ ሆኖ አገኙት እለት እለት የጭሰኛው ችግር እየተባባሰ ስለሄደም መንግስት የተለያዩ የመፍትሂ አርምጃዎችን ለመውሰድ ቢሞክርም አጥጋቢ አልሆነም በዚህ ረገድ መንግስት የጭሰኛውን ሁኔታ በሚመለከት በ አንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጎ ነበር ይህ ኮሚቴ በ ወደ የመሬት ይዞታ ማሻሻልና ልማት ባለስልጣን አድጎ ከዓመት በኋላ የመሬት ይዞታና አስተዳደር ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ለመሆን በቃ በሂደቱም የጭሰኛውን ችግር ለመፍታት ተንቀሳቀሰ ነገር ግን የሚወጡት ረቂቅ ሕጎች የጭሰኛውን ጥቅም በሚመለከት የባለመሬቱን መደብ ጥቅም ስለሚፃረሩ ምክር ቤቱና አባላቱ እያደናቀፉና እያጓተቱ አዘገዩች የጭሰኛውን ችግር ይፈታል ተብሎ የታመነበት የቱ ረቂቅ ሳይፀድቅ በመቅረቱም ነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሬት ሳራሹ ብለው ሰልፍ የወጡት እንደ ፐሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ሠጊ አገላለፅ ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታትም ተመሣሣዩ የመጨረሻ እቅድ ረቂቅ ሳይሰምር ቀርቷል ይህ በእንዲህ እንዳለም ድርቅቫዛአንበጣ መንጋና ሌሎች የተፈጥሮ አደጋዎች ባደረሱት ቀውስ በ በትግራይ በ በወሎ ጥቂት ቆይቶ በም በዚያው በወሎ ተደጋጋሚ ድርቅና ረሃብ ተከስቶ የብዙ ዜጎችን ህይወት ቀጠፈ ተሸፋፍኖ የቆየው ረሃብ በዩኒቨርስቲው ማኅበረሰብና በውጭ ጋዜጠኞች ተጋለጠ የተፈጥሮ አደጋው እንዳለ ሆኖ ዋናው ተጠያቂ ሙስና ነው ሙስና ጉቦ መቀበል ብቻ አይደለም ይህን ጉዳይ በስተመጨረሻ በሰፊው እንቃኘዋለን የጃንሆይ አስተዳደርና መሬት በጣም በአጭሩ ያየነውን ሲመስል በአጠቃላይ የግብርናው ዘርፍ በየጊዜው እየተስፋፋ ሄዶ በ ዓም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጠቅሳሳ የአገር ውስጥ ምርት የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ በመቶ ቢደርስም በውጤቱ ህዝብን መመገብ የሚችል አልሆነም ጃንሆይና ንግድ ንግድ በጃንሆይ ዘመን ነው የዘመነው አብዛኛው ወደ ውጭ የሚላኩ ሸቀጦች የእርሻ ውጤቶች ነበሩከጠቅላላው የውጭ ንግድ በመቶውን የሚይዘው በዘመናቸው ግጥም ተገጥሞ በጅማ ወጣቶች ዜማ የተሰራለትና ዛሬም ድረስ የሚዘመርለት ቡና ነው ቀጥሎ ቆዳና ሌጦ ነው ከዚያም ጥራጥሬና የቅባት እህሎች ይከተላሉ የወጪና ገቢ ንግዱ ከወደመጀመሪያ ተመጣጣኝ ስላልነበረ የውጪ ንግዱ ውጤት እዚሀ ግባ የሚሉት አልነበረም ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን አገር ውስጥ ማምረት ሲጀመርና ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ ግን መጠነኛ ለውጥ ታይቷል የንግድ ሂደቱ የአገሪቱን የዓለም አቀፍ ግንኙነት አቅጣጫ የተከተለ በመሆኑ ሩሪ በመቶው ከአሜሪካ ጋር ሲሆን በተለይ የቡና ንግድ በመቶው በአሜሪካ ገበያ የሚጣራ ነበር በገቢ ንግድ ረገድ ደግሞ በቅደም ተከተላቸው ጣሊያን ጃፓንና አሜሪካ በዋናነት ይጠቀሳሉ ንግዱ ኪሣራ መሆኑ ሲታይም ነው የኢንደስትሪ ፖሊሲው ላይ ማተኮር ያሰፈለገው የውጪ ሸቀጦች ዋጋ እየወረደ የገቢ ሸቀጦች ዋጋ እየናረ ብዙ ኪሳራዎች ታይተው ነበር የአገር ውስጥ ንግድን በሚመለከትም ቀደም ሲል በወደቦች አቅራቢያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ከተሞች ተጧጡፎ በመሐል ከተማው የቀዘቀዘ የነበረው የአገር ውስጥ ንግድ ወደ አዲስ አበባ አተኩሯል የቀድሞው የምኒልክ የአራዳ ገበያ ከወረራው ጊዜ ጀምሮ ፒያሣ በሚል ኣዲስ ስም ተሰይሞ የነጮች መገበያያ ሆኖ ነበርመርካቶን ለሐበሻ መከለላቸውም ይታወቃል ስለዚህ የችርቻሮው ንግድ ከፒያሣ ወጥቶ ወደ መርካቶ ተዛወረ ፒያሣ ሳይ ሰፍረው ይነግዱ የነበሩ የውጭ ገኅ ዜጎች የበላይነታቸው በታታሪው የጉራጌ ብሔረሰብ እየተሸረሸረ ከስሟል የመርካቶ ጉራጌዎች በየመን ዓረቦች ቁጥጥር ስር ሆኖ የነበረውን የችርቻሮ ንግድ ለመቆጣጠር የቻሉትም ከነፃነት በኋላ ነው አንዳንድ የላይኛው መደብ አባላትም አስመጪና ላኪ በመሆን አንዳንዴ በግላቸውአንዳንዴ በመንግስት ሽፋን ተሰማርተውበታልበመንግስት ደረጃም ብሔራዊ ኮርፖሬሽን የተባለው ድርጅት ተቋቁሞ የእህል ምርትን ለአገር ውስጥ ዜጎችም ለውጭ አገር መንግስታትም ይሸጥ ነበር ይህ ድርጅት በኛው የዓለም ጦርነት የኢኮኖሚ ቀውስ ለደረሰባቸው ለአውሮፓውያን ጦርነቱ እየተካሄደ በነበረባቸው ተከታታይ ዓመታት የእሀል ምርቶችን በመላክ በሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አግኝቷል ከዚያም የኮርፖሬሽኑን ተሞከሮ መሠረት በማድረግ የውጭ ንግዱን ለመቆጣጠር ወይም ለማመጣጠን ሌሎች ተመሣሣይ የንግድ ተቋማት በመንግስት ደረጃ ተመስርተዋል ከእነዚሀም ውሰጥ ንግድና የትራንስፖርት ማኅበር ተብሎ የተሰየመው ድርጅት በቀድሞው አጠራር ማኅበር ቤት የሚባለው የተለያዩ የውጭ ሸቀጦችን ወደአገር ውስጥ የማስገባት ሞኖፖል የነበረው ይጠቀሳል ሌሎችም ቡና ቦርድ እሀል ቦርድ ወዘተ ቦርድ የሚባሉ ነበሩ የጃንሆይ ዋና የገቢ ምንጭ ጉምሩክ ነው የወጪና የገቢ ንግድ ቀረጥ ድንጋጌዎች በተለያዩ ጊዜያቶች ተደንግገዋል የአዋጆቹ ትኩረት ከሚወጡት ይልቅ በሚገቡት ላይ ነበር በውጪ ንግድ በኩል ታሪፋቸው የተደነገገው ቆዳና ሌጦ ቡና ሰም እና ዝባድ ነበር ይህም ዘመናዊ የሆነ አሰራር እስኪዘረጋ ድረስ የቆየ ነበር ከገቢ ንግድ የሚገኘውን ቀረጥ ከፍ በማድረግም የመንግስትን ገቢ ማሳደግ ተችሏልሆኖም ከወጪ ንግዱ የሚገኘው ገቢ አናሳ ስለሆነ በንግዱ ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ሳይታይ ቀርቷል በጥቅሉ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ በገንዘብ ሚር አጠቃላይ መመሪያ ስር የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ የገንዘብ ሕትመት የባንክ ብድርና የወለድ ፖሊሲ በሚመለከት ሃላፊነት ነበረበት በ የትራንስፖርት ሕግ ደግሞ በአገሪቱ ታሪክ ለዘመናት በንግድና በመገናኛ ስራዎች እድገት ላይ ተፅዕኖ ሲያደርግ የኖረውን የኬላ ስርዓትና ቀረጥ አስቀርቶ በማዕከላዊ የመገናኛ መሰሪያ ቤት ስር ዘመናዊ የሞተር ተሽከርካሪ ስርዓትና አሰራር በመፍጠር በአገራችን የንግድና የመገናኛ ታሪካ አዲስ የእድገት ምእራፍ ከፈተ የቱ የጉምሩክ ሕግ የኢትዮጵያ መንግስት የገንዘብ ገቢ ዋናው ምንጭ የውጭ ንግድ እቃ ቀረጥ እንደሆነ አሳየ ነገር ግን ምንም እንኳ እነዚህ መሠረታዊ የባንክ የመገናኛ የጉምሩክና የገንዘብ ድርጅቶችና ስራዎች በአገሪቱ ለዘመኖዊ የንግድና የመገኖኛ እድገት አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዳች ቢሆኑም የኢትዮጵያ ሙ ቁልፍ የእርሻና የእደ ጥበብ ክፍለ ኢኮኖሚዎች ኋላቀር በመሆኖቸው ለንግዱ ክፍለ ኢኮኖሚ እድገትና መስፋፋት ሊያደርጉ የሚችሉት አስተዋፅኦ በአይነትም በመጠንም የተወሰነ ሆነ ቢሆንም የንግድና የመገናኛ ክፍለ ኢኮኖሚው ዘርፍ ከኪሣራ ተነስቶ በየእለቱ እያደገ ሄዶ በአብዮቱ ዋዜማ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጠቅላላ የአገር ውስጥ አመታዊ ምርት ገቢ በመቶ ሆኖ ነበር ይህም ከእርሻ ከአገልግሎት ከኢንደስትሪ ዘርፎች ቀጥሎ የመጨረሻ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ ዘርፍ ሆኗል ማለት ነው ጃንሆይ እና ኢንደስትሪ የኢንደስትሪው ዘርፍ ከወረራው በፊት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር ከነፃነት በኋላ የታየው ለውጥ ከፍተኛ የሚባል እንደነበር ብዙዎች ያምናሌ የዚያ ዘመን ንግድና ኢንደስትሪ እንደ አቅሙ መሰፋፋት የቻለው ንጉሠ አገሪቱን ለኢንቨስተሮች ምቹ በማድረጋቸው ነው ለምሳሌ በ ዓም የተደነገገው የገቢ ቀረጥ አዋጅ ከ መቶሺህ ብር በላይ ካፒታል ያለውኖ በማዕድን በኢንደስትሪና በትራንስፖ ርት ዘርፍ የተሰማራ ማንኛውም ኢንቨስተር በመጀመሪያው ዓመት የሚያገኘው ትርፍ ከቀረጥ ነየ ነበር በንግድ ኩባንያዎች ትርፍ ላይ የሚሰበሰበው ቀረጥም ከ በመቶ እንዳይበልጥ ተደርጎ ነበር በሦስተኛው የበጀት ዓመትም ትራክተሮችና ልዩ ልዩ ኬሚካሎች ከቀረጥ ነፃ ሆነው ነበር የሚገቡት የንጉ አስተዳደር የኢንደስትሪ ፖሊሲ ወጪና ገቢው ይመጣጠን ዘንድ ከውጭ የሚገቡ ቨቀጦችን በአገር ውስጥ ምርት መተካት የሚል ነው በዚህም መሠረት መጀመሪያ ጨርቃጨርቅ ትኩረትን አገኘ አቃቂ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካና ባህርዳር ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ በዋናነት ይጠቀሳሉ በኢንደስትሪ መስፋፋት ትልቅ ድርሻ የሚሰጠው በሆላንዱ ኩባንያ ፀበኤችቪኤ ይካሄድ የነበረው የስኳር ኢንደስትሪ ሲሆን ከነፃነት በኋላ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮለት በ ዓም ሁለት የስኳር ማምረቻ ፋብሪካዎች ማለትም ወንጂ እና መተሐራን አቋቋመ የወንጂ ስኳር ፋብሪካ መሠረቱ የጣሊያን ነበር ጣሊያን በአዋሽ ሸለቆ የሸንኮራ ተክል ማሳ መስርቶ ነበር በ ዓም ኤች ቪ ኤ ተብሎ የሆላንድና የኢትዮጵያ ተብሎ ተሰየመ በርካታ ኢትዮጵያውያንም በሥራ ተሳታፊ ነበሩ በኩባንያው አክሲዮንም ኢትዮጵያ አንድ ሦስተኛ ድርሻ ነበራት በ ከፍተኛ የተባለውን ሚሊዮን ብር ትርፍ ያስገኘ ኩባንያ ነበር ለሸማቹም ትልቅ ለውጥ ነበረው ቀድሞ ስኳር ከውጭ ይገባ ስለነበር ሌላው መጠጥ ሲሆን የመንግስት የገቢ ምንጭ በመሆን ሰፊ ድርሻ ነበረው ከወረራው በፊት የተመሠረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ገ ፋብሪካ የረጅም ዘመን ሞኖፖሉን ከሜታ አቦ ቢራ ፋብሪ መ ጀመረ ኮካ ኮላና ፔፕሲም አገር ውስጥ መዘጋጀት የጀመሩት በንሄራ ዘመን ነው የማዕድን ኢንደስትሪን በተመለከተም ከነፃነት በ የተጀመረው የወርቅ ማዕድን ቁፋሮ እጅግ የላቀውን ገቢ ያን ሆኗል ለምሳሌ በ ዓም ከመንግስት ገቢ አንድ አምስተኛ የተገኘው ከአዶላ ወርቅ ነው ይህ ዘርፍ መንግስትን ስሰላከበረ አዶላ የሚለው የአገር ስም በክብረ መንግስት ተቀየረ ይባላል በጥቅሉ የኢጣሊያ መሠረት ያላቸውን ጨምሮ የጨርቃ ጨ ሲሚንቶ ፋብሪካዎችየዘይት መጭመቂያዎችየእንጨት መለንጠቂያዎችና የእሀል ወፍጮዎች በእጅጉ ተስፋፍተዋል የቆቃ ግድብም በ ሚሊዮን ብር ተሰርቷል ይህ ሚሊዮን ብር የኢትዮጵያ መንግስት ከኢጣሊያ ማግኘት የነበረበትን ካሳ ሳያገኝ ቀርቶነገር ግን ሚሊዮን ብር ብቻ በሰጠው ካሣ የተሰራ ነው የኢጣሊያ መንግስት ለሊቢያ ተገቢውን የጦር ካሣ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ቢከፍልምኢትዮጵያ የጠየቀችውን ገንዘብ ግን አልከፈለምከ ሚሊዮን ብር ውጪ ሌላው የኢጣሊያ ጅምር ኢንደስትሪ የአዲስ ፋብሪካ የሚጠቀስ ሲሆን አባ ሳሙኤል ተብሎ ከሚጠራው ግድሰ የተጠለፈው የመብራት ኃይል ምንጭም የእነሱው አሻራ ነው በንጉጮ ጊዜ ባየነው መልኩ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ በመጣል ያገር መስጡን ኢንደስትሪ ለማስፋፋት ተሞክሯል ሪዎች ማዕከል በአብዛኛው በአስመራ በአዲስ አበ ከተሞች ሲሆን በተለይ በአገሪቱ ካሉ ፋብሪካዎች ውስጥ ማማሽ ያህለ በአዲስ አበባ ይገኙ ነበር ለአብነት ያሀል የተነሱት ዘርፎችና መሰል የኢንዶስትሪ ተት እየተሰፋፉ በመሄዳቸውም የሰራተኛው ዢ ጨመ ሁኔታ ከመፈጠሩም በላይ በአ መ ቁጥር ል ደርሶ ነበር ዶ ብዙቱ መዳረሻ የሰራቲኛው የዜጎች አማካይ የዓመት የነብስ ወከፍ ገቢም ከሃ ሣንቲም ደርሶ ነበርየሰራተኛው መደብ ከየክልሉ መቶቶ ኢንደስትሪ በተቋቋሙባቸው ቦታዎች በጋራ ሲሰራም የመሰብሰብ እድሉን ኣግኝቶ በእድርምበእቁብም መልክ የተለያዩ ማኅበራትን መመሰረት ጀመረየክፍያ መሻሻልና የመሣሠሉት ጥያቄዎች በአቤቱታ መልክም በአድማ መልክም መካሄድ ሲጀምሩ መንግስት በ ዓም የመጀመሪያውን የሠራተኛ ማኅበር አዋጅ ደነገገ በዓመቱ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማኅበር ኮንፌዴሬሽን ተቋቋመ የወንጂ አድማ በ ነበር የተቀጣጠለው የመጀመሪያው የስራ ማቆም አድማ በወንጅ ሠራተኞች ተጀምሮ ወደሌሎችም በመዛመቱ ወደኋላ ላይ ሰንጉሠ ውድቀት ዋናውና ኗል አንዱ ፍሩ በኢንደስትሪው ዞርፍ የታየውን መሻሻል ስናይ በ ዓም ፋብሪካዎች ሺ የፋብሪካ ሠራተኞች ነበሩ አጠቃላይ የክፍለ ኢኮኖሚው የብሔራዊ ምርት ድርሻ ከመቶ ሆኖ የታየው በ ዓም ነው ዘርፉ ከባድ በሚባሉት ሳይሆን አነስተኛና መካከለኛ የሚባል ሆኖ የምግብ የመጠጥ የትምባሆ የጨርቃጨርቅ የቆዳና የጫማ የእንጨት የሲሚንቶ የሸክላ የመስታወት ሰራዎች የሚጠቀለሉ ብረት ነክ ያልሆኑ የማዕድኖች ስራ የማተሚያ የኬሚካል የብረታ ብረትና የመሳሰሉትን የሚያካትት ነወ በአጠቃላይ በአብዮቱ ዋዜማ በኢኮኖሚው በኩል ግብርናው በመቶ የአገልግሎት ዘርፉ በመቶ ኢንደስትሪው በመቶ ንግድ ከመቶውን ሸፍነው ነበር ጣት ዝርጋታ የጦር ዓንባታና የመሠረተ ል ዝርጋ ገ መተዱያ ከወርነቱ በፊት ዘመናዊ ጦር አልነበራትም የሆለታ ገነት ጦር ትምሀርት ቤትም የመጀመሪያ ሰልጣኞችን ሳያስመርቅ ነበር ጦርነቱ የተነሳው ነጭ ለባሽ በሚል መጠሪያ የሚታወቁ ጥቂት የከተማ ፖሊሶች ነበሩ ከነፃነት በኋላ ግን ዘመናዊ ፖሊስ ማግኘት ችሳለች በ ዓም በእንግሊዞች እንግሊዞች ከመልቀቃቸው በፊትም ሺህ የሰው ኃይል ያለው ሣክቡር ዘበኛ ጦር የተባሉት ወታደሮች በስዊዲናውያን መኮንኖች እንዲሰለጥኑ ተደረገ የክብር ዘበኛ ጦር በ ዓም ንጉሠ አሜሪካዊው አይዘንሐወር ግብፅ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ ወዴ ግብፅ አምርተው ተገናኗጂቸውና በኢትዮጵያ ስላለው ጊጊ ወቅታዊ ሁኔታ ተነጋገሩ ስለ ኤርትራ ስለኦጋዴን ስለምድር ባቡር አጠቃላይ ሁኔታውን አስረዱ የአሜሪካው የፔትሮሊየም ኩባንያ ሲንክልየር ሊዉስ በኦጋዴን የነዳጅ ዘይት ፍለጋ ጥናት ቢያካሂድ ኢትዮጵያ ፈቃደኛ እንደሆነች ንጉሠ ያስረዱትምየኦጋዴን ግዛት የይገባኛል ጥያቄ መፍትሄ እንዲያገኝና በዚያውም ከአሜሪካ ጋር ጥብቅ ቁርኝት ለመመስረት ነበ ከ ዓም በፊት የአሜሪካውያን ተሳትፎ በሲቪሌ ዘርፍ ነበርና አሜሪካ በወታደራዊው መስክ ልዩ ድጋፍ እንድታደርግ ንጉ ተማፀኑ ሆኖም አሜሪካ ለዘብተኛ አቋም ይዛ ጥቂት ጊዜ ቆየች ከ ዓም ጀምሮ የተወሰኑ ወታደራዊ እዝዎችን ሰታደርግ ቆይታ በ ዓም ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን ስትተሳሰር ግን አሜሪካም አስመራ ባላት የመገናኛ ጣቢያ ምክንያት የመካከለኛው ምሰራቅ ሰትራቴጂካዊ ጥቅሟ ከኢትዮጵያ ጋር ተያያዘ ወዲያውም የእንግሊዝ ወታደራዊ ተራድኦ ቡድን ከኢትዮጵያ ሲወጣ ኢትዮጵያ የተሟላ ድጋፍ ከአሜሪካ ማግኘት ቻለች በ ዓም በገማል አብደል ናስር አማካኝነት በግብፅ የተካሄደው አብዮትም አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅና በቀይ ባህር ዳርቻ ያላትን አቋም በደንብ እንድታጤን አስገደዳትበእነዚህ ሁኔታዎች መነሻነት አሜሪካና ኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ስምምነት ተዋዋሉ የአሜሪካ ተዕፅኖ ከሁሉም ጎልቶ የታየው በስልጠናና በትጥቅ መስክ ነበር ከ እስከ ድረስ አሜሪካ ያደረገችው ወታደራዊ እርዳታ በ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመት ነበር ከ እስከ ባለው ጊዜ ከ ሺ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በአሜሪካን ኣገር የተለያዩ ወታደራዊ ስልጠና አግኝተዋል ከዚህ በተረፈ ጀቱዐረ አውሮፕላን መቃወሚያው የባህር ኃይል መርከቡና ጀልባው የእግረኛው መሣሪያና አንዳንዴ ዩኒፎርሙም ሳይቀር የሚመጣው ከአሜሪካ ነበር በትጥቅም ሆነ በስልጠና የአሜሪካ ወታደራዊ እርዳታ ቁንጮ ውጤት ተብሎ የሚገመተውና በዘመናዊነቱና በቅልጥፍናውም ዝናን ያተረፈው የአየር ኃይሉ ነበር ነር ባህሩ ዘውዴ አሜሪካ በቱ ለስምምነት መሠረት በአስመራ የሚገኘውን የመገኖኛ ጣቢያዋን ማለትም በመካከለኛው ምስራቅ ኮሚኒስት አገሮችን ለመከታተል የሚያስችላትን የስለላ ጣቢያ ቃኘው ጦር ሠፈር በሚል ስያሜ በመሰየም ይዞታዋን ስታረጋግጥበምላሹም ማግ በሚል ምህፃረ ቃል በሚታወቀው የወታደራዊ እርዳታ አማካሪ ቡድን አማካይነት ሦሰት ዘፍለ ጦር ሠራዊት ለኢትዮጵያ አሰለጠነች አሰልጥናም አስታጠቀችየኢትዮጵያ የምድር ጦር ቀደም ብሎ ከሰለጠነው ጋር ተዳምሮ በአራት ክፍለጦሮች ተደራጀና አንደኛው ክፍለ ጦር ክቡር ዘበኛ በአዲስ አበባ ሁለተኛው ክፍለ ጦር መጀመሪያ ደሴ ቀጥሎ ኤርትራ ሦስተኛው ሐረር አራተኛው ከፊሉ አዲስ አበባ ከፈሉ ነገሌ ቦረና ተመደበ በየክፍሉም አሜሪካውያን አማካሪዎች ተመደቡ የምድር ጦሩን በዘመናዊ መንገድ ካደራጁ በኋላም በስዊዲኖች ተጀምሮ የነበረውን የአየር ኃይልና በኖርዌጅያኖች እየተደራጀ የነበረውን የባህር ኃይል ተሳትልውበታል በእንግሊዝ ስር በነበሩት ህንዶች ይተዳደር ለነበረው የሐረር ጦር አካዳሚም የማቴሪያል ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን የአሜሪካውያን አሻራ ያሳረፈባቸው የጦር ክፍሎች ተብለው የሚጠቀሱት ክቡር ዘበኛና ፖሊስ ናቸው በጃፓን አማካሪነትም ባፋጣኝ የማዕረግ እድገትና ሹመት ብዙ ከፍተኛ መኮንኖች ሊፈጠሩ ችለዋል ከ እስከ ድረስ በዘጠኝ ዓመታት ውስጥ አራት ብርጋዴር ጀኔራሎች ብቻ የነበሩ ሲሆን ከ እስከ ድረስ በአስር ዓመታት ውስጥ ብርጋዴር ሜጀርና ሌተናል ጄኔራል መኮንኖች ተፈጥረዋል ፕር ላኢሶ አጠቃላይ ጦር ኃይሌም በአንድ የጦር ሚኒስቴር ስር እንዲተዳደር ተደርጓል ኢትዮጵያ ከዎቹ ጀምሮ በተከታታይ በአሜሪካውያን ሰፊ ድጋፍ በባህር ኃይል በአየር ኃይል በምድር ጦር በኩል በደንብ የተደራጀ የምርጥ ዘመናዊ ጦር ባለቤት ሆነች ከባድ የጦር ካሚዮኖች ታንኮች ወዘተ አሜሪካውያን ለገሱ ምንም እንኳ የኛው የዓለም ጦርነት ቅሪት ቢሆንም በጥቅሉ አሜሪካ ኢትዮጵያ ለኮሚኒዝም ጥቃት እንዳትጋለጥ በደንብ አዘጋጅታታለች ለማለት ይቻላል የሚገርመው ኮሪያ የዘመቱትና ከአሜሪካውያን ወታደሮች ጎን ተሰልፈው የተዋጉት ቃኘው ሻለቃ በአሜሪካውያን ካልሰለጠኑት ከክቡር ዘበኛ የተመለመሉ መሆናቸው ነው የአሜሪካ ድጋፍ በጦር ኃይሉ ብቻም ሳይሆን በአየር ትራንስፖርት በኩልም አለ በ ዓም ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ያቀናው ልዑክ በኢትዮጵያ የአየር መንገድ ለማቋቋም የአሜሪካን እርዳታ ጠየቀ በሚቀጥለው አመትም በኢትዮጵያ መንግስትና በትራንስኮንትኔታል ኤንድ ዌስተርን ኤር ላይን ባላነህል መካከል ስምምነት ተደርጎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ እኤአ ተቋቋመ ዋና ስራ አስኪያጆችና የቴከኒክ ተቆጣጣሪዎች አሜሪካውያን ሆነው ከቀጠሉ በኋላ በ ዓም የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሰራ አስኪያጅ ተሾመ ለየብስ መንገድም ቢሆን አሜሪካ ዋናውን ድርሻ ሀ ትይዛለች ቀደም ሲል በወረራው ጊዜ ተሰርተው የነበሩ መንገዶች በጦርነቱ ፈራርሰው ነበርአዳዲስ መንገዶችም በብዛት አልነበሩም በ ዓም የአውራ ጎዳና ባለስልጣን ተቋቁሞ የኢትዮጵያን መንገዶች ለመጠገንና አዳዲስ መንገዶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀመረ የባለስልጣን መስሪያቤቱም የተቋቋመው በአሜሪካ ድጋፍና ትብብር ነው የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት በአሜሪካውያኑ የበላይነት ተቋቁሞ ስራውን ሲጀምርም ግንባታው እንደ ኣገራቸው አምሳያ ኦፊስ ኦፍ ፐብሊክ ሮድስ ሆኖ ተነድፎ ነበር የቀጠለውበ ዓም የስራ አስኪያጅነቱን ስልጣን ኢትዮጵያውያኑ ቢረከቡምየመንገድ ስራ እንቅስቃሴዎች ይከናወኑ የነበሩት ግን በአሜሪካ ስር ከሚገኘው ከዓለም አቀፍ የመልሶ ግንባታኖ ልማት ባንክ ኢንተርናሽናል ባንክ ኦፍ ሪኮንስትራክሸን ኤንድ ዴቨሎፕመንት በተገኘ ብድር ነበር በዚሀ ምክንያት ባንኩ በባለስልጣኑ ተግባራት ላይ ከፍተኛ የቁጥጥር ኃይል ጎበረው ቴሌን ለረጅም ጊዜ ይዘው የቆዩት ሲውዲኖች የነባሩ ቢሆንም እንደገና በዘመናዊ መልክ ለማደራጀት የአሜሪካ እጅ ነበረበት ከአፄ ምኒልክ ጀምሮም በየጊዜው እየተስፋፋ መሄዱ ይታወቃል ከባንክ ጋር በተያያዘ እንግሊዞች ሰፊ ተሳትፎ ነበራቸው በወረራው ጊዜ ቀደም ሲል ከነበረው ባንክ ውጪ ባንኮ ዲሮማና ባንኮ ዲናፖሊ የሚባሉ የኢጣሊያ ባንክ ቅርንጫፎች ተቋቁመው ነበር ጣሊያኖች ከወጡ በኋላ በ የተቋቋመው የኢትዮጵያ መንግስት ባንክ እንደ ንንድ ባንክም እንደ ብሔራዊ ባንክም ሲያገለግል ከቆዩ በኋላ በ ዓም ተግባራቸው በአዋጅ የተለየ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ብሐራዊ ባንክ ተቋቋሙ ከዚያ በኋላም እየተስፋፋ ሄደ በትምሀፀርቱም እንግሊዝና ፈረንሣይ የማይናቅ ተሳትፎ የነበራቸው መሆኑ እንዳለ ሆኖ አሜሪካ የአንበሳውን ድርሻ ትይዛለች በርካታ ኢትዮጵያውያን ለትምህርት የሚላኩት አሜሪካ ነበር በጥቅሉ በአገር ግንባታው ዘርፍ ሰፊ አስተዋፅኦ ያበረከተችው አገር አሜሪካ ነበረች ሂደቱ በዚህ ቀጥሎ በስተመጨረሻ ግን የንጉሥን አፍቃሬ ካፒታሊዝምነት እየተቃወሙ የመጡትና የኢትዮጵያን መንግስት ፊውዳል እያሉ የሚጠሩት ምሁራን ተማሪዎች ይሄ የኢምፔሪያሊዝም ነፀብራቅ ነው አያሉ መንቀፍ ጀመሩ የሚገርመው ልክ በዚያው ዘመን የሶሻሊስት ርዕዮት ይከተል የነበረውና ለአስዋን ግድብ ከሶቭየት እርዳታ ይጠይቅ የነበረው ሲውዝ ካናልን ከእንግሊዝና ከፈረንሣይ ሊወርስ የተነሳው ጋማል አብደል ናስር ሞቶ አንዋር ሳዳት የግብፅ መሪ ሲሆን ሶቭየትን ትቶ አሜሪካን ወዳጅ አደረገ የቃኘው ጦር ሠፈር አስፈላጊነትም አከተመ አሜሪካም የመካከለኛው ምስራቅ ስጋቷ ተወገደ በዚያ ላይ ዘመን ተራቆ በሳተላይት መረጃን መሰብሰብ ተችሎ ነበርና የስለላ እምብርቱ ዋጋ ቢስ ሆነ ተማሪዎችም አሜሪካን አሜሪካም ተማሪዎችን ተገላገሉ አፄ ኃይለስላሴ ተደጋግሞ እንደተገለፀው ኢትዮጵያን ዘመናዊ አገር ለማድረግ የውጭ እርዳታ የግድ አስፈላጊ መሆኑን በማመን በዲፕሎማሲው መስክ ልዩ ጥረት ኣድርገዋል ከአፍሪካ መሪዎችም ተወዳዳሪ ያልተገኘላቸው አገር ጎብኝ በመሆን የዓለም አገራትን በመጎብኘት የአንደኝነቱን ስፍራ ይይዛሉ ይህም ለመዝናናት ሳይሆን እርዳታ ፍለጋ ነው ከግንቦት እስከ ታሀሳስ ዓም ድረስ ባሌት ወራት ውሰጥ ከፍተኛ ባለስልጣኖቻቸውን አስከትለው አሜሪካን ካናዳን ሜክሰሲኮን ዩጎዝላቪያን ግሪክን ፈረንሣይን ሆላንድን ምዕራብ ጀርመንን ሲውዲንን ኖርዌይን ዴንማርክን ኦስትሪያን የጎበኙ ሲሆን በህዳር ደግሞ ህንድንና ጃፓንን እንዲሁም ሌሎችን ጎብኝተዋል ዋና አላማቸውም የኢኮኖሚና የቴክኒክ እርዳታ ለማግኘት ነበር ለምሳሌ በህዳር ጃፓንን በጎበኙ ጊዜ በቶኪዮ ከተማ ለጠቅላይ ሜኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የአገራችንን የተፈጥሮ ሐብት በስራ ለማዋልና የህዝባችንን የኑሮ ደረጃ ከፍ ለማድረግ በያዝነው ተግባር አፈፃፀም የጃፓን ገንዘብና የቴክኒክ እውቀት ተካፋይ እንዲሆን በደስታ የምንቀበለው መሆኑን ለክቡርነትዎ ለማረጋገጥ እንፈልጋለን ብለዋልበሌሎች አገራትም ተመሣሣይ ተማፅኗቸውን እንደቀጠሉ ግልፅ ነው አገራቱም ኢትዮጵያን በማዘመን ረገድ የየድርሻቸውን ተወጥተዋል እነዚሀን የመሳሰሉ የስልጡን ባዕድ አገራት አስተዋፅኦ ሰናይም እንዲሁ በችሮታና በርህራሄ ለኢትዮጵያ አዝነው እንዳደረጉት መወሰድ የለበትም አገራቱ የየራሳቸውን ጥቅም ክብርና ተወዳዳሪነትን በማሳየት ፖለቲካዊ ትርፍ ለመሸመትና በርዕዮትም በኩል ቀዳሚነትን ለማወጅ ሲሱ የሚራመዱበት መንገድ ነው ሐሮልድ ማርክሰ ግከ ኮዐህቨር ። ሟጪ ቪጪክ ከ ህበሸ በሚል መፃሀፋቸው ይህ አይነቱ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ የወሰዱት ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ በቀዝቃዛው ጦርነት ኢትዮጵያ ወደ ምስራቁ ርዕዮት ልታዘነብል ትችላለች የሚል ፍርሃት አሜሪካን ከፉኛ አንቀጥቅጧት ነበር በማለት ገልፀውታል ስለዚህም እሜሪካ የኢትዮጵያን ጉዳይ ከልቧ እንድታስብበትና ሙሉ ትኩረት ለኢትዮጵያ ፀጥታ እንድትሰራ የሚጋብዝ ነበር ሲሉ ያክሌበታል ገ ጃንሆይና ትምህርት ጃንሆይና ትምህርት አብረው የተወለዱ እስኪመስል ድረስ አስገራሚ ፍቅር ነበራቸውጃንሆይን ለመተቸት ብዕራቸውን የሚቀስሩ ምሁራን ጃንሆይ ያስተማሯቸው ናቸውበራሳቸው ጎንዘብ ከፍለው ባያስተምሯቸውምዜጐች በአገራቸው ሳይ የመማር መብት ቢኖራቸውም መንግስት ትምህርትን የማስፋፋት ግዴታ ቢኖርበትምብዙ ብዙ ነገር ቢባልምየዛሬ አገር መሪዎችን በጊዜ እንዲሰለጥኑ አድርገዋልና ቢያንስ በትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ ሊመሰገኑበት የሚገባ ስራ ሰርተዋል የትምህርት ፖሊሲው ልክ አልነበረም የምዕራባውያን ምንትስ ነው የመኳንንቱ ልጆች ናቸው የሚማሩበት ትምህርቱ የመንግስት ሃብት ነው የቅበላ አቅሙ አነሰተኛ ነው ወዘተ እየተባለ ይወራል ይሄን ሁሉ ወሬ ለማውራት የሚያስችል እውቀት ስድብን ወደ ወረቀት ገልብጦ መፃፍ የሚያስችል ግንዛቤ መፈክር ካርቶን ላይ በቀለም መፃፍን ሳይቀር ያለማመደ ዘመን ግን የጃንሆይ ዘመን ነው ስለዚህ አንዱን መንግስት አግንኖ ሌላውን መንግስት ለማጣጣል ሲባል የሚካሄድ የትችት ዘመቻ ምንም እንኳ ጨቋኝ የሚባል ስርዓት ነበረው ቢባልም በመልካም መታወሳ የሚችልበትን ታሪክ አብሮ ማንቋሸሽ ተገቢ አይሆንምኑ የውጭ አገር ጠላት ይመስል ይህንን ስራቸውን ሳይቀር ሊያዳፍኑ የሚሞክሩ ጥቂት አይደሉም ይሄ አካሂድ የቀጣዩን መንግስት መነሳሳት ሊያዳክመው ይችላል የምናወራው ስለ ኢትዮጵያ ነው እናም ስለ ጃንሆይ የትምህርት አጀማመርና የሚደነቅ የማሰፋፋት ስራቸው አንድ የነበረችውን የምኒልክ ትምህርት ቤት እሱዋም በፈረንሳይኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተወሰነ ትምህርት የሚሰጥባትን ተቋም ከአልጋ ወራሽነት ዘመናቸው ጀምሮ በጥረታቸው በእርዳታም ይሁን በብድር በአገሪቱ ሃብትም ይሁን በምን መልካም ፈቃዳቸው ሆና አስፋፍተው ብዙ ምሁራንን ለኢትዮጵያ እስረከበዋልየጃንሆይ በትምሀርት ማመን ቀደም ብሎ የታወቀ ነው የንግስና መንገዳቸውን ይጠርጉ በነበረበት ጊዜ የወደፊቷ ኢትዮጵያ በምሁራን አሰራር ትገነባ ዘንድ ዘር ሳይመርጡ ብዙዎችን ወደሰለጠነው ዓለም ለትምህርት ልከዋል አፄ ምኒልክ በጣሉት መሠረት ላይ ተንጠሳጥለው ጃንሆይ ከአልጋወራሽነት ዘመናቸው ጆምሮ ልዩ ትኩረት የሰጡት ጉዳይ ነው ምሁራንን ማብዛት ከኢጣሊያ ወረራ በፊት ምሁራን ውጭ አገር ተምረው መጥተው የመንግስት ባለሥልጣን ሆነው ይሰሩ ነበር በወረራው ዘመን የኢጣሊያ ባለስልጣኖች ምሁራኑን ኣያደኑ ገደሏቸው በዚህም ከፊሉ አለቁ የተረፉት ክነፃነት በኋላ አገራቸውን እንዲያገለግሉ ተደረገ ኙ ከጦርነቱ በኋላ ባሉት ተክታታይ ዓመታት ምሁራንን የማበርከቱ ስራ ቀጥሎ ጃንሆይ ብዙዎችን ወደ ውጭ አገር ልከዋልበ ዓም የትምሀርት ሚኒስቴር ተቋቁሞ የትምሀርት ሚኒስትርነት ስልጣኑን ንጉሱ ራሳቸው ደርበው ይዘው እስከ ዓም ድረስ ቆይተዋል ይጠነቀቁለትም ነበር ተዳማዊ ኃይለሥላሴ ተማሪዎችን ሲጎበኙ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሺ ከኛ እስከ ኛ ክፍል ትምህርት የሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች ዩኒቨርሲቲና ኮሌጆች እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲ ዝግጅት የሚያበቁ የተሻለ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው ከፍተኛ ትምሀርት ቤቶችን አቋቁመዋል በዎቹ የመጀመሪያ አመታት አጠቃላይ የተማሪው ብዛት ደርሶ ነበር ለትምህርት ቤቶች መስሪያነት የንጉሱ የግል ርስቶች ነበሩ የሚውሉት በየትምህርት ቤቱ እየዞሩ ድንገት እየደረሱ የትምህርት አሰጣጡን ይፈትሻሉ ጥሩ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ከዘክ እስከ ለወጡ በየአመቱ ሽልማት ይሰጣሉ የገና በዓልን ዘወትር የሚያከብሩት ከሁሉም የአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ጋር ሆነው በልደት አዳራሽ ነው ልዩ ልዩ ስጦታዎችን እየሰጡም ያበረታታሉስከፍተኛ ትምህርት ወደ ውጭ አገር የሚሄዱትንም ሆነ ተምረው የሚመለሱትን አሸኛኘትና አቀባበላቸው የተለየና ዛሬ ለአንድ ዲፕሎማት እንደሚደረገው መሽቆጥቆጥ ያህል ነበር መቋቋሚያ ከመስጠት ጀምሮ ወጪያቸው ይሸፈናል ጃንሆይ ቤተመንግስታቸውን ለትምህርት ቤትነት የሰጡትምህርትን የሚያከብሩ ንጉሰ ነገስት ናቸውጥቂቶችን ለመጠቃቀስ ያህል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ ዓም ከመከፈቱ በፊትና በኋላ በድህረ ነፃነት የኮተቤ ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የጄኔራል ዊንጌት ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ሆነው ተቋቁመዋል የኮተቤው በ ተቋቁሞ የምግብ ማብሰያ ቤት እስኪሰራለት ድረስ የተማሪዎች ምግብ ከቤተመንግስት ነባር የሚሄደው የቱ ዊንጌት ደግሞ በትምህርት ሚኒስትርና በብሪቲሽ ካውንስል ተራድኦ ትብብር የተገነባ እንጂ እንግሊዞች ሰርተው ያበረከቱት አይደለም የትምህርት ስርዓቱ የእንግሊዝን ስርዓት የተከተለ ሲሆን ኢትዮጵያዋ ምሁራን እንዳሉ ሆነው የበላይ ዳይሬክተሮቹ ካናዳውያን ነበሩ የአርትና የሳይንስ ፋክልቲዎችን ያቀፈው ዋናው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከተቋቋመ በኋላ በነበሩት ተከታታይ አመታትም በአዲስ አበባ የመሐንዲስ ኮሌጅና የህንፃ ኮሌጅ በአለማያ የእርሻ ኮሌቿጅ በጐንደር የጤኖ ጥበቃ ኮሌጅ ተከፈቱ በ ዓም እነዚህን የተለያዩ ኮሌጆችና ፋክልቲዎች ጠቅልሎ እንዲያሰተዳድር የአዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ በድሮ አጠራሩ የቀዳማዊ ሃይለስሳሴ ዩኒቨርሲቲ ተመሰረተ ከዩኒቨርሲቲው ምሰረታ በኋላ የህግ የህክምና የንግድ የአስተዳደር ወዘተ ዲፓርትመንቶች ተከፈቱበ ሰባ አንድ የነበረው የተማሪ ቁጥር በኮሌጅ ደረጃ እየቀጠለ ሄዶ በ ዓም የማታ ተማሪዎችን ጨምሮ ሺ ደረሰ ለድህረ ምረቃ ትምህርት ግን ወደ ውጭ አገር በተለይ ወደ አሜሪካ መሄድ የግድ ነበር በ ዓም በአሜሪካ የድህረ ምረቃ ትምህርት የሚከታተሉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር የሚደርስ ነበር በቅኝ አገዛዝ ይማቅቁ ለነበሩት አፍሪካውያንም ኢትዮጵያ ነፃ የትምህርት እድል መስጠት የጀመረችው በጃንሆይ ጊዜ ነው ኢትዮጵያን ዘመናዊ አገር ለማድረግ ለጀመሩት ፕሮግራም ጃንሆይ ትምህርት ወሳኝ ግብአት መሆኑን ስላመኑበት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠታቸው ግልፅ ነው ሆኖም ባከፊል ምሁራን የሚደነቅ ተብሎ ሲገለፅ በተቃራኒውም የትምህርቱን ስርዓት ክፉኛ የሚተቹት ምሁራን ቅሳል ቁጥር የላቸውምምንም እንኳ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የአስተሳሰብ አድማሳቸው እየሰፋ በሄደ ቁጥር የጃንሆይን አገዛዝ ፊውዳላዊነት የተላበሰ መሆኑን ወደመረዳት እያመሩ ለአመፅ ቢነሳሱም ጃንሆይ ይህ ይሆናል ብለው አስበው አያውቁም ነበር ይህን ጉዳይ በተመለከተ ዶር ፍቅሬ ቶሎሣ እለፅበጸበ ል ክሀሺ ዐ። አቶ ብርሃኑ ይቀጥሳሉ ክቡር ሆይ በዚህ ጉዳይ እኔ ከሳሽ ወይም ተከሳሽ አይደለሁም ደረጃዬ ዝቅ ቢልም የመንግስት ሹም ነኝ ስለዚህ ለግርማዊነታቸው ባፃፍኩት ራፖር ምክንያት በችሎት ቆሜ መልስ እንድሰጥ የተጠየቅሁት ያለአግባብ ነው በፅሀፈት ቤት በኩል ነገሩን ክቡርነትዎ ለመረዳት ቢፈቅድ ለማብራራት ፈቃደኛ ነኝ ስው እየከሰሱ መልስ አልሰጥም ማለት የት አለ ሩ ክቡር ሆይ እኔ ማንንም አልከሰስሁም ኣኔ የግል ዘመድ አልተገደለብኝም እኔ የግል ሐብት አልተዘረፈብኝም ሀብታቸውን የተቀሙት ዘመዶቻቸው የተገደሉባቸው ሰዎች ዳኝነት በተሰጣቸው ጊዜ ክሳቸውን እንደሚያቀርቡ አልጠራጠርም እኔ በሹመተ ኃላፊነቴ የፃፍኩት ሪፖርት እውነት ቢመስልዎ ተቀበሉት እውነት ባይመስልዎ ሊተውት ይችላሉ ቆይ የሚሆነውን እናስታውቅነለን ብለው ከችሎት ተነሱ ፊት አውራሪ ተሠማ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ፍርድ ቤት ቀርቦ ታሠረ ፍፃሜውም እዚያው ሆነ የወላይታ ህዝብ እፎይ አለ ራስ አበበ ፊትአውራሪ ትሠማን ለማዳን ያደረጉት ጥረት ሁሉ አልተሳካም አቶ ብርሃኑ እንዲህ ይሉናል እነራስ አበበን የመሳሰሉ ሹማምንቶቻቸውን ይቀየማሌሉ ሳይሉ አፄ ኃይለስላሴ ያሳዩት የፍትህ ሚዛንነት የወላሞን ህዝብ ፍርሃትና ሰጋት ከሞላበት አኗኗር ነፃ አድርጎ ሰላምን ሰለሰጠው በንጉሠነገስቱ ሳይ ያለኝ እምነት ጠንካራ ሆነ አቶ ብርሃኑ የወላይታ ተጠባባቂ ገዥ ከሆኑ በኋላ ወደ አዲስ አበባ የመመላለስ እድል ነበራቸውና ጃንሆይን ለማመስገን በሄዱ ጊዜ እንዲህ እንዳሏቸው ይነግሩናል እኛን አምነህ በቅንነት ከሰራህ ምንም ችግር እያገኝህም ከዚህም በላይ በተለያዩ የአሰተዳደር ጉዳዮች ሳይ አቶ ብርሃኑ ያቀረቧቸውን ምክሮች ጃንሆይ ተቀብለው ተግባራዊ ማድረጋቸውን ይገልፁልናል ከአዲስ አበባ ወደ ወላይታ ሊመለሱ ሲሰናበቱ በቅርብ ጊዜ ለሌላ ስራ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመለሱ ተነግሯቸው ነበርና የሄዱት ወዲያው የወሲሶው ጀግና አርበኛ ደጃዝማች ገረ ዱኪ ተሾመው መጡ አቶ ብርሃኑ ጥቂት አለማምደው ወደ አዲስ አበባ መጡ ብላታ መርስኤ ሐዘን ወልደቂርቆስና አቶ ብርሃኑ ድንቄ ታሪክና የቤተመንግስት ዜና ማሰናጃ» የሚባል መስሪያቤት እንዲያቋቁሙ ታዘዙ ብላታ መርስኤ ሐዘን ዋና ዳይሬክተርረ አቶ ብርሃኑ ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሾሙ ስራቸው የተቃና ይሆን ዘንድም የብርሐንና ሠላም ማተሚያ ቤት በአነሱ ስር እንዲተዳደር ሆነ መስሪያ ቤቱ የዱክ ቤት ቤተመንግስቱ ጊቢ ውስጥ ነበር « መስሪያ ቤቱ ጊቢ ውስጥ ስለሆነ ለጃንሆይ በማኖቸውም የቅርብ አገልጋዮች አደረገንኑ እለት እለት ጃንሆይ የሚፈፅሟቸውን ዋና ዋና ታሪካዊ ጉዳዮች ከመከታተል በቀር አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በአስተዳደር ወይም በፍርድ ያለአግባብ ተወሰኑ ስሰለሚባሌት ነገሮች አጥንተን ኀሳብ እንድናቀርብ እንታዘዝ ነበር ይሉናል ብላታ መርስኤ ሐዘን በአገራችን ጊቆ ባህል ረገድ የተሟሳ ድርጅት ያላቸው ሰው ናቸው ሲሱም ያደንቋቸዋል በታሪክና ዜና ማሰናጃ ጽቤት ሁለት ዓመት ከሰሩ በኋላ ጃንሆይ አቶ ብርሃኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዋና ዳይሬክተር አድርገው ሾሟቸው ብዙዎች ተገረሙ ወይ ጤና። አሉኝ እኔም ቭሸንሆይ በለንደን ስኩል ኦፍ ቴክኖሎጂ የተባለ አንድ ትምህርት ቤት አለ ይህም ትምህርት ቤት የንግድ ጥቅም የለውም ግን ስለአንዳንድ እቃዎች አሰራር በቴክኖሎጂ ረገድ ኢንፎርሜሽን ሲጠየቅ የተጣራ መልስ ይሳጣል አሁን እኔ የማሳስበው ለዚህ ትምህርት ቤት ቴሌግራም አድርገን ለእር እና ነሃሄደር በሆነ የቧንቧ አለራር ልዩነት እንዳለው ጠይቀን ከዚህ ትምህርት ቤት በምናገኘው መልስ መሠረት ነገሩን እንድንወስን ብቻ ነው ጃንሆይ መልካም ነው ብለው የውጨ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ አክሊሉ ሐብተወልድ ቴሌግራሙን እንዲያስተላልፉ አዘዙ ከሁለት ቀን በኋላ የቴሌግራሙ መልስ መጣ እነ አቶ ብርሃኑ እንዳሉት ነፎኗ በማናቸውም የመሬት አይነት ያለአንዳች ስጋት ሊዘረጋ ይችላል የሚል መልስ ሲሆን ከፎለእዚ እንደሚበልጥም ተረጋገጠ ማርማዊነታቸው ቁጣና ሐዘን በተቀላቀለበት መልክ ደጃዝማች ከበደን ገላምጠው ይገርማል እኮዮ አሉ ከዚህ ሌላ አንድ ቃል ሳይጨምሩ የልፍኝ አስከልካዩ ከግርማዊነታቸው ጽቤት እንድንወጣ የእጅ ምልክት አሳየን በዚያን ጊዜ ደጃዝማች ከበደ የተከናነቡት ሐፍረት እንደ ሐምሌ ጥቁር ደመና በፊታቸው አካባቢ ተንጠልጥሎ ይታይ ነበር ስለዚህ የገፈርሳ ውሃ ግድብና የቧንቧ ሰራ እርሳቸው እንደተመኙት ሳይሆን በጨረታ ላሸነፈው ለፈረንሣይ ኩባንያ ለዴግሬሞን ተሰጠ ማዘጋጃ ቤትም ብዙ ሺ ብር አዳነ ቀጥሎም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ራሳቸው ደጃዝማች ከመዘጋጃ ቤት ስራቸው ኃላፊነት ተራገፉ አቶቱ ብርሃኑ ድንቄ በምዕራፍ አንዲህ ይሌናል አንዳንድ ሹማምንቶች በንቅዘት ምክንያት ከስራ ሲወገዱ ወይም ከሹመት ደረጃቸው ዝቅ ሲሉ የሚያስደስተኝ የነርሱ ሐዘን ወይም እኔ ከእነርሱ ጋር ታግዬ ማሸነፌ አይደለም ነገር ግን ሀ የእነርሱን እድል በመመልከት ሴሎች ይታረማሉ ለ በእነርሱ ምክንያት የተበደሉ ወይም የተገፉ ሰዎች ነፃነት ይሰማቸዋል ሐ የፍትህ መተካከል ቀስ በቀስ እያለ በንጉሠነገሰቱ መንግስት አስተዳደር ይዛመታል የሚል ጠንካራ ተሰፋ ነበረኝ የሆነ ሆኖ የግል ጠላቶች ከማብዛቱ በቀር ይህን ተስፋዬን የሚደግፍ አንዳች ምልክት አይታየኝም ነበር በማለት በተሻሩት ደጃዝማች ምትክ ቀደም ሲል ያየናቸው የጤና ጥበቃው ሚኒስትር ብላታ በመተካታቸው ማዘናቸውን ይገልፁልናል የጃንሆይ ትልቁ ጥፋትም ይሄ ነበር ሰለዚህም ወዴ ጃንሆይ ሄደው አለመደሰታቸውን ተናገሩ በዚህ ጊዜ ጃንሆይ አቶ ብርሃኑ ስላደረጉት ብርቱ ትግል አመስግነው እንዲሀ አሉ ብርሃኑ አንድ ህዝብን ማስተዳደር የበጎች መንጋ እንደመጠበቅ ቀላል ነገር አይደለም እግዚአብሔር ሲያስችለን ብቻ የሚቻለውን እናደርጋለን አሏቸው የመልሶ መሾሙ ሁኔታ አንድ ራሱን የቻለ ሙ ሠ ፖለቲካዊ ዱለታ በውስጡ ስለነበረው ይህን ከመፅሐፉ ማግኘት ትችላላችሁ ብቻ ጃንሆይ አጣብቂኝ ውስጥ ነበሩ አቶ ብርሃኑኖ ብላታ ደግሞ በአንድ ክፍል አብረው መስራት ። ኣይታሰብም እንኳን በዚያን ጊዜ ሕጉ መንግስቱ እንደማይለቁ አረጋግጦሳቸውንጉሰነገስት ሆነው ዛሬ እንኳን ፓርቲ ምርጫ ባለበት ዘመን ማንም ኣይለቅም ሶስት ያህል አፍሪካዊ አገሮች ብቻ ታይተዋል ሰልጣንን በምርጫ በሰላማዊ ያስተሳላለፉ በነገራችን ላይ ከነፃነት በኋላ በአፍሪካ መፈንቅለ መንግስት አንደኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ሱዳን ስትሆን ጊዜ የተሳካና ያልተሳካ መፈንቅለ መንግሰት ተካሂዶባታል ኢትዮጵያ ዝቅተኛውን ደረጃ ይዛለች ጊዜ በቻ ስለሆነ ሌላውም በአስራዎቹ ይተመናል ችግሩ ግን ይሄ ብቻ አይደለም ስልጣንን ለማጥበቅ የሚሰሩ ስራዎች ብዙ በመሆናቸውበዚህም ፖለቲካዊ ማኅበራዊና በተለይም ኢኮኖሚያዊ ብክነት ይከሰታል ታማኝ ሹማምንት ሲዘርፉ እንዲኖሩ መፍቀድንም ያካትታል የአባልን አበል ጨምሮ ብዙ ገንዘብ በስልጣን ላይ ኢንቨስት ይደረጋል የጃንሆይ ጥፋት በዚህ ክብ ውስጥ የሚሽከረከር ነው እናም ከክቡ ውጪ ያለውን ህዝብ ዘነጉት ጃንሆይ የከተማውን ንቅዝ ሹማምንት እያወቁ ትተውታልይህም ህዝቡን በንቅዝ ሹማምንት የጭቆና ቀንበር ሰር እንዲኖር መፍቀድ ማለት ሲሆንከህዝቤ ሰልጣኔ ይበልጣል የሚል እንድምታ ያለው ግዙፍ ጥፋት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው ከዚህም ባለፈ ጃንሆይ በወቅቱ የነበረውን ዓለም አቀፍ የአስተዳደር ሰርዓትና የኢትዮጵያ ህዝብም የግንዛቤ አድማሱ መስፋቱንም ሆነ ለውጥ መፈለጉን ማሰብ አልፈለጉም ሴላው ቀርቶ ብዙ የአፍሪካ አገሮች ከቅኝ ገዥዎቻቸው ነፃ ለመውጣት የተንቀሳቀሱበትና ነፃ ከሆኑ በኋላም የይስሙላም ቢሆን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እያካሄዱ በነበረበት ሁኔታ የኢትዮጵያ ሕጉመንግስት ግን ንጉሠነገስቱን ኃይሉ የማይደፈር የማይገሰስ በሚል የእድሜ ልከ ሕግ ሆኖ ይቀጥላል ብለው መታተራቸው አንዱና ዋናው ጥፋታቸው ሲሆን ዘውዱ እንደተከበረ ሆኖ ከዘውዱ በታች እንኳ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ለመመስረት የሚቻልበትን አማራጭ አልተጠቀሙበትም የጳቋጳሥን ግዝትም ሆነ በእግዚአብሔር የተሾሙ የሚለውን ቃል እንደጥንቱ ህዝብ ምሁሩም ጠብቆትና አክብሮት ይቀጥላል ብለው ማሰባቸውም በዘመናቸው ያሳዩት የመጀመሪያው ሣፕዋህነታቸው ሆኖ የሚመዘገብ ነው እነዚህን የመሰሉ የለውጥ አስተሳሰቦች በተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ሊብሳላ አንደሚችል ቢያስቡም ጥቂቶች ሊጠቁሟቸው ቢሞክሩም ፕኢትዮጵያ ህዝብ ለዚያ አይነቱ አስተዳደር ልምድ የለውም ኃላፊነቱን ለመሸከም ገና አልደረሰም የሚል ምላሽ እየሰጡ ነገር ግን በጎን የሁኔታውን አስጊነት ተመልክተው ወደመፍትሔው ከማምራት ይልቅ የመረጡት መንገድ ሥልጣናቸው ከዚህ መሰሉ አደጋ ተጠብቆ የሚቀጥልበትን ሁኔታ ማመቻቸት ሆነ ከዚሁም ጋር ተያይዞ የአስተዳደር ክሽፈት ተፈጠረና አልደረሰም ያሌት ህዝብ ደርሶ ጠበቃቸው ከዚህ አንፃር የጃንሆይ ጥፋት በአፍቃሬ ስልጣንነታቸው ስር ተጠቃሎ የሚገለፅ ሆነ በጃንሆይ ላይ የተነሱ አመጸች ጃንሆይ ለአመፅ ብርቅ አይደሉም ከስደት ከተመለሱ በኋላ በሰጡት ሹመትና ሽልማት ፍትሐዊ አይደለም በሚል ተገቢ መነሻ በርካቶች ባይሆኑም አምፀዋል ለምሳሌ ጀግናው የጎጃም አርበኛ በላይ ዘለቀ የንጉን ሹመት አሰጣጥ ተቃውሟል በጎጃም የጠላትን ጦር ሲያንቀጠቅጥ የነበረ የተዋጣለት ጀግና ነው በላይ ዘለቀ ከእርሱም ጋር ልጅ ኃይሉ በለው ደጃዝማች መንገሻ ጀንበሬና ደጃዝማች ነጋሽ በዛብሀ በድፍን ጎጃም በአርበኝነት ይታገሉ ነበር ከበላይ ዘለቀ በስተቀር ሦስቱ የነገሰታት ዘር ናቸው ከነፃነት በኋላ በ ዓም ጃንሆይ ከጎጃሙ ንጉስ ተክለሐይማኖት ለሚወለዱት ለልጅ ኃይሉ በለው ከራስ ማዕረግ ጋር የጎጃም ጠቅላይ ገዥነት ለደጃዝማች መንገሻ ከቢትወደድ ማዕረግ ጋር የጎጃም ምክትል ጠቅሳይ ገዥነት ለደጃዝማች ነጋሽ ከቢትወደድ ማዕረግ ጋር የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንትነትን ሲሰጡ ለልጅ በላይ ዘለቀ ይግሞ ከደጃዝማች ማዕረግ ጋር በጎጃም የቢቸና አውራጃ ገዥነትን ጮ በአርበኝነቱ ዘመን መሪ የነበረውና በጀግንነት ማንም ያልደረሰበትን ሰው ከእነርሱ ያነሰ ሹመት ሲሰጡት ቅር ተሰኘ የንጉሠን ትዕዛዝና ሹመት ውድቅ በማድረግ ከተከታዮቹ ጋር የጎጃሙን ያሶማ ኮረብታን ይዞ አልገዛም አለ ሙ ሥ ሚያዚያ ቀን ዓም የመንግስት ጦር ዘምቶበት የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ሰዎች ሞተው ቆሰሉከሦስት ወር በኋሳ ከ ተከታዮቹ ጋር ተማርኮ ወዴ አዲስ አበባ መጣየእስራት ቅጣት ተፈረደበትና ወሊሶ ሄዶ ታሰረ ከወሊሶ ሲያመልጥ በድጋሚ ተያዘና ወንድሙን እጅጐ ዘለቀን ጨምሮ ከሌሎች አስረኛ ከሆኑ ባንዳዎች ጋር በአዲስ አበባ ታሰረታህሳስ ቀን ዓም ከ እስረኞች ጋር ከእስር ቤት አምልጠው ወደ ጎጀም ለመገሰገስ ጉዞ ሲጀምሩ በኛው ቀን ሱሉልታ ሳይ ተይዘው እንደገና ወደ አዲስ አበባ አመጧቸው የጦር ፍርድ ቤት የወሰነው የሞት ቅጣት በጥር ቀን ዓም ተግባራዊ ሆነና በአደባባይ በስቅላት ተቀጣ ሌላው አደገኛ አመፀኛ ደጃዝማች ታከለ ወልደሐዋርያት ናችውንጉሥ ስደትን ከመረጡ ጊዜ ጀምሮ ለ ዓመታት ያህል መንግስታቸውን ለመፈንቀል ሲጣጣሩ ነው የኖሩትእኒህ ሰው ሲታሰሩሲፈቱሲሾሙሲሻሩሲያሴሩ ነው ያሳለፉት በመጀመሪያ አርበኞችን አስተባብረው አሳድመዋል ተብለው ታሰሩ እንደገና ተፈትተው በ ዓም ምክትል አፈንጉስ ሆነው ተሾሙ አመት ሳይቆዩ ሌላ ተመሳሳይ ሴራ ሲጠነሰሱ ተደረሰባቸውና ታስረው ዓመታትን አሳለፉ ተፈቱና የአገር ግዛት ምክትል ሚኒስትርና የአፈንጉሥነቱ ሰልጣን ተመለሰላቸው ይሄ ሁሉ ሲሆን ጃንሆይ ከአሁን አሁን ይበርድላቸዋል ብለው በመገመትና ጀግንነታቸውንም በደንብ ስለሚያውቁት ነበር የሚታገሷቸው በመጨረሻ በ ዓም ጃንሆይ የሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን ለመጎብኘት ሲሄዱ ሰበታ አካባቢ ፈንጅ አጥምደው ንጉሠውን ከነመኪናቸው ድምጥማጣቸውን ሊያጠፉ ተዘጋጁ ሁኔታው ቀድሞ በጥቆማ ተደረሰበትና ከሸፈ ደጃዝማች ታከለ ቤታቸው መሽገው ነበርና በወታደር ተከቦ ተኩስ ተከፈተ እጅ አልሳጥም ብለው ሲዋጉ ቆይተው ሲያዙ ሲሉ ራሳቸውን ገደሉ የሕን መወሰኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ቢትወደድ ነጋሽ በዛብህም እንዲሁ በንጉሥ ላይ አምፀው ነባር ወታደራዊ መኮንኖችን አስተባብረው ንጉሠን በመግደል የሪፐብሊክ መንግስት ለመመስረት እንደነበር ይነገራል ይህም ልክ እንደ ደጃዝማች ታከለ አይነት መሆኑ ነው በመጨረሻ ግን በ ዓም ይሄው ሴራ ተደርሶበት በእስራት ተቀጡ የእነዚህን አድመኞች እንቅስቃሴ ሁሉ በቁጥጥር ስር ያውል የነበረውና ለፍርድ ያቀርብ የነበረው ኮሎኔል መንግስቱ ንዋይ ነበር የቱን አመፅ በቁጥጥር ሰር ካዋለ በኋላ ደግሞ በ ዓመቱ ብርጋዴር ጄኔራል መንግስቱ ንዋይ ራሱ ከወንድሙ ከገርማሜ ንዋይ ጋር ሆኖ የታሀሳስ ቀን ዓምቱን መፈንቅለ መንግስት ሞከረ ይህ ሙከራ ከላይ እንዳየናቸው በግል ኩርፊያኖ በመሳሰሉት ሳይሆንምሁራዊ አስተሳሰብ የታከለበትና ፖለቲካዊኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መሠረት የነበረው ስርነቀል ለውጥን የሚሻ እንደነበር ከኣነሳሱ ያሰታውቅ ነበር አነሳሱም ነው ለዘላቂ ለውጥ ፍለጋ ብዙዎችን እንዲነቃቁ በር የከፈተው እንጂ ከዚህ ጊዜ በፊት ምሁሩምጦሩምሠራተኛውም ሆነ ሌላው ምን አይነት ለውጥ እንደሚፈልግ ለይቶ አያውቀውም ነበር ለማለት ይቻላልቢያውቅም እንዴት መነሳት አንዳለበት አያውቅም ወይም አይደፍርምበአጠቃላይ የንጉ ዙፋን እንደሚሜነቃነቅ የተደረሰበት ዘመንና ሁኔታ የተከሰተው በመንግስቱ ንዋይ ሙከራ ነው ገርማሜ ንዋይ በአገር ውስጥም በአሜሪካም በዘመናዊ ትምህርት ከፍተኛ ደረዳ ላይ የደረሰ የዚያ ዘመን ምሁር ነበር ብርጋዴር ጄኔራል መንግስቱ ነዋይም ከወረራው በፊት ተጀምሮ በነበረው ዘመናዊ የጦር ትምህርት ቤት መሰልጠን ጀምሮ የነበረና ከጥቁር አንበሳ አባላት ውስጥ አንዱ የነበረ አርበኛ ነው ከነፃነት በኋላም በወታደራዊ ማዕረጎች በየጊዜው እያደገ የንጉሥ ታማኝ ሆኖ ጄኔራልነት ደርሷል በዚህም የከቡር ዘበኛ ከፍለ ጦር አዛዥ ሆኗል የኀሳቡ አፍላቂ ገርማሜ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ መፈንቅለ መንግስት የኮሎኔል ወርቅነህ ገበየሁ የፀጥፐታ ኃሳፊውና የመንግስቱ ንዋይ የጦር ትብብርን አግኝቶ ጥቂት ተራምዶ ነበር በሬዲዮም በአልጋወራሽ አሰፋወሰን ኃይለስላሴ ንባብ አዋጅ አሰምተው ነበር የኢትዮጵያን ማኅበራዊና ብሔራዊ የእድገት እርምጃ ጥቂት ራስ ወዳድ ግለሰቦች ወደኋላ አስቀርተውታል በቅርቡ የተነሱ የአፍሪካ አገሮች በስልጣኔና በእድገች ጥለውን ሄደዋል አጠቃላይ አገዛዙ ሁሉንም የኅብረተሰብ ከፍል እየጎዳ ነው የህዝቡ ቁጭት ለዚህ ተግባር አነሳስቶናል ፋብሪካዎችን እናበዛለን ትምህርት ቤቶች ይስፋፋሉ የወታደር ደመወዝ ይጨመራል ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ሁሉ እናከብራለንዐ የሚል ማኑፌስቷቸውን ታህሳስ በሬዲዮ እሰራጩ ብዙ ባለሥልጣናትንም አሰሩ ሆኖም የክቡር ዘበኛና የፖሊሰ ሠራዊት ብቻውን በቂ አልነበረም ብርጋዴር ጄነራል መንግስቱ ነዋይ እና ገርማሜ ነዋይ ጃንሆይ በዚህ ጊዜ ለጉብኝት ከሄዱበት ከላቲን አሜሪካ ወዲያው ተመለሱ ጳጳሱም ገዘቱ በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማፐር ሹም የተመራው ጦር ከሁለት ቀን የተኩስ ልውውጥ በኋሳ አመፁን ተቆጣጠረው ንጉሠም ከከሸፈ በኋላ ነበር ኢትዮጵያ የደረሱትእነመንግስቱም መክሸፉን ሲያውቁ በገነተ ልዑል ቤተ መንግስት አሰረዋቸው የነበሩትን ሹማምንት ገድለው ለማምለጥ ሞከሩ ኮሎኔል ወርቅነህ ገበየሁ ራሱን ገደለገርማሜ ዝቋላ ደርሶ ከሚያድኑት ጋር ተታኩሶ ሞተመንግስቱ ቆስሎ ተይዞ ከመጣ በኋላ ለፍርድ ቀርቦ በስቅላት ተቀጣ ትግሉ ግን ቀጠለ እነ መንግስቱ ንዋይ በሬዲዮ ባስተላለፉት ቃል በየትኛው ዘርፍ የትኛው ባለሥልጣን እንደሚሾም ሳይቀር ለመግለፅ ሞክረው ነበር የሚገርመው ግን አድመኞችን ደግፎ ሰልፍ የወጣው ህዝብ ጃንሆይ ሲመጡ በእልልታ መቀበሌ ነው እናም ጃንሆይ በደስታ ወደዙፋናቸው ተመለሱ ሴረኞች ያሏቸውን እያስለቀሙ ቀጡ ታማኝ ሆነው ያከሸፉትን ሾሙ ሸለሙ እነ ገርማሜ ንዋይ ለሠራዊቱ ገብተውት የነበረውን የደሞዝ ይጨመራል ቃል መሠረት በማድረግ ወታደሩ እንዲፈፀምለት ደጋግሞ መጠየቁን የቀጠለው ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው ከረጅም ጊዜ በኋላ ለወታደሩም ለመኮንኖችም ደሞዝ ተጨመረ ወቴ አሁንም ጨምሩ እያለ አላስቀምጥ አለ ቀጠለ ሂደቱ በአጠቃላይ የቴ ሙከራ የንጉን ልዩ ካቢኔ ዋጋቢስነት ከማሳየት ባለፈ የሁሉንም የአገዛዙን ተቃዋሚዎች ያለልክ አነሳስቶ ያለፈ ሆነ ጃንሆይም አመፁን ያስነሱትን የግለሰቦችን ከሃዲነት እንጂ ጥያቄዎቻቸውን ለመመርመር አልሞክከሩም አገዛዛቸውን እርምት ሳያደርጉበት ቀጠሉ ከ ዓም ጀምሮ በተለያዩ ግዛቶች በተለይ ከመሬት ጋር በተያያዘ አመጾች ይነሱ ነበር አንዳንዱ በትክክለኛ ብሶት ያምፃል ሌላው ኢጣሊያ ጥሎት የሸሸውን መሣሪያ ወድቆ ስላገኘ ብቻ ያምፃል አንዳንዱ በግብር ሲያኮርፍ የቀረው በሹመት አነሰኝ ያኮርፍና አሰተባብሮ ያሳምፃል በተለያዩ ግዛቶች ከተነሱ የገበሬ አመጾች ውስጥ የባሌ የጌዲኦ የራያና አዘቦ የየጁ የጎጃምና የትግራይ አመጾች ይጠቀሳሉ ሌሎቹ ሁሉ ስር ከመስደዳቸው በፊት በፍጥነት ሲረግቡ የባሌው አመፅ ግን ለረጅም ጊዜ የቆየና መንግስትን የተፈታተነ ነበር የባሌ አመፅ በገበሬው ላይ የሚደርሰውን ግፍ መነሻ ያደረገና የባላባቱን ሕገወጥ ምዝበራና ዝርፊያ እንዲሁም የመሬት ግፊት መሠረት ያደረገ ነው የመሬት ቀላድ ሲጣል ብዙዎች ለጭሰኝነት ተዳርገዋል በየጊዜው እያደገ የሄደውን ግብር ለመክፈል የሚያስችል በቂ መሬትም ሆነ ምርት አልነበራቸውም በባሌም ብቻ ሳይሆን በአጎራባች ግዛቶች ብዙ የመንግስት ሹማምንት ርስት ተሰጥቷቸው ስለሰፈሩ የአካባቢውን ነባር ሀዝብ በብዝበዛ ተጫኑት ከአቅማቸው በላይ ሲሆን መሬታቸውን እንዲያስረክቡ ሹማምንቱ ያስገድዷቸዋል የሹማምንቱ የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነት በመሬት ላይ ብቻ ሳይሆን በሃይማኖትና በባሀል ላይም ተከሰተ ይህም ለረጅም ጊዜ የቆዬ ተቃውሞ ያስነሳ ቢሆንም በቀላሉ ሲረግብ ነበር በ ዓም ባሌ ከሐረርጌ ተቆርጦ ራሱን የቻለ ግዛት ወይም ክፍለ አገር በሆነ ጊዜ የዶሎ የመንዶዬ የዋቤ የገናሌ እና የኤልከሬፊ በሚል በ አውራጃዎች ተከፈለ። ኤልከሬ ሙሉ በሙሉ የሶማሌ ዘላን ማኀበረሰብ ከልል ነበር ሌሎች ቱ ደግሞ የኦሮሞ ብሔረሰብ ክልሎች ናቺው እነዚህ ህዝቦች የመንግስትን ሹማምንት ጫና አሜን ብለው የሚቀበሉ አልሆኑም ቀደም ካለው ጊዜ ጀምሮ የተጨቆኑት አርሶአደሮችና አርብቶ አደሮች በ ዓም ወደተደራጀ አመፅ አመሩ አመፁንም በአውራጃና በክፍለ አገር ደረጃ እያዋቀሩና ከጎረቤታቸው ከሱማሊያ መንግስት እርዳታ እየተደረገላቸው ራሳቸውን ሻለቃ ኮሎኔል ጄኔራል እያሉ እየሾሙ የደፈጣ ውጊያውን አጧዉፉት ከአነዚህም ውስጥ የዶሎው ጠባሴ ከፍለ አገር የአንዱ አውራጃ ተወላጅ ጄኔራል ዋቆ ጉቶ በዋናነት ሲጠቀስ የኤልከሬው ኮሎኔል ካህን አብዲ የዋቤው ኮሎኔል ሁሴን ቡኒ የገናሌው ኮሎኔል ኡማር ከቤሎ ዋኖ መሪዎች ሆነው የአካባቢው ማኅበረሰብ የዓላማቸው ተባባሪ ሆኖ ከጎናቸው በመሰለፍ በመንግስት ሹሞች ላይ ለ ዓመት ያህል ጥቃት ሲያደርሱ ቆይተዋል የሱማሊያ መንግስትም አጋጣሚውን ተጠቅሞ ሣሶማግሌ ነፃነት እንቅስቃሴ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ ሞክሮ ነበር እንደ ፕሮፌሰር ሙ ሳኢሶ አገላለፅ በ ዓም ንጉሠ በስራ ጉብኝት እስከ ባሌ ክፍለአገር በመሄድ ኛ በሌላ ደቡብ ከፍላተ አዝዢ ድሮ እንደተደረገው ሁሉ አሁን ለባሌም ባላባቶች ከመሬት የባላባት ሲሶ እንደሚሰጣቸው ቃል ገቡ ኛ ከ ዓም የግብር ውዝፍ ምክንያት ግብረ ጠል ተብሎ በመንግስት የተወረሰው መሬት ለዓመታት ግብር ያልተከፈለበት ሆኖ ሲገኝ ይወረስ ስለነበር ለህዝብ እንደሚመለስለት ተናገኅሩ ኛ ለብዙ የከፍለአገሩ ተወላጆች ሹመትና ማዕረግ ሰጡ ኛ የሼክ ሁሴንን መስጊድ ጎብኝተው ወደአዲስ አበባ ተመለሱ ይሁን እንጂ በአመፅ መንፈስና ተግባር አንዴ ከተቀሰቀሰ በኋላ ለረጅም ዘመን በጉልተኞችና ባለሥልጣኖች ጭቆና በኃይል የተመረረው የባሌ ህዝብ በንጉሙ ጉብኝትና መልካም ቃላት ከአመፅ እርምጃው አልተገታም በአጭሩ ከ ዓም የከፍለ አገሩ እንደራሴ በፊትአውራሪ ወርቁ እንቁስላሴ መሪነት የባሌ ክፍለአገር ጉልተኞችና ባለሥልጣኖች ከፖሊስና ከብሔራዊ ጦር ጋር የህዝቡን አመፅ መቆጣጠርና ማቆም ፈፅሞ አቃታቸው በመሆኑም እንደራሴው እንዲነሳ ተደርጎ በታህሳስ ዓም የባሌ አራቱ የኤልከክሬ የዶሎቫገናሌና የዋቤ የአመፅ አውራጃዎች ከአጎራባቹ የቦረና አውራጃ ጋር በወታደር ስር እንዲሆኑ ተወሰነ በፊኛ ክፍለ ጦር ስር መሆኑ ነው እናም በክፍለ ጦሩ አዛዥ በጄኔራል ጃገማ ኬሌ አመራር ሰር ከሆኑ ጊዜ ጀምሮ ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ተደርጎ በ ዓም ጄኔራል ዋቆ ጉቶ ለመንግስት አጁን ሲሰጥ የባሌና የአጎራባቾች አመዕ ተገታ በአብዮቱ መዳረሻ ከአገሪቱ ገበሬዎች ውስጥ ከአጠቃላዩ ሲሶ ያህሉ ጭሰኛ ነበሩ ጭሰኛ ማለት የራሱ መሬት የሌለውና በሌሎች መሬት ላይ በጉልበቱ እያገለገለ የሚኖር በማንኛውም ሰዓት ባለቤቱ ሊያፈናቅለው የሚችል ኣገልጋይ ማለት ነው ተቀጣሪ ማለት ነው ግባር ሲባል ደግሞ በጃንሆይ ጊዜ ግብር ከፋይ ማለት ነው ፊውዳል ማለት ደግሞ መሬትን በሞኖፖል ይዞ እንዳሻው የሚያደርግ አገዛዝ ማለት ነው ጥቂት ምሁራን የጃንሆይን አገዛዝ ፊውዶ ቡርጂ ብለው ወፈር አድርገው ይጠሩታል ከፊል ካፒታሊዝም ማለት ነው ወዝአደር ላብአደር ሠርቶአደር የሚባሉ የዚያ ዘመን ስያሜዎችም ግልፅ ናቸው በጃንሆይ ጊዜ ባላባቱና ባለሐብቱ የያዙት ሰፋፊ መሬት እንዳለ ሆኖ ተራ ገበሬዎች ደግሞ ሔክታር ማሳ ነበራቸው ከአሁኑ ጋር ሲነፃፀር ባለፀጋ የሚያሰኝ ይዞታ ነበር ለማንኛውም በዚያ ጊዜ ገበሬው ሁሉ ከየአቅጣጫው ጭቆናው በዝቶበት ስለነበር አመፀ በየካቲት ወር ዓም ዶር ነጋሶ ጊዳዳ የቀድሞው የኢህፌዲሪ ፕሬዝዳንት በእንድ ሰብሰባ ላይ ለስራ ተገኝቼ ነበርና እንዲህ ሲሉ አደመጥኩ ከዎቹ ጀምሮ መሬት ላራሹን ሳቆነቅን ኖሬያለሁ እሁንም ማሰብ እስካቆም ድረስ ይሄንኑ አቋሜን አልለቅም በጃንሆይ ላይ ከተነሳው ዘርፈ ብዙና ከየአቅጣጫው የተቀጣጠለው አመፅ ይሄን ያህል ፈታኝ አልነበረም በከፍተኛ ሁኔታ ስርዓቱን የተፈታተነው ተማሪው ነው የተማሪው ተቃውሞ ከ ዓም ጀምሮ ውስጥ ውስጡን ሲብላላ ቆይቶ ከ ዓም በኋላ ወደ አደባባይ በመውጣት የተቃውሞ ሰልፍ ማድረግ ተለመደ በድርድር የማይከሽፍና ስር ነቀል ለውጥ የሚፈልግ ሆኖ የተነሳው ምሁር እስከመጨረሻው የሚያቆመው ኃይል ጠፍቶ አብዮቱን አሳብጧል በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የተለያዩ ማኅበራት በተማሪው እየተመሰረቱ የክርክር መድረኮች እየተዘጋጁ ለከፍተኛ ትምህርት ወደሌላው ዓለም የተላኩ ምሁራንም ተመሳሳይ ማኅበር እየመሠረቱ ስርዓቱን በአእጅኾጉ በመተቸት ተግባር ላይ ተጠመዱበተማሪው ልሳን በሆኑ መጽሔቶች የተለያዩ ፖለቲካዊ ትንታኔዎች ይቀርቡ ጀመርርዕዮተ ዓለማዊ መፈክሮችና መግለጫዎች በየጊዜው ይሰራጫሉ እንዲህ እንዲያ እያሉ በ መሬት ለአራሹ ብለው ሰልፍ ወጡ ከመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ጋር ፊት ለፊት መጋተር የተጀመረውም በዚሁ ዘመን ነበር በየጊዜው የሚያነሱት አጀንዳ የተለያዬ እየያነ ቀጠለና በ ዓም የትምህርት ፖሊሲው ይሻሻል የሚል ጥያቄ ሲያነሱ ይህ ጉዳይ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አልፎ በኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ድጋፍ ያለው ጥያቄ ሆነ በ ዓም በደንብ ያላብላሌትን ጥያቄ ይዘው የወጡት ወገኖች ነበር መንግስትን ቁጡ ያደረገው ይሀም በግርግር መሃል ድንገት የተሰነዘረና ብሔር ብሔረሰቦች የራሳቸውን እድል በራሳቸው መወሰን አለባቸው የሚል ነው የጃንሆይ መንግስት ከተራ ድብደባና ግርፋት አልፎ ጠንከር ያለውን እርምጃ ወሰደ በታህሳስ ቀን ዓም ስመጥር የሆነው የተማሪዎች መሪ ጥላሁን ግዛው በአደባባይ ተመታዛየጥላሁንን መመታት በሚመለከት ሁልት ነጥቦች ይነሳሉአንዱ ከመንግስት ታጣቂዎች በተተኮሰ ጥይት የሚል ሲሆንሌላውና ሰፊ ተቀባይነት አግኝቶ ያለው ገለጻ ደግሞ ወደፊት ስውር አሰራራቸውን በስፋት በምናይላቸው የአመጽ አነሳሽ በነበሩ የኤርትራ ድርጅት አባላት አማካኝነት በግርግሩ መሀል በረቀቀ ዘዴ እንደተመታ ነውነበዚህ ጊዜ ተማሪው የጀግናችን ሬሣ እንቀብራለን በሚል ወደ የካቲት ሆስፒታል ሆ ብሎ ሲነጉድ ጥላሁን አርፏልአመፁ ተቀጣጥሎ ቀጠለ የፀጥታ ጥበቃ አባላቱ ተኩስ ከፍተው ጥቂቶች ሲገደሉ ብዙዎች ቆሰሉ ዓለም አቀፉ ተቃውሞም እጅግ እየበረታ ሄደ የጸጥታ ጠባቂዎች እና የተማሪዎች ግብግብ ገሚሱ አገር ውሰጥ ሆኖ ሲፋለም የቀረው በየውጭ አገሩ እየፈለሰ ማኅበራቱን ተቀላቀለ አመፁ የአውሮፕላን ጠለፋንም ያካተተ ነበር ህዳር ቀን ዓም እነዋለልኝ መኮንን እና ማርታ መብራቱን የመሣሠሉ አደራጅና አስተባባሪዎች ወደ ኤርፖርት አምርተው ፕሌን ውስጥ ከገቡ በኋላ ጠለፋውን ከመተግበራቸው በፊት መንግስት ባዘጋጃቸው የጠለፋ አክሻፊ ኃይሎች እዚያው በጥይት ተደብድበው ሞቱ የኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ልዩነት የፓርቲ ምስረታነ የርዕዮት መለያየት በቡድን መደራጀትና ፖለቲካዊ አጀንዳ አንስቶ መንግስትን የመሞገት ተግባር ምንጭም ሆነ አፈሳሰሱ የሚነሳው ከዚሁ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ሆነ በኢትዮጵያ ታሪክም ለመጀመሪያ ጊዜ ያልታጠቀ ኅብረተሰብ መንግስትን ተቃውሞ ድምፁን ያሰማበት ዘመን ተከሰተ የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያዊ ምሁራን ምንም እንኳ የተቀረፁት በምፅራባውያን ትምሀርት የነበረ ቢሆንም የምዕራባውያንን የቡርዣ አገዛዝ አንሸከምም አሉ ሐሮልድ ማርክስ ጣጠፎ ሀዝለልፔ አሃ ብለው እንደገለፁት ጃንሆይ በሰኬታቸው የመውደቃቸው ጉዳይ ግልፅ እየሆነ ሄደ በወቅቱ የጃንሆይ መንግስት በተማሪዎች ሳይ ጨከን ያለ እርምጃ ወስዷል ተማሪውም በተጨከነበት ቁጥር የታጋይነት መንፈሱ እያደገ የማይገሠሠውን ማዕረግ ገሶየማይደፈረውን ክብር ደፍሮ የጃንሆይን ዙፋን ገዝግዞ አብዮቱን አሳበጠ ነገር ግን ሳይፈነዳ ጥቂት ጊዜ ይቆይ ዘንድ የአገዛዙ የዘውዱ ጠበቃ መስለው የራሳቸውን የዘረፋ ጊዜ ጨጨጨጩልፁሬሠህወ ለማራዘም የሚሹ ባለስልጣናት መፍትሔው ኃይል እንደሆነ ገልፀው እሱኑ ተገበሩት ጃንሆይ እና ኪነጥበብ በጃንሆይ ጊዜ ዘመናዊ ማተሚያ ቤቶች ተከፍተዋል የቴአትርና የስነጥበብ ትምህርቶች እንዲሁም የስነጽሁፍ ዲፓርትመንቶች ተከፍተው ትምህርቱ በአገር ውስጥ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መሰጠት ጀምሯል ይህ ከመሆኑ በፊትም በጋዜጠኝነትና በሌሎች ዘርፎች ወደ ውጪ አገር ሄደው እንዲማሩ የጃንሆይ መልካም ፈቃድ ሆኖ ተምረው የተመለሱ ኢትዮጵያውያን ነበሩ ከዚሁም ጋር ተያይዞ ጋዜጦች መፅሔቶች የልብወለድና የኢልብወለድ መጽሐፍቶች የታሪክ መጽሐፍትና የግጥም መድብሎች እየታተሙ ለእንባብያን ይደርሱ ነበር ቴአትር ቤቶችም ተከፍተው በየመድረኩ ተውኔቶች ይቀርቡ ነበር ምንም እንኳ እንደዛሬዎቹ አፍሪካውያን መሪዎች አገዛዛቸውን በብፅር የሚያወግዙ ደራሲያንና ፀሐፌ ተውኔቶች በገዥው አካል የተለመደው ኃይለኛ በትር በጃንሆይ ጊዜም መኖሩ ባይዘነጋ በተጠቀሰው ዘርፍ በርካታ ስራዎች የተሰሩት በጃንሆይ ዘመን ነውበዘርፉ የጃንሆይን አገዛዝ በጥልቀት የሚተቹ የኪነጥበብ ውጤቶች ይታገዱ እንደነበር የመታወቁን ያሀልምለዘብተኛ ትችት የያዙት ሳይታገዱ መቀጠላቸው አይካድምጃንሆይንና አገዛዛቸውን የሚያሞካሹት በርክተው የመገኘታቸውን ያህልምየሚያጣጥሉዋቸውም በጥቂቱ እንደነበሩ ግልፅ ነው ገጣሚያንደራሲያንና ፀሐፌ ተውኔቶች በሰራቸው የመታሰር የመንገላታታቸውን ያህልም በባይቅርታ የታለፉ በርካታ የአገዛዙ ተቺ የሆኑ ባለሙያዎች ነበሩ በዚህ መሰሉ እንግልት ሞራሳቸው የተነካ የኪነጥበብ ሰዎች እንደነበሩ ሁሉም በዘርፉ ባበረከቱት አሰተዋፅኦ የማበረታቻ ሽልማት ከጃንሆይ እጅ የተቀበሉ ሞልተዋል ለአብነትም የቱ የብላቴን ጌታ ፀጋዬ ገብረመድህን ሽልማትን መጥቀስ ይቻላልምንም ቢባል ግን በኢትዮጵያ ታሪክ ለዚህ ዘርፍ የጃንሆይን ያህል ትኩረት ሰጥቶ የተንቀሳቀሰ መንግስት ኖሮ አያውቅም ቴአትር ቤቶችን ብቻ ነጥለን ብናይ በጃንሆይ ጊዜ የተመሠረቱት ናቸው ዛሬም ድረስ አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ከጃንሆይ በኋላ በተነሱ የኢትዮጵያ መንግስታት አንድም ቴአትር ቤት ተገንብቶ አልተጨመረምባቅርቡ በእቅድ ደረጀ ሊገነባ የታሰበው የብሔራዊ ቴአትር አዲስ ተጨማሪ ህንፃ ምናልባት ተግባራዊ ከሆነ ብቻ የጃንሆይ ውጤት ያልሆነ ቴአትር ቤት ሆኖ ይመዘገባል በተረፈ ያሉት ሁሉ የጃንሆይ ዘመን ውጤቶች ናቸው በዘመነ ዛግዌ ብልጭ እንዳለ የሚነገርለትና በጎንደሩ ንጉስ በአፄ ዳዊት ዘመን በቤተመንግስት ደረጃ በኢትዮጵያ እየተለመደ የሄደው ቴአትርበዳግማዊ ምኒልክ ጊዜ ዘመናዊ ቅርፅ ይዞ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ቀጥሎ ነበር ከትምህርት ቤቶች አልፎ ቴኣትር ድራማ ወደ መድረክ የወጣው ግን በጃንሆይ ዘመን በ ዓም በተቋቋመው በአገር ፍቅር ማኅበር አማካኝነት ነው በወቅቱ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ከመውረሯ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ የስነልቦና ጦርነት ተጀምሮ ነበር ይህም በተለያዩ የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎች የኢትዮጵያን ህዝብ የትግል መንፈስ አዳክሞና አንድነቱን ሸርሽሮ ወረራው በሚጀመርበት ወቅት ህዝቡ ከመንግስት ጎን ቢቆም ከሞት በቀር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደማይኖር የሚገልፅ ሆኖ በኢጣሊያ መንግሰት እየተዘጋጀ የሚቀርብ ነበር ከዚያ ይልቅ የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያሰለጥነው ከሚመጣ ቅኝ ገዥ አገር ጋር ቢወዳጅ ትርፋማ እንደሚሆን ለማስገንዘብ የሚጠቀሙበት የፕሮፓጋንዳ ስልት ነበር የኢጣሊያ የፕሮፓጋንዳ ስራ በህዝቡ ዘንድ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ከባድ መሆኑን በመገንዘብም ፕሮፓጋንዳን በፕሮፓጋንዳ የማክሸፉን ስራ ኢትዮጵያውያኑ ጀመሩችት በ ዓም የኢትዮጵያ ሀገር ፍቅር ማኅበር ተቋቋመና በየሳምንቱ እሁድ ስብሰባ እየተደረገ ለሀዝቡ ኪነ ጥበባዊ ለዛ ባለው አቀራረብ የአገርን ፍቅር የሚያስታውሱ የጀግንነት መንፈስን የሚቀሰቅሱ ንግግሮች ግጥሞች መጣጥፎችና መዝሙሮች ይቀርቡ ጀመርበተጠቀሰው ጊዜ የኢጣሊያን ወራሪ ጦር በኦጋዴን ድንበር መክተው የመለሱት የእነደጃዝማች ኡመር ሳመተር ጀግንነት ሲሰማም የአገር ፍቅር ማኅበር ከነበረበት የበለጠ ተሻሽሎ ብዙ ታዳሚዎችንም እያፈራ ተግባሩን በመቀጠል ወኔ ቀስቃሽ ንግግሮች መቅረብ ጀመሩበወቅቱ ታዋቂ ከነበሩ ተናጋሪዎች ውስጥ አቶ ዮፍታሔ ንጉሴ በኋላ ብላታ አቶ ደምሴ ወልደአማኑኤል ደጃዝማች አቶ ክፍለ እግዚኣ ይህደጎ ብሳታ አቶ ተመስገን ገብሬ አቶ ኃይለገብርኤል ነገሮ አቶ መንገሻ ከፈለ ይገኙበታል እነዚህን የመሣሠሉ የአገር ፍቅር አባላት በንጉ ፊት ቀርበው የጠላትን ፕሮፓጋንዳ በመቃወምና የህዝቡን ወኔ በማነሳሳት የተጫወቱት ሚና በቀላሉ የሚታይ አኣልነበረም በዚህ መልኩ የተጀመረው የመጀመሪያው ቴአትር ቤት ኣገር ፍቅር ሆነና ቀጥሎ በ ዓም የዛሬው ብሔራዊ ቴአትር ቤት ተከፍቶ ስራውን ቀጠለ ከዚያም የመዘጋጃ ቤት ቴአትርቀጥሎም የቀድሞው የራስ ኃይሉ ሲኒማ ቤት የቴአትር መድረክ ተዘጋጅቶለት በመከፈቱ የቴአትር ቤቶችን ቁጥር ወደ ከፍ ማድረግ ተቻለ በተጨማሪም የድሮው ሰይጣን ቤት ይባል የነበረው ተሐድሶ ተደርጎለት አምፊ ቴአትር በሚል ስያሜው ስራውን ቀጠለ ከእነዚህ የጃንሆይ ዘመን ውጤቶች ውጪ ባለፉት ዓመታት ውስጥ ምንም አይነት አዲስ ቴአትር ቤቶች አልተሰሩም አልተጨመሩም ድው አርቲለት ህነበባች ታደሰጭራ ቀረጃነበወጣትነቷ ለጃንሆይ በበዓል ጊዜ እቅፍ አበባ ስታብበረክት ጥቅምት ቀን ዓም በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለስሳሴ ቴአትር ቤት የሩሲያ አርቲስቶች መጥተው ጃንሆይኖ እቴጌ መነን በተገኙበት የኪነጥበብ ውጤታቸውን አኣሳይተው ነበር ከትእይንቱ በኋላ ጃንሆይ ለኢትዮጵያውያን የኪነጥበብ ባለሙያዎች ተከታዩን መልዕክት አስተላልፈዋል ትምህርት ለሁሌ የሚሰጥ ነገር ነውእንደባህሪው ለመምረጥ ግን የእያንዳንዱ መንፈስና አካል የሚይዘው ነገር ነው አሁን እዚሀ ያየነው ሁሉ እድላችሁ ለዚሁ የመራችሁ መሆኑን ይገልፃል። ገቡላቸው አይኖርም ከማያውቁት መላዕክ የሚያውቁት ሠይጣንን ካልተረቱት በቀር ከሁለት አውሮፓዊ ገዥ አንዱን የመምረጥ ያህል ነበርኢምፔሪያሊዝምም ፋሺዝምም ተገዥ ለሆነ አገር ልዩነቱ ያዘለና ያቀፈ መሆኑን ስለተረዱም ነው ፃነታችሁን እንመልሳለን ወደማለት ያመሩትበዚህ መሠረት እፍሪካውያን በጦርነቱ ሊሳተፉ ችለዋል ቅኝ ገዥ እገራቱ ከድል በኋላ ቃላቸውን ሙሉ በሙሉ ለመጠበቅ ባይችሉም ለአፍሪካውያኑ ግን ከጦርነቱ ፍፃሜ በኋላ የገዥዎቻቸውን ቀንበር ከላያቸው ላይ ለማውረድ የራሳቸውን ትግል ብቻ እንጂ በገዥዎች ችሮታ እንደማይገኝ አስገንዝቧቸዋል ለጥቁር ሀዝቦች ማንም ያሸንፍ ማን እዚህ ግባ የሚሉት ለውጥ ከዚህም በላይ የጦርነቱ ፍፃሜ በራሱ ለብሔራዊ ነፃ አውጪና ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄዎች መስፋፋት ከፍተኛ ግፊት ፈጥሯል የነበሩት የነፃነት ትግሎች ተጠናክረው ያልነበሩት በአዲስ መልክ ብቅ ብቅ እያሉ የቀጠሉት ከድል በኋላ ምንም ያተረፉት ነገር ባለመኖሩ ነው ለፋሸዝም መሸነፍ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱት በጦርነቱም ቀዳሚ ተዋጊ እየተደረጉ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉትና መራራ ስቃይ የተቀበሉት እፍሪካውያን የተገባላቸው ቃል በመታጠፉም ብቻ ሳይሆን በጦርነቱ ወቅት የተለያዩ አገራት ዜግነት ካላቸው ወታደሮች ጋር ተሰባጥረው ስለተዋኑ አመለካከትና ግንዛቤያቸው ዳብሮ ነበርና ግዳጃቸውን ተወጥተው ወደሰሳማዊ ኑሮዋቸው እንዲመለሱ በተደረገ ጊዜ በቅኝ አገዛዝና በፖለቲካዊ በኢኮኖሚያዊ በአይዲዮሎጂያዊ መሠረቶች ላይ በመነሳት ቀደም ብዕፅው በተጀመሩት በነፃነት ትግሎች ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ጀሙሩ እፍሪካውያን ሚሊቱሪዎች በአገራቸው ውስጥ ሆነው ለነፃነታቸው መታገላቸውን በቀጠሉበት ሁኔታም በውጭ አገር ትምህርታቸውን የተከታተሉ የየአገራቱ ምሁራንና ፖለቲከኛ የሆኑ ሲቪል ዜጎችም በዲፕሎማሲና በተለያዩ የትግል ስልቶች የነፃነቱን ንቅናቄ የሚያጎለብት ስራ ይሰሩ ነበር በመሆኑም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍፃሜ በኋላ አፍሪካውያን የፓንአፍሪካሂዝም ንቅናቄያቸውን አጧጧፉት በአህጉሪቱ ውስጥም ብዙ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ድርጅቶች ፈለቁ የፓን አፍሪካ ጉባኤዎችም በየጊዜው መካሄድ ጀመሩ ኢትዮጵያም ምንም ነፃ አገር ብትሆን የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ደጋፊ መሆኗን ገለፀች ጃንሆይ በማናቸውም ረገድ ቢሆን አፍሪካውያን ወንድሞቻችንን ለነፃነት የሚያደርጉትን ትግል ደግፈን የሚቻለንን ሁሉ እንረዳለን አሉ አፍሪካውያኑ በውስጣቸው ያለውን ምሬት ይፋ ያወጡትና ጠንካራ ውሣኔ የወሰኑት ጦርነቱ በአውሮፓ ሙሱ በሙሉ ሲጠናቀቅ የጥቂት ወራት እድሜ በቀረበት በጥቅምት ወር እኤአ ላይ በእንግሊዝ ማንችሰተር ከተማ ውስጥ በተደረገው በኛው የፓን አፍሪካ ጉባዔ ላይ ነው በዚያ ጉባዔ በአህጉሪቱ የፈለቁ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ድርጅቶች አባላት የተካፈሉ ሲሆን ከእነርሱ ውስጥ የጋናው ክዋሜ ኑክሩማ እና የኬንያው ጆሞ ኬንያታ ይገኙበታል እነርሱና መሰል እውቅ የብሔራዊ ነፃ አውጪ ንቅናቄ መሪዎች በጉባኤያቸው ለአፍሪካ ህዝቦች ያቀረቡት ማሳሰቢያና የወሰዱት አቋም እንዲህ የሚል ነበር ጭሉም ህዝቦች ራሳቸውን ለመምራት መብት እንዳላቸው እናምናለን ሁሉም ቅኝ ግዛቶች ከባእዳን የፖለቲካና የኢኮኖሚ ቁጥጥር ነፃ መሆን አለባቸው የቅኝ ግዛት ህዝቦችም ባእዳን ኃይላት ከሚጥሉት ማንኛውም ገደብ ነፃ ሆነው የየራሳቸውን መንግስታት የመምረጥ መብት ሲኖራቸው ይገባል ሲሉ አስገነዘቡ ይህን የውሣኔ አቋም ኢምፔሪያሊስቶች ለማፈን ጥረት አደረጉ አፍሪካውያኑ ግን የነፃ አውጪ ንቅናቄ መሪዎችን መልዕክት ተቀብለው በተግባር ወደመተርጎም አመሩ ጦርነቱ በአውሮፓ ባበቃበት ግንቦት ቀን እኤአ የፈረንሣይ ቅኝ ገዥዎች በግዛታቸው በአልጀሪያ ውስጥ የተነሳውን የነፃነት አመፅ ለማዳፈን ከፍተኛ ወረራ እካሂደው ሺ አልጀሪያውያንን ገደሉ በ ማዳጋስካር ውስጥ ለነፃነቱ ለመዋጋት በተነሳውና ምንም ባልታጠቀው የማላጋሲ ህዝብ ላይ የፈረንሣይ ወታደሮች በዘመኖዊ መሣሪያ ታግዘው በከፈቱት ተኩስ ሺ የደሴቲቱን ተወሳጆች ፈጆቸው የነፃ አውጪ ንቅናቄ መሪዎች የትግል ስልት አይነቱ ይለያይ እንጂ በአህጉሪቱ በሚካሄዱ ትግሎች ምክንያት ተመሳሳይ የኢምፔሪያሊስቱ የጭካኔ እርምጃ ለዓመታት በየአገሩ ሲፈፀም ቆይቷል በሰሜን አፍሪካ የሚገኙ አገራች ውስጥ ኮሚኒስት ፓርቲዎች እንደመበርከታቸው መጠንም በኃያሏ ሶቭየት እርዳታ ምክንያት የትግላቸው ጊዜ አጭር እንዲሆን አግዚቸዋል ነፃነቷን በመቀዳጀት ረገድ የመጀመሪያዋ የአፍሪካ አገር ሊቢያ ናት ከቀድሞ ገዥዋ ከኢጣሊያ ነፃ ከሆነች በኋላ በእንግሊዝና በፈረንሣይ ወታደሮች ተይዛ የቆየችው ሊቢያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውሣኔ መሠረት መንግስታዊ ሉዓላዊነት ያገኘችው ታሀሳስ ቀን እኤአ ነው ሆኖም ባዕዳኑ አገሪቱን ሙሉ ለሙሉ ለቀው የወጡት እኤአ በ ነበርጋዳፊ ስልጣን እንደያዙ ጠራርገው አባረሯቸው በሐምሌ ወር እኤአ ግብፅ በጋማል አብድል ናሰር መሪነት ፀራኢምፔሪያሊስት አብዮት ተከናውኖ የአብዮታዊ መምሪያ ምክር ቤት ከተቋቋመ በኋላ የአርበኞች ድርጅት አባሎችን የያዘ ቡድን ስልጣኑን ይዞ በጋግል አብድል ናስር ሲመራ ቆይቶበግብፅ አብዮታዊ መንግስት ጥያቄ መሠረት ከረጅም ጊዜ ግብግብ በኋላ እንግሊዝ ወታደሮቿን ሙሉ በሙሉ በሰኔ ወር እኤአ ከአገሪቱ አስወጣችበአገሪቱ የኢምፔሪያሲስት መንግስትን መልሶ ለማቋቋም የሚፈልጉ ኃይሎች ቢኖሩም ሶሻሊስቱ ቦታውን ሳይለቅ ቆዬእንግሊዝና ፈረንሣይ የስዊዝ ካናል ኩባንያን ለግብፅ ማስረከብ እንዳለባቸው የተጠየቁትን ጥያቄ መሠረት አድርገው እስራኤልንም ከጎናቸው አሰልፈው በግብፅ ላይ ጦርነት ቢከፍቱም የግብፅ ህዝብ በጀግንነት ተዋግቶ መከተለዚህም የሶሻሊስት አገሮች በተለይ ሶቭየትና ቺኮዝላቫኪያ ለግብፅ የሰጡት የመሣፈየያ እርዳታ ለድሉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ነበረውሦስቱ አገሮች ግብፅን መልሰው ለማጥቃት ሲዘጋጁም ሶቭየት በሦስቱ አገሮች ላይ ጦርነት እንደምትከፍት ስላስጠነቀቀች ወራሪዎቹ ተኩስ አቁመው ከግብዕ ወጡየግብፅ ድል ለሰሜን አፍሪካና ለዓረቡ ዓለም የነፃነት እንቅስቃሴ ወኔን የሚቀሰትስ ሆኖ ሲገኝናስርም የዓለም ነፃ አውጩ ንቅናቄ እውቅ መሪ ተሰኘበትበመሆኑም ጥር ቀን እኤአ በእንግሊዝ ስር የነበረችው ሱዳን ነፃ ሪፐብሊክ ሆነችፈረንሣይ በበኩሏ መጋቢት ቀን የሞሮኮንመጋቢት ቀን የቱኒዚያን ነፃነት እውቅና ለመስጠት ተገደደች የግብፅ ተፅዕኖ ለተጠቀሱት የአፍሪካ ዓረብ አገራት ነፃነት የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ ነበረውእኤጴአ መጋቢት ቀን ጋና ነፃነቷን መጎናፀፏ ታወጀእኤአ በ ጊኒ ነፃ ወጣችበዚያ ጊዜ በእኛ አቆጣጠር ዓም ነፃ የአፍሪካ መንግስት ጉባዔ ተመሠረተና በጋና አክራ ከተማ የመጀመሪያው ውይይት ተካሄደ እለቱንም አፍሪካ ቀን በማለት በአህጉር ደረጃ ሰየሙትየነፃ መንግስታቱ ድርጅት ጉባዔ በፖለቲካና በኢኮኖሚ ጉዳዮች እየተወያዩ ሌሎች አገራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለነፃነት የሚበቁበትን መንገድ ማመቻቸትና መርዳት እንዲሁም ግፊት ማድረግ ነበረበትለዚህም ምቹ ሁኔታ መፍጠር የምትችለው ኢትዮጵያ ነበረችና ተከታታይ ጉባኤዎች በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመሩ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንም በኢትዮጵያ ተመሠረተነፃ የአፍሪካ አገሮች ኅብረት ፈጥረው ያደረጉት ግፊትም ፍሬ መስጠቱን ቀጠለ ጃንሆይ ከአፍሪካውያን መሪዎች ጋር በኛ አቆጣጠር ሚያዚያ ቀን ዓም ጃንሆይ የአፍሪካን ጉዳይ በሚመለከት በሬዲዮ የተናገሩት ንግግር በአጭሩ እንዲህ ይነበባል ጥአፍሪካ ቀን ክብረ በዓል የተመሠረተበት ሁለተኛው ዓመት በሚውልበት በዛሬው እለት ከልብ የሆነውን የራሳችንን ሠላምታና የምንወደው ህዝባችን ለአፍሪካውያን ወንድሞቹ የሚልከውን የወንድማማችነት በጎ ምኞት ለመላው አፍሪካ ሀዝቦች አንገልፃለን ስለዚህ ታላቅ ስለሆነው ክፍለ ዓለም ህዝቦች ነፃነትና የወደፊት እርምጃ በሚያደርገው ትግል ባለፈው ዓመት ውስጥ የአፍሪካ አገሮች ያሳዩት መተባበር ደስ የሚያሰኝና የሚያበረታታ ነው ካሜሮን ነፃ እንደወጣች እንዲሁም ኮንጎ ናይጄሪያ ሶማሊያኖ ቶጎ ላንድ በዚህ ዓመት ውሰጥ ነፃነታቸውን የሚያገኙ በመሆናቸው ኣፍሪካውያን ወንድሞቻቸው በሙሉ ይደሰቱበታል የእነዚህ አገሮች ነፃ መውጣት የአገሬውን ሀዝብ በተለይ የሚያስደስተው ብቻ ሳይሆን ይህንኑ መልካም ውጤት ለማስገኘት ሳይሰለቹ ለደከሙት እህትማማች አገሮች ሀዝብ ጭምር ብርታትን የሚሰጣቸው ነው በዚህም አኳኋን ከአስር ዓመት በማያንስ ጊዜ ውስጥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል የሆኑት የአፍሪካ አገሮች ቁጥር በዝቶ ከሦስት እስከ አራት መድረሱ ስለአፍሪካ ነፃነት የሚደረገውን እንቅስቃሴ በበለጠ የሚያጠነክረው ስለሆነ ሌሎችም በአፍሪካ ውስጥ የሚገኙ ግዛቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ነፃነታቸውን እየተጎናፀፉ ከአፍሪካውያን ወንድሞቻቸው ጎን ተገቢ የክብር ስፍራቸውን እንደሚይዙ አያጠራጥርም አሁንም እንኳ ቢሆን በማናቸውም አገር የሚገኙ ህዝቦች ሁሉ በዘር ምክንያት ልዩነት እንዳይደረግባቸውና የእድል እኩልነት እንዳይነፈጋቸው ለማድረግ በተባበሩት መንግስታት ሸንጎ በሚደረገው ትልቅ የአፍሪካ መንግስታት ኀሳብና ዓላማ አንድ መሆንና በሰፊው መተባበራቸው ከብዛታቸው ጋር ሆኖ በተባበሩት መንግስታት ሸንጎ የሚናገሩዋቸውን ቃላት በተለይ ተደማጭ አድርጎታል ይህ ኅብረትና መረዳዳት በመጠኑ ከታሪካቸው ቅርስ የተገኘ እንዲሁም የጋራ ተጋድሏቸውን ባለመዘንጋት ላይ የተመሠረተ ሆኖ ሲገኝስለኢኮኖሚና ሰለፖለቲካ ጉዳዮች መመካከሪያ አንዲሆን የተቋቋመው ድርጅት መሠረታዊ ስለሆኑት የኀሳብ አንድነት ተባብሮ በጥንካሬ ስለመስራት መርዳት ደስ የሚያሰኘን ነው በዚህ ዓመት ከአራት ወራት በማይባልጥ ጊዜ ውሰጥ የአፍሪካ አገሮች በቱኒዝ በአክራና በኮናክሪ ሦስት ጊዜ ስብሰባ ያደረጉ ሲሆን በሚመጡት ወራት ውስጥ ደግሞ በመናገሻ ከተማችን ሁለት ጊዜ እንዲሰበሰቡ መታቀዱን እኛን አፍሪካውያንን የሚያኮራን ነው በዚህ በዛሬው የእፍሪካ ቀን ለወንድሞቻችን ነፃነት ደህንነትና መሻሻል እንቅፋት የሆኑትን ነገሮች ሁሉ ለማስወገድ ያለንን ከፍተኛ ፋ ዓላማ በበለጠ እንድናከናውን ኀሳባችንንና ቆራጥነታችንን እንደገና አናድስ ጾሪ ናፍሮ ፖ በዚሁ የአፍሪካ ቀን በተከበረበት እለት አኤአ ዓም የአፍሪካ አገሮች ነፃነታቸውን ተቀዳጁ በተጠቀሰው ዓመት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ለቅኝ ግዛት አገሮችና ህዝቦች ነፃነት ስለመስጠት ጉዳይ የቀረበውን ውሣኔ አፀደቀ የካፒታሊስት አገራት ተወካዮች ረቂቁን ውድቅ ለማድረግ አልሞከሩም ነገር ግን ቅኝ አገዛዙ በተሻሻለ ሁኔታ የሚቀጥልበትን መንገድ ለማመቻቸት ጥረው ነበር ሆኖም የገለልተኛ አገራትና የሶሻሊስት አገራት በተለይ የሶቭየት ኅብረት ተወካዮች ካፒታሊስቶችን ተቃውመው ጥረታቸውን አከሸፉት የእስያና የአፍሪካ አገሮች ያረቀቁትን መግለጫ ጠቅላላ ጉባኤው በከፍተኛ የድምፅ ብልጫ ሲያፀድቀውም ቅኝ አገዛዝ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት መርሆዎች ጋር የማይጣጣም መሆኑን በመግለፅና ህዝቦች የራሳቸውን እድል በራሳቸው የመወሰንና በነፃነት የመኖር መብት እንዳሳቸው በማረጋገጥ ነው ከውሣኔው መፅደቅ በኋላ ለብሔራዊ ነፃነት የሚካሂደው ትግልና የሚከተለው እልቂት ሙሉ ለሙሌም ባይሆን በመጠኑ ጋብ አለ ለ ዓመታት ያህል ደም ያፋሰሳው የአልጀሪያና የፈረንሣይ ጦርነትም ተገታ ሐምሌ ቀን እኤአ አልጀሪያ ነፃ አገር ሆነች ከዚህ በኋሳ ባሉት ተከታታይ ዓመታት የቅኝ ግዛት ስርዓት በመላው ዓለም እየፈራረሰ ሄደ አፍሪካውያን ቀስ በቀስ ነፃነታቸውን እየተጎናፀፉ ለመሄድ ካስቻሏቸው መንገዶች ውስጥ አንዱ ኅብረታቸው እንዳለ ሆኖ በኢኮኖሚ በኩል ሊረዳዱ የሚችሉበት ሣአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን በተባበሩት መንግስታት አማካኝነት ማቋቋም በመቻሉ ነው በእኛ አቆጣጠር ዓም በአዲስ አበባ ከተማ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የመጀመሪያ ጉባዔ ተመርቆ ከተከፈተ ከአንድ ዓመት በኋላ ጃንሆይ በሁለተኛው የአፍሪካ ነፃ መንግስታት ኮንፈረንስን ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ውስጥ ያካተቱት ገለፃም ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው የአፍካ ኢኮኖሚ ኮሚሲዮን የመጀመሪያው ጉባዔ በተደረገበት ጊዜ የአፍሪካ ህዝብ ያደረገውን የተፋጠነ የፖለቲካ እድገት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ከተፈፀሙት እጅግ አስገራሚና አስደናቂ ሆነው ከሚታዩት የስልጣኔ እርምጃዎች ኣንዱ መሆኑን ገልጠናል ከዚያም ወዲህ በተከተሉት ወራት ውስጥ የቀጠለው ትግል በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ አዳዲስ መንግስታት በማስገኘቱና የቅኝ ግዛት ሰዎች ወደነፃነት ግባቸው የሚያደርጉትን እርምጃ በማፋጠኑ መጠን ከታሰበው በላይ የሆነ መልካም ውጤት አስገኝቷል በዚህ ከእግዚአብሔር በተመረጠው እድል ጊዜና ቀን መመስረትኖ መስራት የሚገባን መሆኑን አውቀን እድል ህልም ሆኖ እንዳይቀር የአንድነትን መሠረት መጣል ስራችን እናድርግ ኮንጎ ካሜሩን ቶጎላንድ ናይጄሪያና ሶማሊያ ዛሬ ከመካከሳችን ተገኝተው በዚህ ጉባዔ ስራ ሙሱ ተካፋይ ለመሆን በመቻላቸው ሁላችንም ደስ ይለናል ከአሁን በፊት እንደተናገርነው የአፍሪካ ህዝቦች የፖለቲካ እድገት ወደመጨረሻው ግቡ ሳይደርስ የማያቋርጥ መሆኑን በጥብቅ እናምንበታለንከዚፉሁም ግብ የሚደርሰው መላው የአፍሪካ ህዝብ ነፃነቱንና ሠብዓዊ መብቱን በሙሉ ሲያገኝ ነው በዚያ ወቅት ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን ነፃነትና የወደፊት ዕጣ ሲባል ያደረገችው ድጋፍ ዘርፈ ብዙና ሁሉን አቀፍ መሆኑን ለመገንዘብ የሚያስችለን ጃንሆይ በእኛ አቆጣጠር ሰኔ ቀን ዓም ሁለተኛውን የአፍሪካ ነፃ መንግስታት ኮንፈረንስ በከፈቱ ጊዜ ከተናገሩት ውስጥ ተካቶ እናገኛለን በደቡብ አፍሪካ የሚደረገውን የዘር ልዩነትና ግፍ ተባብረን ለህዝቡ ጠበታ ለመሆን በስራ መግለጥ አለብን አባቶቻቸው በግዓፍ ለሞቱባቸው የደቡብ አፍሪካ ወጣቶች እስኮላርሽፕና የገንዘብ እርዳታ የሰጠነው በዚሁ በመቆርቆር ነው ብለዋል በእለቱ ከወቅቱ ኢትዮጵያዊ ምሁራን ውስጥ አንዱ የነበሩት ክቡር አቶ ይልማ ደሬሳ የታዋቂው የኢኮኖሚ ሊቅ የብላታ ደሬሳ አመንቴ ልጅ በስብሰባው ከተናገሩት ንግግር ውስጥ ጥቂት ሐተታዎችን ሰናኖይም የኢትዮጵያ ሜና እምን ድረስ እንደሆነ በአጭሩ እንገነዘባለን ዝቡራን መልዕክተኞች ወይዛዝርትና መኳንንት ይህ የአፍሪካ ነፃ መንግስታት ሁለተኛ ጉባዔ ሊቀመንበር እንድሆን በመመረጤ ከፍ ያለ ክብር ይሰማኛል ይህ ምርጫ የእኔ መሆኑ ሰለአገሬ ክብርና በተለይም ታላቁ መሪ ገናናው ገዥዩና ንጉሠነገሰቴ ስለአፍሪካ ህዝብ ነፃነት ሀዝባዊ መብትና በመሻሻል ወደፊት መራመድ በዚህ ክፍለ ዘመን ያደረጉትን ተጋድሎ ከማወቅ የተነሳ እንደተደረገ እቆጥረዋለሁ የእፍሪካ ሀዝብ እንደራሴዎች አከታትለው ባደረጓቸው ስብሰባዎች የአክራ ጉባዔ የመጀመሪያ አንደነበረ በደሰታ የምናስታውሰው ነው ይኸውም ጉባዔ ከተደረገ በኋላ ከአንድ ዓመት በሚያንስ ጊዜ ውስጥ የአፍሪካ ኤኮኖሚ ኮሚሲዮን የመጀመሪያው ጉባዔ የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት በተቋቋመበት ከተማ እዚሁ አዲሰ አበባ ላይ ተደረገ ከጥቂት ወራት በኋላ ደግሞ አሁን ስራው ለማለቅ በተቃረበው በአዲሱ የአፍሪካ አዳራሽ የዚሁ ድርጅት ሦስተኛ ጉባኤ እንዲሰበሰብ ተወሰሳኗል ስለዚህ ለኢኮኖሚ ጉዳዮች መመካከሪያ የሚሆን ድርጆት እንዲቋቋም የአክራ ጉባኤ ያሳሰበውም አሟልቶ ከስራ በማዋል ረገድ በጣም የተጋፋበት መሆኑን በአጭር ጊዜ ውስጥ ልናውቀው ችለናል እንደዚሁም ሁለት መቶ አፍሪካውያን ተማሪዎች በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትቤቶች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉ ገናናው ገዥዬ ያቋቋሙት እሰኮላር ሽፕ ስለካልቸር ጉዳዮች የተደረገው ውሣኔ በሥራ ላይ ማዋሉን በጉልህ የሚያስረዳ ነው ጉባኤው የሚመክርባቸውን ጉዳዮች በአጭሩ አጠቃለው ሲገልፁም « ዛሬም ቢሆን ዋናው ችግራችን በአጀንዳችን ተራ ቁጥር የተመለከተውና የቅኝ ግዛትን ከኣፍሪካ ጨርሶ ሰለማስወገድ ሀ ነፃ ያልሆኑት አፍሪካውያን አገሮች ነፃነታቸውን እንዲያገኙ ስለሚወሰደው እርምጃ ለ አዳዲሱ አይነት ኮሎኒያሊዝም ወደ አፍሪካ እንዳይገባ ስለመከሳከል በሚለው እርእስት ተጠቃሎ የሚገኘው ጉዳይ ነው የላይቤሪያ የልዑካን መሪ ሆነው የመጡት ክቡር ሚስተር ሩዶልፍ በእለቱ ከመግቢያ ንግግራቸው አስከትለው የተናገሩት ንግግርም ጃንሆይ ለአፍሪካ ነፃነትና ሠሳም ሲሉ በሰሯቸው ስራዎች በአፍሪካውያን መሪዎች ዘንድ ልዩ አክብሮት እንዳሰጣቸው ከማስረዳት ባለፈ የኢትዮጵያን የአፍሪካ ተምሳሌትነት የሚያረጋግጥ ነው « ግርማዊ ሆይ የውቢቷ አገርዎ ታሪክ የመላው አፍሪካ ህዝብ መመኪያ ሆኖ ይታያል ግርማዊነትዎም በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለምም ጭምር ጥንካሬ ከብሩህነት ጋር የተመላበት መሪ ምልክት ሆነው ይታያሉ ግርማዊነትዎ በታላቅ መከራና ችግር ዘመን ለነፃነቱ እየታገለ ለመዋጋት ለቆረጠው ሀዝብ ምልክት ነው ግርማዊነትዎ ፋሽዝም ለዘለዓለም አይኖርም ይደመሰሳል ብሎ ያምን ለነበረው በሚሊዮን ለተቆጠረው ህዝብ ምሳሌ ነው ኢትዮጵያ የብዙ ሺ ዘመናት የነፃነት ጣዕም የቀመሰች አገር በመሆኗ ነፃነትን ለሚፈልኾጉ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ህዝቦች መፅናኛና መነቃነቂያ መበረታቻም ሆና ትታያለች ግርማዊነትዎ የእኩልነት መብት በሰው ልጅ እንዲኖር በሚጥሩ መካከል ታላቅ ምሳሌ ሆነዋል ካሉ በኋላ በሁለኛው የነፃ አፍሪካ ኣገሮች ጉባዔ ስም ሆጃ ዳግም ምስጋናዬን በማቅረብ ለግርማዊነትዎና ለቤተሰቦችዎ ጤናና ረጅም እድሜ ለኢትዮጵያና ለህዝቧም ብልፅግና እመኛለሁ በማለት ነበር ንግግራቸውን የደመደሙት አፍሪካን በሚመለከት ጃንሆይ የነበራቸውን አቋምና ታሪካዊ ንግግራቸውን እውቁ የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኝ ቦብ ማርሌ ሳይቀር ግላ በሚለው ዜማ አካቶት እናገኛለን በደቡብ አፍሪካ በአንጎላዚ በሞዛምቢክ የሚገኙት ወንድሞቻችን ካሉበት የባርነት ቀንበር ነፃ እስኪወጡ ድረስ መላው እፍሪካውያንና እስያውያን በዓለም ሸንጎ በእኩልነት ደረጃ ድምፃቸው እስኪደመጥ ድረስ የአፍሪካና የእስያ ክፍለ ዓለም ሙሉ ሠሳም አላቸው ለማለት አስቸጋሪ ይሆናል የዘር ልዩነትና ጭቆና የቅኝ አገዛዝ መሠረቱ ኢኮኖሚ ነው እነዚህም አሰቃቂ ተግባሮች የሚወገዱት በኢኮኖሚክ መሣሪያ ነው በአዲስ አበባው የመሪዎች ጉባዔ የአፍሪካ አገሮች በቅኝ አዝቫዝ ስር የሚገኙት አፍሪካውያን ካሉበት የባርነት ቀንበር ነፃ ለመውጣት በሚያደርጉት ትግል እንዲረዷቸው በማለት በገዥዎቻቸው ላይና ሙሉ የኢኮኖሜ አክሲዮን እንዲደረግ ወስነው በስራ ላይ ኣአኣውለውታል እያሉ በማተት በመጨረሻም መልካም መጥፎን ድል እንደሚነሳና እኛም እንደምናሸንፍ ጥርጥር የለውም ባሉት መሠረት የአፍሪካውያን ጥረት ለመጨረሻው ድል በቅቶ በዎቹ አጋማሽ አመታት የአንጎሳላ የሞዛምቢክና የጊኒ ቢሳው ህዝቦች ነፃነታቸውን ተቀዳጁ እነዚህ የፖርቹጋል ይዞታዎች ነፃነታችውን ካወጁ በኋላም እኢአ በ የመጨረሻዋ አፍሪካዊት አገር ናሚቢያ ለህዝቦቿ በተሰጠው የመምረጥ እድል አማካኝነት ነፃ አገር በቀል መንግስት መመስረት ቻለች የደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ አገዛዝም በሕግ ተሸሮ ከዘር ነፃ የሆነ ምርጫ ተካሂዶ በምርጫው ለዚር ኤ ኤን ሲን ወክለው የተወዳደሩት ኔልሠን ማንዴላ እኤአ በ ዓም በከፍተኛ ድምፅ አሸንፈው በደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ የመጀመሪያው ጥቁር ፕሬዝደንት ለመሆን ቻሉ ባየነው መልኩ የቅኝ አገዛዝ ስርዓት ቢያከትምም የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዙ ዛሬም ድረስ እንደቀጠለ መገኘቱ አይዘነጋም ጃንሆይ ፕቅኝ አገዛዝ መሠረቱ ኢኮኖሚ ነው ማስወገጃውም ኢኮኖሚ ነው እንዳሉት የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዙም በኢኮኖሚ ድክመት በኩል የሚተገበር መሆኑን እያየን ነው በእነዚያ ዘመኖት ከኢትዮጵያ በስተቀር መላው አፍሪካና ህዝቦቿ ለነፃነታቸው ሲፍጨረጨሩ ኢትዮጵያ ነፃ የትምህርት እድል ለአፍሪካውያን ከመስጠት ባለፈ ራሱን የቻለ በባለሙያ የተሞሳ የውጭ ገንፕንት የነበራትና ቢሮክራሲዋም ዓለም አቀፍ ይዘት የነበረው አገር ነበረች አጃ ልክ በዚሁ መጠንም ጃንሆይ አፍሪካ ውስጥ ራሱን የቻለ መንግስት ባልተመሰረተበት አህጉር ከታዋቂ መሪዎች ተርታ የተሰለፉ ዓለም አቀፍ እውቅናቸው የዳበረና የተከበሩ ተሰሚነት የነበራቸው መሪ ነበሩ ለውጭ ግንኙነት ምቹ የሆነ የአየር መንገድ ስለነበረም አፍሪካውያን የነፃነት ታጋዮች ባሻቸው ጊዜ በነፃነት ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ በአህጉሪቱ ቀጣይ ዕጣ ፋንታ የመወያየት እድል ነበራቸው በእቸ አቆጣጠር በ ዓም ግንባታው የተጠናቀቀውን የኢ ሲ ኤን ጄርል አዳራሽ የመሰሉ ምቹ መሰብሰቢያዎችን ጃንሆይ በራሳቸው ገንዘብ አስገንብተው የፓን አፍሪካኒዝም ውልድ ለሆነው ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት አበርክተዋል የድርጅቱ ቋሚ መቀመጫ ኢትዮጵያ እንድትሆን የተደረገውም የጃንሆይ መንግስት ለአህጉሪቷ ነፃነት ያበረከተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት ነው ጃንሆይ ጥአፍሪካ እባት ነበሩና ዛሬም ድረስ በዚሁ ስም ይጠራሉ ኢትዮጵያ ጥአፍሪካ እናት የተሰኘችውም በቅኝ ግዛት ያልተያዘች ብቸኛ አፍሪካዊት አገር በመሆኗ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ነፃነት ተምሳሌት በመሆኗ ነው ከአፍሪካም ባለፈ በቆየው የአድዋ ድል ለመላው ተገዥ ህዝቦች የፅናት ተምሳሌት ሆና የተጠቀሰች ብቸኛ አገር ናት ይህን መነሻ በማድረግም በርካታ የአፍሪካ አገሮች ከነፃነታቸው በኋላ የየራሳቸውን ሠንደቅ ዓላማ ሲያዘጋጁ የቀለም ምርጫቸው የኢትዮጵያን ሠንደቅ ዓላማ መሠረት ያደረገ ሆኖ ቀርቷል ይህን ንዑስ ርዕስ ከማጠቃለላችን በፊት አንድ ከአፍሪካ ጉዳይ ውጪ የሆነ የጃንሆይን ተግባር እንይ በእኛ አቆጣጠር በ ዓም በፈረንሣይ አገር የተፈጥሮ አደጋ ደርሶ ነበር በዚያን ጊዜ ጃንሆይ የሐዘን መግለጫቸውን ከሳኩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የገንዘብ እርዳታ ለፈረንሣይ ሰጥተዋል በዚያ አፍሪካውያን ልዩ እርዳታ ባሚያሰፈልጋቸው ወቅት ጃንሆይ ከአፍሪካ አልፈው ለፈረንሣይ ያደረጉት እርዳታ ቀደም ሲል ያየናቸው ሐተታዎች ከወጡበት ከቱ ፍሬ ከናፍር ከተሰኘው መጽሐፍ ተካቶ የሚገኝ ሲሆን የፈረንሣዩ መሪ ቻርለስ ደጎል እና ጃንያይ የተለዋወጧቸው ቴሌግራሞች የሚከተሉትን ይመስሳሉ ለክቡር ፕሬዝዳንት ደጎል ኤሊዜ ቤተመንግስት ፓሪስ የፍሬስ ከተማ በደረሰባት አሰቃቂ አደጋ ምክንያት ጉዳቷን ለማቃለል ይረዳ ዘንድ በፓሪስ ኢንዶቪን ባንክ በኩል አምስት ሚሊዮን ፍራንክ ልከንልዎታል ይህ የተላከው እርዳታ በዚህ መቅሰፍት ለተጎዳው ህዝብ በመሳለዎ አይነት ለእርዳታ ይውል ዘንድ ክቡርነትዎን እንጠይቃለን ጭ ሠ ፎሟታታ ከፕሬዝዳንት ቻርልስ ደጎል የተሰጠ መልስ የኢትዮጵያ ንጉሠነገስት ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ አዲስ አበባ በፍሬስ ከተማ ላይ በወደቀበት አሰቃቂ መቅሰፍት ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት ህዝብ ማቃለያ ይሆን ዘንድ ግርማዊነትዎ ርህራሄ በተመላ ቸርነቱ ስላደረገው ከፍ ያለ ስጦታ በሙሉ ልቤ ሳመሰግን እንዲሁም በእኔና ይህ ጉዳት በወደቀበት ህዝብ ስም ሆፔ ጥልቅ የሆነ ባለውለታ መሆኔን እገልፃለሁ ቻርልስ ደጎል ጃንሆይና ራስ ተፈሪያውያን የጃንሆይ ንጉሠነገስትነት ለኣኛ ነው ለሌሎች ደግሞ አምላክ የሆኑበት ሁኔታ አለ ይህን ታሪካቸውን ላለመዝለል ያህል ጥቂት ማለት ተገቢ ይመሰላል ኢትዮጵያን የዓለም ህዝቦች ዓይን ማረፊያ ካደረጓት ነገሮች ውስጥ እንዱ ነፃነቷን ሳታስደፍር መቆየቷና ብቸኛዋ ነፃ ኣፍሪካዊት አገር መሆኗ ነው አውሮፓውያን በአፍሪካ ምድር ቅኝ ግዛታቸውን አንሰራፍተው ከዚችው አህጉር ጥቁር ህዝቦችን በባርነት እያጋዙ በየአገሮቻቸው የጥጥ የትምባሆ እና የሌሎች ሰፋፊ የግብርና መስኮች ስራ ላይ እያሰማሩ በአሰቃቂ ሁኔታ ጉልበታቸውን በሚበዘብዙበት ጊዜ የጥቁር ህዝቦች ብቸኛ ተስፋና አርአያ የነበረችው ኢትዮጵያ ብቻ ነበረች በተለይም የየካቲት ቱ የዓድዋ ድል የበርካታ ጥቁሮችን ስሜት ያነሳሳና የነፃነት እንቅስቃሴያቸውን ያቀጣጠለ ክስተት ሆኖላቸዋል ከተለያዩ ቅኝ ተገዥ አገራት የሚጋዙ ጥቁር ህዝቦችም በጉዞ ላይ ሳሉ በሚደርስባቸው ስቃይ ሳቢያ ሲታመሙ ሲቆስሉና ጉዳት ሲደርስባቸው እስኪያገግሙ ይቆዩ የነበረበት ቦታ ጃማይካ ነበረች ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የነበረው ፍልሰት ቀጥሎ ብዙሃኑ ለረጅም ዓመታት በአውሮፓ ምድር ሲሰቃዩ ኖረው ከነፃነት በኋላም ዛሬም ድረስ ያልተመለሱ ኑሮዋቸው እዚያው የሆነ ጥቁር ህዝቦች ሞልተዋል ነብይ በአገሩ አይከበርም እንዲሉ ራስ ተፈሪ በእኞ እይታ ከንጉሠነገስትነት ያለፈ ሚኖ ባይኖራቸውም በጃማይካውያን ዘንድም ሆነ በዘመናቸው በነበሩ ጥቁር ሀዝቦች ዘንድ የአምላክነት ወይም የነብይነት ሰፍራ የተሰጣቸው ሆነው እናገኛቸዋለን በተለይም ለማርክስ ጋርቬይ እና ለመሰሎቹ ወደ አፍሪካ የመመለስ እንቅስቃሴ ጽኑ መሠረት ለመሆን ችለዋል አሜሪካ በኢኮኖሚ ቀውስ በምትናወጥበት በዎቹ የመጀመሪያ አመታት ከነበረው የጭቆና አገዛዝ ጋር ተዳምሮ የጥቁር ህዝቦችን ጭቆና የመረረ አደረገው ከ እስከ ዓም ድረሰ ምድር ላይ የነበረው ረ ጃማይካዊ ማርክስ ጋርቬይ « ጳቨዌርኋስ ሼእሃበነከ። በማለት አዲስና አሮጌ የሚባል ነገር እንደሌለ አስመስለው አዞዎቹ ከአልጀሪያው ቡድን ጋር ተመሳጥረው ያወጡትን ጽሁፍ የመጨረሻ አቋግችን በማለት ያንኑ የፖሊሲ አቋም በልዩ መጽሔታቸው አውጥተው በዓለም ላይ አሰራጩት የአውሮፓው ቡድን ኢተማአ ቀደም ሲልም የፊላደልፊያውን አቋም ተቃውሞ ነበርና አሁንም በኢተማሰአ ላይ የተደረገውን ኩዴታ በደስታ መቀበሉን ይፋ አደረገ ሆኖም የአልጀሪያው ቡድንና አዲሱ ኢተማሰአ ኅብረት ፈጥረው የአውሮፓውን የመሪነት ሰልጣን ለመያዝ የተለመደውን የአዞ ዘመቻ ጀመሩ በ ዓም የኢተማአ ኛ ጉባዔ በፈረንሣይ አገር ሲካሄድ በአዞዎቹ ተዘጋጅቶ በቀረበ ጽሁፍ በብርሃነመስቀል ረዳ የሚመራው የአልጀሪያ ቡድን የኢተማአ አመራሮችን ክፉኛ ነቀፋቸው አዞዎቹ በዚህም ሳይወሰኑ በዚሁ ጉባኤ ላይ የኢተማአ የራሱ አባላት ተወካዮች ፕኢትዮጵያ ተማሪዎች የዓለም አቀፍ ማኅበር ኢተዓአማ ደንብና አሰራር የሚሻሻልበትን የውሣኔና የደንብ ረቂቅ በድርጅታዊ አሰራር አዘጋጅተን አቅርበናል ብለው አቀረቡ የቀረበውን ረቂቅ በእለቱ አዲሱ ኢተማሰእ እና የአልጀሪያው ቡድን ተወካዮች ተስማሙበት በዚህ መሠረት ዓለም አቀፉ የኢተዓአማ ጉባኤ በሚያዚያ ወር ዓም በጀርመን በርሊን ከተማ መካሄድ ነበረበት በበርሊኑ ጉባዔ ለኢተዓአማ ምስረታ የአባል ማኅበራት ውክልናና የምርጫ ስነሥርዓት ጥያቄ ተነስቶ ለአንድ ሳምንት ተጨቃጨቁ ከዚሀ ቀደም የነበሩት የኢትዮጵያ ተማሪዎች ዓለም አቀፍ የአመፅ እንቅስቃሴ ማኅበራት አአዩተማ ኢተማሰአ ኢተማአ ነበሩ በቱ ጉባዔ ላይ ግን ከብዙ ውዝግብ በኋላ ሦስት አዳዲስ ማኅበራት እንዲኖሩ ተወሰነና ኛ የአልጀሪያው ቡድን ኛ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ሌባነን ኢተማሌ ኛ የኢትዮጵያ ሴቶች ዓለም እቀፍ ጥናት ክበብ ክ እንዲሆኑ ተወሰነ መን ቅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ የነበሩት የአአዩተማ ተወካዮች በነበረው የፖለቲካ ችግር ምክንያት በጉባፄው ላይ አልተገኙም አሮጌው ኢተማሰአ ከአውሮፓውና ከአዲሶቹ ጋር የአላማ መለያየትና ፀብም ስለነበረ በጉባፄው አልተሳተፈም በመሆኑም ከሳይ የተጠቀሱት ሦስቱ ማኅበራት ለዓለም አቀፉ የአመፅ እንቅስቃሴ ቅርንጫፍ ማኅበራት መሆናቸው ፀና በበርሊኑ ጉባኤ የአልጀሪያ ቡድን ተወካይ ሆነው የቀረቡት ስምንቱ ሰደተኞች ሲሆኑ በሌባነን የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ተወካይ ተብለው የቀረቡት ደግሞ በመካከለኛው ምስራቅ በስደት የነበሩ ተማሪዎች ናቸው ኢሴዓአጥክ ተብለው የተወከሉትና የኣባልነትኖና የምርጫ መብት የተሰጣቸው የሴቶች ቡድንም ኣዲ ኢተማግሰአ በአሜሪካን አገር ለማደራጀት ያሰበውን የሴቶች ማኅበር ለመመስረት ሲል የጣላቸው መሠረቶች ነበሩ በመሆኑም እነዚሀ ግለሰቦች እንጂ በብዙሃኑ ተማሪ የተደራጁ ማኅበራት ተወካዮች አልነበሩም ከኢተማሌ ውጪ ያሌት ሁለቱ ቡድኖች የጀብሃንና የኢትዮጵያ ብሔረሰቦችን ጥያቄ በሚመለከት አንድ አይነት አቋም የያዙ ናቸው የአዲሱ ኢተማሰአ እና የኢተማአኣን የአመራር ቦታ የያዙት አዞዎቹ ኢተአዓማን በአዲስ መልከ አዋቅረው ሁሉንም ስልጣን በአዞ የትግል ስልት ጠቀለሉት የአጠቃላዩና የብዙሃኑ የኢትዮጵያ ተማሪ ተወካይ ሆነው በድርጅት ስም ብቅ አሉ በመጨረሻ ለተሻሻለው ኢተዓአማ ምስረታ ጉባኤ ላይ ከተገኙ አምስት አባል ማኅበራትና ቡድኖች ማለትም አዲሱ ኢተማሰአ ኢተማአ የአልጀሪያ ቡድን ኢተማሌ እና ኢሴዓአጥክ ውስጥ በጉባኤው የምርጫ ሂደትና ውጤት የኢተማአንና የኢተማሌን ተወካዮች በምርጫ ስነስርዓት በማሸነፍ አዞዎቹ በእቅዳቸው መሠረት ራሳቸውን በኅብረት የኢትዮጵያ ተማሪዎች ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽን ኢተዓአፊ ብለው ሰይመው በአዲሰ መልክ መዋቀራቸውን ይፋ አደረጉ በፌዴሬሽኑ ምርጫ የተሸነፉት የቪኢተማአ እኖና የኢተማሌ ተወካዮችም የጉባኤውን ውጤት ውድቅ አድርገው ወደየማኅበራቸው ተመለሱ የኢትዮጵያ ተማሪዎች የአመፅ እንቅስቃሴ ሄዶ ሄዶ በአዞዎቹ ቁጥጥር ስር ሆኖ ኢተዓኣፌ ላይ ተወስኖ ቀረ በበርሊኑ ጉባኤ ያልተገኘው የአገር ውስጡ አአዩተማ ግን የፌዴሬሽኑ አካል ነበር ከዚህ በኋላ አዲሱና አሮጌው ኢተማሰአ ጠላትነታቸው ቀጠለ ስለዚህም በአብዮቱ ዋዜማ የኢትዮጵያ ተማሪዎች የፌዴሬሽን የኢተማአ እና የአሮጌው ኢተማሰአ አመራርና አባላት እርስ በርሳቸው ጎራ ለይተው በፖለቲካና በስልጣን ትግል ሲፋለሙ እንደቆዩ ሁሉም ባልጠበቁት ሁኔታና መንገድ ያሳበጡት አብዮት ሲፈነዳ ለሁሉም አስገራሚ ነበር የጃንሆይ መንግስት የተማሪዎችን አመፅ ለማስቆም የተለያዩ እርምጃዎችን ለመውሰድ ቢሞክርም ሙሉ ለሙሉ መገደብ አልተቻለም ይልቁንም የመንግስትን ተፅዕኖ መቋቋም ያልቻሉት ወደ ሌላ አገር እየተሰደዱ በውጭ አገር ያሉትን ማኅበራት እየተቀላቀሉ የየማኅበራቱን የሰው ኃይል እያጎለበቱ አመፁን አጠናክረው ቀጠሱ እንጂ ከስመው አልቀሩም መንግስት በ ዓም በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የግድያ ተግባር ከፈፀመ በኋላ የአገር ውስጡን ማኅበር ከነመጽሔቱ ሊያከስም ቢችልም ከመጠነኛ ፋታ ያለፈ ዘላቂ ውጤት ስላልተገኘ በ ዓም ንጉሠነገስቱ አልጋወራሹ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ የዘውድ አማካሪዎችና የካቢኔ ሚኒሰትሮች ተሰብስበው በተማሪዎች ጉዳይ ሳይ የሚያተኩር አዲሰ የስራ መመሪያ ቀርፀው በተግባር እንዲተረጎም አዘዙ ለዚሀም አንድ ከፍተኛ ኮሚቴ በአገር ግዛት ሚኒስትር ሰብሳቢነት ተቋቋመና የአገር መከላከያ ሜሂስትር የትምህርት ሚኒስትር የጦር ኃይሎች ኤታማር ሹም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የምድር ጦር ዋኖ አዛዥ የፖሊስ ሠራዊት ዋና አዛዥ የክቡር ዘበኛ ዋና ኣዛዥ የህዝብ ፀጥታ ጥበቃ ዋና ሹም የልዩ ካቢኔ ሹምና የዩንቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደ የኮሚቴው ተሳታፊ ሆነው የተማሪዎችን ፀጥታ ለማስከበር በሚል ተከታዩን ውሣኔ ኣሳለፉ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በየጊዜው እየተነሱ ትምህርት በማቆም በህዝብ ንብረትና ሀይወት ላይ አደጋ በማድረስ ትምህርት ቤቶችን በመስበር የትምህርት እድገት እንዲጨናጎል የልጆች እድል እንዲሰናከል ህዝብና የመንግስት ባለሥልጣን የሚዘልፍ ሕገወጥ ፖለቲካ አዘል የሆነ ልዩ ልዩ ጽሁፍ በመበተን ግርግርና ሽብር ኣድርገው ፀጥታ በመንሳታቸው ጉዳይ ግርማዊ ጃንሆይ ልዑል አልጋወራሽ ክቡር ጠቅላይ ሜኒስትር ክቡራን የዘውድ አማካሪዎችና የካቢኔ ሚኒስትሮች ባሉበት ስብሰባ ተደርጎ አጥፊ እንዲቀጣ ትምህርት የሚፈልግ እንዲማር ፀጥታው በአስራ አራቱም ጠቅላይ ግዛቶች በሚገባ እንዲከበር ተብሎ በተወሰነው መሠረት ከዚህ በላይ በተዘረዘሩት ባለስልጣኖች ስለተማሪዎች ፀጥታ ማስከበር ቀደም ብለው ስለተቋቋሙ ጉባዔው ስብሰባ አድርጎ ከዚህ ቀጥሎ በተመለከተው መሠረት እንዲፈፀም ዐወስኗል ውታሣሃሪኃ ማናቸውም የዩኒቨርሲቲ የኛ ደረጃና የግዛት ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንማራለን ካሉ ፀጥታ ነሾችን ለመከላከለ ፖሊስ ትምህርት ቤት ውስጥ ገብቶ እንዲጠብቅ ብጥብጥ ያስነሱ የተማሪ መሪዎች እንዲያዙና እንዲቀጡ ቅጣትም ከልማት ጋር የተያያዘ አድካሚ ስራ እንዲሆን አንማርም ብለው ከትምህርት ቤት የወጡት ተማሪዎች ዳግመኛ እንዳይገቡና እንደወጡ እንዲቀሩ ተማሪዎች በየጊዜው የሚያደርጉትን ሕገወጥ ስራ ህዝብና ወላጆች እንዲያውቁት በወላጆች ኮሚቴ በኩል በቴሌቪዥን በሬዲዮ በጋዜጣ በገዥዎች ጭምር ያለማቋረጥ እንደሚገባ እንዲገለፅ ሕገወጥ የሆኑ የዩንቨርሲቲ የኮሌጅና የኛ ደረጃ ተማሪዎች ማኅበር ጥፋታቸው በፖሊስና በፀጥታ በኩል ተጣርቶ ለዩኒቨርሲቲ ቦርድና ለትምህርት ሚኒስትር እያቀረቡ ማኅበሩ እንዲፈርስ ማድረግ ትዕዛዙን አክብረን እንማራለን ያሉ ተማሪዎች ጥቂትም ቢሆኑ ጥበቃ አየተደረገሳቸው እንዲማሩ በዚህ ቃለ ጉባዔ በቁጥር የተመለከቱና ከትምህርት ቤት ከወጡ በኋላ ጥፋታቸውን እየቀጠሉ የሚማሩትን እንዳይማሩ የሚያውኩ ለጥፋት ስራ የሚዘጋጁ ተማሪዎች ሲገኙ በኛው ዓመት በቁጥር በአንቀጽ በፊደል ሆ መጋቢት ቀን ዓም በወጣው ነጋሪት ጋዜጣና ይኸው ፀንቶ የሚቆይበትን ጊዜ በማስረዘም በኛው ዓመት ቁጥር በሇ ፊደል ታህሳስ ቀን ዓም በወጣው አዋጅ መሠረት ፖሊስ እየያዘ አስፈርዶ ቅጣታቸውን እንዲቀበሉ ያደርጋል አጥፊ ተማሪዎችን ፖሊስ እየሰበሰበ ብዛታቸው ከፍ ያለ እንደሆነ በፀጥታ ማስከበሪያ አዋጅ መሠረት ለአገር ግዛት አቅርቦና አስወስኖ ለጦር ሠራዊትና ለክብር ዘበኛ ያከፋፍላል ተማሪዎች በጥፋታቸው ሲቀጡ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ለሌሎችም ተማሪዎች የትምሀርት ሚኒስትር ለምግብኖ ለሌላ ወጪ የሚሰጠውን ገንዘብ ተማሪዎች ለተሰሩበት ክፍል ይከፍላል ከዩኒቨርሲቲና ከትምህርት ሜኒስትር የሜገኘው ተመላሽ ባይበቃ በተለየ ቀርቦ እንዲፈቀድ ይደረጋል እነዚህ ከዚህ በላይ የተመለከቱት ውሣኔዎች በአስራአራቱም ጠቅላይ ግዛቶች አውራጃዎችና ወረዳዎች እንዲሰሩባቸው ስለተወሰነ ክቡራን ጠቅላይ ገዥዎችና የጠቅላይ ግዛት እንደራሴዎች የጠቅላይ ግዛት ፖሊስና ዋና አዛኙች የክብር ዘበኛና የብሔራዋ ጦር አዛኙች የጠቅላይ ግዛቱ የችምህርት ስራ መሪ የአውራጃና የወረዳ ትምህርት ቤቶች ስራ መሪዎች በአገረገዥዎች ኃላፊነት እየተሰበሰቡ በኅብረት ፕላን በትእዛዝ እያወጡ ያፈፃፀሙን ውጤት በየጊዜው አንዲሰጡ ማድረግ ነው የሰብሳቢውና የአባሎች ፊርማ ያገር ግዛት ሚኒስትር ማሕተም አንድ የህዝብ አመፅ የተነሳበት መንግስት እንዲህ አይነት ውሣኔ ከማሳለፍ የተሻለ ምርጫ ይኖረዋል ብሎ ማሰብ ቢከብድም የወረዳና የአውራጃ ገዥዎች እንዲሁም ውሣኔውን ለማስፈፀም የተፈቀደላቸው ሹሞች ግን ከዚሀ ጠንካራ ውሣኔ ያለፈ ተጨማሪ በደል በየግዛቱ መፈፀም ጀመሩ የአመፁ ተባባሪ ያልሆኑ የተማሪ ወላጆችን በሌላ ቂም በቀል ተባባሪ ናቸው እነሳስተዋል እያሉ በመወንጀል ማሰር ማንገላታት መዝረፍ መግደል ሆነ ስራቸው በውሣኔው ደስተኛ ያልነበሩ ተማሪዎች መኖራቸው ሳያንስ ይህ መሰሌ ተደራቢ ሕገወጥ የሹማምንቱ ዝርፊያ በመጨመሩም የአውራጃና የወረዳ የኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እና መምህራን የየግዛቱን ጊጊ ሹማምንት ሕገወጥ አመፅ ቅጣትን ተቃውመው ወደ አደባባይ መውጣት ጀመሩ የከተማ ውስጡ ተመሳሳይ እርምጃም አመፁን የበለጠ የሚያጋግል እየሆነ ሄደ አጠቃላዩ የአመፅ እንቅስቃሴ ሁኔታ የሁሉንም የኀብረተሰብ ክፍል ትኩረት በመሳቡም ሁሌም የየራሱን ብሶት ይዞ ወደ አደባባይ እንዲወጣ የሚጋብዝ ነበር ይህ በእንዲህ እንዳለም የኢትዮጵያ መንግሰት ከዓለም ባንክ በተሰጠው የገንዘብ እርዳታ የውጭ አሇር የአገር ውስጥ የትምህርት ባለሙያዎችና የመንግስት ሠራተኞች በጋራ ሆነው ብዙሃኑ መምሀራን ባላወቀው መንገድ በሚስጥር አጥንተው ያቀረቡትና በ ም ሊተገበር የታሰበው አዲስ የትምሀርት ፖሊሲ በመምህራን ማኅበር ዘንድ እንደተሰማ ተጨማሪ ከፍተኛ ቁጣ አሰነሳ በ ባለሙያዎች ለሁለት ዓመታት ተጠንቶ የቀረበው አዲስ የትምህርት ፖሊሲ ሴክተር ሪቪው የተሰኘው ሲሆን ዓላማውም ከ ዓም ድረስ የነበረው የኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲ ተደራሽነቱ ኣጥጋቢ አልነበረምና ለሀዝቡ የሙያ ትምህርት በዝቅተኛ ደረጃ በስፋትና ብብዛት ማዳረስ ያስፈልጋል የሚል ነው ይህ ዓላማ ሊተገበር መሆኑን ዘግይተው የሰሙት መምሀራን ይህ አይነቱ ትምህርት አውሮፓውያን ለቅኝ ተገዥ አገራት ህዝቦች ያስተምሩት የነበረው ዝቅተኛ የሙያ ትምህርት ሰለሆነ እያስፈልግም በማለት የመንግስትን አቋም የሚያጣጥል የቅስቀሳ ዘመቻ ከፈቱ የዚህ ዘመቻ መሪ የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ኢመማ ሆነና እዲሱን የትምህርት ስርዓት በመቃወምና የደመወዝ ጭማሪ ጥያቄን በጥምረት በማንሳት አገዛዙን ተፈታተኑት የኛኖ የኛ ደረጃ ተማሪዎችም ከኢመማ ጎን ተሰለፉ በ ዓም የተመሠረተው የኢትዮጵያ መምህራን ኅብረት የመጀመሪያው የሙያ ማኅበር የነበረና በ ዓም በመንግስት ቭኝድ በይፋ ታውቆ የኢትዮጵያ መምሀራን ማኅበር ኢመማ የሚል ስያሜይዞ የቀጠለ ማኅበር ነው ጻሦ ኢመማ በብሔራዊ ደረጃ ከተደራጀ በኋላም እስከ ዓም ድረስ የአባላቱን ቁጥር እና የገንዘብ አቅሙን እያዳበረ ሄዶ በቱም ጠቅላይ ግዛቶች ቅርንጫፍ ማኅበራት ያሉት ግዙፍ ድርጅት ሆኖ ነበር የመምሀራን የመረዳጃ ድርጅት እስከመመሰረትም ደርሷል የአገሪቱን የፖለቲካ ጉዳይም በየዓመቱ በሚያካሂዱት ጉባዔ ላይ እያነሱ ሲወያዩበት ቆይተዋል ኢመማ በመስከረም ወር ዓም በአርባ ምንጭ ከተማ ባካሄደው በኛው ዓመታዊ መደበኛ ጉባዔ ላይየሴክተር ሪቪውን ጉዳይ ምጭዣ በመቃወምና የደመወዝ ጭማሪን በማመላከት ተወያይትው ያሳለፉት ውሣኔ ሣኀ የእያንዳንዱ መምህር ደመወዝ አስር በመቶ እንዲያድግ መምህራን ከስራቸው በጡረታ እስኪገለሉ ድረስ በደሞዛቸው እድገት የጣራ ወሰን እንዳይደረግ በደሞዝ ጭማሪ ጉዳይ ለቀረበው ጥያቄ መንግሰት እስከ ህዳር ቀን ዓም ድረስ ተገቢውን የስምምነት መልስ እንዲሰጥ የሚል ጠንካራ ጥያቄ ሲያቀርቡና ሲያሳስቡ የትምህርት ስርዓቱን በሚመለከት ደግሞ የስርዓተ ትምህርቱ ብሔራዊ ፍልስፍናው በቅድሚያ ሳይገለፅ የሰርዓተ ትምህርቱ ትምህርታዊ ጽሁፎችና መሣሪያዎች በደንብ ሳይዘጋጁ የግል ትምህርት ቤቶች በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት የሚሰሩ መሆናቸው በቅድሚያ ሳይታወቅ በአዲሱ ሰርዓተ ትምህርት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት እንዲከፈልበት መጠየቁ የማይገባ በመሆኑ እንዲሰረዝ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ለመምህራኑ የስራ ዋጋ የተመደበው ብር ካለው ሁኔታ ጋር የማይመጣጠን በመሆኑ እስኪለወጥ ድረሰ የስርዓተ ትምሀርቱን በሥራ ላይ መዋል በጥብቅ እንቃወማለን በማለት ኢመማ እሰጠነቀቀ መንግሰት የደሞዝ ጥያቄውን በሚመለከት በሀዳር ቀን ዓም የሰጠውን መልስ የኢመማ አመራርና እባላት ጥያቄያችን በከፊል እንጂ ሙሉ ለሙሉ ያልመለሰ ሆኖ ስላገኘነው ውድቅ አድርገናል አሉ ሲቀጥሉም ኸታሀሳስ እስከ የካቲት ድረስ ባሉት ሁለት ወራት ውስጥ ። ሐብተወልድ በድንገት የሰራ መልቀቂያ ደብዳቤ ሰጃንሆይ አቀረቡ ጃንሆይም የአክሊሉን ጥያቄ ተቀብለው ካቢኔውን አሰናበቱ የሁለተኛ ክፍለ ጦር አባላት በመጀመሪያው ቀን ያህል ጥያቄዎችን በሬዲዮ ለንጉሠ ሲገልፁ አንድም ፖለቲካዊ ጥያቄ አላቀረቡም ነበር ከደመወዝ ጀምሮ እስከጡረታ ወዘተ የሚያትቱ ብቻ ነበር ይህንንም እሽ ተብለው ሳለ በፍጥነት አገዛዙን የሚፈትን ከባድ ፖለቲካዊ ጥያቄ በማግስቱ ያስከተሉት ግን በጦሩ ብሶት ተከልለው የራሳቸውን ዙፋን የመንጠቅ የመተካት እቅድ የነበራቸው የንጉ የበታች ሹማምንት የሆኑ መሣፍንት ስለገፋፏቸው ነበር በአንድ በኩል የግራ ክንፎች ሹማምንት ስር ነቀል ለውጥ የሚፈልጉ በሌላ በኩል የቀኝ ክንፎች ጃንሆይን ከስልጣን አውርደው ሌላ ንጉሥ ለመተካት የሚያሰቡት ናቸው የጦሩ ኣመፅ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከፈለጉት መሣፍንት ውስጥ ዋናው አስተባባሪ ቀደም ሲል የኤርትራ ጠቅላይ ግዛት እንደራሴ የነበሩት ልዑል ራስ አስራት ካሣ ነበሩ ምሰክርነት ዓም የጦሩን ቅፅበታዊ የጥያቄ ለውጥና የጥያቄዎችን ይዘትና ጥልቀት የመረመሩ ምሁራንም የመሳፍንቱ ግፊት እንደነበረበት ያምናሉ ይህ የውስጥ ለውስጥ የመሳፍንቱ የፖለቲካ ደባም ጠቅላይ ሚኒስትር አከሲሉ ሐብተወልድ ስልጣን ሲለቁ በምትካቸው ልጅ እንዳልካቸው መኮንን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው እንዲሾሙና አዲሱ ካቢኔ ተቋቁሞ አዲስ ሹም ሽር ተደርጎ አዳዲስ ሚኒስትሮች በየካቲት ማለቂያ ከጃንሆይ ፊት ቀርባው ቃለመሀላ ፈጽመው ስራቸውን እንዲጀምሩ አድርጓል ምንም እንኳን ጃንሆይ ከዚህ ሹም ሽር በፊት ጄኔራል አብይ አበበን አዲስ ካቢኔ እንዲመሰርት አዘውት የነበረ ቢሆንም የጄኔራል አቢይ ካቢኔ ገና ሳይመሠረት ተቃውሞ ስለገጠመው እንዲቀር ሆኗል በመሆኑም የልጅ እንዳልካቸው መኮንን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ መሾም በመሳፍንቱና በመኳንንቱ መካከል የነበረው የስልጣን ትግል መሳፍንቱ አሸንፈው በድል የተወጡበት ሆኖ ታዬ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሐብተወልድ ከመሳፍንት ወገን ያልሆኑና ከታችኛው መደብ የተገኙ ነበሩና ሆኖም ልጅ እንዳልካቸው ከልዑል ራስ አስራተ ካሣ ጋር ሽርክ ነው የሚለው ጉዳይ መሣፍንቱን ረፍት ሊሰጣቸው አልቻለም በሌላ በኩልም የእነ ልዑል አስራተ ካሣ ተቀናቃኝ ሆነው በጦሩ ብሶት የራሳቸውን የስልጣን ጥም ለማርካት የሚሻኮቱት በአዲሱ ካቢኔ የግቢ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት የጃንሆይ የረጅም ጊዜ ታማኝ አገልጋይ ደጃዝማች ከበደ ተሠማ ነበሩ ከመኳንንት ወገን ደጃዝማች ከበደ ከመሳፍንት ወገን ልዑል ራሰ አስራተ ካሣ ሆነው የስልጣን ገመድ ሲጓተቱ ፍፁም እምነት የጣሉባቸውንና ለረጅም ዓመታት ያገለገሏቸውን ያልበደሏቸውን የጃንሆይን ጉዳይ እርግፍ አድርገው ትተዋል በዚህ መካከል የህዝቡ አመፅ ጋብ ሊል ቀርቶ ይብሱኑ ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም እየተባለ ተባብሶ ቀጥሷል ድምፁ ተሰምቶ የማያውቀው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበር ኮንፌዴሬሽን ውጤታማ የተባለውን ለተከታታይ አራት ቀናት የቆየ አጠቃላይ የስራ ማቆም አድማ አደረገ ጥያቄያቸውም የሠራተኛና አሠሪ ሕግ እንዲደነገግና በነፃነት የመደራጀት መብት እንዲከበር እንዲሁም ደሞዝ እንዲጨመር የሚል ነበር አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ፋታ ይሰጠኝ ሁሉንም ነገር አስተካክላለሁ ቢሉም ሰሚ አጡ ተዋከቡ አዲሱ ካቢኔ ግን ተገቢ ስራዎችን በፍጥነት እያከናወነ ነበር ለምሳሌ ካቢኔው ስራ በጀመረ በቀኖት ውስጥ በጃንሆይ ትዕዛዝ ሕገመንግስቱን ለማሻሻል እቅድ ነደፈ በመጋቢት ወር መጀመሪያ የመንግስት ሹማምንትን አለአግባብ መበልፀግ አጣርቶ ለፍርድ የሚያቀርብ የምርመራ ኮሚሻን ተቋቋመ ቀጥሎ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ችግሮችን የሚያብራራና ወደመፍትሄው የሚያደርሰውን መንገድ የሚያሳየውን የእንግሊዝ አገር ፖሊሲን የተከተለውን ኋይት ፔፕር ጭ ሠነድ የተሰኘውን መመሪያ ይፋ አደረገ ነገር ግን ጅብ ከሂደ ውሻ ጮኸ ተብሎ ተጮኸ እነዚያን የመሳሰሉ ወሣኝ ወሳኝ ተግባራት የሚያዩ ኢትዮጵያዊ ዓይኖች የሉም ረፍዷል በዚያም ሳላይ የካቢኔው ሹማምንት የዚያው አዝዛዝ ባለሥልጣን የነበሩ ስለሆኑ ከስራቸው ይልቅ የቀድሞ ታሪካቸው ነውና የሚታየው ስር ነቀል ለውጥ ለሚፈልግ ህዝብ ትኩረት ቢነፈጋቸው አይገርምም ተቃውሞው ሄዶ ሄዶ ሚያዚያ ቀን ከመቶ ሺ በላይ የሚገመት ህዝብ የተሳተፈበት ግዙፍ ሠላማዊ ሰልፍ ተካሄሂደ በእለቱ የወጣው ህዝብ ከሁሉም ዓይነት የኅብረተሰብ ክፍል የተውጣጣ ሲሆን የቤተክህነትኖ የቤተመንግስት ቁርኝት እንዲቀር ከመጠየቅ ጀምሮ ባለሥልጣናትን በየቢሮአቸው እየቆለፉ ለቀናት ታሽገው እንዲቆዩ እስከማድረግ የደረሰ ነበር ይህን ህዝባዊ ማዕበል መግታት የማይሞከር ሆነ ያልተነሳ ጥያቄ አለ ማለት አይቻልም በአጭሩ ሁሉንም ጥያቄዎች መመለስ ማለት ንጉሣዊ አገዛዙ ያብቃ የሚል የማያሻማ ትርጉም ያለው መሆኑ ግልፅ ር አዲሱ ካቢኔ ግራ ሲጋባ በሚያዚያ ብሔራዊ የፀጥታ ኮሚሽን አቋቁሞ ሰላምና ኃይልን ያጣመረ የአመፅ መግቻ ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ ሠራዊቱን ከካቢኔው ጎን ለማሰለፍ ሞከረ ይሀም ያስገኘው ውጤት የቀድሞው ካቢኔ ሚኒስትሮችንና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናትን በሌላ አገላለፅ የልጅ እንዳልካቸውን ተቃዋሚዎች በኮሎኔል ዓለምዘውድ ተሠማ አማካኝነት በኮሚቴው ውስጥ የመሪነት ሰልጣን ተሰጥቶት ስለነበር በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረግን ቶ ነበርልጅ እንዳልካቸው በስተመጨረሻ ራሳቸውም ሳይቀርላቸው በዙሪያቸው የነበሩ ተቃዋሚዎቻቸውን ሲያስለቅሙም የጃንሆይን ፈቃድ በመጠየቅ የነበረ ሲሆን ንጉሥም ይሁን ብያለሁ ባይ ነበሩ ከየካቲት ወር ጀምሮ እስከ ግንቦት ድረስ በነበረው ጊዜ የጦር ሠራዊቱ ጥያቄ በተለይም የደሞዝ ጭማሪው ተደርጎለት ጥያቄዎቹም ተመልሰውለት ነበርና ስቪሉ ኅብረተሰብ ወታደሩ የራሱን ጥቅም ብቻ አስከብሮ የህዝቡን እሮሮ አያገባኝም ያለ ከሃዲ ነው እየተባለ መወረፍ ጀመረ የዚህ ትችት አሰራጮች ለውጥ ፈሳጊ ነን ያሉ ምሁራን ናቸው በዚህም መለዮ ለባሹን ሳላላሰበውና ላልፈለገው ስልጣን መንገድ ጠረጉሉለት ከምሁራኑ ባለፈም ቀደም ሲል ያየናቸው የግራና የቀኝ የቀድሞ የጃንሆይ ታማኝ ሹማምንት ውሻ በቀደደው ጅብ ይገባልን መርህ አድርገው በወታደሩ አመፅ ሳቢያ ጃንሆይ ሲወርዱ ለመተካት አሰፍስፈውና የየራሳቸውን ስልጣን የመያዝ እቅድ ከግብ ለማድረስ ሲሉ አመፁ እንዲቀጣጠል እንጂ እንዲረግብ የወሰዱት ይህ ነው የሚባል ቀና እርምጃ አልነበረም እውነታውን እያወቁትም ለጃንሆይ አይዞዎት ህዝቡም ጦሩም ለኣርስዎ ያለው ታማኝነት ጽኑ ነው የጠሳው አንዳንድ ባለሥልጣናትን ነው እነዚያ ባለሥልጣናት ከተሻሩ አመፁ ይቆማል እያሉ ይደልሏቸው ነበር በተለይ የግቢ ሚሜኒስትሩ ደጃዝማች ከበደ ተሰማ ታማኝም ስለነበሩ ለዚህ መሰሉ የማዘናጋት ተግባር በብርቱ ጥረዋል ምሁራኑም ሆኑ መሣፍንቱ እንዲሁም መኳንንቱ በመለዮ ለባሹ ትግል ስልጣን ለመያዝ ሲያቅዱ ራሱ ጦሩ ስልጣኑን ቢይዘውስ። የሚል ነበርና ውይይቱ ቀጥሎ የጦሩ ሙሉ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ የጦሩን አባላት አስተባብሮ ለመምራት ደግሞ የግድ መኮንን የሆነ መሪ እንደሚሻል ነገር ግን ከፍተኛ መኮንን እንደማያስፈልግና ማዕረጉ ከሻለቃ መብለጥ እንደሌለበት ተሰማሙ ምክንያቱም ከፍተኛ መኮንኖች መሪ ከሆኑ የራሳቸውን ጥቅም አሰከብረው የበታቹን ጥያቄ ቀብረው ያስቀሩት ስለነበር ነው ከሻለቃ መብለጥ የሰበትም የተባለው በውሣኔው መሠረት ሻለቃ አጥናፉ አባተ የሰብሰባው መሪ ሃምሳ አለቃ አበራ አጋ ከፖሊስ ሠራዊት ጁኔር ቴክኒሸያን ዮሐንስ ፍትዊ ከምድር ጦር አቪዬሽን ለኮሚቴው አባልነት ተሰየሙና ተሰብሳቢዎቹ በሻለቃ አጥናፉ መሪነት ወደ ስብሰባ አዳራሽ ግ ወሩ ይህ ሦስተኛው ኮሚቴ የመጨረሻው መጀመሪ በእለቱ ከተሰብሳቢዎች ውስጥ ብዙዎቹ የኛ ክፍለ ጦር እኑ ለሉ እንዲቀነሱ ተደረገ በስብሰባው የተለያዩ ሀሳቦችን እያነሱ እየጣሉ ቆይተው በመጨረሻ የደረሱበት ውሣኔ ግ የምድር ጦር ልዩ ልዩ ክፍሎች የአየርና ባህር ኃይል እንዲሁም የፖሊስ ሠራዊት የየራሳቸውን ወኪል መርጠው እንዲልኩ በአዲስ አበባ ያሉት የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁልፍ ቦታዎችን በጦሩ እንዲጠበቁ ማድረን የስጋት ምንጭ ይሆናሉ ተብለው የሚገመቱ የሲቪልና የጦር ረረ አለቆችን በቁጥጥር ስል ማዋል ለመለዮ ለባሹ ሁሉ ለተጀመረው አንቅስቃሴ ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ ማቅረብ በተለይ ለኮሚቴው አባልነት አዲስ ኣአበባ አሰመራና ሐረር ከሚገኙ ልዩ ልዩ የጦር ክፍሎች ማስመረጥና ማሳተፍ የሚሉ ሲሆን ተወካዮች ከተላኩላቸው በኋላም ሁኔታዎችን የሚከታተል የሚያስተባብርና ድጋፍ የሚያሰባሰብ ለንጉሠ ታማኝነትን የሚገልፅ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ተወያይተው ተስማሙ እነዚህ በኛ ክፍለ ጦር የተሰባሰቡት መለዮ ለባሾች በምርጫ ያልተወከሉ የመጀመሪያ የደርግ አንቀሳቃሾች ናቸው እነዚህን እቅዶች መርጠው ያስቀመጡትና በፍጥነትም በተግባር እንዲተረጎም ያደረጉት ሻለቃ አጥናፉ አባተ ሲሆኑከመኮንንነታቸው ባለፈ በአዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ ቢዝነስ አድሚንስትሬሽን ተምረዋል የዚያኑ ፅለት ምሽት ሁለት ሠዓት ከኛ ክፍለ ጦር በተውጣጡ ወታደሮች ኣቡነ ጴጥሮስ ሐውልት አጠገብ ይገኝ የነበረውን የኢትዮጵያ ሬዲዮ ጣቢያ ማዘጋጃ ቤት ህንፃ ውስጥ የሚገኘውን የቴሌቪዥ ማሰራጫ ጣቢያ ጌጃ ሠፈር የሚገኘውን የብስራተወንፄጌል ሬዲዮ ጣቢያ የቴሌኮሙኒኬሽንን መስሪያ ቤት የመብራትና የውሃ አገልግሎት ማሰራጫዎችንና የአዲስ አበባ ከተማ መግቢያ መውጫ መንገዶችን በወታደር ጥበቃ ስር እንዲሆኑ አደረጉ ለዚህም ከሻለቃ አጥናፉ ጋር የፖሊስ ሠራዊት አባሉ ሻለቃ እንየው ፈረደ ለደርግ ምስረታ አስተዋፅኦ ቢያደርጉም ሻለቃ ፈረደ የደርግ አባል ግን አልሆኑም ጦሩን በማንቀሳቀስና ለጥበቃ በመመደብ ተባብረዋል ለመገናኛ ብዙሃኑም ሻለቃ አጥናፉ ከምሸቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ ኛ ክፍለ ጦር ከተመሠረተው ኮሚቴ የሚሰጠውን ትዕዛዝ መፈፀም ተግባራቸው መሆኑን ለተረኛ ሹሞች ገለፁ ወቅቱ ወታደራዊ ዲሲፒሊንም ሆነ የአዛዥና ታዛ ግንኙነት ቅጥ ያጣበት ነበርና እቅዱን ለማሳካት እንቅፋት አልነበረም በመሆኑም ጦሩ በመስክ ሬዲዮ ያለገደብ አየተገናኘ መልዕክት እንደልቡ ይሰዋወጥ ነበር በኮሚቶው እቅድ መሠረትም በአገሪቱ ካሉት ያህል ልዩ ልዩ የጦር ክፍሎች ኣባላት መርጠውና ወክለው ወደ አዲስ አበባ ኛ ክፍለ ጦር ጠቅላይ መምሪያ ጊቢ እንዲልኩ መልዕክት ደረሳቸው ከአራቱም ክፍለ ጦሮችና በክፍለ ጦሩ ስር ካሉ ልዩ ልዩ ክፍሎች ፖሊስ ሠራዊትን ጨምሮ ተመርጠው የተላኩ አባላት ፈጥነው ደረሱ ገሚሱ ሂድ እስቲ የሚባለውን ስማ ተብሎ የመጣ ነበር እንጂ ለጉዳዩ ብዙዎች ትኩረት የሰጡ ኣልነበሩም ብቻ ግን እንቅስቃሴው ሂደቱን ቀጥሎ ወደ ስኬት እያመራ ነው ነገር ግን የደርግ አባላቱ በመጀመሪያ ተጠራርተው በኛ ክፍለ ጦር ሲሰበሰቡ ሹፌሩም ምኑም ተጠራቅሞ ስለነበር ነበሩ ቆይቶ ሻለቃ መንግስቱ ሰብሳቢ ሆነው ከተመረጡ በኋሳ የየክፍሉ ተወካይ አባላት በአግባቡ ሰም ሦ ዝርዝርራቸው እንዲመዘገብ ስለተደረገ ዎቹ ወደየክፍላቸው እንዲመለሱ ተደርጐ ሆኑ ሆኖም ቀስ በቀስ በመኪና አደጋ ከሞተው አንድ አባል በስተቀር ያህሉ ገና ከጅምሩ መዝረፍ መስከር ቁማር መጫወት አስገድዶ መድፈር በሆነ ባልሆነው ታሳሪዎችን በእሳት እየለበለቡ በማሰቃየትና በሌሎች ወንጀሎች የደርግን ስም እያከፉት በመሄዳቸው የተገደሉ ናቸው ምስክርነት ዓም በመሆኑም አባሳት ረዥም ጉኮዞ ተጉዘዋል በሻለቃ አጥናፉ የሚመራው አስተባባሪ ኮሚቴ ሰኔ ቀን በኛ ክፍለ ጦር ጊቢ ውስጥ መቋቋሙን ዘሬዲዮ ይፋ አደረገ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ስብሰባዎች መካሄድ ቢጀምሩም አባላቱ ተጠቃለው ለመግባት የቀኖት እድሜ ወስዶባቸዋል እነዚህ በጥሪ የመጡ አባላት አብረዋቸው ከመጡ ኣባላት ውጪ ኣይተዋወቁም ለምን እንደመጡ ኣላማቸው ምን እንደሆነ በውል የተረዱ አልነበሩም ሰብሳቢው ሻለቃ አጥናፉ ስብሰባውን ሲከፍቱ በጦሩ ውስጥ ስላለው ያስተዳደር ጉድለት በሰልጣን የባለጉ ሹሞች መበርከታቸው ስልጣንን ተገን አድርገው በሙስና የተሰማሩ በዝባኾች አገሪቱን እያራቆቷት እንደሆነ መተንተን ጀመሩ ተሰብሳቢውም አገዛዙን እየወነጀለ የመሰለውን ይናገራል ምን መደረግ አለበት። ገ በማለት ተንበርክከው የጠየቁት ሰዎችን አልነበረም ኢትዮጵያን አእንጂ ኢትዮጵያ ምን መለሰች ብሎ መጠየቅ ሳይገባ ስራቸው ራሱ መልስ እየሰጠ ይገኛል በጃሦይ ፓርላማ እየተሰበሰብን በጃንሆይ ቴአትር ቤት እየተዝናናን በጃሻንሆይን ስታዲየም እየተጫወትን በጃንሆይ ዘመን የፍትሐብሔር ሕግ እየተዳኘን በጃንሆይ ብዙ ነገር እየተጠቀምን መሆኖችን ማሰቡ ብቻ መልስ ይሆነናል ለማለት ነው ምዕራፍ መናዝርሯጀ መጋ ዱ መስከረም ቀን ዓም አብዮቱ ከፈነዳ በኋላ ኢትዮጵያ በሊቀመናብርቱ ተመርታለች በመጀመሪያ ጄኔራል አማን ሚካኤል አንዶም ለሁለት ወራት ሊቀመንበር ሆነው ቆይተው በመንግስቱ ትዕዛዝ ከተገደሉ በኋላ ቀጥሎ ብርጋዴል ጄኔራል ተፈሪ በንቲ ለሁለት ዓመታት ያህል የሊቀመንበርነቱ ቦታ ተሰጥቷቸው መርተዋል እሳቸውንም ደርግ ገደለና ተተኪው ቫለቃ መንግስቱ ሆኑ እነዚህ ሁለት ጄኔራሎች በጦሩ ዘንድ ተቀባይነት ለማስገኘት ሲባል በሽፋንነት ከፊት እንዲቀድሙ የተደረጉ ይሁኑ እንጂ ከበስተጀርባ መንግስቱ ነበሩ የደርጉ መረ ጄኔራሎቹ የደርግ አባላት አልነበሩም የቀሩት የደርግ መስራች ሻለቃ አጥናፉም ተፈሪ ባንቲ በተገደሉ ማግስት ተወግደው መንጌ ብቸኛው ሊቀመንበር ሆነው ዘልቀዋል ደርግ ንጉሣዊ አገዛዙን አስወግዶ የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ብሎ ራሱን ሰየመ የመጀመሪያ ስራውም አዲሱን ሕገ መንግስት ማገድ ፓርላማውን መበተንና ማናቸውንም አይነት ሠላማዊ ሰልፍንና የስራ ማቆም አድማን መከልከል ነበር ኢትዮጵያ ትቅደም የሚለውን መርህ መቃወም የዘመኑ ቁጥር አንድ ወንጀል ሆነ የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ መቋቋም ወዲያው ነበር ተቃውሞ የገጠመው በዋናነት የተማሪዎች ቡድን ቀጥሎ ፎረም በመባል የሚታወቀው ግራ ዘመም የሆነው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ቡድን እንዲሁም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሲሆኑ እነዚህም ዴሞክራሲያ እና የሠፊው ህዝብ ድምፅ በተባሉ መጽሔቶች ዙሪያ ተሰባስበው የግራ ክንፍ ድርጅቶች ሆነው ተቃወሙ ከወታደሩ በኩል ደግሞ የክቡር ዘበኛና የወታደር የበረራ ክፍል አርሚ አቪየሽን እንዲሁም የመሐንዲስ ክፍል ተቃዋሚ ሆነው ቀረቡ የተቃውሞ መነሻቸውም የጊዜያዊ ህዝባዊ መንግስት ነው መቋቋም ያለበት የሚል ነው ይህንንም ቀደም ካለው የደርግ ምስረታ ጊዜ ጀምሮ በተለይ የመምህራን ቡድን ለደርግ ያቀርቡት የነበረ ሀሳብ ነው ያን ጊዜ ዝዝዝባዊ መንግስት ይቋቋም ሲሉ ቢቆዩም አሁን ከባድ እንደሚሆን ስለተረዱ ጊዜያዊ ህዝባዊ መንግስት በሚል አሻሻሉት ሆኖም የዚህ መፈከር ደጋፊዎች አቋማቸው አንድ ይሁን እንጂ በአመሠራረቱ ላይ የሚያቀርቡት ኣጀንዳ የተለያየ ነበር ከፊሉ ሰራተኞች ከተማሪዎች ከመምሀራንና ገበሬዎች የሚውጣጣ መንግስት ይሁን ሲሉ የቀሩት ጥየካቲቱ ህዝባዊ ንቅናቄ ባፈራቸው ኮሚቴዎችና ድርጅቶች ላይ ይመስረት ይላሉ ይህ የጊዜያዊ ህዝባዊ መንግስት መፈክር አተገባበር ጉዳይም በዴሞክራሲያ እና የሰፊው ህዝብ ድምፅ በተሰኙ የፕሬስ ውጤቶች ዙሪያ የተደራጁትን የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ፓርቲ ኢሕኣፓን እና ጥመላ ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ መኢሶንን ወደፊት የምኖያቸውን የእርስ በርሰ የስልጣን ፍልሚያ ሊፈጥር ችሏል በአብዮቱ ወቅት በአገር ቤት የሰፊው ሀዝብ ድምፅ ሳይ በቀረበ ትንቢታዊ ትንታኔ ወታደራዊ መንግስት ምን ቅን ልቦና ቢኖረው አገሪቱን በአንድ አንባገነን መሪ መዳፍ ስር ይጥላታል የሚል አቋም የያዘ ጽሁፍ ቢሰነዝርም ይህ የመኢሶን አቋም ከአገር ውጪ ካለው የመኢሶን አመራር ጋር የሚጣጣም አልሆነም ምክንያቱም ሰፊውን ህዝብ ለማደራጀት ጊዜ ሰለሚያሰፈልግ ስልጣኑ በወታደሩ እጅ እንዲቆይለት የውጭ አገሩ ቡድን ይፈልግ ስለነበር ነው ከዚህም በላይ ኢህአፓ በብዙሃን ድርጅቶች በመምህራን በተማሪዎችና በሠራተኛው ዘንድ ቀድሞ መስረፅ ችሏልና የሚቋቋመውን ጊዜያዊ ህዝባዊ መንግስት እረከባለሁ ብሎ ያሰብ ስለነበርና መኢሶን ገና ይቀረው ስለነበር ወታደሩን ጊዜ መግዣ ሊያደርግ ሽቶታል የመኢሶን የውጭ ቡድን አገር ቤት ከገባ በኋላም ከኢህአፓ ጋር ቢፎካከር ውጤት አልባ እንደሚሆን ስለተረዳው ያን የጋራ መፈክር ጥሎ የአገርቤቱን አጋሩንም አሰጥሎ ከደርግ ጋር ተንጠላጥሎ ተለጥፎ ስልጣን መያዙን መርጧል የኢህእፓና የመኢሶን የጦፈ ክርክር ማርክሳዊ ጭብጥነቱ አንድ ስለሆነ ፉክክሩ ለርዕዮቱ እኔ ታማኝ ነኝ ሲል አንዱ ሌሳው እኔ የበለጠ ታማኝ ነኝ የሚል እንጂ የርዕዮት ልዩነት የላቸውም ከዚህ አንፃር ፉክክሩ የስልጣንና የስልጣን ብቻ ተብሎ ይደመደማል ደርግ ግን እንኳን ስልጣን አስረክቦ ወደ ካምፕ ለመመለስ ለማጋራት እንኳ የፈለገ አይመስልም እርግጥ ነው ደርግ ስደት ላይ ያሉትን ቀደምት የአመፅ አንቀሳቃሽ የነበሩ ምሁራንንና ማኅበራቱን ከአውሮፓም ከአሜሪካም ለሁሉም ጥሪ አቅርቧል ነገር ግን ምሁራኑን አስቀድሞ ሲጋብዝ ስልጣን ለመልቀቅ ሳይሆን ያሰብ የነበረውበምን መልኩ ተጠቅሜባቸው ነው ስልጣኔን የማጠናክርባቸው። መንጌሾ ሲል ጮኽ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀመናብርቱ በአደባባይ ታዩ መንግስቱም ሳንቃው እስኪሰነጠቅ ስማቸውን እየጠራ ለደቂቃዎች ያህል የቆየውን ህዝብ ሲያዩ ልዩ ሰሜት ተሰማቸው ደርግ የጋራ ውሣኔ አሳልፎ ያንን ግድያ ከፈፀመ በኋላ ሰልጣን አስረክቦ ወደ ካምፕ መመለስ ማለት እራስን ለፍርድ ማቅረብ መሆኑን ያውቃል እንኳን ይህ ምክንያት ኖሮ ባይኖር እንኳ ሰልጣን አስረከቦ የመመለስ እቅድ አልነበረውም ስለዚህ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስትነቱን ትቶ ቋሚነቱን አጠናክሮ ከመቀጠል ሌሳ ምርጫ ስላልነበረው በተቻለ መጠን የምሁራኑን ሀሳብ የራሱ አድርጎ ወደተግባር መተርጎምና አገሪቱን መምራት ነበረበት ጊዜያዊ መንግስትነቱን ግን ለሻፋንም ቢሆን አልቀየረም እናም ደርግ ርዕዮቱን ሶሻሊዝም አድርጎ መጨ ሳይውል ሳያድር የገጠሩን ህይወት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመቀየር የነደፈውን እቅድ ተግባራዊ አድርጓል ይህ ብሔራዊ የእድገት በኅብረት ዘመቻ ዓላማው የሁለተኛ ደረጃና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችንና መምህራንን ወደ ገጠር በማዝመት የኢትዮጵያ ትቅደምን መርህ መሠረት ያደረጉ የልማት እንቅስቃሴዎችን እንዲመሩ ማድረግ ነው እቅዱ በትክክለኛ ሚዛን ሲቀመጥ ኢትዮጵያን ከኋላቀርነት ለማውጣት የሚረዳና በተለይም በተማረው ክፍል የምክር የትምህርትና የጉልበት ድጋፍ የገበሬው ህይወት የተሻለ እንዲሆን የሚያደርግ ነበር ይህን በመረዳትም ነው ብዙሃኑ ምሁራን በደስታ የተቀበሉትና የዘመቱት ሆኖም የደርግ የስልጣን ተፋላሚ የሆነው ኢህአፓ ብቻ የእቅዱ ተቃዋሚ ሆነ ምክንያቱንም ሲያስቀምጥ የተማረውን ክፍል በልማት ስም ወደ ገጠሩ በማግለል ደርግ ብቻውን በስልጣን ላይ ለመደላደል ሲል የነደፈው በማለት ነው ኢህአፓ ሰሚ አላገኘም ዘማቾቹ የድጋፍ ሰልፋቸውን ካሳዩ በኋላ ወደ ገጠር ዘመቱ የገጠሩን ህይወት የመለወጡን ተግባርም ተያያዙት ች ተግባራቸውን ሲወጡ ደርግ የግራ ኃይሎችን ተቃውሞ ወዲያው ለማለዘብ የኢትዮጵያ ትቅደምን መርህ በመከለስ ዓላማችን ኅብረተሰባዊነት ርዕዮታችን ሶሻሊዝም ነው ቢልም ብቸኛ ዓላማቸው ስልጣን ብቻ የነበረው ተቃዋሚዎች ኢህአፓዎች ሊሰሙት አልቻሉም ደርግ እያራመደ ያለው የኢህአፓንናኖ የመኢሶንን ማኑፌስቶ ነው መኢሶን ከደርግ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን ተለጥፎ የነበረ ሲሆን ኢህአፓ በውጭ ሆኖ ነበር የሚሞግተው ደርግም ከመኢሶን መስራች ምሁራን በሚቀበለው እቅድ ስራውን ቀጥሷል የንግድ የኢንደሰትሪና የገንዘብ ተቋማትንም ደርግ ወርሷል ይህ በእንዲሀ እንዳለ የካቲት ቀን ዓም የጃንሆይ ተቃዋሚ የነበሩ ምሁራን ለዘመናት ሲያቀነቅኑት የኖሩትና በጉጉት ይጠብቁት የነበረውን የመሬት ስሪት ኣዋጅ ደርግ ይፋ አደረገ ይሀም ብዙዎቹን ያስፈነደቀ አዋጅ ሆነና በተለይ የገጠሩን ህይወት በመለወጡ ተግባር የተሰማሩትን ዘማቾች የበለጠ በደስታ እንዲሰሩ አደረጋቸው ይህ የመሬት ጉዳይ የጃንሆይን መንግስት ለመገልበጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የሞከሩት የእነመንግስቱ ንዋይ ማኑፌስቶ ውስጥ የተካተተ ነበር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሬት ላራሹ እያሉ የሞቱለት ነበር የመጨረሻው የእንደልካቸው ካቢኔም ትኩረት ሰጥቶ እልባት ሊሰጠው ስራ የጀመረበት ሁኔታ ነበር በመጨረሻ ደርግ እልባት ሲሰጠው የሚኖረውን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ መገመት አይከብድም ለዚህም ነው ሀዝቡ የተለያዩ የድጋፍ መፈክሮችን ይዞ በአደባባይ ደስታውን የገለፀው የካቲት የሰፊው ህዝብ የልደት ቀን ነውኛ ኢትዮጳያ ትንሳኤ ልደት ዛሬ ነው የሚሌ መፈክሮች በደማቁ ህዝባዊ የድጋፍ ሠላማዊ ሰልፍ ሳይ ተነበዋል የየካቲት ቱ እዋጅ በታሪካዊቷ ኢትዮጵያ የመሬት ጥያቄ ጉዳይ ወደር ያልተገኘለት የተሰኘውን ምላሽ ደርግ በመስጠቱ አክራሪ የግራ ክንፍ ተቃዋሚዎችን ሳይቀር ኩምሽሽ ያደረገና የሚቃወሙበትን ነጥብ ያሳጣ ነበር አዋጁ የግል የመሬት ይዞታን የሚያስወግድና የገጠር መሬት የማይሸጥ በሊዝ የማይተላለፍ በዋስትና መያዣነት የማይያዝ ገበሬው በምርት ተግባር ላይ ብም ሊያውለው የሚችል የግል ንብረቱ ሆነ አዋጁ የመሬት ይዞታን በአስር ሔከታር ሲወስን ከዚያ የተረፈውንም ቀድሞ በሰው መሬት ላይ በጉልበቱ ያገለግል ለነበረው መሬት አልባ ጭሰኛ በመስጠት መሬት ኣልባውን ባለመሬት ያደረገ ሆነ ው ፍን ዛፉ ማጨ የመሬት አዋጁን ደግፈው ሰልፍ የወጡ ዜጎች ለአዋጁ ተግባራዊነትና ስኬታማነት እንዲሁም ዘላቂነት ይረዳ ዘንድም እንደአስፈላጊነቱ የመሬት ድልድል የማድረግ ስልጣን ያላቸውን የገበሬዎች ማኅበር አቋቋመ የመሬት ላራሹን ጥያቄ የመለሰው ታሪካዊው አዋጅ የቀድሞዎቹን የመሬት ከበርቴዎች ፍትሐዊ በሆነ መንገድ የሚገባቸውን ጣራ አስተርፎሳቸው ሌላውን ወስዶ ለጭሰኞችና ለመሬት አልባዎች ሲሰጥ በተለይ ከአፄ ምኒልክ ጀምሮ እስከ አፄ ኃይለሰላሴ ዘመን ድረስ ለሹማምንቱ ይሰጥ የነበረው የመሬት ስጦታ በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍል ነበርና በርካታ ጭሰኞችም የነበሩት በዚያ ክልል ስለሆነ በከፍተኛ የደስታ ስሜት ተውጠውእስከመጨረሻው የደርግ ደጋፊዎች ሆነው ሲቀጥሌ በተቃራኒው የመሬት ከበርቴ ሆነው ለዘመናት የቆዩት የሰሜኑ ክፍል ሹማምንት ግን የደርግ ተቃዋሚ ሆነው ዘለቁ በስተመጨረሻም ፖለቲካዊ ጥያቄ ይዘው ቀድመው የትጥቅ ትግል የጀመሩትን ቡድኖች መቀሳቀል ጀመሩ መዝመት ያልቻሉትም ድጋፍ ማድረጋቸውን ቀጠሉ ደርግ እነዚህን አዋጆች በተግባር ላይ ካዋለ ከጥቂት ወራት በኋላ ሐምሌ ቀን ዓም ደግሞ የከተማ መሬትንና ትርፍ ቤቶችን የመንግስት ያደረገውን አዋጅ አወጀ ይህ አዋጅም የንብረተሰባዊነትን መርህ መሠረት ያደረገ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፍትህን ለማስፈን የዜጎችን እኩልነት ለማምጣት የተወሰደ የደርግ ቅን እርምጃ ነበር የቀድሞዎቹ ንቅዝ ሹማምንት ከሕግ ውጪም ሆነ በሕጋዊ መንገድ ካግበሰበሱት ከገጠር መሬት ባለፈ በከተማውም ቦታና ቤት ላይ አስፍተው ይዘው ነበር በዚህ ዘመን አገላለፅ ኪራይ ሰብሳቢነት የጃንሆይ ዘመን ሹማምንት አንዱ መገለጫቸው ነበር ሰለዚህ ደርግ ትርፍ ቤቶቹን ወስዶ ለቤት አልባዎች በአዋጁ መሠረት ሰጠ ትልልቅ የግል ህንፃዎችንም ወርሶ ኪራያቸው ለኣገር ጥቅም በመንግስት በኩል የሚውልበትንና አንዳንዶችንም ለአስተዳደር ስራዎች ይገለገልባቸው ጀመር አነስተኛ ትርፍ ቤቶችን ወስዶ ለቤት አልባዎች ሲያድልም ለገጠሩ መሬት የገበሬ ማኅበራት እንዳቋቋመው ሁሉለዚህም ቤቶቹን እንዲያስተዳድሩ ስልጣን የተሰጣቸው የከተማ ነዋሪዎች ማኅበራት ማለትም ቀበሌዎችን አደራጅቶ ለቁጥጥር መደባቸው እነዚህን የመሳሰሉ የሶሻሊዝም ርዕዮት አምጦ የሚወልዳቸውና የኅብረተሰቡን ኑሮ የሚያሻሽሉ የሐብትን ልዩነት ስፋት ገድበው የሚያቀራርቡ በነት እርምጃዎች ሲወሰዱ እንደማንኛውም ርዕዮት አፈፃፀማቸው ላይ ልዩ ጥንቃቄ ካልተደረገባቸው ውጤታቸው ኣጠያያቂ መሆኑ የማይቀር ነው ርዕዮቱ በራሱ በአንድ አገር ተግባሪዊ ሲደረግ የሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል ይሁንታ ካላገኘ የተጠበቀው ለውጥ አይመጣም በኢትዮጵያም የታየው ይሄነው አብዮት በተከናወነባቸው አገራት ሁሉ አኩራፊ ቡድን ጠፍቶ አያውቅም የሶሻሊስት አራማጅ አብዮተኛ መንግስት እነዚያን አኩራፊ ቡድን አገራዊ ፍቅር እንዲያድርባቸውና በገፍ የያዙት ሐብትና ንብረት ለአገራቸው ተቆርሶ ቢሰጥና ማኅበራዊ ለውጥ ቢመጣ ተጠቃሚዎች ራሳቸው መሆናቸውን ማሳመን ይጠበቅበታል ከራስ ጥቅም ይልቅ የሀገርን ጥቅም የማስተደም ባህል ያሳቸው ህዝቦች ያሏት አገር ብቻ ሳያኮርፉ ይሁን በማለታቸው በርዕዮቱ ተጠቃሚ ሆነው ያለፉ አገራት ታይተዋል በኢትዮጵያ ግን አኩራፊዎችን ማሳመን አልተቻለም አይቻልምም ምክንያቱም ኩርፊያው የርዕዮትና ርዕዮቱን ተከትሎ በሚመጣው ጉዳይ ስላልሆነና በስልጣን ብቻ ስለሆነ ነው የብዙሃኑ ምናልባትም ከጃንሆይ ዘመን ባለስልጣናትና ሹማምንት በስተቀር የሁሉም ህዝቦች የተደራጁ የግራ ክንፍ ተቃዋሚ ቡድኖች በአገር ውስጥም በውጭም ያሉ የቀድሞው አገዛዝ ተቃዋሚዎች ዓላማና ርዕዮት ደርግ እየተገበረው ያለው ነው ከተገንጣይና አስገንጣይ ቡድኖች ውጪ ሁሉም የዚህ መፈክር አራማጅ ነበር ስለዚሀ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው ሆነ ርዕዮቱ በራሱ በአፈፃፀም ችግር የሜፈጥረው ቀውስ አልበቃ ብሎ ጭራሽ የተደራጀ ተቃዋሚ ቡድን በኢትዮጵያ ኖሮ የደርግን የሚደገፍ ሁሉም ። ቀጠሉ የእነ ለገሠ አስፋው የእነ መንጌ የሠደድ አባላት አነጣጥሮ መተኮስ እንጂ አንጥሮ መፃፍ ላይ እምብዛም ነበሩና ወሣኝ ወሣኝ ሀሳቦችን ከሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች እየቀዱ እየተማሩ ዳኒ ላይ ሆነው ምኑንም የማያውቁትን ርዕዮት በውል ተረዱት ይህን እሰከ ድረስ የዘለቀ የጋዜጣ ትምህርት ይዘውም የርዕዮቱ ተንታኝ ብሎም ተግባሪ ሆኑ በእርግጥም የሀሳብ ፍጭቱ ለደርግ ጠቃሚ ነበር የብዕር ተፋላሚዎቹም በልዩነት ላይ ሳይሆን አንዱ አንዱን ለማንቋሸሸና እርቃኑን ለማስቀረት የነበረ ሲሆን ውሎ አድሮ ብዕሩ ቀርቶ በጥይት መፋለም ምራሉ ደርን በመሃል የብሔራዊ ዴሞክራሲ አብዮትን በ ሚያዚያ ካወጀ በኋላም ለአዋጁ አስፈፃሚ አካል የሚሆን ጊዜያዊ የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ቤት ማቋቋም ነበረበትዓላማውም በደርግ አገላለፅ ሰፊውን ህዝብ ማንቃትና ማደራጀት ነው ቤቴን ለመምራትም አባላት ያሌት ኮሚሽን ሲደራጅ ከሊቀመንበርነት ጀምሮ ያለውን ስልጣን መኢሶን ስለያዘው ድርጅቱን ለማጎልበት ተጠቀመበትከኢህአፓ ሙ የማይወዳደር አቅም የነበረው መኢሶን በወራት ው አሳዬከተሞችን ለመቆጣጠር የሚያስችለውን የከተማ ልማትና ሆኖና ሚኒስቴርን ደርግ ሆነ ብሎ በመኢሶን ስር እንዲሆን በማድረጉም በ መገባደጃ ላይ በተካሄደው ተራ የቀበሌ ምርጫ ደጋፊዎቹን ለማስመረጥ ባመቻሌ መኢሶን ደስ ተሰኘነገር ግን ደርግ ይህን ያደረገው ኢህኣፓን ንቁልልጭ ለማለትናስልጣን ለህዝብ በተወካዮች አማካኝነት የሚተላለፈው እኔን የአብዮቱን ባለቤት ቀርቦ በመወዳጀት እንጂ በግትርነት አይደለም በሚል ሾርኒ ለመንካት ነበርበዚህም ኢህአፓ በግኗልስለዚህም ወዲያው ሠራተኛውንና ሌሎች ጥቃቅን ተቃዋሚ ቡድኖችን በመቀስቀስና ደጋፊዎቹን በማነሳሳት የኢሀአፓን መፈክር አንግበው ሰልፍ እንዲወጡ አኣደረገ ኢህአፓ የወዛደሩ ብቸኛ ፓርቲ እኔ ነኝ ሲል በመክረሙና በአማላይ ቃላቶችም ብዙሃኑን መማረክ በመቻሉ የብሔረተኝነት አላማውን የተረዳውም ያልተረዳውም ተሰለፈለት ደርግና የደርግ አሯሯጮች ኢህአፓ መቼም እረፍት እንደማይሰጣቸው «ረዱትም የወሰዱት የኃይል እርምጃ ግን አልነበረም ህ በደርግና በአጋሮቹ ላይ የሽምቅ ው እንደሚገድልም ዛተ መስከረም ቀን ዓም ኢህአፖ መንግለቱ ኃይለማርያምን ለመግደል ያደረጉት ሙከራ ለጥቂት ሳይሳካ ቀረበዚህ ተክለ ክፉኛ የቆሰሉት መንግስቱ ድንጋጤያቸውን በውስጣቸው ይዘው መከራውን ድለቲካዊ ፕሮፖጋንዳ ተጠቀሙበት አስቡት እኔን የመሰለ አብዮቴ ጎን ለጎንም የኢህአፓን ፖለቲካዊ ኪሣራ ከጥቂት ቀናት በኋሳ ቀደም ሲል ያየነውን የመኢሶን አመራ አባልና የህዝብ ድርጆት ጉዳይ ጽቤት ባለደረባ የነበሩትን ዶር ፍቅሬ ደ አ ተራ አካበቢ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው ባለቤታቸውን ኣባት ተከለው ክንዱ ልጥነውበት ተክነውበት የመጡት የኢህአፓ ነጭ ሽብር አሉት የነጭ ሽብር ተግባራቸውንም በተጠቀሱት ኢትዮጵያዊ ዶር ጀመሩትጉ የመጀመሪያውን ጥይት ያጮኸች ኢህአፓ መሆኗ ግልጽ ነው ደርግ ከኢህአፓ የሸብር ተግ አብዮታዊ ህይወት በሺ ፀረህዝቦች ህይወት ይመነዘራል አለ ከዚህ መግለጫ በኋላ የኢህአፓ አባሎችንና ደጋፊዎችን ደርግ በውል ስለማያውቃቸውና አገር ውስጥ ድንበር ሲጠብቅ ስለነበር የፖለቲካ ዲያስፓራዎች እዚያው ይተዋወቃሉና የመኢሶን አባላት ስም ዝርዝራቸውን ለደርግ አቀረቡ ደርግም እየለቀመ ማሰር ቀንደኞችንም መረሸን ጀመረ ሲቪል ታጣቂዎችንም እያደነ ትጥቅ አስፈታ ቀጥሎ በሰርጎ ገብነት የሚጠረጠሩ የራሱ የደርግ አባላትና ደጋፊዎች ለኢሀአፓ ጋ እየሰሩ ነው የሚል ነገር መጣ የነገሩ እውነትነት ባያጠያይቅም ደርግ ሠርጎ ገብ የተባሉትን አባላት በሚመለከት የወሰደው እርምጃ ከኑግ ጋር የተገኘሀ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ የሚባለውን ብሂል የተከተለ ነባር ጠቋሚዎቹም የየራሳቸውን የስልጣን ቦታ ለመያዝ ሲሉም ሆነ ያልተዋጠላቸውን ሹም የማስወገጃ መድረክ አድርገውታል መንግስቱ የደርግን ህልውና አስጠብቀው ለመቀጠል ቀድመው የተዘጋጁ ነበሩና በቤተመንግስቱ ቅልብ ጦር አኑረዋል በኮሎኔል ዳንኤል አስፋው ይመራል መቺ ኃይል የሚሉትን ቡድንም መስርተዋል በሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ ይመራል የደርግ እባላቱ ተራ ወታደር አለቃ እየተባሉ አድሃሪ ተብለው ስለተተቹም ለእያንዳንዱ አባል በውስጥ አሰራር ማዕረግ እንደ ፈንዲሻ እየተዘገነ እንዲሰጥ አድርገዋል በዚህም የእሳቸው ሌተናል ኮሎኔል መሆን አግባብነት ቢኖረውም እያንዳንዱ አባል ከምክትል መቶ አለቃ በላይ እንዲሆን የተደረገው በፍጥነት ነበር ከዚህም አልፎ አብዮታዊ ሠደድ አስ በጥቅሉ ዙሪያውን አጠባብቀው ሲያበቁ ይህ የኢህአፓ ተግባር አገር የማፍረስ ተልዕኮ መሆኑን በመገንዘብ ውስጡ መጥራት እለበት የሚል አቋም ወሰዱ ይሄ ሁሉ የስልጣን ህልመኛ ፓርቲ የአብዮቱ ፀር እንደሚሆን ጠረጠሩ ዝግጅቱን ያዩት ጄኔራል ተፈሪ በንቲ እሣት በእሣት አይጠፋምና ብሔራዊ እርቅ ለማድረግ ጥሪ እናቅርብ ብለው አረፉ ወፉ ዛፉ በኢህአፓነት በሚጠረጠርበት በዚያ ጊዜ ይሄን የመሰለ ቃል ከደርጉ ዋና ሊተመንበር መሠንዘሩ ለኮሎኔል መንግስቱ ሊፈጥራቸውም ጠርጣሪ ናቸውና ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ ነው እርግጥ ነው ከጥር ቀን ዓም በፊትም ለወራት ያህል መጠነኛ አለመግባባት ነበር በተፈሪና በመንግስቱ መካከል ሆኖም የዝግጅት ጊዜ አስፈልጓል በደርግ ውሰጥም ጥርጣሬው ጎልቶ በጎሪጥ መተያየት ተፈጥሯል ስለዚህም የደርግ የፖለቲካና የውጭ ጉደይ ኮሚቴ ሊቀመንበር የነበሩትን የአየር ኃይል አባሉን ሻለቃ ሲሳይ ሀብቴን በአብዮቱ ላይ አሲሯል በሚል ክስ በጦር ፍርድ ቤት ቀርበው ተረሽነዋል ቀጥሎም በኤርትራ ያስው ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ የነበሩት ብርጋዴል ጄኔራል ጌታቸው ናደው ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ተወስዷል ጄኔራል ጌታቸው ናደው ልክ እንደ ጄኔራል እማን እጅ አልሰጥም ብለው ቤታቸው ውስጥ ተታኩሰው ነበር የተገደሉት ከዚያም መቶ አለቃ በወቅቱ ካሣና መቶ አለቃ ስለሺ በየነ የተባሉ ሁለት የደርግ አባላት ሊወሰድባቸው የታሰበውን እርምጃ ቀድመው በማወቃቸው በሽሽት ላይ እንዳሉ በደርግ የተላከው ጦር አሳዶ ይዞ ገድሏቸዋል በተመሣሣይ ቄ ዴ ጥርጣሬም የእድገት በኅብረት ዘመቻ አስተባባሪ የነበሩት ሻለቃ ከሮስ አለማየሁ ተይዘው ታስረው ሳለ ራሳቸውን በእስር ላይ እንዳሉ ገድለዋል ይህ በእንዲህ እንዳለም በተጠቀሰው አመት የመጀመሪያው ወራት የደርግ አወቃቀር ላይ መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ነበርና በዚህም ሁሉም የደርግ አባላት የሚሳተፉበት ሸንጎ ዋናው የስልጣን አካል ሆኖ በተዋረድ ደግሞ የማዕከላዊ ኮሚቴና ቋሚ ኮሚቴ ተቋቋሙ በዚህም ዋና ሲቀመንበሩ ዋናውን ሸንጎ በበላይነት መምራት ሲችሉ ምክትሌ መንግስቱ ግን ከደርግ ጋር ያልተያያዘውን የሚንስትሮች ምክር ቤትን በሊቀመንበርነት ከመምራት ያለፈ ስልጣን እንዳይኖራቸው ሆነ በተጨግሪም የደርጉ ዋና ፀሐፊ የጽቤቱን ስራ ከመምራት ባለፈ ከአዲሱ አወቃቀር በፊት በሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ስር የነበረውን የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽቤትንም እንዲቆጣጠሩት ተደረገ ይህ አወቃቀር ከግራ ቀኝ ሲታይ መንግስቱና ደጋፊዎቻቸውን አስሮ የማሰቀመጥ ዘዴ ሆኖ ስለተገኘ ፍጥጫ ቢፈጠር አይገርምም በዋናነት አዲሱን አወቃቀር አቅደው በተግባር እንዲሰራበት ያደረጉት በኢሀፓነት የሚጠረጠሩ የተባሉት የደርጉ የኢኮኖሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር የነበሩት ሻምበል ሞገስ ወሚካኤልኖ በአዲሱ አወቃቀር የደርጉ ዋና ፀሐፊ የሆነው ሻምበል አለማየሁ ኃይሌ መሆናቸው ነው እንደገናም አወቃቀሩ የአብዮቱ ጠባቂ አለኝታ ተደርገው በብዙሃኑ የሚታዩትን የሚፈሩትን መንግስቱን አግልሏል ከሁሉም የከፋው ደግሞ በዚሀ አሠራር ሠርጎ ገቦች ካሉ እንደልባቸው የመሆን እድል የሚሰጥ መሆኑ ነው ተጠርጣሪዎች ይህን አድርገው እአስጊውን መንግስቱን ቀፍድደው ስራቸውን ቀጠሉ የረሱት ነዝር ቢኖር ለመንግስቱ ፍፁም ታማኝ የሆነውና ከሆለታ ትምህርት ቤት ጀምሮ ጓደኝነት የነበራቸው ከደርግ ምስረታ ጀምሮ የመንግስቱ ቀኝ እጅ የሆነው ጃንሆይንም አማንንም ሲጥ ያደረገው ኮሎኔለ ዳንኤል አስፋው የደርግን ህልውና ለማስጠበቅ የተደራጀው የቅልብ ጦሩ የበላይ አዘዥ መሆኑን ነው እናም ጠላታቸውን በፍጥነት በማንበርከክ ወደር የማይገኝላቸው መንግስቱ የረቀቀ የማጥቃት ዘዴያቸውን ከደጋፊዎቻቸው ጋር አቅደው ጨረሱ ጥር ቀን ዓም ሁሉም የደርግ አባላትና ሊቀመንበሩ ጄኔራል ተፈሪ በንቲ በስብሰባ ላይ እንዳሉ አንድ መልዕክተኛ ይመጣና መንግስቱ አስቸኳይ የስልክ ጥሪ እንዳላቸው ይገልፃል መንግስቱ አስፈቅደው ይወጣሉ ወዲያው ባልተጠበቀ ፍጥነትኖ ሁኔታ የታጠቁ ወታደሮች በኮሎኔል ዳንኤል አስፋው መሪነት ወደአዳራሹ ገብተው እጅ ወደ ላይኛ አሉ ሁሉም በድንጋጤ እጆቻቸውን በጭንቅላታቸው ላይ አጣምረው አፈጠጡ በአንድ አዳራሽ ከታጎሩት ኣባላት ውስጥ ሰባት ለሰዎች መርጠው ስማቸው እየተጠራ ወጡና በአንድ ክፍል ተቆለፉ ሌሎቹ አዓላት እይዚችሁ እናንተን አይደለም ተብለው ተተውና ሰባቱ ወዲያው ተረሸኑ ጄኔራል ተፈሪ በንቲ የደርጉ ሲቀመንበር ሻምበል አለማየሁ ኃይሌ በአዲሱ አወቃቀር የደርጉ ዋና ፀሐፊ ሻምበል ሞገስ ወልደሚካኡል የኢኮኖሚ ኮሚቴ ሲቀመንበር ሌተናል ኮሎኔል አስራት ዶስታ የ ርግ የማስታወቂያ ኮሚቴ ሊቀመንበር ሻለቃ ህሩይ ኃይለስላሴ ምበል ተፈራ ደነቀ አስር አለቃ ኃይሉ በላይ የተረሸኑት የጊዜያዊው ነ መንግስት ከፍተኛ ባለስለጣናት የነበሩና በኢህአፓ ደጋፊነትና አባልነ ው ሰለተ ወበት መፈንቅለ መንግስቱ በስኬት ቢደመደምም ወዲያው በተፈጠረው የተኩስ ልውውጥ ሽብሩ ቀጠለ መንግስቱ ከመፈንፃ ለ መንግስቱ በኋላ ወደ አዳራሹ ሄደው አማንን መርጠን ምሩን ብንላቸው አብዮታችን ለመቀልበስ ተነሱ ዛሬ ደግሞ ጄኔራል ተፈሪ በንቲ ለዘብ ነኛ በመሆናቸው አብዮቱን ለማዳን ርምጃ ተወስዷል እኔ ለአብዮቱ ያለኝ አቋም ቁርጠኛ ነው አሁን በእርጋታ ስራችሁን መቀጠል ትችላለህ እያሉ ሲያረጋጉ የመጨረሻዋን ቃል ሳይጨርሱ የቤተመንግስቱ ጊቢ በተኩስ ሲናጥ መንግስቱ ሮጠው ወጥተው ታንክ ውስሰጥ ተደበቁ ሌ ው ባለበት ሆኖ በሽብር ተናጠ ጉዳዩን ወዲያው የተረዳው ሻለቃ ዮሐ ምትኩ ጊቢ ውስጥ ነበርና የኢህአፓ አባልም ስለነበር ሳይቀድሙኝ ልቅደም ብሎ ተኩስ በመክፈት ዶር ሰናይ ልኬንና ኮሎኔል ዳንኤል አስፋውን ቅል ቅልአቸውን ብሎ አስተኛችው ቀጥሎም ቸቸ ን ለመግደል ነበርና ያሰበው ይገኙበታል ወዳለው ቢሮ ገብቶ አጣ ው ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የመንግስቱን ፎቶ ግራፍ በጥይት ቦረዳድ ከመውጣቱ በፊት አንድ ታንክ ቢሮውን ደርምሶ ገብቶ ሻለቃ ዮሐንስንም ሉም ነገር ፀጥ አለ መፍልዳ እጋግስቱ ድል በወዳጆቻቸው በዶር ሠናይ ልኬና በኮሎኔል ዳንኤል አስፋው መገደል ደበዘዘ ፍንቀላው ግን ተሳካ ከዚህ በኋላ የመንግስቱ አምባገነንነት የበለጠ እልህ የተሞላበት ሆነ የዚህ መፈንቅለ መንግስት አደራጆች መንግስቱ ብቻ ሳይሆኑ የመኢሶን እና የወዝ ሊግ አመራርአባላት የሆኑ ምሁራን ሰፊውን ድርሻ ይይዛሉበዚህ ጊዜ ነው መንግስቱ ለምሳ ያሰቡንን ለቁርስ አደረግናቸው በማለት መግለጫ የአ ሁን ደርግ የኢህአፖ ተሟጋች ሆነው ፇጐርቅ የሚሉትን ሁሉ ደምስሶ ነፃ እርምጃ ለመውሰድ መንገዱን ጠርጓል ኮሎኔል መንግስቱ የጄኔራሎችን መጋረጃ ገላልጠው ከፊት ሆኑ ከተቀዳሚ ለቆመንበ የደርጉ ዋና ሊቀመንበር ሆኑ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥነ ንም ደርበው ያዙ ቀጥሎ አስጊ ያልሆኑት ነገር ግን በየስብሰባው ያው ሙ የተሰኙት ምክትል የደርጉ ሊቀመንበር ኮሎኔል አጥናፉ አባተ ቀሩ አዋኪነታቸው እንዴት ነው። ብሎ ፊቱን ወደ ሰሜኑ ግንባር አዞረ ባለፈው ምዕራፍ እንዳየነው በኤርትራ የትጥቅ ትግል ቀድሞ የጀመረው ጀብሃ እንዲሁም አፈንግጦ የወጣው ሻዕቢያ የአካባቢው ፀረ ሠላም ኃይሎች ሆነው ቆይተዋል ከ ጀምሮ ደርግ በሁለቱም ላይ የከፈተባቸው ዘመቻ እንኳ ኅብረት እንዲፈጥሩ አላደረጋቸውም የደርግ ጥቃት ሲመጣባቸው የተናጠል መክሳከል ሲያደርጉ ጥቃቱ ጋብ ሲል እርስ በርስ እየተዋጉ ዓመታት ካሳለፉ በኋላ በ ጅብሃ በሻዕቢያ ሙሉ ለሙሱሉሱ ተደምስሶ ሻዕቢያ ብቻውን ተጠናክሮ የወጣ ኃይል ሆኗል የመጀመሪያው የደርግ ማጥቃት የተሰነዘረው በ ዘዝመቻ ራዛ በሚል የሰሜን ኢትዮጵያ ኣርሶ አደሮችን አሰባጥሮ ለማዝመት የተደረገው ሙከራ ሲሆን እቅዱ ሙሉ ለሙሉ ባይሰምርም ሺህ የሚሆኑ የሰሜን ወሎ አርሶ አደሮችን አሰባሰቦ ለማዝመት ተችሎ ነበር ነገር ግን የህወኅትና የኢሀአፓ የታጠቁ ሠራዊቶች የኢትዮጵያ ሀዝባዊ አብዮታዊ ሠራዊት ኢሕአሠ በሰነዘረባቸው ወታደራዊና ፕሮፓጋንዳዊ ጥቃት ተዋክበው እንኳን ኤርትራ ሲደርሱ የትግራይንም ግዛት ማለፍ ሳይችሉ ድለ ሆነው ተበታትነዋል ገበሬዎችን ማዝመት ግድ የሆነው ዋናው ጦር ለምስራቁ ግንባር ያስፈልግ ሰለነበር ነው ሁለተኛው ጠንካራ ዘመቻ ደግሞ በ ዓም ክረምት ሳይ ስምንት ግብረኃይሎች ተዋቅረው እንዲዘምቱ የተደረገበት እርምጃ ሲሆን በዚሀ ዘመቻ የደርግ ሠራዊት ጀብሃና ሻዕቢያ ቀደም ብለው የተቆጣጠሩዋቸውን የኤርትራ ዋና ዋና ግዛቶች ለቀው እንዲሸሹ ያደረጋቸው ሆኖ ነበር በዚህ ጥቃት ሻዕቢያ አስተማማኝ ደጀኑ ወደሆነው የተፈጥሮ ምሽጉ ወደ ናቅፋ እንዲያፈገፍግ ተገዷል ያም ቢሆን የሻዕቢያ አስጊነት ቀጣይ ሆኖ በመገኘቱ ሦስተኛና የመጨረሻ የሆነ መጠነ ሰፊ ዘመቻ በሻዕቢያ ላይ መደረግ ነበረበትና ፕቀይ ኮከብ ዘመቻ ታወጀ የዚሀ ዘመቻ ዓላማ በየእለቱ እየተጠናከረና በመሐልም ጀብሃን አስወግዶ ትጥቅና የሰው ኃይሉን በምርኮም በእርዳታም አጎልብቶ ሲችል ፊት ለፊት የሚዋጋውን ሳይችል በየከተሞች ላይ ልዩ ልዩ የመሠረተ ልማት አውታሮችን በፈንጅ እየደረመሰ የመንግስት ተቋማትን እያጋዬ የህዝብ መገልገያዎችን እያወደመ ባለስልጣናትን በሠርጎ ገብ ኃይሎች እያፈነ ወደ በረሃ የሚወስደውን ሻዕቢያን ለመጨረሻ ጊዜ መደምሰሰ ነው የኖቅፋ ተራራ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ብዙ የተወራለትኖ ታዋቂኒታትን ያገኘ የጦር አውድማ ነውሻዕቢያ በዓለም ማኅፀረሰብ ዘንድ ሰሙ ሲነሳ የናቅፋ ተራራም አብሮ ይነሳልሻዕቢያ ይህን ቦታ ለቀቀ ማለት ህልውናው ብቻ ሳይሆን ስሙም አይኖርምይህን ቦታ ለመያዝ ደግሞ ያለውን ኃይልኖ ጉልበት ተጠቅሞ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሷልናቅፋን ቀድሞ የያዘ ጦር ጠላቱን መዋጋት መከላከል ሳይጠበቅበት ቦታው ራሱ ይዋጋለታልለዚሀም ነው ደርግ ፍፁም የማይመጥነውን ኢምንት ኃይል በምድር ጦርም በእየር ኃይልም ድል ለማድረግ የተሳነው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ መንግስት በወቅቱ የሱዳኑን መሪ በ ዓም ወደአዲስ አበባ ጠርተው ለሻዕቢያ የሚያደርጉትን ወታደራዊ እርዳታ ነፃ እንቅስቃሴ መፍቀድ ለሥልጠና ቦታ መመደብና እንደማንኛውም ዓረብ አገር ለሻዕቢያ የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያቆሙ መንግስቱ ሊያግባቧቸው ብዙ ጥረዋል ኑሜሪ ግን በቃል እሺ ብለው በተግባር እምቢታቸውን ገፉበት ሻሶና ሣ ከኛቅፋ ተራሮች ወርዶ የመልሶ ማጥቃት ተግባሩን ጀመረ በዚ ጊ ው መንግስቱ ጆን ጋራንግን ማርታ በማለት የራሳቸውን ችግር ደ በራሳቸው ለመፍታት በሻዕቢያ ላይ የመጨረሻ የማጥቃት ኣርሥጳጽ መውሰድ የሚያስችለውን እቅድ ማሣቀይ ኮከብ ዘመቻን ተግባራዊ ለማድረግ የተፋጠኑት ለአንደ ዓመት ያህል ከፍተኛ ዝግጅት የተካሄደበትና በ ተግባራዊ የሆነው ይህ ጥቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመም ኢትዮጵያ በታሪኳ በአንድ ጊዜ የጦርነት ዘመቻ ብቻ ከፍተኛ ገንዘብ የመደበችበት የመጀመሪያው አክሳሪ ዘመቻ ነው ራሱን የቻለ ጠንካራ ምክር ቤት የተቋቋመለት ይህ ዘመቻ በስራ አሰፈፃሚው በኬል የፖለቲካ ስራ በኅብረተሰቡ ውስጥ የወታደራዊ ዘመቻ እቅድ የኢኮኖሚ ዘመቻ እቅድ የኢንስፔክሽን የወታደራዊ ፖለቲካ ስራ የህዝብ ደሀንነት ጥበቃ መመሪያዎች ያለው ሆኖ በሁለት ዋና ዋና ጥቅል እቅዶች ላይ ያተኮረ ነው ኛ ወታደራዊ ግብ ተገንጣዮችን መደምሰስና በኤርትራ ግዛት ዘሳቂ ሠላም ማስፈን ኛ ኢኮኖሚያዊ ግብ በጦርነት የፈራረሱ የመሠረተ ልማት አውታሮችን መልሶ ማቋቋምና አዳዲስ የልማት ተቋሞችን መገንባት የሚሉ ናቸው የአገሪቱ አጠቃላይ በጀት ከሠራተኞች የወር ደሞዝ በስተቀር ሁሉም ወደዘመቻው ዞረ በዚያ ወቅት አዲስ አበባ ጭልል ብላ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አስመራ ሆነች የየሴክተሩ ሙያተኛ ወደ አሥመራ ተጓዘ የዘመቻው የአንድ ቀን በጀት ብቻ ሚሊዮን ብር ነበር የዚያ ዘመን የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ቀውስ መነሻ ምንጩ ይህ ዘመቻ ሆነ ወደፊት ለምናየው የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት የሆነው በዋናነት ይህ ዘመቻ መሆኑን ለመገንዘብ ያህል በብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሐብተማርያም በ ዓም የጦር ሜዳ ውሎ በሚል ርዕስ ከተፃፈው መጽሐፍ ውስጥ ለዘመቻው ተብሎ የተከናወነውን ዝግጅት የሚገልፁ ጥቂት ዝርዝሮችን እንይ የሰው ኃይል መደበኛ ሠራዊት የኤርትራ ሀዝባዊ ሠራዊት ድምር የአንድ ዓመት ቀለብ ግምቱ ብር ተመድቦ ኩንታል ልዩ ልዩ የምግብ አይነቶች ለጦሩ ታድሏል ብር የፈጀ አልባሳት ታድሷል ለእንድ ዓመት የነዳጅ ፍጆታ ብር ለጥርጊያ መንገድ ስራ ተመድቦ መንገዱ በፍጥነት ተሰርቷል ከባድ ተሽከርካሪዎች ተመድበው ሠራዊት እና ቶን ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች በአንድ ዓመት ከአዲስ አበባ ወደ ኤርትራ ተጉዘዋልየዚህ ወጪም በገንዘብ ሲተመን ብር ይሆናል መሣሪያ ሚሊ ሜትር እና ሚሊ ሜትር መድፍ ቢ ኤም ሚሲ ሜትር ሞርታር ልዩ ካሊበር ያላቸው መትረየሶች ኤኬ ኤም ጠመንጃ ክላሽ ቲይ ታንክ ብረት ለበሶች ከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎች ሲሆን የ ሚሊ ሜትር መድፍ ጥይት የ ሚሊ ሜትር መድፍ ጥይት የቢ ኤም ጥይት የኤ ኬ ኤም ጠብመንጃ ጥይት መደባዊ ጭነት ማለትም በ ሩ ነበር ድም የከተማው ጦር ቀለብ አልባሳት ህክምና ነዳጅ ጥይት ደሞዝ ወዘተ አገሪቱ ከምትችለው አቅም በላይ እየሆነ ቢሄድም አማራጭ አልነበረም ለጦሩ ብቻም ሳይሆን በሸብር ተግባር ከአገርነት ተርታ ወጥታ እንቅስቃሴዋ የቆመው ኤርትራ ዳግም እስትንፋስ መዝራት ስለበረባት መልሶ ግንባታ የግድ ነበርና ለዚህም በጀት ተመድቧል የጦር መሣሪያ በገፍ ተገዝቷል ለአዲስ ምልምል ሠራዊት ወዘተ እያለ ቀጥሎ ለእጠቃላይ የቀይ ኮከብ ዘመቻ ብቻ ከ ቢሊዮን በላይ የሚገመት ብር ወጪ ዛደርጓል ይህም ከፊሉ ለልማት ከፊሉ ለጦርነት መሆኑ ነው በዚህ መልኩ የኢትዮጵያውያን ዓይንና ጆሮ ብቻ ሳይሆን ሁሉ ነገራቸው ኤርትራ ላይ ሆነ በታቀደው መሠረትም በጦርነት የወደሙ ፋብሪካዎች የመንግስት መሰሪያ ቤቶች ትቤቶች የጤና ተቋሞች መንገዶች ባንከ ውሃና መብራች የፈረሱት ተጠግነው ያልነበሩት ተሰርተው እንቅስቃሴ ጀመሩ ሠርቶ አደሩ ሳብ አደሩ ወደየስራ መስኩ እንዲመለስ ተደረጎ ተማሪው ትምህርቱን ቀቅጠለ በሽተኛው ህክምና ማግኘት ጀመረ አያሌ ገንዘብ የወጣበት ፌስቲባልና ባዛር በምፅዋ መሜናዊ ድንበር ጉርጉሱም በተባለ ሥፍራ ተዘጋጅቶ በጓድ ሊቀመንበሩ ተመርቆ ተከፈተ በጦርነት የደቀቀችው ከተማ ነብስ ዘራች ጥር ቀን ዓም ሊቀመንበር መንግስቱ የኤርትራ ህዝብ ሆይ። መሥ ካያ መቃድቸ በዚህም ተፈጠረሳቸውከማይጨው ጦርነት ሸሽቶ ይመጣ በነበረው የኢትዮጵያ ከኢጣሊያ ዳግም ወረራ በፊት ግን በመንግስትና በራያና አዘቦ ህዝብ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እሱንም ተከትሎ የደረሰው ደም መቃባት ለአካባቢው ሠላም መደፍረስ የመጀመሪያው ሆኗል ከንግሳት ዘውዲቱ የግዛት ዘመን ጀምሮ ማዕከላዊ መንግስቱን ሲፈታተንና በየጊዜውም ከሚላክበት ጦር ጋር በሸፍትነት ይፋለም የነበረው የራያና አዘቦ ህዝብ ይህን ተግባሩን በቀጠለበት ሁኔታ የኢጣሊያ ወረራ ተከሰተ ማዕከላዊ መንግስቱን ለመበቀል ምቹ ሁኔታ ጦር ላይ ያደረሱት ግፍም የሚረሳ አይደለም ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ሙሉ ለሙሉ ለቃ ከወጣች በኋላም የጃንሆይ መንግስት እስኪደላደል ድረስ በነበረው የጊዜ ክፍተትና ጣሊያኖች ትተውት የሄዱትን መሣሪያ በገፍ ማግኘት ቀላል ስለነበር በነፃነት ማግስት የመጀመሪያውን የተደራጀ አመፅ ማካሄድ ቻሉ ይህም በነፃነት ማግስት በትግሬ ጠቅላይ ግዛት የተቀሰቀሰው የመጀመሪያው የወያኔ አመፅ ነው የራያና አዘቦ ህዝብ አመፁን የለኮሰውም እንደመጀመሪያ ተግባሩ በአፋሮች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያ በመፈፀም ሲሆን በዚህም የማዕከላዊ መንግስቱን የበቀል እርምጃ በራሱ ላይ አስከተለ የመንግስት ማጥቃትና የአማፅያኑ የመካላከል ተግባር እየተጋጋለ ሄዶ በመጨረሻ አማሪያኑ ከመከላከል ወደማጥቃት አመሩ ይህ ሁኔታ ከተራ የሽፍትነት አመፅ ወደ ፖለቲካዊ አመፅ ተሸጋገኅረ አማፅያኑ የመጀመሪያ ድላቸውን ያገኙት ግንቦት ቀን ዓም በተንቤን አውራጃ አዲ አቡን በተባለ ስፍራ ነው ከዚያም በተከታታይ መቀሌ አጠገብ የሚገኙትን ቅዊሓንና እንዳ እየሱስን በቁጥጥር ስር አዋሉ በመጨረሻም የጠቅላይ ግዛቱን ዋና ከተማ መቀሌን ሙሉ ለሙሉ ያዚት ለዚህ ድል የረዳቸው ዋና ምክንያት የህዝቡን ቅሬታ ዘውጋዊ ወይም ጎሳዊ ርዕዮት በመስጠት ማስተባበር የቻለው የብላታ ኀይለማርያም ረዳ አመራር ነው የአመፁ ስፋት ጥልቀትና እድገት መንግስትን ክፉኛ ስላስደነገጠው በአርበኝነቱ ዘመን በፈፀሙት ጀብድ ስመጥርነትን ያተረፉትን ራስ አበበ አረጋይን የጦር አዝማች አድርጎ ላከ ከሁኔታው አስጊነት አንፃርም በወቅቱ በኢትዮጵያ ከነበሩ የእንግሊዝ ጦር ባለስልጣኖችን እርዳታ መጠየቅ አስፈልጎ ነበር በእንግሊዝ ይሁንታም የጦር አውሮፕላኖች ማግኘት ተችሎ ቀዳማዊ ወያኔን በምድርና በአየር ውጊያ ማሸነፍ ተቻለ መስከረም ቀን ዓም ሙሉ ለሙሱ ድል የሆነው የአማፅያኑ ጦር ተበታተነ ቀዳማዊ ወያኔ ትግሉን የጀመረው ምስራቃዊ ትግራይን መነሻ በማድረግ ነበር ዳግማዊ ወያኔ ደግቺ ከመረብ ወንዝ በስተደቡብ በሚገኘው በምዕራብ ትግሔይ መነሻውን አድርጎ ከ ዓመታት በኋላ የአርነት ንቅናቄውን እንደዋዛ ጀምሮ እየተጠናከረ ቀጥሏል የመጀመሪያው ወያኔ ርዕዮቱን ዘውጋዊ አድርጎ የተነሳ ሲሆን ሁለተኛው ወያኔ ደግሞ ከኢትዮጵያ የተማሪዎች ንቅናቄ በወረሰውና ራስን ፅድል በራስ የመወሰን መብት እስከመገንጠል በሚለው መርህ የሚመራ ነበርቀዳማዊ ወያኔናዳግማዊ ወያኔ የሚመሳሰሉበት ሁኔታ ኖሮ ሳይሆንህወሓት ለራሱ ፕሮፖጋንዳ ታሪካዊ መሰረት ለመስጠት የፈጠረው ነው አካባቢው ዳር አገር በመሆኑ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለማድረግ ምቹ ቢሆንም በአካባቢው ኅብረተሰብ ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት የግድ ነበርኖ ለዚህ የሚረዳ በቂ ምክንያት በጠቅላይ ግዛቱ ውስጥ መኖሩ ለዳግማዊ ወያኔ የበለጠ ምቹ ሁኔታ ፈጠረለት ይሀም ከዎቹ አጋማሽ አመታት ጀምሮ በግዛቱ ውስጥ የተከሰተው ተደጋጋሚ ድርቅኖ የኢኮኖሚ ችግር ነው ከዚህም በላይ የቀድሞ ባለባት ሹማምንት የፖለቲካ ማዕከላዊነት በማጣታቸው ምክንያት ሲሰማቸው የቆየው ቁጭት ስለነበር በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦች የመሰረቱትን የነፃነት ንቅናቄ በግዛቱ የሚኖረው ሁሉም ወገን የየራሱን መነሻ ምክንያት መሰረት በማድረግ ስመደገፍና ለማበረታታት ዝግጁ ነበር ለዚህም ነው በተመሠረተ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቂ የሚባል የሰው ኃይል የስንቅና የትጥቅ አቅርቦቱ ሳይቸግረው ባለበት ፈጥኖ ተደራጅቶ የደርግ መንግስትን መፈታተን የቻለው ህወሓት ይዞት የተነሳውን የራስን ፅድል በራስ የመወሰን እስከመገንጠል የሚለውን የሌኒን መርህ ግን ለትግራይ ህዝብ ከማስረዳት ይልቅ ከእሱ ቀድሞ የመገንጠል ዓላማ ይዞ ለተነሳው ለሻዕቢያ መግለፅ ይቀለው ነበር ያደረገውም ያንን ነውሆኖም ሻዕቢያ የትግራይን የመገንጠል ትግል የኔን ትግል ያዳክምብኛል በሚል የወያኔን የመገንጠል ዓላማ ማኑፌስቶ እንዲያሰወግድ አስገድዶታል ለወያኔ የአካባቢውን ህዝብ ድጋፍ ለማግኘት የኢኮኖሚ ችግር ሰለባ መሆኑን መግለፅ ብቻውን በቂ ስለነበር የርዕዮት ትንተና ውስጥ መግባት አስፈላጊ አልነበረም ለሻዕቢያ ግን ጠቃሚና አስፈላጊ መሆኑ አያጠያይቅምስለዚህ የሣንጣይ እና አስገንጣይ ጥምረት መሰርቶ መደጋገፉ ለሁለቱ ቡድኖች ወግኝ በመሆኑ ከልዩነታቸው ይልቅ አንድነታቸው ጠንክሮ በመቀጠሉ በመጨረሻ የየግል ግቦቻቸውን ዳር ማድረስ ችለዋል ደርግ ጊዜያዊ መንግስት በሆነ ማግስት የወሰዳቸው እርምጃዎችበተለይም የዎቹ ግድያና ሌሎች በፍርደ ገምድልነት የተደረጉ ነገሮች መደራረባቸውም ለሸሽመቁ ተቃዋሚዎች ድጋፍና ትኩረት አስገኝቶላቸዋልየአገር ውስጥ ብቻም ሳይሆን የውጭ አገራት ድጋፍን በተከታታይ አመታት ሊያገኙ የቻሉት የደርግ አምባገነንነት በየጊዜው እየጎላ በመሄዱ ነው ደርግ ለአብዮቱ ሲል የሚወስዳቸው ጥንቃቄ አልባ እርምጃዎች በአብዮቱ ደጋፊዎች ዘንድ ተወዳጅ ያደርገኛል ብሎ ሲያስብ ራሱን ለጠላት ፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ አድርጎ ማቅረቡን ለደቂቃ እስቦት አያውቅም ሀወሓት ወያኔ የሚለውን ወኔ ቀስቃሸ ስያሜ ይዞ የትጥቅ ትግል ሲጀምር ልክ እንደሻዕቢያ የመጀመሪያ ስራው ያደረገው በግዛቱ ውስጥ የበላይነቱን ማረጋገጥ ነበር ስለዚህም በቅድሚያ ከሦስት ተቀናቃኝ ድረጅቶች ጋር መፋለም ነበረበት በመጀመሪያ ከእሱ ቀድሞ የተደራጀውን ሣፕትግራይ አርነት ግንባርን ማስወገድ ቻለ ይህን ግንባር ለማስወገድ ብዙ ድካም አልነበረውም ሁለተኛውን ጥኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ኅብረት በእንግሊዝኛ ምሀፃረ ቃሉ ኢዲዩን ግን ብርቱ የሆነ ውጊያና ከፍተኛ የህይወት መስዋዕትነት በመክፈል ነው መደምሰስ የቻለው ኢዲዩን ከምዕራብ ትግራይ ጠራርጎ ካስወጣ በኋላ ቀጣዩን ፍልሚያ ያደረገው በሰሜን ምስራቅ ትግራይ አሲምባ በምትባለው ተራራማ ቦታ ከመሸገው ከኢህአፓ ሠራዊት ጋር ነበር ኢህአፓ በከተማው ትግል ስኬታማ መሆን ሳይችል ሲቀር ወደ ገጠር አምርቶ አሲምባ ላይ ቢመሸግም ለአካባቢው እንግዳ ነው ኢህአፓ አሲምባን የመረጠው በሁለት ምክንያቶች ሲሆን አንዱ ከመንግስት ጥቃት ለመሸሸሽ ሌላው በትግራይ ያለው ሸማቂ ቡድን የኅብረብሔራዊነት ዓላማ ካለው አብሮ ለመቀናጀትና ለመታገል ነው ህወኅትም ኢህአፓም ግራ ዘመም ከሆነው ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ አብራክ የወጡ ድርጅቶች ይሁኑ እንጂ ዓላማና ግባቸው እጅግ የተራራቀ ነው ከዚህም በላይ ገሃድ በሆነው ትግሳቸው ውስጥ ሰውር የሆነ የየግል ዓሳማ ነበራቸው የትግሉን ይዘት በሚመለከት ኢህአፓ በኀኅብረብሔራዊ ድርጅት የሚመራ የመደብ ትግልን በቀዳሚነትና በአፅንኦት ሲያስቀምጥ ሕውሓት ግን ትግሉ ሊሰምር የሚችለው የተለያዩ ጭቁን ብሔር ብሔረሰቦች በራሳቸው ድርቿት አማካኝነት ትግላቸውን ጀምረው ከዚያ በኋላ የኅብረት ግንባር ሲፈጥሩ ነው የሚል አቋም ያዘ ከዚህ ልዩነት በተጨማሪም ሕወሓት ሙሉ አእምነቱን በገጠር የትጥቅ ትግል ላይ ሲያሳርፍ ኢህአፓ ደግሞ ተቀባይነት አግኝቶ የነበረው በከተማ ነው ብሎ ስላሰበ በከተማ የትጥቅ ቸግል ሳይ እምነቱን አሳድሯልበተጨማሪም ኢህአፓ እንደ ነጭ ማርኒሲስትነቱ አርኦአደሩ አብዮታዊ ሀይል አይደለም ላብ አደሩ እንጅ ብሎ በማመኑ ነበር ከሁሉም በላይ ግን የሻዕቢያን ከጀርባ ሆኖ በሰርጎ ገቦቹ አማካኝነት ኢህአፓን መጠቀሚያ ማድረጉን ሳንዘነጋ ዋናው ልዩነታቸው በህወሓት ውስጥ የነበረው የመገንጠል መሻትና በኢህአፓ ውስጥ የነበረው መገንጠልን ያለመሻት የፀባቸው መንስዔ ነው በዚህ ልዩነት ሕወሓት የኢህአፓን አባላት ቢቻል በእሱ አቋም እንዲስማሙ አድርጎ ማሳመንና መቀላቀል ካልተቻለ ያመኑለትን መርጦ ወስዶ የቀሩትን መደምሰስ ካልሆነም ከአካባቢው ማባረር ነበረበት ያደረገውም ይሄንኑ ነው በዚህ መሠረት ገሚሱ የኢህአፓ አባሳት ተደመሰሰጥቂቶቹ ተባባሪ ሆነው ተቀላቀሉ የቀሩት ጓዛቸውን ጠቅልለው ወደ ጎንደርና ወደ ወሎ አፈገፈጉ አንዳንዶቹም የከተማ ሽብራቸውን ቀጠሴሌሌሎችም ለደርግ እጃቸውን ሰጥተው ከደርግ ጋር መስራት ጀመሩደርግም ምልስ የኢህአፓ አባላትን እጁን ዘርግቶ ተቀበሳቸውዣዛድርጅታችውን ሚስጥር አወጡበደርግ ተይዘው የሚታሰሩ አባላትን መርማሪ ሆነው እስኪሰሩ ድረስ ለደርግ ታማኝ ሆነው ዘለቁይህ በእንዲህ እንዳለም የየራሳቸውን ብሔር እንዲያደራጁ ወደየክልላቸው ቀድመው የተላኩ ምልምሎች የተገኙት በዚህ አጋጣሚ መሆኑ መዘንጋት የለበትም በዚህ ዓይነት በትግራይ ግዛት ውስጥ ብቸኛው የትጥቅ ትግል አራማጅ ሀወኅት ሆነ እነዚህ ጅምር የነፃነት ንቅናቄዎችና የውስጥ ፍጭቶች ለሻዕቢያ ሠርግና ምላሹ ነበሩ ኅብረብሔራዊነት ብሔረተኝነት ወዘተ ለሻዕቢያ ምኑም አይደሌም ብቻ ኢትዮጵያ ውስጥ ሻብሩም ተቃውሞውም ፍጅቱም ይፋፋምለት እንጂ ሌላው ሁሉ ነገር አያገባውምም አይገባውምም የእሱ ስራ በኢትዮጵያውያን የግራ ኃይሎች ውስጥ የራሱን ዓላማ ማስፈፀም የሚችልበት የመገንጠል ግቡን የሚያፋጥኑለትን ልዑካን ማሰማራት ብቻ ነው ለዚህም ምቹ ሆኖ ያገኘው ከሕወሓት ይልቅ ኢህአፓን ነበር መጀመሪያ ላይ ደርግ ሕወሓትን ከመጤፍ አልቆጠረውም ነበር ለድርጅቱ መፈጠር ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎችን ትኩረት በመንፈግ አንድ የሻዕቢያ ተቀፅላ ቡድን አድርጎ ነበር የወሰደው ስለዚህም ደርግ ሙሉ ኃይሱን ያዘመተበት ሻዕቢያ ከተመታ ሕወሓትም አብሮ ይከስማል ብሎ ጥርጣሬ አልባ ግምት ውስጥ ገባ ነገር ግን ሕውሓትና ሻዕቢያ አንድ አልነበሩም አንድነታቸው ሰፊ ልዩነታቸው ጠባብ የሆኑ የተነጣጠሉ ቡድኖች ናቸው ይልቁንም ም ሻዕቢያ መጀመሪያ ላይ ከሕወሓት ይልቅ ቀድሞ ወደጎለበተው ወደ ኢህአፓ ነበር ያተኮረውና በኀብረት ለማመፅ ሁኔታዎችን ያመቻቸው ሆኖም ኢህአፓ ከትግራይ ተጠራርጎ ሲወጣ ፊቱን ወደ ሕወሓት አዞረ ሕውሓት በመላ ትግራይ የበላይነቱን ካሰፈነ በኋላ የተመሠረተው ። ሲል አዘዘ ሕወሓትም በበኩሉ ጦሩ ሲወረወር ተሰወር የሚል ትዕዛዝ ሰጥቶ ስልታዊ ማፈገፈግ አደረገ በዚህ አይነት የሚለቀቁ ቦታዎችን በተነጣይ ክፍል እያስጠበቁ ሲዝሰግሱ የሠራዊቱ ኃይል እያነሰ ቢበታተንም ድል ያልሆነ ድል መሰል ተግባር ሆኖ ሰፊ የፕሮፓጋገዳ ሽፋን ተሰጠው ምርኮ ተብለው ጥቂት መሣሪያዎች በመገናኛ ብዙሃን ታዩ ቀጣይነት ግን አልነበረውም ይልቁንም በጄኔራሉና በሻምበሉ መካከል የነበረው የታዥነትና የአዛዥነት አለመጣጣም እየተካረረ ሄዶ በየጦር ግንባሩ የሚታየውን ችግር አስተውሎ የጋራ የመፍትሄ እርምጃ መውሰድ ተሳናቸው ብዙም ሳይቆይ የቁርጡ ቀን ደረሰና በ ዓም ከሀዳር እስከ ባሉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሻዕቢያ በሳህል አውራጃ ውስጥ በሚገኙ የናደው ዕዝ ክፍለ ጦሮች ላይ ጠንካራ በትሩን አሳረፈ በኛው ክፍለ ጦርና በኛው ተራራ ክፍለ ጦር ሳይ ያረፈው ምት ከቀይ ኮከብ ዘመቻ በኋላ የመጀመሪያው ከባድ ውጊያ ሆኖ አፋቤት የተባለውን ቁልፍ ወታደሪዊ ቦታ ሻዕቢያ በቁጥጥሩ ሰር አደረገው በዚህ ወቅት የናደው ዕዝ አዛዥ ብርጋደር ጄኔራል ታሪኩ ዐይኔ ለአለቆቻቸው ሳያሳውቁ ሠራዊታቸውን ትተው አስመራ ከተማ ነበሩ እኒህ ጄኔራል ወደ ሳሀል ተመድበው ከመሄዳቸው በፊት መቀሌ አካባቢ ለሰፈረው ጦር አዛዥ ሆነው በዎቹ ይሰሩ ነበር በዚያ ወቅት ወያኔ ዝመቻ አግአዚ አግአዚ ኦፕሬሽን ብሎ በሰየመው እስረኞችን የማስለቀቅ ድንገተኛ ወረራው ሲከሰት በወህኒ ቤቱ ዙሪያ የሚገኘው የጥበቃ ኃይል ከአቅም በላይ የሆነ ወረራ እንደመጣባቸው ገልፀው እርዳታቸውን ሲጠይቁ ጄኔራሉ ወህኒ ቤት ጠባቂ አይደለሁም የሚል መልስ ሰጥተው በመቅረታቸው የወያኔ ኃይል ያለ ችግር ወህኒውን ጥሶ ገብቶ የራሱን ሰዎች ስም እየጠራ በ ደቂቃ ውስጥ ይዞ ሄዷል ነበር ቁጥር በተጨማሪም የሊሲቀመንበሩንም ሆነ የሌሎች አዛቻቸውን ትዕዛዝ እላመንኩበትም እያሉ ከመፈፀም ይቆጠቡ እንደነበርና በሁሉም ዘንድ ጥርስ ውስጥ የገቡ ጄኔራል መሆናቸው ይነገርላቸዋል አሁን ደግሞ የአፋ ቤት ውድቀት የመጣው በጄኔራል ታሪኩ ዐይኔ ጥፋት ነው ተባለና ያለፍርድ ተረሸኑ እንዲሁም ብርጄል ከበደ ጋሼ ድል ከሆኑ ሁለት ክፍለ ጦሮች ውስጥ አንዱን ይመሩ ስለነበር በጥፋተኝነት ሙሉ ማዕረጋቸው እንዲገፈፍ ተደረገ እንዲህ ያለው ተግባር በጦሩ ፊት በተግባር መፈፀሙ ደግሞ የጦሩን ሰሜት የሚጎዳና ሞራሉንም የሚነካ መሆኑ አያጠያይቅም በአፋቤት ጦርነት ሺህ የደርግ ሠራዊት በአንድ ጊዜ ያለቀ ሲሆን ስፍር ቁጥር የሌለው የጦር መሣሪያ በሻዕቢያ እጅ ገባ ይህ ቦታ ለሻዕቢያ መጀመሪያ ወደ ቿፅዋ እንዲሁም ወደ አስመራ መረማመጃ ሆነው በጦርነቱ የወደፊት አቅጣጫ ላይም ለሻዕቢያ ድል መፋጠን ትልቁን ሚና ተጫውቷል በርካታ መኮንኖች በመማረካቸውም ሚስጥሩን ሁሉ የሠራዊቱን አሠፋፈር ሳይቀር በቀላሉ ለመረዳት ለሻዕቢያ ጠቅሞታል ሻዕቢያ እስከ መጋቢት ወር ድረስ አፋቤትን የማፅዳትና ሙሉ ለሙሉ የግሉ ለማድረግ በወሰደው ተከታታይ የማጥቃት እርምጃ ከነሙሉ የጦር ግምጃ ቤቷ ተረከባት ዘጠኝ የሶቭየት የጦር አማካሪዎችን ጨምሮ ማረከ የናደው ዕዝ በተጠቀሰው ወር ተናደ የኢትዮጵያ መንግስት ኤርትራን ሊነጠቅ ምንም አእንዳልቀረው እየተረዳ ነበር በትግራይ ላይ የተሰማራው የሶስተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ኛ ኮር የሕወሓትን ሰልታዊ ማፈግፈግ መነሻ አድርጎ ሲገሰግሰና ቅጥ ባጣ ሁኔታ እየሳሳ ሲሄድ በተናጠል ምት እየተደመሰሰ ራሱን መከላከል በማይችልበት ደረጃ ላይ ደረሰ በየካቲት ወር ዓም በሻዕቢያ ሜካናይዝድ ጦር ታግዞ በምዕራብ ትግራይ የምትገኘውን ሽሬ እንዳስላሴን በከፍተኛ መስዋዕትነት መቆጣጠር ቻለ ሺ ወታደር የያዘው ኛ ኮር ሙሉ ለሙሉ ተደመሰሰ ሕወሓት የምስረታውን የልደት ቀንን ጠብቆ የካቲት ያዴረሰው የ ሰዓታት ጥቃት ሽሬን መቆጣጠር ሲያስችለው ብርጋዴል ጄኔራል ክንፈና ብርጋጄል ጄኔራል ገሞራውን ጨምሮ በርካታ መኮንኖችን መማረክም ችሏሷል በኢትዮጵያ ጦርነት ውስጥ ጄኔራል ሲማረክ ይህ የመጀመሪያው ነባር የአፋ ቤት ድል ለሻዕቢያ ወሣኝ የድል ምዕራፍ እንደሆነው ሁሉ ለሕወሓትም የሽሬ ድል ተመሳሳይ ገዕታ ነበረው ቀጥሎ ተመሳሳይ ሽንፈትና ኪሳራ እዳይደርስ በሚል ከየካቲት ጀምሮ የደርግ ሰራዊት ያለውጊያ ከመቀሌ መውጣት ጀመረና ግማሹ ወደ አስመራ ግማሹ ወደ ሳሜን ወሎ ጓዙን ጠቅልሎ እንዲሄድ ተደረገ በሚስጥር የተከናወነው ሽሽት በ ቀናት ተጠናቆ የካቲት ቀን ሙሉ ለሙሉ መቀሌ ተለቀቀች የደርግ መንግስት ያለአንዳች ውጊያ ለሕወሓት የትግራይን ግዛት አስረከበ የሚገርመው ቦታውን ለማስከበር ሰፍሮ የነበረው ጦር ዝመቻ ቅጣው በሚል ስያሜ የዘመተ መሆኑ ነው ሳይቀጣም ሳይቀጣም ሹልክ አለ ከዚህ በኋላ ሕወሓት ትግራይን ደጀን አድርጎ ዘመቻውን ወደ መሐል አገር አስፋፋ የትግራይ ወጣትም ወደ እነሱ ከቀድሞው የበለጠ ይ አየተቀላቀላቸው የሰው ኃይላቸውን አሳደጉ ትግራይን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳው ድርጅት አገር አቀፍ የሆነ ሌላ አጀንዳ ማውጣት ግድ ሆነበት ከኢሠፓአኮ ወደ ኢሠፓ የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር መንግስት ደርግ ከምስራቁና ከሰሜኑ ጦርነት ጎን ለጎን ስልጣኑ ሕጋዊ ከለላ ያለውና በህዝብ ተሹሞ የተሰየመ መንግስት ሊያስመስለው የሚችል ተግባር ለመፈፀም ደፋ ቀና ይል ነበር ይህም በየካቲት ወር ዓም ተጀምሮ በ ወራት ውስጥ እንዲዋቀር የተደረገውን የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ አደራጅ ኮሚሽን ኢሠፓአኮነን መመስረት ሲሆን አደራጅ ኮሚሽኑ ከተዋቀረ በኋላ ደግሞ አምጦ የሚወልደው የኢትዮጵያ ሠርቶ አደር ፓርቲ ኢሠፓ የመጨረሻው አውራ ፓርቲ ይሆንና የደርጉን ሊቀመንበር ሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን ብቸኛ መሪ አድርጎ እስከፍፃሜው እንዲዘልቁ ማድረግ ዓላማና ግቡ ነው ዓላማው ከግቡ ይደርስ ዘንድም ገና ከጅምሩ በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት ነበረበትና የኮሚሽኑ ምስረታ አዋጅ ይፋ ከመደረጉ በፊት በክፍላተ አገራት በአውራጃና በወረዳዎች ላይ ታማኝ ታማኝ የመንግስቱ ተጠሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ቅድመ ስራቸውን እንዲያከናውኑ ተመደቡ በየቦታው ቢሮዎችን ማዘጋጀት ተገቢ ሰዎችን መመልመል መሰናክል ሊሆኑ ይችላሉ የተባሉትን ማጥራት የመንግስቱን መልካም ስብዕና ማንፀባረቅ የሚሉት ከቅድመ ስራዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ከዚህ በኋላ በኢማሌድኅ ጥላ ሰር ተሰባስበው ከነበሩ ድርጅቶች ውስጥ በአባልነት ይሳተፉ ከነበሩ ግለሰቦች ጀምሮ የፖለቲካ ተሳትፎ እስከሌላቸው ግለሰቦች ድረስ ምሁራን የኪነጥበብ ሰዎች ታዋቂ ግለሰቦች የፈጠራ ባለቤቶች አምባሳደሮች ሚኒስትሮች ከጦር ኃይሉም ከፖሊስ ሠራዊትም ጡረተኛ አርበኞችም ሳይቀሩ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በ ኢሠፓአኮ መስራች ጉባዔ ሳይ እንዲሳተፉ ተደረገ እነዚህ ከድፍን ኢትዮጵያ ተመርጠው በጉባዔው ለመገኘት የተጋበዙ ዜጎች ቁጥራቸው ሺ ሲሆን በታላቁ ቤተመንግስት ጊቢ ውሰጥ ባለው የምኒልክ አዳራሽ ጳጉሜ ቀን ዓም ከጠዋት ጀምረው በመስራች ጉባኤው ላይ በጋራ ተገኝተው ያዳራሹን ግድግዳና ኮርኒስ በጋለ ጭብጨባ ሲያናጉት ዋሉ ጉባዔው በማግስቱም ቀጠለኖ ቋሚ ተለዋጭ አባላት ያሉት ማዕከላዊ ኮሚቴውን ሰየመ ከቋሚ የማዕከላዊ አባላት ውስጥ ዎቹ መለዮ ለባሾች ፖሊስን ጨምሮ እንዲሆኑ ሲደረግ ቱ በአፋቤት ጦርነት ሺህ የደርግ ሠራዊት በአንድ ጊዜ ያለቀ ሲሆን ስፍር ቁጥር የሌለው የጦር መሣሪያ በቫዕቢያ እጅ ገባ ይህ ቦታ ለሻዕቢያ መጀመሪያ ወደ ጄፅዋ እንዲሁም ወዴ አስመራ መረማመጃ ሆነው በጦርነቱ የወደፊት አቅጣጫ ላይም ለሻዕቢያ ድል መፋጠን ትልቁን ሚና ተጫውቷል በርካታ መኮንኖች በመማረካቸውም ሚስጥሩን ሁሌ የሠራዊቱን አሠፋፈር ሳይቀር በቀላሉ ለመረዳት ለሻዕቢያ ጠቅሞታል ሻዕቢያ እስከ መጋቢት ወር ድረስ አፋቤትን የማፅዳትና ሙሉ ለሙሉ የግሌ ለማድረግ በወሰደው ተከታታይ የማጥቃት እርምጃ ከነሙሉ የጦር ግምጃ ቤቷ ተረከባት ዘጠኝ የሶቭየት የጦር አማካሪዎችን ጨምሮ ማረካ የናደው ፅዝ በተጠቀሰው ወር ተናደ የኢትዮጵያ መንግስት ኤርትራን ሊነጠቅ ምንም እንዳልቀረው እየተረዳ ነበር በትግራይ ላይ የተሰማራው የሶስተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ኛ ኮር የሕወሓትን ስልታዊ ማፈግፈግ መነሻ አድርጎ ሲገሰግስና ቅጥ ባጣ ሁኔታ እየሳሳ ሲሄድ በተናጠል ምት እየተደመሰሰ ራሱን መከላከል በማይችልበት ደረጃ ላይ ደረሰ በየካቲት ወር ዓም በሻዕቢያ ሜካናይዝድ ጦር ታግዞ በምዕራብ ትግራይ የምትገኘውን ሽሬ እንዳሰላሴን በከፍተኛ መስዋዕትነት መቆጣጠር ቻለ ሺ ወታደር የያዘው ኛ ኮር ሙሉ ለሙሉ ተደመሰሰ ሕወሓት የምስረታውን የልደት ቀንን ጠብቆ የካቲት ያደረሰው የ ሰዓታት ጥቃት ሽሬን መቆጣጠር ሲያስችለው ብርጋዴል ጄኔራል ክንፈና ብርጋጄል ጄኔራል ገሞራውን ጨምሮ በርካታ መኮንኖችን መማረክም ችሏል በኢትዮጵያ ጦርነት ውስጥ ጄኔራል ሲማረክ ይህ የመጀመሪያው ነበር የአፋ ቤት ድል ለሻዕቢያ ወሣኝ የድል ምዕራፍ እንደሆነው ሁሉ ለሕወሓትም የሽሬ ድል ተመሳሳይ ገፅታ ነበረው ቀጥሎ ተመሳሳይ ሽንፈትና ኪሳራ እዳይደርስ በሚል ከየካቲት ጀምሮ የደርግ ሰራዊት ያለውጊያ ከመቀሌ መውጣት ጀመረና ግማሹ ወደ አስመራ ግማሹ ወደ ሰሜን ወሎ ጓዙን ጠቅልሎ እንዲሄድ ተደረገ በሚስጥር የተከናወነው ሽሽት በ ቀናት ተጠናቆ የካቲት ቀን ሙሉ ለሙሉ መቀሌ ተለቀቀች የደርግ መንግስት ያለአንዳች ውጊያ ለሕወሓት የትግራይን ግዛት አስረከበ የሚገርመው ቦታውን ለማስከበር ሰፍሮ የነበረው ጦር ዝመቻ ቅጣው በሚል ስያሜ የዘመተ መሆኑ ነው ሳይቀጣም ሳይቀጣም ሹልክ አለ ከዚህ በኋላ ሕወሓት ትግራይን ደጀን አድርጎ ዘመቻውን ወደ መሐል አገር አስፋፋ የትግራይ ወጣትም ወደ እነሱ ከቀድሞው የበለጠ እየተቀላቀላቸው የሰው ኃይላቸውን አሳደጉ ትግራይን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳው ድርጅት አገር አቀፍ የሆነ ሌላ አጀንዳ ማውጣት ግድ ሆነበት ከኢሠፓአኮ ወደ ኢሠፓ የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር መንግስት ደርግ ከምስራቁና ከሰሜኑ ጦርነት ጎን ለጎን ሰልጣኑ ሕጋዊ ከለላ ያለውና በህዝብ ተሹሞ የተሰየመ መንግሰት ሲያስመስለው የሚችል ተግባር ለመፈፀም ደፋ ቀና ይል ነበር ይህም በየካቲት ወር ዓም ተጀምሮ በ ወራት ውስጥ እንዲዋቀር የተደረገውን የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ አደራጅ ኮሚሽን ኢሠፓአኮን መመስረት ሲሆን አደራጅ ኮሚሽኑ ከተዋቀረ በኋላ ደግሞ አምጦ የሚወልደው የኢትዮጵያ ሠርቶ አደር ፓርቲ ኢሠጋ የመጨረሻው አውራ ፓርቲ ይሆንና የደርጉን ሊቀመንባር ሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን ብቸኛ መሪ አድርጎ እስከፍፃሜው እንዲዘልቁ ማድረግ ዓላማና ግቡ ነው ዓላማው ከግቡ ይደርስ ዘንድም ገና ከጅምሩ በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት ነበረበትና የኮሚሽኑ ምስረታ አዋጅ ይፋ ከመደረጉ በፊት በክፍላተ አገራት በአውራጃና በወረዳዎች ላይ ታማኝ ታማኝ የመንግስቱ ተጠሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ቅድመ ስራቸውን እንዲያከናውኑ ተመደቡ በየቦታው ቢሮዎችን ማዘጋጀት ተገቢ ሰዎችን መመልመል መሰናክል ሲሆኑ ይችላሉ የተባሉትን ማጥራት የመንግስቱን መልካም ስብዕና ማንፀባረቅ የሚሉት ከቅድመ ስራዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ከዚህ በኋላ በኢማሊድኅ ጥላ ሰር ተሰባስበው ከነበሩ ድርጅቶች ውስጥ በአባልነት ይሳተፉ ከነበሩ ግለሰቦች ጀምሮ የፖለቲካ ተሳትፎ እስከሌላቸው ግለሰቦች ድረስ ምሁራን የኪነጥበብ ሰዎች ታዋቂ ግለሰቦች የፈጠራ ባለቤቶች አምባሳደሮች ሚኒስትሮች ከጦር ኃይሉም ከፖሊስ ሠራዊትም ጡረተኛ አርበኞችም ሳይቀሩ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በ ኢሠፓአኮ መስራች ጉባዔ ሳይ እንዲሳተፉ ተደረገ እነዚህ ከድፍን ኢትዮጵያ ተመርጠው በጉባዔው ለመገኘት የተጋበዙ ዜጎች ቁጥራቸው ሺ ሲሆን በታላቁ ቤተመንግስት ጊቢ ውስጥ ባለው የምኒልክ አዳራሽ ጳጉሜ ቀን ዓም ከጠዋት ጀምረው በመስራች ጉባኤው ሳይ በጋራ ተገኝተው ያዳራሹን ግድግዳና ኮርኒስ በጋለ ጭብጨባ ሲያናጉት ዋሉ ጉባዔው በማግስቱም ቀጠለና ቋሚ ተለዋጭ አባላት ያሉት ማዕከላዊ ኮሚቴውን ሰየመ ከቋሚ የማዕከላዊ አባላት ውስጥ ዎቹ መለዮ ለባሾች ፖሊስን ጨምሮ አንዲሆኑ ሲደረግ ቱ ጋ ሲቪሎች ነበሩበዚህም የአማን አንዶምን የመጀመሪያ ዕቅድ ደርግ በመጨረሻ በከፊል መተግበሩን ንረዳለንኣኤ ከተለዋጭ አባላቱ ውስጥ ደግሞ ዱ መለዮ ለባሽ ኙ ሲቪሎች ናቸው በተለዋጮቹ ውስጥ ቱ በቋሚዎቹ ውስጥ ቱ የደርግ አባላት እንዲሆኑ ተደረገ ሁሉንም አባላት በዕጩነት ያቆረቡት ሊቀመንበር መንግስቱ የነበሩ ሲሆን ያለአንዳች ተቃውሞ ይሁንታ ማግኘቱን ቆመው በጋራ ጭብጨባ ያረጋገጡት ደግሞ ሁሉም ተሳታፊዎች ነበሩ ኢሠፓአኮ ከተመሠረተ በኋላ ባደረገው የመጀመሪያ ስብሰባም የአደራጅ ኮሚሽኑ ሊቀመንበር አድርጎ መንግስቱን መምረጡን ለጠቅላላ ጉባዔው ሲያበስር ያ ከፍተኛ ድምፅ ያለው የጋለ ጭብጨባ ያለማቋረጥ ተስተጋባ ኮሎኔል መንግስቱ በደርግ ሊቀመንበርነታቸው ላይ የኢሠፓን ሊቀመንበርነት ደርበው ያዙ ከዚህ በኋላ ሊቀመንበሩና የመስራች ጉባዔ አባላቱ በሲቪልና በወታደራዊ ሰልፍ የደመቀውን የአብዮቱን ኛ ዓመት በንል በአብዮት አደባባይ አክብረው ወደየመጡበት ተመለሱ ወደየመጡበት የተመለሱት የመስራች ጉባዔ አባላት በየክልላቸው ኢሠፓአኮን አቀነቀኑ ሊቀመንበር መንግስቱም በተሰጣቸው ስልጣን መሠረት የማዕከላዊ ኮሚቴውን ስራ አስፈፃሚዎች የፖሊት ቢሮ አባላትን መርጠው በየዘርፉ መደቡ ሻምበል ለሠ አስፋው የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ የርዕዮተዓለም ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ተካ ቱሉ የዲሲፒሊንና ቁጥጥር ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አቶ ታዬ ጉርሙ የኅብረት ስራ ማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ብርሃኑ ባይህ የውጭ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ውብሸት ደሴ የአስተዳደርና ፋይናንስ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ገብረየስ ወልደሃና የአብዮታዊ ጦር ዋና ፖለቲካ አስተዳደር ኃላፊ ሻለቃ ተካልኝ ባልቻ የማዕከላዊ ኮሚቴ ጽቤት ኃላፊ ሆነው ተመድበው ስራቸውን ቀጠሉ ኢሠፓአኮ በዚህ መልኩ ተዋቅሮ ሲያበቃ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ሁሉ በስሩ ሆኑ የኢትዮጵያ ሀዝብ ወሬ ስለ ኢሠፓአኮ እንዲሆን ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ስራ ተሰራ ሲቪልና ቴችጅወታደሩ እየተኖናቀ እንዲሁም ሌሎች የውስጥ ችግሮችን ይዞ ለመቀጠል ከመገደዱም ባለፈ አደራጅ ኮሚሽኑ የፀነሰው ፓርቲ ነውና አብሮ ለመወለድ ሲባል የሚደረገው ሹክቻ የበረታ ነበር በዚህም ላይ የሰሜንና የምስራቁ ጦርነት አለ የኢህአፓ ሠርጎ ገቦችን መከላከልም ሴላ ፈተኖ ነበር የከፍለሃገራት ኮሚቴዎችን ፀብ ማርገብኖ መሸምገልም ተጨማሪ ስራ ሆኗል ምንም ኪሆን ግን ኮሚሽኑን ተንከባክቦ ዳር ማድረስ አላዳገተም ኢሠፓአኮ ከፍተኛ በጀት ተመድቦለትና የህዝብ ድጋፍም አግኝቶ ጠቅሳላ ጉባዔ ማዕከላዊ ኮሚቴ የስራ አስፈፃሚ ኮሜቴ የክፍሳተሃገር ኮሚቴ እና በየቀበሌው ማኅበራትና መስሪያ ቤቶች የተዋቀሩ መሠረታዊ ድርጅቶች እንዲኖሩት ተደርጎና ራሱን የቻለ የአሠራር መዋቅር ተዘርግቶለት ከቀበሌ እስከ አጠቃላይ ምክር ቤት ባለው የአመራር ቦታ ላይ ይመጥናል የተባለ እድሜው ከ ዓመት በላይ የሆነ ዜጋ ከየአቅጣጫው ተሰብስቦ በዕጩነት ተመዘገበ ከሞላ ጎደል የዕጩዎች መመዘኛ አጭር የህይወት ታሪከና ለአብዮቱ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚል ነበር ዕጩዎችን ለማበጠር የተሰየሙት ኮሚቴዎችም የአብዮታዊ ሠደድ አባላት የበረከቱበት ነው በደርግ የበላይነት እየተዳፈኑ የነበሩ የዘመኑ ፓርቲዎችም በዚያ ወቅት ገና ተደመስሰው አልከሰሙም ነበርና በተቻላቸው መጠን ዕጩዎቻቸውን አቅርበዋል የዕጩዎች ዝርዝር ከተጠናቀቀ በኋላም ምርጫው በቀበሌ ቀጥሎ በከፍተኛ በመጨረሻም በአጠቃላይ ምክር ቤት ተካሂዶ በሁሉም ከተሞች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ ከዚሁ ጋር ተያይዞም የሠራተኛና የገበሬ ማኅበራት ተደራጁ በዚህ መሠረት ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን በአንድ በኢሠፓእአእኮ አመራር መዳፍ ስር ማድረግ ተቻለ ኢሠፓአኮ ተልዕኮ በሰፊው ህዝብ የጋራ ርብርቦሽ ይሳካል የሚል መፈክር ያላሰማ ዜጋ ፀረ አብዮተኛ ተብሎ ይፈረጃል የኮሚሸኑ ልሳን ሠርቶ አደር ጋዜጣ ሙሉ ስለኢሠፓአኮ የሚያትት ሆነ እንዲህ ሆኖ የፓርቲው መወለጃ ጊዜ እስኪቃረብ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እንዲፋጠኑ አስፈላጊ ዝግጅቶች እንዲደረጉ የሌኒቐና የትግላችን ሐውልቶች ግንባታቸው አልቆ በጌጣጌጥ እንዲንቆጠቆጡ ዋደረገ ኢሠፓአኮ በተመሠረተ በኛ ዓመቱ በ ጥኢትዮጵያ ሠርቶ አደር ፓርቲን ኢሠፓን ሲወልድ በጥቂቱ በዓሉን የወሎው ድርቅ አደበዘዘው እንጂ አጠቃላይ የከተማዋ በመብራትና በባንዲራ ማሸብረቅና ሌላው ሁሉ ዝግጅት የቀድሞውን የእነጃንሆይን የንግስ በዓል ሬይ የሚያስታውስ ሆኖ ነው የታየው እንዲህ ያማረችው ከተማ የመሳ አገሪቱን የፓርቲ ተወካዮችና የውጭ አገር እኋጋኃዶችን በክብር ተቀበለች ይህ የንግስ በዓል በአብዮቱ ኛ ዓመት የድል በዓል ወቅት በደማቅ ስነስርዓት ከመከበሩ ጥቂት ቀኖናት ቀደም ብሎ ጳጉሜ ቀን ዓም የፓርቲው መስራች ጉባዔ ተሰብስበው ሰኢሠፓ ምስረታ እውቅና ሰጥተዋል በጉባዔው ሳይ ከሺ በላይ የኢሠፓአኮ አባላትና ከ በላይ ታዛቢዎች ተገኝተዋል የኢሠፓአኮ ተመራጭ አባላት ከሠራተኛው ከገበሬውና ከወታደሩ የተወጣጡ ይሁኑ እንጂ በመቶው አባላት ከመለዮ ለባሹ የተውጣጡ ናቸው ያው እንደተለመደው ስለሆነ ዝርዝር ውሰጥ መግባት ሳያስፈልግ በእለቱ የዕጩዎች ስም ዝርዝር ለቋሚ ማዕከላዊ ኮሚቴና ለተለዋጭ አባላት የታሰቡ ሰዎች ቀረቡ ምርጫውም ለብዙሃን መገናኛ የሚሆኑ ቀረፃዎች እስኪከናወኑ ድስ እውነተኛነተን ተላብሶ ሲካሄድ ቆየና የድምፅ መስጫ ሳጥናኙ የምርጫ አስፈፃሚ ሆነው ለተመደቡት ለኮሎኔል ብርሃኑ ባይህ ተለጠ ከ ሰዓት በኋላ የቆጠራ ውጤቱ ተነበበበዚህ መሠረት ኮሎኔል መንኀሰቱ ቁልፍ የሆነውን የፖፓርቴ ዋና ፀሐፊነት ከመያዛቸውም በላይ ሁለት መቶ አባላት ያሉት የማዕከላዊ ኮሚቴና አስራ ስምንት አባላት ያሉት የፖሊት ቢሮ ሊቀመንበር ሆነው ቁጭ ማለታቸው ተረጋገጠ ከኢሠፓአኮው ምስረታ ጋር ተመሣሣይ በሆነ መልኩም የፖሲት ቢሮው አባላት ለመንግስቱ ታማኝነታቸውን ያረጋገጡና በመንግስቱ አቅራቢነት የተመረጡ የደርግ አባላት ቴክኖክራቶችና የማርከሲዝም ሌኒኒዝም አቀንቃኞች ነበሩ በዚህ መልኩ ኢሠፓአኮ ኢሠፓን ወለደ ፓርቲው ሶሻሊስታዊ ሠነዶችን አፅድቆ ስራውን ቀጠለ መንግስቱም እቅዳቸው እየሰመረ በመቀጠሉ ደስ ተሰኙ ሆኖም ከአባላቱ በኩል ሁለት ተቃውሞ ነበር አንዱ በምርጫው ድራማዊ ከንውን ካኮረፉቸ በኩል የተደመጠ ማጉረምረም ሲሆን ሌላው የአገሪቱ ዜጎች በረሃብ እየተቀጠፉ ይህን ያህል ከፍተኛ ገንዘብ ለፓርቲ ምስረታ ተብሎ በመመደቡ ነው በእርግጥም መንግስቱ እስከዚህ ጊዜ ድረስ ትኩረታቸው ፖርቲው ላይ ነበርና ይህንኑ ዳር ካደረሱ በኋላ ነው በፍጥነት ወደ ድርቁ ጉዳይ ፊታቸውን ያዞሩትናኖ ቀደም ሲል አብዮቱ ፍሬዎች በሚል ርዕስ ስር ተካትቶ ያየነውን የመፍትሄ እርምጃ መውሰድ የጀመሩት በተረፈ በምርጫው ፍትሐዊ አለመሆን የተደመጠውን ጉርምርምታ ከመጤፍ አልቆጠሩትም እናም ከዚህ ጊዜ በኋላ ከጓድ ሲቀመንበር መንግስቱ ኃይለማርያም አብዮታዊ አመራር ጋር ወደፊት ተባለ ሊቀመንበር መንግስቱ አሁን የቀራቸው ሁለት ያህል ቀላል ስራዎች ናቸው ሕጉመንግስቱን ማስረቀቅና ማፅደቅ ሪፐብሲኩን አውጆ ህዝባዊ ምርጫ ማከናወን ምርጫውንም አሸንፈው ፕሬዝዳንት መሆንና እስከመጨረሻው መንገስ እነዚህን ተግባራት ከማከናወናቸው በፊት ግን በፓርቲው ምስረታ ማግስት የተከሰተው ከባድ የኢኮኖሚ ቀውስ ኢሠፓን አላራምድ ስላለ አንዳንድ እርምጃዎችን መውሰድ ቀዳሚ ተግባር መሆኑ የግድ ሆኖ ተገኘ ሰማያዊ ካኪ መልበስም የመጣው የኢኮኖሚ ቀውሱን ተከትሎ ነውና እሱኑ ወደማየት እንለፍ የኢኮኖሚ ተሐድሶ ወቅቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ለድርቅ አደጋ የተጋለጡበትና ድርቁን ተከትሎ በተከሰተው ረሃብም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ቬጎች ለአሠቃቂ ሞት የተዳረጉበት ወቅት ነው ይህንን ዛሬም ድረስ አልለቅ ያለ የጎን ውጋት ለማስወገድ ኢትዮጵያ አቅም አልነበራትም አሁንም ያላትም ወደፊት ይኖራት ይሆናል እንጂ ስለዚህ ወደለጋሽ አገራት አኮፋዳ ይዞ መዞር የግድ ነበርና መንግስቱ ይሀን አድርገው የነብስ አድን ሰራ ሠርተዋል ነገር ግን በወቅቱ ብዙ አገሮች በርዕዮት መለያየት ምክንያት ፊታቸውን አሩ በዚህም ላይ በርሃ ያሉ ተቃዋሚዎች ደርግ ጃንሆይን ሲጥል እንዳደረገው ሁሉ ረሃቡንና የፓርቲ ምስረታ ግብዣውን እያቀናጁ ለፕሮፓጋንዳ ስለተጠቀሙበት የተፈለገው እርዳታ በተፈለገው መጠን ሲገኝ አልቻለም የተፈጠረውን ክፍተት በራስ ጥረት ለመሙላት ሲባልም እቅድ ነድፎ የነብስ ኣድን ስራውን ለመስራት የሚያስችል የተፈጥሮ ችግር መቋቋሚያ ኮሚቴ ተቋቁሞ እርዳታውን ለተጎጂዎች ማሰራጨትና ተጎጂዎችን ወደ ሌላ ሠፈራ ማጓጓዝ ተጀመረ ለዚህም ኮሎኔል ብርሃኑ ባይህ የእርዳታ ገንዘብና ቁሳቁስ አሰባሳቢ ሻምበል ለገሠ አስፋው የሠፈራ መርሐ ግብር ኣስፈፃሚ ዘርፎች ኃላፊ ሆነው ተመድበው በየክፍላተአገሩ እስከቀበሌ ድረስ በተዋረድ የሚሰሩ ሰዎች ተመድበው በህዳር ወር ዓም ስራቸውን ጀምረዋል ሂደቱን አጠናክሮ በመቀጠልም ከትንሹ ስንዴ እደላ እስከ ትልቁ የጣና በለስ ግድብ የዘለቀ የመፍትሄ እርምጃ ተወስዷል ድርቁ ያስከተለው ችግር ወደ ከተማም ተዛምቶ በአዲስ ኣበባ ሳይቀር ከፍተኛ የእህል እጥረት ተከስተ በሚያስደነግጥ ሁኔታ አንድ ኩንታል ጤፍ ብር አራት መቶ ብር ተሸጠ ዳቦ ጠፋ አትክልት የለም የውሃ እጥረትም ተፈጠረ በዚህ ምክንያት በየካቲት ወር የኮሌራ ወረርሽኝ የከተማውን ህዝብ አጠቃ ወረርሽኙ የፖለቲካ ኪሣራ እንዳያስከትል አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የሚል መጠሪያውን መንግስት አተት በሚል ምህፃረቃል ሸፈነው የጤኖ ጥበቃ ሚኒስትር በወሰደው ፈጣን የመከላከል ርምጃ ሠዎች ብቻ ገድሎ በሽታውን መግታት ተቻለ አንዲህ እያለ የአገሪቱ ኢኮኖሚ በፍጥነት እያሽቆለቆለ ሲሄድ ጫንግሰት ለህዝቡ የተለያዩ ምክሮችንና የተመጠነ ኑሮ መልመድ እንደሚገባ ማስተማር ጀመረ ቁጠባን ልመዱ ሲል አስጠነቀቀ ጓድ ሊቀመንበር ራሳቸውን አርአያ አድርገው ማሳየት ነበረባቸውኖ ያው የወታደር ልብሳቸውን ካወለቁ ቆይተው ነበርና በምትኩ ሱፍና ከረባት አድርገው ይታዩ ስለነበር አሁን ደግሞ የአገር ውስጥ ምርት የሆነውን ሠማያዊ ካኪ ኮምፕሌቱን ገጥመው መጡ አለው አለውና በካኪው ላይ ጠና የሚል ስንኝ ተቋጠረ ከካኪ ወደ ሱፍ ከሱፍ ወደ ካኪ ማለት ነው ወዲያው የፓርቲው አባላትና ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ይህንኑ ጥቁር ሠማያዊ ካኪ እንዲለብስ የሚያስገድድ ደንብ ወጣ ተግባራዊም ሆነ ያጉረመረሙት ብዙ ቢሆኑም ግን አሁን ካኪ ተለብሶ ምን ለውጥ ሊመጣ ነው። ብለው በጩኸት ከተናገሩ በኋላ ጎራዴውን ከአፎቱ መዥረጥ አድርገው ለጓድ ሊቀመንበር ሰጧቸው አሉሌ እረደው ይሁን እያረድናችሁ ነው ይሁን ትርጉሙን ባውል ባይረዱትም መንግስቱ ስጦታውን ተቀበሉ ከተሰብሳቢው ጉርምርምታ ተደመጠ በእለቱ ጓድ ሊቀመንበር መንግስቱ ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምረው እስከዚያች ታሪካዊ ያሏት ቀን ድረስ የነበረውን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ገፅታ ሰዓት በፈጀ ሐተታቸው አቀረቡ ሲቀጥሉም ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተደደር ደርግ ህዝባዊ አደራ በተቀበለበት በዚያ ቀውጢ ወቅት በገባው ቃል መሠረት ስልጣን ለታሪክ ሰሪውና ከታሪክ ጋር ለሚዘልቀው ለሠርቶ አደሩ ህዝብ እነሆ ሊያስረክብ ነው ደርግ ባለፉት የትግል የድል አመታት ለተከናወኑት አብዮታዊ ተግባራት ከሁሉጃቿ በላይ የድርጊቶቹም ሆነ የውጤቶቹ ባለቤት ለሆነው ለሠርቶ አደሩ ህዝብ ያሰውን ጥልቅና ታሳቅ አክብሮት እየገለፀዐ ለወደፊቱም ህዝቡ ለኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ አመራር በኢትዮጵያ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግንባታ የእድገት ትልሙን ሙሉ በሙሉ ዳር እንደሚያደርስ ከልብ ይመኛል አሉ በዚህም የስልጣን ምርኩዝ ሆኖ ያገለገላቸውን ዴርግ የተባለ ቡድን መክለሰሙን አረዱ የደርግ አባላት መክሰም የጀመሩት ከኢሥሠሥፓ ምስረታ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም ይፋ የወጣው እና በሕገመንግስቱ መሠረትም መኖር እንደሌለበት ግልፅ የሆነው በዚሁ ጊዜ ነው ይህ ማለት ግን አባላቱ ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎችን ከሚገባቸው ስልጣን ጋር ይዘው ሰለዘለቁ መክሰም ሊባል አይችልም ከቡድናዊ ባለሥልጣንነት ወደተናጠላዊ ሹማምንትነት ተለወጡ የሜለው የተሻለ ይገልፃቸዋል ከሊቀመንበሩ ንግግር በኋላ የነበረውን ጊዜም ልዩ ልዩ ሕገመንግስቱን ተንተርሰው የወጡ ኣዋጆችን በማፅደቅ ነበር ያለፈው በዚህም በ እንደራሴዎች አማካኝነት ስልጣኑን ተግባራዊ እንደሚያደርግና ዋናው የመንግስት ምክር ቤት እንደሆነ የመንግስት ምክርቤቱም የጉባኤና የስራ አስፈፃሚ አካል የተሰኙ የስራ ዘርፎች እንዳሉት ተገለፀ በሕገ መንግስቱ መሠረትም የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኢሕዴሪ ብሔረሰቦች በእኩልነት የሚኖሩበት ብሔራዊ መንግስት ነው ሠርቶ አደሩ ህዝብ የስልጣን ባለቤትነቱን ተግባራዊ የሚያደርገው በምርጫ በሚያቋቁመው ብሔራዊ ሸንጎና ያአካባቢ ሸንጎዎች አማካይነት ይሆናል ብሔረሰቦች በሸንጎው መወከላቸው ይረጋገጣል ኢሕዴሪ በዴሞክራሲያዊ ማፅከላዊኒት በሶሻሊስት ሕጋዊነትና ወዝአደራዊ ዓለም አቀፋዊነት መርህ የሚመራ መንግስት ነው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ ኢሠፓ የመንግስትና የመላው ህዝብ መሪ ኃይል ነው የውጭ ፖሊሲው በወዝአደራዊ ዓለምኣቀፋዊነት በሠላም አብሮ መኖርና በገለልተኝነት መርሆዎች ላይ የተመሠረተ ነው ኢህዴሪ በራስ ግዝና በአስተዳደር አካባቢዎች የሚዋቀር አሃዳዊ መንግስት ነው ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን አካል ብሔራዊ ሸንጎው ነው ፋ ብሔራዊ ሸንጎው ዋና ባልሥልጣን መሆኑን ካወጀ በኋላ የራሱን ስብሰባ አድርጎ በመሪነት ሳይ መሪነት በመሪነት ላይ መሪነት እየተቀዳጁ እዚህ የደረሱትን ሊቀመንበር መንግስቱ ኃይለማርያምን የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጦ እንደሾማቸው ይፋ አደረገ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም በዕለቱ ሳቃቸውን መቆጣጠር አእያቃታቸው ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ህዝብ በመረጠው ፕሬዝዳንት ተመራች በማለት የእንጨት መዶሻዋን አንስተው ጠረሌዛዋን ኳ አደረጓት ሸንጎው የኢህዴሪን ልዩ ልዩ የስልጣን አካላት ያዋቀረ ሲሆን እነዚህም የመንግስት ምክር ቤት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና የቁጥጥር አካላት ናቸው በዚህም መሠረት መንግስቱ ኃይለማርያም የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ አሰፋ ሊበን የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሾሙ ሌሎች የደርግ እባል የነበሩና ያልነበሩ መለዮ ለባሾችና ሲቪሎች በሚኒስትርነት በምክር ቤቱ አባልነት በምክትል ፕሬዝዳንትነትና በምክትል ጠቅላይ ሚንስትርነት እንዲሁም በልዩ ልዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ እንዱሾሙ ሆነው በጦርነት አጣብቂኝ ውስጥ ገብታ ውጥረት የነገሰባትን ኢትዮጵያን ማስተዳደር ቀጠሉ የሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የመጨረሻው የስልጣን ጣራ ላይ የመውጣት ህልም እውን ሆኖ በ ዓም ግቡን መምታት ቻለ ስለዚህም ኛው የድል በዓል ላይ ስልጣን ህዝቡ ተረክቧልናነ ወይም ስልጣን የህዝብ ሆኗልና የዚያ ዓመት መስከረም ሁለት ከሌሳው ጊዜ በተለየ መልኩ ደምቆ ተከበረ መፈንቅለ መንግስቱ እና ያስከተለው መዘዝ ግቦት ቀን ዓም ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ወደሚወዷት ምስራቅ ጀርመን ለስራ ጉብኝት ብለው ሄዱ የኢሠፓ የፖሊት ቢሮ አባላት የመንግስት ምክር ቤት አባላት ሚኒስትሮችና ጄኔራሎች ኤርፖርት ድረስ ሄደው በተለመደው መሽቆጥቆጥ በክብር ሸኝተዋቸው ተመለሱ መንግስቱ ግትር ሆነዋል ጦሩ እየተሸነፈ ነው የጄኔራሎች የጦር እቅድ በመንግስቱ ዘንድ ብዙም ተቀባይነት አያገኝም የተለየ ሀሳብ የሚያቀርብ የጦር አዛዥ በጥርጣሬ ዓይን ይታያል ሊቀመንበሩ የመረጡትና ወደተግባር እንዲተረጎም የሚሹት የዘመቻ ሰልት በሶቭየት ህብረት የጦር አማካሪዎች የሚቀርበውን የወረቀት ላይ የዘመቻ ንድፍን ነው ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎች በበታቾቻቸው በደርግ አባላት ይታዘዛሉ አንድ መቶ አለቃ ወይም ኝምበል አንድን ጄኔራል ያዛል መንግስቱ በታማኝነት እንጂ በሙያ ብቃት ማመኝና መሾም አልፈጠረባቸውም የተናቁም ይመስላቸዋል ከዚሁ ጋርም የደርግ አባል የሆኑ የበታች ሹማምንት ቁምነገሩ የበላይና የበታችነት ጉዳይ ሳይሆን የመንግስቱ ታማኝና ቀኝ እጅ ሆኖ መገኘቱን በመረዳታቸው በማዕረግ የሚበልጧቸውን ታላላቅ የጦር ጀግኖች ይንቋቸዋል በእነዚሀኖ እነዚህን በመሣሠሉ መነሻ ምክንያቶች በርከት ያሉ ጄኔራሎች የመንግስቱን አገዛዝ ጠልተውታል ፊት ለፊት መጋፈጥ የማይሞከር በመሆኑም ያለው ምርጫ መፈንቅለ መንግስት ማድረግ ነበርኖ በዚህ ጉዳይ በተለያዩ ቦታዎች ተሰብስበው መመካከር ከጀመሩ ቆይተዋል የጉዳዩ ጀማሪና ጠንሳሽ ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይ ነበሩ እቅዱ ከሁለትና ሦስት ዓመት በፊት ተነድፎ ሲብላላ የቆየ ነው በተለይ መንግስቱ በኤርትራ ያለው ጦር በተሸነፈ ቁጥር ችግሩ የጄኔራሎች ነው ብለው በማሚመናቸው ብዙዎችን ከነበሩበት ቦታ እያነሱና ዝቅ ከፍ እያደረጉ መሾም መሻር የጀመሩት ከ ጀምሮ ሲሆን ለአብነት ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይን ከአየር ኃይል ዋና አዛዥነታቸው አንስተው የኢንደስትሪ ሚኒስቴር ሚንስትር እንዲሆኑ አድርገዋል ይህ መሰሉ ሹም ሽር ለአመታት ተከታትሎ የተከናወነ እንደመሆኑ መጠንና በጄኔራሎቹም ዘንድ ስላልተወደደ ጥርስ ነከሳው ከተጠቀሰው ጊዜ የጀመረና ሲብላላ የኖረ ነገር ግን በ ግንቦት ወር ሲተገበር የተሞከረ ነው የዚችን እለት የመጨረሻ የአድማ ሰብሰባ ለማድረግ የተመረጠው ቦታ በመከላከያ ሚኒስትር መስሪያ ቤት ጊቢ ውስጥ የሚገኝና ከሚኒስትሩ ከሜጀር ጄኔራል ኃይለጊዮርጊስ ቢሮ አጠገብ ያስው ኣነስተኛ የመሰብሰቢያ ክፍል ነው በእለቱ ባልተለመደ ሁኔታ ይህ ጊቢ የጄኔራሎች መጠራቀሚያ ሆታ ታዬ እድመኞቹም በቀጠሯቸው መሠረት አንድ በኣንድ ወደዚያች ክፍል ገቡ በስብሰባው ላይም የተገኙት የል መርዕድ ንጉሴ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማኙር ም ሜጃል ኃይሉ ገብረሚካኤል የምድር ጦር ዋና አዛዥ ሜጃል አምሃ ደስታ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሪሪ አድሚራል ተስፋዬ ብርሃኑ የባህር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄል አለማየሁ ደስታ የምድር ጦር ምክትል አዛዥ ሜጄል ወርቁ ዘውዴ የፖሊስ ሠራዊት ጠቅሳይ አዛዥ ሜጄል አብዱላሂ ዑመር የመከላከያ ሚር አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ሜጄል ፋንታ በላይ የኢንደሰትሪ ሜኒስትር ሜጄል እበራ አበበ የወር ኃይሎች ምክትል ኤታማፕር ሹም ሜጄል ተስፋዬ ትርፌ የአብዮታዊ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ብጄል ሰለሞን ጋሻው የአየር ኃይል ኤታማዥር ሹም ብጄል ደሣለኝ አበበ የጦር ኃይሎች አካዳሚ አዛዥ ብጄል እርቅይሁን ባይሳ የኛው ኮር ዋና አዛዥ ብጄል ተስፋዬ ደስታ የአየር ኃይል ዘመቻ መኮንን ብጄል ነጋሽ ወልደየስ የፀኛው ኮር ዋና አዛዥ ብጄል እንግዳ ወልደአምሳክ የኛው ኮር ዋና አዛዥ ብጄል ገናናው መንግስቱ የኛው አየር ምድር አዛዥ ኮሞዶር ኃይሌ ወልደማርያም የጦር ኃይሎች ዘመቻ መምሪያ ባልደረባ ናቸውነበር ቁ በስብሰባው የተገኙት እነዚህ ብቻ ይሁኑ እንጂ ከየጦር ክፍሉ የተመለመሉ አዛፐችም የሚሰጣቸውን ትዕዛዝ ለመፈፀም ተዘጋጅተዋል እነዚህ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተሰብስበው የመጀመሪያ ውሣኔ ያደረጉት ሊቀመንበሩን ቀይ ባህር ሲደርሱ ፕሌኑን በሚሳኤል መምታትና ማሰናበት የሚል የነበረ ቢሆንም ከመንግስቱ ውጪ የተሳፈሩ በርካታ ንፁሃን ስቪሎች ስላሉ እነሱንም አብሮ መግደል ተገቢ አይደለም የሚል ሀሳብ ስለተነሳ ውሣኔው ተሻረና ከዚህ ይልቅ በወጡበት ማስቀረት እንደሚሻል ስምምነት ላይ ተደረሰ ዋና ሰብሳቢው ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይ ነበሩ ነገር ግን ወደ ስብሰባው የመጡት ዘግይተው ነበርና የሰብሳቢነቱን ቦታ ማጄር ጄኔራል መርዕድ ንጉሴ ይዘውታል ጄኔራል ፋንታ በላይ ወዴ ስብሰባው ገብተው ሲያዩ ቦታው ተይዚል ጄኔራል መርዕድ ዋና ሰብሳቢው ሲመጡ ቦታውን መልቀቅ ሲገባቸው ፀጥ አሱ ቢታይ ቢታይ መርዕድ ለፋንታ ሊለቂ ቀርቶ የመልቀቅ አዝማሚያም ሳያሳዩ ስብሰባውን መምራት ቀጠሉ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ የተሰባሰቡት ጄኔራሎች እዚያው በዚያው ሴላ መፈንቅለ መንግስት አደረጉ ሰልጣን ሠይጣን ነዋ። ፍኀ መ ኖድ አላቸው መሣሪያቸውን ከግምጃ ቤት እንዲያስቀምጡ ካደረገ በኋላ የመጣችሁት ለተሳሳተ ተግባር መጠቀሚያ እንድትሆኑ ነበር ነገሩ እለከሚጣራ በጥበቃ ስር ሆናችሁ እዚሀ ትቆያላችሁ በማለት በቁም እስር አቆያቸው ይሄን ተግባር ፈዕሞ ሲመለስ ሻለቃ ሸለማ በታዘዙት መሠረት በሁለተኛው ዙር የመጣውን አየርወለድ ወደ ቤተመንግስት መርተው አስገብተዋቸው ነበር በሁለት ዙር የመጡት ከታገቱ በኋላ ሦስተኛው አንቶኖቭ አዲስ አበባ ደርሶ ለማረፍ እያንዣበበ እንዳለ ለተሳሳተ ተግባር የተላኩ ወታደሮችን መጫንህሀ ስለተረጋገጠ ወደመጣሀበት ተመለስ እንቢ ካልክ ባለህበት እንደምትጋይ እወቅ የሚል ማስጠንቀቂያ ለአብራሪው ሲነገረው ወደመጣበት ተመለሰ በዚያች ዕለት አገሪቱን እየመሯት የዋሉት ቫምበል መንግስቱ ገመቹና ኮሎኔል ተስፋዬ ወልደስላሴ ነበሩ ለማለት ይቻላል የአድመኞቹን የግንኙነት መስመር በማቋረጥ ደሀንነቱ ኮሎኔል ተስፋዬ የአድመኞቹን አጋዥ ወታደሮችና የአዛሦችን የትብብር መረብ በመበጣጠስ ሻምበል መንግስቱ መተኪያ የሌለው ሚና ተጫውተዋል ከስብሰባው ውጪ ሆነው ጦር እንዲያስተባብሩ የተመደቡት ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ጥቂት ወታደሮችን ይዘው በግራ መጋባት ሲጠባበቁ ከቀኑ ሰዓት በአንድ መቶ አለቃ የሚመሩ በሻምበል መንግስቱ የተላኩ የልዩ ጥበቃ ብርጌድ ወታደሮች እርሳቸው ወዳሉበት ሄዱ እነዚህ ወታደሮች አካባቢውን እንዲቃኙ ቀድመው ተሳኩ እንጂ ሌላ ትዕዛዝ ያልተሰጣቸው ነበሩና ሄደው ከጄኔራል ቁምላቸው ሠራዊት ጋር ተላተሙ ጄኔራሉ ይህን ምንነቱን ያላወቁትን ወታደር አብረዋቸው በነበሩት ወታደሮች አስከብበው ትጥቁንም አስፈትተው ባዶ ቤት ውስጥ አዘጉባቸው እነርሱን ተከትለው የሄዱ ሌሎች ወታደሮችም በታንክ ታግዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ ጄኔራሉ በተመሳሳይ አስከብበው ታንካቹውንም ማርከው በግራ መጋባት መጠባበቃቸውን ቀጠሉ ሜጀር ጄኔራል ቁምላቸው ያለውጊያ እነዚህን ወታደሮችና ታንካቸውንም ጭምር በቀላሉ መማረክ ቢችሉም ከበላዮቻቸው ጋር የነበረው ግንኙነት በመቋረጡና ቀጣይ ስራቸውንም ባለማወቃቸው ምንም ሊያደርጉ አልቻሉም ምሽት ሰዓት ላይ ሻምበል መንግስቱ ገመቹ እንደተከበባ ወደዋለው ወደ መከላከያ ጊቢ አምርቶ በድምፅ ማጉያ ጊቧው እንደተከበበና በውስጡ የሚገኝ ዘበኛ ሲቪል ሠራተኛ ባለሥልጣን ጄኔራል ሁሌም እጁን ጭንቅላቱ ሳይ አጣምሮ በሁለተኛው በር እንዲወጣ አሳሰበ ሁሉም በአምባሳደር ቴአትር ቤት በኩል ባለው በር እጅ ወደ ላይ አድርገው ሲወጡ ብርጋዴል ጄኔራል አምነ ደሰታ እዚያው ራሳቸውን ገደሉ ቀጥስ ሜጀር ጄኔራል መርዕድ ንጉሴ ራሳቸውን በሻጉጥ ገደሉ ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይ እና ኮሞዶር ኃይሌ ወልደሜካኤል ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን እዚያው ውስጥ ተደብቀው ቀሩ ሌላው በሠላም ወጥቶ እጅ ሰጠ ይህ በእንዲሀ እንዳለ በሜጀር ጄኔራል ደምሴ ቡልቶ የተመራው የአስመራው አድማ እንደተጧጧፈ ቀጥሎ የነበረ ሲሆን በአስመራው ሬዲዮ ጣቢያ የመንግስቱ ኃይለማርያም አንባገነናዊ አገዛዝ እንዳበቃና ለውጥ እንደተደረገ ኢትዮጵያ ሠላም የሰፈነባት አገር ሆና እንደምትገነባ ወዘተ እየተገለፀ ነበር ሻዕቢያኖ ወያኔም ጉዳያችሁ ዳር እስኪደርስ ተኩስ አቁመናል ብለዋል በተመሳሳይም በጎንደር አዘዞ የነበሩት የኛው ኮር አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ዘውዴ ገብረየስ በአሰመራ ሬዲዮ የሚሰራጨውን መልፅክት በወረቀት እያባዙ ለህዝብ ይበትኑ ነበር በሰሜን ጎንደር የኢሠፓ ዋና ፀሐፊ የነበረው ሻምበል ገዛኸኝ ወርቄ ለስራ ጉዳይ አዲስ አበባ ወጥቶ ነበርና ወደ ጄኔራል ዘውዴ ደውሎ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ሰር መዋሉን በመግለፅ ጦሩን እንዲያረጋጉ ሲያዛቸው ር በል ያንተ አዛዥነት አክትሟል ብለው ስልኩን ዘጉበት ሻምበል ገዛኸኝ ወርቄ ወደ ዕዙ የፖለቲካ ኮሚሳር ደውሎ እዚህ ያለው አድመኛ ጄኔራል ሁሉ በቁጥጥር ስር ውሎ ታጉሯል ስጠገብህ ያለውን ጄኔራል ከነተከታዩ አፍሰህ አስረሀ ጠብቀኝ አለው ከሚሳሩ የታዘዘውን ፈፀመ አመሻሹ ላይ ግራ የተጋቡት ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ከነበሩበት አርሚ አቪየሽን ጊቢ ወጥተው ሁኔታውን ኣጣርተው ለመምጣት አንድ ታንክ አስከትለው የመከላከያን ጊቢ ከርቀት ለማየት ወደሚያስችለው ወደ ጎማ ቁጠባ ዳገታማ ጎዳና ሂደው ሲያዩ የተለየ ድባብ አስተዋሉ ጄኔራሉ ከአርሚ ኣቭየሻን እንደወጡ ወዲያው ነበር ጊቢው የተከበበው ስለዚህ አየር ወለዶች እዚያው እንዳሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ ጄኔራል ቁምላቸው ባቅራቢያቸው ወዳለው ኛ ፖሊስ ጣቢያ ሄደው የፖሊስ መምሪያ ጠቅላይ አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ወርቁ ዘውዴን በስልክ እንዲያገጀቸው ቢያዙም ቀድመው ከስብሰባው የወጡት ጄኔራል ሏገኙ አልቻሉሌም የፖሊስ አዛ ማምለጫ መንገዱ ሁሉ ተዘግቶባቸው ቤታቸው ውስጥ መሽገው የሚመጣውን ለመቀበል ተዘጋጅተው ነበር ከዚህ በኋላ ጄኔራል ቁምላቸው ሁሉም ነገር ማክተሙን ተረድተው ጥለዋቸው የመጡትን ጥቂት አየርወለዶችንም የራሳቸው ጉዳይ ብለው ራሳቸውን የሚያድኑበትን መንገድ መፈለግ ጀመሩ የአዲስ አበባው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በሻምበል መንግስቱ ገመቹ ብርቱ ትግል በተደረገ ከበባ እኩለ ሌሊት ሳይ በድል ተደምድሟል በሁሉም የጦር ከፍሎች የነበሩት ተባባሪዎች ሁሉ እጃቸውን ተይዘዋል አጠገባቸው ይገኝ የነበረውን ብሔራዊ ሚዲያ መቆጣጠር ሳይችሉ ወታደሮቻቸውን በየቦታው ሳይመድቡ ለህዝብ መረጃውን ሳያሰራጩ እርስ በርስ ሳይስማሙ ለማክሽፍ ማን ምን ሙከራ ሊያደርግ እንደሚችል ሳያውቁ ሳይገምቱና ሳይዘጋጁ በአንድ ጊቢ ውስጥ በምትገኝ ቢሮ ተሰብስበው መፈንቅለ መንግስት አድርገው ስኬታማነቱን ለጥቂት የቢሮው ሠራተኞች እና ለራሳቸው ኣአውጀው ጊቢ ውሰጥ ያሉትን አስጨብጭበው እዚያው ጊቢ ውስጥ ደም ተፋሰው እዚያው ጊቢ ውስጥ ተይዘው ቀሩ የአዲስ አበባው አስቂኝ መፈንቅለ መንግስት ሳይጀመር ተጨረሰ ሳይሞከር ከሸፈ ከሌሊቱ በ ሰዓት ጓድ ሊቀመንበር መንግስቱ ኃይለማርያም የምስራቅ ጀርመን ጉብኝታቸውን አቋርጠው አዲስ አበባ ደርሰው የተቀባይ ጋጋታ በሌለበት በቀጥታ ወደቤታቸው ገብተው እንቅልፍ ይወስዳቸዋል ብለን ባናስብም ተኙ ነግቶ ግንቦት ቀን ዓም ሆነ ማለዳ ላይ አሰመራ የሚገኘው የኛ የአየር ወለድ ክፍለጦር አባላት ፕሬዝዳንት መንግስቱን አመራር የሚቃወም ማንኛውም ድርጊት እብዮቱን የመቀልበስና ኤርትራን የማስገንጠል ሴራ ነው። በሚል ቁጭት ለዚያች ዕለት አስቦ የቀመረው ይመሰል ነበር ይሉናል ጄኔራል ፋንታ በላይ ተይዘው ማዕከላዊ ምርመራ ታሰረው ሳለ ለማምለጥ በመሞከራቸው በጠባቂዎች ተገደሉ ተብሎ በብዙሃን መገናኛ ተሰራጨ ሆኖም ታሪኩ ካለፈ በኋላ እንደተባለው የደህንነቱ ኃላፊ ሚስጥር ያወጡና ተባባሪነቴን ያሳውቁብኛል ብለው የራሳቸውን ሰው ልከው እስር ቤት ውስጥ እንዳስገደሏቸው ነው ለዚህም የተለያዩ የአሟሟታቸውን አይነት መሠረት ያደረጉ አሳማኝ ምክንያቶች ተዘርዝረዋል ከዚሀም በላይ ሊቀመንበር መንግስቱ ዋና ጠንሳሽ የሆኑትን ጄኔራል ፋንታን ማነጋገር ስለምፈልግ እንድታመጡልኝ የሚል ቀጠሮ አስይዘው ስለነበር ሁለቱ ከመገናኘታቸው በፊት ነበር የተገደሉት ከዚያም ሚኒስትሩን ገድለው ያመለጡት ጄኔራል አበራ አበበ አምልጠው እንደሄዱ ዘመዳቸው ቤት ተሸሽገው ለጥቂት ቀናት ከቆዩ በኋሳ ለደህንነቱ ለኮሎኔል ተሰፋዬ የሚያመልጡበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹሳቸው ቢጠይቋቸውም ዳግመኛ እንዳይደውሉ አስጠንቅቀው ቻው አሏቸው ጄኔራል አባራ የደህንነቱ እምቢታ ቢያበሳጫቸውም ምንም ሊሉት አይችሉምና ይልቁንም የት ሆፔ እንደደወልኩ አጣርቶ እንዳያስይዘኝ በሚል ሰጋት የመሸሸጊያ ቦታቸውን ለውጠው ወደ ሌላ ዘመድ ቤት ሄዱ የሴትዮዋ ባለቤት ኮሎኔል ነበርና የባለቤቴን ዘመድ መሸሸግ ለደህንነቱ ተናገረ ወደ ራሱ ቤት እየመራ ወስዶ አስያዛቸው ለባለውለታነቱ ሺ ብር ተሰጠው ከባለቤቱና ከዘመዶቿ ጋር ተኮራረፈ በወቅቱ ጄኔራል አበራ አበበን ለመያዝ የሄደው ቡድን ከነህይወታቸው መማረክ እየቻለ ነገር ግን የእጅ መሰጠት እድልም ሳይሰጣቸው ታዘው በሄዱ ፖሊሶች ትኩስ ተገደሉ በዚያ ወቅት ከሚሊቴሪው አልፎ የአመፁ ተባባሪ ነበር እየተባባሉ መጠቋቆም ወደሲቪሌም ተዛምቶ ነበርና ሁሉም ስጋት ላይ ነው የጄኔራል አበራ ወዲያው መገደልም ለደህንነቱ ሌላ እፎይታ ነበር ሌሳው ሜጀር ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ሲሆኑ በራሳቸው ኣገላለፅ በእለቱ ከአዲስ አበባ ወጥተው በጎጃም አድርገው ሱዳን ከዚያ አሜሪካ ገባሁ ሲሉ ውሰጥ አዋቂ ነን የሚሱ ወገኖች ደግሞ አድማው ሲከሽፍ አሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ ገብተው እንደተሸሸጉና ምቹ አጋጣሚ ተጠብቆ በኤምባሲው ትብብር ከአገር ወጥተው አሜሪካ መግባታቸውን ነው ዞሮ ዞሮ አምልጠው አሜሪካን አገር ገብተዋል የቀሩትን ጄኔራሎች በሚመለከት ፕሬዝዳንት መንግስቱ ለህዝቡ ግጥቂት ጄኔራሎች ጉዳይ በአጭር ጊዜ ውስጥ በፍርድ ታይቶ ይወሰናል ብለው በገቡት ቃል መሠረት ከጠቅላይ ጦር ፍርድ ቤት ጀምሮ ልዩ ልዩ ደረጃ ያላቸው የጦር ፍርድ ቤቶች ተቋቁመው ስራ ለመጀመር ወራት ያህል ጊዜ ወስዶ ክሱ ህዳር ቀን ዓም ተመስቶ ጉዳያቸው መታየት ጀመረ ጄኔራሎችንና ከፍተኛና መካከለኛ ማዕረግ ያላቸውን መኮንኖች ፍርድ ለመስጠት በታላቁ ቤተመንግሰት ውሰጥ ራሱን የቻለ ፍርድ ቤት ተቋቋመ ከእነዚህ ውስጥ የቱ ጄኔራሎች ክሳቸው የታየው በጠቅላይ ጦር ፍርድ ቤት አንደኛ ችሎት ሲሆን ለዳኝነት የተሰየሙት ሌተናል ጄኔራል ተስፋዬ ገብረኪዳን የመሀል ሜጀር ጄኔራል አስራት ብሩ የግራ ብርጋዴል ጄኔራል ዓለማየሁ ሰዩም የቀኝ ዳኞች በመሆን ነው ዐቃቤ ሕጉ ኮሎኔል ታጠቅ ነበሩ የክሱ ዋና ነጥብ የሁሉም መንግስትን በኃይል ለማስወገድ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ማድረግ የሚል ነው የተለያዩ አገራት መንግስታት ለሊቀመንበር መንግስቱ የከፋ እርምጃ አንዳይወሰድባቸው በምክርም በልመናም ሲማፀኑ ቆይተዋል በነፃ እንዲለቋቸው የጠየቁ መንግስታትም ነበሩ መንግስቱ አልሰሟቸውም እናም ሂደቱ ሲጀመር አግባብ ባለው መንገድ እንዲከራከሩ ጠበቃ ማቆም ከቻሉ እንዲያቆሙ ካልቻሉ መንግስት እንዲያቆምላቸው ተፈቅዶላቸው ተከራክረዋል ተከላክለዋል ጠበቃ ቤተሰብ የውጭ ጋዜጠኛ ሳይቀር በችሎቱ ተገኝተው ነበር ያደረሱት የከፋ አደጋ አለመኖሩን እያነሱ ተከራክረዋል ጠበቆችም የቅጣት ማቅለያ ጠይቀዋል ወዘተ የቀኝ ዳኛው የሕግ ምሩቅ ቢሆኑም ሁለቱ ዳኞች ግን እንደማንኛውም ሚሊቴሪ ከውስን የሕግ እውቀት ውጪ ባለሙያ አልነበሩም ያም ቢሆን ክፋት አልነበረውም ህዳር ላይ የተጀመረው ችሎት በቀጠሮ ሄዶ ሄዶ ለውሣኔ ግንቦት ቀን ዓም ተቀጠረ እስከዚሀ ድረስ በአግባቡ ከሄደ በኋላ ግን የውሣኔ ቀጠሮው በ የነበረው ለጠበቆቹ ባልተለመደ አሰራር ስልክ ተደውሎ ወደ ግንቦት መለወጡ ተነገራቸው በተባለው ቀን ተከሳሶችም ጠበቆችም ተገኙ ሌላ ታዳሚ አልተገኘም ጋዜጠኛና ቤተሰብ ተባረረ ክካርካሩ ሙሉ ቀን ወስዶ ከምሽቱ ሰዓት ድረስ ቆየ ረፍት ተወጣ ጠበቆቹ ግን ለእረፍት እንዳይወጡ ተከልክለው እዚያው ቀሩ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ላይ ዳኞች ተሰየሙ ያ ሁሉ ክርክርኖ አግባብነት የነበረው አሠራር ሁሉ በአንዴ ገደል ገብቶ ፍርድ ቤትነቱም ቀረና እስረኞች በካቴና የኋልዮሻ ታሰረው ሽሎቱ ላይ እንዲቆሙ ተደረቱ ችሎት ሲቀረብ ተከሳሽ እጆቹን አይታሰርም ይሄም ባልከፋ ግን መዝገብ ማገላበጡ ሙግት መስማቱ ቀርቶ ተዕፋ የተላከች አንዲት ብጣሽ ወረቀት ይዘው እንባ እየተናነቃቸው ሜጀር ጄኔራል አስራት ብሩ ሊያነቡ ተዘጋጁ ያቺ ግማሽ ገጽ ወረቀት በሊቀመንበሩ ተፅፋ የተላከች ትዕዛዝ መሆኗ ነው እስኪመሽ የተጠበቀውም ለዚሁ ነበር ጄኔራል አስራት የሐዘን እንባቸውን እያፈሰሱ በሲቃ ድምፅ አነበቧት እንግዲህ ቀደም ሲል በአድማው ስብሰባ ላይ የነበሩ ተብለው ከተዘረዘሩት ጄኔራሎች ውስጥ ጄኔራል አበራ አበበ እና ጄኔራል ፋንታ በላይ ስለተገደሉ ጄኔራል መርዕድ ንጉሴና ጄኔራል አምሃ ደስታ ራሳቸውን ስለገደሉ ሌሎቹ ቱ ግን በቁጥጥር ስር ሆነው ስለቆዩ ተከታዩ ፍርድ ተበየነባቸው ሜጀር ጄኔራል አብድላሂ ዑመር በ ዓመት እስራትነ ሪር አድሚራል ተስፋዬ ብርሃኔ በ ዓመት እስራት እንዲቀጡ ሲወሰን ሌሎቹ ቱ ጄኔራሎች የሞት ፍርድ እንደተበየነባቸው የሚገልፀውን ወረቀት አንብበው እንባቸውን እየጠረጉ ፈጥነው ከችሎት ወጡ አንባቢው ማለትም ዳኛው ከተከሳሾች አንደበት የተለያዩ አሳዛኝ ቃሎች በጩኸት ተደመጡ ቤተሰቦቻችን ሳንሰናበት። ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም መንግስታቸው ከወደቀና እሳቸውም በሽሽት ዙምባቡዌ ከሄዱ በኋላሳ እሄ የታገልኩት ከሻዕቢያ ጋር ነው ወያኔ ጎርፍ ያመጣው ድንጋይ ነው ብለው ተሳልቀዋል እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ወያኔ ጎርፍ ያመጣው ድንጋይ አልነበረም እርሳቸውም ይሄንን አሳምረው ያውቁታል ስለዚህ ለማለት የፈለጉት ወያኔን ብቻውን ማሸነፍ እችል ነበር ግን ሻዕቢያ ሲያብርለት ሳላሸንፈው ቀረሁ ው እንደማለ ችን የነርፍ ምሳሌ ስለሰጡን እያመሰገነን ጎርፉ እንዴት እየተንፎለፎሰ የደርግን መንግስት እንደጠራረገው በአጭሩ ለማየት ርግጥም ድርጊቱ በጎርፍ የሚመሰል ነው ጎርፉ የመነጨው ከኤርትራ በርሃ ነው ገድቦ ለማስቀረት የተሞከረውም እዚያው ነበር ሳይሆን ቀረና የናቅፋን ሰንሰለታማ ተራራ አጥለቅልቆ አፋቤትን አዳርሶ መ ወንዝ ገበባረ ያ የተነሳው የሕወሓት ጎርፍም ኃይሉን ጨምሮ ያገኘውን ሁሉ እየጠራረገ ሽሬ ደረሠ የደርግ ሰራዊት ጎርፉ ሽሬ መድረሱን ሲሰማ ከመጥለቅለቅ አደጋ ራሱን ለማዳን የትግራይን ግዛት በ ቀን ጊዜ ውስጥ ለቆ ወጣ ማስቀረት እንደማይችል ሰለተረዳም ምንም ኦይሃት የመገደብ ሙከራ አላደረገም ትግራይን ነፃ ለማውጣት የተነሳው ድርጅት ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሕወሓት ግቡ የነበረችውን የትግራይ ግዛት ሙሉ በሙሉ ቢያጥለቀልቃትም ጎርፍ ነውና ጎርፍ ደግሞ አንዴ ከላይ ከተነሳ ቁልቁል ከመውረድ በቀር ሴላ ምርጫ የለውምና ወረዴ ጋራ ሸንተረሩን ሜዳ ገደሉን እያዳረሰ አማራ ክልል ሲገባ እዚያም ያገኘውን ኢህዴንን በኋላ ብዓዴን ከእነግሳንግሱ ጠራርጎት ቀጠለ ከላይ ከሰሜን የተነሳው ጎርፍ እንዲህ በፍጥነት ነጉዶ ነጉዶ በምስራቅ ኢትዮጵያ በሐረርጌና ባሌ በምዕራብ ኢትዮጵያ በወሰጋ ኣካባቢ ረጋ ብሎ ይወዛወዝ ከነበረው ሐይቅ ከኦነግ ጋር ተገናኝቶ ከሩቅ የመጣ ጎርፍና ረግቶ የቆየ ሐይቅ የሚያደርጉትን አይነት የሠላምታ ልውውጥ እደረጉ ጎርፉ ከላይ ሐይቁ ከስር ሆነው ወዲያ ወዲህ ሲናጡ የተፈጠረው ማዕበል ፕሬዝዳንት መንግስቱን አሸቀንጥሮ ጣላቸው በዚህ መሰሉ ጎርፍ ተገፍትረው ዙምባቡዌ የገቡት መንግስቱም ው ባሉበት ሆነው ስለጎርፍ ተረቱ ተረቱንም ተጠቀምንበት ማን በጎርፍ እንደመጣ ማን በጎርፍ እንደወጣ ተረዳንበት ከሕወሓት በኋላ በመጨረሻዎቹ ዓመታት ደርግ ላይ ያመፁ ብሐረተኛ ድርጅቶች ኢሀዴን ኢትዮጵያ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና ቱነግ ሁሮሞ ነፃነት ግንባር ነበሩ ስለእነዚህ ድርጅቶች መጠነኛ ቅኝት አድርገን ወደ ተነሳንበት ርፅሰ ጉዳይ እንመለሳለን የኦሮሞ ህዝብ የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ በተደራጀ መልኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀሰቀሰው ዋቱለማና ሜጫ ራስ ገዝ ማኅበር በጃንሆይ ዘመን በጥር ወር ዓም ሲመሠረት ነው ሆኖም የማኅበሩ ዓላማ የነፃነት ትግል ሳይሆን በኦሮሞ ግዛቶች የትምህርት የጤና የመገናኛና ሌሎች የመሠረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ነበርፊ በወቅቱ በኦሮሞ ስም ማኅበሩ ይቋቋም እንጂ የአባላቱ ምልመላ የደቡብ ተወሳጆችንም ያካተተ ነበር የማኅበሩ ፕሬዝዳንት የነበሩት የፖሊስ ሠራዊት አዛዥ ሆነው የተሾሙት ብርጋዴር ጄኔራል ታደሰ ብሩ ስለነበሩ የጃንሆይ መንግስት ስጋት ቢያድርበትም እንቅስቃሴያቸው ሠላማዊ ነው ብሎ በማሰብ ተወት አድርጓቸዋል በዚሀ መሐል በ ዓም በጥቅምቱ የጃንሆይ የንግስ በዓል ላይ የግድያ ሙከራ ለማድረግ ሲያሴሩ ተገኙ ተብለው ተወነጀሉ ኣስተባብለው ታለፉኑ ብዙም ሳይቆይ በሲኒማ አምፒር ቦምብ ሲፈነዳ የማኅበሩ አባላት ተጠያቂ ሆኑ አቀናባሪዎቹ ጄኔራል ታደሠ ብሩና ሌላው አባል መቶ አለቃ ማሞ መዘምር ናቸው በሚል ውንጀላ ማኅበሩ እንዲፈርስ ተደረገ ድርጊቱ ከተፈፀመ በኋላ የተሰወሩትን ጄኔራል መንግስት አድኖ ይዞ ለፍርድ አቀረበና የሞት ፍርድ አሰወሰነባቸው ውሣኔው ግን በይግባኝ ወደ እድሜ ልክ ተቀየረ ከአብዮቱ በኋላ ጄኔራሉ እንደ ሌሎች የፖለቲከኛ አስረኞች በምህረት ቢለቀቁም ከህቡፅ የኦሮሞ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ስለፈጠሩና ደርግ አካሄዳቸው ስላለማረው የመሬት አዋጁን በመቃወም በሚል ክስ በ አስረሸናቸውበዚያወቅት ይሙት በቃውን የፊረሙት ሊቀመንበሩ ተፈሪ በንቲ ነበሩ ቀጥሎ በቀድሞው የሜጫና ቱለማ ማኅበር አባል በነበረ ግለሰብ መስራችነት ፕኢትዮጵያ ብሔራዊ ነፃነት ግንባር በሚል ስያሜ በ ዓም አካባቢ ተቋቁሞ የነበረው ሲሆን ኣንዳች ተግባር ሳያከናውንና በአግባቡም መደራጀት ሳይችል በራሱ ጊዜ ተበተነ በአብዮቱ ወቅት የፖለቲካ መፈክሩ ኅብረብሔራዊነት ላይ ያተኮረ ስለነበር የኦሮሞ ብሔራዊ እንቅስቃሴዎች አልታዩም ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን በኅብረብሔራዊ ድርጅቶች ውስጥ በተለይም በመኢሶንና በኢጭአት ውስጥ ስለነበሩ ራሳቸውን እንደ ወኪል ህዝቡም እንደተወካይ ካላያቸው በቀር ሌላ እንቅስቃሴ አልነበረም ከዚህ አንፃር ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ባኦሮሞ ህዝብ ስም የሚንቀሳቀስ ድርጅት የተገኘው በ ዓም ኦነግ ሁሮሞ ነፃነት ግንባር ው አደም ከተመሠረተ ጀምሮ ከሻዕቢያ የማቴሪያልና የቴክኒክ ድጋፍ እየተቸረው በሐረርጌ በባሌ በወለጋና በአካባቢው መሽጎ የሽምቅ ውጊያውን ቢቀጥልም በውስጡ በነበረው የእርስ በርስ ሽኩቻና በህዝቡ ውስጥም ራሱን ለማስረፅ የሚያስችል ዘዴ በአግባቡ ባለመቀየሱ የዓመታት ትግሉ የሕወሓትን ያህል ደርግን መፈታተን አላስቻለውም ነገር ግን ከተመሠረቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ደርግ የፍፃሜ ዘመን ድረስ በደርግ ላይ ካመፁ ብሔረተኛ ድርጅቶች ውሰጥ አንዱ ሆኖ ቆይቷል ደርግን ለመጣልም በደቡብ ምዕራብ ያለውን ይዞታውን በማስፋትና ከወያኔ ጦር ጋር ተቀናጅቶ በማጥቃት የድርሻውን ተወጥቷል ይህ ድርጅት ከአብዮቱ በኋላ በደርግ ላይ ከደርግ ውድቀት በኋላ በኢህአዴግ ሳይ ሀቡዕ እንደገባ ዛሬም ድረስ እለ ሌላው በ ዓም የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ኢሀዴንነ ሲሆን ከተበታተነው የኢህአፓ ሠራዊት ተርፈው በሰሜን ወሎ በትጥቅ ትግል ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጋዮች ስብስብ ነው ሕወሓት አማራ ክልል ሲደርስ ቅንጅት ፈጥረው አብረው ታግለዋል የደርግን ፍፃሜ ለማፋጠን ከፍተኛ መስዋዕትነትም ከፍለዋል የአነሳስ መሠረቱ ግን ከስሙም እንደምንረዳው ኅብረብሔራዊ እንጂ ብሔረተኛ አልነበረም እንግዲህ ሕወሓት ከትግራይ ግዛት ድል በኋላ ያለው አዝማሚያ ሁሉ ቀላል እንደሆነ ሲረዳና አገራዊ አጀንዳ ማውጣት ግድ ሲሆንበት የዚህ አጀንዳ አስፈፃሚ ይሆናሉ ብሎ ያሰባቸውን ድርጅቶች አነሳሳቸው ብሔረተኝነት ከነበረ እሰየው ኅብረብሔራዊም የሆኑ ካሉ በብሔረተኝነት ማጥመቅ በሚል መነሻ ኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ን ወደማዋቀር አመሙመራ መ ያ መሠረት ኢህአዴግ የተዋቀረው በተለያዩ ድርጅቶች ጥምረት ሲሆንአባል ድርጅቶቹም ሕወሓት ኢህዴን ከድል በኋላ ብዓዴን ተብሎ የአማራን ህዝብ እንደሚወክል ይፋ ያደረገውየኦሮሞን ሀዝብ ይወክላል ተብሎ የተቋቋመው የኦሮሞ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አእህዴድኣንዲሁም የተማሩ የደርግ ሠራዊት መኮንኖች የተሰባሰቡበት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ መኮንኖች አብዮታዊ ንቅናቄኢዴመአንነበሩ በእነዚሀ በኢህአዴግ ስር ከተካተቱ ድርጅቶች ውስጥ ሕወሓትና ኦህዴድ በብሔረሰብ ሳይ የተዋቀሩ ሲሆኑየመጀመሪያው በትግራይ ሁለተኛው በኦሮሞነኢህዴንና ኢዴመአን ኅብረብሔራዊ ናቸው ከማይታወቀው ኦህዴድ ይልቅ የሚታወቀው ኦነግ በሀዝቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዳለው ቢታወቅም ከኦነግ ጋር ከድል በኋላ ግንባር ለመፍጠር ሳይቻል ስለቀረ ሕወሓት ኦህዴድን ለማቋቋም ተገዷል ስለዚህ ከኦነግ የጦር ምርኮኞችና በኦነግ ካልታቀፉ ምሁራን የተውጣጡ አባላትን መልምሎ አቋቋመ ኢህዴንም ከድል በኋላ ብዓዴን ነኝ ይበል እንጀ በኣሣራ ክልል ውስጥ ሲታገል በነበረበት ጊዜ የሚታወቅበት ስም ኢህዴን የሚለው ነበር በመኮንኖቹ ስም የተቋቋመው ኢዴመአን የጦር ምርኮኞችን በፖለቲካ መድረክ ዙሪያ ከማሰባሰብ ያለፈ የፖለቲካ ሚና ሳይኖረው የከሰመ ነው እነዚሀን የድርጅት እነሳሶችና አወቃቀሮችን ከወዲሁ ቀድሞ መግለፅ ያሰፈለገው ኢህአዴግ ኢህአዴግነቱን ያወጀውና በዚህ ስምም እየተጠራ ትግሉን የቀጠለው የትግራይን ግዛት በቁጥጥሩ ስር ካደረገ በኋላ እዚያው ትግራይ ላይ ቅድመ የቤት ስራውን አጠናቆ ለኣዲሱ ኢህአዴጋዊ አጀንዳ ኢሀአዴጋዊ ትግሉን ቀጥሎ እየተጠራበት መምጣቱን ለማሰገንዘብና አዲስ አባባንም የተቆጣጠረው በዚሁ ስሙ መሆኑን ከወዲሁ ለመጠቆም ነው በአሁኑ ጊዜም ብዓዴን ኦህዴድ ሕወሓት ከድል በኋላ የተቋቋመው የደቡብ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ደህዴን እና ሌሎች አጋር ድርጅቶች ተጣምረው የሚሜገኙበት ኢህአዴግ መንግስት ሆኖ አገር እየመራ እንዳለ ይታወቃል ይህ በግልፅ የመታወቁን ያህልም በም በውስጡ ካጋጠመው ክፍፍል ውጭ እንደ ድርጅትም የበላይነቱ እንደተጠበቀ ነውበግለሰብ መሪዎች ደረጃም እንደዚያው እናም ኢህአዴግ ትግሉን ቀጠለ የደርግ መንግስት የብሔረተኞችን ጦርነት መቋቋም እየተሳነው ሄደ የደርግ መንግስት ውድቀት እጅግ በተፋጠነ መንገድ የቀጠለው ከ ጀምሮ ነው እስከ ድረስ ያለ የሴለ ኃይሉን ተጠቅሞ ለመፋለም ከመሞከሩም ባሻገርበብፁ ሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ምልምሎችን በውድም በግድም በፍጥነት ወደተገነቡ የማሰልጠኛ ጣቢያዎች እያጋዘ በለብለብ ስልጠና ወደ ጦር ግንባር ቢያሰማራም የጠበቀውን ውጤት ሲያገኝ አልቻለም በተለይ በየካቲት ወር ዓም ሻዕቢያ ከፍተኛ እልቂት በታየበት ጦርነት የደርግን የባህር ኃይል ደምስሶ ምፅዋን ሲቆጣጠር መንግስት የባህር ወደቡን ከማጣቱም ሌሴሌላ ትግራይ ሙሱ በሙሉ በሕወሓት እጅ ሰለነበረች ኤርትራ ውሰጥ ለሚገኘው ጦር ስንቅ የማቅረቢያ መንገድ አጣ በዚሀ መሀል ኢሕአዴግ ወደ አዲስ ኣበባ የሚያረማምዱትን ተከታታይ ዘመቻዎች ከፈተ በ ዓም የመጀመሪያ ወራት የጎንደር ክፍለሀገርን ለመቆጣጠር የከፈተው ዘመቻ ለጊዜው ቢከሽፍበትም ጉና በተባለው ተራራ ላይ በተደረገ ጦርነት በብዙ የህይወት መሰዋዕትነት ደብረታቦርን ተቆጣጠረ ቀጥሎም ደቡብ ወሎ ውስጥ መራኛ በተባለው ስፍራ ባገኘው ወሣኝ ድል ወደ ሰሜን ሽዋ ለመረማመድ ቻለ እነዚህን ድሎች ከተቀዳጀ በኋላ ኢሕአዴግ አዲሰ አበባን ለመቆጣጠር ወኔ በሚቀሰቅሱ ታሪካዊ ስሞች የሰየማቸውን የጦር ዘመቻዎች አወጀ በዝመቻ ቴዎድሮስ ጎጀምን ተቆጣጠረ በቀድሞው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ መሪ አንቀሳቃሽ በነበረውና የወሎ ተወላጅ በሆነው በዋለልኝ መኮንን ስም ዝመቻ ዋለልኝ ብሎ በሰየመው ዘመቻ የደርግን ሠራዊት ከወሎ ከፍለሀገር ጠራርጎ አስወጣ ቀጥሎ ዘመቻ ቤሉሱማፍ ወልቂጡማ በኦሮምኛ ነፃነትና እኩልነት ማለት ነው በሚል ስያሜ ባዘመተው ጦር ከጎጃም ወደ ወለጋ መሸጋገር ቻለ እነዚህን የመሳሰሉ ወሣኝ ድሎች በፍጥነትና በተከታታይ እየተቀዳጀ መጥቶ የኢህአዴግ ሠራዊት አዲስ አበባን ከሰሜን ከምስራቅና ከምዕራብ አቅጣጫ ከበባት የደርግ ሠራዊት በብዙ ግንባሮች ጠንክሮ ለመከላከል ሞከረ በተለይ አምቦ ከተማ ላይ የነበረው ሠራዊትና ህዝቡ የኢህአዴግን ጦር አላሳልፍ ብሎ ክፉኛ ተፈታትኖት ነበር የደርግ መንግስት ከጽኑ የመከላከል ተግባሩ ጎን ለጎን ከዎቹ ጀምሮ ዞር ብሎ አይቶት የማያውቀውን በተቀናቃኞቹ ዘንድም ተቀባይነት ያልነበረውን የሠላም አማራጭ ማማተር የጀመረው ሁኔታው እዚህ ደረጃ በደረሰበት ዜ ነበር ጾ እነዚህ ግንባር የፈጠሩ ብሔተኞች አፍሪካ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ የረጅም ዓመታት የሽምቅ ውጊያ ግዙፉን የደርግ ሠራዊት ደረማምሰው እዚህ ደረጃ ደርሰው ሙሉ ለሙሱም ወታደራዊ ድልን ከተጎናፀፉ በኋላ የሠላም ድርድርን ይፈልጋሉ ይቀበላሉ ብሎ ማሰብ የዋህነት መሆኑ ቢታወቅም በተለይ አፍቃሬ ኢሕአዴግ የነበረችው አሜሪካ የመጀመሪያዋ አደራዳሪ መስላ ለመታየት ሞከረች በዚህ መሠረት የመጀመሪያው የሠላም ድርድር በቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት በጂሚ ካርተር አማካኝነት በ ዓ መጀመሪያ በአትላንታ ቀጥሎ በናይሮቢ የሠላም ድርድሮች ተካሄዱ ይህም በሻዕቢያና በደርግ መንግስት መካከል የተካሄደ ነው በምን እንደሚደራደሩ ግን ሻዕቢያም ደርግም አደራዳሪው ቡድንም ቢጠየቁ መልስ የላቸውም ሊኖራቸውም አይችልም ስለዚህ ለደንቡ ያህል ጥቂት ተጨቃጭቀው ሳይግባቡ ተለያዩ ቀጥሎ በመጋቢት በደርግና በሕወሓት መካከል ሮም ላይ በቀድሞው የኢጣሊያ ኣምባሳደር ቨምጋይነት የተደረገው የሠላም ድርድር ሲሆን ሕወሓት ሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችም መሳተፍ አለባቸው የሚል መከራከሪያ በማንሳቱ ቀድሞ የከሸፈው ድርድር ውጤት አልባ ሆኖ ተበተነ ሦስተኛውና የመጨረሻው አስገራሚ የሠላም ድርድር ለንደን ላይ በደርግና በኢሕኣዴግ መካከል የተካሄደው ነው በ ዓም በግንቦት ወር የመጀመሪያ ቀናቶች ጥለንደን ጉባዔ ተብሎ በሚታወቀውና በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ በነበሩት በሄርማን ኮኸን ሰብሳቢነት የተደረገው ሙከራ ላይ የኢትዮጵያ መንግስትን ልዑክ መርተው የሄዱት ባለቀ ሰዓት ሹመት የተሰጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ተስፋዬ ዲንቃ ነበሩ የመደራደሪያ አቅም ቀርቶ የማምለጫ መንገድ ባልነበራቸው ሁኔታ ለሰሳም ድርድር መሰብሰባቸው ሳያንስ ጉባኤው እየተካሄዴ ባለበት ሰዓት ፕሬዝዳንት መንግስቱ አገር ጥለው መሄዳቸው ተሰማ ጂሚ ካርተርና ሄርማን ኮኸን ወደ አዲሰ አበባ በተደጋጋሚ መጥተው ከመንግስቱ ጋር ውይይቶችን አድርገው ጨርሰዋል ሰለዚህ ቀጣዩን ሂደት በደንብ ያውቁት ነበር በተለይ ሚስተር ኮኸን ለንደን ላይ አደራዳሪ ሆነው ተቀምጠው በነበረበት ጊዜ ፕሬዝዳንት መንግሰቱ ኃይለማርያም ግንቦት ከአገር መውጣታቸውን ግንቦት ጉባዔው ላይ ሲሰሙ የመገረም ፊት ያሳዩት ሲቀልዱ እንጂ ከልባቸው አልነበረም መጨረሻው ደረሰና ግንቦት ቀን ዓም ሻዕቢያ የዓመታት ዒላማው የነበረችውን አስመራን ሙሱ ለሙሉ በአጁ አደረጋት ግንቦት ቀን ዓም ማለዳ ላይ የኢህአዴግ ሠራዊት ኣዲስ አበባን ተቆጣጠረ በእለቱ የመንግስቱና የቤተመንግስቱ ታማኝ ጠባቂዎች ከድል አድራጊው ወገን ጋር ካደረጉት መጠነኛ የተኩስ ልውውጥ በስተቀር የተፈጠረ ሁከት አልነበረም ኤርትራ ውሰጥ ይገኝ የነበረው ሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ከፊሉ ወደ ሱዳን ከፊሉ ወደ ትግራይ ተበተነ በአስመራና በአካባቢዋ የሚገኘው ጦርም ትጥቁን እየፈታ ለሻዕቢያ እጁን ሰጠ በተመሳሳይ ሁኔታ አዲስ አበባ ውስጥ የነበሩ የመንግስት ከፍተኛ የጦር ባለሥልጣናት ምንም አይነት አውሮፕላን ከአዲስ አበባ እንዳይነሳና ሁሉም ባለበት እንዲረጋ ኢህአዴግ የሰጠው ማስጠንቀቂያ አንዳለ ሆኖ በልዩ ልዩ ዘዴ ከአዲስ አበባ ወጥተው ለማምለጥ የሞከሩትን ባለሥልጣናት ግን የራሳቸው ባልደረባ የነበሩት የደህንነት ሚኒሰትሩ ኣከሸፉባቸው ከግንቦት በፊት ከነበሩት ጥቂት ቀናቶች ጀምሮ የአዲስ አበባን መውጫና መግቢያ በአራቱም አቅጣጫ ጠባቂ መድበው የደርግ ባለሥልጣኖችን የማምለጥ ሙከራ በመግታታቸውም ኤምባሲ ውሰጥ ገብተው ከተጠጉትና በረቀቀ ዘዴ ማምለጥ ከቻሉት በጣት የሚቆጠሩ ባለሥልጣናት ውጪ ሁሉም እየተለቀሙ ተይዘው ወደ ወህኒ ወረዱ ከረጅም ዓመታት የፍርድ ሂደት በኋላም የሞት የእድሜ ልክና ከ እስከ ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ተወሰነባቸው ኢህአዴግ ሙሉ በሙሉ አገሪቱን ያዛትየሻዕቢያና የኢሀአዴግ የተባበረ የረጅም ዓመት ውጊያቸው በድል በተጠናቀቀ ማግስትም በዓም ኤርትራ ባሪፈረንደም ተገንጥላና ነጻ አገር ሆና የራሷን መንግስት መሰረተች ኢትዮጵያም ሁለት አገር ሆነችከዓመት በኋላም በኢሳያስ የሚመራው የሻዕቢያ መንግስት በዓም የድንበር ትንኮሳ አድርጎ አንድ የነበሩ ሁለት አገሮች ወይ ጦርነት አምርተው በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያና የኤርትራ ወጣቶች በጦርነቱ ሊያልቁ ግድ ሆነእነዚህ ሁለት መንግስታት ዛሬም ድረስ በክፉ ዓይን የሚተያዩ ሆነዋል ከደርግ ውድቀት በኋላ የኢትዮጵያ የቀድሞው ሕገመንግስት ተሽሮ ኢህአዴግ የራሱን ሕገመንግስት በዓምአፅድቆ በብሔር ተኮር ፌዴራሊዝም አገሪቱን እየመራ ይኅኛል ድል አድራጊው የኢህአዴግ መንግስት ግንቦት ቀን ዓም ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ይህ መጽሐፍ ለሕትመት እስከበቃበት ዓም ድረስ ኢትዮጵያን እያስተዳደረ ነው ይህ ማለት ደግሞ ከ ዓመታት በኋላ የኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓሉን ያከበራል ማለት ነው ወደጓድ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሽሽት እናመራለን የመጨረሻዎቹ ቀናት ፕሬዝዳንት መንግስቱ ብዙ ጣሩ ብዙ ዋተቱ የቻሉትን ሁሉ ሞከሩ ግን አቃታቸው ሁሉም ፊቱን አዞረባቸው የጦር አዛዥች አንጓጠጧቸው ከዷቸው ሚያዚያ ወር ላይ ክፉኛ ተስፋ ቆርጠው ነበር የታዩት እናም ለመጨረሻ ጊዜ ከህዝባቸው ጋር ማውራት ፈለጉ ሚያዚያ ቀን ዓም ሁሉም መስሪያ ቤቶች ተዞግተው ሀዝቡ በየቤቱ ተቀምጦ የፕሬዝዳንቱን ንግግር በብዙሃን መገናኛዎች እንዲያደምጥ ተደረገና ጓድ መንግስቱ ግማሽ ቀን የፈጀ ንግግራቸውን አሰሙ ልብ በሚነካ አገላለፅ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነቱን ሌሉሌዓላዊነቱንና ነፃነቱን ለማጠንከር ያደረገውን መስዋዕትነት እያመሳገኑ የጦሩን አሰላለፍና የጠላትን ግስጋሴ አየጠቆሙ የአብዮቱን ፍሬዎች እየዘረዘሩኮ ብርቱ የመከሳከያ ኃይል ለመገንባት የተደረገውን ጥረት እያብራሩ ቀጠሉና የኢትዮጵያ ህዝብ የሚቃጣበትን ማንኛውንም አይነት አፍራሽ ተግባር በውል እንዲመረምርና ማድረግ ያለበትን ነገር መወሰን እንደሚገባው አስገነዘቡ ገለፃቸውን ሲደመድሙም በዚህ ገለፃዬ ውስጥ እንዲህ ይሁን እንዲህ ይደረግ የሚል ጥቆማና መሪ ሀሳብ ለማቅረብ አልፈለግሁም ነገር ግን የመላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ግልዕፅ ሥ ክ ያ አቋምና ፈጣን ውሣኔ እጠይቃለሁ ካሉ በኋላ አስቸኳይና ልዩ ስብሰባ የጠሩ መሆናቸውን ለህዝቡ አሳድቀኩ ። አሉ የእኒህ ሰው ትንቢት ሙሌ ለሙሉ ባይሆንም በከራል ግን ተፈጽሟል መንግስቱ ሽጉጥ አልጠጡምና ዚህ ንግግር መንግስቱ ሣቁ በዚሀ መል ሀሳቦች ሾርኒዎች ዘለፋዎች ተስፋ አስቆራጭ ትንበያዎች ሲንዘራክሩ ከቆዩ በኋላ የፕሬዝዳንቱ የማጠቃለያ ሀሳብ ደም እንደ ጎርፍ ይፈሳል ህንፃዎች ይደረመሳሉ ከዚህ በኋላ የሚሆነው ይሆናል የሚል ይዘት ያለው ሆኖ ቢጠናቀቅም ጉባዔው ከላይ እስከ ታች በሚወርድ ትዕዛዝ ተፈፃሚ የሚሆን ውሣኔ አሳልፎ ነበር ውሣኔዎቹም ውይይት ድርድር የሠላም ኮሚሽን ህዝባዊ የሆነ የክተት አዋጅ ወዘተ እንዲደረግ የሚያሳሰቡ ቢሆኑም በአገር ውስጥም በውጭም ድጋፍ ቢቸረውም ረፍዷልና ሊተገበር አልቻለም መንግስቱ የመጨረሻ ጊዜያቸው እንደደረሰ ስለተረዱም የመልሶ ማጥቃት ዝርዝር እቅዶችን ማውጣትና ጦሩን እየተዚዚሩ በርቱ ማለታቸውን እርግፍ አድርገው ትተው በትካዜ ተዋጡ ሚያዚያ ቀን ባለቀለት ወንበር ላይ ሹመት ሰጡ በዚህም ሌተናል ጄኔራል ተስፋዬ ገብረኪዳን የኢህድሪ ምክትል ፕ ሬዝዳንት እቶ ተስፋዬ ዲንቃ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም ለሌሎች ሠ ጡበ ተመሣሣይ ኹመት ከሰጡ ላ ሻምበል ለገሠ አስፋውንና ኮሎኔል ፍስሐ ሜያዚያ ዋአሜሪካ መንግስትና ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ፀንቶ መኖር ያላቸውን ድጉ አቋም በድታን በማረጋገጥ የአሜሪካ መንግስት የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ሸንጎ ኛ አስቸኳይ ጉባዔ ያሳለፈውን ውሣኔ የሚደግፍ መሆኑንና ለተግባራዊነቱም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሜሰጥ ያረጋግጣል የሚል መልዕክት ለፕሬዝዳንት መንግስቱ ደረሳቸው ው ያሳለፋቸው ዝርዝር ውሣኔዎች አገ ኢትዮጵያን ከማስቀጠል ጋር እንጂ ከመገንጠል ጋር ፈጸሞ የጣስግግ በባን አልነበረም ባን ከበው የያዚት ተቃዋሚዎች የሚስማሙበት ሆኖም የአሜሪካን የይምሰል መግለጫ ተከትለው ካናዳ ግብፅና ሌሎች አገራት የሸንጎውን ውሣኔ መደገፋቸጠን ቁ ኋሃ ዖ ውዉተሠ ኢትዮጵያውያኑም በሠላማዊ ሰልፍ ድጋፋቸውን አረጋግጠው አማፅያኑን የሚደግፉትን አገራትም አወገዙ በዝምታ ቀናቶችን አሳልፎ የቆየው ኢህአዴግ በውጭ ቢሮ ጽቤቱ በኩል ተከታዩን መግለጫ ይፋ ሲያደርግ የሸንጎው ውሣኔም ሆነ ማናቸውም ዓይነት የሠላም ድርድሮች ሁሉ ከንቱነታቸው ግልፅ እየሆነ ሂደ ከኢህአዴግ የውጭ ቢሮ ጽቤት የተሰጠ መግለጫ ሣኢሀአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከግንቦት እስከ ቀን ዓም በነፃ መሬታችን ላይ አስቸኳይ ስብሰባ አካሂዶ ወቅታዊ ጉዳዮችን በሚመለከትና አስፈላጊ ውሣኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቋል አስቸኳይ ስብሰባው በአሁኑ ወቅት ደርግ ኢሠፓና መሰሎቹ በአንድነት በመሰባሰብ የኢህአዴግ የሽግግር ፕሮግራም ተግባራዊ እንዳይሆን የተጠነሰሰ ሴራ በሚመለከት ሆኖ በሌላ በኩል ደግሞ ደርግ ያወጀው የሽግግር መንግስት ኢህአዴግንና ሌሎች ታጋይ ኃይሎችን በፀረ አንድነት ስያሜ በማግለል ደርግና የትምክህተኞች ኃይል ስብስብ ኢዲኅቅ እና ሌሎችም ስልጣን ሰመያዝ በአሜሪካ ኤምፔሪያሊዝም አይዞህ ባይነት በተለያዩ የውጭ አገር ከተሞች ሽር ጉድ እያሉ ይገኛሉ የኢሀአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ የደርግ ሸንጎ ያሳለፈውን የሠላም ውሣኔ አልተቀበለውም ኢህአዴግ በስመ አንድነት ወይም በወረራ የተመሠረተ የባርነትና የግዛት አንድነት የህዝብ አንድነት ይሁን ብሎ ለመከራና ለጭቆና አሳልፎ እይሰጥም ማንኛውም ብሔርና ብሔረሰብ የራሱን ዕድል በራሱ በመወሰን ነፃ መንግስት መሰርቶ ባስፈለገው መንገድ እንዲጓዝ ይበልጥ ኢህአዴግ ሲታገልለት የቆዬ ዴሞክራሲያዊ መንገድ ከመቼውም ጊዜ በላይ ፍቱን መፍትሄ መሆኑን እአስምሮበታል በኤርትራና በኢትዮጵያ ለ ዓመታት ሲካሂድ የቆየውን ጦርነት በተመለከተ ማንም ወሣኝ ሳይሆን የኤርትራ ቅኝ ግዛት ጥያቄ በሰሳማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እልባት አግኝቶ ኤርትራውያን ከኢትዮጵያ ቅኝ አዝዛዝ ቀንበር ተላቅቀው ነፃ አገራቸውን እንዲመሠርቱ ሁሉ ኢትዮጵያዊ አምኖበት መቀበል አለበት ኢህአዴግ ያቀረበው አስተማማኝና አጥጋቢ መፍትሄ ግልፅና ጠቃሚ ነው ኢትዮጵያ አትቆራረስም ብሎ መጮሀ ትርፉ ጦርነትና እልቂት ስለሆነ አንድነት ለብዝበዛና ለባርነት አሳልፎ የሚሰጥ መሣሪያ ከመሆኑ ባሻገር የሀዝቡን ጥቅም ሲያስጠብቅ አይችልም በዚህ ላይ ኢህአዴግ የሽግግር ፕሮግራም ብዙ የፖለቲካ ኃይሎች በነፃና ዴሞክራሲ የሚሳተፉበት ህዝቡ በየድርጅቱ መሪነት እድሉን በራሱ ወደሚወስንበት መድረክ የሚያሸጋግር ፕሮግራም መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል ያ አስቸኳይ ስብሰባው በቅርቡ በአሜሪካ መንግስት አቀራራቢነት በደርግ በኢህአዴግ በኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባርና በህዝባዊ ግንባር ኅርነት ኤርትራ መካከል ለንደን ውስጥ ሊካሄድ የታቀደውን የሠላም ኮንፍረንስ የኢህአዴግ ስራ አሰፈፃሚ ኮሚቴ በጥልቀት መርምሮ መሳተፍ ተገቢ ሆኖ ቢያገኘውም በዚሁ የለንደኑ ኮንፈራንስ አቀራራቢ የሆኑት መንግስታትና ደርግም ሆነ ቀኞችና ወላዋይ ድርጅቶች ለኢህአዴግ ሠላማዊ ሽግግር ፕሮግራም ያላቸውን ጠማማ አመለካከት አስወግደው የሸግግር ፕሮግራሙን ሲቀበሉ ብቻ ነው ይህ የኢህአዴግ የሽግግር ፕሮግራም ታማኙን በልዩ ልዩ መንገድ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ለህዝቡ የሚባጁ መፍትሄዎች ከቪዘህ የበለጠ ሌላ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በሚገባ አምኖበታል ኢሠፓና መሰሎቹ ያቀረቡት የሽግግር ፕሮግራም የህዝብን የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት በፍፁም የሚፃረር በይዘቱም ለህዝቡ የማይበጅ ፀረ ህዝብ ነው በዚህ መሠረት የለንደኑን ኮንፍረንስ የኢህአዴግ ዓላማ በተግባራዊነቱ ታምኖበት ተቀባይነቱ ካልተረጋገጠ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አጥብቆ ለማሳሰብ የሚወደው ነገር ቢኖር የምንወስደው ሰፊ ወታደራዊ ማጥቃት በአገሪቱ የሚፈጥረው የእርስ በርስ እልቂት ታይቶ ከማያውቅ ደረጃ ይደርሳል የኢህአዴግ ዓላማ ተግባራዊነቱን የሚያገኘው በጦርነቱ ስለሆነ ጦርነቱ በከፋ መልኩ ይቀጥሳላል የአገሪቱ ህዝብ የስቃይና የመከራ ሀይወች ይራዘማል በፀረ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የኢሀአዴግ ሠንደቅ ይውለበለባል ይህ የጦርነት ክስተት እንዳይፈጠር የኢህኣዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጦርነቱን ለማቆም ዋነኛው አማራጭ መንገድ የኢህአዴግ ሠላማዊ ሸግግር ፕሮግራም በውጭና በሃገር ውሰጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን እንዲቀባሉት ሲስገነዝብየኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ የጦርነት እሳት ለመዳን የደርግ የኢሠፓና የግብረአበሮቹ ፀረ ዴሞክራሲያዊ ጎዳናዎች ሳይከተል አጥብቆ እየተቃወመና እየታገለ ከኢህአዴግ ጎን ተሰልፎ የሽግግር ፕሮግራሙን ተግባራዊ እንዲያደርግ ጥሪውን ያሰማል ያሏጴሃኋዴረ ያውጅ ደሮ ሃጴለ ግም ይህ መግለጫ ይፋ ከተደረገ በኋላ ደርግ አንድነትን ኢህአዴግ ፀረ አንድነትን ሲያቀነቅኑና ለአመታትም ሲፋለሙበት የኖሩበት ነጥብ እንደመሆኑ መጠን ከዚሁ ጋር ተያይዞም በመካከላቸው ኣንዳችም ለሠሳም ስምምነትና ድርድር የሚያበቃ ክፍተትም ፍላጎትም እድልም ተስፋም ባለመኖሩ የቀረው አንድ ነገር ብቻ ሆኗል ያም የእርስ በርስ ኔ ፍጅቱን በአዲስ አበባና በዙሪያዋ ባሉ ከተሞች ማጧጧፍዬፍና ህዝቡን ማስጨረስ በጦርነቱም የከተማዎቹን የመሠረተ ልማት አውታሮች ማውደም ህንፃዎቹን ማስደርመስ ነበር ይህ እንዳይሆን አስበው አገሪቱን በሠላም ለቀው በሚስጥር ሹልክ ያሉትን ጓድ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያምን ማመስገን ተገቢ ይመሰሳል በወቅቱ ባልተያዙ ከተሞች አነስተኛም ቢሆን ሠራዊት ነበራቸው ሺ የሚደርሱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማሠልጠኛ ውስጥ ከመኖራቸውም በላይ ከልዩ ብርጌድ ሠራዊቱና ሸሽተው አዲስ እበባ ከገቡት ጋር ተዳምሮ ወደ ሺ የሚጠጋ ሠራዊት ከአእነትጥቁ ነበራቸው ያም ሆኖ መንግስቱም እንደሚሉት በርሃ ውስጥ እንደ አዲስ የሽምቅ ውጊያ ለመጀመር ካልሆነ በቀር ፊት ለፊት ለመጋፈጥ የሚያስችል አይደለም ሁኔታውም ምቹ አይሆንም በዚህ መሠረት ግራ ቀኙን አይተው ተስፋ ያጡት ፕሬዝዳንት የአሜሪካን ግፊት መቀበል ነበረባቸው እናም ግንቦት በጠዋት ብላቴ ማሰልጠኛንና በውስጡ ያሌትን ምልምሎች ለመጎብኘት በሚል ጉዞ ጀመሩ የመንግስቱን ከአገር አወጣጥ በተመለከተ እውነታውን በስተመጨረሻ የምናየው ይሁንና የቅርብ አጃቢዎቻቸውና ሸኝዎቻቸው እንዲሁም ራሳቸው መንግስቱ ለጋዜጠኛ ገነት አየለ ያሉትን እናስቀድም ጄኔራል ቁጥር እንዲህ ይላሉ ለጉብኝቱ በተወሰነው ቀን አብረዋቸው ከሚሄዱት አንዱ በመሆን ከጠዋቱ አንድ ሰዓት አውሮጥላን ማረፊያ ተገኘሁ ሌሳ አንድ ጄኔራልም በቀጠሮው ሰዓት ተገኝቶ ይጠባበቃል ብናይ ብናይ እስከ ሰዓት ድረስ ምንም የለም ብላቴ ካለው አዛዥ ጋር በስልክ ስነጋገር አንድ አውሮፕላን በብላቴ በኩል ማለፉን ቢነግረኝም አካባቢው ብዙ አውሮፕላኖች የሚመላለሱበት ስለነበር አልጠረጠርኩምና ዘግይተው ነው ብዬ መጠበቄን ቀጠልኩ ወዲያው ግን ቺፍ ኦፍ ስታፉ ደወሱና ባስቸኳይ ቤተመንግስት እንድትመጣ ስላሉኝ ሄድኩ ስደርስ ጄኔራል ተስፋዬ በሬዲዮ የተነገረውን ሲነግረኝ ማመን አቃተኝ በማለት እንደሚመስለኝ የመንግስቱን መሄድ አስቀድመው ያወቁ ሰዎች ነበሩ ተገደው ወይም ተፅዕኖ ተደርጎባቸው ሄዱ የሚለውን ለማመን ያስቸግራል ሲሉ ግምታዊ ድምዳሜያቸውን ካዩዋቸው ነገሮች ተነሰተው ያስቀምጣሉ ጓድ ቁጥር ደግሞ ስለአወጣጣቸው ኮሎኔል መንግስቱ ያወሩት ውሸት ነው እሳቸው ያወሩትን የሳቸውን ትረካ አላምንም ሲሉ አጃቢ ቁጥር ተብለው በትዝታዎች ቁጥር መጽሐፍ ቃላቸውን ያሰፈሩት የመንግስቱ የቅርብ አጃቢና ኬንያ ድረስ የሽቸው የሰጡት ምላሽ ደግሞ በአጭሩ እንዲህ ይነበባል ከመንግስቱ ጋር በጣም ስለምንቀራረብኖ አንደወንድማቸው ያዩኝ ስለነበር ስለሚያምኑኝና ቤተኛም ስለበርኩ በዚያን እለት ማለዳ ላይ ወደመኖሪያ ቤታቸው ሃጄ ወሮ ውባንቺን ሠላም ብዬ ጓዶች ለእለቱ ፕሮግራም ዝግጁ መሆናቸውን ሪፖርት አደረኩ በማለት ከሌላው ጊዜ የተለዬ የጉዞ እንቅስቃሴ እንዳልነበር ይጠቁማሉ ሲቀጥሉም ሁላችንም ብላቴ ሞቃታማ ስለሆነ ቀላል ወታደራዊ ዩኒፎርም ነው የለበስነው መንግስቱም ቢሆኑ ዘወትር ከሚይዙት ሳምሶናይትና በትረ መኮንናቸው በስተቀር ሌላ ነገር አልያም ሻንጣ ወይም ቦርሳ ኣልተጫነም ከፓይለቱና ከረዳት ፓይለቱ ጭምር ጠቅላላ አውሮፕላኑ ውስጥ የነበርነው ዘጠኝ ሰዎች ነበርን ሁኔታዎች የተለወጡት ብላቴ ልንደርስ ስንል ነው ፐሬዝዳንቱ ፓይለቱን ቀጭን ትዕዛዝ ሰጡት ከፍተኛ ስብሰባ ስሳለብኝ ወደ ናይሮቢ ሂድ አሉት ወደዚያ እንሄዳለን ስላልተባልኩ ካርታ አልያዝኩም አለ ፓይለቱ አጃቢዎቹም እኔም ደነገጥን እሳቸው ግን ፍንክች ሳይሉ የምቀርበት ጉዳይ አይደለምና እንደምንም ብለህ ሂድ ካስፈለገ ከኮንትሮል ታወር ጋር ተገናኝተህ እንዲመሩህ አድርግ ብቻ ናይሮቢ መድረስ አለብኝ አሉት በዚህ አይነት ሁኔታ ናይሮቢ ደረስን ከዚያ በኋላ የሆነው ፍፁም የተደናበረኖ ውዥንብር የበዛበት ነው በበኩሌ ማታውን ወደዙምባብዌ ከተጓዘው ግሩፕ ጋር እንድሄድ መንግስቱ ጠይቀውኝ ነበር እንደማልሄድና ወደአገሬ መመለስ እንደምፈልግ ስገልፅሳቸው አልተቃወሙኝም ወይም ሊያሳመኑኝና ሲያስቀሩኝ አልሞከሩም ስመለስ የሚጠብቀኝ መጥፎ ነገር ሊኖር እንደሚችል በመግለዕ ግን ስጋታቸውን አልሸሸጉኝም ህሳቤን እንደማልለወጥ ሲረዱ ለጄኔራል ተስፋዬ ገብረኪዳን የሚሰጥ ደብዳቤ ጽፈው ሰጡኝ ይሄንንም በማግስቱ እንደተመለስኩ ለጄኔራሉ ሰጥቻለሁ እንግዲህ በሬዲዮ አወጃው እንደሰማነው የወቅቱ ርዕሰ ብሄር ጄኔራል ተሰፋዬ ስለነበሩ ይጠቅማል ያሉትንና ከመሄዳቸው በፊት ሊነግሯቸው ያልቻሉትን ጉዳዮች ነው ደብዳቤው ላይ ያሰፈሩት ከደብዳቤው ሌላ እኔ በቃል እንድነግርላቸው የላኩኝ መልዕክትም ነበረ እሱም በጓድ መንግስቱ ገመቹ ትዕዛዝ ብቻ ሊወጣ የሚችል ከሰባት ሚሊዮን ተኩል በላይ የሆነ ብር ፍቅረስላሴ ወግደረስና ኃይሌ ይመኑ የሚያውቁት ከድሬዳዋ የጫት ገቢ የሚገኝና ለሱዳንና ለሶማሌ ነፃ ኣውጪዎች በየጊዜው ወጪ እየተደረገ የሚሰጥ ተቀማጭ ገንዘብ በገልፍ ጦርነት ለኩዌት ድጋፍ ስለሰጠን የኩዌት መንግስት በእርዳታ የሰጠን ሚሊዮን ብር ኃይሉ ይመኑና የገንዘብ ሜኒሰትሩ የሚያውቁት ይሄ ሁሉ ገንዘብ እንዳለ አውቀህ ከጓድ ነሲቡ ታዬ ጋር ተነጋግረህ ጦርነቱ ከቆመ ለከባድ ኢንደስትሪዎች ማቋቋሚያ ይሆናል የሚል ነበር ደብዳቤውንም መልዕክቱንም አድርሻለሁ በበኩሌ ምናልባት መንግሰቱ ከመሄዳቸው በፊት ለጄኔራል ተስፋዬ ነግረዋቸዋል የሚል ግምት አለኝ በሬዲዮ የመንግስቱ መጥፋት የተነገረበትን ሰዓት ሳገናዝበው ተስማምተው ያደረጉት ይመስለኛል እኛ ከዚህ ተነስተን እዚያ የደረስንበትን ሰዓትና መሄዳቸው በስድስት ሰዓቱ ዜና ላይ ከመታወጁ በፊት በኋላ እንደሰማሁት ጄኔራል ተስፋዬን ከስብሰባ ላይ አስጠርተው በስልክ ያነጋገሯቸውን ጊዜ ሳሰበው ሁለቱ ተስማምተው ይሆናል የሚል ጥርጣሬ አሳድሮብኛል ባለቤታቸው እኛ ወደ ብላቴ ከሄድን በኋላ በሌላ አውሮፕላን ተሳፍረው ዙምባቡዌ መሄዳቸውን በኋላ ሰማሁ ያኔ ቤተመንግስት ስደርሰና ሠላምታ ስንለዋወጥ ግን መንገድ ሊሄድ እንደተሰናዱ አልነገሩኝም የሚል ቃላቸውን ሰጥተዋል ትዝታዎች ቁጥር ገጽ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ግን አካሄዴ ከሀገር ወጥቼ ለመቅረት ሳይሆን ቀደም ብሎ ከቻይና ተገዝቶ በምሪፅሪዋና አሰብ ወደቦች መያዝ ምክንያት ሊገባ ያልቻለውን መሣሪያ በኬንያ በኩል ለማስገባት ከፕሬዝዳንት አራፕ ሞይ ጋር ለመነጋገር ነው የሚል ሲሆን ለአንባብያን ሁኔታው ግልፅ ይሆን ዘንድ ከጋዜጠኛ ገነት ኣየለ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ቀንጨብ አድርጌ አካትታለሁ ከተጠየቁ በኋላ ዙሪያ ጥምጥም የሆነ መልስ በመስጠት ላይ ሳሉ ገነት ከአገር እንዴት የጠየቅሁዎት ወደዚያ ብንመለስ መንግስቱ ከቻይና መንግስትና ከሌሎችም ወደ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ መሣሪያ ገዝተን ስለነበር ያንን ልናስገባ ስንል ኣሰብን አስያዙት የአሠብ መያዝ ጦርነቱን ውስብስብ ኣደረገው ቻይናዎቹን በአውሮፕላን አቅርቡልን ብንል በአውሮፕላን ማቅረብ አንቼልም የምንችለው በመርከብ ነው አሉን ይሄ በጣም አስቸጋሪ አጣብቂኝ ውስጥ ከተተን በምፅዋ አናስገባ በአሰብ አናስገባ ።