Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የሚለውን ነጥብ ከስር ፍቤት የመዝገብ ግልባጭ ጋር አገናዝቦ በመመርመር የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁ መሠረት የሚታይን ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀመረበት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የአሁኖቹ ተጠሪዎች ከሣሾች ነበሩ በአመልካች ላይ ክስ የመሠረቱትም በአናጺነት ሥራ ተሰማርተን አንድንሠራ በውል ተቀጥረን ስንሠራ የቆየን ቢሆንም ሥራው ሳያልቅ ከሕግ ውጪ የሥራ ውላችን ተቋርጦብናል ስለዚህ ወደ ስራችን እንድንመለስ የማንመለስ ከሆነም ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ተገቢው ክፍያ ተከፍሎን እንሰናበት ዘንድ ይወሰንልን በማለት ነው።
የሚለው ሊመለስ ይገባል የፍሥሥሕቁ ሁለተኛ ጨረታ ወጥቶ ተጫራች ካልቀረበ ንብረቱን ባለገንዘቡ ተረክቦ እንዲይዝ ትእዛዝ ሊሰጥ የሚችል መሆኑን ከማመልከት በቀር ከፍ ሲል የተጠቀሰውን ጥያቄ የሚመልስ ግልጽ ነገር አላስቀመጠም በተመሣሣይ በባንክ በመያዣ የተያዙ ንብረቶችን ሃ በተመለከተ የወጣውን አዋጅ ቁ ዐን ለማሻሻል የወጣው አቁ አንቀጽ ባንክ ሁለት ጊዜ ጨረታ አውጥቶ ገዢ ካልተገኘ ንብረቱን ለመጀመሪያ ጨረታ መነሻ በተሰጠው የዋጋ ግምት መሠረት እንደሚረከበው ከመደንገግ አልፎ በዋጋ ግምቱና በእዳው መዛከል ልዩነት ቢኖር ሊፈፀም የሚገባውን ነገር አያመለክትም ከፍ ሲል እንደተመለከትነው አንድ ባለገንዘብ ሊያገኝ የሚገባው የእዳውን መጠን ብቻ ነው በመሆኑም በፍሥሥሕጉም ሆነ በተጠቀሰው አዋጅ በዋጋው ግምትና በአዳው መዛከል ልዩነት ባለ ጊዜ ስለሚፈፀመው ነገር አልተገለፀም በሚል ባለገንዘቡ ከሚፈለገው እዳ መጠን በላይ የሚገመት ዋጋ ያለው ንብረት ተረክቦ ልዩነቱን እንዳይከፍል ማድረግ ለባለገንዘቡ ያላበደረውን ገንዘብ በማስከፈል አላግባብ ማበልፀግና ባለእዳውም ከአዳው በላይ እንዲከፍልና ጉዳት እንዲደርስበት ማድረግ ይሆናል የሕጉ አላማም ይኹ አይደለም በመሆኑም ባለገንዘቡ የተረከበው ንብረት ዋጋ ግምት ከአዳው በላይ ከሆነ ልዩነቱን ሊከፍል ይገባል ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመለስ ተጠሪ ከአመልካች ላይ የሚፈልገው እዳ ባንኩ ከተረከበው ንብረት በታች መሆነ አላከራከረም በመሆኑም ባንኩ ልዩነቱን የመመለስ ኃላፊነት አለበት ይግባኝ ሰሚው ፍቤትም በፍሥሥሕቁ ላይ ይህንን አስመልክቶ በግልጽ የተመለከተ ነገር የለም በማለት ተጠሪ ልዩነቱን ሊከፍል አይገባም ብሎ የደረሰበት መደምደሚያ ስህተት ነው ከዚህ በመቀጠል ሊታይ የሚገባው አመልካች አለብኝ የሚሉት እዳና ተጠሪ አለባቸው የሚለው የእዳ መጠን ልዩነት ነው ከመዝገቡ እንደተረዳነው ተጠሪ አመልካች ላይ ያስወሰነው ብር ቀምሳ አራት ሺህ ሰባት መቶ አሥራ ስምንት ከሰላሳ ስምንት አና አዳው ተከፍሎ እስከ አለቀ ድረስ ባልተከፈለው የገንዘብ መጠን ላይ የሚታሰብ የባንክ ወለድ ነው ከዚህ ውጪ ለኢንሹራንስ የቅጣት ወለድ የሽያጭ ታክስ ሆነ ሌሎች ልዩ ልዩ ወጪዎች እንዲከፈለው የተሰጠ ውሣኔ የለም በመሆኑም ከፍተኛ ፍቤቱ አፈፃፀም ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ተጠሪ ቤቱን እስከተረከበበት ጊዜ ያለው ወለድ እና በቤቱ ላይ የወጣውን ጨረታ ለማስፈፀም የወጣው ወጪ አመልካች እንዲከፍሉና ተጠሪ ለኢንሹራንስና ሌሎች ወጪዎች ለሸያጭ ታክስ የወለድ ቅጣት ላለባቸው እዳ ቀንሻለሁ ያለው አግባብ ባለመሆኑ የአመልካች ድርሻ እንዲመለስላቸው መወሰኑ በአግባቡ ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የደወሎ መስዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል የአማራ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽራል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር ፋይል ቁ ጥቅምት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ መስፍን ዕቁበዮናስ ሒሩት መለሠ አብዱራሂም አህመድ አመልካች አቶ ድንቁ ገላው ተጠሪ ወሮ ዋለ አሸቴ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለዚህ የሰበር አቤቱታ መቅረብ ምክንያት የሆነው አመልካች ጽፈው ያቀረቡት ማመልከቻ ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ አመልካች ከሳሽ በመሆን በጭልጋ ወረዳ ፍርድ ቤት በተጠሪ ላይ ያቀረቡት ክስ ተጠሪ ቤት ሠርቼ ባዶ ቦታ ስላለኝ ግዛኝ ብለው በሽማግሌዎች አስማሚነት ቦታውን በብር ዐዐ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ገዝቼ ቤት ሠርቼበታለሁ በቤቱም የልብስ ስፌት ድርጀት አቋቁሜ እየሠራሁበት ነው ሆኖም ተጠሪ ቤቱን በስሜ ስላላዛወሩልኝ በፍብሕቁ መሠረት ተገደው እንዲፈጽሙ ይደረግልኝ የሚል ነው ተጠሪም በበኩላቸው ውሉ በሚመለከተው አካል ቀርቦ ያልፀና ከመሆኑም በላይ በማታለልና በተንኮል የተፈፀመ በመሆኑ ሕጋዊነት የለውም በማለት ተከራክረዋል ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ መርምሮ የሽያጭ ውሉ ይፀድቃል ውሉ ለውልና ማስረጃ ቀርቦ እንዲፀድቅና ስመ ንብረቱ ለአመልካች እንዲዛወር የሚል ውሣኔ ሰጥቷል ያሁኗ ተጠሪ በውሣኔው ቅር ተሰኝተው ለሰሜን ጎንደር መስተዳደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ ያቀረቡ ሲሆን ፍቤቱም መሬት መሸጥ የተከለከለ በመሆኑ ውሉ ለሕግ ተቃራኒ ነው በማለት የወረዳውን ፍርድ ቤት ውሣኔ በመሻር እና አመልካች ለቤት ማሠሪያ ያወጡትን ወጭ በሕግ የመጠየቅ መብት በመጠበቅ ወስኗል የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሣኔ በአመልካች ይግባኝ ባይነት ቀርቦ ከተመረመረ በላ ክሱ ሙሉ የባለቤትነት መብትን ለመገልገል ለመሸጥ ለመለወጥ ወይም ለሶስተኛ ወገን ለማስተላለፍ እንዲቻል የቀረበ በሌላም በኩል ተጠሪ ንብረቱ ያላግባብ ከእጄ ወጥቷል በማለት ባልተከራከሩበት ከፍተኛው ፍርድ ቤት ባልተጠየቀው ጉዳይ ዳኝነት ሰጥቷል በሚል ውሣኔውን በመሻር የከፍተኛው ፍርድ ቤት ስመ ንብረቱ ሊዛወር ይገባዋል ወይስ አይገባውም በሚል ጭብጥ ላይ ብቻ ተመሥርቶ በማከራከር እንዲወስን ጉዳዩን መልሶታል የፍተኛው ፍርድ ቤትና በድጋሚ ጉዳዩን አይቶ መሬት መሸጥ ሕገወጥ መሆኑን ተችቶ ተጠሪ ተገደው ለአመልካች ሊያስተላልፉ አይገባም በማለት ወስኗል የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትም እንደገና ይግባኝ ቀርቦለት የከፍተኛውን ፍርድ ቤት ውሣኔ ካፀና በኋላ አመልካች ለቤቱ ማሠሪያ ያወጡትን ወጪ በተመለከተ መብታቸውን በመጠበቅ ቤቱን አፍርሰው ቁሣቁሱን ከወሰዱ በኋላ ቦታውን ለተጠሪ እንዲያስረክቡ በማለት በዚህ ነጥብ ላይ የከፍተኛው ፍርድ ቤት በዝምታ ያለፈውን በማሻሻል ወስኗል አመልካች የሰበር አቤቱታውን ያቀረቡት በዚህ መነሻ ሲሆን የአቤቱታው አንኳር ነጥብ የወረዳው ፍርድ ቤት ውሣኔ ሊፀና ይገባዋል የሚል ነው ይህ ሰበር ፍርድ ቤት በአመልካች የቀረበለትን አቤቱታ ከመረመረ በኋላ ተጠሪን አስቀርቦ ግራ ቀኙን አከራክሯል ክርክራቸውንም ከሕግ ጋር በማገናዘብ መርምሯል ፍርድ ቤቱ መዝገቡን አንደመረመረው ገና ከጅምሩም ክሱን ለማስተናገድ የሚያስችል የክስ መሠረት እንደነበርና እንዳልነበር ተመልክቷል በዚህም መሠረት ለክርክሩ መነሻ የሆነው ጉዳይ ባዶ ቦታን የሚመለከት እንደመሆኑ የመሬት ባለቤት መንግሥት መሆኑ ግልጽ ሆኖ እያለና በአመልካችና በተጠሪ መካከል የተደረገው ውል ከመነሻውም ፈራሽ መሆኑ እየታወቀ ወይም መታወቅ ሲኖርበት ጉዳዩ የክስ መሠረት እንዳለው ተቆጥሮ መስተናገዱ ተገቢ ሆኖ አልተገኘም ምንም እንኳ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትም የከፍተኛው ፍርድ ቤት በሕገ ወጥ ውል ሣቢያ የአመልካችን ክርክር ውድቅ ማድረጋቸው አግባብ ቢሆንም የአመልካችን ጥያቄ ውድቅ ማድረግ የነበረባቸው ጉዳዩን ከክስ መሠረት መኖርና አለመኖር አኳያ በማጤን ነበር ምክንያቱም የክስ መሠረት ሣይኖር ጉዳዩ እንዲስተናገድ በመደረጉ አመልካችና ተጠሪ በየደረጃው በተሰጡ ውሣኔዎች አንዴ የፍርድ ባለመብት በሌላ ጊዜ ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ለመሆን ተዳርገዋል ለዚህም አመልካች በወረዳው ፍርድ በተደረገው ክርክር የፍርድ ባለመብት ሲሆኑ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተሰጠው ውሣኔ የፍርድ ባለእዳ መሆናቸውን መጥቀሱ ይበቃል ሆኖም የክስ ማመልከቻው የቀረበለት የወረዳው ፍርድ ቤት በፍብሕሥሥቁ መሠረት ማመልከቻው የክስ መሠረት መኖሩን አላመለከተም በማለት ተጠሪን ሣያስቀርብ ክሱን መዝጋት ሲኖርበት ግራ ቀኙን አከራክሮ መወሰኑ ተገቢነት እንደሌለው እየታወቀ የመጨረሻ ውሣኔ የሰጠው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህን ነጥብ ትቶ ጉዳዩ የክስ መሠረት እንዳለው አድርጎ መወሰኑ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ውሣኔው መሻሻል ያለበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ ዐ ኅዳር ቀን ዓም እንዲሁም የሰሜን ጎንደር መስተዳደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ዐዐ ታህሣሥ ቀን ዓም በዋሉት ችሎቶት የሰጡት ውሣኔ ተሻሽሎ ክሱ ከመነሻውም የክስ መሠረት የሌለው ነው ብለናል ይፃፍ በዚህ ጉዳይ ለአፈፃፀም የሚቀርብ ነገር ባለመኖሩ የጭልጋ ወረዳ ፍርድ ቤት የአፈፃፀም መዝገቡን እንዲዘጋ የዚህ ውሣኔ ግልባጭ ይድረሰው መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰመቁ የካቲት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ ተገኔ ጌታነህ መስፍን ዕቁበዮናስ ሒሩት መለሠ አብዱራሂም አህመድ አመልካች የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ተጠሪ ማይገነት ብርፃኑ ፍሬ ሰላም በቀለች መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ አቤቱታ የቀረበው አመልካች ታህሣሥ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው የሰበር ማመልከቻ መነሻነት ነው የጉዳዩ የሥር አመጣጥ የአሁን ተጠሪዎች በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እነ መኮንን አስፋው ከተባሉት ጋር በነበራቸው ክርክር ምክንያት በምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጀሬ ወረዳ አዲስ ዓለም ከተማ ቀበሌ ዐ ውስጥ የሚገኘውን ቁጥሩ የሆነውን ቤትና አንዲሁም በ ሜትር ካሬ ላይ የሰፈረው የሆቴል ድርጅት እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ የእግድ ትዕዛዝ መሰጠቱን አመልካች ገልፆ እነዚህን ንብረቶች አመልካች በታህሣሥ ዐ ቀን ዓም በተፈረመ የብድር ውል ብር ዐዐዐ አንድ መቶ ፃምሣ ሺህ ለመኮንንና ሊሻን የእህል ንግድ ሽርክና ማኀበር ሲያበድር በመጀመሪያ ደረጃ ዋስትና መያዙን ተበዳሪዎች በውሉ መሠረት ባለመክፈላቸው ባንኩ በሕግ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመያዣ የተሰጡትን ንብረቶች በጨረታ አወዳድሮ አሸናፊ ለሆኑት ለወሮ ጥሩነሽ ቴሶ ስመንብረቱ እንዲዛወር ለአዲስ ዓለም ከተማ አስተዳደር የዛፈው ደብዳቤ ከላይ ፍርድ ቤቱ ንብረቶቹ እንዳይሸጡ ባስተላለፈው እግድ ምክንያት ተቀባይነት አለማግኘቱን በመግለጽ አግዱ እንዲነሣለት በፍብሥሥሕቁ መሠረት እግዱን ለሰጠው ፍርድ ቤቱ አቅርቦ የአሁኑ ተጠሪዎችም አግዱ ሊሠማ አይገባውም በማለት ያቀረቡትን ተቃውሞ ከመረመረ በላ ፍርድ ቤቱ አመልካች በክርክሩ ወቅት ጣልቃ አለመግባቱን ተጠሪዎቹ በንብረቱ ላይ ባለመብት መሆናቸው ከተወሰነ በኋላም አመልካች ተቃውሞ አለማንሣቱን ምክንያት በማድረግ እግዱ አይነሣም በማለት ወስኗል የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ውሣኔውን አጽንቷል አመልካች የሰበር አቤቱታውን ያቀረበው በዚህ መነሻነት ሲሆን ይህ ፍርድ ቤት ተጠሪዎችን በማስቀረብ ግራ ቀኙን አከራክሯል ክርክራቸውን ከሕግ ጋር በማገናዘብም መርምሯል በዚህም መሠረት እግዱ አይነሣም ተብሎ በሥር ፍርድ ቤቶች የተወሰነው ባግባቡ መሆን አለመሆኑን እንደሚከተለው ተመልክቷል በዚህ ጉዳይ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን አግድ የሰጠው የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አግዱንም የሰጠው ያሁን ተጠሪዎች እነ መኮንን አስፋው ከተባሉት ጋር በነበራቸው የውርስ ንብረት ክርክር ምክንያት ሆኖ እግዱም የሚቆየው ፍርድ ቤቱ ለክርክሩ አልባት እስኪሰጥ ድረስ ነው በዚህ ክርክር አመልካች ተካፋይ አልነበረም የፍብሥሥሕቁ ላይ እንደተመለከተው ከፍርድ በፊት የሚሰጥ የማገጃ ትዕዛዝ በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን የእግድ ትዕዛዙ ከመስጠቱ በፊት ያገኘውን መብት እንደማይነካበት ግልጽ በሆነ መልኩ ደንግጎት ይገኛል በተያዘው ጉዳይ አመልካች ቀደም ሲል ከነ አቶ መኮንን አስፋው ጋር የመያዣ ውል አድርጓል ይህንን ውል መሠረት አድርጎም በአዋጅ ቁጥር ዐ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የመያዣ ንብረቶቹን ፍርድ ቤት መሄድ ሣያስፈልገው በቀጥታ በራሱ መሸጥ የሚችል ቢሆንም በዚህ ጉዳይ ንብረቶቹ በሌሎች ወካዮች መካከል ባለው ክርክር ምክንያት በመታገዱ እግዱ እንዲነሣለት ሲጠይቅ የሥር ፍርድ ቤቶች ተጠሪዎች ከሌሎቹ ወራሾች ጋር በነበረው ክርክር ጣልቃ አልገባም በማለት እግዱን አለማንሣታቸውና ይልቁንም በክርክሩ ተካፋይ ያልነበረ መሆኑ ከላይ በተጠቀሰው የፍብሥሥሕቁ መሠረት ተጠቃሚ መሆን ሲገባቸው ተጎጂ እንዲሆን ማድረጋቸውን ፍርድ ቤቱ ተረድቷል በመሆኑም የሥር ፍርድ ቤቶች ለጉዳዩ እልባት ለመስጠት የሚያስችላቸው ግልጽ ድንጋጌ እያለ እግዱን ያለ ሕጋዊ መሠረት ላለማንሣት የሰጡት ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐዐዐ ሐምሌ ዐ ቀን ዓም እና የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጡት ትዕዛዝ ተሽራል ይፃፍ የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዚህ ጉዳይ የሰጠው እግድ ተነስቷል ይፃፍ ግራ ቀኙ ወጪያቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች የኢት ንግድ ባንክ አልቀረበም ተጠሪ ሞያሌ ከተማ አስተዳደር ቤት ዓሊ ሺዶ ቀረበ ወሮ ብርቄ ያደቹ ዓሊ አብዱልአዚዝ ቀረበ የሐጂ አብዱላዚዝ ካሕሣይ ወራሾች አቶ አሊ አብዱላዚዝ ቀረበ ወት ፋሪያ አብዱላዚዝ ቀረበች ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በቦረና ዞን ከፍተኛ ፍቤት ነው የአሁኑ አመልካች ባቀረበው ክስ ለሐጂ አብዱላዚዝ ካሕሣይ ብድር ሲሠጥ በሞያሌ ከተማ የሚገኘውን መኖሪያና ንግድ ቤት በመያዣ የያዘ ሲሆን ይህን የመያዝ መብቱን ኛ ተጠሪ እንዲመዘግብ ጠይቆ ተጠሪው መያዣውን መመዝገቡን ያረጋገጠለት ቢሆንም ይህንኑ ንብረት የቦረና ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለሚፈልገው የግብር ዕዳ በሐራጅ ለመሸጥ በሂደት ላይ አንዳለ ጣልቃ ገብቶ ቢከራከርም ባንክ ብድሩን ከመስጠቱ በፊት ይህ ንብረት በፍቤት ትዕዛዝ ተከብሮ የቆየ ነው በሚል ጥያቄውን አልተቀበለም በመሆኑም አስተዳደሩ የሙያ ግዴታውን ሣይወጣ በመቅረቱ የተነሣ ገንዘባችንን ስላሣጣን ተበዳሪው ያልመለሠውን ገንዘብ ይመልስ የተበዳሪው ሚስት እና ወራሾቹ ያልተከፈለውን እዳ ይክፈሉ በማለት ጠይቋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር እና ማስረጃ መርምሮ ባንኩ መያዣውን ከማስመዝገቡ በፊት በሌላ እዳ የተያዘ መሆኑን ሣያጣራ እንዲመዘገብለት ብቻ ጠይቆ አስተዳደሩም መያዣውን ባለበት ሕጋዊ ግዴታ መሠረት በቅደም ተከተል በመመዝገቡ ኃላፊነት የለበትም የተበዳሪው ሚስትና ወራሾችን በተመለከተ ሟች ከቦረና ዞን ፋይናንስ መምሪያ ጋር ሲፋለሙ ባንኩ ተከራክሮ ስለተወሰነበት ድጋሚ አዲስ ክስ ሊያቀርብ አይገባም በማለት ወስኗል የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት የቀረበለትን የይግባኝ ቅሬታ መሰጪዎችን ሣይጠራ ዘግቶታል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ ውሣኔ ላይ ነው ይህ ችሎትም ኛ እና ኛ ተጠሪዎች ላይ የቀረበው ክስ ቀደም ሲል ውሣኔ ያገኘ ጉዳይ ላይ ነው በሚል ክሱ ውድቅ መደረጉንና ኛ ተጠሪ ከኃላፊነት ነዛ የተደረገው በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ አድርጓል ግራ ቀኙም ክርክራቸውን በጽሁፍ አቅርበው ፍቤቱ መዝገቡን እንደሚከተለው መርምሯል የመጀመሪያውን ነጥብ በተመለተ በፍሥሥሕቁጥር መሠረት ማንኛውም ፍቤት ክርክሩን ተቀብሎ የመጨረሻ የፍርድ ውሣኔ ከሰጠ በላ ቀድሞ በፍርድ የተወሰነው ክርክር ሥረ ነገርና የተያዘው ጭብጥ አንድ ዓይነት ከሆነ በክርክሩ ላይ የነበሩት ወይም ከተከራካሪዎቹ መብት ያገኙ ኛ ወገኖች በዚያው ነገር ሁለተኛ ክስ ወይም ማናቸውም ዓይነት ሌላ ክርክር ሊቀርብባቸው አይችልም እንግዲህ ይህ የሰነ ሥርዓት ሕጉ ተፈፃሚ አንዲሆን መሟላት ካለባቸው ሁኔታዎች አንደኛው ውሣኔ የተሠጠበትና አዲስ ክስ የቀረበበት ክርክር ሥረ ነገር እና የተያዘው ጭብጥ አንድ ዓይነት መሆኑ ነው በተያዘው ጉዳይ ባንክ ቀድም ሲል ክርክር አቅርቦ የነበረው ለፋይናንስ መምሪያው ዕዳ በሃራጅ እንዲሸጥ የተባለውን ንብረት በመያዣ የያዘው በመሆኑ በንብረቱ ላይ የቀዳሚነት መብቱን ለማረጋገጥ ነው። የሚለው ሆኖ ተገኝቷል የአሁኑ የሰበር አመልካች የክርክሩ መንስኤ የሆነው ቤት በአቁ ተወርሶ ሲያስተዳድረው መቆየቱን በመግለጽ የተከራከረ ቢሆንም የስር ፍቤቱ ስለመወረሱ ተገቢው ማስረጃ አልቀረበም በሚል ቤቱ ለአሁን ተጠሪዎች እንዲመለስ ወስኗል በመሠረቱ አዋጅ ቁጥር ን መነሻ አድርጎ አላግባብ የምርጫ ቤቴ ተወስዷል በሚል የሚቀርቡ አቤቱታዎች አዋጁን ለማስፈፀም በተቋቋመው የሚኒስቴር መቤት በኩል እየተመረመሩ ተገቢውን ውሣኔ ማግኘት ያለባቸው ስለመሆኑ በአዋጁ ተመልክቷል በተመሣሣይ ሁኔታ ምርጫ ቤቴን በቀላጤ በቃል ትዕዛዝ ወይም በመመሪያ ከሕግ ውጭ ተወሰደብኝ በሚል የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በአቁ ዐ መሠረት ለኢትዮጵያ ፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ቀርበው መወሰን እንደሚገባቸው በሕጉ ተመልክቷል ከእነዚህ ክፍሎች የሚሰጡ የባለቤትነት ማስረጃዎችን መሠረት አድርገው በሚቀርቡ የባለቤትነት ጥያቄዎች ላይ ፍሃቤቶች እንደነገሩ ሁኔታ ስልጣን ከሚኖራቸው በቀር ተወርሠዋል ተብለው በመንግሥታዊና ሕዝባዊ ተቋማት ቁጥጥር ስር ያሉ ቤቶች ይመለሱልኝ እንዲሁም ውዝፍ ኪራይ ይከፈለኝ በሚል የሚቀረቡ አቤቱታዎችን መሠረት አድርገው ፍቤቶች የቤቱን መወረስና አለመወረስ ለማረጋገጥ ማስረጃዎችን መርምረው የሚደርሱባቸው መደምደሚያዎች የአስፈፃሚ አካላቱን ስልጣን እና ተግባር በግልጽ የሚቃረን ከመሆኑም በተጨማሪ ለፍቤቶች በሕግ ያልተሰጠ ስልጣን ነው በተያዘው ጉዳይ የአሁን ተጠሪዎች ክርክር በተነሣበት ቤት ላይ ከአስፈፃሚ አካላቱ የባለቤትነት ማረጋገጫ ባላቀረቡበት ሁኔታ የአሁን ተጠሪዎችን ባለቤት ሊያደርጓቸው የሚችሉ ጠቋሚ ማስረጃዎች አቅርበዋል በሚሜል ለፍቤቶች ባልተሠጠ የስልጣን ክልል በመግባት አመልካች በአዋጅ ቁጥር ተወርሰዋል ሲል ያቀረበውን መከራከሪያ ውድቅ በማድረግ ቤቱ ለተጠሪዎች ይመለስ ሲሉ መወሠናቸው መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ብለናል ነዓ ውሣኔ አመልካች ክርክር የተነሣበትን ቤት ለመመለስም ሆነ ውዝፍ ኪራይ ለመክፈል አይገደድም ብለናል የፌመደፍቤት ክርክር ያስነሣው በቀድሞው ወረዳ ዐ ቀበሌ የቤት ቁጥር የሆነው ቤት በአቁ ተወርሷል አልተወረሰም የሚለውን ጭብጥ የመመርመር ስልጣን የለኝም ብሎ ክሱን በፍብሕሥሥቁ ለ መሠረት ወድቅ ሊያደርገው ሲገባ አከራክሮ መወሰነ መሠረታዊ የሕግ ስህተት በመሆነ በመቁ ዐ የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል የፌከፍቤት በመቁ በሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ ተሽራል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም ዳኞችፁ ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሂሩት መለሰ መድህን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ አመልካች የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነፈጅ ቀርቧል ተጠሪ ሴርኮ እስራኤላውያን ጠበቃ ቀርበዋል መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ የተያዘው ክርክር የጀመረው በፌመደፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪ ከሣሽ በመሆን በአመልካቹ ላይ ሚያዝያ ቀን ዓም ያቀረበው ክስ የአሁን አመልካች ቤቴን ያለሕግ አግባብ ይዞ በመቆየቱ ከመጋቢት ቀን ዓም ጀምሮ እስከ የካቲት ቀን ዓም ላለው ጊዜ ያጣሁትን ጥቅም እና የደረሰብኝን ጉዳት ብር ሦስት መቶ ስልሳ ሦስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠላሳ አንድ ከወጪና ኪሣራ ጋር ይክፈለኝ የሚል ነው የአሁን አመልካች ቀርቦ በሰጠው መልስ የተለያዩ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን ያቀረበ ሲሆን ከመቃወሚያዎቹም አንዱ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት ከአዋጅ ውጭ የተወረሱ ቤቶች በመንግስት እጅ ለቆየበት ጊዜ ለታጣ ገቢ ክፍያ መጠየቅ ስለማይቻል ክሱ ተቀባይነት የለውም የሚል ነው የፌመደፍቤትም የቀረበውን መቃወሚያ ከግንዛቤ በማስገባት በሰጠው ውሣኔ ቤቱ በመንግስት እጅ የቆየው ከአዋጅ ውጭ ተወስዶ በመሆኑ አዋጅ ቁ በዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት ይኖረዋል ስለዚህ ወደ ፍሬ ጉዳይ ክርክሩ መግባት ሣያስፈልግ የተጠሪውን ክስ ውድቅ አድርጌዋለሁ በማለት መዝገቡን ዘግቶታል ተጠሪው በፌመደፍቤት ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለፌከፍቤት አሰምተዋል የፌከፍቤትም አመልካችን አስቀርቦ ግራ ቀኙን በማከራከር መዝገቡን መርምሮ በሰጠው ውሣኔ የክፍያው ጥያቄ ከዋጅ ቁ አኳያ ተቀባይነት የለውም ተብሎ በስር ፍቤት በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ቢቀርብም የዚህ አይነቱ መቃወሚያ በፍስስህቁ ስር ያልተሸፈነና የፍሬ ጉዳይ ክርክር ስለሆነ ፍቤቱ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ እስከሰጠበት ድረስ በቁጥር መሰረት ፍቤቱ ጉዳዩን ወደ ስር ፍቤት የሚመልሰው ሆኖ አልተገኘም በሌላ በኩል አመልካቹ በስር ፍቤት ያቀረባቸው ሌሎች የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ላይ ፍቤቱ ብይን ሣይሰጥ በዚሁ ነጥብ ላይ ተመስርቶ የሰጠው ፍርድ አመልካቹን ረቺ ቢያደረግም በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ላይ ብይን ባለመስጠቱ አመልካች መስቀለኛ ይግባኝ ያላቀረበ በመሆኑ ፍቤቱ በራሱ አስተያየት ሊመለከተው የሚችል ሆኖ አልተገኘም በሚል አመልካቹ አላግባብ ለበለፀገበት ብር ስልሣ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ ከተለያዩ ወጪና ኪሣራ ጭምር ለተጠሪው እንዲከፍል ወስኗል የፌከፍቤት በሰጠው ውሳኔ ላይ አመልካቹ ይግባኛቸውን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ቢያቀርቡም የፌጠፍቤት ይግባኙን ሳይቀበለው ቀርቷል የፌከፍቤት እና የፌጠፍቤት በዚህ ጉዳይ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ፈጽመዋል በማለት አመልካቹ ለዚህ ችሎት ሰኔ ቀን ዓም አቤቱታ አቅርበዋል ይህም ችሎት የአመልካቹን አቤቱታ መሰረት በማድረግ በዚህ ጉዳይ አመልካች ለፌመደፍቤት ካቀረባቸው የመልስ መቃወሚያዎች ውስጥ አንዱ ተቀባይነት አግኝቶ ክሱ ውድቅ ቢደረግለትም መስቀለኛ ይግባኝ ካላቀረበ በስተቀር በቀሪዎቹ ነጥቦች ላይ የቀረበው ክርክር ሊታይለት አይገባም የመባሉን አግባብነት ለማጣራት ተጠሪን አስቀርቦ ግራ ቀኙን አከራክሯል መዝገቡንም አግባበነት ካላቸው ህጐች አንፃር መርምረናል ከመዝገቡ መረዳት እንደተቻለው አመልካች ለቀረበበት ክስ በስር ፍቤት ቀርቦ በሰጠው መልስ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ያላቸውን አምስት ነጥቦችን እና መቃወሚያዎቹ ቢታለፉ በሚል ደግሞ ለክሱ ዝርዝር መልሱን አቅርቧል የመደፍቤቱም በሰጠው ውሣኔ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ከተባሉት ነጥቦች አንዱን መርምሮ ወደ ፍሬ ጉዳይ ክርክር መግባት ሣያስፈልግ ክሱን ውድቅ አድርጌዋልሁ በማለት ወስኗል ይህ ከሆነ ደግሞ ፍቤቱ አመልካቹ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ሲል ያቀረበውን ነጥብ እንደመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነቱ ተቀብሎ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አግባብ ቀሪ መቃወሚያዎችንና የፍሬ ጉዳይ ክርክሮችን ሣይመረምር ክሱን ውድቅ ማድረጉን ለመገንዘብ ተችሏል በማንኛውም ቀመር የክሱ ውድቅ መደረግ አመልካችን ተጠቃሚ ወይም ረቺ የሚያደርግ አንደመሆኑ አመልካቹ ቀሪ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች እአና የፍሬ ጉዳይ ክርክሮች ሊመረመሩ ይገባ ነበር ሲል ይግባኝ እንዲል የሚጠበቅበት አይሆንም በሌላ በኩል ደግሞ የፌከፍቤት አመልካቹ ይግባኝ ሊጠይቅ ሲችል አልጠየቀም በሚል የአመልካች መቃወሚያ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አይደለም ለዚህ ጉዳይም አግባብነት የለውም በማለት አመልካቹ ሌሎቹን መከራከሪያዎች እንዳመነ ያህል ሌሎቹን መቃወሚያዎችና የፍሬ ነገር ክርክሮች ሣይመረመሩ ውሣኔ መስጠቱ የአመልካቹን ፍትህ የማግኘት መብት በአጅጉ የሚያጣብብ ሆኖ ተገኝቷል በአርግጥ የፌከፍቤት የቀረበው መቃወሚያ ከፍብስህቁ አንፃር አግባብነት የለውም ማለቱ የሚነቀፍ ባይሆንም የፌመደፍቤት ክሱን ውድቅ ለማድረግ የተከተለው አካፄድ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ተቀባይነት ሲያገኝ በሚፈፀመው አግባብ ከመሆኑ አንፃር ሌሎች በፍቤቱ ያልተመረመሩ መቃወሚያዎችና መከራከሪያዎች መኖራቸው ግልጽ ነው ይህ በሆነበት ሁኔታ ከፍተኛ ፍቤቱ መቃወሚያው በማንኛውም ምክንያት ውድቅ ሲደረግ እንደሚፈፀመው ሁሉ በፍስስህቁ መሰረት ቀሪ መቃወሚያዎችንና መከራከሪያዎችን መርምሮ የመሰለውን እንዲወስን ወደ ስር ፍቤት ሊመልሰው ሲገባ አመልካቹ ይግባኝ አልጠየቁምና ቀሪ መከራከራያዎቻቸው አይታዩም ሲል ውሣኔ መስጠቱ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ተገኝቷል የፌጠፍቤትም የፌከፍቤት ውሣኔ ጉድለት የለበትም ሲል ይግባኙን መሰረዙ በተመሣሣይ ሁኔታ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ነው ውሣኔ የፌመደፍቤት በመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ብይን ውድቅ መደረጉን ተገንዝቦ የቀሩትን መቃወሚያዎችና መከራከሪያዎች መርምሮ የመሰለውን እንዲወስን ጉዳዩ በፍስስህቁ መሰረት ይመለስለት ብለናል የፌከፍቤት በመቁ በግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል ይፃፍ የፌጠፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝ ተሽራል ይዛፍ ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ሂሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ ሠልጣን አባተማም አመልካች አቶ ኪዳኔ ገጊዮርጊስ ተጠሪ ወሮ አብርሃ ተስፋሁን መዝገቡን መርምረን ቀጥሎ የተመለከተውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በትግራይ ክልል ደቡብ ወረዳ ፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪ የአሁን አመልካችን ጨምሮ በ ተከሳሾች ላይ ባቀረቡት ክስ ንብረትነቱ የሟች አባታችንና የባለቤታቸው የዐወሮ ሮማን ቢሆን የሆነውን በመቀሌ ከተማ የሚገኘውን ቤት ከ የተጠቀሱት ተከሳሾች ያለእኔ ፈቃድ ለኛ ተከሳሽ አመልካች የሸጡ ስለሆነ ከሽያጩ ገንዘብ የእኔ ድርሻ ብር ስለሚሆን ይህንኑ ገንዘብ እንዲከፍሉኝ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል አሁን በዚህ የሰበር ክርክር የሌሉት የሥር ከ ተከሳሾች ቀርበው የይርጋ ክርክር ያነሱ ሲሆን የአሁን አመልካችም ቀርበው ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት በሕጋዊ መንገድ እንደገዙትና ውሉም በሚመለከተው መንግስታዊ አካል የተመዘገበ መሆኑን ገልፀው ክሱ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክረዋል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የወረዳው ፍቤት የሽያጩ ውል በሚመለከተው አካል መጽደቁን የቀረበው ማስረጃ የሚያረጋግጥ ከመሆኑን በላይ የተሸጠውም በብር ሺህ እንደሆነ መገንዘብ ስለተቻለ ከዚህ ላይ የሟች ድርሻ ብር ሺህ ስለሆነና ይህም ለ ተወላጆች ሲከፋፈል የከሳሽ ድርሻ ብር ስለሚሆን ይህንኑ ገንዘብ ከ የተጠቀሱት ተከሳሾች እንዲከፍሉ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል ከሳሽ በዚህ ውሣኔ ቅሬታ አድሮባቸው የይግባኝ ቅሬታቸውን ለመቀሌ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ከዚያም ለክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ያቀረቡ ቢሆንም በፍብሕሥሥቁ መሠረት በሁለቱም ፍቤቶች ይግባኙ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል ከዚህ በኋላም የሰበር አቤቱታ ለክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት አቅርበው ሰበር ችሎቱም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ የጋራ የሆነውን የውርስ ንብረት በሽያጭ ለማስተላለፍ የሁሉም የጋራ ወራሾች ፈቃድ ማግኘት አስፈላጊ ሆኖ ሳለ ነገር ግን ከ የተጠቀሱት ተጠሪዎች የአመልካችን ፈቃድ ሳያገኙ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት ለኛ ተጠሪ በሽያጭ ማስተላለፋቸው አግባብ እንዳልሆነ በውሣኔው ላይ አስፍሮ ከ ከተጠቀሱት ተጠሪዎች ጋር ውሉ እንደፀና እንዲቆይ ነገር ግን አመልካችን በተመለከተ ውሉ እንዲፈርስና የቤቱ ኛ በአመልካች ስም እንዲመዘገብ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል በክልሉ ሰበር ችሎት ኛ ተጠሪ የነበሩት የአሁን አመልካች በዚሁ ውሣኔ ቅሬታ አድሮባቸው የሰበር አቤቱታ ያቀረቡ ሲሆን ይህ ሰበር ችሎት የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ተጠሪ ከቤት ሽያጩ ውል ድርሻዋ እንዲከፈላት ባቀረበችው ክስ በእሷ ድርሻ ውሉ ሊፈርስ ይገባል ተብሎ በክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት መወሰኑ ተጠሪ ባሉበት ተጣርቶ ሊወሰን የሚገባው ሆኖ በማግኘቱ በዚሁ መሠረት ተጠሪን ጠርቶ ግራ ቀኙን አከራክሯል ምላሽ ማግኘት የሚገባውም የጉዳዩ ጭብጥ አቤቱታው ያስቀርባል የተባለበት ነጥብ ስለሆነ ከዚሁ አኳያ እንደሚከተለው ተመርምሯል ጉዳዩ በወረዳ ፍቤት ሲጀመር የአሁን ተጠሪ ዳኝነት የጠየቁት ከላይ እንደተመለከተው ለክርክሩ ምክንያት ከሆነው የቤት የሽያጭ ገንዘብ ላይ ድርሻዬ ይከፈለኝ በማለት ነው ተጠሪ ዳኝነት የጠየቁት በዚህ መልኩ ከሆነ በጭብጥነት የሚያዘውም ነጥብ በክሱ የጠየቁት ገንዘብ ሊከፈላቸው ይገባል ወይንስ አይገባም። በመሆኑም በቤቱ ላይ የተደረገው እድሳትና ለውጥ ምን ያሕል የመጠንና የአይነት ለውጥ እንዳመጣ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት ልዩ አዋቂ መድበው በማስጠናት መወሰን ሲገባቸው ስለ ቤትና የግንባታ ሥራ ዕውቀት የሌላቸው ምስክሮች የሰጡትን ቃል መነሻ በማድረግ የሰጡት ውሣኔ መሠረታዊ ስህተት ያለበት ውሣኔ ነው በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ ተሽራል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ታህሣሥ ቀን ዓም ቤቱን በተመለከተ ብቻ የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል ይፃፍ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም ቤቱን በተመለተ የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በቤቱ ላይ የተደረገውን አድሳት ምን ያሕል ገንዘብ እንዳስወጣና በመጀመሪያው ቤት ላይ ምን ያሕል የአይነትና የመጠን ለውጥ ያደረገ መሆኑን በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት በልዩ አዋቂ በማስገመት የመሰለውን ውሣኔ ይሰጥ ዘንድ ጉዳዩን በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት መልሰን ልከንለታል የውሣኔው ግልባጭ ይተላለፍ ግራ ቀኙ በዚህ ፍርድ ቤት ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ራሳቸው ይቻሉ ይህ ፍርድ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ግንቦት ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ መጋቢት ዐ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ አብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች አቶ መሐመድ አብዲ ቀረቡ ተጠሪ አቶ አብዱራሂም አብዲ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪ በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ በውርስ የተላለፈልኝን መሬት ተከሣሽ በጊዜያዊነት እንዲገለገልበት ሰጥቼው ለመልቀቅ ፈቃደኛ ያልሆነ ስለሆነ እንዲያስረክብ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ ለክሱ ምክንያት የሆነው ቦታ የተከሣሽ ስለመሆኑ በማስረጃ የተረጋገጠ ስለሆነ በከሳሽ በኩል የቀረበው ክስ የማስረጃ ድጋፍ የለውም በማለት ሳይቀበለው ቀርቷል ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተውም የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በበኩሉ ግራ ቀኙን አክራክሮ የሥር ፍቤትን ውሣኔ በመሻር ይግባኝ ባይ ክስ ባቀረበበት ቦታ ላይ መብት ያለው ስለመሆኑ ማስረጃው የሚያረጋግጥ ስለሆነ መሰጭ ለይግባኝ ባይ ሊመልስ ይገባል በማለት ውሣኔ ሰጥቷል የሰበር አቤቱታውም የቀረበው ይህንኑ ውሣኔ በመቃወም ሲሆን ይህ ችሎትም አቤቱታው ለሰበር ሊቀርብ ይገባል ብሎ ግራ ቀኙን አከራክሯል በቅድሚያም ችሎቱ የተመለከተው ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረቡት ክስ የክስ ምክንያት ያለው መሆኑን በተመለከተ ነው ከላይ እንደተመለከተው ተጠሪ በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረቡት አቤቱታ ዳኝነት የጠየቁት በውርስ የተላለፈላቸውን መሬት አመልካች በጊዜያዊነት እንዲገለገሉበት ሠጥተዋቸው ነገር ግን አመልካች መሬቱን ለመመለስ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ገልጸው እንዲመልሱ ይወሰንልኝ በማለት ነው የከተማ ቦታና ትርፍ ቤትን የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በከተማ ባለርስትና በከተማ ጭሰኛ መካከል ያለው ግንኙነት እንደፈረሰ ጭሰኛው ለከተማ ባለርስት ከሚከፍለው ኪራይና ሌላ ክፍያ አንደዚሁም ከማንኛውም አገልግሉትና ዕዳ ነፃ እንደሆነ ከመደንገጉም በላይ ማንኛውም ጭሰኛ በያዘው የከተማ ቦታ ላይ የይዞታ መብትም እንደማይኖረው ተመልክቷል ለክሱ ምክንያት የሆነው መሬት በአዋጅ የመንግሥት መሆኑ ከተረጋገጠ ደግሞ ተጠሪ አመልካችን ለመክሰስ የማያበቃ መነሻ ምክንያት ሀፀ ርቪቨበ የሌላቸው መሆኑን መገንዘብ ይቻላል በፍብሕሥሥቁ ላይ እንደተመለከተውም ማንኛውም ፍቤት የክስ አቤቱታ ሲቀርብለት ተከሣሽ የሆነው ወገን ክሱን እንዲከላከል ከመጥራቱ በፊት ከሳሹ ክሱን ለማቅረብ የሚያስችል መነሻ ምክንያት ያለው ስለመሆኑና ፍቤቱም አቤቱታውን ተቀብሎ ለማየት ሥልጣን ያለው ስለመሆኑ መመርመር ይኖርበታል በዚህም መሠረት ተጠሪ አመልካች ሊመልስልኝ ይገባል በማለት አቤቱታ ያቀረበበት መሬት በተጠቀሰው አዋጅ ቁጥር መሠረት የመንግሥት ሀብት ስለሆነ ከመነሻው አቤቱታቸው የክስ ምክንያት እንደሌለው መገንዘብ ሰለሚቻል የጀጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በፍብሕሥሥህቁ ሀ መሠረት አቤቱታው ተቀባይነት የለውም ማለት ሲገባው አከራክሮ ውሣኔ መስጠቱ የክልሉ ጠቅላይ ፍቤትም ይህንኑ ስህተት ሳያርም መቅረቱ የሕግ ስህተት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የጅጅጋ ዞን ከፍፍቤት በዚህ ጉዳይ በሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ እንደዚሁም የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በዚህ ጉዳይ በሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯራል ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው ክስ የክስ ምክንያት የለውም ተብሎ ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃደር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ሱልጣን አባተማም አመልካች አቃቂ ቃሊቲ ክከቀ አጽቤት አልቀረቡም ተጠራ እነ ወሮ ብዙወርቅ ሸዋንግዛው ቀረቡ መዝገቡን መርምረን ቀጥሎ የተመለከተውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ሲሆን ተጠሪዎች በአመልካችና በሥር ኛ እና ኛ ተከሳሾች ላይ ባቀረቡት ክስ ከወላጅ አባታችን በውርስ የተላለፈልንን በአቃቂ ቃሊቲ ክከተማ ቀበሌ ክልል የሚገኝ ቤታችንን ኛ ተከሳሽ ከአዋጅ ውጭ ያለአግባብ በመያዝ ለኛ እና ኛ ተከሳሾች በማከራየት ላይ ስለሚገኝ ይህንኑ ያለ አግባብ ይዘው የሚገኙትን ቤታችንን ለቀው እንዲያስረክቡ ይወሰንልን በማለት ጠይቀዋል ኛ ተከሳሽ የአሁን አመልካች ቀርቦ በሰጠው መልስ ክስ የቀረበባቸው ቤቶች በአዋጅ መሰረት የተወረሱ ወይንም ያልተወረሱ ለመሆናቸው የሚጠቁም ማስረጃ በ ዓም በመዘረፉ ምክንያት ማቅረብ አልቻልንም በአሁኑ ሰአት ይህ ክስ መመስረቱ አግባብነት የሌውና ተከራዮችን የሚጉዳ ነው ጉዳዩም መታየት ያለበት በፍቤት ሳይሆን በኛ ራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ በኩል ስለሆነ መዝገቡ ሊዘጋ ይገባል በማለት ተከራክሯል የሥር ኛ እና ኛ ተከሳሾችም በበኩላቸው ባቀረቡት መልስ ከሳሾች ቁጥራቸው እና የሆኑት ቤቶች ሊመለሱልን ይገባል በማለት ቀደም ሲል ለወረዳ ፍቤት ክስ አቅረበው ፍቤቱም ጉዳዩን አይቶ ለመወሰን በሕግ ሥልጣን የተሰጠው ለኢትዮጵያ ኘሃ ራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ስለሆነ ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም በማለት ውሳኔ የሰጠ በመሆኑ በድጋሚ ለፍቤቱ ክሱ መቅረቡ ከፍብሕሥሥቁ አኳያ ተቀባይነት ስለሌለው ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የአዲስ አበባ ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ጉዳዩ አስቀድሞ ውሳኔ ያገኘ ነው ተብሎ የቀረበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በተመለከተ የወረዳ ፍቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ያለው የኢትዮጵያ ሃኛ ራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ነው ከማለት በስተቀር የፍሬ ጉዳይ ክርክሩን ተመልክቶ ውሳኔ ያልሰጠ በመሆኑ ክርክሩ በፍብሕሥሥቁ ሥር ስለማይወድቅ በዚህ ረገድ የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አግባብነት የለውም በማለት ሳይቀበለው ቀርቷል ከዚህም ሌላ ኛ ተከሳሽ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ያለው ፍቤት ሳይሆን የኢትዮጵያ ኘ ራይቬታይዜሽን ነው በማለት ያቀረበውን መቃወሚያ አስመልክቶም በአዋጅ መሰረት ለኤጀንሲው ሥልጣን የተሰጠው በቃል ትእዛዝ በቀላጤ ወይንም በመመሪያ አንድ ንብረት ተወስዶ በሚገኝበት ጊዜ እንደሆነ ስለተመለከተና ከሳሾች በዚህ መንገድ ቤቱ ተወስዶብኛል ያላሉ ስለሆነ መቃወሚያው ተቀባይነት የለውም በማለት ውድቅ አድርጓል ከዚህ በኋላም በፍሬ ጉዳይ ረገድ የተደረገውን ክርክር ከማስረጃው ጋር አገናዝቦ መርምሮ ክስ የቀረበባቸው ቤቶች የተወረሱ ስለመሆናቸው በማስረጃ ያልተረጋገጠ ስለሆነ ኛ ተከሳሽ ከኛ እና ኛ ተከሳሾች ጋር ያደረገውን የኪራይ ውል በማቋረጥ ለከሳሾች ቤቱቹን እንዲያስረክቡ በማለት ውሳኔ ሰጥቷል ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተውም የከተማ ነክ ይግባኝ ሰሚ ፍቤት በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ የፍብሕሥሥቁ ሊጠቅስ የሚገባው አንድ የክስ ምክንያት በተከራካሪ ወገኖች ወይም ከእነዚህ ወገኖች ጥቅም የሚያገኙ ኛ ወገኖች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ከተሰጠ በተመሳሳይ የክስ ምክንያት ክስ በሚቀርብበት ጊዜ ሲሆን በተያዘው ጉዳይ የቀድሞ ወረዳ ፍቤት የቤት ይለቀቅልኝ ክርክሩን ለማየት ሥልጣን ያለው ሌላ አካል ስለሆነ ጉዳዩን አላስተናግድም በማለት በብይን መዝገቡን በመዝጋቱ በቀረበው የክስ ምክንያት ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ካለመስጠቱም በላይ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ረ መሰረት የከተማው የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የከተማው አስተዳደር ከያዛቸው ቤቶች ጋር የሚቀርቡ ክሶችን ለማከራከር የሥረ ነገር ስልጣን ያለው በመሆኑ የሥር ፍቤት በዚህ ረገድ የቀረበውን መቃወሚያ ባለመቀበል ጉዳዩን አይቶ መወሰኑ በአግባቡ ነው በማለት የሥር ፍቤትን ውሳኔ አጽንቷል የከተማው ይግባኝ ሰሚ ፍቤት ሰበር ችሎትም የሰበር አቤቱታ ቀርቦለት መሰረታዊ የሕግ ስህተት አልተፈጸመም በማለት አቤቱታውን ሳይቀበለው ቀርቷል ለዚህ ችሎትም የሰበር አቤቱታ የቀረበው ይህንነ ለማስለወጥ ሲሆን ይህ ችሎትም የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ በሥር ፍቤት ክርክር ሲደረግ አመልካች ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት የሥረነገር ሥልጣን የለውም በማለት ያቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ ተጠሪዎች ባሉበት ተጣርቶ ሊወሰን የሚገባው መሆኑን በማመኑ ተጠሪዎችን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል የሰበር አቤቱታውም ያስቀርባል ከተባለበት ነጥብ አኳያ እንደሚከተለው ተመርምሯል በአዲስ አበባ ከተማ ነክ መደፍቤት ክርክር ሲደረግ አመልካች ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት የሥረ ነገር ሥልጣን የለውም በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ያቀረበው ከአዋጅ ውጭ የተወሰደን ንብረት ባለቤትነት አጣርቶ ለመመለስ በአዋጅ ቁጥር መሰረት ሥልጣን የተሰጠው ለኢትዮጵያ ሃ ራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ነው በማለት ሲሆን ፍቤቱም መቃወሚያውን ሳይቀበለው የቀረው ለኤጀንሲው ሥልጣን የተሰጠው ንብረቱ በቃል ትአዛዝ በመመሪያ ወይንም በቀላጤ ተወስዶ በሚገኝበት ጊዜ እንደሆነ በአዋጁ ላይ ስለተመለከተና ከሳሾች በዚህ መንገድ ክስ የቀረበበት ቤት ተወሰደብን ያላሉ ስለሆነ ፍቤቱ ሥልጣን አለው በማለት ነው በሌላ በኩልም ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው ፍቤት የከተማ ነክ የመደፍቤት ጉዳዩን ለማየት ሥረ ነገር ሥልጣን አለው ያለው የመጀመሪያው ደረጃ ፍቤት እንዳለው ክስ የቀረበበት ቤት በቀላጤ በመመሪያ ወይንም በቃል ትአዛዝ ተወስጻል ስላልተባለ ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን አለው በማለት ሳይሆን የከተማው አስተዳደር ከያዛቸው ቤቶች ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ክሶችን ለማከራከር የሥረ ነገር ሥልጣን ያለው የአአበባ ከተማ ነክ ፍቤት እንደሆነ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ላይ የተመለከተ ስለሆነ ፍቤቱ ሥልጣን አለው በሚል ነው ይሁንና ተጠሪዎች ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት በቀላጤ በቃል ትእዛዝ ወይንም በመመሪያ ተወስዶብናል ያላሉ በመሆኑ በአቁ መሰረት ጉዳዩ በኢትዮጵያ ኛ ራይቬታይዜሽን በኩል የሚታይ አይደለም መባሉ ተገቢነት የነበረው ቢሆንም በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ረ ስር ለከተማ ነክ ፍቤት ሥልጣን የተሰጠው የአአበባ ከተማ አስተዳደር በባለቤትነት ከሚያስተዳድራቸው ቤቶች ጋር ተያይዘው የሚቀርቡ ጉዳዩችን በተመለከተ ስለሆነና ይህም ባለቤትነቱ የከተማው አስተዳዳር ስለመሆነ ክርክር ሳይኖርበት ከባለቤትነት በመለስ የሚነሱ ክርክሮችን በተመለከተ እንደሆነ መገንዘብ የሚቻል ሲሆን በተያዘው ጉዳይ ተጠሪዎች ለክሱ ምክንያት የሆነው ቤት በውርስ የተላለፈልን የግል ቤታችን ነው በማለት ባለቤትነትን የመፋለም ክስ ፀፀኪበዕዐበ ርበ ያቀረቡ በመሆኑና በቤቱ ባለቤትነት ላይም ክርክር እስከቀረበበት ድረስ ከተጠቀሰው የአዋጁ ድንጋጌ አኳያ የከተማ ነክ ፍቤት የሥረ ነገር ሥልጣን ሊኖረው የማይችል በመሆኑ የሥር ፍቤቶች የከተማ ነክ ፍቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን አለው በማለት ተመልክተው ውሳኔ መስጠታቸው ለአዋጁ የተሳሳተ ትርጉም በመስጠት እንደሆነ መረዳት የተቻለ ስለሆነ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሳኔ የአአበባ ከተማ ነክ ፍቤት በመቁ በታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው ውሰኔ የከተማው ይግባኝ ሰሚ ፍቤት በመቁ በጥር ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ አንደዚሁም ሰበር ችሉቱ በመቁ በግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሰረት ተሽራል የአአበባ ከተማ ነክ ፍቤት ይህንን ጉዳይ ለማየት የሥረ ነገር ሥልጣን የለውም ተብሎ ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሳራ ይቻቻሉ መዘገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሒሩት መለሠ መድህን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ አመልካች የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሠረተ ልማትና ቤቶች ጉዳይ ጽቤት አቶ ተስፋዬ ዘመድኩን ቀረቡ ተጠሪ ኛ አቶ ይርጋ ንጋኔ ቀረቡ ኛ ወሮ በላይነሽ ሙሽጋ ቀረቡ ኛ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ዐ አስተዳደር ጽቤት ኛ አቶ ሰንበት ታደሰ ቀረቡ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ መዝገቡ የተከፈተው አመልካቹ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ዐ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ በሰበር ታይቶ ሊታረም ይገባዋል በማለት ነሐሴ ቀን ዓም አቤቱታ ስላቀረበ ነው የክርክሩን መሠረታዊ ጉዳይ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሰጠው ትዕዛዝና በአመልካችና በተጠሪዎች በኩል ለዚህ ፍርድ ቤት በጽሑፍ ከቀረበው ክርክር እንደተረዳነው አቶ ይርጋ ንጋኔና ወሮ በላይነሽ መሸጋ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ዐ አስተዳደር ጽቤት እና አቶ ስንብት ታደሰ የግል ንብረታችን የሆነውን የቤት ቁጥር ያላግባብ በመያዝ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ዐ አስተዳደር ጽቤት አከራይ አቶ ስንብት ታደሰ ደግሞ ተከራይ በመሆን እየተጠቀሙበት ስለሚገኙ ንብረታችንን እንዲያስረክቡን በማለት ክስ አቅርበው ሶስተኛ እና አራተኛ ተጠሪ መልስና የመከላከያ ማስረጃ ካቀረቡ በኋላ በሥር ፍቤት ተከሣሾች የነበሩት ሶስተኛ እና አራተኛ ተጠሪዎች ለከሳሾች ማለትም ለአንደኛና ሁለተኛ ተጠሪዎች ክስ ያቀረበበትን ቤት እንዲያስረክቡ የፌዴራል የመጀመያ ፍርድ ቤት ውሣኔ ሰጥቷል አንደኛና ሁለተኛ ተጠሪዎች የፍርድ ባለፅዳዎች ማለትም ሁለተኛ እና ሶስተኛ ተጠሪዎች እንደ ፍርዱ እንዲፈጽሙ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው የአፈፃፀም ክስ አቅርበው የፍርድ አፈፃፀሙ በሒደት ላይ እያለ አመልካች የካቲት ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያሉ ቤቶችን አስመልክቶ የማስተዳደርና ተገቢውን ውሣኔ የመወሰን ስልጣን በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት የቤቶች መሠረተ ልማት ኤጀንሲ መሆኑ እየታወቀ ኤጀንሲው በክርክሩ ውስጥ ተሣታፊ ሣይሆን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው ቤት አንደኛና ሁለተኛ ተጠሪዎች የግል ንብረት ነው ተብሎ የተሰጠው ውሣኔ ተሰርዞ ወደ ክርክሩ ገብተን የመከላከያ ማስረጃችንንና መልሳችን እንድናቀርብ ይፈቀድልን በማለት በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት የፍርድ መቃወሚያቸውን አቅርበዋል የፍርድ መቃወሚያ ማመልከቻው የቀረበለት ፍርድ ቤትም አንድ ሰው የፍርድ መቃወሚያ ሊያቀርብ የሚችለው በክርክሩ ሣይካፈል ሲቀርና የተሰጠው ፍርድ መብቱን የሚነካበት ሆኖ ሲገኝ ነው በዚህ ጉዳይ ቤቱን በቀጥታ ሲያስተዳድር የነበረው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ዐ አስተዳደር ጽቤት በተከሣሽነት ቀርቦ የተከራከረ በመሆኑ አመልካች የተሰጠው ፍርድ እንዲነሣና ወደ ክርክሩ አንደገባ ያቀረበው ጥያቄ ተገቢ አይደለም በማለት ትዕዛዝ ሰጥቷል አመልካች የቀበሌ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ከተማ መሠረተ ልማትና የቤቶች ኤጀንሲ ሁለት የተለያዩ የሕግ ሰውነት ያላቸው የተለያየ ሥልጣንና ሀላፊነት በማቋቋሚያ አዋጃቸው የተሰጣቸው ሆኖ እያለ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ዐ አስተዳደር ጽቤት በተከሳሽነት ስለተከራከረ ፍርዱን ለመቃወም አትችሉም በማለት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የሰጠው ትፅዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ይህንን ሰህተት እንዲያርም ያቀረብነውን ይግባኝ የሰረዘው በአግባቡ ስላልሆነና የሥር ፍርድ ቤት የሥረ ነገር ሥልጣን ሣይኖረው የወሰነብን ስለሆነ በሰበር ሊታረም ይገባዋል በማለት የጽሑፍ ክርክር ያቀረበ ሲሆን አንደኛና ሁለተኛ ተጠሪዎች በበኩላቸው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዐ ቀበሌ አስተዳደር በተከሣሽነት ስለተሣተፈ አመልካቹ በክርክሩ አንደተሣተፈ ይቆጠራል የክፍለ ከተማው አስተዳደር ነገረ ፈጆች ቀበሌውን ወክለው የተከራከሩ ስለሆነ የፍርድ መቃሚያ ማመልከቻቸውን ውድቅ መደረጉ በአግባቡ ነው በማለት የተከራከሩ ሲሆን አራተኛው ተጠሪ እኔ ተከራይ በመሆኔ ከክርክሩ ውጭ እንዲሆን በማለት መልስ ሰጥቷል ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በዚህ ፍረድ ቤት ያቀረቡት የመከራከሪያ ፃሣቦች ከላይ የተገለፀው ሲሆን አኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው አመልካች መልስና የመከላከያ ማስረጃው እንዲሰማለትና በክርክሩ ተካፋይ ሣይሆን የተሰጠው ፍርድ እንዲሠረዝለት ያቀረበውን ጥያቄ ጉዳዩን ያየው የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ውድቅ ያደረገው በግባቡ ነው ወይስ አይደለም የሚለው ጭብጥ ማየት አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል የተሻሻለው የአዲስ አበባ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር ቀበሌ ማለት የከተማው ሦስተኛ ደረጃ የአስተዳደር እርከን የሆነ የክፍለ ከተማ አካል እንደሆነ በአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ላይ የተደነገገ ሲሆን የቀበሌ አስተዳደር ስልጣንና ተግባርን የሚደነግገው የአዋጁ አንቀጽ የቀበሌ አስተዳደር በከተማው አስተዳደር ሥር ያሉ ቤቶችን የመሸጥ የመለወጥ እና ከዚህ ጋር ተመሣሣይ ውጤት ሊያስከትሉ የሚችሉ ተግባራትን የማከናወን ስልጣንና ሀላፊነት ያለው ስለመሆኑ አይደነግግም ቻርተሩ በአዲስ አበባ ከተማ ሥር ያሉ ቤቶችን የማስተዳደር የመሸጥና ሌሎች ውሣኔዎችን የሚሰጠው ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ ይህንን ተግባር ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማከናወን የአዲስ አበባ የመሠረተ ልማትና የቤቶች ኤጀንሲን በዋጅ ቁጥር አቋቁሟል ከዚህም የምንረዳው የቀበሌ አስተዳደር ለሕብረተሰቡ በቅርበት አስተዳደራዊ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመ የከተማው አስተዳደር በሶስተኛ ደረጃ የሚገኝ ሲሆን በከተማዋ አስተዳደር ሥር ያሉ ቤቶችን አስመልክቶ በፃላፊነት የሚከታተለውና ተገቢውን ውሣኔ መስጠት የሚችለው የመሠረተ ልማትና የቤቶች ጉዳይ ኤጀንሲ ነው ሁለቱ የቀበሌ አስተዳደርና ኤጀንሲው የተለያየ ባህሪ ስልጣንና ሀላፊነት እንዲሁም ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው አካላት ናቸው አንድ ወደ ክርክር መግባት ያለበት አካል በክርክሩ ተሣታፊ ሣይሆን የተወሰነው ውሣኔ መብቱን የሚነካ ሆኖ ሲገኝ ውሣኔው ከመፈፀሙ በፊት ውሣኔው እንዲነሣና ክርክሩ እርሱ ባለበት እንዲቀጥል መጠየቅ እንደሚችል የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ይደነግጋል አመልካች የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለአንደኛና እና ሁለተኛ ተጠሪዎች እንዲመለስ ውሣኔ የሰጠበትን ቤት የማስተዳደርና በቤቱ ላይ የተሻለ መብት አለኝ የሚል ሰው ሲመጣ በሕግ አግባብ የመፋለም ስልጣንና ኃላፊነት ያለው ከቀበሌ አስተዳደር የተለየና ራሱን የቻለ የሕግ ሰውነት ያለው አካል ነው አመልካችና የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ዐ አስተዳደር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለማስተዳደር አስፈላጊ ናቸው ብሉ ያደራጃቸው የመንግሥት አካላት በመሆናቸው ብቻ ቀበሌው በክርክሩ በተከሳሽነት በመሣተፍ አመልካች በክርክሩ ተሣታፊ ሆኖ ማቅረብ የሚገባውን የመከላከያ መልስና ማስረጃ የማቅረብ እድል አግኝቷል ብሎ ለመደምደም አይቻልም በመሆኑም አመልካች በክርክሩ ውስጥ ተሣታፊ ሣይሆን አሉኝ የሚላቸውን ማስረጃዎችና ሌሉች የመከራከሪያ ፃሣቦች ሳያቀርብ የሚያስተዳድረውን ቤት ለአንደኛ አና ሁለተኛ ተጠሪ እንዲተላለፍ የተሰጠው ፍርድ እንዲነሣና ክርክሩ እሱ ባለበት እንደገና እንዲታይ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም በማለት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትና በፌዴራል የከፍተኛ ፍርድ ቤት የተሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ ክርክር የተነሣበትን ቤት አስመልክቶ ዐ መጋቢት ቀን ዓም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠው ትዕዛዝ ተሽሯል ፍርድ ቤቱ አመልካች የሚያቀርበውን ማናቸውንም የሕግና የፍሬ ጉዳይ ክርክርና ማስረጃ ሰምቶ የመሠለውን ፍርድ ይሰጥ ዘንድ ጉዳዩ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት ተመልሷል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በይግባኝ መዝገብ ቁጥር ነሐሴ ቀን የሰጠው ትዕዛዝ ተሽራል በዚህ ክርክር ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ይህ ፍርድ ቤት መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር መቁ ዐ የካቲት ዐ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ታፈሠ ይርጋ መድህን ኪሮስ ሠልጣን አባተማም አመልካች የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ነፈጅ ቀረቡ ተጠሪዎች እነ አቶ ደጀኔ አበበ ሰዎች ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ ጉዳይ ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ሊቀርብ የቻለው አመልካች የፌመደፍቤት መጋቢት ቀን ዓም በአሸት የምግብ ውጤቶችና መኖ አክሲዮን ማህበር የዱቄት ፋብሪካ ላይ ቀደም ብሎ የተሰጠው እግድ መነሳት የለበትም በማለት የሰጠውን ትእዛዝ እና የፌከፍቤትም ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሥር ፍቤት የሰጠውን ትአዛዝ ማጽናቱን በመቃወም ነው አመልካች ይህን መሠረት በማድረግ ጥቅምት ቀን ዐዐዐ ዓም ጽፎ ባቀረበው የሰበር አቤቱታ ተጠሪዎች በአሸት የምግብ ውጤቶችና መኖ አክሲዮን ማህበር ላይ የሒሣብ ይጣራልን ክስ አቅርበው የዚሁ አክሲዮን ማህበር ንብረት የሆነው ዱቄት ፋብሪካ እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ የሚል የዕግድ ትእዛዝ በፌመደፍቤት አሰጥተዋል በበኩላችን ደግሞ ፋብሪካው ለአክሲዮን ማህበሩ ለሰጠነው የብር ዐዐዐአስራ አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ስድሣ ዘጠኝ ሺህ ብድር በአንደኛ ደረጃ መያዣነት የያዝነው በመሆኑና ብድሩም እስካሁን ስላልተመለሰ ፋብሪካውን ሸጠን ገንዘባችንን ለማስመለስ እንድንችል እግዱ ይነሣልን በማለት ህዳር ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ ጠይቀናል ሆኖም ጉዳዩን የያዘው የፌመደፍቤት ህዳር ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሒሣብ ማጣራቱ ውጤት እስከሚታወቅበት ጊዜ ድረስ የተሰጠው የዕግድ ትእዛዝ የሚነሣበትን ሁኔታ ስላላገኘን አቤቱታውን አልተቀበልንም እግዱ እንዳለ ይቀጥል ሲል ትአዛዝ ሰጥቷል እንደገና ታህሣሥ ቀን ዓም የተሰጠው አግድ እንዲነሣልን ብናመለክትም አሁንም ፍቤቱ ራሴ የሰጠሁትን የዕግድ ትእዛዝ መልሼ የማነሣበት ምክንያት የለም በማለት ጥያቄያችንን ሣይቀበለው ቀርቷል በዚሁ ጉዳይ ለፌከፍቤት ይግባኝ ብናቀርብም ይህ ፍቤትም የሥር ፍቤቱን ትእዛዝ በማፅናት ይግባኛችንን ሰርኮብናል የሥር ፍቤት ሒሣቡ እስኪጠራ ድረስ እግዱ አይነሣም ሲል የሰጠው ትአዛዝ አመልካች በአዋጅ ቁጥር ዐ የተሰጠውን ስልጣን እንዳይጠቀምበት ገደብ የሚጥል መብት የሚነፍግ ከመሆኑም በላይ በአመልካች ባንክ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል ነው ምክንያቱም የሒሣብ ማጣራቱ ሥራ እንደተመለከትነው የጊዜ ገደብ ያልተቀመጠለት በመሆኑና የብድሩ ገንዘብ ወለድ አየጨመረ የድርጅቱ ንብረትም እየተበላሸ በመሆኑ አግዱ ባለመነሣቱ ምክንያት የሚደርሰው ጉዳት በቀላሉ የሚገመት አይደለም የአክሲዮን ማህበሩ ንብረት የሆነው ዱቄት ፋብሪካ የታገደው ለዕዳው ተጠያቂ በሆኑ የማህበሩ አባላት በሆኑት ሰዎች በነበረው የሒሣብ ክርክር መነሻነት ሲሆን ባንኩ የሚፈለገው ብር ዐዐዐዐዐዐክፃያ ሁለት ሚሊዮን ደግሞ የማህበሩ አባላትና የአክሲዮን ማህበሩ የጋራ ዕዳ ነው ፍቤቶቹ የሰጡት ትእዛዝ ደግሞ ባንኩ በአዋጅ ቁጥር ዐ እና ዐ የተሰጠውን በብድር የሰጠውን ገንዘብ የመሰብሰብ ሥልጣን የሚገደብና በሕዝብና መንግሥት ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ ነው በመሆኑም ሰበር ሰሚው ችሎት የሥር ፍቤቶች የሰጡትን ትዕዛዝ በመሻር እግዱ እንዲነሣ እንዲወሰንልን በማለት አመልከቷል ተጠሪዎቹ ፋብሪካው ታህሣሥ ቀን ዐዐዐ ዓም ጽፈው ባቀረቡት መልስ እሽጉ የምግብ ውጤቶችና መኖ አክሲዮን ማህበር ከአባላቱ መዋጮና ከአመልካች ባንክ በተገኘው ብድር በብር ዐዐዐ የተመሠረተ የዱቄት ፋብሪካ ነው የአክሲዮን ማህበሩ ቦርድ ከ ዓም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ዓመታት አባላትን ባለመጥራቱና ሪፖርትም ባለማቅረቡ የተነሣ በስር ፍቤት የሒሣብ ይጣራ ክስ ተመሥርቷል ንብረቱ እንዳይባክን ፋብሪካው ሒሣቡ ተጣርቶ እስከሚያልቅ ጊዜ ድረስ እንዳይሸጥ አንዳይለወጥ ታግዶ እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ባቀረብነው ጥያቄ መሠረት በፌመደፍቤት የአግድ ትእዛዝ ተሰጥቶልናል አመልካችም እግዱ እንዲነሣለት አመልክቶ በፍቤቱ ተቀባይነት አላገኘም በዚሁ ትአዛዝ ላይ ይግባኝ ማለት ሲገባው አመልካቹ እንደገና ተመሣሣይ የሆነ የእግድ ይነሣልኝ ጥያቄ መጀመሪያ የአግድ ትአዛዝ ለሰጠውና እግዱ እንዲነሣ ጥያቄ ቀርቦለትም እግዱ አይነሳም ላለው ፍቤት አቅርቧል ይህ ፍቤት ራሱ የሰጠውን ትእዛዝ የሚያስለውጥ ሌላ ትእዛዝ መስጠት ስለማይችል የአግድ ይነሣልን ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ በአግባቡ ነው ፌከፍቤትም የቀረበለትን ይግባኝ መሠረዙ የሚነቀፍ አይደለም እኛ የእግድ ትእዛዝ እንዲሰጥልን ያመለከትነው የማጣራት ሥራው እስኪያልቅ ጊዜ ድረስ ፋብሪካው ካልታገደ የሒሣቡ ጉድለትና የንብረቱ መባከን ሣይታወቅ ተሸፋፍኖ ይቀራል የሚል ስጋት ስላደረብን ነው ፍቤቶቹም የሰጡዋቸው ትእዛዞች ይህን ስጋት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው የማጣራት ሥራው በአፋጣኝ ሊከናወን ያልቻለው አመልካች የዱቄት ፋብሪካውን በሮች በመበየድ አጣሪዎች እንዳይገቡ በመከላከሉ መክንያት ነው ጉዳዩን እየተመለከተ ያለው ፍቤት አመልካች ብይዱን እንዲያነሣና የሒሣብ ማጣራት ሥራው እንዲቀጥል ሲል ትእዛዝ የሰጠ ቢሆንም እስካሁን የፍቤቱ ትእዛዝ ተግባራዊ አልሆነም በመሆኑም አመልካች የፌመደፍቤት መጀመሪያ እግዱ አይነሳም በማለት በሰጠው ትእዛዝ ላይ ይግባኝ ማለት ሲገባው እንደገና የእግድ ይነሣልኝ ጥያቄ ማቅረቡ አግባብ ባለመሆኑና የሥር ፍቤት ደግሞ ራሴ የሰጠሁትን ትአዛዝ መልሼ ራሴ ላነሣው አልችልም ያለው በአግባቡ በመሆኑ ፌከፍቤት የሰጠው ትእዛዝም የሚነቀፍበት ምክንያት ስለሌለ በስር ፍቤቶቹ የተፈፀመ የህግ ስህተት የለም ሰበር ሰሚው ችሎትም ይህን ተመልክቶ በሥር ፍቤቱቹ የተሰጡትን ትክዛዞች እንዲያፀናልን ሲሉ አመልክተዋል አመልካችም የመልስ መልሱን በማቅረብ በአቤቱታው የተጠቀሱትን ክርክሮች ለማጠናከር ሞክሯራል በበኩላችን ደግሞ በአመልካቹ የቀረበውን የፅግድ ይነሣልኝ ጥያቄ የሥር ፍቤቶች ውድቅ ማድረጋቸው በአግባቡ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም ተጠሪዎች ባቀረቡት መልስ የዱቄት ፋብሪካው የተመሠረተው ከአመልካች ባንክ በብድር በተገኘው ገንዘብ ጭምር መሆኑን ስላመኑና ለዚህ በብድር ለተገኘው ገንዘብም ፋብሪካው በአንደኛ መያዣነት አልተመዘገበም ብለው ስላልካዱ አመልካቹ ያቀረበው የእግድ ይነሣልኝ ጥያቄ በአግባቡ መሆኑን ተገንዝበናል የሥር ፍቤቱ መጀመሪያ የሰጠው የዕግድ ትእዛዝ ደግሞ በአክሲዮን ማህበሩ አባላት መካከል የሒሣብ ይጣራልን ክስ ቀርቦ በክርክር ላይ ባሉበት ጊዜ ከአባላቱ በአንዱ ወገን ሒሣቡ ሣይጣራ ፋብሪካ እንዳይሸጥ ለመከላል እንጂ በብድር ምክንያት በመያዣነት የያዘው ባንክ ገንዘቡን ለማስመለስ በማሰብ አንዳይሸጠው ለመከልከል እንዳልሆነ ከትዕዛዙ መንፈስ ለመረዳት ችለናል አመልካች ባንክ በዋስትና የያዘውን ንብረት በመሸጥ በብድር የሰጠውን ገንዘብ ከነወለዱ የማስመለስ ስልጣን በአዋጅ ቁጥር ዐ አንቀጽ እና መሠረት የተሰጠው በመሆኑ በዋስትና በያዘው ፋብሪካ ላይ የተሰጠው እግድ እንዲነሣለት ጥያቄ ማቅረቡ በአግባቡ ነው ሆኖም የፌመደፍቤት የእግድ ይነሣልኝ ጥያቄው ሲቀርብለት አመልካች በአዋጁ የተሰጠውን ሥልጣን መሠረት በማድረግ መብቱን ለማስጠበቅ እንዲችል የእግድ ትእዛዙን ሊያነሣለት ሲገባ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ የሕግ ስህተት መሆኑን ተመልክተናል መጀመሪያ እግዱ አይነሣም የሚል ትአዛዝ ተሰጥቶ እያለ በዚሁ ትአዛዝ ይግባኝ እንደማለት ተመልሶ እንደገና አመልካች ለዚሁ እግዱ አይነሣም ላለው ፍቤት እግዱ ይነሣልኝ ማለት አይችልም ተብሎ በተጠሪ የቀረበውን ክርክር ስንመለከትም የተሰጠው የእግድ ትእዛዝ ጊዜያዊ እንደመሆኑ መጠን ከጊዜ በኋላ ከሁኔታዎች ጋር በማገናዘብ ሊሻሻል ሊነሣ ወይም ሊሠረዝ የሚችልበት ምክንያት ሲኖር አስቀድሞ የእግድ ትእዛዝ የሰጠው ፍቤት እግዱን እንዲያነሣ ማመልከት እንደሚቻልና ፍቤቱም እንደየሁኔታው እግዱን ሊያሻሽልሊያነሣ ወይም ጨርሶ እንዲሰረዝ ሊያደርግ እንደሚችል በፍሥሥሕቁ የተደነገገ በመሆኑ የተጠሪዎቹ ክርክር ተቀባይነት ያለው ሆኖ አላገኘነውም በመሆኑም የፌመደፍቤት በመጀመሪያም ይሁን በሁለተኛው ጊዜ የቀረበውን የእግድ ይነሣልኝ ጥያቄ ያለመቀበሉና የእግድ ትእዛዙን ያለማንሣቱ ፌከፍቤትም የሥር ፍቤቱን ትእዛዝ ጉድለት የለበትም በማለት የቀረበለትን ይግባኝ መሠረዙ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ትእዛዞቹ መሻር ያለባቸው ሆነው አግኝተናቸዋል ውሣኔ የፌመፊፍቤት በመቁ መስከረም ቀን ዓም የሰጠው የዕግድ ትእዛዝና ህዳር ቀን እና መጋቢት ቀን ዓም እግዱ አይነሣም በማለት የሰጣቸው ትእዛዞች አንደዚሁም የፌከፍፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ትእዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽረዋል እግዱም ተነስቷል ይፃፍ ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሂሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ አመልካች የአዲስ ከተማ ክከተማ አስተዳደር የመሠረተ ልማትና የቤቶች ጉዳይ ጽቤት ነፈጅ ቀረበ ተጠሪ ኛ የቀኛዝማች መኮንን ነጋሽ ወራሾች ከጠ ጋር ቀረቡ ኛ ወሮ ገነት አበራ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረው በፌመደፍቤት ሲሆን የአሁኑ ኛ ተጠሪ መስከረም ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት ክስ ቁጥሩ ለ የሆነው በወረዳ ቀበሌ ዐ ውስጥ የሚገኘው ቤት የቀኛዝማች መኮንን ነጋሽ ጋራዥ ውስጥ የሚገኝና አቶ ተስፋዬ ሃይሌ የሚባሉ የጋራ ሠራተኛ ሲኖሩበት የነበረ የአውራሻችን የቀኛዝማች መኮንን ነጋሽ ቤት በመሆኑ ይልቀቁልን በማለት በወሮ ገነት አበራ ላይ ክስ አቅርበዋል ተከሳሺም የካቲት ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት መልስ የቤቱ ግምት በክሱ ላይ አልቀረበም ዳኝነትም አልተከፈለበትም ከሣሾች በንብረት አጣሪነት አልተሾሙም የሚሉትን ነጥቦች በመጠቃቀስ የመጀመርያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ተከሳሽ በፍሬ ነገሩ ላይ ክደው ስላልተከራከሩ በክሱ የተጠቀሰውን ቤት ለከሳሾች እንዲያስረክቡ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል በመቀጠልም የአከክ ከተማ መሠረተ ልማትና ቤቶች ኤጀንሲ ሚያዝያ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው አቤቱታ ከሳሾች ክስ የመሰረቱበት በቀድሞ ወረዳ ቀበሌ ዐ በአዲስ ከተማ ክከተማ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥሩ ለ የሆነው ቤት ያረፈበት ቦታ በአዋጅ ቁጥር መሠረት የተወረሰ ነው ተከሳሽ የመንግስትን ቦታ ላይ ያለፈቃድ የንግድ ቤት ሠርተው ነበር አስተዳደሩ ቦታውን ለማጽዳት ሲንቀሳቀስ ተከሳሽ ባለሃብትነታቸውን ለመንግስት አስተላልፈው የቤት ኪራይ እየከፈሉ በቤቱ ለመገልገል በመስማማታቸው ከአስተዳደሩ ጋር ውል ገብተው የቤት ኪራይ እየከፈሉ ይገኛሉ የመቃወም አመልካች በመንግስት ባለቤትነት ሥር የሚገኙትን ቤቶች የማስተዳደርና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው ከሣሾች ክስ ባቀረቡበት ቤት ላይ ያቀረቡት ካርታ ወይም ደብተር የለም ተከሳሽ ቤቱን ለከሳሽ እንዲያስረክቡ በማለት ፍቤቱ የሰጠው ውሣኔ የመቃወም አመልካችን መብት የሚሜጋፋ ነው ስለዚህ ፍቤቱ መዝገቡን ለአዲስ አበባ ከተማ የመጀመርያ ደረጃ ፍቤት ያስተላልፍልን እንደዚሁም ቤቱ የመቃወም አመልካች እያከራየ ኪራይ የሚሰበስብበት ስለሆነ ፍቤቱ የሰጠውን ውሣኔ ሽሮ ኪሣራ እንዲቆርጥልን በማለት አመልክቷል ከሣሾች ደግሞ በግንቦት ቀን ዓም በተፃፈ መልስ የመቃወም አመልካች ቀበሌው በከፍተኛው ፍቤት በመቁ እና በፍቤቱ ትዕዛዝ ጣልቃ ገብቶ ቤቶቹ ተወርሰዋል የሚለውን ክርክር አቅርቦ ክርክሩ ተቀባይነት የለውም ተብሎ ተወስኖበታል ክከተማው የቀበሌው የበላይ አካል ስለሆነ እንደገና ተቃዋሚ ሆኖ የሚቀርብበት ምክንያት የለም ቤቶቹ አልተወረሱም እንጂ ተወርሰዋል የሚል ክርክርም ካለ መከራከር የሚችለው የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነው ማስረጃዎችን በተመለከተ ቤቶቹ ተመን እንዲወጣላቸው በነሐሴ ቀን ዓም የተፃፈ የተባለው የቤት መውረሻ ቅጽ አረጋጋጭ ቁጥር ተከሳሾች ከተፈረደባቸው በኋላ በ ዓም የተፃፈ ስለሆነ የቤት መውረስን አያስረዳም የወሮ ገነት አበራ ጉዳይ በሰበር ያለቀለት ነው በመሆኑም ፍቤቱ ጥያቄውን ውድቅ እንዲያደርግልን በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ በመቃወም አመልካች ቁጥሩ ለ የተወረሰ መሆኑን ለማስረዳት ያቀረበው ሰነድ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ፋይናንስ ቢሮ በዞን አንድ የወረዳ ፋይናንስ ቢሮ ጽቤት በ የፃፈው ሠነድ ሲሆን ሰነዱም በቤት ቁጥር በሆነው ቤት ኛ የመቃወም ተጠሪ ይሠሩበት የነበረ መሆኑን የሚገልጽ እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የወረዳ ቀበሌ አስተዳደር ጽቤት በመስከረም ዐ ቀን ዓም የፃፈው ሰነድ ሲሆን ይዘቱም ከላይኛው ማስረጃ ተመሳሳይ ነው በተጨማሪ የመቃወም አመልካች በቤት ቁጥር ላይ የኛ የመቃወም ተጠሪ የንግድና የሥራ ፈቃድ እንዳለውና ቤቱን የክልል መስተዳድር ጽቤት ለኛ የመቃወም ተጠሪ ያከራየበትን በጥቅምት ቀን ዓም የተደረገ ውል ቀርቧል ማስረጃው ሲመረመርም ማስረጃዎቹ በዚህ መዝገብ ውሣኔ ያረፈበት ቤት ኛ የመቃወም ተጠሪ የያዙት መሆኑን ወይም ለኛ የመቃወም ተጠሪ የተከራየ መሆኑን ሊያስረዳ ከሚችል በስተቀር የቤቱ ባለቤት ማን እንደሆነ የሚያስረዳ አይደለም በሌላ በኩል ደግሞ በአዋጅ ቁጥር መሠረት ትርፍ የሆኑ ቤቶች ባለቤቱ የመረጠውን ቤት ከወሰደ ወይም ካስቀረ በኋላ ትርፍ ቤቶቹን ለመንግስት የሜያስረክብበት ስርዓት መኖሩ ይታወቃል ሆኖም የመቃወም አመልካች በክሱ የተጠቀሰው ቤት በዚሁ መልኩ በትርፍነት መንግስት የተረከበው ስለመሆኑ የሚያስረዳ የቀረበ ማስረጃ የለም በመሆኑ በመቃወም አመልካች በዚህ መዝገብ ውሣኔ ያረፈበት ቁጥር የተወረሰ መሆኑን ባላስረዳበት ሁኔታ ቤቱ የተወረሰ ስለሆነ ውሣኔው ይሰረዝልኝ በማለት ያቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም ብሎ ክርክሩን በፍብሥሥሕቁ መሠረት ውድቅ አድርጎታል ፌከፍቤትም ይግባኝ ቀርቦለት የሥር ፍቤት ፍርድ ጉድለት አላገኘሁበትም በማለት ይግባኙን በፍብሥሥሕቁ መሠረት ሰርዞታል የሥር የመቃወም አመልካች የአሁኑ አመልካች ለዚህ ፌጠፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰበር አቤቱታን ያቀረበውም የፌመደፍቤት በሰጠው ፍርድና የፌከፍቤት በሰጠው ትዕዛዝ ቅር በመሰኘት ነው ቅሬታውም ፍቤቶቹ ክሱን በመስማት ግራ ቀኙን አከራክረው ውሣኔና ትዕዛዝ የሰጡት ክሱን የማየት ሥልጣን ሳይኖራቸው ነው ኛ ተጠሪ የተከራዩት ቤት የተሰራው በአዋጅ ቁጥር መሠረት በተወረሰ ባዶ የመንግስት መሬት ወይም ቦታ ላይ ሆኖ የተሠራውን ያለፈቃድ በመሆኑ መፍረስ የነበረበት ሲሆን በወቅቱ በነበረው መመሪያ መሠረት ከሚፈርስ ተጠሪዋ በኪራይ እንዲጠቀሙበት ተወስኖ ከ ዓም ጀምሮ በኪራይ እየተጠቀሙበት ቆይተዋል ይህ ክርክር ያስነሳው ቤት ኛ ተጠሪ በአዋጅ ቁጥር መሠረት አልተወረሰም እያሉ የሚያቀርቡት ክርክር ካቀረብነው መቃወሚያ ጋር ያልተገናዘበ ነው የኛ ጥያቄ ቤቱ የተሰራው በአዋጁ መሠረት በተወረሰ የመንግስት ቦታ ላይ ነው የሚል እንጂ ቤቱ ራሱ በውርስ የተገኘ ነው የሚል አይደለም አመልካች በሕግ በተሰጠው ስልጣን መሰረት በባለቤትነት የሚያስተዳድረውን ቤት በአዋጅ ቁጥር መሠረት የተፈቀደላቸውና ያለአግባብ ከአዋጁ ውጪ ተወስዶብኛል የሚሉ ከሆነ ተጠሪዎች ለሚመለከተው ለፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ጥያቄያቸውን አቅርበው ማስወሰን ይጠበቅባቸዋል በዚሁ መሠረት ጥያቄያቸውን አቅርበው ባላስወሰኑበት ወይም የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተርም ይሁን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በማቅረብ በቤቱ ላይ መብት ያሳቸው መሆኑን ሳያረጋግጡ ክስ ማቅረብ አይችሉም የሥር ፍቤቶች ክሱን በፍብሥሥሕቁ መሠረት ውድቅ ማድረግ ሲገባቸው ክሱን ተቀብለው ማከራከራቸውና ከዚህም አልፈው ቤቱ የተወረሰ ስለመሆኑ የመቃወም አመልካች አላስረዳም በማለት ቤቱን ለኛ ተጠሪዎች እንድናስረክብ መወሰናቸው ሕጉን ያላገናዘበ ነው በመሆኑም ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ የፌመደፍቤትና የፌከፍቤት ውሣኔ ተሽሮ ጉዳዩ በሕግ ሥልጣን በተሰጠው የአዲስ አበባ ከተማ ነክ ፍቤት እንዲዳኝ ተብሎ ሊወሰንልን ይገባል የሚል ነው ኛ ተጠሪ ጥር ቀን ዐዐ ዓም በተፃፈ መልስ አከራካሪው ቤት አዋጅ ቁጥር ከመውጣቱ በፊት በቀኛዝማች መኮንን ነጋሽ የተሰራና አቶ ተስፋዬ ሀይሉ የተባሉ የድርጅቱ የሕግ ክፍል ሰራተኛ የሚጠቀሙበት ነበር ወሮ ገነት አበራም ከዚህ ሠራተኛ ጋር አብረው ይሰሩ ስለነበር ቤቱን ልቀቂ ሲባሉ አለቅም አሉ እንጂ ቤቱን ራሳቸው አልሰሩትም አመልካች ቤቱን መንግስት ተረክቦት ኪራይ እየሰበሰበበት ነው የሚለው ከ ዓም በኋላ ከኛ ተጠሪ ጋር በመስማማት ነው ቤቱ በ ዓም ሆነ ከዚያ ወዲህ ተወርሶ አመልካች የሚያስተዳድረው አይደለም አመልካች በተቃዋሚነት ልግባ ብሎ እኔ የማስተዳድረው ቤት ነው ብሎ ስለመጣ ቤቱ ስለመወረሱ አስረዳ ተባለ እንጂ ቦታው ባዶ ሆኖ ቦታውን ስለመውረሱ ማስረጃ አቅርብ አልተባለም እኛ በግቢው ውስጥ ያሉት ቤቶች ሁሉ የቀኛዝማች መኮንን ነጋሽ ንብረት መሆናቸውን አስረድተናል የፌፍቤቶች ስልጣን የላቸውም ተብሎ ለማስረዳት የተጠቀሱት ሕጐችም ለዚህ ጉዳይ አግባብነት ስለሌላቸው ክርክሩ ተቀባይነት የለውም በመሆኑም የሥር ፍቤቶች የሰጡት ውሣኔ የሕግ ስህተት የሌለበት በመሆኑ እንዲፀድቅልን በማለት ተከራክረዋል ኛ ተጠሪ ደግሞ ጥር ቀን ዐዐዐ ዓም በተፃፈው መልስ በወረዳ ቀበሌ ዐ በአዲሱ አደረጃጀት ደግሞ በአክከተማ ቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥሩ ለ የሆነው ቤት ቀደም ብሎ በሳጠራና በቆርቆሮ ከፍዬ የታይፕ የጽህፈት ሥራ ሳከናውንበት በነበረው ባዶ የመንግስት መሬት ላይ እኔ ራሴ የሰራሁት ቤት ነው አመልካች ቤቱ በአዋጅ ቁጥር መሠረት በተወረሰው ባዶ የመንግስት ቦታ ላይ የተሰራ ቤት መሆኑን ካወቁ በኋላ ቤቱን ለማፍረስ አስበው የነበረ ቢሆንም ቤቱ ቢፈርስ እኔንና ቤተሰቤን የሚያፈናቅል ሆኖ ስላገኙት በኪራይ እንድኖርበት ተፈቅዶልኝ እየሠራሁበት እገኛለሁ ኛ ተጠሪዎች ከአቶ ተስፋዬ ሃይሉ ጋር ጥገኛ ስለነበርሸ አሁን ያለሸበትም ቤት አቶ ሃይሉ ሲሰራበት የነበረው ቤት ነው በማለት ይህን ቤት ከሌሎች ቤቶች ጋር በመደመር ክስ መሰረቱብኝ እንጂ ቤቱ አቶ ተስፋዬ ሲሰሩበት የነበረው ቤት አይደለም እንደዚሁም ኛ ተጠሪዎች ቤቱ የእነሱ ስለመሆኑ የሚያስረዳ የቤት ባለቤትነት ደብተርም ይሁን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ሳያቀርቡ በቤቱ ላይ የባለቤትነት መብት ሳይኖራቸው ነው ክስ የመሰረቱብኝ የሥር ፍቤቶችም ቤቱን እንድለቅ የወሰኑት ኛ ተጠሪዎች ቤቱ የእነሱ ስለመሆኑ የሚያስረዳ ማስረጃ ሳያቀርቡ ነው በመሆኑም የሥር ፍቤቶች ውሣኔ እንዲሻርልኝ በማለት ተከራክራለች ከዚህ በኋላም ግራ ቀኙን በቃል በማነጋገርና አንዳንድ ነጥቦች ላይ ጥያቄ በማቅረብ ተከራካሪዎቹ ተጠቃሹ ቤትና የተጠሪዎች አውራሽ ጋራዥ ያላቸውን የአቀማመጥ ግንኙነት በተመለከተ ግልጽ አድርገውልናል በበኩላችን ደግሞ የፌፍቤቶች ክሱን ለማየት ሥልጣን አላቸው ወይስ የላቸውም። የሚሉትን ጭብጦች በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም ክሱ የባለቤትነት ጥያቄን መሠረት በማድረግ የቀረበ እንጂ ከቤት ኪራይ ጋር በተያያዙ ሁኔታዎች መነሻነት የቀረበ ባለመሆኑ የፌፍቤቶች ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ያላቸው መሆኑን ተገንዝበናል በመሆኑም አመልካች የፌፍቤቶች ክሱን ያዩት በሌላቸው ሥልጣን በመሆኑ ጉዳዩ በከተማ ነክ ፍቤት እንዲታይ ይወሰንልኝ በማለት ያቀረበውን ጥያቄ አልተቀበልነውም ሁለተኛውን ጭብጥ በተመለከተ ደግሞ ኛ ተጠሪዎች በክሱ የተጠቀሰው ቤት ያለአግባብ የተወረሰ ነው በማለት እንዲመለስላቸው ለፕራይቤታይዜሽን ኤጀንሲ በማቅረብ ቤቱ እንዲመለስላቸው የተወሰነላቸው ስለመሆኑ ወይም ቤቱ የራሳቸው ስለመሆኑ የሚያስረዳ የቤት ባለቤትነት ደብተር ወይም ደግሞ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ያላቸው ስለመሆኑ ማስረጃ በማቅረብ አላሳዩም ክሱን ያቀረቡት ለክሱ መነሻ በሆነው ቤት ላይ መብት ያላቸው መሆኑን ሳያረጋግጡ ነው በክርክሩ ሂደትም የባለቤትነት መብት ያላቸው ስለመሆኑ አላስረዱም በመሆኑም ክሱ ከመጀመርያው የቀረበው መብቱ ያሳቸው ስለመሆኑ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ስለሆነ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ውድቅ መሆን የነበረበት ሆኖ አግኝተነዋል ሶስተኛውን ጭብጥ በተመለከተም የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሃብትነት የሚረጋገጠው ከአስተዳደር ክፍል የተሰጠ የምስክር ወረቀት በማቅረብ ስለመሆኑ በፍብሕቁ ተደንግጓል አዋጅ ቁጥር ደግሞ ከታህሳስ ቀን ዓም ጀምሮ የከተማ ቤትን በንብረትነት የያዘ ሰው መብቱ በሜኒስትሩ ካልፀደቀ በስተቀር ንብረትነቱ አይፀናለትም ይላል የእነዚህን ሕጐች ድንጋጌ መሠረት በማድረግ ስንመለከተው ደግሞ ማንኛውም የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ነኝ የሚል ሰው ንብረቱ የራሱ ስለመሆኑ በአስተዳደር ክፍል ተረጋግጦ የምስክር ወረቀት ወይም ውሣኔ ካልተሰጠው በስተቀር ወይም ለአስራ አምስት ዓመት ግብር እየገበረበት በይዞታው ስር አድርጐ ካላቆየው በስተቀር የንብረቱ ባለሃብት እንደሆነ እንደማይቆጠር ለመረዳት ይቻላል የሕጉ ድንጋጌ የሚያዘው ይህ ሆኖ ሳለ የሥር ፍቤቶች ቤቱ የእኛ ነው ያስረክቡን በማለት ክስ የመሰረቱት ኛ ተጠሪዎች የቤቱ ባለቤትና የሃብቱም ባለመብት ስለመሆናቸው ማስረዳት ሲኖርባቸው አመልካቹ ቤቱ የተወረሰ መሆኑን ያስረዳ ማለታቸው በአግባቡ ሆኖ አላገኘነውም እንደዚሁም ቤቱ የተሰራው በአዋጅ ቁጥር መሠረት በተወረሰው ባዶ ቦታ ላይ ነው በማለት አመልካች እየተከራከረ እያለ ቤቱ የተገኘው በውርስ ነው በማለት እንደተከራከረ በመቁጠር ክርክሩ ቤቱ የተገኘው በውርስ ነው ወይስ አይደለም በማለት ግራ ቀኙን ማከራከራቸው ተገቢ ያለመሆኑን ተገንዝበናል በመሆኑም የፌመደፍቤት የሰጠው ፍርድና የፌከፍቤት የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትና ሊታረም የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የፌመደፍቤት በመቁ ሕዳር ቀን ዓም እና በመቁ ሐምሌ ዐ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የፌከፍቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽረዋል ይፃፍ በአዲስ ከክከተማ በቀበሌ ክልል የሚገኘው ቁጥር ለ የሆነው ቤት በአዋጅ ቁጥር መሠረት በተወረሰው ወይም በተገኘው ባዶ የመንግስት ቦታ ላይ የተሰራና አመልካች የሚያስተዳድረው የመንግስት ቤት ነው ብለናል ይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ዙዘ የሰመቁ በሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ ሱልጣን አባተማም አመልካች እነ አቶ ዋለልኝ ንጉሱ ወራሽ ቀረቡ ተጠሪ እነ አቶ አለሙ ወንድሙ ጠበቃ አቢይ ወርቁ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ጉዳይ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ነክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪዎች በአመልካቾች ላይ ባቀረቡት ክስ በወረዳ ቀበሌ ቁጥር ዐ የሆነውን ቤት ከአዋጅ በፊት የሰራነው ሲሆን በአዋጁም አልተወረሰም በዚሁ ቤት በስማችን የንግድ ፈቃድ አውጥተን በኃይለስላሴ ጊዜ ተከሣሾችን በግል ድርጅታችን እንዲሰሩ አስጠግተናቸው ነገር ግን እንዲለቁ ተጠይቀው ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንዲለቁ ይወሰንልን በማለት ጠይቀዋል ተከሳሾችም ቀርበው ክስ የቀረበበት ቤት በአዋጁ ተወርሶ የአከራይ ተከራይ ግንኙነታችን ተቋርጧል ኪራይም ለቤቱ ባለቤት ለቀበሌው አስተዳደር እየከፈልን ስለሆነ ከሣሾች ቤቱ ይለቀቅልን በማለት ያቀረቡት ክስ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክረዋል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለት የከተማ ነክ የመደፍቤት ክርክር የቀረበበትን ቤት ማኀደር አስቀርቦ በመመልከት ቤቱ የተወረሰ ስለመሆኑ አልተረጋገጠም በማለት ተከሳሾች ይህንኑ ክስ የቀረበበትን ቤት ሊያስረክቡ ይገባል ሲል ውሣኔ ሠጥቷል ከዚህ በኋላም ጉዳዩ በይግባኝና በሰበር ለከተማው ፍቤት ቀርቦ ቤቱ ሊመለስ ይገባል ተብሎ በበታች ፍቤት የተሰጠው ውሣኔ በአብላጫ ድምጽ ጸንቷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንኑ በመቃወም ሲሆን ይህ ችሎትም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሯል ይህ ችሎት በቅድሚያ የተመለከተው የክርክሩን አመራር በተመለከተ ነው የሥር ከሳሾች የአሁን ተጠሪዎች ዳኝነት የጠየቁት የግል የሆነ ቤታችን በሥር ተከሳሾች በአሁን አመልካቾች ያለአግባብ የተያዘብን ስለሆነ እንዲመለስልን ይወሰንልን በማለት ነው ተከሳሾችም በበኩላቸው ቤቱ በመንግሥት በመወረሱ ምክንያት ከከሣሾች ጋር የነበራቸው የኪራይ ውል ተቋርጦ ከቤቱ ባለቤት የቀበሌው አስተዳደር ጋር የኪራይ ውል በመዋዋል ኪራይ እንደሚከፍሉ ገልፀው ክሱ ሊሰረዝ ይገባዋል ብለዋል ከሳሾች በአንድ በኩል የቤቱ ባለቤት ነን የሚሉ ከሆነና በሌላ በኩልም ቤቱ በአዋጅ በመንግሥት ተወርሷል ከተባለ ክርክሩ ባለቤትነትን የመፋለም ዞቨርቫ ርቪበ ስለሚሆን ቤቱን በውርስ ይዞ በማስተዳደር ላይ ይገኛል የተባለው የቀበሌው አስተዳደር ለክርክሩ እጅግ አስፈላጊ ወገን በሀበኗ ዞጸፎ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል ምክንያቱም ለክርክሩ እጅግ አስፈላጊ የሆነው ወገን በሌለበት የሚሰጥ ውሣኔ መብቱን ጥቅሙን ሊነካ እንደሚችል ስለሚታመን ነው ይህ ለክርክሩ አጅግ አስፈላጊ የሆነው ወገን በከሳሾች በኩል በተከሳሽነት እንዲጣመር ባይደረግም ፍቤቱ በፍብሕሥሥህቁ ዐ ላይ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ወደ ክርክሩ እንዲገባ ማድረግ ነበረበት ስለሆነም በየደረጃው ባሉ የከተማ ነክ ፍቤቶች ለጉዳዩ እልባት የተሰጠው ለክርክሩ እጅግ አስፈላጊ የሆነው የቀበሌው አስተዳደር የክርክሩ ተካፋይ ባልሆነበት ሁኔታ ስለሆነ የሕግ ስህተት ተፈፅሟል ነዓ ውሣኔ የአዲስ አበባ ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደፍቤት ይግባኝ ሰሚ ፍቤትና ሰበር ችሎት በዚህ ጉዳይ የሰጡት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል ይፃፍ የሚመለከተው የቀበሌ አስተዳደር ለጉዳዩ እጅግ አስፈላጊ ወገን በሀከ ፀዝ ስለሆነ የከተማ ነክ የመደፍቤት ይህንኑ ወገን ወደ ክርክሩ በማስገባት አከራክሮ እንዲወስን ጉዳዩ ተመልሶለታል ግራ ቀኙ ወጭና ክሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ፏ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሂሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ መድህን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ አመልካች የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ነገረ ፈጅ ሣሙኤል ክፍሉ ተጠሪ ከበደ ታደሰ ተወካይ ግዛው ከበደ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ነበር መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ መዝገቡ የቀረበው አመልካች የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ እና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ፍርድ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ይታረምልኝ በማለት ታህሣስ ቀን ዓም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ በመጠየቁ ነው የክርክሩ መነሻ ተጠሪው ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የማዕድንና ኢነርጅ ቢሮ በተሰጠኝ ፈቃድ መሰረት አስቆፍሬ ያከማቸሁትን አስር ሺ ስምንት መቶ ዛምሳ ሜትር ኪዩብ በአስራ ዘጠኝ መኪና አስጭኖ የተጠቀመበት በመሆኑና ቦታውን በመያዝ የወደፊት ጥቅም ያስቀረብኝ ስለሆነ ብር አራት መቶ ሰማኒያ ስምንት ሺ ሁለት መቶ ሐምሳ ብር እንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት በሥር ተከሳሽ በሆነው የድራጋዶስ የመንገድ ሥራ ድርጅት ያቀረበው ክስ ሲሆን አመልካቹ ወደ ክርክሩ የገባው ቦታው ከማናቸውም ሰው የይገባኛል ጥያቄ ነፃ ነው በማለት ያስረከበኝ የኢትዮጵያ መንገድ ባለስልጣን ስለሆነ ቦታውን አስመልክቶ ለተነሳው ክርክር በሶስተኛ ወገን ተከሳሽነት ጣልቃ እንዲገባ ተከሳሹ በማመልከቱና ክሱን ያየው ፍርድ ቤት ትአዛዝ በመስጠቱ ነው አመልካች በሶስተኛው ወገን ተከሳሸነት ቀርቦ ክርክር የተነሣበትን ቦታ ለተከሳሹ ያስረከበው በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ሐላፊነት መሆኑንና ከሳሽም የመንግስት ሐብት ከሆነው መሬት ገረጋንቲ በማምረት የማገኘው የወደፊት ጥቅም ተቋርጦብኛል በማለት ለመክሰስ ህጋዊ መሰረት እንደሌለው ተከሳሽ ወስዷል ለተባለው ገረጋንቲ በሐላፊነት ሊጠየቅ የማይችል መሆኑን በማንሣት ተከራክሯል ክርክሩን በመጀመሪያ ያየው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ተከሳሹ የከሳሽን አስር ሺህ አራት መቶ ኪዩብ ሜትር ገረጋንቲ የተጠቀመ ለመሆኑ በማስረጃ ተረጋግጧል በማለት የመንገድ ስራ ድርጅቱና አመልካች የገረጋንቲው ጠቅላላ ዋጋ ብር ሥስት መቶ ስልሣ ሺ ብር እንዲከፍሉ ወስኗል አመልካች ይግባኝ አቅርበው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ የከፍተኛውን ፍርድ ቤት ውሣኔ በማሻሻል አመልካች ከመንገድ ሥራ ድርጅቱ ጋር በጋራ ለተጣራው ብር አንድ መቶ ሐምሳ ሺ ብር ይክፈሉ በማለት ወስኗል አመልካች ጉዳዩን አይቶ የመወሰን ስልጣን የፍርድ ቤቶች አይደለም መሬቱንም ለመንገድ ስራ ድርጅቱ የሰጠነው በአዋጅ ቁጥር ድንጋጌ መሰረት ሆኖ እያለና መሬት የመንግስት መሆኑ እየታወቀ በህገ መንግስቱ አንቀጽ እና በፍታብሔር ሕግ ቁጥር የተደነገጉት ድንጋጌዎች ታልፈው የተሰጠ ውሣኔ በመሆኑ በሰበር ሊታይ ይገባዋል የሚል አቤቱታ ያቀረቡ ሲሆን ተጠሪው በበኩሉ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን አይቶ የመወሰን ስልጣን አለው የእኔ ክስ በገንዘቤና በድካሜ ያመረትኩትን አስር ሺህ ስምንት መቶ ሀምሳ ኪዩብ ገረጋንቲ የአመልካች ወኪል አላግባብ ወስዶ የተጠቀመበት በመሆኑ ዋጋውን ይክፈለኝ የሚል በመሆኑ በሰበር አቤቱታው አመልካች የጠቀሰው የህገ መንግስቱ ድንጋጌም ሆነ የፍታብሔር ህግ ድንጋጌች ከተያዘው ጭብጥ ጋር ግኑኝነት የላቸውም በማለት መልስ ሰጥቷል አመልካች መሬቱን በሚመለከት ካልሆነ በቀር የመንገድ ሥራ ድርጅቱ አላግባብ ወስዶ ጥቅም ላይ አውሎታል ለሚለው ገረጋንቲ ተጠያቂና ሐላፈ የምንሆንበት የህግ መሰረት የለም በማለት የመልስ መልስ አቅርቧል በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል የተሰጠው ውሣኔና ግራ ቀኙ በሰበር ያቀረቡት ክርክር ይዘት ከላይ በአጭሩ የተገለፀ ሲሆን እኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመረነው አመልካች የሶስተኛ ወገን ተከሳሽነት ጣልቃ ገብ ሆኖ በተከራከረበት ጉዳይ ፍርድ ቤቱ ለወሰነው የገንዘብ መጠን በአንድነትና በነጠላ ሐላፊ ነው ተብሎ የተሰጠው ውሣኔ ህጋዊ መሰረት አለው ወይስ የለውም የሚለውን ጭብጥ ማየት አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል ከከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሣኔ ለመረዳት እንደሚቻለው ተጠሪው በመጀመሪያ ያቀረቡት ክስ ሁለት የክስ ምክንያቶች ያሉት ነው የመጀመሪያው በሥር ተከሳሽ የነበረው ድራጋዶስ የመንገድ ሥራ ድርጅት አስር ሺህ ስምንት መቶ ፃምሳ ኪዩብ ገራጋንቲ አምርቼ አስቀምእጳ እያለ ከእኔ ፈቃድ ውጭ አላግባብ ስለተጠቀመበት ዋጋውን እንዲከፍለኝ የሚል ሲሆን ሁለተኛው ተከሳሽ ስልጣን ካለው ከኦሮሚያ የማዕድንና ኢነርጅ ቢሮ ፈቃድ አውጥቼ በአጄ አድርጌ ገረጋንቲ እያመረትኩ ከምጠቀምበት ስፍራ በመግባት የምርት ሥራዬን ስላስተጓጎለ ከቦታው አገኝ የነበረው የወደፊት ጥቅም ታስቦ ካሣ ሊከፍለኝ ይገባል የሚል ነው በሥር ተከሳሽ የሆነው የድራጋዶስ የመንገድ ሥራ ድርጅት አመልካችን በሶስተኛ ወገን ተከሳሸነት በክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ የጠየቀው ተጠሪው በሁለተኛ ደረጃ ላቀረበው ክስ ነው የመንገድ ሥራ ድርጅቱ ቦታውን ገረጋንቲ እያመረትኩ እንድጠቀምበት ከማናቸውም ሰው የይገባኛል ጥያቄ ነፃ መሆኑን አረጋግጠው ያስረከቡኝ የወሊሶ ከተማ አስተዳደርና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በመሆናቸው ከየቦታው አላግባብ በመግባት የወደፊት ገቢዬን አሳጥቶኛል የሚለውን የከሳሸ ክስ አስመልክቶ እነዚህ አካላት በሶስተኛ ወገን ተከሳሽነት እንዲጠሩ አመልክቷል ከዚህ አንፃር ስንመለከተው አመልካቹ ለተከሳሹ ቦታውን ያስረከበ መሆኑን አልካደም አመልካች ቦታውን ለመንገድ ሥራ ድርጅት ያስረከበው በአዋጅ ቁጥር መሰረት መሆኑን በመጥቀስ ተክራክሯል ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ ያየው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ተጠሪው በቦታው ላይ ገረጋንቲ እያመረትኩ አገኝ የነበረው የወደፊት ጥቅም ስለተቋረጠ ተከሳሽ ካሣ ሊከፍለኝ ይገባል በማለት ያቀረበውን ጥያቄ በማለፍ ተጠሪው ተከሳሽ አላግባብ ወስዶ ተጠቅሞበታል ያለውንና በማስረጃ ተረጋግጧል ብሎ ፍርድ ቤቱ ያመነበትን አስር ሺ አራት መቶ ኪዩብ ሜትር ጠቅላላ ዋጋ እንዲከፍል ወስኗል በመሆኑም የሶስተኛ ወገን ጣልቃገብ ተከሳሽ ሐላፊነት የሚመነጨው ከተከሳሹ ሐላፊነት በመሆኑና በዚህ ጉዳይ ተከሳሽ አላግባብ ቦታውን በመያዝ የከሳሽን የወደፊት ጥቅም በማስቀረትህ ካሣ ትከፍላለህ ተብሎ ያልተወሰነበት በመሆኑ አመልካች በሐላፊነት የሚጠየቅበት ህጋዊ መሰረት የለም ሁለተኛው የተጠሪው የክስ ምክንያት ድራጋዶስ የመንገድ ሥራ ድርጅት አላግባብ እኔ ያመረትኩትን ገረጋንቲ ተጠቅሟልና ዋጋውን ይክፈለኝ የሚለው ነው በዚህ ጉዳይ በሥር ፍርድ ቤት ተከሳሽ የሆነው የመንገድ ሥራ ድርጅት አመልካች በሶስተኛ ወገን ተከሳሽነት ጣልቃ ገብ እንዲሆን ያልጠየቀ ከመሆኑም በላይ የመንገድ ሥራ ድርጅቱ አራሱን የቻለ የህግ ሰውነት ያለው ሥራውን በሚያከናውንበት ሰአት አላግባብ በሰው ሐብትና ንብረት ላይ ጉዳት ቢያደርስ ተጠያቂ የሚሆነው የመንገድ ሥራ ድርጅቱ እንጂ ኮንትራክት ሰጭ የሆነው አመልካች ባለመሆኑ የከፍተኛው ፍርድ ቤትም ሆነ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመልካች ተከሳሹ አላግባብ ለተጠቀመበት ገረጋንቲ በሶስተኛ ወገን ተከሳሽነት ከተከሳሹ ጋር የአንድነትና የነጠላ ሐላፊነት አለበት በማለት የሰጡት ውሣኔ የፍታብሔር ሥነ ሥርአት ሕግ ቁጥር ንኡስ አንቀጽ ጋር የሚጣጣም ሆኖ አላገኘውም የሥር ፍርድ ቤቶች በመጀመሪያ ተከሳሽ የሆነው የመንገድ ሥራ ድርጅት አመልካቹ እንዲያስረዳለትና በሐላፊነት እንዲጠየቅለት ባልጠየቀበት ጉዳይ እንደዚሁም በተከሳሽ በኩል ጥፋት እንኳን ቢኖር አመልካቹ በሶስተኛ ወገን ተከሳሽነት ቀርቦ ለጥፋቱ ተጠያቂ የሚሆንበት ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ግዴታ መኖሩን ሣያረጋግጡና የፍታፃብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ድንጋጌዎችን በመተላለፍ መሰረታዊ የህግ ስህተት ፈጽመዋል በማለት ፍርድ ሰጥተናል ውሣኔ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የደቡብ ምአራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል ይፃፍ አመልካች ለተጠሪው ብር አንድ መቶ ፃምሳ ሺ ብር የመክፈል ሐላፊነት የለበትም ለሚመለከተው ይፃፍ ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኛቸው የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል ይህ ፍርድ መጋቢት ቀን ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ግንቦት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ መድህን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ዓሊ ሱልጣን አባተማም አመልካች አቶ ዓብዱልነጢፍ ሙሔ ከጠበቃው ጋር ቀርቧል ተጠሪ ትፅግሥት በርዛ ወኪል ቀረበ ደምስስ ተማም ከጠበቃው ጋር ቀርቧል መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበው ክርክር የተነሣው በደብብሕክመከጉራጌ ዞን የወልቂጤ አካባቢ ከፍተኛ ፍቤት ሲሆን ግራ ቀኙ የንግድ መደብርን በተመለከተ ሲከራከሩ ቁቀይተው ፍቤቱ አመልካቹን ረቺ የሚያደርግ ውሣኔ ከሰጠ በኋላ ተጠሪዎች የፍብሥሥሕቁ ን መሠረት አድርገው ዳኝነት እንደገና እንዲታይ አቤቱታ በማቅረባቸው መዝገቡ ዳግመኛ ተንቀሣቅሶ ፍቤቱ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ለአመልካቹ መጥሪያ በተጠሪዎችና በቀበሌ በኩል ልኮለት ተጠሪዎቹ በመሐላ ቃል አስደግፈው አመልካቹ መጥሪያ ደርሶት ደረሰኝ አልሰጥም ብሏል በሚል በሌለበት ጉዳዩ እንዲታይ ባቀረቡት አቤቱታና የጎምሽ ቀበሌ ገማጽቤት አመልካቹ መጥሪያው ደርሶት ለመቀበሉ ደረሰኝ ለመሰጠት ፈቃደኛ አልሆነም ሲል የፃፈውን ደብዳቤ በመመርኮዝ ጉዳዩን አመልካቹ በሌለበት መርምሮ ቀደም ሲል የሰጠውን ውሣኔ በመሻር ተጠሪዎቹን ረቺ ያደረገ ውሣኔ በታህሣሥ ዐ ቀን ዓም ሰጥቷል ከዚህ በኋላ አመልካቹ በወልቂጤ አካባቢ ከፍቤት መጋቢት ቀን ዓም የተፃፈ አቤቱታ ይዞ በመቅረብ በፍቤቱ ቀርቤ ያልተከራከርኩት መጥሪያ ሥላልደረሰኝ በመሆኑና ይህም በቂ ምክንያት በመሆኑ የሰጠው ውሣኔ ተነስቶ በጉዳዩ ላይ መልስ ሰጥቼበት ይወሰን ሲል ፍቤቱን ጠይቋል የወልቂጤ አካባቢ ከፍቤትም የአመልካቹን አቤቱታ መርምሮ ሚያዝያ ቀን ዓም በሰጠው ትአዛዝ የተጠሪዎቹን በመሐላ ቃል ተደግፎ የቀረበ አቤቱታና የቀበሌውን ደብዳቤ በማውሣት መጥሪያ አልደረሰኝም ተብሎ የቀረበው አቤቱታ የፍብሥሥሕቁ ድንጋጌ መንፈስ ባሟላ መልኩ የቀረበ ባለመሆኑ አቤቱታው ተቀባይነት የለውም ሲል መዝገቡን ዘግቶታል በዚህ ትአዛዝ ቅር የተሠኙት አመልካች ቅሬታቸውን በየደረጃው ላሉ ፍቤቶች ቢያቀርቡም የወልቂጤ አካባቢ ከፍቤት የሰጠው ትእዛዝ እስከ ክልሉ ጠፍቤት ሠበር ችሉት ድረስ ባሉት ፍቤቶች ፀንቷል የጉዳዩ አመጣጥ ከላይ እንደተዘረዘረው ሲሆን ይህ መዝገብ ለዚህ ለፌጠፍቤት ሠበር ችሎት ሊቀርብ የቻለውም አመልካች ጥር ቀን ዐዐዐ ዓም በተፃፈ የሠበር ማመልከቻ የቀበሌ ገማህበሩ በቁዐ በሚያዝያ ቀን ዓም በተፃፈ ደብዳቤ የፍቤት መጥሪያ ለአሁን አመልካች አንዳልሰጠኝ አያረጋገጠ እና መጥሪያውን ተቀብዬ አልፈርምም ማለቴ በምስክር ሣይረጋገጥ የስር ፍቤቶች መጥሪያ ደርሶት ለመከራከር ፈቃደኛ አልሆነም በሚል ውሣኔው ተነስቶ መከራከሪያዬን እንዳላቀርብ መከልከላቸው መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ሲሉ አቤት በማለታቸው ነው ይህም ችሎት የአመልካቹን አቤቱታ ተመልክቶየስር ፍቤቶች አመልካች በፍብሥሥሕቁ መሠረት ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸው በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ተጠሪዎቹን አስቀርቦ ግራ ቀኙ የጽሁፍ ክርክራቸውን አካሂደዋል እኛም ጉዳዩን እንደሚከተለው መርምረናል በመሠረቱ የፍብሥሥሕቁ ተከሣሹ መጥሪያ በሚገባ ያልደረሰው መሆኑን ገልፆ ሲያመለክት እና ፍቤቱም ተከሣሹ ቀርቦ መልስ ያልሰጠው በበቂ ምክንያት መሆኑን የተረዳው ሲሆን ትእዛዙን ወይም ብይኑን በማንሣት ክርክሩ እንደገና እንዲሰማ እንደሚያደርግ ይደነግጋል በሌላ በኩል ደግሞ ማንኛውም ግለሰብ ለቀረበበት ክስ መልስ የመስጠት መብት እንዳለው ይታወቃል ይህ ከሆነ ደግሞ አንድ ፍቤት የአንደኛውን ተከራካሪ መከራከሪያ ላለመስማት በተቻለው መጠን ይኸው ተከራካሪ በቀነ ቀጠሮው ያልቀረበው በቂ ባልሆነ ምክንያት መሆኑን የቀረቡለትን ማስረጃዎች በሚገባ መርምሮ ማረጋገጥ እንደሚኖርበት መገንዘብ አያዳግትም በተያዘው ጉዳይ የሥር ፍቤት አመልካቹ በፍብሥሥሕቁ መሠረት መጥሪያ እንዳልደረሰው ገልፆ አቤቱታ ሲያቀርብም ቀድሞ ከተጠሪዎቹ በቀረበለት በመሐላ ቃል የተደገፈ ማመልከቻ ላይ አመልካቹ መጥሪያ ተቀብሎ ደረሰኝ አልሰጥም ሲል አይተዋል ተብለው የቀረቡትን ምስክሮችም ሆነ መጥሪያው በቀበሌው በኩል ሲሰጥ የነበሩት ምስክሮች እንዲሰሙ አላደረገም እንደውም ከዚህ በኋላ ቀደም ሲል የጎምሽ ቀበሌ ገማአስጽቤት የላከውን ደብዳቤ ፃፉ የተባሉት የቀበሌው ሠራተኛ አራሣቸው በሚያዝያ ቀን ዓም በተፃፈ ሌላ ደብዳቤ ክስም ሆነ መጥሪያ ደርሶን የሰጠነው ነገር የለም ሲሉ በቀበሌው ስም የሰጡት ማረጋገጫ መኖሩን ለመገንዘብ ተችሏል ይህ በሆነበት ሁኔታ ደግሞ አመልካቹ መጥሪያ ደርሶት ያለበቂ ምክንያት ስላለመቅረቡ ተረጋግጧል ለማለት አይቻልም ከዚህ ይልቅ ቀበሌው ሚያዝያ ቀን ዓም የዛፈው ደብዳቤ የሚያረጋግጠው አመልካቹ ቀርቦ ያልተከራከረው መጥሪያው ሣይደርሰው መሆኑን ነው። የሚሉት በመሆናቸው እነዚህን ጭብጦች በመያዝ አቤቱታውን መርምረናል የመጀመሪያውን ጭብጥ በተመለከተም ኛ እና ኛ ተጠሪዎች የኛ ተጠሪ ወኪል ስለመሆናቸው ግራ ቀኙን አላከራከረም አንድ ተወካይ በተሰጠው የውክልና ሥልጣን ሥር ሆኖ የሚያከናውናቸው ማናቸውም ተግባራት የአስገዳጅነት ውጤት የሚኖራቸው በተወካዩ ላይ ሳይሆን በወካዩ ላይ እንደሆነ በውክልና ሕግጋት ሥር ከተደነገገው ከፍብሕቁ እና ተከታታዮቹ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል ኛ እና ኛ ተጠሪዎች ክስ የቀረበበትን ገንዘብ ከአመልካች ሲቀበሉ የነበሩት ከኛ ተጠሪ በተሰጣቸው የውክልና ሥልጣን ስለመሆኑም በአመልካች ታምኗል ይህም ክፍያው እንደተፈጸመ የሚቆጠር ለተወካዮቹ ሳይሆን ለወካዩ ለኛ ተጠሪ ነው ስለሆነም አመልካች ኛ እና ኛ ተጠሪዎች የኛ ተጠሪ ወኪል መሆናቸውን እየተገነዘበ ያለአግባብ ተከፍሏል የሚለው ገንዘብ እንዲመለስለት ስለሆነ የፌመደፍቤት ኛ እና ኛ ተጠሪዎችን የከሰሰው ያለአግባብ የቀረበውን ክስ መሰረዙና የፌከፍቤትም ይህንኑ ማጽናቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የሌለበት በመሆኑ አመልካች በዚህ ረገድ ያቀረበውን አቤቱታ አልተቀበልነውም አመልካች ያቀረበው የክፍያ ጥያቄን በተመለከተም ኛ ተጠሪ የቤቁጥር የሆነውን ቤት በለውጥ ያገኙት መሆኑን የሚያረጋግጥ ውል በማቅረብ ቤቱን አመልካች እንዲያስተዳድርላቸውና በኪራይ ከሚሰበስበውም ገንዘብ ማካካሻው ለኛ እና ኛ ተጠሪዎች እንዲከፍልላቸውና ውክልና ቢሰጡም ይሄው ቤት የኛ ተጠሪ ሳይሆን የሕብረት አምባ የመኖሪያ ቤት ኀሥማህበር እንደሆነና አመልካችም ቤቱን ለማኀበሩ እንዳስረከበ ቤቱም በባንክ ብድር ተሰርቶ የነበረ በመሆኑ ለባንክ መከፈል የነበረበትን ዕዳ አመልካች ከቤቱ የሰበሰበውን የኪራይ ገቢ በማኀበሩ ስም ለባንክ ስለመክፈሉ የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን በፌመደፍቤት ክርክር ሲያደርግ አመልካች አቅርቧል የቤት ቁጥር የሆነው ቤት በፍርድ ጭምር የኛ ተጠሪ አለመሆኑ ከተረጋገጠ የአራሳቸው ያልሆነን ቤት አመልካች በአደራ እንዲያስተዳድርላቸው በማስረከብ የኪራይ ማካካሻ በወኪሎቻቸው አማካይነት ያለአግባብ ሲቀበሉ እንደነበር መገንዘብ አያዳግትም ይህም አመልካች መክፈል የማይገባውን ክፍያ ሲፈጽም እንደነበር የሚያሳይ ሲሆን ሊከፍል የማይገባውን የከፈለ ደግሞ እንዲመለስለት መጠየቅ እንደሚችል በፍብሕቁ ላይ ተመልክቷል ሰለሆነም የፌመደፍቤትና የፌከፍቤት አመልካች ገንዘቡ ይመለስልኝ በማለት መጠየቅ አይችልም በማለት የሰጡት ውሣኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ስላለበት በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯራል ውሳኔ አመልካች ክስ ያቀረበበት ብር ሃያ ሺህ አምስት መቶ አርባ ሁለት ከያ በፌመደፍቤት ክስ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ተከፍሎ እአስካለቀ ድረስ ከሚታሰብ ጠኝ በመቶ ወለድ ጋር ኛ ተጠሪ ለአመልካች እንዲከፍሉ ተወስኗል ውሳኔው የተሻረ መሆኑ እንዲታወቅ ለሥር ፍቤቶች ይተላለፍ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ መስፍን ዕቁበዮናስ አሰግድ ጋሻው ተሻገር ገሥላሴ ብርሃኑ አመነው አመልካች የጅማ ከተማ የአካባቢ አስተዳደር ቤት ተወካይ ቲጃኔ አባቡልጉ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ሸዋረገድ አባድር ቀረቡ መዝገቡን መርምረን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታ የቀረበው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ ላይ ነው የአሁን ተጠሪ በወረዳው ፍቤት ከሳሽ አመልካች ደግሞ ተከሣሽ በመሆን ተከራክረዋል ተጠሪ የተፈጠረው ሁከት ይወገድልኝ በማለት በጠየቀው ዳኝነት መነሻ አድርጎ ያቀረበው ምክንያት እናቴ በካርታ ቁጥር ካሬ ሜትር በሆነው ቦታ ላይ የቤት ቁጥር የሆነ ቤት አላቸው የእናቴ ወራሽ መሆኔን አረጋግጫለሁ ሆኖም ተከሣሽ የአሁን አመልካች ለሌላ ግለሰብ ስለሸጠብኝ ሁከት ተፈጥሮብኛል የሚለውን ነው አመልካችም ይህ በካርታ ቁጥር የተመዘገበው ካርታ የተሰጠው በ ዓም ነው የከተማ ቦታ እና ትርፍ ቤትን ለመንግሥት ባደረገው አዋጅ ቁጥር መሠረት ይህ ክስ የቀረበበት ንብረት የተወረሰ ነው የተፈጠረ ሁከት የለም በማለት ተከራክራል የሥር የወረዳ ፍቤትም በውርስ አግኝቼ የእራሴ ሆኗል በማለት ከሳሽ ይከራከር እንጂ ይህ ስለመሆኑ ማስረጃ አላቀረበም ንብረቱ በአዋጅ ቁጥር የተወረሰ ስለሆነ የተፈጠረ ሁከት የለም በማለት ወስኗል ይህም ውሣኔ በከፍተኛው ፍቤት ፀንቷል የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ግራ ቀኙን በይግባኝ ካከራከረ በኋላ የአሁን አመልካች ተወርሷል ይበል እንጂ ስለመወረሱ ማስረጃ አላቀረበም ንብረቱ በከሳሽ በአሁን ተጠሪ ስም መሆኑን አልካደም የወራሽነት ማስረጃ ቀርቦ እያለ የሥር ፍቤት መልስ ሰጭ የባለቤትነት ማስረጃ የለውም ማለቱ ተገቢ አይደለም ስለሆነም ካርታ እና ፕላን ያለውን ንብረት በሊዝ መሸጡ ተገቢ አይደለም በማለት በሥር ፍቤቶች የተሰጠውን ውሣኔ ሽሮታል የሰበር አቤቱታ የቀረበለት የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ይኸው የጠቅላይ ፍቤት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለበትም በማለት አመልካችን አሰናብቷል የሰበር አቤቱታ የቀረበውም የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት እና ሰበር ሰሚ ችሎት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ዳኝነት መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ ሊታረምልን ይገባል በማለት ነው ግራ ቀኙም በዚህ ሰበር ችሎት የቃል ክርክር አድርገዋል አኛም ጉዳዩን ተመልክተናል እንደተመለከትነውም ተጠሪ ሁከት ተፈጠረበት በተባለው ንብረት መብት ወይም ጥቅም ያለው መሆኑን ለማሣየት መሠረት ያደረገው ወራሽ ነኝ በማለት ነው ንብረቱም የአውራሽ የእናቴ ነው ለማለት ያበቃው በካርታ ቁጥር የተመዘገበው ካርታ ነው ይሁን እንጂ ይህ ካርታ በ ዓም የተሰጠ ነው በማለት አመልካች ላቀረበው ክርክር ማስተባበያ አላቀረበበትም ክዶም አልተከራከረም አመልካች ይህ የንብረቱ የባለቤትነት ማረጋገጫ የተሰጠው አዋጅ ቁጥር ከመውጣቱ በፊት ሲሆን ይህ አዋጅ ከወጣ በኋላ ግን ተወርሷል በማለት ይህንኑ ሕግ መሠረት አድርጎ ለቀረበው ክርክር ተጠሪ አልተወረሰም በማለት ተከራክሯል የቤቱ ካርታ የተሰጠበትን ጊዜ እና አዋጁ የወጣበትን ጊዜ እንደ መነሻ ፍሬ ነገር በመያዝ ንብረቱ የተወረሰ መሆኑን የግምት መነሻ በመስጠት አመልካች ያስረዳ ሲሆን ተጠሪ በበኩሉ ይህ ንብረት ያልተወረሰ መሆኑን በሚያመለክት ሁኔታ የፍሬ ነገር ክርክርም ሆነ ማስረጃ በማቅረብ አላረጋገጠም ይልቁንም በቃል በተደረገው ክርክር አዋጅ ቁጥር ሲወጣ እኔ እስር ቤት ነበርኩኝ የደርግ መንግሥት በአምባገነንነት በቀበሌ አማካኝነት ለሌሎች ሰዎች በኪራይ ሰጠብኝ የሚለውን መግለፁ ንብረቱ በእርግጥም የተወረሰ መሆኑን የሚያመለክት ነው ስለሆነም ንብረቱ ተወርሷል ወይስ አልተወረሰም የሚለውን ነጥብ በሚመለከት ማን ክርክሩን መጀመርና ማስረዳት እንዳለበት የሚያመለክተውን ድንጋጌ ባለመከተል እና ይህም ሥርዓት ቢዛነፍም እንኳ ከግራ ቀኙ ማን የተሻለ ማስረጃ አቅርቧል የሚለውን ነጥብ የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ከግምት ውስጥ ሳያስገባ የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ አመልካች ክርክር ባስነሳው ንብረት ላይ የፈፀመው ሁከት የለም ብለናል የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በመቁ በሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ እና የሰበር ሰሚው ችሉት በሰበር መቁ ዐ በህዳር ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ በፍብሥሥቁ መሠረት ተሽሯል የወረዳው ፍቤት በመቁ በጥቅምት ቀን ዓም እንዲሁም የከፍተኛው ፍቤት በመቁ ዐ በታህሣሥ ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔ ፀንቷል መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሠመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ አሠግድ ጋሻው ሒሩት መለሰ ተሻግር ገሥላሴ ታፈሰ ይርጋ አመልካችፁ የጅጀጋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤክርስትያን አልቀረበም ተጠሪ እነ አዳነች መንግስቱ ሰዎች የቀረበ የለም ፍርድ በዚህ መዝገብ የተያዘው ጉዳይ የህዝብ የሆኑ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ባለቤትነት የሚረጋገጥበትን መንገድ የሚመለከት ነው የአሁንየአሁኗ አመልካች በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረበችው ክስ ለክርክር ምክንያት የሆነውና በ ቀበሌ ክልል ውስጥ የሚገኛው ክፍል ቤት ቀድሞ የቤክርስትያኗ የነበረና ከአዋጅ ቁ በኋላ ቀበሌው ቤቱን የያዘ ቢሆንም ቤቱ አንዲመለስላት ስለተወሠነ ተጠሪዎቹ ቤቱን ለቀው እንዲያስረክቡ ጠይቃለች ተጠሪዎች በሠጡት መልስ ቤክርስትያኗ የቤቱ ባለቤት ለመሆኗ ያቀረበችው የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር ባለመኖሩ ክሱ ውድቅ እንዲሆን ጠይቀዋል ጉዳዩን ያየው ፍቤትም ይህንኑ ክርክር ተቀብሉ አመልካች ባለቤት ለመሆኗ አላረጋገጠችም በማለት ክሷን ውድቅ አድርጎታል ይግባኝ የቀረበለት የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤትም ይህንኑ ውሣኔ አፅንቶታል የአሁነ የሰበር አቤቱታ የቀረበው የህዝብ የሆነ የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለቤትነት የሚረጋገጠው እንዴት ነው የሚለውን ለመመርመር አቤቱታው ለሠበር ችሎት ቀርቦ ለተጠሪዎች መጥሪያ ቢላክም ባለመቅረባቸው ጉዳዩ በሌሉበት አንዲታይ ታዛህል ፍቤቱም መዝገቡን መርምሯል ከፍ ሲል እንደተገለፀው የአመልካች ክስ ውድቅ የተደረገው እንዲመለስላት ለጠየቀችው ቤት ባለቤትንቷን የሚያርጋግጥ የባለቤትነት ምስክር ወረቀት አላቀረበችም በሚል ነው የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሃብትነትን በማረጋገጥ በተገቢው አስተዳደር ክፍል ለአንድ ሰው የተሠጠው የባለፃብትነት የምስክር ወረቀት ይህ ሰው የዚሁ የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለህዛብት እንደሆነ እንደሚያስቆጥረው በፍህቁ የተመለከተ በመሆኑ አንድ ሰው የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለቤት መሆኑን ለማረጋገጥ ይህንኑ ምስክር ወረቀት እንዲያቀርብ ይጠበቅበታል ነገር ግን ይህ የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለሀብትነት ማረጋገጫ መንገድ የግል ሃብት የሆነውን ንብረት የሚመለከት ነው የግል ሀብት ያልሆነው እና ለህዝብ የሚያገለግል የማይንቀሣቀስ ንብረትን በተመለከተ ህጉ የተለየ ሁኔታን አስቀምጧል ለህዝብ የሚያገለግል የማይንቀሣቀስ ንብረት እሱን የሚመለከት ግዙፍ መብቶች ከሌሉበት በቀር በማይንቀሳቀስ ንብረት መዝገብ ውስጥ መመዝገብ እንደማያስፈልገው የፍህቁ ያመለክታል በመሆኑም ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ባለሃብትነት ለማረጋገጥ የግድ መዝገብ የገባ የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት እንዲቀርብ ህጉ አያዝም በሌላ አነጋገር እነዚህን ንብረቶችን በተመለከተ ባለሀብትነት በሌላ ሁኔታ ወይም ማስረጃ ሊረጋገጥ ይችላል ማለት ነው ወደ ተያዘው ጉዳይ ስናመራ ቤቶቹ የቤተክርስትያኗ በመሆናቸው ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ እንጂ የግል ዛብት ስላልሆኑ የንብረቶቹ ባለሃብትነት የግድ በባለቤትነት የምስክር ወረቀት መረጋገጥ የለበትም በመሆኑም በሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ታይቶ ሊወሠን ይችላል በዚህ ጉዳይም ቢሆን መዝገቡ እንደሚያስረዳው ቀበሌው ራሱ በሠጠው መልስ በማዕከላዊ መንግስት ቤቱ ለአመልካች እንዲመለስ መታዘዙንና የጅጅጋ ማዘጋጃ ቤትም ቤቱን ለአመልካች አንዲያስረክብ ያዘዘ መሆኑን ገልዷል ከዚህ በተጨማሪ ይህ ችሎት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የተለያዩ የመንግስት አካላት ከፃፉት ደብዳቤ ቤቱ ለአመልካች የተመለሠ መሆኑን ተገንዝቧል ከላይ እንደተገለፀው ቤቱ ለህዝብ አገልግሎት የሚውል እንጂ የግል ዛብት ባለመሆኑ ቤክርስትያኗ ባለቤትነትን ለማረጋገጥ የባለቤትነት የምስክር ወረቀት አንድታቀርብ ስለማትገደድ የሥር ፍቤቶች የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት አልቀረበም በማለት የሠጡት ውሣኔ የህግ ስህተት አለበት ውሣኔ የጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በሰኔ ዐ ቀን ዓም የሠጠው ውሣኔና የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በመቁ በጥቅምት ቀን ዓም የሠጠው ውሣኔ ተሽራል ክርክር የቀረበበትን ክፍል ቤት ተጠሪዎች ለአመልካች ያስረክቡ የጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በዚህ ውሣኔ መሠረት እንዲያስፈፅም የዚህ ትዕዛዝ ግልባጭ ይድረሠው መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞችኹ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ተገኔ ጌታነህ ተሻገር ገሥላሴ ብርፃነ አመነው አመልካች የአአከተማ አስተዳደር ሥራና ከተማ ልማት ቢሮ ተተኪ የመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን አልቀረቡም ተጠሪ አቶ ነጋሽ ዱባለ ጠበቃ አቶ መኮንን ኪዳኔ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ መዝገቡ ለሰበር ችሎት ሊቀርብ የቻለው የፌከፍቤት በይግባኝ መቁ ላይ ታህሳስ ቀን ዓም በሰጠው ፍርድ የፌመደፍቤት የሰጠውን ውሳኔ በማፅናቱ የሥር ፍቤቶች ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት አለበት እና እንዲታረም ሲል አመልካች ጥር ቀን ዓም የተፃፈ አቤቱታ በማቅረቡ ነው በአቤቱታው መሠረት ሰበር ችሉት መዝገቡን ከመረመረ በኃላ የተሰረዘው የቤት ባለቤትነት ደብተር እና ካርታ ተፈፃሚነት እንዲቀጥል ሲል የሥር ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ አግባብነት ለመመርመር ተጠሪ እንዲቀርብ አዞአዝዞ ግራ ቀኙ ክርክርራቸውን አሰምተዋል የሰበር ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ መዝገቡን ከሥር ፍቤት ክርክርና ውሳኔ አንፃር አግባብነት ካለው ሕግ ጋር አገናዝቦ መርምሯል የጉዳዩ መነሻ በአጭሩ ሲታይ በወረዳ ቀበሌ የሚገኙ በቁጥር እና ቤቶች በካርታ ቁጥር እና በቤት ባለቤትነት ደብተር ቁጥር ማረጋገጫ መሠረት የተጠሪ መሆናቸው ተረጋግጦ በፍመቁ እና በአፈጻጸም መቁ ተጠሪ እንዲረከብ ከተደረገ በኋላ አመልካች እና የመቤቱ የሥራ ሐላፊዎች በሥር ፍቤት ኛ እና ኛ ተከሳሾች ይህንን የባለቤትነት ማረጋገጫ እንዲመክን በማድረጋቸወ ለዚህ ሕገወጥ ተግባራቸው ተጠያቂ እንዲሆኑ እና የሰነዶቹ ትክክለኛነት ተረጋግጦ ካርታ እና ደብተሩ ተዘጋጅቶ ለተጠሪ ለሥር ከሳሽ አንዲሰጥ ይወሰንልኝ ሲል ባቀረበው ክስ የሥር ፍቤት ከአከራከና የግራ ቀኙን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ የአመልካች ድርጊት ሕገወጥ ነው በማለት የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነዶቹ ተፈፃሚነት እንዲቀጥል ሲል ውሳኔ ሰጥቷል ከዚህ ውሳኔ እና ለሰበር ከቀረበው ክርክር አንፃር በመሠረታዊነት ሊታይ የሚገባው ነጥብ የተጠሪ የሥር ከሳሽ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነዶች በአስተዳደር አካል ከተሰረዘ ክስ ለማቅረብ የክስ ምክንያት አለን። ተጠሪዎች ያቀረቡት አቤቱታ የፍቤት ሥልጣን አይደለም በማለት ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር መቁ ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ታረቀኝ ሞላ ቀረበ ተጠሪ ተክለማርያም መኮንን ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለአቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ ተጠሪ ባቀረበው የቤት ይለቀቅልኝ ጥያቄ ላይ የተመሠረተ ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀረመበት የፌመደፍቤት ተጠሪ የከሰሰው አዳነ ገብሩ እና ወሮ ፈትለወርቅ ጌታቸው የተባሉትን ሰዎች ሲሆን አመልካች ክርክሩ ውስጥ የገባው ለክርክሩ መነሻ በሆነው ቤት ላይ የተነሣው ጥያቄ ይመለከተዋል ስለተባለ ጣልቃ እንዲገባ ታዞ ነው ተጠሪው ክስ የመሠረተውም በወረዳ ቀበሌ ክልል የሚገኝ ቁጥር ለ የሆነው ቤት የግል ንብረቴ ሲሆን አዳነ ገብሩ በተባለው ተከሣሽ በውል አከራይቼው ሲጠቀምበት ቆይቶአል በሌላ በኩል ደግሞ ከኔ ፈቃድ ውጪ ለወሮ ፈትለወርቅ ጌታቸው አከራይቶታል ስለዚህ ተከሣሾች ኪራዩን እንዲከፍሉና ቤቱን እንዲያስረክቡኝ ሊወስንልኝ ይገባል በማለት ነው ፍቤቱም ከተከሣሾች እና ከጣልቃ ገቡ የቀረቡትን የመከራከሪያ ነጥቦች ከሰማ በኋላ ኛ ተከሣሽ አና ጣልቃ ገቡ ቤቱን ለከሣሽ ያስረክቡ ከመስከረም ወር ዓም ጀምሮ እስከ ሰኔ ዐ ቀን ዓም ድረስ ያለውን የኪራይ ገንዘብም በአንድነትና በነጠላ ይክፈሉ ሲል ወስኖአል በዚህ ውሣኔ ላይ ከአሁኑ አመልካች ይግባኝ የቀረበለት የፌከፍቤትም ውሣኔው ጉድለት የለበትም በማለት ይግባኙን ሳይቀበለው ቀርቶአል የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚሁ ላይ ነው የሰበር ችሎቱ አመልካች ሚያዝያ ቀን ዓም በፃፈው ማመልከቻ የቀረበውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርቦ ክርክሩን ሰምቶአል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው ተጠሪ ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ቤት የሠራው ባልተፈቀደለት የከተማ ቦታ ላይ ነው እየተባለ ቤቱን ሊረከብ ይገባል የመባሉን አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም በጭብጥነት የተያዘው ነጥብ ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ከሥር ጀምሮ ከተደረገው ክርክር ይዘት መገንዘብ እንደቻልነው ተጠሪ ቤቱን ሠርቻለሁ በሚል ለሌላ ሰው በውል አከራይቶ ከመገኘቱ በቀር በቦታው ላይ ቤት እንዲሠራ አግባብ ካለው ባለስልጣን የተፈቀደለት ወይም በቦታው የመጠቀም መብት ያገኘ መሆኑን ለማስረዳት ያቀረበው ማስረጃ የለም የሥር ፍቤቶችም አቤቱታ የቀረበበትን ውሣኔ የሰጡት ማስረጃ አግኝተናል በማለት ሳይሆን አመልካች ቤቱ ያረፈበት የከተማ ቦታ ለመወረሱ የመንግሥት ንብረት ለመሆኑ ማስረጃ አላቀረበም የሚል ምክንያት በመስጠት እና ቤቱ በሕገ ወጥ መንገድ የተሠራ ነው ከተባለም የሚመለከተውና ሥልጣን ያለው አካል ነው ተገቢውን እርምጃ የሚወስደው የሚል ትችት በማከል ብቻ ነው ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው የከተማ ቦታና ትርፍ ቤትን የመንግሥት ንብረት ለማድረግ የወጣው አዋጅ ቁ ከታወጀ ወዲህ የከተማ ቦታ የመንግሥት ዛብት ሆኖአል ይህ ማለት በግል የሚያዝ የከተማ ቦታ የለም ማለት ነው ግለሰቦች በከተማ ቦታ የመጠቀም የመያዝ መብት የሚኖራቸው አግባብ ባለው የመንግሥት አካል ባለስልጣን ሲሰጣቸው ነው በተያዘው ጉዳይ የምናየው ግን ተጠሪ በቦታው ላይ ይጠቀም ዘንድ ቤቱን እንዲሠራ ሳይፈቀድለት ነው ቤት ሠርቼ አከራየሁ የሚል ክርክር ያቀረበው የከተማ ቤት አሠራርና አጠቃቀምን በተመለከተ በወጣው አዋጅ ቁ በአንቀጽ እንደተደነገገው ከሚመለከተው ባለስልጣን ፈቃድ ሳይኖር የተሠራ የከተማ ቤት ሕጋዊነት አይኖረውም ቤቱ እንዲወረስ ወይም እንዲፈርስ እንደሚደረግም ሕጉ ያመለክታል ከዚህ አንፃር የተጠሪ ክርክር ሲታይ ተቀባይነት ያለው አይደለም አቤቱታ የቀረበበት ውሣኔም እነዚህን ሁኔታዎች አና ሕጉን ያላገናዘበ በመሆኑ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ አቤቱታ የቀረበባቸው የፌመደፍቤት በመቁ ዐ ታህሣሥ ቀን ዓም የሰጠው እና የፌከፍቤት በመቁ ዐ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽረዋል ተጠሪ ያቀረበው የቤት ልረከብ ጥያቄ ተቀባይነት የለውም ብለናል ወጪና ኪሣራ የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ የካቲት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሂሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች አቶ ገእግዚአብሔር ከበደው ቀረቡ ተጠሪ ወት ሠላዊት ወገብርኤል ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ክርክር የተጀመረው በትግራይ ክልል በመቀሌ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪ በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ የሟች እናቴ ወሮ ድንቅነሽ ድምጹ ወራሽ ስሆን በአውራሽ ስም የተመዘገበውንና በመቀሌ ከተማ የሚገኘውን ዐ ክፍል ቤት እኔ በማላውቀው ሁኔታ ተከሣሽ ይዞ በማከራየት ላይ ስለሚገኝ የ ወር የቤት ኪራይ በጠቅላላው ብር ሠላሳ አምስት ሺህ በመክፈል ቤቱን አንዲያስረክበኝ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል ተከሣሽም ቀርበው ለክሱ በሰጡት መልስ ከሳሽ የሟች ወሮ ድንቅነሽ ድምጹ ልጅ መሆኗን እንደማይክዱ ነገር ግን ከሟች ጋር በ ዓም ተጋብተን አብረን ስንኖር ልጆች የወለድን ከመሆኑም በላይ ክስ የቀረበበትንም ቤት አብረን ሠርተናል የሚያከራክረው ቤትና ቦታ ግማሹ የራሴ ሲሆን ግማሹ ደግሞ የሟች ወሮ ድንቅነሽ ድምጹ ስለሆነ ከሣሽ ከሌሎች ወራሾች ጋር በመሆን ድርሻዋን ብትካፈል አልቃወምም ብለው የቤት ኪራይን በተመለከተ ቤቱ በወር ብር ዐዐዐ ሁለት ሺህ ይከራይ እንደነበረ አምነው ነገር ግን ከሰኔ ቀን ዓም እስከ ሕዳር ዓም ድረስ ያለውን ሟች በሕይወት እያለች በጋራ የተጠቀምንበት ሲሆን ቀሪውንም ከከሳሽ ጋር በጋራ ስለተጠቀምንበት ክሱ ያለአግባብ ስለቀረበ ሊሰረዝ ይገባል በማለት ተከራክረዋል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት የግራ ቀኙን ማስረጃ ሰምቶ ክስ ከቀረበበት ቤት መካከል ክፍል ቤት የከሳሽ አናትና ተከሣሽ በ ዓም ከተጋቡ በኋላ በ ዓም የተሰራ መሆኑ ስለተረጋገጠ ግማሹ የተከሳሽ ሆኖ ግማሹ ደግሞ ከሳሽን ጨምሮ ወራሾች እንዲካፈሉት ቀሪው ክፍል ቤት ደግሞ ከመጋባታቸው በፊት መሠራቱ ማስረጃ ስለተረጋገጠ ከሣሽና ሌሎች የሟች ወራሾች እንዲከፋፈሉት በማለት ውሣኔ ሠጥቷል እንደዚሁም ቤቱ ያረፈበትን የቦታ ይዞታ በተመለከተ የቦታው ስፋት በማዘጋጃ ቤት ደንብ መሠረት ለሁለት ለማካፈል የሚቻል ከሆነ ግማሹን ከሳሽና ሌሎች ወራሾች አንዲወሰዱ ቀሪውን ግማሽ ደግሞ ተከሣሽ እንዲወሰዱ የማዘጋጃ ቤት ደንብ ቦታውን ለሁለት ለማካፈል የማይቻል ከሆነም ቤቱና ቦታው ተሸጦ ከላይ በተመለከተው ዓይነት ወራሾችና ተከሣሽ እንዲከፋፈሉ በማለት በአብላጫ ድምጽ ውሣኔ ሠጥቷል የአነስተኛው ድምጽ ደግሞ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት የተሰራበት ቦታ የከሳሽ እናት ወሮ ድንቅነሽ ድምጽ ተከሣሽን ከማግባቸው በፊት የነበራቸው ይዞታ ስለሆነ ተከሳሽ መብት የሚኖራቸው በዚህ ቦታ ላይ ከጋብቻ በኋላ ለተሠራዉ ቤት ግማሹን በተመለከተ ስለሆነ የዚህን ቤት ግምት ይዞ እንዲሄድ ከሚወሰን በስተቀር ከጋብቻ በፊት የከሳሽ እናት ባረጋገጡት ቦታና ቤት ላይ መብት ሊኖረው አይገባም የሚል ነው ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተውም የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ በአብላጫ ድምጽ የተሰጠውን የከፍተኛ ፍቤት ውሣኔ በመሻር የአነስተኛውን ድምጽ አጽንቷል አመልካች በዚሁ ውሣኔ ቅሬታ አድሮባቸው የሰበር አቤቱታ ለክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት ቢያቀርቡም መሠረታዊ የሕግ ስህተት አልተፈጸመም በማለት ችሎቱ አቤቱታውን ሳይቀበለው ቀርቷል ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም የቀረበለትን የሰበር አቤቱታ መርምሮ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤትና የቦታ ይዞታን ክፍፍል አስመልከቶ በትግራይ ክልል ጠፍቤት የተሰጠው ውሣኔ አግባብነት ተጣርቶ ሊወሰን የሚገባው መሆኑን በማመኑ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል በአጠቃላይ የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን የሰበር አቤቱታውም እንደሚከተለው ተመርምሯል ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት የተሰራበትን ቦታ የተጠሪ እናት ወሮ ድንቅነሽ ድምጹ ከአመልካች ጋር ከመጋባታቸው በፊት ይዘውት እንደነበር በዚሁ ቦታም ላይ አመልካችን ከማግባታቸው በፊት ክፍል ቤት ሠርተው እንደነበር ቀሪው ክፍል ቤት ደግሞ ከአመልካች ጋር ከተጋቡ በላ እንደተሰራ በዞኑ ከፍተኛ ፍቤት ክርክር ሲደረግ በማስረጃ ተረጋግጧል በሌላ በኩልም በፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግም ሆነ በአዋጅ ቁጥር በታወጀው የትግራይ ክልል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ መሠረት ከጋብቻ በፊት የነበረ የባልና ሚስት ንብረት የግል ንብረት እንደሚሆን የተመለከተ ቢሆንም የከተማ ቦታን የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት የከተማ ቦታ በግል ባለቤትነት ሊያዝ እንደማይችል ከመደንገጉም በላይ በኢፌዲሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ ዐ ላይ መሬት የመንግሥትና የሕዝብ ንብረት እንደሆነ ስለተደነገገ ግለሰቦች በመሬት ላይ የይዞታ መብት እንጂ የባለቤትነት መብት ሊኖራቸው ስለማይችል የተጠሪ እናት ቤቱ በተሰራበት ቦታ ላይ አመልካችን ከማግባታቸው በፊት የነበራቸው የይዞታ መብትም ቢሆን ከተጠሪ ጋር ከተጋቡ በጊላ በነበራቸው የቦታ ይዞታ ላይ ተጨማሪ ቤት እንዲሰራ በፈቀዱት መሠረት አራት ክፍል ተጨማሪ ቤት በጋራ ስለመስራታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ ጋብቻው በሞት ምክንያት ሲፈርስ አመልካች ከሚደርሳቸው ቤት በተጨማሪ በቦታው ላይ የይዞታ መብትም የሚገባቸው በመሆኑ በዚሁ መሠረትም የዞነኑ ከፍተኛ ፍቤት ቦታውን ወራሾችና አመልካች በማዘጋጃ ቤት ደንብ መሠረት አኩል ለመካፈል የሚችሉ ከሆነ እኩል እንዲካፈሉት አኩል ለማካፈል ካልተቻለም ተሸጦ ገንዘቡን በውሣኔው መሠረት እንዲካፈሉ በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ ሆኖ ሳለ የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ይህንን ውሣኔ በመሻር በጋብቻ ጊዜ የተሰራውን ቤት የግማሹን የዋጋ ግምት አመልካች ሊወስድ ይገባል በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ ካለመሆኑም በላይ የክልሉ ጠፍቤት ሰበር ችሎትም ይህንኑ ስህተት ሳያርም መቅረቱ የሕግ ስህተት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ችሎት በመቁ በግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ዐ በኀዳር ዐ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል የመቀሌ ዞን ማዕከላዊ ፍቤት በመቁ በሐምሌ ቀን ዓም በአብላጫ ድምጽ የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ ስለሆነ በፍብሕግሥሥቁ መሠረት ጸንቷል ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር መቁ ዐ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ አብዱልቃድር መሐመድ አብዱራሂም አህመድ ታፈሰ ይርጋ አመልካች እነ ግሙኤል ውብሸት ቀረቡ ተጠሪ ብዙነህ በላይነህ አልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀረብ የቻለው አመልካቾች ተጠሪ በይዞታችን ላይ የፈጠረው ሁከት ይወገድልን የሚል አቤቱታ ለጆጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርበው ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ ተጠሪ በአመልካቾች ላይ የፈጠረው ሁከት ሊወገድ ይገባል በማለት ውሣኔ ሰጥቶ ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት የከፍተኛ ፍቤቱን ውሣኔ በመሻር ሁከት የለም በማለት ውሣኔ በመስጠቱ አመልካቾች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት ቅሬታ በማቅረባቸው ነው ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀረብ በተሰጠው ትእዛዝ ተጠሪ የአመልካቾች አቤቱታ ደርሷቸው መልስ የሰጡ ሲሆን አመልካቾችም የመልስ መልስ በመስጠት አቤቱታቸውን አጠናክረው ተከራክረዋል የጉዳዩ አመጣጥም ባጭሩ ሲታይ አመልካቾች በጀጆጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረቡት ክስ በጅጅጋ ከተማ ቀበሌ ዐ የሚገኝና የምንኖርበት ቤት በአዋጅ ቁጥር ተወርሶ ቀበሌው የሚያስተዳድረውና ላለፉት ዓመታት በተከራይነት ኖረንበታል ይሁን እንጂ ተከሣሽ ይሄው ቤት የአውራሼ የሟች ወሮ ተዋበች ዘርፉ ነው በማለት እኛ በሌለንበት ይህንኑ ከቀበሌው አስተዳደር በኪራይ የያዝነውን ቤት እየተገለገለበት ሰለሆነ የተፈጠረው ሁከት ይወገድልን በማለት ጠይቀዋል ተጠሪም በበኩሉ በሰጠው መልስ ለክሱ መነሻ ምክንያት የሆነው ቤት ከአክስቱ በውርስ የተላለፈለት ንብረት መሆኑን በመግለጽ አቤቱታው ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክራል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት ለክርክሩ ምክንያት የሆኑት ቤቶች የጅጅጋ ከተማ አስተዳደር መሆናቸውን ከሣሾችም በእነዚሁ ቤቶች በሕጋዊ መንገድ እየኖሩ አንደሆነ ከቀረበው ማስረጃ ማረጋገጥ የተቻለ ስለሆነ በተከሣሽ በኩል የተፈጠረው ሁከት በፍብሕቁጥር መሠረት እንዲወገድ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል ክርክሩን በይግባኝ የተመለከተውም የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ ለክርክሩ ምክንያት የሆኑት ቤቶች በአዋጅ ያልተወረሱ ስለመሆናቸው የሚመለከተው የቀበሌ አስተዳደር ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ይግባኝ ባይ ተጠሪ የቤቱ ባለንብረት የነበሩት ግለሰብ ወራሽ መሆናቸው ባቀረቡት ማስረጃ ስለተረጋገጠ የዞኑ ከፍተኛ ፍቤት በተጠሪ በኩል የተፈጠረው ሁከት ሊወገድ ይገባል በማለት የሰጠው ውሣኔ ከጭብጡ ያፈነገጠ ነው በማለት ሽራል ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም አቤቱታው ለሰበር ቀረቦ መታየት አለበት በማለት ትእዛዝ የሰጠው ለክርከሩ ምክንያት የሆነውን ቤት የቀበሌው አስተዳደር እያከራየ ገቢ ይሰበስብ ነበር ከተባለ በአዋጅ አልተወረሰም በሚል የተጠሪ የውርስ ሀብት ነው የመባሉን አግባብነት ለማጣራት ሲሆን ከዚሁ አኳያም አቤቱታው እንደሚከተለው ተመርምራሯል አመልካቾች በጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በተጠሪ ላይ ክስ የመሠረቱት ከጅጅጋ ከተማ ቀበሌ አስተዳደር በተከራይነት የምንኖርበትን ቤት ተጠሪ ወራሽ ነኝ በማለት ያለአግባብ ይዘው የሚገኙ ስለሆነ የተፈጠረው ሁከት ይወገድልን በማለት ነው ሁከት ይወገድልኝ የሚል አቤቱታ የሚያቀርብ ወገን በንብረቱ ላይ የይዞታ መብት እንዳለውና በእርግጥም የሚያዝበት መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባው ከፍብሕቁዐ ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል በተያዘው ጉዳይ አመልካቾች ሁከት ተፈጥሮብናል የሚሉበትን ቤት በኪራይ ውል መነሻነት ይዘው እንደሚገኙና የይዞታ መብት እንዳላቸው በጀጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ክርክር ሲደረግ በማስረጃ አረጋግጠዋል የአመልካቾች አቤቱታ ሁከት ይወገድልን የሚል ከሆነ ክርክሩ የይዞታ መብትን ቫ ርቪከ የሚመለከት በመሆኑ በጭብጥ ተይዞ ዕልባት ሊሰጠው የሚገባው ነጥብ ሁከት ተፈጥሯል ወይስ አልተፈጠረም የሚለው ነው ይሁንና ተጠሪ በዞኑ ከፍተኛ ፍቤት ያቀረቡት ክርክር ለክሱ ምክንያት የሆነው ቤት በውርስ የተላለፈልኝ የግል ቤቴ ሰለሆነ የአመልካቾች አቤቱታ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት እንጂ ሁከት አልፈጠርኩም በማለት አይደለም ተጠሪ በባለቤትነት ረገድ የሚያነሱት ክርክር ሁከት ተፈጥሯል ወይስ አልተፈጠረም ተብሎ ለሚያዘው ጭብጥ ተገቢነት የሌለውና እራሱን የቻለ ባለቤትነትን የመፋለም ክስ ፔጩፀቪርቫ ርበ በሚመለከተው ላይ አቅርበው ከሚታይ በስተቀር ሁከት እንዲወገድ በቀረበ ክስ የባለቤትነት ክርክር ማንሣት አግባብነት አይኖረውም ስለሆነም የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በተጠሪ በኩል ባለቤትነትን የመፋለም ክስ ባልቀረበበትና አመልካቾች ሁከት ይወገድልን በማለት ባቀረቡት ክስ ተጠሪ የቤቱ ባለቤት ናቸው በማለት ውሣኔ መስጠቱ መሠረታዊ የሕግ ሰህተት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ በየካቲት ቀን ዓም ተጠሪ በአመልካቾች ላይ የፈፀመው ሁከት ይወገድ በማለት የሰጠውን ውሣኔ በማጽናት የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ዐ በኀዳር ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለበት በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽራል ይፃፍ ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማየነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ዐዐ ታህሣሥ ቀን ዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ሕብረት ባንክ አክሲዮን ማኀበር ነፈጅ ንጉሴ ኪዳኔ ተጠሪ አቶ ጀማል መሐመድ አልቀረበም ወሮ ማይሙና ሼህ አብዱልሰመድ አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው አመልካች በተጠሪዎች ላይ የፈጠረው ሁከት ይወገድ በማለት የሥር ፍቤቶች የሰጡትን ውሣኔ በመቃወም ነው የጉዳዩ አመጣጥም ባጭሩ ሲታይ ተጠሪዎች በአመልካች ላይ በአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ባቀረቡት ክስ ከአመልካች ላይ ገንዘብ ስንበደር በካርታ ቁጥር ዐ በተመዘገበና በዐዐ ካሬ ሜትር ክልል ውስጥ የተሠራን መጋዘን ብቻ ለብድሩ አከፋፈል ዋስትና የሰጠን ሲሆን ከዐዐ ካሜትር ውጭ የተሠራና በዋስትና ያልተያዘ ቤት ጨምሮ በአዋጅ ቁጥር ዐ መሠረት አመልካች በሽያጭ ለኛ ወገን በማስተላለፍ ላይ ስለሚገኝ የተፈጠረው ሁከት እንዲወገድ ይወሰንልን በማለት ጠይቀዋል ተከሣሽ የአሁን አመልካች ቀርቦ በሰጠው መልስ በዋስትና የተያዘው ይዞታ የማይነጣጠል መሆኑን ውሉም መኖሪያ ቤትና መጋዘን በሚል አእንዳልተከፋፈለ የተመዘገበውም ይዞታ ዐዐ ካሜትር እንደሆነና የብድር ውሉ ሲፈረም መኖሪያ ቤቱ በጆምር እንደነበርና በኋላ የተሰራ ነው ቢባል እንኳን የመያዣው አካል መሆኑ አንደማይቀር በመግለጽ ክሱ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክራሯል የግራ ቀኙ ክርክር በዚህ መልኩ የቀረበለትም የአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ለክሱ ምክንያት የሆነውና ሁከት ተፈጥሮበታል የተባለው ቤት የብድርና የመያዣ ውሉ ከተፈረመ በላ የተሰራ ስለመሆኑ የተረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ውሉም ሲፈረም ከሳሾች በካርታ ይዞታ ከነበራቸው ዐዐ ካሜትር ቦታ በመጨመር በአሁኑ ጊዜ ይዞታቸው ወደ ዐዐ ካሜ ከፍ ብሎ ቤቱም በተጨማሪ ባገኙት ቦታ ላይ ስለመሠራቱ የተረጋገጠ ስለሆነ በፍብሕቁ ዐ መሠረት ይሄው ቤት የመያዣው አካል ሊሆን ስለማይችል ተከሣሽ መያዣ ያላደረገውን ንብረት ሊሸጥ አይችልም በማለት ውሣኔ ሰጥቷል ተከሣሽ በዚህ ውሣኔ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ያቀረበ ቢሆንም በፍብሕሥሥቁ መሠረት ፍቤቱ ይግባኙን ሳይቀበል ቀርቷል ይህ ሰበር ችሎትም የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ተጠሪዎችን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል ምላሽ ማግኘት የሚገባውም የጉዳዩ ጭብጥ አመልካች በተጠሪዎች ላይ ሁከት ፈጥሯል። ተጠሪዎች የቤቱ ባለሃብት ለመሆናቸው የባለቤትነት የምስክር ወረቀት አላቀረቡም ወይም በቤቱ ላይ በስማቸው ከ ዓመት በላይ ግብር እየከፈልን የቤቱ ባለሃብት ሆነናል በማለት ያቀረቡትም ክርክር የለም በመሆኑም ተጠሪዎች የቤቱ ባለሃብት ናቸው ለማለት የሚያስችል ሁኔታ አላገኘንም በዚህም ምክንያት ተጠሪዎች የቤቱ ባለቤት ስለሆነ የከፈሉት የኪራይ ገንዘብ እንዲመለስላቸው ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የከተማ ነክ ይግባኝ ሠሚ ፍቤት ሠበር ችሎት በመቁ በሐምሌ ዐ ቀን ዓም የከተማ ነክ ይግባኝ ሠሚ ፍቤት በመቁ በታህሣሥ ቀን ዐ ዓም አንዲሁም የአአ ከተማ የመደረጃ ፍቤት በመቁ ግንቦት ዐ ቀን ዓም የሠጡዋቸው ውሣኔዎች ተሽረዋል ተጠሪዎች ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለውም ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሠ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ሂሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ሀሰን ኢብራሂም ተጠሪ ኢብራሂም ይመር ሐሰን መዝገቡን መርምረን ቀጥሎ የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ ያለአግባብ የተያዘብኝ ቤት ይለቀቅልኝ በሚል አመልካች ባቀረበው ክስ መነሻነት የተደረገውን ክርክር የሚመለከት ነው ክሱን ያስተናገደው የደሴ ወረዳ ፍቤት ተጠሪን በማስቀረብ የግራ ቀኝ ወገኖችን ክርክር ሰምቷል በመጨረሻም ከሳሽ የቤቱ ባለሀብት መሆኑን በማስረጃ አረጋግጧል በማለት ተጠሪ ቤቱን እንዲለቅና ለአመልካች እንዲያስረክብ ወስኖአል በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ ውሣኔውን በመቃወም ለደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ በማቅረቡ ክርክሩ በድጋሚ ተሰምቶአል በመቀጠልም ፍቤቱ ተጠሪ በቤቱ ላይ የተሻለ መብት ስላለው ለአመልካች ሊያስረክብ አይገባም በማለት የወሰነ ሲሆን በዚህ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የአማራ ብክመጠፍቤትም ውሣኔው ጉድለት የለበትም ብሎአል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው ይህ የሰበር ችሎትም አመልካች ህዳር ቀን ዐዐ ዓም በፃፈው ማመልከቻ ያቀረበውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርቦ ክርክሩን ሰምቶአል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው ክርክር የተነሳበት ቀደም ሲል ፍቤት በሰጠው ውሣኔ መሠረት በአመልካች ስም ስለመመዝገቡ ማስረጃ ቀርቦአል እየተባለ በቤቱ ሳይ የተሻለ መብት ያለው ተጠሪ ነው የመባሉን አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ይህን ነጥብ ከስር ጀምሮ ከተደረገው ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል በመዝገቡ ከሰፈረው የግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር እና የስር ፍቤቶች ከሰጡአቸው ውሣኔዎች ይዘት መገንዘብ እንደቻልነው ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት በሚመለከተው የአስተዳደር ክፍል ተመዝግቦ የሚሜገኘው በአመልካቹ ስም ነው ወደኋላ ያለውን የቤቱን ታሪክ ስንመለከትም ቀደም ሲል ብርሃኔ አድማሱ ጣይቱ አድማሱ እና አበበ ፋሪስ የተባሉት ሰዎች ንብረት እንደነበረ እነዚህ ሰዎች ከአመልካች ብር አስራ ሁለት ሺህ በመበደራቸው ቤቱን ለ ዓመት በመያዣ ለአመልካች መስጠታቸውን በተባለው ዓመት ውስጥ ገንዘቡን ካልመለሱ አመልካች ቤቱን በስሙ ለማዞር እንዲችል መስማማታቸውን አመልካችም በተባለው ዓመት ውስጥ ገንዘቡ ስላልተመለሰልኝ በውላችን መሠረት ቤቱ በኔ ስም እንዲመዘገብ ይወሰንልኝ በማለት ለፍቤት ክስ አቅርቦ ማስዐወሰኑን በዚህ ረገድ የተሰጠው የፍቤት ውሣኔም በይግባኝ ቀርቦ አለመሻሩን ለመገንዘብ ችለናል ይህ እንግዲህ ከአመልካች አንፃር ያለው ሁኔታ ሲሆን ተጠሪ ደግሞ ቤቱ እኔም ከተባሉት ሰዎች በይዞታ ተሰጥቶኛል በማለት ነው የተከራከረው ክርክሩን በይግባኝ የሰሙት ፍቤቶች በወረዳ ፍቤት የተሰጠውን ውሣኔ በመለወጥ የወሰኑትም ተጠሪ አለኝ ለሚለው የመያዣ ውል ከፍተኛ ግምት በመስጠት እና አመልካች ቤቱን በስሙ ያስመዘገበው ያለአግባብ ነው የሚል ምክንያት በመስጠት እንደሆነ ከውሣኔው ይዘት ለመገንዘብ ችለናል በበኩላችን እንደምናየው ክርክሩ ውስብስብነት የሌለው እጅግ ግልጽ ቀላልም ነው አመልካችም ሆነ ተጠሪ ከቀድሞ የቤቱ ባለቤቶች ጋር የመያዣ ውል ማድረጋቸውን በተመሳሳይ ሁኔታ የገለፁ ቢሆንም አመልካች ግን አንድ እርምጃ ወደፊት በመሄድ የመያዣ ውል ነው ያለውን መሠረት በማድረግ ክስ መስርቶ ቤቱ በሱ ስም እንዲመዘገብ አስወስኖአል ይህ ውሣኔ በማንኛውም ይግባኝ ሰሚ ፍቤት ያልተሻረ ሲሆን አመልካችም በውሣኔው መሠረት በሚመለከተው የአስተዳደር አካል ቤቱን በስሙ አስመዝግቦ የባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ አግኝቶአል ከዚህ እንግዲህ በግልጽ መገንዘብ የሚቻለው በአሁኑ ደረጃ የቤቱ ባለቤት ሊባል የሚችለው አመልካች እንደሆነ ነው በፍብሕግ ቁ የተቀመጠው ድንጋጌ ይመለከቷል ይግባኙን የሰሙት ፍቤቶች ተጠሪ አለኝ የሚለውን የመያዣ ውል በፍብሕግ ቁ በተደነገገው መሠረት የተመዘገበ እና በሕግ የሚታወቅ ስለመሆኑ እንኳን ሳያረጋግጡ በቤቱ ላይ ከአመልካች የተሻለ መብት አለው ወደሚለው መደምደሚያ መድረሳቸው አግባብ አይደለም የመያዣ ውሉ በሕግ የታወቀ ቢሆን እንኳን ተጠሪን በቀጥታ የቤቱ ባለቤት የሚያደርገው አይደለም ከሁሉ በላይ ደግሞ አመልካች ቤቱን በስሙ ያስመዘገበው በፍቤት ባሰጠው ውሣኔ መሠረት በመሆኑና ይህ ውሣኔም በበላይ ፍቤት ያልተሻረ በመሆኑ በአሁኑ ደረጃ የስም ዝውውሩ ትክክል አልነበረም ወደሟለው ነጥብ መግባት የሚቻልበት ምንም የሕግ ምክንያት የለም ሲጠቃለል በሕግ በግልጽ የተረጋገጠ የባለቤትነት መብት ያለው አመልካች ሆኖ ሳለ ከዚህ ውጪ በሆነ ሁኔታ በሕሊና ግምት ላይ በመመስረት ፍርድ መስጠቱ በማንኛውም መለኪያ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም ስለዚህም አቤቱታ የቀረበበት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው ለማለት ችለናል ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት በአማራ ብክመበደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ተሰጥቶ የአማራ ብክመጠፍቤት በፍብይመቁ ጥቅምት ቀን ዓም በሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽሮአል ዙዘ አከራካሪው ቤት የአመልካች ንብረት መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ የደሴ ከተማ ወረዳ ፍቤት በፍብመቁ የካቲት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ፀንቶአል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ ውሣኔው ለስር ፍቤቶች ይተሳላለፍ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሒሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ አመልካች ወሮ ገብርኤላ ሂኮላቶማስ ጠአስቴር አርአያ ቀረቡ ተጠሪ የኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ነፈጅ ቤዛ አስራት ቀረቡ ፍርድ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ክስ የጀመረው በፌከፍተኛ ፍሃቤት ነው የአሁን አመልካች ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ ከአባቴ በውርስ የተላለፈልኝን ቤት ተጠሪው በአደራ ተረክቦ እያስተዳደረ ቢቆይም ቤቱን እንዲያስረክበኝ ብጠይቀው ፈቃደኛ ባለመሆነ ቤቱን እንዲያስረክበኝና ከ ዓም ጀምሮ የሰበሰበውን የኪራይ ገንዘብ እንዲመልስልኝ በማለት ጠይቀዋል ተጠሪም ለክሱ በሰጠው መልስ ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም አመልካች ክሱን ለማቅረብ መብት ወይም ጥቅም የላቸውም ክሱ በይርጋ ቀሪ ይሆናል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርቧል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ አመልካች ቤቱ የአባታቸው የግል ቤት ለመሆኑ የሚያስረዳ በህጉ መሰረት የተሰጠ የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ አላቀረቡም ወይም ቤቱ ከአዋጅ ውጪ የተወረሰ ተብሎ ከሚመለከተው አካል እንዲመለስላቸው የተፈቀደ ማስረጃ አላቀረቡም በመሆኑም ክስ በተመሰረተበት ንብረት ላይ ጥቅም ወይም መብት የላቸውም በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል የሰመቁ በዚህ ውሳኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የፌጠቅላይ ፍቤትም ይግባኙን ሣይቀበለው ቀርቷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ ይህንን ውሣኔ ለማስለወጥ የቀረበ ነው ይህ ችሎትም አመልካች የመክሰስ መብት የላቸውም መባሉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ አድርጓል በዚሁ መሰረት ተጠሪ ቀርቦ ክርክሩን በጽሁፍ አቅርቧል ችሎቱም መዝገቡን እንደሚከተለው መርምራሯል ከላይ እንደተገለፀው አመልካች ክስ የመሰረቱት ተጠሪ በአደራ ሲያስተዳድረው የቆየውን የአባታቸውን ቤት እንዲያስረክባቸው ነው አንድ ከሣሽ ክስ እንዲያቀርብ የሚፈቀድለት ለክሱ ምክንያት በሆነው ነገር ወይም ክሱ በተመሰረተበት ሃብት ላይ ጥቅም ወይም መብት ያለው መሆኑን ካረጋገጠ እንደሆነ በፍሥሥህቁ ሥር ተመልክቷል ስለሆነም አመልካች ለመረከብ ክስ በመሰረቱት ቤት ላይ መብት ወይም ጥቅም ያላቸው መሆኑን ሊያረጋግጡ ይገባል የሥር ፍቤቶች የአመልካችን ክስ ወድቅ ያደረጉት የቤቱ የባለቤትነት ማረጋገጫ ባለመቅረቡ አመልካች በንብረቱ ላይ መብት ያላቸው መሆኑን አላረጋገጡም በማለት ነው እኛ እንዳየነው ግን አመልካች ክስ የቀረበበት ቤት የሟች አባታቸው ቤት ለመሆኑ የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ባያቀርቡም በስራና ከተማ ልማት ሚር የተፃፈ ደብዳቤና የቤቱን የቦታ ካርታ አቅርበዋል በማስረጃነት የቀረበው ደብዳቤ ክርክር የተነሣበት ቤት የአመልካች አባት የነበረና እሳቸው ሲሞቱ ቤቱን ተረክቦ የነበረው የግሪክ ኤምባሲ ቤቱን ለስራና ከተማ ልማት ያስረከበ በመሆኑ ግሪክ አገር አሉ የተባሉት የሟች ልጆች ባለመብቶች መሆናቸው ከተረጋገጠ ቤቱን እንዲረከቡ የሚያሣስብ መሆኑን ያመለክታል የከተማ ቤቶችን ባለቤትነት ለመወሰን ስልጣን ያለው አካል የፃፈው ይህ ደብዳቤ ቤቱ የአመልካች አባት መሆኑን የሚጠቁም ሆኖ አግኝተነዋል አመልካች ደግሞ የሟች አባታቸው ወራሽ መሆናቸውን አረጋግጠው የቀረቡ በመሆነ በቤቱ ላይ ጥቅም ወይም መብት ያላቸው መሆኑን አላረጋገጡም ለማለት የሚያስችል ሁኔታ አላየንም የፍህቁ ም ቢሆን ለአንድ ሰው የተሰጠው የቤት ባሃብትነት ምስክር ወረቀት ይህ ሰው የዚሁ ቤት ባለሃብት እንደሆነ ግምት ከሚወሰድ በቀር የቤቱ ባለሃብትነት በሌላ ሰነድ ሊረጋገጥ አይችልም የሚል አንድምታ የለውም በአርግጥ አመልካች ቤቱን ሊረከቡ ይገባል አይገባም የሚለው ከግራ ቀኙ ክርክርና ማስረጃ አንፃር ተመርምሮ የሚወሰን ቢሆንም አመልካች ግን ክስ በቀረበበት ቤት ላይ መብት ወይም ጥቅም ያላቸው መሆኑን አላረጋገጡም ማለት ስለማይቻል የሥር ፍቤቶች የቤቱ የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት አለመቅረቡን ብቻ መሰረት አድረገው ሌሎቹን የአመልካች ማስረጃዎች ሳያገናዝቡ አመልካች በንብረቱ ላይ መብት ወይም ጥቅም የላቸውም ማለታቸው ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ የፌከፍተኛ ፍቤት በመቁ በሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ብይን እንዲሁም የፌጠቅላይ ፍቤት በመቁ ህዳር ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ ተሽረዋል አመልካች ክስ በተመሰረተበት ንብረት ላይ ጥቅም ወይም መብት ስላላቸው የፌከፍተኛ ፍቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ የመሰለውን እንዲወስን ጉዳዩ በፍሥሥህቁ መሰረት ተመልሷል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰመቁ ሚያዚያ ቀን ዓም ዳኞችኹ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ መልዱ ሒሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ ሠልጣን አባተማም አመልካች ወሮ መገርቱ ነጋሣ አልቀረቡም ተጠሪ እነ ወሮ ፀሃይ ልጋ አልቀረቡም ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የጀመረው በፌመደፍቤት ነው የአሁኑ ተጠሪዎች ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ የኛ ተጠሪ ባለቤት የቀሪዎቹ ተጠሪዎች አባት በህይወት በነበሩበት ጊዜ ክስ የቀረበበትን ቤት ለአቶ ደረጀ መንግስቱ አከራይተው የነበረ ሲሆን ተከራዩ አመልካችን ቤቱ ውስጥ አስገብተው አካባቢውን ለቀው ጠፍተዋልፎ አመልካችንም የግል ቤታችንን ለቀው እንዲወጡ ጠይቀን ፍቃደኛ አልሆኑምለሚመለከተዉ ቀበሌም አመልክተን አመልካችም ቤት ሲያገኙ ለቀው የሚወጡ መሆኑን በእማኞች ፊት አረጋጠው የፈረሙ ቢሆንም ቤቱን ስላለቀቁ ቤቱን አንዲያስረክቡን ያለምንም ክፍያ ከመጋቢት ቀን ዓም ክስ እስከቀረበበት ድረስ ስለኖሩ በወር ብር አንድ መቶ ፃምሳ ታስቦ በድምሩ ብር አስራ አንድ ሺህ ሁለት መቶ ፃምሳ እንዲከፈሉ ይወሰንልን ብለው ጠይቀዋል አመልካችም ለቀረበባቸው ክስ በሰጡት መልስ ክስ የቀረበበት ቤት ተጠሪዎች በሚኖሩበት ቤት ይዞታ ስር የሚጠቃለል ለመሆኑ ማስረጃ አላቀረቡም ቤቱ ለአቶ ደረጀ መንግስቱ የተከራየበት ማስረጃ አልቀረበም ቤቱን በወረራ ይዛለች ካሉ ይህን ካወቁ ዓመት በላይ ስለሆነ በይርጋ ይታገዳል የደረሰባቸው የጥቅም ጉዳት ከውል ውጪ እንደመሆኑ መጠን የኪራይ ማስከፈል ጥያቄአቸው ሁለት አመት ካለፈው በይርጋ ይታገዳል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ካቀረቡ በቷላ ለፍሬ ጉዳዩ በሰጡት መልስ ቤቱን የተጠሪዎች አውራሽ አልሰሩትም ለአቶ ደረጀም አላከራዩም ቤቱ የአቶ ደረጀ ሲሆን ለአመልካች አከራይተውኛል ቤቱን ለማስረከብ ቃል ገብታለች የተባለው ተገድጄ የፈረምኩት ስለሆነ አልገደድበትም በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ መርምሮ የአመልካችን መቃወሚያዎች ውድቅ ካደረገ በኋላ አመልካች ይዘውት የሚገኘው ቤት የኛ ተጠሪ ባለቤትና የቀሪዎቹ አባት ይዞታ ስር የሚካተት መሆኑ ተረጋግጧል በማለት አመልካች ቤቱን ለተጠሪዎች እንዲያስረክቡና አመልካች ቤቱን አለቃለሁ ብለው ከፈረሙበት ጊዜ ጀምሮ በወር ብር መቶ ፃምሣ እየታሰበ ክሱ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ብር አስራ አንድ ሺህ ሁለት መቶ ዛፃምሣ ይክፈሉ በማለት ወስኗልፎ ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የፌከፍቤትም ውሣኔውን አጽንቷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም ውሣኔው የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በማለት ነው ይህ ችሎትም አመልካች ከመጋቢት ቀን ዓም አስከ ሐምሌ ቀን ዓም ድረስ ያለውን የተጠሪዎችን ቤት ያላግባብ የያዙበትን ብር አስራ አንድ ሺህ ሁለት መቶ ዛምሳ እንዲከፍሉ የተሰጠውን ውሣኔ አግባብነት ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት ቀርቦ እንዲታይ አድርጐ ተጠሪዎች ክርክራቸውን በጽሁፍ አቅርበዋል ፍቤቱም መዝገቡን መርምሯል ተጠሪዎች አመልካች ቤታቸውን ያለአግባብ ስለያዙ እንዲያስረክቧቸውና በቤቱ ያለአግባብ ለተገለገሉበት ካሣ እንዲከፍሉ ጠይቀዋል አመልካች በበኩላቸው ቤቱ የተጠሪዎች አለመሆኑንና ቤት እንዲለቁም ሆነ ካሣ እንዲከፍሉ የቀረበው ክስ በይርጋ ቀሪ የሚሆን ነው ሲሉ ተከራክረዋል ከክርክሩ ክስ የቀረበበት ቤት የተጠሪዎች መሆነ በማስረጃ መረጋገጡን የተገነዘብን በመሆኑ አመልካች የቤቱን ባለቤትነት በተመለከተ ማስረጃ ላይ ተንተርሰው ያቀረቡትን ክርክር ይህ ችሎት አልተቀበለውም ሌላው አመልካች ያነሱት ክርክር ቤት እንዲያስረክቡ የቀረበው ክስ በይርጋ ቀሪ ነው የሚል ነው አመልካችዋ ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው ያሉት ክሱ ሁከት ይወገድልኝ በማለት የቀረበ ስለሆነ ነው በማለት ነው ነገር ግን ተጠሪዎች ይዞታችን በሃይል ተወስዷል ወይም በይዞታችን ላይ ሁከት ተፈጥሯል በማለት ያቀረቡት ክስ የለም ክሣቸው በኪራይ ለአቶ ደረጀ ያስረከቡትን ቤት አመልካች መብት ሣይኖራቸው ገብተው አልወጣም ብለዋልና ያስረክቡን የሚል ነው ስለሆነም አመልካች አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲለቁ የቀረበ ክስ ስለሆነ የአመልካች ተቃውሞ ተቀባይነት የለውም በመጨረሻ አመልካች ያቀረቡት ክርክር የቀረበው የካሣ ጥያቄም ቢሆን በይርጋ ቀሪ ይሆናል የሜል ነው ክስ የቀረበበት ቤት የተጠሪዎች በመሆኑ ቤቱን ያላግባብ ይዘው ለተጠቀሙበትና ያላግባብ ለበለፀጉበት ካሣ እንዲከፍሉ ክስ ቀርቧል በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም በሌላ ሰው ፃብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ ሰው ጥቅም ባገኘበት መጠን ለባለሃብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ኪሣራ መክፈል እንዳለበት በፍህቁ ሥር ተመልክቷል በመሆኑም አመልካች በቤቱ አላግባብ በበለፀጉበት መጠን ኪሣራ እንዲከፍሉ መጠየቃቸው ህጉን መሰረት ያደረገ ነው በሌላ በኩል ግን ይህ የካሣ ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባበትን የጊዜ ገደብ በተመለከተ ክርክር ቀርቧል ያለአግባብ ስለመበልፀግ የሚናገረው ምዕራፍ የካሣ ጥያቄ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ አይናገርም ነገር ግን አላግባብ ስለመበልፀግና ከውል ውጪ ስለሚደርስ ዛላፊነት የሚናገሩት ድንጋጌዎች በአንድ አንቀጽ ውስጥ ተካትተው መገኘታቸው እንዲሁም ያለአግባብ መበልፀግም ከውል ውጪ የሚደርስ ፃዛላፊነት በመሆኑ ከውል ውጭ በሚደርስ ዛላፊነት ሥር የተመለከተው የይርጋ ዘመን በተመሣሣይ አላግባብ መበልፀግን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል በዚህ መሰረት ከውል ውጭ ፃላፊነትን በተመለከተ ተበዳዩ ክስ ማቅረብ የሚችለው ካሣ የሚጠይቅበት ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ አስከ አመት ድረስ መሆኑ በፍህቁ ሥር ተመልክቷል በተያዘው ጉዳይ አመልካች ቤቱን ያለማቋረጥ ለረዥም ጊዜ ይዘው እየተገለገሉበት በመሆኑ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ ላሉት ሁለት አመታት አላግባብ በቤቱ በተገለገሉበት መጠን እንዲከፈሉ የተጠየቁት ካሣ በይጋ የሚታገድ አይሆንም ከዛ በፊት ያሉት ግዜያት ግን በይርጋ ቀሪ የሚሆኑ ናቸው በመሆኑም የሥር ፍቤቶች የ አመት ካሣ እንዲከፍሉ የሰጡት ውሣኔ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ብለናል ውሣኔ የፌመደፍቤት በመቁ በሐምሌ ቀን የሰጠው ውሣኔ የፌከፍቤት በመቁ በኀዳር ቀን ዓም የሰጡት ውሣኔዎች ተሻሽሸለዋል አመልካች ክስ የቀረበበትን ቤት ያስረክቡ ከሐምሌ ቀን ዓም አስከ ሐምሌ ቀን ዓም ላለው ጊዜ ብቻ በቤቱ አላግባብ ለተጠቀሙበት በወር ብር አንድ መቶ ፃምሣ ታስቦ በድምሩ ብር ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ለተጠሪ ይክፈሉ ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ ይርጋ የሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ አሰግድ ጋሻው ተሻገር ገስላሴ ታፈሰ ይርጋ ብርፃኑ አመነው አመልካች አቶ ደጀኔ ለገሠ ቀረቡ ተጠሪ እነ አቶ መላኩ ጌታቸው ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው አመልካች የውርስ ሀብት ለመረከብ በተጠሪዎች ላይ ያቀረቡት ክስ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ተብሎ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃና ከፍተኛ ፍቤት ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ ነው የጉዳዩ አመጣጥም ሲታይ አመልካች በፌመደፍቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት ክስ ከሳሽ በእናታቸው በወሮ የልፍኝ አጅጉ ተተክተው የወሮ ያምሮት አጅጉ ወራሽ መሆናቸውን ሰኔ ቀን ዓም በፍቤት ውሳኔ አረጋግጠዋል የተከሳሾች አያት ወሮ ታደለች አርጋው ከወሮ ምንትዋብ ሙሴ ጋር በመሆን የአክስቴ የወሮ ያምሮት እጅጉ ወራሽ ናቸው ተብሎ የካቲት ቀን ዓም በፍቤት የተሰጠውን ውሳኔ መቃወሚያ አቅርቤ ሰኔ ቀን ዓም ተሰርዚል ከዚያም ቤት ለማስለቀቅ ሚያዚያ ቀን ዓም በተከሳሾች እናትና በወሮ ምንትዋብ ሙሴ ላይ ክስ ብመሠርትም ተከሳሾች በሞት በመለየታቸው መጥሪያ ሳይደርሳቸው ክሱ ተቋርጣጧል በአጠቃላይ ተከሳሾች ከወሮ ያምሮት እጅጉ የሚደርሰኝን የውርስ ሀብት ያስረክቡኝ በማለት ጠይቀዋል ተጠሪዎችም በሰጡት መልስ ከሳሽ የወሮ ያምሮት እጅጉ ሕጋዊ ወራሾች መሆናቸውን ያረጋገጡት ሐምሌ ቀን ዓም ተከሳሾች ይዘውብኛል የሚሉትን ቤት ላለፋት ዘጠኝ ዓመታት ያልጠየቁ ስለሆነ ክሱ በፍብሕቁ መሠረት በ ዓመት ይርጋ ይታገዳል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያና በፍሬ ጉዳዩም ሙሉ መልስ በመስጠት ተከራክረዋል ክርክሩ በዚህ መልኩ የቀረበለትም የፌዴራሉ መደፍቤት የከሳሽ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም የሚለውን ጭብጥ መሥርቶ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ክርክሩን መርም ል በዚህም መሠረት ከሳሽ የወሮ ያምሮት አጅጉ ወራሽ መሆናቸውን ያረጋገጡት ሐምሌ ቀን ዓም ነው ከዚህም በኋላም በተከሳሶሾች እናት ላይም ሆነ በተከሳሾች ላይ የውርስ ሀብት ይልቀቁልኝ በማለት ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መብት እንዳገኙ ይቆጠራል ይህ የይርጋ ጊዜ ሊቋረጥ ከሚችልባቸው ምክንያቶች አንዱ ክስ ቀርቦ በሆነ ጊዜ ሲሆን ከሳሽ በመቁ የካቲት ቀን ዓም የተከሳሾች ወላጅ እናትና ወሮ ምንትዋብ ሙሴ ወራሾች ናቸው ተብሎ የተሰጠን ውሳኔ በመቃወም አቤቱታ ያቀረቡ ቢሆንም ይህ የመቃወሚያ ክርክር የወራሽነት መብት ላይ ብቻ ያነጣጠረ በመሆኑና የውርስ ንብረት ይሰጠኝ በሚል የቀረበ ባለመሆኑ በፍብሕቁ ለነ መሠረት ይርጋው ተቋርጧል ለማለት አይችልም ስለሆነም ከሳሽ የወራሽነት መብታቸውን ካረጋገጡና የውርሱ ንብረቶች በተከሳሾች መያዛቸውን ካወቁ በ ዓመት ጊዜ ውስጥ በተከሳሾች ላይ ክሱን ያላቀረቡ ስለሆነ በፍብሕ ቁጥር መሠረት በ ዓመት ይርጋ ይታገዳል በማለት ክሱን ሳይቀበለው ቀርቷል ጉዳዩን በይግባኝ የመረመረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ግራ ቀኙን አከራክሮ ተመሳሳይ ጭብጥ በመያዝ የፍብሕ ቁዐዐዐ ተፈፃሚነቱ አንድ የወራሽነት ማስረጃ ያለውና ነገር ግን ይህ ማስረጃው በሕግ ዓይን ተቀባይነት የሌለው ሆኖ ውርሱን ወይም የውርሱን አንድ ክፍል የያዘ ከሆነ በሕጉ ዓይን ተቀባይነት ያለው ማስረጃ የያዘው ወራሽ ወራሽነቱ እንዲታወቅለትና የተወሰዱበት የውርስ ንብረቶች እንዲመለሱለት በሚጠየቅበት ጊዜ እንደሆነ በውሳኔው ላይ አስፍሮ በተያዘው ጉዳይ ግን መሰጭዎች ተጠቃሹን ንብረት የያዙት ምንም ዓይነት የወራሽነት ማስረጃ ሳይኖራቸው ስለሆነ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው ድንጋጌ የፍብሕቁጥር ሳይሆን ቁጥር ነው ካለ በኋላ ከዚሁ አኳያ ሲታይም የይባይየተጠሪ አውራሽ በ ዓም መሞታቸው የተረጋገጠ ሲሆን ተጠሪም በመብታቸው መሥራት የሚችሉት ከዚህ ጊዜ በኋላ ስለሆነ ቤት ይለቀቅልኝ በማለት ክስ የመሠረቱት ምንም እንኳን መጥሪያው ለመሰጭዎች አውራሽ ያልደረሰ ቢሆንም በ ዓም ከ ዓመት በኋላ ስለሆነ በፍብሕቁ ላይ በተቀመጠው የዐ ዓመት ጊዜ ክሱ ያልቀረበ ስለሆነ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት ምክንያቱን ቀይሮ የፌመደፍቤት ውሳኔን አጽንቷል የሰበር አቤቱታውም የቀረበው ይህንነ በመቃወምና መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ሲሆን ይህ ሰበር ሰሚ ችሎትም የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ የመሰጪዎች አውራሽ የሟች ወሮ ያምሮት እጅጉ ልጅ ነኝ በማለት ያወጡትን የወራሽነት ማስረጃ አመልካች ጥር ዐ ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ መቃወሚያ በማቅረብ እንዲሰረዝ ካደረገ የወራሽነት ማስረጃ ያሰረዘበት ውሳኔ ከግምት ሳይገባ ንብረቱን ለመረከብ የጠየቀው አውራሹ ከሞቱ ከዐ ዓመት በኋላ ነው ተብሎ ክሱ በይርጋ ቀሪ የመደረጉን አግባብነት ለማጣራት ሲሆን ተጠሪዎች ቀርበው ክሱ በይርጋ ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ አግባብነት በመዘርዘር አቤቱታው ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክረዋል በአጠቃላይ የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን በሥር ፍቤቶች በተጠሪ በኩል የቀረበው ክስ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ተብሎ የተሰጠው ውሳኔ አግባብነት ከሕጉ አኳያ እንደሚከተለው ተመርምራሯል አመልካች በፌዴራል መደፍቤት በተጠሪዎች ላይ ያቀረቡት ክስ ባጭሩ ከአክስቴ ከወሮ ያምሮት እጅጉ በውርስ የተላለፈልኝን ቤት ይዘው የሚገኙ ስለሆነ ያስረክቡኝ በማለት ነው ተጠሪዎች የአመልካች አክስት የሆኑት የወሮ ያምሮት እጀጉን ንብረት በመውረስ ረገድ የቅድሚያ መብት እንደሌላቸው ቢረጋገጥም ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት ይዘው የተገኙት ወራሽ ነን በማለት ነው ተጠሪዎች ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት በመውረስ ረገድ ከአመልካች የቀደመ መብት ባይኖራቸውም ንብረቱን ይዘው የሚገኙት የመውረስ መብት ሳይኖራቸው ነው ለማለት ግን የሚያስችል አይሆንም ተጠሪዎች ቤቱን ይዘው የሚገኙት በወራሽነት መብት ነው ከተባለ ደግሞ የፍብሕቁ ዐዐዐ በዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት አለው ማለት ነው ስለሆነም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የተጠቀሰው ድንጋጌ ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት የለውም በማለት የይርጋ ክርክሩን ከቁጥር ድንጋጌ ጋር አያይዞ በዚሁ ድንጋጌ መሠረት ክሱ በይርጋ ተቋርጧል የሚል ውሳኔ የሰጠው ሕጉን በተገቢው ካለመተርጐም እንደሆነ ታምኖበታልበሌላ በኩልም አመልካች ተጠሪዎች የያዙትን የውርስ ንብረት ያስረክቡኝ በማለት በተጠሪዎች ላይ ክስ የመሰረቱት ሰኔ ዐ ቀን ዓም ሲሆን የአክስታቸው ወራሽነታቸውን ያረጋገጡት ደግሞ ሐምሌ ቀን ዓም ነው አመልካች ወራሽነታቸውን ካረጋገጡ በኋላ በፍብሕቁ ላይ የተቀመጠው የ ዓመት የይርጋ ጊዜ ከማለፋ በፊት በተጠሪዎች ተይዞብኛል የሚሉት ንብረት እንዲመለስላቸው መጠየቅ ይገባቸው እንደነበር የሚታመን ከመሆኑም በላይ የተጠሪዎች አውራሽ የአመልካች አክስት ወራሽ ናቸው ተብሎ የተሰጠውን ውሳኔ አመልካች ለማሰረዝ አቤቱታ አቅርበው ክሱን ማቅረብ የሚችሉት ውሳኔው ከተሰረዘ በኋላ ነው ቢባል አንኳን ይፄው ውሳኔ በ ዓም ተሰርዞ ክሱን ግን ያቀረቡት የ ዓመቱ የጊዜ ገደብ ካለፈ በኋላ በ ዓም ስለሆነ ከተጠቀሰው የፍብሕቁ ዐዐዐ አኳያ በይርጋ የማይታገድበት ምክንያት አልተገኘም ውሳኔ የሥር ፍቤቶች የቀረበው ክስ በይርጋ ተቋርጧል በማለት የሰጡት ውሳኔ ከውጤት አኳያ በአግባቡ ሆኖ ስለተገኘ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ፀንቷል የፍርዱ ግልባጭ ለሥር ፍቤቶች ይተላለፍ ግራ ቀኙ ወጭና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል ተጨማሪ ትዕዛዝ በአራዳ ክከተማ ቀበሌ ዐዐ የቤት ቁጥር ዐ የሆነው ቤት እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ ባለበት ሁኔታ ተከብሮ እንዲቆይ በዚህ ፍቤት በግንቦት ቀን ዓም የተሰጠው የዕግድ ትዕዛዝ በዚህ ትዕዛዝ ተነስቷል ይፃፍ የማይነበብ አምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ መስፍን ዕቁበዮናስ ተሻገር ገሥላሴ አብዱራሂም አህመድ አመልካች ወት አይናለም አበበ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ደገፋ ጉርሙ ጠበቃ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በአመልካች ሰኔ ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ መነሻነት ነው ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በቀረበ ክርክር ሲሆን ፍሬ ነገሩም ያሁኑ ተጠሪ የሥር ከሣሽ በመሆን በሥር ኛ በመቃወም በተጠሪ ወሮ ደስታ ይመር በዚህ መዝገብ የሌሉበት እና ባሁኗ አመልካች የሥር ኛ በመቃወም ተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ሟች ወንድማቸው አቶ አበበ ጉርሙ ልጅ አለመውለዱ እየታወቀ አመልካች የሟች ልጅ ናት ተብሎ ወራሽነቱ የተረጋገጠው ባግባቡ ስላልሆነ ውሣኔው ይሻር የሚል ነው ለክሱም ኛ የመቃወም ተጠሪ በርግጥ አመልካች ከኔም ሆነ ከሟች አትወለድም ልጄ ነች ብዬ ውሣኔ ያሰጠሁት ከሕፃንነቷ ጀምሮ ስላሳደኳትና አንደ ልጅ ስለምቆጥራት ነው ሲሉ አመልካችም በበኩሏ ተጠሪ ሕፃን ሆፔ ውሣኔ ሲሰጥ ቀርበው መቃወም ሲችሉ ከ ዓመት በኋላ መቅረባቸው በፍብሕቁ ዐዐዐ መሠረት ተቀባይነት የለውም በማለት በየበኩላቸው መልስ ሰጥተዋል ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከሰማ በላ የፍብሕቁ ዐዐዐ የሚሠራው የፈረሰ ንብረት ይገባኛል ለሚል ክርክር እንጂ ወራሽ ናት አይደለችም ለሚል ክርክር አይደለም በሚል የይርጋ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎ አመልካች ከሟች የማትወለድ በመሆኑ ስለ ነዛዜ ወራሽ ልትሆን አትችልም በማለት ወስኗል ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለት የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤትም በበኩሉ የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከመረመረ በላ ሟችና ኛ የመቃወም ተጠሪ በቤተሰብ ሕግ አንቀጽ ሠ መሠረት አመልካችን ወደ ቤት በመውሰድ በማንከባከብና በማስተማር እንደ አባት በመሆን የተሣተፉ በመሆኑ አመልካች የሟች ልጅና የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ ነች በማለት ወስኗል ያሁኑ ተጠሪ በዚህ ውሣኔ ቅር ተሰኝተው ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርበው ፍርድ ቤቱም የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሣኔ ሽሮ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትን ውሣኔ አጽንቷል አመልካች ይህን የሰበር አቤቱታ ያቀረቡት በዚህ መነሻነት ሲሆን ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን መርምሮ ተጠሪን በማስቀረብ ግራ ቀኙን አከራክሯል ክርክሩንም ከሕጉ ጋር በማገናዘብ መርምሯል በዚህም መሠረት አመልካች ኅዳር ቀን ዓም የወራሽነት ማስረጃ ካገኙ በኋላ የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ መሆናቸውን በመግለጽ በቤቱ ላይ ያገኙት የጋራ ባለሀብትነት መብት ከሥር ኛ የመቃወም ተጠሪ ጋር ተቀባይነት ያጣው ባግባቡ መሆን አለመሆኑን ፍርድ ቤቱ አንደሚከተለው ተመልክቷል አመልካች በሥር ፍርድ ቤቶች ያቀረቡት ክርክር ባንድ በኩል የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ ነኝ በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ ከዐ ዓመት በላይ ቆይተው በቤቱ ላይ አለኝ የሚሉት የወራሽነት መብት በፍብሕቁ ዐዐዐ መሠረት የሚታገድ ነው የሚል ሲሆን የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የጠቀሱት የፍብሕቁ ዐዐዐ ተፈፃሚነት ያለው የውርስ ንብረት ይገባኛልና ይሰጠኝ ለሚል ክርክር እንጂ ወራሽ ናት አይደለምችም ለሚል ክርክር አይደለም በማለት የሰጠውን ውሣኔ እንደተመለከትነው ድንጋጌው ባግባቡ አለመፈጸሙን ተረድተናል ያሁኑ ተጠሪ በሥር ፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ በራሱም ሲታይ ይዘቱ ወንድሜ ልጅ አለመውለዱ እየታወቀ አመልካች በሐሰት ልጅ ነኝ ብላ የወራሽነት ማስረጃ የወሰደች ስለሆነ ትመልስ እንዲሁም በቤቱ ላይ ያለው የሟች ድርሻ ለኔ ይሰጠኝ የሚል ሲሆን አመልካችም በበኩሏ የሟች ልጅ መሆኗን እና ንብረቱም እንደሚገባት መከራከራቸው ከክርክሩ ትክክለኛ ገጽ ታይቷል ከክርክሩ ትክክለኛ ገጽ ይህ ሆኖ እያለ የሥር ፍርድ ቤት አመልካች ክሱን ያመኑ ይመስል ገና ከጅምሩ ድንጋጌውን አጥብቦ በመተርጎም የልጅነት ጥያቄ ቢነሣ ድንጋጌው ተፈፃሚነት የለውም ማለቱ ተቀባይነት ያለው ሆኖ አልተገኘም ይህ ድንጋጌ መገኛው አንቀጽ ሆኖ እውነተኛ ወራሽ እኔ ነኝ ከሚል ጥያቄ ጀምሮ የውርስ ንብረት ያላግባብ ተወስዲልና ይመለስልኝ በማለት የሚቀርቡትን ክሶች ጥያቄዎች የሚያካትት ለመሆኑ አንቀጽ ን መመልከቱ ይበቃል በዚህ ረገድ አመልካች ክርክሩን ባስነሳው ቤት ላይ ከ ዓመት በላይ የቆየ የባለሀብትነት ድርሻ ማግኘታቸው እየተመለከትም ተጠሪም ድርሻቸውን ለመጠየቅ ከሚያስችላቸው ጊዜ በላይ ቆይተው ክስ ለማቅረባቸው አመልካች ያቀረቡት የይርጋ ክርክር ተቀባይነት ያጣው ድንጋጌው በጠባቡ በሥር ፍርድ ቤት በመተረጎሙ ሳቢያ መሆኑን ይህ ፍቤት ተገንዝቧል በመሆኑም የመጨረሻ ውሣኔ የሰጠው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይርጋውን ነጥብ አልፎ ውሣሄ መስጠቱ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል የከፍተኛው ፍርድ ቤት ምንም እንኳ የአመልካችን ልጅነት ተቀብሎ የሥር ፍቤቱ ውሣኔ የሻረ ቢሆንም ፍቤቱ ለይርጋው ጥያቄ በቅድሚያ ምላሽ ቢሰጥ ኖሮ ወደዚህ ነጥብ መግባት የሚያስፈለገው እንዳልነበር ተገንዝበናል ስለሆነም ክሱ በይርጋ ታግዲል ብለናል ውሣኔ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ዐ ጥር ቀን ዓም የሰጧቸው ውሣኔዎች ተሽረዋል ይፃፍ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል ይፃፍና ነዓ የከፍተኛ ፍርድ ቤት መቁ በመጣበት አኳኋን በመሸኛ ተመልሶ ይላክ መዝገቡ ተዘግቷል ክሱ በይርጋ ይታገዳል ተብሏል መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁጥር ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ተገኔ ጌታነህ መድኅን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሠልጣን አባተማም አመልካች አቶ ተገኝ ይማም አልቀረቡም ተጠሪዎች እነ አቶ ካሣሁን ደሳለኝ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረው በፌመደፍቤት ሲሆን የአሁን ተጠሪዎች ነሐሴ ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት የክስ ማመልከቻ እህታችን ወሮ ያልጋ ደሳለኝ እና አቶ ተገኝ ይማም ተጋብተው እየኖሩ ሳሉ እህታችን ጥቅምት ቀን ዓም ከዚህ ዓለም በሞት ስለተለየች አብረው የሠሩትን ቤትና አብረው ያፈሩትን ሌላ ንብረት ለእኛው ለሟች ወራሾች ግማሹን እንዲሰጡን እንዲወሰንልን በማለት ክስ አቅርበዋል የአሁኑ አመልካች ደግሞ በታህሳስ ቀን ዓም ጽፈው ያቀረቡት መልስ ክሱ በፍብሕቁ እና መሠረት በይርጋ ቀሪ ሊሆን የሚገባው ነው ከሟች ጋር ከግብረ ሥጋ ግንኙነት በስተቀር የጋብቻ ግንኙነት አልነበረንም ቤቱ የግል ንብረቴ ነው የሌሎቹን ንብረቶች ግምትም የተጋነነ ነው። የሚለው በመሆኑ ይህንኑ ጭብጥ ይዘን ከሕጉ አኳያ እንደሚከተለው መርምረናል ተጠሪ ከላይ የተመለከተውን ክስ ለባህርዳር ወረዳ ፍቤት ሲያቀርብ አመልካች ለክሱ ምክንያት የሆነው ነገር የተፈፀመው በ ዓም ሲሆን ክሱ ግን የቀረበው በ ዓም ከ ዓመት በኋላ ስለሆነ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት የመጀመያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርቧል የወረዳው ፍቤትም ጉደዩ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቀርቦ ክርክሩ የግል የሥራ ክርክር እንጂ የወል የሥራ ክርክር ስላልሆነ ፍቤቱ ጉዳዩን አይቶ ውሣኔ የመስጠት ሥልጣን አለው በማለት ውሣኔ የሰጠ ስለሆነ መቃወሚያው በአግባቡ አልቀረበም በማለት ሣይቀበለው ቀርቷል ከሣሽ የሆነ ወገን ክሱን ለፍቤት ከማቅረቡ በፊት የትኛው ፍቤት ክሱን ለማየት የግዛትና የሥረ ነገር ሥልጣን እንዳለው አጣርቶ ማቅረብ አንዳለበት ይታመናል በዚሁ መሠረትም ተጠሪ ክሱን በቅድሚያ ለባህርዳር ወረዳ ፍቤት አቅርቦ ነበር ሆኖም ፍቤቱ ጉደዩን ለማየት የሥረ ነገር ሥልጣን የለኝም ሲል ከሣሹተጠሪ የመረጠው ይግባኝ ማለትን ሣይሆን ክሱን ለአሠሪና ሠራተኛ ወሣኝ ቦርድ ማቅረብን በመሆኑ በዚሁ መሠረት ክሱን ለቦርዱ አቅረቦ ክርክሩ ቀጥሎ መጨረሻ ጉዳዩ ለፌዴራል ጠፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቀርቦ ችሎቱም የዚህ ዓይነት ክርክር በወል የሥራ ክርክር ሊሸፈን ስለማይችል ቦርዱ ይህን ጉዳይ ተመልክቶ ውሣኔ የሰጠው ሥልጣን ሣይኖረው ነው በማለት የበኩሉን ውሣኔ ሰጥቷል ከዚህ በኋላ ተጠሪ ክሱን ለባህርዳር ወረዳ ፍቤት ሲያቀርብ ክሱ በይርጋ ቀሪ መሆኑን በመግለጽ አመልካች የይርጋ መቃወሚያ አቅርቧል ከሥራ ክርክር ጋር በተያያዘ የሚቀርብ ክስ የይርጋ ጊዜ ከፍተኛው ዓመት እንደሆነ በአሠሪና ሠራተኛ አቁጥር አንቀጽ ላይ የተመለከተ ሲሆን ይህ የይርጋ ጊዜ ከማለፉ በፊት ተጠሪ በቅድሚያ ክሱን ለወረዳ ፍቤት አቅርቦ ነበር ሆኖም ፍቤቱ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለኝም በማለት ክሱን ሣይቀበል ሲቀር ክርክሩ የግል የሥራ ክርክር ከመሆኑ አኳያ በይግባኝ ሥነ ሥርዓት በመጠቀም ይህንኑ ውሣኔ ተጠሪ ማስለወጥ ሲገባው ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ለሌለው ለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ክሱን ማቅረብ አልነበረበትም የፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም በመቁ ግራ ቀኙን አከራክሮ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ከአዋጅ ቁጥር አንፃር ይህንን ጉዳይ ለማየት የሥረ ነገር ሥልጣን የለውም በማለት ውሣኔ ከመስጠቱ በስተቀር አስቀድሞ ክርክሩ በተጀመረበት በባህርዳር ወረዳ ፍቤት ክርክሩ ይቀጥል በማለት ውሣኔ አልሰጠም ስለሆነም ለባህርዳር ወረዳ ፍቤት ድጋሚ ክስ ሲቀርብ በሕጉ ላይ የተመለከተው የይርጋ ጊዜ ካለፈ ከ ዓመት በላ ቀርቦ ባለበት ሁኔታ ፍቤቱ የይርጋ መቃወሚያውን ሊቀበለው ሲገባ ውድቅ ማድረጉ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ተገኝቷል አመልካች በዚሁ ውሣኔ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍቤት አቅርቦ ፍቤቱ ሁለቱም ተከራካሪ ወገኖች ያቀረቡት ይግባኝ ተጣምሮ አንደሚታይ ትእዛዝ የሰጠ ቢሆንም በተጠሪ በኩል የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ከመወሰኑ በስተቀር የአመልካችን የይግባኝ ቅሬታ ሣይመለከተው አልፎታል ዳኝነት የተጠየቀበት ነገር ተቀባይነት ሣያገኝ የታለፈ እንደሆነ እንደተከለከለ እንደሚቆጠር በፍብሕሥሥቁ ላይ የተመለከተ ስለሆነ በዚህም ጉዳይ ይርጋን አስመልክቶ አመልካች ለምዕራብ ጎጀም ዞን ከፍተኛ ፍቤት ያቀረበው ቅሬታ ስለታለፈ እንደተከለከለ የሚቆጠር ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የባህርዳር ወረዳ ፍቤት ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ አንደዚሁም የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍቤትም በዚሁ ጉዳይ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽራል ተጠሪ በአመልካች ላይ ክሱ ያቀረበው በሕጉ ላይ የተቀመጠው ጊዜ ካለፈ በኋላ ስለሆነ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ተብሎ ተወስኗል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰመቁጥር ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ሠልጣን አባተማም አመልካች የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ነፈጅ ቀረቡ ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነፈጅ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ጉዳይ በመድን ውል ላይ የተመሠረተን ይርጋ የሚመለከት ሲሆን የአሁን ተጠሪ በአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በአሁን አመልካችና በሥር ኛ አና ኛ ተከሣሾች ላይ ባቀረበው ክስ ኛ ተከሣሽ በሚያዝያ ቀን ዓም በተፈረመ ውል ከከሣሽ ብር ሺህ ሲበደር በኛ ተከሣሽ ስም የተመዘገበች መኪና በዋስትና አስይዚል በብድሩ ውል መሠረት ኛ ተከሣሽ ዕዳውን አጠናቆ ሳይከፍል በዋስትና የተያዘችው መኪና ጉዳት የደረሰባት ስለሆነና ከሣሽ በመድን ውሉ መሠረት ኛ ተከሣሽ ለኛ ተከሣሸ ሊከፍለው የሚገባው ገንዘብ ቅድሚያ መብት ስላለው ኛ ተከሣሽም ለመክፈል ፈቃደኛ ሆኖ ነገር ግን ዛሬ ነገ በማለት ክፍያውን ሳይፈጽም ስለቀረ ሦስቱም ተከሣሾች ክስ የቀረበበትን ገንዘብ እንዲከፍሉ ይወስንልን በማለት ጠይቋል የሥር ኛ ተከሣሽ የአሁን አመልካችም ቀርቦ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባነሣው ክርክር በዋስትና ተይዛለች የተባለችው መኪና በአደጋ ጉዳት የደረሰባት በነሐሴ ቀን ዓም ሲሆን ክሱ የቀረበው መስከረም ቀን ዓም ነው ኛ ተከሣሽ ዕዳውን አምኗል የተባለው ደግሞ የካቲት ቀን ነው ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ክሱ እስከቀረበበት ድረስ ያለው ሲታሰብ ዓመት ከ ወር ከ ቀን ነው ይህም በንግድ ሕግ ቁጥር ላይ እንደተመለከተው ጉዳቱ በደረሰ በ ዓመት ጊዜ ወስጥ ክሱ መቅረብ ሲገባው እንደዚሁ ተቋርጧል ቢባል ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ በሁለት አመት መቅረብ ሲኖርበት በዚህ ጊዜ ውስጥ ክሱ ያልቀረበ ስለሆነ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆን ፍቤቱ ክሱን ውድቅ ሊያደርግ ይገባል በማለት ተከራክሯል የፌዴራል መደፍቤት በዚህ ረገድ የቀረበውን ክርክር መርምሮ በፍብሕቁ መሠረት ይርጋ ከተቋረጠ በኋላ ድጋሚ የሚኖረው የይርጋ ጊዜ ዓመት እንደሆነ መገንዘብ የሚቻል በመሆኑና ይህ የ ዓመት የይርጋ ጊዜም ከመጠናቀቁ በፊት ክሱ ስለቀረበ ኛ ተከሣሽ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት ያቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ተቀባይነት የለውም ካለ በኋላ ግራ ቀኙ በፍሬ ጉዳይ ረገድ ያቀረቡትን ክርክር ውሣኔ ሰጥቷል ኛ ተከሣሽ የአሁን አመልካች በዚህ ውሣኔ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለኦሮሚያ ጠፍቤት አቅርቦ ፍቤቱም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ ይርጋ ከተቋረጠ በኋላ ድጋሚ የይርጋ ጊዜ የሚታሰበው አስቀድሞ በነበረው የይርጋ ጊዜ ልክ እንደሆነ ከፍብሕቁ ድንጋጌ መረዳት የሚቻል እንደመሆኑ መጠን በዚህም ጉዳይ ይግባኝ ባይ ፅዳውን አምኗል ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ የ ዓመት የይርጋ ጊዜ ከሚታሰብ በስተቀር አመት ሊሆን ስለማይችል ይርጋው ከተቋረጠም በላ በዚህ የሁለት አመት ጊዜ መልስ ሰጪ ክሱን ያላቀረበ በመሆኑ የሥር ፍቤት ክሱ በይርጋ ቀሪ አልሆነም በማለት መቃወሚያውን ውድቅ ማድረጉ በአግባቡ አይደለም ብሎ ይህንኑ የከፍተኛውን ፍቤት ውሣኔ ሽሮ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት ውሣኔ ሰጥቷል የአሁን ተጠሪም በዚህ ውሣኔ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታውን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት አቅርቦ ጠቅላይ ፍቤቱም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት የሰጠውን ውሣኔ በመሻር በይርጋ አልተቋረጠም ሲል ዋናው ክርክር በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት እንዲታይ ብሎ ጉዳዩን ወደ ኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት መልሷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንኑ ውሣኔ ለማስለወጥ ሲሆን ይህ ችሎትም አቤቱታውን መርምሮ ጉዳዩ በንግድ ሕግ ቁጥር ላይ የተመለከተው የ ዓመት ጊዜ ተቋርጧል ከተባለ አዲሱ የይርጋ ጊዜ የሚታሰበው በንግድ ሕግ መሠረት ወይንስ በፍትሐበሔር ሕግ የሚለው ተጣርቶ ሊወሰን እንደሚገባው በማመኑ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክሯል በአጠቃላይ የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን የሰበር አቤቱታው ያስቀርባል ከተባለበት ነጥብ አኳያ እንደሚከተለው ተመርምራል በኢንሹራንስ ውል ላይ ተመስርቶ የሚቀርብ ማንኛውም ክስ ጉዳቱ በደረሰ በ ዓመት ጊዜ ውስጥ መቅረብ እንዳለበት የኢንሹራንስን ጉዳይ በተለይ በሚገዛው በንግድ ሕጉ በቁጥር ላይ ተመልክቷል በሌላ በኩልም በሕጉ ላይ የተመለከተው የይርጋ ጊዜ ሲቋረጥ እንደ አዲስ ስለሚቆጠረው የይርጋ ጊዜ በንግድ ሕጉ ላይ አልተመለከተም ይህ ነጥብ በልዩ ሕጉ ማለትም በንግድ ሕጉ ካልተሸፈነ ወደ ጠቅላላ ሕግ መፄድ ከሕግ አተረጓጐም መርህ አኳያ ተቀባይነት ያለው ስለሆነ በዚሁ መሠረት ጠቅላላ ሕጉን መመልከት አግባብነት ይኖረዋል ለጉዳዩ አግባብነት የሚኖረውም ድንጋጌ የፍብሕቁ ሲሆን በዚህ ድንጋጌ መሠረትም ይርጋ በተቋረጠ ገዜ ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ እንደገና አዲስ የይርጋ ዘመን መቁጠር እንደሚጀምር በዚሁ ድንጋጌ በንዑስ ቁጥር ሥር ተመልክቷል ከዚህ ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የሚቻለው ይርጋው በተቋረጠ ጊዜ ቀድሞ የነበረው የይርጋ ጊዜ አንደ አዲስ መቁጠር የሚጀምር መሆኑን ነው በእርግጥ በዚሁ ድንጋጌ በንዑስ ቁጥር ሥር ይርጋው ተቋርጦ በሚገኝበት ጊዜ የይርጋ ዘመኑ አቆጣጠር ሁልጊዜ ዓመት እንደሆነ ተመልክቷል ይሁንና ይህ ድንጋጌ የሚገኘው ጠቅላላ የውሎች ሕግ በሚለው ክፍል ከመሆኑም በላይ ውልን አስመልክቶ የሚቀርብ ክስ በ ዓመት ይርጋ ቀሪ እንደሚሆን በፍብሕቁ ላይ ስለተመለከተ ከዚሁ ከጠቅላላ ውል ጋር በተያያዘ አንድ የይርጋ ጊዜ ሲቋረጥ ሌላ አዲስ የ አመት የይርጋ ጊዜ ሊኖር እንደሚችል ከሚያስገነዝብ በስተቀር በልዩ ሕግ የይርጋ ጊዜው ከ ዓመት ዝቅ ብሎ የሚኘው ሁሉ ተቋርጦ በሚገኝበት ወቅት አዲሱ የይርጋ ጊዜ ዓመት ነው ማለት ሕግ አውጪው ለተለያዩ ክሶች የተለያየ የይርጋ ጊዜ የሰጠውን እንደመለወጥ የሚቀጠር ነው ስለሆነም የፌዴራል ጠፍቤት ክሱ በይርጋ አልተቋረጠም በማለት የሰጠው ውሣኔ ለድንጋጌው ተገቢውን ትርጉም ባለመስጠት ስለሆነ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ተሰጥቷል ውሣኔ የፌዴራል ጠፍቤት በመቁ በሚያዝያ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯል ተጠሪ የይርጋ ጊዜው ከተቋረጠ በላ ክሱን በንግድ ሕግ ቁጥር ላይ እንደተመለከተው በ ዓመት ጊዜ ማቅረብ ሲገባው ይህ ጊዜ ካለፈ በኋላ ያቀረበው ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆን የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት በዚሁ መሠረት ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ ስለሆነ አጽንተነዋል መጨ ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤኃ የሰበር መቁ ግንቦት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ አሰግድ ጋሻው መድሕን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ በላቸው አንሺሶ አመልካች ቴሌኮሚኒኬሽን ኮርፖሬሽን ቀረቡ ተጠሪ አቶ ጫሊ ሐሰን ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረው በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ መጀመርያ ደረጃ ፍቤት ሲሆን የአሁኑ ተጠሪ ባቀረቡት የክስ ማመልከቻ ድርጅቱ ከ ዓም ጀምሮ ያደረገውን የደመወዝ ጭማሪ በድምሩ ብር ከሐምሌ ወር ዓም ጀምሮ የተደረገውን የደመወዝ ጭማሪ በድምሩ ብር ከሚያዝያ ሰኔ ያልተከፈለኝ የትራንስፖርት አበል ብር ዐዐ በድምሩ ብር ከወለድ ጭምር እንዲከፍለኝ ይወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል የአሁኑ አመልካች ደግሞ በሰጠው መልስ ከሣሽ ያቀረቡት የክፍያ ጥያቄ ወር ያለፈበት በመሆኑ በአዋጅ ቁጥር አንቀፅ መሠረት በይርጋ ይታገዳል ቦነሱና ሌላው ጥቅማጥቅምን በተመለከተም ከሣሽ ክፍያው እንዲከፈላቸው የጠየቁት በሥራ ላልነበሩበት ጊዜ በመሆኑ ጥያቄው ተቀባይነት የለውም በመሆኑም ክሱ ውድቅ ሊሆን የሚገባው ነው በማለት ተከራክረዋል ፍቤቱም ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ አንድ ሠራተኛ ለስድስት ወር የሥራ ከሆነ ለበጀት ዓመቱ የተፈቀደውን ጭማሪና ቦነስ እንደሚያገኝ በሕብረት ስምምነቱ የተደነገገ በመሆኑ ድርጅቱ በክሱ የተጠቀሰውን ገንዘብ ለከሣሽ ይክፈል በማለት ወስኗል በድርጅቱ ስለቀረበው የይርጋ ጥያቄ ግን ምንም ሣይል አልፎታል ይግባኝ የቀረበለት በጉራጌ ዞን የወልቂጤ አካባቢ ከፍተኛ ፍቤትም የግራ ቀኙን ክርክር ከተመለከተ በላ ከሣሽ በሌሉበትና ለኮርፖሬሽኑ እድገትና ብልጽግና ያደረጉት አስተዋፅኦ ሣይኖር ሊከፈላቸው የሚገባ የደመወዝ ጭማሪም ሆነ የቦነስ ክፍያ የለም በ ዓም በጀት ዓመት የተደረገው የደመወዝ ጭማሪም ሆነ የቦነስ ክፍያ ሊከፈላቸው አይገባም በሌላ በኩል ግን ከሣሽ ከደርጅቱ ከመሰናበታቸው በፊት በ ዓም ለአሥራ አንድ ወራት ያክል በድርጅቱ የሠሩ በመሆኑ የሥር ፍቤት ድርጅቱ በዚሁ ዓመት ለሌሎች ሠራተኞች የከፈለውን የደመወዝ ጭማሪና ጥቅማጥቅም ለከሣሽም እንዲከፍል በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ ነው በመሆኑም ድርጅቱ የ ዓም የደመወዝ ጭማሪና ቦነስ ለከሣሽ እንዲከፍል በማለት የመደፍቤቱን ውሣኔ በማሻሻል ወስኗል በአመልካች ስለቀረበው የይርጋ ክርክር ደግሞ ምንም ሣይል አልፎታል አመልካች ያቀረበው የሰበር አቤቱታም ይህን በጉራጌ ዞን የወልቂጤ አካባቢ ከፍቤት የሰጠውን ውሣኔ ለማስለወጥ ሲሆን ቅሬታውም ፍቤቱ የይርጋ ክርክሬን ወደጎን በመተው የ ዓም የደመወዝ ጭማሪና ቦነስ ለአሁን ተጠሪ እንድከፍል የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት የ ዓም ክፍያ ተከፍሎ የተጠናቀቀው በጥቅምት ወር ዓም ሲሆን ክሱ ደግሞ የቀረበው ጥቅምት ቀን ዓም ልክ በዓመቱ ነው ክሱ የስድስት ወር ጊዜ ሣያልፍ መቅረብ ሲገባው የቀረበው በዓመቱ በመሆኑ ጥያቄው በአዋጅ ቁጥር አንቀፅ መሠረት በይርጋ ቀሪ መሆን አለበት በመሆኑም የሥር ፍቤት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ሊሻር ይገባዋል የሚል ነው ተጠሪው ደገሞ በሰጡት መልስ በጊዜው ክስ ላቀርብ ያልቻልኩት ያለአግባብ ተሰናብቻለሁ ወደሥራ ልመለስ ይገባል የሚል ክስ አቅርቤ ስለነበረ ነው ወደሥራ ከተመለስኩኝ በኋላም ክፍያው እንዲከፈለኝ በተደጋገሚ ጥያቄ አእያቀረብኩኝ ስለነበር ክሱ በይርጋ አይታገድም የሥር ፍቤቶች የሰጡት ውሣኔም መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለበትም በመሆኑም ውሣኔው ሊፀናልኝ ይገባል በማለት ተከራክረዋል በበኩላችን ደግሞ ክሱ በይርጋ ቀሪ መሆን የሚገባው ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም የ ዓም የደመወዝ ጭማሪ የተከፈለው ጥቅምት ዓም በመሆኑና ክሱ ደግሞ የቀረበው በጥቅምት ወር ዓም በመሆኑ ጥያቄው በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋ ቀሪ መሆን ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል። ወደ ሥራ ከተመለስኩም ከግንቦት ቀን ዓም ጀምሮ እንዲከፈለኝ እጠይቅ ነበር ያሉትም ቢሆን በድርጅቱ ጥያቄው ተቀባይነት ያላገኘ በመሆኑ የይርጋ ጊዜውን የሚያቋርጥ አይደለም በመሆኑም የሥር ፍቤቶቹ ክሱ በይርጋ የሚታገድ ሆኖ እያለ የ ዓም የደመወዝ ጭማሪና ቦነስ ለተጠሪው እንዲከፈል በማለት የሱጡት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትና መታረም የሚገባው መሆኑን ተገንዝበናል የ ዓም እና የ ዓም ክፍያን በተመለከተ ደግሞ ተጠሪው መስቀለኛ የሰበር አቤቱታ ያቀረቡበት ባለመሆኑ እንዲሁ መታለፍ የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አካባቢ ከፍተኛ ፍሃቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔና የወልቂጤ ከተማ መደፍቤት በመቁ ዐዐዐዐ የካቲት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽረዋል ይፃፍ የሥር ፍቤቶች ክሱ በይርጋ ቀሪ ሊሆን የሚገባው ነው በማለት መወሰን ሲገባቸው በቀረበው የይርጋ ጥያቄ ምንም ሣይሉ ማለፋቸውና ክፍያው እንዲፈፀም በማለት የሰጡት ውሣኔ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ሥር የተደነገገውን የይርጋ ሕግ የሚጋፋ በመሆኑ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት ወስነናል ይፃፍ ወጪና ኪሣራን በተመለከተ ግራ ቀችኙ እንዲቻቻሉ ብለን መዝገቡን ዘግተን ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ተወ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድህን ኪሮስ አሊ መሐመድ አመልካችፁ መሐመድ አብደላ ቀረቡ ተጠሪ የድሬደዋ ኢትዮ ጅቢቲ ምባቡር አልቀረበም ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበው አሠሪው የሥራ ውሉን ለማቋረጥ ያለው መብት የሚቋረጥበት የጊዜ ገደብን የሚመለከት ጉዳይ ነው ተጠሪ በፌመደረጃ ፍቤት ያላግባብ ከሥራ መሰናበታቸውን ጠቅሰው ለስንብቱ ምክንያት የሆነው ጉዳይም ከታወቀ አንድ ወር ያለፈው በመሆኑ ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ክስ አቅርበዋል ፍቤቱም አመልካች ፈፀሙት የተባሉው ድርጊት ከታወቀ ከዐ ቀናት በኋላ የተወሰደው የሥራ ውል ማቋረጥ እርምጃ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ተቀባይነት የለውም ሲል አመልካች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ወስኗል ጉዳዩ በይግባኝ ለፌከፍተኛ ፍቤት ቀርቦ ፍቤቱ ችግሩ መኖሩ ከተረጋገጠበት ቀን ጀምሮ የሥራ ውሉ እስከተቋረጠበት ቀን ድረስ ዐ የሥራ ቀናት ስለማያልፍ የአሠሪው መብት በይርጋ አይቋረጥም ሲል የሥር ፍቤትን ውሣኔ ሽሮ በፍሬ ጉዳዩ ላይ አከራክሮ የመሠለውን እንዲወስን ጉዳዩን ለሥር ፍቤት መልሷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ ውሣኔ ላይ ነው የአመልካችም ቅሬታ በተጠሪ ድርጅት ቅዳሜ ቀን የሥራ ቀን በመሆኑ የገዜ ገደቡ አልፏል የሚል ነው ይህ ችሎትም መዝገቡን አንደሚከተለው መርምሯል በዚህ ጉዳይ ክርክር ያስነሣው አመልካች ፈፀሙ የተባለውን ድርጊት ምክንያት በማድረግ ተጠሪ ከሥራ ለመባረር ያለው መብት በይርጋ ቀሪ ሆኗል አልሆነም የሚለው ነጥብ ነው የፌከፍተኛ ፍቤት አመልካች ፈፀሙ የተባለው ድርጊት የታወቀው እኤአ በፌብሩዋሪ ቀን ዓም ቅዳሜ ወይም በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር የካቲት ቀን ዓም መሆኑንና አመልካች ከሥራ የተሰናበቱት እኤአ ኤፕሪል ቀን ዓም መሆኑን አረጋግጧል ከዚህም በመነሣት ድርጊቱ ከታወቀበት ቀን ጀምሮ የስንብት ደብዳቤው እስከተሰጠበት ቀን ድረስ ያለው ቅዳሜና እሁድን እንዲሁም የበዓላትን ቀን ሳይጨምር ቀን ብቻ ስለሆነ አሠሪው የስንብት እርምጃ የመውሰድ መብቱ በይርጋ አይቋረጥም ብሏል ይህ ችሎት ለግራ ቀኙ ባደረገው የቃል ክርክር የተጠሪ ሠራተኞች በሣምንት ሰዓት የሚሠሩ መሆኑን አረጋግጧል በቀን ሰዓት እየተሠራ በሣምንት ሰዓት ሊሠራ የሚችለውም በሣምንት ቀናት ሲሠራ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል በመሆኑም የተጠሪ መቤት የሥራ ቀን ቅዳሜንም የሚጨምር መሆኑን ተገንዝበናል ስለሆነም ድርጊቱ ተፈፀመ ከተባለበት እኤአ ፌብርዋሪ ቀን ዓም ጀምሮ የስንብት ደብዳቤው እስከተሰጠበት እኤአ እስከ ኤፕሪል ቀን ዓም የፌከፍተኛ ፍቤት ባረጋገጠው መሠረት አርባ ሁለት ቀናት ያሉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ቅዳሜና እሁዶች እንዲሁም አንድ የበዓል ቀን ነበር ስለሆነም ካሉት ቀናቶች ውስጥ በተጠሪ መሥሪያ ቤት የነበረው የሥራ ቀን መሆኑን ተገንዝበናል በዚህም ምክንያት አመልካች ፈፀሙ የተባሉት ድርጊት ከታወቀበት ቀን ጀምሮ ተጠሪው የሥራ ውሉን የማቋረጥ መብቱን በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ እንደሚያዘው በዐ ቀናት ውስጥ ያልተጠቀመበት በመሆኑ በይርጋ ቀሪ ይሆናል የፌከፍተኛ ፍቤትም በተጠሪ መቤት ቅዳሜ ዕለት የሥራ ቀን መሆኑን ግንዛቤ ሣያስገባ የደረሰበት ውሣኔ ስህተት ሆኖ ተገኝቷል ነዓ ውሣኔ የፌመደረጃ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል የፌከፍተኛ ፍት በመቁ ዐ ግንቦት ቀን የሰጠው ውሣኔ ተሽሯራል ግራ ቀኙ ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ዐ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ አመልካች ደምስ ጥበበሥላሴ ቀርቧል ተጠሪ ቴዎድሮስ ጥበበሥላሴ ወኪል ቀርባለች መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የውርስን ጥያቄ መነሻ ያደረገ ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀመረበት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሣሽ የነበረው የአሁኑ ተጠሪ ነው በአመልካች ላይ ክስ የመሠረተውም የሁለታችን አባት የሆኑት አባ ጥበበሥላሴ ካሣሁን ስለሞቱ ወራሽነቴ ተረጋግጧል የውርስ ሀብቱ ግን ያልተከፋፈለ በመሆኑ የውርስ አጣሪ ይሾምልን በማለት ነው አመልካችም ለክሱ በሰጠው መልስ ጥያቄው በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት ተከራክሪል በመጨረሻም ፍቤቱ ክርክሩን ከመረመረ በኋላ ጥያቄው በይርጋ ቀሪ አልሆነም በማለት ወስኗል በዚህ ውሣኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ውሣኔው ጉድለት የለበትም በማለት ይግባኙን ሰርዛል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው እኛም አመልካች ሐምሌ ቀን ዓም በፃፈው ማመልከቻ ያቀረበውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው አመልካች ያነሳው የይርጋ መቃወሚያ ውድቅ የተደረገው በሕግ አግባብ ነው ወይ የሚለውን ነጥብ መመርመር ያለበት ሆኖ በመገኘቱ ነው በዚህ መሠረትም ይህ ነጥብ ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ፓፖ ከስር ጀምሮ ከተደረገው ክርክር መገንዘብ እንደቻልነው አመልካች የይርጋ መቃወሚያውን ያነሳው ተጠሪ ክሱን ያቀረበው አባታችን ከሞቱ ከስምንት ዓመት በላ ነው በሌላ ሰው እጅ ያለአግባብ ተይዞ የነበረውን የውርስ ሃብት ብቻዬን ተከራክሬ በማስለቀቅ ለስምንት ዓመት ሙሉ በይዞታዬ ሥር የያዝኩት በመሆኑ አሁን አካፍል ልባል አይገባም በማለት ነው በአርግጥም ተጠሪ ክሱን ያቀረበው በአመልካች ክርክር የተነገረው ሁሉ ከተከናወነ በኋላ ስለመሆኑም አልተካደም የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ተቃውሞውን ውድቅ ያደረገው የይርጋውን ድንጋጌ የያዘው የፍብሕግ ቁ ዐዐዐ ተገቢነት የሚኖረው የውርስ ዛሃብቱ የተያዘው ትክክለኛ ወራሽ ባልሆነ ሰው ሲሆን ነው አመልካች ግን የስር ተከሣሽ ትክክለኛ ወራሽ ነው የሚል ምክንያት በመስጠት እንደሆነ ከውሣኔው ለመመልከት ችለናል እንደምንመለከተው አከራካሪው ጉዳይ ከውርስ ሃብት ክፍፍል ጋር የተያያዘ ነው አመልካች እና ተጠሪ የአንድ አባት ልጆች ናቸው እየተከራከሩ ያሉት አባታቸው በተውት የውርስ ዛብት ላይ ነው ስለ ውርስ ወይም አወራረስን በተመለከተ ተገቢነት ያለው ሕግ በፍትሐብሔር ሕጉ በአንቀጽ አምስት ሥር ያሉትን ድንጋጌዎች አጠቃሎ የያዘው የሕጉ ክፍል ነው በዚህ አንቀጽ ሥር ያሉት ከቁጥር እስከ ድረስ ያሉት ድንጋጌዎች እንደየአግባቡ ከውርስ ጋር ተያይዘው ለሚነሱት ክርክሮች መፍቻ የሚውሉ ወይም አግባብነት ያላቸው ናቸው የፍብሕግ ቁ ዐዐዐም ከነዚሁ አንዱ ነው በመሆኑም አግባብነቱ በወራሾች መካከል ለሚነሳው የይርጋ መቃወሚያ ክርክር እንደሆነ የሚያከራክር አይደለም አግባብነት የማይኖረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ካለው በተቃራኒው ማለትም አንደኛው ተከራካሪ ወገን ወራሽ ባልሆነበት ጊዜ ነው አውነታው ይህ ከሆነ ደግሞ የስር ፍቤቶች ለፍብሕግ ቁ ዐዐዐ የሰጡት ትርጉም ትክክል አይደለም ማለት ነው ሌላው ለጉዳዩ አወሳሰን አግባብነት ያለው ድንጋጌ የፍብሕግ ቁ ነው ይህ ድንጋጌ ሟቹ ከሞቱ ከአምስት ዓመት በኋላ ስለውርስ ክፍያ አመዳደብ ወይም ድልድል በማናቸውም አስተያየት ቢሆን መቃወሚያ ማቅረብ አንደማይቻል ያመለክታል በያዝነው ጉዳይ እንደምናየው አመልካች በፍብሕግ ቁ እንደተደነገገው ያለ አንዳች ፎርማሊቲ የውርስ አጣሪነት መብት አለው በዚህ መሠረትም የውርሱ ዛብት የሆነውን ንብረት ካለበት ፈልጎና ይዞት ከነበረው ሰው አስለቅቆ በራሱ ይዞታ ስር አድርጎታል በዚህ አይነት ሁኔታም ለስምንት ዓመት ያሕል ቆይቶአል አመልካች ንብረቱን የያዘው ለኔ የሚገባ የውርስ ሃብት ነው በሚል እንደሆነ መገመት የሚያስቸግር አይደለም ተጠሪ ግን ይህ ንብረት ለኔም የሚገባ የምወርሰው ዛፃብት ነው ወይም አመልካች ብቻውን ሊይዘው አይገባም የሚል ጥያቄ ሳያነሳ ለ ስምንት ዓመት ያክል ቀይቶአል በመሆኑም የጊዜ ገደቡ ካለፈ በላ ያቀረበው የውርስ ዛብት ክፍፍል ጥያቄ በአምስት ዓመቱ ይርጋ ቀሪ ሆኖአል ሲጠቃለል የተጠሪ የውርስ ፃብት ክፍፍል ጥያቄ በፍብሕግ ቁ ዐዐዐ በተመለከተው የሦስት ዓመትም ሆነ በፍብሕግ ቁጥር በተቀመጠው የአምስት ዓመት የጊዜ ገደብ በይርጋ ቀሪ ሆኖአል ስለዚህም አቤቱታ የቀረበበት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው ለማለት ችለናል ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ ዐዐ ግንቦት ቀን ዓም ተስጥቶ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም በሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሣኔ ትዕዛዝ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽራል ተጠሪ ያቀረበው የውርስ ይጣራልኝ ክስ በይርጋ ቀሪ ሆኗል ብለን ወስነናል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግን ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ታህሣሥ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታፈሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ወሮ እማዋይሽ አበራ ተጠሪ ወሪት እልፍነሽ ሸዋዬ ጠበቃ ዳኝ ረዳ ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ በውርስ ፃብት ክፍፍል ላይ ተመስርቶ የቀረበን ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀመረበት በትግራይ ብክመበምስራቃዊ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ከሳሽ የነበረችው የአሁንዋ ተጠሪ ስትሆን ከአባትዋ በውርስ አገኘሁ ያለችውን ንብረት እንዲያካፍሉዋት በአሁንዋ አመልካችና በሌሎች ሁለት ሰዎች አህቶችዋ ላይ ክስ መስርታ ክርክሩ ተሰምቶአል በመጨረሻም ተጠሪ ለክሱ ምክንያት ከሆነው ንብረት ላይ ድርሻዋን ትውሰድ ተብሎ ተወስኖአል በሌላ በኩል ደግሞ አመልካች በተሰጠው ውሣኔ ላይ ባለመስማማት ለክልሉ ጠፍቤት ይግባኝ አቅርባ ክርክሩ በድጋሚ ከተሰማ በኋላ በከፍተኛው ፍቤት የተሰጠው ውሣኔ ፀንቶአል ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት ተብሎ እንዲሻር በሚል ለክልሉ ጠፍቤት ሰበር ችሎት የቀረበው አቤቱታም ተቀባይነት አላገኘም አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው ይህ የሰበር ችሎት አመልካች ሐምሌ ቀን ዓም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርቦ ክርክሩን ሰምቶአል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው አመልካች ይርጋን መሠረት በማድረግ ያቀረበችውን መቃወሚያ ውድቅ የመሆኑን አግባብነት ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ይህን ነጥብ በግራ ቀኝ ወገኖች ከቀረበው ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ቀደም ሲል እንደተገለፀው ክርክሩ የውርስ ንብረት ክፍፍል የሚመለከት ሆኖ ተጠሪ ያቀረበችው የድርሻዬን ይሰጠኝ ክስ የይርጋ መቃወሚያ ቀርቦበታል የስር ፍቤቶች በሰጡአቸው ውሣኔዎች ላይ እንደተመለከተው የተጠሪ አባት ማለትም የንብረቱ የቀድሞ ባለሃብት የሞቱት በ ዓም ሲሆን ተጠሪ የውርስ ንብረት ይገባኛል ክስ የመሠረተችው ደግሞ በ ዓም ነው ፍቤቶቹ በአመልካች በኩል የቀረበውን የይርጋ ክርክር ውድቅ ያደረጉት ከሣሽ ክሱን ያቀረበችው በፍብሕግ ቁ ዐዐዐ የተመለከተው የ ዓመት የጊዜ ገድብ ከማለፉ በፊት ነው የሚል ምክንያት በመስጠት እንደሆነም ተገንዝበናል እንደምናየው የተጠሪ አውራሽ በሞቱበት እና ክሱ በቀረበበት ጊዜ መካከል ያሉት ዓመታት ሲቆጠሩ ከዐ ዓመት በላይ አልፎአል ወራሽ የሆነው ሰው በሌላ ሰው የተያዘበትን የውርስ ዛብት ለማስመለስ ክስ መመስረት እንደሚችል በሕጉ የተመለከተ ቢሆንም የፍብሕግ ቁ ክሱን የሚያቀርብበት ጊዜ ግን በሕግ ተወስኖአል ከሣሹ መብቱንና የውርሱ ንብረቶች በተከሣሹ መያዛቸውን ካወቀ ሦስት ዓመት ካለፈ በኋላ ስለወራሽነት ጥያቄ የሚያቀርበው ክስ ተቀባይነት እንደሌለው በፍብብሕግ ቁ ዐዐዐ ተመልክቶአል በተያዘው ጉዳይ ተጠሪ ይመለስልኝ የምትለው የውርስ ዛፃብት አመልካች እንድትመልስላት ክስ የመሠረተችው በአመልካች መያዙን ካወቀች የሦስት ዓመት ጊዜ ከማለፉ በፊት ነው የሚል በፍሬ ነገር ረገድ የቀረበ ክርክር የለም ይልቁንም ተጠሪ ክሱን የመሠረተችው የሦስት ዓመት ጊዜ ካለፈ በኋላ አንደሆነ ነው በሥር ፍቤቶች ጭምር ግንዛቤ የተወሰደው በዚህ ዓይነት ሁኔታ በሕጉ የተመለከተው የሦስት ዓመት የጊዜ ገደብ ካለፈ ደግሞ ወደ ዓመት የሚኬድበት ምክንያት የለም በፍብሕግቁ ዐዐዐ የተመለከተው የ ዓመት የጊዜ ገደብ አስፈላጊ የሚሆነው በንኡስ ቁ በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት ለጉዳዩ እልባት መስጠት የማይቻል ሆኖ በተገኘ ጊዜ ነው ሲጠቃለል ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበችው ክስ በሕጉ በተመለከተው የሦስት ዓመት የይርጋ ጊዜ ቀሪ ሆኖአል በመሆኑም ክሱ በይርጋ ቀሪ አልሆነም በሚል በስር ፍቤቶች የተሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት በትግራይ ብክመ በምስራቃዊ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐ በሕዳር ቀን ዓም በክልሉ ጠፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም እና በክልሉ ጠፍቤት ሰበር ችሎት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽረዋል ተጠሪ ያቀረበችው የውርስ ንብረት ይሰጠኝ ክስ በይርጋ ቀሪ ሆኖአል ብለናል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ ሠልጣን አባተማም አመልካች የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት ነፈ ቀረበ ተጠሪ አቶ ግርማ ተገኝ ጠበቃ ቀርበዋል መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የጉዳዩ አመጣጥ መጀመሪያ የአሁኑ ተጠሪ ከየካቲት ወር ዓም ጀምሮ ለሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ስለተደረገላቸው ለእኔም ሊደረግልኝ ይገባል በማለት ግንቦት ቀን ዓም በተፃፈው ማመልከቻ ለፌመደፍቤት ክስ ያቀርባሉ የአሁኑ አመልካችም ከሥራ የተሰናበትከው በ ዓም በመሆኑ የደመወዝ ጭማሪ ጥያቄህ በይርጋ ይቋረጣል በማለት መቃወሚያ ያቀርባል ፍቤቱም ይህን መቃወሚያ በመቀበል ክሱ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋ የሚቋረጥ ነው ሲል ክሱን በመሠረዝ መዝገቡን ዘግቶታል በመቀጠልም የአሁኑ ተጠሪ ለፈከፍቤት ይግባኝ ስላቀረቡ ፍቤቱ ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋው ተጠያቂ የሆነው ሰው ወይም ወገን የሌላውን መብት በጽሑፍ ሲያውቅለት ተብሎ በተደነገገውን መሠረት ሲታይ በሕብረት ስምምነቱና በደመወዝ ስኬል አፈፃፀም መመሪያው ሠራተኛው ከተጠያቂነት ነፃ መሆኑ ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ የኋላ ቀሪ ክፍያ የሚያጠቃልል የደመወዝ ጭማሪ ሊያገኝ ይችላል ተብሎ ስለተደነገገ ይህ ድንጋጌ የይርጋውን ጊዜ ያቋርጠዋል በመሆኑም የሥር ፍርድ ቤት ክሱን በመቀበል ግራ ቀኙን አከራክሮ የመሰለውን እንዲወስን በማለት ይወስናል የሰበር አቤቱታውም ሊቀርብ የቻለው በዚሁ የከፍተኛው ፍቤት ውሣኔ ቅር በመሰኘት ነው የሰበር አመልካች ያቀረበው ቅሬታ ተጠሪው ያቀረቡት የተጨማሪ ደመወዝና የጥቅማጥቅም ጥያቄ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋ ቀሪ የሚሆን በመሆኑ ክሱ ተቀባይነት የለውም በማለት ብንከራከርም የከፍተኛው ፍቤት ይህን የመቃወሚያ ክርክራችንን ውድቅ በማድረግ የሥር ፍቤቱን ትፅዛዝ በመሻር ክሱ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋ ቀሪ አይሆንም በማለት መወሰኑ አግባብ አይደለም ድርጅቱ ለተጠሪው ይርጋውን ለማቋረጥ የሚችል በጽሑፍ ያወቀለት መብት የለም በሕብረት ስምምነቱና በደመወዝ ስኬል አፈፃፀም መምርያውም ይህን የሚያረጋግጥ ድንጋጌ የለም በመሆኑም የሥር ፍቤቱ ውሣኔ ተሽሮ ክሱ በይርጋ ቀሪ የሚሆን ነው ተብሎ እንዲወስንልን የሚል ነው ይህ የፌጠፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም የሰበር አቤቱታውን በመመርመር የስር ፍቤት ክሱ በይርጋ አይታገድም በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ መሆን ያለመሆኑን ለመመርመር እንዲቻል አቤቱታው ያስቀርባል በማለት ተጠሪ መልሳቸውን እንዲያቀርቡ አዛል ተጠሪም ጥር ቀን ዐዐዐ ዓም ጽፈው ባቀረቡት መልስ በሕብረት ስምምነታችን አንቀጽ እና መሠረት እንዲሁም በድርጅቱ የደመወዝ ስኬል አፈፃፀም መመሪያ ከ ዓም ጀምሮ በሚሠራበትና በ ዓም በሥራ አመራር ቦርዱ በተሻሻለው መመሪያ ቁጥር እና በቁጥር መሠረት አንድ ሠራተኛ በጥፋት ምክንያት በክርክር ላይ እያለ የደመወዝ ጭማሪ መጠየቅ እንደማይችል ነገር ግን ተጣርቶ ከጥፋቱ ሙሉ በሙሉ ነባ መሆኑ ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ የደመወዝ ጭማሪውን ያለፈ ውዝፍ ክፍያም ጭምር ማግኘት እንደሚችል ተደንግጓል እኔም የተሰናበትኩት በአግባቡ ያለመሆኑን ተረጋግጦ ስንብቱ ሕገወጥ ነው ተብሉ ስለተወሰነልኝ ውሣኔ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ስድስት ወር ሳይሞላ ነው ክሱን ያቀረብኩት በመሆኑም ክሱ በይርጋ አይቋረጥም ተብሎ በፌከፍቤት የተሰጠው ውሣኔ የሚነቀፍበት የሕግ ምክንያት ባለመኖሩ ውሣኔው ይጽናልኝ በማለት ተከራክረዋል አመልካች ድርጅትም የመልስ መልሱን በማቅረብ ክርክሩን ለማጠናከር ሞክሯል በበኩላችን ደግሞ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሊሆን ይችላል ወይስ አይችልም የሚለውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነውም ሐምሌ ዐ ዓም በወጣው የሕብረት ስምምነት በአንቀጽ የደመወዝ ጭማሪ በሚሰጥበት ወቅት በጥፋት ምክንያት በጊዜያዊ እገዳ ላይ የሚገኝ ሠራተኛ በዚህ የሕብረት ስምምነት መሠረት የደመወዝ ጭማሪ ለማግኘት የአስተዳደር ውሣኔ የማያግደው ከሆነ ጭማሪውን ከተፈቀደበት ጊዜ ጀምሮ ያገኛል ተብሎ የተደነገገው የአስተዳደር ውሣኔው ሊያግደው ይችላል ወይስ አይችልም የሚለውን ቅድመ ሁኔታ ከተመለከቱ በኋላ የሚታይ እንጂ በቀጥታ የደመወዝ ጭማሪን ለማግኘት በሚፈቅደው መንገድ አይደለም በሌላ በኩል ደግሞ ምንም እንኳን በድርጅቱ የደመወዝ ስኬል የአፈፃፀም መመሪያ በአንቀጽ ዐ በዲስፕሊን ጉድለት ወይም በሌላ ጥፋት ምክንያት በሕብረት ስምምነት ወይም በሥራ አመራር አባላት የአስተዳደር ደንብ መሠረት በቅጣት የሪከርድ የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች የሪከርድ የጊዜ ገደቡ እስኪያበቃ ድረስ የደመወዝ ጭማሪ እንዳይሰጣቸው ተከልክለው የቆዩት ሠራተኞቹ ፈፀሙት የተባለው ድርጊት ተጣርቶ ከተጠያቂነት ሙሉ በሙሉ ነፃ መሆናቸው ከተረጋገጠ ወይም የደመወዝ ጭማሪ እንዳይሰጣቸው በአስተዳደር ውሣኔ ካልተወሰነ ከተጠያቂነት ነዛባ መሆናቸው ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ ብቻ የኋላ ቀሪ ክፍያን የማያጠቃልል የደመወዝ ጭማሪ ሊያገኙ ይችላሉ ተብሎ ቢደነግግም ይህ ድንጋጌ የሚመለከተው ከድርጊታቸው ከተጠያቂነት ነፃ ከወጡ በኋላ በዚያው ድርጅት መሥራት የሚቀጥሉ እንደሆነ ብቻ ስለመሆኑ ሰኔ ቀን ዓም ተሻሸሎ በወጣው የደመወዝ አስኬል አፈፃፀም መመሪያ አንቀጽ ለ ስለተደነገገና ተጠሪው ደግሞ ይህን የደመወዝ ጭማሪ ክስ ከማቅረባቸው በፊት ጥር ቀን ዓም በዋለው ችሎት በፌመደፍቤት በሥራ ክርመቁ የተሰጠው ውሣኔ ተጠሪው ካሣ ተከፈሎአቸው ከድርጅቱ እንዲሰናበቱ የተወሰነ በመሆኑ ተጨማሪ ደመወዙን የሚጠይቁበት የሕግ ምክንያት የለም በመሆኑም እነዚህ ተጠሪው በሰበር መልሳቸው የጠቀሱዋቸውና የሥር ፍቤትም ለውሣኔው መሠረት ያደረጋቸው የሕብረት ስምምነቱና የደመዝ ስኬል አፈፃፃም መመሪያ አንቀፆች ለተጠሪው መብት የሚሰጡ ባለመሆናቸው የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ጊዜውን ለማቋረጥ ምክንያት የሚሆኑበት መንገድ የለም የሥር ፍቤትም በሰጠው ውሣኔ ድርጅቱ ለከሣሹ የአሁን ተጠሪ መብታቸው በጽሑፍ ያወቀላቸው በመሆኑ ክሱ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋ ቀሪ የሚሆንበት ምክንያት የለም በማለት የፌከፍቤት የሰጠውን ትፅዛዝ በመሻሩ መሠረታዊ የሕግ ስህተት መፈፀሙ ተረጋግጧል ውሣኔ ከፍፍቤት በመቁ ዐ ሐምሌ ቀን ዓም የተሰጠው ውሣኔ ተሽራል የፌመደፍቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ ፀንቷል ይፃፍ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በይርጋ ቀሪ ሆኗል ይፃፍ ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መቤት ይመለስ የማይነበብ የሦስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ ዐ መጋቢት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ ሒሩት መለሠ መድህን ኪሮስ ዓሊ መሐመድ ፀጋዬ አስማማው አመልካች እልፍነሽ አማረ ወኪል ቀረቡ ተጠሪ አቶ ግርማ አማረ ቀረቡ ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው የሰሜን ሸዋ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት ነው ተጠሪ ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ አመልካች የጋራ አእናተቸውን የውርስ ሀብት ይዘው ስለሚገኙ የንብረቶቹን ግማሽ አርባ ሰባት ሺ ሰባት መቶ ሰላሳ ሰባት ከፃምሳ እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል አመልካችም በሰጡት መልስ የግራ ቀኙ እናት የሞቱት ግንቦት ቀን ዓም ስለሆነ ከሞቱ ዓመት በላ የቀረበው ክስ በይርጋ ይቋረጣል በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ ያየው ፍቤትም የተጠሪ ጥያቄ የበፍሕቁ ዐዐዐ መሠረት በይርጋ ይታገዳል በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል ጉዳዩ በይግባኝ የተመለከተው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ጥያቄው የማይንቀሳቀስ ንብረትን የሚመለከት በመሆኑ የፍሕቁ ዐዐዐ ተፈፃሚነት የለውም ጉዳዩ መታየት የነበረበት ከፍሕቁ ዐዐዐ ጋር ተገናዝቦ ነው በማለት የተጠሪ ክስ በይርጋ ስለማይታገድ የሥር ፍሃቤት በፍሬ ጉዳዩ ላይ አከራክሮ እንዲወስን በማለት ወስኗል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ነው ይህ ችሎትም ተጠሪ የውርስ ንብረት በመካፈል ከ ዓመት በኋላ ያቀረቡት ጥያቄ በይርጋ አይታገድም መባሉ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሎት ያስቀርባል በማለቱ ተጠሪ ቀርበው ጥር ቀን ዐዐዐ ዓም የተዓፈ መልስ አቅርበዋል ችሎቱም መዝገቡን መርምሯል ተጠሪ ክስ የመሠረቱት ከእናታቸው በውርስ ሊተላለፍላቸው የሚገባውን ቤትና ሌሎች ንብረቶች ለመካፈል ነው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ክስ በይርጋ አይታገድም ያለው ተጠሪ ያቀረቡት የውርስ ክፍፍል ጥያቄ የማይንቀሣቀስ ንብረትን የሚመለከት በመሆኑ በፍሕቁ ዐዐዐ መሠረት በይርጋ ቀሪ የሚሆን አይደለም በማለት ነው ይኸው ፍቤቱ የጠቀሰው የፍትሐብሄሩ ድንጋጌ እንደዚሁም ሟች ከሞቱበት ወይም ከሣሹ በመብቱ ለመሥራት ከቻለበት ቀን አንስቶ አሥራ አምስት ዓመት ካለፈው በላ ከዘር የወረደ ርስት ካልሆነ በቀር የተባለው የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን ተቀባይነት አያገኝም በማለት ይደነግጋል በመሆኑም በዚህ ድንጋጌ አኳያ በይርጋ የማይታገደው ከዘር የወረደ ርስት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል እዚህ ላይ ሊነሣ የሚገባው ቤት የማይንቀሣቀስ ንብረት በመሆኑ ርስት ነው ሊባል ይችላል አይችልም የሚለው ጥያቄ ነው በመሆኑም ርስት የሚለው ቃል በፍሕጉ ውስጥ ከተካተቱ ድንጋጌዎች ምን ማለት እንደሆነ ማየቱ ተገቢ ይሆናል በፍሕቁ ዐ የማይንቀሣቀሱ ንብረቶች የመሬት ርስቶችና ቤቶች ናቸው በማለት የስቀምጣል ከዚህም ድንጋጌ ርስት የሚለው ቃል መሬትን የሚያመለክት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል እንደዚሁም ስለ ንብረቶች በሚናገረው የፍብሔር ሕጉ ክፍል የሚገኙት የተለያዩ ድንጋጌዎች ርስትን ከመሬት ጋር የሚያያዙ ሆነው እናገኛቸዋለን ከዚህ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው የአማርኛ መዝገበ ቃላት ርስት የሚለው ቃል ቤተ ዘመድ የሆነ እያረሠ የሚጠቀምበትና ለተወላጅ በውርስ የሚተላለፍ የመሬት አጽመ ርስት የግል ወይም የራስ ይዞ የሆነ ቦታ መሬት በማለት ትርጓሜ ይሠጠዋል በመሆኑም ከተለያዩ የፍሕጉ ድንጋጌዎችም ሆነ ከአማርኛው ትርጉም ርስት መሬት እንጂ ቤትን የማይመለከት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል ወደ ፍሕቁ ዐዐዐ ስንመጣም ከዘር የወረደ ርስት ካልሆነ በቀር የሚለው ሀረግ በተለይ ከፍ ሲል ከተገለፀው የአማርኛ ትርጉም ለተወላጅ በውርስ የሚተላለፍ መሬት ከሚለው ጋር የሚጣጣም መሆኑን እንገነዘባለን ከዚህ ተነስተን ወደተያዘው ጉዳይ ስንመለስም የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍሃቤት ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የሟች ቤት ርስት ነው ወደሚለው መደምደሚያ የደረሰውና ክርክሩ በፍሕቁ ዐዐዐ መሠረት በይርጋ አይቋረጥም በማለት የሰጠው ውሣኔ የሕግ መሠረት ያለው ሆኖ አላገኘነውም ውሣኔ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት በመቁ ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዓም የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል የሰሜን ሸዋ መዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐዐ በሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰመቁ የካቲት ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካችፁ ይስማው ድረስ ቀረበ ተጠሪ ይበልጣል ፍቅር ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቤት ይለቀቅልኝ ጥያቄን መነሻ የደረገ ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ ሲጀመር ከሣሽ የነበረው የአሁነ ተጠሪ ነው በመልካች ላይ ክስ የመሠረተው ከአባቴና እናቴ በውርስ የተላለፈልኝን ቤት ከሕግ ውጪ ይዞብኛል እና ያስረክበኝ በማለት ነው አመልካች ደግሞ ለክሱ በሰጠው መልስ ቤቱ በተጠሪ አባት በውል ገዝቶ በስሙም ግብር እየገበረ ከ ዓመት በላይ ይዞት እንደሚገኝ ገልጾአል ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው በማለትም ተከራክሮአል ክሱን የሰማው ፍቤት የይርጋውንም ሆነ በፍሬ ነገር ረገድ የቀረበውን ክርክር ውድቅ በማድረግ አመልካች ቤቱን ለተጠሪ እንዲያስረክብ ወስኖአል ጉዳዩን በይግባኝ የሰማው የምስራቅ ጎጃም ከፍተኛ ፍቤትም በስር ፍቤት የተሰጠውን ውሣኔ አጽንቶአል እኛም አመልካች ሐምሌ ቀን ዓም በፃፈው ማመልከቻ የቀረበውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው በአመልካች በኩል የቀረበው የይርጋ መቃወሚያ ውድቅ የተደረገበትን አግባብ ለመመርመር ነው በዚህ መሠረትም ይህን ነጥብ ከሥር ጀምሮ ከተደረገው ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ግራ ቀኝ ወገኖች ከስር ጀምሮ ካደረጉት ክርክር አና የሥር ፍቤቶች ከሰጡት ውሣኔ ይዘት መገንዘብ እንደቻልነው አመልካች አከራካሪውን ቤት ሊይዝ የቻለው ከተጠሪ አባት ጋር ባደረገው የቤት ሽያጭ ውል መነሻነት ነው የሽያጭ ውሉ የተደረገው በዐ ዓም ሲሆን ይህን ውል መሠረት በማድረግም አመልካች ቤቱን በይዞታው ስር ከማድረጉም በላይ ቤቱ ለሚገኝበት ከተማ ማዘጋጃ ቤት አቅርቦ በስሙም ግብር ሲከፍል እንደቆየ መዝገቡ ያስረዳል ተጠሪ የቤት ይለቀቅልኝ ክስ የመሠረተው መጋቢት ቀን ዓም ነው እንደምንመለከተው አመልካች ቤቱን የያዘው ከተጠሪ አባት ጋር ባደረገው የሽያጭ ውል መሠረት ነው ገንዘቡንም በወቅቱ ለተጠሪ አባት የከፈለ ስለመሆኑ በክርክሩ ተመልክቶአል ተጠሪ ቤቱ ከመሠረቱ የሱ አይደለም የአባቱን ወራሽነት መሠረት አድርጎ ነው ክሱን የመሠረተው ቀደም ሲል አንደተገለጸው አመልካች ቤቱን የያዘው ከዐ ዓም ጀምሮ ሲሆን ተጠሪው ክስ የመሠረተው ደግሞ በ ዓም ማለትም ከ ዓመት በኋላ ነው ከዚህ የተነሣም ወደክሱ ፍሬ ነገር ከመገባቱ በፊት አመልካች ያቀረበው የይርጋ መቃወሚያ አግባብነት ማየቱ ተገቢ ይሆናልፎ ተደጋግሞ እንደተገለጸው በአመልካች እና በተጠሪ መካከል የውል ግንኙነት የለም የተጠሪ አባት በሕይወት በነበሩበት ጊዜ የውል ይፍረስልኝ ክስ መስርተው ክርክሩ ከመወሰኑ በፊት በመሞታቸው ምክንያት ተጠሪ ተተክቶ የክርክሩ ተካፋይ የሆነ ሳይሆን የወራሽነት መብቱን መሠረት በማድረግ በራሱ ክስ አንደ መሠረተም ተገንዝበናል በመሆኑም አመልካች ያነሳው የይርጋ መቃወሚያ መታየት ያለበት ከፍብሕግ ቁ እና አንፃር ነው በፍብሕግቁ እንደተመለከተው ግዴታው ከውል የተገኘ ባይሆንም በፍትሐብሔር ሕጉ አራተኛ መጽሐፍ በአንቀጽ ስር የተመለከቱት ስለ ውሎች በጠቅላላው የተቀመጡ ድንጋጌዎች ይፈጸሙባቸዋል በእርግጥ የአንዳንድ ግዴታዎችን አመጣጥ ወይም አይነት በመመልከት በተቀጠሰው አንቀጽ ስር ከተመለከቱት ደንቦች የተለዩ ድንጋጌዎች በሕግ ተመልክቶ ከተገኘ እነዚህ በተለይ የተመለከቱት ድንጋጌዎች አግባብነት እንደሚኖራቸው በተጠቀሰው ቁ ተመልክቶአል ወደያዝነው ጉዳይ ስንመለስ ተጠሪ የመሠረተውን ክስ በተመለከተ በተለይ አግባብ ያለው የይርጋ ደንብ የለም ስለዚህም በፍብሕግ ቁ የተደነገገው የአስር ዓመት ገደብ ይርጋ ይፈጸምበታል ክሱ የቀረበው ቤቱ በአመልካች ከተየዘ ከአሥራ ዘጠኝ ዓመት በኋላ በመሆኑም በዚሁ የይርጋ ደንብ ተቋርጧል ማለት ነው አውነታው ይህ ከሆነ ደግሞ የሥር ፍቤቶች በይርጋ ረገድ የቀረበውን የአመልካች መቃወሚያ ውድቅ ያደረጉት የለአግባብ ከሕጉ ውጪ ነው ከዚህ የተነሣም አቤቱታ የቀረበበት ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው ለማለት ችለናል ውሣኔ አቤቱታ የቀረበበት በሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ፍቤት ሚያዝያ ቀን ዓም ተሰጥቶ የምስራቅ ጎጃም አስተዳደር ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐዐ ሰኔ ቀን ዓም በሰጠው ውሣኔ ያፀናው እንዲሁም የአማራ ብክመጠፍቤት በፍብይመቁ ሐምሌ ቀን ዓም በሰጠው ትዕዛዝ የፀናው ውሣኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ተሽሮአል ተጠሪ በአመልካች ላይ የመሠረተው ክስ በይርጋ ቀሪ ሆኖአል በማለት ወስነናል ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የአሰሪና ሰራተኛ ህግ የሰመቁ ኀዳር ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ጌታቸው ምህረቱ አሰግድ ጋሻው ሒሩት መለሠ አብዱራሂም አህመድ አመልካች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ነገረ ፈጅ ልኡል ሰገድ ቀረቡ ተጠሪ እነ አቶ ከበደ ቱሉ ሰዎች ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበው ጉዳይ የጀመረው በሐረሪ መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ነው ተጠሪዎች ለፍቤቱ ባቀረቡት ክስ አመልካች መስሪያ ቤት ያላግባብ ከስራ ስላሰናበታቸው ሕጉ የሚፈቅድላቸውን ክፍያዎች አመልካቹ እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል አመልካች ለቀረበበት ክስ በሰጠው መልስ ተጠሪዎች በጡረታ የተገለሉ ሠራተኞች ሲሆነ የተቀጠሩትም ለተወሰነ ጊዜ ነው የስራ ውሉ የተቋረጠው ተጠሪዎች ለአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ክስ አቅርበው ከጡረታ አበል እና ከደሞዛቸው አንዱን እንዲመርጡ ተወስኖ በዚህ መሠረት ተጠይቀው ጡረታ አበሉን በመምረጣቸው ነው ዘላቂ የጡረታ አበል ክፍያ ያለው ሠራተኛ በአቁ እና አንቀጽ መሠረት የስንብት ክፍያ አይከፈለውም በማለት ተከራክሯል ፍቤቱም በአቁ አንቀጽ ዐ መሠረት የተቀጠሩ መሆናቸውን አመልካች ስላላስረዳ ላልተወሰነ ጊዜ የተቀጠሩ ሠራተኞች ናቸው የጡረታ አበላቸውን ስለመምረጣቸው አላስረዳም የጡረታ አበል ያለው ሠራተኛ ተጨማሪ ስራ እንዳይሰራ አልተከለከለም ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት የተለያየ ክፍያ እንዲከፈላቸው ወስኗል ይግባኝ የቀረበለት የሐረሪ ከፍተኛ ፍቤት መልስ ሰጪዎችን ሳይጠራ ይግባኙን ሰርዞታል የአሁኑ የሰበር አቤቱታም የቀረበው በዚህ ውሣኔ ላይ ነው የአመልካች ቅሬታም ተጠሪዎች የተቀጠሩት ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ነው ይህንንም አላስተባበሉም በአድሜ ምክንያት በጡረታ ስለተገለሉ ላልተወሰነ ጊዜ ሊቀጠሩ አይችሉም የደንብ ልብስ አና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች በገንዘብ ተተምኖ እንዲከፈላቸው የሚፈቅድ ሕግ የለም የሚል ነው ይህ ችሎትም ተጠሪዎች የጡረታ አበላቸውን መርጠው ጡረታቸውን ወስደዋል እየተባለ ከሥራ መሰናበታቸው ከሕግ ውጪ ነው ተብሉ መወሰኑ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱታው ለሰበር ችሉት ቀርቦ እንዲታይ አድርጓል ግራ ቀኙም ክርክራቸውን በጽሁፍ አቅርበዋል ይህ ችሎትም መዝገቡን እንደሚከተለው መርምራሯል ከመዝገቡ ተጠሪዎች በአመልካች መቤት የተቀጠሩት እድሜያቸው ለጡረታ በመድረሱ በጡረታ ከተገለሉ በኋላ መሆኑን ተረድተናል ጡረታ አንድ ሠራተኛ እድሜውን ሙሉ ብቃት ያለው ሠራተኛ ሆኖ እንደማይቀጥል ከአድሜው መግፋት ጋር የሥራ ውጤታማነቱ እንደሚቀንስ ስለሚታመን አድሜውን ሙሉ በተቀጠረበት ስራ ላይ እንዲቀጥል መደረጉ የአሰሪውን ጥቅም ይጎዳል ተብሎ ስለሚታመን ሠራተኛው ከስራ ተሰናብቶ አሰሪው ብቃት ያለው ሠራተኛ በቦታው እንዲተካ ለማስቻል ሠራተኛው በጡረታ የሚገለልበት ስርአት ነው ተጠሪዎች በዚህ መልኩ የጡረታ አድሜአቸው ደርሶ በጡረታ የተገለሉ ናቸው ምንም እንኳን በጡረታ የተገለለ ሰው ስራ መስራት አይችልም የሚባል ባይሆንም አንድ አሰሪ በጡረታ የተገለለን ሠራተኛ በድጋሚ ላልተወሰነ ጊዜ ቀጥሮ ያሰራል ለማለት አይቻልም ከዚህ በተጨማሪ ተጠሪዎች ራሳቸው ለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ባቀረቡት ክስ ለተወሰነ ጊዜ መቀጠራቸውን አምነው ለቋሚ ሠራተኛ የተጨመረው ደሞዝ ለእነሱም እንዲጨመርላቸውና በሌሎችም ጥያቄዎች ላይ ክስ አቅርበው የነበረ መሆኑን ተረድተናል እንግዲህ በአንድ በኩል ተጠሪዎች የተቀጠሩት ለተወሰነ ጊዜ መሆኑን አምነው ሲከራከሩ የነበረ መሆነ በሌላ በኩል ደግሞ አድሜያቸው ለጡረታ ደርሶ ከስራ የተሰናበቱ መሆነ ተዳምሮ ሲታይ አመልካች ተጠሪዎችን የቀጠረው ላልተወሰነ ጊዜ ነው ለማለት አይቻልም የስር ፍቤቶችም ተጠሪዎች የተቀጠሩት ላልተወሰነ ጊዜ ስለሆነ ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት የደረሱበት መደምደሚያ ስህተት ሆኖ ተገኝቷል ለተወሰነ ጊዜ የተቀጠረ ሠራተኛም የተወሰነው ጊዜ ሲያበቃ ሊሰናበት አንደሚችል በአቁ አንቀጽ ተመልክቷል ለተወሰነ ጊዜ የተቀጠረ ሠራተኛ የተወሰነው ጊዜ ከማብቃቱ በፊት የስራ ውሉ ያለበቂ ምክንያት ከተቋረጠ ግን ሠራተኛው የውሉ ጊዜ ወይም ስራ እስኪያቅ ቢቆይ ኖሮ ያገኝ የነበረውን ደሞዝ የሚያሕል ደሞዝ እንደሚከፈለው በአዋጁ አንቀጽ ለ ተመልክቷል ተጠሪዎቹ ደግሞ የተሰናበቱት የውሉ ጊዜ ከማብቃቱ ቀናት በፊት መሆኑን አመልካች ራሱ አምኗል አመልካች ከተጠሪዎች ጋር ባደረግነው የስራ ውል ላይ በተስማማነው መሠረት በአቁ አንቀጽ መሠረት የ ወር ማስጠንቀቂያ በመስጠት ማቋረጥ እችላለሁ ሲል ተከራክሯል ነገር ግን ተፈፃሚነት ያለው አመልካች የጠቀሰው አንቀጽ ሳይሆን አንቀጽ ሲሆን ይህም ቢሆን አመልካቹ የተወሰነው ጊዜ ሳያልቅ ውሉን ለማቋረጥ መብት አይሰጠውም ይህ ከሆነ ሠራተኞቹ ሊከፈላቸው የሚገባው ለቀሪው ቀን ማግኘት የሚገባቸውን ደሞዝ ብቻ ነው ውሣኔ የሐረሪ መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ በታህሣሥ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የተጠሪዎች የሥራ ስንብት ሕገወጥ ነው በማለት የካሣ ክፍያ የደንብ ልብስ በገንዘብ ተቀይሮ እና ክፍያ ለዘገየበት እንዲከፈላቸው የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል በሌላ በኩል ተጠሪዎች በመጨረሻዎቹ ሁለት ዓመት ያልተጠቀሙበት የአመት እረፍት በገንዘብ ተቀይሮ እንዲከፈላቸው እና ኛ እና ኛ ተጠሪዎች ሠርተው ያልተከፈላቸው ቀሪ ደሞዝ እንዲከፈላቸው የሰጠው የውሣኔ ክፍል ብቻ ጸንቷል ነዓ አመልካች ለተጠሪዎች ለእያንዳንዳቸው የ ቀን ደመዛቸውን ይክፈላቸው ወጪና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ለመዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ዐ ታህሣሥ ዐ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ አመልካች አቶ ቢኒያም ገረመው ቀረቡ ተጠሪ የቻይና መንገድና ድልድይ ሥራ ድርጅት ፍርድ ለሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ የጀመረው በደቡብ ጎንደር መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍቤት የፎገራ ወረዳ ፍቤት ነው አመልካች ተሻሽሎ በቀረበ የክስ ማመልከቻ ተጠሪ ከሥራ ያላግባብ ያሰናበታቸው ስለሆነ አዋጁ የሚፈቅድላቸውን ክፍያዎች እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል ፍቤቱም ተጠሪ አመልካችን ከሥራ ያሰናበተው ከሕግ ውጭ በመሆኑ የስንብት ክፍያ የማስጠንቀቂያ ክፍያ የአመት ፈቃድ በገንዘብ ተቀይሮ አንዲሁም የካሣ ክፍያ እንዲከፈላቸው ወስኗል በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ተጠሪ በደቡብ ጎንደር መዞን ከፍተኛ ፍቤት ይግባኙን ያቀረበ ሲሆን ፍቤቱም አመልካች ከስራ የተሠናበቱት በሕገ ወጥ መንገድ መሆኑን በመቀበል የሥር ፍቤት ግን ክሱ እንዲሻሻል ሲያዝ በቂ ምክንያት ያልነበረው በመሆኑና የተጠየቀውን ገንዘብ ከፍ ለማድረግ ብቻ ክስ ሊሻሻል እንደሚችል በፍሥሥሕቁ ስላልተመለከተ አመልካች ክርክሩን ሊቀጥል የሚገባው መጀመሪያ ባቀረበው የገንዘብ መጠን ነው በማለት አመልካች በመጀመሪያ ደረጃ ክስ የጠየቁትን የአገልግሎት ክፍያና የ ወር ደመወዝ ብቻ እንዲከፍላቸው ወስኗል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው ይህንኑ ውሣኔ በመቃወም ነው ይህ ችሎትም ይግባኝ ሰሚው ፍቤት የተሻሻለውን ክስ ውድቅ በማድረግ በመጀመሪያ በቀረበው ክስ መሠረት ውሣኔ መስጠቱ ተገቢ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር አቤቱተው ለሠበር ችሎት ቀርቦ እንዲታይ በማድረግ ተጠሪ ለአቤቱታው መልስ እንዲሰጡ መጥሪያ ልኳል ነገር ግን ተጠሪው መጥሪያ ደርሶት ባለመቅረቡ ችሎቱ መዝገቡን እንደሚከተለው መርምራል ከላይ እንደተገለፀው ጉዳዩን በመጆመሪያ የተመለከተው ፍቤት ውሣኔ የሠጠው የአመልካችን የተሻሻለ ክስ መሠረት በማድረግ ነው ይግባኝ ሰሚው ፍቤት ግን አመልካች በመጀመሪያ ክሣቸው ላይ የጠየቁትን የገንዘብ መጠን ከፍ ለማድረግ ብቻ ክሱ እንዲሻሻል መደረጉ ተገቢ አይደለም በማለት የአመልካችን የመጀመሪያ ክስ መሠረት አድርጎ ውሣኔ ሠጥቷል ይህ ችሎትም ይግባኝ ሠሚው ፍቤት የተሻሻለውን ክስ ውድቅ ለማድረግ የሕግ መሠረት ነበረው ወይ። ሆኖም የሥር ፍርድ ቤት ስድስት ሺ ስምንት መቶ ዘጠኝ ብር ከስልሣ ስምንት ሣንቲም ቀሪ ተከፋይ ሒሣብ እንዳለኝ አምኖ እያለ እንዲከፈለኝ አለመወሰኑ መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት በመሆኑ ይታረምልኝ በማለት የመልስ መልስ ሰጥቷል ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር ግራ ቀኙ ያቀረቡት የጽሑፍ ክርክር ከላይ በአጭሩ የተገለፀው ሲሆን እኛም መዝገቡን መርምረናል መዝገቡን እንደመረመርነው አመልካች ተጠሪው እንዲከፍለው የጠየቀውን የሥራ አገልግሎት ካሣ የሥራ ስንብት ክፍያና የዓመት አረፍት ክፍያ አኔን አይመለከተኝም ከእኛ የሚጠይቀው ገንዘብ የለም በማለት በግልጽ ክዶ አልተከራከረም ተጠሪው በሰበር ያነሣው የይርጋ ጊዜ መከራከሪያም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በውሣኔው ውስጥ ያልገለፀው በመሆኑ በሥር የተነሣ ክርክር መሆኑን ለማረጋገጥ አልተቻለም ተጠሪው የይርጋ ክርክሩን በሥር አንስቶት ከሆነም ጥያቄውን ፍርድ ቤቱ ሲያልፍበት ደረጃውን ጠብቆ በይግባኝ እንዲስተካከል ያላደረገ በመሆኑ ይህ ፍርድ ቤት ሊያስተካክለው አይችልም በመሆኑም ተጠሪው አመልካች የጠየቀውን የሥራ አገልግሎት ክፍያ እና የሰባ ቀን የዓመት እረፍት ክፍያ በግልጽ ክዶ ያልተከራከረ በመሆኑ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት እንዳመነ የሚቆጠር በመሆኑ ተጠሪው ለአመልካች አግባብነት ባለው የህብረት ስምምነትና የሕጉ ድንጋጌ መሠረት የአገልግሎት ካሣ ክፍያና የሰባ ቀን የዓመት እረፍት ክፍያ የመክፈል ኃላፊነት አለበት በሌላ በኩል ተጠሪው የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ መሠረት ከአመልካች የሚጠይቀው ዕዳ እንዳለ ለክሱ ባቀረበው መልስ ገልጂል ከተጠሪው ከአመልካች እፈልጋለሁ ብሎ የጠየቀው ዕዳ ውስጥ አመልካች ብር አስራ ሶስት ሺ አንድ መቶ ሰባ አንድ ብር ከስልሣ ዘጠኝ ሣንቲም ብድርና አርባ ብር ዋጋ ያለው መጽሐፍ በአጠቃላይ አስራ ሶስት ሺ ሁለት መቶ አስራ አንድ ብር ከስልሣ ዘጠኝ ሣንቲም እንዳለበት በማመን ተከራክሯል ተጠሪው ከዚህ በተጨማሪ ከአመልካቹ አራት ሺ ሰባዘጠኝ ብር ከስልሣ ሁለት ሣንቲም ዕዳ እንዲቻቻልለት የጠየቀ ቢሆንም ይህንን አመልካቹ አልተቀበለውም የሥር ፍርድ ቤትም ይኸ ገንዘብ በበቂ ማስረጃ የተረጋገጠ ዕዳ ለመሆኑ ግልፅ ውሣኔ አልሰጠበትም ስለሆነም በዚህ ጉዳይ አመልካች ለተጠሪው መክፈል ከሚገባው የአገልግሎት ካሣና የሰባ ቀን ዓመት እረፍት ክፍያ በሕጋዊ መንገድ ሊቻቻልበት የሚችሉ ብር አስራ ሶስት ሺ ሁለት መቶ ብር ከስልሣ ዘጠኝ ሣንቲም ብቻ ነው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በፍታብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ በተደነገገው መሠረት በመጀመሪያ አመልካች በክሱ ከጠቀሣቸው ክፍያዎች ውስጥ ተጠሪው ሊከፍለው የሚገባውን የገንዘብ መጠን በመወሰን ከዚያ በማስከተል ደግሞ በተጠሪው በኩል ከቀረበው የመቻቻል ጥያቄና ከአመልካች የሚፈለግ ዕዳ የትኞቹ ማስረጃ የቀረበባቸውና መቻቻል እንደሚገባቸው መወሰን ነበረበት የሥር ፍርድ ቤት በዚህ መንገድ ሣይሆን በጥቅሉ አመልካች እዳውን ስላላወራረደ ያቀረበው የሥራ አገልግሎት ክፍያና ሌሎች የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች ተቀባይነት የለውም በማለት የሰጠው ውሣኔ የአመልካቹ ፍትህ የማግኘት መብት የሚያጣብብ ክርክሮችን ያለ ብዙ ወጭ በቀረቡበት መንገድ በአጭር ጊዜ ውስጥ አጣርቶ ለመወሰን ታስቦ የተደነገገውን የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ድንጋጌዎችን ያልተከተለ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው በማለት ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የካቲት ቀን ዓም በጥቅሉ አመልካች የተጠሪውን ዕዳ ያወራርድ በማለት የሰጠው ውሣኔ ተሻሽሏል የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አግባብነት ያላቸውን የሕብረት ስምምነትና የሕግ ድንጋጌዎች መሠረት በማድረግ ተጠሪው ለአመልካች መክፈል የሚገባውን የአገለግሎት ካሣ ክፍያና የሰባ ቀን የዓመት እረፍት ክፍያ በአግባቡ ለይቶ እንዲወስንና ከዚህ ውስጥ አመልካች ለተጠሪው መክፈል የሚገባውን ብር አስራ ሶስት ሺ ሁለት መቶ አስራ አንድ ብር ከስልሣ ዘጠኝ ሣንቲም በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር መሠረት በማቻቻል ቀሪ ገንዘብ የሚኖር ከሆነ ለአመልካች እንዲከፈል እንዲያደርግ ጉዳዩን በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ንዑስ መሠረት መልሰን ልከንለታል ይፃፍ የከፍተኛው ፍርድ ቤት መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ትአዛዝ ተሽሯል ይፃፍ ይህ ፍርድ ሚያዚያ ቀን ዐዐዐ ዓም በሙሉ ድምጽ ተሰጠ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ዓብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሂሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ መድህን ኪሮስ አመልካች ቻይና ዋንቦ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አልቀረበም ተጠሪቡ ወርቅነህ ምህረቴ አልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርደ በዚህ መዝገብ የቀረበው ጉዳይ የሥራ ውል የሚመሰረትበትን ሁኔታ የተመለከተ ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው የአሁን ተጠሪ ለአመልካች ድርጅት የጥብቅና አገልግሎት ለመስጠት ተቀጥሬ ደመወዝ እየተከፈለኝ በጥቅምት ቀን ዓም በተሰጠኝ የውክልና ሥልጣን ድርጅቱን በጥብቅና ሥራ በማገልገል ላይ ሳለሁ አመልካች የስራ ውሌን ያቋረጠው ስለሆነ በአመልካች ሊከፈከኝ ይገባል ያሉትን ክፍያ በመዘርዘር በአማራ ክልል ደማርቆስ ወረዳ ፍቤት በመሰረቱት ክስ ነው የአሁን አመልካች በሰጠው መልስ ድርጅቱ ተጠሪን በሠራተኛነት አልቀጠረም ደመወዝም አልከፈለም የድርጅቱ ጠበቃ የነበሩት አቶ የስጋት ንጉሴ ሥራቸውን ሲለቁ አዲስ አበባ የሚገኙትንና የድርጅቱ የህግ አማካሪ የነበሩትን አቶ ጥበቡ ጋሹ የተባሉትን ግለሰብ መጥተው ደማርቆስ አካባቢ ያለውን የድርጅቱን ጉዳይ እንዲከታተሉ ስንጠይቃቸው አዲስ አበባ ያለው ጉዳይ ብዙ ስለሆነ መምጣት አልችልም ነገር ግን እኔ ደመወዝ አየከፈልኩት የአኔን ቦታ ሸፍኖ የሚሰራ ሰው ስላገኘሁ ድርጅቱ ውክልና ብቻ ይስጠውና የጥብቅና አገልግሎት ይስጥ በማለት በጠየቁን መሰረት ለአሁን ተጠሪ የውክልና ስልጣን ሰጥተናቸው ሲያገለግሉ ከመቆየታቸው በስተቀር ከእኛ ጋር የሥራ ውል የላቸውም በመሆኑም በመካከላችን የቅጥር ውል ሳይኖር ተጠሪ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት የለውም በማለት ተከራክሯል ፍቤቱም የቀረበለትን ክርክርና ማስረጃ መርምሮ በተጠሪ የቀረበው የሰነድ ማስረጃ የሚያስረዳው ተጠሪ በአመልካች መወከላቸውን ነው በተጠሪ የተቆዋጠሩት ምስክሮች የመሰከሩትም ተጠሪ በድርጅቱ ውስጥ ተቀጥረው መስራታቸውን እንደማያውቁ ነው በአመልካች በኩል የተቆጠሩት ምስክሮች ደግሞ አመልካች የሰጠውን መልስ በሚደግፍ መልኩ መስክረዋል በግራ ቀኙ የጋራ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት አቶ ጥበቡ ጋሹ ቀርበው እኔ በስሬ ሌሎች ባለሙየዎችን እየቀጠርኩ በተመሳሳይ ሁኔታ በሌሎች ክልሎችም የሙያ ስራ ስለምሰራ ተጠሪንም በዚሁ መልክ ቀጥሬአቸው ደመወዝ አእየከፈልኳቸው አመልካች በሚሰጣቸው የውክልና ሥልጣን በጥብቅና እንዲያገለግሉ ተደርጎ አኔ ከአመልካች ድርጅት ጋር ያለኝ ውል ሲቋረጥ ተጠሪ ሥራቸውን አቁመው በእጃቸው የሚገኙትን መዝገቦች እንዲያስረክቡ በነገርኳቸው መሰረት አስረክበዋል በማለት የመሰከሩ ስለሆነ አመልካች ባቀረቧቸው ማስረጃዎች ስላላስረዱ በግራ ቀኙ መካከል የሥራ ውል የለም መካከላቸው የሥራ ውል ከሌለ ደግሞ ተጠሪ የሥራ ውልን መሰረት አድርገው ክስ ለማቅረብ የሚያስችል ህጋዊ መብት ስለሌላቸው ያቀረቡት ክስ በፍሥሥህቁ መሠረት ውድቅ ተደርጓል በማለት ወስኗል የአሁን ተጠሪ በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለምስጎጃዞከፍፍቤት አቅርበው ፍቤቱ በአዋጅ ቁ አንቀጽ እና መሠረት የሥራ ውል በጽሁፍም ሆነ ያለጽሁፍ ሊመሰረት ስለሚችል ተጠሪ ያቀረቡት የውክልና ሥልጣን ማስረጃ በግራ ቀኙ መካከል ውል መኖሩን የሚያስረዳ ሆኖ ሳለ የስር ፍቤት ለህጉ የተሳሳተ ትርጓሜ በመስጠት ተጠሪ የጠየቋቸው ክፍያዎች አይገቧቸውም በማለት የሰጠው ውሳኔ ሚዛናዊነት የጎደለው ነው በሚል ተጠሪ የጠየቋቸው ክፍያዎች ይከፈሏቸው ሲል ወስኗል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህን ውሳኔ ለማስለወጥ ሲሆን ይህ ችሎት የስር ፍቤቶችን ውሳኔዎች አግባብ ካለው ህግ ጋር አገናዝቦ በመመርመር በአመልካችና በተጠሪ መካከል የሥራ ውል አለ የተባለው በአግባቡ መሆን አለመሆኑ ተጣርቶ መወሰን ያለበት ነጥብ ሆኖ ስላገኘው ጉዳዩ ለሰበር እንዲቀርብ አድርጓል መዝገቡን እንደመረመርነው የምስጎጃከፍፍቤት በግራ ቀኙ መካከል የሥራ ውል አለ ለማለት የቻለው በተጠሪ የቀረበው የውክልና ሥልጣን ማስረጃ በግራ ቀኙ መካከል በቅጥር ላይ የተመሰረተ የውል ግንኙነት እንደነበረ ያረጋግጣል በሚል መሆኑን ተገንዝበናል በመሠረቱ በሁለት ወገኖች መካከል በቅጥር ላይ የተመሰረተ የሥራ ውል በጽሁፍ ቢደረግም ባይደረግም ውጤቱ ተመሳሳይ መሆኑ የማያከራክር ነው ይህ የሚሆነው ግን ግንኙነቱ በውል ላይ የተመሠረተ ሲሆንና ይህም በማስረጃ ሲረጋገጥ ነው በዚህ ጉዳይ ተጠሪ በአመልካች ድርጅት ተቀጥረው ደመወዝ እየተከፈላቸው የጥብቅና አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውን ለማረጋገጥ ያቀረቡት በአመልካች ተሰጥቷቸው የነበረውን የውክልና ሥልጣን ማስረጃ ሲሆን ይህ ማስረጃ የሚያረጋግጠው አመልካች በተጠሪ ተወክለው እንደነበረ እንጂ ተቀጥረው ሲያገለግሉ እንደነበረ አይደለም በሌላ በኩል በግራ ቀኙ የጋራ ምስክር ሆነው የተቀጠሩት ግለሰብ ለአመልካች ድርጅት የጥብቅናና የህግ ማማከር አገልግሎት ሲሰጡ በነበረበት ወቅት ተጠሪን በመቅጠር ደመወዝ አእየከፈሏቸው ከአመልካች በሚያገኙት የውክልና ሥልጣን ለድርጅቱ የጥብቅና አገልግሎት እንዲሰጡ ያሰማራቸው መሆኑንና ድርጅቱ ከእሳቸው ጋር የነበረው ግንኙነት ሲቋረጥም ተጠሪ ከድርጅቱ ጋር የነበራቸው ግንኙነትም አብሮ የተቋረጠ መሆኑን መስክረዋል ከዚህ መረዳት ሚቻለው ተጠሪ የተቀጠሩት አመልካች ድርጅት በቀጠራቸው ግለሰብ እንጂ በአመልካች አለመሆኑ ራሳቸው ተጠሪ ባቀረቧቸው ምስክር የተመሰከረ መሆኑን ነውፎ በመሆኑም በግራ ቀኙ መካከል የውል ግንኙነት እንዳልነበረ ተገንዝበናል በተጠሪና በአመልካች መካከል የውል ግንኙነት ካልነበረ ደግሞ ተጠሪ በአመልካች ላይ ከውል የመነጨ የመብት ጥያቄ ማቅረብ አይችሉም በዚህም ምክንያት ተጠሪ አገልግሎቱን ሲሰጡ የነበረው ከአመልካች ጋር በነበራቸው የጡስ ግንኙነት መሆኑን ባላስረዱበት ሁኔታ የስር ፍቤት የውክልና ሥልጣን ማስረጃው በግራ ቀኙ መካከል የውል ግንኙነት እንደነበረ ስለሚያስረዳ በተጠሪ የተጠየቁትን ክፍያዎች አመልካች መክፈል አለበት በማለት መወሰኑ መሰረታዊ የህግ ስህተት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የአማራ ክልል ደማርቆስ ወረዳ ፍቤት በመዝገብ ቁ ታህሣስ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ ጸንቷል የክልሉ የምስጎጃዞከፍፍቤት በመዝገብ ቁ ጥር ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ ተሸራል ተጠሪ የአመልካች ተቀጣሪ ስላልነበሩ አመልካች በተጠሪ የተጠየቀውን ክፍያ ለመክፈል አይገደድም በማለት ተወስኗል ይጻፍ ግራ ቀኙ ወጪና ኪሳራቸውን ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ነዓ የሰበር መቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍስሐ ወርቅነህ አብዱራሂም አህመድ ታፈሰ ይርጋ ብርሃኑ አመነው አመልካች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ነፈጅ አለሙ ዋሴ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ዋሲሁን አዳነ አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ የተመለከተው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀረብ የቻለው በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ፍቤት ተጠሪ በአመልካች መቤት ከዐ ዓም ጀምሮ እንዲቀጠርና በዚያን ጊዜ የተቀጠሩ ሠራተኞች የደረሱበት የደመወዝ ስኬል ላይ እንዲደርስ በማለት ውሣኔ በመስጠቱና በይግባኝ የተመለከተውም የክልሉ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ይግባኙን ባለመቀበል ይህንኑ ውሣኔ በማጽናቱ አመልካች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት የሰበር አቤቱታ በማቅረቡ ነው የክርክሩ ሂደትም ባጭሩ ሲታይ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ፍቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ክስ መስርቶ ፍቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ ተጠሪ በአመልካች መቤት የሠራበት የ ቀን ደመወዝና ብር ዐዐ ሁለት መቶ ኪሣራ አመልካች ከፍሎት ከሥራ እንዲሰናበት በማለት ጥቅምት ቀን ዐ ዓም በዋለው ችሎት ውሣኔ የሰጠ ሲሆን በዚህ ውሣኔ መሠረት አፈፃፀም ሣይቀጥል እንደዚሁም አመልካች የክርክሩ ተካፋይ ባልሆነበት ተጠሪ በአመልካች መቤት ተቀጥሮ እንዲሰራ ፍቤቱ በተለያየ ጊዜ ውሣኔ መስጠቱን አመልካች ከሰበር አቤቱታው ጋር አያይዞ ያቀረባቸው የፍቤቱ ውሣኔዎች ያስገነዝባሉ በዚህም መሠረት ኀዳር ቀን ዐ ዓም በዋለው ችሎት ተጠሪ በተገኘው ክፍት የሥራ ቦታ ተቀጥሮ እንዲሰራ ሐምሌ ቀን ዓም ደግሞ በአዋሽ በሚከፈተው የአመልካች የዲስትሪክት ቅርንጫፍ መቤት በተገኘው ክፍት ቦታ ተጠሪ ተቀጥሮ እንዲሰራ አንደዚሁም ነሐሴ ቀን ዓም በዋለው ችሎት በአዋሽ የዲስትሪክት ጽቤት በተገኘው ቦታ ተጠሪ ተቀጥሮ እንዲሰራ በማለት ፍቤቱ ውሣኔ ሰጥቷል ተጠሪ በአመልካች ቅርንጫፍ መቤት እንዲቀጠር በማለት ናቤቱ በሰጠው ተደጋጋሚ ውሣኔ መሠረት አፈፃፀሙ ቀጥሎ ከታህሣሥ ቀን ዓም ጀምሮ ተጠሪ በአመልካች ቅርንጫፍ ጽቤት እንዲቀጠር የተደረገ ቢሆንም መቀጠር ከነበረብኝ ከዐ ዓም ጀምሮ መድረስ የሚገባኝ የደመወዝ ስኬል ላይ መድረስ ይገባኛል በማለት ተጠሪ ክርክር በማቅረቡ ፍቤቱ ይህንኑ የተጠሪን ክርክርን ተቀብሎ ከዐ ዓም ጀምሮ እንዲቀጠርና በዚያን ጊዜ የተቀጠሩ ሠራተኞች የደረሱበት የደመወዝ ስኬል እንዲደርስ በማለት ጥር ቀን ዓም በዋለው ችሎት ትአዛዝ የሰጠ ሲሆን ጉዳዩ በይግባኝ የቀረበለትም የዞን ከፍተኛ ፍቤት ይግባኙን ባለመቀበል ይህንኑ ትእዛዝ አጽንቷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንኑ በመቃወም ሲሆን አቤቱታው ተመርምሮ ተጠሪ ከዐ ዓም እስከ ዓም በሥራ ላይ ያልነበረ መሆኑ እየታወቀ በሥራ ላይ ላልነበረበት ጊዜ ጥቅማ ጥቅምና የደረጃ ዕድገት ይከፈለው የመባሉ አግባብነት ለሰበር ችሎት ቀርቦ ሊወሰን እንደሚገባው በመታመኑ ፍቤቱ ተጠሪን በመጥራት ግራ ቀኙን አከራክራሯል ተጠሪም በበኩሉ የሰበር አቤቱታው በአግባቡ የቀረበ እንዳልሆነ በመዘርዘር የወረዳውና የዞነ ከፍተኛ ፍቤት ውሣኔ ሊፀና ይገባል በማለት ተከራክሯል በአጠቃላይ የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን ተጠሪ ሥራ ላይ ባልነበረበት ጊዜ ሊደርስበት የሚገባው የደመወዝ ስኬል ተጠብቆለት ደመወዝ እንዲከፈለው የተሰጠው ውሣኔ አግባብነት ከሕጉ አኳያ እንደሚከተለው ተመርምሯል በአመልካችና በተጠሪ መካከል የነበረው የሥራ ክርክር በፈንታሌ ወረዳ ፍቤት ቀጥሎ ጥቅምት ቀን ዐ ዓም በዋለው ችሎት ፍቤቱ ውሣኔ የሰጠው ከላይ እንደተመለከተው አመልካች ለተጠሪ የ ቀን ደመወዝ እንደዚሁም ብር ዐዐ ሁለት መቶ ኪሣራ እንዲከፍልና ተጠሪም ከሥራ እንዲሰናበት በማለት ነው በዚህ ውሣኔ መሠረትም ተጠሪ የአፈፃፀም አቤቱታውን አቅርቦ ፍቤቱ በውሣኔው መሠረት አፈፃፀሙን መቀጠል ሲገባው በተለያየ ጊዜ ፍርድ ያላረፈበትን የአፈፃፀም ትእዛዝ በመስጠቱ ተጠሪ በአመልካች ቅርንጫፍ መቤት ከታህሳስ ቀን ዓም ጀምሮ አንዲቀጠር መደረጉን ተገንዝበናል ጉዳዩ ይህ ሆኖ የአመልካች አቤቱታ ተጠሪ ሥራ እንዲቀጠር በመደረጉ ሣይሆን የደመወዝ ስኬል ተጠብቆለት ደመወዝ ይከፈለው ተብሎ በተወሰነው ላይ በመሆኑ ይህም የአፈፃፀም ትእዛዝ ሲታይ ቀድሞውንም ቢሆን ተጠሪ ወደ ሥራ እንዲመለስ ባልተወሰነበት ሁኔታ የተሰጠ የአፈፃፀም ትእዛዝ ሆኖ ተገኝቷል ፍርድ ባላረፈበት ነገር የአፈፃፀም ትእዛዝ መስጠት ደግሞ ጉልህ የሆነ የሥነ ሥርዓት ግድፈት ዘህ ፀዕርሀህሟ ፐፀሀሸከ ነው ስለሆነም ተጠሪ ወደ ሥራ እንዲመለስ በፍርድ ባልተወሰነበት ሁኔታ ከዐ ዓም ጀምሮ ሥራ ላይ እንዳለ በመቁጠር በዚያን ጊዜ የተቀጠሩ ሠራተኞች ከደረሱበት የደመወዝ ስኬል እንዲደረስ ተደርጎ ደመወዝ እንዲከፈለው በማለት የተሰጠው የአፈፃፀም ትእዛዝ ጉልህ የሆነ የሥነ ሥርዓት ግድፈት ያለው ከመሆኑም በላይ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ላይ የተደነገገውንና ደመወዝ የሚከፈለው ለተሰራ ሥራ ነው የሚለውን የሚናረር ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የፈንታሌ ወረዳ ፍቤት በመቁ ጥር ቀን ዓም የሰጠው ብይን የዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁጥር ዐ መጋቢት ዐ ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለተገኘ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽሯራል ይፃፍ ተጠሪ በአመልካች መቤት እንዲቀጠር በፍርድ ውሣኔ ያላገኘ ስለሆነ ሥራ ላይ ላልነበረበት ጊዜ የደመወዝ ስኬል ሲጠበቅለትም ሆነ ደመወዝ ሊከፈለው አይገባም ተብሉ ተወስኗል መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ መስፍን እቁበዮናስ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ አመልካች የወረዳ አጠቃላይ ነጋዴዎች ማኅበር ቀረቡ ተጠሪ አቶ በድሉ ጫላ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በጉዳዩ ላይ ክርክር የተጀረመው በፌመደፍቤት ሲሆን የአሁኑ ተጠሪ የሥር ከሣሽ ሰኔ ቀን ዓም አዘጋጅተው ባቀረበው የክስ ማመልከቻ ከጥቅምት ቀን ዓም ጀምሮ እስከ ግንቦት ዐ ቅን ዓም በማኅበሩ በጥበቃ አባልነትና በጥበቃ ቡድን መሪነት በወር ብር ዐ ደመወዝ እየተከፈለኝ ሳገለግል የቆየሁ ሲሆን ድርጅቱ ግንቦት ዐ ቀን ዓም ያለ አንዳች ጥፋትና ማስጠንቀቂያ ከሥራ በቃል አሰናብቶኛል በመሆኑም በአዋጅ ቁጥር መሠረት የስንብት የካሣ የማስጠንቀቂያ የዓመት ዕረፍት ክፍያ እንዲሁም የሥራ ልምድ ማስረጃ እንዲሰጠኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርበዋል ተከሣሽ ማኀበርም ሐምሌ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው መልስ ከሣሸ ከሥራ በተደጋጋሚ ስለሚቀሩ ትዕዛዝ ስለማያከብሩ የተመደቡበትን የጥበቃ ቦታ ለቀው ስለሚሄዱ በስራ ላይ አምባጓሮ ስላነሱ እና የሥራ ሰዓት ስለማይቀበሉ በአዋጁ አንቀጽ ሀ መሠረት የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶቸው በአግባቡ የተሰናበቱ በመሆኑና ደመወዛቸውም ብር ዐዐ እንጂ ብር ዐ ባለመሆኑ ክሳቸው ተቀባይነት የለውም ተብሎ አንዲወስንልን በማለት ተክራክራል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ካዳመጠ በጊላ ከሣሽ የተሰናበቱት በፈፀሙት ጥፋት መሠረት ስለመሆኑ በማስረጃ በመረጋገጡ የጠየቁት ክፍያ ሊከፈላቸው አይገባም ያልወሰዱት የዓመት ዕረፍት ክፍያ ግን በደመወዛቸው መሠረት እንዲከፈላቸው የሥራ የምስክር ወረቀትም እንዲሰጣቸው ሲል ውሣኔ ሰጥቷል በሌላ በኩል ደግሞ የፌከፍቤት የቀረበለትን ይግባኝ ተመልክቶ ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ የአሁኑ ተጠሪ የሥር ከሣሽ ከሥራ የተሰናበቱት በሕገወጥ መንገድ በመሆኑ የስድስት ወር ውዝፍ ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው ወደ ሥራም እንዲመለሱ በማለት ወስኗል የአሁኑ አመልካች የሥር ተከሣሽ ያቀረበው የሰበር አቤቱታም የፌከፍቤት የሰጠውን ውሣኔ በመቃወም ሲሆን ቅሬታውም ተጠሪው ከስራ የተሰናበቱት ለክሱ በሰጠነው መልስ በጠቀስናቸው ጥፋቶች ምክንያት መሆኑን አስረድተን አያለ የከፍተኛው ፍቤት ስንብቱ ሕገወጥ ነው ተጠሪው ወደ ሥራ ይመለሱ የስድስት ወር ውዝፍ ደመወዝም ይከፈላቸው በማለት የሰጠው ውሣኔ ማስረጃችንን ያላገናዘበና ተጠሪው ካቀረቡት ክስ እና ዳኝነት ከጠየቁበት ጥያቄ ውጭ በመሆኑ ውሣኔው መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው በመሆኑም የፌከፍቤት የሰጠው ውሣኔ ተሽሮ የፌመደፍቤት የሰጠው ውሣኔ እንዲፀና እንዲወስንልን የሚል ነው አቤቱታው የቀረበለት የሰበር ሰሚ ችሎትም ተጠሪው ወደ ሥራ ለመመለስ ክስ ሳያቀርቡ ፈከፍቤት ስንብቱ ሕገወጥ ነው ተጠሪው ወደ ሥራ ይመለሱ ብሎ የመወሰነው በአግባቡ መሆን ያለመሆኑን መመርመር በማስፈለጉ አቤቱታው ያስቀርባል ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል ተጠሪው ደግሞ በሰጡት መልስ የተሰናበትኩት ያለ አንዳች ጥፋትና ያለማስጠንቀቂያ ስለመሆኑ በማስረጃዬ ያረጋገጥኩኝ በመሆኑ የፌከፍቤት ስንብቱ ሕገወጥ ነው ሠራተኛው ወደ ሥራው መመለስ አለበት የስድስት ወር ውዝፍ ደመወዝም ሊከፈለው ይገባል በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ የተሰጠ እንጂ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት አይደለም እንዲያውም ውሣኔው ተሻሽሉ የዓመት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈለኝ ሊወሰንልኝ ይገባል ሲሉ ተከራክረዋል አመልካችም የመልስ መልሱን በማቅረብ ከመዝገቡ ጋር አያይዛል በበኩላችን ደግሞ አመልካች ተጠሪውን ያሰናበታቸው በአግባቡ ነው ወይስ አይደለም። ወይንስ አይደለምፃ የሚለው ኛው ጭብጥ ሲታይ አመልካች ለተጠሪ በፃፈው ደብዳቤ ከጥር ቀን ዓም ጀምሮ አዲስ ወደተዛወረበት ቦታ በመፄድ ሥራ መጀመር እንደሚገባው አስታውቆት ወደዚሁ ቦታ ፄዶ ሥራውን ያልጀመረ ከመሆኑም በላይ ከጥር ቀን ዓም በፊትም ቀድሞ ሲሰራበት በነበረው መቤት ከጥር ቀን ዓም ጀምሮ በሥራ ላይ እንዳልተገኘና በአጠቃላይም ለ ተከታታይ የሥራ ቀናት ያለበቂ ምክንያት በሥራ ገበታው አለመገኘቱ የተረጋገጠ ስለሆነ ይህ ሁኔታ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ለ መሠረት በአሠሪው አነሣሽነት የሥራ ውልን ለማቋረጥ የሚያበቃ ርሃታ እንደመሆኑ መጠን በዚሁ መሠረትም አመልካች የሥራ ውሉን ባቋረጠበት ሁኔታ የበታች ፍቤቶች ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት ተጠሪው ወደሥራ እንዲመለስ በማለት የሰጡት ውሣኔ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የአላባ ቁሊቱ ከተማ የመደፍቤት በመቁ ዐዐ በመጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ እንደዚሁም የደቡብ ክልል ጠፍቤት ሰበር ችሎት በመቁ በየካቲት ቀን ዓም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ተሽራል አመልካች ተጠሪን ከሥራ ያሰናበተው ከሕግ ውጭ ስላልሆነ ተጠሪ ወደ ሥራ ለመመለስ ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት የለውም ግራ ቀኙ ወጭና ኪሣራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰበር መቁ ጥር ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ አብዱልቃድር መሐመድ ሐጐስ ወልዱ ሂሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ጂሰቨን የንግድና ኢንዱስትሪ የመኸር ቃጫ ውጤቶች ፋብሪካ ተጠሪ መኩንን አበራ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ይህ ጉዳይ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁ መሰረት የቀረበ የሥራ ክርክርን የሚመለከት ነው ተጠሪ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ክስ የመሰረተው የሥራ ውሌ በሕገ ወጥ መንገድ ተቋርጦብኛል በማለት ነው ይህን ምክንያት መሰረት በማድረግም የአገልግሎት እና የማስጠንቀቂያ ጊዜ እንዲከፈለው እንዲሁም የስራ መፈለጊያ ክፍያክፍያ ለዘገየበት ጊዜም ክፍያ እንዲወሰንለት ጠይቆአል ፍቤቱ ተከሣሽ የነበረውን የአሁኑን አመልካች በማስቀረብ ክርክሩን ከሰማ ብላ ከሣሽ የዓመት እረፍት እንደወጣ ለተከሣሽ ሳያሳውቅ ያለበቂ ምክንያት ለአምስት የስራ ቀናት የቀረ በመሆኑ አመልካች የሥራ ውሉን ማቋረጡ አግባብ ነው በማለት ክሱን ውድቅ አድርጎአል በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ ውሳኔውን በመቃወም ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ በማቅረቡ ክርክሩ እንደገና ተሰምቶአል በመጨረሻም ፍቤቱ ተጠሪ ከሥራ የቀረው በቂ በሆነ ምክንያት ነው የሚል ምክንያት በመስጠት በሥር ፍቤት የተሰጠውን ውሳኔ ሽሮአል ተጠሪ የጠየቃቸውን ልዩ ልዩ ክፍያዎች እንዲከፈሉትም ወስኖአል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው ይህ የሰበር ችሎትም አመልካች ነሐሴ ቀን ዓም በጻፈው ማመልከቻ ያቀረበውን አቤቱታ መሰረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል አቤቱታው በሰበር ችሎት እንዲታይ የተወሰነው አመልካች የስራ ውሉን ያቋረጠበትን የሕግ አግባብ ለመመርመር ነው በዚህ መሰረትም ይህን ነጥብ ከግራ ቀኝ ወገኖች ክርክር አቤቱታ ከቀረበበት ውሳኔ እና ከሕጉ ጋር አገናዝበን መርምረናል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ተጠሪ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት ከሥራ ገበታው ላይ ሳይገኝ እንደቀረ አላከራከረም የሥር ፍቤቶች ለውሳኔአቸው መሰረት ያደረጉት ጭብጥ የተጠሪው ከሥራ መቅረት በበቂ መክንያት የተደገፈ ነው ወይስ አይደለም የሚለው ነው ተጠሪ ከሥራ መቅረቱን ካመነ በእርግጥም በቂ ምክንያት የነበረው መሆኑን ያስረዳ ዘንድ የግድ ነው አመልካች ከሥር ጀምሮ አጥብቆ የተከራከረው ተጠሪ ለአረፍት አንደወጣ በዚያው ከመቅረቱ ውጪ ባለበት ቦታ ሆኖ እንኳን ሊያሳውቀኝ አልቻለም በማለት ሲሆን ተጠሪ ደግሞ በጎርፍ አደጋ የተጠቁትን ዘመዶቼን ለመጠየቅ ወደ ድሬዳዋ ፄጄጁ ነበር የሚል የመከራከሪያ ነጥብ ማንሳቱን ተመልክተናል ይህንን የመከራከሪያ ነጥብ ግን በቃል ከመግለጽ አልፎ በየትኛውም የማስረጃ አይነት አስረዳለሁ አላለም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም አባባሉን እንዳለ ከመቀበል አልፎ ያረጋገጠው ነገር የለም ይህ በመሆኑም በዚህ ረገድ የተፈጸመ ከማስረጃ ሕግ አኳያ የሚታይ ስህተት እንዳለ አእንገነዘባለን በሌላ አነጋገር ፍቤቱ ውሳኔውን የሰጠው በምንም አይነት ማስረጃ ላይ ሳይመሰረት ነው ማለት ነው አመልካች ግን ተጠሪ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁ አንቀጽ ለ የተመለከተውን ያለማስጠንቀቂያ የሥራ ውል ለማቋረጥ የሚያስችል ድርጊት ስለመፈጸሙ አስረድቶአል ያለው እውነታ ይህ ከሆነ ደግሞ አመልካች የሥራ ውሉን ያቋረጠው በሕግወጥ መንገድ ነው የሚባልበት የሕግ ምክንያት የለም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የሰጠው ውሳኔም ከዚህ አንጻር ሲታይ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል ቤኃ ውሳኔ አቤቱታ የቀረበበት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ በፍብሥሥሕግ ቁ መሰረት ተሽርአል በአመልካች እና በተጠሪ መካከል የነበረው የሥራ ውል የተቋረጠው በሕጉ መሰረት ነው ብለናል ስለዚህ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ ፀንቶአል ይጻፍ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች አብዱልቃድር መሐመድ መስፍን ዕቁበዮናስ ሒሩት መለሠ ታፈሰ ይርጋ መድንን ኪሮስ አመልካችፁ መሪጌታ ልሣነወርቅ በዛብህ ቀረቡ ተጠሪ ጠቅላይ ቤክህነት ቤት ነፈጅ ፍቅረማርያም ካሣ ቀረበ መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበው ጉዳይ የሥነ ሥርዓት ሕጉን የተመለከተ ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው የአሁን አመልካች በተጠሪ ጽቤት የኦጋዴን ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሆፔ በመስራት ላይ ሣለሁ ከታህሣሥ ቀን ዓም ጀምሮ የቁልቢ ነዋየ ቅድሣት ማደራጃ ዋና ፀሐፊ ሆፔ እንድሰራ ተደርጓል ተጠሪው ደረጃዬን ከሥራ አስኪያጅነት ወደ ፀሐፊነት ዝቅ ማድረጉ አግባብ ስላልሆነ ወደ ሥራ አስኪያጅነት ደረጃና ደመወዝ እንድመለስ ይወስንልኝ በማለት ለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ባቀረቡት ክስ ነው ተጠሪ በሰጠው መልስ አመልካች የሥራ መሪ ስለሆኑ ቦርዱ ጉዳዩን የማየት ሥልጣን የለውም አመልካች ከ ዓም ጀምሮ በቦታቸው ሌላ ሥራ አስኪያጅ መመደቡን እያወቁ ሣይቃወሙ ቆይተው አሁን ያቀረቡት ክስና የክፍያ ጥያቄ በይርጋ የታገደ ነው በማለት ተከራክሯል ቦርዱም አመልካች የሥራ መሪ ስለሆኑ ቦርዱ ክሱን ተቀብሎ የማየት ሥልጣን የለውም ክሱ ግን በይርጋ የታገደ ነው በማለት ክሱን በብይን ውድቅ አድርጎታል በመቀጠልም አመልካች ይህንኑ ክስ ለፌዴየመጀደፍቤት አቅርበው ተጠሪ በሰጠው መልስ ክሱ ቀደም ሲል ለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ቀርቦ ቦርዱ ውሣኔ የሰጠበት ስለሆነና ፍቤቱ ደግሞ ይግባኝ ሰሚ ስላልሆነ ክሱ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ውድቅ ሊደረግ ይገባል የሚለውንና ሌሎች መከራከሪያዎችን በማቅረብ ተከራክሯል ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ ቦርዱ በዚህ ዓይነቱ ክርክር ላይ የዳኝነት ሥልጣን ሣይኖረው በክርክሩ ላይ የሚሰጠው ውሣኔ ስለማይኖር ፍቤቱ የቦርዱን ብይን የሚረዳው ክሱ በይርጋ ቀሪ ቢሆንም ቦርዱ ጉዳይን የማየት ሥልጣን የለውም የሚል መሆኑን ነው ስለዚህ አመልካች አሁን ክሱን ሥልጣን ላለው ፍቤት ያቀረቡ ስለሆነ በዚህ ረገድ ተጠሪ የፍብሥሥሕግ ቁ ን በመጥቀስ ያነሣው መቃወሚያ ተቀባይነት የለውም በማለት ብይን ከሰጠ በኋላ ተጠሪ አመልካችን ከሥራ አስኪያጅነት ወደ ሌላ የሥራ መደብ የለወጣቸው ያለአግባብ በመሆኑ ተጠሪ አመልካችን ቀድሞ ወደነበሩበት የሥራ መደብ ወደ ሥራ አስኪያጅነት በመመለስ በመደቡ የሚከፈለውን ደመወዝና አበል ሊከፍላቸው ይገባል በማለት ወስኗል የአሁን ተጠሪ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለፌከፍፍቤት አቅርቦ ፍቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር በመስማት ቀደም ሲል ክሱ ለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ቀርቦ ቦርዱ ክሱ በይርጋ የታገደ ነው ሲል ብይን ሰጥቶበታል ብይኑ ይግባኝ ተብሎበት በፍርድ ውሣኔ አልተሻረም በመሆኑም የስር ፍቤት የቀረበለትን ክስ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ውድቅ ማድረግ ሲገባው ይህ ያልተሻረ ብይን እያለ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ መስጠቱ አግባብ ስላልሆነ የፌመጀደፍቤት በዚህ ጉዳይ የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል በማለት ወሰነ የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንን ውሣኔ ለማስለወጥ ነው የአቤቱታው ይዘትም ባጭሩ የሥር ፍቤት ክሱ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት መወሰኑ የሕግ ስህተት ስለሆነ ሊታረም ይገባል የሚል ሲሆን ይህ ችሎት የሥር ፍቤቶችን ውሣኔዎች አግባብ ካለው ሕግ ጋር አገናዝቦ በመመርመር የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ በጉዳዩ ላይ የዳኝነት ሥልጣን የለኝም ሲል ከወሰነ በኋላ ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው በማለት በብይኑ ላይ ማስፈሩ አመልካች በመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ያቀረቡት ክስ ቀደም ሲል ውሣኔ አግኝቶ የበቃ ነው ለማለት የሚያስችል መሆን አለመሆኑ ተጣርቶ ሊወሰን የሚባው ነጥብ ሆኖ ስላገኘው ጉዳዩ ለሰበር እንዲቀርብ አድርጓል መዝገቡን እንደመረመርነው አመልካች በመጀመሪያ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ክስ አቅርበው ቦርዱ ጉዳዩን የመዳኘት ሥልጣን የለኝም አንጂ ክሱ በይርጋ የታገደ ነው ሲል መበየኑን በመቀጠልም አመልካች ክሱን ለፌመጀደፍቤት አቅርበው ተጠሪ ጉዳዩ ቀደም ሲል የቦርዱ ውሣኔ ብይን ያረፈበት ስለሆነ ክሱ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ሊታገድ ይገባል የሚል መቃወሚያ ያቀረበ መሆኑን ፍቤቱ ቦርዱ ጉዳዩን የመዳኘት ሥልጣን ሣይኖረው ይርጋውን አስመልክቶ ብይን መስጠት አይችልም በማለት መቃወሚያውን በብይን ውድቅ አድርጎ በፍሬ ጉዳዩ ላይ ውሣኔ መስጠቱን አንዲሁም ጉዳዩን በይግባኝ ያየው የፌከፍተኛ ፍቤት ቦርዱ ቀደም ሲል ክሱ በይርጋ የታገደ ነው ሲል የሰጠው ብይን በይግባኝ ስላልተሻረ የመጀደረጃ ፍቤት የቀረበለትን ክስ በፍብሥሥሃሕቁ መሠረት ውድቅ ማድረግ ሲገባው በፍሬ ጉዳዩ ላይ ውሣኔ መስጠቱ አግባብ አይደለም በማለት የስር ፍቤትን ውሣኔ የሻረው መሆኑን ለመገንዘብ ችለናል በዚህ መዝገብ የሚያከራክረውን ጉዳይ በየደረጃው ያዩት ፍቤቶች የሰጡት ውሣኔ የተለያየ ሲሆን ለዚህ ልዩነት መነሻው ቦርዱ የዳኝነት ሥልጣን የለኝም ነገር ግን ክሱ በይርጋ የታገደ ነው ሲል የሰጠው ብይን መሆኑን መዝገቡ ያስረዳል ይኸውም የመጀደፍቤቱ ሥልጣን የለኝም የሚለውን የብይኑን ክፍል ይዞ ውሣኔውን ያሣረፈ ሲሆን ከፍፍቤት ደግሞ ክሱ በይርጋ የታገደ ነው የሚለውን ክፍል በመያዝ ይርጋውን አስመልክቶ የተሰጠው ብይን ስላልተሻረ ለመደፍቤት ክስ ሊቀርብ አይችልም በማለት ወስኗል በመሠረቱ አንድ ፍቤት የቀረበለትን ጉዳይ የመዳኘት ስልጣን ያለው መሆኑን ካላረጋገጠ የግራ ቀኙን ክርክር መመርመር አይጀምርም የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ክሱ ለቦርድ መቅረብ ያልነበረበት መሆኑን ከተገነዘበ ጉዳዩን የመዳኘት ሥልጣን እንደሌለው በመግለጽ እዚያው ላይ ማቆም ሲገባው በተጠሪ የቀረበውን የይርጋ ክርክር መርምሮ ክሱ በይርጋ ይታገዳል የሚል ሀሣብ በብይኑ ላይ አስፍሯል ቦርዱ የዳኝነት ሥልጣን ከሌለው ይርጋውንም አስመልክቶ ብይን መሰጠት አይገባውም ስለሆነም ቦርዱ በአንድ በኩል የዳኝነት ሥልጣን የለኝም እያለ በሌላ በኩል ደግሞ ሥልጣኑ ቢኖረው ኖሮ ሊመረምር ይገባው የነበረውን ጉዳይ በብይኑ ላይ መጥቀሱ ስለይርጋው ብይን ሰጥቷል ለማለት የሚያስችል ስላልሆነ አመልካች ለመደፍቤት ያቀረቡት ክስ በፍብሥሥሕግ ቁ መሠረት ውድቅ የሚያደረግ አይደለም በዚህ ምክንያት ቦርዱ ቀደም ሲል ይርጋውን በተመለከተ ብይን የሰጠ ስለሆነ ብይኑ በይግባኝ ሣይሻር ክሱ ለመጀደፍቤት ሊቀርብ አይገባም በማለት የፌከፍቤት የሰጠው ብይን መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ተገኝቷል ውሣኔ የፌከፍተኛ ፍቤት በመዝገብ ቁ ሰኔ ቀን ዓም የሰጠው ብይን ተሽሯል የፌከፍተኛ ፍቤት ብይኑ የተሻረ መሆኑን ተገንዝቦ በይግባኝ የቀረበለትን ጉዳይ በመመርመር የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ በፍሬ ጉዳዩ ላይ ውሣኔ እንዲሰጥ ጉዳዩ ተመልሶለታል የዚህን ፍቤት ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሰመቁ ሚያዝያ ቀን ዐዐዐ ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ሒሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ አመልካች ሬቫ ኢንጂነሪንግ ኃየተየግማኀበር ጠበቃ ንጉሴ ገዛኸኝ ቀረቡ ተጠሪዎች እንዳለ ታደሰ በሌለበት ማሞ ዋቅጅራ በሌለበት ሚሊዮን ዘውዴ በሌለበት ሰይድ መሐመድ በሌለበት አባቡ ውበቱ ቀረበ ግዛው ፈይሳ ቀረበ ከፍያለው ጌታቸው በሌለበት ምስጋና አዲስ በሌለበት ገመዳ ሞገስ በሌለበት ዐ ታምራት ኃይሉ ቀረበ ጨ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ አከራካሪው ጉዳይ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁ መሠረት የሚታይን ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀመረበት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የአሁኖቹ ተጠሪዎች ከሣሾች ነበሩ በአመልካች ላይ ክስ የመሠረቱትም በአናጺነት ሥራ ተሰማርተን አንድንሠራ በውል ተቀጥረን ስንሠራ የቆየን ቢሆንም ሥራው ሳያልቅ ከሕግ ውጪ የሥራ ውላችን ተቋርጦብናል ስለዚህ ወደ ስራችን እንድንመለስ የማንመለስ ከሆነም ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ተገቢው ክፍያ ተከፍሎን እንሰናበት ዘንድ ይወሰንልን በማለት ነው።