Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የኔ_ጋሻ,_ከ_ክፍሌ_አቡቸርመ,አ_1978_አዲስ_አበባ (1).pdf


  • word cloud

የኔ_ጋሻ,_ከ_ክፍሌ_አቡቸርመ,አ_1978_አዲስ_አበባ (1).pdf
  • Extraction Summary

ተፈጥሮን ኃቁርጥ አቋም ነው የሚያወዳጅ።» ሲለኝ «ልብ» ስለው «በዚች ምድር በዚች አገር የምናየው መልካም ነገር ዕድገትና ድንቅ ውበቱ እና ፉቶባሪሽ» ይኸውልሽ «ሞስክቫ» እንዲያ ነበረች በችግር በኩረ ልጆችዋ ዛሬ ይኸው እንዲህ ሆነች» ሣተኩረው ሲያተኩረኝ ለአንድ አፍታ ለደቂቃ በውስጥ ሕይወት ሚስጢር ሲቃ እኔን በኔ ቆም አድርጌ አንዱን ካንዱ ሣስቲያየው በጭንቅ ቀን በሩቅ ስሜት ሂደትሽን ሳስታውሰው አንዳች ነገር ጠቅ። ዘመን ፀአዳ ሽቱ ወንድ ከሴት ሴት ከወንዱ በአንድ ስሜት በአንድ ክንዱ ቀና ደፋ ደፋ ቀና የእርሱ ሕይወት «ሥራ» ሁና የሃገር ፍቅር ቅን ማህተሙ የአንድነቱ ደም ቀለሙ ዓላማው ግብ ውሎ ስሌት የቀን ተሌት ቋንቋ ግሱ ለሰው ልጆች መልካም ኑሮ ሠላም። «ሲነገር ሲከበር የኖረው የዘመናት ሕያው ታሪክሽ የአንድነትሽ ጽኑ ዋልታ የነፃነት መንበር ክብርሽ የአዲስ ሕይወት መስተንግዶ የዓለም ሰላም ሰንሰለትሽ በቅን መድረክ ፍልሚያ ውሎ በልጅሽም ደም ፍሳሽ ወኔ ይጠበቃል እናት በእኔ።

  • Cosine Similarity

የግፈኞች ሥርዓት «ክብረ ስብዕናውን» የገፋው የስግብግቦች መዳፍ «ጥሪት ገበናውን» ያስከፋው ፉእረ ያገር ያለህ አገር ለኔ አልሆነኝ እረ የሰው ያለህ ሰው መሆን መረረኝ በላይ ቤት አልሠራሁ በሥር አልተመቸኝ» ሲል ዕለተ ልደቱን የረገመውን ባክኖ መና «የኔ ጋሻ» በዓይነ ሕሊናዋ ማስታወስ ብቻ ሳሆይ የዚህን የአገር ቋንቋ ተናጋሪ የአገር ብሶት መስካሪ የቅርብ ሕይወት «እማኝ» በማድረግ ነው። በ «የኔ ጋሻ» ውስጥ የተካተቱት ግጥሞች የታሪክ ምስክርነታቸውን የሚጀምሩት ከ ጊ ጀምሮ ሲሆን ከውቅያኖስ ከሰፋ የአያሌ ዘመናት ውስብስብ የአስከፊ ሕይወት ትግልና እንደ ጨረቃ ከደመቀ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ የድል ታሪክ የጨለፈችውን የሰፊውን ሕዝብ የመከራ ሕይወት ገጽታና የበቃኝ አመጽ እንጉርጉሮ የቃኙ የአዲሱን ሥርዓት እውነተኛ የሰው ልጆች የነፃነትና የሠላም ድል ስምረት ጅምር ትግልና በተከፈለው ሁለንተናዊ መስዋዕትነት የተገኙትን ታላላቅ ድሎች በአንኳር በአንኳሩ ያማትሩ ወላዊና ግላዊ ሕይወት ዕለታዊ ገጠመኞችን የሰው ልጆችን ሕይወት ምስጢራዊ ስሜት በወፍ በረር እይዳሰሱ የስነ ቃል ግጥምጥሞሽን ያካተተች ሲሆን በተለይም የዚህን ትውልድ ሕዝባዊ ዓላማ ጽናትና የአብዮታዊ እናት ሀገር ፍቅር ስሜት በማይፋታ ቃል ኪዳን ያረገገጠችበት ሰነድ ይዛ ቀርባለች። የአዲስ ሕይወት ብስራት ተስፋ ያለመብሽ ደም ሰጥቶ ደም ወስዶ ውሎ ያደረብሽ «እምቢኝ» ባለ ወኔ ለአፈር ጥሪት ክብርሽ ጀግና ልጅ ተወልዶ ጀግና የቀረብሽ የታሪኩ ግኝት ማገር ድምድማቱ የሕይወቱ ሰንደቅ የሙት አካል ቤቱ አንቺ ስለሆንሽ ንገሪኝ ምሽጉ ምን ተብሎ ይፃፍ የዚህ ጀግና ወጉ። ይልቅ ገለል እሳት እንጂ ቋያ ሰደድ በልቤ እልፍኝ የሚነድ ሕይወት እንጂ የሕዝብ ዕምነት የአገር ፍቅር የአገር ዕውነት ፍቅር እንጂ ቀና መንገድ የወል ሕይወት የወል አፀድ የታሪክ ውል ትግል ጽናት ቀንዲል እንጂ የድል ንጋት ከእንግዲህ መች ግዞት ለኔ ገባርነት በራብ ጐኔ። የጀግኖች ደም ሕይወት የጀግኖች ደም ጐራ። ሸቶት የአገር ፍቅር ሞቱ ስሜቱ አምጾ የጀግናው ጀግንነት ደም አጽሙ ተናውጾ «ይኸው ዛሬ ደርሶ አጽሜ ታሪክ ለብሶ በኖረበት አገር በአለፈበት ምድር የደም ሕይወት እያለ ታሪክ ምስክሩ የዘር ሐረግ ቆሞ ታሪክ መዘክሩ ሐቅ እውነት ተጽፎ የታሪክ ምግባሩ የእናት ሃገ ዋልታ እያለ ማገሩ የታሪክ ቅርስ እምነት እያለ ማህደሩ ጀግና ጠንቀቅ በል እንዳይጣስ በሩ እንዳይጐድፍ ክብሩ የእናት ሀገር እውነት ኢምንት ላይሰእይፍ የሐቅ ዕምነቷ ድል ቅንጣት ላይዛነፍ ጀግኖች ማዕከል የወላዶች ማህፀን ጀግና ከማበርከት ከማፍራት ሳይመክን የታጋዮች ቁጥር ታሪክ ላይመነምን ባህረ መዝገቧ በጠባቦች ምኞት ቅዝት ላይወሰን በውዳሴ ከንቱ ጋለበ ነፈሰ በውዳሴ ከንቱ ጉራ ተነፈሰ በቀቢጾ ተስፋ ጉራ ተነፈሰ በአኩሪ ጀግኖች መድረክ የአገር ፍቅር አንጀት የትውልድ አተላ። ስለዚህ ማየት እምነቴ ነው የድል ምላሽ መሌን መስማት ምኞቴ ነው የአደራ ቃል ውሌን» ብሎ ተናገረ የጀግኖች ደም ጐራ ብሎ ተማጸነ ታሪኬን አደራ መሰል ባለወኔ መሰል የአካል ክፋይ መሰል ጀግና ጠራ። የዓላማህ ውል ቅንጅት የብሩህ ዘመን ግኝት ፋና የችግር ተቸጋሪ የመከራህ ተናጋሪ የትግል ክንድህ ነኝና እንደአሰብኩህ አንተም አስበኝ እንዳመንኩህ አንተም እመነኝ «ወንድም» ስልህ «እህት» በለኝ «ጓድ» ስልህ «ጓድ» በለኝ ለሩቅ ዓላማ ግብ አልመኝ ለጋራ ትግል ለጋራ ድል ሕይወት ተመኘኝ እንጂ ወንድም «በጾታዬ» አትፈትነኝ። ለስሜትህ አትመኘኝ ለፍትወትህ አታቅልመኝ ትዝታ የዕልፍ አዕላፍ ዕልፈተ ቀን የሩቅ ዕድሜ የሩቅ ዘመን የኑሮ ትግል ሂደት ትውስታ የዕውነታው «እውነት» ዕውነታ የትላንት ሕይወት አካል እሙን የደግ የክፉ ነገር ክንውን በሩቅ ምናብ በአሁን ቅኝት በሰመመን አመጽ ፍጭት በዛሬ ዕድሜ ሲዳሰስ ደስታው በሲቃ ሲታመስ ሃዘኑ በሃዘን ሲታወስ ጓድ ገበናው ሲታሰስ ያለፈ ሕይወት ሚስጢር ኑሮ በፉጨት እንጉርጉሮ በጥላቻን በሰቀቀን በፍቅር በሰመመን በትዝብት መነጽር ዕይታ በዓይነ ሕሊና ሲፈተሽ ትውስታው «ትውስ» ሲል ሕይወት ወዲያ ወዲህ ሲሸሽ ትዝታ። ትዝታ የአባት የእናት የጓደኛ የቤተ ሰብ የፍቅረኛ የጫጉላው ቤት ፍንድቅ ድቁ የጦር ሜዳው ትንቅንቁ የጀግንነት ሕይወት ስንቁ የልጅነት ለጋ ቋንቋ ጣፋጭ ልሳን ጣመ ዜማ የአፍላ ጉልበት ፍርጥም ግርማ የነበረው እንዳልነበር ትላንት ዛሬ ሳይሆን ሲቀር የሩቅ አካል የሩቅ ሕይወት ከአሁን ዕድሜ ከአሁኑ ስሜት ፍጭት ይዞ የሃሳብ ቅኝት ሲያብጠለጥል ሲያነታርክ ሲያብሰለስል አንጀት ሲያኝክኒ ሂሳብ ወዲህ ሃሣብ ወዲያ ተወጥኖ ተወጥሮ ሰው እያየ ሰው የማያይ ትላልቅ ዓይን አሣውሮ ዛሬም ነገር ነገም ዛሬ ሁሌም እንጭጭ ሁሌም ፍሬ ሁሌም ብስል ሁሌም ጥሬ ትኩስ ሆኖ ሃሣብ ሲያምጽ አፈር ምሶ ሙት አላውሶ ብትን አካል ንዶ ሲያንጽ «ትላንትና» ሲበረበር በደቂቃ ዘመን ሲያመሽ በዓይነ ሕሊና ሲፈተሽ ትውስታው «ትውስ» ሲል ሕይወት ወዲያ ወዲህ ሲሸሽ ትዝታ። እህል ጋሻ ስቁ ሃቅ የሕይወት ስንቁ መደፈር ኩዳዴው ድል የባህል ወጉ ሞት የታሪክ ሠርጉ የሀገር ሕይወት ሰንደቅ እኔም እንደቋራው «የመቅደላው» መብረቅ አንተም እንደ «ታጠቅ» እንደ እምዬ አደባሩ ኩስትሬ ኩይሳው እንደ «አድዋው» ቀንጥስ እኔም እንደ አርበኛው አንተም እንደ «ዳኘው» እንደ «አላጌው» ኮርማ እኔም እንደዚያ ሰው አንተም እንደ «ቃኘው» እንደ አገር ዳር ወሰን «የቀይ ባህር» ግርማ እንደ ሰሜን ኮከብ ያንን አገር ደም ግርማ እኔም እንደዚያ ሰው እንደዚያ ሰው ሎጋ አንተ እንደ «አባ ነጋ» እኔም እንደ ጃሎ እንደዚያ ሰው ውሎ አንተም እንደ «ቡሎ» በዕብሪት ከፈለሰው ከተርመሰመሰው ቼ። እናት አገር። በከንቱ ዓላማ ውርዴ በታሪክ ወራዶች ዲቃላ በሰላም አጥፊ ቅጥረኛ በትውልድ አስወቃሽ አተላ የእናት ዓለም ክብር ማዕድ የልጆችሽ የልጅ አንጀት በረሀብ ሾተል ሲሰረጐድ በእናት ቋንቋ በእናት ፍቅር በእናት አገር በእናት ምድር ጥማት እርዛት ስቃይ ውርደት ጐጆ ዘግቶ ዞሮ ስደት በልጆችሽ ሕይወት ሲደሰት የጥንተ ጥንት አኩሪ ታሪክ የቆራጥ ልጆችሽ ሃቅ ማኅተም ለአንድነትሽ ሕልውና ለሕዝቦችሽ ብልጽግና የወረደው የደም ቀለም ምን ይል ይሆን እናት ዓለም። በአዲስ ታሪክ አዲስ ዘገባ በሀቀኞችሽ ሕይወት ዕልፈት በክቡር ዓላማቸው የደም አምባ ቃል ይግባልን ከእንግዲህ ወዲያ ጡትሽ ከሃዲ ልጅ ላያጠባ። የባርነት ግርዶሽ ጽልመት የመከራ ቀንበር ጭነት እንክት ብሎ ሲወድቅ ስንጥቅ ሲል ሰንሰለቴ ነፃ ሲወጣ ነፃነቴ የአገር ምድር የአገር ሰማይ የአገር ሌሊት የአገር ፀሐይ የአገር ዙሪያ ክቡር አጽም የኔ ጋሻ የኔ ወንድም ባየሁህ ምነው ባየኸኝ «እከሌ» ብዬ በጠራሁህ «እከሌ» ብለህ በጠራኸኝ። የሰው የመሆን ምኞቴ የክብረ ስብዕና ጉጉቴ ጥሮ የማግኘት አምሮቴ የማይጨበጥ ባዶ ተስፋ በግፈኞች ግፊት የተደፋ በዕብሪተኞች ዕብሪት የተገፋ ለሰዓት ለደቂቃ በተፈጥሮ ስሌት ፈረቃ በቀን ውሎ በጨረቃ አቅመ ጉልበቴ ከአዋይ ምድር ጥረት ልፋቴ ከኔ ላይቀር እንዲሁ ብቻ በሰው ምስሌ በዕውን ሽፋን ባዶ ቅሌ ሲለገጥበት ዕጣ ዕድሌ በተረት ተረት የላም በረት ሲፌዝበት የኔ ዕውነት በኔ ወንድም በኔ ጋሻ በታሪኬ ማስታወሻ በእንተ ውሎ በእንተ ትግል በእንተ ሕይወት ዕልፈት ገድል ይኸውና አገግሜ በእንተ መሞት እኔ ቆሜ ሽብብ አንደበቴ ተፈቶ ጭልም ተስፋዬ ንጋት ቃኝቶ ጥውልግ ሕይወቴ ሕይወት ዘርታ «ባዶ» ገበናዬ «አዋይ» ሽታ ብሩህ ዘመን ብሩህ ፀሐይ በአገር ምድር በአገር ሰማይ በሁለንተናዬ ሕይወት አድማስ ወጋገኑ ደምቆ ሲታይ «ጋሻዬ» ዛሬ ብታየኝ። «የኔ ጋሻ» የኔ ወንድም የእናት አገር ክቡር አጽም ይኸውና በእንተ ትግል በሕይወትህ ዕልፈት ገድል ቋንቋዬ ቋንቋ ሆኖ የቃል ፍቺ ትርጉም ናኝቶ አድማጭ ሰሚ ወግ አግኝቶ ከኔም አልፎ የኔ ሕይወት የሀገር ሕይወት ሰው ተብዬ ሃሳብ ሰጥቶ ሃሳብ መውሰድ መናገርም ይኸው ችዬ የሕይወትን ድብቅ ሕይወት የፍጥረትን ሚስጢር አየሁ ሁሉን ነገር አስተዬ ሁሉን ነገር በውል ለየሁ። የአገር ምድር የአገር ሰማይ የአገር ጀንበር የአገር ፀኖይ የአገር ዙሪያ ክቡር አጽም «የኔ ጋሻ» የኔ ወንድም በእንተ ዓላማ በእንተ ትግል በሕይወትህ ዕልፈት ገድል የሕይወቴ ሕይወት ማህጸን የትውልዴ ዕድገት ዕርከን የነፃነቴ ምንች ጉልላት ክብሬ ካባዬ የምላት ልጄ ክንዴ የምትል የአንድነቴ ጋሻ መከታ የታሪኬ ሐረግ ድርና ማግ የሕልውናዬ አጥር አለኝታ በእናትነቷ የኮራሁ በልጅነቴ የኮራች በልጅ ልጅዋ ደም የጸናች እኔም የሀገሬ ሀገሬም ይኸው የኔ ሆነች። «የኔ ጋሻ» የኔ ወንድም የእናት ዓለም ክቡር አጽም የታሪክ ሐቅ ዕድገት ቅምር የዓላማ ደም ሕይወት ድምር የሩቅ ጉዞ አለኝታዬ ሐቅ አብሳሪ ሀቅ አላሚ የጥቃቴ ጋሻ ምክት ሊድል ግቤ ተፋላሚ የአገር ምኞት ሕያው ድርሳን የመራራ ትግል ክንዴ የወል ቋንቋ የወል ልሳን ክልል አልባ ተጓዥ ማዕበል የዓላማዬ መሪ «ማዕበል» ይኸውና በእንተ ውሎ በእንተ ትግል የደም ፍሬ ሕያው መልኩ ታዬ ዛሬ። «የኔ ጋሻ» የኔ ወንድም የእናት አገር ክቡር አጽም ለኔ ስትል አንተ አልፈውኸው አፈር ትቢያ የለበስከው መከራዬን በእንተ መክረህ የቁም ስቅሌን ሞቴን ሞተህ ጋራ ቋጥኝ የተጫነህ አፈር ትቢያ የተበየህ በእርግጥ ሞቴ ሞትህ ሆኖ ጽልመተ ሞት በእንተ ሰፍኖ ዓይነ ውሀህ በውል ቢፈስ አካል ገላህ አፈር ቢለብስ ቋንቋ ሆኖ «ባሕለ ሰው» ሕሊናዬን አጽጽቼ ሞትክን «ፉሞት» ነው ማለት ባልተው የአንተ ዓላማ ዓላማ የአንተ ዕምነት የአንተ መድረክ የአንተ ዕውነት ቋሚ ታሪክ ቋሚ ሰንደቅ ያልሞተ ሰው የማይሞት ሀቅ የአንተ ትግል የአንተ እልፈት ሕያው ታሪክ ሕያው ሕይወት ፀጋ ክብር የኔ ሸማ የአንድነቴ ሕይወት ማገር የነፃነት መቅረዝ ሻማ መሆኑንስ መች አጥቼ የታሪክ ምንጭ ባሕር ቅጂ የሀገረ ሰብ ቋንቋ ሆኖ ሞትክን ሞት ነው አልኩት እንጂ። የአገር ምድር የአገር ሰማይ የአገር ድንበት የአገር ፀሐይ የአገር ዙሪያ ክቡር አጽም «የኔ ጋሻ» የኔ ወንድም መከራዬን በአንተ መክረህ የቁም ስቅሌን ሞቴን ሞተህ ጋራ ቋጥኝ የተጫነህ አፈር ትቢያ የተበየህ በእርግጥ ሞቴ ሞትህ ሆኖ ጽልመተ ሞት በአንተ ሰፍኖ ዓይነ ውሀህ በውል ቢፈስ አካል ገላህ አፈር ቢለብስ የአንተ ዓላማ ላፍታም አይፈርስ ንጹሕ ገድልህ አይደፍርስ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact