Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የጥርጣሬዎቻችን መነሻው ምን ነበር። የማይመስል ወሬ ለሚስትህ ይላሉ አባቶቻችን በዚያው ጊዜ በነበረው አስተሳሰብ በእቁዱ መሠረት የተወሰነውን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ለመያዝ በመቻሉ ነው አንደዚህ የልብ ልብ ተሰምቶት እንደ እምቦሳ እየቦረቀብን የነበረውና ያለው ከላይ ለማሳየት እንደተቻለው ተስፍሻ እንደሆነ ገና ናይሮቢ ከመግባቱ ነው የኤርትራ ዜግነትና ፓስፖርት የተሰጠው ጊዜ ጊዜን ወልዶ ቀን ቀንን ተከቶ የውሸት ከር መዘዝ እስኪል ድረስ አንጂ እውነት አስከነካቴው እንደተሸሸገች እስከ ዘለዓለሙ አታሸልብም ተስፋዬ ግን ያየው የፊቱን በዚያ በዚህ በጋዜጠኛው ማስታወሻ ሰብሮ ገብቶ ምንም ለማለት ምንም ለማድረግ አንደሚችል ከተረዳ በኋላ ከየሰው ከቃረመው ተነስቶ በረቀቀ መንገድ ቀሪውን ሥራ እስከሚችለው ድረስ ለማድረስ በዚህ በደራሲው ማስታወሻ ላይ ከበረሃ ወደ በረሃ በሚለው ምዕራፍ ላይ የራሴን ደካማ ጎን ቢያደበዝዝልኝ በሚል የሌሎችን ኋጢአት አዝርከርኬው ነበር። ሆላንድ ኡትል በተባለች ከተማ ከሌንጮ ለታ ጋር ተግናኝቻለሁ። ይላል ተስፋዬ በዚህ ሰነዱ። ከዘረዘራቸው አገሮችንም አንደዚሁ ስሜተኞችን የሚያጣ አይመስለኝም በአስመሳይ መፈከሩ የቢሾፍቱ ልጅ ነኝ በሚል። በዝርዝሩ መግለጫ ላይ ትንታጉ የሚለው ልጅ ግን ጉድ እንደሰራው ተስፋዬ አላወቀም በብልጥ ላይ ብልጥም እንዳለ አልተገነዘብም የለመደች ጦጣ ሁልጊዜ ሽምጠጣ ይባል የለየ እናም ሁሉን ማየት መታደል ነው አንቀጥል። የባከኑ አበሾች በሌላ ርዕስ የምተርከበት መጽሐፍ ነው የሚሆነው። በግላጭ የሚጽፈው የኤርትራን ታሪክ ነው የሚነሳው። ደግሞም ተስፋዬ አውነትም አራዳ ነው። በማስታወሻው ላይ ሌላ ዝፍ ያለ ነገርም አለ እንዲህ በሚል። ከተራሮቹ ስር ያለው ለጥ ያለ የእርሻ ሜዳ የአባቴ አገር ነው። አማረ እና በረከት ተገኝተው ነበር። በመሠረቱ እኔ ከሲቢል ሰርቪስ ከተባለው ትምህርት ቤት ከወጡት እና እዳኝነቱ ውስጥ አብረውኝ ሲሰሩ ከነበሩት በተለያዩ ጊዜ የወያኔን ምስጢራዊ አንፎርሜሽን በተለይም ከከፍፍሱ በኋላ አገኝ ነበር። ደርግ እንደወደቀ ምንም ሳይቆዩ ነው ስዬና ሟቹ አየሎም ከመለስና ተከታዮቹ ጋር ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ የገቡት እንደነገሩኝ ስዬ የደርግ ወታደሮች እና ፖሊሶች በሙሉ አንዲባረሩ አይፈልግም እንደነበር የኢትዮጵያ መከላከያ ከግራ ቀኙ መሳለመሳ ሆኖ ተወጣጥቶ እንዲመሰረት አሳብ አቅርቦ ለመግፋት ሞክሮ እንደነበር አየሎምና ሌሎች የተወሰኑ ይህንኑን ደግፈው እንደነበር በኋላ ግን የመለስ ወገን በተጠናከረ መንገድ ተነስቶ እንዳከሸፈው አስረግጠው ከመንገራቸውም በላይ ስዬ ከፍተኛው የሆነ አስተዋይነት ያለው ሰው በሠራዊቱም ከፍተኛ ተደማጭነት የነበረው ሰው መሆኑን ሁላችም የርሱን አሳብ በጊዜው ብንከተል ኖሮ ይህ ሁሉ አይመጣም ነበር። የወያኔኢህአዴግ ጊዜያዊ መንግሥት በቻርተር ሲቋቋም ተስፋዬ ሀቢሶ የሃዲያን ሕዝብ ወክሎ እምክር ቤት ከመግባቱም በላይ የምከር ቤቱ ጸሐፊ አንደነበርም የሚታወስ ነው። ይሁንና በዚህ በተጠቃሹ ማስታወሻ ላይ ተስፋዬ እንደ አንድ ርዕስ የያዘው ከተስፋዬ ሃቢሶ ተነገረኝ የሚለውን ፕሮፌሰር መስፍን ሃዲያ እንደነበሩ ነግሮኛል ሊለን ነው ደህና የመጽሐፉ መቸብቸቢያ ምክንያት አገኘ ማለት ነው። መቼም የዚያ የወያኔ በዘር ኢትዮጵያን ከፋፍሎ የማጥፋት ጥንስስ ጋር ተስፋዬ አስከወዲያኛው ሳያሸልብ እንደማይቀር ቁልጭ አድርጎ እያሳየን ነው። እውነት ይዘገያል አንጅ መውጣቱ አይቀርም ከነገሩ ከላይ እንዳልሁት ከራሱ ጽሑፍ ብቻ ስንነሳ ተስፋዬ።
በተስፋዬ አባት አገር ማለት አንደኛ አናት አገር እንደማለት ዓይነት ነው የራስን አገር ፈረንጆቹ በሚጠሩት መልክ መሆኑ ነው የኤርትራ ባለሥልጣናትን ልብ ለመማለልና ለመግዛት ተስፋዬ የመረጠው ጥበባዊ ስያሜ እናም ተስፋዬ የመኖሪያ ቤትን አንኳን ሳይጠይቅ ነው ጉዞውን ወደ ኤርትራ ተጣድፎ ያደረገው ሚስቱና ልጆቹ ወዳሉባት አባት አገር ወደ ኤርትራ ስለመሄዱ ግን በግልጽ አልነገረንም የነገረን ወደ ኾሸከን ወደ ተወለደባት ወደ ሩሲያ ነበር ለምን። ታዲያም ተስፋዬ በቡርቃ ዝምታ የደረሰበትን ያንን ሕዝብን ከሕዝብ ጋር የማጨራረስ ወራዳ ሥራውን በተለይም ኮብሊያለሁ ብሎ በወጣበት ውጭ አገር ባለው የኢትዮጵያን ዘንድ ጎልቶ እንዳይወጣ ለማድረግ መሰሪ ዕቅዱን ይዞ ወጣ በመጽሐፈየጋዜጣ ማስታወሻ ይህንኑ እውነታ የሚያሳዩ ከሮችን አለፍ አለፍ ብዬ እንደ ቡርቃው ዝምታ ዓይነት መዘዝ መዘዝ አድርጌ ለእይታ አቀርባለሁ። በሚል። ምናልባትም በረከት በወቅቱ የተስፋዬ ዓላማና መንገዱ እስከምን ድረስ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር ለማለት ይቻል ይሆናል ወገን በወገኑ ላይ ቂም እያበቀለ አገራችን በዘር በጎሳ እንድትከፋፈል ተስፋዬ በጋዜጠኝነቱ በደራሲነቱ የሚያደርገው ለበረከት ምንም አልነበረም ያስጨነቀው እርሱ እየመራው የመጣበት ኢህድን ወይም በኋላ ብአድን የተባለው የወያኔ ውላጅ ሥራን አንደሚፈልገው ዓይነት ተስፋዬ በመጸፉ ላይ ባለማውደሱ ነው ወደ ገጽ ስናልፍ የኢትዮኤርትራ ግጭት እንደተከሰተ ከበረከት ጋር በከረረ ሁኔታ ለመጋጨት በቅተን ነበር ይላል ተስፋዬ ግጭቱን በተመለከተ በበረከት ጸሐፊነት ኢህአዴግ ያወጣውን መግለጫ በተሳሳተ መንገድ ጋዜጣችን ላይ አትመን ስናወጣ ሣሻቢያ ርምጃዎች ጦርነቱን ያቃርበዋል የሚለውን አረፍተ ነገር ጦርነቱ ተቃርቦአል በሚል ባደረግነው ስህተት እንደገና ከፍተኛ ግጭት ውስጥ ገብተናል ይለናል። በተለይም ኦሮሞች የገዛ ሀብታቸው ጠላት እንደሆነባቸውም ማስተዋል ችዬ ነበር የሚለው አነጋገር አንዴት ተስፋዬ ለኦሮሞ ማህበረሰባችን በሌሎች ማህበረሰቦች ወይም በፈረደበት ነፍጠኛ ወይም አማራ በተባለው ዘር ላይ እንዲነሳሱ የማድረግ ትልሙ እንዳላበቃ አመላካች ነው ይህም የሚያሳየን ኢትዮጵያ ተበጣጥሳ ከምድረገጽ አስካልጠፋች ድረስ ተስፋዬ አረፍት የሌለው መሆኑን ነው የተሰለፈበት አላማ ነውና አይፈረድበትም ምንም ያህል ጉድጓድ ተስፋዬ ከጌቶቹ ጋር ቢቆፍርና ቢቆፋፍር በኢትዮጵያ ያሉት ሕዝቦቻችን በፍጹም አንዳይለያዩ ተማምለዋል ከንቱ ልፋት ግና ስንቶቻችን ነን መጽሐፉን ስናነብ ይህንኑ የተስፋዬን ሥውር ደባ የተገነዘብን። ተስፋዬ ታደሰ የትምህርት ቤት ጓደኛዬ ነበር አንድ ጊዜ ካመነበት ፍንክች የማይል ነው እንዲህም አንደሚደርስበት ያውቅ እንደነበር አንድ ቀን አቢሮዬ መጥቶ ስንጫወት እንደነገረኝ ታዲያም ግድየለህም ተስፋዬ። ተስፋዬ በአንዲህ በወጣበት ወቅት አንደ ተስፋዬ የመሳሰሉት የእምዬ ኢትዮጵያ ጠሮች አሜሪካ ውስጥ በቀላሉ ሊኖርቧት አይችሉም ነበር እናም ለራሱ ለሕይወቱ በመስጋት ወይም ወደ አገር ተመልሶ የጀመረውን እንዲጨርስ ጌቶቹ አዘውት ይሆናል የአሜሪካ ስደቱን ያቆመው እንጂ በአሜሪካ መሰደዱን አንደሚለው ጠልቶት አይመስለኝም በዚህም ሆነ በዚያ በዚህ በጋዜጠኛው ማስታወሻ ላይ ተስፋዬ ያደረገው እና የተሳካለት ነገር ቢኖር የወያኔን ምስጢር አወጣለሁ በሚል በዋናነት ስዬ ላይ በማተኮር እውጭ ባለው ማህበረሰብ ውስጥ ሰብሮ ሰርጎ በመግባት የውጭውን ማህበረሰብ ልብ ለሁለት መሰንጠቅ መቻሉ ነው በዚህም ቀሪውን የስለላ ሥራውን ለማከናወን ምቹ መድረከ ለማግኘት መቻሉ ነው። በደራሲው ማስታወሻ ተስፋዬ እንግዲህ የውጭውን ማህበረሰብ ልብ በጋዜጠኛው ማስታወሻ ሰብሮ ገብቶ ምንም ለማለት ምንም ለማድረግ አንደሚችል ከተረዳ በኋላ ከየሰው ከቃረመው ተነስቶ በረቀቀ መንገድ ቀሪውን ሥራ እስከሚችለው ድረስ ለማድረስ በዚህ በደራሲው ማስታወሻ ቀጠለ። ይህንኑ ከጋዜጠኛው ማስታወሻ እንደወጣ ከማስታወቂያው ጀምረን ወደ ኤዎሮፓ የገባበትን ከዚያም የደራሲውን ማስታወሻ እንዴት አንዳሳተመና አንደሸጠ አንስተን ስንመረምረው የምናገኘው ነው ታዲያም ተስፋዬ በጋዜጠኛው ማስታወሻ ላይ የበለጠ ትኩረት የሰጠበት በቡርቃ ዝምታ የጀመረውን ኦሮሞንና አማራውን ማለያየቱን በውጭም ማህበረሰባችን ከመቀጠሉም አልፎ በአገር ቤት ወደ ሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ድርጅቶች ውስጥም ዘው ብሉአል አገር ቤት የጀመረው ሕዝብን ከሕዝብ የማጋጨቱ ትልም እንደፈለገው ሳይሳካለት ቀርቶ ነው መሰለኝ በደራሲው ማስታወሻ ውስጥ በተለየ የጥበብ ከህሎት በየመንገዱ ግለሰቦችንም እየጠራረበ ሄዶበታል። በዚህ ዓይነት ወደ ሳይበሩ ማህበረሰባችን የገባው ተስፋዬ ኢትዮጵያንን የማከፋፈል በሽታ ወደ ሕብረኢትዮጵያን ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ አሸጋግሮ እናያለን ወደፊት ስንጓዝ የእውነታውን ገሃድነት እንመለከታለን ሁለቱ ዝሆኖች በሚል ጮሌው ተስፋዬ ገጽ ላይ ሁለቱ ዝሆኖች በሚል ርዕስ በመለስና በስዬ መካከል ነበረ ስለሚለው የሥልጣን ሽኩቻ መተንተን ከመጀመሩ በፊት ከሁለት ገጣሚዎች መግቢያ እንዲሆነው ቀንጨብ ቀንጨብ አድርጎ አቅርቦ እናያለን እኔ በተለይ ጌትነት አንየውን ወደ ራሱ አዙሬ አየሁ። መቼም ተስፋዬ በተከፈተ ቀዳዳ አንዴት አንደሚገባ ነው የምንመለከተው ከዚህ አባባሉ አንድ ወቅት የውጭው ማህበረሰብ ስዬ ከእስር እንደወጣ ላደረገው ስህተት ይቅርታ አልጠየቀም እያለ የሰላ ትችት ሲያወርድበት ሲሰማና ሲያስተውል የነበረው ይሁዳው ተስፋዬ በመሃከላችን ዘው ለማለት ምቹ ሁኔታ አገኘ እናም ሆድ ያባውን ብቅል ያወጠዋል አንዲሉ ዓይነት ሆነና ስዬ ላይ ሰንቆ የነበረውን የብቀላ ከር መተርተሩን ጀመረው አጋጣሚውንም በደንብ ተጠቀመበት አኛም ስዬ በወያኔ ካምፕ ከነበረበት ሁኔታ ውስጥ በስሜት ባቡር ፈጥነን ተቀላቀልነው ለጊዜውም ቢሆን ተመቸነውና ሜዳ አንዳይበቃው አደረግነው። ገጽ ን ስንመለከት ስዬ አብርሃ መቀሌ ከገባበት ዕለት ጀምሮ አንደ ትግሉ ጊዜ አንገቱ ላይ ከሹከ መጠቅለሉን ሆን ብሎ ቀጠለበት ከኤርትራ ጋር በድንበርና በጉምሩክ ነከ ጉዳይ መተናኮል አበዛ ይህም መለስን የሚረብሸው ሆኖ ተገኘ ወደ ኤርትራ የሚያልፉ ኤርትራዊያን መንገደኞችን አያስፈተሸ ግማሽ ኪሎ በርበሬ መውረስ በመጀመሩ መለስ ወደ ስዬ ደውሉ ማዋፖለቲካ ዝምድናውን ወደ በርበሬና ሽሮ ደረጃ እያወረዳችሁት ነው ብሎ ስለማለቱ የአንድ ሰሞን የሰፈራችን ወሬ ለመሆን በቃ አለን ተስፍሽ ይህ የተስፋዬ አባባል የሚያስረግጠው ቀደም ሲል እየተስተዋለ በሚለው ጽሑፌ ላይ ስዬና ተከታዮቹ ምናልባትም ከትግል ሜዳ ጀምሮ ከነመለስ ግሩፖች ጋር ፍትግያ እንደነበራቸው የገለጽሁትን ነው ኤርትራ የቡና አግር ሳይኖራት አንድ ወቅት በቡና አቅራቢነት ከዓለም ሦስተኛ ሆና እንደነበር የማንረሳው ነው አናም ተስፋዬ ስዬን ለማዋረድ በጠነሰሰው በዚህ ጽሑፉ ስዬ በአንድ ወቅት ከአቅሙ በላይ የሆነውን ነገር ወደ ነበረበት ለማስመለስ ያደረገውን ጥረት ቁልጭ አድርጎ እያሳየን ነው መቼም ተስፋዬ መለስን በአጨዋችነት ገጸባሕርይ ከስዬ ጋር ለማወዳደር ተጠቀመ እንጂ የተነሳበት አላማ ልብ ላለው በግልጽ እንደመስተዋት ቁልጭ ብሎ ይታያል። ታዲያም ተስፋዬ በዚሁ የቆጥባጥ ትረካው አግረ መንገዱንም ፕሮፌሰር መስፍንን በአግቦ ነካ ሳያደርጋቸውም አላለፈም የስዬ ምስጢር ተካፋይ ዓይነት አድርጎ ለማሳየት ተስፋዬ ትክከለኛ አእምሮ ያለው ሰው ሊረዳው በሚችለው መልክ እየነገረን ያለው ስዬ በኢትዮጵያዊያን ላይ ስለሰራው አስነዋሪ ነገር ሳይሆን ስዬ የአባቱ አገር የኤርትራ ጠላት መሆኑን እና በእንዲህ ዓይነት ዘዴም ስዬን ከኢትዮጵያዊያን ጋር አጋጭቶ ከትግል ሜዳው ለማስወጣትና ለሻቢያ እፎይታ ለመስጠት እንደሆነ ከአተራረኩ በቀላሉ ለመረዳት ይቻል ይመስለኛል። ይህን ማድረግ እንችላለን የሚል ግልጽ አላማ ይዞ ተነሳ መለስ ደግሞ በድርድር ብቻ ውዝግቡን ማስወገድ ይቻላል የሚል አቋም ነበረው በውይይትም ወቅት ሚዛን ወደ ስዬ ወገን ሆነ አለን ተስፋዬ። እንግዲህ ሆድ ያባውን ብቅል ያወጠዋል ዓይነት ሆነና ተስፋዬ በአእምሮው ሊደብቅ የሞከረውን ሳያስበው እየወጣበት ነው አለዚያም እኛን እንደእውር ቆጥሮናል ማለት ነው እዚህ ላይ ለምን ተስፋዬ ስዬን ጠመደው። በዚህም ስዬ በህወሃት ውስጥ ትግሉን የጀመረው ትናንት በወጣበት ሰሞን ሳይሆን ቀደም ብሎ በጧቱ እንደሆነ ስንረዳ በአንድ በኩል በሌላም ትጉሉም በአጎብዳኞች ላይ በበረታና ጽናት ባለው መንገድ መሆኑን ነው ከዚህም በላይ ይህ የተስፋዬ በስዬ ላይ አሰሱን ገሰሱን ከምሮ የማስመታት ጥንስስ ስዬ እንደሌሎቹ መለስ እንደፈለገው ሊያሸከረከረው የማይቻለው ሰው እንደሆነ በገሃድ አመላካች ነው ይህ ደግሞ አንዳንድ ጊዜ የምንለው ሲጠፋን ስዬንና መለስን ያጋጫቸው የፖለቲካ ልዩነት ሳይሆን የኤኮኖሚ ጉዳይ ነው የምንለውን አነጋገር የሚያስሰርዝ ነው ተስፋዬ መቼም ስዬን በተገኘው ቀዳዳ እየገባ ለማስመታት ጉድጓድ በቆፈረ ቁጥር ሳያስበው ስለስዬ ጠንካራና ጥሩ ጎን እየነገረን ያልፋል። ነገሩ ልብ ያለው ልብ ያድርግ ነው አናም እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ነገር ተስፋዬ እንዲህ ዓይነት ችቦውን የለኮሰበትን ጊዜ እና ሁኔታ ነው ጊዜው በሁለት ሺህ ምርጫ መቃረቢያ አከባቢ በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል የትብብር ጥያቄ ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ በሆነበትና ሕዝቡ ልከ እንደ ቱ ተቃዋሚዎችንተባበሩ ወይ ተሰባበሩ እያለ ባለበት ሰዓት መሆኑን ነው አንዲህ ሕዝቡ ከማለት ጋር ቀደም ሲል በኢህአዴግ ውስጥ ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ የነበራቸውንና በግል ይንቀሳቀሱ የነበሩትን ስዬ አብርሃንና ዶር ነጋሶ ጊዳዳ ወደ ሕብረብሔር ፓርቲዎች እንዲቀላቀሉ ጠይቆ እነርሱም ተቀብለው አንድነት ፓርቲን በተቀላቀሉበት ወቅት ነው አንደዚህ እንደ ወያኔ ዓይነት አሸባሪ መንግሥትን ለመጣል የግለሰቦችም ሆነ የድርጅቶች ሕብረት ልክ እንደ ቱ በጅጉ አስፈላጊ የሆነበት ጊዜ ነው ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ ተብሎአልና በደራሲው ማስታወሻ ገጽ ላይ ራሱ ተስፋዬ ሣሬ ይህች አገር በጎሳ ፖለትከኞች አና በኢትዮጵያዊነት አራማጆች ጽንፋዊ ትግል መካከል የስንግ ተይዛለች። አባት አገር ቀጥሎ በምትመለከቷት ረቂቅ ሰንድ ላይ ተስፋዬ ጉዞው ወዴት እንደሆነ በቀስት አሳይቶን እናያለን አባት መሬት በሚል ርዕስ ስለኤርትራ ትግል ሙሉ በሙሉ አንድ መጽሐፍ ለመጻፍ ያለመበትን የሚያሳይ ረቂቅ ሰነድ አለማየሁ ከተስፋዬ በተለየ ዘዴ ያገኘውን እንመለከታለን በዚህች ረቂቅ ሰንድ ላይ ተስፋዬ የነደፋቸውን ከፍሎችን እናያለን። አነርሱንም እንመለከታቸዋለን በሕሊና መነጽርም እንጓዛለን ተስፋዬ ኢትዮጵያዊ ነኝ የቢሾፍቱ ልጅ ነኝ አሁንም ነኝ ይህንኑ ማንም አይከለከለኝም ስለን የነበረው መረን የለቀቀ የአስመሳይነት ባሕርይው ይኸውና ቀኑ ሲደርስ ብቅ አለ ታዲያም ተስፋዬ የራሱን አንዲህ ዓይነት ጉዱን በጉያው ወትፎ አኛን እያሞኘን አግሌ እውነቱን አልነገረንም እገሌ አንዲህ ዓይነት ሰው ነው እያለ ተዘባብቶብናል። በዚሁ ማስታወሻ ወረድ ይልና ተስፋዬ ከኢሳያስ ተቃዋሚዎች ጋር ብዙ ጊዜ እንገናኝ ነበር። ሌላው ተስፋዬ እኛን ሽጦን አሻሽጦን ባገኘው የኤርትራዊነት እምነቱ አባት አገር አባት መሬት በሚል ርዕሱ ገና ያልተቆረጠለት ከስደተኛው ማስታወሻ ቀጥሎ የሚያወጣው መጽሐፍ እንዳለው አስረግጦ እየነገረን ነው ከላይ ከተመለከተው ማስታወሻ በተጨማሪ አለማየሁ ካገኛቸው ውስጥ ለአቶ አለም ሰላምታ ምናልባት ተቆጣጣሪው ሊሆን ይችላል ብሎ በነደፈው ረቂቅ ላይ አንዲህ በሚል በአምስት ተከፍለው የሰፈሩ ቁም ነገሮችን እናገኛለን። አስገራሚው ነገር ደግሞ ይህን መጽሐፍ ስደት ከወጣም በኋላ አሳትሞ መሸጡ ነው ይህ ምን ማለት እንደሆነ ለኛ ምስጢር ሲሆነን የሚገባ አይመስለኝም ሌላ አንኳር ቁም ነገርም እናያለን ከዚህ ከተስፋዬ ማስታወሻ የርሱ ግጭት ከወያኔ ጋር ብቻ መሆኑን ያውም ወያኔ ኤርትራን ስለተቃረነ በተቀረ ግን ኢትዮጵያ ለምትባል አገር ለኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ ምንም ዓይነት ደንታ የሌለው መሆኑን ነው እፌ ተመልከቶ አንዳንድ ነጥቦች ተብሎ ለአቶ አለም ሰላምታ ተብላ የተነደፈች የጋዜጠኛው ማስታወሻ ወደ ትግሪኛ እየተተረጎመ እንደነበር ከ ወራት በፊት ገልጩ ነበር። ንጹህ ኢትዮጵያዊ ነኝ እያለ የሚፎከረው ሰው ውስጡ ሲገለጥ እንዲህ ሆኖ እናገኛዋለን ትዳርና ልጅ እንደሌለውና ዋልጌነቱን የሚደሰኩርልን ተስፋዬ ሲገለጥ እንዲህ ዓይነት ሰው ሆኖ እአናገኘዋለን መቼም ከገሙ ላይቀር ብሽሸቅጥ ነውና ተስፋዬ አልገኝም በሚል አባዜ ተወጥሮ ለእንዲህ ደረሰ። እናም በእጅጉ ተስፋዬ ድንጋጤ ውስጥ የወደቀበትና ተስፋም የቆረጠበት ሁኔታን የሚያሳይ ኑዛዜ በአንድ በኩል ሲመስል በሌላ በኩል ደግሞ ሆድ ያባውን ብቅል አንዲሉ አፍኖ ውስጥ ውስጡን ሲሰረስር የነበረው ግንድ በራሱ ላይ ሊወድቅበት ሲቃረብ የተፋው ማስታወሻ ነው አንዳንድ የማብራሪያ ነጥቦች አንዳንንድ የማብራሪያ ነጥቦች ይላል የሚቀጥለው የተስፋዬ ማስታወሻ በዚህ ላይ ተስፋዬ ለመጠቃቀስ ከሞከራቸው ውስጥ በዋነኛነት ኤውሮፓ ላይ ሥራ የምሰራ ከሆነ በእግረመንገዴም የጽሑፍ ሥራ እየሰራሁ የተሳካ ውጤት ማምጣት አንደሚቻል አምፔ እንደነበር አይዘነጋም እዚህ ከመጣሁ በኋላ ግን ሥራውን በሚሜፈለገው ደረጃ መሥራት የሚቻል አለመሆኑን ቀደም ባለው ደብዳቤዬ ገልጫለሁ። ልፋት በከንቱ ይሉታል እንዲህ ነው እብድ እርሱ እንጅ ማንም ኢትዮጵያዊ እብድ አይደለም ሆኖም እንቀጥል አሁንም ከዚህ በኋላ ስለሚኖረኝ ፕሮግራም ተስፋዬ ከዚህ በኋላ ስለሚኖረኝ ፕሮግራም ብሎ ከአናቱ ላይ በጸፈው ማስታወሻ ላይ ከስደተኛው ማስታወሻ ቀጥሎ የምጽፈው መጽሐፍ ምናልባት የቀይ ወጎች የሚል ሳይሆን አይቀርም ይህንንም የምጽፍላችሁ እዚያው ድባርዋ ሆፔ ነው ኢትዮጵያን ነጻ ለማውጣት በሜደረገው ትግል ምከንያት በድንገት ወደ ኤርትራ ብቅ ካላችሁ ድባርዋ በየት በኩል ነው። የሚል ሃይለ ቃል አስፍሮአል ተስፋዬ ጉድ ነው ተስፋዬ የኢትዮጵያዊያን ወዳጅ ሆኖ ተናፍቆ ሊጠይቅ። ከሌንጮ ለታ ጋር ተስፋዬ ያደረገው ንግግር ቁም ነገር ቀጥሎ በቁጥር ማስታወሻ ላይ የተመለከተው ነው ወረድ ይልና ተስፋዬ ሣጉል እንደጎለጎለው ከሆነ የስደተኛው ማስታወሻን ከማንበብዎ በፊት በሳቅ ብዛት ለመሞት መዘጋጀት አለብዎ። እንኳንስ ውሸት እውነት ሲደጋገም ሬት ሬት ማለቱ አይቀሬ ነው ተስፋዬ በዚያ በመጽሐፈርኩሳት ላይ ስዬን ባማንቸውም መልክ አላንሳም ነገር ግን ከጋዜጠኛው ማስታወሻ ጀምሮ የደራሲው መጽሐፍ ውስጥ ብሎም በየሚዲያ ጽሑፎቹ ሁሱ ስዬ የተስፋዬ ጆከር ከሆነ ሰነባበተ እንዲያው የጉሮሮ ላይ አጥንት ዓይነት ሆኖበታል ለማለት ይቻላል።