Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የሚለው በመሆኑ ከዚሁ ጭብጥ አኳያ የሰበር ችሎቱ መዝገቡን መርምሯል በከፍተኛ ፍቤት ውሳኔ ሐተታ እንደተመለከተው ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ ይታረምልኝ በማለት አመልካቾች ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዓም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ ስላቀረቡ ነው የክርክሩ መነሻ በአፈፃፀም የባልና የሚስት የጋራ ንብረት ነው።
የሚለው ነጥብ ሆኖ ተገኝቷል እንደሚታወቀው የፌመደፍቤት ለውሣኔው መሠረት ያደረገው የውሉን አንቀጽ ሲሆን ይህም አንቀጽ የኢንሹራንስ ሠነዶቹን ማቅረብ የአመልካቹ ግዴታ መሆኑን ይገልፃል በመሠረቱ የኢንሹራንስ ዋነኛ ጠቀሜታ ኢንሹራንስ የተገባለት ዕቃ አደጋ ቢደርስበት በአደጋው ምክንያት የደረሰው ጉዳት ሣይካስ እንዳይቀር መሆነ ይታወቃል በዚህ በተያዘው ጉዳይ ከመዝገቡና ከግራ ቀኙ ክርክር መረዳት የሚቻለው ደግሞ እቃዎቹ ጅቡቲ ወደብ በሠላም መድረሳቸውን አልፎ ተርፎም እቃዎቹ በወደብ ለ ቀናት ከዘገዩም በኋላ ቢሆን የኢንሹራንስ ሠነድ ባልቀረበበት ሁኔታ አቃዎቹ ከተጠሪው እጅ በሠላም መድረሳቸውን ነው ከዚህ መገንዘብ የሚቻለው አቃዎቹን ከወደብ ለማንሣት የኢንሹራንስ ሠነዱ መቅረብ አስፈላጊ አንዳልነበረ ነው በመሆኑም ተጠሪው እቃዎቹ በወደብ የዘገዩት አመልካቹ በውሉ መሠረት የኢንሹራንስ ሠነድ ባለማቅረቡ ነው ሲል ያቀረበው መከራከሪያ ተቀባይነት የሌለው ነው ከዚህ ይልቅ አመልካቹ ለክፍያ የተዳረጉት እቃዎቹን ከወደብ ለማንሣት አስፈላጊ የሆኑትን የማጓጓዣ ሠነዶች በተለይም የገንዘብ ሚኒስቴር ከቀረጥ ነፃ ብሎ ለተጠሪው የሚሠጠው ደብዳቤ ተጠሪው መቤት ለአመልካቹ በጊዜው ለማቅረብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው መሆኑ ታውቋል በአጠቃላይ አመልካቹ ለተጠሪው ጥቅም በሌለበት ግዴታ የከፈለውን የወደብ ኪራይና የደመራዥ ክፍያ ተጠሪው ሊተካ አይገባም መባሉ አላግባብ መሆኑን ይህ ፍቤት ተገንዝቧል ውሣኔ ተጠሪ ለአመልካች ብር አስራ አራት ሺህ አምስት መቶ ፃምሣ ስምንት ከአስራ ሰባት ክሱ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ ጋር ይክፈል አመልካች ለዳኝነቱ የከፈለው ገንዘብ ተጠሪ ይተካለት የዚህን ፍቤት ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር መቁ ዐ ታህሣሥ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ሐጎስ ወልዱ መስፍን እቁበዮናስ ሒሩት መለሠ ተሻገር ገሥላሴ አመልካች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነፈጅ ዘውዱ አሊ ቀረቡ ተጠሪ አቶ አሰበወርቅ ዘገየ አልቀረበም ፍርድ በሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የጀመረው በፌመደረጃ ፍቤት ነው ተጠሪ ለሥር ፍቤት ባቀረቡት ክስ አመልካች መቤት የሥራ ውላቸውን ያላግባብ ስላቋረጠባቸው ውዝፍ ደሞዝ የተጠራቀመ የዓመት አረፍትየቦነስ ክፍያ አበል የአቃ ማጓጓዣ የኤርፖርት ታክስየካሣ ክፍያ የማስጠንቀቂያ ክፍያ እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ ከስራ የተሰናበቱት ያለአግባብ በመሆኑ ውዝፍ ደመወዝ የአረፍት ጊዜ በገንዘብ ተለውጦ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ እና የአገልግሎት ካሣ የ ወር ደመወዛቸውን እንዲከፈላቸው ወስኗል የፌከፍተኛ ፍቤትም ይህንነ ውሣኔ አጽንቷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ ውሣኔ ላይ ሲሆን ይህ ችሎትም የአመት እረፍትና የአገልግሎት ካሣ እንዲከፈላቸው የተሰጠውን ውሣኔ ሕጋዊነት ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሉት እንዲቀርብ አድርጓል ተጠሪም ቀርበው ክርክራቸውን በጽሁፍ አቅርበዋል አመልካች በሰበር አቤቱታው ውዝፍ ደሞዝ በተመለከተ ቀደም ሲል ከሰው ተወስኖላቸው የወሠዱ በመሆኑ በድጋሚ ሊከፈላቸው አይገባም አመልካች የተመደቡበት የስራ ኃላፊነት ከፍተኛ እምነትን የሚጠይቅ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸው በድርጅቱ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት ሊያደርሱ ስለሚችሉ በፍሕቁ መሠረት ያለማስጠንቀቂያ ሊሰናበቱ ችለዋል ከስራ የተሰናበቱት በጥፋት ስለሆነ ካሣ ሊከፈላቸው አይገባም ብሏል ተጠሪም የሥር ፍቤቶች ውሣኔ በአግባቡ ነው ሲሉ ዝርዝር መልስ ሰጥተዋል ይህ ችሎትም መዝገቡን እንደሚከተለው መርምራሯል ተጠሪ ያለአግባብ ከሥራ ተሰናብቻለሁ በማለት ሊከፈላቸው የሚገባውን ክፍያ ዘርዝረው ክስ አቅርበዋል ከመዝገቡ አንደተረዳነውም አመልካች የተጠሪን የሥራ ውል ያቋረጠው ጥፋት ፈጽመዋል በሚል ቢሆንም ጥፋት መፈፀማቸውን እንዳላስረዳ የሥር ፍቤቶች አረጋግጠዋል ጥፋት መኖር አለመኖሩ ደግሞ የፍሬ ነገር ክርክር በመሆነ በዚህ ሠበር ችሎት በድጋሚ የሚታይ አይሆንም በመሆኑም የተጠሪ የሥራ ውል ያለበቂ ምክንያት ከተቋረጠ ተጠሪ ሊያገኙ የሚገባቸው ክፍያዎች ምንድናቸው የሚለውን መመለከት ተገቢ ነው በተለይ አመልካች ቅሬታ ያቀረበባቸው ክፍያዎች የተጠራቀመ ደመወዝ የዓመት እረፍት የማስጠንቀቂያና የካሣ ክፍያዎችን የሚመለከቱ በመሆናቸው እነዚህ ክፍያዎች ለተጠሪ ሊከፈሉ ይገባል ወይስ አይገባም የሚለውን ተመልክተናል ተጠሪ የሥራ መሪ በመሆናቸው የሣቸው ጉዳይ የሚታየው በፍትሐብሔር ሕጉ እንደመሆኑ የተያዘው ጉዳይ ስለሥራ ውል በፍብሕጉ ከተደነገጉት ድንጋጌዎች አኳያ ተመርምራል የካሣን ጥያቄ በተመለከተ ከፍ ሲል እንደተገለፀው አመልካች የተጠሪን የሥራ ውል ያቋረጠው ተጠሪ ጥፋት ፈጽመው ነው ቢልም ይህንን አንዳላስረዳ የሥር ፍቤቶች አረጋግጠዋል በመሆኑም የተጠሪ የሥራ ውል የተቋጠረው ከሕግ ውጪ መሆኑን ተገንዝበናል አሠሪው ውሉን ቀሪ ለማድረግ በቂ ምክንያቶች የሌለው እንደሆነ ለሠራተኛው ተገቢ የሆነ ኪሣራ ለመክፍል እንደሚገደድ በፍሕቁ ሥር ተመልክቷል በመሆኑም አመልካች ተጠሪ ከሥራ የተሰናበቱት በጥፋት ስለሆነ ካሣ ልከፍል አልገደድም በማለት ያቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም የኪሣራውን ልክ በተመለከተ ግን ለሠራተኛው የሚከፈለው ባለፈው ወር ከተቀበለው ደመወዝ ሊበልጥ እንደማይችል በፍህቁ ሥር የተመለከተ በመሆኑ የሥር ፍቤቶች የ ወር ደመወዝ በካሣ መልክ እንዲከፈል መወሰናቸው ተገቢ አይደለም ሌላው የማስጠንቀቂያ ክፍያን የሚመለከት ሲሆን አሠሪው ውሉን ቀሪ ለማድረግ አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ መስጠት እንደሚገባው በፍሕቁ ዐ ሥር ተቀምጧል የሥራ ውሉ ከአንድ አመት በላይ ቆይቶ ከሆነ ማስጠንቀቂያው ቢያንስ ከ ወር አስቀድሞ ሊሰጠው ይገባል የፍህቁ ይመለከታል አመልካች ማስጠንቀቂያ ሊሰጥ አይገባም የሚለው ስራው ልዩ ችሉታንና ከፍተኛ እምነት የሚጠይቅ ነው በማለት የፍሕቁ ን መሠረት አድርጎ ሲሆን የተጠሪ የሥራ አስኪያጅነት ሥራ ግን በዚህ አንቀጽ የሚሸፈን ባለመሆኑ የአመልካች ክርክር ተቀባይነት የለውም የተጠራቀመ ደሞዝን በተመለከተ አመልካች በሰበር አቤቱታው ለተጠሪ በባንክ ሂሣባቸው ደመወዛቸውን ገቢ ሲያደርግ ቆይቶ ደመወዝ ለተጠሪ ሊከፈል እንደማይገባ ሲረዳ ከሂሣባቸው ወጪ አድርጎ በመውሰዱ አመልካቹ የወሰደውን ገንዘብ እንዲመልስ ተጠሪ ክስ አቅርበው ስላስወሰነበት በአፈፃፀም ገንዘቡን የተቀበሉ በመሆኑ በድጋሚ ደመወዝ ሊከፈላቸው እንደማይገባ ገልዷል ይህ ችሎቱም መዝገቡን አንደመረመረው ተጠሪው አመልካች ወደ ሂሣባቸው ገቢ አድርጎ መልሶ የወሰደውን ገንዘብ እንዲመልስ በሌላ መዝገብ ክስ መስርተው አስወስነውበት ገንዘቡን የተቀበሉ መሆኑን ይህም ገንዘብ የተጠሪ ደመወዝ መሆኑን ለመገንዘብ ችለናል በመሆኑም አመልካች የተጠሪን ደመወዝ እንዲመልስ በሌላ መዝገብ ተወስኖበት ከከፈለ በኋላ ተጠሪ በድጋሚ ውዝፍ ደመወዝ ሊከፈላቸው የሚገባበት ሕጋዊ ምክንያት የለም የመጨረሻው ነጥብ የዓመት አረፍትን የሚመለከት ነው ተጠሪ የሚከራከሩት የዓመት እረፍት ካልተወሰደ ተጠራቅሞ ሠራተኛው በሚመቸው ጊዜ እንደሚወስደው ካልወሰደ ግን በገንዘብ ተቀይሮ እንደሚከፈለው እና ከዐ ቀናት በላይ እረፍቱ አይተላለፍም የሚለው ክርክር የሕግ ድጋፍ እንደሌለው ነው አመልካች በበኩሉ በወቅቱ የነበረው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ እረፍት ከዐ ቀናት በላይ ሊተላለፍ እንደማይችል ይገልፃል ያም ቢሆን ተጠሪ አረፍታቸውን ተጠቅመውበታል አላቸው ቢባል እንኳን በፍሕቁ መሠረት ከዐ ቀናት በላይ ያለው አረፍት ተቀባይነት የለውም በማለት ይከራከራል የሥር ፍቤት የአመልካችን ክርክር ውድቅ ያደረገው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ አልቀረበም ቢቀርብም በፍሕጉ ላይ ገደብ የማያስቀምጥ በመሆኑ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም በሚል ነው ነገር ግን የፍሕጉ የዓመት እረፍት ላልተወሰነ ጊዜ እንደሚተላለፍ ያስቀመጠው ነገር ስለሌለ መመሪያው በፍሕጉ ላይ ገደብ አስቀምጧል ለማለት አይቻልም በሌላ በኩል ተጠሪ የብሔራዊ ባንክ መመሪያ እረፍት ከዐ ቀናት በላይ ሊተላለፍ አይችልም በማለት ያስቀመጠው ገደብ የለም በማለት በግልጽ ያቀረቡት የተቃውሞ ክርክር የለም በፍሕጉ ላይ ያልተመለከቱ ነገሮችን ደግሞ የመቤቱ አስተዳደር መወሰኑ ሕገ ወጥ ነው ለማለት አያስችልም በሌላ በኩል ግን አመልካች ተጠሪ አረፍታቸውን በሙሉ ተጠቅመዋል ይባል እንጂ የሥር ፍቤት የተጠሪን ማህደር አስቀረቦ ተጠሪ ያልወሠዱት እረፍት መኖሩን ስላረጋገጠ በዚህ በኩል የቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም በመሆኑም ተጠሪ የተጠራቀመ የዐ ቀን ብቻ ሊሰጣቸው ሲገባ የሥር ፍቤት ቀናት አረፍት እንዲያገኙ መወሰኑ ስህተት ነው ውሣኔ የፌመደረጃ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ዐ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የፌከፍተኛ ፍቤት በመቁ ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሻሽሏል ለተጠሪ የተጠራቀመ ደመወዝ እንዲከፈል የተሰጠው ውሣኔ ተሽሯራል አመልካች ለተጠሪ የ ወር ደመወዝ ካሣ ክፍያ እንዲከፍላቸው ተወስኗል አመልካች ለተጠሪ የ ወር ደመወዝ የማስጠንቀቂያ ክፍያ ይክፈላቸው አመልካች ለተጠሪ የዐ ቀን የዓመት እረፍት በገንዘብ ቀይሮ ይክፈላቸው ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰበር መቁ ዐ ጥር ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሂሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች አቶ የሺወንድም አቡሐይ ተጠሪ አቶ አየነው ማለደ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሉ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው በተጠሪ ላይ ተሰጥቶ የነበረው የመጥፋት ውሣኔ ሲሰረዝ አመልካች ለኛ ወገን በሽያጭ አስተላልፈውታል የተባለውን ቤት ለተጠሪ ሊመለሱ ይገባል የሚሉት በበታች ፍቤቶች የተሰጡት ውሣኔዎች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል ሲሉ አመልካች የሰበር አቤቱታ በማቅረባቸው ነው የጉዳዩ አመጣጥም ባጭሩ ሲታይ ተጠሪ ለሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረቡት አቤቱታ በአመልካች ጠያቂነት ቀደም ሲል በወረዳ ፍቤት በተጠሪ ላይ የተሰጠው የመጥፋት ውሣኔ የተነሣ መሆኑን ገልፀው የግል ንብረቴ የሆነውና የዋጋ ግምቱም ብር ዐዐዐዐ ህፃምሣ ሺህ የሆነው ቤት አመልካች ለኛ ወገን በሽያጭ ያስተላለፈው ስለሆነ አንዲመለስ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል አመልካችም ቀርበው በሰጡት መልስ ተጠሪ ከእናቴ ጋር ጋብቻ መሥርቶ እያለ አናቴን ጥሎ በመጥፋቱ በሽተኛ ስለነበረች እሷን ለማሣከም ገንዘብ በማስፈለጉ ቤቱ የተሸጠ ሲሆን የሽያጩ ዋጋም በከሣሽ እንደተጠቀሰው ብር ቀፃምሣ ሺህ ሣይሆን ብር ፃያ አምስት ሺህ ነው በማለት ክሱ ሊሰረዝ ይገባል በማለት ተከራክረዋል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ክርክሩን ከቀረበው ማስረጃ አኳያ መርምሮ ተከሣሽ ለክሱ ምክንያት የሆነው ቤት የከሣሽና የእናቴ የጋራ ሀብት ነው የሚል ክርክር ቢያቀርብም ከጎንደር ከተማ አገልግሎት ጽቤት የቀረበው የሰነድ ማስረጃና እንደዚሁም በከሣሽ በኩል የቀረቡት ምስክሮች በሰጡት ቃል ከሣሽ ከተከሣሽ አናት ጋር ጋብቻ ከመመሥረታቸው በፊት የሠሩት ቤት እንደሆነ ስለሚያረጋግጥ ተከሣሽ ቤቱ የጋራ ንብረት ነው በማለት ያቀረቡት ክርክር ተቀባይነት የለውም ካለ በኋላ ጠፍቷል የተባለ ሰው ከመጣ ጠፍቷል መባሉ ተሠርዞ ወደ ሌላ ሰው ተላለፎ የሚገኝ ንብረትም ሊመለስለት እንደሚገባ በፍብሕቁ ላይ የተመለከተ በመሆኑ በዚሁ መሠረት ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት ለከሣሽ ሊመለስ ይገባል በማለት ውሣኔ ሰጥቷል ተከሣሽ በዚሁ ውሣኔ ቅር በመሰኘት የይግባኝ ቅሬታቸውን ለአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ያቀረቡ ቢሆንም በፍብሕሥሥቁ መሠረት ፍቤቱ ይግባኙን ሣይቀበለው ቀርቷል ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም የቀረበለትን አቤቱታ መርምሮ አመልካች ተጠሪ ጠፍተዋል በማለት የመጥፋት ውሣኔ ካገኙ በኋላ ወራሽነታቸውን አረጋግጠው የተጠሪን ቤት ለኛ ወገን መሸጣቸው በተረጋገጠበት ሁኔታ ተጠሪ ሲመለሱ ሊመለስላቸው የሚገባው የቤቱ ሽያጭ ዋጋ ወይንስ ቤቱ አራሱ የሚለው ነጥብ ከፍብሕቁ አኳያ አቤቱታው ለሰበር ቀረቦ ተጣርቶ ሊወሰን የሚገባው ሆኖ በማግኘቱ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል በአጠቃላይ የክርክሩ ነጥብ ከላይ የተመለከተው ሲሆን የሰበር አቤቱታው ያስቀርባል ከተባለበት ነጥብ አኳያ እንደሚከተለው ተመርምሯል በተጠሪ ላይ የመጥፋት ውሣኔ ከተሰጠ በላ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት በሽያጭ ወደ ኛ ወገን የተላለፈ መሆኑ ግራ ቀኙን አላከራከረም የመጥፋት ውሣኔን ውጤት ቀሪ ከሚያደርጉ ምክንያቶች ር ር መጠበበቧ ርየ አንዱ ጠፍቷል የተባለው ሰው መመለስ እንደሆነ በፍብሕቁ ላይ ተመልክቷል በዚህ ድንጋጌ መሠረትም ጠፋ የተባለው ሰው በተመለሰ ጊዜ ንብረቶቹን በሚገኙበት አኳን መልሶ የመረከብ እንደዚሁም የተሸጡትን ንብረቶች ዋጋ የማግኘት መብት እንዳለው በግልጽ ተመልክቷል በተያዘውም ጉዳይ ንብረትነቱ የተጠሪ የሆነው ቤት መሸጡ ከተረጋገጠ ከላይ ከተጠቀሰው ድንጋጌ አኳያ ተጠሪ ሊረከቡ የሚገባቸው የተሸጠውን ቤት ሣይሆን የሽያጩን ዋጋ ነው ማለት ነው የሸያጩን ዋጋ በተመለከተም አመልካች በብር ፃያ አምስት ሺህ መሸጡን ሲገልፁ ተጠሪ ዋጋው ብር ዐዐዐዐ ሃምሣ ሺህ አንደሆነ ከመግለጽ በስተቀር በዚህ ዋጋ የተሸጠ መሆኑን ማስረጃ አቅርበው አልተከራከሩም ስለሆነም የበታች ፍቤቶች በሽያጭ የተላለፈው ቤት ለተጠሪ ሊመለስላቸው ይገባል በማለት የሰጡት ውሣኔ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐ በጥር ቀን ዓም በሰጠው ውሣኔ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት ለአመልካች ይገባል ማለቱ እንደዚሁም የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ዐ በመጋቢት ቀን ዓም ይግባኙን ባለመቀበል የሰጠው ትአዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሰለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት በብር ዐዐዐ ፃያ አምስት ሺህ ስለመሸጡ የተረጋገጠ ስለሆነ ይህንኑ የሽያጭ ገንዘብ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ተከፍሎ እስካለቀ ድረስ ከሚታሰብ ዘጠኝ በመቶ ወለድ ጋር አመልካች ለተጠሪ እንዲከፍሉ ተወስኗል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሣቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የመያዣ ውል የሠመቁ መጋቢት ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ነፈጅ አስያድ ጋዲሳ ተጠሪ ወሮ አስካለ ሁንዴ አልቀረቡም አቶ አንቻሎ ቡሬ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን ቀጥሎ የተመለከተውን ፍርድ ሠጥተናል ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በምስራቅ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪዎች በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ ኀዳር ቀን ዓም በተፈረመ የገንዘብ ብድር ውል ተጠሪዎች ከአመልካች ብር መቶ አርባ ሺህ ተበድረናል ገንዘቡም ተከፍሎ የሚጠናቀቀው ጥር ቀን ዓም የነበረ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ጥር ቀን ዓም በተፈረመ የገንዘብ ብድር ውል ብር ዐ ሺህ ተበድረናል ሁለተኛውም የብድር ገንዘብ ተከፍሎ የሚጠናቀቀው የካቲት ቀን ዓም ነበር ሆኖም የብድሩ የመጨረሻ መክፈያ ጊዜ ሳይደርስ በሕገወጥ መንገድ የመያዣ ንብረቶቹን የአንድ ወር ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠን በዋስትና ያልተያዘውንም ንብረታችንን ጭምር በኃይል አስፈራርቶ ወስዶብናል ስለዚህ ከሱቅ ከእንጨትና ቁርስ ቤት የተቋረጠ ገቢ ብር ዐዐዐዐዐ ሁለት መቶ አሥር ሺህ ስምንት መቶ ንብረቶቹ በሕገወጥ መንገድ በመወረሳቸው የደረሰብን ጉዳት ብር ዐ መቶ አርባ ስድስት ሺህ ስምነት መቶ ዘጠና የተወሰደብን ቤት ቢሸጥ ብር ዐዐዐዐ ሥስት መቶ አስር ሺህ ሲሆን የሚፈለግብን ዕዳ ከተቀነሰ በኋላ ብር ዐ መቶ ሠላሳ አራት ሺህ አምስት መቶ ሁለት ከአርባ ሦስት ሊከፍለን ይገባል በማለት በአጠቃላይ ሌሎች ወጭዎችን ጨምረው ብር አራት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ አንድ መቶ ዘጠና ሁለት ከአርባ ሦስት ተከሣሽ እንዲከፍል ይወሰንልን በማለት ጠይቀዋል የከሣሾች ክስና ማስረጃ ለተከሳሽ ደርሶም በሰጠው መልስ ባንኩ ንብረቱን የተቆጣጠረው በአዋጁ ቁጥር ዐ መሠረት ሕጋዊ ሥርዓትን ተከትሎ ስለሆነ ከፍብሕሥሥቁ አኳያ ከሳሾች ክስ ባቀረቡበት ነገር መብትና ጥቅም ስለሌላቸው መዝገቡ ሊዘጋ ይገባል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል በፍሬ ጉዳይ ክርክር ረገድ የሰጠው መልስ ተጠቃሎ ሲታይ የብድሩ መክፈያ ጊዜ ሳይጠናቀቅ ዕርምጃ ተወስዷል በማለት ከሣሾች ያቀረቡትን አቤቱታ በተመለከተ በፍብሕቁ መሠረት ውዝፍ ዕዳው ከጠቅላላ ፅዳው ዐ ከሆነ የመጨረሻ መክፈያ ጊዜውን ሳንጠብቅ ዕርምጃ መውሰድ አንችላለን ከዚህም ሌላ ባንኩ የንብረት ርክክብ ያደረገው በአዋጅ ቁጥር መሠረት የሚመለከታቸው ተወካዮች በተገኙበት ነው በማለት ተከራክሮ ከሳሾች በጠየቁት የካሣ መጠንም ላይ ግምቱ የተጋነነ ነው በማለት መልስ ሰጥቷል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት በተከሣሽ በኩል የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በብይን ተቀባይነት የለውም ካለ በላ በጥር ቀን ዓም በግራ ቀኙ መካከል በተፈረመው የብድር ውል ከሳሾች የብድሩን ገንዘብ አጠናቀው መክፈል የሚገባቸው በየካቲት ቀን ዓም ሆኖ ሳለ አንደዚሁም ቀደም ብሎ በህዳር ቀን ዓም ባደረጉት የብድር ውልም በአዋጅ ቁጥር ዐ አንቀጽ መሠረት ተከሳሽ የ ወር ማስጠንቀቂያ ለከሳሾች መስጠት ሲገባው ይህን ሳያደርግ በመያዣ ያልያዘውንም የከሳሾችን ንብረት ጭምር ማሸጉ አግባብነት የሌለው በመሆኑ ኃላፊነት አለበት ካለ በኋላ በመያዣ ከተያዘው ቤት ጋር የታሸጉት የከሳሾች ንብረት የዋጋ ግምታቸው እንዲገለጽለት ለሚመለከተው መቤት ትዕዛዝ ሠጥቶ ብር ዐ አንድ መቶ ሰማኒያ ሦስት ሺህ አንድ መቶ ሠላሳ ከ ስድስት እንደሆነ የተገለጸለት ቢሆንም በዚህ ረገድ ከሳሾች የጠየቁት ክፍያ ብር ዐ መቶ አርባ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና ስለሆነ ይሄው የንብረት ዋጋ ግምት ሊከፈላቸው ይገባል ብሏል በሌላ በኩልም የብድሩን ክፍያ በተመለከተ ከሳሾች የሚፈለገባቸው ቀሪ የብድር ገንዘብ ብር አንድ መቶ ሰባ አምስት ሺህ አራት መቶ ዘጠና ሰባት ከፃምሳ ሰባት ሲሆን ተከሳሽ የተረከበው የከሳሾች ቤት ደግሞ ብር ዐ ሦስት መቶ አሥር ሺህ እንደሆነ ስለተረጋገጠ ከከሳሾች የሚፈለገው ዕዳ ከቤቱ ግምት ሲቀነስ ብር ዐ አንድ መቶ ሠላሳ አራት ሺህ አምስት መቶ ሁለት ከአርባ ሦስት ስለሚመጣ ይህንንም ተከሣሽ ለከሳሾች መክፈል አለበት ብሏል ከዚህም በተጨማሪ ተከሣሽ የተረከባቸው የከሳሾች ሱቅ ቁርስ ቤትና እንጨት ቤት ታሽገው በቆዩበት ቀናት ከሣሾች ባቀረቡት የተጣራ ትርፍ ማስረጃ መሠረት በድምሩ ብር ዐይዐዐ ሁለት መቶ አሥር ሺህ ስምንት መቶ ተከሣሽ ለከሳሾች መክፈል አለበት በማለት ውሣኔ ሰጥቷል በአጠቃላይ ድምርም ብር አራት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ አንድ መቶ ዘጠና ሁለት ከአርባ ሦስት የጠበቃ አበል በዚሁ ልክ ዐ አስር በመቶ ወጭና ኪሣራ በቁርጥ ብር ዐዐ ሁለት መቶ ጨምሮ ተከሳሽ ሊከፍል ይገባል በማለት ውሣኔ ሠጥቷል ተከሣሽ በዚህ ውሣኔ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ቢያቀርብም በፍብሕሥሥቁ መሠረት ፍቤቱ ይግባኙን ሳይቀበለው ቀርቷል ይህ ችሎትም የቀረበለትን አቤቱታ መሠረት በማድረግ አመልካች በመያዣነት የያዛቸውን ንብረቶች በሕገወጥ መንገድ ይዚል በማለት ከላይ የተጠቀሰውን ገንዘብ ለተጠሪዎች ሊከፍል ይገባል በማለት በሥር ፍቤቶች የተሰጠው ውሣኔ ተጠሪዎች ባሉበት ሊታይ የሚገባው መሆኑን በማመኑ ተጠሪዎችን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል የዚህን ችሎት ምላሽ ማግኘት የሚገባውም የጉዳዩ ጭብጥ አመልካች የተጠቀሰውን ገንዘብ ለተጠሪዎች እንዲከፍል መወሰነ አግባብነት አለውን። የሚለው በመሆኑ ከዚሁ ጭብጥ አኳያ የሰበር አቤቱታው እንደሚከተለው ተመርምሯል በአዋጅ ቁጥር ዐ አንቀጽ እና መሠረት እንደዚሁም በአዋጅ ቁጥር በተደረገው ማሻሻያ ባንኮች ለሰጡት ብድር አከፋፈል በመያዣነት በዋስትና የተቀበሉትን የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት የብድር ፅዳው እንዲከፈል በተወሰነው ጊዜ ሳይከፈል ከቀረ ከሠላሣ ቀናት ያላነሰ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የመያዣ ንብረቱን በሐራጅ ለመሸጥና ባለቤትነቱንም ለገገዢርው ለማዛወር ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል ከአዋጁ ድንጋጌዎችም መረዳት የሜቻለው አበዳሪው ባንክ በዋስትና የያዛቸውን ንብረቶች የብድር ገንዘቡ ካልተመለሰለት ያለማንም ጣልቃገብነት አግባብነት ያላቸውን የሕጉን ድንጋጌዎች በመከተል በሐራጅ ሸጦ ለዕዳው ክፍያ ማዋል እንደሚችል እና በአሻሻጡ ሂደት ባንኩ ሕጉን ባለመከተል የፈጸመው ስህተት ቢኖርና በዚህም በባለዕዳው ላይ ጉዳት ቢደርስ ለዚህ ጉዳት ባንኩ ለባዕዳው ካሣ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት መሆኑን ነው በሕጉ ላይ የተቀመጡትም ዝርዝር ድንጋጌዎች ዓላማም በአዋጁ መግቢያ ኮጠ ላይ በግልጽ እንደተመለከተው ባንኮች የሚሰጧቸውን ብድሮች በተቀላጠፈ አኳን ለመሰብሰብ እንዲችሉ ነው ከዚህ ጋር በተያያዘም አዋጁን ለማስፈጸም እንዲረዳ አመልካች የፎርክሎሉዣር መመሪያ ለማውጣት እንዲችል ሥልጣን የተሰጠው ሲሆን በዚሁ መሠረትም አመልካች ባወጣው የፎርክሎዝዢር መመሪያ ተበዳሪው በገባው የብድር ውል መሠረት ሁለት ተከታታይ ክፍያዎችን ወይም ከአጠቃላይ ብድሩ ዐኛ ካልከፈለ አበዳሪው ባንክ የፎርክሎዝዢር ውሣኔ እንደሚሰጥ ከዚህ በኋላም ተበዳሪው ከባንኩ የሚፈለግበትን ዕዳ በዐ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ እንዲከፍል ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጠው በዚህ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ከባለዕዳው የሚፈለገው ዕዳ ሳይከፈል ከቀረ ባንኩ የመያዣ ንብረቱን እንደሚይዝ መያዣ ሰጭው ንብረቱን ለማስረከብ ፈቃደኛ ካልሆነ ከሬጅስትራርና ከፖሊስ ጋር በመተባበር ንብረቱን በኃይል እንደሚይዝ ንብረቱ ከተያዘም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በባንኩ ባለሙያዎች አማካይነት እንደሚገመትና ከዚያም በ ቀናት ጊዜ ውስጥ የሐራጅ ማስታወቂያ ወጥቶ ንብረቱ በሐራጅ እንደሚሸጥ ተመልክቷል የተያዘውም ጉዳይ ከአዋጁ ከመመሪያውና እንደዚሁም ግራ ቀኙ ካደረጉት ውል አንፃር ሲታይ ተጠሪዎች ለሁለት ተከታታይ ጊዜ የብድር ክፍያ ማቋረጣቸው የተረጋገጠ ሲሆን አመልካች በአዋጁ በመመሪያውና በውሉ ባለበት ግዴታ መሠረትም የሠላሳ ቀን ማስጠንቀቂያ ለተጠሪዎች መሰጠቱ በማስረጃ መረጋገጡን ይህ ችሎት ለመገንዘብ ችሏል አመልካች ለተጠሪዎች የዐ ቀን ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ዕዳው ሳይከፈል በመቅረቱ በመያዣ የያዘውን ንብረት የተረከበ ሲሆን ይህም ከላይ እንደተመለከተው የፎርክሎዣር መመሪያው የሚፈቅድለት ከመሆኑም በላይ ተጠሪዎችም በገቡት የውል ግዴታ ዕዳው በከፊል ወይንም በሙሉ ሳይከፈል ቢቀር የሰላሣ ቀን ማስጠንቀቂያ ከተሰጠ በኋላ ንብረቱ ሊሸጥ እንደሚችል በውል ስምምነታቸውን የሰጡ በመሆኑ የአመልካች አድራጎት በአዋጁ በመመሪያውና በውሉ የተደገፈ ስለሆነ ሕገወጥ ነው የሚያሰኝ አይሆንም አመልካች የመያዣ ንብረቱን ለመያዝ ሲዘጋጅ ተጠሪዎች ቀርበው ንብረቱን ለማስረከብ ፈቃደኛ እንዳልነበሩም በማስረጃ ተረጋግጧል እንዲህ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ አመልካች የሚመለከታቸው አካላት እንዲገኙ በማድረግ ንብረቱን በኃይል ለመያዝ እንደሚችል የፎርክሎዢዥር መመሪያው ሥልጣን የሚሰጠው ስለሆነ ተጠሪዎች በመያዣ የተያዘውን ንብረት ለአመልካች ለማስረከብና ክስ ያቀረቡባቸውንም የተለያዩ ንብረቶች ቀርበው ለመረከብ ፈቃደኛ ካልሆኑ እነዚህ ንብረቶች ተመዝግበው በንግድ መደብሮቹ ውስጥ እንዳሉ መታሸጋቸው ስለማይቀር ንብረቶቹን ከአመልካች ጠይቀው መውሰድ ከሚችሉ በስተቀር የዋጋ ግምታቸው እንዲከፈላቸው እንደዚሁም የንግድ መደብሩ በመታሸጉ ምክንያት ተቋርጦብናል የሚሉት ጥቅም እንዲከፈላቸው መጠየቃቸው ከእራሳቸው ተግባር የመነጨ በመሆኑና አመልካችም የአዋጁን ድንጋጌዎች በመተላለፍ የፈጸመው ተግባር ባለመሆኑ በዚህ ረገድ አመልካች ኃላፊ ነው ተብሎ በበታች ፍቤቶች መወሰኑ አግባብነት ያለው ሆኖ አልተገኘም በሌላ በኩልም አመልካች የተረከበው የተጠሪዎች ቤት የዋጋ ግምት ብር ዐ ሦስት መቶ አስር ሺህ እንደሆነ በተጠሪዎች በኩል የቀረበውን የዋጋ ግምት አስመልክቶ አመልካች ግምቱን በመቃወም ያልተከራከረ ስለሆነና ቤቱን ከተረከበ ጊዜ ጀምሮም ብድሩ እንደተከፈለ ሊቆጠር ስለሚችል የቤቱ ግምትና ከተጠሪዎች በቀሪነት የሚፈለገው የብድር ፅዳ ተቀናንሶ በልዩነት ከአመልካች የሚፈለገውን ብር ዐ አንድ መቶ ሠላሳ አራት ሺህ አምስት መቶ ሁለት ብር ከአርባ ሶስት ለተጠሪዎች እንዲከፍል በሥር ፍቤቶች የተሰጠው ውሣኔ የሕግ ስህተት ያልተፈጸመበት ስለሆነ አመልካች በዚህ ረገድ ያቀረበው ቅሬታ ተቀባይነት ያለው ሆኖ አልተገኘም ውሣኔ የምሥራቅ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በዚህ ጉዳይ በመጋቢት ቀን ዓም በዋለው ችሉት የንብረቶቹን የዋጋ ግምትና የንግድ መደብሮቹ በመታሸጋቸው ምክንያት በተጠሪዎች ላይ ደርሷል የተባለን ኪሣራ በድምሩ ብር ዐ ሶስት መቶ ሀምሳ ሰባት ነዓ ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና ብር አመልካች ለተጠሪዎች ሊከፍል ይገባል በማለት የሰጠው ውሣኔ እንደዚሁም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ዐ በሰኔ ቀን ዓም በዚህ ረገድ የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት የሰጠው ውሣኔ የሚነቀፍ አይደለም በማለት የሰጠው ትዕዛዝ አመልካች የአዋጁን ድንጋጌዎችንም ሆነ የአፈፃፀም መምሪያውን ባልተላለፈበት ሁኔታ ስለሆነ ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ስለተገኘ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል አመልካች የተጠሪዎችን የንግድ መደብር ተረክቦ ያሸገው አዋጁና መመሪያው የሚፈቅድለት በመሆኑ ስለሆነ በንግድ መደብሩ ውስጥ ያሉትን ንብረቶች ለተጠሪዎች ከሚያስረክብ በስተቀር የንብረቶቹን የዋጋ ግምትም ሆነ የተቋረጠ ገቢ ሊከፍል ስለማይገባ አይከፍልም ተብሎ ተወስኗል አመልካች በተረከበው ቤትና በብድሩ ገንዘብ መካከል ያለውን ብር ዐ አንድ መቶ ሠላሣ አራት ሺህ አምስት መቶ ሁለት ብር ከአርባ ሶስት ሳንቲም ለተጠሪዎች እንዲከፍል መወሰኑ በአግባቡ ስለሆነ ይህንነ ገንዘብ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ተከፍሎ አስካለቀ ድረስ ከሚታሰብ ዘጠኝ በመቶ ወለድ ጋር እንደዚሁም የጠበቃ አበል በዚሁ ልክ ዐ አሥር በመቶ ጨምሮ ለተጠሪዎች ይክፈል በማለት ተወስኗል መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሠ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሰ ታፈሠ ይርጋ አመልካች የኢትልማት ባንክ ነፈጅ አዲስ ወልዴ ተጠሪ የኢትንግድ ባንክ ነፈጅ ቀረቡ ፍርድ በዚህ መዝገብ የተያዘው ጉዳይ በመያዣ በተሠጠ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለን የቀዳሚነት መብት የሚመለከት ነው የአሁኑ ተጠሪ በሥር ፍቤት የአፈፃፀም ባለዕዳ ከሆኑት ግለሠብ ጋር በነበረው የአፈፃፀም ክርክር አመልካች በፍሥሥህቁ መሠረት መቃወሚያ በማቅረቡ ነው ክርክሩ የጀመረው አመልካች ለጎጂ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረበው አቤቱታ በአፈፃፀም በሃራጅ እንዲሸጥ የታዘዘው ንብረት አመልካች ለአፈፃፀም ባለዕዳው ብር አንድ መቶ አስራ ስምንት ሺህ አምስት መቶ ሲያበድር በመያዣ የያዘው በመሆኑ መያዣውም ቀድሞ የተመዘገበ ስለሆነ በንብረቱ ላይ የቅድሚያ መብት ያለው በመሆኑ ሐራጁ እንዲሰረዝለት ጠይቋል ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ ክርክር የተነሣበትን ንብረት በመያዣ የያዘውና የቀዳሚነት መብት ያለው ተጠሪ ነው ሲል የአመልካችን ክርክር ውድቅ አድርጓል ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤትም በፍሥሥህቁ መሠረት ይግባኙን ሠርዞታል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ነው ይህ ችሎትም ክርክር የተነሣበት ንብረት ላይ የቀዳሚነት መብት ያለው ማን አንደሆነ ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ አድርጓል ግራ ቀኙም ክርክራቸውን በጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን ይህ ችሎትም መዝገቡን እንደሚከተለው መርምራል ከመዝገቡ ሂደት እንደተረዳነው አመልካች የሚከራከረው ክርክር የተነሣበትን የእህል መጋዘን ለሰጠው ብድር በመያዣ መያዙን እና መያዣውንም መጋቢት ቀን ዓም ያስመዘገበ መሆኑን ነው በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ የአመልካች መያዣ አግባብ ባለው አካል ፊት ያልተመዘገበና በሠነዱ ላይ የሰፈረው ማህተምም በወቅቱ ሥራ ላይ ያልነበረና አጠራጣሪ መሆኑንተጠሪ ግን ከአመልካች በፊት መያዣውን ሰኔ ቀን ዓም በማስመዝገቡ የቀዳሚነት መብት ያለው መሆኑን ተከራክሯል ይህ ችሎትም ቀዳሚ መብት ያለው ማነው የሚለውን እንደሚከተለው መርምሯል እንድ የማይንቀሣቀስ ንብረት ለብዙ ዕዳዎች በመያዣ ሊሠጥ የሚችል መሆኑ በፍህቁ ሥር ተመልክቷል ነገር ግን አንድ የማይንቀሣቀስ ንብረት በመያዣ ከተሰጠ በመብቱ ለመገልገል መያዣው አግባብ ባለው አካል መመዝገብ እንዳለበት የፍህቁ ያስገነዝባል ከሌሎች የመያዣ መብት ካላቸው ባለገንዘቦች በፊትም የቀዳሚነት መብት ለማግኘት መያዣውን ከሌሎቹ በፊት ቀድሞ ማስመዝገብ ይገባል የፍህቁ ይመለከቷል በተያዘው ጉዳይ አመልካች መያዣውን ከተጠሪ በፊት ቀድሞ ማስመዝገቡን ገልጦ የቀዳሚነት መብት ያለው መሆኑን ተከራክሯል ከመዝገቡም እንዳየነው አመልካች የመያዣ ውሉን በቦረና አስተዳደር አካባቢ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ የነገሌ ከተማ አስተዳደር ፅቤት የመያዣ ውሉን ተቀብሎ ማህተሙን በማኖር መመዝገቡን አረጋግጧል አመልካች መያዣው የተመዘገበው መጋቢት ቀን ዓም ነው በማለት ባቀረበው ክርክር ላይ የሥር ፍቤት ያለው ነገር የለም ፍቤቱ የአመልካችን ጥያቄ ውድቅ ያደረገው መያዣው ተመዝግቧል በተባለበት ወቅት ሠነዱ ላይ ያረፈው ማህተም አጠራጣሪ ነው በሚል ብቻ ነው እዚህ መደምደሚያ ላይ የደረሥውም በወቅቱ ክልሉ የሚሠራው በኦሮሚኛ ሆኖ ይህ ማህተም እንዴት በአማሪኛ ሊሆን ቻለ ከሚል ጥርጣሬ ብቻ ነው የማህተሙን ትክክለኛነት ወይም ሐሠተኛነት በተጨባጭ ያረጋገጠው ነገር የለም ማህተሙ የአስተዳደር ፅቤቱ አይደለም የሚባል ከሆነ ተቃራኒ ማስረጃ ሊቀርብ ይገባ ነበር ተቃራኒ ማስረጃ ሣይቀርብና የማህተሙ ሀሰተኛ መሆን ሣይረጋገጥ በጥርጣሬ ብቻ የተደረሰበት መደምደሚያ ህጋዊ መሠረት የለውም አንግዲህ የማይንቀሣቀስ ንብረት መያዣ ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው መመዝገብ አስፈላጊ በመሆኑ የፍህቁ ን ይመለከቷል አመልካችም ሆነ ተጠሪ መያዣቸውን በመዝጋቢው አካል አስመዝግበዋል በአንድ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ብዙ ገንዘብ ጠያቂዎች የመያዣ መብት አስመዝግበው እንደሆነ ደግሞ የቀደምትነት መብታቸውን የሚሠሩበት ተራ የሚወሠነው መብታቸውን ያስመዘገቡበትን ቀን በመከተል እንደሆነ በፍህቁ ተመልክቷል በተያዘው ጉዳይ አመልካች መያዣውን መጋቢት ቀን ዓምያስመዘገበ ሲሆን ተጠሪ ደግሞ ሰኔ ቀን ዓም ነው ያስመዘገበው ይህ ከሆነ ደግሞ የቀደምትነት መብት ያለው ቀድሞ መብቱን ያስመዘገበው አመልካች ነው በሌላ በኩል ግን አመልካች እየጠየቀ ያለው የሐራጅ ሽያጩ እንዲሠረዝ ነው በማይንቀሣቀስ ንብረት የመያዣ መብት የተሠጠው ገንዘብ ጠያቂ ንብረቱ በሌሎች ባለገንዘቦች የተያዘ እንደሆነ ከንብረቱ ዋጋ ላይ የሚፈልገው ገንዘብ ከሌሎቹ ገንዘብ ጠያቂዎች ለርሱ በቀዳሚነት እንዲከፈለው ከመጠየቅ ያለፈ መብት የለውም የፍህቁ ይመለከቷል የማይንቀሣቀሠው ንብረት ክፍያቸው በደረሠ ማንኛውም ባለገንዘቦች ሊያዝና ሊሰጥ የሚችል ሲሆን የቀዳሚ መብት ያለው ባለገንዘብ ከሺያጩ ገንዘብ የርሱ እዳ በቅድሚያ እንዲከፈለው ከመጠየቅ በቀር ሺያጩ እንዳይከናወን ሊቃወም አይችልም በመሆኑም አመልካች ምንም እንኳን መያዣውን ከተጠሪው በፊት በማስመዝገቡ ቀዳሚ መብት ቢኖረውም ይህ መብቱ ከሺያጩ ከተገኘው ገንዘብ የአርሱ አዳ ቀድሞ እንዲከፈለው ከማድረግ በቀር ሺያጩ እንዲሰረዝ ሊጠይቅ አይችልም በአጠቃላይ የሥር ፍቤት ማህተሙ አጠራጣሪ ነው በሚል ብቻ የአመልካችን ክርክር ውድቅ ማድረጉ መሠረታዊ የህግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የጉጂ ዞን ከፍተኛው ፍቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም የሠጠው ብይን እና የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ሚያዚያ ቀን ዓም የሠጠው ትዕዛዝ ተሽሯል ክርክር የተነሣበት የመያዣ ንብረት በሐራጅ ተሸጦ ከሚገኘው ገንዘብ አመልካች የሚፈልገው እዳ ተከፍሎት ተራፊ ገንዘብ ካለ ለተጠሪ እንዲከፈል ተወስኗል መጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ መስፍን ዕቁበዮናስ ተሻገር ገስላሴ አብዱራሂም አህመድ አመልካች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ ቀረቡ ተጠሪ ኛ አቶ ዋለልኝ አያሌው ቀረቡ ኛ ወሮ ለመች ላቀው ቀረቡ መዝገቡን መርምረን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የአማራ ብሔራዊ ክልልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍቤት በፍብይመቁጥር ታህሳስ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ ሊታረምልኝ ይገባል በማለት ዝርዝር ቅሬታ በማቅረባቸው ነው የአሁን ኛ ተጠሪ የፍርድ ባለመብት ኛ ተጠሪ ባለዕዳ ሆነው በምዕጐጃ መስተዳደር ዞን ከፍተኛው ፍቤት በአፈፃፀም መቁ በሆነው መዝገብ ላይ የአፈፃፀም ክሱ እየታየ ባለበት ጊዜ የአሁኑ አመልካች የፍብሥሥሕቁ ን መሠረት በማድረግ ጣልቃ ገብቶ ተከራክሯል ጣልቃ ለመግባት ያቀረበውም ምክንያት የፍርድ ባለመብት እንዲረከብ ትዕዛዝ የተሰጠበትን የባለዕዳዋን ንብረት አስቀድሜ ያስከበርኩት ስለሆነ ቤቱን ባለመብቱ አንዲረከብና ስመ ንብረትነቱም እንዲዛወርለት የተሰጠው ትዕዛዝ ቀሪ አንዲሆንልን ይታዘዝልን የሚል ነው በማስረጃነትም በዚሁ ንብረት ላይ የማስከበሪያ ትዕዛዝ ጥቅምት ቀን ዓም ያሰጠበት መሆኑንና ባለዕዳ በተባለችው በአሁን ኛ ተጠሪ ላይ በዋስትና ግዴታ ምክንያት ከሶ ፍርድ ያሰጠበት መሆኑን የሚገልፅ የሰነድ ማስረጃ አቅርቧል በዚሁ አቤቱታ ላይ መልስ የተሰጠበት መሆኑን የሥር ፍቤት ከገለፀ በኋላ የግራ ቀኙን ክርክር ተመልክቶ ምንም እንኳን የአሁን አመልካች በዚሁ ንብረት ላይ የማስክበሪያ ትዕዛዝ ያሰጠበት መሆኑ ቢረጋገጥም ማስከበር ብቻውን የቀዳሚነትን መብት የሚያሰጥ ሆኖ አላገኘነውም ስለሆነም የቀረበው የአፈፃፀም ክስ ይቋረጥልኝ አቤቱታ ውድቅ ነው በማለት በይኗል በዚህም ብይን የአሁን አመልካች ቅር ተሰኝቶ የይግባኝ አቤቱታ ለክልል ጠቅላይ ፍቤት አቅርቧል ፍቤቱም በጉዳዩ ላይ ግራ ቀኙን አከራክሮ ታህሳስ ቀን ዓም በዋለው ችሎት በግራ ቀኙ መካከል የተነሳው አከራካሪ ነጥብ ክርክር ባስነሳው ቤት ላይ የቀዳሚነት መብት ያለው ወገን ማን ነው። የሚለው በመሆኑ ይህንኑ ጭብጥ ይዘን አቤቱታውን እንደሚከተለው መርምረናል አመልካችና ኛ ተጠሪ ባቋቋሙት የቤት ኪራይ ውል አንቀጽ እና ላይ ተከራይ የተከራየውን ቤት ያለአከራይ ፈቃድ ለሌላ ወገን ቢያስተላልፍ ውሉ እንደሚሰረዝ ተመልክቷል ተጠሪዎች አጥብቀው የሚከራከሩት ኛ ተጠሪ በሕክምና ምክንያት ወደ ውጭ አገር ሲሄዱ ንብረታቸውን እንዲያስተዳድሩላቸው ለኛ ተጠሪ ውክልና ሰጥተዋል እንደዚሁም ኛ ተጠሪ ከአዲስ አበባ ውጭ ሲሄዱ በበኩላቸው ለኛ ተጠሪ ውክልና የሰጡ በመሆኑ ድርጊቱ ውሉን የሚጻረር ባለመሆኑ ውሉ ሊሰረዝ አይገባም በማለት ነው በእርግጥ ማንም ሰው ከባለቤትነት መብትም ይሁን ከይዞታ መብት በመነጨ በሚያዝበት ንብረት ላይ ውክልና የመስጠት ከሕግ የመነጨ መብት እንዳለው የሚያከራክር አይሆንም በተያዘው ጉዳይ ኛ ተጠሪ እንደተባለው ለሕክምና ከኢትዮጵያ ውጭ ሲሄዱ ለኛ ተጠሪ ውክልና የሰጡ ቢሆንም ኛ ተጠሪ ረዘም ላለ ጊዜ በቤቱ ውስጥ መኖራቸው ሲታይ ከዚህም አልፎ እሳቸውም በበኩላቸው ኛ ተጠሪን መወከላቸው እንደዚሁም ለሕክምና ወደ ውጭ አገር ሄደዋል የተባሉት ኛ ተጠሪ ለረጅም ጊዜ ሳይመለሱ መቅረታቸው እነዚህ ሁኔታዎች በድምሩ ሲታዩ ኛ ተጠሪ ከአመልካች በኪራይ የያዙትን ቤት ለኛ ተጠሪ ማስተላለፋቸውን የሚያረጋግጡ ፍሬ ነገሮች ናቸው ይህ ፍሬ ነገር ከተረጋገጠ ደግሞ ግራ ቀኙ ባቋቋሙት የቤት ኪራይ ውል ላይ ከላይ እንደተመለከተው ተከራይ ያለአከራይ ፈቃድ በኪራይ የያዘውን ቤት ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ እንደማይችል የተሰማሙትን የሚጻረር እንደሆነ የሚያስገነዝብ ነው የውል ይሰረዝልኝ አቤቱታም ለፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ ዳኞች ውሉ እንዲሰረዝ ከመወሰናቸው በፊት የተዋዋዮችን ጥቅምና በቅን ልቦና የሚያስፈልገውን መሠረት ማጤን እንዳለባቸው እንደዚሁም ዓይነተኛ የውል መጣስ ተግባር ኪከበዐጠፀበፎ ከልርከ ርዐበህርሀ ካልተፈጸመ ውሉ ይሰረዝ ሊሉ እንደማይችሉ በፍብሕቁ ላይ የተመለከተ እንደመሆኑ መጠን ከዚህም አንጻር ሁኔታው ሲታይ ኛ ተጠሪ በኪራይ የያዙትን ቤት በውክልና ሽፋን ለሌላ ማስተላለፋቸውን መገንዘብ ስለተቻለና ይህም ቅን ልቦና የጎደለው መሆኑን የሚሜያሳይ ከአመልካች ጥቅምም አኳያ ሲታይ በአዋጅ የተቋቋመው የመኖሪያ ቤት ችግርን የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት ቤት ለተቸገሩ ሰዎች የኪራይ መብት እንዲያገኙ ማድረግ በመሆኑ በዚህም ጉዳይ ውሉ እንዲሰረዝ የጠየቀው ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት እንደሆነ የሚታመን ከመሆኑም በላይ የተከራዩ ኛ ተጠሪም ተግባር ዓይነተኛ የሆነ የውል መጣስ ተግባር መሆኑን መገንዘብ የተቻለ በመሆኑ የበታች ፍቤቶቹ ውሉ ሊሰረዝ አይገባም በማለት የሰጡት ውሳኔ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሳኔ የፌመደፍቤት በመቁ በግንቦት ቀን ዓም በሰጠው ውሳኔና የፌዴከፍቤት በመቁ በጥር ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸው ሆነው ስለተገኙ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽረዋል በአመልካችና በኛ ተጠሪ መካከል በሰኔ ቀን ዓም የተደረገው የቤት ኪራይ ውል በኛ ተጠሪ በኩል ዓይነተኛ የሆነ የውል መጣስ ተግባር የተፈጸመበት ስለሆነ ሊሰረዝ ይገባል በማለት ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሳራ ይቻቻሌ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልቧል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞችፁ ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ አመልካች የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ነፈጅ አያሌው ሊበን ተጠሪ የአቶ ገሕይወት ከበዶም ወራሾች ሰዎች አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበው ጉዳይ ውዝፍ የቤት ኪራይ ክፍያን የተመለከተ ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው የአሁኑ አመልካች በወረዳ ቀበሌ ዐ የሚገኘውንና ቁጥሩ ዐዐ የሆነውን ቤት በብር ክንድ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ዘጠኝ ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ ውል ተከራይተው ከመስከረም ወር ዓም እስከ መጋቢት ወር ዓም ያለውን የኪራይ ሂሣብ ስላልከፈሉ ይህንኑ የኪራይ ሂሣብ መቀጫ ዐ አና የውፃ አገልግሎት ሂሣብ በድምሩ ብር አንድ መቶ ሰባ ስድስት ሺህ አምስት መቶ ስልሳ አራት ከነወጪና ኪሣራው ይክፈሉ በማለት ለፌመደፍቤት በመሠረተው ክስ ነው የአሁን ተጠሪዎች በሰጡት መልስ በማስረጃነት የቀረበው የኪራይ ውል በአመልካች ያልተፈረመና በሁለት ምስክሮች ፊት ያልተረጋገጠ ስለሆነ ፈራሽ ነው የአመልካች ድርጅት የወቅቱ የደንበኞች አገልግሎት ኃላፊ በብር ዐ አምስት መቶ አስር ሂሣብ መከራየት እንደምንችል ገልፀውልን የሂሣብ ክፍሉ ሊቀበሉን ባለመፈለጋቸው የኪራዩን ሂሣብ ብር ዐዐዐ አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ በአመልካች የሂሣብ ቁጥር ገቢ አድርገናል ስለዚህ ልንከፍል የሚገባን ተመሣሣይ ቤት ለኢትዮጵያውያን በሚከራይበት ዋጋ ተሰልቶ በባንክ የተከፈለው ገንዘብም ተቀንሶ ነው በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም የቀረበው የውል ሰነድ በተከራይ የተፈረመ በአከራይ ግን ያልተፈረመ በመሆኑ የውሉ ረቂቅ አንጂ ውል አይደለም ሆኖም ግን ተጠሪዎች ቤቱን ያለውል በመያዝ ሲጠቀሙበት በመቆየታቸው ያለአግባብ የበለፀገበትን ከመስከረም ዓም እስከ መጋቢት ዓም ድረስ ያለውን ሂሣብ ተጠሪዎች ራሳቸው ባመኑት በብር ዐ አምስት መቶ አስር ሒሣብ ተሰልቶ ከሚመጣው ብር ዐዐዐ ሃያ ስምንት ሺህ ላይ ተከሣሽ የከፈሉት ብር ዐዐዐ አሥራ አምስት ሺህ ተቀንሶ የሚቀረውን ብር ይዐ አሥራ ሁለት ሺህ ስድስት መቶ ዛምሳ ለአመልካች ይክፈሉ ቅጣቱን በተመለከተም በግራ ቀኙ መካከል ውል በሌለበት ሁኔታ ተጠሪዎች ቅጣት እንዲከፍሉ አይገደዱም የተጠየቀውን የውፃ ሂሣብ ግን ተጠሪዎች መክፈል እንደማይገባቸው ስላላስረዱ ብር ዐዐ አንድ ሺህ አንድ መቶ ለአመልካች ይክፈሉ በማለት ወስኗል የአሁን አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት የይግባኝ ቅሬታውን ለፌከፍቤት ቢያቀርብም ፍቤቱ ቅሬታውን ባለመቀበል ውሣኔውን አጽንቶታል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንን ውሣኔ ለማስለወጥ ነው ችሎቱም በአቤቱታው መነሻነት የስር ፍቤቶችን ውሣኔ አግባብ ካለው ሕግ ጋር አገናዝቦ በመመርመር የኪራይ ውል ነው ተብሎ በአመልካች በቀረበው ሰነድ ላይ አከራዩ አልፈረመበትም ተብሎ በግራ ቀኙ መካከል የኪራይ ውል የለም በማለት የተወሰነው በአግባቡ መሆን አለመሆነ ተጣርቶ ሊወሰን የሚገባው ነጥብ ሆኖ ስላገኘው ጉዳዩ ለሰበር አንዲቀርብ በማድረግ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቷል መዝገቡን እንደመረመርነው የስር ፍቤት በግራ ቀኙ መካከል ተደርጓል የተባለው ውል ረቂቅ እንጂ ውል አይደለም ለማለት የበቃው በማስረጃነት ባቀረበው ሰነድ ላይ አከራይና ምስክሮች አልፈረሙበትም ከሚል መንደርደሪያ በመነሳት መሆኑን ከመዝገቡ ተረድተናል በመሠረቱ በሁለት ተዋዋይ ወገኖች በማናቸውም ሁኔታ የተደረገ ስምምነት ውል ለማድረግ በቂ አንደሆነ የፍብሕቁ ይደነግጋል ከዚህ ድንጋጌ በግልጽ መገንዘብ እንደሚቻለው በሁለት ተዋዋይ ወገኖች መካከል የሚፀና ወይም ሕጋዊ ውጤት ያለው ውል ለመመስረት በሁለቱም መካከል ስምምነት መኖሩ ብቻ በቂ ነው ስለዚህ ከኢትዮጵያ የውል ሕግ መሠረታዊ መርህ አንፃር በሕግ ወይም በተዋዋዮች በራሳቸው የተለየ ፎርም ካልተፈለገ በስተቀር ውልን ለመመስረት በተዋዋዮች መካከል ስምምነት መኖሩ ብቻ በቂ ነው በመሆኑም አንድ ውል ሕጉ ያስቀመጠውን የፎርም መስፈርት አያሟላም ተብሎ ውድቅ ሊደረግ የሚችለው ይህንን ውል የሚመለከት በግልጽ የተቀመጠና የተለየ የአፃፃፍ ሥርዓት ፎርም ኖሮ ተዋዋዮች ይህንን ፎረም ሳይከተሉ ከቀሩ ወይም በተዋዋዮች ምርጫና ፍላጎት ስምምነቱ በጽሁፍ ከመሆኑ በተጨማሪ ሌሎቹንም ፎርማሊቲዎች እንዲሟሉ መፈለጋቸው በጽሁፉ በራሱ ወይም በሌላ መልክ ተገልፆ ሲረጋጥና ውሉም ይህንን በመከተል የተደረገ ካልሆነ ብቻ ነው ስለሆነም የውልን አፃፃፍ ፎርምን የሚመለከትው የፍብሕግ ክፍል አንቀጽ ዐ የኪራይ ውል የተለየ ፎርም መከተል እንዳለበት የሚያስገድድ ድንጋጌ የለውም በዚህም ምክንያት ሕጉ የኪራይ ውልን በጽሁፍ እንዲሆን የሚያዝ አስገዳጅ ድንጋጌ ባላስቀመጠበትና ተዋዋዮች ውሉ በጽሁፍ እንዲሆን የተስማሙ መሆናቸው ባልተረጋገጠበት ሁኔታ የስር ፍቤት ውሉ የሕጉን ፎርማሊቲ ያላሟላ ስለሆነ ፈራሽ ነው ሲል የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ አግኝተነዋል በተጨማሪም የፍብሕግ በተለይ የኪራይ ውልን በሚመለከተው ልዩ ድንጋጌው በአንቀጽ ላይ የኪራዩ ውል መከናወን ጀምሮ እንደሆነ የውሉን መኖር በምስክሮች ወይም በግምት አስተያየት ማስረዳት አንደሚቻል ደንግጓል በመሆኑም ክርክር የተነሳበት የኪራይ ውል መከናወን የጀመረ መሆኑ ያላከራከረ ጉዳይ ከመሆኑ ባሻገር አመልካች የዚህን ውል መኖር በምስክር ወይም በግምት አስተያየት ከማስረዳት ይልቅ ተከራይ የፈረመበትን ማስረጃ በማቅረብ ያስረዳ ሲሆን ፍቤቱ ይህ ማስረጃ ሕጉ በቂ ናቸው ከሚላቸው የማስረጃ አይነቶች የተሻለ መሆኑን ከግምት ውስጥ ባለማስገባት በግራ ቀኙ መካከል የኪራይ ውል የለም ሲል መወሰኑ መሠረታዊ የሕግ ሥህተት ነው ብለናል ውሣኔ የፌመደፍቤት በመዝገብ ቁ ዐዐ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ እና የፌከፍቤት በመዝገብ ቁ ዐ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽረዋል በግራ ቀኙ መካከል የኪራይ ውል መኖሩን በመገንዘብ አመልካች በስር ባቀረባቸው ጥያቄዎች ላይ ግራ ቀኙን አከራክሮ እንዲወስን ጉዳዩ ለፌመደፍቤት መሠረት ለፌመደፍቤት ተመልሶለታል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራቸውን ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር መቁ ዐ ጥር ዐ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረ ፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነፈጅ አያሌው ሊበን ተጠሪ አቶ ታደለ አበበ ቀረቡ ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉደይ የተጀመረው የፌመደፍቤት ነው አመልካች በተጠሪ ላይ በመሠረተው ክስ ተጠሪ በወረዳ ቀበሌ ዐ ክልል ውስጥ ቁጥር የሆነውን ቤት ተከራይተው ያልከፈሉት ውዝፍ ኪራይ አና የውፃ ክፍያ ያለባቸው ከመሆኑም በተጨማሪ ቤት መስራታቸው ስለተረጋገጠ የኪራይ ውሉ ፈርሶ ቤቱን እንዲያስረክቡ እና ውዝፍ ኪራይ እና የውሀ ሂሣብ እንዲከፍሉ ይወሰንልን በማለት ጠይቋል የስር ፍቤትም የግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ ባልተወሰነ ጊዜ የተደረገ የኪራይ ውል ሊፈርስ የሚችለው አከራዩ ለተከራዩ የ ወር ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሲሆን አመልካች ግን ይህን ስላላደረገ ውሉ ፈርሶ ቤቱን ለመረከብ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም ተጠሪ ያለባቸው ቀሪ ዕዳ ብር ዐ አራት መቶ አርባ ሁለት ከፃያ ስለሆነ ይህንን ገንዘብ ለአመልካች ይክፈሉ በማለት ወስኗል በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት አመልካች ለፌከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ ያቀረበ ቢሆንም ፍቤቱ የመጀመሪያውን ውሣኔ አጽንቷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታም የቀረበው ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ሊሻር ይገባዋል በሜል ነው ከመዝገቡ እንደተረዳነው አመልካች የኪራይ ውሉ እአንዲፈርስለት የጠየቀው ተጠሪ ግዴታቸውን አክብረው የኪራይ ገንዘቡን ባለመክፈላቸውና ቤት የሠሩ በመሆኑ ሲሆን ቤት ባይኖራቸውም እንኳን በፍህቁ መሠረት የኪራይ ውል በአንድ ወገን ብቻ ሊፈርስ እንደሚችልም ተከራክሯል ተጠሪ በበኩላቸው ተጠራቅሟል የተባለውን የቤት ኪራይ አጠናቀው በመክፈላቸው እና ማስጠንቀቂያ ያልተሰጣቸው በመሆኑ እንዲሁም ግዴታቸውን መፈፀም ባይችሉ ወደ ሌላ ቤት አንዲዛወሩ ከሚደረግ በቀር ቤቱን እንዲለቁ ሊጠየቁ እንደማይገባ ተከራክረዋል ችሎቱም የግራ ቀኙን ክርክር እና የሥር ፍቤቶችን ውሣኔ አግባብነት ካላቸው የቤትን ኪራይ ከሚመለከቱ ድንጋጌዎች አኳያ መርምሯል በአመልካችና በተጠሪ መሃከል የተደረገው የኪራይ ውል ላልተወሰነ ጊዜ የተደረገ መሆኑን ተገንዝበናል ላልተወሰነ ጊዜ የተደረገ የኪራይ ውል ደግሞ ለተከራዩ በሚሰጥ ማስታወቂያ በማንኛውም ጊዜ ሊቋረጥ የሚችል መሆኑ በፍሕቁ ሥር ተመልክቷል አከራዩ በፈለገ ጊዜ ለተከራዩ ማስታወቂያ በመስጠት የኪራይ ውሉን ሊያፈርስ መብት አለው ከፍ ሲል እንደተባለው አከራዩ ውሉን ለማፍረስ ማስታወቂያ ለተከራዩ መስጠት እንደሚያስፈልግው የተመለከተ ቢሆንም ማስታወቂያ መስጠት ግን ውሉን ለማፍረስ አስገዳጅ የሆነ ቅድመ ሁኔታ አይደለም ተከራዩ ማስጠንቀቂያ ባለማግኘቱ የደረሰበት ጉዳት ወይ ኪሣራ ካለ ይህንነ ከመጠየቅ በቀር ውሉ ሊፈርስ አይችልም በማለት ለመከራከር መብት አይሰጠውም በተያዘው ጉዳይም በአመልካችና በተጠሪ መፃሣከል የተደረገው ውል ላልተወሰነ ጊዜ የሚቆይ በመሆኑ አመልካች በማንኛውም ጊዜ ማስታወቂያ ሰጥቶ ሊያቋርጠው ይችላል ማስታወቂያ አለመስጠቱም ከፍ ሲል እንደተገለፀው በተጠሪ ላይ ኪሣራ ያደረሰ ከሆነ ተጠሪ ይህንነ ሊጠይቁ ከሚያስችላቸው በቀር የውሉን መፍረስ አያስቀረውም ተጠሪውም በክሱ ቤቱን እንዲለቁ ከተጠየቁበት ጊዜ ጀምሮ የፌመደፍቤት ውሣኔ እስኪሰጥበት ጊዜ ድረስ እንኳን ወደ አንድ ዓመት የሚጠጋ ጊዜ አልፏል በመሆኑም ቤቱን ለመልቀቅ እንድችል ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ስላልተሰጠኝ ልለቅ አይገባም በማለት ያቀረቡት ክርክር ተቀባይነት የለውም የኪራይ ውሉ ላልተወሰነ ጊዜ የተደረገ በመሆኑ በማንኛውም ጊዜ አከራዩ ውሉን ማቋረጥ የሚችል ስለሆነ የፍሕቁ ይመለከቷል ተጠሪ የቤቱን ኪራይ ከፍዬ አጠናቅቄአለሁ ሌላ ቤት መስራቴ ቤቱን እንድለቅ አያደርገኝም የሚለው ክርክራቸው ተቀባይነት ያለው አይደለም በአጠቃላይ የሥር ፍቤት ማስጠንቀቂያ ባለመስጠቱ የኪራይ ውሉ ሊፈርስ አይገባም በማለት የደረሰበት መደምደሚያ የፍሕቁ አኳያ ሲመረመር ስህተት የተፈፀመበት ነው ውሣኔ ኛ የፌመደፍቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የኪራይ ውሉ ሊፈርስ አይገባም በማለት የሰጠው የውሣኔ ክፍልና የፌከፍቤት በመቁ በጥቅምት ቀን ዓም ይህንኑ የውሣኔ ክፍል በማጽናት የሰጠው ውሣኔ ተሽረዋል ኛ በአመልካችና በተጠሪ መዛከል በወረዳ ቀበሌ ዐ ቁጥር በሆነው ቤት ላይ የተደረገው የኪራይ ውል ፈርሷል ይህንኑ ቤት ተጠሪ ለአመልካች ያስረክቡ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰበር መቁ ሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞችቡ ዓብዱልቃድር መሐመድ አሰግድ ጋሻው ደስታ ገብሩ መስፍን ዕቁበዮናስ መድሕን ኪሮስ አመልካች ወሮ መዓዛገነት ዳሼ ተጠሪ ኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረው በፌመደፍቤት ሲሆን የአሁኑ ተጠሪ የስር ከሣሽ ነሐሴ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው የክስ ማመልከቻ የአሁኑ አመልካች የስር ተከሳሽ በአራዳ ክከተማ ቀበሌ ዐ የሚገኘው ቁጥሩ የሆነውን ቤት በማካካሻነት ነው የያዝኩት ኪራይ አልከፍልም ስላሉ ያልከፈሉትን ኪራይ እንዲከፍሉ ቤቱንም እንዲያስረክቡን ይወሰንል ሲል ክስ አቅርቧል የአሁኑ አመልካች የሥር ተከሳሽ ደግሞ ጥቅምት ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት መልስ ቤቱ በማካካሻነት መንግስት የሰጠኝ በመሆኑ መንግስት የወሰደውንና በቀበሌ አጅ የሚገኘውን ቤቴን ሳይመልስልኝ በማካካሻነት የያዝኩትን ቤት እንድመልስ የቀረበው ክስ ተገቢነት የሌለው በመሆኑ ክሱ ውድቅ ሊደረግልኝ ይገባል በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ ተከሳሽ ያለአግባብ የተያዘባቸው ቤት ካላቸው ከሰው ከሚጠይቁ በስተቀር የያዙትን የመንግስት ቤት ያለኪራይ ሊኖሩበት አይገባም ብር አስራ ሦስት ሺህ አምስት መቶ ክስ ፏ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ተከፍሉ እስካለቀበት ጊዜ ድረስ ከሚታሰብ ወለድ ጋር ለከሳሽ ይክፈሉ ቤቱንም ለከሳሽ ያስረክቡ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል አመልካች ግንቦት ቀን ዓም ያቀረቡት አቤቱታም የፌመደፍቤት በሰጠው ውሣኔና የፌከፍቤት በሰጠው ትዕዛዝ ቅር በመሰኘት ነው የአቤቱታው ቅሬታም የከተማ ቦታንና ትርፍ ቤቶችን የመንግስት ያደረገው አዋጅ በወጣ ጊዜ በመንግስት ቤት እንዳለኝ በቅጽ ተረጋግጦ አሁን የምኖርበትን የመንግስት ቤት ያለክፍያ እንድኖርበት ነሐሴ ቀን ዓም ተወስኗል። የሚሉትን ጭብጦች በመያዝ አጣርቶ መወሰን ሲገባው የማጣራት ቅድመ ሁኔታ የሚያስቀምጠውን ሜኒስቴሩ መቤት ጥቅምት ቀን ዓም የዓፈውን ደብዳቤ ቀደም ብሉ የተሰጠውን የማካካሻነት ውሣኔ የሚሽር ነው በማለት በተሳሳተ ሁኔታ በመተርጐም ማካካሻነቱ ቀሪ ሆኖአል የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሱን ተገንዝበናል የሥር ፍቤቱ በማካካሻነት በያዝሽው ቤት ምትክ መንግስት የወሰደብሸሽ ቤት ያለው በቀበሌ እጅ ከሆነ ቀበሌውን ከሰሽ ከምትጠይቂ በስተቀር ቤቴን መንግስት ሳይሰጠኝ በማካካሻነት የያዝኩትን ቤት ልለቅ አይገባም በማለት ልትከራከሪ አትችይም በማለት የሰጠው ውሣኔም ቀበሌና ኪራይ ቤቶች ሁለት የመንግስት አካላት ቢሆኑም በማካካሻነት ተያዘ የተባለው ቤት ሁለቱንም የሚያቆራኛቸው በመሆኑ በአንድ ዘንግ ቆመው በጉዳዩ መከራከር የሚገባቸው መሆኑን የሥር ፍቤት እንዳልተገነዘበው ለመረዳት ችለናል ፖያ ተደረገ የተባለው መቻቻል ወይም መካካስ አመልካች ሲያከራዩት የነበረው ቤት ውስጥ የነበሩት ተከራይ ግለሰቦችን ላለማፈናቀል ሲባል ይህ ቤት በመንግስት እጅ ሆኖ እንዲቆይ መደረጉ አመልካች ኪራይ እየከፈሉ ሲኖሩበት የነበረውን የመንግስት ቤት አመልካችዋ ኪራይ ሳይከፍሉ እንዲኖሩበት በአመልካችዋና በመንግስት ፈቃድና ስምምነት የተደረገ ነው የሚመስለው በፍብሕቁ መሠረት ተዋዋዮቹ አስቀድመው የመቻቻሉ ጉዳይ በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሚፈፀም በመግለጽ የወሰነበት ሆኖ ከተገኘ ደግሞ የውሉ መሰረዝ ወይም መፍረስ ጥያቄ ሲነሳ በፍብሕቁ መሠረት ተዋዋዮቹ ወደነበሩበት የሚመለሱበት ሁኔታ ስለሚኖር የሥር ፍቤት እነዚህን ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት ቤቱ የተያዘው በማካካሻነት መሆን ያለመሆኑን እንደዚሁም ቤቱ በማካካሻነት የተያዘው በአንድ ቤት ወይም በብዙ ቤቶች መሆን ያለመሆኑን ለማረጋገጥ እንዲቻል ቀበሌውን በጣልቃገብነት ክርክሩ ውስጥ አስገብቶና ግራ ቀኙን አከራክሮ ተገቢውን መወሰን ሲገባው ይህን መንገድ ሳይከተል ማካካሻው ለጊዜው እንዲቆም የሚለውን የከተማ ልማትና ቤት ሚኒስቴር ደብዳቤ ማካካሻነቱ ተሰርዚኳል እንደሚል አድርጐ በመተርጐም አመልካች ቤቱን ለተጠሪ እንዲያስረክቡ በማለት የሰው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትና መሻር የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የፌመደፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም ወሮ መዓዛ ገነት ዳኘ ክርክር ያስነሳውን ቤት ለኪራይ ቤቶች እንዲያስረክቡ እንደዚሁም ኪራይ ብር አስራ ሦስት ሺህ አምስት መቶ አንዲከፍሉ በማለት የሰጠው ውሣኔና የፌከፍቤት በመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽረዋል ይፃፍ ሃ ዙዘ የፌመደፍቤት የሥር ተከሳሽ የአሁኑ አመልካች የሆነውን ቤት በማካካሻነት በመያዝ ቤቱን እያከራየ ይገኛል የተባለው ቀበሌ በጣልቃ ገብነት ክርክሩ ውስጥ አንዲገባ በማድረግ ማካካሻ የተደረገላቸው የአመልካችና የመንግስት ቤቶች የትኞቹ መሆናቸውን ለመለየት እንዲቻል ግራ ቀኙን አከራክሮ የመሰለውን እንዲወስን ጉዳዩ እንዲመለስለት ብለናል ይፃፍ ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ዐ የካቲት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድህን ኪሮስ አመልካች ወሮ መዓዛ ይሕደጎ ጠበቃ ግራዝማች አወቀ አአምሮ ቀረበ ተጠሪዎች አየለ ወልዴ ቀረበ ጌታቸው ሃይለማርያም ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የኪራይ ውልን መነሻ በማድረግ የቀረበ የገንዘብ ክፍያ እና ቤት ልረከብ ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ የተጀመረው በማኀበራዊ ፍቤት ሲሆን ከሣሽ የነበረችውም አመልካች ናት አመልካች በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሠረተችው በውክልና የማስተዳድረውን ቤት በኪራይ ውል ይዘው እየተገለገሉበት ቢሆንም ኪራዩን ግን ሊከፍሉ አልቻሉም ስለዚህ የተጠራቀመውን ኪራይ ከፍለው ቤቱን ሊያስረክቡኝ ይገባል በማለት ነው የማኀበራዊ ፍቤቱም ግራ ቀኝ ወገኖችን ካከራከረ በኋላ ተከሣሾች የኪራዩን ገንዘብ ይክፈሉ በኪራዩ መቀጠል ሁለቱ ወገኖች የማይስማሙ ከሆነም የሚፈለግባቸውን ኪራይ ከፍለው ቤቱን ለከሣሽ ያስረክቡ በማለት ወስኖአል በዚህ ውሣኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤትም ክርክሩን የሰማ ሲሆን በመጨረሻም የማኀበራዊ ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም በማለት ውሣኔውን ሽራል ይግባኝ ሰሚው ፍቤትም ይህንኑ አጽንቷል አቤቱታው የቀረበው በዚህ ላይ ነው በበኩላችንም አመልካች ሰኔ ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት አንዲታይ የተወሰነው ክሱ በቀረበ ጊዜ የኪራይ ገንዘብ የተጠየቀበትን ቤት ግምት ጭምር መቅረብ ነበረበት ግምቱ ቢቀርብም ኖሮ ጉዳዩ ክሱን ካየው የማኀበራዊ ፍቤት ሥልጣን በላይ ይሆን ነበር በሚል የተሰጠውን ውሣኔ አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ይህን ነጥብ ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ በቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ቀደም ሲል እንደተገለጸው አመልካች በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሠረተችው በመዛሃከላቸው በተደረገው የኪራይ ውል መሠረት የሚፈለግባቸውን የኪራይ ገንዘብ እንዲከፍሏት እና በኪራይ ይዘውት የሚገኙትን ቤትም አንዲለቁላት ነው በመዝገቡ እንደተገለጸውም በክሱ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ብር ዐዐ አራት ሺህ ስምንት መቶ ነው በተሻሻለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁ አንቀጽ ዐ አንደተመለከተው የቀበሌ ማኀበራዊ ፍቤቶች ግምታቸው ከብር ዐዐዐ አምስት ሺህ ያልበለጠ የንብረትና የገንዘብ ክርክሮችን የማየት የመዳኘት ሥልጣን አላቸው አመልካች ክሱን ለማህበራዊ ፍቤት ያቀረበችው በዚህ መሠረት ሲሆን ማኀበራዊ ፍቤቱም ሥልጣን አንዳለው በመገንዘብ ክርክሩን ሰምቶአል በመሆኑም በዚህ ረገድ የማኀበራዊ ፍቤቱ ከስልጣኑ ውጪ ጉዳዩን አይቷል ለማለት አይቻልም ተደጋግሞ እንደተገለጸው ለክሱ መነሻ የሆነው ምክንያት የኪራይ ገንዘቡ አለመከፈሉ ነው አመልካች የከሰሰችው የኪራይ ውሉን መሠረት በማድረግ እስከሆነ ድረስ በቤቱ ላይ የንብረት ጥያቄ የባለ ሃብትነት ያነሳች ይመስል በቤቱ ግምት መጠን ዳኝነት ከፍለሽ አልጠየቅሽም ወይም መጠየቅ ነበረብሽ የምትባልበት የሕግ ምክንያት የለም የተጠየቀው የኪራይ ገንዘብም በውሉ መሠረት ተሠልቶ ቀርቦ ሳለ ይግባኙን የሰማው ፍቤት የፍብሥሥሕግ ቁ ጋን በመጥቀስ የዓመቱን ክፍያ በዐ ተባዝቶ መቅረብ ነበረበት የሚል ትችት መስጠቱ አግባብ አይደለም እንደምንመለከተው የኪራይ ገንዘቡ የሚከፈለው በየወሩ ሲሆን በዚህ መሠረት ባለመከፈሉ ሂሣቡ ተሰልቶ ክሱ ቀርቧል አመልካች ከዚህ ውጪ እንድታደርግ አትጠበቅም በፍብሥሥሕግ ቁ የተመለከተው ድንጋጌ ተሟልቷል ሲጠቃለል የቀበሌ ማኀበራዊ ፍቤት ክሱን ያስተናገደው በሕጉ የተሰጠውን ሥልጣን መሠረት አድርጎ ነው በመሆኑም ክሱን ለማየት ሥልጣን አልነበረውም ተብሎ በይግባኝ ሰሚው ፍሃቤት የተሰጠው ውሣኔ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ ዐ ሚያዝያ ቀን ዓም የተሰጠው አና በከተማው አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍቤት በመቁ ዐ ሚያዝያ ቀን ዓም በተሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽረዋል በቂርቆስ ክከተማ የቀበሌ ዐ ማኀበሪዊ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ ፀንቷል ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ታፈሰ ይርጋ መድህን ኪሮስ ሱልጣን አባተማም አመልካች ኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ተጠሪዎች የአቶ ወርቁ ደመሣ ሚስት ወሮ ጽጌ በየነ በራሳቸው እና ሞግዚት በሆኑላቸው ሀ ትዝታ ወርቁ ለ ሚካኤል ወርቁ ሐ ቤተልሔም ወርቁ ወሪት ትዕግሥት ወርቁ አቶ መላኩ ወርቁ አቶ ዮሴፍ ወርቁ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለዚህ ጉዳይ መነሻ የሆነው የአሁኑ አመልካች በጥር ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ በወረዳ ቀበሌ የሚገኘው ቁጥር ዐ አምስት መቶ ፃምሳ ብር የሆነው ቤት አቶ ወርቁ ደመሳ ከኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ በወር በብር ዐዐአምስት መቶ ተከራይተዋል ተከራይ ከሞቱ በኋላም ተከሣሾች የተከራዩን መብትና ግዴታ በመያዝና በመሸከም ተስማምተው በቤቱ መኖር ቀጥለዋል ሆኖም ከሚያዝያ ቀን ዓም አስከ ጥቅምት ዐ ቀን ዓም የተወዘፈውን ኪራይ እንዲከፍሉ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ሊከፍሉ ባለመቻላቸው የቤቱን ውዝፍ ኪራይ ብር ዐዐ ፃምሳ አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር ወለድ ብር ሠላሳ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ዛፃምሳ ሰባት ብር ከ አርባ አምስት እና ተጨማሪ አሴት ታክስ ብር ሰባት መቶ ሰባ በድምሩ ብር ሰማኒያ አራት ሺህ አምስት መቶ ፃያ ሰባት ከአርባ አምስት በመክፈል ቤቱን ሊያስረክቡኝ ይገባል በማለት በፌመደፍቤት የመሰረተው ክስ ነው የፌመደፍቤትም ግራ ቀኙን በማከራከር ከሚያከያ ቀን ዓም እስከ መስከረም ቀን ዓም ድረስ መከፈል የነበረበት የቤት ኪራይ ለማስከፈለ ክሱ የቀረበው ዓመት ካለፈ በኋላ በመሆኑ ኪራዩ በፍብሕቁ ዐመ መሠረት እንደተከፈለ ይቆጠራል ከመስከረም ቀን ዓም በኋላ መከፈል የነበረበት ኪራይ ደግሞ ያለመከፈሉን ተከሳሾች ስላመኑ መክፈል አለባቸው ወለዱን በተመለከተ ደግሞ ኪራዩ ሊከፈል ያልቻለው ተከሣሾች እንክፈል ሲሉ ከሣሽ ውዝፉን ካልከፈላችሁ ሌላውን አልቀበልም በማለቱ ምክንያት መሆኑን ስለተረጋገጠ ተከሣሾች ወለዱን መክፈል አይገባቸውም በመሆኑም ተከሣሾች ከመስከረም ዓም ጀምሮ ውሣኔ እስከተሰጠበት ጊዜ ድረስ የቤት ኪራይ ብር ሀያ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ተጨማሪ እሴት ታክስ ብር ዐሰባት መቶ ሰባ በድምሩ ብር ሀያ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ለከሣሸ እንዲከፍሉ በሌላ በኩል ደግሞ ተከሣሾች ያልፈፀሙት ግዴታ አለመኖሩ ባለመረጋገጡ ቤቱን ለከሣሽ ሊያስረክቡ አይገባም ሲል ወስኗል ይግባኝ የቀረበለት የፌከፍቤትም ፍርዱ ጉድለት የለበትም በማለት ይግባኙን በመሠረዝ መዝገቡን ዘግቶታል አመልካች በሁለቱም ፍቤቶች ውሣኔ ቅር በመሰኘቱ ምክንያት ለዚህ ፌጠፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ባቀረበው አቤቱታ የጠቀሳቸው ቅሬታዎችም አቶ ወርቁ ዳመሣ ከመስከረም ዓም እስከ መጋቢት ዐ ቀን ዓም ያለውን የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ ተከሰው ተወስኖባቸው አፈፃፀሙን እየተከታተልን እያለን በሞት ከዚህ ዓለም ተለይተዋል የቤቱን ኪራይ አስመልክቶ መብትና ግዴታ ያለው ሰው ካለ ማንነቱን እያጠያየቅን ቆይተናል ኪራዩን በወቅቱ ለመሰበስብ የልቻልነውም በዚሁ ከዓቅም በላይ በሆነ ምክንያት ነው በመሆኑም የሥር ፍቤቶች ኪራዩ በፍብሕቁ ዐመ መሠረት እንደተከፈለ ይቆጠራል ያሉት አግባብነት የለውም መልስ ሰጭዎች ውዝፉን ሳይከፍሉ ከ ዓም ጀምሮ ኪዩን እንክፈሉ ሲሉ መጀመሪያ ውዝፉን ካልከፈላችሁ የአሁኑን ብቻ አንቀበልም ማለታችንም በአግባቡ ነው የሥር ፍቤቶች መልስ ሰጭዎች ውዝፉን መክፈል የለባቸውም ከ ዓም ጀምሮ ያለውን ኪራይም ያለወለድ መክፈል የለባቸውም ከ ዓም ጀምሮ ያለውን ኪራይም ያወለድ መክፈል አለባቸው። የሚሉትን ጭብጦች በመያዝ መዝገቡን መርምረነዋል መዝገቡን አንደረመመርነውም አመልካች ተከራዩ በሞት ከዚህ ዓለም ከተለዩ በኋላ ኪራዩን መሰብሰብ ወይም ደግሞ ቤቱን መረከብ ሲኖርበት የሟች ወራሾች ቤቱን እየተጠቀሙበት መሆኑን እያወቀ ኪራዩን ሳይሰበስብ ከሚያዝያ ዓም አስከ ነሐሴ ዓም መቆየቱ በማናቸውም መስፈርት ከአቅም በላይ ነው ሊባል የሚችልበት ምክንያት የለም በመሆኑም በዚህ ነጥብ ላይ የሥር ፍቤቶች ኪራዩ በፍብሕቁ ዐመ መሠረት እንደተከፈለ ተደርጎ መቆጠር አለበት በማለት መወሰናቸው በግባቡ መሆኑን ተገንዝበናል ከ ዓም በኋላ ያለውን የኪራይ ክፍያን ስንመለከትም ተጠሪዎች ኪራዩን እንክፈል በማለት እየደጋገሙ ሲጠይቁት ከሚያዝያ ቀን ዓም ጀምሮ ያለውን ውዝፍ ኪራይ ካልከፈላችሁ በስተቀር ከ ዓም ጀምሮ ያለውን የቤት ኪራይ አልቀበልም እያለ ሳይቀበል ቀርቶ ሲያበቃ አመልካች በዚሁ ራሱ ሳይቀበል ባቆየው ክፍያ ወለድ መጠየቁ አግባብነት ስለሌለው አመልካቹ ወለድን አስመልክቶ ያቀረበው ክርክር ተቀባይነት ያለው ሆኖ አላገኘነውም የመጨረሻውን ጭብጥ በተመለከተ ደግሞ ተጠሪዎቹ አቶ ወርቁ ዳመሣ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩበት ጊዜ ጀምሮ በየወሩ የቤቱን ኪራይ የመክፈል ግዴታ እያለባቸው ይህን ግዴታቸውን ያለመፈፀማቸውን ይልቁንም ኪራዩን እንዲከፈል መጠየቅ ከሚገባው ቀን ጀምሮ አመልካች ሳይጠይቅ ጠይቆ ፈቃደኝነት ካላገኘም ክስ ሳይመሰርት ሁለት ዓመት ያለፈ በመሆኑ ከ ዓም እስከ ዓም የነበረው የቤት ኪራይ በፍብሕቁ ዐመ መሠረት እንደተከፈለ ይቆጠራል ማለታቸው በወቅቱ ማለት ሁለተ ዓመት ሳያልፍ እኛን በመክሰስ ገንዘብህን መሰብሰብ ነበረብህ ይህን ባለማድረግህ መንግሥት የጣለብህን ግዴታ አልተወጣህም የሚል ትርጉም የሚሰጠው እንጂ ተጠሪዎች ኪራይ የመክፈል ግዴታቸውን ተወጥተዋል ማለት አይደለም በፍብሕቁ መ ዕዳው እንዲከፈል መጠየቅ ከሚገባው ቀን ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ሳይከፈል የቀረ ገንዘብ እንደተከፈለ ይቆጠራል በማለት የተደነገገው ደግሞ ባለገንዘቡ ሁለት ዓመት ሳይሞላው ክስም መስርቶ ቢሆን ገንዘቡን በወቅቱ ተግቶ እንዲሰበስብ ለማድረግ እና ሁለት ዓመት ካለፈው በጊላ ከሶም ቢሆን ገንዘቡን ለመሰብሰብ እንደማይችል ለማስገንዘብ እንጂ ባለዕዳው ሁለት ዓመት እስከሚያልፍ ዕዳውን ሳይከፈል ቢቆይ የመክፈል ግዴታውን እንደተወጣ ለመቁጠር ወይም ለማረጋገጥ አይደለም በተጨማሪ የዚህ አንቀጽ ድንጋጌ ኪራይ ያልከፈሉትን ተከራዮች ኪራዩን በክስ እንዲከፍሉ ከመገደድ የሚያድናቸው እንጂ ኪራዩን የመክፈል ግዴታቸውን እንደተወጡ የማያረጋግጥላቸው እንዳልሆነ ለመረዳት ችለናል ይህን መሠረት በማድረግ የሥር ፍቤቶች የሰጡትን ውሣኔ ስንመለከተው ከ ዓም እስከ ዓም የነበረው የቤት ኪራይ መጠየቅ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ ሲታይ ሁለት ዓመት ያለፈበት በመሆኑ በፍብሕቁ ዐመ መሠረት እንደተከፈለ ይቆጠራል ከ ዓም ጀምሮ መከፈል የነበረበት የቤት ኪራይም በወቅቱ ሳይከፈል የቀረው አመልካች ክፍያውን አልቀበልም በማለቱ ምክንያት በመሆኑ ወለድ ሊጠየቅበት አይገባም በማለት መወሰናቸው በአግባቡ ነው ተጠሪዎች ያልተወጡት ግዴታ የለም በማለት ቤቱን ለአመልካች ማስረከብ የለባቸውም በማለት የሰጡት ውሣኔ ደግሞ ተጠሪዎቹ በወቅቱ ያልተወጡትን በየወሩ ኪራይ የመክፈል ግዴታ እንደተወጡ የሚያረጋግጥ አና በውላቸው አንቀጽ ላይ የተደነገገውን ግዴታ ያላገናዘበ እንደዚሁም የፍብሕቁ መንፈስንም የሳተ በመሆኑ ውሣኔያቸው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት መሆኑን ተገንዝበናል ውሣኔ የፌመደፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ፍርድና የፌከፍቤት በመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ የሚፀናና የሚሻር ነጥብ ያለበት በመሆኑ ሀ ፍርድ ቤቶቹ የቤቱን ኪራይ የተመለከተውን ክፍያ መልስ ሰጭዎች ለአመልካች ብር ሃያ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ እንዲከፍሉ በማለት የወሰኑትን በፍብሥሥሕቁ መሠረት አጽንተናል ለ በሌላ በኩል ደግሞ ፍቤቶቹ መልስ ሰጪዎች ቤቱን ለአመልካች ማስረከብ የለባቸውም በማለት የሰጡትን ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽሯል መልስ ሰጭዎች በፌመደፍቤት በዚህ ጉዳይ ውሣኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ ጋር የቤቱን ኪራይና ተጨማሪ አሴት ታክሱን በድምሩ ብር ህያ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ለአመልካች ይክፈሉ ይፃፍ መልስ ሰጪዎች በክሱ የተጠቀሰውን ቤት ለአመልካች እንዲያስረክቡ ቤቱን እስካስረከቡበት ቀን ድረስም ኪራዩን ይክፈሉ ይፃፍ ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞችኹ ዓብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ አልማው ወሌ አመልካችፁ የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነገረፈጅ ድጋፌ ለገሰ ተጠሪ ወሮ ለምለም ገትንሳኤ በሌሉበት ይታያል መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቀረበው አመልካች የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ታህሣስ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ እና የከፍተኛው ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ትአዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለበት በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት የሰበር አቤቱታ በማቅረቡ ነው የክርክሩ ፍሬ ጉዳይ ተጠሪ የንግድ ድርጅት ከሌላ ሰው ስትገዛ ንግድ ይካሄድበት የነበረውን ቤት የመከራየት መብቷ ተጠብቆላታል ቤቱ የአመልካች በመሆኑ በፊት የነበረው የኪራይ ተመን ተስተካክሎ ብር ሁለት ሺ ዘጠኝ የተተመነ ቢሆንም ኪራዩ በዛብኝ ብላ በማመልከቷ ብር አንድ ሺ አራት መቶ አርባ ስምንት እንደተደረገባት አመልካች በማመልከቻው ገልዷል ሆኖም ተከሳሽ ወይም ተጠሪ በቀድሞው ኪራይ ብር አንድ መቶ ፃያ አምስት ብቻ የከፈለች በመሆኗ ከታህሣስ ወር ዓም እስከ ግንቦት ቀን ዓም ያለው የቤት ኪራይ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ቀሃምሣ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ አስራ አራት ከሐያ ከወጭና ኪሣራ ጋር እንድትከፍል ይወሰንልኝ በማለት አመልክቷል አመልካች ይህንን ክሱን የሚያስረዱ የጽሑፍ ማስረጃዎችንም አቅርቧል ተጠሪ የአመልካች ክስና ማስረጃ ከፍርድ ቤቱ መጥሪያ ጋር ደርሷት መልሷን ይዛ እንድትቀርብ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትእዛዝ መሠረት ቀርባ ባለመከራከሯ ጉዳዩን ተጠሪ በሌለችበት ታይቷል ጉዳዩን ተጠሪ በሌለችበት ያየው የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ከሳሽ አመልካች በቀድሞ የኪራይ ተመን ከተከሳሽ ተጠሪ ኪራይ ሲቀበል ከቆየ በኋላ አንደገና አዲስ ተመን አውጥቻለሁ ይከፈለኝ በማለት መጠየቅ ስለማይችል ተከሳሽ የሁለት ወር ከሁለት ቀን ሂሳብ ብቻ በአዲሱ የኪራይ ተመን መሠረት ትከፍላለች በማለት ወስኗል አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያቀረበ ቢሆንም ከፍተኛው ፍርድ ቤት የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሣኔ የሕግ እና የፍሬ ጉዳይ ስህተት የለበትም በማለት ይግባኙን ሰርዞታል አመልካች ይኸ ውሣኔ መሠረታዊ ስህተት አለበት ተጠሪ በአዲሱ የኪራይ ዋጋ ካልተስማማች ቤቱን ለአከራዩ ማስረከብ ነበረባት ይህን አላደረገችም እንደዚሁም በተመሣሣይ ጉዳይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር የሕግ ትርጉም የሰጠ ሲሆን የሥር ፍርድ ቤቶች ይህንን በመተላለፍ የሰጡት ውሣኔ ተገቢ ባለመሆኑ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት አመልክቷል ተጠሪ በአድራሻዋ ባለመገኘቷ በጋዜጣ ጥሪ የተደረገላት ሲሆን ያልቀረበች በመሆኑ የሰበሩ ክርክር በሌለችበት እንዲታይ ብይን ተሰጥቷል በሥር እና በሰበር የቀረበው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው ተጠሪ የድርጀት ቤት ኪራይ ሲተመን ሙሉ እውቀት የነበራት መሆኑንና የኪራዩ መጠን በዝቶብኛል ብላ በማመልከቷ ኪራዩ ከሁለት ሺ ዘጠኝ ብር ወደ አንድ ሺ አራት መቶ አርባ ስምንት ብር ዝቅ እንዲል ተወስኖላታል ተጠሪ ይህንን ለማስረዳት በአመልካች በኩል የቀረበውን ማስረጃ ቀርባ አላስተባበለችም ተጠሪ ባቀረበችው አቤቱታ መነሻ ተሻሽሎ በተወሰነው የቤቱ ኪራይ የማትስማማ ከሆነ ቤቱን ለአከራዩ በማስረከብ ከአመልካች ጋር የነበረው የአከራይ ተከራይ ውል ማቋረጥ ነበረባት ተጠሪ የንግድ ድርጅቱን ስትገዛ የንግድ ድርጅቱ ያለበትን ቤት የመከራየት መብት የሚተላለፍላት እንደሆነ በንግድ ሕጉ ተደንግጓል ስለሆነም ተጠሪ የመከራየት መብት ስለተላለፈላት ከአመልካች ጋር የኪራይ ውል አላት ይኸም በአመልካችና በተጠሪ መካከል ያለው የኪራይ ውል ላልተወሰነ ጊዜ የተደረገ የኪራይ ውል ነው ይህ ከሆነ አከራዩ በፍታብሔር ህግ ቁጥር ንኡስ አንቀጽ መሰረት የኪራዩን ዋጋ እንደጨመረ አስታውቋል ተጠሪ የታደሰው የኪራይ ውል በዝቷል በማለት አመልክታ ተሻሽሎላታል ተጠሪ በተሻሻለው የኪራይ ውል ዋጋ ከደረሳት በላ በቤቱ መኖር ከቀጠለች በፍታብሔር ሕግ ቁጥር ንኡስ አንቀጽ መሰረት ውሉ እንደታደሰ የሚቆጠር ይሆናል ይህ ከሆነ ተጠሪ በተሻሻለው የኪራይ ውል መሠረት የመክፈል ግዴታ አለባት ይህ ሆኖ እያለ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪ በተሻሻለው የኪራይ ዋጋ መሠረት የመክፈል ግዴታ የለባትም በማለት የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ ስህተት ያለበት ስለሆነ ተጠሪ በተሻሻለው የቤት ኪራይ ዋጋ መሠረት ተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር የመክፈል ግዴታ አለባት በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የከፍተኛው ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ትአዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸው በመሆኑ ተሽረዋል ተጠሪ አመልካች ክስ ያቀረበበትን የኪራይ ሂሳብ ብር ሐምሣ ሰባት ሺ ስድስት መቶ አስራ አራት ከፃያ ተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር መክፈል ይገባታል ብለን ወስነናል ወጭና ኪሣራ አመልካች ራሱን ይቻል ይህ ፍርድ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግንቦት ቀን ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ አመልካች የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነፈጅ አብርዛም አጥላባቸው ተጠሪ እነ ዳባ ኢጃቶ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሉ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ሲሆን አመልካች በተጠሪዎች ላይ ባቀረበው ክስ በአዲስ አበባ ከተማ በወረዳ ቀበሌ ክልል የሚገኘውንና ቁጥር ዐ የሆነውን ቤት ለቢሮ አገልግሎት በወር ብር አንድ ሺ ስምንት መቶ ለኦሮሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት አከራይቶ የነበረ ሲሆን ተከራዩ ቢሮውን ወደ ሌላ ቦታ በመቀየሩ ከታህሳስ ዓም ጀምሮ በድርጅቱ ውስጥ የነበሩ አባሎች ወደ ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ስለተዛወሩ በቤቱ ውስጥ የነበሩት እዚያው እንዲቆዩ ስለፈለገ የኪራይ ውሉ ወደ ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ተዛውሮ በቢሮነት እንድንጠቀምበት ይፈቀድልን በማለት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በደብዳቤ ጠይቆ ሲከታተል ከቆየ በኋላ ውል ሳይፈጸም አባሎቹ በቤቱ እንዲጠቀሙ አድርጓል በዚህ መሠረት የአሁን ተከሣሾች የኪራይ ውል ሳይኖራቸው ኪራይም ሳይከፍሉ ያለከሳሽ ፈቃድ ከጥር ቀን ዓም ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀሙበት ስለሚገኝ በአጠቃላይ ያለውን ውዝፍ ኪራይ ብር ዐዐ አንድ መቶ ሰማኒያ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ወለድ ብር አንድ መቶ አሥራ ሦስት ሺህ አምስት መቶ አሥራ አንድ ከሰላሳ በድምሩ ብር ሁለት መቶ ዘጠና ሰባት ሺህ አንድ መቶ አሥራ አንድ ከሰላሳ አምስት ከፍለው ቤቱን ለከሣሽ እንዲያስረክቡ ይወሰንልን በማለት ጠይቋል የከሣሽ ክስና ማስረጃ ለተከሳሾች ደርሶ መልስ አንዲሰጡ በታዘዘው መሠረት የተወሰኑት ተከሣሾች ቀርበው መልስ ሲሰጡ የተወሰኑት ደግሞ በአግባቡ ተጠርተው ባለመቅረባቸው በሌሉበት ጉዳዩ እንዲታይ ፍቤቱ ትፅዛዝ ሠጥቷል የቀረቡት ተከሣሾች በሰጡት መልስ ክስ የቀረበበት ቤት የከሣሽ ስለመሆኑ የቀረበ ማስረጃ ካለመኖሩም በላይ ከሣሽም አስተዳድሮት አያውቅም ከሣሽ ከእኛ ጋር ውል ስላልፈጸመ በማናውቀው ውል መነሻነት የኪራይ ገንዘብ ልንጠየቅ አይገባም በማለት ክሱ ውድቅ ሊደረግ ይገባል ሲሉ ተከራክረዋል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ጉዳዩን መርምሮ ለክሱ መሠረት የሆነውን ውል ከሳሽ ያደረገው ከኦሮሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ጋር ሲሆን በዚህ ውል መሠረትም ተከሣሾች በቤቱ ውስጥ ሊገቡ መቻላቸውን ከሣሽ በክሱ ከመግለጹም በላይ በውሉ መሠረት ኪራይ ሊከፍል የተስማሙና ሲከፍል የቆየው ይሄው የኦሮሞ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት እንጂ ተከሣሾች አይደሉም ካለ በኋላ ውሉ ሳይታደስ ቀርቶ ቤቱ ያለ አግባብ ተይዞብኛልና ይለቀቅልኝ ወይም ውዝፍ ኪራይ ይከፈለኝ በማለት ሊጠይቅ የሚችለው በውል የተከራየውን ወገን እንጂ ተከሣሾችን አይደለም አንደዚሁም ውሉ ስላለቀ ሊያስረክበን ይገባል ከሆነም ውሉን ለማፍረስ ውል የገባውን ወገን መክሰስ እንጂ ውሉ ባልፈረሰበት ሁኔታ ቤቱ እንዲለቀቅለት ያቀረበው ጥያቄ በአግባቡ አይደለም በማለት ክሱን ሳይቀበለው ቀርቷል ከሣሽ በዚህ ውሣኔ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት አቅርቦ ፍቤቱም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ የሥር ፍቤት ውሣኔ ጉድለት የለበትም በማለት በፍብሕሥሥቁ መሠረት አጽንቷል የሰበር አቤቱታውም የቀረበው ይህንኑ በመቃወም ሲሆን ይህ ችሎትም በበኩሉ አቤቱታው ለሰበር ይቀርባል ብሎ ግራ ቀኙን አከራክራል ምላሽ ማግኘት የሚገባውም የጉዳዩ ጭብጥ ተጠሪዎች ለክሱ ምክንያት የሆነውን ቤት ለአመልካች ሊያስረክቡ ይገባል ወይንስ አይገባም። የሚለው ነው የሥር ፍቤት አመልካች ቤቱን ለተጠሪ እንዲያስረክቡ የወሰነው የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ ክስ በቀረበበት ጉዳይ ላይ እነዚህ ሁለት ቤቶች በሽያጩ አለመካተታቸው ተረጋግጦ ተወስኗል በማለት ነው ውሣኔ ማለት ተከራካሪዎቹ ወገኖች ያቀረቡትን ክስና መልስ እንዲሁም ማስረጃዎቹን መርምሮ ስለተከራካሪዎቹ ወገኖች መብትና ስለክሱ አወሳሰን ፍቤቱ የሚሰጠው ውሣኔ ለመሆኑ የፍሥሥሕጉ ለውሣኔ ከሰጠው ትርጉም መረዳት ይቻላል በተያዘው ጉዳይ ግን ፍቤቱ በቀድሞ ክስ ተጠሪ ተገቢውን ዳኝነት ከፍለው ይጠይቁ ከማለት በቀር አሁን ክርክር የተነሳባቸውን ቤቶች በተመለከተ ክሱንና መልሱን አንዲሁም ማስረጃዎቹን መርምሮ ስለተጠሪም ሆነ ስለ አመልካች መብት የሰጠው ውሣኔ የለም ግራ ቀኙ ተከራክረው ውሣኔ ባልተሰጠበት ጉዳይ ደግሞ ቤቶቹ በሽያጩ ውል ላይ አልተካተቱም በሚል በውሣኔ ትችቱ ላይ መግለፁ ብቻ በጉዳዩ ላይ ውሣኔ መሰጠቱን አያመለክትም በመሆኑም የሥር ፍቤት ክርክር ተደርጎ ውሣኔ ያልተሠጠበትን ጉዳይ እንደተሰጠበት በመቁጠር ለውሣኔው መሠረት ማድረጉ አግባብ ሆኖ አላገኘነውም ፍቤቱም ቀድሞ ውሣኔ ተሰጥቶበታል ወደሚለው መደምደሚያ በመድረሱም ግራ ቀኙ በቤቶቹ ላይ ያላቸውን ክርክርና ማስረጃ በአግባቡ ሣይመረምር ውሣኔ መስጠቱን ተገንዝበናል እኛ መዝገቡን እንደመረመርነው ተጠሪ መጋቢት ቀን በተደረገ የሽያጭ ውል በወረዳ ቀበሌ የሚገኘውንና የቤት ቁጥር የሆነውን ቤት መሸጣቸውን ተረድተናል የሸያጭ ውሉን እንደተመለከትነውም በከተማ ቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር ቁጥር ዐዐዐ በስማቸው የተመዘገበውንና በፕላን ቁጥር በቦታ ይዞታ ዐ ካሜ ላይ በ ካሜ ቦታ ላይ የሰፈረውን ቤት አዋሳኞቹን በመጥቀስ በብር ዐዐዐስልሳ ሁለት ሺ ለአመልካች ሸጠዋል ይህ በሸያጭ ውሉ ላይ በተገለፀው የከተማ ቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር ላይ ደግሞ የተጠቀሱት ቁጥር እና የሆኑ ቤቶች ናቸው የሽያጭ ውሉ እና የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተሩ አንድ ላይ ተገናዝበው ሲታዩም ተጠሪ ለአመልካች የሸጡት ሦስቱን ቤቶች በሙሉ መሆኑን መረዳት ይቻላል በተለይ በሽያጭ ውሉ ላይ ተጠሪ የቤቁ ን ብቻ ለይተው እንደሸጡ የገለፁት ነገር አለመኖሩ ሲታይም የሽያጭ ውል በባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተሩ ላይ የተጠቀሱትን ቤቶች በሙሉ የሚያጠቃልል መሆኑን ያመለክታል በሌላ በኩል ተጠሪ አሁን ክርክር የተነሳባቸውን ቤቶች ለአመልካች ያስረከብኩት ወደፊት ቤቶቹን አጠቃልዬ እገዛለሁ ስላሉኝ ነው ያሉ ቢሆንም ይህ ፍሬ ነገር እውነት ለመሆኑ በሥር ፍቤት የተረጋገጠ ነገር አላገኘንም በአጠቃላይ ከላይ እንደተመለከተው አመልካች ቤቱን የያዙት መጋቢት ቀን ዓም በተደረገው የሽያጭ ውል መሠረት ገዝተው በመሆኑ ቤቱን ለተጠሪ እንዲያስረክቡ የተሠጠው ውሣኔ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የፌመደፍቤት በመቁ በሐምሌ ቀን ዓም እና በፌከፍቤት በመቁ ዐዐ በግንቦት ቀን ዓም የተሰጡት ውሣኔ ተሽረዋል አመልካች ቤቶቹን የያዙት ገዝተው በመሆኑ ቤቶቹን ሊለቁም ሆነ ኪራዩን ሊከፍሉ አይገባም ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች ፍስሐ ወርቅነህ ዳሼ መላኩ ደስታ ገብሩ አማረ አሞጌ ታፈሰ ይርጋ አመልካች አቶ ማሞ ደምሴ አልቀረቡም ተጠሪ ኛ አቶ አያሌው ገእግዚአብሔር አልቀረቡም ኛ ወሮ ታየች ብርፃኑ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው የሐረር አውራጃ ፍቤት በአመልካችና በኛ ተጠሪ መካከል የተደረገው የቤት ሽያጭ ውል የኛ ተጠሪ ባለቤት የሆኑት የኛ ተጠሪ ስምምነት ሳይኖርበት የፍብሕቁጥር ን በሚጻረር ሁኔታ ስለሆነ ውሉ ፈራሽ ነው በማለት ውሳኔ በመስጠቱና ይሄው ውሳኔ በክልሉ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍቤቶች በመጽናቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት አመልካች ቅሬታ በማቅረባቸው ነው የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ አሁን አመልካች ከኛ ተጠሪ ጋር ተደርጓል የሚሉት የቤት ሽያጭ ውል ይጽደቅልኝ በማለት ለሐረር አውራጃ ፍቤት አቤቱታ አቅርበው ፍቤቱም ሰኔ ቀን ዓም በዋለው ችሎት ውሉ ፀድቋል በማለት ውሳኔ ሠጥቶ ተጠሪዎች ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለክልሉ ከፍተኛ ፍቤት የይግባኝ አቤቱታ አቅርበው ይግባኝ ሰሚው ፍቤትም የፍብሕሥሥ በሚፈቅደው መሠረት ይባዮች ወደ ክርክሩ ገብተው ጉዳዩ በድጋሚ እንዲታይ በማለት ጉዳዩን ወደ አውራጃው ፍቤት መመለሱን የመዝገቡ ግልባጭ ያስረዳል ከዚህ በኋላም በአውራጃው ፍሃቤት ኛ ተጠሪ ባቀረቡት አቤቱታ ከኛ ተጠሪ ጋር ሕጋዊ ባልና ሚስት መሆናቸውን ገልጸው ለክርክሩ ምክንያት የሆነውና በሐረር ከተማ ከፍተኛ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥር የሆነው ቤት ከኛ ተጠሪ ጋር በጋብቻ ዘመን በጋራ መሥራታቸው ሆኖም ይህንኑ ቤት ኛ ተጠሪ ያለ ባለቤታቸው ስምምነት ለአመልካች መሸጣቸውና ይህም የፍብሕቁ ን የሚጻረር ስለሆነ የሽያጩ ውል እንዲጸድቅ አስቀድሞ በፍቤቱ የተሰጠው ውሳኔ መብቴን የነካ ስለሆነ ይሄው ውሳኔ ይሰረዝልኝ በማለት ተከራክረዋል ኛ ተጠሪም በይዘቱ ከኛ ተጠሪ ጋር ተመሳሳይ የሆነ የሕግና የፍሬ ነገር ክርክር በማቅረብ አስቀድሞ የተሰጠው ውሳኔ ሊሰረዝ ይገባል ብለዋል አመልካችም በበኩላቸው አቤቱታው መሠረት የሌለው መሆኑን በመዘርዘር ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት የተከራከሩ ሲሆን በሌላ በኩልም ወሮ ከበቡሽ በጅጋ የተባሉት በክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት ሰኔ ቀን ዓም በተጻፈ ውል ከባልና ሚስቱ ከተጠሪዎች በመግዛት የቤቱ ካርታና ቁልፍ በእጃቸው እንደሚገኝ ገልፀው አመልካች ከኛ ተጠሪ ጋር በዚሁ ቤት ላይ ያደረጉት ውል ሕገ ወጥ ስለሆነ ፍቤቱ ውድቅ ሊያደርግው ይገባል በማለት የበኩላቸውን ክርክር አቅርበዋል ክርክሩ በዚህ መልኩ የቀረበለትም የአውራጃው ፍቤት የተጋቢዎች የጋራ የሆነን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ የተጋቢዎች ስምምነት አስፈላጊ ስለመሆኑ በፍብሕቁሀ ላይ የተመለከተ ስለሆነና በተያዘው ጉዳይ ኛ ተጠሪ ቤቱን ለአመልካች የሸጡት ያለ ባለቤታቸው ኛ ተጠሪ ስምምነት ስለሆነ ይሄው ውል ፈራሽ ነው በማለት ውሳኔ ሠጥቷል ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከቱትም የክልሉ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍቤቶች ይህንነ ውሳኔ አጽንተዋል የሰበር አቤቱታውም የቀረበው ይህንኑ በመቃወም ሲሆን ይህ ሰበር ችሎት የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ግራ ቀኙ ያደረጉት የቤት ሽያጭ ውል ይፈርሳል ተብሎ ውሳኔ መሰጠቱ ለሰበር ችሉት ቀርቦ ሊመረመር አንደሚገባው በማመን ተጠሪዎች ቀርበው መልስ እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሠጥቷል ይሁንና ኛ ተጠሪና የኛ ተጠሪ ወራሾች በጋዜጣ እንዲጠሩ ትዕዛዝ ተሰጥቶ በዚሁ መሠረት በጋዜጣ ቢጠሩም አልቀረቡም በአጠቃላይ የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን የሰበር አቤቱታውም እንደሚከተለው ተመርም ል ከላይ አንደተጠቀሰው የአሁን አመልካች በሐረር አውራጃ ፍቤት አቤቱታ ያቀረቡት ከኛ ተጠሪ ጋር ተደርጓል የሚሉት ውል ይጽደቅልኝ በማለት ነው ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ማናቸውም አቤቱታ ተመርምሮ ውሳኔ ርፎጨ ሊሰጠው የሚችለው የቀረበው አቤቱታ ለፍቤት ሊቀርብ የሚችል በጨጩመጪ ሆኖ በሚገኝበት ጊዜና እንደዚሁም አቤቱታው የክስ ምክንያት ያለው ሆኖ በሚኝበት ጊዜ ነው በተያዘው ጉዳይ አመልካች ያቀረቡት አቤቱታ የቤት ሺያጭ ውል ይጽደቅልኝ የሚል አንደመሆኑ መጠን ማናቸውም ውል በፍብሕቁ ላይ የተመለከቱትን የውል አመሠራረት መርሆዎች በር ር ርክር መሠረት አድርጎ እስከተቋቋመ ድረስ በሕግ አግባብነት ተቋቁሟል ለማለት የሚቻል ሲሆን ከዚህ አልፎ ውሉ በፍቤት እንዲጸድቅ የሚያስገድድ የሕግ ማዕቀፍ የለም በመሠረታዊ ሕጉ ጨጩፎበጩዩ ኢመጩሃ ላይ የዚህ ዓይነቱ ግዴታ ከሌለ ደግሞ የሥነሥርዓት ሕጉ በመሠረታዊ ሕግ የተሰጠን መብትና ግዴታን ማስፈጸሚያ እንጂ በእራሱ የመብትና ግዴታ ምንጭ ሊሆን አይችልም ስለሆነም የቤት ሽያጭ ውል ይፅደቅልኝ በማለት አቤቱታ ማቅረብ ለፍቤት በማይቀርብና የክስ ምክንያትም በሌለው ነገር አቤቱታ እንደማቅረብ የሚቆጠር በመሆኑ የአውራጃው ፍቤት ይህንኑ አቤቱታ በፍብሕሥሥቁ ሀ መሠረት ተቀባይነት የለውም ማለት ሲገባው ውሳኔ መሰጠቱ እንደዚሁም ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የክልሉ ከፍተኛ ፍቤት በዚሁ መሠረት ማረም ሲገባው ተጠሪዎች በተቃዋሚነት ገብተው ጉዳዩ በድጋሚ እንዲታይ መወሰኑና ከዚህም በኋላ ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት አቤቱታው የክስ ምክንያት የለውም ማለት ሲገባው በዚህ ሁኔታ የተሰጠውን ውሳኔ ማጽናቱ ያለአግባብ ሆኖ ተገኝቷል ውሳኔ የሐረር አውራጃ ፍቤት ታህሳስ ቀን ዓም በመቁ የሰጠው ውሳኔ የሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍቤት ግንቦት ቀን ዓም በመቁ የሰጠው ውሳኔ እንደዚሁም የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ኅዳር ቀን ዓም በመቁ የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለተገኘ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽ ል ይጻፍ አመልካች ለሐረር አውራጃ ፍቤት የቤት ሽያጭ ውል ይዕደቅልኝ በማለት ያቀረቡት ለፍቤት የማይቀርብና የክስ ምክንያት የሌለው ነው ተብሎ ተወስኗል መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ ቤኃ የሰበር ፍይል ቁጥር ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ መስፍን ዕቁበዮናስ ተሻገር ገስላሴ አብዱራሂም አህመድ አመልካች ኦርቢስ የንግድና ቴክኒክ ክፍል አማህበር ግርማ ሥላሴ ጠበቃ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ሙሉነህ ካሣ ጠበቃ ቀረቡ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው አመልካች ታህሣሥ ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት መነሻ ነው የጉዳዩ የስር አመጣጥ ተጠሪ ጥር ቀን ዓም ከአመልካች ጋር ባደረገው ውል የመርቸዲስ ቤንዚን አክተርስ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች በወቅቱ ዋጋቸው ለመግዛት ተስማምቶ ውሉ ሲደርግ ብር አምስት መቶ ሺህ ሊከፍልመኪኖቹ ጂቡቲ ወደብ ሲደርሱ ኛውን ክፍያ ብር ሰባት መቶ ስልሳ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ሠላሰ ስድስት ለመክፈልና መኪኖቹን ከተረከበ በኋላ በየደረጃው ሌሎች ክፍያዎችን ለመፈፀም ተስማምቶ በዚሁ መሠረት ብር አምስት ሺህ የመጀመሪያ ደረጃ ክፍያ ፈፅሞ እያለ መኪኖቹን አመልካች በወቅቱ ሊያስረክበው ባለመቻሉ የከፈለውን ገንዘብ አጠፌታ እንዲከፍለው ክስ አቅርቧል አመልካችም በበኩሉ መኪኖቹን ለማስረከብ ያልተቻለው ተጠሪ ሁለተኛውን ክፍያ ባለመክፈሉ እንደሆነ በመግለፅ ለክሱ መልስ ሰጥቷል ክሱ የቀረበለት የፌከፍቤት ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በርግጥም ተጠሪ በውሉ መሠረት የሚፈለግበትን ክፍያ አለመፈፀሙን በመግለፅ ኛውን ክፈያ ለተከሣሽ ከፍሎ መኪኖችን እንዲረከብ በማለት ወስኗል ተጠሪም በዚሁ ውሳኔ ላይ በመመርኮዝ የአፈፃፀም ፋይል የከፈተ ሲሆን በአፈፃፀም የጠየቀውም ሁለተኛውን ክፍያ ብር ሰባት ሺ ስልሳ ሰባት ሁለት መቶ ሠላሳ ስድስት ከፍሉ መኪኖቹን እንድረከብ የሚል ነው አመልካችም በበኩሉ ተጠሪ ተረቺ እንጅ ረቺ ስላልሆነ የአፈፃፀም መዝገብ ሊከፍት አይችልምየፍርድ ቤቱም ውሣኔ ይህን ለማድረግ የሚያስችለው አይደለም በማለት ተከራክሯል ፍርድ ቤቱም በጥቅምት ቀን ዓም በዋለው ችሎት ተጠሪ በውሉ መሠረት የመኪናዎቹን ቀሪ ዋጋ ከፍሎ መኪናዎቹን ይረከብ በማለት በሠጠው ትዕዛዝ መሠረት አመልካች ለተጠሪ በውሉ መሠረት የመኪናዎቹን ዋጋ ብር አሥራ ሁለት ሚሊየን አንድ መቶ ዛፃምሳ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ከሰባ ከፍሎ መኪኖቹን እንዲረከብ መግለጫ ቢሰጥም ተጠሪ ግን ኛውን ክፍያ ብር ሰባት መቶ ስልሳ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ሠላሳ ስድስት ብቻ ከፍዬ መኪናዎቹን እንድረከብ ብጠይቅም አመልካች ፈቃደኛ አልሆነም በማለት ለፍቤት በማመልከቱ ፍርድ ቤቱም በጥቅምት ቀን ዓም በዋለው ችሎት የተሰጠውን ትዕዛዝ በመሻር አመልካች ብር ሰባት መቶ ስልሳ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ሰላሳ ስድስት ብር ተቀብሎ መኪኖቹን እንዲያስረክብ በግንቦት ቀን ዓም የፌጠፍቤትም ትዕዛዝ ሰጥቷል ለፍቤት ጉዳዩን በይግባኝ አይቶ ውሣኔውን አፅንቷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚህ መነሻነት ሲሆን ይህ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን በማስቀረብ አከራክሯል ክርክሩንም ከሕግ ጋር በማገናዘብ መርምሯል በዚህ ጉዳይ ለቀረበው ክርክር መሠረት የሆነው የፌከፍቤት በዋናው ጉዳይ ጥር ቀን ዓም በሰጠው ውሳኔ ላይ ከሳሽ በውሉ መሠረት ኛ ክፍያውን ለተከሣሽ ከፍሎ መኪናዎቹን ከሚረከብ በቀር ውሉ የሚፈርስበት ምክንያት የለም ብሎ ወስኗል በማለት ያሠፈረው የድምዳሜ ዐረፍተ ነገር ነው ተጠሪም ዐረፍተ ነገሩ የፍርድ ባለመብት አድርጐኛል በማለት አፈፃፀም የከፈተ ሲሆን አመልካችም በበኩሉ ባንድ በኩል ተጠሪ የፍርድ ባለመብት አለመሆኑን በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ መኪኖቹን ለመረከብ የሚችለው በውሉ ላይ በተመለከተው ዋጋ መሠረት ሣይሆን አሁን ባለው የገበያ ዋጋ መሠረት ነው የሚል ነው ፍርድ ቤቱ ከላይ የተመለከተውን የመደምደሚያ ዐረፍተ ነገር ያስቀመጠው አመልካች ቀደም ሲል ለክሱ ሰጥቶት በነበረው መልስ ላይ ተጠሪ በፍብሕቁ መሠረት በቅድሚያ የበኩሉን ግዴታ ሣይወጣ አመልካች መኪናዎቹን ከጂቡቲ አስመጥቶ እንዲያስረክብ ለመጠየቅ በማለት ያቀረበውን በመቀበል የሰፈረ አንጂ ተጠሪን የፍርድ ባለመብት ለማድረግ አይደለም በሌላ አነጋገር ተጠሪ በቀብድ የከፈልኩትን ገንዘብ በአጠፌታ መመለስ ይገባዋል በማለት ባቀረበው የውል ይሰረዝልኝ ክስ ፍርድ ቤቱ ውሉ ሊሰረዝ አይገባውም ምክንያቱም ተጠሪ የበኩሉን ግዴታ አልተወጣምተጠሪ መብቱን መጠየቅ የሚችለው ግዴታውን ከተወጣ በላ ነው በማለት ክሱን ውድቅ ከማድረግ በስተቀር ተጠሪን የፍርድ ባለመብት ማድረጉን አያመለክትምይልቁንም ፍርድ ቤቱ በሥረ ነገር ክርክሩ በዋናው ጉዳይ ላይ ውሣኔ ለመስጠት ለውሉ መፍረስ የሚያበቃ ምክንያት አለ ወይ። በማለት ጭብጥ መያዙ ከላይ የተገለፀውን አባባል ያጠናክራል ይህን መነሻ በማድረግ ተጠሪ በቀብድ መልክ የከፈልኩት ገንዘብ ይመለስልኝ በማለት ውሉ እንዲፈርስለት ክስ አቅርቦ የሥር ፍርድ ቤትም ውሉ አይፈርስምምክንያቱም ውሉ ሊፈፀም ያልቻለው በአመልካች ጥፋት አይደለም በማለት አመልካች ያቀረበውን ክርክር በተቀበለበት ሁኔታ የአሁኑ ተጠሪ የፍርድ ባለመብት ሆኗል ለማለት አልተቻለም በተጨማሪም ተጠሪ ከሥር ጀምሮ ዳኝነት ባልተጠየቀበት ጉዳይ የፍርድ ባለመብት ሆኗል መባሉ ተገቢ ካለመሆኑም በላይ አመልካች ለክሱ ሰጥቶት በነበረው መልስ ላይ ተጠሪ ኛውን ክፍያ በመፈፀም መኪኖቹ ከጂቡቲ ወደብ ተነስተው ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ባለማድረጉ ለከፍተኛ የወደብ ኪራይ ተዳርገናል በማለት ካቀረበው ክርክር አንፃር ተጠሪ የበኩሉን ግዴታ እንዳልተወጣ የሥር ፍርድ ቤት አረጋግጦ የቀረበውን ክስ ውድቅ ማድረጉን ተገንዝበናል በመሆኑም ውል ይፍረስ ተብሎ በቀረበ ክስ ላይ ውሉ መፍረስ የለበትም ተብሎ በአሁኑ አመልካች የቀረበው የክስ መከላከያ ተቀባይነት አግኘቶ ክሱ ውድቅ በሆነበት ሁኔታ ክሱ ውድቅ የተደረገበት ተጠሪ የፍርድ ባለመብት ሆኗል መባሉ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ ተገኝቷል ምክንያቱም በፍብሥሥሕቁ በተመለከተው መሠረት የፍርድ እንዲፈፀም ለመጠየቅ ችሎታ ያለው ፍርድ የተፈረደለት ሰው ወገንን ብቻ በመሆኑና በተያዘው ጉዳይ ግን ተጠሪ ክሱ ውድቅ የተደረገበት በመሆኑ ነው ውሣኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአፈፃፀም መቁ እንዲሁም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁጥር ህዳር ቀን ዓም አመልካች ያልተከፈለውን ቀሪ ገንዘብ ተቀብሎ መኪናዎቹን ያስረክብ በማለት የሰጡት ውሣኔ ተሽሯል ይፃፍ የአሁን ተጠሪ በስር ፍቤት በሥራነገር ክርክሩ በዋናው ጉዳይ በተሰጠው ውሳኔ መሠረት አፈፃፀም ሊጠይቁ የሚችሉበት የህግ አግባብ የለም ብለናል ግራ ቀኙ ወጪያቸውን ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷልይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ የካቲት ቀን ዓም ዳኞችመንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ሰንላይት ኢንዱስትሪና ማከፋፈያ ኩባንያ ነፈጅ ብርፃኑ ወንደሰን ተጠሪ አቶ ካሣዬ ዘውዴ አልቀረበም ፍርድ ለሰበር አቤቱታው ምክንያት የሆነው ጉዳይ የጀመረው የፌመደፍቤት ነው አመልካች በሥር ፍቤት ከሣሽ የነበረ ሲሆን ለተጠሪ በሁለት የዱቤ ሰነዶች የውሃ ማሞቂያ መሸጡንና ተጠሪ ግን ለገዙት ዕቃ ዋጋቸውን ስላልከፈሉ የፅቃዎቹን ዋጋ ብር ዐ አርባ አራት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠላሣ ብር እንዲከፍሉ ጠይቋል ተጠሪም ክሱን ክደው ተከራክረዋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ በከሣሽና በተከሣሽ መሀከል የተደረገ የሽያጭ ውል አልቀረበም የዱቤ ሰነዱ በፍሕቁ መሠረት ተጠሪን አያስገድዳቸውም የሽያጭ ውል ተያይዞ ባለመቅረቡም ውሉ በከሣሽና በተከሣሽ መሀከል አለ ለማለት አይቻልም ሲል የአመልካችን ክስ ውድቅ አድርጓል አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለፌከፍቤት አቅርበው ፍቤቱ ይግባኙን ባለመቀበል ሠርኮዞታል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ነው አቤቱታው በአጭሩ ሲጠቃለል ሽያጩ የተደረገው በዱቤ ሰነድ ርዕጩዌዐቪ በህ ሆኖ ሣለ የዱቤ ሰነዱ ጋር የሸያጭ ውል አልተያያዘም በማለት ፍቤቱ ክሱን ውድቅ ማድረጉ ስህተት ነው የሚል ነው ይህ ችሎትም ከዱቤ ሰነዱ በተጨማሪ ሌላ የሽያጭ ውል አልቀረበም በማለት ክሱ ውድቅ መደረጉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት ቀርቦ አንዲታይ አድርጓል ተጠሪም ቀርበው ለቀረበው ክስ ምንም ዓይነት ማስረጃ ስላልቀረበ ውሣኔው ስህተት የለውም ሲሉ ተከራክረዋል ችሎቱም የግራ ቀኙን ክርክር የሰበር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔና አግባብነት ካላቸው ሕጎች ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው መርምሯል አመልካች በሥር ፍቤት ክስ የመሠረተው ተጠሪ በዱቤ ሽያጭ የገዙትት ውፃ ማሞቂያ ዋጋ እንዲከፍሉ ነው አንድ ግዴታ እንዲፈፀምለት የሚጠይቅ ሰው ለግዴታው መኖር ማስረጃ ማቅረብ አንዳለበት በፍሕቁ ዐዐ ሥር ተመልክቷል በመሆኑም አመልካች ተጠሪው ውዛ ማሞቅያውን መግዛታቸውንና ገንዘብ የመክፈል ግዴታ ያለባቸው መሆኑን ማስረዳት ይጠበቅበታል አንድ ግዴታ መኖሩን ለማስረዳት ሕጉ የተለየ ማስረጃ እንዲቀርብ ያዘዘ ካልሆነ በቀር ግዴታው መኖሩን በጽሑፍ በምስክር በሕሊና ግምት በተከራካሪው ወገን እምነት ወይም በመሐላ ማስረዳት እንደሚቻል በፍሕቁ ዐዐ ሥር ተመልክቷል በተያዘው ጉዳይ አመልካች እንዲያስረዳ የሚጠበቅበት ተጠሪ በዱቤ የውሃ ማሞቂያ ገዝተው የተረከቡ መሆኑን ነው የውዛ ማሞቂያ ሽያጭ ውል ደግሞ በተለየ ሁኔታ አንዲደረግ ወይም ውሉ ስለመደረጉ የተለየ ማስረጃ እንዲቀርብ ሕጉ የማያስገድድ በመሆኑ አመልካች ሽያጩ ለመከናወኑ ማንኛውንም ማስረጃ ማቅረብ ይችላል በቢህም መሠረት አመልካች ሽያጭ ለመደረጉ የዱቤ ሰነድ ርቪ በህ አቅርቧል ይህ የዱቤ ሰነድ ግራ ቀኙ ተስማምተው አእስከፈረሙት ድረስ የዱቤ ሽያጭ መከናወኑን ለማስረዳት በቂ ነው ሕጉ ይህ አይነቱ ሽያጭ በጽሁፍ እንዲሆን ስለማያዝም ከዱቤ ሰነዱ በተጨማሪ ሌላ የጽሁፍ ውል እንዲቀርብ የሚጠየቅበት ምክያት አይኖርም በመሆኑም የሥር ፍቤት ከዱቤ ሽያጩ ጋር የጽሁፍ ውል ባለመያያዙ ሽያጭ ተከናውኗል ማለት አይቻልም ሲል የደረሰበት መደምደሚያ ስህተት መሆኑን ተገንዝበናል በሌላ በኩል ግን አመልካች ሽያጭ መከናወኑን ለማስረዳት ባቀረበው የዱቤ ሰነድ ላይ የፈረሙት አመልካችና ሌላ አብይ የተባሉ ግለሰብ እንጂ ተጠሪ አይደሉም በአርግጥ ተጠሪ ፈርመውበት ቢሆን ኖሮ የጽሁፍ ሠነድ በላዩ ላይ ስለሚገኘው የስምምነት ቃልና በላዩ ላይ ስለተፃፈው ቀን በተፈራራሚዎቹ መካከል ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ይሆን ነበር የፍሕቁ ዐዐ ይመለከቷል በተያዘው ጉዳይ ግን ተጠሪ በሰነዱ ላይ ያልፈረሙ በመሆኑ በሰነዱ ላይ ሰለሠፈረው ጉዳይ ተስማምተዋል ወይም ግዴታ ገብተዋል ለማለት አይቻልም በዚህ ችሎት በተደረገው የቃል ክርክር አመልካች ሰነዱ ላይ የፈረሙት ግለሰብ የተጠሪ ወኪል ናቸው ይበል እንጂ ይህ ክርክር ከስር ያልተነሣ አዲስ ነገር በመሆኑ በፍሥሥሕቁ መሠረት ተቀባይነት የለውም በመሆኑም አመልካች ያቀረበው ሰነድ በአመልካችና በተጠሪ መሀከል የዱቤ ሽያጭ ውል መደረጉን እና በዚህም ምክንያት ተጠሪ የእቃውን ዋጋ የመክፈል ግዴታ ያለባቸው መሆኑን አያስረዳም በዚህም ምክንያት ምንም እንኳን የሥር ፍቤት የአመልካችን ክስ ውድቅ ለማድረግ የሰጠው ምክንያት ስህተት ቢሆንም ክሱን ውድቅ ማድረጉ ግን በአግባቡ ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የፌመደፍቤት መጋቢት ቀን ዓም በመቁ የሰጠው ውሣኔ እና የፌከፍተኛ ፍቤት በመቁ ኀዳር ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ በፍሥሥሕቁ መሠረት ፀንተዋል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ታህሳስ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጐስ ወልዱ ሂሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ጀማል ሐሚድ ቀረበ ተጠሪዎች ወሮ ለተሃይማኖት ተክሌ ወሮ ኪሮስ ወልዱ ወሮ ምዕራፍ ወልዱ ተመስገን ወልዱ መብራቱ ወልዱ ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ ከሕግ ውጭ ተይዞ የሚገኘውን ቤት ይለቀቅልን በማለት ተጠሪዎች በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ መነሻነት የተጀመረውን ክርክር የሚመለከት ነው አመልካች ለቀረበበት ክስ መልስ የሰጠ ሲሆን በዚህም አከራካሪው ቤት ከ ያሉት ተጠሪዎች እህት ከሆነችው ገዝቶ የያዘው እና ከገዛው በኋላም ለውጦ አሻሸሎ በመስራት እየተጠቀመበት መሆኑን በመግለጽ ተከራክሮአል ክስ የቀረበበት የወረዳ ፍቤትም የሁለቱንም ወገኖች ክርክር ከሰማ በኋላ አመልካች ቤቱን ለተጠሪዎች እንዲለቅ ወስኖአል በዚህ ውሣኔ ላይ በየደረጃው ይግባኝ የቀረበላቸው የበላይ ፍቤቶችም ውሣኔውን አፅንተዋል አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው አኛም አመልካች የካቲት ቀን ዓም በጻፈው ማመልከቻ ያቀረበውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ስምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት አንዲታይ የተወሰነው በአመልካች እና ቤቱን በሸጠችለት የተጠሪዎች እህት መካከል የተደረገው የሸያጭ ውል ሳይፈርስ አመልካች ቤቱን ለተጠሪዎች እንዲያስረክብ የመወሰኑን አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ይህንን ነጥብ በግራ ቀኝ ወገኖች ከቀረበው ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከሥር ጀምሮ ከተደረገው ክርክር ይዘት መገንዘብ እንደቻልነው አከራካሪው ቤት በቀበሌው ገበሬ ማህበር ውስጥ የሚገኝ ነው ተጠሪዎች ቤቱ እንዲለቀቅላቸው ክስ የመሠረቱት ሠርተነዋል በማለት ሳይሆን አባታችን መሬቱን በ ዓም ከሌላ ሰው ገዝቶ የቆርቆሮ ቤት ሠርቶበታል በማለት ነው አመልካች ደግሞ ቤቱን መስከረም ቀን ዓም ከወሮ ንግሥት ወልዱ ጋር ባደረገው የሽያጭ ውል ገዝቶና አሻሽሎ በመስራት የሚኖርበት መሆኑን በመግለጽ ተከራክሮአል የሁለቱ ወገኖች ክርክር ይህን ሲመስልም በአመልካች እና በወሮ ንግስት ወልዱ መካከል የተደረገው የሽያጭ ውል ደግሞ ፈርሶአል አልተባለም ውሉ የሕግን መስፈርት አያሟላም የሚል ክርክርም አልቀረበበትም። ጀማ ዞን ከፍቤት በሰጠው ውሣኔ ላይ ይግባኝ ለኦብክመጠፍቤት የቀረበ ሲሆን የክልሉ ጠፍቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ በሚያዝያ ቀን ዓም በሰጠው ውሣኔ የተጠሪዎችን መቃወሚያ ከግምት ውስጥ በማስገባት የአሁን አመልካች በስር መሠጭ ቁጥሩ በሆነ ሌላ መዝገብ በተጠሪዎቹ በስር ይባዮች ላይ የዚህ ክርክር መነሻ በሆነው ውል መሠረት ስመንብረቱን በስሜ አንዲያዛውሩልኝ በዚህ ፋብሪካ ምክንያት ያወጣሁትን ወጭ እና በድርጅቱ ላይ ያለውን ዕዳ እንዲከፍሉኝ ሲሉ ክስ አቅርበው ተጠሪዎቹ በውሉ መሠረት የድርጅቱን ግማሽ ስመንብረት እንዲያዛውሩ እና ለድርጅቱ የወጣውን አዳ ከተለያዩ ወጪዎች ጭምር ብር ዐሁለት መቶ አሰራ አምሰት ሺህ አራት መቶ ሰልሳ ከአስራ ሦሰት እንዲከፍሉት ተወስኖ እያለ አመልካች ውል ይፍረስልኝ ብሎ የተከሣሽ ከሣሽነት ክስ በማቅረቡ ብቻ ውሉ እንዲፈርስ ተብሉ መወሰኑ ትክክል ሆኖ አልተገኘም ተጠሪዎቹም ግዴታቸውን እንደስምምነቱ ሣይፈጽሙ ቀሪው ገንዘብ ሊከፈለን ይገባል በማለት ያቀረቡት ቅሬታም ተቀባይነት የለውም ያለ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም የአሁን አመልካች የፋብሪካው ስራ አስኪያጅ ሆኖ በሠራበት ጊዜ ከፋብሪካው የሚገኘው ገቢ በማስረጃ ተጣርቶ ተጠሪዎቹ የድርጅቱ ገቢ ይከፈለን በማለት ያቀረቡት ጥያቄ ውሣኔ እንዲያኝ በማለት መዝገቡን በፍብሥሥሕቁ መሠረት ወደ ጅማ ዞን ከፍቤት መልሶታል የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍቤት በይግባኝ መዝገቡ በሰጠው ውሣኔ ቅር የተሠኙት የአሁን አመልካች ለክልሉ ሰበር ችሎት አቤቱታቸውን ቢያቀርቡም የኦብክመጠፍቤት ሰበር ችሎት አቤታቸውን ሣይቀበለው ቀርቷል አመልካች በመስከረም ቀን ዓም በተፃፈ የሰበር ማመልከቻ የክልሉ ጠፍቤት በስር ፍቤት ውሉ ፈርሶ ተጠሪዎች አመልካች የከፈሉትን ቀብድ እጥፍ አድርገው ይመልሱ ሲል የሰጠውን ውሣኔ በመሻር ከድርጅቱ የተገኘውን ገቢ በተመለከተ አጣርቶ የመሠለውን ይወስን ሲል መወሰኑ እና የክልሉም ጠፍቤት ሰበር ችሎት ይህንን ውሣኔ ማጽናቱ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው በማለት አቤቱታቸው ለዚህ ችሎት አቅርበዋል ይህም ችሎት የአመልካችን አቤቱታ ተመልክቶ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውና አመልካች የገዙት ፋብሪካ በእዳ በባንክ የተሸጠ በመሆኑ ስም ሊዛወር ስለማይችል ውሉ ሊፈርስ ይገባል ተብሎ በስር ፍቤት የተሰጠው ውሣኔ እንዲሻር መወሰኑ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ተጠሪን አስቀርቦ ግራ ቀኙ የጽሁፍ ክርክር አድርገዋል ከመዝገቡ መረዳት እንደተቻለው የኦጠፍቤት የጅማ ዞን ከፍቤት ውሉ ፈርሶ ተጠሪዎቹ የተቀበሉትን ቀብድ አጥፍ አድርገው ይክፈሉ ሲል የሰጠውን ውሣኔ ለመሻር መሠረት ያደረገው አመልካቹ ከዚህ ቀደም በመቁ ተጠሪዎቹ የፋብሪካውን ስመንብረት ያዛውሩልኝ ለፋብሪካው እዳ የተከፈለ ገንዘብ ይመለስልኝ ሲሉ ባቀረቡት ክስ በተጠሪዎች ላይ ያስወሰኑ በመሆኑ በፍሥሥሕቁ መሠረት ዳግመኛ ክስ ሊመሠርቱ አይችሉም በሚል ነው በመሠረቱ የፍብሥሥሕቁ ተፈፃሚነቱ ቀድሞ በተወሰነው ክርክር የስረ ነገር እና የተያዘው ጭብጥ አንድ አይነት በሆነ ጊዜ ነው በዚህ ጉዳይ ግን ምንም እንኳ ቀድሞ በመቁ የቀረበው ክርክር በፋብሪካ ሽያጭ ውሉ ዙሪያ የሚያጠነጥን ቢሆንም በክሱ የተጠየቀውም ዳኝነት ይሁን አከራካሪ የነበረው ጭብጥ ከውሉ መፍረስና አለመፍረስ ጋር የተገናኘ ባለመሆኑ አመልካች ውል ይፍረስልኝ ሲሉ ያቀረቡት ክስ በድጋሚ የቀረበ ክርክር ነው ሊባል የሚችል ሆኖ አልተገኘም አመልካቹ በተያዘው ጉዳይ ያቀረቡት ክርክር በፍብሥሥሕቁ ሥር የሚካተት አይደለም ከተባለ ደግሞ የውሉን መፍረስ አግባብነት መመርመሩ ተገቢ ይሆናል የክርክሩ መነሻ በሆነው ውል የተሸጠው ፋብሪካ በአሁኑ ሰዓት ባንክ ለእዳው ማስፈፀሚያ ያዋለው መሆኑን ከስር ፍቤት ጀምሮ ከተደረጉት ክርክሮች እና ከተሰጡት ውሣኔዎች ለመገንዘብ ተችሏል ይህ ከሆነ ደግሞ የውሉ ጉዳይ የሆነው ፋብሪካ በአመልካቹ ስም ሊዛወርም ሆነ አመልካች በውሉ ላይ ተመርኩዞ ሊተላለፍለት የሚችል መብት አይኖርም በሌላ አነጋገር የዚህ ውል ጉዳይ የሆነው አንደ ፍብሕቁጥር ድንጋጌ አነጋገር ሊፈፀም የማይችል ሆኖ ተገኝቷል የውሉ ጉዳይ ሊፈፀም የማይችል በሆነ ጊዜ ውሉ እንደሚፈረስ ይኸው ድንጋጌ ይገልፃል አንድ ውል ሲፈርስ ደግሞ ውጤቱ የሚሆነው ተዋዋዮቹን ወደ ነበሩበት ቦታ መመለስ መሆኑን የፍብሕቁ ይደነግጋል ይህም ችሎት የጅማ ዞን ከፍቤት ውሉ ይፈርሣል ሲል የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ መሆኑን የተገነዘበ ሲሆን ከፍተኛ ፍቤቱ አመልካች የፈፀሙት ክፍያ ቀብድ በመሆነ ተጠሪዎች አጥፉን ይመለሱ ሲል የሰጠውን ውሣኔ ግን በውሉ ክፍያው ቀብድ መሆኑ ካለመገለፁ አንፃር አልተቀበለነውም በመሆኑም ይህ ችሎት የፋብሪካ ሽያጭ ውሉ ይፈርሣል ተጠሪዎቹም አመልካች የከፈሉትን ብር ዐዐዐዐ አንድ መቶ ስልሳ ሺህ ሊመልሱ ይገባል ሲል ወስኗል ውሣኔ የኦብክመጠቅላይ ፍቤት በመቁ በሚያዝያ ቀን ዓም አመልካች በውሣኔ ያለቀውን ክርክር በድጋሚ ማቅረብ አይችልም ሲል ፍብሥሥሕቁ ላይ ተመርኩዞ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ተሽራል ይፃፍ የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ተጠሪዎቹ የወሰዱትን ቀብድ እጥፍ አድርገው ብር ሥስት መቶ ፃያ ሺህ ይክፈሉ ሲል የሰጠውን ውሣኔ አሻሽሸለንክፍያው ቀብድ ለመሆኑ ውሉ ስለማይገለጽ ተጠሪዎች ሊመልሱ የሚገባው የወሰዱትን ብር ዐዐዐዐ አንድ መቶ ስልሳ ሺህ ነው በማለት ውሉ ይፈርሣል ሲል በመቁ በሰኔ ቀን ዓም የሰጠውን ውሣኔ አጽንተነዋል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰመቁ ታህሳስ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ ኮል ደነቀው ተጠሪ ዘላቂ ግብርና ተሐድሶ ኮሚሽን አልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሉ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት የግራ ቀኙን ክርክር በይግባኝ ተመልክቶ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በማለት አመልካች ቅሬታ በማቅረቡ ነው የጉዳዩ አመጣጥም ባጭሩ ሲታይ የአሁን ተጠሪ በአሁን አመልካችና በሥር ኛ ተከሣሽ ላይ በምፅራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረበው ክስ ኛ ተከሣሽ ልዩ ልዩ የቢሮ ዕቃዎችን ለመግዛት በወጣው ጨረታ ተካፋይ በመሆን ብር ዐ አራት መቶ ሺህ አምስት መቶ አርባ የሚያወጡ ልዩ ልዩ ዕቃዎችን በዐ ቀን ውስጥ ሊያቀርብ ስምምነት ተፈራርሞና ኛ ተከሣሽ በቀረበው የሥራ አፈፃፀም ዋስትና አሸናፊ ሆኖ ሙሉ ክፍያ የተፈፀመለት ቢሆንም በውሉ መሠረት ጊዜውን ጠብቆ አብዛኛውን ዕቃ በጥራት አሟልቶና አስተካክሎ ያላቀረበ ስለሆነ በክስ የተጠየቀውን ተከሳሾች ባልተነጣጠለ ኃላፊነት እንዲከፍሉ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቆ ተከሳሻች ቀርበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያና ሙሉ መልስም በመስጠት ተከራክረዋል በተከሳሾች በኩል በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት የተነሳው ክርክርም በውሉ አንቀጽ መሠረት ጉዳዩ ለፍርድ ቤት ሊቀርብ የሚችለው ሐምሌ ቀን ዓም በተፈረመው ውል አንቀጽ መሠረት በሁለት ተዋዋይ ወገኖች መካከል አለመግባባት ቢከሰት ጉዳዩ ወደ አስታራቂ ኮሚቴ ሊመራ እንደሚገባውና አስታራቂ ኮሚቴውም ውሣኔ ከሰጠ በኋላ ቅሬታ ቢኖር ሲሆን በቀጥታ ወደ ፍቤት መፄድ ግን ውሉን የሚቃረን ስለሆነ ፍቤት ሊቀበለው አይገባም የሚል ነው የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍቤትም በዚህ ረገድ የቀረበውን መቃወሚያ መርምሮ ግራ ቀኙ ባቋቋሙት ውል አንቀጽ ላይ ተከሳሾች በጠቀሱት መልኩ ስምምነት የተደረገ ስለሆነና በሕግ አግባብነት የተቋቋሙ ውሎች በተዋዋዮች ላይ አሳሪ ስለሚሆኑ በዚህ ሁኔታ የቀረበው ክስ ከፍብሕሥሥቁ ረመሠረት ተቀባይነት የለውም በማለት ክሱን በብይን ውድቅ አድርጓል ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለትም የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ መሰጪዎች በይባይ አማካይነት በውሉ መሠረት በስምምነት ለመጨረስ በደረሰባቸው ማሳሰቢያና ማስጠንቀቂያ መሠረት መቅረብ ሲገባቸው ያልቀረቡ በመሆኑና ይህ ከሆነ ደግሞ በውላቸው ላይ አለመግባባት ከተከሰተ ጉዳዩ ወደ ፍቤት ከመቅረቡ በፊት በመከራከር ወይም በሚመርጧቸው አስታራቂ ኮሚቴዎች ለመፍታት መስማማታቸው ብቻውን ይግባኝ ባዮችን ወደ ፍቤት ጉዳዩን ከማቅረባቸው በፊት በስምምነታቸው መሠረት መጨረስ ነበረባቸው ተብሉ ጉዳያቸውን ወደ ፍቤት የማቅረብ መብታቸው የሚነፈግበት ምክንያት የለም የሚል ትችት በውሣኔው ላይ አስፍሮ የሥር ፍቤት ብይን በመሻር የፍሬ ጉዳይ ክርክሩ በዞኑ ከፍተኛ ፍቤት ይታይ በማለት ጉዳዩን መልሷል ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም የቀረበለትን አቤቱታ መርምሮ ጉዳዩ በፍቤት መታየት አለበት ተብሎ በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት የተሰጠው ውሣኔ ሊጣራ የሚገባው መሆኑን በማመኑ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል ምላሽ ማግኘት የሚገባውም የጉዳዩ ጭብጥ ክርክሩ በፍቤት ሊታይ ይችላል። የሚሉትን ጭብጦች በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም አመልካችና ተጠሪ የቤቱን ሽያጭ አስመልክቶ የተዋዋሉት የቤት ሽያጭ ውል የሽያጩ ስምምነት በጽሑፍ ሰፍሮ ከተፈራረሙ በላ የሁለቱን ቤቶች ካርታ ይዘው በውል ክፍል ቀርበው ከተፈራረሙ በላ ሽያጩን አስመዝግበው ለመጨረስ እንደነበር ግራ ቀኙ ካቀረቡት ክርክርና የሥር ፍቤት ከሰጠው ውሣኔ ለመረዳት ችለናል በውል ጽሑፋቸው ባሰፈሩት ስምምነት መሠረት በውል ክፍል ቀርበው ሽያጩን አእንዳያስመዘግቡ በአመልካች በኩል በስምምነት ጽሁፍ ላይ የሰፈረውን ግዴታ ያለመፈፀም ሁኔታ እንቅፋት መሆኑንም ግራ ቀኙ ካደረጉት ክርክር ለመገንዘብ ተችሏል እነዚህ ሁኔታዎች ተሟልተው ግራ ቀኙ ማስረጃዎቻቸውን ይዘው በመቅረብ የሽያጭ ውሉን በፍቤት መዝገብ ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካላስመዘገቡት ደግሞ ውሉ በፍብሕቁ መሠረት በተቀዳሚ ውልነት ወይም በረቂቅነት ደረጃ ላይ የቀረበ እንጂ በፍብሕቁ መሠረት የተደረገ የተሟላ ውል ነው ለማለት የሚቻል አይሆንም በመሆኑም የፌጠፍቤት በአመልካችና በተጠሪ መካከል በሕግ የሚታወቅ የቤት ሽያጭ ውል የለም በማለት የሰጠው ውሣኔ የተደረገው ውል ተቀዳሚ ውል ወይም ረቂቅ ውል እንጂ ሊፈፀም የሚገባው የተሟላ ውል አይደለም ማለት በመሆኑ ፍቤቱ የደረሰበት ድምዳሜ ተገቢ መሆኑን ተገንዝበናል በሌላ በኩል ግን ውሉ በተቀዳሚ ውልነት ወይም በረቂቅ ውልነት ደረጃ ላይ ባለበት ጊዜ በውል ስምምነት አድራጊዎቹ የተደረገ የገንዘብ ወይም የሌላ ነገር ልውውጥ ቢኖር ውሉ ሊፈፀም የሚያስችለው ደረጃ ላይ ባልደረሰበት ጊዜ የውል አድራጊዎቹ ወደነበሩበት መመለስ ተገቢ በመሆኑና በዚህ ጉዳይም አመልካች ለተጠሪ ከፈልኩ የሚሉት ብር ዐዐዐዐክምሳ ሺህ ስላለና ተጠሪም በስር ፍቤትም ይሁን በዚሁ ሰበር ሰሚ ችሎት ይህንን ክደው የተከራከሩ ባለመሆኑ የግራ ቀኙ ወደነበሩበት መመለስ አስፈላጊነት በግልጽ ስለሚታይ የፌጠፍቤት በግራ ቀኙ የተደረገ የሚፈፀም የቤት ሽያጭ ውል የለም በማለት ሲወስን ግራ ቀኙ ወደነበሩበት እንዲመለሱ በማለት በፍብሕቁ መሠረት መወሰን ሲገባው ይህን በማለፉ ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትና ሊሻሻል የሚባው ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የፌጠፍቤት በመቁ ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሻሸሏል በመልካችና በተጠሪ መካከል ተደረገ የተባለው የቤት ሽያጭ ውል ያልተሟላና በረቂቅነት ደረጃ ላይ ያለ በመሆኑ ውሉ እንዲፈፀምልኝ በማለት በመልካች የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም ይህን አስመልክቶ በፌጠፍቤት የተሰጠው ውሣኔ ፀንቷል ግራ ቀኙ ወደ ነበሩበት እንዲመለሱና ተጠሪ በቅድሚያ ክፍያነት የተቀበሉትን ብር ዐዐዐዐ ፃምሣ ሺህ ለአመልካች እንዲከፍሉ ተወስኗል ይፃፍ ውሣኔውን ፌከፍተኛ ፍቤት ያስፈጽም ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአራት ዳኞች ፊርማ አለበት የሀሣብ ልዩነት አኔ በአምስተኛ ተራ ቁጥር የተሰየምኩት ዳኛ ከአብላጫው ድምጽ በአመልካችና በተጠሪው መካከል ያለው ውል ፈርሶ ሁለቱም ወደነበሩበት እንዲመለሱ በሰጠው ማጠቃለያ ተስማምቼ አብላጫው ድምጽ ከዚህ ውሣኔ ለመድረስ ከሰጠው ምክንያት የተለየ ምክንያት ያለኝ በመሆኑ ይህንን የልዩነት ፃዛሣብ ጽፌአለሁ አንድ ተዋዋይ ወገን ሌላው ወገን ውል ይፈጽምልኝ የሚል ክስ ለማቅረብ የሚችለው በራስ በኩል ያለውን ግዴታ ሲፈጽም እንደሆነ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ለመረዳት ይቻላል በያዝነው ጉዳይ አመልካች ለተጠሪው የሸጠውን ቤት ካርታና ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች እንዲያስረክቡ በተጠሪው ተጠይቀው የቤቱን ካርታና ኘላን እንደዚሁም ሌሎች ሰነዶችን ለማስረከብ ባለመቻላቸው ምክንያት ውሉ ያልተፈፀመ በመሆኑ አመልካች በራሳቸው በኩል የገቡትን የውል ግዴታ ስላልተወጡ ተጠሪው ውል ይፈጽምልኝ በማለት ለመጠየቅ አይችሉም እንደውም በራሳቸው በኩል የነበረውን ግዴታ የተወጡት ተጠሪ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት አመልካች ውሉን እንዲፈጽም ወይም ውሉ ፈራሽ አንዲሆን መጠየቅ የሚችሉ በመሆኑ ተጠሪ አመልካች በአሳቸው በኩል ያለውን ግዴታ አልፈፀሙም በማለት ያቀረቡት መከራከሪያ ውሉን ፈራሽ ለማድረግ በቂ ምክንያት ነው ከዚህ ውጭ በግራ ቀኙ መካከል የተደገው ውል ረቂቅ እንጂ በሕግ ውጤት ሊያስከትል የሚችል ውል አይደለም በማለት አብላጫው ድምጽ የሰጠው የሕግ ምክንያት እኔን የሚያሣምን ባለመሆኑና በአመልካችና በተጠሪው መካከል ያለው ውል አመልካች የበኩሉን ግዴታ ባለመፈፀሙ ምክንያት በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት ፈራሽ መሆን ያለበት በመሆኑ አብላጫው ድምጽ በሰጠው የመጨረሻ ውሣኔ በመስማማት ውሉ ፈራሽ በሚሆንበት ምክንያት ላይ ያለኝን የልዩነት ሀሣብ አስፍሬያለሁ የማይነበብ የአንድ ዳኛ ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞችፁ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ ሠልጣን አባተማም አመልካች ወሮ ለምለም መኩሪያ ቀርባለች ተጠሪቡ ወሮ ሙሉእመቤት ጌታሁን ጠበቃው ቀርቧል መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ከመዝገቡ እንዳየነው ለአቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የቤት ሽያጭ ውል አፈፃፀምን የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀመረበት የፌመደፍቤት ከሣሽ የነበረችው የአሁንዋ አመልካች ናት በተጠሪዋ ላይ ክስ የመሠረተችውም ቀደም ሲል በተደረገው የሽያጭ ውል መሠረት በቀሪ የሚፈለግባትን የቤቱ ዋጋ እንድትከፍላት የውሉን አፈጻጸም በማዘግየትዋም በውሉ የተመለከተውን መቀጫ እንድትከፍል እንደውሉ የማትፈጽም ከሆነ ደግሞ ውሉ ፈርሶ ወደየነበሩበት እንዲመለሱ እንዲወሰን በመጠየቅ ነው ፍቤቱ ተከሣሽን አስቀርቦ ክርክሩን የሰማ ሲሆን በመጨረሻም ገንዘቡ የሚከፈለው ሻጭ የሆነችው ከሣሽ የቤቱን ስም በተከሣሽ ስም ስታዛውር ነው የሚል ምክንያት በመስጠት ክሱን ሰርዞአል ይግባኝ የቀረበለት የፌከፍቤትም ውሣኔውን አጽንቶአል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው እኛም አመልካች ሰኔ ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው የስር ፍቤቶች የአመልካችን ክስ ውድቅ ያደረጉበትን አግባብ ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ይህን ነጥብ ከስር ጀምሮ ከተካሄደው ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከፍ ሲል እንደተመለከተው የግራ ቀኙ ወገኖች ግንኙነት የተመሠረተው በውል ላይ ነው ይህም ሚያዝያ ቀን ዓም የተደረገው የተፈረመው የቤት ሽያጭ ውል ሲሆን የሁለቱን ወገኖች መብትና ግዴታ በዝርዝር ይዞአል አመልካች ቤትዋን በብር ዐዐዐ አንድ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ለተጠሪ ለመሸጥ መስማማትዋን ውሉ በተፈረመበት ፅለትም ከዋጋው ላይ ብር ዐዐዐዐ ስድሳ ሺህ መቀበልዋን ቀሪውን ብር ዐዐዐ አንድ መቶ ፃያ አምስት ሺህ ደግሞ ቀደም ሲል በቤቱ ላይ በፍቤት የተሰጠውን ውሣኔና ለፍርድ አፈፃፀም የተላለፈውን ትፅዛዝ አስነስታ ማስረጃውን ቤቱ ለሚገኝበት የሕብረት ሥራ ማኀበር አቅርባ በሷና በሟች ባለቤቷ ስም የተመዘገበውን ቤት በተጠሪ ስም አንዲመዘገብ ስታደርግ ወዲያውኑ እንዲከፈላት መስማማቷን ውሉ ያመለክታል በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ በውሉ በተመለከተው መሠረት ቤቱን ለመግዛት መስማማቷ እና ውሉ በተፈረመበት አለት ከከፈለችው ብር ዐዐዐዐ ስልሳ ሺህ ሌላ በቀሪ የሚፈለግባትን ብር አንድ መቶ ፃያ አምስት ሺህ አመልካች ግዴታዋን እንደተወጣች ወዲያውኑ ለመክፈል እንደተስማማች በውሉ በግለጽ ተመልክቷል አመልካች ወደ ክስ ያመራችው ተጠሪ እንደውሉ ለመፈጸም ፈቃደኛ አልሆነችም በማለት እና የበኩልዋን ግዴታ ግን እንደተወጣች በመግለጽ ነው ከእርሷ የሚፈለገው ግዴታ ከላይ በዝርዝር የተመለከተው ሲሆን በእርግጥም ይህ በሚገባ ስለመፈጸሙ በጽሑፍ እና በቃል በተደረገው ክርክር ተረጋግጧል ቀደም ሲል በቤቱ ላይ ተሰጥቶ የነበረውን የፍርድ ቤት ውሣኔ አና ለፍርድ አፈፃፀም መመምሪያ ተላልፎ የነበረውን ትዕዛዝ አስነስታ ማስረጃውንም ለሕብረት ስራ ማኀበሩ አቅርባ ተጠሪን አንድትተካ ስለማድረግዋ በዚህ ሰበር ችሎት በተደረገው ክርክር ጭምር ግራ ቀኝ ወገኖች አረጋግጠዋል የስር ፍቤት የሰጠው ውሣኔ እንደሚያመለክተው ናፍሃቤቱ በውሉ ላይ ያልተመለከተው እና ግራ ቀኝ ወገኖች በግልጽ የስምምነታቸው አካል ያላደረጉትን የስም ማዛወር የሚል አስተሳሰብን መሠረት በማድረግ ነው ውሣኔ የሰጠው በበኩላችን እንደምናየው በአመልካች እና በተጠሪ መካከል የተፈረመው ውል ግልጽ ነው ጠቅላላ አነጋገር የሚመስል አገላለጽ በፍጹም አይታይበትም ውሎች ግልጽ ሆነው በሚገኙበት ጊዜ ዳኞች ግልጽ ሆኖ ከሚሰማው መራቅ ውሉን መተርጎም እንደማይችሉ እንደማይገባቸው በፍብሕግ ቁ ተደንግጓል በተያዘው ጉዳይ ተጠሪ ቀሪውን ገንዘብ ለመክፈል በግልጽ የተስማማችው በቤቱ ላይ የነበረው መሰናክል ተወግዶ በማኀበሩ ዘንድ አመልካችንና ሟች ባለቤትዋን ተክታ ስትመዘገብ ነው። በኑዛዜው ግዴታ የተገባላቸው ኛ አመልካችም በፍብሕቁ መሰረት የታዘዘላቸውን እንዲፈጽሙላቸው ወራሾችን ለማስገደድ ይችላሉ ወራሾቹ ተሰብስበው በውርስ ስለተሰጣቸው ቤት አጠቃቀም ለመወሰን ጥር ቀን ዓም የደረሱበት ስምምነትም የአውራሹን ኑዛዜ የሚያስቀይር ይዘት ስለሌለው ተጠሪዎቹ ላቀረቡት ክስ በምክንያትነት ሊጠቀስ የሚገባው አይሆንም ኛ እና ኛ አመልካቾች በነዛዜ አገኘነው ያሉትን ቤት በተመለከተ ደግሞ የአሁን ተጠሪዎች ባቀረቡት ክስ ተለይቶ ክስ ያልቀረበበትና የሥር ፍቤትም ይህን አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ ባለመኖሩ በግራ ቀኙ የተደገው ክርክር አግባብነት የለውም በመሆኑም ኛ አመልካች በኑዛዜ የተሰጣቸውን በህይወት ዘመናቸው ክርክር ያስነሳውን ቤት የመገልገል መብት ወራሾች ሊያሳጡዋቸው የሚችሉበት ምክንያት ባለመኖሩ ተጠሪዎች የውርስ ንብረት የሆነው ቤት ተሽጦ ገንዘቡን ወራሾች እንድንከፋፈለው በማለት ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለውም የሥር ፍቤቶች የሰጡት ቤቱ ተሽጦ ገንዘቡ ወራሾች እንዲከፋፈሉት የሚለው ውሳኔም የኛ አመልካችን በቤቱ የመገልገል መብትና የወራሾቹን ኛ አመልካች በህይወት እያሉ ቤቱን ያለመሸጥ ግዴታ የጣሰና መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ስለተገኘ የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ የፌመደፍቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔና የፌከፍቤት በመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽረዋል አቶ ስዩም አየለ ኛ አመልካች በቤቱ ውስጥ መኖር አእንዳይከለከሉ እሳቸው በህይወት እያሉ ቤቱን ሸጩ ልካፈል ማለት አይቻልም በማለት የተናዘዙ በመሆኑ በወረዳ ቀበሌ ቤኃ ክልል የሚገኘው ቁጥሩ የሆነው ቤት እማሆይ ወይንሸት አድማሱ በህይወት እያሉ መሸጥ የለበትም በማለት ወስነናልይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ አቶ ሐጐስ ወልዱ አቶ ታፈስ ይርጋ አቶ መድሕን ኪሮስ አቶ ሥልጣን አባተማም አመልካች ወሮ ባዩሽ ደጀኔ ከጠበቃ ዳኛቸው ተስፋዬ ጋር ቀረበች ተጠሪዎች ወሮ ሃሳብ ከፋይ ጌራወርቅ ቀረበች ደረጀ ጌራወርቅ አልቀረበም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ ነዛዜን መሠረት በማድረግ የቀረበውን ክርክር የሚመለከት ነው ከመዝገቡ እንደሚታየው ክርክሩ በተጀመረበት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመጀመያ ደረጃ ፍቤት የአሁንዋ አመልካች ሟች አቶ ጌራወርቅ ህሩይ ባለቤትዋ አድርገውት ያለፉት ኑዛዜ መሠረት ተደርጐ የወራሽነት ማስረጃ ይሰጣት ዘንድ በመጠየቅዋ ፍቤቱም ጥያቄዋን በመቀጠል የኑዛዜ ወራሽነት በማለት ማስረጃውን ሰጥቶአት ነበር በሌላ በኩል ደግሞ የአሁኖቹ ተጠሪዎች ማስረጃው መሰጠት አልነበረበትም በማለት መቃወሚያ በማቅረባቸው ናሃቤቱ ጉዳዮን በድጋሚ ያየ ሲሆን በመጨረሻም ሟች አድርገውታል የተባለውን ኑዛዜ ከፊሉን በመሻር የተወሰነውን ክፍሉን ደግሞ በማጽደቅ ወስናአል በዚህ ላይ ከአሁንዋ አመልካች ይግባኝ የቀረበላቸው ይግባኝ ሰሚ ፍቤቶችም ውሳኔው ጉድለት የለውም ብለዋል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው እኛም አመልካች ነሐሴ ቀን ዓም በጻፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው አቤቱታ የቀረበበትን ውሳኔ አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ጉዳዩን ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሳኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከላይ አደተመለከተው ክርክሩ ሊነሳ የቻለው ሟች አደረገው የተባለው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል የሚል ክስ በመቅረቡ ሳይሆን የፍብሕቁ ነዛዜውን መሠረት በማድረግ የወራሽነት ማስረጃ የምስክር ወረቀት ይሰጠኝ የፍብሕቁ በማለት አመልካች ጥያቄ በማቅረብዋ ነው በፍትሐብሔር ሕጉ በግልጽ አንደተመለከተው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል በሚል የሚቀርበው ክስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ከሚቀርበው ጥያቄ አቤቱታ የተለየ ነው ጥያቄዎቹ የተለያዩ በመሆናቸውም የተለያየ ውጤት ነው ያላቸው በፍብሕቁ እንደተደነገገው ወራሽነኝ የሚል ማንኛውም ሰው የወራሽነት ምስክር ወረቀት ይሰጠው ዘንድ ለፍቤት ሊያመለክት ይችላል ፍቤቱም ጥያቄውን ከመቀበሉ በፊት ጠያቂው ማስረጃዎቹን ሁሉ እንዲያቀርብ በማድረግ እና አስፈላጊ መስሎ የታየውን ዋስትና እንዲሰጥ በማስገደድ ጭምር ዋስትናውን ካገኘ በኋላ የተጠየቀውን የምስክር ወረቀት ሊሰጥ እንደሚችል በፍብሕቁ ተመልክቶአል በሌላ በኩል ደግሞ ፍቤቱ የአመልካቹን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ሰጥቶት የነበረውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት ሊሰርዘው እንደሚችል በፍብሕቁ የተቀመጠው ድንጋጌ ያመለክታል ከዚህ እንግዲህ መገንዘብ እንደሚቻለው የምስክር ወረቀቱ በጠያቂው አቤቱታ መነሻነት የሚሰጥ ቢሆንም የተሰጠው ያለአግባብ ነው የሚል መቃወሚያ ሊቀርብ የሚችልበት ሁኔታ መኖሩንና መቃወሚያው ተገቢ ሆኖ ከተገኘም የምስክር ወረቀቱ የሚሰረዝ መሆኑን ነው ወደ ያዝነው ጉዳይ ስንመለስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ጥያቄ የቀረበለት ፍቤት ጥያቄውን ተቀብሎ የምስክር ወረቀቱን ሰጥቶ አንደነበር አንመለከታለን ይህም በፍብሕቁ የተመለከተውን ድንጋጌ ተከትሎ የተፈጸመ በመሆኑ ትክክል ነው ሌላው ቀጥለን የምናየው ተጠሪዎች የተሰጠውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት በመቃወም መቅረባቸው ሲሆን ፍቤቱም መቃወሚያውን መሠረት በማድረግ ለምስክር ወረቀቱ መሰጠት መሠረት የሆነውን ኑዛዜ ይዘት እና ሕጋዊነትን መርምርአል በመጨረሻም ኑዛዜውን በከፊል በመሻር በከፊል ደግሞ አጽድቄአለሁ ብሎአል በበኩላችን ትክክለኛ አካሄድ ሆኖ ያላገኘነውም ይህንን ነው በመጀመሪያ ደረጃ ፍቤቱ በሕጉ የተቀመጠውን ድንጋጌ መሠረት በማድረግ ነዛዜው ፈራሽ ነው እንዲባል ክስ አልቀረበለትም የፍቤቱ የዳኝነት ሥልጣን የተወሰነ በመሆኑ በሥልጣን ክልሉ ስር የሚወድቀውን የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ነው ጥያቄ የቀረበለት ይህን ጥያቄ ተቀብሎ ሰጥቶት የነበረውን የምስክር ወረቀት ተጠሪዎች ካቀረቡለት መቃወሚያ አንጻር ሲመዝነው ተገቢ አልነበረም የሚል ድምዳሜ ከደረሰም በፍብሕቁ በተደነገገው መሠረት መሠረዝ ነው የነበረበት ከዚህ አልፎ ኑዛዜው ፈራሽ ይባል የሚል ክስ በቀረበ ጊዜ ሊደረግ እንደሚችለው ሁሉ ኑዛዜውን በከፊል ሽሬአለሁ ማለቱ ትክክል አይደለም የሕግ መሠረትም የለውም ከሁሉ በላይ ደግሞ ፍቤቱ ወደ ኑዛዜው ይዘት እና ሕጋዊነት ሁኔታ ገብቶ ውሳኔ መስጠት የሚችልበት ሕጋዊ መንገድ አልነበረውም እንጂ ሕጋዊ መንገድ ነበረው ተብሎ ቢሆን ኖሮ እንኳን የደረሰበት መደምደሚያ የኑዛዜን ፎርም እና ማስረጃ ከሚመለከተው ሕግ አንፃር ሊታይ ፍጹም የተሳሳተ ነው ለክርክሩ መነሻ የሆነው ኑዛዜ በግልጽ የተደረገ ኑዛዜ አንደሆነ በፍቤቱ ውሳኔ ተመልክቶአል በግልጽ የተደረገ ኑዛዜ ሊያሟላቸው የሚገቡትን በፍብሕቁ ስር የተመለከቱትን መስፈርቶች ያሟላ አንደሆነም ፍቤቱ ማረጋገጡን በውሳኔው ላይ አመልክቶአል ይህን ሁሉ ካረጋገጠ በኋላ በከፊል ሽሬዋለሁ ያለው ሟች ንብረቱ ባልሆነው ንብረት ላይ ጭምር ተናዚል በማለት እንደሆነ ከውሳኔው ይዘት ለመገንዘብ ችለናል በሕጉ በግልጽ እንደተመለከተው በግልጽ የተደረገው ኑዛዜ በሕጉ መሠረት አልተደረገም ተብሎ ሊነቀፍ የሚችለው በፍብሕቁ የተቀመጡትን መስፈርቶች ያላሟላ ሆኖ ሲገኝ ነው የስር ፍቤት ነዛዜውን ለመንቀፍ ምክንያት ያደገው ነጥብ የኑዛዜውን ሕጋዊነት በተመለከተ አግባብነት የለውም ተናዛ የአሱ ባልሆነው ንብረት ጭምር ተናዚል የሚባል ቢሆን የንብረት ክርክር ሲቀርብ እራሱን ችሎ የሚታይ ጉዳይ ነው ፍቤቱ ይህን ነጥብ በማድረግ የኑዛዜውን ሕጋዊነት ፎርም መንቀፍ ተገቢ አይደለም የምንለውም በዚህ ምክንያት ነው ሲጠቃለል የስር ፍቤቶች የተጠሪዎችን መቃወሚያ መሠረት በማድረግ የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለት ሆኖ አግኝተነዋል ውሳኔ አቤቱታ የቀረበበት በድሬዳዋ ጊዜያዊ አስተዳደር የድሬዳዋ ከተማ የመጀመያ ደረጃ ፍቤት በመቁ የካቲት ቀን ዓም ተሰጥቶ በይግባኝ ሰሚው ፍቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም በተሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሳኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽሮአል ቀደም ሲል ለአመልካች የተሰጠው የወራሽነት የምሰክር ወረቀት የሚሰረዝበት የሕግ ምከንያት የለም ብለናል ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ፀመ የሰመቁ ሰኔ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ አመልካች ወሮ ዘነበወርቅ ወልዱ ፀጋ ወኪል እስክንድር ወልዱ ቀረቡ ተጠሪዎች አማሆይ ድብቅነሽ ግዛው ወሮ አዳነች ወልዱ ፀጋ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ በውርስ ንብረት ክፍፍል ላይ የተነሳውን ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ ሲጀመር ከሳሽ የነበረችው የአሁንዋ አመልካች ስትሆን በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሰረተችው ይዘውት ከሚገኘው የውርስ ንብረት ላይ ድርሻዋን እንዲያካፍሉአት ነው የውርስ ንብረት የተባሉት በአዲስ አበባ እና በደሴ ከተማ የሚገኙ ሁለት ቤቶች እንደሆኑም ተገልያፆአል ክሱ የቀረበለት የደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤትም ወደ ክሱ ስረ ነገር ከመግባቱ በፊት አዲስ አበባ ከተማ ይገኛል በተባለው ቤት ላይ የዳኝነት ስልጣን የለኝም ማስተናገድ የምችለው ደሴ ከተማ ውስጥ የሚገኘውን ቤት በሚመለከት የሚቀርበውን ክስ ነው በማለት መዝገቡን ዘግቶአል በዚህ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የአማራ ብክመጠፍቤትም የግዛት ክልል ስልጣን የለኝም ተብሎ በሚሰጥ ትእዛዝ ላይ ይግባኝ ሊቀርብ አይችልም የሚል ምክንያት በመስጠት ይግባኙን ሳያስተናግድ ቀርቶአል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው እኛም አመልካች ሕዳር ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪዎችን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ የተወሰነው አመልካች ለደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ያቀረበችው የውርስ ንብረት ክፍፍልን የሚመለከተው ክስ በግዛት ክልል የዳኝነት ስልጣን ምክንያት አይስተናገድም የመባሉን አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህም መሠረት ይህን ነጥብ ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ትእዛዝ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር መገዝብ እንደቻልነው አመልካች እና ኛ ተጠሪ የሟች አቶ ወልዱ ፀጋ ልጆች ሲሆኑ ኛ ተጠሪ ደግሞ የሟቹ ሚሜስት ናቸው ሟች ይኖሩ የነበሩት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን አንደሆነና የሞቱትም በዚሁ ቦታ ስለመሆኑ በክርክሩ ተመልክቶአል ከዚህም በተጨማሪ ተጠሪዎች ሟች በኖሩበትና በሞቱበት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን በደሴ ወረዳ ፍሃቤት የውርስ ንብረት ክፍፍል ጥያቄ ማቅረባቸውን ከቀረበው ክርክር ተመልክተናል እንደምናየው ጉዳዩ የውርስ ንብረት ክፍፍልን የሚመለከት ነው አመልካች በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሰረተችው የውርስ ዛብት ነው ከተባለው ንብረት ላይ ድርሻዋን ለማግኘት ነው በአጠቃላይ ክርክሩ የፍትሐብሔር እንደመሆኑ የሚመራው በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ መሠረት ነው በግዛት ክልል ስለሚወሰን የዳኝነት ሥልጣን በተመለከተ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንደኛ መጽሐፍ በምዕራፍ ስር ካሉት ድንጋጌዎች ውስጥ በቁጥር የተመለከተውም ለጉዳዩ አወሳሰን ተገቢነት ያለው ነውፎ ይህ ድንጋጌ በውርስ ምክንያት የሚቀርብ ክስ የሚታይበትን ቦታ የሚወሰን ነው ክሱ መቅረብ ያለበት ወይም የሚቀርበው የውርሱ ክፍያ በተጀመረበት ቦታ ለሚገኘው ፍቤት እንደሆነም ያመለክታል ሕጉ ይህን ያህል ግልጽ ከሆነ ደግሞ የውርስ ሃብት የሆኑ ንብርቶች በተለያዩ ቦታዎች የመኖራቸውን ጉዳይ ግምት ውጥስ የሚገባ አይደለም አቤቱታ የቀረበበት ትእዛዝ ከዚህ አንጻር ሲታይም የሕግ መሰረት ያለው አይደለም ይልቁንም መሠረታዊ የሕግ ሥህተት ያለበት ሆኖ ነው ያገኘነው ስለዚህም የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በአማራ ብሔራዊ ክመደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም ተሰጥቶ የክልሉ ጠፍቤት በመቁ መስከረም ቀን ዓም በሰጠው ትአዛዝ ይግባኝ አይባልበትም የተባለው ትእዛዝ በፍብሥሥሕግ ቁ መሰረት ተሽሮአል አመልካች ያቀረበችው የውርስ ክፍፍል ክስ መታየት ያለበት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ፍቤት በመሆኑ ፍቤቱ ክሱን በማስተናገድ በበኩሉ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ ይስጥበት ብለናል ጉዳዩ ይመለስለት ይፃፍና ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ መድን የሰመቁ ጥቅምት ቀን ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ መስፍን እቁበዮናስ አቶ ተሻገር ገስላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አመልካች የቀድሞው የኢትዮጵያ ጭነት ማመላለሻ ኮርፖሬሽን በሕግ የተካው የመንግሥት የልማት ድርጀቶች ባለአደራ ቦርድ ነፈጅ ፍቅሩ ሸዋ አማረ ቀረቡ ተጠሪዎች እነ አጂ ኢትዮጵያ አክሲዮን ማህበር ሰዎች ጠበቃ አጥናፉ ቦጋለ ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ ጉዳይ አንደኛ ተጠሪ የሆነው አጂኛ ኢትዮአክሲዮን ማህበር በሥር ፍቤት ባቀረበው ክስየአሁኑ አመልካች ነዳጅ ለማጓጓዝ ገንዘብ እየተከፈለው የትራንስፖርት አገልግሎት ሲሰጥ በአጓጓዥነት የተሰጡትን የነዳጅ ውጤቶች ልማድንና የማጓጓዝ ውልን በመጣስ ብቃት የሌላቸውን መኪናዎች በማሰማራትና በሾፌሮች ጥንቃቄ ጉድለት በተለያዩ ቦታዎች በደረሱ አደጋዎች የተጫነው ነዳጅ በመፍሰሱ የብር አራት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺ ሁለት መቶ ሰባ ሦስት ብር ከሰባ ሳንቲም ኪሣራ የደረሰበት መሆኑን ገልጾ አንደኛ ተጠሪ የነበረው የአሁነ አመልካች ከወለዱ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል የአሁኑ አመልካች በበኩሉበአዋጅ ቁጥር እንዲሁም በሕግ ክፍል ማስታወቂያ ቁጥር እና መሠረት አመልካች ከተራ ቁጥር የተዘረዘሩት ተጠሪዎች ጭነት አንዲያገኙ በተራ መዝግቦ ከአስጫኝ ጋር በማገናኘት ከሁለቱም ወገኖች ማለትም ከአስጫኝና ከአጓጓዥ የተፈቀደለትን የአገልግሎት ዋጋ ከመቀበል ውጭ የእነርሱ ወኪል ያለመሆኑንእንዲሁም በስማቸው የተዋዋለው ውልና የተረከበውም ነዳጅ ስለሌለ በኃላፊነት ሊጠየቅ የማይገባ መሆነንእያንዳንዱ መኪና ላጓጓዘው ነዳጅ ኃላፊነቱ የእርሱ መሆኑን በማስረዳት ተከራክሯል የራሱ በሆኑት ተሽከርካሪዎች ለጫኑትና ደረሰ ለተባለው የነዳጅ ጉድለት ደግሞ በንሕቁ መሠረት ከአቅም በላይ የደረሰ አደጋ ስለሆነ ሊጠየቅ የማይገባው መሆኑን በመግለጽ በሰፊው ተከራክሯልፎ ከተራ ቁጥር የተዘረዘሩት የጭነት ማጓጓዣ ባለቤቶችም በበኩላቸው ከአሁኑ ተጠሪ ጋር የውል ግንኙነት የሌላቸውና ከአቅም በላይ በደረሰ አደጋ ሊጠየቁ የማይገባቸው መሆኑን ገልፀው ተከራክረዋል የፌመደፍቤት በጉዳዩ የቀረበውን ሰፊ ክርክር መርምሮ ከፍ ብሎ በተጠቀሰው አዋጅና የሕግ ክፍል ማስታወቂያ መሠረት በአሆኑ አመልካችና ከተራ ቁጥር በተጠቀሱት ባለንብረቶች መካከል የባለኮሚስዮንነት የሕግ ውክልና ግንኙነት ተፈጥሯራል በንሕቁ መሠረት አንደኛ መልስ ሰጭ ከሆነው አስጫኝ ጋር ውል አድርጓል ውሉም በቀረቡት የገንዘብ መክፈያ ደረሰኞች ተረጋግጦአል በመሆኑም በተቀሩት መልስ ሰጭዎችም ላይ ለደረሰው ጉዳት የአሁኑ አመልካች ኃላፊ ነውፎ በራሱ ተሽከርካሪዎች ለጫነውና ደረሰ ለተባለው ጉድለትም ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ስለሌለ ከኃላፊነት ነፃ አይደለም በማለት ወስኖ የደረሰው ጉድለት ለመተመን የቀረቡት ማስረጃዎች ክብደት የሚሰጣቸው ባለመሆናቸው ሂሳቡ በባለሙያ ተሰርቶ እንዲቀርብ አዚል ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለት የፌከፍቤት የሥር ፍቤትን ውሳኔ አንዳለ አጽንቶታል ይህ የሰበር ቅሬታ የቀረበው በዚህ ውሳኔ ላይ ሲሆን ይህ ሰበር ችሎት የካቲት ቀን በዋለው ችሎት የአሁኑ አመልካች በተጠሪዎች ከ በተጠቀሱት ተጭኖ ሲጓጓዝ ብክነት ለደረሰበት ነዳጅ ኃላፊ መባሉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ሲባል መዝገቡ ለሰበር እንዲቀርብ በማድረግ ጉዳዩ በሚሰማበትና ከዚያ በኋላ በተያዙ ተከታታይ ቀጠሮዎች ተጠሪዎች ባለመቅረባቸው ጉዳዩ በሌሉበት እንዲታይ ታዞ መዝገቡ ተመርምሯል በዚህ ጉዳይ የአሁኑ አመልካች በአዋጅ ቁጥር መሠረት ለተሽከርካሪዎች የስምሪት ፈቃድ ይሰጥና በሕግ ክፍል ማስታወቂያ ቁጥር እና መሠረት የተፈቀደለትን የአገልግሎት ክፍያ ይቀበል የነበረ መሆኑ ታውቋል ከዚህ በተጨማሪ አመልካች የራሱ በሆኑ የጭነት ተሽከርካሪዎችም የጭነት ማጓጓዝ ሥራ ይሰራ የነበረ መሆኑም አላከራከረም የአሁኖቹ ተጠሪዎችም በአመልካች አማካኝነት በሚያገኙት ስምሪትና ጭነት ባለንብረት በሆኑባቸው የግል ተሽከርካሪዎቸቸው ከሳሽ የነበረውን የአሁኑን አንደኛ ተጠሪ ነዳጅና የነዳጅ ውጤቶች ከቦታ ወደ ቦታ ያጓጉዙ አንደነበረ አልተካደም የሥር ፍቤት የንግድ ሕግ ቁጥር ያለውን መሠረት በማድረግ በሥር ጣልቃ ገብ በነበሩት በአሁኖቹ ከ በተመለከቱት ተጠሪዎችና በአሁኑ አመልካች መካከል የባለ ኮሚስዮን የሕግ ውክልና ግንኙነት ተፈጥሯል በማለት የአሁኑ አመልካች ከከሳሽ ጋር በገባው የኮሚስዮን ወኪልነት መሠረት በከሳሽ ላይ ለደረሰው ጉዳት በሙሉ ኃላፊ ነው ብሏል በመሠረቱ በንግድ ሕግ ቁጥር ላይ የተመለከተው የባለኮሚስዮንነት ትርጓሜ ማንም አበል ለማግኘት ባለኮሚስዮን ስላደረጋቸው ሰው በራሳቸው ስም ሸቀጦችን ወይም የሚንቀሳቀሱ ዕቃዎችን ወይም ማናቸውም እነዚህን የመሣሰሉ ዕቃዎችን ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ወይም የማጓጓዝ ውል ለመዋዋል በራሳቸው ሥም ግዴታ የሚገቡ ሰዎችን ወይም የንግድ ማህበሮችን እንደሚሸፍን ይደነግጋል በያዝነው ጉዳይ የአሁኑ አመልካች በወቅቱ በነበረው ፖሊሲ መሠረት የመንገድ ትራንስፖርት ቅንጅትን ለመጠበቅ ሲባል የግል ተሽከርካሪዎች ጭነት እንዲያገኙ ሥራውን በማዕከላዊነት እንዲመራና ስለአገልግሎቱ ከአስጫኝ እና ከጫኙ ክፍያ እንዲያገኝ መደረጉ ብቻውን እንደ ሕጉ አነጋገር ባለኮሚስዮን ስላደረጉት ሰዎች በራሱ ሥም የማጓጓዝ ውል ለመዋዋል ግዴታ የገባ ነው መባሉ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል። ሆኖም ግን የምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በዚህ ጉዳይ አመልካች የመዳረግ መብት የለውም በማለት ክሱን ሳይቀበል መቅረቱ እንደዚሁም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ይህንኑ ስህተት ሳያርም መቅረቱ ለድንጋጌው የተሳሳተ ትርጉም በመስጠት መሆኑን ለመገንዘብ ችለናል ወደ ኛው ጭብጥ ስናልፍም የመድን ሽፋን የተገባለት የተጠሪዎች መኪና ቅሪቱ ተገምቶ ብር ዐ ሺህ እንደሆነ እንደዚሁም የጉዳት ካሣ ብር ሺህ እንደሆነና በድምሩ ብር ሺህ አመልካች ለተጠሪዎች መክፈል እንደሚገባው በሥር ፍቤት ክርክር ሲደረግ በማስረጃ የተረጋገጠ ሲሆን ተጠሪዎች ባቀረቡት የተከሳሽ ከሣሽነት ክስ የዚህ ገንዘብ ግማሹ ብር ፏ ሺህ ለወሮ ለተብርፃን እንዲከፈል መወሰኑ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አላገኘነውም በሌላ በኩልም ተጠሪዎች እንዲከፈላቸው የጠየቁትን የተቋረጠ ገቢ በተመለከተም አመልካች የሚከራከረው ግራ ቀኛችን ባደረግነው ውል የተቋረጠ ገቢ እንደማይከፈል ተስማምተናል በማለት ሲሆን ነገር ግን አመልካች ጉዳት የደረሰበትን የተጠሪዎች መኪና ጠግኖ ለማስረከብ ስምምነቱን የገለጸ አንደመሆኑ መጠን ከውሉ አኳያ የተቋረጠ ጥቅም ለመክፈል የማይገደደው መኪናውን ለመጠገን አስፈላጊ ለሆነው ጊዜ ማመስጠገኑ ለሚወስደው ጊዜ ብቻ እንጂ ከዚህ አልፎ መኪናው ሳይጠገን ለቀረበት ጊዜ በሙሉ ሊሆን አይችልም በዚሁ መሠረትም መኪናውን ለመጠገን ያስፈልጋል የተባለው የ ወር ጊዜ በአእምሮ ግምት ተቀባይነት ያለው ነው በዚህ ጊዜ መኪናውን አመልካች ጠግኖ ለተጠሪዎች ካላስረከበ ደግሞ ተጠግኖ ቢሆን ኖሮ ሊያስገኝ ይችል የነበረውንና ነገር ግን ሳይከፈል የቀረውን የተቋረጠ ገቢ መክፈል ይኖርበታል ማለት ነው መጠኑን በተመለከተም መኪናው በቀን ብር ዐዐ ገቢ ያስገባ አንደነበር ተጠሪዎች ገልጸው በዚሁ ልክ ካሣ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል ሆኖም ግን ጉዳት የደረሰበት መኪና ይህን ያሕል ገቢ ያስገባ እንደነበር በማስረጃ አላረጋገጡም ከውልም ሆነ ከውል ውጭ ባለ ግንኙነት የጉዳት ካሣ እንዲከፈለው የሚጠይቅ ወገን የደረሰበትን ኪሣራ « በማስረጃ ማረጋገጥ አንደሚገባው ከፍብሕቁ ዐ እና ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል ይሁንና ጉዳት መድረሱ እስከተረጋገጠ ድረስ የነገሩን አካባቢ ሁኔታ ግምት ውስጥ በመክተት የካሣ መጠኑን ዳኞች በርትፅ መወሰን እንዲችሉ ሕጉ ሥልጣን የሰጣቸው እንደመሆኑ መጠን በተያዘውም ጉዳይ የከፍተኛው ፍቤት አመልካች በክሥ የተጠቀውን የገንዘብ መጠን በበኩሉ አስልቶ እንዲከፈል ውሣኔ መስጠቱ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አላገኘነውም ነዓ ውሣኔ አመልካች በዚህ ጉዳይ የመዳረግ መብት ስለሌለው በክስ የጠየቀው ገንዘብ ሊከፈለው አይገባም ተብሎ በሥር ፍቤቶች የተሰጠው ውሣኔ ለንግድ ሕግ ቁጥር የተሳሳተ ትርጉም በመስጠት ስለሆነ ይህንነ ሽረን አመልካች የመዳረግ መብት አለው ብለናል ስለሆነም አመልካች በመዳረግ ከጠየቀው ብር ሶስት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ሶስት መቶ አርባ ሁለት ላይ ግማሹን ብር አንድ መቶ ዘጠና ስምንት ሺህ አንድ መቶ ሰባ አንድ ብር ተጠሪ ወሮ ለተብርፃን በየነ ሊከፍሉ ይገባል ብለናል አመልካች በድምሩ ብር ዐዐ ሥስት መቶ ሠማንያ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ብር ለተጠሪ ሊከፍል ይገባል ተብሉ የተወሰነው የካሣ መጠን በአግባቡ ስለሆነ አጽንተነዋል ግራ ቀኙ አንዱ ከሌላው የሚፈልገው ገንዘብ ሲቻቻል አመልካች ብር ዐ አንድ መቶ ሰማንያ ሰባት ሺህ ሀያ ዘጠኝ ብር ለተጠሪ መክፈል የሚገባው ስለሆነ ይህንነ ገንዘብ እንዲከፍል ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ወንጀል የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች አቶ ሐጐስ ወልዱ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ አብዱራሂም አህመድ አቶ ታፈሰ ይርጋ አመልካች የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዐሕግ ቀርቧል ተጠሪ ወር ሰይድ እንድሪስ ዩሱፍ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው አመልካች ነሐሴ ቀን ዓም ፅፎ ባቀረበው ማመልከቻ መነሻነት ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ ተጠሪ የወመሕቁ ሀን በመተላለፍ መጋቢት ቀን ዓም ከምሽቱ ሰዓት ላይ በፖዌ ልዩ ወረዳ በዳንጉር ቀበሌ መክላከያ ካምኛ አካባቢ ሰውን ለመግደል አስቦና አቅዶ ሟች ማስተዋል አማርቸኩል የተባለችውን በእኔ ላይ ወንድ ደርባለች በሚል ምክንያት ቂም ይዞ በመነሳሳት በያዘው ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ጭካኔበተሞላበት ሁኔታ በሶስት ጥይት ደብድቦ ገድሏል የሚል ክስ ቀርቦበት ድርጊቱ በማለስረጃ ከተረጋገጠ በኋላ በተጠቀሰበት አንቀጽ መሠረት ጥፋተኛ ተብሎ በአድሜ ልክ ፅኑ አስራት እንዲቀጣ የመተከል ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፈርዷል ተጠሪ በቅጣት ውሣኔው ላይ ቅር በመሰኘት ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርቦ ፍርድ ቤቱም በአብላጫ ድምፅ ቅጣቱን ወደ ፃያ አመት ፅኑ አስራት ዝቅ አድርጐለታል የክልሉ ዓቃቤ ሕግም በዚሁ የቅጣት ውሣኔ ቅር ተሰኝቶ ይህን የሰበር አቤቱታ አቅርቧል ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም የሰበር አቤቱታውን መርምሮ ተጠሪን በማስቀረብ ግራ ቀኙን አከራክሯልፎ ክርክሩንም አግባብ ካለው ሕግ ጋር በማገናዘብ መርም ል ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ተጠሪ ድርጊቱን መፈፀሙን ያለመካዱን ተጠሪ ድርጊቱን ቢያምንም የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ ዓቃቤ ሕግ ማስረጃዎቹን እንዲያቀርብ ማድረጉን እና ተጠሪም እንዲከላከል መብቱ ቢጠበቅለትም የመከላከያ ማስረጃ አንደሌለው መግለፁን አስፍሮ በቀረበው የዓቃቤ ሕገ ማስረጃ መሠረት የጥፋተኝነት ውሣኔ ካሣለፈ በኋላ ዓቃቤ ሕግ ቅጣቱ በተጠሪው ላይ ከብዶ እንዲወሰንበት በመጠየቅ ተጠሪም በበኩሉ ቀደም ሲል ሌላ ወንጀል አለመፈፀሙን እና ለ ዓመት በመከላከያ ሠራዊት አባልነት ማገልገሉን በመግለፅ ግራ ቀኙ የየበኩላቸውን የቅጣት አስተየየት ካቀረቡ በኋላ ፍርድ ቤቱ በአንድ በኩል ተጠሪ በመጥፎ አመል በቂመኝነትና በወራዳነት ፍፁም በሆነ ፈቃደኝነትና ከፍተኛ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ሟችን አያ ጠ መግደሉ ጨካኝነቱን እንደሚያመለክት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ማገልገሉና የቀድሞ ሪከርድ የሌለበት መሆኑን መገንዘቡን ገልፆ ቅጣቱን ከማቅለል ይልቅ የወንጀል አፈፃፀሙ ቅጣቱ እንዲከብድ የሚያመዝን ሆኖ መገኘቱን በመግለፅ ተጠሪ በዕድሜ ክል ፅነ አሥራት እንዲቀጣ ወስኗል ተጠሪም በዚህ ውሳኔ ቅር ተሰኝቶ ባቀረበው ይግባኝ ወንጀሉን የፈፀመው የትዳር ጓደኛው የሆነችው ሟች በርሱ ላይ ሌላ ወንድ መደረቧ ለወንጀል ያነሣሣው መሆኑን እና በወቅቱም በስካር መንፈስ ራሱን ሊቆጣጠር የማይችልበት ደረጃ ላይ በመድረሱ መሆኑን በተጨማሪም የስካር መንፈሱ እንደበረደለት በድርጊቱ ተፀፅቶ እጁን ለፖሊስ መስጠቱን ገልፆ ጠቀላይ ፍርድ ቤቱም ይግባኙን ከመረመረ በኋላ ተጠሪ ድርጊቱን በደም ፍላትና በስካር መንፈስ ለመፈፀሙ ያቀረባቸው ምክንያቶች ቅጣቱን ለማቅለል የሚያስችሉ ቢሆኑም ተጠሪ ድርጊቱን በዚህ መሠረት ለመፈፀሙ ማስረጃ ያለማቅረቡን በመግለፅ ክርክሩን ውድቅ አድርጓል ፍርድ ቤቱ ከዚህ በመቀጠል ተጠሪ ጥፋቱን አምኖ ለመንግሥት እጁን መስጠቱ በሌላ ማስረጃ ባይረጋገጥም ሟች ሌላ ወንድ ደርባለች በማለት መጠርጠሩ ስሜቱን ሊነካና መረበሽንም የሚያስከትልበት ሆኖ መታሰቡና ተጠሪ አስካሁን ባሉት ክርክሮች የወንጀል ድርጊቱን አምኖ መፀፀቱን ስለሚያመለክት በወመሕቁ መ እና ሠ እንዲሁም መ መሠረት ከመነሻው አድሜ ልክ በመፍረድ ቅጣቱን ወደ አመት ዝቅ አድርጓል በመሆኑም በተጠሪ ላይ በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተወሰነው የአድሜ ልክ ፅኑ አሥራት በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተሻሸሉ መወሰኑ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ቀጥሎ እንመለከታለን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቅጣትን ለማቅለል ከተጠቀመባቸው ሦስት ምክንያቶች ውስጥ ሁለቱ ማለትም ተጠሪ ድርጊቱን ከፈፀመ በላ አጁን ለመንግሥት መስጠቱ መፀፀቱን ያመለክታል በማለት እና እስካሁን በተካሔዱት ክርክሮችም ተጠሪ ድርጊቱን አምኖ ቅጣቱ ብቻ ይቀነስልኝ ማለቱም በተመሳሳይ ሁኔታ ፀፀትን ያመለክታል በማለት የጠቀሳቸው ምክንያቶች ተቀባይነት ያላቸው ሆነው አልተገኙም ለማለት አልተቻልም ምክንያቱም በ ዓም በወጣው አዲሱ የወንጀል ሕግ በአንቀጽ መ ላይ ወንጀለኛው ወንጀሉን ካደረሰ በኋላ በእውነት የተፀፀተ መሆኑን ለማስረዳት ጥፋቱን በመገንዘብ ራሱን ለፍትሕ አካላት ካቀረበ በክስ ማመልከቻው የተገለፀውን የወንጀል ዝርዝር በሙሉ ካመነ ቅጣቱ አእንደሚቀልለት ተደንግጓል ምንም እንኳን ተጠሪ ድርጊቱን በፈፀመበት ወቅት ተፈፃሚው ሕግ የቀድሞው የ ዓም የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ቢሆንም ጉዳዩ በይግባኝ ታይቶ ውሣኔ በተሰጠበት ሰኔ ቀን ዓም አዲሱ የወንጀል ሕግ ከግንቦት ቀን ዓም ጀምሮ በሥራ ላይ የዋለ በመሆኑና በአዲሱ የወንጀል ሕግ አንቀጽ ሥር አዲሱ ሕግ ከፀና በላ በሥራ ላይ ከነበረው ከቀድሞው የወንጀል ሕግ ይልቅ አዲሱ ሕግ ቅጣት የሚያቀል ከሆነ በዚሁ ሕግ መሠረት ቅጣቱ እንደሚቀል የተደነገገ በመሆኑ ተጠሪ ድርጊቱን ከፈፀመ በኋላ እጁን ለመንግሥት መስጠቱና የቀረበበትንም ክስ ገና ከመነሻው ጀምሮ አምኖ መገኘቱ የቅጣት ማቅለያ ተጠቃሚ የሚያደርገው ሆኖ ተገኝቷል ስለዚህ ከላይ የተመለከቱት ምክንያቶች ቅጣቱን ለማቅለል የሚያስችሉ በመሆናቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአብላጫ ድምፅ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ አልተገኘም ውሣኔ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በወይመቁ ሰኔ ቀን ዓም በአብላጫ ድምፅ የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል ውሳኔው መዕናቱን እንዲያውቁት የውሣኔው ግልባጭ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ለተጠሪ በየአድራሻቸው ይድረሳቸው መዘገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች አቶ አብዱልቃድር መሐመድ አቶ ሐጐስ ወልዱ አቶ ተገኔ ጌታነህ አቶ ተሻገር ገሥላሴ አቶ ብርፃኑ አመነው አመልካች የአማራ ብክመንግሥት ፍትሕ ቢሮ ዓቃቤ ሕግ አቶ ደረጀ ኃይሉ ተጠሪ አስማማው አራጌ ከጠበቃ ወሮ አዜብ ፋንታሁን ጋር ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ መዝገቡ ለሰበር ችሎት የቀረበው ተጠሪው በፈጸመው የወንጀል ድርጊት በሥር ፍቤት ጥፋተኛ የተባለበት የወመህ አንቀጽ በክልሉ ጠፍቤት መለወጡ አግባብ አይደለም ሲል አመልካች ህዳር ቀን ዓም አቤቱታ በማቅረቡ ነው የሰበር ችሎትም መዝገቡን ከመረመረ በኋላ ጠቅላይ ፍቤቱ የተጠቀሰውን የሕግ አንቀጽ ለመቀየር ሕጋዊ ምክንያት የነበረው መሆን አለመሆኑን ለማጣራት ግራ ቀኙን አስቀርቦ አከራክሯል ከሥር ፍቤት ውሳኔ መረዳት እንደተቻለው ለከፍተኛው ፍቤት የቀረበው ክስ ተጠሪ ሟችን ሚስቱ የነበረችውን ገነት ገበዬን ጨካኝና ነውረኛ በሆነ አኳኋን በመግደሉ በወመህግ አንቀጽ ሀ አመልካች መስሪያ ቤት ክስ አቅርቦ የስር ፍቤትም የግራ ቀኙን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ከተጠሪው የወንጀል አፈጻጸም አኳያ በተጠቀሰው የወንጀል ሕግ አንቀጽ የጥፋተኛነት ውሳኔ ሰጥቶ በፃዛያ ዓመት ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ፈርዶበታል በዚህ ፍርድ ቅር በመሰኘት ተጠሪ ለክልሉ ጠፍቤት ይግባኝ በማቅረቡ የክልሉ ጠፍቤት ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ የወንጀሉን አፈጻጸም መነሻ ምክንያትና ሁኔታ በመዘርዘር ከፍተኛው ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ በማሻሻል በወመህ አንቀጽ መሠረት ጥፋተኛ በማለት በዚሁ መሠረት በአሥራ ሦስት ዓመት ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ፍርድ ሰጥቷል ይህ ፍርድ በመሠረቱ የሕግ ስሕተት አለው ሲል አመልካች ያቀረበው አቤቱታ የተጠሪ የወንጀል አፈጻጸም በወመህ አንቀጽ ሀ ጥፋተኛ የሚያደርገው ሆኖ ሳለ ወደ ለመለወጥ የሕግ መሠረት የለውም የሚል ነው ከዚሁ አኳያ የሰበር ችሎቱ መዝገቡን መርምሯል በከፍተኛ ፍቤት ውሳኔ ሐተታ እንደተመለከተው ሐምሌ ቀን ዓም ከቀኑ ሰዓት ላይ ተጠሪና ሟች መኖሪያ ቤት ውስጥ ሆነው ተጠሪ የመኖሪያ ቤታቸውን በር ከዘጋ በኋላ ሟችን በበር መቀርቀሪያ ግንባራን መትቷት በወደቀችበት ቦታ ሁለት እጆቿን በማሰር ብልቷ ውስጥ እጁን በማስገባት ከባድ ጉዳት እንዳደረሰባት እና በዚሁ ምክንያት ሐምሌ ቀን ዓም ሕይወቷ እንዳለፈ በስር ፍቤት ተረጋግጧል ይህንን የወንጀል ድርጊት አፈጻጸም ከቀረቡት ማስረጃዎች ጋር በማገናዘብ የድርጊቱ አፈጻጸም የተጠሪን ጨካኝነት እና ነውረኛነት ያረጋግጣል በማለት የከፍተኛው ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ ለመለወጥ የጠቅላይ ፍቤቱ ያስቀመጠው ምክንያት የተጠሪው ድርጊት ዘግናኝ ቢሆንም ሟችን ለመግደል አስቀድሞ ያሰበና የተዘጋጀ ለመሆኑ አልተረጋገጠም የሚል ነው። የሚለው ነው በዚህ መሠረትም ይህን ነጥብ ከቀረበው ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ቀደም ሲል እንደተመለከተው አመልካች ለአፈፃፀም ያቀረበችው ውሣኔ በዐ ዓም የተሰጠው ነው ይህ ውሣኔ ሦስት አባላት ባሉት የሽምግልና ጉባዔ የተሰጠ ነው የሽምግልና ጉባዔው ሊቋቋም የቻለው ጉዳዩ ስለህበረት ስራ ማህበራት በወጣው አዋጅ ቁ መሠረት መታየት ያለበት በሽምግልና ነው ተብሎ በፍቤት ቀደም ሲል በመበየኑ ምክንያት አንደሆነም ከመዝገቡ ተመልክተናል በዚህ መሠረት የሽምግልና ጉባዔው ከተቋቋመ በኋላም አመልካች በከሣሽነትተጠሪ ደግሞ በተከሣሽነት ቀርበው ተከራክረዋል በመጨረሻም ጉባዔው ውሣኔ ሰጥቶአል በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ የሽምግልና ጉባዔው በሰጠው ውሣኔ ላይ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ በማቅረቡ በዚህ ይግባኝ ደረጃም ክርክሩ ተሰምቶአል ፍቤቱም የሽምግልና ጉባዔውን ውሣኔ አጽንቶአል አመልካች የአፈፃፀም ክሱን ያቀረበችው ከዚህ በኋላ ነው እንደምንመለከተው በፍቤት ቀደም ሲል በተሰጠው ብይን መሠረት ሦስት አባላት ያሉት የሽምግልና ጉባዔ ከመቋቋሙም በላይ አመልካች እና ተጠሪም የጉባዔውን ስልጣን በመቀበል ቀርበው ተከራክረዋል በመሆኑም ውሣኔውን የሰጠው የሽምግልና ጉባዔ በፍብሥሥሕግ ቁ እንደተመለከተው በፍቤት ሊፈፀም የሚችል ውሣኔ ሊሰጥ የሚችል አካል ነው ማለት ነው በግልግል ወይም በቤተዘመድ ሽምግልና ዳኞች የተሰጠ ውሣኔ የሚፈፀመው በመደበኛ ፍቤት የተሰጠ ውሣኔ በሚፈፀምበት አይነትና ሁኔታ እንደሆነ በፍብሥሥሕግ ቁ በግልጽ ተመልክቶአል የስር ፍቤቶች የሰጡት ውሣኔ ግን ይህን በግልጽ የተመለከተውን ሕግ የተከተለ አይደለም ስለዚህም ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ለማለት ችለናል ውሣኔ በዚህ ጉደይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽረዋል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሣቸውን ይቻሉ ውሣኔው ለሰበር ፍቤቶች ይተላለፍ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የሦስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ዐ ታህሣሥ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች አቶ ብርሃኔ ገእግዚአብሔር ጠበቃ መሰለ ገጊዮርጊስ ተጠሪ ወሮ ገርጊስ ናይዝጊ ጠበቃ ወንድሙ ግዛው መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው በአመልካችና በተጠሪ መካከል የነበረው ጋብቻ በፍቺ ከፈረሰ በኋላ የጋራ ንብረት ክፍፍልም በተመለከተ ፍቤቱ ውሣኔ ሲሰጥ አሁን ለዚህ ክርክር ምክንያት የሆነው በወረዳ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥር ዐ የሆነውን ቤት የገበያ ዋጋ ግምት ግማሽ የአሁን ተጠሪ ለአሁን አመልካች ሰጥተው ቤቱን እንዲያስቀሩ ተጠሪ በዚህ መልኩ የቤቱን የገበያ ዋጋ ግማሽ ለአመልካች ለመስጠት ፈቃደኛ ካልሆኑ ግራ ቀኙ ተስማምተው ቤቱን በገበያ ዋጋ ሸጠው የቤቱን ሽያጭ ዋጋ ገንዘብ ለሁለት እንዲካፈሉ በዚህ መልኩም ቤቱም ለመሸጥ ካልቻሉም በፍርድ አፈፃፀም መምሪያ በኩል በሐራጅ ተሸጦ ገንዘቡን አኩል አንዲካፈሉ የሜል ውሣኔ ሰጥቶ በዚሁ ውሣኔ መሠረት አፈፃፀሙ ቀጥሎ ፍቤቱ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ መሬት አስተዳደር ቤቱን በመሐንዲስ አማካይኝነት ገምቶ ውጤቱን እንዲልክ ትዕዛዝ ሠጥቶ የቤቱ ግምት ብር አንደሆነ በመግለጽ ክፍለ ከተማው ለፍቤቱ መልስ በመስጠቱ የዚህን ግምት ግማሹን ተጠሪ ለአመልካች ሰጥተው ቤቱን እንዲያስቀሩ በማለት የአፈፃፀም ትፅዛዝ ሠጥቶ በዚሁ ትዕዛዝ አመልካች ቅሬታ አድሮባቸው የይግባኝ ቅሬታቸውን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው በፍብሕሥሥሃቁ መሠረት ይግባኙ ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት ቅሬታ በማቅረባቸው ነው ይህ ሰበር ችሎትም የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ አፈፃፀሙ የቀጠለው በፍርዱ መሠረት ስለመሆኑ ለሰበር ቀርቦ ተጣርቶ ሊወሰን የሚገባው መሆኑን በማመኑ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል ምላሽ የሚሻውም የጉዳዩ ጭብጥ አፈፃፀሙ የቀጠለው በፍርዱ መሠረት ነው ወይንስ አይደለም የሚለው ሲሆን በዚሁ ነጥብ ላይ በመመስረት አቤቱታው ተመርምራል በግራ ቀኙ መካከል የነበረው ጋብቻ በፍቺ ከፈረሰ በላ የጋራ ንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ ዐዐ መጋቢት ቀን ዓም በዋለው ችሎት ውሣኔ ሠጥቷል በዚህ ውሣኔ መሠረትም ለዚህ ክርክር ምክንያት የሆነው በወረዳ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥር ዐ የሆነው የጋራ ቤት ከላይ እንደተመለከተው የገበያ ዋጋ ግምቱን ተጠሪ ለአመልካች በመስጠቱ ቤቱን እንዲያስቀሩ ፈቃደኛ ካልሆኑም በሁለቱ የጋራ ስምምነት በገበያ ዋጋ ተሸጦ የሽያጩን ገንዘብ አኩል እንዲካፈሉ ይህም ካልተቻለ በፍርድ አፈፃፀም መመሪያ እኩል በሐራጅ ተሸጦ ገንዘቡን እኩል እንዲካፈሉ በማለት ውሣኔ ሠጥቷል ሆኖም ግን አፈፃፀሙ ሲቀጥል በዚሁ ውሣኔ መሠረት መፈጸም ሲገባው የግራ ቀኙ የጋራ ንብረት የሆነው ቤት በክፍለ ከተማው መሐንዲስ በኩል እንዲገመት መደረጉ ከውሣኔ ያፈነገጠ ከመሆኑም በላይ በውጤት ደረጃም ቢሆን የመሐንዲስ ግምትና የገበያ ዋጋ ልዩነት እንዳለው የሚታመን ስለሆነ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የሰጠው የአፈፃፀም ትዕዛዝ በመቁ ዐዐ መጋቢት ቀን ዓም ፍቤቱ ከሰጠው ውሣኔ ጋር የተጣጣመ ሆኖ አልተገኘም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ጉዳዩ በይግባኝ ሲቀርብለት ይህንኑ ስህተት ማረም ሲገባው ይግባኙን ሳይቀበል በመቅረቱ በአግባቡ ሆኖ አልተገኘም ውሣኔ የፌዴራል መደፍቤት በመቁ በ ዓም የሰጠው የአፈፃፀም ትፅዛዝ እንደዚሁም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ በ ዓም የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯራል የፌዴራል መጀመሪያ ደረፍቤት በመቁ ዐዐ መጋቢት ቀን ዓም በተሰጠው ውሣኔ መሠረት ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት በገበያ ዋጋ አስገምቶ የግምቱን ግማሽ የአሁን ተጠሪ ወሮ ገርጊስ ናይዝጊ ለአሁን አመልካች ለአቶ ብርዛኔ ገእግዚአብሔር በመስጠት ቤቱን እንዲያስቀሩ በዚህ መልኩ ተጠሪ ካልተስማሙ ቤቱን በጋራ በገበያ ዋጋ ሸጠው ገንዘቡን እንዲከፋፈሉ ይህም ካልተቻለ ቤቱ በፍርድ አፈፃፀም መመሪያ በኩል በሐራጅ ተሸጦ ገንዘቡን እኩል እንዲከፋፈሉ እንዲያደርግ ጉዳዩ ተመልሶለታል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ሒሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ አመልካች የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነፈጅ አለሙ ኢብሳ ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነፈጅ የምስራች ደሳለኝ መዝገቡን መርምረን ቀጥሎ የተመለከተውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ ጉዳይ የፍርድ አፈጻጸምን የሚመለከት ሲሆን በፍርድ ባለመብት የአሁን ተጠሪና በፍርድ ባለአዳዎች እና አቶ ካሊድ የሱፍ ሰዎች መካከል የነበረው የፍርድ አፈጻጸም ክርክር በሥር ፍቤት ቀጥሎ በከፍተኛ ቀበሌ ክልል በኛ የፍርድ ባለአዳ ስም ተመዝግቦ የሚገኘው ቁጥር የሆነው መጋዘን ተሽጦ ሕዳር ቀን ዓም በተሰጠው ውሳኔ መሰረት ለፍርድ ባለመብት እንዲከፈል በማለት በቅድሚያ መጋቢት ቀን ዓም ከዚያም በ ዓም የአፈጻጸም ትአዛዝ መስጠቱን ከመዝገቡ የተረዳን ሲሆን ኛው የአፈጻጸም ትአዛዝ ከተሰጠ በላ በፍርድ አፈጻጸም እንዲሸጥ ትአዛዝ የተሰጠበት መጋዘን ላይ መብት ያለኝ ስለሆነ አፈጻጸሙ በዚህ መጋዝን ላይ ሊቀጥል አይገባም በማለት የአሁን አመልካች በፍብሕሥሥቁ መሰረት መቃወሚያ አቅርቦ አፈጻጸሙን በጊዜው ይዞት የነበረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት መቃወሚያው ለፍርድ ባለመብት እንዲደርስ በማድረግ አከራክሮ መቃወሚያው በአግባቡ አልቀረበም የሚልበትን ምክንያት በዝርዝር አስፍሮ ተቀባይነት የለውም ብሉ አስቀድሞ በተሰጠው የአፈጻጸም ትእዛዝ መሰረት ይፄው መጋዘን ተሽጦ በውሳኔው ከፍርድ ባለአዳዎች የሚፈለገው ገንዘብ ለፍርድ ባለመብት እንዲከፈል በማለት ትእዛዝ ሰጥቷል አመልካች በዚሁ ትአዛዝ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት አቅርቦ ፍቤቱም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ የሥር ፍቤት የሰጠው ትእዛዝ ጉድለት የሌለው ነው በማለት ይግባኙን ባለመቀበል ይህንኑ የሥር ፍቤትን ትእዛዝ አጽንቷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንኑ በመቃወም ሲሆን ይህ ችሎትም አቤቱታውን መርምሮ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል ይህም ችሎት በቅድሚያ የተመለከተው የአሁን አመልካች በፍብሕሥሥቁ መሰረት አፈጻጸሙን በመቃወም ለፌዴራል መደፍቤት ያቀረበው አቤቱታ ለፍርድ ባለመብት ብቻ እንዲደርስ ተደርጐ የፍርድ ባለእዳዎች በዚህ ላይ ክርክራቸውን ሳያቀርቡ ትእዛዝ መስጠቱን አግባብነት በተመለከተ ነው በተያዘ ወይም በተከበረ ንብረት ላይ ኛ ወገኖች መብት ያቋቋምን ስለሆነ በዚህ ንብረት ላይ አፈጻጸም ሊቀጥል አይገባም በማለት ኛ ወገኖች በፍብሕሥሥቁ መሰረት መቃወሚያ ሲያቀርቡ ተከራካሪ ወገኖች ይህንኑ መብት የሚቃወሙ ከሆነ ፍቤቱ የተከራካሪ ወገኖችን ክርክር ከሰማ በኋላ ውሳኔ እንደሚሰጥ ከተጠቀሰው የፍብሕሥሥቁ ከፍ ብሎ ከተመለከተውና ከቁጥር ድንጋጌ በግልጽ መገንዘብ ይቻላል በተያዘው ጉዳይ በፍርድ አፈጻጸም እንዲሸጥ የተባለው መጋዘን የኛ የፍርድ ባለእዳ ንብረት ነው እንደተባለ በትእዛዙ ላይ የተመለከተ ሲሆን በዚህ ንብረት ላይ ተቃዋሚው የአሁን አመልካች አፈጻጸሙን በመቃወም አቤቱታ ሲያቀርብ ከላይ ከተጠቀሰው የሥነ ሥርአት ሕጉ ድንጋጌ አኳያ አቤቱታው ለፍርድ ባለመብቱና ለባለአዳዎች ደርሶ የሁሉንም ወገኖች ክርክር በመስማት በፍብሕሥሥቁ መሰረት ፍቤቱ ውሳኔ መስጠት ሲገባው አቤቱታው ለፍርድ ባለመብት ብቻ እንዲደርስ በማድረግ ለዚህ አቤቱታ ምክንያት የሆነውን ትአዛዝ መስጠቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ይህንኑ ጉድለት ሳያርም መቅረቱ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሳኔ የፌመደፍቤት በመቁ በሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ትአዛዝ የፌዴራል ከፍቤትም በመቁ በታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ፍርድ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽራል አመልካች በፍብሕሥሥቁ መሰረት ያቀረበው አቤቱታ ለፍርድ ባለእዳዎችም እንዲደርስ ተደርጐ ግራ ቀኙን አከራክሮ ተገቢ መስሎ የታየውን ውሳኔ እንዲሰጥበት ጉዳዩ ለፌዴራል መደፍቤት ተመልሷል በዚህ ችሎት ትእዛዝ የቀረበው መዝገብ በመጣበት አኳን ይመለስ ግራ ቀኙ ወጭና ኪሳራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሠልጣን አባተማም አመልካች አቶ መሐመድ ትር ጅብሪል ቀርቧል ተጠሪ እነ ወሪት ውበት ላሊሶ ሰዎች ቀርባለች መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ጉዳይ በፍርድ አፈፃፀም ላይ የቀረበ አቤቱታ ሲሆን በደቡብ ብብሕክመ በአዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ በፍርድ ባለመብት ኛ እና ኛ ተጠሪዎች እንደዚሁም በፍርድ ባለዕዳ ኛ ተጠሪ መካከል የነበረው የአፈፃፀም ክርክር ቀጥሉ በአዋሳ ከተማ በከፍተኛ ቀበሌ ክልል የሚገኝ ቤት በሐራጅ እንዲሸጥ የአፈፃፀም ትዕዛዝ ተሰጥቶ እንዳለ የአሁን አመልካች በፍርድ አፈፃፀም በሐራጅ እንዲሸጥ ትዕዛዝ የተሰጠበትን ቤት የፍርድ ባለዕዳ ኛ ተጠሪ በስማቸው ተመዝግቦ እንደሚገኝ የሚያረጋግጥ የባለቤትነት የምስክር ወረቀት አቅርበውልኝ ቤቱን ከእሳቸው ላይ የገዛሁ ከመሆኑም በላይ ባለቤትነቱ በስሜ ተዛውሮ የሚገኝ ስለሆነ ቤቱ በሐራጅ እንዲሸጥ የተሰጠው ውሣኔ ያለአግባብ በመሆኑን ፍቤቱ ይህንኑ ትዕዛዝ ያንሳልኝ በማለት መቃወሚያ አቅርበው ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ በፍርድ አፈፃፀም በሐራጅ እንዲሸጥ ትዕዛዝ የተሰጠበት ቤት አቤቱታ አቅራቢው ያልተከፋፈለ የውርስ ሀብት መሆኑን እየተገነዘበ ከፍርድ ባለዕዳ ላይ ስለመግዛቱ መገንዘብ የተቻለ ስለሆነ አቤቱታው ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ አፈፃፀሙ ሊቀጥል ይገባል በማለት ብይን ሰጥቷል አመልካች በዚሁ ብይን ቅሬታ አድሮባቸው አቤቱታቸውን እስከ ክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት ድረስ ያቀረቡ ቢሆንም አቤቱታቸው ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል ለዚህ ሰበር ችሎትም የቀረበው አቤቱታ ይህንኑ ለማስለወጥ ሲሆን ይህ ችሎት አቤቱታው ለሰበር ይቅረብ ብሎ ተጠሪዎችን በመጥራት ግራ ቀኙን በጽሑፍና በቃል አከራክሯል የዚህን ችሎት ምላሽ ማግኘት የሚገባውም የጉዳዩ ጭብጥ ለክርክሩ ምክንያት በሆነው ቤት ላይ አፈፃፀም ሊቀጥል አይገባም በማለት አመልካች ያቀረቡት አቤቱታ በሥር ፍሃቤቶች ተቀባይነት አለማግኘቱ በአግባቡ ነው ወይንስ አይደለም የሚለው ነው ከዚሁ ጭብጥ አኳያም ጉዳዩን መርምረናል እንደመረመርነውም ኛ ተጠሪ ለክርክሩ ምክንያት በሆነው ቤት በስማቸው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ከሚመለከተው መንግስታዊ ተቋም ካገኙ በኋላ ሐምሌ ቀን ዓም በተፃፈ ውል ለአመልካች በሽያጭ ያስተላለፉ ስለመሆኑ የሽያጭ ውሉ ከተደረገ በኋላም አመልካች እንደውሉ ይፈፀምልን በማለት በኛ ተጠሪ ላይ ክስ መስርተው ፍቤቱ ግራ ቀኙን አከራክሮ በመቁ በ ዓም ኛ ተጠሪ በሽያጭ ውሉ መሠረት ቤቱን ለአመልካች እንዲያስረክቡ በማለት ውሣኔ መስጠቱንና በዚሁ ውሣኔ መሠረትም አፈፃፀሙ ቀጥሎ እንዳለ ኛ ተጠሪ አፈፃፀሙን በመቃወም በፍብሕሥሥቁ መሠረት አቤቱታ አቅርበው ፍቤቱም አከራክሮ ኛ ተጠሪ አቤቱታቸው በማስረጃ ያልተደገፈ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም ብሎ አፈፃፀሙ እንዲቀጥል በማለት ትዕዛዝ መስጠቱን ከመዝገቡ ተረድተናል አመልካች በኛ ተጠሪ ላይ ክስ መስርተው ከፍ ብሎ እንደተጠቀሰው ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት ኛ ተጠሪ ለአመልካች ሊያስረክቡ ይገባል ተብሎ ውሣኔ ከተሰጠ ይፄው ቤት በፍርድ አፈፃፀም በኩል በሐራጅ ተሸጦ ተጠሪዎች ገንዘቡን ሊከፋፈሉ ይገባል ተብሎ የተሰጠውን ውሣኔ ተከትሎ አፈፃፀም ሲቀጥል አመልካች በዚሁ ቤት ላይ በፍቤት ውሣኔ የፍርድ ባለመብት የሆኑ በመሆኑ አፈፃፀሙ በዚህ ቤት ላይ ሊቀጥል አይገባም በማለት ያቀረቡት አቤቱታ ግራ ቀኙ በቤቱ ላይ ካቋቋሙት መብት አኳያ ታይቶ የአፈፃፀም ትፅዛዝ መስጠት ሲገባው አመልካች በዚህ ቤት ላይ መብት የላቸውም በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ አፈፃፀሙ ይቀጥል ተብሎ በአዋሳ ከተማ የመደፍቤት የተሰጠው የአፈፃፀም ትዕዛዝና እስከ ክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስም ይህንኑ ትፅዛዝ በማጽናት የተሰጠው ትዕዛዝ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የአዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ብይን እንደዚሁም የአዋሳ ከተማ ከፍቤት በመቁ በ ዓም የሰጠው ትዕዛዝ የክልሉ ጠፍቤት ሰበር ችሎት በመቁ ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ፍርድ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽራል ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነው የፍርድ አፈፃፀም አመልካችና ተጠሪዎች በየበኩላቸው ያቀረቡትን ክርክር መርምሮ እንዲወስን ለአዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ተመልሶለታል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአራት ዳኞች ፊርማ አለበት የልዩነት ሐሳብ የአዋሳ ወረዳ ፍቤት የፍርዱ አፈፃፀሙ እንዲቀጥል በማለት በሰጠው ትዕዛዝ የይግባኝ ቅሬታ ለሲዳማ ዞን ከፍቤት ቀርቦ በይግባኝ ክርክሩ የአሁኑ አመልካች ተካፋይ ሳይሆኑ ተጠሪዎችን ብቻ በይግባኝ አከራክሮ ኛ ተጠሪ በሽያጭ ለአመልካች ያስተላለፉት ቤት ሙሉ በሙሉ የግላቸው ሳይሆን የኛ እና የኛ ተጠሪዎችም ድርሻ ያለበት ስለሆነ በሽያጭ ውሉ መሠረት በገዢው ስም ሊዛወር የሚችለው በድርሻቸው ልክ እንጂ የኛ አና ኛ ተጠሪዎችን ድርሻ ጨምሮ ስለማይሆን የወረዳው ፍቤት የቤቱ ባለክፃብትነት ሙሉ በሙሉ ወደ ገዢው ይዛወር በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ አይደለም በማለት አሻሽሎ በኛ ተጠሪ ድርሻ ብቻ ስም ይዛወር ሲል ውሣኔ የሰጠ በመሆኑ ይህ የከፍተኛው ፍቤት ውሣኔ ጉድለት አንዳለበት መገንዘብ ቢቻልም በይግባኝ እስካልተለወጠ ተፈፃሚነት ያለው ስለሚሆን አመልካች በአዋሳ ወረዳ ፍቤት በመቁ አፈፃፀሙ በዚህ ቤት ላይ ሊቀጥል አይገባም በማለት ያቀረቡት መቃወሚያ ከከፍተኛው ፍቤት ውሣኔ አኳያ ታይቶ አፈፃፀሙ ሊቀጥል ይገባል በማለት በተራ ቁ ላይ ስሜ የተጠቀሰው ዳኛ በዛፃሳብ ተለይቻለሁ የማይነበብ የአንድ ዳኛ ፊርማ አለበት ዙዘ የሰበር መቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞችፁ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ተገኔ ጌታነህ ሂሩት መለሠ መድህን ኪሮስ አመልካች ወሮ ዝማም ህሉፍ ወኪል ቀረበ ተጠሪ አቶ መረሣ ገዮሐንስ ጠበቃው ቀርቧል ፍርድ ለሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ የጀመረው በመቀሌ ዞን ማፍርድ ቤት ነው የአሁኗ አመልካች የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍሃቤት በመቁ በመስከረም ቀን ዓም በግራ ቀኙ መካከል የተደረገው የቦታ ሽያጭ ውል ፈርሶ ወደነበሩበት እንዲመለሱ በሰጠው ውሣኔ መሠረት እንዲፈፀምላቸው ጠይቀዋል ፍቤቱም ተጠሪ ቤት እና ቦታውን ለአመልካች እንዲያስረክቧቸው ትዕዛዝ ሰጥቷል ጉዳዩ በይግባኝ የተመለከቱት የመቀሌ ዞን ከፍተኛ ፍቤት እና የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤትም ይህንኑ ትዕዛዝ ስህተት የለውም በማለት የቀረበላቸውን የይግባኝ ቅሬታ ውድቅ አድርገውታል የአሁኑ ተጠሪ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት የሰበር አቤቱታ ለትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት ያቀረቡ ሲሆን ችሎቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ በግራ ቀኙ የተደረገው የቦታ ሽያጭ ውል ሻጭ ባለቤት ሳይሆኑ የተፈፀመ ስለሆነ ውሉ ፈራሽ ሆኖ ተዋዋዮቹ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ተወስኗል ይህም ማለት ገዢ ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው ቦታው ደግሞ ቦታውን ለማስተዳደር ስልጣን ላለው ማዘጋጃ ቤት እንጂ ለተጠሪ አይደለም በማለት ተጠሪ ለአመልካች ቦታውን እንዲያስረክቡ የተሰጠውን ትዕዛዝ ነው የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ነው ይህ ችሎትም የተሰጠው የአፈፃፀም ውሣኔ ዋናውን ውሣኔ የተከተለ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ቀርቦ እንዲታይ አድርጓል ከመዝገቡ እንደተረዳነው ከአመልካች ክርክር የሰበር ችሎቱ የሰጠው የአፈፃፀም ውሣኔ በዋናው ጉዳይ ላይ የተሰጠውን ፍርድ የሚለውጥ ነው ኛ ወገኖች ክርክር ባላቀረቡበት ጉዳይ መብት እንዲያገኙ የሚደረግበት ህጋዊ መሠረት የለም የሚሉ ይገኙበታል ይህ ችሎትም ጭብጥ የያዘው በአፈፃፀም የተሰጠው ውሣኔ ዋናውን ፍርድ መሠረት አድርጐ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ስለሆነ ዋናው ውሣኔ ምን ይላል የሚለውን ማየት ያስፈልጋል ምክንያቱም አንድ ውሣኔ የሚያስፈጽም ፍቤት በውሣኔው መሠረት ከማስፈፀም ውጪ በአፈፃፀም ጊዜ ዋናውን ፍርድ ሊለውጥ የሚችልበትን የህግ መሠረት የለውም ለአፈፃፀም ምክንያት ከሆነው ውሣኔ ላይ እንደተገነዘብነውም አመልካች ለከብት እርባታ ተብሉ በጊዜያዊነት የተሰጣቸው የመሬት ሽያጭ ውል እንዲፈርስላቸው ያቀረቡት ክስ እስከ ትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት ድረስ ከታየ በኋላ አመልካች በቦታው ላይ የባለቤትነት መብት ሳይኖራቸው ያደረጉት የሽያጭ ውል ህግን የሚፃረር በመሆኑ ውሉ እንዳልነበር ተቆጥሮ እንዲፈርስና ተዋዋይ ወገኖች የሽያጭ ውል ከማድረጋቸው በፊት ወደነበሩበት ሁፄሄታዎች እንዲመለሱ ተወስኗል ከዚህ ውሣኔ እንግዲህ መገንዘብ የሚቻለው የውሣኔው ውጤት ሻጭ የሸጠው መሬት እንዲመለስለት ገዢ ደግሞ ለሻጩ የከፈለው ገንዘብ እንዲመለስለት የሚያደርግ መሆኑን ነው የሰበር ችሎቱ በዋናው ጉዳይ ላይ ከፍ ሲል የተመለከተውን ውሣኔ ከሰጠ በኋላ ደግሞ በመቀጠል የመቀሌ ከተማ ቦታን የማስተዳደር ስልጣን የመቀሌ ማዘጋጃ ቤት አሲሆን እያከራከረ ያለው ቦታ ወደፊት እንዴት ይሁን የሚለውን ሊወስንና እርምጃ ሊወስድ የሚችለው አራሱ ስለሆነ ተከታትሎ አንድ ነገር የማድረግ መብቱ ተጠብቀለታል ብሏል በዚህም ጉዳይ አከራካሪ የሆነው ግራ ቀኙ ውሉ ከመደረጉ በፊት ወደነበሩበት ቦታ እንዲመለሱ ከተወሰነ በኋላ የመቀሌ ማዘጋጃ ቤትን በተመለከተ ፍቤቱ ያለው ነገር ነው ከፍ ሲል እንደተመለከተው የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት ዋናው ፍርድ ግራ ቀኙ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ሲወሠን ገዢ የከፈሉት ገንዘብ እንዲመለስላቸው እና ቦታው ግን ማዘጋጃ ቤቱ እንዲረከበው ከመወሰኑ በቀር አመልካችን የፍርድ ባለመብት የሚያደርግ ውሣኔ አልተሰጠም በማለት ለደረሰበት መደምደሚያ መሠረት ያደረገው ከውሣኔው በኋላ ማዘጋጃ ቤቱ ወደፊት ቦታውን በተመለከተ ተገቢ ነው ያለውን እርምጃ እንዲወስድ የተሰጠውን ማሳሰቢያ ነው እኛ እንደተረዳነው ግን ሰበር ችሎቱ ማዘጋጃ ቤቱ ቦታውን አስመልክቶ እርምጃ እንዲወስድ ማሳሰቢያ ከመስጠቱ በቀር ቦታው በክርክሩ ተካፋይ ላልነበረው አካል እንዲመለስ የተሰጠው ውሣኔ አለመኖሩን ነው ስለሆነም የትግራይ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት የሰጠው የአፈፃፀም ውሣኔ ከዋናው ውሣኔ ያፈነገጠ መሆኑን ተገንዝበናል በሌላ በኩል ግን ይህ ችሎት ግራ ቀኙን በቃል በአነጋገረበት ወቅት ቦታው ከ ዓም ጀምሮ በተጠሪዎች እጅ መሆኑንና ማዘጋጃ ቤቱም ቦታውን ለተጠሪዎች ሰጥቶ ቦታውን የሚመለከቱ ሰነዶች ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እንዳሉ በዚህ ችሎት የዕግድ ትዕዛዝ ምክንያት መቆሙን ተገንዝበናል ከዚህም የቦታው ባለቤት የሆነው ማዘጋጃ ቤት ቦታውን ለተጠሪዎች አሳልፎ መስጠቱን ተረድተናል የፍባለዕዳው በማናቸውም ምክንያት ቢሆን ፍርድን በከፊልም ሆነ በሙሉ ለመፈፀም የማይችል መሆኑን ፍቤቱ ከተረዳው ደግሞ ፍርድ እንዲፈፀም ትዕዛዝ እንደማይሰጥ በፍሥሥህቁ ሥር ተመልክቷል በመሆኑም ምንም እንኳን በዋናው ውሣኔ ውሉ ፈርሶ ቦታው ለአመልካች እንዲመለስ የተወሰነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ማዘጋጃ ቤቱ ቦታውን ለተጠሪዎች የሰጠ በመሆኑ ፍርዱ ሊፈፀም የሚችል አይደለም በዚህም ምክንያት የትግራይ ክልል ሰበር ችሎት የሰጠውን ምክንያት በመቀየር ውሣኔውን አጽንተናል ውሣኔ የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት በመቁ በታህሳስ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ ተጨማሪ ትዕዛዝ ይህ ችሎት ነሐሴ የሰጠው የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ለሚመለከተው ክፍል ይፃፍ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ዙዘ የሰመቁ ታህሣሥ ቀን ጋዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካቾች ሶፊያ መሐመድ ቀረበች ከድጃ መሐመድ ቀረበች ተጠሪዎች ኢብራሂም መሐመድ ፋጡማ መሐመድ ጠበቃ ዘላለም ባይህ ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ መሠረቱ የውርስ ንብረት ክፍፍልን የሚመለከት ሆኖ ክርክሩም በአፈፃፀም ደረጃ ላይ ያለ ነው ከመዝገቡ እንዳየነው ለአፈዓፃሙ መሠረት የሆነው ውሣኔፄ የተሰጠው ተጠሪዎች ወንድማቸው በሆነው አብዱልቃድር መሐመድ ላይ ባቀረቡት ክስ መነሻነት ነው ተጠሪዎች በአማራ ብክመየኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍተኛ ፍቤት ባቀረቡት ክስ ተከሣሽ ይዞት የሚገኘው ከአባታቸው የተገኘውን የውርስ ፃብት እንዲያካፍላቸው የጠየቁ ሲሆን ተከሣሹም ክሱን አምኖ በመቀበሉ ንብረቱ ተከራካሪዎቹን ጨምሮ ለሰባት የሟች ልጆች አኩል ይካፈል በማለት ፍቤቱ ወስኖአል።