Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ጥያቄውን ለመመለስ ይከብዳል ኢህአፓ እስከ አሁን ድረስ ደርጎች የፈጠሩት የስም ማጥፋት ነው እንጂ የሶማሊያን ወረራ የደገፍኩበት ወቅት የለም በማለት ያስተባብላል የተወሰኑ የቀድሞ የኢህአፓ አባላትና አንዳንድ የታሪከ ምሁራን ግን ኢህአፓ ጦርነቱ የሁለት አድሃሪ መንግሥታት ጦርነት ነው ጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ የሶማሊያ ህዝብ አድሃሪያንን ደግፎ በጦርነቱ መሳተፍ የለበትም የሚል አቋም ወስዷል ይላሉ ይህ ምን ማለት ነው።
ጭብጨባው ጋብ ሲል ጋሸ ደመቀ ያስጨበጡንን መዝሙር መዘመሩን ቀጠልንበት የመዝሙሩ ግጥም የሚከተለው ነው የኢትዮጵያ ጀግና ጀግና ነው ሄደ በረሃ ሚሊሻው ፊቱ ደም መስሏል ተቆጥቷል ሶማሊያ ዛሬ ፈርዶባታል የሶማሊያ ጦር እርቦት ሰማይ ሰማዩን በማየት ቃፊሩ መጥቶ በድንገት ዳቦ አስመስሎ ቦምብ ጣለላት ዳቦ ነው ብላ ስትሻማ ተቀጣጠለች እንደ ሻማ ድድድቱቴቴ በምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ ካራ ማራ የሚል ስያሜ ያላቸው ሆቴሎችና ሻይ ቤቶች በብዛት ይገኛሉ በኔዋ ገለምሶም ካራ ማራ ሆቴል አለ ሆኖም ጣራ ማራ አኩሪ ጀግንነት የተፈጸመበት የድል ሜዳ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስረዱን ጋሸ ደመቀ ነበሩ በርግጥም ካራ ማራ የኢትዮጵያ ጦር ትልቁን ድል የተቀዳጀበት ወሳኝ የትግል ሜዳ ነው ጦርነቱ የተካሄደው በጄኔራል ዚያድ በሬ የምትመራው ሶማሊያ ኢትዮጵያን በመውረሯ ነው የኢትዮጵያ ጦር በካራማራ ተራራ ላይ ታላቁን ድል እስኪያገኝ ድረስ በብዙ ሂደቶች ውስጥ ማለፍ ነበረበት አነሆ ዓመታት ወደ ኋላ ተጉዘን ያንን ጦርነት እንዘከረዋለን ቅድመታሪከ የእንግሊዝ ሶማሊላንድ የምትባለው ግዛት በ ነጻነቷን ተቀዳጀች ከአራት ቀናት በኋላ ደግሞ የኢጣሊያ ሶማሊያ የምትባለው ምድር ነጻ ሆነች በወቅቱ የተበታተኑትን የሶማሊ ግዛቶች አንድ ላይ ሰብስቦ ታላቋ ሶማሊያን መፍጠር የሚል እሳቤ ይንቀለቀል ሰለነበር የሁለቱ ግዛቶች ፖለቲከኞቹም የጉዞ መስመራቸውን በዚህ ፈር ለመቀየስ ወሰኑ በመሆኑም ሁለቱ የሶማሊ ግዛቶች ከስድስት ወር በኋላ በመቀላቀል የሶማሊ ሪፐብሊክን መሰረቱ እነዚያ የሶማሊያ መሪዎች በያዙት መሬት ሳይብቃቁ እያንዳንዱ የሶማሊ መሬት በአዲሲቷ ሶማሊያ ሰር መግባት አለበት የሚል አጀንዳ እንደ መርህ ያዙ በመሆኑም ኢትዮጵያ ኬንያ እና ጅቡቲ የያዙትን መሬቶቻችንን አንፈልጋለን የሚል ሰበካ ጀመሩ በዚያ ወቅት ጅቡቲና ኬኒያ ነጻነታቸውን አላገኙም ስለዚህ ሶማሊዎቹ ከቅኝ ገዥዎቹ ፈረንሳይና እንግሊዝ ጋር መጋጠም አንደማያዋጣቸው ስላወቁ ትኩረታቸውን በኢትዮጵያ ላይ አደረጉ ከአንድ ዓመት በኋላም አነስተኛ የሰርጎ ገብ ሃይል በማደራጀት ኦጋዴን ለመውረር ሞከሩ ነገር ግን በጄኔራል አማን ሚካኤል አንዶም የሚመራው ሶስተኛ ከፍለ ጦር በአስር ቀናት ውስጥ ሶማሊዎቹን አባረራቸው ከዚያ በኋላ ሶማሊዎቹ በኢትዮጵያ ላይ የፕሮፓጋንዳ ጦርነት አፋፋሙ በ የተመሰረተው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ሊገስጻቸው ቢሞክርም እነርሱ ግን ከአድራጎታቸው አልታቀብ አሉ መሪያቸው የነበረው አደን አብደላ ዑስማን ዳሂር በአዲስ አበባ በተሰበሰበው የአፍሪቃ መንግሥታት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ መሬታችንን ወስዳለች ሲል ከሰሰ በአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ማቋቋሚያ ቻርተርም ላይ የአፍሪቃ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ ሲወጡ ያላቸውን ድንበር ይዘው ይቆያሉ የሚለውን አንቀጽ አልፈርምም አለ በ ደግሞ ሶማሊያ በይፋ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት አወጀች ይሁንና ጦርነቱ ረጅም ጊዜ ሳይቆይ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ ድድድቱቴቴ ሶማሊያ ከ ሽንፈት በኋላ ይፋዊ ጦርነቱን ትታ በአጅ አዙር መዋጋቱን ነው የመረጠችው ለዚህም ይረዷት ዘንድ የአጋዴን ሶማሌ አርነት ግንባር እና የምዕራብ ሶማሌ ነጻነት ግንባር ምሶኒግ የተባሉ ድርጅቶችን አቋቋመች የኦጋዴን ሶማሌ አርነት ግንባር ከአሁኑ የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻነት ግንባር ጋር አንድ አይደለም አሁን ያለው ኦብነግ በ ነው የተመሰረተው የነዚህ ድርጅቶች ዓላማ የኦጋዴንን በረሃ ከኢትዮጵያ ገንጥሎ ወደ ሶማሊያ መቀላቀል ነበር ይሁንና ድርጅቶቹ የኦጋዴን በረሃን ሊገነጥሉት ይቅርና የሚረባ ውጊያ አንኳ ማድረግ አልቻሉም በዚህም የተነሳ ከሁለቱ ድርጅቶች መካከል በደካማ አቋም ላይ የነበረው የኦጋዴን ሶማሌ አርነት ግንባር ብዙ ሳይቆይ ከስሟል ምሶነግ ግን አየተንደፋደፈም ቢሆን ውጊያውን ቀጥሏል ጄኔራል ሙሐመድ ዚያድ ባሬ በ በመንፈቅለ መንግሥት ስልጣን ሲይዙ ደግሞ ሁሉም ነገር ከመሰረቱ ተቀየረ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ የምትፈልገው ኦጋዴንን ብቻ አይደለም ተባሰ ብኢትዮጵያ የተወሰደብን መሬት የሀረርጌ ባሌ አና ሲዳሞ ከፍለ ሀገራትን የሚያጠቃልል ነው የሚል አዋጅ ታወጀ ይህ ሰፊ ግዛት በጥቅሉ ሶማሊ ገልቤድ ምዕራብ ሶማሌ ተብሎ ተሰየመ በውስጡ የሚኖሩት ሶማሌ ያልሆኑ ህዝቦችም ከጊዜ ብዛት ቋንቋቸው ቢቀየርም ጥንተ ማንነታቸው ሶማሊ ነው ተብሎ ተነገረ በሶማሊያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ስደተኞችም አዲሱን መርህ እንዲያቀነቅኑ ተገደዱ እምቢ ያሉት ደግሞ ወደ አስር ቤት ተወረወሩ ከዚህ በተጨማሪም በባሌና በሲዳሞ ከፍለ ሀገር የሚደረገውን ውጊያ የሚያስተባብር የሶማሌ አቦ ነጻነት ግንባር ለኢነግ የተባለ ድርጅት ተመሰረተ በጥቅሉ የሶማሊያ መንግሥት ከአዋሽ ወንዝ በታች ያለው መሬት በሙሉ የኔ ነው የሚል አቋም ማራመድ ጀመረ ይህ በዚህ አንዳለ የሶማሊያ መንግሥት የሶሻሊዝም ተከታይ መሆኑን በይፋ በማወጁ ከሶቪየት ህብረት ጋር የወታደራዊ ተራድኦ ስምምነት ተፈራራመ በስምምነቱ መሰረት ከሶቪየት ህብረት አዳዲስ የጦር መሳሪያዎችን በገፍ አገኘ ለሰባት ዓመታት ያህልም ሰራዊቱን ሲያሰለጥንና ሲያደራጅ ሰነበተ በውጤቱም የዚያድ ባሬዋ ሶማሊያ ከ የማያንሱ ዘመናዊ የውጊያ አውሮፕላኖችን የታጠቀ አየር ሀይል እና አራት ሜካናይዝድ ከፍለ ጦሮችን ያቀፈ ግዙፍ የጦር ሰራዊት ባለቤት ለመሆን ቻለች እንግዲህ የሶማሊያ መንግሥት ይህንን ሁሉ ካደረገ በኋላ ነው በኢትዮጵያ ላይ ወረራ የፈጸመው ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል ሁለት የድብቅ ወረራ የሶማሊያ መንግሥት ወረራውን በቀጥታ አልጀመረም በቅድሚያ በድብቅ ያደራጃቸውን የምዕራብ ሶማሌ ነጻ አውጪ ግንባር ምሶነግ ህፐ አና የሶማሊ አቦ ነጻነት ግንባር ሶአነግ ኗላ አሸማቂዎችን በማስቀደም ነው እድሉን የሞከረው በዚህም መሰረት በመጋቢት ወር የምሶነግ ተዋጊዎች ከሀርጌሳ መስመር እየተነሱ በኦጋዴንና በደጋማው የሀረርጌ ከፍል ተሰማሩ የሶኢነግ ተዋጊዎች በበኩላቸው በባሌ ከፍለ ሀገር ወደ ውስጥ እየሰረጉ እስከ ጊኒር እና ጎሮ አውራጃዎች ድረስ ለመግባት ቻሉ እነዚህ ሀይሎች ወደ ኢትዮጵያ በገበብት ወቅት የደርግ መንግሥት ከኢህአፓ ጋር በገጠመው ትግል እየተናጠ ነበር ጀብሃና ሻዕቢያም በሰሜኑ በኩል ወጥረው ይዘውታል ኢዲዩ የተባለው ድርጅትም የሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የጠረፍ ከተሞቸን ይዞ ደርግን እያስጨነቀ ነው የምሶነግ እና የሶኢኒግ ሀይሎች አንደሚፈልጉት ድል ሊቀናቸው አልቻለም ራቅ ባሉ ጫካዎችና ተራራዎች ከመመሸግ በስተቀር ወደ ከተሞች እየተጠጉ የኢትዮጵያን ሰራዊት ማስጨነቅ አልቻሉም በመሆኑም የሲቪል ልብስ የለበሱ የሶማሊያ ሰራዊት አባላት በምሶኒግ ውስጥ በብዛት እንዲቀላቀሉ ተደረገ ነገር ግን ይህኛውም ስትራቴጂ ውጤት ማስገኘት አልቻለም ሁለቱ የምሶኒግ እና የሶኢነግ ሀይሎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የትኛውንም ከተማ መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር በዚህ ተስፋ የቆረጡት የሶማሊያ የጦር አዝማቾችም ፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬ መደበኛ ሰራዊታቸውን እንዲያንቀሳቅሱ ይወተውቷቸው ጀመር ፕሬዚዳንት ዚያድ ግን ለጦር አዝማቾቹ ውትወታ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት አልፈለጉም ይህም የሆነው ከሶቪየት ህብረት አማካሪዎቻቸው የተሰጣቸውን ተግሳፅ በመፍራታቸው ነው ሶቪየቶቹ ኢትዮጵያን እየወረራቸሁ ነው የሚል ስሞታ ሲያቀርቡባቸው እኛ አይደለንም የአጋዴን ሶማሊዎች ለነጻነታቸው የሚያደርጉት ትግል ነው እያሉ ሲከላከሉ ቆዩ በግንቦት ወር ደግሞ ያልተጠበቀ ከስተት ተፈጠረ የጎዴን ከተማ እንዲያጠቃ የታዘዘ አንድ የምሶነግ ሻለቃ ከኢትዮጵያ ጦር በገጠመው የመከላከል አርምጃ ሙሉ በሙሉ ተደማመሰሰ ያህል ተዋጊዎቹ በአንድ ቀን አለቁ በርካቶች ቆሰሉ የሽምቅ ተዋጊውን ቡድን አንዲመሩ የተመደቡ አስራ አራት የሶማሊያ የጦር መኮንኖችም ከሟቾቹ መሀል ነበሩ ይህ ከፉ ዜና በሞቃዲሾ ሲሰማ በጦር ሀይሉ ውስጥ ከፍተኛ ቁጣ ተቀሰቀሰ በፕሬዚዳን ዚያድ ባሬ የሚመራው የሶማሊያ ከፍተኛ አብዮታዊ ምከር ቤት ለአስቸኳይ ውይይት ተቀመጠ በውይይቱ መጨረሻ ላይ በተደረሰበት ስምምነት መሰረትም ለአንድ ወር ያህል የድብቅ ወረራው ተጠናከሮ አንዲቀጥል ተወሰነ በዚህ ጊዜ ትኩረት የተደረገባቸው ከተሞች በኢትዮ ሶማሊያኬንያ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘው የዶሎ ኦዶ ከተማ በደቡባዊ ኦጋዴን የምትገኘው የባሬ ከተማ እና በደቡባዊ ባሌ ያለው የኤልከሬ ቆላማ ስፍራ ነው በዚህ የድብቅ ውጊያ ወደ ኢትዮጵያ የዘመተው የሶማሊያ ሰራዊት መደበኛ ዩኒፎርም እንዲለብስ አልተደረገም የዚህ ድብቅ ውጊያ ዓላማ የኢትዮጵያን ሰራዊት ማስበርገግና የውጊያ አቋሙን መፈተሽ ነበር የይፋ ወረራ ሀምሌ ኑ በድብቅ የሚደረግ ማንኛውም አንቅስቃሴ አበቃ ፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬ የታላቋ ሶማሊያ ምስረታ እውነት የሚሆንበት ጊዜ የመጣ መስሎ ታያቸው በመሆኑም ለዘመናት ሲያደራጁት የነበረው ሰራዊት ሙሉ ማጥቃት አንዲጀምር ትዕዛዝ ሰጡ ለዓመታት ለወረራ ሲዘጋጅ የነበረው የሶማሊያ የጦር ሀይል በኢትዮጵያ መሬት ላይ ዘመተ የሶማሊያ ጦር ወደ ኢትዮጵያ የገባው በሁለት መስመሮች ነው የአጋዴን መስመር በዚህ መስመር ወደ ኢትዮጵያ የገባው የሶማሊያ ጦር በኦጋዴን የፌርፌር ከተማ ትይዩ ካለችው የበለድወይን ከተማ ይነሳል የመጨረሻ ግቡ ደግሞ መላውን የኦጋዴን ቆላማ አውራጃዎች መቆጣጠር ነው የዶሎ አዶ መስመር በዚህ መስመር የተሰለፈው ጦር ደግሞ ከሶማሊያዋ የባይዶዋ ከተማ ይነሳል ዶሎ ኦዶ ከምትባለው የድንበር ከተማ ከደረሰ በኋላም ለሁለት ተከፍሎ ወደ ባሌና ሲዳሞ ከፍለ ሀገራት ይዘምታል በሁለት የተከፈለው የጠላት ሀይል የመጨረሻው ግብ የባሌ ጎባ እና ነጌሌ ቦረና ከተሞችን መቆጣጠር ነው ከባይዶዋ አካባቢ የተነሳው የሶማሊያ ጦር ይህ ነው የሚባል መከላከል አልገጠመውም በመሆኑም በሲዳሞ ክፍለ ሀገር እየገሰገሰ ሄዶ ከነጌሌ ቦረና አርባ ኪሜ ርቀት ላይ ደረሰ በባሌ ከፍለ ሀገር ደግሞ አስከ ደሎ መና ከተማ ያለውን መሬት ለመያዝ ቻሰ ሶማሊዎች ውጊያው አንዲህ የቀለላቸው ብዛታቸው ስለረዳቸው አልነበረም ይልቁንም ኢትዮጵያ በነዚህ መስመሮች ጠንከር ያለ ሰራዊት ስላልነበራት ነው የነጌሌ እና የጎባ ከተሞች እንኳ በጠላት እጅ ከመውደቅ የተረፉት የኢትዮጵያ አየር ሀይል ለእግረኛ ተዋጊዎቹ ከፍተኛ የሸፋን አገዛ በማድረጉ ነው የኢትዮጵያ መከላከያ ሀይል ጠላትን በዐይነ ቁራኛ ሲጠብቅ የነበረው በኦጋዴን መስመር ነበር በመሆኑም ከበለድወይን የተነሳው የሶማሊያ ሰራዊት የአጋዴን አውራጃዎችን በቀላሉ መቆጣጠር አልቻለም የኢትዮጵያ ተዋጊዎች ኦጋዴንን ላለማስነጠቅ እስከ መጨረሻው ተሟሙተዋል በተለይም በሐምሌ አጋማሽ በ ማብቂያ ላይ የቀብሪደሃር ከተማን ላለማስለቀቅ በተደረገው ትግል በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ተሰውተዋል ሶስተኛው የወረራ ግንባር የኢትዮጵያ ሰራዊት ኦጋዴንን ላለማስነጠቅ በሚታገልበት ወቅት ሶማሊዎች በጦርነቱ ሂደት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያስከተለ እርምጃ ወሰዱ ይህም የሶስተኛ የወረራ ግንባር መከፈት ነው በዚህ የወረራ ግንባር የተሰማራው የሶማሊያ ሰራዊት የተነሳው ከሰሜን ሶማሊያዋ የሀርጌሳ ከተማ ነው የመጨረሻ ግቡ ደግሞ የሀረርና የድሬ ዳዋ ከተሞችን ጨምሮ የደጋማውን የሀረርጌ ከፍል መቆጣጠር ነው በሶስተኛው ግንባር የተሰማራው የሶማሊያ ጦር በብዛቱ በሌሎች ግንባሮች ከዘመተው ይበልጣል በጣም ምርጥ የተባሉ የጦር መሳሪያዎችንም ታጥቋል ሶማሊያ ካላት አራት ሜካናይዝድ ከፍለ ጦሮች መካከል ሁለቱ በዚህ ግንባር ተሰልፈዋል የሶማሊያ አየር ሀይልም ሙሉ ሙሉ ትኩረቱን በዚህ ግንባር ላይ አድርጓል የሶማሊያ የፕሮፓጋንዳ ሀይሎችም ሀረር ተከበበችቸ ድሬ ዳዋ ተያዘች አያሉ ማሸበር ጀምረዋል የኢትዮጵያ መንግሥት አመራሮች ሶማሊያ በሶስተኛው ግንባር ውጊያ ትከፍታለች ብለው አልጠበቁም ነበር በመሆኑም ወረራውን ለማስቆም ምን ዓይነት አርምጃ መውሰድ አንዳለባቸው ከውሳኔ ላይ ለመድረስ ተቸገሩ የሶማሲያ ጦር የመጨረሻ ጉዞ የት ሊሆን አንደሚችል ማወቅም ተሳናቸው በመሆኑም ሊቀመንበር መንግሥቱና ሌሎች ጓዶቻቸው በጉዳዩ ዙሪያ ለመወሰን አስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጡ በስብሰባው ላይ የሶቪየት አማካሪዎችም ተገኝተው ነበር ስብሰባው በዝግ ከተደረገ በኋላ ኦጋዴንን በስልታዊ ማፈግፈግ መልቀቅና ድሬ ዳዋና ሀረርን ማዳን የሚለው ሃሳብ ተቀባይነት አገኘ ስለዚህ የኢትዮጵያ ጦር ከኦጋዴን ለቆ በጅጅጋና ጉርሱም አውራጃዎች ውስጥ እንዲሰፍር ተደረገ ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ ኙኛዐፊሪ ነሪ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል ሶስት ። እና ኤጵኤስ አንደሚተኩም ቃል ተገብቶለታል የግርኖቭ መትረየሶችና ላውንቸሮችም ከሶቪየት ህብረት አንደሚመጡ ተነግሯል የአየር ሀይሉም የሚግ ጄቶችና ለወታደራዊ አቪየሽን የሚያገለግሉ አንቶኖቭ አውሮፕላኖችን ሊታጠቅ ተዘጋጅቷል ይሁንና ኢትዮጵያ ቃል የተገባላትን መሳሪያ በቶሎ ለማግኘት አልቻለችም በመሆኑም ከሀምሌ እስከ ህዳር ድረስ ድሮ በነበሯትና ከቻይናና ከዩጎዝላቪያ ባገኘቻቸው መሳሪያዎች መከላከል ነበረባት ኩባ የሚሆን ሚቺ የሚባለውን ባለ አገልግል ጠመንጃ ለኢትዮጵያ ብትሰጥም መሳሪያው ጥይት እየነከሰ ስለሚያስቸግር ለውጊያ መጠቀም አልተቻለም ሊቀመንበር መንግሥቱ እንደሚሉት እነዚያ ጠመንጃዎች በመጋዘን ውስጥ ከቆዩ በኋላ እነ ጄኔራል ፋራህ አይዲድ በፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬ ላይ ሲያምጹ በእርዳታ ተሰጥቶአቸዋል በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የሶቪየትና የሌሎች ሶሻሊስት ሀገራት መሳሪያዎቹ በፍጥነት ቢመጡላት አንኳ መሳሪያዎቹን ወዲያኑ በጥቅም ላይ ለማዋል የምትቸልበት ሁኔታ አልነበረም ምከንያቱ ደግሞ መሳሪያዎቹ ለኢትዮጵያ ሰራዊት አዲስ በመሆናቸው ስለ አጠቃቀማቸው ማወቁ ጊዜን የሚጠይቅ በመሆኑ ነው ከዚሁ ጎን ለጎንም የኢትዮጵያ መደበኛ ሰራዊትና የአየር ሀይል ከፍተኛ የውጊያ ስልጠና ያስፈልገው ነበር የኢትዮጵያ መሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ሁኔታዎች ካጤኑ በኋላ ሁለት ውሳኔዎችን ወሰኑ አንደኛው መደበኛ ሰራዊቱን ለማጠናከር የሚረዳ ተጨማሪ ሀይል በብዛት ተመልምሎ በስልጠና ላይ እንዲቆይ የሚል ነው ሁለተኛው በታጠቅ ካምፕ ሲሰለጥን የነበረው የሚሊሻ ሰራዊት በቶሎ ወደ ግንባር ተልኮ ወረራውን በመከላከል ላይ የነበረውን ሰራዊት እንዲያግዝ የሚል ነው በተጨማሪም ሚሊሻውን የማሰልጠኑ ተግባር በየከፍለ ሀገሩ እንዲጀመር ተደርጓል የኢትዮጵያ መሪዎች የወሰዱት አርምጃ ከወታደራዊ ስልት አንጻር ሲታይ በጣም ትክክል ነው ተብሎ ተወድሷል ከላይ እንደተገለጸው የኢትዮጵያ መደበኛ ሰራዊት በብዙ እጥፍ የሚበልጠውን የሶማሊያ ሰራዊት ከሀገሩ ለማባረር የተጠናከረ ስልጠና ይፈልጋል የውጊያ ስልጠናውን ካጠናቀቀ በኋላም ከሶቪየት ሰራሽ መሳሪያዎች ጋር እስኪተዋወቅ ድረስ በቂ ልምምድ ማድረግ ይኖርበታል ለዚህ ደግሞ በቂ ጊዜ ይሰጠው ዘንድ የግድ ይላል በተለይ የከባድ መሳሪያ ተኳሾችንና የአውሮፕላን አብራሪዎችን በአጭር ጊዜ ለውጤት ማብቃት አይቻልም ስለዚህ እነርሱ እስኪሰለጥኑ ድረስ የነርሱን ቦታ ሸፍኖ የሚዋጋ ሀይል መኖር ነበረበት ይህንን ለማድረግ የተሻለው አማራጭም የሚሊሻ ሰራዊቱን በፍጥነት አሰልጥኖ ወደ ግንባር ማሰማራት ነው የመከላከል ውጊያ በምስራቅ ግንባር በከፍል ሁለት እንደተገለጸው ሶማሊያ አደገኛ ወረራ ያደረገቸው በሀርጌሳ ግንባር ነው የኢትዮጵያ ሰራዊትም በዚህ ግንባር ተጠቃልሎ በመግባት ከፍተኛ የመከላከል ውጊያ ሲያደርግ ነበር በወቅቱ ለኢትዮጵያ መሪዎች ያስቸገረው የሶማሊያ ጦር የስምሪት አቅጣጫዎችንና የመጨረሻ ዒላማዎችን ማወቁ ነው ቀደም ሲል በነበረው ግምት ወራሪው ሰራዊት ጅጅጋን ከያዘ በኋላ በማስከተል ወደ ሀረር ይመጣል ተብሎ ይጠበቅ ነበር በመጀመሪያ ላይ በጅጅጋ ላይ በከፍተኛ ብዛት በመረባረቡ ግምቱ ትከከል ነው ተባለ የኢትዮጵያ ጦር ለአራት ቀናት ከተከላከለ በኋላ በመስከረም ወር አጋማሽ የጅጅጋ ከተማን ለቆ ወደ ኋላ አፈገፈገ ከዚያም የመከላከያ ወረዳውን ከጅጅጋ በስተምዕራብ በ ኪሎ ሜትር ላይ በምትገኘው የቆሬ ከተማ ላይ አደረገ በሚቀጥሉት ቀናት የሶማሊያ ሀይሎች በቆሬ በከተመው የኢትዮጵያ ጦር ላይ ከፍተኛ ውጊያ ከፈቱ ነገር ግን ኢትዮጵያዊያኑ በቆራጥነትና በጀግንነት ተከላከሉ በዚህ ጊዜ ሶማሊዎች ሳይታሰብ አንድ አደገኛ እርምጃ ወሰዱ ይህም በበብዙ ታንኮች የተጠናከረ ጦር ከጅጅጋ በስተሰሜን አቅጣጫ ማዝመታቸው ነው የኢትዮጵያ የጦር መሪዎች ሶማሊዎቹ በጉርሱም አውራጃ በማሳበር ወደ ሀረር ከተማ የሚያመሩ ነው የመሰላቸው በመሆኑም በሀረር ዙሪያ የነበረውን ጥበቃ አጠናከሩ ነገር ግን በነሀሴ ወር መጀመሪያ ላይ የሶማሊ ሀይሎች ወደ ድሬ ዳዋ እየገሰገሱ መሆናቸው ታወቀ በዚህም ጊዜ በኢትዮጵያ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤ ተፈጠረ ለድሬ ዳዋ የሚረባ መከላከያ አልተደረገም በሚል መወቃቀስ ተጀመረ በከተማዋ የነበሩትን ሁለት ሚሊሻ ከፍለ ጦሮችና አንድ ነበልባል ብርጌድ ከከተማዋ አርቆ ጠንካራ መከላከያ ማበጀት እንደሚገባም ትዕዛዝ ተላለፈ ከነዚህ ብርጌዶች ጋር ተደራቢ ሆኖ የሚዋጋ አንድ ሜካናይዝድ ብርጌድ በአፋጣኝ ተመደበ ከዩጎዝላቪያ የተገኙት ሰባ ታንኮችም በዚህ ግንባር እንዲሰለፉ ተደረገ አንድ ሚሊሻ ከፍለ ጦርና አንድ መደበኛ ብርጌድም ከተማዋን አንዲጠብቁ ተደረገ ደቡብ የመን ለኢትዮጵያ የሰጠቸው ሰላሳ ሶስት ታንኮችም ከስፍራው ደረሱ የኢትዮጵያ ሰራዊት የመከላከያ ጣቢያውን ሟልዴሳ በተባለ ስፍራ ላይ መሰረተ ይህ ስፍራ ከድሬ ዳዋ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በ ኪሎ ሜትር ላይ ነው የሚገኘው ነሀሴ ቀን ወደ ድሬ ዳዋ የሚያመራው የሶማሊያ ሰራዊት ሟልዴሳ ሲደርስ ያልጠበቀው ውጊያ ገጠመው ሶስት ቀናት ሙሉ ቢዋጋም ጀልዴሳን ማለፍ አቃተው በመሆኑም ተጨማሪ ጦር አስመጥቶ እንደገና ሌላ ጥቃት ከፈተ ነገር ግን የኢትዮጵያ ሀይሎችን አንበርከኮ ለማለፍ ሳይቸል ቀረ የሶማሊያ ሰራዊት በዚህ ተስፋ ሳይቆርጥ ለሶስተኛ ጊዜ ሀይለኛ የሜካናይዝ ውጊያ ከፈተ ይሁን እንጂ የሶስተኛው ዙር ጥቃት ለሶማሊዎቹ ከበፊቱ የባሰ ውድቀትን ነው ያስከተለው ምከንያቱም የኢትዮጵያ ሰራዊት የውጊያ ስልቱን በመለወጡ ነው ይህም ማለት ሰራዊቱ አንደ በፊቱ መከላከሉን ትቶ ወደ ማጥቃቱ አንዲገባ ነው የተደረገው የኢትዮጵያ የጦር ኤክስፐርቶች ይህንን ለውጥ ያደረጉት የአካባቢው ሜዳማነት ለሜካናይዝድ ውጊያ የሚያመች መሆኑን በማጤናቸው ነው ከዚህም ሌላ በኮሎኔል ፋንታ በላይ የሚመራው የኢትዮጵያ አየር ሀይል ሙሉ ትኩረቱን በዚህ ግንባር ላይ አንዲያደርግ ታዝዞ ነበር በመሆኑም የሶማሊያ ጦር ያልጠበቀው ሽንፈት ገጥሞታል ለውጊያው ካሰለፋቸው ታንኮች መካከልም ብዙዎቹ ተቃጥለውበታል በዚህም የተነሳ ሶማሊዎቹ በነሀሴ ወር መገባደጃ ላይ ድሬ ዳዋን የመያዝ አቅዳቸውን እርግፍ አድርገው በመተው ሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ሀረር አዞሩት ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል አምስት ሀረርን የመከላከል ውጊያ ከምስራቅና ደቡብ ኢትዮጵያ ከተሞች ሁሉ የሶማሊያ ጦር ከፍተኛ ትኩረት ያደረገው በሀረር ላይ ነው ለዚህም ምከንያት አለው ሀረር ረጅምና ጥንታዊ ታሪከ ያላት ከተማ በመሆኗ የሶማሊያ መሪዎች የኛ ከተማ ናት ይሏት ነበር በሁለተኛ ደረጃ ሀረር የዘመኑ ትልቁ የኢትዮጵያ ከፍለ ሀገር የነበረው የሀረርጌ ዋና ከተማ ናት በሶስተኛ ደረጃ ኢትዮጵያ ከነበሯት አራት ከፍለ ጦሮች መካከል በጣም ግዙፍ የሆነው የሶስተኛ ከፍለ ጦሮች ዋና የማዘዣ ጣቢያ የሚገኝባት ከተማ ነበረች በአራተኛ ደረጃ ሀረር ብቸኛው የአትዮጵያ የጦር አካዳሚ የሚገኝባት ከተማ ናት የሶማሊያ መሪዎች ይህንን ሁሉ በማመዛዘን ነው ሀረርን የትልቋ የድል ብስራት ማወጃ ማዕከል በማድረግ ያተኮሩባት የሶማሊያ ጦር ሀረርን የመያዝ ጥረቱን የጀመረው በጥቅምት ወር መጀመሪያ ላይ ነው ውጊያውንም የጀመረው ከሀረር በ ኪሎሜትር ከጅጅጋ በ ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው የቆሬ ግንባር ነው ኢትዮጵያዊያኑ በዚህ ውጊያ ሲወጠሩ የሶማሊያ ሰራዊት ከጭናከሰን ከተማ አቅራቢያ ተነስቶ በጉርሱም አውራጃ ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት በመራመድ የኤጀርሳ ጎሮ ከተማን ያዘ በዚህም ሳያበቃ ሀይሉን ለሶስት በመከፈል አንደኛውን ቡድን በትንሺ የፈላና ከተማ ከተማ አቅጣጫ ወደ ሀረር ላከለው ሁለተኛው ሀይል ከሀረር በስተሰሜን በመገስገስ የኮምቦልቻ ከተማን ከያዘ በኋላ ወደ ሀረር መግፋት ጀመረ ሶስተኛው በአስደናቂ ፍጥነት ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ተጉዞ ከሀረር በስተምዕራብ ካለችው የአዴሌ ከተማ አጠገብ ደረሰ የዚህኛው ግብረ ሀይል ዓላማ የኢትዮጵያ ሰራዊት ከድሬ ዳዋ አቅጣጫ ድጋፍ አንዳይመጣለት መከላከል ነው የኢትዮጵያ ሰራዊት ሀረርን ላለማስነጠቅ ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረግ ጀመረ ለውጊያው ከተሰለፈው ሀይል በተጨማሪ በተጠባባቂነት የተያዙ የመደበኛና የሚሊሻ ሰራዊት አባላት በሙሉ ሀረርን ለመከላከል እንዲሰማሩ ታዘዙ ነገሮች ሁሉ አንዲህ በከረሩበት ጊዜ ደግሞ የሶማሊያ ሰራዊት አንድ ግብረ ሀይል ሌላ ያልታሰበ የውጊያ ግንባር ከፈተ ይኸውም ሀይል የመጣው ከሀረር ከተማ በስተደበብና በደቡብ ምዕራብ በኩል ነበር በዚህ በኩል ወደ ሀረር የደረሰው የሶማሊያ ሰራዊት ከሁለት አካባቢዎች ነበር የተነሳው የአንደኛው መነሻ በባሌ ከፍለ ሀገር የምትገኘው የኤልከሬ ከተማ ናት ከዚያች ከተማ የተነሳ አንድ የሶማሊያ ብርጌድ ሽቅብ ወደ ላይ እየተጓዘ የዋቢ ሸበሌን ወንዝ በማቋረጥ ከሀረር ከተማ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ ከምትገኘው ትንሺ የፊቅ ከተማ ገባ ሁለተኛው ሀይል ደግሞ በኦጋዴን ካለችው የደጋሀቡር ከተማ ከተነሳ በኋላ ወደ ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ እየገሰገሰ ፊቅ ከተማ ደረሰ እነዚህ ሁለት ሀይሎች አንድ ላይ በመጣመር በቀድሞው የሀረር ዙሪያ አውራጃ ውስጥ ካለው የፈዲስ ወረዳ ከገቡ በኋላ ለሁለት ተከፈሉ አንደኛው ሀይል የሰሜን ምስራቅ አቅጣጫን በመያዝ ሀረርን በደቡብ ምስራቅ የሚያዋስነውን የሀኪም ጋራ እንዲቆጣጠር ግዳጅ ተሰጠው ሁለተኛው ሀይል ቀጥታ ወደ ሰሜን እየተጓዘ የሀረር ከተማ ምዕራባዊ ድንበር የሆነውን የአቦከር ተራራን እንዲይዝ ታዘዘነ የሶማሊያ ሀይሎች ፍጥነት በታየበት በዚህ ዘመቻቸው ሀረርን ሙሉ በሙሉ ለመከበብ ቻሉ አልፎ ተርፎም በደቡብና በሰሜን በምዕራብ የመጡት ግብረ ሀይሎች መድፎቻቸውን የሀረር ከተማ ተጎራባች በሆኑት የአው ሀኪም እና የድሬ ጠያራ ቀበሌዎች ውስጥ በማስቀመጥ ከተማዋን መደብደብ ጀመሩ ኮሎኔል መንግሥቱ በመጽሐፋቸው ገጽ ላይ የሶማሊያ ጦር ሀረርን ያዘ ይላሉ አንዳንድ ምንጮች ደግሞ የሀረር ከተማ የተወሰኑ ከፍሎች በሶማሊያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ወድቀው ነበር በማለት ጽፈዋል ይሁንና በሀረር ከተማ ቆይታዬ ያነጋገርኳቸው የከተማዋ ነዋሪዎችና የያኔው የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት የሀረር ከተማ በሶማሊ ሰራዊት አንዳልተያዘች አረጋግጠውልኛል የሶማሊያ ሰራዊት ሀረርን ቢይዝ ኖሮ ከተማዋን ማስመለስም ሆነ ለቀጣዩ ጦርነት የኢትዮጵያን ሰራዊት መልሶ ማደራጀቱ በጣም አስቸጋሪ ይሆን ነበርነ የሶማሊያ ጦር ከሀረር ከተማ በአራት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ደርሷል ታዲያ ከተማዋን ለመያዝ ያልቻለበት ምከንያት ምንድነው። ሶስት ምከንያቶች አሉት አንደኛው ኢትዮጵያ በስልጠና ላይ የነበረውን የሚሊሻ ጦር በከፊል አስመርቃ በውጊያው እንዲሳተፍ ለማድረግ መቻሏ ነው በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የነበሩትን የጦር ሀይሎች በፍጥነት አጓጉዞ በመከላከሉ ውጊያ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ መቻሉ ይጠቀሳል ይሁንና እነዚህ ሁለት ምክንያቶች አንደ ደጋፊ ተደርገው ነው ሀረርን በሶማሊያ ወራሪ ሰራዊት ከመወሰድ የዳነችበት ዋነኛ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር ሀይል ያደረገው ተጋድሎ ነው የኢትዮጵያ አየር ሀይል በወቅቱ ጥቂት የጦር አውሮፕላኖች ናቸው የነበሩት ከሶቪየት የተገኙት አውሮፕላኖችም በዚያን ጊዜ ወደ ሀገር ቤት አልገቡም ነገር ግን የአየር ሀይሉ አብራሪዎች በጣም የተዋጣላቸው በመሆናቸው ዒላማቸውን ሳይስቱ ይመቱ ነበር በድሬ ዳዋ መልዴሳ ግንባር በርካታ ታንኮቸን ከጥቅም ውጪ እንዳደረጉት ሁሉ በዚህም ግንባር የሶማሊያ መድፎችንና ሞርታሮችን በመደምሰስ ከዒላማቸው አሰናከለዋል ታዋቂው የኢትዮጵያ አየር ሀይል አብራሪና የህብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጄኔራል ለገሰ ተፈራ ብቃቱን ካሳየባቸው ግዳጆች አንዱ ያ ሀረርን ለመከላከል የተደረገው ውጊያ ነው በነገራቸን ላይ የሶማሊያ ሰራዊት ሀረርን ለመያዝ በተደረገው ዘመቻ መድፍና ቢ ኤም እንጂ ታንከ መጠቀሙ አልተዘገበም የሶቪየትኩባደበብ የመን አጋርነት ለኢትዮጵያ ነሀሴ ወር ሶቪየት ህብረት ለመጨረሻ ጊዜ ፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬን ወደ ሞስኮ ጠራቻቸው በሀይል የያዙትን የኦጋዴንን ግዛት እንዲለቁ እና ጉዳዩን በሰላም እንዲጨርሱም መከረቻቸው ፕሬዚዳንት ዚያድ ግን በእምቢታቸው ጸኑ በዚህም የተነሳ ታላቋ ሶቪየት ህብረት ተግባራዊ አርምጃ መውሰድ ጀመረች ቀደም ሲል በተስማማችው መሰረት በመስከረም ወር ለኢትዮጵያ የ ሚሊዮን ዶላር መሳሪያ የሚሸጥበትን ሂደት ገቢራዊ ማድረግ ጀመረች በመርከቦቿ ወደ ሶማሊያ ነዳጅ ማጓጓዙን አቋረጠች ለሶማሊያ የምታደርገውን የጦር መሳሪያ ሽያጭንም አቆመት ሶማሊያ በህዳር ወር በሀገሯ የነበሩትን የሶቪየት አማካሪዎች ስታባርር ሶቪየት ህብረት ወራሪ በማለት አወገዘቻት ወረራውን ለመቀልበስ ከኢትዮጵያ ጋር በሙሉ ፍላጎት አንደምትሰራም አስታወቀች በዚህም መሰረት እንደ እርሷ ሁሉ የኢትዮሶማሊያ ውዝግብን በሰላም ለመቋጨት ጥረት ሲያደርጉ የነበሩትን ኩባና ደቡብ የመንን የሚያካትት ወታደራዊ አከሲስ ተመሰረተ የዚህ አከሲስ ተግባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት የሶማሊያ ሰራዊትን ማባረር ነው ሶስቱ ሀገራት በጦርነቱ የነበራቸው ተሳትፎ ሲጠቃለል የሚከተለውን ይመስላል ሀ ሶቪየት ህብረት ሶቪየት ህብረት የምድር ጦር ሀይሏ ምከትል አዛዥ የነበሩትን ሜጀር ጄኔራል በኋላ ፊልድ ማርሻል ቫሰሊ ፔትሮቭን የዓለም አቀፉ ቡድን ሃላፊ አድርጋ መድባለች የጄኔራሉ ሃላፊነት የኢትዮጵያን ሰራዊት ማማከርና በኢትዮጵያ መሪዎችና ሞስኮ በሚገኘው የሶቪየት ህብረት የጦር ሀይሎች ጠቅላይ መምሪያ መካከል እንደ አገናኝ ሆኖ ማገልገል ነው ከጄኔራል ፔትሮቭ በተጨማሪ ሶቪየት ህብረት በከፍለ ጦርና በብርጌድ ደረጃ የሚያገለግሉ የጦር አማካሪዎችን መድባለች የከባድ መሳሪያና በረራ አሰልጣኞችን አስመጥታለቶ የሶማሲያ የጦር ሀይል ከምችትና የስምሪት አቅጣጫዎችን የሚያሳዩ የጦር መረጃዎችን ስታቲስቲከስ ካርታ ወዘተ ለኢትዮጵያ ሰጥታለች ለጦር ቁስለኞች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታና የቀዶ ጥገና ህከምና የሚሰጡ ሀኪሞችን መድባለች ከዚህ ሌላ ሶቪየት ህብረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ አጋር ሆና ቆይታለች ሆኖም ሶቪየቶች ድጋፍ ሰጪ ከመሆን ባሻገር ተዋጊ የጦር ሀይል አልመደቡም ሊ ኩባ በቆዳ ስፋቷ ትንሽ የሆነችው የኩባ ሶሻሊስት ሪፐብሊክ በጦርነቱ ሂደት በቀጥታ ከተሳተፉት ሁለት ሀገራት አንዷ ናት በወቅቱ ኩባ ያስመጣቸው የተዋጊ ብዛት ከ እስከ ይገመታል ከዚህ ሀይል መካከል ሁለቱ ሜካናይዝ ብርጌድ ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የኩባ ጦር የሚመራው የሀሪቱ ምየመከላከያ ሚኒስትር በነበሩት በጄኔራል አርናልዶ ኦቾዋ ሲሆን በዘመኑ በአንጎላ ተመድቦ የነበረውንም የኩባ የጦር ሀይል የሚያዙት እርሳቸው ናቸው ሐ ደቡብ የመን ደቡብ የመን ለጦርነቱ የመደበቸው መድፈኞችን ነው አነዚያ መድፈኛ የመኒዎች በቁጥራቸው አነስተኛ ቢሆኑም አልሞተኳሽ መሆናቸው በብዙዎች ዘንድ ተደንቆላቸዋል ድድድቱቴቴ ሶስቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የሶማሊያ አጋር ነበሩ ሶማሊያ የመሬት ጥያቄዋን ባነሳቸበት ጊዜም ሀሳቧን እንድትቀይር ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል ከዚህም አልፎ ፕሬዚዳንት ካስትሮ ማሊያ ኢትዮጵያና ደቡብ የመን በኮንፌዴሬሽን ተያይዘው አንድ ታላቅ ህብረት መመስረት አለባቸው የሚል ሃሳብ እስከ ማቀንቀን ደርሰዋል የሶማሊያ ወረራ ገፍቶ ሲመጣ ግን ከኢትዮጵያ ጋር ተሰልፈዋል ድድድቱቴቴ ባለፈው ከፍል አንደገለጽኩት ሌሎች የሶሻሊስት ሀገራት በጦርነቱ ሂደት በቀጥታ ባይሳተፉም ለኢትዮጵያ የመሳሪያ ድጋፍ አበርከተዋል ሶማሊያ በግልጽ ሶሻሊዝምን ወርውራ ወደ ምዕራቡ ዓለም መጓዝ የጀመረችው በዚያን ጊዜ ነው ይሁን እንጂ ቀደም ብሎም ቢሆን ከምዕራባዊያን ጋር ድብቅ ግንኙነቶችን ማድረግ እንደ ጀመረች አንዳንድ ምንጮች ያወሳሉ ለምሳሌ ከአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ጋር ቁርኝት ካለው አንድ ተቋም የተገኘ ጥናታዊ ጽሑፍ አሜሪካ ብሪታኒያ አና ፈረንሳይ ለሶማሲያ የጦር መሳሪያዎችን ለመሸጥ በድብቅ የተስማሙት ወረራው በተጀመረበት የሀምሌ ወር በ መሆኑን ይገልጻል ከዐረብ ሊግ ሀገራት መካከል ግብጽና ሳዑዲ ዐረቢያ በድብቅ ሶማሊያን ይረዷት ነበር ሊቢያ ግን የኢትዮጵያ ደጋፊ ነበረች ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል ስድስት የኢትዮጵያ ህዝብ በሶማሊያ ወረራ ላይ የነበረው አቋም ሶማሊያ ኢትዮጵያን የወረረችበት ወቅት ኢጣሊያ በኢትዮጵያ ላይ ወረራ ፈጽማ በአድዋ ላይ ድል ከተመታትበት ዘመን በአጅጉ ይለያል ኤርትራ በ ባድመን ከወረረችበት ወቅትም በጣም ይለያል በሁለቱ ወቅቶች ማዕከላዊውን መንግሥት ገትሮ ያስጨነቀ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሀገሪቱ ውስጥ አልነበረም በ ግን ደርግ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ነበር ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ከኢህአፓ ጋር በከረረ የከተማ ውጊያ ውስጥ ገብቶ ነበር ቀይ ሽብርም የታወጀው በዚያን ጊዜ ነው ጀብሃና ሻዕቢያ አስመራን በ ኪሎሜትር ራዲየስ ከበው ከዛሬ ነገ እንገባለን እያሉ በመጠባበቅ ላይ ነበሩ ኢዲዩ የሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የጠረፍ ከተሞችን ይዚዘል ህወሐት ኦነግ የአፋር ነጻ አውጪ ግንባር አና ሌሎችም በደርግ ላይ ብረት አንስተዋል ደርግ ያንን ውጥረት ሁሉ ተቋቁሞ የሶማሊያን ወረራ መመለስ ነበረበት አንደተመኘውም ሶማሊያን ለማባረር ችሏል በቀጣዩ ጽሑፍ እናየዋለን ታዲያ ደርግ ሶማሊያን ያባረረበትን ጉልበት ከየት አገኘ። አንድ ማንም የማያስተባብለው ሐቅ አለ ጦርነቱ የተከሰተው ሶማሊያ ኦጋዴን በመውረሯ ነው በመሆኑም በዘመኑ የነበረው ኢትዮጵያ መንግሥት ወረራውን ለመቀልበስ ያደረገው ትግል በማንኛውም መመዘኛ ቢታይ ፍትሐዊነቱ አያጠያይቅም ደርግ ጨፍጫፊ ስለነበረ ብቻ ህዝቡ ከርሱ ጋር ሆኖ ሀገሩን ከወረራ እንዳይከላከል ጥሪ ማድረግ በምንም መልኩ አይሞገስም ነገር ግን ይህንን አደረገ የተባለው በደርግ መንግሥት የጭካኔ ብትር በከፍተኛ ደረጃ የተመታው ኢህአፓ ነው በመሆኑም የኢህአፓ እርምጃ በደርግ የደረሰበትን ፍጅት ለመበቀል በሚል የተፈጠረ ነው ሊባል ይትላል ድድድቱቴቴ በዚያ ዘመን አነስተኛ ሀይል የነበራቸው ህወሐትና ኦነግ በሶማሊያ ወረራ ላይ የወሰዱትን አቋም በማስረጃ አስረግጦ መተንተን አስቸጋሪ ነው ይሁንና ድርጅቶቹ በጦርነቱ ወቅት ከሶማሊያ መንግሥት ጥቅሻ ያላገኙ መሆናቸው ይታወቃል የዚያድ ባሬ መንግሥት ሁለቱን ድርጅቶች ወደ ሞቃዲሾ የጠራው ጦርነቱ ካበቃ በኋላ ነው ጀብሃና ሻዕቢያ ደግሞ ወረራውን ደግፈዋል የኢትዮጵያ የመልሶ ማጥቃት ቅድመዝግጅት ከህዳር የካቲት የሶማሊያ ሰራዊት ሀረርን ለመቆጣጠር ያደረገው ጥረት ከከፈሸበት በኋላ ይዞታውን ለማስፋት አልሞከረም ሶቪየት ህብረት ኩባ እና የመን ኢትዮጵያን በመደገፍ በጦርነቱ ውስጥ መግባታቸውን ሲረዳ በያዛቸው አካባቢዎች መከላከያውን ማጠናከሩን ነው የመረጠው ኢትዮጵያ በበኩሏ የመልሶ ማጥቃት ዝግጅቷን አጧጧፈችው ሶቪየት ህብረት በቃሏ መሰረት ሚግ ተዋጊ ጄቶችን ለኢትዮጵያ ሰጠች ታንኮች ከ በላይ ብረት ለበሶች ያህል መድፎች የቢኤም ሮኬት ማስወንጨፊያዎች ዙ የአየር መቃወሚያዎች ቀላልና ከባድ መትረየሶች ቦምቦች ሮኬቶች ወዘተ ወደ ኢትዮጵያ መጡ ዘመናዊ የሆኑ ሶቪየት ሰራሽ ዋዝ ጂፖች ሽፍን ወታደራዊ መኪናዎችቸ ራል አይፋ እና ማዝ የሚባሉ ከባድ መኪናዎች ለኢትዮጵያ ተሰጡ የአውሮፕላንና የሂሊኮፕተር አብራሪዎች ወታደራዊ መኮንኖችና የውጊያ አሰልጣኞች የፈንጂ መሐንዲሶች ወዘተ በአስቸኳይ ወደ ሶቪየት ህብረት እየተላኩ ተጨማሪ ስልጠና እንዲወስዱ ተደረገ በሀገር ውስጥ ደግሞ ቀደም ብለው የተጀመሩት የፓራ ኮማንዶ የአየር ወለድ የባህር ወለድ የከባድ መሳሪያ ተኳሾች የበታች አዛኙች የመደበኛ ተዋጊዎች አና የሚሊሻ ስልጠናዎች ተጠናከረው ቀጠሉ የያኔውን ታሪከ በትከከል ለማወቅ እንዲቻለን የኢትዮጵያ መንግሥት ስልጠና ያካሄደባቸውን ማዕከላት ዝርዝር ማሳወቅ ያለብኝ ይመስለኛል ታጠቅ የጦር ሰፈር በሸዋ ከፍለ ሀገር ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ ኪሜ የሚገኝ ሲሆን ኢትዮጵያ በታሪኳ የገነባቸው ትልቁ የጦር ማሰልጠኛ ማዕከል ነው በኢትዮሶማሊያ ጦርነት ወቅት በታጠቅ ይሰለጥኑ የነበሩት ሚሊሻዎች ናቸው ይህ ማዕከል በአንድ ጊዜ መቶ ሺህ ሰልጣኞችን ለመቀበል ይችላል ኩሃ የጦር ሰፈር በትግራይ ከፍለ ሀገር የሚገኝ የጦር ማሰልጠኛ ነው በዚህ ማዕከል የሰጠለኑት የመደበኛ ጦር ተዋጊዎች ናቸው ዘዞ ጦር ሰፈር በጎንደር ክፍለ ሀገር ነው የሚገኘው በዚህኛውም ማዕከል የሰለጠኑት መደበኛ ተዋጊዎች ናቸው ለምለም ጦር ሰፈር ለምለም ግቢ በሸዋ ከፍለ ሀገር ደብረ ዘይት ከተማ የሚገኝ የጦር ማሰልጠኛ ነው በዚህ ማዕከል የሰለጠኑት መደበኛ ተዋጊዎችና የአየር ወለዶች ናቸው ዝዋይ ጦር ሰፈር በሸዋ ከፍለ ሀገር ነው የሚገኘው በዚህ ማዕከል የሰለጠኑት ፓራኮማንዶዎች ናቸው አዋሳ የጦር ሰፈር በሲዳሞ ከፍለ ሀገር ነው አዋሳ ሀይቅ ዳር ነው የሚገኘው በዚህኛውም የጦር ሰፈር የሰለጠኑት የፓራኮማንዶ ተዋጊዎች ናቸው ለገዳዲ የጦር ማሰልጠኛ ከአዲስ አበባ በሰሜን አቅጣጫ ላይ ነው የሚገኘው በዚህኛውም ማዕከል የሰለጠኑት ፓራኮማንዶዎች ነበሩ አዋሸ አርባ የጦር ትምህርት ቤት በሸዋ እና በሀረርጌ ድንበር አቅራቢያ ከአዋሽ ሰባት ኪሎ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው በዚህ ማዕከል የሰለጠኑት በአብዛኛው የታንከ የመድፍና የሌሎች ከባድ መሳሪያ ተኳሾች ሲሆኑ አንድ የፓራኮማንዶ ብርጌድም በማዕከሉ ሰልጥኗል የተዋጊ የመኮንንና የከባድ መሳሪያ ተኳሾች ስልጠና በተጧጧፈበት ወቅት የጦር መሳሪያዎቹ ወደ ኢትዮጵያ በመጓጓዝ ላይ ነበሩ ታዲያ ከባድ መሳሪያዎቹ በታቀደላቸው ለመልሶ ማጥቃት ዘመቻው መዋላቸውን ለማረጋገጥ የኢትዮጵያ መሪዎች የታንከኛና የመድፈኛ ተኳሾችን ስልጠና ከአዋሽ አርባ ወደ አሰብ ለማወዛር ተገደዋል ይህም የተደረገው በጉዞ የሚባከነውን ጊዜ ለመቆጠብ እንዲቻል ተብሎ ነው ታንኮቹን ከአሰብ ወደ ምስራቅ ግንባር በማጓጓዙ ሂደት የኩባ ጓዶች ተሳታፊ ነበሩ ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል ሰባት የኢትዮጵያ የፕሮፓጋንዳና የዲፕሎማሲ ስራዎች ኢትዮጵያ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ለመከፈት ያቀደችው በየካቲት ወር ሁለተኛው አጋማሽ ነበር ከዚያ በፊት በሁሉም የእርከን የሚሰሩ ተግባራትን ማከናወን ነበረባት ከነዚህ ተግባራት መካከል አንዱ ቅስቀሳ እና ፕሮፓጋንዳ ነው ይህም በሶስት ዘርፎች የተከፈለ ነው በኢትዮጵያ ህዝብና ሰራዊት ላይ ያነጣጠረ ቅስቀሳ አና ፕሮፓጋንዳ ዓላማው የኢትዮጵያ ህዝብ የመጨረሻው ድል እስኪገኝ ድረስ ለዘመቻው ደጀን ሆኖ አንዲቀጥል ማድረግ ነው የፕሮፓጋንዳ ስራው በዋናነት የሚካሄደው በመገናኛ ብዙሃንና በጋዜጦች ነውጉ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና የኢትዮጵያ ሬድዮ በፕሮፓጋንዳው ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው ሲሆን የአዲስ ዘመንና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦችም ለጦርነቱ ሙሉ ሽፋን አንዲሰጡት ተደርገዋል ከዚህ ሌላ ለሰራዊቱ አባላት የሚሰራጭ ታጠቅ የተሰኘ ጋዜጣ በወረራው ማግስት ተፈጥሯል የኢትዮጵያ አርቲስቶችና ደራሲያን በቅስቀሳው ዘርፍ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል ስለሀገር አና ስለ ዳር ድንበር የሚያወሱ ዘፈኖች ድራማዎችና ጭውውቶች እየተዘጋጁ ለህዝቡና ለሰራዊቱ እንዲቀርቡ ተደርገዋል በየቀበሌውም የቲያትርና የድራማ ቡድኖች ተቋቁመው ህዝቡን ይቀሰቀሱት ነበር የመልሶ ማጥቃት ውጊያ ሲጀመር ደግሞ የኢትዮጵያ ሬድዮ የጦርነቱን ውሎ በቀጥታ ይዘግብ ነበር በዚያ ዘመን ለቅስቀሳ ስራ በስፋት ያገለገለው ዋነኛ መፈከር አብዮታዊት እናት ሀገር ወይም ሞት የሚለው ነው በሶማሊያ ህዝብና ሰራዊት ላይ ያነጣጠረ ፕሮፓጋንዳ ዓላማው የሶማሊያን ህዝብ ከዚያድ ባሬ አመራር መነጠልና በሶማሊያ ሰራዊት ላይ ስነልቦናዊ ሽብር መፍጠር ነው በዚህም መሰረት ሀረር እና አዲስ አበባ ያሉት የኢትዮጵያ ሬድዮ ቅርንጫፎች በሶማሊኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የዚያድ ባሬን መንግሥት ነውር እአና ውስጣዊ ገመና የሚተረትሩ ተከታታይ ፕሮግራሞችን አንዲያስተላልፉ ተደርጓል በተጨማሪም ልዩ ሌላ በራሪ ጽሑፎች እየተዘጋጁ በአውሮፕላንና በተወንጫፊ ሮኬቶች አማካኝነት ለሶማሊያ ህዝብ እንዲበተኑ ተደርገዋል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ላይ ያነጣጠረ ፕሮፓጋንዳ ዓላማው የሶማሊያን መንግሥት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፊት ማዋረድና ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ድል ተጨማሪ ድጋፍ ማስገኘት ነው በዚህ መሰረት ለዓለም አቀፉ ህብረተሰብ መረጃ የሚሰጥ ራሱን የቻለ ጽቤት ተቋቁሟል የፕሬስ ሳምንት በተባለ ፕሮግራም አማካኝነትም የውጪ ጋዜጠኞች ኢትዮጵያን እየገበኙ ጦርነቱ ያደረሰውን ጥፋት እንዲመለከቱ ተደርጓል ድድድቱቴቴ በሌላ በኩል የዘመኑ የኢትዮጵያ መሪዎች በዓለም ዙሪያ ሰፊ የዲፕሎማሲ ስራ ሰርተዋል በውጤቱም የሶሻሊስቱ ካምፕ በየሶማሊያን ወረራ ሊያወግዝ በቅቷል የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትም የሶማሊያን ወረራ በማውገዝ ከኢትዮጵያ ጋር ቆሟል የምዕራብ ሀገራት ግን ሶማሊያ ወራሪ መሆኗን እያወቁ አንኳ ሊያወግዚት አልፈቀዱም ይህም የሆነው ሶቪየት ህብረት የኢትዮጵያ አጋር ሆና በመቆሟ ነው ከመከላከል ወደ ማጥቃት የካቲት ኢትዮጵያ የማጥቃት ዘመቻዋን የምትከፍትበት ወሳኝ ወቅት መምጣቱን የሀገሪቱ መሪዎች ተናገሩ በመሆኑም ስልጠናውን በብቃት ያጠናቀቀው ሰራዊት በሚከተለው ሁኔታ ተደራጀ በምስራቅ ግንባር አራት ታንከኛ ብርጌድ ሁለት መድፈኛ ብርጌድ ሁለት የከባድ መሳሪያ ቢኤም ተኳሽ ብርጌድ ሁለት መደበኛ ከፍለ ጦር አራት ህዝባዊ ሚሊሻ ከፍለ ጦር በደበብ ግንባር ሁለት ህዝባዊ ሚሊሻ ከፍለ ጦር አንድ መድፈኛ ሻለቃ እየር ሀይል የኢትዮጵያ አየር ሀይል በጠቅላላው ከታጠቃቸው አውሮፕላኖች መካከል የሚሆኑትን ለግዳጅ አሰልፏል የኢትዮጵያ ጦር ካሰለፈው ሀይል በተጨማሪ ቀደም ሲል የጠቀስኳቸው አንድ ከፍለ ጦር የሚሆን የኩባ ሰራዊትና አንድ የደቡብ የመን መድፈኛ ብርጌድም በምስራቁ ግንባር ተሰልፈዋል የኢትዮጵያ ሰራዊት ለረጅም ጊዜ ሲከላከል የቆየው በሁለት መደበኛ ከፍለ ጦሮች ሶስት ሚሊሻ ክፍለ ጦሮች ሁለት ሜካናይዝድ ብርጌድና ሁለት ነበልባል ብርጌድ ብቻ ነው ድድድቱቴቴ የኢትዮጵያ ሰራዊት የማጥቃት ዘመቻውን በሚከተለው ሁኔታ ለመፈጸም ነበር ያቀደው ሶስት ፓራኮማንዶ ብርጌዶችን ከጅጅጋ በስተሰሜን ባሉት የጭናከሰን አና የማርዳፓስ ገዥ መሬቶች ላይ በጃንጥላ ፓራሹት በማውረድ ድንገተኛ ጥቃት መከፈት ከአሰብ የተነሳ አንድ ታንከኛ ብርጌድና አንድ መድፈኛ ብርጌድ በጅበቲ ድንበር ጥግ እየተጓዘ አውበሬ ተፈሪ በር በምትባለው ከተማ አቅጣጫ ወደ ጅጅጋ እንዲመጣና ጥቃት እንዲከፍት ማድረግ በቆሬ ግንባር ያለው የኢትዮጵያ ጦር ወደ ፊትና ወደ ሰሜን እንዲነቃነቅ በማድረግ በጅጅጋና በጉርሱም አውራጃ ያለውን የሶማሊያ ሰራዊት እንዲከብብ ማድረግ በተመሳሳይ መንገድ ከአሰብ የተነሳ ሁለት ታንከኛ ብርጌድና አንድ መድፈኛ ብርጌድ በድሬ ዳዋ በስተምስራቅ በኩል እየተጓዘ ጀልዴሳ በተባለው ቦታ የተከማቸውን የሶማሊያ ሰራዊት እንዲያጠቃ ማድረግ የሶማሊያ ጦር ከላይ በተጠቀሰው መንገድ በተከፈበት ጥቃት ሲበረገግ በሀረር የሚገኝ አንድ ግብረ ሀይል ወደ ሰሜን ተጉዞ በኮምቦልቻና ኤጄርሰ ጎሮ የከተመውን የሶማሊያ ሰራዊት እንዲያጠቃ ማድረግ በሀረር ያለ ሌላ ግብረ ሀይል ወደ ደቡብ ተነቃንቆ ሀኪም ጋራ እና አቦከር አቅራቢያ የከተመውን የሶማሊያ ሰራዊት ካጠቃ በኋላ እግር በእግር እየተከተለው በፈዲስ ወረዳ በኩል ወደ ፊቅ አቅጣጫ እንዲጓዝ ብሎም ወደ ኦጋዴን አንዲገሰግስ ማድረግ በባሌ እና ነጌሌ ቦረና የተመደቡት ሁለት ሚሊሻ ከፍለ ጦሮች ከአየር ሀይል ጋር በመሆን በደቡብ አቅጣጫ እንዲያጠቁ ኮሎኔል መንግሥቱ እንደሚሉት ኢትዮጵያ ይህንን የውጊያ እቅድ ያወጣቸው የሶቪየትና የኩባ አማካሪዎች ከመምጣታቸውና ኢትዮጵያ ከሶቪየት ያኘችውን የመሳሪያ ድጋፍ ከመረከቧ በፊት ነበር በዚያ ዕቅድ መሰረት የታንከና የመድፍ ተኳሾች በአሰብ ላይ ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ታንካቸውን ይዘው ወደ ጦርነቱ ቦታ አንዲሄዱ ነበር የተፈለገው የውጊያው የመጨረሻ ፕላን ላይ ውይይት በሚደረግበት ወቅት የሶቪየት አማካሪዎች ዕቅዱ ሶማሊያን ለመውረር የተዘጋጀ ይመስላል በማለታቸው ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ውጥን ለመከለስ ተገዳለች ሶቪየቶች ይህንን አንዲሉ ያደረጋቸው ኢትዮጵያ ካደራጀችቸው ሜካናይዝድ ጦር ውስጥ ሰባ አምስት በመቶ የሚሆነው ለሰሜን ሶማሊያ ቅርብ በሆነቸው የጅጅጋ መስመር እንዲሰለፍ በመደረጉ ይመስላል ሀርጌሳ ከጅጅጋ በቅርብ ርቀት ላይ ያለች መሆኗን ልብ በሉ የሶቪየት ህብረት እና የኩባ አጋሮች ከሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ጋር ብዙ ከተወያዩ በኋላ የኢትዮጵያ ጦር በሚከተለው አኳኋን እንዲያጠቃ ተወሰነ የፓራኮማንዶ ጦር በአውሮፕላን ተጓጉዞ ከጅጅጋ ጀርባ ባለችው የጭናከሰን ቀበሌ ላይ እንዲከማችና ውጊያውን ከዚያ እንዲጀምር በቆሬ ግንባር ያለው ጦር በሜካናይዝድ ተጠናክሮ ውጊያውን አንዲጀምር የኩባ ሜካናይዝድ ጦር እና የየመን መድፈኛ ብርጌድ ከኢትዮጵያ ሜካናይዝድ ጦር ጋር በመቀናጀት በጀልዴሳ አካባቢ ያለውን የሶማሊያ ሰራዊት እንዲያጠቁ ግዳጃቸውን ከጨረሱ በኋላም ወደ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በማምራት በስፍራው ያሉ የኢትዮጵያ ከተሞችን ነጻ እንዲያወጡ ከሀረር የተነሳው ጦር በኮምቦልቻ እና በፈዲስ አቅጣጫዎች ማጥቃት እንዲጀምር ከዚያም ፊቅን ይዞ ወደ ኦጋዴን እንዲዘምት በባሌና በነጌሌ ቦረና አቅጣጫዎች የተመደቡ ሚሊሻ ከፍለጦሮች በተመሳሳይ ቀን ማጥቃት እንዲጀምሩ የኢትዮጵያ አየር ሀይል በሁሉም አቅጣጫዎች የተጠናከረ ድብደባ እንዲፈጽም ድድድቱቴቴ የካቲት የኢትዮጵያ ጦር በጭናከሰን እና በቆሬ በኩል በጅጅጋ ላይ የተጠናከረ ጥቃት ከፈተ የሶማሊያ ጦር ጥቃት ይመጣብኛል ብሎ ባልጠበቀው አቅጣጫ በመወጋቱ ተደናገጠ ጅጅጋን ላለመልቀቅ መሟሟት ጀመረ ሶማሊዎች በዚህ ውዥንብር ውስጥ እያሉ በጀልዴሳ ግንባር ሌላ ጥቃት ገጠማቸው የኢትዮጵያ አየር ሀይልም እስከ ሶማሊያ ድንበር እየገባ የአቅርቦት መስመሮችን በመደብደብ ከጥቅም ውጪ አደረጋቸው የሶማሊያ ሰራዊት ጅጅጋን ከለቀቀ ትልቅ የሞራል ውድቀት እንደሚገጥመው ያውቃል በመሆኑም ከጅጅጋ በስተምዕራብ ከዘህር ባለው የካራ ማራ ተራራ ላይ ማዘዣውን በመስራት በከፍተኛ ደረጃ ተከላከሏል ሆኖም በለስ አልቀናውም ጥቃቱ በሁሉም ግንባር የተከፈተ በመሆኑ አጋዥ ሰራዊት ማንቀሳቀስ አልቻለም በመሆኑም የካቲት በካራ ማራ ተራራ ከባድ ሽንፈት ገጠመው ጅጅጋን ለኢትዮጵያ ሰራዊት በመልቀቅ ወደ ሀርጌሳ መስመር አፈገፈገ የኢትዮጵያ ሰራዊትም የካቲት ንጋት ላይ ጅጅጋን ያበዘ የኢትዮኩባየመን ጥምር ጦር በጀልዴሳ የተከማቸውን የሶማሊያ ሰራዊት ለሶስት ተከታታይ ቀናት ወጋ ይህ ውጊያ ታንከ ከታንከ ጋር የተፋጨበት በመሆኑ በርካታ የጦር መሪዎች የጦርነት ፊልም ይመስል ነበር እያሉ አድናቆታቸውን ሰጥተውታል የሶስቱ ሀገራት ጥምር ጦር ከሶስት ቀን በኋላ ግዳጁን በማጠናቀቅ በቆላው ምድር ላይ ገሰገሰ የካቲት ግዳጁን በማጠናቀቅ ከኢትዮጅቡቲ የባቡር መስመር በስተደቡብ ያሉ ከተሞችን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ ከሀረር የተንቀሳቀሰው ጦር ደግሞ በሰሜን በኩል ግዳጁን በቀላሉ በመወጣት ኮምቦልቻን አልፎ እስከ ኤጀርሳ ጎሮ ድረስ ገስግሷል ከሀረር በስተደቡብ የተነቃነቀው ግብረ ሀይል ግን ከሶማሊዎች ከፍተኛ የሆነ መከላከል ገጥሞታል የኢትዮጵያ ጦር የካቲት ፈዲስን የተቆጣጠረው ከባድ መስዋዕትነት ከከፈለ በኋላ ነው በባሌ እና በነጌሌ ቦረና ግንባር የተሰለፈው ጦር ግን ጠንካራ መከላከል ሳያጋጥመው እስከ ጠረፍ ድረስ ለመቆጣጠር ችሏል የኢትዮጵያ ጦር ባገኘው ድል ተብቃቅቶ አልቆመም ከመጋቢት ጀምሮ ሁሉም ሀይሎች ወደ ኦጋዴን አቅጣጫ ዘምተዋል ሆኖም የሶማሊያ ሰራዊት በከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ገብቶ ስለነበር ጠንካራ ጦርነት ይደረግበታል ተብሎ በታሰበው የኦጋዴን መሬት ላይ የሚረባ ውጊያ ለማድረግ አልተቻለውም በመሆኑም የኢትዮጵያ ጦር መጋቢት ፊቅን መጋቢት ደጋሀቡርን መጋቢት ቆራሄን ሰገግንና ቀብሪ ደሃርን መጋቢት ወልወልንና ዋርዴርን መጋቢት ጎዴን ያለ ምንም ውጊያ ተቆጣጥሯል ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ዝ ተጻፈ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል ስምንት የጦርነቱ ውጤት የኢትዮሶማሊያ ጦርነት በስምንት ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ የበላይነት ተጠናቋል የሶማሊያ መንግሥት ከመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ ሰራዊቱን ከኢትዮጵያ ምድር አስወጥቷል ሶማሊዎች ኦጋዴንን ስልታዊ ማፈግፈግ የለቀቁ መሆናቸውን ገልጸው ነበር ነገር ግን ከያኔው ዘመቻ ወዲህ ኦጋዴንን በከፍተኛ ሀይል ለመውረር አልሞከሩም ከ ባለው ጊዜ የምሶነግ የምዕራብ ሶማሊ ነጻ አውጪ ግንባር ከሶማሊያ ምድር እየተነሳ የደፈጣ ጥቃቶችን ለማድረግ ቢሞክርም እንኳ የኢትዮጵያ ጦር በአነስተኛ ሀይል ያባርረው ነበር በጦርነቱ የደረሰው ጉዳት በልዩ ልዩ ወገኖች በተለያየ መንገድ ተገልዷል ለምሳሌ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም የጦርነቱን ጉዳት በሚከተለው ሁኔታ ጽፈውታል የሞተየሶማሊያ የኢትዮጵያ የቆሰለ የሶማሊያ የኢትዮጵያ የተማረከ የሶማሊያ የኢትዮጵያ ዊኪፒዲያ የተሰኘው የኢንተርኔት ኢንሳይከሎፒዲያ ደግሞ ጉዳቱን እንደሚከተለው ያስቀምጠዋል የሞተየሶማሊያ የኢትዮጵያ የቆሰለ የሶማሊያ የኢትዮጵያ የተማረከ የሶማሊያ የኢትዮጵያ ከዊኪፒዲያ የተገኘው መረጃ አንድ ተቃርኖ አለው ይኸውም ግኛ የሚሆን የሶማሊያ ሰራዊት ከጥቅም ውጪ ሆነ እያለ በሶማሊዎች ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን አሳንሶ የሚያቀርብ መሆኑ ነው በመሆኑም በጦርነቱ በሶማሊያ ሰራዊት ላይ የደረሰው ጉዳት በሁለቱ ምንጮች ከቀረበው የሜበልጥ እንደሆነ እሙን ነው ሁለቱ ሀገራት ለጦርነቱ ካሰለፏቸው ከባድ መሳሪያዎች መካከል ብዙዎችን አጥተዋል በዚህ ረገድ በሶማሊያ ጦር ላይ የደረሰው ጉዳት ከበድ ይላል ሶማሊያ ለጦርነቱ ካሰለፈቻቸው ታንኮች መካከል የሚሆኑትን አጥታለች ኢትዮጵያም ታንከ ተደምስሶባታል የኢትዮጵያ አየር ሀይል ያህል አውሮፕላኖች ወድመውበታል ሶማሊያ ግን ጢያራዎችን አጥታለች የሚገርመው ነገር የኢትዮጵያ የአየር ሀይል ብዙ አውሮፕላኖችን የደመሰሰው በአየር በአየር ውጊያ ነው ጦርነቱ በሲቪሉ ህብረተሰብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ነው ያደረሰው ለምሳሌ የሶማሊያ ጦር በፈጸመው ጥቃት ቆሬ የምትባለውን አነስተኛ ከተማ ከሀረር በ ኪሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ሙሉ በሙሉ አውድሟል የጅጅጋ ከተማን በሚለቅበት ጊዜም ከፍተኛ ፍጅትና ዘርፋ ፈጽሟል የከተማዋ ህንጻዎች ሆን ተብለው ተደምስሰዋል በሌላ በኩል የሶማሊያ አየር ሀይል በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ በኦጋዴን ከልል ባሉት የደጋሃቡር እና አዋሬ ከተሞች ላይ በፈጸመው ድብደባ በርካታ ሰላማዊ ዜጎችን ገድሷል በስምንቱ ወራት ውስጥ ከከ ያላነሱ ኢትዮጵያዊያን በሶማሊያ ጦር ተግዘው ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ለአስራ አንድ ዓመታት ታስረዋል የሶማሊያ ጦር በተለይም የሶማሊ ብሄረሰብ አባላት ባልሆኑት ላይ የሚያደርሰው ግፍ እጅግ የበረታ እንደነበረ ከልዩ ልዩ ምንጮ የተገኙ ሰነዶች ያረጋግጣሉ በሶማሊያ ጦር እጅ የወደቁ ምርኮኞችም ዓለም አቀፍ ድንጋጌን በጣሰ ሁኔታ ይሰቃዩ እንደነበረ ተረጋግጧል የኢትዮጵያ ጦርም ኦጋዴንን መልሶ ከያዘ በኋላ የሶማሊያን ሰራዊት ደግፈዋል ባላቸው ላይ የግድያና የዘረፋ እርምጃ መውሰዱ ይነገራል እንዲህ ዓይነቱ ጥቃት የደረሰው በፊቅ ጎዴ ደጋሃቡርና ቀብሪ ደሃር አካባቢዎች ነው አንዳንድ የጦር መሪዎች ደግሞ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ሶማሊዎችን ከሶማሊያ ጦር ባለመለየት ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ውርጅብኝ ሲያካሄዱባቸው ነበር ይባላል በዚህም የተነሳ ከአንድ ሚሊዮን ያላነሱ ኢትዮጵያዊ ሶማሊዎች ሀገር ጥለው ተሰደዋል ይሁንና የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ድንበር ገብቶ ሲቪሎችን ምርኮኛ አላደረገም በተጨማሪም በኢትዮጵያ እጅ የወደቁ የጦር ምርኮኞች ሰብዓዊ ክብራቸውን በማይነካ መልኩ ነው የተያዙት የሶማሊያ ጦር ከኦጋዴን ሲወጣ በአካባቢው የተሰሩ የመሰረተ ልማት አውታሮችን አውድሟል ይህ የውድመት እጣ ከደረሳቸው ግንባታዎች መካከል በዘመኑ ከአዲስ አበባው የቦሌ አየር ማረፊያ ቀጥሎ ሁለተኛ ደረጃ የነበረው የጎዴ አየር ማረፊያ አና ባሌና ሀረርጌን የሚያገናኘው ትልቁ የዋቢ ሸበሌ ድልድይ ይጠቀሳሉ የኢትዮጵያ ጦር የመልሶ ማጥቃት ውጊያውን በከፍተኛ ፍጥነት ያገባደደ በመሆኑ አካሄዱ የሶማሊያ መሪዎችን በጣም አስፈርቶአቸው ነበር በመሆኑም ፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬ ኢትዮጵያ ሀገራችንን ልትወርር ስለሆነ አያንዳንዱ ዜጋ ለውጊያው ይሰለፍ የሚል አዋጅ አስነግረዋል ከኢትዮጵያ ጋር የተባበሩት የሶቪየት አማካሪዎችም ሶማሊያን ልትወርሩ ነው አንዴ አያሉ መጨቅጨቅ ጀምረው ነበር ይሁንና የኢትዮጵያ ጦር አጋዴንን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠረ በኋላ በድንበሩ ላይ ቆሟል ጦርነቱ በሁለቱ ሀገራት ጂኦፖለቲካ ላይ ያስከተለው ለውጥ የኢትዮሶማሊያ ጦር በአካባቢው ጂኦፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ነው ያስከተለው በጦርነቱ ያሸነፈችው ኢትዮጵያ የአካባቢው ልዕለሀያልና ባለተጽእኖ ሀገር ሆና ወጥታለች የኢትዮጵያ ጦር ሀይልም በፊት ከፍተኛ እድገት በማሳየት ከአፍሪቃ ታላላቅ ሰራዊቶች አንዱ ሊሆን በቅቷል በተጨማሪም በሶማሊያ ላይ በተገኘው ድል የተነቃቃው የኢትዮጵያ ሰራዊት በምስራቅ የተገኘው ድል በሰሜንም ይደገማል የሚል መፈከር በማንገብ ወደ ኤርትራ ከዘመተ በኋላ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጀብሃና ሻዕቢያን ከደጋማው ምድር በማባረር ወደ ሳህል በረሃ ናቅፋ መልሶአቸዋል ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ድሮ የሶቪየት ህብረት ወዳጅ የነበረችው ሶማሊያ ከጦርነቱ በኋላ ጭልጥ ብላ ወደ ምዕራባዊያን ጉያ ገብታለች ከሶቪየት ህብረት ጋር የማኑጣጣመው ቻይናም ከጦርነቱ በኋላ ዋነኛዋ የሶማሊያ መሳሪያ አቅራቢ ሆና ብቅ ብላለች በሌላ በኩል በጦርነቱ ሂደት ገለልተኛ ሆነው የቆዩት ጅቡቲና ሱዳን ከጦርነቱ በኋላ የሶማሊያ ደጋፊ ሆነዋል ከትልቁ ጦርነት በኋላ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችን ማስታጠቁን ቀጥላለች በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ለተነሱ ሀይሎች ሁሉ የዲፕሎማሲና የማቴሪያል ድጋፍ ታደርግም ነበር በመሆኑም በዚያ ወቅት የነበሩት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች ጀብሃ ሻዕቢያ ኢህአፓ ህወሐት አነግ አነእግ ሲአን ወዘተ አመራሮች በሶማሊያ ፓስፖርት ነበር የሚጠቀሙት በተጨማሪም እያንዳንዱ ድርጅት በሞቃዲሾኮና በሀርጌሳ ጽቤቶች ነበሩት በሌላ በኩል በጦርነቱ ሽንፈትን የቀመሱት ፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬ የመሬት ይገባኛል ጥያቄአቸውን ለመከለስ ተገደዋል ድሮ እስከ አዋሽ ድረስ የኛ ነው በማለት እንዳልሞገቱት ሁሉ ከጦርነቱ በኋላ አቋማቸውን በማለሳለስ ኦጋዴን የኛ ነው የሚል ፖሊሲ ማራመድ ጀምረዋል በዚህም የተነሳ በትውልድ ሶማሊ ያልሆኑትን የኦሮሞና የሲዳማ ህዝቦችን ነጻ ያወጣል ተብሎ ለተቋቋመው የሶማሊ አቦ ነጻነት ግንባር ላ የሚሰጡትን ድጋፍ በማቋረጥ ለኦጋዴን ነጻነት ይታገላል የሚሉትን የምዕራብ ሶማሊ ነጻ አውጪ ግንባርን ቢነ ብቻ መደገፍ ጀምረዋል በውጤቱም ሶኢነግ ለቦ የተባለው ድርጅት ከ በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያደርገውን አንቅስቃሴ ለማቆም ተገዷል የሶማሊያ መንግሥት በጦርነቱ በመሸነፉ ውስጣዊ ቀውስና መፈካከስ አጋጥሞት ነበር በጦርነቱ አካሄድ ላይ ልዩነት የነበራቸው ጄኔራል ፋራህ አይዲድ አና ኮሎኔል አብዱላሂ ዩሱፍ ከስልጣናቸው ተባረው ወደ እስር ቤት ተወርውረዋል እኒህ አውቅ የጦር መሪዎች ከአስር ቤት ከወጡ በኋላ ከሶማሊያ ጠፍተው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በአጭር ጊዜ ውስጥ የተቃውሞ ድርጅት ለማቋቋም በቅተዋል የዚያድ ባሬን መንግሥት ለስድስት ዓመታት ከወጉት በኋላም በ ከስልጣን አስወግደውታል ድድድቱቴቴ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም ሶማሊያን ማሸነፋቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ህዝብ የድሉን ብስራት በድምቀት እንዲያከብር አዋጅ አስነገሩ በተለይም የኢትዮጵያ ጦር ስትራቴጂካዊውን የካራማራ ተራራን የተቆጣጠረበት ውጊያ የድሉን ቁልፍ ያስጨበጠ በመሆኑ በብሄራዊ ደረጃ መዘከር እንዳለበት ተነገረ በመሆኑም መላው ኢትዮጵያ ህዝብ የካራማራውን ድል በቅድሚያ በአውራጃ ደረጃ በተቋቋሙ ኮሚቴዎች አማካኝነት በየአካባቢው አከበረ በማስከተልም ድሉ በጅጅጋ ከተማ በብሄራዊ ደረጃ በተዘጋጀው ታሪካዊ ከብረበዓል ተከበረ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም ጦርነቱን በአጭር ጊዜ መፈጸማቸው ታላቅ ፖለቲካዊ ድል ነው ያስገኘላቸው ከጦርነቱ በፊት እርሳቸውን ይጋፉ የነበሩ ባልደረቦቻቸው ከጦርነቱ በኋላ ድምጻቸውን ሙሉ በሙሉ አጥፍተዋል ኢህአፓ የሚባለው ድርጅት ከድሉ በፊት ከጉያቸው ስር ሆኖ ሲያንጨንቃቸው እንዳልነበር ሁሉ ከድሉ በኋላ የት እንደገባ ሳይታወቅ ከአዲስ አበባ ከተማ ተሰውሯል ሺህ ምንተሺህ የሚሆኑት የፖለቲካ ካድሬዎች ቆራጡ መሪ አያሉ የሊቀመንበሩ ስም በሀገሪቱ እንዲናኝ አድርገዋል ሊቀመንበሩ ካዋቀሩት አብዮታዊ ሰደድ ጋር በደግም ሆነ በከፉ እየተጎሻሸሙ የፖለቲካ ስልጣን ለመቀራመት ያሰፈሰፉት ወዝሊግ እና ማሌሪድ የተሰኙ ድርጅቶችም ከድሉ በኋላ ቀስ እያሉ መከሰም ጀምረዋል ይሁን እንጂ አንደ ዚያድ ባሬ ሁሉ ሊቀመንበር መንግሥቱም ከስልጣን ከመባረር አልዳኑም እርሳቸው ከሊቢያው ሙአመር አልቀዛፊ ጋዳፊ ጋር ሆነው ዚያድን ለመፈንገል ሲታገሉ ካልጠበቁት አቅጣጫ በመጣ ሀይል ተወረሩ ትልቁን የሶማሊያ ወራሪ ሰራዊት በኦጋዴን በረሃ የመከቱት ጀግና ወንበዴ እያሉ በሚንቁት አነስተኛ ሀይል ተበልጠው ከስልጣን ተወገቶ ድድድቱቴቴ ኢትዮጵያና ሶማሲያ ከጦርነቱ በኋላም በጠላትነት መፈላለጋቸውን አላቆሙም በ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ባደረገው ጥረት የተኩስ ማቆሚያ ስምምነት ቢፈራረሙም እስከ ድረስ በእጅ አዙር ሲዋጉ ነው የሰነበቱት ሁለቱ መንግሥታት በጋራ የፈጸሙት መልካም ነገር ቢኖር በ የአስረኛ ልውውጥ ማድረጋቸው ብቻ ነው ያ ታሪካዊ ጦርነት ሙሉ ፍጻሜውን ያገኘው በጥር የዚያድ ባሬ መንግሥት ከስልጣን በተወገደበት ጊዜ ነው ይህንን የምለው ኢትዮጵያዊ ስለሆንኩ አይደለም ጦርነቱ ሲሰኮስ የነበረው የዚያድ ባሬ መንግሥት በዓለም አቀፍ መድረከ እውቅና የተሰጠውን የኢትዮጵያ ህጋዊ ድንበርን የማያከብር በመሆኑ ነው ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ከፍል ዘጠኝ የጦርነቱ መሐንዲሶች ይህ ታሪካዊውን የኢትዮሶማሊያ ጦርነት የምንቃኝበት የመጨረሻው ከፍል ነው በዚህ ከፍል በኢትዮጵያ ወገን ሆነው ጦርነቱን ሲመሩ ከነበሩት አዋጊዎችና የጦር ሜዳ ጀግኖች መካከል ከአንዳንዶቹ ጋር እንተዋወቃለን ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ሊቀመንበር መንግሥቱ የኢትዮጵያ ጦር የበላይ አዛዥ ነበሩ የጦርነቱን የዘመቻ አቅድ በመንደፍና ጦር በመምራት ሰራዊቱን ባያዋጉትም ለጦርነቱ የሚያስፈልገውን አመራር በመስጠት ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል በየሀገሩ እየዞሩ መሳሪያ በመለመንና የኢትዮጵያን ህዝብ በመቀስቀስ ረገድ የአንበሳ ድርሻ የነበራቸው በተጨማሪም ሶስት መቶ ሺህ ሚሊሻ ጦር በአጭር ጊዜ ውስጥ የሰለጠነበትን የታጠቅ ጦር ሰፈር የመሰረቱት እርሳቸው ናቸው ሊቀመንበር መንግሥቱ ተኩስ በሚደረግበት ትርዒት ውስጥ አልገቡም ነገር ግን የሶማሊያ ጦር የሀረርን ከተማ ከቦ ሲያስጨንቃት በነበረበት ጊዜ በከተማዋ መሀል ላይ ባለው የሀረር የጦር አካዳሚ የጦር መሪዎቻቸውንና የሶቪየት ጓዶቻቸውን በመሰብሰብ ስለውጊያው ይነጋገሩ ነበር ከዚህ እንደምንረዳው መንጌ ጭካኔ ቢኖርባቸውም ድፍረትም ነበራቸው በጣም የሚገርመው ደግሞ የኢትዮጵያ ጦር ጅጅጋን ከተቆጣጠረ በኋላ በማግስቱ ሊቀመንበር መንግሥቱ ከተማዋን መጎብኘታቸው ነው ፊልድ ማርሻል ቫሰሊ ፔትሮቭ ሶቪየት ህብረት ከነበሯት እውቅ የውጊያ ስትራቴጂስቶች አንዱ ነው የሶማሊያ ጦር ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የሶቪየት ምድር ጦር ምከትል አዛዥ ነበር በምዕራባዊያን የተጻፉ ሰነዶች ጄኔራል ፔትሮቭ ሶማሊያን ከኦጋዴን ያስወጣው ዘመቻ እቅድ ነዳፊ እና የሶስቱ ሀገራት ጥምር ጦር ኢትዮጵያ ኩባ እና ደቡብ የመን ዋና አዛዥ ነበር ይላሉ በደርግ በኩል ሆነው ታሪኩን የጻፉ ወገኖች ግን ማርሻል ፔትሮቭ አማካሪ ነው አንጂ የጥምር ጦሩ አዛዥ አልነበረም ነው የሚሉት የማርሻል ፔትሮቭ ኢትዮጵያ ሲመጣ ጄኔራል ነበር ወታደራዊ ችሎታ ብዙ ተደንቆለታል ነገር ግን ከኢትዮጵያ አዛዥች ጋር ተግባብቶ የመስራት ችሎታ አልነበረውም በተለይም ከአየር ሀይሉ አዛዥ ከኮሎኔል ፋንታ በላይ ጋር በከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ገብቶ ነበር የውዝግቡ መነሻ የኢትዮጵያ የጦር አውሮፕላኖች ሶማሊያ ድንበር ውስጥ ገብተው ጥቃት መፈጸማቸው ነውማርሻል ፔትሮቭ አውሮፕላኖቹ ሶማሊያ መግባታቸውን ይቃወማል ኮሎኔል ፋንታ ደግሞ መሬታችንን የያዘብንን ጠላት እስከ ሞቃዲሾ ድረስ ሄደን የመውጋት መብት አለን ባይ ነበር በዚህም የተነሳ ማርሻል ፔትሮቭ ከሱን ለሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም አሰማ መንጌም ፋንታ ያደረገው ትከከል ነው በማለት ፈረዱበት በዚህም አኩርፎአፋቸው ነበር ይባላል ማርሻል ፔትሮቭ ባለፈው የካቲት ወር ውስጥ በ ዓመቱ አርፏል ሌፍትናንት ጄኔራል አርላንዶ ኦቾዋ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የኩባ ጦር አዛዥ ነው ይህም ጄኔራል ግሩም የሆነ ወታደራዊ ችሎታ የነበረው ሲሆን ከኢትዮጵያ የጦር መኮንኖችም ጋር ተግባብቶ በመስራት ተደናቂነትን አትርፏል አርሱ ያዘመተው ጦር ለፈጸመው ጀብዱ መታሰቢያ ይሆነው ዘንድ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ደረጃ ኒሻን ተሸልሟል ጄኔራል ኦቾዋ ወደ አንጎላ የዘመተውንም የኩባ ጦር ይመራ ነበር ነገር ግን በአንጎላ ምድር በለስ ሊቀናው አልቻለም በደቡብ አንጎላ በተደረገ አንድ ውጊያ ብዙ የኩባ ወታደሮች ሲሞቱ ለውድቀቱ ተጠያቂው አንተ ነህ የሚል ወቀሳ ከፕሬዚዳንት ፊደል ካስትሮ ቀርቦበታል በዚሁ ጦስ ከስልጣኑ ወርዶ በቁም እስር ላይ እያለ በአደንዛዥ አጽ እና በህገወጥ የአልማዝ ንግድ ውስጥ እጁን ነከሯል የሚል ከስ ቀረበበት ከሱ በዝግ ችሎት ከታየ በኋላም የሞት ፍርድ ተፈረደበት ሀምሌ በጥይት ተደብድቦ ተገደለ ብጄኔራል ለገሠ ተፈራ የህብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ ጀግና የኢትዮጵያ አየር ሀይል ካፈራቸው ምርጥ አብራሪዎች አንዱ ነው በአየር በአየር ውጊያ ስድስት የሶማሊያ ሚግ ጄቶችን በማጋየት ጀብዱ የፈጸመ ተዋጊም ነው ሆኖም በመጨረሻው ዙር ባደረገው በረራ በሶማሊያ ድንበር ውስጥ ጥቃት አድርሶ ሲመለስ አውሮፕላኑ በመመታቱ ሊማረከ በቅቷል ሶማሊዎቹ ጄኔራል ለገሠን ለአስራ አንድ ዓመታት ካሰሩት በኋላ በ ለቀውታል ጄኔራሉ በእስር ቤት ሳለ ከፍተኛ ስቃይ ስለደረሰበት ከአስር ተፈትቶ ወደ አዲስ አበባ በመጣበት ጊዜ ሰውነቱ አልቆ ከሞት የተነሳ አጽም ይመስል ነበር ሊቀመንበር መንግሥቱ ጄኔራል ለሠን በልዩ ወታደራዊ ስነስርዓት ከተቀበሉት በኋላ የሀገሪቱ የመጨረሻ ደረጃ ኒሻን የሆነውን የህብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ ሸልመውታል ከጄኔራል ለገሰ ሌላ ይህንን ሜዳይ የተሸለሙት ሁለት ሰዎች ብቻ ናቸው አንደኛው ሊቀመንበር መንግሥቱ ራሳቸው ሲሆኑ ሁለተኛው ብጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማሪያም ናቸው ሌኮ ፋንታ በላይ የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዋና አዛዥ ሲሆን አየር ሀይሉ በሶማሊያ ባለጋራው ላይ የበላይነት አንዲቀዳጅ ያስቻለውን ወታደራዊ ስልት የነደፈ እውቅ መኮንን ነው በተለይም የኢትዮጵያ አየር ሀይል በሶማሊያ ድንበር ውስጥ እየገባ የሶማሊያ ሰራዊት የእአደላና የስምሪት መስመሮችን አንዲደበድብ የሚለውን ሃሳብ ያመነጨው እርሱ ነው በዚህም ከፍተኛ ውጤት አስገኝቷል ሌኮ ፋንታ በላይ በአየር ሀይል አዛዥነቱ እስከ አገልግሏል በማዕረጉም እስከ ሜጀር ጄኔራል ደረጃ ደርሷል በ ተሞክሮ የከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት ዋነኛ ጠንሳሽ እርሱ እንደነበረም ይነገራል መፈንቅለ መንግሥቱ ከከሸፈ ከሁለት ወር በኋላ ግን አስከ ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ በሆነ ሁኔታ ተገድሏል ሐታም አዲጋዖኖፏዖ ስጣር ሃያ ኮሎኔል ተስፋዬ ገብረኪዳን የኢትዮጵያ ታንከኛ ጦርን በማደራጀት ለውጊያው ያዘጋጀ መኮንን ነው ኮሎኔል ተስፋዬ ከጊዜ በኋላ በሌፍትናንት ጄኔራል ማዕረግ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር ሆኗል ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ሀገር ጥለው ከሄዱ በኋላም ለስድስት ቀናት የኢትዮጵያ መሪ ነበር ሌኮ ሙላቱ ነጋሽ በኋላ ሜጀር ጄኔራል ጄኔራል ሙላቱ በኢትዮሶማሊያ ጦርነት ወቅት በአዲስ መልክ የተቋቋመው የምስራቅ እዝ ዋና አዛዥ ነበር ሌኮ ተካልኝ ንጉሜ በድሬ ዳዋ እና በጀልዴሳ ግንባር የተሰፈለውን የኢትዮጵያ ጦር የመራ መኮንን ነው ኮሎኔል ተስፋዬ ሀብተማሪያም በኋላ ብጄኔራል በጭናከሰን ግንባር አስደናቂ ጥቃት በመፈጸም ለታላቁ የካራማራ ድል መንገድ የከፈተው የኢትዮጵያ የፓራኮማንዶ ሀይል አዛዥ አዛዥ ነበረ ሌኮ ደምሴ ቡልቶ በኋላ ሜጀር ጄኔራል በደቡብ ግንባር የዘመተው የኢትዮጵያ ሰራዊት አዛዥ ነበር ኮሎኔል ደምሴ በኢትዮጵያ ሰራዊት ውስጥ በነበረው ቆይታ እስከ ሜጀር ጄኔራል ማዕረግ ድረስ ለማደግ በቅቷል በዚህ ማዕረግ የምስራቅና የሰሜን አዞች አንደኛው አብዮታዊ ሰራዊትና ሁለተኛ አብዮታዊ ሰራዊት ዋና አዛዥ ሆኖ ካገለገለ በኋላ ግንቦት በተደረገው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ጦስ ተገድሏል ድድድቱቴቴ ሚያዚያ ተጻፈ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ላቭ ፐከዙህሄ ገዬሕየ ዐ ነጓቋፐ ቋጠባ ኋክጐበዩ ከ ከ ላክ ለክዝር ነላርከ ከ ክፎ ገዐዢ ኮርክካክርዮ ዩከቨዌ ፐልፐፎፎ ፐከዩ ከሀቨ ጓላጸዮ ዐ ቪጮባቪዩቧ ዐ ላክገርክ ር ክርቨር ኦኮ ዩከቨዌ ፐፐፎዩፎ ፐከዩ ከኮካ ከጩዐክ ነጓጡፐ በ ከዩ ፐክ ዐ ላክዝር አፍፎ ዝጠጡጓፎክ ፐ ኘር ከከፎፍፐቪነሃ ኮፎ ፒፀከከፎሂከ ርን ነፎ ከፎ ፍዐነገፎ ጠህዐፎዘጠፎከፒ ከ ሂከፎ ርንደኋበፎከ ነላቋኮ ርፎከሂፎፐ ክዣ ከ ላከከ ለላ ጓቫዌጠ ፐዩከህፐሃ ለላፎሬክከ ነላዐበፎእፌ«በ ክበ እ ኮከክርዘበ ከቨ እክር ዝአከዩከኗ ጀከዩፎ ፐከዩ ቪዐ ዐ ከ ፐክ ዐ ክዕቨቪከ ላክገርክ ር ነዐ እክዚከበኮከፎፐ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም ትግላችንየኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ የትግል ታሪከ ጸሐይ አሳታሚና አከፋፋይ ድርጅት ሎስ አንጀለስ ብጄኔራል ካሳዬ ጨመዳ የጦር ሜዳ ውሎዎች ከምስራቅ እስከ ሰሜን አዲስ አበባ ብጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማሪያም የጦር ሜዳ ውሎ አዲስ አበባ ዘነበ ፈለቀ በር አዲስ አበባ ገነት አየለ አንበሴ የሌኮ መንግሥቱ ኃይለማሪያም ትዝታዎች ሜጋ አሳታሚ ድርጅት።