Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ከምርጫው ማግስት እስከ ሰኔ አንድ በኋላ የቅንጅት አመራር ሊታሰር የሚችል መሆኑንና ድርጅቱ ሊዘጋና ሕገወጥ ሊባል እንደሚችል ግምት የነበራቸው አመራርች ነበሩ በዚያው ልክ ግን ኢህአዴግ ጭራሽኑ ጨርቁን ጥሉ ካላበደ በቀር እንዲህ ዓይነት የውስጥ ዴሞክራሲ ያለበት ድርድት ኢህአዴግ የወሰደውን ዓይነት አገርን ሊጎዳ የሚችል ውሳኔ ሊወስን ይችል ነበር።ሃ ህክ ሥርዓት ስለሆነ ነው ታዲያ የሚቀየረው እንዴት ነው። ተቀይሮ የሚተካው ሥርዓት ምን ዓይነት ነው። ድምጽ የጳማርኛ ሰርጭታቻውን ቋማሰዕፇም እፇደሚምጃረ ግርናኃ ጾር ብርዛኑ ነጋ በዚህ ሁኔታ ሰላማዊ ትግል ማለት ምን ማለት ነው።
ለሚለው ምርጫ ለጀመረውና ግን ለጊዜው በጉልበት እና በአፈና ምክንያት የተቋረጠ ለሚመስለው ውይይት አስተዋፅዖ የነባነት ገህ ሲቀደ እንዲያደርግ ነው በሌላ በኩል በምርጫ ሒደት ውስጥ በተቃዋሚዎች ጎራ በተለይም በቅንጅቱ አካባቢ የነበረውን የውይይት መንፈስ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አደረጃጀትና የመሳሰሉትን በቅንጅቱ የመጨረሻ ውሳኔዎች ላይ አስተዋፅዖ ያደረጉትን ጉዳዮች በመተንተን ለቅንጅቱም የወደፊት እንቅስቃሴ አቅጣጫ ለመጠቆም ከዚያም አልፎ ግን መጪው ትውልድ ይህ ትውልድ ከወሰዳቸው አርምጃዎች ተጠቃሚም ተጎጂም ሊሆን ስለሚችል እኛ ከወሰንናቸው ውሳኔዎች ወይንም ከመረጥነው መንገድ እውነተኛውን ትምህርት ቀስሞ የእኛን ስህተት እንዳይደግም በዚህም ከእኛ የተሻለ ሕይወት እንዲኖር ለመርዳት ነው ለልጆቹ የተሻለ ሕይወትን የማይመኝና በተቻለ መጠን የተሻለ የሕይወት እድልን ትቶ ለማለፍ የማይችል ትውልድና አገር በቁሙ እየሞተ ያለ አገር ነው የሚል ፅኑ እምነት አለኝ ምንም እንኳን እንዲህ ዓይነት ጽሑፍ ሲፃፍ በተቻለ መጠን የጸሐፊውን የራሱን ስሜት ሳይጨምር ገለልተኛ ሆኖ መፃፍ እንዳለበት ቢታመንም በተለይ ጸሐፊው የጉዳዩ ቀጥተኛ ተሳታፊ በሆነበት ሁኔታ እንዲህ ዓይነት ፍፁም ገለልተኛነትን ቢፈልገውም እንኳን በቀላሉ የሚሳካለት አይሆንም በውሳኔዎች ላይ ሲሳተፍ የገባበት በአዕምሮው ብቻ ሳይሆን በውስጥ ስሜቱም ስለሆነ እነኝህ ስሜቶች ጸሐፊው ሳያውቀውም በጽሑፉ ውስጥ ለመንፀባረቅ ያላቸው እድል ሰፊ ነው በትንሹም ቢሆን የራሱን ማንነት እና በጉዳዩ ላይ ያለውን ተሳትፎ መጠንና ዓይነት መጀመሪያውኑ ለአንባቢው በግልፅ ማቅረቡ አንባቢው የቀረቡለትን ቁምነገሮች ትክክል ነው በሚለው መልክ እንዲገነዘበውና ቁምነገሮቹንም ከራሱ አመለካከትና የውስጥ ስብዕና ጋር እያጣጣመ እንዲሞግተው ይረዳዋል የሚል እምነት አለኝ ስለዚህም በዚህ መግቢያ ላይ በትንሹም ቢሆን ከዚህ ጋር ይያያዛሉ በምላቸው ጉዳዮች ዙሪያ የራሴን ታሪክ እና አመለካከት እገልፃለሁ የፖለቲካ ስብዕና ጅማሮ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ የገባሁት ገና በለጋነቴ ነው ክፉም ሆነ በጎውን አይቼ አይደለም ሁለቱም ታላላቅ እህቶቼ ማትሪክ አልፈው በ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ ከዚያ በፊት ከቤተሰቦቼ ጋር ያደገ አጎቴም ዩኒቨርሲቲ ገብቶ በሕግ ፋከልቲ ውስጥ ይማር ነበር ጾር ብርዛኑ ነጋ እነኝህ ዘመዶቼ ቅዳሜ አና አሁድ ወደ ቤት ሲመጡ ብዙ ይጨዋወቱ የነበረው ስለ ዩኒቨርሲቲው እና በጊዜው ስለነበረው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ነበር በተለይ አጎቴ በጊዜው የተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎች ግርማቸው ለማ ወርቅነህ ቸርነት ወዘተ ጋር ጓደኛ ስለነበር አንዳንድ ጊዜ ሆን ብዬ አናቴን ምግብ አሰርቼ ለአጎቴ ይፔለት ወደ ዩኒቨርሲቲ እሄድ ነበር በጊዜው እነሱ ይህን ያመጣሁትን ምግብ ሲበሉ ብርቄ የነበረውን የካፊቴሪያ ምግብ እየበላሁ የእነሱን የፖለቲካ ውይይት ማዳመጥ ለአኔ በጣም ትልቅ ደስታ ነበር በ ዓም ኛ ክፍል ስገባ በዩኒቨርሲቲው የሚወጡ አንዳንድ የተማሪ ጽሑፎችን ማንበብ ጀመርኩ ትንሽ ቆይቼም በጊዜው በተማሪዎች አካባቢ ይነበቡ የነበሩ የማርክሲዝምና በተለይም የሌኒን ጽሑፎች በደንብ ባይገባኝም ማንበብ ጀምሬ ነበር መጽሐፎቹም ሆኑ በተማሪዎች የሚወጡት ጽሑፎች ሙሉ ለሙሉ ማለት ይቻላል የሶሻሊስት ወገንተኛ ጽሑፎች በመሆናቸው እኔም ፖለቲካን የጀመርኩት በዚያው ስሜት ነበር አነኝህን ጽሑፎች በማንበብ ከተፈጠረው ርዕዮተዓለም ይልቅ በንባቦቻችን ዓይኖቻችን ተከፍተው በአገራችን ውስጥ የነበረው የፍትህ ጥማት እና የድህነት ለከት ማጣት ከዚህም ጋር ተያይዞ አገራችን ከሌሎቹ አገሮች በጣም ወደቷላ ለምን ቀረች የሚለው ቁጭት ለብዙዎቻችን በዚያን ጊዜ ወጣት ለነበርነው ፖለቲካ ውስጥ ለመሳተፍ የበለጠ አስተዋፅዖ የነበረው ይመስለኛል የየካቲት አብዮት በግልፅ እስከሚፈነዳ ድረስ ከዚህ ውጪ ምንም ዓይነት ተሳትፎ አልነበረኝም በ የተማሪዎች እንቅስቃሴ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሲስፋፋ በአጠቃላይ የጠለቀ እውቀት ሳይኖረኝ በጊዜው የተነሱ ተማሪ ነክ እና አንዳንዴም አገራዊ ጥያቄዎች በማንበብ ከተማሪው እንቅስቃሴ ጋር ተቀላቀልኩ በ ዓም ማትሪክ መውሰድ የነበረብን ተማሪዎች ማትሪክ አንወስድም ብለን ስናምፅ በጊዜው የነበረው የወታደር ኮሚሽን የየትምህርት ቤቱን የተማሪ መሪዎች ለማነጋገር ሲጠራ ከንፋስ ስልክ አጠቃላይ የኛ ክፍል ተማሪዎችን በመወክል ተሳትፌአለሁ ከዚያም እድገት በሕብረት ዘመቻ እስከምፄድ ድረስ አዲስ አበባ ውስጥ በጥናት ቡድን ተቧድነን ከጥቂት ጓደኞቼ ጋር የፖለቲካ ጽሑፎችን በማንበብና በመወያየት ጊዜአችንን እናጠፋ ነበር እድገት በሕብረት እያለን የዘመቻው የፖለቲካ ኮሚቴ ውስጥ ተመርጩ እሰራ ነበር በዚሁ ዘመቻ ላይ እያለን ነበር ኢህአፓ አራሱን ፋ የነባነት ገህ ሲቀደ ያስተዋወቀበትን የፓርቲውን ፕሮግራም እና ጽሑፎችን ማግኘት የጀመርነው ጥቂት ሆነን በዚህ ፕሮግራም ላይ መወያየት እንደ ጀመርን ብዙም ሳይቀይ ዘመቻውን ትተን ወደ አዲስ አበባ ተመለስን ለመጀመሪያ ጌዜ የተደራጀ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የገባሁት አዲስ አበባ ከተመለስኩ በኋላ ነው ከዘመቻ ተመልሼ ብዙ ሳልቆይ በፍቅሬ ዘርጋው አማካኝነት ኢህአፓን ተቀላቀልኩ ይህ ሲሆን የ ዓመት ወጣት ነበርኩ ድርጅቱ ውስጥ ስገባ በአንድ በኩል አንድ የድርጅት ሕዋስ ውስጥ ገብቼ የፖለቲካ ውይይት ስናካሂድ በሌሳ በኩል ግን ቀጥተኛ የድርጅት ሥራ የምሰራው በፍቅሬ ዘርጋው በኩል የድርጅቱን ከፍተኛ አመራሮች በጊዜው ማን ምን አንደሆነ አላውቅም ነበር በየስብሰባውና ከተለያዩ የድርጅቱ አባሎች ጋር ሲገናኙ ወደ ቀጠሯቸው ማድረስና ከተወሰነ ሰዓት በኋላ መልሶ መውሰድ ነበር በዚህ ጊዜ ውስጥ በራሴ የፖለቲካ አመለካከት ላይ ትልቅ አስተዋፅዖ ካደረጉት ነገሮች አንዱ በጊዜው ከተስፋዬ ደበሳይ ጋር የነበርኝ ግንኙነት ነበር ተስፋዬ ደበሳይን በጊዜው እሱ መሆኑን አላውቅም ነበር ያወቅሁት በሞተ ጊዜ ሜዳ ሆፔ ፎቶውን ሳይ ነው ብዙውን ጊዜ በመኪና የማመላልሰው እኔ ነበርኩ በስብሰባዎች እና በቀጠሮዎች መሐከል በሚኖር ጊዜ ሰዋራ የሆኑ ቡና ቤቶች ወይንም ምግብ ቤቶች ፈልገን መኪና ውስጥ ቁጭ ብለን ለረጅም ጊዜ እናወራ ነበር ምንም እንኳን በጣም ትልቅ የዕድሜ ልዩነት ቢኖረንም በእውቀትም በድርጅቱም ውስጥ በነበረው ኃላፊነት አንፃር የማንገናኝ ቢሆንም በነኝህ ጊዜያት ያወራኝ የነበረው እንደ እኩያው ልጅ መሆኔን አስረስቶኝ ነበር ምንም እንኳን ስለ ሰውዬው ሙሉና ጥልቅ እውቀት ነበረኝ ለማለት ባልችልም በዚያ በልጅነት እድሜዬ የነበረኝና እስከ አሁንም በኅሊናዬ የቀረው የሰውየው ምስል በጣም ጭምት የሆነ በምንም ዓይነት የበላይ ነኝ የሚል ስሜት የማይታይበት በጊዜው በአዕምሮዬ ለሚጉላሉ ጥያቄዎች በቅን ልቦና መልስ የሚሰጠኝ ይበልጥ በጊዜው ይገርመኝ የነበረውና አሁንም ከትውስታዬ የማይጠፋው ያኔ በእኔ ጨቅላ እድሜ ለምጠይቃቸው መጠነ ብዙ ጥያቄዎች አንዳንድ ጊዜ «ለሱ ጥያቂ መልስ የለኝም» ወይንም «ይህን አላውቅም» ማለት ምንም የማይቸግረው መሆኑ ነው ከዚያ በተጨማሪ አንዳንድ ጊዜ መጽሐፍት ቤት እንሂድ ብሎኝ ስንሔድ የሚገዛቸው የመጽሐፍት ዓይነቶች በጣም የተቀየጡና ከሁሉም ጾር ብርፃኑ ነጋ ዓይነት ጸሐፊዎች ሶሺያሊስቶች እና ሶሻሊስት ያልሆኑ ብቻ ሳይሆን የተቃዋሚዎቻቸውን የተውጣጡ መሆናቸው በጊዜው በእኔ እድሜ አካባቢ ከነበረው «የሚያምነብበትን እምነት ያዘሉ ጽሑፎችን ብቻ የማንበብ» ኢ ምሁራዊ እና ኢዴሞክራሲያዊ አመለካክት ጋር የተለየ መሆነ ምናልባት እኔ ኢህአፓን አይበት የነበረበት እይታ በጊዜው እኩዮቼ ያዩበት ከነበረው የተለየ እንዲሆን ሳያደርገው አልቀረም ሜዳ ገብቼ የትጥቅ ትግሉን እስከምቀላቀል ድረስ ኢህአፓ በእርግጥም በዴሞክራሲ የሚያምንና በተለይም ለውስጠፓርቲ ዴሞክራሲ በሕቡዕ በመደራጀቱ ምክንያት ከሚፈጠሩ አስፈላጊ ከሆኑ ሚስጥራዊነት እና ግልፅነት ማጣት በስተቀር እራሱን የሰጠ ድርጅት ነው የሚል እምነት ነበረኝ ለድርጅቱም ያለኝ ፍቅርና በአመራሩም ላይ ያለኝ እምነት ምንም የማያወላዳና ሙሉ ነበር በ ዓም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቼ አንድሁለት ወር ሳንቆይ በተፈጠረው ብጥብጥ ምክንያት ዩኒቨርሲቲውን ለቅቄ ወደ በረሐ እንድሄድ ሲነገረኝ ያለምንም ማቅማማት እንደውም በደስታ ነበር ትግሉን የተቀላቀልሁት ስለ ፖለቲካ ምንነት አዲስ ግንዛቤ ምንም እንኳን የፖለቲካ ትግሉን የተቀላቀልኩት በንፁህ ልብ ቢሆንም የተቀላቀልኩትን ድርጅት ንፅህና ጥያቄ ላይ ሊጥል የሚችል ምንም ነገር አዲስ አበባ በነበርክበት ጊዜ ባላይም የኢህአፓን ሰራዊት የተቀላቀልኩ ቀን ከስራዊቱ አመራር የተነገረኝ በተወሰነ ደረጃ ይህንን ንፅህና ያጎደፈ እና ስለ ፖለቲካ ያለኝን አመለካከት በአጠቃላይና በተለይ ደግሞ ስለ ተቀላቀልኩት ድርጅት ምንነት ለመጀመሪያ ጊዜ እንድጠይቅ ያደረገኝ ነበር ማለት ይቻላል ሰራዊቱ ነፃ መሬት አንደ ደረስኩ የተቀበለኝ ጌራ የሚባል የአመራር አባል ስለ ሰራዊቱ መግለጫ ከሰጠኝ በኋላ አዲስ አበባ ስላለው ሁኔታ ይጠይቀኛል እኔም የወጣሁበት ጊዜ ብዙ ወጣቶች እየተያዙ የሚታሰሩበት እና ብዙዎችም የተገደሉበት ጊዜ ስለነበር ይህንነ በመግለፅ «የከተማው የትጥቅ ትግል» የሚያዋጣ አንደማይመስሰኝ እና በተቻለ መጠን መውጣት የሚችሉትን አባሎች እና ወጣቶች በቶሉ ማስወጣት እንደሚገባ አገልፅለታለሁ በዚህን ጊዜ ቁጣ በተሞላበትና በከረረ ድምፅ ይህንን ነገር የነካነት ገህ ሲቀደ እዚህ ሰራዊት ውስጥ ይህ የገባሁበት ወታደራዊ ድርጅት መሆኑን ለማንም መናገር እንደማልችል ድርጅቱን አደጋ ላይ የሚጥል ወይንም ሊጥል የሚችል መሆኑን ይነግረኛል ሁሉን ነገር በቀጥታና በንፁህነት ለሚያይ የወጣትነት እድሜ ይህ ንግግር በጊዜው በጣም እንዳስደነገጠኝ ትዝ ይለኛልየጌራ ቁጣ የተሞላ ምላሽ እኔ ጭንቅላት ውስጥ ከነበረው ድርጅቴ ጋር በፍፁም አልገጥምልህ አለኝ በዚህ ድርጅት ውስጥ ክአባሎች የሚደበቅ ያውም ማንም ከተማ ያለ ሰው የሚያውቀው ሚስጥር እንደሚኖር ብቻ ሳይሆን ሆን ተብሎ እንደሚዋሽ ስገነዘብ አራሴን ከውስጥ እምነት መናጋት ለማዳን በጊዜው የተጠቀምኩበት ስልት አውቂ ወይም አስቤበት ሳይሆን የከተማውን እና የገጠሩን አመራር በመለየት እውነተኛው አመራሮች ከተማ ያሉት ሲመጡ ይህ የመጀመሪያ ገጠመኝ የሚስተካከል ጊዜያዊ ችግር አድርጎ መውሰድ ነበር ይህ ችግር ግን የአንድ ጊዜ ሳይሆን በተደጋጋሚ የሚከሰት እየሆነ ሔደ በወታደራዊ ልምምድ ላይ በነበርንበት ጊዜም የልምምዱ ቦታ አካባቢ በሰራዊቱ የደኅንነት አባላት ጋንታ ይባል የነበር የሚታዘዝ እስር ቤት እንደነበረ ሰማሁ በዚህ እስር ቤት በተለያየ ምክንያት የታሰሩ የሰራዊቱ አባሎች እንደ ነበሩና በእነኝህ እስረኞች ላይ ሰቆቃ ይደርስ እንደ ነበር ስንሰማ በብዙዎቻችን በተለይ ከከተማ በመጣነው አባላት ላይ ከፍተኛ ግራ መጋባት ዘህዐበጠበፀበ ተፈጠረ በምንም ዓይነት የኢህአፓ ስራዊት አመራር አባላት ላይ ሰቆቃ ይፈፀማል ብሰን ለማመን ኣቃተን ከዚህም አልፎ በተለያየ ደረጃ የነበሩ የሰራዊቱን አመራር አባላት በግላጭ ስናያቸው እና በኛ ግምት የእነኝህ ሰዎች የመምራት ችሉታ ከምንጠብቀው ያነሰ ሲሆን በያለንበት እነኝህን ጉዳዮች በውይይት ክፍለ ጊዜ በቀጥታ ግን በተነጣጠለ መልኩ ማንሳት ተጀመረ እኔ በነበርኩበት ጋንታ በሚደረጉ ውይይቶች በጣም በለዘበ መልኩ በከተማ ውስጥ ያለውን ሁኔታ በሰራዊቱ ውስጥ የተመለከትናቸውን ችግሮችና በአጠቃላይም የድርጅቱን የወደፊት የትግል ስትራቴጂ በሚመለክት ድርጅቱ አንድ ሰፋ ያለ ጉባዔ ቢያካሂድ ጥሩ እንደሚሆን እስከዚያ ድረስ ደግሞ ከከተማ የመጡ የፓርቲው አመራር አባላትም ስላሉ በነሱ አማካይነት በሰራዊቱ ውስጥ የእርማት እንቅስቃሴ መካሄዱ ጥሩ እንደሚመስለን ይህ ደግሞ በፓርቲው አመራሮችም የታመነበት ነበር በውይይት ጊዜ በግልጽ እያነሳን እንወያይ ነበር ጾር ብርዛኑ ነጋ የእርማት እንቅስቃሴውም ታምኖበት ተካሄደና በዚያም መሠረት የተወሰነ የአመራር ለውጥ ቢደረግም በብዙ የሰራዊቱ አባላት በተለይም ከከተማ በመጣነው ዘንድ በበቂና በአመርቂ ሁኔታ ተካሂዲል የሚል እምነት አልነበረም ለማንኛውም በድርጅቱ ውስጥ በተለይ አጠቃላይ የፓርቲ ጉባዔ መካሄዱ ይጠቅማል የሚለው አስተያየት አልጠፋም ነበር ይህ ውይይት በተለያየ መልኩ እየተካሄደ ባለበት በዚህ ጊዜ ነበር በሰራዊቱ ውስጥ ሰራዊቱን ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ ሌላ ድርጅት አንኳ ተፈጥሯል የሚል ወሬ በአመራሩ አካባቢ መወራት ጀመረ ይህ ወሬ ብዙም ሳይቆይ በዚህ ጉዳይ ተጠርጥረዋል የተባሉ ጠደ ሰዎች እንዲታሰሩ ይደረጋል ከነኝህ ከታሰሩት ሰዎች መካከል አንዱ እኔ ነበርኩ ከነኝህ ውስጥ ግማሽ ያህል የምንሆነው በመጀመሪያው ቀን የታሰርን ሲሆን ቀሪዎቹ ይህንን «የአንጁ እንቅስቃሴ ከሥሩ ለመመንጠር በሚል በተካሄዱ ተክታታይ ስብሰባዎችገሚሱ በሌሎች «ሐቀኛ ታጋዮች ስለአንጃነታቸው የተጋለጡ ገሚሶቹ ደግሞ የታሰርነው ሰዎች ፃጢያት በአደባባይ ሲገለፅ ተደናግጠው «ራሳቸውን አጋልጠው» የታሰሩ ነበሩ ከኛ በኋላ ታስረው በመጡ ጳዎዶች ስለእነኝህ ስብሰባዎች የተነገረን ነገሮች በዕውነቱ በጣም የሚያስደነግጡና የሚያሳፍሩ ነበሩ በመጀመሪያ አንጃዎች» በድርጅቱ ላይ ምን ዓይነት አደጋ እንደ ፈጠሩ እና በቅርቡም እንዲህ አይነት በአዲስ አበባ ተፈጥሮ ድርጅቱን ያስመታው ይኸው አንጃ እንደሆነ በዚህም ምክንያት ብዙ ጓደኞቻችን በደርግ እንደ ተገደሉ በምሬትና እንባ በተቀላቀለው ስሜት ከአዲስ አበባ በቅርብ የመጡ የተመረጡ አባሎች ገለፃ ያደርጋሉ ይህን ተከትሎ በአመራሩ የተወከሉ አንድ ሁለት ካድሬዎች በዚህ በሰራዊቱ በተፈጠረው «አንጃ» ተመሳሳይ እንደሆነና ዋና ዓላማውም ከኢህአፓ ጠላቶች ጋር በመመሳጠር ሕወሓት ደርግ ወዘተ ሰራዊቱን ለማስመታት እንደሆነ ለዚህም ሙሉ ማስረጃ እንደተገኘና ይህም በፍርድ ሂደቱ በግልፅ እንደሚቀርብ ገለፃ ያደርጋል ከዚያ በኋላማ በየጥጉ የተቀመጡ የአመራሩ ታማኖች በየተራ እየተነሱ እኛ ያኔ በእስር ላይ ያለነው «ወንጀለኞች» የሰራናቸውን ወንጀሎች በሚመለከት ምስክርነት ይሰጣሉ ከዚያ ቀጥሎ ብዙኃኑ ታጋይና በተለይም ልክ እንደ እኛው በሰራዊቱ ውስጥ ችግር መኖሩንም ያምን የነበረ ተጋዳይ አንድም አራሱን ለማዳን አንድም በእርግጥም እኛ የታሰርነው ሰዎች አንጃ ሆነን» እሱን ለማሳሳት የሞከርን እንደሆነ በመውሰድ በስብሰባው ላይ የተነሳ በኛ የነባነት ገህ ሲቀደ በታሰርነው ሰዎች ወንጀለኛነትና እሱም እስከ አሁን የተሳሳተ መንገድ በመከተሉ መፀፀቱን በመግለፅ ድርጅቱ በእኛ «በአንጀኞች» ላይ በአስቸኳይ የሞት ቅጣት እንዲፈፅምብን ሲማፀን እንደነበር ስንሰማ በፍፁም ማመን ነበር ያቃተን በመጀመሪያ ላይ በድርጅቱ ላይ በነበረን እምነትና ከዚያም በላይ በተለይ እነኝህ በአኛ ላይ ሞት እንድንቀጣ የሚጠይቁብን ሰዎች በቅርብ የምናውቃቸው ጓዶቻችን ስለነበሩ ምናልባት አንዳንዶቻችን ሳናውቀው የተፈጠረ «አንጁ ነበር ወይ ብለን እዚያው «ሰንገደ እስር ቤት መጠያየቅ ጀምረን ነበር ከመሀላችን አንዳንዶቹ በዚህ ላይ የነበረው እምነት የፀና በመሆኑ ምክንያት ምንም እንኳን እሱ ራሱ ከተፈጠረው አንጃ መሪዎቹ አንዱ በመሆኑ አንደ ተከሰሰ እያወተና እንዲህ ዓይነት ድርጅት እሱ የሚመራው እንደሌለ እየተገነዘበም በድርጅቱ ላይ የነበረው እምነት ፅናትና በተለይ እነኝህ ሁሉ ጓዶች ሊሳሳቱ አይችሉም በሚል ስሌት ሠራ የተባለውን ወንጀል አምኖ ወንጀሉ እንዴት እንደ ተፈሀመ የሚገልፅ የአምነት ቃል በዝርዝር ጽፎ ለከሳሾቻችን የሰጠ ነበር በፍፁም ከማልረሳቸው አጋጣሚዎች እና በዚያ በወጣትነት አድሜዬ የስውን ልጅ የውስጥ ጭንቀትና በዚህም ምክንያት የሚገጥመሙትን የሕይወት ፈተናዎች የሚቋቋምባቸው አካሄዶች እስከምን ደረጃ ሊደርስ አንደሚችል ያየሁበት አንድ ሁኔታ ነበር ከታሰርነው ሰዎች መሐል አንዱ በእድሜው ከብዙዎቻችን ከፍ ያለ በዚያን ጊዜ ውጭ አገር ተምሮ የሁለተኛ ዲግሪ ያለው ሰው ነበር በተፈጠረው ሁኔታም በጣም ከተደናገጡት እና ከተረበሹት ሰዎች ውስጥ አንዱ ነበርሱ «ከአንጃው» መሪዎች አንዱም ተደርጎ ይወሰድ ነበር የፍርድ ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት ወንጀሉን በሚመለከት ሁለት ደብተር ሙሉ የእምነት ጽሑፍና ወንጀሉ እንዴት እንደ ተፈፀመ እነማን በወንጀሉ እንደተሳተፉ ምንም በሌለ ወንጀል ዘርዝሮ ለከሳሾቻችን ይሰጣል አስር ቤቱ ትንሽ ስለነበር ሁላችንም የምናደርገውን እንተያይ ስለነበር ከመሐከላችን አንዱ «እንዴ ምን ታሪክ ቢኖርህ ነው ይህንን ሁሉ የጻፍከው» ብሎ እንደ ቀልድ ይጠይቀዋል ለዚህ ምንም መልስ ሳይሰጥ በማግስቱም ይህንን ጽሑፍ ሲጽፍ ውሎ በሶስተኛው ቀን ጽሑፉን ለከሳሻችን ይሰጣል በሶስተኛው ቀንና ጽሑፉን ካስረከበ በኋላ ይኽው የቀድሞው ልጅ አሁንም ትንሽ መረር ባለ ቃል «የእውነት ይህ ሁሉ ታሪክ የፃፍከው ምንድን ነው። የዚህ ግንባታ አካል በመሆን የዴሞክራሲ ግንባታውን ለማገዝ በተወሰነ ደረጃ የሥልጣን ማጣትን ወይንም መገደብን ይቀበላል ወይንስ ከሥልጣኔ ምንም አይነካም በሚል በአክፈንጋጭ ጉዞ የአገሪቱን ችግር ያባብሳል የሚለውን ነው የፖለቲካ እንቅስቃሴው ውስጥ በቀጥታ ስገባ እነኝህን አመለካከቶች ይፔ የሚታየኝን የአገራችንን የወደፊት አደጋ ከተፈጠረ በኋላ ከንፈር ከመምጠጥ ይልቅ አደጋው እንዳይፈጠር መክላከል አውነተኛ የዜግነት ኃላፊነትን መወጣት ነው ከሚል እምነት ነው በአጠቃላይ ፖለቲካው ውስጥ እስከምገባ ድረስ የፖለቲካ አመለካከትን ብቻ ሳይሆን ስለ ፖለቲካው አካፄድ ያለኝን ስሜት በፀጠፀየበፀክህ የቀረፁትን የራሴን የሕይወት አጋጣሚዎች በሚመለከት ይህን ያህል ካልኩ ይህ ጽሑፍ የተፃፈበት ቦታና ጊዜ ሲፈጥራቸው የሚችላቸውን ወይም የፈጠራቸውን የጽሑፉን ድክመቶች ለአንባቢዎቼ በአጭሩ አስረድቼ ይህንን መግቢያ ልዝጋና ወደ ዋናው ቁምነገር ልግባ ይህ ጽሁፍ ለምን እንዳስፈለገ እና የሚያካትታቸው ቁምነገሮች ይህ ጽሑፍ የሚያጠነጥንባቸው ቁምነገሮች ቢያንስ ለስምንት ወራት በተካሔዱ ክስተቶች ላይ ነው ይህ ጊዜ በጣም ብዙ ነገሮች የሆነበትሁኔታዎች በጣም በቶሎ የሚቀያየሩበትና በፍፁም አረፍት የሚነሳ ብዙ ሥራ በጥቂት ሰዎች የሚሰራበት ጊዜ ነበር ጽሑፉን የፃፍኩት በጊዜው በተያዙ ማስታወሻዎች ላይ በመመስረት ሳይሆን ዝም ብዬ በአዕምሮዬ ከማስታውሰው የርዕቨበ ዘፀጠዕሰባ ስለሆነ ብዙ አስፈላጊ ቁምነገሮች ሊረሱ ይችላሉ ብቻ ሳይሆን መረሳታቸውም አይቀርም ይህም የጽሑፉን ምሉዕነት ርጠፀከ ያሳጣዋል የዚህን ጊዜ ታሪክ በተረጋጋ መልኩ ወደፊት ሲፃፍ ይህ ችግር ይወገዳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ቅንጅት እንደ ተመሰረተ ለእኔ የተሰጠኝ የምርጫ ዘመቻ ኮሚቴውን የመምራት ኃላፊነትና ከዚያም በተጨማሪ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው አባል በመሆኔ በምርጫ ዘመቻው ወቅትም ሆነ ከዚያ በኋላ ቅንጅቱ ባደረጋቸው ውይይቶችም ሆነ ውሳኔዎች በሙሉ እንኳን ባይሆን በጣም የነባነት ገህ ሲቀደ በአብዛኛው ተካፋይ ስለነበርኩ ወሳኝ ናቸው የምላቸውን ጉዳዮች በቀጥተኛ ተሳታፊነት ስለማቀርበው ብዙ ጉዳዮች አይረሱኝም የሚል ተስፋ አለኝ በጊዜው በቅንጅቱ ውስጥ ባሉ አመራር አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተለያየ አመለከከት ስለነበረ በተወሰነ ደረጃ ይህ ከተለያየ ድርጅትና ድርጅታዊ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነበር እንደ ቅንጅቱ አንድ አቋም ለመውሰድ በጣም ብዙ የጦፉ ክርክሮች ይደረጉ ነበር በእነኝህ ክርክሮች ውስጥ ከነበረኝ የነቃ ተሳትፎ አኳያ የነበሩትን የተለያዩ አመለካከቶች በሙሉ እንዳለ ማቅረብ እንኳን ባልችል መሠረታዊ የሆኑትን ነጥቦች ለማቅረብ የምችል ይመስለኛል ሌላው ቢቀር ግን በጊዜው እኔ ራሴ ይዢ ስከራከርባቸው የነበሩትን አቋሞች በጊዜው ከነበሩኝ ምክንያቶች ጋር በእውነተኛነት ለማቅረብ የማስታወስ ችሎታዬ አይከዳኝም የሚል ተስፋ አለኝ በቅጡ ማስታወስ ያልቻልኳቸውን ነገሮች በጊዜው አብረውኝ የነበሩ ጓደኞቼ እዚሁ አብረውኝ ታስረው ስላሉ እነሱን እየጠየቅሁ ለማሚላት ሞክሬአለሁ ነገር ግን እውነት ናቸው ብዬ ያቀረብኳቸውን ቁምነገሮች በጊዜው ከተፃፉ ፅሑፎች መግለጫዎችና ሌሎች ሰነዶች ጋር ለማመሳከር ያለሁበት ሁኔታ አይፈቅድልኝም ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነት ስህተት ሊፈጠር ይችላል ብሎ በማስብ በመጠኑም ያስታወስኩትን ነገር ከመጫር ከምታቀብ ይልቅ ባለመመሳከር ምክንያት ሊፈጠሩ የሚችሉ ልዩነቶች ቢኖሩም እንኳ ጽሑፉን ለአንባብያን ማቅረቡ የተሻለ አማራጭና የታሪክ ግዴታ ነው ብዬ አስባለሁ በእርግጥም ይህን ጽሑፍ ቆይቶ ማውጣት ይቻላል መቼ እንደሆነ ባይታወቅም ከእስር መፈታታችን አይቀርም በዚያን ጊዜ ያሉትን የሰነድ ማስረጃዎች አሰባስቦ የተሻለ ጽሑፍ ማቅረብ ይቻል ይሆናል የዚህ ችግር ይህ ጊዜ መቼ እንደሆነ አለመታወቁና ከላይ እንደጠቀስኩት ጊዜው እየረዘመ ሲሔድ ብዙ ቁምነገሮች በተለይ በጊዜው የነበሩ አስተሳሰቦችና ምክንያቶች መረሳታቸው ነው ከዚያም በላይ ግን ይህ ጽሑፍ በቶሎ ሊወጣ የሚያስፈልግበት ምክንያት አለ የግንቦቱን ምርጫ ተከትሉ የተፈጠሩትን ሁኔታዎች ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ ብቻ ሳይሆኑ በግል ድክመታቸው ምክንያት ለኢህአዴግ መሣሪያ የሆኑ ኃይሎች የራሳቸውን የተዛባ ታሪክ እየፃፉበት ነው ኢህአዴግ ያልተገደበ ሥልጣኑን ይዞ ለመቆየት ሲል የጀመረውን የግንቦቱን ዴሞክራሲያዊ ሂደት የመቀልበስ ጉኮ ምክንያታዊ ለማስመሰል በሰፊው የያዘው የበሬ ወለደ ፕሮፖጋንዳ አለ በዚህ ሂደት ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ የነበራቸውንና ይህንን የቅልበሳ ጾር ብርሃኑ ነጋ ጉዞ ያደናቅፉብኛል ያላቸውን የተቃዋሚ መሪዎች አስሯል የፈጠረውን አስቂኝ ክስ አሳዛኝ ባይሆን ኖሮ እውነት ለማስመሰል ማድረግ ያለበት ታሪክን ፍፁም መቀየር ነው ይህንን ደግሞ የኢህአዴግ መሪዎች ይከተሉ ከነበረው የርዕዮተ ዓለም መሪዎች ታሪክ ተምረዋል ለዚህም ነው የኃይል ቅልበሳ እርምጃውን መውሰድ ሲጀምሩ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውን ብቻ ሳይሆን ይህን እውነት ሊያወጡ ይችላሉ ብለው የፈሯቸውን ጋዜጠኞች አጠገባቸው ያሉትን ማሳሰር በሩቅ ያሉትን በክሱ ውስጥ ማስገባትና በዚህም እንዲሸማቀቁ ማድረግ ያፈኑት እንዲሁም ኢህአዴግ ትንሽም ነፃ የሆነ የሲቪክ ማኅበረሰብ ካለና በተለይ እነኝህ በምርጫው ውስጥ የተደረገውን ቅጥፈት ያውቃሉ ያወቁትን ለመናገር ደግሞ አይፈሩም ያላቸውን እዚህ አስቂኝ የፈጠራ ክስ ውስጥ በመቀላቀል እነሱን ለማቆየት ብቻ ሳይሆን እንዲህ ዓይነት ፃሳብ ሊኖራቸው የሚችሉ የሲቪክ ማኅበረሰብ አባላት አሁንም ከእስር ውጭ ካሉ እነሱንም ለማሸማቀቂያ ደራርቦ በእስር የክተተው ትንሽ የሚከብድ ሆኖባቸው ነው አንጂ የተከሳሾቹን ዝርዝር ሲያዘጋጁና በውጭ አገር የሚገኙ አይደግፉንም የሚሏቸውንና ወደፊትም ተሽማቅቀው ከተቃውሟቸው አይታቀቡም ያሏቸውን የኢትዮጵያ ዝርያ ያላቸውን ሁሉ ሲከትቱ የአውሮፓ የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን መሪ የነበሩትን ወይዘሮ አና ጎሜዝን በዚሁ ክስ ውስጥ ከትተው ቢያርበደብዲቸው ምንኛ ደስ ባላቸው ነበር ስለዚህ ይህ የቅልበሳ አካሄድ ታሪክንም ለመቀልበስ የመሞከር ሂደት ስለሚያካትት ይህንን ለመክላከል በጊዜው የነበሩት አውነቶች ሳይረሱና በተቻለ መጠን ሳይሸራርፉ በቶሎ ማቅረቡ የታሪክ ቅልበሳውን ብቻ ሳይሆን በዋነኛነትም የዴሞክራሲ ቅልበሳውን ሂደትም ሊገታው ይችላል በሚል ስሌት ነው ይህን መጽሐፍ በቶሎ ለመፃፍና ለማውጣት የተሞከረው ከግንቦት ሰባት ጀምሮ በኢህአዴግ መሪዎችና በአንዳንድ አጫፋሪዎቻቸው እየተወሰደ ያለው እርምጃና ከእርምጃውም በኋላ ሕብረተሰቡን ዓይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ የሚለው የሚገርም ዓይነት የተራ ብልጥነት አካፄድ የኅብረተሰቡን የማመዛዘን ችሎታ የሚያኮስስ ስለሆነም በጣም የሚያናድድ ብቻ ሳይሆን በእኔ እምነት በኢህአዴግ ውስጥ ላሉና የደርግን ስርዓት ሲታገሉ ለነበሩ በዚሀም ምክንያት ብዙ የሚወዷቸውን ጓደኞቻቸውን ላጡ ታጋዮች የሚያሳፍር ይመስለኛል ይህን ጽሑፍ ስፅፍ ለኔ በግል የማውቃቸውና በውስጣቸው ምንም ክፋት የሌለ ትንሽም ቢሆን በጊዜው ከሥልጣን ከሚገኝ ፍርፋሪ በላይ ሊያስብ የነባነት ገህ ሲቀድ ው ው የሚችል አዕምሮና እውነተኛ የአገር ፍቅር ስሜት ያላቸው ተጋዳዮች እንደማናችንም አብረው አንጀታቸው ሲቃጠል ይታየኛል ስለዚህም ይህን ጽሑፍ የምፅፈው በምንም አይነት በጥላቻ ላይ ተመስርቼ አይደለም በጥላቻ ላይ የተመሰረተ አስተሳሰብና ፖለቲካ ሁሉንም ይዞ ገደል የሚገባ እንጂ ምንም አዎንታዊ ውጤት እንደማይኖረው በምርጫ ዘመቻው ጊዜ እየዞርኩ አስተምር የነበረውን አሁን በእነኝህ ኃይሎች በመታሰሬ አልቀየርኩትም እንዲያውም አጠናክርኩት እንጂ ባለቤቴ «ጥላቻ ራስን የሚጎዳ በሽታ ነው አንድን ሰው ጠላሁ ብለህ የምታሳርረው ቆሽት የአንተን እንጂ የጠላኽውን ሰው አይደለም አሱማ መጥላትህንም ሳያውቀው ይችላል» ትለኝ ነበር የኢህአዴግ መሪዎች እየፈፀሙት ያለውን ለአገር ብቻ ሳይሆን ለራሳቸውም የማይበጅ በደል መነሾው ከሥልጣን ፍቅርም በላይ እኛ በቅጡ ያልተረዳንላቸው በውስጣቸው ያለ መጥፎ ጥላቻ ይመስለኛል የዚህን የጥላቻ ጋኔን ለማስወጣት መልሱ ሌላ ጥላቻ ሊሆን አይችልም መልሱ ፍቅርና መተሳሰብ ነው ስለዚህም ነው ይህን ጽሑፍ በተቻለ መጠን አዎንታዊ ዞርዚክ በሆነ ስሜት ለመፃፍ የሞክርኩት ይህ ማለት ግን ስሀተቶችን ዝም ብሎ ማለፍ ሳይሆን በተቻለ መጠን ሙግቱ ከፃሳቦች ጋር እንጂ ከሰዎች ጋር እንዳይሆን ሞክሬአለሁ ሁኔታው አስገድዶ የግለሰብ ስሞች በሂስ መልክ ከተነሱ የስማቸው መገለፅ ለሚቀርበው ቁምነገር በጣም አስፈላጊ ሲሆንና ከዚያም በላይ ደግሞ ወደፊት እነኝህ ግለለቦች በዚህ ጽሑፍ ላይ በቀረቡት ቁምነገሮችና እውነቶች ላይ የተለየ አመለካከት ካላቸው ይህንኑ ለማቅረብ እንዲችሉ ለመጎንተል ነው በዚህ ጽሑፍ ምክንያት የማንንም ስሜት ለመጉዳት አልታሰበም የጽሑፉ አላማም አይደለም በዚያው ልክም የአገራችንን የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሒደት የሚያሰናክሉ ዛፃሳቦችንና አመለካከቶችን ለማጭበርበሪያ የሚቀርቡ ተራ ውሽቶችን እስካወቅኋቸው ድረስ ዝም ብዬ አላልፋቸውም ይህን ደግሞ በኢህአዴግና በአማካሪዎቻቸው ላይ ብቻ ሳይሆን በተቃዋሚው ጎራም ከተከስተ ማንሳቴ አይቀርም ይህ ጽሑፍ በምንም መልኩ የቅንጅቱ ኦፊሴላዊ ግምገማ ተደርጎ ሊወሰድ አይችልምአይገባምም ምንም እንኳን አጋጣሚው ከተፈጠረ ብዬ ጽሑፉ ከመውጣቱ በፊት አጠገቤ ያሉትን አንዳንድ የአመራር አባላት እንዲያዩትና ስህተቱን እንዲያርሙት ለማድረግ ብሞክርም ባለንበት ሁኔታ እስር ቤትም ውስጥ የምንሰራውን ነገር ሁሉ በቅርብ የሚከታተሉ ስላሉ ሊሳካልኝ አልቻለም ከዚህም በላይ ግን አንዳንድ የቅንጅቱ አመራሮች ጾር ብርፃኑ ነጋ በዚህ ጽሑፍ ላይ ከተነሱት አንዳንድ ነጥቦች ጋር በሐቁ ዞ ወይንም በትንተናው ልከዘህ ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል በቅንጅቱ ውስጥ ከተመሰረተ ጀምር ምናልባትም በአመሰራረቱ ሁኔታ የተለያዩ አስተሳሰቦችና አመለካከቶች ይንዐባረቃሉ ቅንጅት ከዚህ በፊት አንደምናውቃቸው ማርክሲስት ፓርቲዎች ሁሉም አንድ አይነት አስተሳሰብ ያለው ግለሰባዊ ማንነቱን ለድርጅቱ የሸጠ ሰው የተሰባሰበበት ድርጅት አልነበረም ድርጅቱ እንኳን ይህንን ቢፈልግ በድርጅቱ አመራር ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰዎች በምንም አይነት የሚቀበሉት አልነበረም እነኝህን የተለያየ አመለካከት ያላቸውን ሰዎች በተወሰኑ ቁልፍ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ተመሳሳይ አቋም ይዘው በጋራ እንዲንቀሳቀሱ ማድረጉና ልዩነቶች በሚነሱ ጊዜም ማቻቻልና እርስ በርስ እየተሞራረዱ ለመራመድ መቻል ቀስ በቀስ እየተለመደ ይሄድ የነበረ የቅንጅት ባህል ነበር ለዚህም አስተዋጽዖ ካደረጉት ነገሮች አንዱ በእኔ ግምት በቅንጅቱ አመራር ውስጥ በሁሉም ጉዳይ በአስተሳሰብ በሥራ ችሉታ በፖለቲካ አውቀት ወዘተ የበላይነት የያዘ ወይም ሊይዝ የሚችል ግለሰብ አለመኖሩ በዚህም ምክንያት በስብሰባችን ላይ በሚደረጉ ክርክሮች አቋም ይያዛል እንጂ ቀድሞ ይዞ የመጣውን ወይም የነበረውን አቋም በአመራሩ ላይ ለመጫን የሚችል ሰው አልነበረም ብዙዎቻችን በተለያዩ ጊዜዎች በተለያዩ ጥያቄዎች ላይ ስብሰባ ከመግባታችን በፊት የነበረንን አመለካከት በስብሰባው ላይ በሚቀርቡ የተለዩ ዛሳቦችና ምክንያቶቻቸው በመመርኮዝ እንቀይር ነበር ይህ ማለት ከስብሰባ ውጭ በአመራሩ አባላት መካከል ቅስቀሳ ቢዐከነ መደራረግ አልነበረም ለማለት አይደለም ብዙው ነገር ግን ከስብሰባ በፊት በቅስቀሳ የተወሰደ አቋም እንኳን በስብሰባ ላይ የተሻለ ምክንያት ልየፀህጠፀበከህ ከቀረበ በቀላሉ ይቀየር ነበር ይህ እየተለመደ የፄደ ባህል የውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲን የማስፋት እድል ነበረው እንዲህ ዓይነት የውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲያዊ ባህል በሌለበት ደግሞ ለሰፊው ማኅበረሰብ ያውም የፖለቲካ ሥልጣን ከያዙ በኋላ በአስተማማኝ መልኩ ማቅረብ ይቻላል ብዬ አላምንም ለማንኛውም ቅንጅት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምር የነበረውን ታሪክና አጠቃላይ የፖለቲካ ግምገማ ወደፊት ኦፊሴላዊ በሆነ መንገድ ያቀርባል የሚል አምነት አለኝማቅረብም አለበት አሁን ያለው የአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ግን ይህንን መጠበቅ ስለማይችል እስከዚያው ድረስ ይህችው የኔ ጽሑፍ መውጣቷ ይጠቅማል አላለሁ በመጨረሻም ለእኔ የዚህ ጽሑፍ መለያ እንዲሆን የምሻው የጽሑፉ ትኩረት ባለፈው ላይ ለመንገታገት ሳይሆን የወደፊቱ የፖለቲካ ሕይወታችን ላይ መሆነ ነው በእኔ ግምት ፖለቲካችንን እንዲህ መቋጫ እንዲያጣ የሚያደርገው የፖለቲካ ልሂቆቻችን በጣም የሚያስቡትና አስተሳሰባቸውንም የነባካነት ገህ ሲቀደድ ክፉኛ የተጠናወተው የኋላው ታሪካችን መሆኑ ነው ማንም አገር ስለታሪኩ ማሰብ አለበት ታሪኩን የሚያስበውና የሚያውቀው ግን ከታሪኩ ጥሩውንና መጥፎውንም አውቆ በተለይ ያለፈ ስህተቱን እንዳይደግም ለማድረግ ነው የአሁኑ ትውልድ የአሁኑን ሕይወት ለማሻሻል አሁን ማድረግ እንዳለበትና ከዚያም አልፎ ግን ለልጆቹ ለመጪው ትውልድ የተሻለ ሕይወትን ትቶ የሚያልፍበት መንገድን መተለም አለበት ይህ ነው ሁሌም ሊያስጨንቀው የሚሜገባው ጉዳይ የታሪካችን ጠባሳዎች የአሁኑንና የወደፊቱን ሕይወታችንን ሊያጨልሙብን አይገባም ለእኔ ዘመናዊ ፀወየበ አስተሳስብ ማለት ስለወደፊቱ የሚያስብና የሚመለከት ዮርዮ ህቋየበ ሀፌዷ« አስተሳሰብ ነው በተለይ አሁን ሁሉም ነገር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረና ዓለሙም ፍፁም እየጠበበ ባለበት በአንድ ጊዜ በፍዑም ጠላትነት እርስ በእርስ ሲጨራረሱ የነበሩ አገሮችና ብሔሮች ለምሳሌ ቻይናና ጃፓን በፍጥነት የሚሔደው የዓለም የሥልጣኔ ባቡር እንዳያመልጣቸው የድሮውን ቂም ወደ ኋላ አድርገው የወደፊቱን በማሰብ ለከፍተኛ ትብብር በሚሰሩበት ዓለም ያውም በአንድ አገር ውስጥ ያለን ሰዎች ያለፈውን ይዘን በቂም ልጆቻችንን መጉዳት ትክክል አለመሆነ ብቻ ሳይሆን በእውነት ፍፁም ኋላ ቀር በሆነና ከጊዜው ጋር የማይሄድ አስተሳሰብ ነው ሁላችንም ያለምንም ማመንታት ልንጠላው የሚገባ የአድህሮት አስተሳሰብ ትሪት ነው ስለዚህም ይህ ጽሑፍ ሲፃፍ ዓላማው ያለፈውን ከማስታወስም በላይ ሀዲዱን የሳተውን የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት መልሰን ወደ ሀዲዱ የምንመልስበት ከዴሞክራሲያዊ ግንባታ ጋር ድህነትንና ኋላቀርነትን ተባብረን የምናሽንፍበትን መንገድ ለመሻት ነውወ ይህ ጽሑፍ አራት ዓብይ ክፍሉት አሉት አያንዳንዱ ክፍል በተለያዩ ምዕራፎች ተከፍሏል ክፍል አንድ የግንቦቱን ምርጫ በተገቢው አውድ ክፎሄህ ለማስቀመጥ እንዲረዳ ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ ለምን ያስፈልጋል። ይህ ወደፊት የበለጠ የምናየው ይሆናል መብቱን በጉልበቱ ሊቀማው ከሜፈልግ ኃይል ጋር ምን ያህል ተጋፍቶ ይሄዳል የሚለው ብቻውን ለሕዝዙ የዴሞክራሲ ፍላጎት መኖር አለመኖር ወሳኝ አይመስለኝም የጉልበት እመቃ በሌለበት በሰላማዊ መንገድ ፍላጎቱን ያለምንም ስጋት በሚገልጽበት ጊዜ ያሳየው ፍላጎት ይመስለኛል የእውነተኛ ፍላጎቱ መለኪያ ሕብረተሰቡ ነፃነትንና ዴሞክራሲን ይፈልጋል ማሰት በራሱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በአገራችን በአስተማማኝ መልኩ ለመገንባት በቂ ነው ማለት አይደለም በአገራችን እውነተኛ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የሚያጋጥሙ ችግሮችንና እንቅፋቶችን ከወዲሁ ለማወቅ መሞከር ቢያንስ ሂደቱን የጨለማ ጉዞ ከመሆን ያድነዋል በሚቀጥለው ምዕራፍ በእኔ ግምት ወሳኝ ናቸው በምላቸው የዴሞክራሲያዊ ሂደት ግንባታ ጋሬጣዎች ላይ አተኩራለሁ ጾር ብርፃኑ ነጋ ምዕራፍ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በኢትዮጵያ ለመገንባት የሚገጥሙ ዋና ዋና ችግሮች ሕገመንግሥት ስለተጻፈና ስለፀደቀ ዴሞክራሲ አለ ማለት እንዳልሆነ ሩቅ ሳንፄድ እዚሁ በአገራችን ያየነውና እያየን ያለነው ነው እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ከሕጎችና ከመንግሥታዊ መዋቅሮችም በላይ መሠረታዊ እና ለዚያ ዓይነት ሥርዓት የሚመች በማኅበረሰቡ ውስጥ የሰረፀ አስተሳሰብ ዚህ ያስፈልጋል ይህ ደግሞ በአንድ ጊዜ የሚመጣ ሳይሆን በጊዜ ብዛት ከዚያ ቀደም የነበሩት ኢ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰቦችና ባህሎች እየደከሙ እና በአዲሱ አስተሳሰብ እየተቀየሩ ሲሄዱ የሚመጣ ነው ይህ ሥርዓት ከነሙሉ አስተሳሰቡ ለመስረፅ የሚወስደው ጊዜ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመሥረት ከልባቸው በሚፈልጉ ዘመናዊ ኃይሎችና በተለያየ ምክንያት የቀድሞውን አስተላሰብ የሙጥኝ ብለው በያዙ ኃይሎች መካከል ፖለቲካው ዴሞክራሲያዊ ከተባለ በኋላ ሳይቀር በሚደረግ የረጅም ጊዜ የፃሳብ ትግል ሞክራሲያዊ ሥርዓት መፈለግና እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመሥረት ለየቅል ናቸው ዴሞክራሲያዊ የሚባል የነፃነት ገህ ሲቀድ በኋላ ሁለቱ የተቃርኖ ኃይሎች በሚያሳዩት ድክመት እና ጥንካሬ ይወሰናል የፖለቲካ ሥርዓቱ ዴሞክራሲያዊ መሆን እንዳለበት በኅብረተሰቡ ዘንድ ስምምነት ኖሮ በዚህ ምክንያትም ለዴሞክራሲ ሥርዓት አስፈላጊ የሚባሉት የመንግሥት ተቋሞች ተዘርግተውና የመንግሥት ሥልጣን የያዙት ኃይሎችም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ሙሉ ፍላጎት ኖሯቸው ሳይቀር እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ለዚህ ዓይነት ሥርዓት መሠረት የሚሆኑ ማኅበራዊ አስተሳሰብ በሌለባቸው አገሮች የዴሞክራሲ ጉዞ ቀላል አይሆንም በሥልጣን ላይ የሚቆዩት መንግሥታት እንዲህ ዓይነት ሥርዓት መመስረቱን የማይፈልጉና በተለያየ መንገድ እንቅፋት የሚሆኑ ከሆነ ይህን ሥርዓት መመሥረት የዚያኑ ያህል አስቸጋሪ ትግሉንም ረጅም ያደርገዋል በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመሥረት የሚገጥሙ ችግሮችን በሁለት ክፍሎች ለይቶ ማየት ይጠቅማል የመጀመሪያው የዴሞክራሲ ትግሉ በሚካፄድበት ወቅት ካለው የመንግሥት ምንነት ውጪ በጠቅላላው ከባህላችን ከታሪካችን እና የዚሁ ውጤት ከሆነው አጠቃላይ አስተሳስባችን ጋር የተያያዘ እና ምናልባትም በመንግሥትነት መንበር ላይ ያለው ኃይል ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባት ከልቡ ቢፈልግ እንኳን የሚገጥሙትን ችግሮች ታሳቢ የሚያደርግ ነው ሁለተኛ ው ደግሞ የመንግሥት ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል ለእውነተኛ ዴሞክራሲ መኖር እንቅፋት ሊሆን የሚችልባቸውን ምክንያቶች እና መንገዶች ታሳቢ የሚያደርግ ነው በዚህ ምዕራፍ እነዚሀን ሁለት ክፍሎች በየተራ እናያለን ከመንግሥት ምንነት ውጪ ያሉ የዴሞክራሲ ግንባታ ችግሮች ከመንግሥት ምንነት ውጪ የሚገጥሙ ችግሮች ሲባል መንግሥታት በእነዚህ ችግሮች ላይ ምንም ተፅዕኖ የላቸውም ወይም እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ አስተዋጽዖ አይኖራቸውም ለማሰለት አይደለም በማኅበረሰባችን ውስጥ ያለውን አመለካከት በመቅረጽ ረገድ በታሪክ የነበሩን መንግሥታት ወይም የመንግሥት ሥርዓቶች በተወሰነ ደረጃ ሁነኛ ሚና ተጫውተዋል ነገር ግን ከመንግሥታትም ውጪ በተለይ አስተሳሰባችንን ቅርፅ የሚሰጡ ባህላዊና ዛይማኖታዊ እሴቶቻችን የዚያኑ ያህል ወይም ከዚያም በላይ ተፅዕኖ ስላላቸው ሰየብቻ ለይቶ መመልከቱ በጣሙን ይረዳል ከዚያም በላይ ግን እነዚህን ችግሮች በአዋጅ ወይም መንግሥት በሚያወጣው መመሪያ በቀላሉ የምንገላገላቸው አይደሉም ስለዚህም ጾር ብርፃኑ ነጋ የበለጠ በፈጠራ የተሞላ መፍትሔ መፈለግና ማሰብ አለብን በዚህ ዙሪያ ከማነሳቸው ነጥቦች አንዱ ማኅበረሰባችን ስለ መንግሥትና ስለ ሥልጣን ያለው አስተሳሰብ ነው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መነሻ የሆነው «ሥልጣን የሕዝብ ነው» ለሚለው ፃሳብ መንደርደሪያ የሆነ የመንግሥት ምንነት ጽንሰሃሳብ አለ ይኸው ጽንሰ ፃሳብ መንግሥት የሕዝብ መገልገያ ተቋም ነው ብሎ ይነሳል የሰው ልጆች በጋራ አብረው ሲኖሩ የተለያዩ ድሮች ያስተሳስሯቸዋል እነዚህ ግንኙነቶች በብዙ በጎ ነገር የሚያስገኘ ትን ያህል ግጭቶች ሊፈጠሩ ይችላሉ ሰዎች እነዚህ ግጭቶች የሚፈቱባቸውን ስልቶች ማመቻቸት አለባቸው በተጨማሪም ግለሰቦች ብቻቸውን የማይሰሯቸው በርካታ ሥራዎች አሉ ለምሳሌ መንገድ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ይጠቅማል ነገር ግን አንድ ግለሰብ ብቻውን የሚሠራው አይደለም የዚህ ዓይነት ብዙ ምሳሌዎች አሉ ኢኮኖሚስቶች እንደነዚህ ዓይነት ምርቶችን የሕዝብ የወል ምርቶች ዖሀይዘር ፀ ይሏቸዋል በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉ ግጭቶችን ለመፍታትም ሆነ በግለሰብ ደረጃ ማቅረብ የማይቻሉትን የጋራ መገልገያ ምርቶች ለማቅረብ ኅብረተሰቡ አንድ የጋራ ተቋም ያስፈልገዋል ይህም የጋራ ተቋም መንግሥት ይባላል እነዚህን የጋራ ሥራዎች እንዲተገበሩ የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን እያንዳንዱ ሰው ለዚህ ተቋም ግብር ይከፍላል ይህ ተቋም ከሕዝብ በግብር መልክ በሰበሰበው ገንዘብ የኅብረተሰቡን የጋራ ጥቅም ያስጠብቅበታል ይህ ተቋም የኅብረተሰቡን ጥቅም ለማስጠበቅ ሥራውን በተቀላጠፈ ለሁሉም እኩልና ሚዛናዊ በሆነ መልክ መሠራት አለበት ግለሰቦች ከመብታቸው እና ከንብረታቸው አዋጥተው የፈጠሩት ይህ ተቋም ከመጠን በላይ ገዝፎ መልሶ የፈጠሩትን ሰዎች እንዳይበላ ፈጣሪዎቹ ይህን ተቋም የሚቆጣጠሩበት መንገድ ማበጀት አለባቸው የሕዝብ የበላይነትን ለማረጋገጥ ፍቱን መድኃኒቶቹ የሚከተሉት ናቸው አንደኛ ይህ ተቋም በሕዝብ የተፈጠረ መሆኑን ለማረጋገጥ የተቋሙን መሪዎች ሕዝቡ ራሱ በነዓነት የመረጣቸው መሆን አለባቸው ሁለተኛ ይህ የተመረጠውም ኃይል አንዴ ተመርጫለሁ ብሎ ከዚያ በኋላ የፈለገውን እንዳያደርግ ምርጫው በተወሰነ ጊዜ የሚደገምና የሕዝብ ውክልናው የጊዜ ገደብ እንዳለው መረጋገጥ አለበትፁ ሦስተኛ ኅብረተሰቡ በጋራ የሚሠራቸው እና ከዚህ ተቋም የሚፈልጋቸው ግልጋሎቶች ሰፊ ስለሆኑ ይህን ሁሉ ግልጋሎት ለአንድ ሰው መስጠት አጉል የአምባገነንነት ስሜት እንዳይፈጥር በዚህ ጊዜ ገደብ ውስጥም ቢሆን ሥራውን ከፋፍሎ ሥራውን የተከፋፈሉት የነባነት ገህ ሲቀድ አ ው ው የተለያዩ ተቋሞችና ግለሰቦች እርስ በእርሳቸው እንዲጠባበቁ ማድረግ ያስፈልጋል በመጨረሻም ይህ ተቋም በሥልጣን ተከፋፍሎም ግለሰቦች አዋጥተው ከሰጡት መብት እንዳያልፍ ለመጠበቅ በምንም መልኩ ሊረግጣቸው የማይችሉ ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መብቶች መኖራቸውን እና እነዚህንም በዝርዝር አስቀምጦ በእነዚህ መብቶች ላይ ለዚህ ተቋም መንግሥት ማስጠንቀቂያ የሚሆን ቀይ መሥመር አስምሮ ማስቀመጥ ወሳኝ ነው በዚህ መሠረት በፈጣሪው ሕዝብ እና በተፈጠረው ተቋም መንግሥት መካከል በመከባበር ላይ የተመሠረተ በግልፅ በታወቀ ኃላፊነት እና ግዴታ የታጠረ ጤናማ ግንኙነት ይፈጠራል ሕዝቡ ተቋሙ ለመገልገያ የሚያስፈልገውንና በቂ ነው የሚለውን ወጪ በግብር መልክ የመክፈል ግዴታ አለበት በዚህ ግዴታው መሠረትም ይህንን ተቋም የሚመሩትን መሪዎች የመምረጥ መብትም ኃላፊነትም አለበት ተቋሙ መንግሥት ኅብረተስቡ ገንዘቡን ሲያዋጣ ባወጣው ገንዘቡ እንዲሠሩልኝ እፈልጋለሁ ያላቸውን የጋራ ሥራዎቹን በአመርቂ ሁኔታ መሠራታቸውን የተሰጠውም ገንዘብ ለተባለው ሥራ እንጂ በአልባሌ ተግባራት ባክኖ እንዳይቀር የማረጋገጥ ግዴታ አለበት ይህ ተቋም ማኅበረሰቡ አዋጥቶ ከሰጠው መብቱ ውጪ የማኅበረሰቡ የግሉ የሆኑትን መብቶቹን የማክበር እነዚህ መብቶች በማንም ኃይል በበመንግሥት አካላትም ሆነ በሌላ የኅብረተስብ አባል ወይም ከማኅበረሰቡ ውጪ ባሉ ኃይሎች እንዳይረገጡ የናፃረጋገጥ ግዴታ አለበት በዚያው ልክ ኅብረተሰቡ እንዲሠራለት ላዘዘው ተግባር የሚያስፈልገውን እና በጋራ በተስማማበት መሠረት በወኪሎቹ በኩል የመንግሥትን ወጪ ለመቻል የሚደርስበትን ግብር ከማኅበረሰቡ የመሰብሰብ መብት አለው መንግሥት ዴሞክራሲያዊ ማኅበረሰብን የሚያይበት እና የማኅበረሰቡ አባላት ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ግንኙነት የሚያዩበት መነፅር ይህ ከሆነና ዴሞክራሲያዊ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የዚህ ዓይነት ጤናማ በጋራ ኃላፊነት እና ግዴታ የታጠረ አመለካከት የሚያስፈልግ ከሆነ በሀገራችን ባህል እና ታሪክ ስለ መንግሥት ማኅበረሰቡ ያለው አመለካከት እና መንግሥትም ስለራሱ ያለው እይታ ከዚህ በእጅጉ የራቀ መሆኑን አንባቢው ይገነዘባል ብዬ እገምታለሁ ይህ ግን ለኢትዮጵያችን ብቻ የተፅየ ችግር አድርጌ አላቀርበውም በየአገሩ ያሉ መንግሥታት ዴሞክራሲያዊ የሆኑት ሲፈጠሩ ጀምሮ አይደለም እንደየአገሩ ሁኔታ መንግሥታት ሲጀምሩ ሁሌም በጉልበት ስለሆነ በጉልበት ተጀምሮ ወደ ጾር ብርፃኑ ነጋ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመሻገር እና ከላይ የጠቀስኩትን ዓይነት የመንግሥት ግንዛቤ በኅብረተሰቡ ውስጥ እስኪሰርጽ ጊዜ ወስዲል በአገራችንም መውሰዱ አይቀርም በአብዛኛው የአገራችን ሕዝብ መንግሥት ያልተገደበ ሥልጣን ያለው በየትኛውም ሕይወታችን መግባት የሚችል ከማኅበረሰቡ ውጪ ባለ አንድ ኃይል የተቋቋመ እና የማይበገር ኃይል አድርጎ ይወስደዋል ከመንግሥት መጥፎ ተግባራት ወይም በደሎች የሚያስጥለን የመንግሥት «ርኅራቴ» እና «ሆደ ሰፊነት» አንጂ መንግሥት እንደ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ተቋም ከእኛ ጋር በውል ርዐበህወር መሠረት የሚሠራ በዚህ ውል መጽናት ያለበትና ከውሉ ቢወጣ ሊቀጣ የሚችል ኃይል ተደርጎ አይወሰድም ለዚህ ግንዛቤ ምክንያቱ የአገራችን የቅርብ እና የሩቅ ጊዜ የፖለቲካ ታሪክ ቢሆንም አስተሳሰቡ በባህላችን ካለው በቤተሰብም ውስጥ ለቀጥታ የሥልጣን ተዋረድ ዘቋርስነ ካሰን አክብሮት ጋር ይጣጣማጣል ይህ ለመንግሥት ያለን አመለካከት ያለማወቅ ችግር ብቻ አይደለም ምናልባት ብዙው ሕዝብ በተግባርም ሆነ በጽንሰፃሳብ ደረጃ የሚያውቀው የመንግሥት ሥልጣን ይኸው ብቻ ስለሆነ በመንግሥት ሥልጣን ላይ የተለየ ግንዛቤ እንዲኖረው መጠበቅ የለብንም ይባል ይሆናል ችግሩ ግን ያለው ከዚህ የተሻለ ግንዛቤ አለው በንባብም በተለያየ አገር ተዘዋውሮ በማየትም በሚባለውም የኅብረተሰብ ክፍልም ዘንድ መሆኑ ይህ የኅብረተሰብ ክፍልም ሆነ ሌላው በዕለት ተዕለት ኑሮው አንኳን ሳይቀር ከራሱ ትንሽ ዝቅ ያሉ ናቸው ብሉ ለሚያምናቸው ዜጎች ያለው ንቀትና እነሱን ለመጫን የሚያሳየው ጽኑ ፍላጎት ይድዘክየአሀ ጉዳዩ ስለመንግሥት ምንነት ከማወቅና ካለማወቅ በላይ በመሠረታዊ አስተሳሰብ ደረጃ ያለ ችግር እንደሆነ ያመላክታል ከላይ የጠቃቀስኩት በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ስለ መንግሥት ያለው ግንዛቤ በመሠረቱ በገንዘብ ወይም በሌላ ችሎታ ይበላለጡ እንጂ «ሰዎች በሰውነታቸው እኩል ናቸው» የሚል ጽንሰፃሳብ በውስጡ ያዘለ ነው በእኛ አገር የገነነው አስተሳሰብ ግን ይህን የሚቀበል አይመስልም ምንም እንኳን በየቤተሃይማኖቶቻችን የሰውን ልጆች እኩልነት በፈጣሪ ፊት ይስበኩ እንጂ የዛይማኖት ተቋሞቻችን ራሳቸው በተግባር በሰዎች መካከል በሀብታቸውም ይሁን በተለይ በመንግሥት ላይ ባላቸው ሥልጣን ትልቅ ልዩነት ስለሚያደርጉና በተለይ በሥልጣን ላይ ላለው ኃይል ትልቅ አክብሮትና ፍርሀትም ስላላቸው መንግሥትን የመንግሥት የነባነት ገህ ሲቀድ ባለሥልጣንን ከዚያም አልፎ በምንም መልክ ክእኛ በላይ ነው የምንለውን ሰው መፍራት በሥነልቦናችን ሥር እንዲሰድ አስተዋጽዖ አድርገዋል ስለ መንግሥት እና ስለ ባለሥልጣን ያለው የገዘፈ አመለካክት ግልባጭ ገጹ ግለሰቡ ስለ ራሱ እና ስለ ኑርርው ያለው ዝቅተኛ አመለካከት ነው መንግሥት በሕይወቱ ላይ ባሉ ጉዳዮች ሁሉ የማዘዝ ሥልጣን አንዳለው የሚቀበል ግለሰብ በራሱ ሕይወት ያለውን የማዘዝ ሥልጣን በዚያው ልክ አኮስሶ ስለሚያይ ሕይወቱን ለማሻሻል ሥልጣኑ በእጁ መሆኑን አይቀበልም ይህ የሚፈጥረው በራስ ሕይወት ፍፁም ሥልጣን የማጣት ስሜት ፀበ ዐያ ቦዐበፀ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ብቻ ሳይሆን የተሻለ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመፍጠርም በጣም አስቸጋሪ እንዲሆን ያደርጋል ሁልጊዜ ስለ ኢትዮጵያ የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚ ሳስብ ከዚህ የራስን ሕይወት አሳልፎ ከሚሰጥ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውጪ መልስ ላገኝለት ያልቻልኩት ጥያቄ ደጋግሜ አነሳለሁ ይህም ጥያቄ «አንድ ኅብረተሰብ ለሦስት ሺህ ዓመታት አንድ ዓይነት የምርት ዘዴ ጠሁለት በሬ ማረስነ ሲጠቀም እና ኑሮው እያደር እያቆለቆለ ሲሄድ ከራሱ የወጣና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚበጅ የተለየ የምርት ቴክኒክ መጠቀም ያልቻለው እንዴት ነው። የሚለው ጥያቄ ሁሉን አቀፍ ባይሆንም መለስተኛ የነቫነት ገህ ሲቀድ ምላሽ የሚያስፈልገው ነው አንዱ ችግር ነው ብዬ የማስበው ከዘውዳዊው አስተዳደር ስለ ሥልጣት ያለው ኋላ ቀር አመለካክት ነው ንጉሣዊው አስተዳደር ለመግዛት የሚያስፈልገውን የሕዝብ ይሁንታ ዐፀሀጠቋ ለማግኘት የሚጠቀምበት «የመለኮታዊ» ርፅዮተ ዓለም ሁኔታዎችን እያዩ ለመቀያየርና ፖለቲካዊ ማሻሻያዎች ለማድረግ እንቅፋት የሆነ ይመስለኛል ንጉሠ በተለይ በመጀመሪያ የሥልጣን ዘመናቸው እስከ ሁለተኛው ሀገመንግሥት ድረስ አገሪቱን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው መስክ ማዘመን እንዳለባቸው ተገንዝበው በመካከላቸው ካሉ ኋላ ቀር አስተሳሰብ ከነበራቸው ሰዎች ጋር እስከ መጋጨት የሚደርስ ትግል እንዳደረጉ የታሪክ ጸሐፊዎች ያወሳሉ በዚህም የማዘመን ሂደት የተፈጠረው ማኅበራዊ ኃይል በፖለቲካው መስክም የተሻለ የነፃነትና የዴሞክራሲ አየር መተንፈስ እየፈለገ ሲፄድና ይህም ፍላጎት የዴሞክራሲን መስፋፋት ሲጠይቅ ይህንን ጥያቄም በለዘብተኛ መንገድ ለማስተናገድ የሚፈልጉ የዘውዱ አማካሪዎችም በሚሻሻለው ህገ መንግሥት ለዘውዱ የተገደበ ሥልጣንን የሚሰጥ የህገመንግሥታዊ የዘውድ ሥርዓትን ሀሳብ ሲያተቀርበቡ ንጉሠ ይህንን ለመቀበል አለመፈለጋቸው በአገር አድገትና ዘመናዊነት በአንድ በኩልና በራሳቸው ያልተገደበ ሥልጣን በሌላ በኩል ለቀረበው ምርጫ ያልተገደበ ሥልጣናቸውን እንደሚመርጡ ግልጽ አድርጓል ንጉሠ ላልተገደበ ሥልጣን የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ ከመሆኑ የተነሣ ይህንን ሥልጣናቸውን እንኳን ለራሳቸው ቤተሰቦች ለልጃቸው በሰላም ማስተላለፍ ተስኗቸው በፍጹም በብቃት ማስተዳደር የማይችሉበት እድሜ ድረስ የሙጥኝ ብለው ለራሳቸው ለቤተሰባቸው ለዘውዱ ሥርዓት እንደ ተቋም እንኳን ሳያስቡ አገሪቱን በኋላ ለመጣው አደጋ ዳርገዋታል ከዚህ አንፃር የኃይለሥላሴ መንግሥት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በዝግታ ለማምጣት የሚያስችለውን እድል ባለመጠቀም ለአገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት ሆኗል እላለሁ ይህ ብቻ ግን አይደለምፁ የዘውዱ ሥርዓት በንጉሠ አመራር እራሱን ከህዝቡ ባያርትና ዘመናዊ የፖለቲካ ሥርዓት መዓዝ ቢያቅተው በጊዜው የነበሩ ከዘውዱ ሥርዓት መሻሻል የሚጠቀሙ የዘውድ ሥርዓት ቀስ ባቀስ መሻሻል ካልቻለ ሊያመጣ የሚችለውን አደጋ ሊታያቸው የሚችል ልሂቃን የዘውዱን ሥርዓት ለማሻሻልና ትንሽም ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የተጠናከረ ፍላጎትና ችሎታም ማጣታቸው የሚያስገርም ነበር በተለይ በጊዜው ጾር ብሂፃኑ ነጋ የፀረዘውድ ሥርዓት ትግሉ እያደር ከርሮ አብዮታዊ መልክ እየያዘ ሲፄድ ይህንን በአገሪቱ ሥር እየሰደደ የመጣውን የአብዮታዊ ርዕዮተ ዓለም ለመቋቋም የሚችል አማራጭና ለዘብተኛ ርዕዮተ ዓለም ይዞ የወጣቱን ቀልብ ለመሳብ የሚችል ምንም እንቅስቃሴ መፈጠር አለመቻሉ በአንድ በኩል በጊዜው የነበሩትን ልሂቃን ደካማነት በሌላ በኩል ደግሞ የዘውዱ ሥርዓት እንደ ሌሎች አምባገነን ሥርዓቶች ከንጉው ውጪ ምንም ዓይነት አዲስ ሀሳቦች በውስጡ እንዳይበቅል የሚከሳከል እንደነበር ያሳያል በአገራችን የፀረዝውድ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የአብዮታውያን ፍጹም የበላይነት መቀዳጀት የአዲሶቹ ኃይሎች ጠንካራነት ብቻ ሳይሆን ይበልጡንም የቀድሞውን ሥርዓት ልሂቃን ደካማነት የበለጠ ያሳያል አላለሁ ይህን በሚመለከት የንጉሠ ዘመን ባለሟሎች የነበሩ የተማሩ ሰዎች የእኛን ትውልድ ፀረዴሞክራሲያዊነት አምርረው ሲወቅሱ ሁሌም የሚገርመኝና ከአንዳንዶቹም ጋር አምርሬ የምከራከረው በጊዜው የነበረው ወጣቱ ትውልድ በጨቅላነት» የከረረ አብዮተኛ በመሆኑ በታሪክ ሊወቀስ ከቻለ የዚያን ያህል ምናልባትም ከዚያ በላይ የበለጠ ያውቃሉ ሊባሉ የሚችሉት የዘመኑ ልሂቃን በአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በዝግታ እንኳን እንዲገነባ ምንም ዓይነት ዓይነ ግቡ እንቅስቃሴ ማድረግ አለመቻላቸው ያስወቅሳቸዋል እያልኩ ነው በዘውዱ ሥርዓት የመጨረሻ ዓመታት ላይ የነበረውን የሥርዓቱን አጠቃላይ መዳከምና በዚህም ምክንያት በኋላ ለተፈጠረው አደጋ ያደረገጡን አስተዋጽዖ ለማየት ከሚያስችሉት ነገሮች አንዱ የለውጡ አቅጣጫ በውል ባልታወቀበት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ዓመታት ገደማ የነበረውን ውይይት መቃኘት ይበቃል ምንም እንኳን በጊዜው የግራ ኃይሎች የብዙውን ወጣት ቀልብ የሳቡ ቢሆንም የወደፊቱ የአገራችን የፖለቲካ አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ተወስኗል ማለት አይቻልም ጠመንጃውን የያዘው የወታደር ኃይሉ ሥልጣኑን መፈለጉን እንጂ አገሪቱን ወዴት እንደሚወስዳት ግልጽ አልነበረም በጊዜው በነበሩት የመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን በተለይም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በዚህ ዙሪያ ሰፊ ውይይቶች ይካሄዱ ነበር መጽሐፍትም በሰፊው ይዘዋወሩ ነበር በእነዚህ ውይይቶች ውስጥ በሚታይ መልክ የጠፋው በለዘብተኛነት የዴሞክራሲዊ ሥርዓት እንዲገነባ የሚጎተጉት አመለካከት ነበር ምናልባት ለእኔ ትዝ ከሚለኝ የአቶ ሀዲስ ዓለማየሁ መጽሐፍ በስተቀር ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ቆመናል የሚሉ በተለይ የዘውዱ ሥርዓት አገልጋዮች የነበሩ ግን የሥርዓቱን መሻሻል የነባነት ገህ ሲቀደ የሚፈልጉ ኃይሎች በዚህ ውይይት ይህ ነው የሚባል አስተዋጽዖ አላደረጉም ስለዚህም የለውጡን ሜዳ ሙሉ ለሙሉ ለአክራሪ የግራ ኃይሎች ትተውላቸው ነበር ለማለት ይቻላል በአጭሩ የጃንሆይ ዘመን ለዘብ ያለ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመሥረት የሚያስችለውን እድል አንድም በሥርዓቱ የተገደበ ሥልጣን አልቀበልም ባይነት አልያም በጊዜው የነበሩ ልሂቃን ለራሳቸውና ለአገራቸውም ሲሉ በዝግታም ቢሆን ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሊወሰድ የሚችል ምንም ዓይነት የተቀነባበረ የሀሳብም ሆነ የተግባር እንቅስቃሴ ለማድረግ ባለመቻላቸው ምክንያት በማባከኑ ኢትዮጵያ ይበልጡኑ ወደ ከፋ የአምባገነን ሥርዓት እንድትሄድ ተገዳለች ሉ የደርግ ዘመን ምናልባት በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት በሥልጣን ዘመኑ የሚያበቃ ብቻ ሳይሆን ከዚያም የሚዘልቅ ሁለንተናዊ እንቅፋት በመፍጠር ደርግን የሚስተካከለው ያለ አይመስለኝም ደርግ ለዴሞክራሲ ፀር የሆኑ ሁለት ባሕርያትን አዋህዶ የያዘ ኃይል ነበር ከእነዚህም ሁለት ባሕርያት አንዱ ከወታደርነቱ የመጣ በጠመንጃና በኃይል የማመን ባሕርይ ሲሆን ሌላው በጊዜው ገንኖ ከነበረው የግራ ርዕዮተ ዓለም የተወሰደ ለአደረጃጀትና ኅብረተሰብን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር የሚፈልግ ርዕዮተ ዓለም ነው ደርግ የሶሻሊስት ርዕዮተ ዓለምን በዋናነት እንደ ጥሩ የመግዢያ መሳሪያ በተለይም ከተወሰነ የኅብረተሰብ ክፍል ድጋፍ ማግኝያ ከዚያም ሥልጣን ለማቆየት የሚያስፈልገውን የውጭ እርዳታ ማግኝያ አድርጎ ተጠቅሞበታል ምናልባት እያደር ከተቀላቀሉት እና ከበፊትም ጀምረው የግራ ርዕዮተ ዓለምን ሲያያራምዱ ከቆዩት ሲቪሎች በስተቀር በጊዜው ሥልጣኑን የያዙት ወታደሮች ያንን ያህል በውስጣቸው የተጠናከረ የሶሻሊስት ወገንተኛነት ነበራቸው ለማለት ያስቸግራል ለመግዢያ መሳሪያነትም ይሁን አምነውበት የተከተሉት የሶሻሊስት ርዕዮተ ዓለምና የያዙት ጠመንጃ ሲደባለቅ ግን ለአገራችን ጠባሳው ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ክፉ የፀረ ዴሞክራሲ የመንግሥት አስተዳደር እና አጉል የሆነ አስተስተሳሰብ ሥነልቦና ትቶ አልፏል በመጀመሪያ ደረጃ ደርግ ከሶሻሊዝም የወሰደው ጠንካራ የድርጅታዊ አወቃቀር መሠረት ነው ይህንን የአደረጃጀት እውቀት ቀስሞ የማኅበረሰቡን አባላቾ በሙሉ በቀላሉ ሊቆጣጠራቸው በሚችለው የመንግሥት መዋቅሮች ውስጥ ከትቷቸዋል የገጠሩን ሕዝብ በገበሬ ማኅበራት የከተማውን ሕዝብ ደግሞ በቀበሌ ማኅበራት ወይም በሙያ ማኅበራት አደራጅቶ በመዳፉ ጾር ብርዛኑ ነጋ ያለውን ኅብረተሰብ እንቅስቃሴ በሙሉ ለመቆጣጠር ማኅበረሰቡን በፈለገ ጊዜ መንግሥት ለሚፈልጋቸው ድርጊቶች ለማሳለፍ በማኅበራት አማካይነትም ዜጎች የሚያደርጉትን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ለመሰለልም ሆነ እርስ በእርሳቸው እንዲጠባበቁ ለማድረግ አስችሎታል ይህም ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ የሆነውን የዜጎችን እርስ በእርስ የመተማመንና የመደጋገፍ ስሜት አሳስቶታል እዚህ ጠንካራ መንግሥታዊ መዋቅር የፈጠረው የመታፈን ስሜት ላይ ለማንኛውም ችግር እስከ መግደል የሚደርስ ኃይልን ለመጠቀም ያለመሳሳት የወታደር ባሕርይ ተጨምሮበት የደርግ ሥርዓት ማኅበረሰቡ መንግሥትን እጅግ እንዲፈራና በመንግሥት ፊት እንዲሸማቀቅ አድርጎታል ይህ መንግሥትን ክፉኛ የመፍራት ስሜት እስከ አሁንም በቀላሉ ሊጠፋ ያልቻለ የማኅበረሰቡ ሥነልቦና አካል ሆፍል ኅብረተሰቡን ከዚህ የፍርፃት ስሜት ማላቀቅ የዴሞክራሲ ግንባታው አንዱና ምናልባትም ዋነኛው አካል ይሆናል ደርግ ከሶሻሊዝም የወሰደው ሌላው አስጨናቂ የመልካም አስተዳደር ፀረመንግሥት በዜጎች ሁለንተናዊ ሕይወት ውስጥ ለመግባት የሚያስችለው ሥልጣን ነው በጣም ትናንሽ የሚባሉ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን ሳይቀር በቀጥታ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር በማዋል ወይም በእርሱ ይሁንታ ብቻ የሚሠሩ ሥራዎች በማድረግ ኅብረተሰቡ ለዕለት ተፅለት ኑሮው ሳይቀር የመንግሥት ጥገኛ እንዲሆን ፈርዶበታል ገበሬውን ነፃ በማውጣት ስም የተጀመረው የገጠር መሬት አዋጅ መሬቱን ከባላባቶች ወስዶ በቀጥታ ወደ መንግሥት ይዞታነት በማዛወሩ በአገሪቱ ያለው ገበሬ በሙሉ አርሶ ለመብላት የመንግሥትን መልካም ፈቃድ እንዲጠብቅ አደረገው መንግሥትን በፈለገ ጊዜ የገበሬውን ማሳ ልክ ወሳኝ በዚሁ ማሳ ላይ ያመረተውን ምርት መቼ ለማን በምን ዋጋ መሸጥ እንዳለበት ደንጋጊ ሆነ ገበሬው ምርቱን ለማሻሻል የሚጠቀምበትን ዘዴ የሚነግረውም ሆነ ለዚህም የሚያስፈልገውን ግብዓት የሚገዛበትን ቦታ የሚቆጣጠርም መንግሥት ሆነ የከተማውም ሕዝብ እንደዚሁ የዕለት ተዕለት ኑሮው በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ገባ የሚኖርበትን ቤት የሚከራየው ከመንግሥት ሥራ የሚቀጥረው ወይም የሚመድበው መንግሥት ቤተሰቡን ለመመገብ የሚያስፈልገውን እቃ የሚያገኘው ከመንግሥት ሱቅ ብቻ በአጠቃላይ በሁሉም ሕይወቱ ውስጥ መንግሥት ድንቅር አለበት ይህ የመንግሥት እንደ እርጎ ዝንብ ሁሉም ቦታ ጥልቅ ማለት የመንግሥትን ሥራ በእጅጉ የነባነት ገህ ሲቀደፎ በማግዘፍና ኅብረተሰቡም በተቀላጠፈ መልኩ አነዚህን ከመንግሥት የሚፈልጋቸውን ግልጋሎቶች ማግኘት ባለመቻሉ በህጋዊ መንገድ ከሚደረገው ልውውጥ ጎን ለጎን አንዳንዴም በከፋ መልኩ የሙስና ባህል ተስፋፋ እቃ ለመግዛት ልጅን ለማስተማር የተሻለ ህክምና ለማግኘ ት ሥራ ለመቀጠር ብቻ ለሁሉም ነገር ጉቦ መስጠት እየተለመደ መጣ የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት አንድም ኅብረተሰቡ በገዛ ኃይሉ ሊሠራ የሚችላቸውን ነገሮች በሙሉ ቀስ በቀስ በመንግሥት አስወስዶ እያደር በራስ የመተማመን ችሎታውን እያጣና በራሱ ተነሳሽነት የሚሠራቸው ሥራዎች እየቀነሱ በዚህም ምክንያት በራስ ሕይወት ላይ ፍጹም ቁጥጥር የማጣት ስሜት ዶዖዐህፀዘሀፀበ እንዲጠናወተው አደረገ በሌላ በኩል ደግሞ የሙስናው እጅግ እየተስፋፋ መፄድ ዜጎች በአጠቃላይና የበለጠ ቀልጣፋ የሆኑት የኅብረተሰብ ክፍሎች በተለይ ለምሳሌ በንግድ ሥራ የተሰማሩት የተሻለ ኑሮ ለመኖር የሚያስፈልገው ታታሪነት መሆኑ ቀርቶ ከመንግሥት ወይም ከመንግሥት ባሥልጣናት ጋር መሞዳሞድ ነው የሚል በአጭር ጊዜና በትንሽ ድካም የመክበር ባህል እንዲያዳብሩ ሁኔታዎችን አመቻቸ ሁለቱም ውጤቶች በማኅበረሰባችን ላይ የፈጠሩት ጫና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ሆነ በአጠቃላይ ለአገሪቱ የኢኮኖሚ እድገትም የማይበጅ የመንግሥት ቢሮክራሲና በቀላሉ የማይለቅ አስከፊ የሥነልቦና ጠባሳ ነው ይህ ችግር በአገራችን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና መልካም አስተዳደር ለማስፈን መታለፍ ካለባቸው ፈተናዎች አንዱ ነው የደርግ አምባገነንነት ሥርዓት ከእነዚህም በላይ በኅብረተሰቡ ውስጥ ያሉና ቀደም ብለውም የነበሩ ለዴሞክራሲና ለብልጽግና የማይመቹ ባሕርያትን የበለጠ እንዲጠናከሩና ሥር እንዲሰዱ አድርጓል እንደ ማንኛ ውም አምባገነናዊ ሥርዓት ደርግም ሕዝቡን ለመግዛት የሚያስፈልገው የህዝብ ነፃነትና ነባ መንፈስ ሳይሆን ፍርፃትና መሸማቀቅ ለሚያምነብት መቆምንና መከራከርን ሳይሆን አድርባይነትን ልበ ሙሉነትን ሳይሆን በራስ አለመተማመንን ተስፋ ሰንቆ መጓጓዝንና ይህንን እውን ለማድረግ መሥራትን ሳይሆን ተስፋ መቁረጥን በሌሎች ስኬት መደሰትንና እንደ ሴላው እንዲሳካለት መጣርን ሳይሆን ምቀኝነትን የተዳከመውን እየደገፉ የመፄድ የትብብር መንፈስን ሳይሆን በሰው ችግር ራስን ከፍ ማድረግን እውነተኛነትን ሳይሆን ቀጣፊነትን በአጠቃላይ የዜጎችን ጥሩነት ሳይሆን መጥፎነት እነዚህን ፀባዮች በማኅበረሰቡ ውስጥ እየተከለ ውሃ እያጠጣና ጾር ብርሃኑ ነጋ እየኮተኮተ እንዲያብቡ አደረገ በቪህም ምክንያት በኅብረተሰቡ ውስጥ በእውቀትም ሆነ በፀባይ ደካማ የሆኑትን በማሰባሰብ የማኅበረሰቡን የመሪነት ቦታ እንዲይዙ አደረገ የተሻለው የኅብረተሰብ ክፍል ሥልጣን አካባቢም አንዳይጠጋ በሩን ከረቸመ ከላይ የጠቀስኳቸው በኅብረተሰቡ ውስጥ እንዲስፋፉና እንዲያብቡ በአምባገነን ሥርዓቱ የተፈቀዱለት እኩይ ፀባዮች ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባት ከሚያስፈልገው አዎንታዊ ዐባይ ጋር አይጣጣምም በእነዚህ እኩይ ባሕርያት መስፋፋት ብዙኃኑን የኅብረተሰብ ክፍል የተበከለ ከሆነና በተለይም ኅብረተሰቡን ወደፊት ለመውሰድ የመሪነቱን ቦታ ሊጫወቱ የሚችሉ የእውተትና የገንዘብ ልሂቃንን የብከላው ዋነኛ ተጠቂ ከሆኑ የዴሞክራሲው ግንባታ የዚያኑ ያህል እክል ይገጥመዋል እነዚህ ለዴሞክራሲ እንቅፋት የሆነ ፀባዮችን ሁሉ ደርግ የፈጠራቸው ናቸው ባይባልም በደርግ የ ዓመታት አገዛዝ ዘመን ጥሩ የመራቢያ ቦታ ማግኘታቸው ግን አሌ አይባልም ሌላው የደርግ ዘመንና ኢዴሞክራሲያዊ አስተዋጽኦው ሲነሳ ሊረሳ የማይገባውና ጣጣው እስከ አሁን ያልለቀቀን ከዚሁ «ከሶሻሊስት» ተግባራዊ አስተዳደር የመነጨው የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ነው ዴሞክራሲያዊ እንኳን ባይሆን ከደርግ በፊት በነበረው የንጉሥ አስተዳደር ኅብረተሰቡ ለመንግሥት የተወሰነ ክብር ነበረው ቢያንስ መንግሥት እንደ ተራ ሰው ይዋሻል ብሎ አያምንም ደርግ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ በሰፊው ያስተዋወቀው «ለጊዜያዊ ፖለቲካ እስከ ጠቀመ ድረስ ሕዝቡን መዋሸት ችግር የለውም» የሚል የፕሮፖጋንዳ አካፄድ ሥር ከመስደዱ የተነሳ አሁንም ከፖለቲከኞቻችን ሀሰትን እንጂ እውነትን እንዳንጠብቅ የሚያደርግ የፖለቲካ ስብፅና የዳበረበት ሁኔታ ነው ያለው ይህም በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ በእጅጉ የሚያስፈልገውን የህዝብ በመንግስት ላይ እምነት ማሳደርን ለማሳደግ ጊዜ እንዲወስድብን ያደርጋል እዚህ ላይ ግን የደርግን የፕሮፖጋንዳ አካሄድ አሁን ካለሰው ሥርዓት አካሄድ ጋር የሚለይበትን አንድ መሠረታዊ ፀባይ ጠቁሞ ማለፍ አስፈላጊ ይመስለኛል የደርግ ፕሮፖጋንዳ መሠረታዊ ማንነትን ለመደበቅ የሚያደርግ አልነበረም አብዮተኛ ነኝ ስለዚህ ምንም ህግ አይገድበኝም ለአብዮቱ ይጠቅማል እስካልኩ ድረስ የመግደል የማሰር ወይም የፈለግሁትን የማድረግ መብት አለኝ ብሉ ስለሚያምን በዚህ ዙሪያ ምንም መዋሸት አላስፈለገውም ሰዎችን ከህግ ውጪ ሲገድል በሬድዮና ቴሌቪዥን የነባነት ገህ ሲቀድ «የፍየል ወጠጤ» አዘፍኖ ነው የመንግሥት ሥልጣን ምንም ለከት የሌለው መሆኑን መንግሥት በእያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት ላይ የማዘዝ ጭምር ሥልጣን እንዳለው በጃንሆይ ጊዜ ሥርዓቱ ቢያንስ የሰው ሕይወት በእግዚአብሔር እጅ ነው ብሎ ያምን ነበር አያንዳንዱ ዜጋ እንዲያውቀው ስለሚፈልግ ማሰርና መግደልን መደበቅ አላስፈለገውም ፕሮፖጋንዳው ውሸቱ ያስፈለገው «ሰፊው ሕዝብ» አብዮቱ በተለይ በቁሳዊ ሕይወት አመጣሁለት የሚለውን ጥሩ ነገር በተጨባጭ ማየት ሲሳነው ይህንፕኘ በተጨባጭ ያጣውን ነገር ቢያንስ በሬድዮና በቴሌቪዥን አግኝቶት «አንዲረጋጋ» ለማድረግ የታለመ ነው የፕሮፖጋንዳው ዒላማ ግን አስልቺነትና ተአማኒነት ማጣቱ ቀድሞውንም ተጠራጣሪ ለነበረው የኢትዮጵያውያን ሥነልቦና «መንግሥትን ማመን ቀብሮ ነው» የሚል አዲስ የጥርጣሬ መነሻ ፈጠረለት ይህ ጥርጣሬ መንግሥትን እሺ ማለት ወይም መከተል መንግሥትን መፍራት እራስን ለማዳን እንደሆን እንጂ ለኅብረተሰብ የሚጠቅም ሀቀኛ ነገር ያደርጋል ከሚል እምነት የመነጨ እንዳይሆን አድርጎታል በኋላ እንደምናየው ይህ በመንግሥትና በሕዝብ መካከል የተፈጠረ የመተማመን እጦት በኢህአዴግ ዘመን በተጀመረው ራስን የመደበቅ የተለየ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል ሒ ኢህአዴግና ልዩ የሚያደርገው ፀረዴሞክራሲያዊ ፀባዮች ኢህአዴግ ከራሱ የአፈጣጠር ታሪክና ከተፈጠረም በኋላ በተለይ ለሥልጣን ሲበቃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከነበረው የለውጥ ሁኔታ አኳያ ከአገራችን የቀደሙ ሥርዓቶች ምናልባትም ከሌሎችም አገሮች አንፃር ልዩ የሆኑ ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት እንዲሆን የሚያደርጉት ባሕርያት አሉት እነዚህ ባሕርያት ለወትሮው በአንድ ድርጅት ወይም በአንድ ሰው ሊያዙ የማይችሉ ናቸው ነገር ግን ኢህአዴግ ለተፈጠረበት ታሪካዊ አጋጣሚ በጋራ ይዞ እንዲያስኬዳቸው የተፈረደበት ወይም ቢያንስ ከእነዚህ ባሕርያት አንዱን ለይቶ መያዝ ስላቃተው ይመስላል በዚህም ምክንያት ድርድር የተጠባበቀ ተክለ ሰውነት ሀሸ ይፀወበቤጎ እንዲኖረው ሆኗል በእኔ እምነት እነዚህ ኢህአዴግን ለመቅረጽ የሚታገሉት ሁለት የውስጥ ባሕርያቱ ዘውጌ ብሄረተኛነት በአንድ በኩልና የግራ አብየተኛነት ርዕዮተ ዓለም በሌላ በኩል የሚፈጥሩት የውስጥ ቀውስ አልበቃ ብሎ ሥልጣን ለመያዝ ሲቃረብ ለመኖር ያስፈልገኛል ብሎ የደረበው ሦስተኛ ው የዴሞክራሲና የከበርቴ ሥርዓት ጭንብል ከሁለቱ ባሕርያቱ ጋር ይበልጡኑ የሚጋጭ በመሆኑ ድርጅቱ ለተዘፈቀበት ግራ መጋባት የተንኮል ጾር ብርዛኑ ነጋ ፍላጎትን ሳንጨምርበት አስተዋጽዖ ያደርገ ይመስለኛል ይህ የተምታታበት አካሄድ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ፈር እንዳይዝና አሁን ያለበት ትርምስ ውስጥ እንዲገባ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱና ምናልባትም ዋነኛው ነው የእነዚህን ሦስት ባሕርያት የውስጥ ግጭት ለማሳየት እያንዳንዱን ለየብቻ መመልከቱ ይጠቅማል። የሚለው ክርክር በበርሀ እያሉ ብዙ ቀለም የጠፋበት የእውነተኛ ታጋይነት መለኪያ ነበር ይህ ደግሞ በአንድ ወቅት ብቅ ብሎ የጠፋ ጊዜያዊ ስሜት ሳይሆን ሥር የሰደደ አመለካከት ለመሆኑ የኢህአዴግ አመራርች ሥልጣን ለመያዝ ወራት ሲቀራቸው ከሶቭየት ሕብረትና ምሥራቅ አውሮፓ የሶሻሊስት መንግሥታት መፈራረስ በኋላ ለአንድ የምዕራብ ጋዜጠኛ በሰጡት ቃለ ምልልስ በኢትዮጵያ ሊያንጹት የሚፈልጉት ኅብረተሰብ የአልባንያውን ዓይነት «ንጹህ» የሶሻሊስት ማኅበረሰብ እንደሆነ አስረግጠው መናገራቸው እንደ ምሳሌ ይጠቀሳል ይህ ብቻ አይደለም በተለይ ሁለቱ ድርጅቶች በፊት ለፊት ከያዙት የአርነት» እንቅስቃሴ ውጪ ጠቅላላ ትግሉን የሚመራ የማርክሲስት ሌኒኒስት ድርጅት ማሌ በህቡዕ አይሉት በፊት ለፊት አዋቅረው መሪ ድርጅቱ ይኸው መሆኑን በግልጽ አሳውቀዋል ከስምንት ዓመታት ድምጽ ማጥፋት በኋላና «ለካፒታሊስቱ ሥርዓት ግንባታ» የአፍ ፕሮፖጋንዳ በሰፊው ሲሰጥ ከቆየ በኋላ በድርጅቶቹም ውስጥ የተፈጠሩት የማሌ ድርጅቶች ያለ ምንም ውይይት የት እንደተቀበሩ የተረሳ በመሰለበት ጊዜ በሕወሀት ውስጥ ልዩነት ሲፈጠር የነበረውን ውይይት በጥሞና ለተመለከተ ማን የበለጠ ሶሻሊስት እንደሆነ ለማሳየት ይሞከር የነበረው ሙከራ በድርጅቱ ውስጥ ይህ አመለካከት በተለይ በአመራሩ ውስጥ የተቀባይነት ቨቪክክሃ መሠረት ተደርጎ እንደሚወሰድ ይረዳል ኢህአዴግ ይህንን ርዕዮተ ዓለም ምን ያህል ከምር እንደሚወስደው ለማየት ግን ክዚህ የግራ አስተሳሰብ በመነሳት የወሰዳቸውን የአመለካከትና የአደረጃጀት መርሐ ግብሮች መመልከቱ በቃል ከሚናገረው የበለጠ ግንዛቤ ይሰጣል ልክ እንደ ደርግ ኢህአዴግ ከግራ ርዕዮተ ዓለም የወረሰውን የድርጅቱን ጥቅምና የአደረጃጀቱን መልክ በጥብቅ ይዞታል ለኢህአዴግና ጠቀቂይ ሟኒሰዕታሩ ያሄው ዖዞረው ቦውዕፖ ሳይኑ በሟመሰሳ ወጣው ያዖዖናሃጀጄም ጽታሥፍ ታው ይልቅ ፅማርዝዕና ሰፅሐታሥቻ ማረዝሲሱዕዖቻ የሦወፅዕደ ጥቀሰ ሃሃ ጎበር ያላቋም ምነሦ ጎዳሁንም ያሚፅጳው ማረዝሳ ጋ ያገሐጠ ዳ ሃደሚሟሃረዝ «ማጎየዖ መሆ ድርጅቱ ዕነመራሩ ዚሀ ረሪዖፖ ዓለም ያሰው ዩፇረ ዖሏፅሳ ጾር ብርዛኑ ነጋ ለአባል ድርጅቶቹ ድርድት ሁሉም ነገር ነው ግለሰቦች ሥራቸው ድርጅቱን ማገልገል ነው ሊደረስ የሚፈለግበት አዲስ ዓለም የሚደረሰው በድርጅት ጥንካሬ ነው የድርጅቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላቱ ብዛትና አባላቱ በሚከተሉት ከብረት የጠነከረ ዲሲፕሊንና ለድርጅቱ ባላቸው ራስን መስዋዕት እስከ ማድረግ የሚደርስ ፍቅር ነው በአንዲህ ዓይነት ድርጅት ከምንም በላይ ከአባላት የሚጠበቀው ታማኝነት ነው ድርጅቱ በዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መርሕ መሠረት አንዶ ተወያይቶ የወሰነውን ያለምንም ማመንታት ራሱ አባሉ ከሚያምንበት እምነት ውጪ እንኳን ቢሆን በተግባር ማዋል እውነተኛ የታማኝነት መገለጫ ነው የድርጅት መዋቅሩም እንደ ማንኛውም የኮሙኒስት ድርጅት ከላይ ወደታች የተዋተረ በአመራር ላይ ያሉት ድርጅቱን የሚቆጣጠሩበትና አንዴ በአመራር ላይ ከተቀመጡ ላልተወሰነ ጊዜ በብዙ ሁኔታ እስከ ዕለተ ሞታቸው እዚያው ቦታቸው ላይ የሚቆዩበት አወቃቀር ነው ምንም እንኳን እንዲህ ዓይነቱ የፓርቲ አወቃቀር የውስጥ ፓርቲ ዴሞክራሲ እንዳለው ለማስመሰል ቢሞክርም በተግባር በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ይህ ተግባራዊ በሆነባቸው አገሮች የታየው ምንም ዓይነት ፋይዳ ያለው የውስጥ ፓርቲ ዴሞክራሲ የሌለው መሆኑ ነው በእንዲህ ዓይነት ድርጅት አባል የሆነ ሰው እሱነቱን ትቶና አሱነቱን በድርጅቱ ለውጦ እንዲኖር ይጠበትበታል ከግራው ርዕዮተ ዓለም የመጣው የድርጅት ፍቅርና አደረጃጀት በዚያው በፓርቲው አባላት ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም እንዲህ ዓይነት ፓርቲዎች ወደ ሥልጣን ሲወጡ በተቻለ መጠን ማኅበረሰቡን በሙሉ በራሳቸው ቅርጽ ለማዋቀር ይፈልጋሉ የራሳቸውን የፓርቲ አባሎች ብቻ ሳይሆን ሌላውንም የኅብረተሰብ ክፍል በተለያዩ እነሱ በሚቆጣጠሯቸው ማኅበራት ሥር ማደራጀት ቀዳሚ ተግባራቸው ነው በአንዲህ ዓይነት ድርጅት ፍልስፍና የተጠመቁ ሰዎችና ድርጅቶች የማይዋጥላቸው ነገር እነሱ የማይቆጣጠሩት ነፃ ድርጅት መፈጠር ነው የሙያ ማኅበራት እውነተኛ የሙያ ማኅበራት የሚሆኑት በእነሱ ሥር የተደራጁ ከሆኑ ብቻ ነው ለዚህ ነው በዚህ ርዕዮተ ዓለም የሚያምኑ ድርጅቶች መድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ ከሚባል ነገር ጋር በፍጹም የማይተዋወቁት በሁኔታ አስገዳጅነት ስለ መድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ በአዎንታዊ ደረጃ ማውራት ካለባቸው ወይም መድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ የመመሥረት ዓላማ አለን ብለው ለውጪው ዓለም ራሳቸውን መሸጥ ካለባቸው በዚህ በመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ውስጥ ያሉትን ሌሎች የነቫነት ገህ ሲቀድ ፓርቲዎችም ቢችሉ መቆጣጠር ካልቻሉም ቢያንስ መሪዎቻቸውን እነሱ መምረጥ ይፈልጋሉ ይህን የሚያደርጉት የማይቆጣጠሩት የፖለቲካ ድርጅት ጋር እንዴት መሥራት እንዳለባቸው እንኳን ስለማያውቁት ነው በአጭሩ ይህ ከግራ ርዕዮተ ዓለም የተወሰደ የአደረጃጀት ስልትና ስለ ድርጅት ያለ አመለካከት በሕዝብ ነፃ ስሜትና ፍላጎት ላይ ከሚመሠረት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ጋር በመሠረቱ ዘይትና ውፃ የሆነበት ምክንያትም ይኸው ነው ዴሞክራሲ ነፃ ድርጅቶችን ይፈልጋል ሌላው ኢህአዴግ ከግራ ርዕዮተ ዓለም የወሰደውና ስለ ድርጅት ካለው አመለካከት ጋር የሚያያዘው ኅብረተሰብን ራሱን የሚያይበት ዕይታ ነው ይህ ርዕዮተ ዓለም በመሠረቱ ኅብረተሰብን የሚያየው በመደብ መነፅር ነው ኅብረተሰብ የግለሰቦች ስብስብ አይደለም ኅብረተሰብን የሚገፋው ወይም የሚዘውረው አንዱ መዘውር በመደቦች መካከል የሚደረግ ትንቅንቅ ነው የመደብ ጥቅምች ግጭት ስለ ኅብረተሰብ እንቅስቃሴ አስፈላጊ ግንዛቤ የሚሰጥ ቁም ነገር መሆኑን መካድ አይቻልም ሰዎች ያላቸውን የፖለቲካ አመለካከት በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉበት የኢኮኖሚ ቦታ እንደሚቀርጸው አሌ አይባልም ሰዎች ግን ከዚያም በላይ የተወሳሰቡ ማንነቶች ይኖሯቸዋል ስለዚህ ግለሰቦችን የሚያንቀሳቅሳቸውን ነገሮች በኢኮኖሚ ቦታቸው ላይ ብቻ መወሰን አይቻልም ኢህአዴግ በኅብረተሰብ ውስጥ ያሉ ቅራኔዎች የመደብ ብቻ አይደሉም እንዲያውም አንዳንዴ ከመደብ ይልቅ ለሌሎች ስሜቶች ሰምሳሌ ዘውጌነት የበለጠ የገነነ ቦታ ይሰጥና ማኅበረሰቡን የመደብ ብቻ ሳይሆን የሌሎች የቡድን ስሜቶች ሰብሰብ አድርጎ ይወስዳል ለምሳሌ መደብ ጾታ ብሄር ወዘተ ስለዚህም ፖለቲካውን የሚያየው በእነዚህ ቡድኖች መካከል የሚደረግ የጥቅም ጨዋታ አድርጎ ነው ዴሞክራሲንም የሚያው በዚሁ በቡድን ጥቅም ግጭት ዙሪያ ነው በመሆኑም ዜግነት ርቪሠፀክ ከቹ የሚለው ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሠረት የሆነው ጽንሰ ሀሳብና ይህም የሚጠይቀው የግለሰብ ስሜትና ፍላጎት ለኢህአዴግ ብዙም የሚጥመው አይደለም በዜግነት ዙሪያ የዳበረ ግንዛቤ በሌለበት ደግሞ የዜግነት የግለሰብ መብቶችን መሠረት ያደረገ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የሚቻል አይሆንም ሌላው ከግራ ርዕዮተ ዓለም የተወሰደውና በንድፈ ሀሳብ ደረጃ የተቀመጠው የኢኮኖሚውና የፖለቲካው ትስስር ነው የግራ ፖለቲካ ኢኮኖሚውን የተቆጣጠረው ፖለቲካውን ይቆጣጠራል ብሎ ያምናል ጾር ብርሃኑ ነጋ ስለዚህም ክመደብ ደረጃ ከበርቴው የኢኮኖሚ የበለይነቱን በያዘበት የከበርቴ ስርአት ፖለቲካውም የከበርቴው ጥቅም ማስጠበቂያ ብቻ ሳይሆን የሚመራውና ሊመራ የሚችለውም በከበርቴው ነው የግራ ድርጅት የፖለቲካ ሥልጣኑን ከያዘ የከበርቴውን የፖለቲካ የበላይነት መቆጣጠር የሚቻለው ኢኮኖሚውን በመቆጣጠር ብቻ ነው ብሎ ያምናል ስለዚህም የግራ የፖለቲካ ኃይሎች ሥልጣን ሲይዙ ከሚያደርጉት ነገር አንዱና ዋናው ዋና ዋና የሚባሉትን የኢኮኖሚ መስኮች በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ማዋል ነው የሚመሠረተው ሥርዓት የሶሻሊስት ሥርዓት በሆነበት ሁኔታ ይህ አካሄድ ግልጽ ነው የኢኮኖሚ ኃይሉችን ከከበርቴው ወርሶ ላብ አደሩን በሚወክለው መንግሥት ሥር በማዋል የክበርቴውን የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ኃይሉንም ያዳክማል ይህ አመለካከት ግን ችግር የሚገጥመው በዚህ የሚያምን መንግሥት ለመመሥረት የሚፈልገው የከበርቴ ሥርዓት ሲሆን ነው ያኔ ኢኮኖሚውን ማን ይቆጣጠረው የሚለው ጥያቄ ግራ የተጋባ መልስ ማግኘት ይጀምራል እንዲህ አይነት መንግስት የግሉን ክፍለ ኢኮኖሚ ክፉኛ ስለሚጠረጥረው ከባለሀብቱ ጋር ጤነኛ ግንኙነት ሊኖረው አይችልም ስለዚህ ወይ ሥልጣን የያዘው ፓርቲ ራሱ ኢኮኖሚው ውስጥ በተለያየ መንገድ ገብቶ ኢኮኖሚውን ለመቆጣጠር ይሞክራል አለበለዚያም የፓርቲው ደጋፊዎች ናቸው የሚባሉ ግለሰቦች ከሌላው የተለየ ድጋፍ በማግኘት የኢኮኖሚውን የበላይነት እንዲይዙ ይሞክራል ሁለቱም አካሄድ በመጨረሻ የሚፈጥረው በሙስና የተጨማለቀና አቅጣጫ የጠፋው የኢኮኖሚና የፖለቲካ ሥርዓት ይሆናል በዚህ ሳቢያ ፓርቲውና የሥርዓቱ ደጋፊዎች በፖለቲካ ሥልጣን ላይ መቆየት የሚሰጠው የኢኮኖሚ ጥቅም እያሳሳቸው በምንም ዓይነት የራሳቸውን የፖለቲካ ሥልጣን ሊሸረሸር ወይም ሊቀማ የሚችል የሕዝብ ወሳኝነትን የሚቀበል የፖለቲካ ሥርዓት ለማዋቀር ይክብዳቸዋል ከዚህ በተጨማሪም ኢህአዴግ ከግራ ርዕዮተ ዓለም የቀሰመው ትምህርት የሚመስለኝ በግብና በመሳሪያ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚመለከት ነው እንደ ኢህአዴግ ላለ ድርጅት ዓላማዬ ብሉ የተነሳውን ጉዳይ ከግብ ለማድረስ ምንም ዓይነት መሳሪያን መጠቀም ተቀባይነት ይኖረዋል በዚህ ደረጃ ጉልበት አፈና በአጠቃላይ ፀረዴሞክራሲያዊ አካፄዶች በሙሉ በራሳቸው ችግር አይደሉም ያንን ግብ ለመምታት እስክጠቀሙ ድረስ በግራው ርፅዮተ ዓለም አምባገነንነት በተለይ በመደብ የነዛነት ገህ ሲቀድ ር ጠላት ላይ በአብዮት ጠላት እስከተፈፀመ ድረስ ተቀባይነት ያለው እንዲያውም አስፈላጊ አካሄድ ነው ይህ ደግሞ ከኢዴሞክራሲያዊ አካሄድ ጋር የሚጋጨው የዴሞክራሲ ትኩረት ግብ ላይ ሳይሆን ሂደት መሳሪያ ላይ በመሆኑ ነው ግቡ ምንም ሆነ ምን ሕዝብ እያፈኑና እየረገጡ መሠረታዊ መብቶችን እየነፈጉ የሚገኝ ዴሞክራሲ የለም ይህ የኢህአዴግ «ግቡ ትክክል እስከሆነ ድረስ ለአካፄዱ ብዙ አልጨነቅም» አስተሳሰብ በአሁኑ ጊዜ የገጠመን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ፈተና አንዱ አካል ነው በመጨረሻም ለበኋላ ውይይታችን የሚረዳን አንድ ነጥብ እዚህ ላይ ላንሳ የግራ ርፅዮተ ዓለም ከሌሎች ሁሉ በኅብረተስብ ውስጥ ካሉ ቅራኔዎች ለመደብ ቅራኔ ቅድሚያ ቦታ ይሰጣል በኋላ እንደምናየው ሌሎች ቅራኔዎች በአንዳንድ ታሪካዊ አጋጣሚ የቅድሚያ ቦታ በሚይዙበት ጊዜ እነኛ ቅራኔዎች ከቁጥጥር ውጪ እንዳይወጡ ማኅበረሰቡን አስተሳስሮ የሚይዘው ይኸው የመደብ ሰንሰለት ነው የሥራተኛው መደብ ሳብአደሩ ከአገሩ ውጪም ካሉ ወገኖቹ ጋር መደባዊ አጋርነት አለው እንኳን በአገሩ ውስጥ ካሉ የተለያዩ ብሄረሰቦች ከመጡ ላብ አደሮች ጋር ይቅርና ስለሆነም እንደ በዚህ አካሄድ ኢትዮጵያ ባሉ ሌሉች ቅራኔዎች ለምሳሌ የብሄረሰብ ባሉበት አገር እነዚህን ቅራኔዎች በተገቢው መንገድ መፍታት የሚቻለው በአቋሙ ምክንያት ሰፋ ያለ ከሁሉም የተውጣጣ ማኅበራዊ ድጋፍ ያለውና ሊኖረውም የሚችለው በግራ ርዕዮተ ዓለም የታነጸ የላብ አደሩ ፓርቲ በሥልጣን ላይ ሲኖር ነው ስለዚህ ኢህአዴግ የግራው ርዕዮተ ዓለም በአገሪቱ ውስጥ ያለውን የመደብ ቅራኔ ለሰፊው ሕዝብ በሚወግን መልኩ የሚፈታ ርዕዮተ ዓለም ብቻ ሳይሆን በኅብረተሰቡ ውስጥ ያሉትን ሌሎች ቅራኔዎችንም በትክክል ሊፈታ የሚችለው ብቸኛ መስመርም ነው ብሎ ያምናል በአጠቃላይ ይህ የግራ ርዕዮተ ዓለም በአገሪቱ ያሉትን ሁሉም ዓይነት ጭቆናዎች መደብ ብሄር ጾታ የሚፈታ ብቸኛ ትንግርታዊ መሳሪያ ተደርጎ ነው የተወሰደው በዚህም ምክንያት ኢሀአዴግ ሌላ ዓይነት ርዕዮተ ዓለም ለሚከተሉ የፖለቲካ ኃይሎች ትዕግስት የለውም በአገሪቱ ያሉትን ቅራኔዎች ለመፍታት አይችሉም ብሎ ያምናል ለዚህም ይመስለኛል ብዙ ጊዜ አንዳንድ እውነተኛበህበ የኢህአዴግ ባለሟሎች ኢህአዴግ ከሥልጣን ከተወገደ አገሪቱ ትበታተናለች እየተባለ በመሪዎቻቸው የሚለፈፈውን አምነው የሚቀበሉት አንዳንዶቹ ይህን አመለካከት በሥልጣን ለመቆያ ማስፈራሪያ የሚጠቀሙበትን ያህል ሌሎች ጾር ብርፃኑ ነጋ የፖለቲካ ኃይሎች በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ቅራኔዎች ሊፈቱ አይችሉም ብለው ከልባቸው የሚያምኑ ሰዎች በመካከላቸው የሉም ብዬ ለመናገር አልደፍርም በእርግጥ ይህን ማመን ማለት እውነታ ነው ማለት እንዳልሆነ በኋላ በዝርዝር የምናየው ይሆናል ኢህአዴግና የዘውጌ ብሔረተኝነት ፎከከበር ከበ የኢህአዴግን ምንነት ከቀረጹት አስተሳሰቦች አንዱ ሥር የሰደደው የዘውጌ ብፄረተኛነት ስሜቱ ነው ይህ በ አብዮት ወቅት በአገራችን የብሄር ጥያቄ እንዴት መፈታት አለበት የሚለውና ከተማሪዎች እንቅስቃሴ ጀምሮ በግራ አብዮተኞች መካከል ብዙ ያወዛገበው ጥያቄና አንዱ የመወያያ አጀንዳ ነበር በተለይ በጊዜው የጃንሆይን አገዛዝ በግልጽ በመቃወም ጠመንጃ ይዞ ይታገል የነበረው የኤርትራ ብሔረተኞች ኃይል በተማሪው እንቅስቃሴ ለነበሩ ለብዙ የግራ አብዮተኞች አንድም እንደ ምሳሌና የወደፊት የትግል አጋር ተደርጎ ይታይ ነበር አልያም ደግሞ ይህ የትግል ጥያቄ እንዴት ይፈታል ለሚለው ሌላ ጥያቄ ከኤርትራም አልፎ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚነሱና በመጠትም ቢሆን ለተነሱ ዘውጌ ብሔረተኞች አቅጣጫ አመላካች ተደርጎ ይወሰድ ነበር በጊዜው በብሄር ጥያቄ ዙሪያ የሚወጡ የግራ ጽሁፎች በተለይ ከስታሊን ጽሁፍ በመነሳትና እሱን በቀጥታ ለኢትዮጵያ ሁኔታ በመገልበጥ ብሄር ለመባል መሟላት ስላለባቸው መስፈርቶች በኢትዮጵያ የብፄርን መስፈርት ያሚለ እነማን እንደሆኑእነዚህ ብሔሮች የሚገባቸው መብት ምን እንደሆነና የብሔር መስፈርቶችን ያላሟሉት ምን እንደሚገባቸው የሚተነትኑ ነበሩ ምንም እንኳን የኤርትራ ብፄረተኞች ራሳቸውን እንደ ቅኝ ተገዢ አድርገው ቢያቀርቡና በዚህም ምክንያት መገንጠል ይገባናል ብለው ቢሰብኩ በአብዛኛው የግራ አመለካከት ይህንን ከቁምነገር የወሰደ አኣልነበረም የኤርትራ ጥያቄ ምንም ሆነ ምን ግን ሕዝቡ ከፈለገ የመገንጠል መብት አለው የሚለው በነዋለልኝ ይገፋ የነበረው የብሄር ጥያቄ ትንተና አብዛኛ ው በመርህ ደረጃ ተቀባይነት ነበረው ለማለት ይቻላል ያም ሆኖ ግን ሶሻሊስቶች ሥልጣን ከያዙ በያዘበት ሁኔታ የጭቁን ብፄሮች ላብ አደሮች የነፃነት ገህ ሲቀደድ ባላቸው የጋራ የመደብ አጋርነት ምክንያትና በእዚህ ዓይነት ሥርዓት ውስጥ የብሄር ጭቆናም ሊኖር ስለማይችል መገንጠል የሚባለው ጥያቄ በተግባር የሚነሳ ጥያቄ አይሆንም ተብሎ ይታመን ነበር ከዚያም አልፎ በእንዲህ ዓይነት ሥርዓት ውስጥ የብሄር ጥያቄን ራሱን አክርረው የሚያነሱ ኃይሎች ከብፄራቸው በላይ ማሰብ የማይችሉ «ጠባብ ብሄረተኞች» ስለዚህም ፀረአብዮተኞች ናቸው በመሆኑም የሁሉም ብፄሮች ተራማጅ ኃይሎች በጋራና በግራ ርዕዮተ ዓለም ጥላ ሥር መሰባሰባቸውና መደራጀታቸው ቅድሚያ የሚሰጠው የትግል አቅጣጫ ነው የሚለው አመለካከት ሰፊ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር ደርግ ሥልጣን ይዞ በግራ ኃይሎች እየተገፋ «የሶሻሊስት» አቅጣጫ የመያዝ ምልክት አሳየ በግራ እንቅስቃሴው ውስጥ ከነበሩት ኃይሎች ውስጥ የተወሰነው ክፍል ለደርግ «ሂሳዊ ድጋፍ» መስጠት ይቻላል የሚል አቋም ያዘ በተለይ ደግሞ ደርግ ባልተጠበቀ ሁኔታ ለግራ አብዮተኞች የሚጥም ሥር ነቀል የመሬት አዋጅ ሲያውጅና ይህንንም ለማስፈጸም ተማሪዎችን ወደ ዘመቻ ለመላክ ማሰቡን ሲያሳውቅ በተለይ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ መከፋፈልን ለመፍጠር ችሎ ነበር በዚህ ጊዜ ተማሪውን ወደ አንድ አቋም ለማስመጣት በሚል ተማሪዎች በየመጡበት አካባቢ አየተሰበሰቡ ይወያዩበት በሚል የግራ አብዮተኞች የሚባሉትም በአገራዊ ጉዳይ ላይ የየዘውጌ ብፄሄረሰበን የተናጠል እንቅስቃሴ መጀመራቸውን እንደ አዎንታዊ እርምጃ ለታክቲክ ሲባል መውሰድ ጆመሩ በዚህ ጊዜ አካባቢ ይመስላል የሕወሀት አስኳል ነው ተብሎ የሚታሰበው የትግራይ ተራማጆች ማኅበር ማኅበር ገስገስቲ ትግራይ የተቋቋመው ደርግ በሶሻሊዝም ስም መማል ከጀመረና በተወሰነም ደረጃ ቢሆን የተራማጁን የፖለቲካ ጩኸት የመደብ ጭቆናን ማስወገድ ከቀማው በአገሪቱ ያለውን የቅራኔዎች ደረጃ እየቀየረው ነው ማለት ነው ስለዚህም ቢያንስ ደርግንና የመንግሥትን ጥያቄ በሚመለከት በአገራችን ያለው ዋነኛ ቅራኔ የመደብ ሳይሆን የብሄር ቅራኔ ነው ስለዚህም ደርግን ለመጣል የሚደረግ ትግል በአደረጃጀት ደረጃ በብሄሮች ላይ የተመረኮዘ መሆኑ ትክክለኛው አካፄድ የሜል ሀሳብ መንፀባረቅ ጀመረ ይህም የሕወሀትን በብሄር መደራጀት እንቅስቃሴ የጽንስ ሀሳብ ድጋፍ ሰጠው አንዴ ተራማጆች በብፄር መደራጀታቸው ትክክል ነው የሚል መስመር ከተያዘ በኋላ ግን ዘውጌ ብሄረተኝነት ሕዝቡን ለማደራጀትና ጾር ብርፃኑ ነጋ ለማነሳሳት የሚጠቀምበት የብሄረተኛነት ስሜት በቋንቋና በባህል የራሉ የዘውጌውን የተለየ ታሪክ በመፃፍ ዘውጌውን በተለየ ተጨቁኗል ወይም የተለየ ነው የሚለውን የማነሳሳት ስሜት ለመፍጠር ወዘተ የግራው ርዕዮተዓለም ከሚሰብከው የመደብ ወገንተኛነትና የጭቁኖች አንድነት ጽንለ ሀሳብ ጋር ቀስ እያለ መላተሙ የማይቀር ነበር ዘውጌ ብሄረተኝነት ዘውጌውን ለማሰባሰብ የሚጠተምባቸውን የታሪክ ምሳሌዎች ለምሳሌ የወያኔ እንቅስቃሴ ከተራማጅነት ባሕርይ ጋር ለማጣጣም መባዘንን ያስከትላል ደረሰብን የሚባል ጭቆናን አግዝፎ ማቅረብ ማኅበረሰቡን በእልህ ለትግል ሊያነሳሳው ይትላል ነገር ግን በሌላ በኩል ከሌሎች ዘውጌዎች ጋር ያለውን ግንኙነት የማሻከር ባሕርይ ይኖረዋል በዚህም ምክንያት ከተለያዩ ዘውጌ ማኅበረሰባት የመጡ የግራ ኃይሎች በራሳቸው በታሪክ አተረጓጎምና በመሳሰለው ግጭት ውስጥ ሊገቡ የሚችሉበት ዕድል እየሰፋ ይሄዳል ይህ ብቻ አይደለም የግራ ትግሉ በየዘውጌው ተከፋፈለ ማለት ዘውግ ዘለል በህዘ ከክር የሆነ በርዕዮተ ዓለም ደረጃ የተደራጁ ኃይሎች በየትኛው አካባቢ ሆነው ነው የሚታገሉት የሚለው ጥያቄ በዘውግ ተኮር ፎከክበፎ ባሕርያቸውና ከዚያ በዘለለው የግራ አብዮተኛ ነታቸው የውስጥ ስሜቶች ላይ ግጭት መፍጠሩ አይቀሬ ነው። ይህ በአንድ በኩል የዘውጌ ድርጅቶችን ከህብረ ብሄራዊ ድርጅቶች የሚመርጠው በሌላ በኩል ደግሞ የዘውጌ ድርድቶቹን ለመቆጣጠር አለመቻል የፈጠረው የውስጥ ትግር እስከ አሁንም ኢህአዴግ ሊፈታው ያልቻለው ትልቁ ራስ ምታቱ ሆፍል ሠራም አልሠራም በኢህአዴግ በኩል ለዚህ የውስጥ ጭንቅት የተሰጠው መልስ በየዘውጌው እሱ ሊቆጣጠራቸው የሚችላቸውን ድርጅቶች መፍጠር ነው በዘመኑ የፖለቲካ ቋንቋ ተለጣፊዎች የሚባሉትን ማለት ነው ይህ ብሄር ብፄረሰቦች የራሳቸውን ዕድል በራስ የመወሰን እስከ መገንጠል መብት አላቸው የሚልን ዴሞክራሲያዊነት አንግቤያለሁ የሚል ድርጅት በሌላ በኩል ራሳቸውን እንዳያስተዳድሩ የሚመስላቸውን ድርጅት በራሳቸው እንዳይፈጥሩና ለዘውጌአቸው ጥቅም እንዳይታገሉ እንቅፋት የመሆን ተግባራዊ አካሄድ የኢህአዴግን የተጨነቀችና ግራ የገባት ነፍስ የሚያሳይ ነው በተግባርም በተለይ ሕወሀት ኢህአዴግን ሲመሠርት ለሕብረብፄሄራዊ ድርጅቶች ያሳየውን ትዕግስት ለምሳሌ ለኢህዴን ከሥልጣን በኋላ ለውጦ በውስጡ የነበሩትን የተለያዩ ዘውጌ ማኅበረሰብ አባላት አስወጥቶ በየዘውጌያቸው እንዲደራጁና ኢህዴንና ራሱን ወደ አማራ ድርጅት ብአዴን እንዲቀይር ማድረጉ አመለካከቱ በተግባር የፈጠረውን ችግር በመገንዘብ ነው በኋላ በዝርዝር እንደምናየው ይህ የኢህአዴግ ሕወሀት የዘውጌ ብሄረተኛነትና የግራ አብዮተኛነት ከሁለት ትልልቅ የኅብረተሰብ ክፍሉች ጾር ብርዛኑ ነጋ ጋር ግጭት ውስጥ ከቶታል በአንድ በኩል ዘውጌ ብፄረተኛነትን ከምር የሚወስዱና በዚህም ምክንያት በነፃ ተደራጅተው ዘውጡጌያቸውን በፖለቲካ ዙሪያ ለማሰባሰብ የሚሞክሩ ኃይሉች ስለዚህም ለዘወጌያቸው ከአገራዊው ኬክ የየሚገባውን ለማስገኘት በነፃ መደራጀት ከማይወደው የኢህአዴግ ባሕርይ ጋር ይጋጫሉ በሌላ በኩል ራሳቸውን እንደ ኢትዮጵያዊ ብሄረተኛ የሚወስዱ ኃይሎች በእምነት ደረጃ ሳይሆን በትውልዳቸው ከምንም «ንጹህ ዘውጌ ራሳቸውን መመደብ የማይችሉ የተደባለቁ ኢትዮጵያውያን ወይም ደግሞ በትውልድ ምክንያት ወይም በጋብቻ ምክንያት ሳይሆን በአስተዳደጋቸው ዘውግ ዘለል የሆነ ሥነልቦና ያላቸው ለምሳሌ የከተማ ሰዎች ከዘውግ በላይ መደራጀትን ከማይወደው ባሕርዩ ጋር ይጋጫሉ ኢህአዴግ መፈረጅ በሚወደው ሌላው ባሕርይ የተነሳ የመጀመሪያዎቹን «ጠባብ ብፄረተኛ» የኋለኞቹን ትምክህተኛ ወይም የበለጠ ለማጥላላት ሲፈልግ «ነፍጠኞኛ «ጥገኛ ነፍጠኛ ወዘተ እያለ ግጭቱን የበለጠ ያካርረዋል በውስጡ ያለውን የአመለካከት ችግር መፍታት ሳይችል ትግሉን ወደ ኅብረተሰቡ ለማሻገር የሚያደርገውን ጥረት የበለጠ የኅብረተሰቡን ውስጣዊ ሰላም አናጊ አድርጎታል ይህን ሁሉ የኢህአዴግ የውስጥ ችግር ስናወራና ችግሩም በማኅበረሰቡ ላይ ሊፈጥር የሚችለውን አደጋ ስንተነትን ኢህአዴግ ከሚያምንበት እምነት ውጪ ሆን ብሉ አገርን ወይም ሰዎችንና ድርጅቶችን ለመጉዳት ፍላጎት አለው ሳንልና የሚያደርገውን ነገር ሁሉ የሚያደርገው እምነቱን በተግባር ለማዋል እንጂ በእምነቶቹ ሥር ተደብቆ በተግባር የሚያሳድደው ምድራዊ ጥቅም ሥልጣንና ከሥልጣን የሚገኝ ፍርፋሪ አለው ብለን ሳናስብ ነው እነዚህ ችግሮች ደግሞ ቀመሩ ውስጥ ሲገቡ ኢህአዴግ በዴሞክራሲ ግንባታ ላይ ሊያመጣና እያመጣ ያለውን ችግር ለማየት አይከብድም ለጊዜው በእምነቱ ዙሪያ ባጠነጠኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ እናተኩር ሌላው በዚህ ዙሪያ የሚነሳ ተግባራዊ ችግር የቅድሚያ አሰጣጥ ይዘዐዘህ ችግር ነው ከኢህአዴግ ሁለቱ እምነት እንነሳ በኢህአዴግ ውስጥ ያሉት አራቱ የዘውጌ ድርጅቶች በአንድ በኩል እንደ ዘውጌ ብሄረተኛ ዋና ተግባራቸው የዘውጌ ማኅበረሰባቸውን ጥቅም ማስጠበቅ ነው በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉም በጋራም ሆነ በየድርጅቱ ውስጥ ያሉት የግራ ኃይሎች ወገንተኝነታቸው ከሁሉም «ጭቁን ሕዝብ ጋር ነው አንዱ ሰዎችን የሚከፋፍለው በኢኮኖሚ አቅማቸው ነው ሌላው የኢኮኖሚ አቅማቸው የነባነት ገህ ሲቀድ ምንም ሆነ ምን የዚያ ዘውጌ ማኅበረሰብ አባል መሆናቸው በራሱ የዘውጌ ድርጅቱ ወገንተኛ ያደርጋቸዋል ይህ ሁኔታ ከሚተገበሩ ፖሊሲዎች ጋር ግልጽ ግጭት ይፈጥራል በምሳሌነት ለመጥቀስ ያህል የኢህአዴግን የከተማ ቤት ፖሊሲ በመቃወም ቤታችን ይመለስልን ብለው የጠየቁ ዜጎችን አይቻልም ይህ ድሆችን ይጎዳል የአድኃሪያን ጥያቄ ነው ብሎ ዘግቶታል ሆኖም ይኸው ድርጅት በትግራይ ውስጥ ቤት ለተወረሰባቸው ሰዎች ቤታቸውን መልሷል ይህ መቼም በዜግነት እኩልነት መብት ለሚያምኑ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በፍጹም የሚዋጥ አይደለም ለኢህአዴግ ግን የውስጥ ቅራኔው ንጹህ መገለጫ ነው እንዲህ ዓይነት የተዘባረቀ የአድልዎ አሠራር ከመሠረታዊ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሂደት ጋር የሚጋጭ ነው ከዚህ ጋር አብሮ የሚያያዘው ቀደም ብዬ የጠቀስኩት መንግሥት ዜጎቹን እንዴት ያያቸዋል የሚለው ጥያቂ ነው ዜጎችን እንደ ግለስብ ዜጋ ሲታዩ የሚኖሯቸው መብቶችና ግዴታዎች እንደ ቡድን በውጌ ይገባቸዋል ከሚባሉት መብቶችና ግዴታዎች ጋር ሊፈጥር የሚችለውን ግጭት ከሕገመንግሥት ድንጋጌዎች ጋር በማያያዝ ለማስረዳት ሞክሬያለሁ ለኢህአዴግ በተለይም ለሕወሀት ሌላ ራስ ምታት የሚሆነው በአንድ በኩል በዘውግ ጥምረት ላይ የተመሠረተ ጀየከቨር ርዘከክ መንግሥት ለማቆም መፈለግና ይህን ጥምረት ደግሞ በአገሪቱ ውስጥ ካሉ ዘውጌ ብሄረሰቦች አናሳውን ክፍል የያዘው ኃይል በነበረው ዩታሪክ አጋጣሚ ሊመራው ብቻ ሳይሆን ሊቆጣጠረው ሲፈልግ የሚፈጠረው ፍትጊያ ነው የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ በአንዲህ ዓይነት ጥምረት ውስጥ ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት ያላቸው ዘውጌዎች የመንግሥትን ሥልጣን በተለይም ከፍተኛ የሆኑትን የሥልጣን እርከኖች መመኘታቸው አይቀርም ምንም እንኳን ለመጀመሪያ ጊዜ እነዚህ ከመሪው ድርጅት ውጭ በኋላ በመሪው ድርጅት የተቋቋሙት የዘውጌ ድርጅቶች የሁለተኛ ደረጃ ቦታቸውን ቢቀበሉም ትንሽ እየተጠናከሩ ሲፄዱ የሚገባንን እናግኝ ማለታቸው አይቀርም እንዲህ ዓይነቱ ውጥረት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታውን ብቻ ሳይሆን የአገሪቱን ሰላምና መረጋጋት ማወኩ አይቀርም የኢህአዴግ ዘውግ ተኮር ፖለቲካ ከዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አንፃር የሚፈጥረው ሌላም መዘዝ አለ ይህም የአገር ሀብት ክፍፍልን በሚመለከት የሚፈጠረው ችግር ነው የዘውግ ስሜት ብዙውን ጊዜ ኃይለኛ ስሜት የሚጭር ለአምክህኖታዊ ውይይትና መረዳዳት የማይመች ጾር ብሂዛኑ ነጋ መ ነው የዘውግ ብፄረተኛነት ተጠቃሁ ወይም ተበደልሁ የሚል ስሜት ክፉኛ ይጎነትለዋል መሠረት በሌለው ወሬ እንኳን በተበደልኩ ስሜት የዘውግ ብሄፄረተኛነትን ማነሳሳት አይከብድም በዚህ ዙሪያ በተለይ በልሂቃን በኩል የሚነሳው የጥቅም ግጭት የዘውግ መልክን እንዲይዝ በቀላሉ ሊገፋፋ ይችላል በክልሎች መካከል በሚደረግ የበጀት ድልድል ዙሪያ በኢህአዴግ ውስጥ ባሉ ድርጅቶች ውስጥ እንኳን ያለውን የከረረ አለመግባባት በየዓመቱ በበጀት መጽደቅ የፓርላማ ውይይት የምንሰማውና የምናየው ነው ችግሩ ግን ከዚያም ይልቃል በዘውግ ላይ ለተመሠረተ መንግሥት የበላይነት አለው የሚባል የዘውግ ብሄረተኛ ደርጅት ካለ ነገሩ እውነትነት ኖረውም አልኖረውም አንድ ክልል በተለይ ተጠቅሟል የሚል ስሜት መፈጠሩ የሚቀርም አይደለም በአድልዎ ምክንያትም ባይሆን በዚያ በክልል ውስጥ ትንሽም የተሻለ እንቅስቃሴ ከታዬ ሌሉች የራሳቸውን ዘውግ ለማሰባሰቢያ ዘውጋቸው እንደተበደለ በማስረጃነት ማቅረባቸው አይቀርም ኢትዮጵያን በተመለከተ በዚህ ዙሪያ በትግራይ ላይ የሚነሱት ዘርፈ ብዙ ፃሜታዎች ምሳሌዎች ናቸው እነዚህ ዛነሜቶች እውነትም ሆነ ሀሰት ይህ አመሰካከት የርፀፀ መኖሩ ብቻ በአገሪቱ ዜጎች መካከል የመተባበር ፀሃ ስሜት ሳይሆን የመፎካከርና የምቀኝነት ስሜት መፍጠሩ አይቀሬ ነው ይህ በመሆኑ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታውን ይጎዳዋል ይህ ያልተመጣጠነ የአገር ሀብት ክፍፍል ስሜት ግን ከክልሉች አንፃራዊ አድገት ጋር ብቻ የተያያዘ አይደለም የዚህ ኢፍትዛዊነት ጥርጣሬ በመንግሥት ሥራዎች ላይ ማን ይቀጠራል በሚለውም ላይ ከፍተኛ አለመግባባቶች በግልጽም ባይሆን መፍጠሩ አይቀርም የዴሞክራሲ ግንባታ እና የአገር የኢኮኖሚ እድገት ጠንካራ አገራዊ ተቋማትን ይፈልጋሉ እነዚህ ጠንካራ አገራዊ ተቋማት ሊፈጠሩ የሚችሉት በተቋማቱ ውስጥ ብቃቱና ችሎታው ያላቸው ሰዎች ሲሠሩ ነው ከብቃት ይልቅ በሌሎች ከሥራው ጋር ባልተያያዙ መስፈርቶች ሰዎች ሲቀጠሩ ተቋማቱ ይጎዳሉ ይዳከማሉ እንዲህ ዓይነት ብቃት የሌላቸው ሰዎች በተቋሞቹ ውስጥ ሊሠሩ የሚችሉባቸው ሁለት ምክንያቶች አሉ አንደኛ ው እንደ ኢትዮጵያ በዘውግ በተከፋፈለና ዘውጌ ብሄረተኛነት በግልጽ ከፍተኛ ቦታ በተሠጠው እና በድህነት ምክንያት የመንግሥት ሥራ ማግኘ ትን እንደ ትልቅ ጥቅም በሜታይበት አገር የመንግሥት ሥራን በተቻለ መጠን ከተለያዩ ዘውጌዎች ለመጡ ሰዎች ማደላደል ለፖለቲካ መረጋጋት የነባነት ገህ ሲቀድ ጮምመምጅይም ጅሚ ዱክ አስፈላጊ አንደሆነ ተቆጥር የመንግሥት ሥራን በዘውግ የማደላደል ቢቻል ተመሳሳይ ችሉታ ባላቸው ሰዎች መሀል አሠራር ተቀባይነት ሊያገኝ ይችላል ይህ በተለይ ወደኋላ የቀሩ የዘውጌ ብፄረሰቦችን ለማገዝ የሚወሰድ ርምጃ በመርህ ደረጃ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በተግባር ግን በተለይ ግን በማደላደሉ ሂደት ብቃት ለዕፀዘከ ሁለተኛ ደረጃ ከያዘ ለተቋሞች ድክመት አስተዋጽዖ ማድረጉ አይቀርም መንግሥታዊ ተቋሞችን የሚያዳክመው ከዚህ ጋር በተያያዘ ችግር በቅጥር ጊዜ ወይም የውስጥ እድገት ላይ አድልዎ የሚደረግ ሲሆንና ወይም አድልዎ ይደረጋል ተብሎ ሲታመን ነው ከዚያም በላይ ግን የዚህ አድልዎ መሠረቱ የዘውግ መበላለጥ ነው ተብሎ ከታመነ የተቋሞችን የውስጥ ጥንካሬ የበለጠ ክፉኛ ሊሸረሽረው ይትላል በሠራተኛ ሞራል ላይ የሚጥለው ጫና ቀላል አይሆንም ለተቋሞች ቀልጣፋ አሠራር አስፈላጊ የሆነውን የሠራተኞችን መደጋገፍ በመቀነስ በአጠቃላይ በሠራተኛ ው ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ይኖረዋል የተቋሞች የውስጥ አሠራር መዳከም ደግሞ ሙስናን ያበረታታል በአጠቃላይ ዘውጌ ብሄረተኛ ነት ሲበረታታ ለአገር እድገት በአጠቃላይ ለሰላምና መረጋጋት በተለይም ደግሞ በዜግነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ከፍተኛ እንቅፋት ሊፈጥር እንደሚችል በአገራችን በተግባር እያየነው ያለ ችግር ነው የዓለም ሁኔታ መቀየርና ኢህአዴግ ያልሆነውን የማያምንበትን ለመሆን መሞክር ኢህአዴግ ከላይ ባነሳኋቸው ሁለት የተምታቱ እምነቶቹ መወጠሩ አላንስ ብሎት የትጥቅ ትግሉን አሸንፎ ሥልጣን በያዘበት ጊዜ የዓለም ሁኔታ ክፉኛ ተቀየረ በአንድ በኩል ኢህአዴግ በጽኑ የሚያምንበት የግራ ርዕዮተ ዓለም በሶቭየት ሕብረትና በምሥራቅ አውሮፓ ከዚያም ቀስ በቀስ በሁሉም ሶሻሊዝምን እንከተላለን አልባንያን ጨምሮን በሚሉ አገሮች ዘንድ ተቀባይነት አጥቶ በሕዝብ ግፊት የታሪክ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ ውስጥ ተጣለ ከዚያው ጋር አብሮ ግን ከዚህ ቀደም እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ድሀ አገሮች በጥብቅ የሚፈልጉትን የውጭ እርዳታ በሚከተሉት ርዕዮተ ዓለም መሠረት ከምሥራቅ ወይም ከምዕራብ ተጠግተው ለማግኘት የሚችሉበት በተለይ ወታደራዊ አማራጭ አካሄድ ተዘጋ በዓለም ውስጥ ያለው ጨዋታ አንድ ዓይነት ሆነ ይኸውም የከበርቴ ሥርዓት የመመሥረት ሂደት ነው ይህ ሥርዓት ለመመሥረት በኢኮኖሚ ፖሊሲ ዙሪያ መወሰድ ጾ ብርሃኑ ነጋ ከሚያስፈልገው «የመዋቅር ማሻሻም» ርምጃዎች በተጨማሪ በፖለቲካ አደረጃጆት ደረጃም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ቢያንስ በወሬ ደረጃ መገንባት ከሀብታሞቹ አገሮች ጋር ለሚየናር ጤናማ ግንኙነት አስፈላጊ ሆነ ይህ ደግሞ የኢህአዴግ ማንነት ዘኑት ከግራ ርዕዮተ ዓለም ከወሰዳቸው አመለካከቶቹ ጋር ክፉኛ የሚጋጭ ሆነ ከላይ በጠቀስናቸው ሁለት የሚቀናቀኑ አመለካከቱች የተወረጠ ው የኢህአዴግ ነፍስ ሌላ ሦስተኛ በአፍ ዩሚዘምረው ክሁለቱም ማነነቶች ጋር የሚጋጭ አመለካከት ተጨምሮበት ድርጅቱን ዛር የተጠናወተው ያህል አንዘፈዘፈው ይህ በሦስት በኩል የተበጠረ የኢህአዴግ ነፍስ በመጀመሪያ ያጣው ግልጽና ለትግሎቹ የሚገባ ርዕዮተ ዓለምና አጠቃላይ አቅጣጫ ነው ከዚህ በፊት ትክክልም ሆነ ስሀተት አባላቱን የሰበሰበበት ግልጽ ዓላማና አቅጣጫ ነበረው ሥልጣን መያኙ የሚታየው ቢያንስ ለሚያምኑት አባላቶቹ ዋና ዓላማን ከግብ ለማድደፎስ እንደሚያስፈልግ መላሪያ ነበር አሁን ግን ያ ዓላማ የሚታፈርበትና ፊት ለፊት የማይነገር ሆነ ከዚህ በፊት የትግለ ዓላማ የነበረው አድኃሪው የከበርቴ ሥርዓትና ኢምፔሪያሊዝም አሁን አእንደተፈላጊ ሥርዓትና ወገን ሆኖ መቅረቡ በድርጅቱ በራሱ ውስጥ በተለይ በአማኛቹ በ ዘፀህየ በኩል ክፉኛ የአእምሮ አለመረጋጋት መፍጠሩ አይቀርምበኝዚህ አማኞች ዘንድ ድርጅቱ እምነት የሌለው አጠቃላይ ዓላማው መሪምቹን በሥልጣን ለማቆየት የሆነ በዚህም ምክንያት ለዓላማው የተሰዉት ጓዶቻቸው ሕይወት በከንቱ የወደቀ ያስመሰለ ሆኗል በመጀመሪያ ዘር ድርጅቱን የለቀቁት አባሎች በኋላም ላይ በተለይ በሕውሀት ዮውጡውስጥ ክፍፍል ጊኬ የተባረሩት ከፍተኛ የአመራር አባላት ያነሷቸውን ብዙ ጥያቂዎች ከዚህ «ዓላማን ከመሳት ጉዳይ ጋር የተያያዙ አንደነበር ይታ ወሳል ይህ ችግር ግን የድርጅቱ ብቻ አይደለም ጭራሽ ዓላማውን ያሳተና የመኖሩ ምክንያት ሥልጣን ላይ መቆየት ብቻ የሆነ ድርጅት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እንዴት ችግር እንዴሚፈጥር ከኢህአዴሣግ በፊት በህሩ ት ሁለት የአገዛዝ ሥርዓቶች ያየነው ነው ኢህአዴግ ሥልጣን ሲይዝ የተቀየረውን ዓላማ አይቶ በዚህም መሠረት የራሱን የእስከአሁን አመለካከት በዝርዝር ገምግሞ የወደፉት አካፄዱ መለወጥ እንዳለበት አምኖ በዚህም ምክንያት ተለዋጭ አዲስና ከጊዜው ጋር የሚሄድ ዓዳማ አንግቦአባላቱንም ይህንኑ አሳምኖ የአቅጣጫ ቅያሬ አድርጎ ቢሆን ለኣ ገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አዎንታዊ የነባነት ገህ ሲቀደ አስተዋጽዖ ይኖረው ነበር የሆነው ግን ይህ አይደለም ኢህአዴግ በምንም ቦታ የቀድሞ አስተሳሰቡን የግራ ርዕዮተዓለሙን ወይም ዘውግ ተኮር እምነትን ቀይሬያለሁ አላለም ይህንንም ለአባላቱ በግልጽ አላስረዳም በዓለም ላይ የተፈጠረውን ሁኔታና ይህም የሚጠይቀውን እራስን የመተየር ሂደት ኢህአዴግ ያየው እንደ ጊዜያዊ ማፈግፈግ ነው በዚህም ምክንያት የተቀበለው በአንዳንድ ሁለተኛ ደረጃ ጉዳዮች ላይ የሚደረግ ማስተካከል ማስፈለጉን ነው ከሁሉም በላይ ግን ድርጅቱ እውነተኛ እምነቱን ለሦስተኛ ወገኖች በተለይ ለውጭ ኃይሎች ለመሸሸግ የሚያስችል የተራቀቀ የፕሮፖጋንዳ ሥራ መሥራት እንዳለበት እንጂ መሠረታዊ እምነቱን መቀየር አስፈላጊ ሆኖ አላገኘውም በሌላ አነጋገር በኢህአዴግ መሪዎች ዓይን አዲስ የተፈጠረው ሁኔታ የሚጠይቀው የተራቀቀ ብልጥነት እንጂ የራስን የውስጥ እምነት መፈተሸን አይደለም በኋላ በዝርዝር እንደምናየው ለአባላቱ የቀድሞ ዓላማዎች አሁንም ሕያው ናቸው የሚል መልእክት በማስተላለፍ ከቀድሞዎቹ እምነቶቹ ፋጹም ተቃራኒ የሆነ ስራው የፈጠረው ግጭትና ያስነሳው የአካሄድ ቀውስ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ኢህአዴግ ይህንን እውነተኛ አምነትና በማስመሰል መካከል ያሰውን ልዩነት ለማጥበብ የሚያስፈልገው የረቀቀ የፕሮፖጋንዳ ሥራ ብቻ ሳይሆን ለዚያ የሚበጅ የአገዛዝ መሳሪያም መዳበር ነበረበት ይህም ለኢህአዴግ የፀረዴሞክራሲ አካፄድ ከማድረጉም በላይ ለወደፊትም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት ሆኗል በአዲሱ የዓለም ሁኔታ አምባገነናዊ መንግሥታት ዓይን ያወጣ የጭፍጨፋና የኃይል ርምጃ በሕዝባቸውም ላይ እንኳ ቢሆን ለመውስድ ይቸግራቸዋል በመጀመሪያ ያለነው እንዲህ ዓይነት የሰብዓዊ መብት ረገጣን ለሰመደበቅም አስቸጋሪየሚያደርግ በጣም ፈጣንና በቀላሉ ከሌላው ዓለም ጋር የሚያገናኝ ቴክኖሎጂ በተንሰራፋበት ዘመን ላይ ነው ግልጽ የሆነ ግፍ በሚፈጸም ጊዜ ዓለም በቀላሉ እና በቶሎ ያውቀዋል የዓለም እየጠበበች መሄድም በሕዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት እያጠናከረው በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሰው ልጅና ለዴሞክራሲ መብቶች የሚታገሉ ድርጅቶች እንዲበዙ አድርጓል እነዚህ ድርጅቶች በየትም ቦታ ግፍ ሲፈጸም በቶሉ ለመንግሥታቶቻቸው መንገርም ሆነ መንግሥቶቻቸው ርምጃ እንዲወስዱ መግፋት የሚችሉበት ዘመን ነው በዚህም ምክንያት ኢህአዴግ ክእርሱ በፊት የእርሎ ዓይነት ርፅዮተ ዓለም አቀናቃኞች ሥልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ ይጠቀሙበት የነበረበትን በማሳበር የመግዛት እድል አላገኘም ጾር ብርፃኑ ነጋ ለዚህ «ችግር» ኢህአዴግ ያገኘው ፍቱን መሳሪያ ሆአገሪቱን የፍትህ ሥርዓት አስፈራርቶ በመግዛት መሳሪያው ማድግ ነሙ በአንድ በኩል የፍትህ ሥርዓት ከመንግሥት አስፈፃሚ ሐቫል ነፃ ነው የሚለውን የዴሞክራሲ መሠረታዊ መርህ በህገመንሄሥጭ አካቶና ሲሰሙትና ሊታለሉለት ለሚፈልጉት ሁሉ በአስልቺው ኙሮፎፖጋንዳው እየተናገረ በተግባር ግን የፍትህ ሥርዓቱን በሚያሳፍር መንገድ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹን የሚመታበት ፍቱን መሳሪያ አደረገው ይህን ተማሟሩን በትጋት እንዲወጣ በመጀመሪያ መደረግ የነበረበት ተቋሙን ክሪፉኛ ግዳከ ም ነው ለዚህም ልምድ ያላቸውን ዳኞች አባሮና ገና ከህግ ትምህር ቤት በወጡ ወጣቶች ሞልቶ ፍትህን ማግኘት በጣም የሚናፈቅ ነጐር ግ ን የማይገኝ ውድ ነገር እንዲሆን አደረገው በኢትዮጵያ የዳኝነት ታፎክ ለመጀመሪያ ጊዜ የፍርድ ቤት ቀጠሮ ለቀናትና ለሳምንታት መሆኑ ቋር ቶ ለመራት ብዙ ጊዜም ለዓመታት የሚሰጥ ሆነ ፍርድ ቤቶች በሚያስገርም ሁኔታ ከመዳከማቸው የተነሳ አንድ የወንጀል ተጠርጣሪ በእስር ሆኖ ገዳፍዊን ሲከታተል ከአሥር ዓመት በላይ ቆይቶ በመጨረሻ ጥፋተኛ አይጆለህጮ ተ ብሎ የሚለቀቅበት አሳፋሪ ሁኔታ እየተለመደ መጣ ምስክር መስማ ት የተጀመረበት ጉዳይ «ዳኞች አልተሟሉም» በሚል ምስክሮች ሳ ይታዌ ለ ዓ መታት መቆየት ባህል ሆነ ቀጠሮና ፍርድ በተከሳሹ ዓይን ስከ ሚደበላለቁ ድረስ ተደጋጋሚና ረጅም ቀጠሮዎች መስጠት በጥም ሞተለመደ ክስተት ሆነ የፍትህ ሥርዓቱ «ፍትህ የዘገየበት ፍትህ የተግሪ ገወ። በገበሬው ላይ የነበረው የእዝ ኢኮኖሚ ተጽዕኖ መነሳቱና መንግሥት ሰእርሻው ክፍለ ኢኮኖሚ የስጠው ትኩረትና በዚህም ምክንያት የእርሻ ቴክኖሎጂ አቅርቦት ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በዋነኛነት መጨመር ከጥሩ የዝናብ ሥርጭት ጋር ተደማምሮ አጠቃላይ የአገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት በደርግ ጊዜ ከታየው ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እመርታ እንዲያስመዘግብ አደረገው ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ከ ዓም ጀምሮ የኤርትራ ጦርነት እስከተጀመረበት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት የተመዘገበው አድገት አገሪቱ ድህነትን ለማጥፋት ከሚያስፈልጋትና ያላትን የተፈጥሮና የሰው ኃይል በአግባቡ ብትጠቀም ልታገኝ ከምትችለው በእጅጉ ያነሰ ቢሆንም ከራሳችን የቅርብ ጊዜ ታሪክም ሆነ በአካባቢው ከሚገኙት የአፍሪካ አገራት እድገት ጋር ሲመዛዘን የሚያሳጣ አልነበረም ይህ ሁሉ አዎንታዊ የአኮኖሚ እንቅስቃሴ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ሆነው የኢትዮጵያን ሁኔታ በሚከታተሉና ያገባናል በሚሉ ኃይሎች ዘንድ በተለይም ደግሞ በአገር ውስጥ ባለው የባለሀብትና የመካከለኛ ኢኮኖሚ ክፍል ዘንድ ተጨማሪ ድጋፍ አስገኝቶስታል የድጋፍ መሠረትም የነበረው እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ አመርቂ ነው በሚል ሳይሆን አካፄዱ ተስፋ ስጪ ነው በዚህ ከቀጠለ የበለጠ ጥሩ ነገር የታፈጥሮና ያዕው ኃይልን ፅጎፇዑ መጠፇም ያምዕው ለድ ማገረታያ ያሥሐፈይ ያያዕው ቦጎው ኃይል ዕሙታ ዮጎፃየነቅ ለንዲኖርና ለሃዲንቀሳቀሰ በመፍቀድ ሒያሃኝ ይቻል የጎባረውሃ መያመታ ነው የነባነት ገህ ሲቀድ ይመጣል ከሚል አዎንታዊ ስሜት የመነጨ ነበር የወደፊቱ ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ነው የሚል ግምት ለመውሰድ ካስቻሉት ነገሮች አንዱ በጊዜው የነበረው የድርጅቱና የመሪዎቹ የመማር ፍላጎት ነበር ምንም እንኳን ከላይ በምዕራፍ ሁለት ለመግለፅ እንደሞከርኩት ኢህአዴግ በ ዓም ሥልጣኑን ሲረከብ ከበረሀ ይዞት የመጣው ጠንካራ የሚባል የግራ ርፅዮተዓለምና ሥር የሰደደ ዘውጌ ብሔረተኛነት ቢኖረውም ሥልጣኑን በያዘበት ጊዜ የተለወጠውን የዓለም ሁኔታ ከግምት በማስገባት በተወሰነ ደረጃ የማይወደው ቢሆንም በኢኮኖሚ ፖሊሲውም ሆነ በፖለቲካ አስተሳሰቡ በመጠኑ የሊበራል አስተሳሰብን ማንፀባረቅ እንዳለበት ቢያንስ የተወሰኑት የድርጅቱ መሪዎች በቅጡ ተገንዝበውት ነበር ይህንንም ለአነሱ አዲስ የሆነ አመለካከት ለማስመሰልም ቢሆን ትንሽ መማር ነበረባቸው ስለዚህም በተወሰነ ደረጃ በመሪዎቹ አካባቢ እያደር እየደነደነ የመጣው ሁሉን እናውቃለን የሚል ትዕቢት አልነበረም ከተለያዩ ሰዎች ጋር ይወያዩ ነበር ከፍተኛ የሆነ የመማር ፍላጎት ነበራቸው በራሳቸው ለመቀለድ የሚያስችል ትህትናም ነበራቸው ከሁሉም በላይ ደግሞ በፊት በከፍተኛ ጥርጣሬ ሲያዩት ከነበረው የከተሜው ማኅበረሰብ ጋር በሰፊው በመቀላቀል አንዳንዱን አክራሪ አመለካከታቸውን በፖለቲካና በኢኮኖሚ ዙሪያ ብቻ ሳይሆን በማኅበራዊ ኑሮም በመጠኑም ቢሆን ለመሞረድ ችለው ነበር በዚህ ሁሉ ምክንያት አብዛኛው ሰው በየጊዜው የሚያደርጓቸውን አንዳንድ ስህተቶችም በክፋት ባለማየትያስመዘገቧቸውን ጠቃሚ ውጤቶች በአዎንታዊነት በመመልከት በይበልጥም ይህ አዳዲስ ሁኔታዎችን ለመምሰል የሚያደርጉትን ሙከራና ለመማር የሚያሳዩትን ፈቃደኛነት ከግምት በማስገባት ስለወደፊቱ የነበረው ግምት በአብዛኛው አዎንታዊና ተስፋን የተላበሰ ነበር ለማለት ይቻላል ይህ ማለት በጊዜው በኢህአዴግ ላይ ተቃውሞ አልነበረም ማለት አይደለም ነገር ግን የነበረው ተቃውሞ አንድም በየጊዜው በሚከሰቱ ጊዜያዊ ችግሮች ላይ ያተኮረና እነዚያ ችግሮች በድጋሚ እንዳይከሰቱ ለመከላከል ሌላም እነኝህ ስሀተቶች መሠረታዊና የአስተሳሰብ ሲሆኑም ሂሶቹ ከነምክንያታቸው በአሳማኝ መልክ ከቀረቡ ድርጅቱ ራሱን ለማረም ይችላል ከሚል በገንቢነት የሚቀርቡ ነበሩ ለማለት ያስደፍራል ይህ ግን በእርግጥም ኢህአዴግ ለሥልጣን ሲቃረብ ጀምሮ በፍፁም ሰአገሪቱ አይበጅም በሚል ድርጅቱን እንደ አጥፊ ድርጅት የሚያየውንና አናሳ ነበር ያልኩትን የፖለቲካ ኃይል አይመለክከትም ከዚህ ውጭ ያለው ተቃዋሚ ግን ጾር ብርዛኑ ነጋ ተቃውሞው የተለሳለሰና መንግሥትን ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ ለመግፋት የሚሞክር ነበር የተቃውሞው ስሜታዊ መለኪያ ምንም ሆነ ምን በጊዜው የሚነሱት የተቃውሞ ፃሳቦች መንግሥት በሚከተለው የዘውጌ ብሔረተኛ ነት ፖሊሲና ይህም ሊያስከትል ይችላል ተብሎ በሚፈራው መዘዝ ላይ ያተኮረ ነበር ማለት ይቻላል ኢህአዴግ ሥልጣን ላይ እንደወጣ ያካሂድ በነበረው ዘውግ ተኮር የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ ተነሳስቶም ሆነ በጊዜው አጋጣሚውን በመጠቀም ራሳቸውን የተመቻቸ የፖለቲካ ይዞታ ላይ ለማስቀመጥ በሚፈልጉ በኢህአዴግ ውስጥም ሆነ ከኢህአዴግ ውጪ ባሉ ዘውጌ ፖለቲከኞች ቅስቀሳ ምክንያት በአርባጉጉ በበደኖና በሌሎችም ቦታዎች የተከስቱ አስቃቂ ግድያዎችና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ብዙ ተመልካቾችን ማስደንገጡ ብቻ ሳይሆን አንዳንዶቹን ከእንዲህ ዓይነት የጅምላ ጥቃት ራስን ለመከላክል በሚል በተደራጀ መልኩ የፖለቲካ ተቃውሞ ለማካሄድ ገፋፍቷቸዋል በዚህ መልክ የሚነሱ ተቃውሞዎች በተለይ ኢሕአዴግ እያደር የዘውጌ ድርጅቶችን በነፃ መደራጀት መፍራት ሲጀምርና በእነኝህ ድርጅቶች ላይ እንቅፋት ሲፈጥር ወይም በላያቸው ላይ የኢህአዴግን መስመር ይክተላሉ የሚባሉ የራሱን የዘውግ ድርጅቶች ማራባት ሲጀምር በዚያው ልክ በኢህአዴግ ላይ ያለው ተቃውሞ እየከረረ ሊሄድ ችሏል በጊዜው የነበረው ሌላው ለኢህአዴግ ተቃውሞ እርሾ የሆነው በኤርትራ ጉዳይ ላይ ይወስድ የነበረው አቋም ነበር ለብዙ ኢትዮጵያውያን ብሔረተኞች ኤርትራ የተገነጠለችበት ሁኔታ ጥሩ ስሜት ያልፈጠረ ቢሆንም በጊዜው ሊያቆሙት የማይችሉት እና በጉልበት በኤርትራ ጦርነት የተፈፀመ በመሆኑ እንዲሁም በዚያ ጊዜ ተመልሶ ጦርነት ውስጥ መግባትን ስለማይቀበሉ የኤርትራን መገንጠል እያንገራገሩም ቢሆን ለመቀበል ፈቃደኞች ነበሩ ሆኖም ይህንን በጦርነት የተወሰደን እርምጃ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት ኢህአዴግ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ያልወደዱ ብዙ እንደነበሩ አሁንም እንዳሉ አሌ አይባልም በነሐሴው ጉባዔ ላይ የኤርትራን ሕዝበ ውሳኔ ሪፈረንደም በሚመለከት ኢትዮጵያ እንደሚያገባት አካል ሳይሆን እንደ ተመልካች ሆና መቅረቧ ወይም ሪፈረንደሙ በትክክል የኤርትራን ሕዝብ ስሜት ማንፀባረቁን በአጠቃላይና በተለይም ደግሞ የኤርትራን ከኢትዮጵያ መገንጠል የማይደግፉ ኃይሎች በሪፈረንደሙ ጊዜ ያለምንም መሳቀቅ በነፃ ለማስተማርና ሕዝበውሳኔው የእነሱን አመለካከት በሚጠቅም መልኩ እንዲወሰን በሰላማዊ መንገድ የመሞከር እድል እንዲኖራቸው የነዛነት ጎህ ሲቀድ አለመፍቀዱ ከሪፈረንደሙ በኋላ በኢትዮጵያና በኤርትራ መሐል ሊኖር የሚችለውን ግንኙነት በሚመሰከት በተለይም የዜግነት ጥያቂ ተድበስብሶ ማለፉ ሪፈረንደሙ እስከሚካፄድም ሆነ ከዚያ በኋላ በሁለቱ አገርች መሐከል ጦርነት እስከሚነሳ ድረስ የነበረው ቅጥ ያጣ ግንኙነት ለምሳሌ የኤርትራ በብር ላይ የራሷን የውጭ ምንዛሪ አስከመተመን የደረሰ በአንድ አገር ሁለት የገንዘብ ፖሊሲ ያለ እስኪመስል ያልተገራ የኢኮኖሚ ግንኘ ነትኢህአዴግ የኤርትራን መገንጠል ለማወቅ የመጀመሪያ መሆን ብቻ ሳይሆን በቶሎ አስክትገነጠልለት ድረስ መጠበቅ ያቃተው አስኪመስል ድረስ የኢትዮጵያን ጥቅምች ከግምት አለማስገባት ወዘተ ተደማምር ብዘ ኢትዮጵያውያን የኢሀአዴግን አቋም አልወደዱለትም ነበር ለማለት ይቻሳላል ከዚህ በተጨማሪ ግን ኢህአዴግ ከኤርትራ ጋር በተያያዘ አገሪቱን ወደብ አልባ ማድረጉና የወደብ ጥያቄን እንደ አልባሌ መሬት የማግበስበስ ጥያቄ አድርጎ ማየቱይህንንም በተለያየ ዲስኩሩ ለሕዝብ በግልጽ ማቅረቡ በፍፁም አልተወደደለትም ነበር ይህ መንግሥት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ደንታ የለውም ወይም ደግሞ የብሔራዊ ጥቅም ምንነት ግልጽ አልሆነለትም በሚል ድርጅቱን በጥርጣሬ የሚያዩ ቁጥራቸው ትንሸ አልነበረም በኢኮኖሚ ዙሪያ አንዳንድ ተመልካቾች አንዳንድ ጊዜ የተወሰነ ጭብጥ በመያዝ ብዙውን ጊዜ ደግሞ እንዲሁ በአሉባልታ ላይ በተመሠረተ ወይም በዘር ላይ የተመሠረተ መንግሥት ይህን ማድረጉ አይቀሬ ነው ከሚል ግምት ኢህአዴግን አድሏዊ ነው በማለት ከሰውታል በይበልጥ ደግሞ ከሜዳ ሰብስቦ ያመጣቸውን ንብረቶችና አንዳንዴም በአጠራጣሪ መንገድ የመንግሥት ሥልጣን ክያዘ በኋላ የመንግሥትን ሀብት በመጠቀም ያደራጃቸው የፓርቲ የንግድ ተቋማት አጠቃላይ የገበያ ኢኮኖሚ ሂደቱን ያደናቅፋሉ በሚል ተቃውሞ ሲቀርብበት ነበር ቢሆንም በመጀመሪያዎቹ የጫጉላ የሥልጣን ዓመታት ከሳይ በጠቀስኳቸው አዎንታዊ የኢኮኖሚ እርምጃዎች ምክንያት ኢህአዴግ ይፈጥራቸው የነበሩት ችግሮች ውሎ አድሮ እንዳየነው በጣም ጎልተው አልተስተዋሉም ነበር በአጠቃላይ ግን በዚህ ጊዜ በኢህአዴግ ላይ የሚቀርቡት ሂሶች እንደተጠበቁ ሆነው የኢህአዴግ አዎንታዊና አሉታዊ ገጽታዎች በሁለት ሰንጠረዥች ተደርድረው ቢቀርቡ በጊዜው ከነበረው ሁኔታና ኢህኦዴግ አሽንፎ ከመጣው ኃይልና ተሸናፊው ትቶት ከፄደው መሠረታዊ የኅብረተሰብ ችግሮች ጋር በማነፃፀር በእኔ ግምት ብዙው ሰው አዎንታዊ ገጽታዎቹን አጉልቶ አሉታዊ ገጽታዎቹን ወደፊት ሊሻሻሉ እንደሚችሉ ችግሮች ጾር ብርፃዛኑ ነጋ በመመልከት የአገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጥሩ ሊሆን አንደሚችል በማስብ ለኢህአዴግ «ሂሳዊ ድጋፍ» የሚሰጥበት ጊዜ ነበር ለማለት ያስደፍራል ይህ ደግሞ ሊገርም አይገባም ሁሉም ዓይነት አዲስ ለውጥ በተግባር ትክክለኛ ምንነቱን እና ይዘቱን እያደር ግልጽ አያደረገ እስከሚመጣ ድረስ ለለውጡ ፃሳቦች መተግበር ኅብረተሰብ ግዜ ሰጥቶ መጠበቁ የተለመደ ነው ኅብረተሰቡ በለውጥ ፃዋርያ ነን ባዮቹ ላይ እንኪን ጥርጣሬ ቢኖረውም ሁኔታዎች ሊቀየሩ ይችላሉ የሚል ተስፈኛነቱ መቀጠሉ አይቀርም ይህም ሁኔታ ለለውጥ መምጣት እድልና ጊዜ እንዲሰጥ ያድርገዋል ይህንን ነው የፖለቲካ ተመልካቾች አዲስ መንግሥት በተፈጠረ ጊዜ ማኅበረሰቡ ይህ መንግሥት እስከሚለማመድ እና በተግባር አገሪቱን የሚወስድበት አቅጣጫ እስኪለይ ድረስ የመጀመሪያዎቹን ወራት ወይም ዓመታት በሕዝቡ የሚሰጠውን የእስኪ እንየው ሂሳዊ ድጋፍ» የጫጉላ ሽርሽር ጊዜ የሚሉት በ ዓም የአብዮት ዘመን በተመሳሳይ ለደርግ ወታደራዊ መሠረት ያለው ጥርጣሬ እንደተጠበቀ ሆኖ በ«ያለምንም ደም» እና «በኢትዮጵያ ትቅደም» መፈክሩ ለተወሰነ ጊዜ ይህ መንግሥት መሠራት ያለባቸውን አገራዊ ሥራዎች በሽግግር መልክ በቶሎ ሠርቶ ወደ ጦር ካምኾኙ ይመለሳል በሚል ሂሳዊ ድጋፍ የሰጡት ቀላል ግምት የሚሰጣቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች አይደሉም በእንዲህ ዓይነት የታሪክ አጋጣሚ ሥልጣን የሚይዙ ኃይሎች የያዙትን ሥልጣን ከሕዝቡ የተቸራቸውን ጥሩ ስሜትና ድጋፍ ሀ ቨዘስ ሳያበላሹ ኅብረተሰቡን ጥሩ መሰረት ላይ ጥለው ሥልጣናቸውን የሚለቁ አርቆ አሳቢ መሪዎች ሊፈጠሩ የሚችሉትን ያክል በተለይ በአኛው አህጉሩ እንደተለመደው አገርና ሕዝብ ከማስቀደም ይልቅ በሥልጣን ፍቅር ሰክረው ያገትን መልካም የታሪክ አጋጣሚ አበላሽተው ለአገራቸውም ለራሳቸውም ሳይበጁ የሚያልፉ መሪዎች ብዙ ናቸው የደርግ ወታደሮች በታሪክ አጋጣሚ ያገኗትን ሥልጣን ለጥፋት እንደተጠቀሙበት የሚያጠያይቅ አይደለም የደርግ ወታደሮች ከሌሎች አገር ታሪኮች ካልተማሩ በስተቀር የሚወስዲቸው እርምጃዎች በአገሪቱም ሆነ በራሳቸው ላይ ሊያስከትል የሚችለውን መዘዝ የሚማሩበት የተግባር ታሪክ በኢትዮጵያ ነበር ለማለትም ያስቸግራል የኢህአዴግ መሪዎች ግን ከደርግ የተሻለ የሚማሩበት የታሪክ እድል ነበራቸው ከራሱ ከደርግ አወዳደቅና ውርደት መማር ይችሉ ነበር ስለዚህም ኢህአዴግ በጫጉላ ሽርሽር ዘመኑ ቢያንስ ደርግ ያደረጋቸውን ዓይነት ስህተቶች አይደግምም ስህተቶቹንም በቶሎ ያርማል የሚል የነባነት ገህ ሲቀድ ግምት ነበር ኢህአዴግን የመጀመሪያዎቹ ዓመታት የወደፊት በጊዜ ብዛት ኢህአዴግ አብዛኛው ኅብረተሰብ ወደሚፈልገው ዓይነት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አገሪቱን ሊወስዳት ይችላል በፍጥነት እንኳን ባይሆንም በዝግታ ግን በእርግጠኝነት ወደዚያ ይሄዳል የሚለውን አዎንታዊ ስሜት እኔም ራሴ እጋራው የነበረ ነው ይህንንም ስለማምን ነበር በተሰማራሁበት የሥራ መስክም ሆነ እንዲሁ እንደ ዜጋ በይፋ በኦፊሴል በምጽፋቸው ጽሑፎቼም ሆነ በግል የኢህአዴግን ባለሥልጣናት በማገኝበት ጊዜ በእኔ ግምት ስህተት ናቸው ብዬ የማምናቸውን እርምጃዎቻቸውን ያለምንም ይሉኝታ በግልጽ እነግራቸው የነበረው ይህ ዓይነት «የሂሳዊ ድጋፍ» አመለካከት ቢያንስ እስከ ኤርትራ ጦርነት ፍፃሜ ድረስ በሁሉም ሰው ዓይን እንኳን ባይሆን በብዙ ሰዎች ዘንድ ነበር ለማለት ይቻላል በኋላ ለማሳየት እንደምሞክረው በዚህና ከዚህ ጋር በተያያዙ ሌሎች ጉዳዮች ምክንያት በዚህ ጊዜ በኢህአዴግ ላይ የተነሳው ሰላማዊና ሕጋዊም ሆነ ከዚያ ውጪ ያሉ ተቃውሞዎች በጣም ቀዝቃዛ ነበሩ ለማሰት ያስደፍራል ይጫ ጄጋሩ ሲዖሳቀ ያይያጴሀጳዳዴሃ ለጳትሄድ ጳያደሮ ። የሚለውን በአጭሩ እንመለከታለን ከዚያ በፊት ግን ኢህአዴግ በማኅበረሰቡ ዘንድ ድጋፍ ያስገኝልኛል ብሎ የሚያምንበት «የሰላምና መረጋጋት» ጉዳይ የኢህአዴግ የጫጉላ ሽርሽር ሲያልቅ ጥያቄ ውስጥ መግባት ከጀመሩት ጉዳዮች አንዱ ስለሆነ በዚያ ላይ አጭር አስተያየት ሰጥቼ ልለፍ ሰላምና መረጋጋት የኢህአዴግ ትልቅ የስኬት መግለጫ መሆኑን በተደጋጋሚ በመንግስት መገናኛ ብዙኃን የሚሰማና ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ የሚውል ነው ምንም እንኳን የኢህአዴግ መንግሥት ከተቋቋመ ጀምር እንደ ደርግ በሁሉም አቅጣጫ የሚወጥረው የተቃውሞ የትጥቅ ትግል ባይኖርም የነበረው አንፃራዊ ሰላም ሙሉ ነበር ማለት አይቻልም በተለይ በየአካባቢው የሚነሱ የሕዝብ ግጭቶች የኢህአዴግን የሰላም አመጣሁ ፕሮፖጋንዳ ጥያቄ ውስጥ ከትተውታል ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ የተነሱት ግጭቶች በአብዛኛው ግንባሩ በሚገፋው ዘውግ ተኮር ፕሮፖጋንዳ ምክንያት የተፈጠሩ ወይም የተባባሱ የአካባቢ የአርስ በእርስ አንድ ጎሳ ከሌላ ጎሳ ግጭቶች ነበሩ እንዲህ ዓይነት ግጭቶች በተለይ በደቡብ ጾር ብርዛኑ ነጋ ክልል በአፋርና ኢሳ መሀከል ነበሩ በሶማሌና በኦሮሚያ ሕዝቦች መሀከል እንዲሁ በእነዚህና በሌሎችም የተነሱት ከመሬት ይገባኛል ማለትም የተወሰነው የግጦሽ ወይም ሌላ መሬት የእኔ ጎሳ መሬት ነው ሲል ያንኛ ው ጎሳ አይገባውም የሚል ዓይነት ዘውግ ተኮር ውዝግብ ናቸው ሌሎች ግጭቶች ደግሞ በብሔር ብሔረሰብ መስፈርት የተዋቀሩ ክልሎች ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ ዘውጌ ማኅበረሰቦች የሚያነሷቸው የፖለቲካ ሥልጣን ይገባኛል ግጭቶች ነበሩ በዚህ ዙሪያ እንደ አብነት የሚጠቀሱ ችግሮች በጋምቤላ በአኝዋክና በኑዌር ዘውጌ ማኅበረሰቦች መሐክል የሚነሱ ውዝግቦች በከፋሽካና መንገር ዘውጌ ማኅበረስባት መሐከል የነበሩ ግጭቶች ዓቸው ወደ ግልጽ የጉልበት ግጭት አይሽሸጋገር እንጂ በሀረሪ ክልል በሀረሪና በኦሮም እንዲሁም በሴሎች ማኅበረስባት መሐከል የሚክሰቱ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ከዚህ ዓይነት ግጭቶች ጋር የሚደመሩ ናቸው እነሺሂህ ሁሉ ግጭቶች ግን ኢህአዴግ ሰላምና መረጋጋት አምጥቻለሁ የሚለውን ፕሮፖጋንዳ ተዓማኒነት ነስተውታል ለብዙ ተመልካች እነኘ ህ ግጭቶች በጣም አይለው አጠቃላይ ማኅበራዊ መናጋት ባይፈጥሩም ቢያንስ ኢህአዴግ ለአገሪቱ የቀየሰላት ዘውግ ተኮር የማኅበረሰብ አደረጃጀት ሞዴል ዘላቂ ሰላም ማምጣቱን ክፉኛ ጥርጣሬ ውስጥ ከትቶታል ይህ ብቻ አይደለም የአገሪቱን የብሔር ችግር ይፈታል የተባለው ሞዴልና ኢህአዴግ ሥልጣን ስይዝ በፈጠርኩት አዲስ ሥርዓት ምክንያት ብዙ ጠመንጃ ይዘው ይታገሉ የነበሩ የዘውጌ የፖለቲካ ድርጅቶች ጠመንጻቸውን ትተው በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወሰኑ በዚህም ምክንያት በአገሪቱ ሰላም ሰፍኗል የሚለው አባባል በመጀመሪያው ዓመታት እውነት ቢመስልም ብዙም ሳይቆይ በተግባር እየተፈተነ መጣ የኦነግ ከሽግግር መንግሥቱ መውጣትና የወታደር ኃይሉን ማጣት ከጥቂት ጊዜ በኋላ አንደገና ተደራጅቶ የትጥቅ ትግሉን ለመቀጠል ኣላስቸገረውም ከዚያም ውጭ በሶማሌ በጋምቤላ በተወሰነ የደቡብ አካባቢዎች መንግሥትን ለመቋቋምና ለመፈታተን ያላቸው አትም ይነስም ይብዛም በጠመንጃ የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት የሚታገሉ ኃይሎች አልጠፉም ይህ ሁሉ ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከጠመንጃ አውጥቼ ሰላማዊ አድርጌዋለሁ ይህም የምመሠርተውን ማኅበራዊ ሞዴል ትክክለኛነት ያሳያል የሚለው መልዕክቱ ከፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ያለፈ መሠረት የሌለው መሆኑን በተለይ ከኤርትራ ጦርነት በኋላ በነበሩት ዓመታት በግልጽ አሳይቷል ሰላምና መረጋጋትን በተመለከተ የኢህአዴግን አትም ማጣት የሚያሳየው የነዛነት ገህ ሲቀድ ግን ግጭቶች መፈጠራቸው በራሱ ሳይሆን የተፈጠሩ ግጭቶችን ለመፍታት ይወስድ የነበረው እርምጃ ሰላምን በዘላቂነት ለማምጣት መቻሉን ተጨማሪ ጥርጣሬ ውስጥ ከትቶታል በአጠቃላይ ሥርዓቱን በተቃወሙ ኃይሎች ላይ ብቻ ሳይሆንብብዙ መልኩ በአካባቢ የታጠሩ ችግሮችንም ለመፍታት የሚሞክረው ኃይልን በመጠቀም በመሆኑ አራሱ ኢህአዴግ የሰላም ኃይል መሆኑን ማኅበረሰቡ እንዲጠራጠር አድርጎታል በአዋሳ የተነሳውን የሲዳማ ማኅበረሰብን የክልል ይገባኛል ጥያቄ ብዙ ሰዎች በመግደል ለማቆም መሞከሩ በጋምቤላ ለነበረው ግጭት የሰጠው ዘግናኝ የጭፍጨፋ መልስ በከፋ ሸካ ዞን በመንግሥት ታጣቂ ኃይሎች የተፈፀመው እልቂት ኢህአዴግ ግጭቶችን ለመፍታት ሰላማዊ ዘዴን የሚከተል ሳይሆን ጥሎት እንደመጣው አንደ ደርግ መንግሥት ጉልበትን ማምለኩን የሚያሳይና «የሰላምና የመረጋጋት» ዲስኩሩንም የሚያፈርስ ሆናበታል በጥቅሉ የግንቦት ምርጫ ከመምጣቱ በፊት ኢህአዴግ በመጀመሪያ ሥልጣን ላይ ሲወጣ የነበረውን የሕዝብ በጎ ስሜት በአብዛኛ ው አሟጧል ድርጅቱ አምንበታለሁ የሚለውን የርዕዮተ ዓለም መሠረቶች አመናምኖ በተሻለና ሕዝቡን ሊስብ በሚችል አዲስ ርዕዮተ ዓለም አልተካም ድርጅቱ አራሱ ከኤርትራ ግጭት ጋር በተያያዘና ከዚያም በላይ በድርጅቱ ዘላቂ ዓላማ ማጣት ምክንያት በውስጡ የነበረው የቀድሞው አንድነትና የዓላማ ጽናት ተናግቷል የአገሪቱ ስላምና መረጋጋት አስተማማኝ መሠረት አልያዘም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው አመርቂ ያልሆነና በተሰይ በከተማው እያደር እየጨመረ በሄደው ሥራ አጥነትና ድህነት እንዲሁም የተመሰቃቀለ የከተማ ኑሮ ችግሮች ምክንያት ጥልቅ አዘቅት ውስጥ ተገብቷል ጥርጣሬ ውስጥ ገብቶ የነበረው የኢህአዴግ ብሔራዊ ጥቅም አስጠባቂነት በኤርትራው ጦርነት መጀመር ጊዜ በነበረው የጋራ አገራዊ ብሔርተኝነት አገግሞ ብዙ ሳይቆይ ኢህአዴግ ከጦርነቱ በኋላ ባደረጋቸው ስምምነቶችና በሄጉም ፍርድ ቤት ውሳኔ ምክንያት እንደገና የመነመነበት ጊዜ ነበር በዚህም ምክንያት በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሕዝቡን ድጋፍ የማግኘት እድሉ ደካማ ነበር ቢሆንም ግን በዴሞክራሲ ስም ኢ ዴሞክራሲያዊ ሥራዎች እየሠራ የደጋፊ አገሮቹን ገንዘብ ያለገደብ ማግኘ ት እንደማይችል ስለዚህም በተወሰነ ደረጃ በ አንጻውን ሲያባርር የገባውን የአገሪቱን የተሻለ ዴሞክራሲያዊ የማድረግ ቃሉን ዝም ብሎ ለማጠፍ እንደማይችል የተገነዘበበት በመሆኑም የ ምርጫ የተወሰኑ መሻሻሎች አድርጎ ምርጫውን ቢያንስ በውጭ ተመልካቾች ዘንድ ጾር ብርፃኑ ነጋ ዴሞክራሲያዊ መሆኑን ማሳመን አማራጭ እንደሌለው ተረድቶ ለዚህም በተወሰነ ደረጃ ተዘጋጅቶ ነበር የ ዓም ምርጫ ዝግጅትን የጀመረው ይህም የተሰላው ምርጫውን ለማሸነፍ እንደሚችል በመገመት ብቻ ሳይሆን እንደሚያሸንፍ እርግጠኛ ሆኖ ነበር ለዚህ ጽኑ እምነቱ መሠረት የሆኑትን ስሌቶች በኋላ በዝርዝር አንመጣባቸዋለን ከእነሂህ ውስጥ አንዱ ግን በተቃዋሚ ኃይሎች ውስጥ አለ ብሎ የገመተው ትልቅ ድክመት ነው የዚህን ስሌት እውነትነት ለመመልክትና በቅድመ ምርጫ የነበረውን የአገሪቱን ፖለቲካ ሙሉ ገጽታ ለማሳየት ከምርጫ በፊት የነበረውን የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶች ሁኔታ በአጭሩ እንመልከት ቆድመ ምርጫ ዕሏጉምሾቷቋያ ሰምጋ ጠጋሳራ ፖቃምሟጃ መፍጠረ ለኋታቻሰምዖ ይህን ክፍል በምጽፍበት ጊዜ ማመን ያለብኝ አንድ ቁም ነገር አለ ከ ዓም ምርጫና ለዚህም ዝግጅት መደረግ ከጀመረበት ጊዜ በፊት የነበረውን የተቃዋሚዎች ሁኔታ ጠልቄ አላውቅም እንደማንኛ ውም የውጭ ተመልካች በሚዲያ ከምከታተላቸው ከእኔ በተሻለ ከሚያውቁ ከአንዳንድ ጓደኞቼ ጋር የተቃዋሚውን ጎራ በሚመለከት ባደረኳቸው ውይይቶችና በ ምርጫ ጊዜ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማኅበር «በ ምርጫ የኢኮኖሚ ፖሊሲ» በሚል ባዘጋጃቸው የተለያዩ መድረኮች በክርክሮቹም በአጠያይነት በተሳተፍኩባቸው ጊዜያት ካየሁትና ከታዘብኩት ውጭ በተለይ በተቃዋሚ ድርጅቶች የውስጥ ሁኔታ ላይ የማውቀው ብዙ ነገር አልነበረም ከዚህ የተለየ የማውቀው ነገር ቢኖር ምርጫ ከመምጣቱ ከዓመት በፊት የተቃዋሚ ድርጅቶችን ለማቀራረብና በምርጫ የተሻለ ተዘጋጅተው እንዲቀርቡ ለማድረግ በተደረገ የማስታረቅ አና የማቀራረብ ሙከራ ላይ በሽማግሌነት ከተመረጡት ሰዎች አንዱ በመሆኔ በሂደቱ የታዘብኩትን ጉዳይ ብቻ ነው ለማንኛውም የዚህ ክፍል ዓላማ ስለድርጅቶቹ የውስጥ ሁኔታ ለማውራት ሳይሆን በአጠቃላይ የተቃዋሚው ኃይል የተዳከመባቸውን ዓብይ ጉዳዮች ለመመልከት ስለሆነ በእነኝህ አበይት ጥያቄዎች ላይ ብቻ አተኩራለሁ የኢህአዴግ ዘውግ ተኮር ፖለቲካ በብዙ መልኩ ችግር ያለበት ቢሆንም ከራሱ ፖለቲካ አንፃር የፖለቲካው ትኩረት በሥልጣን መቆየት የነዛነት ጎህ ሲቀጀፎ ነው ከሚል ግምት ይህ ፖለቲካ ቢያንስ የተቃዋሚውን ጎራ በማዳከም በኩል በደንብ ተሳክቶለት ነበር ለማለት ይቻላል ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ከምንም በላይ የሚጠረጥረውና የማይስማማው ዘውግ ዘለል የሆነ ፖለቲካ ነበር የርዕዮተ ዓለሙ አንድ ምርኩዝ የሆነው ዘውግ ተኮር ፖለቲካው በርዕዮተ ዓለም ደረጃ የሚቀናቀነው ሕብረ ብሔራዊ ፖለቲካ መሆኑን ስሰሚያውቅ በዚህ መልክ የሚደራጁ የፖለቲካ ኃይሎችን ለማደከም በአንፃሩ ደግሞ በኢህአዴግ ጥላ ሥር ባይሆኑም እንኳን በዘውግ አጥር ውስጥ የሚደራጁ ኃይሎችን ማበረታታት አንዱ ሥራው ነበር በፕሮፖጋንዳ ደረጃ ራስን በኢትዮጵያ ደረጃ ማየት ራሱን የቻለ የፖለቲካ አመለካከት ሳይሆን «ትምክህተኛ አማራ በኢትዮጵያ ጥላ ሥር ተደብቆ የሚያራምደው ሥውር ፖለቲካ» አንደሆነ ነበር የሚቀርበው ስለዚህ በተቻለ መጠን ማንነትን ከዘውግ ጋር እንጂ ከኢትዮጵያዊነት ጋር ማቆራኘ ት የሚወገዝ ነበር ይህ ፕሮፖጋንዳ ሥር ከመስደዱ የተነሳ የዘውግ ፖለቲካን ጭራሽ ግራ መጋባት ዳዕይሠያሃካጓ የሚያሳየው ከተለያዩ ብሔረሰቦች የተወለዱ ኢትዮጵያውያን በምን መልክ በፖለቲካው ውስጥ ይሳተፉ ለሚለው ጥያቄ አንድ ድርጅት በ ምርጫ ይመስለኛል ይዞ የቀረበው መፍትሔ «የቅይጥ ብሔር ብሔረሰቦች» የፖለቲካ ድርጅት የሚል አስቂኝ ስብስብ ነበር በዚህም ምክንያት በአንድ ወቅት የአገሪቱ ፖለቲካ በአብዛኛው የመንግሥት ሥልጣን በያዘውም ሆነ በተቃዋሚው በክውግ ስብስቦች የታጠረ ነበር ይህ አካፄድ በአንድ በኩል በዘውግ ተኮር ፖለቲካ የማያምኑ ሰዎችን አንድም ከልብ በማያምኑበት ግን በአልህና «በራስን መከላከል» መርህ ስም ራሳቸውን በዘውግ እንዲያደራጁ ገፋቸው በሌላ በኩል የዚህ ዓይነት ፖለቲካ የማይጥማቸው ግን በፖለቲካው ዙሪያ ብዙ አስተዋጽዖ ሊያደርጉ የሚችሉ ሰዎችን ከፖለቲካው አገለላቸው ሁለቱም አካሄድ ግን የተቃዋሚ ፖለቲካውን ሂደት ማዳከሙ አልቀረም የኋለኛው በተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ የሚሳተፈውን የሰው ኃይል ሲያመናምነው የመጀመሪያው የተቃውሞውን ፖለቲካ ካለው የመንግሥት ፖለቲካ የተሻለ አማራጭ ይዞ የቀረበ ሳይሆን ራሱን አንድን ዘውጌ ማኅበረሰቡ ለመከላከል የተነሳ ዘውጌ ማኅበረሰቡ ብቻ ደረሰብኝ ለሚለው በደል ምላሽ ለመስጠት ወይም ለዘውጌ ማኅበረሰቡ «መከታ» ለመሆን የተቋቋመ ስለሆነም ለሌሎች ከውጌ ማኅበረሰባት «አስፈሪ ድርጅት አስመሰለው በዚህ መልክ በዘውግ ስም ተደራጅቶ ነገር ግን በፕሮግራም ደረጃ ሕብረብሔራዊ ነኝ የሚለው ጾር ብርዛኑ ነጋ አካሄድ በአንድ ወቅት መአህድ ውስጥ ይታይ የነበረው አመለካከት እንዲያውም የኢህአዴግን አማራ በኢትዮጵያ ስም» ክስ አውነት ያለው አስመስለው መአህድ ይህ አካፄድ እንደማያዋጣው አውቆ ራሱን ወደ ሕብረብሔራዊነት ቀይሮ ከአማራ ክልል ውጪ በተለይ በደቡብና በአፋር በአነስተኛ ደረጃም በትግራይ የድርጅቱን መረብ መዘርጋት እስኪጀምር ድረስ ከሌሎች ውስጣዊ ችግሮቹ ጋር ተደማምሮ ክፉኛ ተዳክሞ እንደነበር የሚታወቅ ነው በሌላ በኩል የዘውግ ፖለቲካ ኦፊሴላዊ ድጋፍ ማግኘቱን ያወቁና በዘውግ መደራጀት ቁሳዊ ጥቅም ሊያስገኝ እንደሚችል የተረዱ የየዘውጌ ማኅበረሰቡ ንዑስ ዲታዎች በጥቂቱ እየተሰባሰቡ የፖለቲካ ድርጅት በመፍጠር ለመቁጠር እስከሚያቅት ድረስ የአገሪቱን የፖለቲካ ሜዳ አጨናነቁት የተጨዋቹ አለቅጥ መብዛት ደግሞ ጨዋታውን እውነተኛ ላይሆን ፍጹም ቀልድ አደረገው ሁለት ቡድኖች አስራ አንድ አስራ አንድ ተጫዋች ይዘው በሚጫወቱበት የእግር ኳስ ሜዳ አስር ቡድኖችና አንድ መቶ አስር ተጫዎቾች ቢገቡበት ሊሆን የሚችለው ዓይነት ትርምስ ማለት ነው ይህ የተጫዋቾች መብዛት ደግሞ ኢህአዴግን በአጅጉ ጠቅሞታል ኢህአዴግን የሚቃወሙ ኃይሎችና የኅብረተስብ ክፍሎች አትኩሮት የሚሰጡት አንድ ድርጅት ወይም የተቀናጀ የድርጅቶች ስብስብ ለመፍጠር አዳጋች እንዲሆን አድርጎታል ከዚያም በላይ ግን እነኝህ ሁሉ ድርጅቶች በዘውግ ስም የተደራጁ መሆናቸው በአንድ ላይ ተባብሮ ኢህአዴግን ለመታገል እንዳይችሉ የዘውግ ፖለቲካ በራሱ በሚፈጥረው የእርስ በእርስ መጠራጠር ምክንያት አዳጋች አደረገው ከዚህ በተጨማሪም ኢህአዴግ ራሱ የዘውግ ድርጅቶች ስብስብ እንደመሆኑ እያንዳንዱ የዘውግ ማኅበረሰብ በክንድ መልኩ ወይም ወይም በሌላ በኢህአዴግ በራሱ ውስጥ ወይም «በአጋር» ድርጅቶች ስም በኢህአዴግ ሥር የተደራጀ ስለነበረና በተለይ በዘውግ ማንነታቸው ቁሳዊ ጥቅም ለማግኘት የሚፈልጉ የየዘውጌው ንዑስ ዲታዎች የኢህአዴግን ደጋፊ ድርጅቶች መቀላቀል ስለቀለላቸው በተቃውሞ ስም የተደራጁት የዘውግ ድርጅቶች ብዙ የራሳቸውን አባላት ለማሰባሰብ የሚችሉ ጠንካራ ድርጅቶች አልነበሩም እነሺህ ብዙ ደካማ ሩ ቋላድ ወዖ ምርጫ ሰርድ ዳሳ ዲዱነታወቃው ላሪታ ውሰዕፖ ያሳይ ደፖታያት ድረጅዶቻ በሠጋዊንታ ሦመሃሇጋያዎሳ ይሏታዮጵያጋ ፖታቷጎ ለጥ ዖሟሰዕታታፖሰ ማጋም ዕው ፕራ ቢታታ ፀ በሏይ መፕራቱን ፇ ሕጠራጠራሰታ የነባነት ገህ ሲቀደድ ድርጅቶች በፖለቲካው ለመቀጠል መተባበር እንዳለባቸው ቢያምኑም እንኳን ብዙዎቹ አጥብቀው የሚያምኑበት ዓላማም የሌላቸው በምሆናቸውና በድርጅቱ ውስጥ ያሉት ጥቂት የአመራር አባላት ዋና መደራደሪያቸው ጥቅም ስለሚሆን አስተባብሮ እና ተባብሮ መስራቱም በራሱ ቀላል አልነበረም ይህም ሆኖ ግን ሜዳውን ከሞሉት ብዙ ድርጅቶች ውስጥ በተለያየ ምክንያት የተወሰኑት መአህድ ደቡብ ሕብረት ኦብኮ ጎልተው ወጥተው ስለነበረ በእነዚህ ድርጅቶች መሐልና በሌሎች ትንንሽ በኢትዮጵያ ብሔረተኛነት ሥር የተደራጁ ድርጅቶች ተደማሪነት ትግሉን ለማስተባበር እስከ ምርጫ ድረስ የተለያዩ ግን ያልተሳኩ ሙከሬዎች ተደርገው ነበር በተቃዋሚ ድርጅቶች መጠናከር ላይ እንቅፋት ከሆኑት ጉዳዮች አንዱ ከአገር ውጪ የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በትግሉ ውስጥ እንዴት ይሳተፋሉ የሚለው ጉዳይ ነበር በተለያየ ምክንያት በአገር ውስጥ ገብተው በሰላማዊ ትግሉ ውስጥ መሳተፍ ያልቻሉ ብዙ ድርጅቶች ርአብዛኞቹ የኢህአዴግን ፈቃድ ባለማግኘታቸው በስደት ይገኛ ሉ ከእነሂህ ድርጅቶች ውስጥ የተወሰኑት በአገር ውስጥ መጥተው የተቃዋሚውን ጎራ ለመቀላቀል የተለያዩ ተቃዋሚ ድርጅቶች በጋራ ባዘጋጁት ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ በመጡበት ጊዜ በኢህአዴግ ታስረው ተሳትፎአቸውን በሰላማዊ መንገድ ለማድረግ ያልቻሉ ናቸው ሆኖም በውጭ አገር ሆነው ሰፊ የሕዝብ ድጋፍ እንኳን ባይኖራቸው በማቴሪያል አቋማቸው አገር ውስጥ ካሉት ይሻላሉ እነሺህ ኃይሎችን በተለያየ ጊዜ አገር ውስጥ ካሉት ድርጅቶች ጋር በጋራ እንዲሰሩ ለማድረግ ሙከራዎች ተደርገዋል በአገር ውስጥ ያሉት ድርጅቶች በአገሪቱ የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው መሥራት ስላለባቸው በውጭ ካሉት ይልቅ በጥንቃቄ መንቀሳቀስን ይሻሉ በውጭ የሚገኙት እንዲህ ዓይነት ገደብ የለባቸውም ይህ በራሱ የሚፈጥረው ችግር አለ በዚህ መልክ የሚቋቋሙ ስብስቦች ብዙውን ጊዜ አመራሮቹን ከሁለቱም ቦታዎች ስለሚያደርጉ በፖለቲካም ሆነ በድርጅት ጉዳዮች ዙሪያ በአካል ተገናኝተው ሰፊ ውይይቶች ማድረግ አይችሉም ስለዚህ በአገር ውስጥ ያለው የአመራር አካል በራሱ የሚወስዳቸው እርምጃዎች በውጭ አገር ላሉት የማይጥም ሲሆኑ በሌላ በኩል ደግሞ በአገር ውስጥ ያሉት ድርጅቶች ለገንዘብ ምንጭነት በአብዛኛው የሚጠቀሙት ከውጭ አገር ከሚገኙት ድርጅቶችና ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎቻቸው መሆኑ በሁለቱ ጾር ብርፃኑ ነጋ ኃይሎች መካከል ጠንካራ መተማመን ሊፈጥር እንዳልቻለ ይታየኛል ከዚህም በተጨማሪ በአገር ውስጥ ያሉት ድርጅቶች ራሳቸው በአብዛኛው በዘውግ የታጠሩ ስለሆኑ በውስጣቸው ያለው የእርስ በርስ መተማመን ጠገካራ አይደለም በዚህና በሌሎችም ተያያዥ ምክንያቶች እስከ ምርጫ መዳረሻ ድረስ በተለያዩ ኃይሎች የተሞከሩት የማሰባሰብ ጥረቶች አንድም ፍሬ ሳያስገኙ ቀርተዋል ስለዚህም በአገሪቱ የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደ ድርጅት ጠንከር ብለው ኢህአዴግን ለመፈታተን የሚያስችል አቅም ሳያጎለብቱ ቀርተዋል በዚሁ ልክ ግን የኢህአዴግ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ድክመቶች እየጎሉ ኅብረተሰቡ በሰላማዊ መንገድ የሚያታግለው ሁነኛ ኃይል ባለማግኘቱ በሚቆጭበት ጊዜ ነበር የ ምርጫ ላይ የተደረሰው ይህ ስሜት በተወሰነ ደረጃ መኖሩን ለማወቅ የ ምርጫ በተቃረበበት ወቅት ጥቂት በሌሎች ድርጅቶች ያልተደሰቱ ወጣቶች በምንም ምክንያት ይሁን በምን አንድ ዘውግ ዘለል የሆነ ኢዴፓ የሚባል ድርጅት መስርተው በአጭር ጊዜ ጠንካራ የሚባል እንቅስቃሴ ማድረግ መቻላቸው በኅብረተሰቡ ዘንድ ጥሩ አመራር መስጠት የሚችል ጠንካራ ድርጅት ቢፈጠር ለእንዲህ ዓይነት ድርጅት የፖለቲካ ድጋፍ ለመስጠት የሚፈልግ የኅብረተሰብ ኃይል እንደነበር የሚያመላክት ነው ይህንን በይበልጥ ግልጽ የሚያደርገውና የድርጅቶቹም መተባበር ማጣት ለስኬት ማጣታቸው ምክንያት መሆኑን የሚያሳየው በአዲስ አበባ የ የምርጫ ውጤት ነው እንደሚታወቀው በጊዜው የተቃዋሚ ድርጅቶች ተባብረው በምርጫው እንዲሳተፉ ብዙ ጥሪዎች ይቀርቡላቸው ነበር በተለይ በአዲስ አበባ ለኢህአዴግ አንድ እጩ በተቀናቃኝነት የሚቀርቡት ብዙ የተቃዋሚ እጩዎች የመራጩን ድምጽ በመከፋፈል ኢህአዴግን እንዲመረጥ ይረዱታል የሚል ፍርሐት ነበር እንደተፈራውም ለእያንዳንዱ የኢህአዴግ ተወዳዳሪ ብዙ የተቃዋሚ ድርጅትና የግል ተወዳዳሪዎች ቀርበው ነበር በውጤቱም ከሁለት ወረዳዎች በስተቀር በተቀሩት ወረዳዎች ኢህአዴግ አሸንፏል ከምርጫው በኋላ የነበረውን የመራጮች ድምጽ ብዛት ተከታትዬ በጊዜው በአንድ ስብሰባ ላይ እንዳቀረብኩት ለእያንዳንዱ የኢህአዴግ ተወዳዳሪ አንድ ተፎካካሪ ቀርቦለት ቢሆን ኖሮ ከአንድ ወረዳ በስተቀር በተቀሩት ወረዳዎች የተቃዋሚዎች ድምር ድምጽ ከኢህአዴግ ተወዳዳሪዎች ድምጽ ይበልጥ ነበር እስከምርጫ ድረስ ጠንካራ ተቃዋሚ ድርጅት መኖር ያልቻለው የነዓነት ጎህ ሲቀድ ግን በተቃዋሚ ድርጅቶች በራሳቸው ውስጥ በነበረው ድክመት ብቻ አልነበረም እንደሚታወቀው የተቃውሞው ፖለቲካ ወክባ የሌለበት የሰሳም ፖለቲካ አልነበረም በዚህም ምክንያት ወደ ፖለቲካው የገቡት ከሌላው ይልቅ ትንሽ ደፈር የሚለሌነት ወይም ደግሞ የበለጠ ቁጭትና ብሶት ያለባቸው ሰዎች ነበሩ ድፍረት መኖር ብቻውን ደግሞ ብቃትን አያመለክትም ለተቃውሞው ፖሰቲካ ደካማነት ምናልባትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ የነበረው የአገሪቱ ልሂቅ ከፖለቲካው በፍጹም መሸሽ ነው ይህ በደርግ ሽብር ምክንያት አንገቱን ቀብሮ የነበረ ልሂቅ በተለይም የተማረው ማኅበረሰብ ኢህአዴግ ሲገባና ስለ ዴሞክራሲ አስፈላጊነትና ስለ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መፈጠር ሲያወራ ትንሽ ቀና ብሎ በቀጥታ ፖለቲካው ውስጥ ባይገባም እንኳን ፖለቲካውን በአመክንዮ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን በስፋት በውይይትና በጽሑፍ ይሳተፋል ተብሉ ተጠብቆ ነበር ኢህአዴግ አዲስ አበባን እንደተቆጣጠረና ከዚያ በኋላ በነበሩት ጥቂት ወራት ይህ አዝማሚያ ታይቶ ነበር የኢህአዴግ መሪዎች ለምሁራን በጎ አስተያየት አላቸው ብቻ ሳይሆን እነሱ ራሳቸው ምሁራን እንደሆነ ለማሳየትም በተለይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየተመላለሱ ከመምህራን ጋር ምሁራዊ» ክርክር ይገጥሙ ነበር በእነኝህም ውይይቶች ብዙ ምሁራንን ከጎናቸው ማሰለፍ እንደሚችሉ እምነቱ ነበራቸው በዚህም ምክንያት ዩኒቨርስቲዎች የነፃ ፃሳብ መንሸራሸሪያ ቦታዎች እንዲሆኑ የሚፈቅዱም መስለው ነበር በዚህን ጊዜም የቀድሞ የአስተማሪዎች ማኅበር እንደገና ተቋቁሞ የማኅበሩም መጽሔት ተመስርቶ በአገሪቱ የፖለቲካ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ምሁራዊ ሊባል የሚችሉ የውይይቶች ሐሳቦችና ጽሁፎች መውጣት ጀምረው ነበር በዩኒቨርስቲው ውስጥ ከሚወጡ ጽሑፎችም ባሻገር በጊዜው በስፋት በተጀመሩት ነፃ ጋዜጦችና መጽሔቶች ለተራው ሕዝብ ፍጆታ የሚውሉ የተለያዩ ጽሑፎችና ቃለ መጠይቆች በአገሪቱ ታዋቂ ምሁራን ይወጡ ነበር ይህ እንቅስቃሴ ግን እንደተጠበቀው በዘላቂነት ሊቆይ አልቻለም ምሁራንን ለማወያየት የሞከሩት የኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎች የገጠማቸው ሙግት ቀላል አልነበረም ከታሪክ ጀምሮ እስከ ጊዜው ፖለቲካ ድረስ የገጠማቸው ክርክሮች እነሱ ለካድሬዎች በቀላሉ ትክክለኛነቱን ያሳመኗቸው ጉዳዮች ከጠበቁት በላይ የፍሬ ነገር ውይይት እንደሚያስነሳ ሲገነዘቡና ይህም ከተስፋፋ በጉልበት ያገኙት የመሰላቸውን «የርዕዮተ ዓለም የበላይነት» እንደሚፈታተነው ሲያውቁ ጾር ብርዛኑ ነጋ በተካኑበት የፍረጃ ስልት መሠረት የዩኒቨርስቲውን ምሁራን በጅምላ «ትምክህተኛነት የተጠናወታቸው ኢዲሞክራሲያዊ ኃይሎች» አድርገው ፈረጂቸው ሴሎቹን የደርግ ቅሪት እያሉ ተሰላቁባቸው በዚህም አላቆሙም ከዩኒቨርስቲው ውስጥ በመለመሏቸው ጥቂት አድርባዮች ጠቋሚነት በጣም ይቃወሙናል የሚሏቸውን መምህራን መርጠው ብዙ ዓመታት ከሰሩበት የመምህርነት ሥራ አባረሯቸው በአጭር ጊዜም የዩኒቨርስቲው የመምህራን ማኅበር እንደገና ፈረሰ ኢህአዴግም ከዚህ ልምዱ የኅብረተሰቡን ተገዢነት ለማግኘት የግድ ጉልበት መጠቀም እንደሴለበት አንደ ደርግ ይልቁንም የንዑስ ከበርቴውን እሽታ ለማግኘት ፍቱን መሣሪያው በኢኮኖሚው በኑሮው ላይ መምጣት መሆኑን በመረዳት ይህንን ስልት በሌላው ማኅበረሰብ ዘንድ በሰፊው ተጠቀመበት ይህም በእርግም ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ ለኢኮኖሚ ሕይወቱ የሚራራውን በኅብረተሰቡ ውስጥ የተሻለ የኢኮኖሚም ሆነ የእውቀት አቅም የነበረውን ኃይል ልሂቅ ከፖለቲካው ቀጥታ ተሳታፊነት ብቻ ሳይሆን ከውይይቱም አራቀው የልሂቁ ከጨዋታው በአብዛኛው መውጣት ለተቃውሞ ፖለቲካው መዳከም በሁለት ወሳኝ መልኩ አስተዋጽዖ አድርጓል የሚል እምነት አለኝ የመጀመሪያው የተቃውሞ ኃይሉን በአመራር ደረጃም ሆነ በከፍተኛ ካድሬነት ደረጃ ሊመራ የሚችለውን የሰው ኃይል ስብስብ ፆዖዐዐስፅ ክፉኛ ቀንሶታል ይህ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ለተማረ ሰው ከፍተኛ አክብሮት ባለበት አገር የመሪዎች ማንነት የፖለቲካ እንቅስቃሴውን በመቀላቀልም ሆነ በመደገፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ይኖረዋል ይህ ጉዳይ በጊዜው የነበሩ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በደንብ የተረዱት ግን ብዙ ቢሞክሩም ያልተሳካላቸው ጉዳይ ነበር የፖለቲካ ድርጅቶች በኅብረተሰቡ ዘንድ ታዋቂነት ወይም ተሰሚነት አሏቸው የሚሏቸውን ሰዎች እየዞሩ መለመንና ማስለመን የተለመደ ሥራ ነበር ምናልባት በዚህ ሂደት ወደ መጨረሻ ላይ ባደረገው ከፍተኛ ጥራት ትንሽም ተሳክቶለት የነበረው ከ ምርጫ በኋላ እንዲህ ዓይነት መሪዎችን ይዞ ብቅ ያለው አዲስ ሕብረብሄራዊ ድርጅት ኢዴፓ ነበር ከዚያም ቀጥሎ በዚህ ዙርያ ትንሽ የተሳካለት ሩ ዔዜሀ ላይ ጥቃዌ ያሰፈሰሳጋሳ። በእርግጥ ዓይን ያወጡ የመብት ረገጣዎች ሲታዩ እነሱን ማውገዝ ይቻላል ብዙ ጊዜ ይወገዛሉም ግን አንድ ተግባር ወይም ጥቂት ምሳሌዎች አጠቃላይ ሂደትን ኣያመለክቱም በተለይ በአሁኑ ዓለማችን ዓይን ያወጡ አምባነገኖች እንኳን በዴሞክራሲ ስም በሚምሉበትና በሚገዘቱበት ጊዜ በመንግሥቶች የሚወሰዱ የተለያዩ እርምጃዎች ተደምረው ዴሞክራሲያዊ ሂደቱን የሚቀለብሱ ወይም ያ መንግሥት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባት የማይችል ነው ብሎ ለመደምደም በተለይ ለፈረንጆቹ ይከብዳቸዋል በተለይ ደግሞ ለዚያ መንግሥት ያለው አማራጭ ምን መሆኑ በግልጽ በማይታወቅበት ሁኔታ ላለው መንግሥት ተጨማሪ እድሎችን ለመስጠት ይፈቅዳሉ በተለይ ለአገሮቹ ለምሳሌ በአፍሪካ ያላቸው ግምት መጀመሪያውኑም ዝቅተኛ ከሆነ በቀላሉ በትንንሽ ዴሞክራሲ መሰል እርምጃዎች ሊታለሉ ይችላሉ በአንድ ወቅት የአሜሪካ መሪዎች የሩዋዳውን ካጋሜ የኤርትራውን ኢሳያስ የኡጋንዳው ሙሴቬኒና የኛኑ አቶ መለስን አፍሪካን ወደ እድገትና ዴሞክራሲ ጎዳና የሚወስዱት የአዲስ ትውልድ መሪዎች ብለው ሲያሞኳጂቸው እንደነበረ የተመለከተ ሰዎቹ ለአፍሪካ አገሮች ያላቸውን ዝቅተኛ አስተያየት መገመት አያቅተውም ይህም ሆኖ ግን የነባነት ገህ ሲቀድ ከህኮህኮህመ ደ ፎፎምመመይዎይሬዎሬወጃልጳም በእንዲህ ዓይነት ግምታቸው ሁልጊዜም ይዘልቃሉ ማሰት አይደለም ከዴሞክራሲ ይልቅ ሥልጣናቸውን የሚወዱ መሪዎች ባሉበት የእነኝህ መሪዎች የማታለል ሂደት የፈረንጆቹም የመታለል አንዳንዴ አውቆ ጉዞ ዘላቂ አይሆንም ችግሮች እየተወሳሰቡ ሲሄዱ የተጠበቁ ውጤቶች አልገኝ ሲሉ ቃል የተገቡ ማሻሻያዎች በተግባር መዋል ሲያቅታቸው ወዘተ ለጋሽ አገሮቹም ጥያቄዎቻቸው እየበዙ ከወሬ ይልቅ ተግባርን መለኪያ እያደረጉ ይሄዳሉ በኢትዮጵያም የሆነው ይህ ነው የውጭ አገር መንግሥታትና ዲፕሎማቶች የኢህአዴግን መንግሥት በጣም አዎንታዊ በሆነ ስሜት ነው በመጀመሪያ የተቀበሉት የኢህአዴግ መንግሥት የነበረውን የግራ ርፅዮተ ዓለም ቢያውቁም ከተቀየረው የዓለም ሁኔታ ጋር አብሮ ተለውጧል ወይም በሂደት ይቀየራል ከሚሜል ለአገሪቱ እድገት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለአገር ውስጥ ሰላም ከዚያም አልፎ ለአካባቢው መረጋጋት አዎንታዊ ሚና መጫወት የሚችል ኃይል አድርገው ወስደውታል በተለይ የኢህአዴግ መሪ የሆኑት አቶ መለስ የዴሞክራሲንና የነፃ ገበያን ዘይቤ በቶሎ በመረዳትና ፈረንጆቹ መስማት የሚፈልጉትን እነሱ ከሚሉትም በተሻለ በማቅረብ ችሎታቸው ሊያነጋግሯቸው የቀረቡትን ፈረንጆች ሁሉ ለመማረክ እንደቻሉ በፈረንጆቹ ሁሉ ይመሰከርላቸዋል የመንግሥት መሪ ደግሞ ዓይን ያወጣ ውሸት አይዋሽም ብለው ከልብ ለሚያምኑት ፈረንጆች የአቶ መለስን አቀራረብ የማስመሰል ሳይሆን ከልባቸው የሚያምኑበት ነው ብለው መቀበልፍያለውና ፈረንጆቹ አይከብዳቸውም ለዚህም ነው ለአቶ መለስ ያላቸው የነበራቸው አክብሮት በኢትዮጵያ ደረጃ የተወሰኑ መሪ አድርገው ሳይሆን ለሌሎችም የአፍሪካ መሪዎች እንደምሳሌነት ይወስዷቸው የነበረው በዚህም አክብሮት ምክንያት ኢህአዴግ በመጀመሪያዎቹ የሥልጣን ዘመኑ በወሰዳቸው አዎንታዊ እርምጃዎች ከፍተኛ የገንዘብና የዲፕሎማሲ ድጋፍ ችረውታል ይህ ሰፊ ድጋፍ ግን ልክ ኢትዮጵያውያን ለኢህአዴግ የመጀመሪያ ዘመን ይሰጡት እንደነበረውና እያደር እየመነመነ እንደመጣው ድጋፍ ቀስ በቀስ ጥያቄ ውስጥ እየገባ ሄደ በአገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች የተከሰቱት ግጭቶችና የሰብዓዊ መብት ጥስቶች ለውጭው ዓለም እያደር እንዳላየ የሚያልፉት አነስተኛ ጉዳይ ሊሆን አልቻለም በተሰይ እነኝህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በሪፖርት መልክ እየተዘጋጁ በዘመኑ የኢንተርኔት ቴክኖሎጂ በሰፊው ጾር ብርፃኑ ነጋ መሰራጨታቸው ቢያንስ ምንም እርምጃ አልወሰዱም እንዳይባል ያህል በግልጽ ከማውገዝ አንስቶ በገለልተኛ ወገኖች ይጣሩ የሚሉ ጥሪዎችን እስከማስተላለፍ አድርሷቸዋል የተለያዩ የዓለም አቀፍ የሲቪክ ማኅበረሰብ ተቋማትና የሠራተኛ ድርጅቶችም በኢትዮጵያ የሚታየውን በነፃ የመደራጀት መብት አለመከበርና ሌሎች የሲቪክ መብቶች ረገጣ ለማውገዝ በመንግሥቶቻቸው ላይ ጫና ማሳረፋቸው አልቀረም ከዚህ በተጨማሪም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ይፈጠራሉ የተባሉና በለጋሽ ሀገሮች ድጋፍ ይቋቋማሉ የተባሉ ተቋሞች ሆን ተብሎ አለመቋቋምና መጠናከር አለባቸው የሚባሉት እያደር መዳከም የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ኮሚሽንና የእንባ ጠባቂ ተቋማት በመጀመሪያው የፍትሕ ሥርዓቱ በሁለተኛው የሚመደቡ የተቋማት ምሳሌዎች ናቸው በእርዳታ ሰጪዎች ዘንድ የኢሕአዴግ መንግሥት ለዴሞክራሲ ያለውን ወገንተኛነት ጥያቄ ውስጥ ይከተው ገባ የተቋማት ጥንካሬ ለዴሞክራሲ ግንባታ ወሳኝ ነው በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ለመገንባት አንዱ ችግር የተቋማት መዳከም ነው ብሎ ለሚያምን የውጭ ታዛቢ መንግሥት ተቋማትን ሆን ብሎ ሲያዳክም አንድን የፖለቲካ ባላንጣ በእስር ለማቆየት ሲባል ብቻ ሕገመንግሥትን የሚሽር ሕግ በአንድ ቀን በፓርላማ ሲወጣ ለሚያይ ታዛቢ ሁኔታዎች እየተሻሻሉ እየሄዱ እንዳልሆነ ለመገመት በጣም የሚከብድ አልነበረም በአገር ውስጥ ላሉ የውጭ ዲፕሉማቶች በኢህአዴግ ላይ እየተነሳ ያለውን ተቃውሞና ሕዝብ እያደር ኢህአዴግን እየሸሸ መሄዱን ቀስ በቀስ የተገነዘቡት እውነት ነው ከዚያም በተጨማሪ ግን በእርዳታ ሰጪዎች በአጠቃላይና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት በተለይ የጠበቋቸውን የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በተግባር አለማዋል ወይም በጣም መዘግየት በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ለምሳሌ በመሬት ፖሊሲ በፋይናንስ ፖሊሲ በቴሌኮም ለግል ይዞታ መፈቀድ ወዘተ የኢህአዴግ መንግሥት እያሳየ ያለው ገታራ የግራ ርዕዮቱን የሚያንፀባርቅ አቋም ለገበያ ኢኮኖሚ ምስረታ ያለውን ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ ሳያስገቡት አልቀረም «የመጀመሪያዎቹ ትውልድ» የማክሮ ዶ በዚህ ዙሪያ ፀሃፈፀ ይጋምዜጎውና ይላነዎሳው ፇጭዶቻና ይጎዕያዩዊ መቋወም ረፇጣሥቻ ይጠፇታ በቱሳይ ያላሜሪነሳው የውጭ ዳይ መሥሪዖ ቤጉ በየዓመሩ በሚያወጣው ሪፖርቶ የሏሊገዮሞቶያን ያዕበዓዊ መብታ ሪስርድ በመሰስታ ሰሉጠቃይና በጋዜጠሾቻ ጎይ የሚደርታን ወነባዎሥቻ በሃመለሰሦ ዝ ሂቃቻ ፇረም የነፃነት ገዝ ሲቀድ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ከሆኑ በኋላ በተለይ በአፍሪካ የታየው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የተጠበቀውን ያህል ባለመሆኑ ምክንያት ለጋሽ አገሮች «በሁለተኛ ትውልድ ማሻሻያዎች» እስከዚያ ወቅት ድረስ ከኢኮኖሚ ጉዳዮች ጋር አያይዘው የማያይዋቸውን የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች የማሻሻያዎቹ አካል አደረጓቸው ይህም የለጋሽ አገር ዲፕሎማቶች እነኘህን ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በበለጠ አትኩሮት እንዲያዩዋቸውም አድርጓቸዋል ከዚህ ጋር በተያያዘም ብዙ የለጋሽ አገሮች በአገሪቱ ከሚገች የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ከበፊቱ የጠነከረ ግንኙነት እየፈጠሩ ሲፄዱ ያላቸው የመረጃ ፍሰትም ከመንግሥት ከሚያገኘ ት እንዲሰፋ የአገሪቱን ሁኔታም በተሻለ መልክ እንዲያውቁ እድል ሰጥቷቸዋል በኢትዮጵያ የሚገኙ የለጋሽ አገር ዲፕሎማቶች በአካባቢው ባሉት አዲሶቹ ተራማጅ መሪዎች» ላይ ያላቸውን አዎንታዊ ስሜት የበለጠ ያናጋው ደግሞ የኢትዮጵያና የኤርትራ ግጭት ነው ይህ ደግሞ በእነኘ ህ መሪዎች ብልህነት ምክንያት በአካባቢው ሰላም ሰፍኗል ብለው የገመቱትንና በተለይ ደግሞ እነፒህን መሪዎችና አገሮች ለዓለም አቀፍ ፀረሽብርተኝነት ትግል የተሰለፉ የመረጋጋት ኃይሎች አድርገው የወሰዲቸው መንግሥቶች በግጭቱ በፍጹም ደስተኞች አልነበሩም የግጭቱን እውነተኛ ምክንያት በግልጽ የማያቀርቡት የሁለቱ አገር መሪዎች ደግሞ በኦፊሴል ምክንያት ነው ብለው የሚጋጩበት ጉዳይ በኣምክንዮ ለሚያምኑ የውጭ ተመልካቾች ግራ ሳያጋባቸው አልቀረም ለማንኛ ውም ግን በዚህ ወቅት ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ ለጋሽ አገሮች ለኢትዮጵያ እርዳታቸውን ሊያቋርጡ እንደሚችሉ የገለጡትና የተወሰኑ አገሮችም በተለይ ቀጥታ የባጀት ድጎማቸውን ለጊዜው ያቆሙት ይህን ግጭት በሰላማዊ መንገድ መፍታት አቅቷቸው በጣም አስከፊ ወደሆነ ጦርነት ሲቀየርና የብዙ ስዎችን ሕይወት ሲያጠፋ ሲያዩ ግን የሕዝብ ተጠያቂነት የሌለባቸው መንግሥታት ምን ያሀል ለጦርነትና ለጉልበት የቀረቡ እንደሆኑና እንዲህ ዓይነት መንግሥታት ሰላም ያመጣሉ የሚለው እምነት የተሳሳተ እንደሆነ ተገነዘቡ ይህም በራሱ በኢትዮጵያ የእውነተኛ ዴሞክራሲን አስፈላጊነት የበለጠ ሳይገልጥላቸው አልቀረም ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት የኤርትራ ጦርነት በሚካሄድበት ጊዜ የአገሪቱ ሁለተኛ ምርጫ እየተቃረበ ነበር በዚህ የ ምርጫ የለጋሽ አገሮች ተወካዮች በተወሰኑ ቦታዎች በታዛቢነት ተገኝተው ነበር ከዚያም ጾር ብርፃኑ ነጋ በተጨማሪ ግን አጠቃላይ «የዲሞክራሲ ሥርዓቱን አካሄድ ቀረብ ብሎ ለመከታተል እድል አግኝተው ነበር በዚህን ጊዜ ባዩትም ብዙ ደስተኞች አልነበሩም ምርጫው ይህ ነው የሚባል ፉክክር ያልነበረበት መሆኑ ትንሽ ፉክክር በነበረባቸው ቦታዎችም የመንግሥት ታጣቂዎች ሲፈጽሙ የነበረውን የመብት ረገጣ በዓይናቸው ያዩት ስለነበር ከላይ ከጠቀስኳቸው ሌሎች ችግሮች ጋር ተደራርቦ በኢህአዴግ መንግሥት ላይ የነበራቸውን ፍፁም አዎንታዊ አመለካከት ቢያንስ ወደ ከፍተኛ ጥርጣሬ ሲያልፍ ደግሞ ወደ ግልፅ ተቃውሞ ቀየረው ብዙዎች የለጋሽ አገር ዲፕሎማቶች የኢትዮጵያ ሁኔታ በዚህ ሊቀጥል እንደማይችል በአገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ጥያቄው ከምር መወሰድ እንዳለበት አመኑ በጊዜው የለጋሽ አገሮች ቡድን በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደቱን ለማጠናከር መወሰድ ስላለባቸው አርምጃዎች በአማካሪዎች እንዲጠና አድርጎ ለሚቀጥለው ግንቦት ኻ ምርጫ ዝግጆት የረጅም ጊዜ ሰሌዳ አወጣ የሚቀጥሉት ዓመታት ከመንግሥት ጋር የሚያደርጋቸው የእርዳታ ስምምነቶችና ድርድሮችም በእነዚህ የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ላይ በሚገኝ አመርቂ ውጤት ላይ እንዲመሠረትም ተስማማ ይህ ጊዜ ደግሞ አንጃውን ያሸነፈው የአቶ መለስ ቡድን ለዴሞክራሲ ግንባታ እንቅፋት የሆኑትን አንስቻለሁ እያለ አይደርስ መስሎት የሚፎክርበት ጊዜ ስለነበር መንግሥትም መጪውን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ ብዙ ተቃውሞ አላሰማም ነበር የበለጠ ትኩረቱ በኤርትራ ምክንያት የተቋረጠበትን የገንዘብ ድጋፍ መልሶ ማግኘት በድርጅቱ ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል ከቁጥጥር እንዳይወጣ ማብረድ አንዲያውም የተፈጠረውን የውስጥ ቀውስ ለአሸናፊው ኃይል የዴሞክራሲያዊነትን ካባ እንዲከናነብ አድርጎ በነበረው በአመነው ፀረዴምሞክራሲያዊነት ምክንያት የሸሹ ኃይሎች ካሉ ወይም «በአዲሱ» ማንነቱ የሚማረኩ ኃይሎች ካሉ አነሱን ማሰባሰብ ነበር በዚህም ምክንያት ይመስላል አሸናፊው ጠቅላይ ሚኒስትር በአገሮች ታሪክ ምናልባት የመጀመሪያው ሊባል የሚችል ረጅም ቀናት የፈጀ «ምሁራዊ» ውይይት ከዩኒቨርስቲ መምህራን ጋር ያደረጉት በእርግጥም ብዙ የዋህ «ምሁራን» ይህን ውይይት ወደ ዴሞክራሲ የሚያስኬድ ምልክት አድርገው ሳያዩት አልቀሩም ለማጠቃለል ወደ ግንቦት ምርጫ ሲመጣ ብዙ ነገሮች የነፃነት ገህ ሲቀድ ተደማምረው ምርጫው ከበፊቱ የተለየ ሊሆን እንደሚችል ምልክቶች እየታዩ ነበር ኢህአዴግ በአገር ውስጥ የደረሰበትን ከፍተኛ ተቃውሞ ለማለዘብና ዴሞክራሲያዊነቱን እየተጠራጠሩ የነበሩትን ለጋሽ አገሮች «አሁን ታድሻለሁ ከአሁን በኋላ ማስተዳደር የምፈልገው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ነው» በሚል ጥርጣሬያቸውን ለማሳረፍ ብዙ የማሻሻያ እርምጃዎችን ለመውሰድ ቃል የገባበት ወቅት ሆነ ለጋሽ አገሮችም እንደ ቀድሞው እያዩ እንዳላዩ ለማለፍ እንደማይችሉና የወደፊት ትብብራቸው መንግሥት ከሚወስዳቸው ተጨባጭ ዴሞክራሲያዊ ማሻሻያዎች ዐፀዘገ ርየቋሸር ጸፀያልገ ጋር እንደሚያያይዙት ግልጽ አደረጉ ብዙው የአገሪቱ ሕዝብም የጠሬ ዴሞክራሲ ሰልችቶት እውነተኛ ዴሞክራሲ የናፈቀበት ተቀናቃኝ ድርጅቶችም እርስ በእርስ በመናቆር የተቃውሞ እንቅስቃሴውን ማዳከሙን አቁመው የተባበረና የተጠናከረ አመራር እንዲሰጡ የሕዝብ ግፊት በበዛበት ሁኔታ ነው ለግንቦት ምርጫ ዝግጅት የተጀመረው በሚቀጥሉት ሁለት ምዕራፎች የግንቦት ምርጫን በተመለከተ ኢህአዴግና ተቃዋሚው ኃይል የነበረውን ስሌትና ያደረገውን ዝግጅት እንመለከታለን ጾር ብርፃኑ ነጋ የኢህአዴግ የአልሸነፍም ባይነት የተሳሳተው ስሌት ይ በዐነዌኀፀ ርወሀፀፀሪ ጽእ ዐ ዐፀፀ ክሀሀ ፀሃያ ሀበዐፀያፎፍሀቋ ዐርያያ ዕዐያ ህሀ ለፀር ያሀ ሕፀ ፀ ዕፀዐይ «አምባገነኖች ስለ ራሳቸው ባላቸው የተሳሳተ ግምት የተነሳ ራሳቸውን ለማሞኘት ያላቸውን ከፍተኛ ብቃት ማንም አሳንሶ ሊያየው አይገባም» ጎፊዕ ራፅሰ «ኦሰሳሰቀ መሪዎቻ ናሻ እ ት ግንቦት ምርጫ ጋር ተያይዞ የመጣውን የሕዝብ የነፃነት ፍላጎትና ስሜት ኢህአዴግ በጉልበት ለማፈን ከጥቅምት ጀምሮ እየወሰደ ያለውን ዓይን ያወጣ የኃይል እርምጃ በአንድ በኩልና ሕዝቡ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ከምርጫው ጀምሮ ያገኘውን አንፃራዊ ነፃነት አላስረክብም ተመልሼም የፍርፃት ሕይወት አልኖርም ብሎ የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ትግልና በዚህም ምክንያት በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረውን አለመረጋጋት የሚያዩ ታዛቢዎች በተደጋጋሚ የሚጠይቁት ጥያቄ ኢህአዴግ በህዝብ ድምፅ ለመገዛት ቀድሞውንም ካልወሰነ ለምን እንከን የለሽ ምርጫ አደርጋለሁ ብሎ እዚህ ሁሉ ጣጣ ውስጥ ገባ። እነዚህንና መሰል ምክንያቶችን በማቅረብ ለእውነተኛ ሰላም የበለጠ የሚጠቅመው መገነጣጠል ሳይሆን አንድነት እንደሆነ የኢትዮጵያዊነት ስሜት የለም ከዘውግ በስተቀር የሚለው አመለካከት ምን ያህል የልጅ ጨዋታ እንደሆነ በኤርትራ ጦርነት ጊዜ የታየ መሆኑንና የኢትዮጵያዊነት ስሜት ከኢትዮጵያዊ ዜግነት መብቶች ጋር አብሮ ከተጓዘ የነባነት ገህ ሲቀደ የሚያሳፍር ሳይሆን የሰለምና የጥንካሬ መሠረት እንደሆነ ማስረገጥ ይገባል የሚል ጽኑ እምነት ነበር ስለዚህም ከእነዚህ ውይይቶች ዘልቆ የወጣው የአገሪቱ ፖለቲካ ዘላቂ መፍትፄ የተባለው በአጭሩ ሲቀመጥ የሚሆነው «ነፃነትና አንድነት» ሂከፀዘዘዐ ሀክከ ወይም ዴሞክራሲና አንድነት የሚል ይሆናል በዚህም የእውነተኛ ዴሞክራሲንና የአብሮነትን ሁለት ጠንካራ እሴቶች በኅብረተሰቡ ውስጥ ማስረጽ ይቻላል ብለን አምነናል ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት በአገራችን ብዙ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ችግሮችም አሉ ግን እነዚህን ችግሮች በቅጡ ለመፍታት የሕዝቡ ነዛና ቀጥተኛ ተሳታፊነት ያስፈልጋል ይህ ደግሞ ሊሆን የሚችለው እውነተኛ ነፃነት ያለበት ከፍርፃት የተላቀቀ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲኖር ብቻ ነው ስለዚህም የምርጫ የክርክር እምብርት ሊሆን የሚገባው የዚህ ነፃ ማኅበረሰብ ዞዖፀፀ የመፍጠር ወሳኝ የፖለቲካ ጥያቄ ነው የምርጫው ትኩረት በሊሉች በሁለተኛ ደረጃ ጥያቄዎች ዙሪያ እንዳያጠነጥን ጥንቃቄ መወሰድ እንዳለበትም አምነናል ለ ሰላማዊ ትግል ምርጫው አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑ በእነሂህ ውይይቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶት የተነሳው ሌላው ጉዳይ የአገራችን የፖለቲካ ትግል ምን መልክ መያዝ አለበት የሚለው ጉዳይ ነው ይህ ጥያቄ አስፈላጊ የሚሆነው በአገሪቱ የተለያየ የትግል ስልት የሚከተሉ የተቃውሞ የፖለቲካ ድርጅቶች ስላሉ ብቻ አልነረም ከላይ በተራ ቁጥር «ሀ» ከተነሳው የፖለቲካ አመለካከት ጋር በቀጥታ የተገናኘ ስለሆነ ነው በዚህ ውይይት ውስጥ የተሳተፍንና በኋላም ቀስተ ደመናን የመሠረትን ሰዎች በሙሉ ነፃነታችንን የምንወደውን ያህል ሰላምንም የምንወድ ግለሰቦች ብቻም አልነበርንም በግልጽ እንደሚታወቀው ለምሳሌ ፕሮፌሰር መስፍን የጠመንጃ ትግልን አምርሮ በመቃወም ከብዙ ተቃዋሚ ኃይሎች ከፍተኛ ትችት ይደርስበት ነበር ከምንም በላይ ግን አመለካከታችንን የቀረፀው የጉልበት መንገድ የምናስበውን የተደላደለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመፍጠር እንቅፋት ይሆናል ከሜል እምነት ነው ለዚህም ሁለቱ መሠረታዊ መከራከሪያዎች ይቀርባሉ የመጀመሪያው በአስተሳሰብ ደረጃ የምንፈልገውን ውጤት ለማምጣት ምንም ዓይነት መሳሪያ መጠቀም ተገቢ ነው ወይም ውጤቱ ትክክለኛ ከሆነ ውጤቱን ለማምጣት የተጠቀምክበት መሣሪያ ምንም ይሁን ተቀባይነት አለው የሚለው አስተሳሰብ መሠረታዊ ስህተት አለው የሚል ጾር ብርፃኑ ነጋ ነው ይህ አስተሳሰብ ብዙውን ጊዜ የተባለውን ውጤት ራሱን ሲያበላሸው ይታያል ወደ ነፃነት ለመሄድ በሚደረግ የአመጽ የትጥቅ እንቅስቃሴ የሰዎችን ነፃነት እየገፈፉ በሰዎች ላይ ግፍ እየሰሩ ጠላት ናቸው ከሚል መሄድ የሚፈጥረው ኢዴሞክራሲያዊ ባህል ሥልጣን ከተያዘ በኋላ እየተደላደለ ፄዶ ነፃነት የሚለውን ዓላማ ደብዛውን እንደሚያጠፋው ከብዙ አገሮች ልምድ ያየነው ነው «ለዓላማ» ተብሎ በአንድ ሰው ላይም ግፍ መሥራት ከተጀመረ ማቆሚያው የት ላይ እንደሚሆን ለመወሰንም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው የጠመንጃ ትግል በውስጡ በኃይል ስለሚያምን በትግሉ ሂደት እንዲህ ዓይነት ኢፍትሃዊና ኢዴሞክራሲያዊ አርምጃዎች ለመውሰድ ያለው እድል በጣም ሰፊ ነው ከዚህ በተጨማሪም በጠመንጃ ትግል ሥልጣን ላይ የሚወጣ ኃይል ዓላማው ምንም ሆነ ምን የጠመንጃ የወታደር ባህል አደረጃጀት አስተሳሰብ ይዞ ነው የሚመጣው ስለዚህም በእንዲህ ዓይነት አስተሳሰብና ባሕል ሥልጣን የያዘ ኃይል የተነሳበትን ዓላማ በቀላሉ መርሳት እንደሚችል ለማወቅ የብዙ አገሮች ምሳሌዎች መጥቀስ አያስፈልገንም ይህን ልምድ እዚሁ እየኖርነው ነው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በመሠረቱ ሰላማዊ ነው የሚያምነውም የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይትና በጦፈ ክርክር ካለፈም በድርድር መፍታት ይቻላል ብሎ ነው ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብና እምነት ያላቸው ነፃነታቸውን አጥብቀው የሚወዱ ሰዎች አንዱ መለያቸው የሌላውንም ነፃነትና መብት ማክበር ነው የፖለቲካ ባላንጣቸውን መግጠም የሚሹት በሰላም ሜዳ በዛሳብ ክርክርና በአምክንዮ መስፈርት ነው እንዲህ ዓይነት እምነት ያላቸው ሰዎች የሚወዱትን የነፃባነት ኑሮ ለማግኘት በሚያደርጉት ትግል የትግሉ ዓይነትና መንገድ እንዲሁም የትግሉ መሳሪያ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣሉ ከሰላማዊ መንገድ ውጪ የሚደረግ ትግል ከዋናው ግብ አንፃር ሊያደናቅፉት የሚችሉ የተቀበሩ ፈንጂዎች እንዳሉ ያውቃል ስለዚህም በምንም ዓይነት መንገድ ሌሎች አማራጮች በሙሉ ጥርቅም ብለው ተዘግተዋል ብለው ካልወሰኑና ያለው አማራጭ ዝም ብሎ መገዛትና ያለነፃነት መኖር ብቻ ነው የሚሉበት አማራጭ ላይ ካልደረሱ በቀር የጉልበት አማራጭን አይወስዱም ይህንን በሚመለከት የሰላማዊ ትግል አባት ነው ተብሎ ከሚታመትት ሰዎች አንዱ የሆነው ጋንዲ ይህንን በግልጽ አስቀምጦታል ጋንዲ «ለሰላማዊ መንገድ ያለውን ወገንተኛነት የሚፈታተን ነገር ቢኖር ምንም ሳያደርጉ ዝም ብሎ መቀመጥንና መገዛትን ብቻ ነው» ዝም ብሎ ከመገዛት ግን በጉልበትም ቢሆን መታገልን የነዛነት ገህ ሲቀደድ ይመርጣል በጋንዲ አመለካከት ሁሉም ቢሆን ሰላማዊ ትግል ይመርጣል ነገር ግን «በሰላማዊነት ሽፋን ዝም ብሎ ከመቀመጥ በጉልበት ማመጽ ይሻላል በተለይ ጉልበትን ለመጠቀም የሚችል አንጀት ካለን ወኔው ተሰልቦ ከተቀመጠ ምንጊዜም ግፍን በጉልበት የሚቋቋም ይመረጣል ጉልበትን መጠቀም የለመደን ሰው ወደ ሰላማዊ መንገድ የማምጣት አድል አለ ወኔው የተሰለበ ሰው ግን ምንም ተስፋ የለውም» ነበር ያለው ያለምንላት አንድነቷ የተጠበቀ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ዝም ብሎ በመቀመጥ እንደማትመጣ አናውቃለን ስለዚህም በሂደቱ ውስጥ በቀጥታ በመሳተፍ የራሳችንን አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለብን እናውቃለን ከዚያም በተጨማሪ ግን የምናደርገው ነገር ያሰብነውን ዓላማ መምታት የሚችለው በሰላማዊ ትግል መሆኑን እናውቃለን ለዚህም የምርጫ አንዱና ዋነኛው የመታገያ መሣሪያ መሆኑን በጥብቅ ተገንዝበናል ሥ ሠላማዊው መንገድ ብቸኛው ተመራጭ ነው በማለት ያመንበት ተጨባጭ ተግባራዊ ምክንያቶች ነበሩን ከዚህ ውስጥ ዋናው አገሪቱ ከበቂ በላይ ጦርነት የእርስ በርስ አይታለች ከአሁን በኋላ እንደገና የእርስ በርስ ጦርነት መሸከም አትችልም የሚለው ጽኑ እምነታችን ነበር ዓመት የደርግ ዘመን ያልተቋረጠ የአርስ በርስ ጦርነት ዘመን ነበር ለማሰት ይቻላል ይህ ጦርነት «ተጠናቅቆ በጠመንጃ ደርግን የታገሉት ኃይሎች ሥልጣን ይዘው ኤርትራ ተገንጥላ መገንጠሏም ሰላምን ያስገኛ ል ተብለን ብዙ ሳንቆይ ነው እንደገና በጣም አሳዛኝ ወደ ሆነ ጦርነት ውስጥ የገባነው በጠመንጃ ከሥልጣን ላይ የወጡ ኃይሎች ሰላምን ለማምጣት እንዴት ከባድ እንደሚሆንባቸው አይተናል ይህ ብቻም አይደለም ጦርነት ምን ያህል አጥፊ እንደሆነ የኅብረተሰብን አቅም አዎንታዊ ወደ ሇነ ግንባታ ሳይሆን ወደ ውድመት የሚወስድ እንደሆነ ከራሳችን የቅርብ ጊዜ ታሪክ ያየነው ነው ስለዚህም ከጠመንጃ አመፅ መንገድ ጠቃሚ ነገር ይመጣል ብሉ ለማሰብ አይቻልም ቢመጣም እንኳን ለዚያ የሚከፈለው ዋጋ በጣም ከፍተኛ ነው ብለን እናምናለን ይህ ብቻ ግን አይደለም የጠመንጃ አመጽ በተለይ የአመጹ የፖለቲካ ምክንያት ግልጽ ካልሆነና ማኅበረሰቡም ሌላ አማራጭ የለም ብሎ በሰፊው ማሀታመ ጋንዲ በበህፀበ ርከፀ ይ ላ ደጋቃዕው ፕለ በርዐበሀ ሃዕበ ህስ ቦ ዖክር ክርበዐየ ስ ሀነ ሃጽያክ ጾር ብርሃኑ ነጋ ካላመነ እንደ ትግል መሳሪያ ሰላምን ከሚወዱ የዴሞክራሲ ኃይሎች ይልቅ አመጽን ለለመዱ ኢዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የሚመች መሳሪያ እንደሆነ እምነታችን ነው እንደ ኢህአዴግ ዓይነቱን ጠመንጃ አምላኪ ኃይል ለመታገል የሚመቸው በማያውቅበት ሰላማዊ መንገድ ነው የጠመንጃውን መንገድማ የተካኑበት ነው ስለዚህም የተሻለ ውጤት ለማምጣትም እንደ ትግል መሳሪያ የሚሻለው ሰላማዊውና የምርጫው መንገድ ነው የሚል ጽኑ እምነት ነበረን በእኛ እይታ የሰላማዊ መንገድ ተመራጭነት አሁን ካለንበት ሁኔታ አንፃር ሲታይ ትንሽ የዋህነት ቢመስልም ከዚያም በላይ የሚፄድ ፋይዳ ነበረው በ ማለቂያ እነዚህን ውይይቶች ስናደርግና የተለያዩ አቋሞችን ስንይዝ አንዱ ከግምት ያስገባነው ኢህአዴግን እንደ ጠላት ማየት አይገባምፁ ይልቁንም እንደ ፖለቲካ ባላንጣ ብቻ አይቶ ከጥላቻ በፀዳ መልክ ቀርቦ ከእውነተኛ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ድርጅቱ ተጠቃሚ እንደሚሆን የድርጅቱን ጥቅም ከጊዜያዊ የሥልጣን ፍላጎት ባሻገር በማየት ማሳየት የትግሉ አንድ አካል መሆን አለበት ብለን አምነናል በዚህ ዙሪያ በተለይ ሁለት መሠረታዊ ልዩነቶችን አጽንኦት ሰጥተን ተመልክተናል የመጀመሪያው የኢህአዴግን መሪ ድርጅት ሕወሀትንና የትግራይን ሕዝብ በፍጹም ለይቶ ማየት የሚል ነው ይህ ለእኛ የስልት ሳይሆን ከልባችን የምናምንበት ጉዳይ ነበር በተለይ ፕሮፌሰር መስፍን ከማናችንም በላይ የሁለቱን ልዩነት አጽንዖት ይሰጣል የቀድሞ ባለቤቱ የትግራይ ተወላጅ መሆኗና በዚህም ምክንያት ልጆቹ በሙሉ ግማሽ የትግራይ ደም ያላቸው በመሆናቸው ከትግራይ ማኅበረሰብ አባላት ጋር በፖለቲካ ብቻ ሳይሆን ሰፊ የሆነ ማኅበራዊ ግንኙነት አለው ከዚህ በፊትም በትግራይ ላይ ጥናቶችን አድርጓል በመሆኑም የትግራይን ማኅበረሰብ በደንብ አውቀዋለሁ ብሎ ያምናል ከዚህም እውቀቱ በመነሳት ሕወሀት የሚከተለው የፖለቲካ መስመር የብዙኃኑን የትግራይ ማኅበረሰብ ስሜትና ፍላጎት የሚያንፀባርቅ አይደለም ብሎ ያምናል በኢትዮጵያዊነት ስሜቱ የትግራይ ሕዝብ ከማንኛውም የኢትዮጵያ ዘውግ ማኅበረሰብ ይበልጥ እንደሆን እንጂ አያንስም በዚህም ምክንያት በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ሕወሀት መራሹ ኢህአዴግ የሚወስዳቸው አቋሞችና አርምጃዎች በተለይ በኤርትራ ላይ ባለው አቋም ለሌላው ሕዝብ ካልተዋጡለት በዚያው መጠን ወይም ከዚያም በላይ ለትግራይ ሕዝብ አይዋጥለትም የሜል እምነት አለው ስለዚህም በአንድ የነዛነት ገህ ሲቀደ በኩል በኢህአዴግ መሰሪ ፕሮፖጋንዳ በመታለል በሌላ በኩል ደግሞ ሌላው ኢትዮጵያዊ እኛን ከኢህአዴግ ነጥሎ አያየንም ከሚል የመለየት ስሜት ለኢህአዴግ ድጋፍ እንዳይሰጠ መጠንቀቅ እንደሚያስፈልግ አይተናል ይህም ለታክቲክ ተብሎ ሳይሆን ትክክል ነው ብሎ በማመን ነው ከዚህ በተጨማሪም የዴሞክራሲ ፍላጎት ዘር የሚለይ ነገር አይደለም የኢህአዴግ ፀረዴሞክራሲያዊ ባሕርይ ዘር ለይቶ የሚንፀባረቅ አይደለም በሌሎች ክልሎች ያለውን አፈና ያህል ምናልባትም በባሰ መልኩ በትግራይ ይኖራል በዘውግ ፖለቲካ ለአንድ ዘውግ ቆሜያለሁ ስላለ ብቻ ለዚያ ዘውግ ማኅበረሰብ እውነተኛ ነፃነትንና ዴሞክራሲን ያጎናጽፋል ማለት አይደለምነ ይህማ ቢሆን ኖሮ ኤርትራ ነፃነት የተስፋፋባት የዴሞክራሲ ማማ በሆነች ነበር በምንም መለኪያ ግን የሻዕቢያ መንግሥት በዴሞክራሲያዊነት አይጠረጠርም ልክ እንደዚያው ብዙ የትግራይ ልጆች አቋማቸው ከሕወሀት ጋር ስላልተጣጣመ ብቻ ሌላው የሚደርስበት ግፍ ይደርስባቸዋል ኢዴሞክራሲያዊ መንግሥታት ፀረ ዴሞክራሲነታቸው ሥልጣናቸውን በሚቀናቀናቸው በማንኛውም ሰው ላይ ነው እዚሁ አገራችን በሕወሀት «አንጃዎች» ላይ የተወሰደውንና እየተወሰደ ያለውን የምናየው ነው ስለዚህም የትግራይ ሕዝብ እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ይፈልጋል ያለፍርፃት በመረጠው ድርጅትና መንግሥት ሥር መተዳደር ይፈልጋል ብለን እናምናለን በመሆኑም በምንም ዓይነት የትግራይ ሕዝብ በእውነተኛ ዴሞክራሲ ተጎጂ እሆናለሁ ብሎ እንዲያስብ ሊገፋፋ አይገባም በዘውግ ፖለቲካ ባጠቃላይና ኢዴሞክራሲያዊ በሆነ የዘውግ ፖለቲካ ተጠቃሚው የዘውጉ ማኅበረሰብ ሳይሆን በዘውጉ ስም ሥልጣኑን የያዙት ጥቂት ግለሰቦች መሆናቸው ሊታመንበት ይገባል ይህንን የግል ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ሲሉ የዘውግ ልዩነትን ወይም ጥላቻን ሲነዙ የዚህ መርዝ ማርከሻው ለዘውጉ ማኅበረሰብ ፍቅርን በማሳየት ይህን ጥላቻ ከሚገፉት ኃይሎች መለየት ነው ይህ አጠቃላይ አመለካከት ግን የትግራይን ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የኢህአዴግ አባላትንም የምናይበት መሥፈርት መሆን አለበት የሕወሀት ኢህአዴግ ተጋዳዮች በወጣትነታቸው የትግል ሜዳ በገቡበት ጊዜ መቼም ያመኑበት የነፃነትና የመብት ጥያቄ አላቸው እነዚህ ብዙኃኑ አባላት በትግላቸው ደርግን ጥለው የሚያቋቁሙት ሥርዓት ሕዝብን የሚበድል የሰውን መብት የሚረግጥ በሥልጣን ለመቆየት ማንኛውንም እርምጃ ጾር ብርዛኑ ነጋ ለመውሰድ የሚችል እና መርህ አልባ ይሆናል ብለው አይጠብቁም ሥርዓቱ ይህን መልክ ይዞ ሲያዩት ደስተኛ ይሆናሉ ብሎ ማመን ወይም ከሥልጣን በሚገኝ ትንሽ ፍርፋሪ ምክንያት ሥራ ደሞዝ ምናልባትም ጥሩ ቤት ጠቅላላ የታገሉለትንና ባዶቻቸው የተሰዉለትን የነፃነትና የፍትህ ዓላማ እርግፍ አድርገው ይተውታል ማለት ይከብዳል እንደዚህማ ቢሆኑ ኖሮ ድርጅቱ የቆመለትን መርህ እያጣ ሲፄድ እንደዚህ በርካታ አባላቱ ትተውት አይሄዱም ነበር ስለዚህ እነዚህን ኃይሎች የዴሞክራሲያዊ ትግሉ አካል ናቸው ብሎ ማመን ይገባል በጊዜው የነበረን እምነት ግን ከዚያም ይልቃል የሥልጣኑ ዋነኛ ተጠቃሚዎች የሆኑት የኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎችም ቢሆኑ የራሳቸውን ጥቅም የሚያውቁና ከጊዜያዊ የሥልጣን ጥቅም ባሻገር መመልከት የሚችሉ ናቸው ብለን አምነናል በ የሚደረገው ምርጫ እውነተኛና ዴሞክራሲያዊ መሆን እነሱንም ይጠቅማቸዋል ብለን ከምር አምነን ነበር ኢዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በአመጽ ጥለው የመጡ ኃይሎች ሕዝቡ በደል ሲበዛበትና ዴሞክራሲ ሲያጣ ወደ አመጽ ሊፄድ እንደሚችልና ይሄ ሌላው ቢቀር አሟሟታቸውን የማያሳምረው መሆኑን ለማወቅ የሚያስችል ጭንቅላት አያጡም የሚል ተስፋም ነበረን በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የሰላማዊውና የምርጫው መንገድ ከየትኛውም አማራጭ ይልቅ የተሻለውና ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲና እውነተኛና ዘላቂ ሰላም የሚወስደን ብቸኛ መንገድ ነው ብለን በሙሉ ልባችን አምነናል በዚህም ምክንያት የስብስቡ አጠቃላይ ጉልበት ድዘፀጩ መዋል ያለበት መጪውን ምርጫ በምን መንገድ ነው እውነተኛ ፉክክር ያለበት ለዴሞክራሲ በር ከፋች የሆነ ክስተት የምናደርገው በሚለው ላይ መሆን እንዳለበት ለዚህም በተቃዋሚው ጎራ እነዚህ ሀሳቦች የበላይ ሀሳብ የሚሆነበትን መንገድ መሻት ላይ መሰራት እንዳለበት እናምናለን ሔሑ የድርጅት ጥያቄ በሦስተኛ ደረጃ በጥቅሉ የተመለከትነው ጥያቄ ለዚህ ዓይነት የፖለቲካ ትግል የሚያስገፈልገው ምን ዓይነት ድርጅት ነው። የሚለውን ጥያቄ ነበር ይህም ጥያቄ እንዳለፉት ሁለት ጥያቄዎች በንድፈ ሀሳብ ደረጃም ሆነ በተግባር የሚጭራቸው ጉዳዮች አሉ የመጀመሪያው ጉዳይ ከላይ በተራ ቁጥር «ሀ» ላነሳናቸው አጠቃላይ የፖለቲካ ችግሮች መፍትፄ ነው ብለን ላስቀመጥነው መስመር የሚበጀው የፖለቲካ ድርጅት ምን የነዛነት ገህ ሲቀደ ዓይነት ነው የሚል ነው በዚህ ዙሪያ ወዲያውኑ የሚታየን ድርጅቱ በአምነት ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት ነው የፖለቲካ ድርጅት አንድ ዓይነት የፖለቲካ መሥመር የሚከተሉ ሰዎች የሚሰባሰበብት ከሆነ የመሰባሰቢያው መሠረት መሆን የሚችለው የፖለቲካ እምነት ብቻ ነው ዘውግ በመሠረቱ የአመለካክት ጉዳይ አይደለም የፖለቲካ አመለካከት አንድ ጭንቅላት ያለው ሰው አስቦና አመዛዝኖ በፍላጎቱ የሚይዘው የመረጠው አመለካክት ነው ማንም ሰው ከየትኛው ቤተሰብ ከየትኛው ዘውግ ወይም ከየትኛው የሰው ዘር ቀለም ወይም የትኛውን ጾታ ይዞ እንደሚወለድ መምረጥ የሚችለው ጉዳይ አይደለም ስለዚህም እነዚህ ግለሰቡ ያለ ምርጫው የሜሳበሳቸው የማንነት መገለጫዎች የፖለቲካ ድርጅቶች መሰባሰቢያ መሥፈርት ሊሆኑ አይችሉም በዚያው ልክ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በምንም ዓይነት በእነዚህ የማንነት መገለጫዎች ሰበብ በዜጎች ላይ ምንም ዓይነት በደል ወይም ጭቆና እንዲደርስ አይፈቅድም በእርግጥ በእነዚህ የማንነት መገለጫዎች ምክንያት በዚያ የፖለቲካ ማኅበረሰብ ውስጥ አገር የሚደርስ የተለየ በደል ወይም ጭቆና በሚኖርበት ጊዜ ይህንን በደልና ጭቆና ለመቋቋም መሰባሰብና መደራደት ይቻላልም ተገቢም ነው ነገር ግን መሠረታዊ በደሉ መነሻው ኢዴሞክራሲያዊነት ሲሆንና በዚያ አገር ውስጥ ያሉ ሰዎች በሙሉ የዚህ ኢዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሰለባ ከሆኑ ትግሉ በመጀመሪያ ደረጃ እነዚህን የዜግነት መብቶች የማግኘት የሁሉም ዜጋ ትግል ይሆናል ስለዚህም በአንድ አገር ውስጥ ለዴሞክራሲ የሚደረግ ትግልን ለማቀናጀት የተፈጠረ ድርጅት የማሰባሰቢያ መሠረቱ ለዚህ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መቆም ብቻ ይችላልሰ በዚያ አገር ውስጥ ሁሉም ዜጎች ከሚደርስባቸው ጭቆና በተጨማሪ የተለየ ጭቆና የሚደርስባቸው ኃይሎች ካሉና በዚያ መሠረት ከተደራጁ የዚህ አጠቃላይ የዴምክራሲያዊ ትግል አካሉች ነው የሚሆነት ይህ አጠቃላይ አመለካከት ግን ቀላልነቱ በአመለካከት ደረጃ ብቻ ነው በኢትዮጵያ በዚህ ዙሪያ የነበረውና ከግራ ርፅዮተ ዓለም የተወረሰው ልምድ ዘውግን የፖለቲካ መሰባሰቢያ ዋና መሥፈርት አድርጎ የሚያይ ነው ከዚህ በፊት በክፍል አንድ ውስጥ በዝርዝር ለማየት እንደተሞከረው የሕወሀትኢህአዴግ የፖለቲካ ፕሮጀክት ከአነሳሱም ይህን መሠረት አድርጎ የተነሳ ነው በሥልጣን ላይ ከወጣም በኃላ ይህንን አመለካከት ከፋፍሉ ለመግዣ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተጠቅሞበታል በዚህም አካሄዱ አምነውበትም ሆነ ለጥቅማቸው ሲሉ በሥሩ የተሰባሰቡትንና በኋላም ራሱ ጾር ብርሃኑ ነጋ የከበበ የፈጠራቸውን ድርጅቶችና የድርጅት አባሎች ብቻ ሳይሆን ኢህአዴግን አጥብቀው የሚቃወሙ የተቃዋሚ ኃይሉችም በዚህ የተሳሳተ መሥመር ውስጥ ገብተወበታል በየዘውጉ ላለው ንዑስ ዲታ ደግሞ ከፖለቲካ ንግድ የሚገኝ ጥቅም አለ ተብሉ ከታሰበ ምንም ቢሆን መሪ እንዲ ዝም ብሉ አባል መሆን ብዙ ቁሳዊ ጥቅም አያስገኝም መሪ ለመሆን ደግሞ የሚመቸው ብዙ ተፎካካሪ በሌለበት በራስ ዘውግ አጥር ሥር ሲኮን መሆነ አያጠያይቅም በዚህና በሌሎች የተሻለ የመርህ መሠረት ባላቸው ምክንያቶች የተነሳ አብዛኞቹ ተቃዋሚ ድርቶች ራሳቸው ዘውግ ተኮር ናቸው በአርግጥ ብዙዎቹ ከዚህ ፖለቲካ ጽንፈኛ መገለጫዎች የመገንጠል ጥያቄ የፀዱ ናቸው ቢባልም ከላይ ባነሳነው የፖለቲካ ምንነት መርህ አንፃር ለዘውግ ዘለል ዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ የማይመቹባቸው ብዙ ነገሮች አሏቸው ከዚያ በላይ ግን የሚነሳው የተግባር ጥያቄ ቀደም ብዬ እንዳልኩት በምርጫ ጥሩ ፉክክር ለመፍጠርና ሥርዓቱን ወደ ዴሞክራሲያዊነት ለመግፋት የተቃዋሚ ድርጅቶች ትብብር አጥብቆ ጅጠይቃል የዚያኑ ያህል ግን የዓላማ ግልጽነትን ከኢህአዴግ ጋር ያለን የፖለቲካ ልዩነት በግልጽ ማስቀመጥን ይፈልጋል የዚህ የዓላማ ግልጽነት ድርጅታዊ መገለጫው በዓላማ አንድነት ላይ የተመሠረተ ዘውግ ዘለል የፖለቲካ ስብስብ ከሆነ በሌላ ወገኑ ደግሞ የድርጅቶችን ትብብር የሚሻው የፖለቲካ ትግል ከዘውግ ተኮር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋርም አብሮ መሥራትን የግድ ይላል አነዚህን ሁለት በተቃርኖ የተቀመጡ አስፈላጊ ነገሮች ማጣጣሙ ነው እንግዲህ አንዱ በድርጅት ዙሪያ መመለስ ያለበት ጥያቄቂ ለዚህ ጥያቄ ስብስቡ የሰጠው መልስ ዘውግ ዘለል ድርድቶችን በአንድ ላይ ማሰባሰብና ጠንካራ የፖለቲካ ድርጅት እንደ አንድ ድርጅት ወይም የድርጅቶች ጥምረት መመሥረት በሌላ በኩል ግን ዘውግ ተኮር ከሆኑ ተቃዋሚ ድርጅቶች ጋር ቢያንስ እርስ በእርስ መፎካከርን የሚቀንስ ስልታዊ የፖለቲካ ትብብር መፍጠር ግን እያደር ከእነዚህ ድርጅቶች ጋር ከምርጫው በኋላ በመርህ ላይ የተመሠረተ ውይይት ማድረግ የሚለው መንገድ ተመረጠ ከዚሁ ከድርጅት ዙሪያ ሳንወጣ የሚነሳው ሌላው ጉዳይ እነዚህን አመለካከቶች የሚያንፀባርቅ ሌላ አዲስ የፖለቲካ ድርጅት ቀስተ ደመና ማቋቋም ያስፈልጋል ወይ የሚለው ጥያቄ ነው ይህ በጣም ብዙ ያከራከረ ጉዳይ ነው የፖለቲካ ድርጅቶች እንደ አሸን በፈሉበት አገር ሌላ የፖለቲካ የነባነት ገህ ሲቀደድ ድርጅት መፍጠር የበለጠ ነገሮችን ግልጽ ከማድረግ ይልቅ ውዥንብር ሊፈጥር ይችላል ሕዝቡ ያሉት ድርጅቶች ተባብረው እንዲሰሩና ኢህአዴግን ሊመክት የሚችል ጠንካራ ስብስብ እንዲፈጠር በሚፈልግበትና በሚጠበቅበት ጊዜ ሌላ ድርጅት መፍጠር ሁሉም የራሱን ምሽግ መፍጠር የሚፈልግበት ለሥልጣን የሚደረግ መሯሯጥ ያስመስለዋል ይህ ደግሞ ፖለቲካውን ይጎዳዋል እንጂ አይጠቅመውም የምናምንባቸው የተለዩ ሀሳቦች ቢኖሩም እነሺህን ሀሳቦች በአንዱ ድርጅት ውስጥ ገብቶ ተቀባይነት እንዲያገኙ መግፋት ይሻላል የሚል አመለካከት በአንድ በኩል ሲኖር በሌላ በኩል ደግሞ በ ማለቂያ ላይ በተቃዋሚ ድርጅቶች መሀከል ያለው ግንኙነት ከፍተኛ መናቆር ውስጥ ያሉበት በመሆኑ በምንም ዓይነት ከአንዱ ኃይል ጋር ከወገንን የሌላውን ተዓማኒነት እናጣለን ይህ ደግሞ በዋናነት አስፈላጊ ነው ብለን ያመንነውን ጠንካራ የዘውግ ዘለል ድርጅቶች ሕብረትና ብሎም ውሕደት የመፍጠር ዓላማ ያሰናክላል ከዚህ በተጨማሪም እኛ መሠረታዊ ብለን የምናምንባቸውን ሀሳቦች ይፈጠራል ብለን በምናምነው ሕብረት ውስጥ አጠንክረን እንድንገፋቸውና ተቀባይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ ራሳችንን በድርጅት መልክ ማዋቀሩ ይጠቅማል የራሳችንን ድርጅት ማቆም ሌላም ጥሩ ጥቅም ይኖረዋል ቀደም ተብሉ እንደተጠቀሰው የአገሪቱ ልሂቃን ከፖለቲካው ርተዋል ለመራቃቸው ከሚሰጡት ምክንያት አንዱ ከእምነታቸው ጋር የሚሄድ ድርጅት አለመኖር ነው በእኛ የሚፈጠረው ድርጅት እስከ አሁን ከዳር ቆመው የነበሩ ልሂቃንን በተለይም በምሁራን አካባቢ ፖለቲካውን የመቀላተል ፍላጎት ሊፈጥር ይችላል ከዚህ በፊት በነበሩት ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዳለ ይታወቃል ይህን ጥርጣሬ ለመቅረፍ የቀስተ ደመና መፈጠር ጠቃሚ እና ለድርጅቱ መፈጠርም ተጨማሪ ምክንያት ይሆናል እነዚህንና መሰል ምክንያቶች በሰፊው ከመረመርን በኋላ የደረስንበት አቋም በሁለቱም በኩል ያሉትን ጥቅሞችና ጉዳቶች አገናዝቦ ጉዳቶቹን የሚቀንስና ጥቅሞቹን የሚያጎላ የተቀየጠ አቋም ነበር በዚህም መሠረት የስብስቡ ዋና ዓላማ መሆን ያለበት በአገሪቱ ውስጥ በህጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ዘውግ ዘለል ድርጅቶችን ማስተባበር መሆን እንዳለበት ይህንን ማድረግ ካልተቻለ የቀስተ ደመና መፈጠር ጥቅም አጠያያቂ እንደሚሆን በተለይ ያሉት ድርጅቶች ቀስተ ደመና ከማንም ያልወገነ መሆኑን ማወቃቸጡ ለስብስቡ መፈጠር ብቻ ሳይሆን ከተፈጠረም በኋላ በዘላቂነት ለመቆየትና ቀጥሉም ተዋህዶ አንድ ድርጅት ጾር ብርዛኑ ነጋ ለመሆን ያለውን እድል እንደሚያሰፋው በመተማመን ሌላው የማሰባሰብ ሂደት ጥሩ መሥመር መያዝ ሲጀምር የቀስተ ደመናን የምሥረታ ሂደት አብር ማካሄድ ይገባል በሚል ተወሰነ በመጨረሻም ከድርጅት ጉዳይ ጋር በተያየዘ የተነሳው ወሳኝ ጥያቄ በተለያዩ ድርጅቶች ኅብረት የሚቋቋመውም ድርጅት ሆነ ቀስተ ደመና የሚከተሏቸው የድርጅት መርሆዎች ምን መሆን አለባቸው የሚለው ነው ይህ ጉዳይ በእኛ በኩል በጣም አትኩሮት ሰጥተን የተወያየንበትና መሠረታዊ እምነቶቻችን ብለን ከያዝናቸው የፖለቲካ አቋሞች ባልተለየ መንገድ አጽንኦት ሰጥተን የምንከራከርለት ጉዳይ ነው ይኸውም የድርጅቱን የራሱን የውስጥ ዴሞክራሲ ይመሰከታል በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ የግራ ርፅዮተ ዓለም ሥር የሰደደበት ቦታ ቢኖር በድርጅቶች አወቃቀርና የውስጥ አሠራር ላይ ነው የግራ አመለካከት አይስማማንም የሚሉ ድርጅቶች እንኳን የድርጅት አወቃቀራቸውና አሠራራቸው ከግራው ተሞክር የተወሰደ ነው ለዚህ አንዱ ምክንያት በፖለቲካ ፓርቲ የመደራጀት ታሪክ በአገራችን የተጀመረው በግራ አቀንቃኞች መሆኑ ነው ቀደም ብዬ እንዳልኩት የሊበራል ዴሞክራሲ መርህን እንቀበላለን ብለው የሚያምኑ ሰዎች በንጉሠ ዘመን ቢኖሩ እንኳን የፖለቲካ ጫናውን ሙሉ ለሙሉ ለአብዮተኞች ለቅቀው ነበር ስለዚህ የፖለቲካ ድርጅት ሲባል የሚታወቁት አብዮታዊ ድርጅቶች ናቸው ከኢህአዴግ በኋላ የተፈጠሩ የፖለቲካ ድርጅቶችም አብዮታዊ ሆኑ አልሆኑ ዘውግ ተኮር ሆኑም ዘውግ ዘለል ለድርጅቱ መቋቋሚያ የሆኑ የውስጥ ደንቦች የድርጅት መዋቅሮች ወዘተ ሙሉ ለሙሉ እንኳን ባይባል የተገለበጡት ከዚህ ቀደም ከነበሩት አብዮታዊ ድርጅቶች ነበር የዚህ ዓይነት አደረጃጀት ደግሞ ከሌሎች አገሮች ተመክሮ ብቻ ሳይሆን ከራሳችን አገር ታሪክም በደንብ ያየነው ነው አንዳንድ ሰዎች ይህንን ከድርጅቱ መዋቅር የተፈጠረ ችግር ሳይሆን ድርጅቶቹና ግለሰቦቹ ራሳቸው ኢዴሞክራሲያዊ ወይም አብዮታዊ ስለሆኑ ነው እውነተኛ ዴሞክራቶች ከሆኑ የተደራጁት የድርጅቱ መዋቅርና የውስጥ ደንብ ያንን ያህል ለውጥ አያመጣም ብለው ይከራከራሉ ይህ ግን ሩቅ የሚያስኬድ ክርክር አይደለም በዴሞክራሲ የሥልጣን ክፍፍል የሚኖረው አንዱ አካል ሌላውን ሊቆጣጠር የሚችልበት ማንም ግለሰብ ወይም ቡድን አምባገነን የሚሆንበትን መንገድ ከሰዎቹ ማንነት ባሻገር ለመዝጋት ነው በድርጅቱ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ያልሆነ ተቋም ደግሞ በመንግሥት ሥልጣን ላይ ሲወጣ ዴሞክራሲያዊ ይሆናል ብሎ መጠበቅ የነባነት ገህ ሲቀደድ የዋህነት ነጡ ስለዚህም በድርጅቱ መዋቅር የውስጠ ደንብ በተለይ የአባላትን መብት የሚገድቡ ነገሮች እንዳይኖሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አንደሚገባ ይታመናል በዚህም መሠረት ቀስተ ደመናም ሆነ የሚፈጠረው የድርጅቶች ትብብር በተቻለ መጠን ውስጡ ዴሞክራሲያዊ የሆነ የአባላቱ የውስጥ መንፈስ ነፃ የሆነ ለክርክርና ለልዩነት ቦታ የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን አክብሮት ያለው በምንም መልክ ማንም ሰው ያልተገደበ ሥልጣን አንዳይኖር የሚገታ በድርጅቱ ውስጥ ባሉ የተለያዩ መዋቅሮች ውስጥ የእዝ ሰንሰለት ብቻ ሳይሆን የአሠራር ነፃነት የሰፈነበት አንዳንድ ወሳኝ የሆኑ በነፃነት መሠራት ያለባቸው የድርጅት አካላት ለምሳሌ የድርጅት ጋዜጦችና ሥነጽሁፎች የሚወጣባቸው ተቋማት ወዘተ ከድርጅቱ አመራር ነዓ ሆነው የሚዋቀሩ መሆን አለባቸው የሚል ጽኑ እምነት ነበርን በተለይ በግራ ድርጅቶች ውስጥ የነበርን ሰዎች አሁንም በአገሪቱ ውስጥ ባሉ ድርጅቶች ውስጥ የምናያቸው የውስጥ ድርጅቶች አካሄዶች በተለይ ከድርጅቶች ውስጥ አንድሰው ወይም ጥቂት ሰዎች ፈላጭ ቆራጭ ሆነው የሚሰሩበት ሁኔታ በፍጹም መቀየር አለባቸው ብለን አምነናል ይህን በቀስተ ደመና ላይ መንፀባረቅ ያለበት ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ በድርጅቶቹ ሕብረት ውስጥ እንዲንፀባረቅ መታገል አለብን የሚል ጽኑ እምነት ነበረን አንግዲህ በእነዚህ ሦስት አጠቃላይ ጉዳዮች ላይ በተደረጉ ውይይቶችና ከፖለቲካ ጥያቄው ውጪ የድርጅቱ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ፖሊሲ በጥቅሉ የማኅበራዊ ዴሞክራሲ ዐር ዐፀበገዐርያቋርህ ቅኝት እንደሚኖረውና በዚህም ቅኝት ዋና ዋና መገለጫዎች ላይ ከተስማማን በኋላ ነበር ወደ ተግባራዊ ሥራ የገባነው ይህ ተግባራዊ ሥራ በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ዘውግ ዘለል ድርጅቶች አቋም መመርመርና በጋራ መሥራት ይችላሉ የሚባለትን በማነጋገር የድርጅቶቹ ሕብረት የሚፈጥርበትን የመጀመሪያ ደረጃ እንቅስቃሴ መጀመር ነበር ቅንጅቱን ለመፍጠር ቀስተ ደመና የጀመረው እንቅስቃሴና የገጠሙት ችግሮች ሩ በዚሀ ይ ቀሰፉ ደመና ያጎነገረው ሂግሮር ሃተሃ በቅንዕቻራ ውሐደን ቹ በጽሥፍ ፖዚጋቾዖ ፅውሀደ ለመቻቻ ሶሚሜሄው ሃርጻ ያዎንኞራ ለኑም ዕውሕደቱ ሰፊት እንዲመያገ በቀነፖ ደመና ድራሃጽ ላይ ወም ይሀሃ ቦቃዕዎ ድረጅታ ነፃነት በሚመነታ እኔ ራሕ ፉው የሃገረ ፅረ ዴምህራሲያፎማሪነጎፎዊኑታ ለቋም ጎሰር እኔ ዳምቀታ ሐድ ይፖርራፈ አዛል ድርጅራ በሉዓጫ ድምጽ ሶጎፅፈታንሃ ውሳኔ ፍዱም ያየሚሰምያሦ ሰሆነ ፅፓርቷው ፅላቋም ፖሐይፉ የራታሀ ጳቋም በሐሪ ፊታ ሀ ዐሀር የማቅረዝና ዖቦመዕራር መዘቋታ ፈሃረው ይሃባሳ የድርድሪ ፉሦመራጭ መሪዖሃው መለዖታ ይቻታ የሜሷጳ ጎፅር ጾር ብርፃኑ ነጋ የቀስተ ደመና መስራቾች የዘውግ ዘለል ድርጅቶችን ሕብረት ለመፍጠር ተግባራዊ እንቅስቃሴ የጀመርነው በ ክረምት ነበር በጊዜው ፕሮፌሰር መስፍን እና እኔ የ ምርጫን በሚመለከት የሲቪክ ማኅበረሰቡ ሚና በሚል ርዕስ ላይ ንግግር እንድናደርግ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የአንድ ኢትዮጵያ ሬዲዮ ባለቤት ተጋበዘን ነበር በዚህ ወትት የሕብረቱ የመጀመሪያ ጉባዔ በዋሽንግተን አካባቢ እንደሚደረግ ይታወት ነበር የቀስተ ደመና መሥራቾች ይህንን አጋጣሚ እንድንጠተምበትና እዚያ ለስብሰባ ከሄዱት በአገር ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንድንፈጥርና ያለውን ዓላማ በሚመለከት አጠቃላይ ውይይት እንድናደርግ ኃላፊነት ሰጡን በሁላችንም አእምር ውስጥ ያለውና ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ያልነው በምንም ዓይነት ሕብረቱን ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ እንዳልሆነና በተቻለ መጠን ከሕብረቱ ስብሰባ በኋላና ውጤቱ ከታወተ በኋላ እንዲሆን ማድረግን ነበር ሁለተኛ በተቃዋሚ ድርጅቶች ውስጥ ያለውን የጥርጣሬ መንፈስ ከግምት በማስገባት በተቻለ መጠን የእኛ ሥራ ሕብረቱ እንዲፈጠርና ከተፈጠረም በኋላ በሥራ ማገዝ እንጂ ያለውን አመራር ለመተካት ወይም ለመነካካት ምንም ዓላማ የሌለን አንደሆነ እንዲያውቁት በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ መንገድ መንገሩ ተገቢ እንደሆነ ነበር በስብስቡ በመጀመሪያ ደረጃ ማወያየት ይገባል ተብሉ የታመነው ኢዶአፓ መድኅንን እና መኢአድን ነበር በዚህ ጊዜ መኢአድ በሕብረቱ ጉባኤም ላይ እንደማይገኝና አመራሩም ወደዚያ አንዳልሄደ ስናውት እዚህ ከተቀሩት አባሎቻችን ውስጥ ሁለቱ የመኢአድን አመራር እንዲያናግሩ እኔና ፕሮፌሰር መስፍን ዋሽንግተን እንደሄድን የኢደአፓ ኘ መድኅን አመራርን እንድናነጋግር ተወሰነ ሌሎች ድርጅቶችን የእነዚህ የሁለቱ ትላልቅ ድርድቶች አዎንታ ከተገኘ በኋላ ማናገሩ ይሻላል በሚል ተስማማን በመሠረቱ መመሥረት አለበት ብለን ያሰብነው ቅንጅት ከመነሻው ሁለት መስፈርቶችን ያሟላ መሆን አለበት ብለናል እነዚህም አንደኛ ድርጅቱ ዘውግ ዘለል ሕብረ ብሄራዊ መሆን አለበት ሁለተኛ ድርጅቱ በአገሪቱ ሕግ መሠረት ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስና በምርጫ ለመወዳደር የተዘጋጀ መሆን አለበትፈ እነዚህን ሁለት መስፈርቶች የሚያሟሉ ድርጅቶችን በሙሉ ማነጋገር ብቻ ሳይሆን የቅንጅቱ አካል እንዲሆኑ መጣር አለብን የሚል ጽኑ እምነትም ነበረን ይህንን ስንወስን ግን ከመሬት ተነስተን አልነበረም በመጀመሪያ በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ዘውግ የነዓነት ገህ ሲቀድ ዘለል ድርጅቶችን ፕሮግራሞች በሙሉ ፈልገን ለማየት ሞክረናል እነኝህን ፕሮግራሞች መርምረን በአንዳንድ ዝርዝር የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ የሚኖሩ ልዩነቶች ካልሆነ በስተቀር በመሠረታዊ እምነት ደረጃ ሁሉም የሚያምትባቸው ተመላሳይ እምነቶች አሏቸው በተለይ ከላይ በጠቀስነው የአገሪቱን የፖለቲካ ችግርና መፍትሄውን በሚመለከት ባቀረብነው ትንተና ላይ ብዙ ችግር ያለባቸው አልሆኑም ከዚህም በፊት በሽምግልናችን ወቅት እንደተረዳነው ቅንጅቱን በመፍጠር በኩል የሚኖረው ችግር የአመለካከት ልዩነቶች ሳይሆኑ ከዚያ ውጪ ያሉ በድርጅቶች ውስጥና መካከል ያሉ ፉክክሮችና የግለሰብ ሽኩቻዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ገምተናል ለዚህም ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለብንና በተለይም ደግሞ እኛ እራሳችን ከዚህ አንፃር የችግሩ አካል እንዳንሆን መጠንቀቅ እንዳለብን ተግባብተናል ሁለታችን ወደ አሜሪካ ከመሄዳችን በፊት የመኢአድን አመራር ለማነጋገር ቀጠሮ የያዘው ቡድን በአጭር ቀጠር ተገናኝቶና በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ተነጋግሮ የድርጅቱ መሪዎች ይህንን ተነሳሽነት ዘቋበህ በጣም እንደሚደግፉትና ከቀስተ ደመና ሰዎች ጋርም ሙሉ ለሙሉ ለመተባበር ፈቃደኞች እንደሆኑ ይነግሩናል ለዝርዝር ውይይት እኛ ከአሜሪካ ስንመለስ ከሌሎች ድርጅቶችም የሰማነውን ካጣጣምን በኋላ በሰፊው ለመገናኘት ተስማምተው ይለያያሉ ይህ ለመንገዳችን ጥሩ ስንቅ ነበር አሜሪካ በደረስንበት ጊዜ የሕብረቱ ጉባዔ ሊጀመር አንድ ሁለት ቀናት ነበር የቀረው በዚህ ጊዜ በዋናነት ከሄድንበት ዝግጅት ጋር በተያያዘ ካልሆነ በስተቀር በፖለቲካ ጉዳይ ከማንም ጋር አልተወያየንምጹ ጉባዔው እንደተጠናቀቀ የጉባዔውን ውጤት በዝርዝር ሰማን ኢዴአፓመድኅን የሕብረቱ አካል እንደማይሆንም አወቅን ከዚህ በኋላ ድርጅቱን ወክለው ሄደው ከነበሩት ውስጥ ዶር አድማሱንና ልደቱን አገኘናቸው ከእነሱም ስለ ሕብረቱ ጉባዔ ውጤት ከሰማን በኋላና በሕብረቱ ውስጥ እንደማይቀጥሉ ካወቅን በኋላ ነበር ኽኛ በኩል ያለንን ሀሳብ ገለፅን በሁለቱም በኩል የነበረው ስሜት በጣም የመደሰት ብቻ ሳይሆን ምናልባት በመኢአድ በኩል ችግር ይፈጠር ይሆን ወይ የሚል ሥጋት ነበር ይህም ችግር ይሆናል ብለን እንደማናስብ ነገርናቸው በቶሉ ወደ አገር ተመልሰን ይህን ሥራ እንድንጀምር ተስማምተን ተለያየን ከዚያ በኋላ አሜሪካን አገር ከምናውቃቸው ጓደኞቻችንና የፖለቲካ ጉዳዩን በቅርብ ይከታተላሉ ከምንላቸው ጥቂት ሰዎች ጋር በእኛ ሀሳብ ላይ ውይይቶች አደረግን በዚህ ውይይት ውስጥ በአሜሪካ የተመሠረተውን ጾር ብርዛኑ ነጋ የሕብረቱን አካሄድ ከሚደግፉ ኃይሎች የተወሰነ ተቃውሞ የገጠመን ሲሆን ሕብረቱ ሩቅ አይሄዱም ብለው ከሰጉ ኃይሉች ደግሞ የድጋፍ ድምጽ አገኘ ን ከሁሉም በላይ ግን በተለይ የቀስተ ደመና ዓይነት ድርጅት መፈጠር አለበት ብለው የሚያምኑ የተወሰኑ ሰዎች ዝም ብሉ ድጋፍ ሳይሆን እንዲህ ዓይነት ድርጅት ከተመሠረተ በሙሉ ልባቸው አብረውን እንደሚሠሩ ነገሩን ይህም የጀመርነውን መሥመር ትክክለኛነት በመጠኑም ቢሆን አስረገጠልን አበረታታንም ከአሜሪካ መልስ በቀጥታ የገባነው ከሁለቱ ድርጅቶቸ ውጪ ያሉ ሌሎች ዘውግዘለል ድርጅቶችን ፈልጎ ማነጋገር ነበር በዚህም ዙሪያ በመጀመሪያ ያነጋገርነው በኢድህ ስም የሚንቀሳቀሰውን ድርጅት ነበር በጊዜው የኢድህ ዋና ፀሐፊ በአሜሪካው ጉባዔ ለመሳተፍ መሄዱንና ከፈለግን ከሌሎቹ ጋር መነጋገር እንደምንችል በተነገረን መሠረት በአገር ውስጥ የነበረውን የኢድህ አመራርን አገኘን ከብዙ ውይይት በኋላ በሀሳቡ እንደሚስማመሙበት ነገር ግን የድርጅቱ ፀሐፊ በአሜሪካን አገር የደረሰበትን ሳናውቅ ማለትም ድርጅቱ ሕብረቱ ውስጥ መግባት አለመግባቱን ሳናውቅ የመጨረሻ ውሳኔ ልንነግራችሁ አንችልም አሉን ከፀሐፊያቸው ጋር ያንኑ ዕለት በስልክ ተገናኝተው በነጋታው ውጤቱን እንደሚስታውቁንም ነገሩንፊ በማግስቱ በሕብረቱ ውስጥ መግባት ብቻ ሳይሆን የኃላፊነት ቦታም እንዳላቸው አስታውቀውን ከእነሱ ጋር የነበረው ግንኙነት በዚህ ተቋጨጩ ከዚያ ቀጥሎ ያነጋገርነው ከኢዴአፓ ተገንጥለው መኢዴፓ የሚባል አዲስ ድርጅት የፈጠሩትን ሰዎች ነበር ከእነሱ ጋር አንድ ሁለት ጊዜ ከተነጋገርን በኋላ በእነሱ በኩል በኢዴፓ አመራር ላይ በተለይ ልደቱ በተመለከተ ብዙ ችግር እንዳላቸው በእነሱ እይታ በእነሱና በኢዴፓ መሀል የተፈጠረውን ችግር ነግረውን የችግሩ ዋና ምክንያት የልደቱ መሠሪነት እንደሆነና በፍጹም ሊታመን እንደማይገባው አጽንኦት ሰጥተው ነበር የተናገሩት ቢሆንም ግን ተባብር ከመታገል ውጭ አማራጭ የለም ብለው እንደሚያምነ ስለዚህም ቅንድቱን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳላቸውና በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ለመወያት ፈቃደኛ እንደሆነ ነገሩን በመጨረሻም ያነጋገርነው ድርጅት የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ሊግ ኢዴሊ የሚባለውን ነበር እንደሚታወቀው ኢህአዴግ በ እኔና ፕርፌፌስር መስፍንን የከሰሰን ኢዴሊ የሚባል ድርጅት በሕቡዕ ፈጥረዋል ብሉ ነበር እኛ በዚያን ጊዜ ድርጅቱ በምሥረታ ላይ ስለነበረ ነው መሰለኝ የፕርግራማቸውን የነባነት ገህ ሲቀድ ረቂቅ ሰዎች እንዲያዩላቸውና ሀሳብ እንዲሰጧቸው ለጥቂት ሰዎች አሰራጭተው ነበር በአጋጣሚ ይህ ረቂቅ በእኔና በፕሮፌሰር መስፍን ቤትም ስለተገኘና ይህም በኢህአዴግ ወርቃማው የፍትህ ክዘመን ትርጓሜ መሠረት የሚያሳየው «ሕገመንግሥታዊውን ሥርዓት በኃይል ለመቀየር ኢዴሊ የሚባል ድርጅት አቋቁመዋል» የሚል ነበር በእውነቱ በዚያን ጊዜ እኛ እንኳን አባል ልንሆን የድርጅቱ አባሎች እነማን እንደሆኑም አናውቅም ነበር ለማንኛውም ይህ ድርጅት በሕጋዊነት መመዝገቡን ስላወቅን አመራሩን ፈልገን እንደዚሁ በሰፊው ተወያየን ድርጅቱ በዚያ ወቅት በ ምርጫ ለመሳተፍ ሀሳብ ያልነበረው ቢሆንም ይህ ስብስብ ጥሩ ሊሆን እንደሚችልና በአመሰካከት ደረጃ ሊኖሩ የሚችሉ ልዩነቶችን ማጥበብ ከተቻለ ቅንጅቱን ለመቀላቀልም ሆነ በምርጫው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አሳወቁን የሚቀጥለው ሥራ ከእነዚህ ድርጅቶች ጋር ያገኘነውን ፈቃድ ይዘን ለመጀመሪያ ዙር ውይይት ቀጠሮ መያዝ ነበር ከዚያ በፊት ግን ሁለቱ ትልልቅ ድርጀቶች ማለትም መኢአድና ኢዴአፓመድህን በአምስቱ ድርጅቶች ዙሪያ ያላቸውን ሀሳብና አስተያየት ማወቁ ይጠቅማል በሚል ይህንኑ አቅርበን በመኢአድ በኩል ምንም ችግር እንደሌለ ተገልጸልን በኢዴአፓ መድህን በኩል ግን የመኢዴፓን መግባት በጣም እንደሚቃወሙትና ለቅንጅቱ እንደማይጠቅመ ነገር ግን ዝርዝር ምክንያቶቻቸውን አራቱ ድርጅቶች ከተሰበሰቡ በኋላ እንደያሚቀርቡና የአራቱን ውሳኔ እንደሚቀበሉ አስታወቁ በዚህም መሠረት የመጀመሪያው ውይይት የአራቱ ድርጅቶች አመራሮች በአራት አራት ሰው ተወክለው እንዲደረግና ስብሰባውም በሰሜን ሆቴል እንዲሆን ተወሰነ በቀስተደመና መሥራቾች በኩልም ለስብሰባው መነሻ የሚሆኑ የመንደርደሪያ ሀሳቦች ተዘጋጁ በስብሰባው ውስጥ ከመግባታችን በፊት እንቅፋት ሊሆኑ ይችላሉ ያዜው መረማሪያቻፇ የሺያረው መፆ ለሐቃ ሰሪ ድረጀራ ቃል ጳጋድጋዕፖ ጨይፇሃ ምጋም ሕደማናውቅ ሰነፇረው ታ ድረጀቱ ማሃ ዳጋደሆነና ምርጫ ዕርድ ፖመቻግ ዳደሆፇ ሐመጠየዎቅ ሄድ ደድረድራ መሥራፇ ይላባትቻፖው ሰም ሂጋና ፊረማ ሕደይያው ማመሰለቻ ማሰሃፇባታቻው ሰማያ ሰች ይሀጋጋም ዝታ ድረጅራጋ መሰርታቻል ታ ቃዜ ሐግፇ ዕኃታ ። ጠኛ ይፖጋነው ን በፍም ሰፇሰሦ ደመና ዳናሚይያን ነው የነባነት ገህ ሲቀድ ሮምሙመርርርርርጮ ም ምም ምጮም ጵር ምምም ኃይሉ ስብእና ላይ የሚቀርቡ ሂሶች ነበሩ በዚህ ዙሪያ የተነሱት ግለሰባዊ የአመራር ዘይቤ የንግድ አመራርንና የፖለቲካ አመራርን አለመለየት ለልዩነት ትእግስት ማጣት ግትርነት ለሕዝብ የሚቀርብ ንግግር ላይ አለመጠንቀቅ እና መሰል ፀባዮች ትብብሩን ገና ከመነሻው ችግር ውስጥ ይከቱታል እነዚህን ፀባዮች ደግሞ በተሰያዩ አጋጣሚዎች በተለይ በሁለቱ ድርጅቶች የውህደት ሙከራ ወቅት አይተናቸዋልና የምናወራውን እናውቃለን ከመሬት ተነስተን አይደለም የሚል ክርክር ነበር በእነሂህ ጉዳዮች ላይ ብዙ የስብስባ ውጪ ውይይቶች ይካሄዱ ነበር በተለይ አቶ ኃይሉን በግል ለማናውቀው ሰዎች እነዚህን የሰማናቸውን ችግሮች አውነተኛነት ከሌላ ወገንም ማረጋገጥ ስለፈለግን ለስብሰባው በመኢአድ የተወከሉትን አንዳንድ አባሎች በእነዚህ ጥያቄዎች ዙሪያ አወያይተን ነበር በአቶ ኃይሉ የአስተዳደር ዘይቤ ቋፀፀየ ላይ የሚቀርቡ ሂሶች እውነትነት እንዳላቸው ግን የዚያኑ ያህል ጠንካራ ጎኖች እንዳሉት መኢአድን ከወደቀበት አንስቶ በአጭር ጊዜ በአርግጥ ጠንካራ ሊባል የሚችል በጥቂት የአማራ ዞኖች ታጥሮ የነበረን ድርጅት በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ምናልባት ከጋምቤላና ከሶማሌ ክልል በስተቀር በአጭር ጊዜ ያስፋፋው በተወሰነ ደረጃ በዚህ የአስተዳደር ዘይቤ እንደሆነ ግትርነቱንም በተመለከተ በአርግጥ አሳማኝ የሆነ ምክንያት ከሰማ የሚቀበል መሆኑንና ከዚያ ቀደም የተሳሳተ አቋም ይዞ ከነበር ተሳስቼ ነበር ብሎ ለማረም ምንም የማይቸግረው መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው ውስጥ ጠንካራና አምክንዮታዊ ሰዎች ካሉ አቶ ኃይሉ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ተስማምቶ መሥራት የሚችል መሆኑንና ከጠባብ ድርጅታዊ ስሜት ውጪም የአቶ ኃይሉን ሊቀመንበርነት ለቅንጅቱ ጥቅም ሲሉ እንደሚደግፉት ገልጸውልናል ዶር አድማሱንም በጉዳዩ ላይ ስናወያየው በአቶ ኃይሉ ሊቀመንበርነት ላይ ተቃውሞ እንደ ሌለው ነገር ግን ላእላይ ምክር ቤቱና በተለይም ሥራ አስፈዓፃሚው ጠንካራ ሰዎች ኖረውበት እውነተኛ የቡድን አመራር ሊሰጡ የሚችሉበት ሁኔታ መፈጠር እንዳለበት እንደሚያምን ገለጸልን በዚህም ተማመንን ከሁሉም በላይ ግን ምርጫችንን የወሰነው ያለው አማራጭ ምንድን ነው የሚለው ነው በነልደቱም በኩል ቢሆን ከኢዴአፓመድኅን መሆን አለበት ብለው አልነበረም የቀረቡት እንዲያውም እነሱ ሊቀመንበሩ ከቀስተ ደመና በተለይም እኔ እንድሆን ነበር ከበስተኋላ የሚቀሰቅሱት ይህን ደግሞ በምንም ዓይነት እኔም ሆንኩ ሌሎቹ የቀስተ ደመና ተወካዮች በምንም ዓይነት የማንቀበለው ነበር ጾር ብርፃኑ ነጋ በምንም ዓይነት ለቀስተደመና እንዲህ ዓይነት የመሪነት ሚና አልተመኘ ንለትም ይልቁንም ለራሳችን የሰጠነውን የገለልተኛነትና የአሳላጭነት ዛዐበፀ ፀያዐጸፀያ ሚና ያበላሸዋል ብለን ስለምናምንና በተለይ ሁለቱን ድርጅቶች ለመሪነት እንደማንፎካከራቸው ማወቃቸው ሰትብብሩ መጠናከር ይጠቅማል ብለን ቀድሞውኑም ያሰብንበት ጉዳይ ስለነበር ለእኛ መሪነቱን መውሰድ የሚታሰብ አልነበረም በኢዴሊም በኩል ይህንን ሚና ለመጫወት ድርጅቱም ሆነ የድርጅቱ ተወካዮች ሀሳብ አልነበራቸውም በእነልደቱ ቅስቀሳ በተወሰነ ደረጃ የኢዴሊ ሰዎች እኔ የሊቀመንበርነቱን ቦታ እንድይዝ ያስቡ የነበሩ ቢሆንም ከእኛ ጋር ባደረግነው ውይይት የዚህን ምርጫ ችግር አሳምነናቸው ነበር በመጨረሻ ከብዙ ውጣ ውረድ በኃላ በአቶ ኃይሉ ሊቀመንበርነት እና በዶር አድማሱ ምክትል ሊቀመንበርነት ላይ ተስማማን ከዚያም በተጨማሪ የሊቀመንበሩ የሥልጣን ዘመን ለስድስት ወራት ብቻ እንዲሆንና ከምርጫው በኋላ ሌላ ሊቀመንበር እንደሚመረጥ ከየድርጅቶቹ በዙር ተወሰነ ከዚህ በተጨማሪ ግን ይህ ጥምረት ከአሁኑ ታስቦበት ቀስ እያለ ወደ ውህደት የሚያመራ እንደሚሆን ይህም በስምምነት ሰነዱ ውስጥ እንዲጠቆስ ተደረገ አቶ ኃይሉ ሊቀመንበር ሲሆን ሌላ ኛ ሰው መመረጥ ያለበት ሲሆንም ከመኢአድ አስከ መጨረሻው ድረስ አልተመረጠም ነበር በቅንጅቱ ምሥረታ ጊዜ ድርጅቶቹን የወኩሉት በኢዴሊ ከተደረገ አንድ ቅያሬ በስተቀር የላእላይ ምክር ቤቱ አባላት እንዲሆነ ከየድርጅቶቻቸው ስማቸው ሲሰጥ ፕሮፌሰር መስፍን ምክር ቤቱ ውስጥ ለመቀጠል አልፈለገም ነበር በእሉ እምነት ከሞላ ጎደል መሰራት አለበት የሚለው የቅንጅቱ መፈጠር ጉዳይ ስላለቀ እሱ የቅንጅቱ ተራ አባል ሆኖ ከውጭ ሂስ እያቀረበና እያማከረ መቆየት እንደሚፈልግ የእለት ተእለት የድርጅት ፖለቲካ ውስጥ መሥራት እንደማይፈልግ ብቻ ሳይሆን ለዚያ የሚሆን ፀባይ ይፅፀወገፀፀ እንደሌለው ገልጾ በቦታው ሌላ ሰው እንዲተካ ጠይቆ ነበር ግን በጊዜው እንደዚህ ያለ ለጋ ድርጅት ቢያንስ እስከሚጠናከርና መቀጠሉም እርግጠኛ እስኪሆን የሞራል መሪ ያስፈልገዋል በሚል የሁሉም ድርጅት ተወካዮች በጠየቁት መሠረት ለተወሰነ ጊዜ ቀጥሏል ሥራ አስፈፃሚውን በሚመለከት በስምምነቱ መሠረት ኢንጅነር ኃይሉ ኢንጅነር ግዛቸውና አቶ ዓባይነህ ከመኢአድ ዶር አድማሱና ልደቱ ከኢዴአፓመድህን እኔና ዶር በፍቃዱ ከቀስተ ደመና አቶ ቸኮል ጌታሁን ከኢዴሊ ሆነን ተሰየምን በሥራ አስፈፃሚው ውስጥ የነባነት ጎህ ሲቀድ በተደረገ የሥራ ክፍፍል ደግሞ ልደቱ የሕዝብ ግንኙነት ዶር በናቀዱ ፋይናንስ እኔ የምርጫ ዘመቻ አስተባባሪ አቶ ቸኮል የአጩ ተመራጮች ምደባ ዶር አድማሱ የጽሕፈት ቤት ኃላፊነት ኢንጅነር ግዛቸው የምርጫ ችግሮች አስወጋጅ ሆነን ተሰየምን በአነዚህ ሰዎች ሊቀመንበርነት የሚመሩ ኮሚቴዎች ደግሞ ከላእላይ ምክር ቤት አባላትና ከየድርጅቶቹ ሌሉች አባላት ተጨምረው እንዲሰራ ተጠሰነ በመጨረሻም በአራቱ ድርጅቶች መሀክል ያሉት ልዩነቶች ጠብበው የድርጅቱ ፕሮግራም መተዳደሪያ ደንብና የዲሲፕሊን እርምጃዎች ሰነዶች ተዘጋጅተው የድርጅቱ መመሥረት አውን ለመሆን ሲቃረብ ለበኋላ ቆይቶ የነበረው የመኢዶፓ ቅንጅቱን የመቀላቀል ጥያቄ እንደገና ቀረበ በዚህ ላይ ኢደፓመድኅን በጣም የክረረ ተቃውሞ አቀረበ የተቃውሞው መሠረትም እነኝሀ መኢዴፓን የመሰረቱት ልጆች በአንድ ወቅት ኢዴአፓን ለማፍረስ የተንቀሳቀሱ እንደነበሩ ምንም የድርጅት ዲሲፕሊን የሌላቸው እንደሆኑና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስም በኢዴአፓ መድኅን ላይ መጥፎ የሀሰት ቅስቀሳ እያካሄዱ እንደሆነ በጥቀሉ ግን ቅንጅቱ ውስጥ ቢገቡ ቅንጅቱን የሚጎዱ እንደሆኑ አቀረቡ ከዚያም በላይ ግን ፊት ለፊትም ባይቀርብ ይህ ድርጅት ቅንጅቱን የሚቀላቀል ከሆነ ኢዴአፓመድኅን አባል ሊሆን እንደማይችል የሚጠቁሙ ብዙ ነገሮች ተነገሩ በመኢአድ በኩል ከተወከሉት ውስጥ ብዙዎቹ የዚህን ድርጅት መግባት አልጠሉትም ነበር በኤዴፓና በመኢዴፓ መካከል ስለተፈጠረው ችግር በዝርዝር የሚያውቁና በአንድ ወቅት እራሳቸው የኢዴፓ አባል የነበሩ ከዚሁ ጭቅጭቅ ጋር በተያያዘ ኢዴፓን የለቀቁ ሰዎችም ነበሩበት እነዚህ ሰዎች በዚያ ልዩነት ምክንያት መኢዴፓን አለማስገባት ኢፍትዛዊ ነው ብለው ያምኑ ነበር በቀስተ ደመና በኩል የነበርነው ሰዎች በመርህ ደረጃ አንድ ድርጅት ሌላ ድርጅት ቅንጅቱ ውስጥ እንዳይገባ ሰብቻው መክሳከል አይችልም የሚል ስሜት ነበረን ከዚያም በላይ ግን ብዙውን ጊዜ በድርጅቶች ውስጥ ተነሱ የሚባሉ ጭቅጭቆች በግለሰቦች ፀባይ ዙሪያ ያጠነጠኑና በመርህ ላይ ያልተመሠረቱ መሆናቸው ልዩነቱ ከተፈጠረ በኋላም ብዙ ሀሰት የሆኑ ነገሮች ከትንሽ እውነት ጋር ተደባልቀው እየገዘፉ የሚሄዱ እንጂ ጭቅጭቆቹ የተጀመሩባቸው ጉዳዮች አነስተኛ እንደሚሆኑ ጥርጣሬ ስለነበረንና ከዚያም በላይ ግን በቅንጅት ውስጥ እንዲፈጠር የምንፈልገው መንፈስ ከእንዲህ ዓይነት ትንንሽ ጭቅጨቅ የፀዳ መቻቻልንና ይቅር ጾር ብርዛኑ ነጋ ባይነትን የተቀበለ መሆን አለበት ብለን ስለምናምን ኢዴአፓመድኅን የቀድሞ ልዩነቱን ችላ ብሎ ይህ ድርጅት ቢቀላቀል ጥሩ ነው ብለን ተከራክረናል በመጨረሻ ግን የኢዴአፓመድኅን ተቃውሞ በጣም ሥር የሰደደ ስለነበርና አኛም ከወጣቶቹ ይልቅ የኢዴአፓመድኅን አዛውንቶች በጉዳዩ ላይ ያላቸውን አመለካከት ጠይቀን በዚህ ጉዳይ ላይ የእነሱም እምነት እንደነ ልደቱ ጠንካራ ስለነበር የሚያቀርቡትን ክስ በዝርዝርና ከማስረጃ ጋር እነዲያቀርቡ ጠይቀንና በክሱና በማስረጃው ላይ ተወያይተን መኢዴፓ ለጊዜው ቅንጅቱን እንዳይቀላቀል ወሰንን በመጨረሻም የሚቋቋመውን የአራቱን ድርጅቶች ቅንጅት ምን ስም እንስጠው በሚለው ላይ የተለያዩ አማራጮችን ተመልክተን ስሙ የድርጅቱን መሠረታዊ እምነቶች የሚያንዐባርቅ ቢሆን ጥሩ ነው በሚልና በዚህም ዙሪያ የድርጅቱ ሁለት መሠረታዊ የፖለቲካ እምነቶች እውነተኛ ዴሞክራሲና የአገር የዜጎች አንድነት መሆኑ ታውቆ ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ የሜለው ስም ተመረጠ የድርድቱን መሠረታዊ ዶክመንቶች ለመፈራረምና የድርጅቱን ሥራ ለመጀመር የቀስተደመና እንደ ሕጋዊ ድርጅት መቋቋም አስፈላጊ ስለሆነ ይህንን ሂደት ቀስተደመና በአስቸኳይ ጨርሶ መስራች ስብሰባው ለጥቅምት ቀን እንዲጠራ ተወስኖ ስብሰባው ተጠናቀቀ የቅንጅት ምስረታ በዚህ መልክ ያለ ብዙ መሰናክል መጠናቀቅ አሁን ወደ ኋላ ተመልሼ ሳየው በእውነት የሚገርም ነው ቅንጅቱ ከተመሠረተ በኋላ የተፈጠሩትን ችግሮች ሳጤንና በተለይ በሁለቱ ትልልቅ ድርጅቶች መሀከል የነበረውን ሥር የሰደደ አለመተማመን ስመለከት የቅንጅት አፈጣጠር በራሱ በአንፃራዊነት ሲታይ በጣም ቀላል ሂደት ነው ለማለት ይቻላል ይህ ሊሆን የቻለው ደግሞ በጊዜው ሁለቱም ድርጅቶች የቅንጅትን መፈጠር በየራሳቸው ምክንያት በጣም ይፈልጉት የነበረ በመሆኑ እንደሆነ መገንዘብ አያዳግትም ሁለቱ ድርጅቶች ኅብረቱን ከለቀቁ በኋላ ለየብቻቸው ነበሩ ሁለቱ ድርጅቶች በግላቸው ተነጋግረው ወይም በሦስተኛ ወገን አስማሚነት ምንም ዓይነት የመተባበር ስራ ለመሥራት የሚያስችላቸው አነስተኛ እንኳን ትን ፍላጎት ዐፀሀ አልነበራቸውም ነገር ግን እርስ በእርስ ከተወዳደሩ ደግሞ ውጤቱ መጥፎ እንደሚሆንባቸው ያውቃሉ ምርጫው ደግሞ በጣም በከፍተኛ ፍጥነት እየተቃረበ ነው ከዚህ አጣብቂኝ የሚወጠበት ተዓምር ሲፈልት ነው የቀስተ ደመና ሙከራ ጠሀፀ የተደመረው ሁለቱም በየራሳቸው ምክንያት በቀስተ ደመና የነባነት ገህ ሲቀደድ ሥር የተሰበሰቡትን አዛውንቶች ገለልተኛነት ቢያንስ በሁለቱ ግጭት ውስጥ የተቀበሉ ይመስለኛል ኢዴሊም አንዱን በተለይ ይወግናል ተብሎ የሚጠረጠርበት ምንም ምክንያት አልነበረም ሁለቱም ከዚያ ቀደም በነበራቸው ከድርጅቶች ጋር የመሥራት ልምድ አውነተኛዎቹ ችግሮት በኋላ ዝርዝር ላይ ሲመጣ የሚከሰቱ እንደሆነ የሚያውቁ ይመስለኛል እዚያ ዝርዝር ላይ ሲመጣና ግጭቶች ሲፈጠሩ በመሀል ሆነን የምንዳኘው እኛ እንደሆንን ስለሚያውቁ ሁለቱም በየራሳቸው ከእኛ ጋር ከቀስተ ደመናም ከኢዴሊም የቀረበ ግንኙነት ለመፍጠር በተለያየ መንገድ ይሞክሩ ነበር አንዱ ስለሌላው በድርጅት ደረጃም ሆነ በተለይ በግለሰብ ደረጃ ስላለባቸው ችግሮች ብዙ ብዙ ሰምተናል በዚህ ጊዜ ሁሉ በተቻለን መጠን ክፍት አእምር ይዘን ከመስማትና ስለድርጅቶቹም የበለጠ ለማወቅና ለመማር ከመፈለግ በቀር በተቻለ መጠን አድሏዊ ግንዛቤ ላለመያዝ ላለመሆን ከምር ጥረናል በእኛ እምነት ቅንጅት ከተፈጠረ በኋላ የሚነሱ ችግሮች እያንዳንዳቸው ጉዳዮች በራሳቸው ጥቅምና ጉዳት ታይተው የሚመዘኑ እንዲ ከኋላ የተደበቀ ሌላ ስሌት አለ ብሎ መፈለግ ለመፍትሄ አስቸጋሪ እንደሆነ አምነናል በተወሰነ ደረጃም በፍጹም የዋህነት ማንኛውም ችግር በአምክንዮ መለኪያ ርየፀ ያፀ መፍታት ይቻላል በተለይ ወገንተኛ ባለመሆን እና በቀና አሳቢነቱ የተገኝው የሞራል የበላይነት እንዳለ ከቆየ ብለን አምነናል ከዚያ በላይ ግን ቅንጅቱ ሲመሠረት የተሰማማንበት አንድ የውሳኔ አሰጣጥ መመሪያ ለዚህ ሂደት ጠቃሚ ይሆናል ብለን አስበናል ይኸውም በላእላይ ምክር ቤቱም ሆነ በሥራ አስፈፃሚው ውስጥ በየድርጅታቸው የተወከሉ ሰዎች አንዴ ከተወከሉ በኋላ እንደ ግለሰብ ማሰብና ውሳኔ መስጠት ይጠበቅባቸዋል የሚለው መመሪያ ነው ይህም ማለት የአንድ ድርጅት ወኪሎች የመጡበትን ድርጅት አቋም ለማንፀባረቅ አይደለም መምጣት ያለባቸው እንዲያውም በቅንጅት ስብሰባ የሚወሰኑ ጉዳዮች ይህን አስፈላጊ የሚያደርግ የተለየ ሁኔታ ካልተፈጠረ በስተቀር የድርጅት አቋም ተብሎ የሚመጣ ነገር ሊኖር አይገባውም ይህም ማለት በስብሰባ ላይ እንደሚነሳው ጉዳይ የአንድ ድርጅት ተወካዮች የተለያየ አቋም ሊይዙ በዚህም ምክንት ድምጽ ሊሰጡ ይችላሉ ማለት ይህንም የቅንጅቱን አመራር የበለጠ ያቀራርበዋል «ድርጅታዊ ጥቅም» የሚባልን ጥቅም ወደ ኋላ ያስቀራል ስለሆነም አመራሩ ከምንም በላይ ለቅንጅቱ እንዲያስብ ያደርገዋል ይህ በጽሁፍ ያልወጣ መመሪያ በእርግጥም በብዙ ጾር ብርፃኑ ነጋ ጥያቄዎች ዙሪያ የተዘበራረቀ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት እንዲታይ አድርጎታል የመኢአድ ተወካዮች የተለያየ አቋም የያዙበት በኢዴአፓ መድኅንም ሆነ በቀስተ ደመና ሁሉም የድርጅት አባል አንድ ዓይነት ድምጽ የማይሰጥበት ሁኔታ በጣም የተለመደ ነበር ለማለት ይቻላል ይህም ሆኖ ግን ቆየት ባሉት ድርጅቶች ውስጥ የነበረው ድርጅታዊ ባህል የአሠራር ልምድ የአስተሳሰብ ይዘት አዲሱ ድርጅት መሠረት ካደረጋቸው ቢያንስ ከላይ የጠቀስኳቸው በቀስተደመና ውስጥ ታምነውባቸው የቀረቡት የአስተሳሰብና የአደረጃጀት ፍላጎት ጋር ሙሉ ለሙሉ እንደማይጣጣምና ይህንን የቀድሞ ባሕል በአዲሱ አመለካከት ለመቀየር ብዙ ጊዜና ሥራ እንደሚጠይቅ ተገንዝበናል በቀስተደመና ውስጥ የተሰባሰብነው ሰዎች ሁላችንም በራሳችን በሁለት እግራችን የቆምንና በግል ጠንካራ እምነቶች ያሉን በመሆናችን በማንኛውም ጉዳይ ላይ የሚደረግ ውይይት በእኩልነት መንፈስና በጠንካራ ፍጭት ነበር የሚወሰነው በዚህ አጋጣሚ ብዙ ጊዜ ከውጭ ስንሰማ ፕሮፌሰር መስፍን ቀስተ ደመናን በኋላም ቅንጅትን ከኋላ ሆኖ የሚያሽከረክረው እንደሆነ ተደርጎ ሲወራ ነበር የመንግሥትም አመለካከት ይህ ሳይሆን አይቀርም አለበለዚያ ከምርጫው ቢያንስ ከሁለት ወራት በፊት በየትኛውም የቅንጅት ስብሰባ ላይ ተገኝቶ የማያውቅና ከላዕላይ ምክር ቤት እንዲሁም ከቀስተ ደመና ሥራ አስፈፃሚነት ለሦስት ወራት ያህል ብቻ ከሰራ በኋላ በራሱ ፍላጎት በተወሰነ ደረጃ በቅሬታ ከኃላፊነቱ የወረደን ሰውና በየትኛውም ክስ በቀረበባቸው የቅንጅት ውሳኔዎች ላይ ያልተገኘን ሰው ማሰር ባላስፈለገም ነበር ነገር ግን በቀስተ ደመና ክርክሮች ፕሮፌሰር መስፍን አንድ ጠንካራ አመለካከት ያለው ሀሳቡን አጠንክሮ መግለጽ የሚትል አባላችን ነበር ለድርጅቱ ብዙ ሀሳቦችን ያበረከተውን ያህል በብዙ ሌሎች ሀሳቦች ላይ ደግሞ የእሱ ሀሳብ ተቀባይነት ያለገኙባቸውና የወደቀባቸው ጊዜያት ነበሩ የእኔ ፃሳብ የግድ ካልሆነ ብሎ አያስቸግርም የእሱ ፃሳብ ሲሳሳት ደግሞ ተሳስተሀል ለማለት ወደ ኋላ የሚል አልነበረም በቀስተ ደመና ውስጥ የአመለካከት አንድነትና በመሀከላችንም የነበረው የመከባበር ግንኙነት ከጓደኝነትም በላይ ስለነበር የተሳሳተ ሃሳብን በይሉኝታ የማያሳልፍ ነበር በተጨማሪ የዳበረ ጓደኝነትም ስለነበር እክሌ የድርጅቱ መሪ ነው ብሎ የሚወጣ ግለሰብም አልነበረም ቀስተ ደመና ሲቋቋምም እኔ ሊቀመንበር የሆንኩት ከሌሎቹ ስለተሻልኩ ሳይሆን ድርጅቱ ብዙ ስለማይቆይ እና ለጊዜው የቅንጅት ጉዳይ አልቆ መስመር እስከሚይዝ ጉዳዩን ለማቀላጠፍ የነቫነት ገህ ሲቀደድ ያህል ከውስጣችን የነበርኩት «ወጣት» እኔ ስለነበርኩ ነው ቅንጅቱ ሲፈጠር በሁለቱ ድርጅቶች ላይ ያየነው ከዚህ እኛ ከለመድነው የተለየ ነበር በድርጅቶቹ ላይ ጠንካራ ተጽእኖ ለማሳረፍ የሚችሉ ግለሰቦች የነበሩበት ምክንያትም ለድርጅቱ ባላቸው አስተዋጽዖና በዚህም ምክንያት ያገኙት ክብር ሊሆን ይችላል ይህም ቢሆን ግን ለውስጥ ድርጅት ዴሞክራሲ እንዲህ ዓይነት የግለሰብ ተጽዕኖ ጤነኛ እንዳልሆነ እንገምታለን አቶ ኃይሉ በመኢአድ ውስጥ ያለው ተሰሚነት ልደቱ በኢዴአፓመድኅን ላይ የነበረው ሁሉን አቀፍ ይዞታ ዛዐ በፍፁም እኛ ከምንመኘው ጋር የሚሄድ አልነበረም ይህ ሁሉ ግን ሰፋ ያለ ጠንካራ አመራር ሲፈጠር እየሰለለ ይሄዳል የሚል እምነት ነበረን በዚህም ላይ ብዙ አልተሳሳትንም በኋላ እንደምናየው የቅንጅቱ አመራር ከነችግሮቹ በእውነትም የቡድን አመራር ነበር ከመጀመሪያው ጀምሮ ማንም አንድ ሰው የፈላጭ ቆራጭነት ቀርቶ የበላይነት ዐዐበህፀ ሚና እንኳን ሳይኖረው ቆይቷል በተጨማሪም ያየነው በልሂቁ ከፖለቲካው መሸሽ ምክንያት የየድርጅቶቹ የሰው ኃይል ጥንካሬ ከገመትነው ያነሰ መሆኑን ነበር በብዙው አባላት በተወሰነ ደረጃ በመሀክለኛና ከፍተኛ አመራር ደረጃም ያሉትንም ጨምር ዘንድ ድርጅቶቹ የነበራቸው የአመሠራረት ታሪክም ተጨምሮበት ለዴሞክራሲ ለመታገል ያለው ቁርጠኝነት በተወሰነ ደረጃም በኢህአዴግ ለደረሰው በደል ከመቆጨት ውጪ ጠንካራ የፖለቲካ ትንተና ችሎታ ነበር ለማለት አያስደፍርም ከዚህ አንፃር በመጠኑም ቢሆን የኢዴአፓመድኅን አመራር የተሻለ ነበር ለማለት ይቻላል በመኢአድ በኩል ጠንካራ የማደራጀት ችሉታ ለትግሉ ያላቸው የልብ ድጋፍ በተወሰነ ደረጃም እውነተኛነት ያለውን ያህል በንድፈ ሀሳብ ደረጃ ሊነሱ የሚችሉ የፖለቲካ ጥያቂዎችን ለመመለስም ሆነ በዴሞክራሲ ዙሪያም ያሉትን በተለይ ከአገራችን ሁኔታ አንፃር ሊነሱ የሚችሉትን የተለያዩ ዝርዝር ትንተናዎች በሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ የጠለቀ አስተያየት ለመስጠት የሚችሉ በተለይ የመሀከለኛ ካድሬዎች ችግሮች ነበሩባቸው ይህም ሆኖመቀናጾቱ የአንዱን ድክመት የአንዱ ጥንካሬ ለመሸፈን በመቻሉ ቅንጅቱ እንደ ድርጅት ሲወጣ ከአራቱ ድርጅቶች ድምር በላይ ሆኖ ነበር የወጣው ይህም ሆኖ ግን የከፍተኛና የመካከለኛ አመራር ክፍተት ሊኖር እንደሚችል ድርጅቱ እየሰፋ ሲፄድ መገመት አይከብድም ነበር በዚህም ምክንያት በቀስተ ደመና በኩል በጣም በቶሉ ጥሩ ትምህርትና ጾር ብርፃኑ ነጋ ግንዛቤ ያላቸው በመሀከለኛ እድሜ የሚገኙ ቢቻል የተወሰነ የፖለቲካ ልምድ ያላቸው ሰዎች መመልመል ማስፈለጉን በማመን በዚህ ዙሪያ የተቻለንን እንቅስቃሴ ማድረግ ጀመርን ቅንጅት እንደተፈጠረ የታዘብነውና በቶሉ ካልተቋቋምነውም ወደፊት የድርጅቱን ዴሞክራሲያዊነት ከዚያም በላይ አጠቃላይ የውስጥ ጤንነቱን ይፈታተነዋል ብለን የፈራነው የወሬና የሀሜት ባህል ነው ይህ በተወሰነ ደረጃ በፍርሃት ማኅበረሰቦች ዓይነተኛ መለያ የሆነውና በአገራችንም በጣም የተንሰራፋው ባህል በድርጅቶች ውስጥ ክፍትነት ዐዐፀበበ ማጣት የሚፈጥረው ነው በአመራር ደረጃ በርካታ የድርጅቱን ሕልውና የሚነኩ ነገሮችን በውይይት መፍትሄ መስጠት ሲቻል ጉዳዮች አዙር በሀሜት ደረጃ እንሰማቸዋለን ለወሬዎቹ ማስረጃ አምጡ ሲባል በምሥጢር» የተገኘ ወሬ ስለሆነ ማስረጃ ሊቀርብባቸው አይችልም ይባላል ታዲያ በእንዲህ ዓይነት ማስረጃ በሌለው ወሬ ላይ ተመስርቶ ምን ዓይነት ውሳኔ እንዲወሰን ይጠበቃል። ይህ አካሄድ ለዴሞክራሲያዊ ድርጅት የሚበጅ አይደለምና በተቻለ መጠን ሁሉንም ነገር ፊት ለፊት ለመናገር የሚያስችል ክፍትነትና ደፋርነት ያስፈልገናል የሚል አቋም ነበረን ስለዚህም ከማንኛውም አቅጣጫ ወሬ ሊመጣ በተቻለ መጠን ወሬውን በፊት ለፊት አውጥተን ምን ያህል እውነትነት እንዳለውና ወሬውም የውስጥ አንድነታችንንና ንጽህናችንን የሚያጎድፍ ነው ብለን ካመንን አመራሩን በመጠየቅ በዚያ ላይ አቋም እንዲወስድ ለማድረግ እንሞክራለን በዚህ ዙሪያ ዓይነተኛ ምሳሌ ሆኖ የሚቀርበውና በተለይ ከጥቅምት በኃላ ብዙ ሰው ጥያቄውን እንደገና እንዲመረምር በተደረገበት የልደቱ ምንነት ላይ የሚነሱ ተደጋጋሚ ወሬዎች ናቸው በመኢአድ እና በኢዴአፓመድኅን መካከል የሚነሱና በተለያየ ጊዜ የተነሱ ጥያቄዎች በአብዛኛው በልደቱ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ናቸው የመኢአድ ሰዎች ልደቱ የሚያደርገውን ነገር ሁሉ በከፍተኛ ጥርጣሬ ነበር የሚያዩት በተለይ እጩ ተወዳዳሪዎችን በማቅረብ ዙሪያ በተነሱ ከፍተኛ ጭቅጭቆች የዚህን ዝርዝር በኋላ እመጣበታለሁ የመኢአድ ሰዎች ልደቱ መኢአድን ለማዳከም ሆን ብሎ የሚያደርገው ይህም ከዚህ በፊት መአህድን ለማዳከም የወሰዳቸው እርምጃዎች ቀጣይ እንደሆነ ይህንንም የሚያደርገው በመሠረቱ የኢህአዴግ ሰሳይ ስለሆነ ነው ብለው ያምናሉ ይህንንም የነፃነት ገህ ሲቀድ በተደጋጋሚ ለእኛም ለኢዴሊ ሰዎችም ይናገራሉ እንዲህ ዓይነት ነገር በውስጣቸው እያመኑ እየጠረጠሩ ከዚህ ሰው ጋር አብሮ ለመሥራት ችግር ነው የሚሆነው ስለዚህ የዚህን ጉዳይ እውነትነት ወይም ሀሰትነት በግልጽ መወያየት አለብን በማለት ደብረዘይት አንድ ሙሉ ቀን ባደረግነው ስብሰባ ላይ ጉዳዩን ፊት ለፊት ለውይይት አቀረብነው በመኢአድ አባሎች በኩል በማስረጃነት የቀረበው ከዚህ በፊት መአህድ እያለ አንድ በደኅንነት ሥር በሚንቀሳቀስ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ ይሠራ ነበር በዚህ ወቅትም ለደኅንነት ተመልምሎ ነበር ምንም እንኳን ከጥቂት ወራት በኋላ ከዚያ መስሪያ ቤት ቢለቅም ከዚያን ጊዜ ጆምሮ በተቃዋሚዎች መሀከል በመአህድ ላይ ልዩነት ለመፍጠርና ለመከፋፈል የሚወስዳቸው እርምጃዎች ስላሉ አሁንም ለደህንነት ይሠራል የሚል ጥርጣሬ አለን የሚል ነው ከዚህ ውጭ ግን ከዚያን በኋላ ለደህንነት መስራቱን የሚያረጋግጥ ምንም ማስረጃ አልቀረበም ልደቱ ለዚህ የሰጠው መልስ በእርግጥ በጊዜው እዚያ መሥሪያ ቤት ውስጥ ለጥቂት ወራት መሥራቱን ሆኖም በሚቀጠርበት ጊዜ ይህ መሥሪያ ቤት የደህንነት መሥሪያ ቤት መሆኑን እንደማያውቅ በመሥሪያ ቤቱም ሥራ ለመቀጠር የሥራ ማስታወቂያ አይቶ ማመልከቱን ይህንንም ማመልከቻ ሲያቀርብ ከመአህድ አመራሮች ውስጥ ለሁለቱ መንገሩንና እነሱም እንደደገፉትና የድጋፍ ደብዳቤ እንደፃፉለት አንዴ ሥራውን ከጀመረ በኋላ የመሥሪያ ቤቱን ምንነት እየተረዳ የደኅንነት ሰዎችም አብሯቸው እንዲሠራ በጣም ስላስቸገሩት በፍጹም አላደርገውም ብሉ ሥራውን ጭራሽ ትቶት እንደወጣ ከዚያም በኋላ ከዚያ መሥሪያ ቤት ጋርም ሆነ ክደህንነት መስሪያ ቤቱ ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌላው እንዲያውም ይህ እየታወቀ ይህን ወሬ አሁን ድረስ የመኢአድ ሰዎች የሚያናፍሱት የእሱን የፖለቲካ ስብዕና ጥላሸት ለመቀባት እንደሆነ እና ይህም በፍጹም ተቀባይት እንደሌለውና አንዲህ ዓይነት ወሬዎች ለቅንጅቱ አካሄድ አደገኛ እንደሆነ በከፍተኛ ስሜት አስረዳ ጉዳዩም በቂ ማስረጃ በሌለበት አንዲህ ዓይነት ጥርጣሬዎች መያዝ በውስጣችን ያለውን ግንኙነት እንደሚጎዳና ወደፊትም ምንም ዓይነት ጥርጣሬዎች ሲናሩ በሆድ ይዞ ከመቆየትና በድርጅቱ ውስጥ ሀሜት ከማስፋፋት ፊት ለፊት መነጋገሩ እንደሚጠቅም ተስማምተንበታል ምንም እንኳን የወሬና የሀሜት ባህል ከድርጅቱ ተወግዲል ለማለት ባይቻልም ከዚያም በኋላ ወሬ የሚያወሩ ሰዎችን ጾር ብርፃኑ ነጋ ማስረጃቸውን እንዲያቀርቡ ወይም ወሬውን ያወራውንና የተወራበትን ሰው በአንድ ላይ በማምጣት የወሬውን እውነተኛነት ለማረጋገጥ የተደረጉ ሙከራዎች ይህንን የውስጥ ድርጅት ዴሞክራሲ የሚቦረቡር ነቀዝ ባህል መረን እንዳይለቅ ለማድረግ ተሞክሯል ከቅንጅት መፈጠር እስከ ምርጫ ዘመቻ መጀመር ከባድ ይሆናል ብለን የፈራነው የቅንጅት መፈጠር በአንፃራዊ ደረጃ በትንሽ ችግር ከተጠናቀቀ በኋላ ወዲውኑ ብዙ በቅጡ ያልተቋጩ ነገሮች የጎሉ ችግሮች እየሆነ መጡ የቅንጅት መመሥረት በታላቅና ደማቅ ዝግጅት በግሎባል ሆቴል ጥቅምት ከተጠናቀቀ በኋላ እንደጠበቅነው በቅንጅቱ መመሥረት በጣም የተደሰቱም በጣም የተከፉም ኃይሎች የመጀመሪያውን ሳምንት የሚዲያ ሽፋን ተቆጣጠሩት በሕብረቱ መመሥረት የተደሰቱና ሕብረቱን እንደ ብቸኛ መፍትሔ የቆጠሩት ኃይሎች ደስተኛ አልነበሩም የተቃዋሚዎችን አንድነት በጥቅሉ ይፈልጉ የነበሩ ኃይሎችም የተቃዋሚው ኃይል በእነፒህ ሁለት ቡድኖች ቅንጅትና ሕብረት መከፈል አስደስቷቸዋል ማለት አይቻልም ከዚያ ውጪ ግን ቅንጅት ይዞ የመጣውን ግልጽ ዘውግ ዘለል ፖለቲካ የተስማማቸውና ይህንንም ሲጠብቁ የነበሩ ብዙ ሰዎች መደሰት ብቻ ሳይሆን ከገመትነው በላይ በብዛት ሊቀላቀሉ መፈሰጋቸውን ስናይ በእርግጥም ሕዝቡን ሊያነቃቃ የሚችል ነገር ይዘን እንደተነሳን ያረጋገጠልን ነበር ከዚያም በላይ ሚዲያውን በደንብ መጠቀምና ዓላማችንን ለሕዝቡ በግልጽ ማሳወቅ አስፈላጊነቱን በጣም ስላመንንበት በተለይ አዳዲሶቹ ፖለቲከኞች ለግሉ ሚዲያ ሰፋፊ ቃለመጠይቆችን መስጠት ጀመርን በአጭር ጊዜም በተለይ በግል ጋዜጦች የነበረውን አንዳንድ አሉታዊ ሽፋን ለማለዘብ ቻልን ድጋፋቸውን እንኳን ባይሰጡን በክፍት አእምሮ እንዲከታተሉን አደርግናቸው በሕዝብ አስተያየት ዘንድ የነበረውን የመጀመሪያው አንዳንድ አሉታዊ ስሜት በዚህ መልክ ተከላክለን ወደ ሌሎች ሥራዎቻችን ገባን ይህ ግን ከገጠሙን ችግሮች በጣም ቀላሉ ነበር ትላልቆቹ ችግሮች በውስጣችን የነበሩት ናቸው ቅንጅት በጥቅምት ማለቂያ ተፈጥሮ የምርጫው ዋና ዘመቻ ለመጀመር የቀረው ከሦስት ወር ያልበለጠ ጊዜ ነበር በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ የነፃነት ገህ ሲቀድ በጣም ብዙ መሰራት ያለባቸው ነገሮች ነበሩ ስለዚህም ገና በከፍተኛ አመራር ደረጃ የተሠራው መዋቅር ወደታች ወርዶ ሌሎቹን የድርጅቱን እርከኖች ለማዋቀሪያ ጊዜ እንኳን ሳይኖር ነበር የምርጫው ጉዳይ ያጣደፈን የጀመረው በዚህም ምክንያት ገና ከመጀመሪያው በግልጽ በተቀመጡ ድርጅታዊ መስፈርቶችና የአሠራር መመሪያዎች ሳይሆን ብዙውን ነገር ዝም ብሎ በመተማመን ነበር የሚሠራው በመጀመሪያ ለቅንጅቱ የሚሆን ቢሮ መፈለግና ቢያንስ የቅንጅቱን አመራር በአንድ ቦታ ላይ አሰባስቢ መሥራት አስፈላጊነቱን ስላመንንበት ቢሮ መፈለግ ተጀመረ አሱም ቢሆን ግን በፈለግነው ፍጥነት እየሄደ አልነበረም በመጨረሻ ያገኘነው ቦታ ለቅንጅቱ ይተልቃል በሚልና ቀስተደመናም ለራሱ ቢሮ እየፈለገ ስለነበር ቦታውን በመከፋፈል አነስተኛውን ቦታ ቀስተደመና ትልቁን ቦታ ቅንጅት አንዲከራየውና በየደረሳቸው ካሬ ሜትር መሠረት የቤት ኪራዩን አዋጥተው እንዲከፍሉ ተወስኖ ሻላ አዳራሽ አጠገብ ያለውንና በፖሊስ ኃይሎች ተሰብሮ እስከሚዘረፍ ድረስ የቅንጅቱ ቢሮ የነበረውን ቦታ ተከራየንቃ የቅንጅቱን ቢሮ የሚያውቁ ሰዎች ምን ያህል ትንሽ ቢሮ እንደሆነ ያውቃሉ ቅንጅት ሲጀመርና እስከ መጨረሻውም በጣም ከባድ የገንዘብ ችግር ነበረበት የሁለቱንም ቢሮዎች ኪራይ በወር ብር ነበር ቅንጅቱ በአንድ ላይ ለመያዝ አቅም ስላልነበረውም ነው ለመጋራት የተወሰነው የቤቱን የስድስት ወር ኪራይ ለመክፈል የሚያስፈልገውን ወደ ሺህ ብር የቅንጅቱን ድርሻ የሚሆን ገንዘብ ለመክፈል አራቱ ድርጅቶች እንዲያዋጡ ሲጠየቅ ኢዴሊ መክፈል አልችልም በማለቱሦስቱ ድርጅቶች በብዙ ጉትቶታ ነበር ያዋጡት ቢሮውንም ከተከራየን በኋላ ለቢሮ እቃ እና ለሌሎች ወጪዎች ገንዘብ ማግኘት በተለይ በመጀመሪያው ጊዜ ቀላል አልነበረም ቢሮውም ከተከፈተና አሮጌ የቢሮ እቃዎችም ከገቡ በኋላ የድርጅቱን አመራር ወደ አዲሱ ቢሮ እንዲመጣ ማድረግ ቀላል አልነበረም ሁሉም በየእናት ድርጅቱ ቢሮ መቆየትን ነበር የሚመርጠው የድርጅቱ አመራር አንድ አካባቢ ሆኖ መሥራቱ ለብዙ ነገር ይጠቅማል የሚለው ሀሳብ በየስብሰባው አ ሏ ለዚሀ ደሮ ፊታ ፇ ቃዕፖ ደመና ሐራታ ሷረሪ ዳዖፈሰሃ ረበፖ ሂሼዜ ቀድም ይመድሀ ፈሮ ጋያረው»ና ፅዚያ ቋቋ ጴዴጳፓ ጋር ፈዎምኃቶ ቦ ጥም ፖቀምጦ ያነገረው ሦኃሔ ጤናው ሕንፃ ውፅዕጥ ያሃረውፇ ዲሮ ያሏዴላፓ መድሃሀሃ ለመራረ ፅነዖፃ ላ ኃድኋወፇሃም ፊቆደውጳንጋ ነገር ፇ ሰማሃም ድርሯፖ ጾሮታ ማፇኘራ ሰጎሰፈሐፇሃ ሰመድመሪቦባው ምጋ ንሰ እይነፈሳ እ ፊኃጠፇምሃታ ጎበር ጾር ብርፃኑ ነጋ ላይ ቢነሳም ብዙዎቹን ከቀድሞ ቢሯቸው ማምጣት አልተቻለም ነበር በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙም ያልተቸገረው ዶር አድማሱ ነበር ጽሕፈት ቤቱ ስለሚመለከተውም ቅንጅቱንም ከልብ ስለተቀበለ ቢሮው ከተመሠረተ ጆምሮ በአዲሱ ቢሮ ነበር የሚሠራው ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አቶ ኃይሉ ግማሽ ቀን ቅንጅት ቢሮ መሥራት ጀመረ ቀስተ ደመናም ዋናውን ቢሮውን ወደዚህ ስላዞረ የቀስተ ደመና ተወካዮች ሁልጊዜ ቢሮው አካባቢ ነበርን ምንም እንኳን የሁሉም ኮሚቴዎች ቢሮ አዚሁ አዲሱ ቢሮ እንዲሆን ቢወሰንም ይህም ለረጅም ጊዜ አልተሳካም ነበር ለምሳሌ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው ልደቱ በስብሰባዎች ለመገኘት ከምርጫው በኋላ ደግሞ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠትና አንዳንዴም ለመፃፍ ይመጣ ነበር እንጂ የቅንጅቱን ጽቤት ቢሮዬ ብሉ አንድም ቀን ሰርቶበት አያውቅም በሁለቱ ድርጅት ውስጥ የነበሩት ሰዎች በዚህን ጊዜ በየእናት ድርጅታቸው ሥራ በተለይ በኋላ የቅንጀቱ ራስ ምታት የሆነውን ተወዳዳሪ አጩዎችን በማዘጋጀቱ ሰፊ ሥራ ላይ ተጠምደው ነበር ይህም ሆኖ ግን በአመራር ደረጃ ላይ የነበሩት ሰዎች አይምጡ እንጂ ለምርጫው ዝግጅት ለማድረግ ሲባል ከሁለቱ ድርጅቶች የተውጣጡ የቀጠና ኃላፊዎች በቋሚ ሠራተኛነት ድርጅታቸው ደሞዝ እየከፈላቸው በቅንጅቱ ቢሮ መሥራት ጀምረው ነበር እነዚህ ሰዎች በተወሰነ ደረጃ አብረው በመሥራት በውስጣቸው የነበረውን አለመተማመን እየጣሱ ራሳቸውን እንደ ቅንጅት አባሎች መቁጠር ጀምረውም ነበር የቢሮው ሥራ መጀመርና የቋሚ ሠራተኞች መኖር በተወሰነ ደረጃ የቅንጅቱን ሥራ ያስጀምር እንጂ አሁንም ፊት ለፊት የማይወጡ ግለሰባዊና ግለ ድርጅታዊ ስሜቶች ውስጥ ለውስጥ ይንፀባረቁ ነበር ነገር ግን የምርጫው ጊዜ እየተቃረበ መምጣቱ እነፒህን ውስጥ ለውስጥ እየፈሉ የነበሩ ጉዳዮችን በቂና መዋቅራዊ ትኩረት በመስጠት ለመመለስ ብዙ ለመሞከር ሳይቻል ቀረ ይልቁንም በጊዜው ብዙውን ሥራ የሚሠራው በመተማመን ደረጃ ስለነበር ቅንጅቱ ያወጣቸውን የተለያዩ የውስጥ ሕጎች ለምሳሌ የዲሲፕሊን መመሪያ እና መመሪያዎች ለመጠቀምና የሚነሱ ችግሮችን በአነዚሁ መመሪያዎች መሰረት ለመፍታት አልተሞከረም ይልቁንም ቅንጅቱን በመመሥረት ሂደት በእጅጉ የጠቀመንን «የሞራል ግፊት» በመሳሪያነት በመጠቀም ችግሮቹን ከሥራቸው ከመፍታት ይልቅ ልዩነቶችን የማቻቻል ትልቅ ጥረት አድርገናል ይህ አካሄድ የተወሰነ መንገድ ድረስ አስኪዶናል ግን እውነተኛዎቹ የግል ድርጅት ጥቅሞች» የነፃነት ገህ ሲቀድ ፊት ለፊት አግጥጠው መምጣት ሲጀምሩ በሞራል ግፊት ብቻ ሊፈቱ እንደማይችሉ ግልጽ ሆነ የዚህ የሞራል ግፊት መሠረት የነበረው ፕሮፌሰር መስፍንም አንድ ቦታ ላይ ሲደርስ ከሚችለው በላይ ስለሆነበት በአመራሩ ስብሰባዎች ላይ ላለመገኘት ወስኖ ከላዕላይ ምክር ቤቱ ወጣ የመጀመሪያውና ምናልባትም ቅንጅቱን ከገጠሙት ችግሮች ሁሉ ከፍተኛው በብዙ ሰዎች እንቅልፍ ያሳጣ ጥረትና ፊት ለፊት የማይታይ ኃይል የፈጠረው ተዓምር ባይጨመርበት ኖሮ ቅንጅቱን አፍርሶት የነበረው ችግር ለምርጫው እጩ ተወዳዳሪዎችን በማቅረብ ሂደት ውስጥ የተፈጠረ ነበር እንደሚታወቀው ቅንጅቱን መፍጠር ያስፈለገበት ከምርጫው ጋር የተያያዘው ዋናው ምናልባትም ብቸኛው ምክንያት በተቃውሞ ድርጅቶች መሀከል የእርስ በርስ መፎካከርን ማስቀረት ነው ይህንን ለማድረግ በማንኛውም የመወዳደሪያ ቦታ ቅንጅትን ወክሉ የሚወዳደረው አንድ ሰው ብቻ ነው ይህ ሰው ማን ይሁን። ፍ ዳይቦጣጫቋ ያሄድጋያፖ ጄደታ ሃር ሐሂ ዕው ማ ምጋ ሪ ዖሜኃውሃ በኋርጥጠኛንኦ ሰሳናር ያሰፖሰሉታ ጾር ብርሃኑ ነጋ የቅንጅቱ «ተዓምረኛ የምርጫ ምልክት ተወለደ ከዚህ በኋላ ነው መልዕክቶቻችንን ለማስተላለፊያ የምንጠቀምበት ዋና መሣሪያ ከመንግሥት የሚሰጠን የኤሌክትሮኒክ ሚዲያ ሰዓት መሆኑን ስላመንን የሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ አንድ አጠቃላይ ስትራቴጂ እንዲኖረን በማሰብ በዚህ ዙሪያ እውቀት ያላቸውን ወጣቶች አሰባስበን ምክሮች እንዲሰጡንና ያለንን የሚዲያ ሰዓት እንዴት መጠቀም እንዳለብን አቅድ እንዲያወጡልን ጠየቅናቸው ይህ ኮሚቴ በተቻለ መጠን የሚዲያ ጊዜያችንን በሁለት ከፍለን እንድንጠቀምበት ዛሳብ ሰጠን የመጀመሪያው በጣም አጭር የአንድ ደቂቃ ማስታወቂያዎችን ለብዙ ጊዜ መጠቀም የሚል ሲሆን ሁለተኛው ረዘም ያሉ ትምህርትና መረጃ ሰጭ ዘዝዐጠበፀየር ፕሮግራሞችን መጠቀም ነበር ኅብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝባቸው የምንፈልጋቸውን በተለይ ቅንጅቱ ዋና ዋና በሚላቸው ከላይ በጠቀስናቸው አቋሞች ዙሪያ የሚዘጋጁ ረጃጅም ፕሮግራሞች ማቅረብን ይመለከታል የተመደበልንን ሰዓት በየትኛው ዓይነት ስልት እንጠቀምበታለን የሚለውን ዝርዝር በማዘጋጀት ላይ እያለን ማስታወቂያ ሜኒስቴር የተመደበልንን ሰዓት እንዴት እንደምንጠቀምበት የሚገልፅ መመሪያ አወጣ በዚህ መመሪያ መሠረት ከምርጫ ጋር የተያያዙ ፕሮግራሞች በሙሉ በተወስነ ሰዓት በተከታታይ የሚሰራጩትና የሚተላለፉት በተደለደለልን ሰዓት በሳምንት ሦስት ቀን የሰባት ደቂቃ ብቻ እንደሆነ ተነገረን ይህንን ለመቀየርና ይበልጡኑም ተለዋዋጭ ሸፀኣዘክ የሆነ ሰዓት እንዲሰጠን ለማድረግ ከአቶ በረከት ጋር ያደረግሁት ውይይትም ምንም ፋይዳ አላመጣም ስለዚህም ሁሉም ፕሮግራማችን ይህንን የተጫነብንን መመሪያ መከተል ነበረበት በተለይ እኔ በአሜሪካን አገር ካየሁት ልምድ በአጫጭር የአንድና የግማሽ ደቂቃ ፕሮግራሞች ላይ ትልቅ ተስፋ ጥዬ ነበር ግን አልሆነም የበለጠ ነገሩን ያወሳሰበው ደግሞ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ሰዓታችን የተለያየ መሆኑ ነው በሬዲዮ በአንድ ጊዜ የተሰጠን ወደ ደቂቃ የሚጠጋ ጊዜ ሲሆን በቴሌቪዥን ሰባት ደቂቃ ብቻ ነው ስለዚህም ለሁለቱ የተለያዩ ፕሮግራሞች ማዘጋጀት ግዴታ ነበረብን ካለን የሰው ኃይል አንፃር ደግሞ ይህ ቀላል እንደማይሆን እናውቅ ነበር በመጨረሻ ይህንን ለማለፍ የተጠቀምንበት ዘዴ መጀመሪያ ለሬዲዮ ተብሎ የሚፃፍ ረጅም ጽሑፍ ማዘጋጀትና ከዚያ ይህንን ጽሑፍ ማሳጠር ነበር በአጠቃላይ ግን በሚዲያ በኩል ያለው አጠቃቀም ምን እንደሚመስል የነባነት ገህ ሲቀደ በማስታወቂያ ሚኒስቴር በተነገረን በሳምንት ጊዜ ውስጥ የፕሮግራም ሥርጭት ተጀመረ በዚህ ጊዜ በእኛ በኩል የተዘጋጀ ምንም ፕሮግራም አልነበረንም የመጀመሪያውን ፕሮግራም እስከምናዘጋጅ የተመደበልንን አንድ ሁለት ጊዜያት ሳንጠቀምባቸው ቀርተናል ከዚህም በላይ ግን ምንም የተዘጋጀ ጥርቅም ስላልነበረን በየቀኑ ለሚተላለፈው ፕሮግራም ለመዘጋጀት መሯሯጥ ጀመርንገ ይህ ጥድፊያ የሚዲያ ስትራቴጂያችንን በአመርቂ መንገድ ለመተግበር አላስቻለንም እንዲያም ሆኖ ግን የሚዲያ አጠቃቀማችንን ብንመዝን ከኢህአዴግና ከሌሎች ተቃዋሚዎች የተሻልን ነበርን ለማለት ያስደፍራል መልዕክት ማስተላለፊያው ሌላው መንገድ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ናቸው ምንም እንኳን የመገናኛ ብዙኃን በተለይ የኤሌክትሮኒክ ሚዲያው ሰፊ ሽፋን ያለው ትልቁ የመልዕክት ማስተላለፊያ መሣሪያችን እንደሆነ ብንገነዘበው ሕዝባዊ ስብሰባዎች በምርጫ ዘመቻ ወቅት የራሳቸው ትልቅ ሚና እንዳላቸው እናውቃለን በዚህም ምክንያት እነዚህን ስብሰባዎች የሚያዘጋጅና የሚመራ አንድ ንዑስ ኮሚቴ በዘመቻ ኮሚቴው ሥር ተቋቋመ ይህንን ኮሚቴ እንዲመራ ኃላፊነቱን የወሰደው ሙሼ ሰሙ ነበር ሙሼ በጊዜው ኢዴአፓመድኅን አመራር ውስጥ ትልቅ ቦታ የነበረው ጠንካራ የሚባል ጎልማሳ ነበር ነገር ግን ሙሉ ጊዜውን ዳሽን ባንክ ይሠራ ስለነበረ የኮሚቴውን ሥራ ምንም ሊያራምደው አልቻለም በእርሱ የሚመራው ኮሚቴ ተሰብስቦ ሥራውን መሥራት አለመቻሉን ስንገነዘብና ይህም ለሁሉም ግልፅ ሲሆን ሙሼ ራሱ የድርጅቱን የዘመቻ ሥራ እንዳንበድል በአሱ ቦታ ሌላ ሰው ቢተካ እንደሚሻል በጠየቀው መሠረት ከኢዴአፓመድኅን በሱ ቦታ ዶር ሙሉዓለም ተተክታ እንድትሠራ ተደረገና ኮሚቴው እንደገና ተዋቅሮ መሥራት ጀመረ ከዚያ በኋላ የመስክ ሥራው በተሻለ ፍጥነት መንቀሳቀስ ጀመረ በመስክ በሚደረጉ የምረጡን ስብሰባዎች በአኛ እምነት ሁለት አስፈላጊ ሥራዎች ይሠራሉ የመጀመሪያው ድርጅቱ በየክልሉ ከተሞችና ከዚም አልፎ በወረዳ ከተሞች ሲንቀሳቀስ ለአካባቢው ሕዝብ የሚሰጠው የአስታውሰውናል» ስሜት አለ ለድርጅቱም በአካል ተገኝቶ ስብሰባዎችን ማዘጋጀቱ ሁሉንም የሚያካትትና የሚያስብ «ቦታ አለኝ» ለማለት ያስችለዋል ሕዝባዊ ስብሰባው ከዚያም በላይ ትልቅ ጥቅም አለው በሬዲዮና በቴሌቪዥን የሚደረጉ ቅስቀሳዎች ግለሰቡ መራጭ ብቻውን አሊያም ከጓደኞቹና ቤተሰቡ ጋር ሆኖ የሚከታተላቸው ናቸው ሕዝባዊ ጾር ብርፃኑ ነጋ ው ው ው መመ መሙ ስብሰባ የዚያ ዓይነት አመለካከት ያላቸውን ብዙ ሰዎች በአንድነት በማምጣት የሚፈጥረው የፍንደቃ ስሜት ፀጀርቨፀጠፀበ በምርጫ ወቅት ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም በውስጡ የያዘውን አመለካከት በተለይ ተቃዋሚውን የሚደግፈውዝ የብቻው እንዳልሆነና በጣም ብዙ ሰዎች እንደሚጋሩት ማወቁ የሚፈጥረው የውስጥ ኃይል በሃ አለ ከዚያም በላይ ሕዝቡ የሚለውን መስማት የሚቻለው በእነዚህ ስብሰባዎች ነው ይህንን ኃይል ሕዝቡ እንዲሰማው ማድረጉ በምርጫ ወቅት በጣም ከፍተኛ ፋይዳ አለው በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የተነሳ በየቦታው ለሚደረጉ ሕዝባዊ ስብስባዎች የቅንጅቱ የምርጫ ዝመቻ ኮሚቴ የሰጠው ትልቅ ትኩረት ነበር የነበረው ችግርና ትልቁ ጥያቄ ድርጅቱ ባለው የገንዘብና የስው ኃይል አቅም ምን ያህል የዚህ ዓይነት ስብሰባዎች ማድረግ ይችላል ወይ የሚለው ነበር የመድረክ ዝግጅት ኮሚቴው አንዱና ትልቁ ሥራው ያለንን የጊዜ የገንዘብ አና የሰው ኃይል አጥንቶ ከምርጫ ዘመቻ መጀመር ጊዜ አንስቶ እስከ ፍፃሜው ድረስ የሚያዘልቅ ዝርዝር ፕሮግራምና የጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀት ነበር ይህም ቢሆን እንደሚገመተው ቀላል ሥራ አልነበረም በመጀመሪያ ሁሉም የየክልል ወረዳ ተወዳዳሪ እሱ በሚወዳደርበት ወይም እሷ በምትወዳደርበት ቦታ ስብሰባ እንዲዘጋጅና በስብሰባውም ላይ በተወሰነ ደረጃ «በአገር አቀፍ ደረጃ የሚታጠቁ» የቅንጅቱ አመራሮች እንዲገኙ ይፈልጋሉ ይህ ደግሞ ካሉን እንዲህ ዓይነት ሰዎች ቁጥር አንፃር የሚቻል አልነበረም ከዚያም በላይ በቅንጅቱ ውስጥ ያሉት ድርጅቶች ራሳቸው በግልፅ አይበሉት እንጂ «የእነሱ አጩ» የሚወዳደርበት ቦታ እንዲፄድላቸው ይፈልጋሉ በዚህም ምክንያት የመድረክ ዝግጅት ኮሚቴው ያዘጋጀው ዝርዝር ሰሌዳ ከአንዴም ሁለቴ እንደገና እንዲከለስ ተደርጓል በኋላም የምርጫ ዘመቻ ሂደቱን በዝርዝር ስንገባበት እንደምናየው ሕዝባዊ ስብስባዎችን ማድረግና አለማድረግ በኢህአዴግና በእኛ በኩል የነበረው አንዱ የምርጫ ዘመቻ ስትራቴጂ ልዩነት ነበር ቅንጅት በእነዚህ ስብሰባዎች በብዙ መልኩ ተጠቅሟል በመጨረሻም የቅንጅቱን የዘመቻ ስትራቴጂ በአጠቃላይና የመልዕክት ማስተላለፊያ ስልቶችን የሚመለከት ጉዳይ ከመዝጋታችን በፊት አንድ የቅንጅቱን ጠቃሚ መለያ ጠቅሼ ልለና ምንም እንኳን የምርጫ ዘመቻው ከመጀመሩ በፊት ዘመቻው የሚሄድባቸውን መንገዶችና የሚከተላቸውን ስልቶች በጥቅሉ አይተን አካሄዳችንን የቀየስን ቢሆንም ከነበረው ጥድፊያ ከቅንጅቱ አወቃቀርና አቅም ብሉም በድርጅቱ ውስጥ የነዛነት ገህ ሲቀድ በነበረው የአዲስነት ስሜት የተነሳ የምናደርገው ነገር በሙሉ በሁሉም መልኩ የተወሰነና የተቆረጠ አልነበረም በየጊዜው አካሄዳችን እያየን የሚሠራውን መከተል የማይሠራውጡን እየጣልን መሄድ የተለመደ ነበር በዚህም ምክንያት የዘመቻው ሂደት በጣም ለማጣ ፎእክሄ እና ለግለሰብ ተነሳሽነት ክፍት ነበር እኛም በየቦታው የሚመጡ አዳዲስ ተነሳሽነቶች በበዘፀከሄፀ በተለይ ያለንን የገንዘብና የሰው ኃይል እስካላመናመነኑት ድረስ አንቃወማቸውም ነበር በዚህ ዙሪያ በተለይ ከቅንጅቱ ጋር ለመሥራት ከየቦታው የመጡ ባለሙያ ወጣቶች በራሳቸው ተነሳሽነት የሰሯቸው ሥራዎች ለምርጫ ዘመቻው ስኬት የነበራቸው አስተዋፅዖ ቀላል አልነበረም ከዚህ አንፃር በተለይ መጠቀስ ያለበት ዘመናዊ የግንኘ ነት ቴክኖሎጂን ለምርጫ ዘመቻው አንድንጠቀም የሠሩት ሥራ ነው የሞባይል መልፅክት ማስተላለፊያ አገልግሉት ሸ ለዘመቻው የመጠቀምን እንቅስቃሴ የጀመሩት እነዚህ ወጣቶች ነበሩ አንደሚታወቀው ይህ መንገድ ከደጋፊዎች ጋር የነበረውን ግንኙነት በማቅለል የመገናኛ ሰንሰለታዊ ምላሽ ርከ የበ በመውሰድና በስልክ ብቻ ሳይሆን ከዚያ ቀጥሎ ያለው የእኛ ለእኛ ግንኙነትን አጫጭር መልዕክቶችን በማስተላለፍ በዘመቻው ወቅት ትልቅ አስተዋጽዖ አድርጓል በተለይ ደግሞ አንዴ ከተጀመረ በኋላ ሰው የራሱን ተነሳሽነት በመውሰድ የሚፈጥራቸው አንዳንድ መልዕክቶች የምርጫ ዘመቻውን አጓጊ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በተወሰነ ደረጃ አስቂኝና ቀልድም የሞላበት እንዲሆን አድርጎታል ለእኔ በግሌ እነዚህን ሁሉ የግለሰቦች ተነሳሽነትና የአፍላቂነት ችሎታ ስመለክት በነፃነት የሚኖር ሕዝብ ሊያደርግ የሚችለውን ማቆሚያ የሌለው የእድገት ግስጋሴ ላይ ያለኝን እምነት አጠናክረው አረጋገጡልኝ በአንፃሩ ደግሞ የዚህን ዓይነት የመገናኛ ቴክኖሎጂ በአፈና ላይ የተመሠረቱ የአገዛዝ ሥርዓቶች እንዴት አንደሚፈሯቸው በዚሁ በምርጫ ዘመቻ ምክንያት የኢህአዴግ መንግሥት ይህንን አገልግሎት በመዝጋት የወሰደው እርምጃ ፍንትው አድርጎ ያሳያል ለዚህ ነው ሕዝብን እያፈኑ እድገትን እና ሥልጣኔን መመኘት አይቻልም ነፃነት የአድገትና የሥልጣኔ መሣሪያም ግብም ነው የሚባለውም በዚህ ምክንያት ነው ሕ የቆጋጆ የምርጫ መቻ ለደረዳጀ እና ቻቨሮቿ ከላይ የተጠቀሱትን አጠቃላይ የስትራቴጂና የስልት መንገዶችን መቀየስና መተግበር ለየቅል ናቸው ቅንጅት ገና ከመፈጠሩና በዝርዝር ጾር ብርዛኑ ነጋ ድርጅቱን ሳያዋቅር በቅንጅቱ ውስጥ ያሉት ድርጅቶች ገና ጠንካራ የመተማመን ስሜት ሳያዳብሩ በየውስጣቸው ካሉ ሕመሞች ጋር እንዳሉ የምርጫ ዘመቻው ተጀመረ በዚህም ምክንያት የምርጫ ዘመቻ አካሄዱ በብዙ ችግርች የተተበተበ ነበር በጣም የሚገርመው እነዚህ ሁሉ ችግሮችም እያሉ የተመዘገበው ውጤት በቅንጅቱ ውስጥ ባሉ የተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ የታቀፉ አባላት እንደ ቅንጅት አብረው መሥራት ሲጀምሩና ሲለማመዱ ችግሮቹን በቶሎ ለመቅረፍና ወደፊት ለመፄድ ያሳዩት ቁርጠኝነት ውጤት ነው የቅንጅቱ የምርጫ ዘመቻ ዓብይ ኮሚቴ ቅንጅቱን ከመሠረቱት አራት ድርጅቶች በተውጣጡ አራት ሰዎች የተዋቀረ ሆኖ በሥሩ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል ከየድርጅቶቹ እየወሰደ የሚሠራ እንዲሆን ታስቦ ተመሠረተ በጣም በአጭር ጊዜ ኮሚቴው በጣም ብዙ ሰዎች እንደሚያስፈልጉት ግልፅ በመሆነ ከየድርጅቶቹ ተጨማሪ ሰዎች እንዲሰጡን ጠይቀን በአንድ ወቅት በኮሚቴው ውስጥ በአንድ መልኩ ወይም በሌላ የሚሠሩ ወደ የሚጠጉ አባሉች ነበሩ እነዚህ ሰዎች በዋናው ኮሚቴ ባሉ ሦስት ሰዎች የሚመሩ ከሊቀመንበሩ ውጭ ሦስት ንዑስ ኮሚቴዎች ውስጥ ገብተው ይሠራሉ እነዚህም የመገናኛ ብዙኃን የመድረክ ወይም የሕዝባዊ ስብሰባና የሥነጽሑፍ ኮሚቴዎች ነበሩ እነዚህ ኮሚቴዎች ችሎታ አሏቸው ከሚባሉ የድርጅቱ አባሎች ወይም ደጋፊዎች እርዳታን መጠየቅና ማግኘት ይትላሉ በተለይ የሥነጽሑፍ ኮሚቴው እስከ ምርጫ ዘመቻው ባለው ጊዜ ለሚዲያ የሚቀርቡ ጽሑፎችን ፕሮግራም አውጥቶ ችሎታው ላላቸው ሰዎች ከኮሚቴው ውጪ ኃላፊነቱን ያካፍላል እነዚህን በተመለከተ በማዕከል የነበረው ኮሚቴ በአደረጃጀት በኩል ችግር አልነበረበትም ነገር ግን ከማዕከል ውጭ ችግሮች ተስተውለዋል የመጀመሪያው ችግር በአደረጃጀት ደረጃ በየክልሉ ያለውን የምርጫ ዘመቻ ለማስተባበር ቢያንስ በዞን ደረጃና ቢቻል ደግሞ በወረዳ ደረጃ ይህንን ኮሚቴ ማዋቀር ላይ ነበር ይህ ደግሞ በፍፁም ቀላል አልነበረም ቀደም ተብሎ የተጠቀሰው በተለይ በሁለቱ ድርጅቶች መሐከል የነበረው ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት እስኪሰክን ድረስ ትንሽ ጊዜ መፍጀቱ አልቀረም በቅንጅቱ በኩል እነዚህ አባላት አብረው እንዲሠሩ ለማድረግ የምንችለው በየእናት ድርጅቶቻቸው በኩል በሚደርሳቸው መልዕክት ነው ይህ የነፃነት ገህ ሲቀድ መልዕክት ደግሞ አንድ ዓይነት ነው ብሎ ለመናገር አይቻልም ይህንን ችግር ለመፍታት ሳይሆን ትንሽም ለመቅረፍ የተቻለው ከሁለቱ ድርጅቶች የተውጣጡ የቀጠና ኃላፊዎች በድርጅቶቹ ውስጥ ደሞዝ ተክፍሏቸው በሙሉ ሰዓት የሚሠሩ በቅንጅቱ ቢሮ መጥተው ሙሉ ለሙሉ መሥራት ከጀመሩ በኋላ ነበር እነዚህ ሰዎች በቀጥታ ከዘመቻ ኮሚቴው ጋር እንዲሠሩ በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት ከእኔ ጋር ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን ሙሉ ስብሰባ እያደረግን አጠቃላይ ሥራውን መቆጣጠር ከዚያም በላይ ግን በየቀኑ ደግሞ ከዚያው ቢሮ ውስጥ እየተገናኘን ሥራውን አብረን መከታተል ጀመርን ከእነዚህ ሰዎች ጋር በመጀመሪያ ባደረግነው ስብሰባ ከዚያች ሰዓት ጀምር የየድርጅቶቻቸውን ኮፍያ አውልቀው በአንድ ላይ ለቅንጅቱ ጥቅም ብቻ መሥራት እንዳለባቸውና የመጠብት ድርጅት ጥቅም ብሎ ነገር እንደሌለ በሰፊው ተወያይተን ተማመንን እውነት ለመናገር እነዚህ ሰዎች ይህንን ለመቀበል ብዘ ጊዜ አልፈጀባቸውም እነርሱም የሚፈልጉትት ነገር ነበር በአጭር ጊዜ ውስጥ በጣም ተግባብተውና ተከባብረው ለአንድ ዓላማ መሥራት ጀምረዋል የሁሉንም ሥራ የሚያቀናብሩ ከሁለቱ ድርጅቶች የተመረጡ ሁለት ኃላፊዎች ተመድበው በእርግጥም እናት ድርጅታቸውን ረስተው ቅንጅቱን በሙሉ ልባቸው አኣገልግለዋል እነዚህን የቀጠና ኃላፊዎች በመጠቀምም ቀስ በቀስ በየክልሉ ያለት የሁለቱን ድርጅቶች አባሎች አብረው የሚሠሩበትን መንገድ ማመቻቸት ጀመርን በዚህ ሂደት ውስጥ የነበረውን አንድ ጥያቄ የምርጫ ዘመቻውን ሂደት በየወረዳው የሚቆጣጠሩት በየወረዳው ያሉት የድርጅት አመራርች ይሁኑ ወይስ ለምርጫው በእጩነት የሚቀርቡት አባላት። ፇ ሐኦንቻራ የሟሰራአዕሩሁ ቋዎሥቻ ልታመሪርጡሳ ለሦፖታም ፅሜል ያመረሃ ዕርነሮ ጳዲውፉ ፐፓደረጎ ለድ ረዝሮ ፇቀማጋ ያዚዖጋ ሪሐኦ ልደቱና ዶር በየነ ዖይደረሦኑ ዱጎ ረጃ ሰድድቋ ጎፅርነ ጾር ብርፃኑ ነጋ ፓርቲ ብዙውን ጊዜ «የአስተዳደር ልምድ» አለው ስለሚባል እንደገና የመመረጥ ዕድሉ በተለይ ከአዲሶቹ ተወዳዳሪዎች አንፃር ሲታይ ከፍተኛ ነው ይህ በዴሞክራሲያዊ አገሮች በሥልጣን ላይ የመሆን ጥቅም በክ ርህቨበከክርሃ ሃበ የሚባለው ነው በእነዚህ ክርክሮች ኢህአዴግ ይህንን ጥቅም አይደለም ያጣው በደሉን ለራፖር ጸሐፊ የነገረ ተበዳይ ጸሐፊው በጥሩ ቋንቋ ከሽኖ ማመልከቻውን መልሶ ሲያነብለት ሲሰማ ስትስቅ ብሎ አንዳለቀሰውና ምነው ታለቅሳለህ ቢሉት «ለካ ይህን ያክል ተበድዬ ነበር» እንዳለው በመራጩ አዕምር ውስጥ ለካ ያለፉትን ዓመታት ክፉኛ ተበድለን ነበር የሚል ቁጭት እንዲያድርበት በኢህአዴግ በኩል በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ክርክሮች እየተጠቀመ እንዳልሆነ በደንብ አውቆ ነበር ግን ከዚያ በኋላ ደግሜ አልከራከርም ማለት «ተሸናፊቱን የማመን» ያክል ስለቆጠረው ይመስለኛል ክርክሩን ለማስቆም አልፈለገም የነበረው ምርጫ የተለያዩ እንቅፋቶችን በመፍጠር የክርክሩ ፎርማት እሱን እንዲጠቅም ማድረግ ብቻ ነበር ክርክሩን በሚመለከት አንድ የመጨረሻ ነጥብ አንስቼ ልለፍ በእኔ እምነት በክርክሩ ላይ ኢህአዴግ የነበረው ችግር የዴሞክራሲያዊ ምርጫን ምንነት በቅጡ ያለመረዳት አልለቅ ካለው የድሮ ፀባዩ ጋር ተዳምሮ ያመጡት ትግር ይመስለኛል ይህ መንቻካ የኢህአዴግን ፀባይ ተቃርኖ የመፈለግና የመውደድ ፀባይ ነው ገና ከመጀመሪያው ሲቪክ ማኅበረሰቡን በሚመለክት በተደረገ ክርክር ይህንን ፀባዩን አሳየ ከዚያ በኋላ እስከ መጨረሻው የምርጫ ዕለት ድረስ በክርክሩ ብቻ ሳይሆን በሚዲያ ማስታወቂያዎች ላይ በተደጋጋሚ የታየው «የጠላት ያለህ» የሚለው የኢህአዴግ አካፄድ በምርጫ ወቅት ያለውን አንደምታ በደንብ አልተረዳውም በምርጫ ሂደት በተቻለ መጠን ደጋፊን ለማብዛት መሞከር ብቻ ሳይሆን የማይወዱህንም ለመቀነስ መጣር ወሳኝ ነው የሚቃወምህን ድርጅት በተቻለ መጠን ከሌላው ሕዝብ ለመነጠል ትሞክራለህ እንጂ ሰውን በቡድን እየፈረጅክ አትሰድብም የሲቪክ ማኅበረሰቡን በተለይ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በድዛፃው አራስ ላይ የተቀመጡ የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ ብቻ የሚሯሯጡ ኃይሉች ብሎ ማቅረብ በጥቅሉ ተጨባጭ ሁኔታን የሚያንፀባርቅ ብቻ ሳይሆን አንዳንድ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች የሉም ማለት አይደለም በምርጫ ወቅት በደፈናው ይህን ማለት ጠላትን ማብዛት ነው ከዚያ በተጨማሪም በብዙ የኢህአዴግ ተከራካሪዎች ዘንድ የነበረው አሉታዊ አቀራረብ በመንግሥት ሥልጣን ላይ ላለ ኃይል አይጠቅምም የነባነት ገህ ሲቀድ ምክንያቱም ተቃዋሚው ኃይል ራሉን እንዳይቆጥብ ያደርገዋል በመጨረሻው ክርክር ላይ የነበረው የነ አቶ ስዩም መስፍን «የኢንተርዛፃምዌ ክስ እኛ ክርክሩ ላይ ስንቀርብ አስበን ከነበረው አዎንታዊ የክርክር መስመር አስለውጦናል ዶር ያዕቆብ በዚህ ተቆጥቶ የራሱን የሩዋንዳ ልምድ ማቅረቡና እኛም ኢሕአዴግን ብዘ ማክበር አያስፈልግም ብለን የተከራካሪዎቻችን የግል ድክመት እንድናነሳ መገደዳችን ኢህአዴግን በፍፁም አልጠቀመም ከዚያም በላይ ግን በኢህአዴግ በኩል የነበረው የክርክር ዝግጅት አመርቂ ነበር ለማለት ያስቸግራል ካለው አቅምና የመንግሥትን ባለሙያዎች የመጠቀም ዕድል አንፃባር በደንብ አለመጠቀሙ ከብዙ ክርክሮች የፖለቲካ ሰዎች ለእኛ የነበራቸውን ፍፁም ንቀት ያሳያል ይህ ንቀታቸው ደግሞ እኛን በጣም የጠቀመን እነሱን ግን ክፉኛ የጎዳ ይመስለኛል ከዚያም በላይ ግን በኢህአዴግ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ባሕል የተለመደው በአንድ ጭንቅላት የማሰብ ባህል ከሞላ ጎደል አንድ ዓይነት በሆኑ ሰዎች መካከል ለሚደረግ ውይይት ይጠቅም እንደሆነ እንጂ በጣም ተለዋዋጭ የሆነ ጉዳዮች በሚነሱበትና በፍጥነት በሚቀያየሩበት ክርክር «ከሳጥኑ ውጪ» ማሰብ አስፈላጊነቱ አያጠራጥርም በክርክሩ ወቅት በነበሩት የኢህአዴግ ተከራካሪዎች ዘንድ የተከሰተው አንዱ ችግር ይህ ይመስለኛ ል ሐ ያጴሀዳዴፇና የቅጋቾሯኑ ቦፉሦቶፈጥ የምርጫ መቻ ለትጳሄደች ኢህአዴግ በምርጫ የደረሰበት ውድቀት መሠረታዊ ምክንያቱ የ ዓመታት አገዛዙ የፈጠራቸው ችግሮች ወሳኝ በሆኑ የአገሪቱ የፖለቲካ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ችግሮች ዙሪያ ያለው አቋም ግጭትን ጠላትነትን እንደ የትክክለኛነቱ ማረጋገጫ የሚመለከተው የውስጥ ድርጅት የፖለቲካ ባህሉና መሰል ይዞታዊ ህህጸክክህዩ ችግሮቹ ናቸው ይህ ማለት ግን የምርጫ ዘመቻውን ያካሄደባቸው ስልቶች ትክክል ነበሩ ማለት አይደለም እንዲያውም በዘመቻው አካሄድ ላይ የፈፀማቸው ብዙ ስህተቶች ተቃዋሚዎችን በጣም ጠቅመዋል የሚል እምነት አለኝ በቅንጅት ምርጫ ዘመቻ ኮሚቴ አካባቢ ያለን ሰዎች ማድረግ የምንፈልገውን ነገር በአቅም ማጣት ምክንያት ማድረግ ሲያቅተን «ግድ የለም ኢህአዴግ አንድ ትልቅ ስህተት ፈፅሞ ይክሰናል» አያልን እንዕናና ነበር በዚህ ንዑስ ክፍል በኢህአዴግና በቅንጅቱ የምርጫ አካፄድ ልዩነቶች ዙሪያ ጥቂት ነጥቦችን ጾር ብርፃኑ ነጋ በማንሳት አንባቢው በሁለቱ ድርጅቶች መካከል የነበሩት እነዚህ ልዩነቶች በምርጫው ውጤት ላይ ያላቸውን አንደምታ እንዲያጤነው ለማድረግ እሞክራለሆ በሁለቱ ድርጅቶች የዘመቻ አካሄድ ላይ ያለው አንደኛው መሠረታዊ ልዩነት ከሁለቱ ድርጅቶች አንፃራዊ አቋም በመነሳት የተጠቀሙበት የተለያየ ስልት ነው ኢህአዴግ በመሠረቱ ጠንካራ ድርጅትና የጎለበተ የገንዘብ አቅም ያለው ነው ከድርጅት ጐንም አስፈላጊ በሆነ ጊዜ በእርዳታ ሊመጣ የሚችል የመንግሥት ኃይል አለው ከሞላ ጎደልም ከ ዓም ጀምሮ ምርጫውን በሚመለከት ሲዘጋጅበት ቆይቷል በዚህም ምክንያት ከተቃዋሚው የተሻለ የተደራጀና የጎለበተ ግልፅ የሆነ የአመራር ተዋረድ ያለው ከሞላ ጎደል በሙሉ የአገሪቱ ክፍል በበቂ የሰው ኃይል የተጠናከረ የድርጅት መዋቅር አለው ድርጅታዊ የቁጥጥር ሥርዓቱም በሰፊው የተዘረጋ ነው ከዚህ አንፃር መልዕክቱን በደንብ ካዘጋጀና ተቀባይነት ያለው መልዕክት ከሆነ መልዕክቱን አስተላልፎ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ድርጅታዊ መሠረት ልማቱ አለው በዚያው ልክ ግን ድርጅቱ ቢሮክራሲያዊ ስለሆነና በየቦታው ያሉት አባሎቹ አስፈፅሙ የተባሉትን ከማስፈፀም ውጪ ከሁኔታዎች መቀያየር ጋር የሚቀያየር የራስ ተነሳሽነት እምብዛም የሌላቸው ስለሆነ በቶሎ ለመቀየርና ከሁኔታዎች ጋር ለመመሳሰል አይችሉም በዚህም ምክንያት ዘመቻውን በተመለከተ ሲጀመር የተዘጋጀበትን የአካሄድ ስልት እምብዛም ሳይቀይረው ሰረጅም ጊዜ ቆይቷል የዘመቻው አካሄድ ለድርጅቱ አጥጋቢ አለመሆኑ ሲታወቅ በቦታው ለአዲሱ ሁኔታ የሚመጥን የተሻሻለ አካሄድ ቀርፆ ለመክተል ረጅም ጊዜ ይወስዳል በዚህ ጊዜ ውስጥም ብዙ ጥፋት ሊፈፀም ይችላል በአንዓሩ ቅንጅቱ ደካማ ድርጅትና በጣም ደካማ የገንዘብ አቅም ያለው ለዘመቻውም የመዘጋጃ በቂ ጊዜ ያልነበረው ስለዚህም በጣም ዝብርቅርቅና በየጊዜው የሚለዋወጥ አካፄድ መከተሉ በምርጫ ብቻ ሳይሆን በሁኔታዎች አስገዳጅነትም ጭምር ነው ጠንካራና ወጥ የሆነ የእዝ ሰንሰለቱ የጠነከረ የድርጅት መዋቅር ስሳልነበረው የየአካባቢው የድርጅቱ አካሎች ከሞላ ጎደል የራሳቸውን እርምጃ ለመውሰድ የሚገደዱት ጊዜ ብዙ ነበር በመልዕክት ደረጃ ቅንጅቱ የሚያምንባቸውና በምርጫው ላይ የሚገፋቸው አቋሞቹ በሕዝብ ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት አላቸው ተብሎ ቢገመትም ይህንን መልዕክት በሕዝቡ ውስጥ ለማሳለፍ እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታዎች የሚለያዩ የማስተላለፊያ መንገዶችን የመጠቀም የነባነት ገህ ሲቀድ ግዴታ ነበረበት በዚህም ምክንያት የበለጠ ለማጠናከርና ቅንጅቱን ለመርዳት የሚፈልጉ አባሎችና ደጋፊዎች የየራሳቸውን መንገድ ተጠቅመው እንዲሠሩ የሚያስችላቸው የራስ ተነሳሽነትን የሚያደፋፍር አካሄድ ከመጠቀም ውጪ ምርጫም አልነበረም ኢህአዴግ ባለው ጠንካራ ድርጅት ክፉኛ ተማምና ነበር ስለዚህም በምርጫው ወቅት ሕዝቡ ጋር በሚዲያው ወይም በየአካባቢው ባሉ የድርጅቱ ተወካዮች ካድሬዎች አማካይነት እንጂ በተለይ ተወዳዳሪዎቹ ከሚመርጣቸው ሕዝብ ጋር ምንም ይህ ነው የሚባል ግንኙነት አልነበራቸውም የምርጫ ዘመቻውን በመሠረቱ ያደረጉት ምስጢራዊ የድርጅት ሥራ የሚሠራበት መድረክ ነበር በራሱ በድርጅት ወይም በተመራጮቹ ወይም ተመራጮቹ በተገኙበት ሕዝባዊ ስብሰባዎች የተደረጉባቸው የምርጫ ወረዳዎች ካሉም በጣም ጥቂት ነበሩ ስለዚህም በመሠረቱ መራጩ እንዲመርጥ የተጠየቀው ድርጅቱን ነው ድርጅቱን የሚወክለውና በሕዝብ የሚመረጠው ግለሰብ በምርጫው ወቅት ምንም ቦታ አልነበረውም ይህ በድርጅት የመመካት የምርጫ አካፄድ ድርጅቱ ጥሩ ተሰሚነት ያለው መልዕክቱም በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው በሚሆንበት ጊዜ ይሠራ ይሆናል እንደ ኢህአዴግ ያለ ከፍተኛ የመልዕክት ችግር ያለበት ድርጅት ከድርጅቱ በላይ ግለሰብ ተወዳዳሪዎቹን የበለጠ ቢያስተዋውቅ በተለይ በሕዝብ ዘንድ ይጠላሉ ከሚባሉት በስተቀር መራጩ ግለሰቦቹን ከተቃራኒ ተወዳዳሪዎቻቸው ጋር እያስተያየ እንዲመዝናቸው ዕድል ይሰጠው ነበር ተቃዋሚ ድርጅቶች እግራቸው እስኪነቃ ከአንድ የአገሪቱ ጫፍ እስከ ሌላኛው እየተዘዋወሩ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ሲያደርጉ ኢህአዴግ ምናልባት በመጨረሻው ሳምንት ላይ ከእነቅልፉ ነቅቶ በቶሎ ለመጥራት ከሞከራቸው ስብሰባዎች በቀር ይህ ነው የሚባል ሕዝባዊ ስብሰባ አላደረገም የዚህ ምክንያቱ ከላይ እንደ ጠቀስኩት በድርጅቱ ጥንካሬ ላይ የነበረው ከፍተኛ እምነትና በካድሬ በኩል ሁሉንም ሕዝብ እደርሰዋለሁ በሚል አዝናኝ ስሜት ውስጥ በመግባቱ ነበር ቅንጅቱ ግን እንደዚህ ሊያዝናናው የሚችል የድርጅት አቅም አልነበረውም ምንም እንኳን በተለያዩ የወረዳ ከተሞች ከ በላይ ቢሮዎች ቢኖሩንም ድርጅታዊ ሰንሰለታችን እንደ ኢህአዴግ በቀበሌ ወይም በጎጥ ደረጃ የተዘረጋ አልነበረም ስለዚህ ተመራጮቻችን በዘመቻው ወቅት በሰፊው መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አምነን ነበር ቢያንስ በዘመቻው በመጨረሻ ወር ሁሉም ተወዳዳሪ በተለይ በክልሎች ያሉ ጓዛቸውን ጾር ብሂፃኑ ነጋ ጠቅልለው በየወረዳቸው ፄደው እስከ ምርጫው ቀን ድረስ እንዲቆዩ የዘመቻ ኮሚቴው የጠዩቀው ቀደም ብሎ ነበር ለዘመቻው በየወረዳው የሚሰጠው ገንዘብም ተመራጩ እዚያ ከሆነ ብቻ የሚሰጥ ነበር በዚህም ምክንያት ተመራጮች በሙሉ በየወረዳቸው ተደጋጋሚ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ ነበረባቸው በአዲስ አበባ ከተማ የየወረዳውን የምርጫ ዘመቻ ኃላፊነት ተወዳዳሪዎቹ ራሳቸው ወስደው በየሳምንቱ በብዙ ወረዳዎች ስብሰባዎች በማድረግ ተወዳዳሪዎች ራሳቸውን ከሕዝበ ጋር ከማስተዋወቃቸው በተጨማሪ በከተማው ሕዝብ ዘንድ ተደማጭነት አላቸው የሚባሉ የቅንጅቱ አመራሮችን በእነዚህ ስብሰባዎች ተወዳዳሪዎች እየተጋበዙ በስብሰባው ላይ አጫጭር ንግግሮችን እንዲያደርጉ ማድረግ የተለመደ ነበር በአንድ ቀን ሁለት ሦስት ቦታዎች መድረስና ንግግር ማድረግ ለአንዳንድ የቅንጅት አባላት የተለመደ ነበር አኔና ኢንጅነር ኃይሉ በተወዳደርንበት በወረዳ ሁሉም ተወዳዳሪዎች የተገኘንበት ቢያንስ ስብሰባዎች በተለያዩ ቀበሌዎች አድርገናል በአንፃሩ በወረዳው ኢህአዴግን ወክለው የሚወዳደሩት እነ አቶ ጌታቸው በላይ አንዳችም እንዲህ ዓይነት ሕዝባዊ ስብሰባ አላደረጉም ይልቁንም ቀደም ብዬ በምዕራፍ እንደገለፅኩት እንዲህ ዓይነት ስብሰባዎች በኢህአዴግ ሲዘጋጁ ብዙ ጊዜ ጥሪው በብሔር ወይም በፆታ አለበለዚያ ደግሞ በእድሜ የተከለለ ስለሆነ ኢህአዴግን ከሚጠቅመው ይልቅ በሕዝቡ ዘንድ «የመከፋፈል አባዜ ያለበት ድርጅት አስመስሎታል እነዚህ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ተመራጩን ከመራጩ ጋር ከማገናኘ ትም የበለጠ ሌላ አስተዋፅዖ ነበረው በሕዝቡ ሥነልቦና የሚፈጥረው የፍንደቃ ስሜት ሕዝቡ በእነዚህ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ላይ የሚገኘው አንድም ከተወዳዳሪው የሚሰጠውን መልዕክት ለመስማት ያልተረዳው ነገር ካለ ለመረዳት ሲሆን ምናልባትም ከዚያም በላይ ከሌላው የሰፈሩ ሰው ለመስማትና በራሱ ውስጥ ያለውን ገና ያልተረጋገጠ ስሜት ለማረጋገጥ ከአካባቢው ሕዝብ ድጋፍ ለማግኘት ነው በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ የነበረው የደስታና የጋለ ስሜት በፍፁም የሚታመን አልነበረም በአንድ ወቅት በአንድ የሳምንት ማለቂያ ቅዳሜና እሁድ ከ በላይ የቅንጅት ስብሰባዎች ይካሄዱ ነበር ከእኛ ጋር የሚፎካከሩት ድርጅቶች ግን ምንም ስብሰባ አያደርጉም ነበር ይህ በከተማው ሕዝብ ዘንድ «ቅንጅቶች ከተማውን ተቆጣጠሩት» የሚልና በዚህም የቅንጅት ደጋፊ መሆን ከብዙኋን ጋር የመሰለፍ ስሜትን እንዲፈጥር ያደርገዋል ከዚህም በላይ ግን የኢህአዴግ የነፃነት ገህ ሲቀደ ተወዳዳሪዎች ከሕዝቡ ጋር አለመገናኘታቸው የእኛን ተወዳዳሪዎች ብሎም ድርጅቱን ለሕዝብ የቀረበ ሕዝብን የሚሰማ የድርጅቱ መሪዎች ከሕዝብ ጋር እየተጨባበጡ ማውራት ያለምንም ጥበቃ የሚችሉ የማይከብዱ ያስመስላቸዋል ስለዚህም ስብስባዎቹ ቅንጅት በእርግጥም የሕዝብ ድርጅት ነው የሚል ስሜት ሊፈጥሩ አስችሏቸዋል የኢህአዴግ ተወዳዳሪዎች ይህን ባለማድረጋቸው ቀድሞውንም ከሕዝብ የራቀ ድርጅት ነው የሚለውን ጥርጣሬ ለማስወገድም ባይሆን ለመቀነስ ምርጫው የፈጠረለትን ዕድል እንዳይጠቀምበት አድርጎታል ሌላው የምርጫ አካሄድ ላይ የነበረው ልዩነት የመረጃ ምንጭን የሚመለከት ነበር ኢህአዴግ በአብዛኛው ይጠቀምበት የነበረው የመረጃ ምንጭ ድርጅቱ ራሱ የነበረ ይመስለኛል በሰፊ ድርጅትነቱ በመረጃ አሰሳ ሁሉንም ቦታ ለማዳረስ የሚያስችል አቋም ስላለውና ከምንም በላይ ደግሞ ከድርጅቱ አባሎች የሚመጣ መረጃን የበለጠ ስለሚያምን በዚሁ መዋቅሩ በኩል የሚመጣው መረጃ የእንቅስቃሴውን አቅጣጫ የሚወስን ነበር እንደሚታወቀው የመረጃ ጥቅሙ የሚመሠረተው እውነተኛነቱ ላይ ነው ኢህአዴግ በድርጅታዊ መዋቅሩ ክፉኛ ከተማመነና ይህንን መረጃውን የሚያረጋግጥበት አማራጭ ከሌለው መረጃው የተሳሳተ ሲሆን በጣም የተሳሳቱ ውሳኔዎች ላይ ይጥለዋል ይህ ችግር በኢህአዴግ ዘንድ መኖሩን ለመጠራጠር የቻልኩት ከማውቃቸው የኢህአዴግ ሰዎች ጋር ስለምርጫው ስንነጋገር እነሱ ያላቸው መረጃ እኛ ከነበረን ጋር በጣም የተራራቀ አንዳንድ ጊዜም ፍፁም ተቃራኒ ስለነበር ነው በቅንጅቱ በኩል የመረጃ አሰባሰቡ ሂደት በጣም የተዘበራረቀ ነበር በድርጅቱ በኩል የምናገኘው መረጃ በራሱ ከአንድ አቅጣጫ ብቻ አልነበረም በተለይ የቅንጅቱ አባል ድርጅቶች በአንድ ላይ ባሉባቸው ቦታዎች ክአንድ ምንጭ ያገኘነውን መረጃ ከሌላው ድርጅት ሰዎች ፈልገን ለማረጋገጥ እንሞክራለን ከዚያም በላይ ግን አባል ካልሆኑ ዜጎች ጋር በተለያየ መንገድ መረጃ እናገኛለን በተለይ በምርጫው ሰሞን የሥልክ ቁጥራችንን በሚዲያ ለቀን ስለነበረ ከሕዝቡ የሚመጡ መረጃዎችን ሴላ ቢቀር ከድርጅት አባላት ከምናገኛቸው መረጃዎች ጋር ለማመሳከርና አንድ ዓይነት የሆነውን በእውነተኛነት ለመውሰድ በሚጋጩ ጊዜ ሌላ ዙር ማጣራት ለማድረግ አስችሎናል በዚህም ምክንያት ብዙውን ጊዜ የምንንቀሳቀሰው ለእውነት የተጠጋ መረጃ ይዘን ነበር በኢህአዴግ በኩል ይህንን ማለት አይቻልም ብዜ የተሳሳቱ ጾር ብርፃኑ ነጋ መረጃዎች ለምሳሌ በአንድ አካባቢ ስላለው ድርጅታዊ ጥንካሬና የማሸነፍ አድል ከካድሬዎቻቸው ይደርሳቸዋል ይህንን የተሳሳተ መረጃ በመያዝም ማድረግ የሚገባቸውን የማሻሻያ እርምጃ ሳይወስዱ ይቀራሉ በተለይ «ሕዝቡ ምን ይላል። የሚሉ ጥያቄዎችን በውስጣችን መጫር ጀመሩ በቅንጅት በኩል ይህንን የእነሱን አካፄድ የመመክት ኃላፊነት አለብን እነሱ በፍፁም ኃላፊነት የማይሰማቸው ከሆኑ የአገሪቱን ሰላም የመጠበቅ ኃላፊነት እኛ ጫንቃ ላይ በግድ ይወድቃል ስለዚህ ይህ የመከፋፈልና የመነጣጠል መርዝ በጣም ከመዛመቱ በፊት አንድ የማስታገሻ መግለጫ ማውጣት ይገባል ብለን ወሰንን ኢህአዴግ እንዲህ ዓይነቱን ከፋፋይ የነዓነት ገህ ሲቀድ ም ሚጅም ሬይ ም ረሙሙኃሙም ምው ቅስቀሳ በትግራይ ተወላጆች ዘንድ በፊቱንም ይጠቀም እንደነበር ጠንቅቀን እናውቃለን ነገር ግን እንደ ቅንጅት በምንም ዓይነት ማንኛውንም ዘውጌ ማኅበረሰብን ነጥሎ ማንሳቱ የሚነገረው ነገር ጥሩ እንኳን ቢሆን ያንን ማኅበረሰብ በተዘዋዋሪ መንገድ ከሌላው መነጠል ይሆናል የሚል እምነት ነበረን ስለዚህም ቅንጅት ፀረትግሬ ነው ለሚለው የኢህአዴግ አሉባልታ እኛ ፀረትግሬ አይደለንም» የሚል መልስ መስጠት የዚህ ዓይነት ፕሮፖጋንዳን ሥራዬ ብለው የያዙትን ቀላል ሰዎች አክብዶ ከማየት በቀርና ይልቁንም የትግራይ ተወላጆች እውነትም በተለየ መልኩ ያዩናል ወይ ብለው እንዲጠይቁ ከማድረግ በስተቀር የሚፈይደው ነገር የለም ብለን ትተነው ነበር በድርጅታችን ውስጥ ያሉ ብዙ የትግራይ ተወላጆችም ድርጅቱ እንዲህ ዓይነት የመከፋፈል ወጥመድ ውስጥ እንዲገባ አይፈልጉም ነበር ለዚህ ከፋፋይ ፕሮፖጋንዳ ተግባራዊ መልስ ብለን የያዝነው በተቻለ መጠን ብዙ የትግራይ ተወላጆች ድርጅቱን እንዲቀላቀሉ መገፋፋት ችሉታው ያላቸውን በአመራር ደረጃ እንዲወከሉ ማድረግ በትግራይ ክልል ያለንን ድርጅታዊ መዋቅር ማጠናከርና የተቻለውን ያህል አባሎቻችንም በክልሉ ውስጥ ለክልልም ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲወዳደሩ ማድረግ ነበር የአቶ በድሩን ንግግር ቀንጭበው ማራገብ ሲጀምሩ ግን ለዚህ መልስ እንስጥ በሚል አንድ መግለጫ አወጣን መግለጫው በአጭሩ ቅንጅቱ በአገሪቱ የሚገኙ ዘውጌ ማኅበረሰባት በሙሉ የተወከሉበት እንደሆነ ስለዚህም ቅንጅቱ ማንንም ሰው በትውልድ ማንነቱ እንደማይፈርጅ የአቶ በድሩ ንግግር አንድምታ «በዚህ ምርጫ ኢህአዴግን እንደ ድርጅት ከሥልጣን እናወርዳለን» የሚል እንጂ ማንኛውንም ዘውጌ ማኅበረሰብ ከአዲስ አበባ እናስወጣለን የሚል አለመሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ በአጠቃላይ የትግራይ ተወላጆችም በተለይ እንዲገነዘቡልን የሚጠይቅ ነበር መግለጫችን የአቶ በድሩ ንግግርን ከታሰበለት ዓሳማ ውጪ በአንድ ዘውግ ላይ ያነጣጠረ ለማስመሰል የሚደረገው ሙከራ በአንዳንድ ጨዋ ሰዎች ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ ከሆነ ወይም ይህንን ስሜት በተዘዋዋሪ ፈጥሮ ከሆነ ለዚህ ቅንጅቱ ከፍተኛ ይቅርታ የሚጠይቅ መሆኑን የሚያስቀምጥ ነበር ይህ መግለጫ እንደ ተዘጋጀ ወዲውኑ ቅጂውን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሳክን መግለጫው ማታ ይተላለፋል ብለን ስንጠብቅ የአቶ በድሩን ንግግር ደገሙት በእርግጥ ሰዎቹ ተስፋ እየቆረጡ እንደሆነና በተስፋ መቁረጥም ጾር ብርፃኑ ነጋ የተነሳ ምንም ዓይነት እርምጃ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ሊወስዱ እንደሚችሉ እየተገለፀልን መጣ «ኢህአዴግ ከሥልጣን ከወረደ አገሪቱ ትበታተናለች» የሚለው የድርጅቱ ሟርት «እኔ ከሥልጣን ከምወርድ እንዲህ ዓይነት መበታተን ቢመጣ ይሻለኛል» የሚል አንድምታ እና ውሳኔም በውስጡ ሊያዝል ይችላል ከሚያዚያ በኋላ ኢህአዴግ በተስፋ መቁረጥ የወሰዳቸው እርምጃዎች ሁሌም አስፈሪ አልነበሩም አንዳንዶቹ በእውነት አስቂኝ ነበሩ ከሚያዚያ በኋላ ባሉት ጥቂት ቀናት አቶ አርከበ ያደርግ የነበረው ከእነዚህ አስቂኝ እርምጃዎች ይመደባል ፍፁም ዓይን ባወጣ መንገድ ተቃወመን ብለው ያሰቡትን የኅብረተሰብ ክፍል እየሰበሰቡ መንግሥታዊ ጫና ማሳረፉን ተያያዙት የታክሲ ባለቤቶችንና ሹፌሮችን በሙሉ ሰብስበው የትራፊክ ቅጣታችሁን በሙሉ ሰርዘንላችኋል ነጋዴዎችን ግብር ቀንሰናል ወይም ያለፈ ውዝፍ ካለ መቀጫውን አንስተናል ለእያንዳንዱ የከተማው ቤት አጥ በሙሉ ቤት እንሰራለን በአጭር ጊዜ ወዘተ ያላሉት አልነበረም አንድ ቀልደኛ ወዳጀ የዚያን ሰሞን አቶ አርከበ «የሞቱትን ዘመዶቻችሁን ሁሉ አስነሳላችኋለሁ» ቢሉ አይገርመኝም ነበር ያለኝ ይህ በጊዜው የነበረውን የኢህአዴግን መተራመስ የሚያሳይ ነበር በጣም የሚገርመው ግን «ምህረት» የተደረገላቸው የታክሲ ባለንብረቶች ከስብሰባው አመስግነው እየወጡ «ዕድሜ ለቅንጅት ስንት ጊዜ ስንለምን ያጣነውን አገኘን እያሉ ለቅንጅቱ ያላቸውን ድጋፍ የበለጠ ይገልጡ ነበር የሕዝብ ልብ ሲሸፍት ክፋቱ እዚህ ላይ ነው ባልወደደው ኃይል ጥሩ ነገር ቢደረግለት እንኳ ተደረገልኝ አይልም ኢህአዴግ ከሚያዚያ በኋላ በነበሩት ቀናት እስከዚያ ድረስ ዘንግቷቸው የነበሩትን የመንግሥት የማፈኛ መሣሪያዎች በግልፅ መጠቀም ጀመረ የተቃዋሚ ደጋፊ ሊሆኑ ይችላሉ የሚባሉ ሰዎችን ማንገላታት የውሸት ውንጀላ እየፈጠሩ ማሰርና በአስቸኳይ ለቀበሌ ፍርድ ሸንጎዎች እያቀረቡ የምርጫውን ቀን ትንሽ የሚያሳልፍ የጥቂት ቀናት የእስር ቅጣት መበየን እየተለመደ መጣ በተቃዋሚ ድርጆቶች ስብሰባ ላይ በየቦታው የሚሰሙት የግፍ እርምጃዎች የሚሰቀጥጡ ነበሩ ለሁላችንም ግልፅ እየሆነ የመጣው የዚህኛው አፈና ዋናው ዒላማ ታዛቢዎች ወይም ታዛቢ ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች እንደሆኑና ይህም የሚያሳየው ድርጅቱ ከምርጫው በኃላ ችግር ሊፈጥር እንዳሰበ አመላካች ነበር የታዛቢዎቻችንን ስም አዘግይተን አንስጥ ባልነው መሠረት የነዛነት ገዝ ሲቀድ በመጨረሻው ቀን ሐሙስ የታዛቢዎችን ስም ዝርዝር በየአካባቢው ለሚገኘ የምርጫ ቦርድ ተወካዮች ሰጠን የፈራነው አልቀረም አርብ ዕለት ሙሉ ቀን ከየክልሉ የምንቀበለው የስልክ መልዕክት ያስመዘገብናቸውን ታዛቢዎች በብዛት መታሰር መጀመራቸውን አረዳን የአባሎቻችን የደኅንነት ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ከመድረሱም በላይ ምርጫውን ከምርጫው ቀን ጀምሮ ለመከታተል ያለን አቅም ክፉኛ እየተሽረሸረ መሆኑ ገባን ከኅብረቱ አመራር ጋር ባደረግነው ውይይት ሳይ ምርጫውን ትተን እንውጣ የሚል ዛሳብ መንሸራሸር ጀምሮ ነበር በዚህ ባለቀ ሰዓት እንውጣም ብንል ምርጫው መካሄዱ ስለማይቀር ባለን አቅም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡንና ጋዜጠኞችን እንዲሁም የምርጫ ታዛቢዎቹን ማሳወቅ ይሻላል በሚል ከምርጫው አንድ ቀን በፊት አሥራ አንድ ሰዓት ሳይ በግሎባል ሆቴል አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ ጠራን በዚያ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በምርጫ ታዛቢዎች መታሰር ዙሪያ ብቻ የኡኡታ ጥሪ አደረግን ይህ ግን ምናልባት የውጭ አገር የምርጫ ታዛቢዎችን ትንሽ አንቅቶ እንደሆን እንጂ ብዙ የፈየደው ነገር አልነበረም የምርጫው ቀን ቀላል በማይባሉ የምርጫ ወረዳዎችና ጣቢያዎች ላይ የተቃዋሚዎች ታዛቢዎች ሳይገኙ ምርጫው ተካሄደ ከሚያዚያ በኋላ በተለይ በአዲስ አበባ የተደረገው የቅስቀሳ ሄደት መደምደሚያ ሐሙስ ግንቦት ቀን የነበረው የነአቶ አርከበ «የሻማ ማብራት ምሽትን» ነበር ቅንጅት ከሚያዚያ በኋላ በአዲስ አበባ ምንም የተቀነባበረ ቅስቀሳ የማድረግ ዛሳብም አልነበረውም የኢህአዴግን የሻማ ማብራት ፕሮግራም ከሰማን በኋላ ረቡዕ ከሰዓት ቢሮ ቁጭ ብለን ስንወያይ ታምራት ታረቀኝ ለምን አንድ የመዝጊያ ነገር አናደርግም ይላል «አይ አሁንማ ምንም ማድረግ አይቻልም ጊዜም ሆነ ቦታ አይኖርም» አልነው ከአጠገባችን ተሰይቶ ሄደና ስድስት ኪሎ የስብሰባ ማዕከል ደውሎ ቦታ መኖር አለመኖሩን ጠይቆ ቦታው እንዳለ ሲነገረው በራሱ ተነሳሽነት ቦታውን ለቅንጅቱ አስያዘ ታዲያ ምን እናድርግ ተባለና ዩኒቨርስቲ አካባቢ ላሉ ተማሪዎች ትንሽ የመዝጊያ ስብሰባ እናድርግ የሚል ፃሳብ መጣ ወዲያው ዩኒቨርስቲ አካባቢ ላሉ ወጣቶች የኤስ ኤምኤስ መልዕክት ተላከ አንድ ሺህ ሰው ያክል ካገኘን ትልቅ ነገር ነው ብለን ነበር በማግስቱ ከቀኑ ሰዓት ያ ትልቅ አዳራሸ ግጥም ብሎ መሙላቱ ተነገረን እኛ ስብሰባው አዳራሽ ስንደርስ አዳራሹ ብቻ ሳይሆን ጾር ብርፃኑ ነጋ ግቢው በሙሉ ሞልቷል የወጣቱ ጩኸትና መዝሙር አዳራሹ ውስጥ ስንገባ የነበረውን ስሜት በሕይወቴ አይቼ አላውቅም የቅንጅቱ መሪዎች በሙሉ ተገኝተው ነበር እኔ በአስር ሰዓት ደብረዘይት ትልቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ስላለኝ መሄድ ነበረብኝ ስለዚህ ቀድሜ እንድናገር ተፈቅዶልኝ የንግግሬን መክፈቻ ያደረኩት «ክቡራትና ክቡራን የከተማችን አደገኛ ቦዘኔዎች» የሚል የሰላምታ ስያሜ ነበር ከዚያ በኋላ ግን የንግግሩ ይዘት በሙሉ በተለይ ወጣቶች የእኛን ትውልድ የጥላቻና የቂም ፖለቲካ አውልቀው መጣል እንዳለባቸውና ጥላቻ ላናወዘው ጭንቅላት ፍቱን መድሃኒቱ ፍቅር ነውና አሁን ከዚህ ስትወጡ በዩኒቨርስቲው ውስጥ ያለ በማንነቱ ምክንያት ብቻ የጠላችሁት ሰው ካለ ሄዳችሁ ይቅርታ እንድትጠይቁ ለሚጠሏችሁም ሰዎች መልሳችሁ ጥላቻ ከሆነ እነሱን ሆናችሁ ማለት ነውና የምትበልጧቸው ለጥላቻቸው ፍቅር ስትመልሱላቸው ነው የሚል ፍቅርን በመስበክ ላይ ያተኮረ ነበር ለእኔም ለራሴ በጣም ስሜታዊ በባከክ የሆነ የመጨረሻውን የአዲስ አበባ ንግግሬን አድርጌ ወደ ደብረዘይት ሄድኩ ደብረዘይት ስታዲየሙ ሞልቶ ጠበቀን በደብረዘይት ታሪክ በሕዝብ ቁጥር ተወዳዳሪ የሌለው ትልቁ ሰልፍ ነበር ማታ አዲስ አበባ ስመለስ የኢህአዴግ የሻማ ማብራቱ ፕሮግራም ብዙም እንዳልተሳካ ሰማሁ ከሚያዚያ ጋር በትንሹም ቢሆን የሚገናኘው ግን ይበልጡኑ ከተካፄዱት የክርክር ፕሮግራሞች ጋር ስለተያያዘ አንድ ጉዳይ በአጭሩ ገልጩ ወደ ምርጫው ዕለት ልለፍ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲን በሚመለከት የተደረገው ክርክር የመጨረሻው መስሉን ነበር ያም ክርክር ቢሆን ቅንጅቱ የበላይነት ያሳየበት ስለነበር በአጠቃላይ የክርክሩ ፕሮግራም ተቃዋሚዎችን በአጠቃላይ እና ቅንጅቱን በተለይ በጣም የጠቀመ ሆኖ በመጠናቀቁ ተደስተን ነበር ምርጫውም የቀረው ሁለት ሳምንታት ብቻ በመሆኑ እኛም በሌሎች ሥራዎች ተጠምደን ነበር ኢህአዴግ ግን በሂደቱ እንዳልረካ ግልፅ ነበር ከዚህ ከመጨረሻው ክርክር ጥቂት ቀናት በኋላ አቶ በረከት የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን አንድ የመጨረሻ ፕሮግራም ለማስተላለፍ ማሰባቸውን ነገረኝ ይህ ፕሮግራም ሦስቱን ድርጅቶች የሚመለከት ሆኖ በአጠቃላይ ስለ ምርጫውና በምርጫው ዙሪያ ስለሚነሱ ጉዳዮች ድርጅቶቹ ከጋዜጠኞች ጥያቄ እየወሰዱ የሚመልሱበት ይሆናል ፕሮግራሙ በስቱዲዮ ተቀርፆ እያንዳንዱ ፕሮግራም ለየቱቻ አንድ ቀን ተሰጥቶት ከዜና በኋላ ይተላለፋል ብዙ አድማጭም ያገኛል አለኝ እኛ ምንም ዓይነት የሚዲያ የነባነት ገህ ሲቀደድ ጊዘ ኻካኽእንደማንጠላ ግን ጥያቄ አቅራቢዎቹ ጋዜጠኞች ከሆኑ ያለውን የዴሞክራሲ ሂደትም እንዲያንፀባርቅ ከመንግሥትም ከግልም ሚዲያ የተውጣጡ ይሁኑ አልኩት ይህ ችግር የሌለው መሆኑንና ዝርዝሩን ሊነግረኝ መልሶ እንደሚደውልልኝ ገለፀልኝ እስከ አሁን ዝም ብሉ የነበሩት የአቶ መለስ ተራ መድረሱንና ግን ከእኛ ጋር ፊት ለፊት ለመግጠም እንዳልፈለገ ገባንከዚያ በኋላ አቶ በረከት ደውሉ እንዲያውም ምንም ዓይነት ወገንተኛ ነትን ለመከላከል እያንዳንዱ ድርጅቱ የሚጠየቀውን ጥያቄ ራሱ ያወጣና ለተመደቡት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች የውይይቱ ቀን ይስጥ ጋዜጠኞች ከተሰጣቸው ጥያቄ ውጪ ተከታይ ጥያቄ እንኳን መጠየቅ አይፈቀድላቸውም በዚህ መልክ ድርጅቱ ሊያብራራ የሚፈልገውን ጥያቄ ራሱ ይመርጣል አለኝ ይህ እኔ ከለመድኩት አሰራር ጋር በፍጹም የሚጋጭ ቢሆንም ከዚህ ውጪ እንደማይሆን ሲገባኝ የተፈቀደልንን የሁለት ሰዓት ተኩል የቴሌቪዥን አና የሬዲዮ ሰዓት እንዴት እንደምንጠቀም አያሰላሰልኩ ጉዳዩን ለሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አቀረብኩ ይህ ፕሮግራም እንደሚኖር የሰማው ልደቱ ወዲያውት ሁለታችን መሆን እንዳብን ፃሳቡን አቀረበ በሥራ አስፈፃሚው ስብሰባ ላይ ይህ የመጨረሻው መልዕክታችን ስለሆነ በየመራጩ አዕምሮ ውስጥ ይጉላላሉ ብለን ያሰብናቸውን ጥያቄዎች በሙሉ የምናብራራ መሆን እንዳለበት ተስማማን ከእነዚህ ውስጥ ቢነሱ ጥሩ ነው የምንላቸውን እያነሳን አንዳንዱን መዘገብን አነማን ይቅረቡ በሚለው ላይ የተለመደው ክርክር ተነሳ የድርጅቱ ሊቀመንበር አንዱ መሆን አለባቸው የሚል ሃሳብ ቢቀርብም ኢንጅነር ኃይሉ ራሱ ከእኔ ይልቅ በሚዲያ ፃሳባቸውን በደንብ መግለጽ የሚችሉ ሰዎች ቢሆኑ ይሻላል ብሎ እኔን ጠቆመ በዚህ ላይ ስምምነት ተደርሶ በሁለተኛው ሰው ላይ ክርክር ተጀመረ እኔ ሁለተኛው ሰው ልደቱ ቢሆን ይሻላል አልኩ በዚህን ጊዜ ልደቱ ቢሮ አካባቢ አይመጣም ፉ በነራቻጋ ይ በውጭ ዳይ ፖፈ ዙሪያዖ ፀዖደረው አረዝር ለዚጋድቻ ረዝሩ ሥዕት ቃና ፈፇረው ደውኃው ቀጅሪ ያታታጋፇ ታላልቅ መሪዎሥቻ ለፇዲል ሏሀላዳዴፇ ት ጠቀላይ ሚኒዕታሩ ዳንደሚሃቕኙ ጎሩ። ሪደቻያ ያሟኗባውቃ እዳቭዳደቻ ለድረ ነገር የሚደዖቻው የነባነት ጎህ ሲቀድ የገባው ወዲያውኑ ነው በየክልሉና በወረዳዎች ያሉት የድርጅት መዋቅሮች ገና አልተሠሩም ያሉን ለምርጫ ዘመቻው ተብለው በጊዜያዊነት የተመሠረቱት ኮሚቴዎች ናቸው እነዚህ ኮሚቴዎች ሲሰሩት የነበረው የዘመቻ ሥራና ጊዜው የሚጠይቀው የማደራጀት ሥራ ለየቅል ናቸው ሕዝባዊ እርምጃዎች እንኳን እንውሰድ ብንል ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የምንችልበት ድርጅታዊ አቅምም ተቋምም የለንም ስለዚህ በዝግታና በብልህነት መፄዱ ለቅንጅቱ የተሻለ ይሆናል የሚል ምክንያት ነበረን ከዚያ በተጨማሪ በአካሄድ ደረጃም የሚነሳ ልዩነት ነበር በተቻለ መጠን ለሕዝብ የምናቀርበው ነገር ሁሉ በእውነት ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት በእኛ በኩል «አሸንፈናል» ብለን ማውራት ያለብን እርግጠኛ የሆንንባቸውን ቦታዎች ብቻ ነው ይህን ለማድረግ መጠቀም የምንችለው አንድም የአንድን ወረዳ ሙሉ በሙሉ ውጤቱን በማቅረብ አሊያም የብዙ ምርጫ ጣቢያዎችን ውጤት ስናገኝ እና የቀሩት ጥቂት ውጤቶች አጠቃላይ የምርጫ ወረዳውን ውጤት አይቀይሩትም ብለን ስናምን መሆን አለበት ከዚያ ውጪ የእኛ ታዛቢዎች የተባረሩባቸወው ግልፅ ዘረፋ የተካሄደባቸውንና እኛም ሆንን ሌሎች ታዛቢዎች እውነተኛ ውጤቱን የማናውቃቸውን ማቅረብ ያለብን የተዘረፉ ወረዳዎች ወዘተ ብለን እንጂ ማስረጃ እስከምንይዝ ድረስ እኛ ያሸነፍንባቸው ወረዳዎች ብለን መሆን እንደማይኖርበት አቋም ያዝን ይህ አቋም አጠቃላይ የመርህ አቋም ነበር ፖለቲካው ይለወጥ ብለን የምንታገል ከሆነ የአገዛዝ ሥርዓቶች ከተጠናወታቸው የውሸት በሽታ መላቀቅ አለብን ዝም ብሎ ለማስፈራሪያ ወይም ለማደናገሪያ የሚደረግ ውሸት ጊዜያዊ ጥቅም የሰጠ ይምሰል እንጂ ለዘለቄታው እኛንም ፖለቲካውንም ይጎዳል በሕዝቡ ውስጥ ልናሰርፅ የምንፈልገው አንድ አመለካከት ፖለቲካንና ውሸትን ማራራቅ ነው የሚል አስተሳሰብ ነበር እነዚህ የተለያዩ አመለካከቶች ወደ ተግባር ሲለወጡ ብዙ አንደምታ ይኖራቸዋል በተለይ በጊዜው በነበረው ከፍተኛ ስሜታዊ ሁኔታ ትንሽም የተሳሳተ አካፄድ ትልቅ ውጤት ሊያመጣ ይችላል የሰዎች ስሜቶችም በየቀኑ ኢህአዴግና ምርጫ ቦርድ በሚወስዷቸው እርምጃዎች የተነሳ የሚወጡና የሚወርዱ ነበሩ ኢህአዴግ ከምርጫው ቀን በቷላሳ የመንግሥት ሚዲያን በሙሉ በቁጥጥሩ ውስጥ አስገብቶ የድርጅቱ የፕሮፖጋንዳ መሣሪያ አድርጎት ነበር በየምሽቱ የምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ ውጤት እያለ እኛ ራሳችን በግልፅ መጭበርበራቸውን የምናውቃቸው ጾር ብርፃኑ ነጋ ወረዳዎች ኢህአዴግ «አሸንፏቸዋል» እያለ ይገልፅ ነበር የእነዚህ ወረዳዎች ነዋሪዎችና የድርጅት ሠራተኞች አንዳንድ ጊዜ የወረዳ የምርጫ አስፈፃሚዎች ሳይቀር ቅንጅት ቢሮ እየደወሉ ይህ በቴሌቪዥን የተወራው ውሸት እንደሆነ በዚያ ወረዳ ኢህአዴግ መሸነፉን የምርጫ ኮሮጆዎችን ወስደውና ገልብጠው አዲስ ካርዶች እየሞሉ እንደሚያመጡ እንደሚያውቁ ይነግሩን ነበር በዚያን ወቅት በሚደረግ ስብሰባ በአመራሩ በኩል ከፍተኛ የቁጭትና የብስጭት ስሜት ይንፀዐባረት ነበር ቁጭትና ብስጭት በሚወሰኑ ውሳኔዎች ላይ እንዳይንፀባረቅና ውሳኔዎቹ በተቻለ መጠን የሰከነ እንዲሆኑ ከፍተኛ ትግል አድርገናል ይህ ስሜታዊነት ከላይ ካነሳሁት የአመለካከት ልዩነት ጋር ሲዳበል ልንገፋ የምንችልበት አቅጣጫን ማስተዋል አይከብድም ይህንን የአካሄድና የውሳኔ አሰጣጥ አንድምታ በግልጽ ለማሳየት አንድ ምሳሌ ልስጥ ወደ ምሳሴው ከመሄዴ በፊት ግን ከዚህ ጊዜ ጀምሮ እስከ ጥቅምት ድረስ የነበረውን የቅንጅቱን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የውይይትና የውሳኔ አሰጣጥ አካሄድ በጥቅሉ ላቅርብ የቅንጅቱን የአወሳሰን ሂደት በደንብ የማያውቁ ሰዎች ድርጅቱ በጥቂት ግለሰቦች ከፍተኛ ተጽዕኖ ሥር የወደቀ በተለይ በሊቀመንበሩ አቶ ኃይሉ ሻውል አድርገው ይወስዱታል እኔ እስከማውቀው በቅንጅት ሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ የሚያሸንፈው ዛሳብ ሁልጊዜ የተሻለ ምክንያት ያለው ዛሳብ ነው በዚህም ምክንያት ብዙውን ጊዜ ውይይቱ ሲጀመር የሚነሱ ዛሳቦችና በመጨረሻ ስምምነት ከሚደረስባቸው ዛሳቦች በፍፁም የተለዩ ወይም በእጅጉ የተሻሻሉ ናቸውፎ ብዙ ሰዎች በስብሰባው ሂደት አቋማቸውን ሲቀይሩ ይታያሉ ይህ ደግሞ በእኔ እምነት ጤነኛ አካሄድ ነበር የሊቀመንበሩም ሚና ይህንን ውይይት ማስተናገድና የራሱን ፃሳብ እንደ ሌላው ማቅረብና መከራከር ነው ኢንጅነር ኃይሉ አንዳንድ ጊዜ ሊቀመንበርነቱን ይረሳና ክርክሩ ውስጥ ገብቶ ብዙ ሰዓት ይወስዳል ይህ ሲሆን «ይህንን አትችልም ለራስህ ብዙ ጊዜ እየሰጠህ ነው በትክክል ስብሰባውን ምራ» እየተባለ ተግሳጽ ይቀርብበታል ብዙውን ጊዜ ወዲያውኑ ይታረማል አንዳንድ ጊዜ የበለጠ ንዴት ውስጥ ሲገባም «ተናደደ» ብሎ የሚተወው አልነበረም አንድ ቀን ትዝ ይለኛል በጣም የተሟሟቀ ክርክር እየተካሄደና አቶ ኃይሉ የክርክሩ ዋና ተዋናይ ስለሆነ የሊቀመንበርንቱን ሥራ ረስቶት ብዙ ለሰዎች እጃቸውን ቢያወጡም በደንብ አይመለከትም ነበር ከዚያም በባሰ ለአንድ ሰው እድል ሰጥቶ ያ ሰው የተናገረው እሱ ካለው ጋር የሚፃረር የነባነት ገህ ሲቀድ ከሆነ እሉ ሲጨርስ ወዲያውኑ ለተነሳው ሃሳብ መልስ ራሱ ይሰጥና ይህን ሊያብራራ ብዙ ጊዜ ይወስዳል በዚህ ጊዜ የተወሰኑ ሰዎች በጣም በመበሳጨት የሥነሥርዓት ጥያቂ አቀረቡ ሁለት ሦስት ሰዎች በአንድ ላይ ስብሰባውን የራሱን ፃሳብ መግፊያ እንዳደረገው ለተለያዩ ፃሳቦች ዕድል እንዳልሰጠ በጉዳዩ ላይ በጣም መሳተፍ የሚፈልግ ከሆነ ሊቀመንበርነቱን ለጊዜው ለምክትሉ ሰጥቶ እሱ ክርክሩ ውስጥ እንደ ማንኛውም አባል ተሳታፊ ቢሆን እንደሚሻል ይናገራሉ አቶ ኃይሉም በዚህ ተበሳጭቶ ይዞት የነበረውን የእጅ ቦርሳ ዘጋግቶ «እንዲያውም ሊቀመንበርነቱን ትቼላችኋለሁ» ብሎ ተነስቶ ሊወጣ ሲል እዚያ የነበረው ሰው ሁሉ የእሱን ፃሳብ የሚደግፉትም ጭምር ተቆጥተው የተነሳው ፃሳብ ልክ እንደሆነ ከሁለቱ ሚናዎች መምረጥ እንዳለበትና ስብሰባውን በትክክል መምራት እንደሚገባ ነግረውት እሱም ብስጭቱ ጋብ ሲልለት ስህተቱን ተቀብሎ ውይይቱን መምራት ቀጠለ በቅንጅት የአመራር ስብሰባዎች ያለ አሳማኝ ምክንያት እከሌ» ስለ ተናገረ ወይም የእከሌ አቋም ስለሆነ ተብሉ በማፈር ማክበር ወይም በመፍራት የሚወሰን ውሳኔ አልነበረም በዚህ ላይ አንድ ነገር ላክል አቶ ኃይሉ አንዳንድ ጊዜ በቃለመጠይቅ ወይም በአጋጣሚ በጭንቅላቱ ውስጥ ያለን ነገር ገና በቅንጅቱ አቋም ሳይወሰድበት ይናገራል ይህንን ሲያደርግ አንዳንዴ የግሌ አቋም ነው ይላል አንዳንዴ ምንም አይልም ይህ ሲታወቅ ሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የሰላ ሂስ ይቀርብበታል «ቅንጅት ያልወሰነውን ውሳኔ እንደ ተወሰነ አድርገህ ማቅረብ አትችልም የግሌም ነው ብትል ሊቀመንበር ስለሆንክ በተለይ ፈረንጆቹ የድርጅቱ አቋም እንደሆነ አድርገው ስለሚወስዱት ተጠንቀቅ» እየተባለ ይወቀሳል ይመከራልም በውጭ አገር ሆኖ እንዲህ ዓይነት ነገር ከተናገረ «ይህ የድርጅቱ አቋም አይደለም» የሚል መግለጫ በቅንጅቱ ይወጣል ስለዚህ በቅንጅቱ አሠራር አንድ ሰው ማንም ሰው ቅንጅቱን በመሰለው መንገድ ይመራዋል ወይም መርቶታል ማለት አይቻልም ስለ ቅንጅቱ አሠራር ይህን ያህል ካልኩ ወደ ምሳሌው ልሂድ ከምርጫው በኋላ በነበሩት ሁለት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ከኢህአዴግ ጋር የመጋፋት ጠንካራ አቋምን ይዞ ይከራከር የነበረው ልደቱ ነው በመጀመሪያ ስብሰባ ሲጀመር አቶ ኃይሉም እንደ ልደቱ ከረር ያለ አቋም ይዞ ይከራከር ነበር በአንዱ ስብሰባችን በቴሌቪዥን በተሰጡት የኢህአዴግ የአሸንፌአለሁ መግለጫዎች ሁሉም ሰው እንደ ተለመደው ተናድዶ ነበር ጾር ብርዛኑ ነጋ በዕለቱ ይህንን የኢህአዴግ ፕሮፖጋንዳ ለማርከስ እና የሕዝቡንም ቁጣ ለማቀዝቀዝ የሚሰጠው መግለጫ ምን ይሁን በሚል ውይይት ሲጀመር ልደቱ እንደ ተለመደው በጣም ጠንካራና ኢህአዴግን «የሚያስፈራራ» መሆን እንዳለበት ፃሳብ ያቀርባል አቶ ኃይሉም ይህንኑ ደግፎ ይናገራል ሌሎችም በዚሁ ላይ አየጨመሩ ያብራራሉ በዚህ ጊዜ ኢህአዴግን ማስደንበሩ ምንም አይጠቅምም የበለጠ ወደ ኃይል ይገፋዋል ስለዚህ መቅረብ ያለበት ማስፈራሪያ ሳይሆን አቋማችንን በግልፅ እንዲረዳው የሚያደርግ መልዕክት የሕዝብ ድምጽ መክበር እንዳለበት ለዚህም እስከ መጨረሻው በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ እንደምንታገል ይህ አካሄፄድ አገሪቱን ችግር ውስጥ እንደሚከት እንዲተላለፍ ከሁለቱ በተቃራኒ ያለ ፃሳብ በዝርዝር ቀረበ ቀስ እያለ ይህንን ፃሳብ የሚደግፉት ሰዎች እየጨመሩ ፄዱና በመጨረሻ ጠንካራ ነገር ግን የማያስፈራራ ዓይነት መግለጫ ይውጣ ተብሎ ተወሰነ በዚያን ሰሞን እንደሚደረገው በዚህ ፃሳብ ላይ ተመሥርቶ ልደቱ የሕዝብ ግንኙነቱ ኃላፊ መግለጫውን ያዘጋጀው ተብሎ ስብሰባው ተበተነ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ልደቱ ያዘጋጀውን ጽሑፍ እኔ ስመለከተው ኢህአዴግን ሊያስደነብሩ የሚችሉ ቃላት ነበሩበት ይህንነ ለልደቱ ገልጨለት በተለይ አንድ ሁለት ጠንካራ ዓረፍተ ነገሮችን ቢያወጣቸው እንደሚሻል ነገርኩት ልደቱ ግን በሃሳቡ አላመነበትም ነበር እኔና ዶር ሽመልስ እነዚህ ዓረፍተ ነገሮች አልተስማሙንም ነበር በወቅቱ የፈራነው ኢህአዴግ ሆን ብሎ መልዕክታችንን ለማጣመም አባላቱንም ለማስደንበር ይጠቀምበታል ብለን ነበር ስለዚህ ጉዳዩን ለአቶ ኃይሉ ነገርነው በዚያን ጊዜ በነበረው አሠራር ሊቀመንበሩ አይቶ የስብሰባውን ዛሳብ አያንፀባርቅም ካለ ማስተካከል ይችል ነበር አቶ ኃይሉም አምኖበት እነዚህን ዓረፍተ ነገሮች አስወጣቸው ይህ ያስከፋው ልደቱ በዚህ ዓይነት ሁኔታ መቀጠሉ አልጣመውም ከሕዝብ ግንኙነት ኃላፊነት ብለቅ ይሻላል የሚል ፃሳብ ማቅረብ የጀመረው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው አሁን ለቀረበብን የፈጠራ ክስ በማስረጃነት ከቀረቡት የቅንጅት መግለጫዎች አብዛኛዎቹ ልደቱ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ በነበረበት ወቅት የተዘጋጁ ነበሩ አሁን የታሰርነው «ነውጠኞች» በጊዜው ጠንክረዋል ብለን በአርትዖት እያለሳለስን ያሳለፍናቸው መግለጫዎች የወንጀላችን» አስረጅ መሆናቸውን ሳይ በሁኔታው መገረሜ አልቀረም በጊዜው ግን የልደቱን የአጻጻፍ ድምፀት ከወጣትነት ከመጣ ደመሞቃትነት በላይ አድርጌ አላየሁትም ነበር እነዚህ የተለያዩ አቋሞች በተለያየ ጊዜ ይንፀባረቁ እንጂ በአጠቃላይ የነባነት ገህ ሲቀድ የብዙቷኋኑ የቅንጅት አመራር ግንዛቤ ከላይ ከ የዘረዘርኳቸው ነበሩ በዚያም መሠረት በአንድ በኩል በብዙ ጭቅጭቅ በየዕለቱ እነዚህን ጋዜጣዊ መግለጫዎች ስንሰጥ በሌላ በኩል እነዚህ ተጭበረበሩ የምንላቸውን ቦታዎች በሚመለከት በተቻለ መጠን ጠንካራ ማስረጃ መሰብሰብ እንዳብን በማመንና በአጠቃላይ ግን በገጠሩ ያለውን ሁኔታ ለመገንዘብ እንዲያመቸን የተወሰኑ ሰዎች በየክልሉ ሄደው ሁኔታውን እንዲያጣሩ በመላክ በየአካባቢው የተፈጠረውን ሁኔታ በሚመለከት አጠቃላይና ተጨባጭ ዘገባዎች እንዲቀርቡልን ለማድረግ ሞክረናል ሆኖም ከአቅም ማነስ የተነሳ በፈለግነው መልክ ዝርዝር ማስረጃ ለማሰባሰብ በጊዜው አልቻልንም ይህ በደጌብ የተሞከረው የምርጫ ማጣራት ሂደት ሊጀመር ሲል ነበር ቀደም ብዬ እንዳልኩት በዚህን ጊዜ መሠራት አለበት ብለን ካሰብነው ነገር አንዱ ዕለት ተፅለት ለኢህአዴግ ምላሽ ከመስጠት ባሻገር በስፋትና ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ ማሰብ ነው ለዚህም ውይይት ጀምረን ነበር በዚህን ጊዜ ለመነሻ የተወሰደው ፃሳብ ከምርጫው ጥቂት ጊዜ ቀደም ብሎ በምርጫው ሊሆኑ የሚችሉ ሁኔታዎች በሚል ከተዘጋጀ አንድ አጭር ጽሑፍ ነበር የዚህ ጽሑፍ መነሻ የነበረው ምርጫው ከመደረጉ በፊት ከምርጫው በቷላ ሊሆኑ የሚችሉ አማራጭ ሁኔታዎችን አስቀምጦ ለእያንዳንዱ አማራጭ ቅንጅቱ ሊወስደው የሚችለውን እርምጃና ለዚያ የሚያስፈልገውን ዝግጅት በመተንተን ቅንጅቱ ሥነልቦናዊ ዝግጅት እንዲያደርግ ለማድረግ ነበር ይህ የአማራጮች ትንተና ፀበቨ ከክህ ሲቀርብ ሊሆን ይችላሉ የተባሉት አማራጮች በአጭሩ የሚከተሉት ነበሩ ሯራ ጴሀጎዴፇ ያሻጋፉሳ ማሸንፉጋም ግሐምእዳፇፍ ታሃዷሥቻ ያምም ጥርጣሪ ይመፅዕራታ ። የሚል ጥያቄ አነሳ የልደቱም መልስ ከዚህ እንቅስቃሴ ቅንጅቱ ከሕዝብ ጋር ሳይጋጭ ፓርላማ ለመግባትና አዲስ አበባን ለመረከብ የሚያስችለው ምክንያት በህዘበጸክ ያገኛል ከዚያም በላይ ግን የሕዝብ መሪነቱን የነዛነት ገህ ሲቀደ እንደያዘ ለሚቀጥለው ምርጫ ይዘጋጃል በሚቀጥለው ምርጫም ያሸንፋል የፖለቲካ ትግል ዒላማውም ይኸው ነው የሚል ነበር በጊዜው በዚያ ስብሰባ ላይ ለነበርነው በተለይ ከቀስተ ደመና ለመጣነው ሰዎች ይህ ሎጂክ ሁለት መሠረታዊ ስህተቶች ነበሩት የመጀመሪያው በዚህ ሉጂክ መሠረት ከዚህ ምርጫ ሊገኝ የታሰበው ዋነኛ ፍሬ ኢህአዴግ የወሰናቸው የፓርላማ ወንበሮችና የአዲስ አበባ ምክር ቤት መሆኑን ከመቀመጫዎች ውጪ የዴሞክራሲያዊው ፖለቲካ መጨናገፍ ወይም ፈር መልቀቅ በሉጂኩ ከቁብ አለመቆጠሩ ነበር ኢህአዴግ የሕዝቡን ድምጽ አጭበርብር በዚህ ምክንያት የሚነሳን የሕዝብ እንቅስቃሴ በጉልበት ከጨፈለቀ በቷላ ምንም ነገር እንዳልሆነ ነገሮች ይቀጥላሉ የሚሰው ስሌት ከተነሳንበት ዓላማ ጋር የሚጣጣም አልነበረም ለእኛ የዚህ ምርጫ ዋና ውጤት መሆን ያለበት ማንም በሥልጣን ይቆይ ማን ፖለቲካው ከጉልበት ተለያይቶ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚመሰረትበት መንገድ ቢችል በፖለቲካ ኃይሉች የጋራ ውይይት ቢመቻች ይህ በሌለበት ኢህአዴግ በጉልበት የሚቀጥል ከሆነና ልዩነቱ በምክር ቤት የመቀመጫው ቁጥር መጨመር ብቻ ከሆነ የመጠን ልዩነት እንጂ የዓይነት ልዩነት አልተደረገም ይህ ደግሞ ለወደፊቱ ፖለቲካ ለሰላምና ለመረጋጋት አይበጅም ሁለተኛውና ዋነኛው የልደቱ የሉዲክ ችግር ከአምስት ዓመታት በኋላ የሚገኝን ሥልጣን ለማመቻቸት እያወቅን ዜጎች ሊሞቱ የሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ ማስገባቱ ነበር ለእኛ የተወሰነ ሰዎችን በሥልጣን ለማቆየት ወይም ሥልጣን ላይ ለማውጣት ሲባል የአንድም ዜጋ ሕይወት መጥፋት የለበትም ለነዓነት ተብሎ በሚደረግ ትግል እንኳን በተቻለ መጠን ምንም ሕይወት መጥፋት የለበትም ብለን የትጥቅ ትግልን ተቃውመን ሰላማዊና ሕጋዊ ትግልን መርጠናል ይህንን መንገድ ስንመርጥ በዋናነት ለሰው ልጅ ሕይወት ክፍተኛ ክብር ስላለን ነው ለዚህ ትግል ተብሉ እኛ ባልፈለግናውና ባልመረጥነው መንገድ ሌላው ወገን ለሥልጣኑ ሲል በሚጠቀመው ኃይልና በሚፈጠረው ሁከት ምክንያት የሰው ሕይወት ቢጠፋ እያመመንም ቢሆን ልንቀበለው እንችላለን ነገር ግን ዒላማው ከአምስት ዓመታት በኋላ የሚገኝ ሥልጣን ሆኖ መንግሥት የሰው ሕይወት እንደሚያጠፋ እያወቅን ይህንን ለመከላከል የሚያስችል ምንም ዝግጅት ሳናደርግ ርምጃ እንውሰድ የሚል ያውም የፖለቲካ አዋቂነትን» መሠረት ያደረገ ፃሳብ ሲቀርብ በፍፁም ልንቀበለው አንችልም ይህንን ሃሳብ የሚያፈልቅ ጭንቅላት ጤንነት ጥያቄ ውስጥ እንድንከት ተገደድን በዚህም ምክንያት ልደቱ ያቀረበውን ሃሳብ በጣም አጠንክረንና አክርረን ተቃወምነው ይህ የተቃውሞ ፃሳብ ሲቀርብ ጾር ብርፃኑ ነጋ ቀደም ሲል ርምጃ እንውሰድ የሚለውን አቋም ሲደግፉ የነበሩ አባላትም ለምሳሌ አቶ ኃይሉ አሁን ካለው የሕዝብ ድምጽ ይከበር ከሚለው ትግል ጋር ያልተያያዘና ውጤቱም በዚያ የማይለካ ርምጃ መውሰድ እንደሌለበት ተቀበሉ የልደቱን ፃሳብ ከሞላ ጎደል ሁሉም ሰጡ ተቃውሞት ከኢዴአፓ መድኅን የመጡትን አባሎች ጨምሮ ጡድቅ ተደረገ ከዚህ ጊዜ በኋላ ልደቱ እንደገና ክቅንጅቱ አካባቢ በድጋሚ መጥፋት ጀመረ ከሕዝብ ግንኘ ኀት ሥራውም ራቀ የልደቱ የሎጂክ ስህተት የሚመነጨው አንድን ርምጃ በመቃወም እንጂ አማራጭን በግልጽ አውቆ መፍትሑን አያመላክትም ይህ ክርክር በልደቱ ፃሳብ መውደቅ ሲቋጭ በአማራጭ ደረጃ ቅንድቱ የሚከተለውን የትግል ስልት ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ አስቦ አላስቀመጠም በድጋሚ ኮሚቴው ዝርዝር ጥናቱን ያቅርብልን ከማለት በቀር ጥናቱን በቶሉ አስጨርሶ አንድ አጠቃላይ አቋም በቶሎ ይዞ ያንን አቋም ተግባራዊ የማድረግ እንቅስቃሴ መጀመር አልተቻለም በዚህ ጊዜ በግልጽ የተወሰደው አቋም ምርጫው መጭበርበሩንና የኢህአዴግ አሸነፍኩ ባይነት ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ ነበር ለዚህ ችግር የመጀመሪያ ደረጃ መፍትሔ ሊሆን የሚችለው ፍፁም ገለልተኛ በሆነ አካል የምርጫው ውጤት ሲጣራና በዚህ ገለልተኛ አካል ውላኔ መሠረት በድጋሚ ምርጫ ማካሄድ አስፈላጊ ከሆነ በተለይ በተጭበረበሩት ቦታዎችን ድጋሚ ምርጫ ይደረግ እንደሆነ ብዙኋኑ የተስማማበት አቋም ነበር ይህን አቋም እያደር እያጠናከረው የፄደው ደግሞ በተለይ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡና የውጭ ታዛቢዎች አቋማችን ትክክል መሆኑንና ምርጫው በገለልተኛ ወገን የሚጣራበትን መንገድ ማመቻቸት አስፈላጊ እንደሆነ ሲቀበሉ ነው ከዚያም በተጨማሪ በኅብረቱም አካባቢ የነበረው አቋም ከሞላ ጎደል ይኸው ነበር ስለዚህ ይህንን አቋም ይዘን በፖለቲካም ሆነ በዲፕሎማሲው መስመር እየተጓዝን እስከዚያው ድረስ ይጠና የተባለው ጥናት ዝርዝር ደርሶ የረጅም ጊዜ አቋማችንን እንይዛለን ተባለ ይህንን አቋም የያዝነው አቋም ለመያዝ ብቻ ሳይሆን አቋሙ የሚጠይቃቸውን ዝርዝር ሥራዎች ለመሥራት የሚያስችለን ዝግጅት ይኖረናል ብለን አምነናል በቪቢህም መሠረት በዲፕሎማሲው መስክ እኔ ኢንጅነር ኃይሉ እና ዶር ያዕቆብ እንድንሰራ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ድርድርም ካለ ከሥራ አስፈፃሚው መመሪያ እየተቀበልን እንድንደራደር ኢንጅነር ግዛቸው የሚመራው ሌላ ኮሚቴ በምርጫው ወቅት የተከሰቱትን ችግሮች ዝርዝር ከነማስረጃቸው እንዲያዘጋጅ የመጀመሪያው ኮሚቴ ደግሞ የነዛነት ጎህ ሲቀድ በጀመረው መልክ አማራጭ ሁኔታዎችን ገምግሞ ከትንታኔው ጋር የሚመጡ የተግባር ሥራዎች ካሉ እነሱን እንዲያዘጋጅ ከሚዲያው ጋር ያለውን ግንኙነት በሚመለከት ልደቱ ሥራውን በተግባር ስለተወው እና ኢዴአፓ መድኅን በቦታው ዶር ኃይሉን ስለተካ ዶር ኃይሉ ክእነ ደበበ ጋር ሆኖ የሚሰራበት አንድ ኮሚቴ ተዋቅሮ በዚያ በኩል ሥራው እንዲሠራ የሥራ ክፍፍል አደረግን በዚህ መልክ ትንሽ ተዘበራርቆ የነበረው የቅንጅት አሠራር መልክ እንዲይዝ ተደረገ ይህ ሁሉ በሚሆንበት ጊዜ ቅንጅቱ በአደባባይ የሚያደርገው የሕዝቡን ቁጣ ማብረድ ሕዝቡን ትዕግስት እንዲያደርግ መማፀን አብሮ ግን የምርጫው ውጤት በገለልተኛ ወገን እንዲጠራ ጥሪ ማድረግ ነገር ግን ይህ በገለልተኛ ወገን ይጣራ የሚለው ትክክለኛው ጥያቄ አመርቂ መልስ ካላገኘ ስላማዊና ሕጋዊ ትግሉ እንደሚቀጥልና ይህም ምን መልክ እንደሚይዝ በዝርዝር ወደፊት የሚያቀርብ መሆኑን መናገር ነበር ይህንን መልዕክቱን በግል ሚዲያው በኩል ለሕዝብ እንዲደርስ ያደርግ ነበር ይህ የቅንጅቱ «የትዕግስት» ገዞ ጥሪ ግን የሕዝቡን የብስጭት ግፊት ለሁልጊዜም ሊቋቋም እንደማይችል እናውቃለን በቢያው ልክ «ሽማግሌዎች» ትግሉን መምራት አልቻሉም የሚል ቅስቀሳ በራሱ በቅንጅቱ ውስጥ ባሉ ያኮረፉ አባላት ይካፄድ ነበር በውጭ ደግሞ በዩኒቨርስቲው ውስጥ ያሉ ተማሪዎችና ሌሎች ወጣቶች የወላጆቻችንን ድምጽ ለማስከበር በራሳችን እርምጃ እንወስዳለን» እያሉ የሚጋበዙበት ጊዜ ነበር ቅንጅቱ ደግሞ በዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ በኩል ምርጫው በገለልተኛ ወገን የሚጣራበትን መንገድ ይገፋፋ ነበር በዚህ ጊዜ የቅንጅቱ አመራር በሁለት በኩል የሚወጣን እሳት የመከላከልና አጠቃላይ ሂደቱ ፈሩን እንዳይለቅ የማድረግ የማያስቀና ዕዳ ተሸከሞ ነበር በቅንጅቱ አመራር ውስጥ ደግሞ እያደር ያደገው ስሜት መንግሥት ሁኔታውን የማረጋጋትና በሰላማዊ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ሂደቱን ጠብቆ እንዲጓዝ የሚደረግ ኃላፊነቱን የማይወጣ ብቻ ሳይሆን የሕዝቡን እንቅስቃሴ በኃይል ለመደፍጠጥ ምክንያት እየፈለገ እንደሆነ ስለዚህም የሰላምና የማረጋጋቱም ኃላፊነት የወደቀው በተቃዋሚው ላይ እንደሆነ ነበር አንድ ያገኝውን ድምፅ ለተሰረቀ የተቃዋሚ ድርጅት በቅንጅቱ ይሀ ሰሜም ስመሪም ታፅዕፉ ያመጣ ሳይሆ ሰዚሀጋ ዜ ሰፉታፖቻ ዖደሀሃነታ ዳቀሷቃፊሐ ሃደምሮ ፀረ ምርጫው ባፅፊ ፀጥ ቀናተ ውሰፕ የሃወሰኑ ያቀጋቻራጋ ላመራሮቻ ደሀንኑዶቻ በመጴና ዳቦሦስታሇታ ማወሃ ደምረው ፀር ዐታሐይ ለዞ ኃይታን ልደታና ኔ ይ ለአዴይ መሷኖዎቻ ፀ ሰላይ ይደሀሃነታ ሐሥቻ ለየሦሦዕታሦሃታ መሀድ መዝያጋታና ለደፊ ሰድዝ መኅደሇ ቦፉሐመደ ዳያሃን ፅለር ጾር ብርዛኑ ነጋ ውስጥ የነበረው የኃላፊነት ስሜትና አገሪቱ ችግር ውስጥ እንዳትገባ የነበረው መጨነቅ የሚገርም ነበር በዚህ ጭንቀት ውስጥ እያለን ነበር የተወሰነ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ቢሯችን መጥተው እኔን ማነጋገር እንደሚፈልጉ የነገሩኝ በዚህ ወቅት በዩኒቨርስቲ የረሀብ አድማ ለማድረግ እየተዘጋጁ እንደሆነ ይህ የረሀብ አድማ ምንም ውጤት ካላመጣ በዚያው ወደ ትምህርት ማቆምና ሰልፍ ሊያድግ እንደሚችል ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች መሪነቱን ወስደው ሕዝቡን ማታገል ስላልቻሉ እንደሆነ ነገሩኝ እኔም አንዱን የተማሪዎች ስብስብ ይህን አድርጉ ወይም አታድርጉ ማለት እንደማልችል ነገር ግን የቅንጅቱን አቋም ቅንጅቱ በተናጠል የሚደረግ ትግል አመርቂ ውጤት ያመጣል ብሉ እንደማያምን አሁን መንግሥት ግጭት የሚፈጥርበትን መንገድ እየፈለገ ያለ እንደሚመስል በተለይ ከመንግሥት ኃይሎች ጋር በቀጥታ ግጭት ውስጥ ሊያስገባ የሚችል ርምጃ መውሰድ የመንግሥት መሣሪያ እንደሆነ ገለፅኩላቸው ይህም ሆኖ ግን ቅንጅቱ የሕዝብ ድምጽ እንዳይሰረቅና በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ የሚያደርገውን ግፊት እንደሚቀጥልና ቢያንስ ያ ግፊት ውጤት አላመጣም እስኪባል ድረስ ቢታገሱ ጥሩ አንደሚመስለኝ አስረዳሁ በጊዜው በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መሀከል የነበረው ፍርዛፃት ክረምቱ እየተቃረበ ስለሆነ ተማሪው በተደራጀ መልክ ምንም እርምጃ ሳይወስድ ይበተናል የሚል ነበር ይህን ፍርሐት ብረዳም ተማሪው ይበተናል በሚል ምክንያት ሁኔታውን ያለ ጊዜው መግፋቱ በእኔ እምነት ትክክል ነው አላልኩም ይህ ውይይት ምን ያህል እንደጠቀመ አላውቅም ብዙ ሳይቆይ የዩኒቨርስቲው ችግር ተከሰተ የዩኒቨርስቲው ችግር የተጀመረበትን ሁኔታ ሳጤነው እስከ አሁን ድረስ ግልጽ ያልሆነልኝና እንድጠራጠር የሚያደርጉኝ ብዙ ነገሮች አሉ እሁድ ግንቦት ቀን ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ገደማ ጳዕዕጎለሥጋ ድረሰ ምጋጩን ቦዓወቆታ እድ ነሃር ለሐ ዚሀን ዜ ያረ ጋሮ ያኣነሪፇ ንኙኑታም ዕም ዕደሳ ፖቋር ነገር መጀመሪዖ ለጳጓዛ በወዉውጡታ መጋሰጫዎሥቻ ታጎጭዶ ለጋድ ፇ። አንዱ አሰቃቂ ግድያ ከመፈፀሙ አስቀድሞ የምርጫ የነባነት ገዘ ሲቀድ ስኔ ለገድ የሚጀመረሁ ድርድር ሳይ የምንሳተፈው ሁለታችን ነበርን ይህ ድርድር ከመጆመሩ በፊት ግን ሁሉም ድርጅቶች ምርጫው በትክክል አልተካሄደም የሚሉባቸውን ወረዳዎች እና ተከሰቱ የሚሏቸውን ችግሮች ለምርጫ ቦርዮ የቀርቡ ነበር በቅንጾት በኩል እነዚህ ችግሮች ተከስቱ የተባላባቸውና ችገሮች ባይፈጠሩ ኖር ቅንጅቱ ያሸንፍባቸው ነበረ ተብለው በተወሰነ ደረጃ ሠስክ ድረስ ተኪዶ ማስረጃ ለመሰብሰብ የተሞከረባቸው የምርጫ ወረዳዎች ወጠደ አካባቢ ነበሩ ከዚህ ውጭ በሕብረቱም እንደዚሁ የብዙ ዐረዳዎች ዝርዝር ቀርቧል ኢህአዴግም በጣም በሚያስቅ ሁኔታ የአቶ በረክትን ቡግና ወረዳ የአቶ ጁነዲን እና የአቶ አባዱላን ኢተያ ጨምሮ ጥቂት ወረዳዎች እንዲመረመሩልኝ ብሎ አቅትርቧል በጠቅሳሳው ሰምርጫ ቦርድ በአንድ ድርጅት ወይም በሌላ ቅሬታ የቀረበባቸው ወረዳዎች ነበሩ ይህም ማለት ከአጠቃላይ ወረዳዎች ከግማሸ በላይ ነው ስለዚህ የድርድሩ ትኩረት የሚሆነው ኙን ተዓማኒና ገለልተኛ በሆነ መንገድ ማጣራት ነው እንዲጣሩ የቀረቡት ቦታዎች ብዛት በራሱ በምርጫው አሸናፊውን ለመለየት የማያስችል መሆኑን ግልፅ የሚያደርግ ነው ይህ ዝም ብሎ ተቃዋሚዎች ያነሉተ ጥያቂ ብቻ አይደለም ችግሮቹን በሚመለከት ገለልተኛ ወገኖች ባቀረቧቸው ሪፖርቶችም ከስኞ በኋላ የሆነውን ነገር በፍፁም ማንም የማያውቀው ዝግና ጨለማ ሀጳባሀ አንደነበር ገልፀዋል ከዚህ ባሻገር ለሕዝብ በይፋ አይውጣ እንጂ የአውሮፓ ሕብረት ታዛቢዎች ቡድን ባዘጋጀውና ከተለያዩ ቦታዎች ከወስደው ናሙና ጥናት ተነስቶ የአገሪቱን የክተማ ገጠር ስብጥር ከግምት በማስገባት ኢህአዴግ ምርጫውን አንዳላሸነፈ ይልቁንም ሙሉ ለሙሉ ያሸነፈ ድርጅት ባይኖርም ቅንጅት ከኢህአዴግ በሩ አካባቢ የበለጠ ድምፅ እንዳገኘ የሚጠቁም የውስጥ ሪፖርት ለአባላቆች አሰራጭቷል ቅንጅቱ አሸንፈናል የሜለውን ግምት የወሰደው ግን በራሱ ባደረገው ጥናት እንጂ ከዚህ የአውሮፓ ሕብረት ታዛቢዎች ቡድን ጥናት በመነሳት አልነበረም በእኛ በኩል በአብዛኛው የወሰድነው በመጀመሪያ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያገኘናቸው ውጤቶችን ሂደት በመመልከት ቆጣሪዎቹ በመሐል ባይቋረጡ ኖሮ ሊሆን የሚችለውን የወረዳውን አጠቃላይ መስመር ይሀ ሪፖሮታ ዕወማ አዕጎምጋታ ዕጎሪድ ያውግ አረሮ ጋዜወም ቃጂውን ያመጀመሪያ ያሃንፉፉ ኔኔ ዕዘርሉ ስዚዖ በፊ ቦነ ለጭሮ ሪፖረርታ በለንድ ያሄና ለውታረ በሱል ሰራጭቶ ነበር በጴህለዴፇ በትል ሪፖር በታዛቢ ቡድን በትሰ ዳድ ደረሳፇ ሦደረ የሟረሃ ፅፅ ጎተሥ ነው ጾር ብርፃኑ ነጋ በመቃኘት ዞዌርጩዕከዘ የራሳችንን ግምት ወስደናል ከዚህ ግምታችን በመነሳት ቅንጅቱ ሙሉ በሙሉ እንኳን ባያሸንፍ ማለትም ባያገኝ አብዛኛውን ድምፅ የዘዘከ እንደሚያገኝና ከሌሎች ተቃዋሚ ድርጅቶች ለምሳሌ ሕብረት ጋር መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችል ድምፅ አግኝቷል የሚል እምነት ነበረን የአውሮፓ ሕብረት ታዛቢዎች ቡድን የናሙና ጥናት ይህን ግምታችንን አጠናከረልን እንጂ እንደ አዲስ ግኝት አላየነውም ነዘር በሕብረቱ መሪዎች በኩልም የነበረው ግምት ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነበር ስለዚህ ምርጫው ተጭበርብሯል ተቃዋሚዎች ያሸነፉትን ድምፅ ኢህአዴግ በጉልበት ለመውሰድ እየሞከረ ነው የሚለው ክስ ተቃዋሚዎች ለማጋነን ብለው የሚያነሱት አልነበረም በሕዝቡም በኩል የተቃዋሚ ደጋፊዎች ብቻ ሳይሆኑ ለተቃዋሚዎች ያንን ያህል ፍቅር የሌላቸው በአንፃሩ ለኢህአዴግ መለስተኛ ድጋፍ የሚሰጡ ሰዎችም ይህንን አምነውበት ነበር የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ አቶ አማረ አረጋዊ ይህን አምኖ ኢህአዴግ እና አባሎቹ ተደናግጠው የኃይል እርምጃ እንዳይወስዱ በመፍራት «የብሔራዊ አንድነት መንግሥት» መቋቋም አለበት ለአገሪቱ የሚበጀው እና ሰላምና ፍትሕ የሚያመጣው ብሉ በዚሁ ጊዜ አካባቢ በጋዜጣው ርዕሰ አንቀፅ ፃሳቡን ገልፆ ነበር ለአገሪቱ የሚበጀውና ሰላምና ፍትሕ የሚያመጣ ከሆነ ይህን አካፄድ በምርጫ ማኒፌስቷችን ያወጣነውና የደገፍነውም ስለሆነ ፃሳቡን ለመቀበል አዕምሯችን ክፍት ነበር ከዚያ በፊት ግን በመጀመሪያ የምርጫ ማጣራቱ በንፁህ ሁኔታ ተጠናቅቆ የሕዝቡ እውነተኛ ድምፅ ምን እንደሆነ መታወቅ ነበረበት የሰኔ አንዱ ጭፍጨፋ የተካሄደው የማጣራት ሂደቱ እውነተኛ ድርድር ከመጀመሩ በፊት ወይም እየተጀመረ እያለ ነበር ይህ በራሱ በድርድሩ ውስጥ በተቃዋሚዎች ተወካዮች ዘንድ ምቾት የማጣት ስሜት ዉሸፀዌ ፈጥሯል የነበረው ሥነልቦናዊ ድባብ በፍፁም በንፁህ ልቦና ድርድር ሊካፄድበት የሚችል አልነበረም አደራዳሪው ቲም ክላርክም በዚያ ሁኔታ ድርድሩን ከመጀመር ማስተላለፉ ይሻላል የሚል ፃሳብ አቅርቤለት ነበር የእሱ እምነት ግን አንድ ዓይነት ድርድር እየተካሄደ ነው ሰላማዊ የሆነ መፍትሔ እየተፈለገ ነው የሚል እምነት ካልተፈጠረ ግጭቱ ይባባሳል በኋላ መፍትሔ ማፈላለግም በጣም አስቸጋሪ ይሆናል የሚል ነበር አምነቱ ከእውነተኛ ስሜት ጋር የተደባለቀ ምክንያት በመሆኑ ድርድሩ እንዲቀጥል ሆነ የነዛነት ገህ ሲቀድ ይህም ሆኖ ግን በመጀመሪያው ቀን ብዙም አርምጃ ሳንራመድ ለሚቀጥለው ቀን ቀጠር ተይዞ ተለያየን አሁንም ድርድሩን ከመቀጠል ሌላ አማራጭ የለም የሚለው ግምት የሁላችንም ነበር ለማንኛውም ድርድሩ የሚያተኩረው የማጣራት ሂደቱ ገለልተኛ እንዲሆንና በሁሉም ዘንድ ተዓማኒነት እንዲያገኝ በምን መልክ እንዓጓዝበት የሚል ጉዳይ ላይ ስለነበረ አደራዳሪው ቲም ክላርክ የምርጫ ቦርድን ለማማክርና የምርጫውን ሂደት ለማገዝ ከለጋሽ አገሮች በተዋጣው ገንዘብ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም አስፈፃሜነት የተቀጠረው ዓለም አቀፍ የምርጫ ማሻሻያ የባለሙያዎች ድርጅት ኡሪስ ደቨ የመነሻ ሃሳብ ይዞ እንዲመጣ ኃላፊነት ተሰጥቶት ስለነበር አሱ ይዞ በመጣው መንደርደሪያ ላይ ነበር ድርድሩን ያስጀመረው ድርድሩ ተግባራዊ ሥራውን የጀመረው ይህንን በኤሪስ ኃላፊ ሜር ሪቻርድ በሚባል ሰው የቀረበውን የመነሻ ሣሳብ ከነምክንያቶቹ ከሰማን በኋላ ነው የመንደርደሪያ ጽሑፉ በተለያዩ የሂደት መግለጫ ላዕሎች ዩየ ርከህ ታጅቦ የቀረበ የባለሙያ ሥራ ይመሰላል በጥቅሉ የሪቻርድ መግለጫ ሂደቱን በሁለት ከፍሉ ያየዋል የመጀመሪያው ቅድመማጣሪያ ሂደት ሲሆን ሁለተኛው ዋናው የማጣሪያ ሂደት ነበር የቅድመማጣሪያ ሂደቱ በራሱ በምርጫ ቦርድና የምርጫ ቦርድ በቀጠራቸው «ገለልተኛ» የሕግ ባለሙያዎች አማካይነት በዚያው በምርጫ ቦርድ የሚካሄድ ሲሆን ዋናው ሥራው ምንም መሠረት ወይም ጭብጥ ያልቀረበባቸውን ጉዳዮች በቶሎ ማስወጣት ነበር ከዚህ አንፃር በምሳሌነት የቀረበው አንድ ጉዳይ አንድ ተወዳዳሪ ሕገ የሚጠይቀውን የሁለት ዓመት የመኖሪያ ሁኔታ አላሟላም የሚል ስሞታ ቢያቀርብ ይህን በቀላሉ የምርጫ ቦርድ ሠራተኞች ከዋናው የማጣራት ሂደት ሲያስወጡት ይችላሉ የሚል ነበር ምክንያቱም በሕጉ መሠረት እንዲህ ዓይነት ስሞታ መቅረብ ያለበት የተመራጮች ምዝገባ ሲጠናቀቅ እንጂ አሁን ምርጫው ከተደረገ በኋላ አይደለም እንዲህ ዓይነት ቀላልና ምንም የሕግ መሠረት የሌላቸውን በቶሉ ማጣራት የዚህ የቅድመ ማጣራት ሥራ ይሆናል ተብሉ ቀረበ ሁለተኛው ደረጃና ዋናው የማጣራት ሂደቱ የሚሠራው እዚያው ችግሩ በተፈጠረበት ወረዳ ሲሆን አጣሪ ቡድኑ የቀረበለትን አቤቱታ እውነተኛነት ማጣራት በቀረቡት መዛግብቶች ምስክሮችን በመስማት ወዘተ ሆነ ከቀረበለትም ማስረጃ ውጭ የራሱን ማስረጃ የማሰባሰብና በዚያ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔ የመስጠት ጾር ብርፃኑ ነጋ መብት አለው ይህ ውሳኔ ግን በመጨረሻ የሚፀድቀው በምርጫ ቦርድ ሆኖ ምርጫ ቦርድ ውሳኔውን የመሻር መብት ይኖረዋል የአጣሪ ቡድኑ የሚዋቀረው ከከሳሽና ከተክሳሽ በተውጣጡ አንዳንድ ሰዎች ሆኖ ይመለከተኛ ል የሚል ሦስተኛ ወገን ካለ ድርጅቱ ቢያንስ ድምፅ ያገኘ መሆን አለበትን አሱም በአንድ ሰው መወከል ይችላል ከሳሽና ተከሳሽ ብቻ ባለበት የምርጫ ቦርድ የቡድኑ ሰብሳቢ ሆኖ ውሳኔው ላይ ሁለቱ ቡድኖች ከተለያዩ ወሳኙን ድምፅ ይሰጣል ሦስተኛ ወገን ሙግቱ ውስጥ ከገባ ምርጫ ቦርድ በሁለት ሰው ይወከልና አሁንም ወሳኙን ድምፅ ይሰጣል በሁሉም የማጣራት ሂደት ውስጥ ወሳኝ አካል የሚሆነው የምርጫ ቦርድ ይሆናል ማለት ነው ይህንን የኤሪስ ሰነድ ቅንጅቱም ሆነ ኅብረቱ በሁለት መሠረታዊ ፍሬ ነገሮች በመነሳት ተቃውመውታል በመጀመሪያ የቅድመማጣራት ሂደቱ በሙሉ በምርጫ ቦርድ እጅ መውደቁ በፍፁም ተቀባይነት አይኖረውም ይህ የሪቻርድና የኤሪስ ሰነድ መነሻ የሚያደርገው አመለካከት ምርጫ ቦርዱ በፍፁም ገለልተኛ ነው ከማንም ጋር አይወግንም አለመወገን ብቻ ሳይሆን እንደዚህ ያለን የፖለቲካ ውጥረት ከመርህ አንፃር በመመልከት ለመፍታት የሚያስችለው የሰውና ተቋማዊ ብቃት አለው በውስጡ የሚሠሩት ከቦርዱ እስከ ጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች ድረስ በመንግሥትና በገዢው ፓርቲ የሚመጣባቸውን ጫና ለመቋቋም የሚያስችል የሞራል ወኔ አላቸው የሚል ነው ተቃዋሚ ድርጅቶች ካላቸው የረጅም ጊዜ ልምድ አኳያ የዚህን መነሻ ፃሳብ እውነትነት የሚጠራጠሩት ብቻ ሳይሆን ሐሰትነቱን በተግባር የሚያውቁት ነው በዚህም ምክንያት ተቃዋሚዎች የምርጫ ቦርድ እንደገና ገለልተኛ ሆኖ ካልተዋቀረ በስተቀር በምርጫው ውስጥ አንገባም ብለው ተቃውመው በዚህ ዙሪያ ብዙ ድርድር ተደርጎ ኢህአዴግ በምንም ዓይነት በዚህ ላይ አልደራደርም ብሎ ምርጫው ከሚቀር ወይም ኢህአዴግ ብቻውን ከሚሮጥ እንሞክረው ብለው የገቡበት ነው ከዚያም አልፎ የማጣራቱ ሂደት ይካሄድ ተብሎ ድርድር የተቀመጥነው ራሱ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በትክክል ማካሄድ ባለመቻሉ በተፈጠረ ቀውስ ምክንያት ነው ስለዚህ ለዚህ ድርጅት ለብቻው ይህን ኃላፊነት መስጠት በፍፁም የማይታሰብ ነው ቅድመማጣራት ሂደቱ በራሱ መጣራት አያስፈልጋቸውም የሚለውን ውሳኔ ከሰጠ በኋላ አቤት የሚባልበት እንኳን በሌለበትና የቅድመ የነባነት ገህ ሲቀደድ ማጣራት ሂደቱን የሚወስኑት ጉዳዮች ርያቭፀዘወ ግልፅ ባልሆነበት ሁኔታ ውሳኔውን ለምርጫ ቦርድ መተው ጠቅላላ ማጣራቱን ምርጫ ቦርዱ ያድርገው ከሚለው የተለየ አይሆንም ከቀረቡት አዜቱታዎች ውስጥ በቅድመማጣራት ሂደቱ ምርጫ ቦርድ የሚፈልገውን ውድቅ ቢያደርገው በተግባር የምርጫውን ውጤት ወሰነው ማለት ነው ስለዚህ ይህ የሚያስኬድ አይደለም ይልቁንስ ተቃዋሚዎችም ሆኑ ገዢው ፓርቲ በእኩልነት የሚሳተፉበት የቅድመማጣራት ሂደት ያስፈልጋል አለበለዚያ ቅድመማጣራት የሚባለው ቀርቶ ሁሉም ቦታዎች በቀጥታ በአጣሪ ቡድኑ መጣራት አለባቸው የሚል አቋም ያዝን በሁለተኛ ደረጃ በማጣራት ሂደቱም ቢሆን የፓርቲዎች ተወካዮች ቢኖሩበትም በዋናነት ውሳኔውን የሚሰጠው ምርጫ ቦርድ ነው ተፎካካሪ ፓርቲዎች የየራሳቸውን አቋም ይዘው ውሳኔው በድምፅ ብልጫ ከተወሰነ በተግባር ወሳኝ አካል የሚሆነው የምርጫ ቦርድ ነው ይህ ደግሞ ከላይ ለማቅረብ እንደ ተሞከረው የምርጫ ቦርድ ፍፁም ገለልተኛና እውነተኛ ባለሙያዎች የሞሉበት መሥሪያ ቤት ቢሆን ኖሮና በምንም ዓይነት ለጉልበት የማይንበረከኩ ወይም በጥቅም የማይገዙ ቢሆኑ ምንም ችግር አልነበረውም ግን የአገራችንን ሁኔታ በአጠቃላይ በተለይ ደግሞ የምርጫ ቦርድን በደንብ ስለምናውቀው ምርጫ ቦርድ ፍትሐዊ ውሳኔ ይሰጣል ብሎ መጠበቅ አይቻልም ቀድሞውኑም የምርጫ ቦርዱን መሠረታዊ ችግር በተደጋጋሚ ስንገልፅ ሰሚ ቢኖር ኖሮ እዚህ ችግር ውስጥ አንገባም ነበር አሁንም ለዚህ የምርጫ ችግር ዘላቂ መፍትሔ ከሆነ የምንፈልገው የምርጫ ቦርድ ዋና መሳሪያችን ሊሆን አይችልም የሚል መከራከሪያ አቀረብን ለእነዚህ መቃወሚያዎች የሚቀርበው አንፃራዊ መከራከሪያ በተሰይ በሪቻርድ በኩል በመጀመሪያ በአገሪቱ ሕግ ይህንን የማጣራት ሂደት በባለቤትነት መምራት የሚችለው የምርጫ ቦርድ ነው። ከዚህ ጊዜ ጥቂት ቀደም ብሎ ለኢህአዴግ ትንሽም ቢሆን አዎንታዊ አመለካከት ባለው ሪፖርተር ጋዜጣም ይህ ሃሳብ መንፀባረቁ በኢህአዴግ ውስጥ ይህንን ሃሳብ የሚያንሸራሽሩ ለዘብተኛ የሆኑ ኃይሎች ሊኖሩ ይችላሉ የሜል ግምት ነበር ጊዜው ከኅብረቱ ጋር በቅርብ የምንሠራበት ነበር በእኛ በኩል ማወቅ ከምንፈልጋቸው ነገሮች አንዱ ኅብረቱ በዚህ ትግል እስከምን ድረስ ይሄዳል የሚለውን ነበር ይህንን ጥያቄ በቀጥታ ከዶር መረራ ጋር ነበር የመከርኩበት ዶር መረ ራ በዚህ ሂደት ከብሔራዊ አንድነት መንግሥት ያነሰ አንቀበልም የሚል አቋም ነበረው ይህ አቋም ደግሞ የሱ ብቻ ሳይሆን የኅብረቱም እንደሆነ ነበር የገለፀልኝ ከዚያም አልፎ ግን ኅብረቱ ይህንን በተመስከተ አንድ ጽሑፍ ዖጩይዐ እያዘጋጀ እንደሆነና ቅንጅቱ ፃሳቡን በጥቅሉ የሚደግፈው ከሆነ የራሱን ዛሃሳብ አቅርቦ ከሁለታችን የተጨመቀ ሃሳብ በጋራ ማቅረብ እንደሚቻል ይነግረኛል ኅብረቱ ሲቋቋም ጀምሮ ከምርጫ በኋላ መፍጠር የሚፈልገው ብሔራዊ አንድነት መንግሥት እንደሆነ በኅብረቱ አባል ድርጅቶች ዘንድ ስምምነት ስለነበር ሃሳቡን የሚቀበሉት ብቻ ሳይሆን አጥብቀው የሚፈልጉት ነበር ቅንጅቱ የኅብረቱን የቀድሞ አቋም አልደገፈውም ኅብረቱን ጥለው የወጡት የቅንጅት አባል ድርጅቶች ከኅብረቱ ጋር የተለያዩበት አንዱ ነጥብ ይኸው ነበር በወቅቱ ድርጅቶቹ ምርጫ ላይ ከተሳተፍንና ሕዝቡ ድምጽን ከሰጠ በኋላ በውጭ የሚገኙትን ድርጅቶች ለማስገባት በሚል ጊዜያዊ የሆነ የሽግግር መንግሥት የሚቋቋምበት ምክገያት የለም የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ያሸነፈው ድርጅት ወይም የድርጅቶች ጥምረት የመንግሥት ሥልጣኑን ይረከባል የተመረጠበትን ጊዜ ይጨርሳል በእርግጥ አሸናፊው ድርጅት የፖለቲካ መረጋጋት ለመፍጠርና የተገለሉ የፖለቲካ ኃይሎችን ለማካተት ብሎ የነፃነት ገዝ ሲቀድ በዚህ መንግሥት ውስጥ ሊያስገባቸው ይችላል ተገቢም ነው ሕገ መንግሥቱም የሚፈቅደው ይህንን ነው ግን በምንም ዓይነት ጊዜያዊ መንግሥት አይሆንም» የሚል ተቃውሞ አቅርበው ነበር ከምርጫ ማጣራት ሂደቱ መክሸፍ በኋላ ለተፈጠረው የፖለቲካ ችግር ግን እንደ መፍትሄ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ፃሳብ አግባብነት ይኖረዋል ምርጫው ግልጽ ውጤት ባልሰጠበትና በተጨበረበረበት ሁኔታ ተጭበረበርኩ ከሚሉት ድርጅቶች ይህ ሃሳብ መቅረቡ ድግሞ የድርጅቶቹን ሠላም ፈላጊነት እና አርቆ አስተዋይነት እንዲሁም ከምንም በላይ ለአገሪቱ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ማበብ እንደሚጨነቁ ስለሚያሳይ ስለዚህ ቅንጅቱ ይህንን መደገፍ አለበት የሚል አቋም አያደር እየጠነከረ መጣ ከዚያም በላይ ግን ቅንጅቱ በምርጫ ማኒፌስቶው የብሔራዊ ዕርቅን አስፈላጊነት በሰፊው የሰበከበት በመሆኑ ይህ አካፄድ ከቅንጅቱ አጠቃላይ መርሆ ጋር የሚጋጭ ሳይሆን ተደጋጋሚ መሆኑ ታመነበት ከሕብረቱ ጋር በሚደረገው የጋራ መድረክ ቅንጅቱን ወክለን የምንገኘው እኔ ዶር ሽመልስ ተክለፃድቅ አንዳንዴም ደግሞ ቸኮል ነበርን እኛ ከኅብረቱ ጋር ባደረግነው ውይይት ይህ ሃሳብ ተነስቶ በተጠቀሱት ምክንያቶች አምነንበት ስለነበር ጉዳዩን ከመግፋታችን በፊት የሥራ አስፈፃሚውን ፈቃድ ማግኘት ነበረብን የሥራ አስፈፃሚው አባላትም በጉዳዩ ላይ ከመከሩበት በኋላ ሃሳቡን እንደሚደግፉት ገለጹ ነገር ግን ይህ ጉዳይ ጥንቃቄ የሚፈልግ ዘሀ ስለሆነና በዚያን ጊዜ የሥራ አስፈፃሚው ስብሰባዎች በማናውቀው መንገድ እየተቀዱ በኢፍቲን ጋዜጣ ላይ ይወጡ ስለነበር ነገሩ በዝርዝር ለሕዝብ ከመገለጹ በፊት ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተሉና ከኅብረቱ ጋር በጋራ ሆነው አንዲወስነ የአራቱን ድርጅቶች በቅንጅት ውስጥ የተካተቱንና የሥራ አስፈፃሚው አባላት የሆኑትን መሪዎች ይወክላል በዚህን ጊዜ ከኢዴአፓመድኅን ዶር አድማሱ በህመም ምክንያት ብዙ ጊዜ ስብሰባ ስለማይመጣ ዶር ኃይሉ አርአያ ተወክሎ ነበር እነዚህ አራት ሰዎች የቅንጅቱን አቋም አንድናዘጋጅና ዋና ዋና ነጥቦቹን ከተነጋገርን በኋላ ከኅብረቱ ጋር ተደራድረን የመጨረሻውን ውጤት ለውሳኔ እንድናቀርብ ከኅብረቱ ጋር ለመደራደር ውክልና ሰጡን በዚህን ጊዜ በኅብረቱ በኩል በዶር በየነ በኩል ሪዚሀ ዜ እቭዚሀ ለራት ሐሥቻ የሦወስታታ ሰዚሀ ሦዳይ ይ ብቻ ሳይፖጋ ማሃቅውም ዕዕ ሂዜያቻው ሦዕፇኛ ወ እቾ ዕወደቆ ቀጪኞጋ ያሚ ወይም ያሕሃያጋያ ዕሜፖ ጥርጣሪ ውዕምፖ ያሟፅራታ ፖዳዶዖቻ ኋዲኋታታታና ዳዲወዕ ያረ ጾር ብርፃኑ ነጋ የመጀመሪያው ረቂቅ በውጭ የተዘጋደ የሚመስል የተዘጋጀው ረቂቅ አልቆ ነበር ይህንን ረቂቅ ቀደም ብሎ ዶር በየነ ለቲም ክላርክ ከመንግሥት ጋር አደራዳሪው እሱ ስለሆነ ሳያሳየው አልቀረም ለማንኛውም እኔም ከዶር በየነ ኮፒውን አግኝቼ አይቼው አልጣመኝም ነበር ጽሑፉ ከዚህ ቀደም በነበረው የኅብረት አቋም ላይ በመመሥረት የቀረበ እንጂ አሁን ያለንበትን የተለየ ሁኔታ ያገናዘበ አልነበረም ለምሳሌ ለዚህ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ዕድሜ የተወሰነ ገደብ ይሰጥና በዚህ መንግሥት ውስጥ በምርጫው የተወዳደሩ ብቻ ሳይሆን ከምርጫው ውስጥ እንዲያውም ያልገቡ አገር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ያልተመዘገቡ ድርጅቶችንም ማካተት አለበት ይላል ከዚያም በላይ የዚህ ብሔራዊ አንድነት መንግሥት አንዱ ሥራው ለአገሪቱ ሌላ ህገመንግሥት ማውጣትን እንደሆነ ያትታል በእኔ ግምት እንደዚህ የሰፋ ኃላፊነት የተሰጠውን መንግሥት ኢህአዴግ እንዲቀበል መጠየቅ የሚያስኬድ አልነበረም በዚህ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ጥያቂ ላይ መካተት ያለበት ዋና ዓላማ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በእግሩ ማቆም እንደሆነና ለዚህ ደግሞ የሚያስፈልገው ወላኝ የሆኑ የዴሞክራሲ ግንባታ ተቋማትን በተለይ ፍርድ ቤቶችን ምርጫ ቦርድን የደኅንነት ኃይሉን ፓርላማን ወዘተ ፍጹም ነፃና በሕገመንግሥቱ መሠረት እንዲሰሩ ማድረግ ስለሆነ ይህንን በማይጎረብጥ መልኩ ማቅረቡ እንደሚመረጥ አምኛለሁ በዚህ መሠረት እኔና ዶር ሽመልስ በሰፊው ተነጋግረንና ከቅንጅቱ አመራር የተሰጡትን ነጥቦች ወስደን አንድ ዝርዝር ጽሑፍ አዘጋጀን ይህንንም ጽሑፍ ለተወከሉት የቅንጅቱ አመራሮችና ለኅብረቱም አመራሮች ከውይይታችን በፊት እንዲያዩት ላክንላቸው የተወከሉት የቅንጅቱ አመራሮች መስማማታቸውን ከገለጹልን በኋላ የሚያርሙትን አርመው ከኅብረቱ አመራር ጋር በእነሱ እና በእኛ ጽሑፍ ይዘት ላይ ተወያየን በዚህም መሠረት ከሁለቱ የተውጣጣ አንድ ጽሑፍ ተዘጋጀ ይህም ጽሑፍ በቅንጀቱ ተወካይ አመራር የመጨረሻ ስምምነት አግኝቶ በቅንጅቱና በኅብረቱ ማሕተም እኔና ዶር በየነ ፈርመንበት የጋራ ዶክመንት ሆኖ ለኢህአዴግና ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ተላከ ይህ ጽሑፍ ከአባሪ ደብዳቤ ጋር ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተላከው ከዚህ ጋር በቀጥታ ባልተያያዘ ጉዳይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የመጀመሪያ ውይይት አድርገን ስለነበርና ከዚያ ውይይት በኋላ አቶ መለስ ከእኛ የሚጠብቀው መልስ ስለነበር በኅብረቱና በቅንጅቱ በኩል ላለንበት ችግር የነፃነት ጎህ ሲቀደ መፍትፄ መሆኑን የምናምንበትን መልስ በዚህ አጋጣሚ መስጠቱ ይጠቅማል ብለን ስላመንን ነው ስለዚያ ውይይት ትንሽ ቆይተን እንመለስበታለን ይህ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ዛሳብ በዝግጅት ላይ አያለና ኢህአዴግ ከቅንጅቱ የቀረቡለትንና ያሉትን የማግባቢያ አማራጮች በሙሉ እየዘጋ ባለበት ወቅት የቅንጅቱ አቅጣጫ ምን መሆን አለበት የሚል ውይይት ከሕዝቡ ጋር ማድረጉ ይበጃል የሚል አቋም ይዘን ነበር በዚህም መሠረት የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ይወክላሉ የተባሉ ሰዎችን እየጋበዝን ማወያየት ጀምረን ነበር ለዚህ ውይይት መንደርደሪያ የሚሆን ጽሑፍ እኔ እንዳዘጋጅ ኃላፊነት ተሰጥቶኝ ስለነበር የምርጫውን ሂደት በመዘርዘር አሁን የደረስንበት ደረጃ ላይ እስከምንደርስ ድረሳ በቅንጅቱ በኩል የቀረቡ የስምምነት ፍለጋ ዛፃሳቦችን በመዘረዝር በአንድ ቦታ የቅንጅቱና የኅብረቱን የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ጥያቄ ጠቀስ ያደርግ ነበር ይህን ያደረግሁት ሆን ብዬ ነበር በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ይህ ዛሳብ ለሕዝብ ይፋ ስለሚሆን በዚህ አጋጣሚ የተሰብሳቢውን ስሜትም ለማወቅ ነበር በእነዚህ ውይይቶች በአጋጣሚ ትልቅ ትኩረትን የሳበው የፓርላማ መግባትና አለመግባት ጉዳይ ነበር በአጠቃላይ እነዚህ በተመረጡ ሰዎች ዘንድ ይቀርብ የነበረው ፃሳብ ሁሰት ዓይነት ቅኝቶች ነበሩት አንዱ ቅንጅቱ እየሄደ ያለበትን የትዕግስት ጉዞ በማድነቅ ነገር ግን ኢህአዴግ ምንም ላለመስጠት የወሰነ እንደሚመስልና ይልቁንም የዴሞክራሲ ሂደቱን እየቀለበሰ አንደሆነ በተለይም አዲስ የወጣው የፓርላማ ሕግ በፍጹም የማይሠራና ዝም ብሎ አድማቂ ከመሆን ሌላ ፋይዳ የሌለው ስለሆነ ፓርላማ አትግቡ የሚል ድምፀት ያለው ነበር ሁለተኛውም እንደዚሁ የቅንጅቱን የትዕግስት ሂደት አድንቆ ኢህአዴግ በጣም የተሽበረ እንደሆነና አገሪቱን ችግር ውስጥ ሊከታት እንደሚችል አሁንም የበለጠ ከቅንጅት ትዕግስት እንደሚጠብቅ ፓርላማ ገብቶ የማያሰራ ከሆነ ጥሎ መውጣት እንደሚሻል በሕዝቡ በኩል ያለው ቁጣ ሊፈነዳ እንደሚትል በዋናነት ግን የዴሞክራሲያዊ ሂደቱ ላይ ማተኮርና ኢሕአዴግ ሥልጣኑ ሳይነካበት የዴሞክራሲ ሥርዓቱን በመገንባት ላይ እንዲተባበር እንኳን ማድረግ ቢቻል የተሻለ እንደሆነ የቀረበ ክርክር ነው በእነዚህ ስብስባዎች የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ጉዳይ ኢህአዴግ ቢቀበለው ጥሩ እንደሆነ ግን እንደማይቀበለው ከመነሳቱ በቀር ዝርዝር ውይይት አልተደረገበትም በነጋታው ጋዜጦች ላይ ሲወጣ ግን ለስብሰባው ከቀረበው ጽሑፍ ላይ ጾር ብርፃኑ ነጋ ተቀንጭቦ ይህ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ጉዳይ ይዘገባል በዚህን ጊዜ ለረጅም ጊዜ ከቅንጅቱ ስብሰባም ሆነ ውይይት ጭራሽ ጠፍቶ የነበረው ልደቱ ሁለተኛውንና ከቅንጅት ጋር መታገያ የሚሆነውንና በሕዝብ ዛንድ ተቀባይነት የማይኖረውን ዛሳብ ያገኘ መስሎት ይሰፍርበታል የሄደበት አካፄድ ግን ቅንጅቱ ተሳስቶ ከሆነ ከስህተቱ ለማረም ሳይሆን በቅንጅቱ ውስጥ ልዩነትን ለመፍጠር አባላትን ማሰባሰቢያ ማድረግ ነበር ነገሩን በጋዜጣ እንዳየው በመጀመሪያ ለቅንጅቱ የኢዴአፓመድህን ተወካዮች በድርጅቱ ሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ ይህን የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ፃሳብን በአይቤክስ ሆቴል ለተደረገው ስብሰባ ጽሑፉን ያዘጋጀው ማን እንደሆነ ይጠይቃል ዶር ኃይሉም በስብሰባው ላይ የተረበውን ጽሁፍ እኔ እንዳዘጋጀሁት ይነግረዋል በጽሑፉም ላይ የቅንድቱ ሥራ አስፈፃሚ እንዳልተወያየበትና መወያየትም አንዳላስፈለገው ይነግረዋል ይህንን ጽሑፍ ማን አዘጋጀው። ፇ ያጥሂታ ሰሥቻ መፅነሳ በሚደረሦ ውይይፉጾ ይሀ በመጩረሻ ያምዝሰው ሳህ ላ ርሆን በቂ ፇቃዛ ጎር ሐዚሀ አው በፇርላማ መጋግዛ ውኔ ይ እህዚሀ ሃሳጦቻ ፈረዙ ያ ብዙ ርዘዝር በሙሉ ድምጽ ጎፊው ጾር ብርፃኑ ነጋ መሄዱን የሚያረጋግጥ ከሆነ ብቻ ነው የሚል ነበር ኢህአዴግ በምርጫ ከዚህ በፊት የነበረውን ዓይነት ተቃዋሚዎች በቃን አሁንስ ስልጣን ሰለቸን» ብለው በራሳቸው ስልጣናቸውን እስኪለቁ ድረስ አሉ አለ ብሉ ለማውራትና ዴሞክራሲን ለፈረንጆች ማሻሻጫ ለማድረግ አስቦ ይህንን ደግሞ ተቃዋሚዎችን በማስፈራራትና በኃይል ለመተግበር ከቆረጠ ቅንጅቱ በምንም ዓይነት የዚህ ዓይነት ጨዋታ አካል አይሆንም የዚህ አካል የማይሆነው ደግሞ የመርህ ጉዳይ ሆኖበት ብቻ አልነበረም የምርጫ ውጤት ይህ ከሆነና እውነተኛ ዴሞክራሲን ማምጣት ካልቻለ ቅንጅቱ ወደደውም አልወደደውም ከ በኋላ የሚኖረው ፖለቲካ ሰላማዊ ፖለቲካ መሆነ ቀርቶ በሰላማዊ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ማምጣት አይቻልም ብለው የወሰነ ኃይሎችና በተለያዩ የኢህአዴግ ስህተቶችና በደሎች የተማረሩ ኃይሎች ተባብረው ጠመንጃ አንስተው የሚፋለመብት ሁኔታ ይፈጠራል በዚህም ምክንያት ቅንጅቱ ከልቡ የሚያምንበትና የታገለለት የሰላምና የዴሞክራሲ ዓላማ ራሱ ገደል ይገባል ስለዚህ ኢህአዴግ ነገሩ ሁሉ ድንገተኛ ሆኖበት ከሥልጣን አልወርድም ብሎ ምርጫውን ካጭበረበረ ቢያንስ ሥልጣኑ ላይ ቆይቶም ቢሆን በነዚህ የዴሞክራሲ ሥርዓት መሠረት በሆኑ ጉዳዮች ላይ በህገመንግሥቱ ላይ በግልጽ የተፃፉ መስማማት አለበት አሁን አልተዘጋጀሁም ህዝቡም ባይፈልገኝ ከሥልጣን አልወርድም ብሉ ሙጭጭ ካለና ቅንጅቱ እያመመውም ቢሆን ሰላምን በመሻት በአሁኑ ዙር የሕዝብን ድምጽ ማስከበር እንኳን ባይቻል በሚቀጥሉት ምርጫዎች በእውነተኛ የሕዝብ ተመራጮች የመንግሥትን ሥልጣን የሚረከቡት ሰብዓዊ መብቶች የሚከበሩበት ነፃ የሆነ ፍትሐዊ ሥርዓት የሚኖርበት የፖሊስ የደኅንነትና ወታደራዊ ኃይሉ ከፖለቲካ ፍጹም ነፃ ሆኖ ሙያዊ ተግባሩን የሚያከናውንበት በአጠቃላይ ማኅበረሰቡ ከፍርሃት ነዛ ወጥቶ የነዓነት አየር የሚተነፍስበት ሁኔታ ከተፈጠረ የዚህን ምርጫ ቀውስ ለመፍታትና አገሪቱን ለማረጋጋት ይችላል ብሎ ካመነ እንቀበለው ኢሕአዴግ ይህንንም መቀበል ካልቻለ ወደፊት በሌሎች ኃይሉች በኃይል እስከሚወርድ ወይም በአንድ ተዓምራዊ ኃይል የኢሕአዴግ ሰዎች «አይ ይበቃናል» እስኪሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአገዛዝ ሥርዓት ሥር እንዲማቅቅ መፍረድ ነው የሚሆነው ይህ አካሄዱ ደግሞ ሰላምን ሳይሆን ብጥብጥን ፖለቲካዊ መረጋጋትን ሳይሆን ትርምስን እድገትና ብልጽግናን ሳይሆን ድህነትን የሚያባብስ ነው ስለዚህ የቅንጅቱ የመጨረሻ «ቀይ መስመር» እነዚህ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የነባነት ገህ ሲቀድ መሠረቶች ተግባራዊ መሆናቸውን በድርድር ማረጋገጥ ነው ይህ ከተገኘ በእርግጥ ከዚያ በላይ የሚጠብቀውንና የሚነሳውን ድምጹ ይከበር ብሎ የሚጮኸውን ሕዝብ ለትንሽ ጊዜ እንዲታገስ ማግባባት አንችላለን የሚል እምነት ነበረን ይህ አጠቃላይ ግንዛቤም ስለነበረ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ፕሮፖዛል በቅንጅቱ በኩል ሲዘጋጅ የብሔራዊ አንድነት መንግሥቱ ይሰራቸዋል ተብለውወ የተዘረዘሩት እነዚህ ዋና ዋና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገለጫዎች እንዲሆኑ የተደረገው ይህንን የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ፕሮፖዛል ስናዘጋጅ ኢህአዴግ አንደማይቀበለው ግምት ነበረን ምንም እንኳን ራሳችንን በኢህአዴግ ጫማ ላይ አድርገን ፖለቲካን ከጊዜያዊ ሥልጣን ባሻገር ለሚያይ ድርጅትና በምርጫ ከተፈጠረው ችግር አንፃርና ሥልጣን ላይ አወጣጥን ብቻ ሳይሆን ጥሩ አወዳደቅንም ከስሌት ለሚያስገባ ብልህ ድርጅትና መሪ ይህ ፕሮፖዛል በጣም ደግ ፕሮፖዛል ነው ብለን ብናምንም ስለዚህም ከብሔራዊ አንድነት መንግሥት በታች እንሄድበታለን ያልነው በዚህ ፕሮፖዛል ላይ ያለውን የሥልጣን ጥያቄ ስናወጣ እስከሚቀረው የዲሞክራሲ ግንባታ ጥያቄ ድረስ ነው ይህንን የመጨረሻ ያልነውንና «ቅንጅቱ ከዚያ በታች ሊፄድ አይችልም» የምንለውን ይዘን ነበር ኢህአዴግን ለማግባባት ሙከራ ያደረግነው ማድረግ የጀመርነው እነዚህን የማግባባት ሙከራዎች የተለያዩ መስመሮች በመጠቀም ለመግፋት ሞክረናል ለዲፕሎማቶችና በውጭ ከሚገኙ ኢህአዴግ ሊሰማቸው ይችላል ላልናቸው ኃይሎች ባገኘ ናቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ገልጸናል የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ ኮፊ አናን አዲስ አበባ በመጡ ጊዜ ባረፉበት ሆቴል ቀጠሮ ተይዞልን አግኝተን ጉዳዩን በዝርዝር ነግረናቸዋል በመጀመሪያ ስናገኛቸው እኔ ኢንጅነር ኃይሉ ዶር በየነና ዶር መረራ ሆነን ሲሆን ገና የምርጫው ችግር እንደተፈጠረና የማጣራት ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት ነበር ከዚያ በኋላ ግን ቢያንስ ሦስት ጊዜ በቴሌ ኮንፈረንስ ተገናኝተን የመጨረሻው ፓርላማ የመግባት ውሳኔ ለመወሰን ስብሰባ ላይ እያለን ይህንን የመጨረሻ ያልነውንና እሳቸውም አቋማችን አምክህኖታዊ እንደሆነና በዚህ ምክንያት አገሪቱ ግጭት ውስጥ መግባት የለባትም ያሉትን ሳብ አቅርበናል ከዚያ ውጪ የኮፊ አናን ልዩ መልዕክተኛ የሆኑትን አምባሳደር ሳህኑንን እኔ ራሴ በግሌ አግኝቼ ይህንን አቋማችን በዝርዝር አስረድቻለሁ ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር የታተመውን ሪፖርታቸውን ለማቅረብ የመጡ ጊዜ እንደዚሁ ለአንድ ሰዓት ያህል ተገናኝተን ምርጫው እንደተጭበረበረ እያወቅን ጾር ብርፃዛኑ ነጋ የእሳቸውም ወኪሎች በግልጽ እያወቁ ሌላው ቢቀር የካርተር ማዕከል ሪፖርት የምርጫ ማጣራት ሂደቱ ከንቱ አንደነበር በመጨረሻው ሪፖርትም ገልጾታል ለሰላምና ለመረጋጋት ብለን ሥልጣነንን ትተንላቸው በእነዚህ የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደቶች ላይ እንወያይም ብንላቸው እምቢ ብለዋል ስል ነግሬያቸዋለሁ እሳቸውም የአቋማችንን ለዘብተኛነት አድንቀውና የጥያቄያችንንም ትክክለኛነት ተቀብለው ወደ አሜሪካ ሲሄዱ እግረ መንገዳቸውን ለንደን ላይ እንደሚቆሙና ወዳጄ ያሉትን አቶ መለስን እንደሚያነጋግሩ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ከአቶ መለስ አዎንታዊ መልስም እንደሚጠብቁ ነግረውኝ ነበር የሄዱት የቀድሞው የፊንላንድ ፕሬዚዳንት አቲሳሪም ለሌላ ጉዳይ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ እሳቸውንም አግኝቼ ጉዳዩን አብራርቼ እሳቸው ካላቸው የማስታረቅ ልምድ በመነሳት ይህንን ጉዳይ ከቁጥጥር ከመውጣቱ በፊት ሊሸመግሉ የሚችሉበት መንገድ ካለ ጠይቄያቸዋለሁ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ወኪሎች በዚያኑ ሰሞን ለሥራ አዲስ አበባ በመጡበት ጊዜ ኅብረቱ በጉዳዩ ላይ ገብቶ የሽምግልና ሥራ ሊሠራ ይችል እንደሆን እኔም ሌሎችም ተማጽነናል በአሜሪካ የሕግ መምሪያ ምክር ቤት የአፍሪካ ጉዳይ ኮሚቴ ሲቀመንበር ክሪስ ስሚዝና ምክትል ሲቀመንበሩን ዶናልድ ፔይን ኢህአዴግ ምናልባት ከማንም በላይ አሜሪካኖችን ይሰማ ይሆናል ብለን አየፄደ ያለበትን መንገድ አደገኛነት በዝርዝር ገልጸናል ቅንጅቱ ግጭትን ለማዳን ያለመውን ይህንን የመጨረሻ አቋማችንን አስረድተናል ኢህአዴግ በዚህን ጊዜ እኛን አስፈራርቶ የሚፈልገውን ለማድረግ የሚያደርገውን የደኅንነት ወከባ ለኮንግረስማን ክሪስ ስሚዝ ስንነግራቸው «ይህ በፍጹም ሊሆን አይችልም አንድ ዴሞክራሲያዊነት የጎደለው መንግሥት እንኳን ቢሆን እንዲህ ዓይነት ጋጠ ወጥ ነገር ሊያደርግ አይችልም የምትሉት እውነትነት ያለው ከሆነ በዓይኔ ማየት ስለምፈልግ አሳዩኝ ብሰው ዋና አማካሪያቸውን በአሜሪካ ኤምባሲ በእኔ መኪና ይዢ ወጥቼ የደኅንነት ተከታታዮቻችን የሚያደርጉት አፀያፊ ሥራ በዓይናቸው እንዲያዩት አድርጌያለሁ የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሐፊ የሆኑትን አምባሳደር ዶናልድ ያማሞቶን በቅንጅቱ አቋም ዙሪያ በሰፊው አነጋግረናቸው ከዚህ በታች ቅንጅቱ ምንም ሊያደርግ እንደማይችል በግልጽ ተረድተውናል በአገር ውስጥ ዲፕሎማቶች በኩል ደግሞ ዘወትር ከምናገኛ ቸውና በድርድሩ ወቅት በቀጥታ ተሳታፊ ለነበሩት ለአውሮፓ ኅብረት ሦስቱ አምባሳደሮችና ለአሜሪካ አምባሳደር እንዲሁም ለሌሎች አገሮች የነባነት ገህ ሲቀደ አምባሳደሮች በተለይ በስተመጨረሻው ኢህአዴግ ምንም ነገር አልሰማም ብሎ በጉልበት ደፍጥጦ ለመሄድ በሚዘጋጅበት ወቅት እነዚህ አገሮች ያላቸውን ግንኙነት ተጠቅመው ኢህአዴግን ወደ ድርድር እንዲያመጡት ጠይቀናል ከዚህ አንፃር በኖርዌይ ኤምባሲ በኩል ያደረግሁት ሙከራና በአንድ የስዊድን ዳፕሎማት በኩል የተሞከረው የግል ዲፕሎማሲ የሚጠቀሱ ናቸው እነዚህን ሁሉ ሙከራዎች ስናደርግ ያለምንም ማጋነን የቅንጅቱን ለዘብተኛ አቋም ያላወደሰ ከተነሳንበት የሕዝብ ድምጽ መጭበርበር አንፃር የፄድንበትን መንገድ በእርግጥም ሰላም ፈላጊና ከሥልጣን በላይ ለአገራችን የምናስብ መሆናችንን «ተረዳሁ» ያላለ አንድም ሰው አልገጠመንም ሁሉም በየራሳቸው ባደረጉት ሙከራ ከኢህአዴግ በኩል ምንም የመለመጥ ሁኔታ እንደማያዩና ጉዳዩን በጉልበት ለመፍታት እንደቆረጠ በመገረም ከመታዘብ በስተቀር ምንም ሊያመጡ አልቻሉም በአገር ውስጥ ያደረግናቸው ሙከራዎች አንድም ሌሎች ዜጎች የወሰዲቸውን ተነሳሽነቶች መደገፍና በተለይ በግል የምናውቃቸውን የኢህአዴግ ባለሟሎች ማነጋገር ነበር አገሪቱ የገባችበት አጣብቂኝ በጣም ያሳሰባቸውና ይህንን ችግር በራሳችን ጥረት መፍታት ያገባናል ብለው የተነሱ ሁለት የዜጎች ስብስቦች ነበሩ አንደኛው እነ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ታምራት ከበደ ወዘተ የመሳሰሉ ሥመ ጥር ጉዳዩ ይመለከተናል ያሉ ዜጎችን የያዘ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በእነ አምባሳደር ዘውዴ በኩል የተስበሰበና ችግሩን በአገራችን ባጋል መሠረት ለመሸምገል የተነሳሱ አስታራቂዎችን ያቀፈ ነው ከመነሻው ጀምሮ የሁለቱንም ጥረት አድንቀን በእኛ በኩል ሙሉ ትብብር እንደሚያገኙ ገልፀናል ከዚያም በላይ ግን የቅንጅቱን ስላም ፈላጊነትና በተለይ ከተፈጠረው የምርጫ ማጭበርበር ችግርና በዚህም ምክንያት ከተነሳው የሕዝብ ቁጣ አንፃር ችግሩን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚፈልግ ገልፀንላቸዋል ኢህአዴግም ለሥልጣን ብሎ አገሪቱን ችግር ውስጥ እንዳይከታት በማስብ ቅንጀቱ የመጨረሻ የሚለውን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጥያቄዎችን ስንነግራቸው በተለይ የሁለተኛው ግሩፕ አባላት መፍትሄ ያገኙ መስሏቸው «ይህንንማ ይቀበላሉ ራሳቸው ሁሌ እንፈልገዋለን የሚሉት ነው። ከዚህ ሁሉ ሙከራ በኋላ ነበር ቅንጅት ውስጥ ላለነው ሰዎች ሁሉ ችግሩ በድርድር እንደማይፈታና ኢህአዴግ በጉልበት ለመጨረስ መወሰኑ ሙሉ በሙሉ ግልጽ የሆነው ከዚህ በኋላ በቅንጅት ውስጥ የነበረው ስሜት ድርጅቱ የመጨረሻና አነስተኛ ያላቸውን ጥያቄዎችን በድርድር ማግኘት ካልቻለ መሥራት ያለበት እነዚህን የመጨረሻ ያልናቸውን የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ጥያቄዎች በሕዝቡ ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል እንዴት ማግኘት አንደሚቻል መሆን አለበት የሚል ነበር ከዚያ በፊት ግን እያደር እያፈጠጠ የመጣውን የፓርላማ መግባት አለመግባት ጥያቄ መመለስ በዚህ ዙሪያ ያለውን የሕዝብ ስሜት ማዳመጥ እና ሲጓተት የቆየውን የቅንጅቱን የውህደት ጉዳይ መወሰኑ አጣዳፊ ነበር በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ቅንጅቱ የወሰዳቸውን አቋሞችና በድርጅቱ ውስጥ የነበሩ ክርክሮችን ይዘት በሚቀጥለው ምፅራፍ እንተነትናለን ጾር ብርፃኑ ነጋ ቅንጅት ኅብረትና የፓርላማ መግባት አለመግባት ጥያቄ ዘርፈ ብዙና መጠነ ስፊ ጥረቶች ባለመሳካቱና መና በመቅረቱ በቅንጅቱ ውስጥ ያለን ጉልበታችንን ቀጣዩን መንገዳችንን በማዘጋጀቱ ላይ ማጥፋት እንዳለብን ግልጽ ነበር ይህን መንገድ በግልጽ ከመቀየሳችን በፊት ግን መሥራት ያሉብን ተያያዥ የሆኑ ብዙ ሥራዎች ነበሩ የመጀመሪያው በሕዝቡ ውስጥ ያለውን ስሜት በደንብ ማወቅና በተቻለ መጠን ሕዝቡን የቀጣይ እርምጃጻትን አካል ማድረግ ነው ከዚህ ጋር አብሮ መደረግ ያለበት በእንጥልጥል ላይ ያለውን የቅንጅቱን ድርጀታዊ ቅርጽ ጉዳይ መቋጨት ነው በተለይ የቅንጅቱን ውህደት ጉዳይና በውህደቱ መሠረት የሚፈጠረውን ድርጅታዊ መዋቅር መወሰን አስፈላጊ ነበር ክዚያ ቀጣዩ ደግሞ በእነዚህ ውይይቶችና ድርጅታዊ መዋቅር ላይ በመመሥረት መጭውን የዴሞክራሲያዊ ትግል በ መፍትሄ ይገኛል የሚለው ምኞታችን ባደረግናቸው የነባነት ገህ ሲቀደድ አቅጣጫና ስልት መወሰንና መተግበር ነበር እነዚህ አብይ ጉዳዮች ከነሐሴ ጀምሮ እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ በነበረው የሥራ መርሐ ግብር ተካተዋል ቅንጅቱ የሞከራቸው የሰላምና የድርድር መንገዶች ሁሉ በኢህአዴግ እምቢተኛነት ሲከሽፉ ኅብረተሰቡ የሚደረጉትን እንቅስቃሴዎች በሙሉ በከፍተኛ ትኩረት ይከታተል ነበር ይህን ክትትል የሚያደርገው ግን በተለይ የግል ሚዲያውን በማንበብና በእነዚህ ጋዜጦች ላይ ከቅንጅቱና ከሌሎች ተቃዋሚ ድርጅቶች የሚሰጡትን መግለጫዎች በመቃኘት ነበር ቅንጅቱና ኀብረቱ ለኢህአዴግ እምቢተኝነት የሚሰጡትን ለዘብተኛ መልሶች የሚደግፉ እና የሚቃወሙ ነበሩ የሚደግፉት መነሻቸው ግጭትን ለማስወገድ በተቃዋሚው አመራር በኩል እየተወሰደ ያለው የተረጋጋና ብልህ አካሄድ ኢህአዴግ አገሪቱን ትርምስ ውስጥ ለመክተት የሚያደርገውን ኃላፊነት የጎደለው አካሄድ ለመቋቋም ያለው ብቸኛ አማራጭ ነው ከሚል የጥንቃቄ ጉዞን መምረጥ ሲሆን በተጨማሪም የግጭት መንገድ ዋናውን የግንቦት ዋና ግኝት የሆነውን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን አቅጣጫ አስቀይሮ አገሪቱን አሁንም እንደገና የፖለቲካ ችግሮች በጠመንጃ ወደሚፈቱበት መድረክ ይቀይሩታል የሚል ፍርሐት የነበራቸው ናቸው ይህንን የሚሉት ሰዎች ኢህአዴግ «አኛ ከሌለን ወይም ከሥልጣን ከወረድን አገሪቱ ትበታተናለች» የሚለውን ሟርት ሆን ብሎ እውን ለማድረግ ይንቀሳቀሳል የሚል ፍርፃትም ነበራቸው በሌላ በኩል ለተቃዋሚዎች የዝግታና አስቦ የመጓዝ አካሄድ ትዕግስት ያልነበራቸውና ፈጣን እርምጃ እንዲወስድ የሚፈልጉም ሰዎች ቀላል ቁጥር አልነበረም እነዚህ ኃይሎች የሚያቀርቧቸው ምክንያቶች በጥቅሉ «ኢህአዴግ በውይይት የሚያምን ድርጅት አይደለም ኢህአዴግ ዓለምን በመነጽር ሲመለከት የሚያየው ጥቁርና ነጭ ብቻ ነው ግራጫ አይታየውም ለኢሕአዴግ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ያለው ጠላትና ወዳጅ ብቻ ነው ጠላት ደግሞ መደፍጠጥ አለበት ተቃዋሚዎች ጠላት ናቸው ኢሕአዴግ ከእነሱ ጋር ተወያይቶ ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚደርግ ስምምነት እንደሚፈጠር አይታየውም ስለዚህ ውይይት ቢፈልግ እንኳን ለመጨረሻ የኃይል እርምጃው ጊዜ ለመግዢያ ይጠቅመኛል ብሉ አምኖ እንደሆነ እንጂ በእርግጥ ከውይይትና ከድርድር ምንም መፍትሄ ይገኛል ብሎ አይደለም ስለዚህ ሕዝቡ ድምጽን ተቀምቶ ዝም ብሎ ስለማይቀመጥ ተቃዋሚዎች ከኢህዴግ ጋር ከሚደረግ ድርድር መፍትሄ ከመጠበቅ ከአሁኑ ሕዝቡን ለሰላማዊ ትግል ማንቀሳቀስ ጾር ብርሃኑ ነጋ አለባቸው ኢሕአዴግ የሚስማውና የሚገባው ቋንቋ ይህ ብቻ ነው» የሚል ሀሳብ ነው ይህ ከላይ የቀረበው ዛሳብ ትዕግስታችን አልቋል የሚለው ሁሉም ሰው የሚገፋው ሳይሆን ከዚያ ውስጥ በደንብ አስበው የሚከራከሩት የሚናገሩት ነው የዚያነ ያህል በስሜት ተገፋፍተው በቶሎ እርምጃ እንውሰድ የሚሉም ነበሩ ይህንን በተወሰነ ደረጃ የተበታተነ የሕዝብ ስሜት ማሰባሰቡና በአንድ የትግል አቅጣጫ መምራቱ የተቃዋሚው ኃይል ችግሩን በድርድር መፍታት አልችል ብሉ ለሚወስደው ቀጣይ እርምጃ ትልቅ ፋይዳ ነበረው ከዚያም በላይ ግን በተለይ በቅንጅቱ እምነት ከግንቦት ምርጫ ወዲህ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በመሠረታዊ መልኩ ተቀይሯል ሕዝቡ የፖለቲካ ትግሉ አካል ሆኗል ከዳር ቆሞ «አዋቂ ፖለቲከኞች» የሚሉትን ዝም ብሎ የሜሰማ ሳይሆን በቀጥታ ተሳታፊ ሆኗል ድጋፉን ለማግኘት ከሕዝቡ የሚመጣውን ፃሳብ ማድመጥ እንዳለበትና አጠቃላይ የሕዝቡን ድጋፍ በተፈለገ ጊዜ የሚገኝ አድርጎ መውሰድ ሀዐ ዘ የ እንደማይቻል የቅንጅቱ አመራር ተገንዝቧል ስለዚህም በአገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት በሚመለከትና የወደፊቱ አካፄድ ምን መሆን እንዳለበት ለመምከር ሕዝባዊ ስብሰባዎች መጥራቱ ይጠቅማል የሚል ስምምነት ላይ ደረስን እነዚህን ስብስባዎች መጥራቱና ሕዝቡን ማወያየቱ ሌላም ጠቀሜታ እንዳለው አምነንበታል ከግንቦት ምርጫ በኋላና እሉን ተከትሎ ከሰኔ አንድ ጀምሮ ኢህአዴግ በወሰደው አጠቃላይ የአፈና እርምጃ ምክንያት በሕዝቡ ሥነልቦና «ከኃይል በቀር ኢህአዴግ ሌላ ነገር አይስማም» የሚል እምነትና በጭፍጨፋውም ምክንያት የተፈጠሪ ጠንካራ የቁጭትና አልፎም የጥላቻ ስሜት እየተስፋፋ መሆኑን የሚገልጹ ምልክቶች ነበሩ እነዚህ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ሕዝቡን ተመልሶ ወደ ግልጽ የሕዝብ ፖለቲካ ለመመለስ ይጠቅማሉ ሕዝቡም በቅንጅቱ አመራር ሳይ ያለውን እምነት ለመለካት ይረዳሉ የሚለው ፅነ አቋማችን ነበር ከሁሉም በላይ ግን ምርጫው ከተካሄደ ከሦስት ወር በላይ ስላለፈና በዚህ ጊዜ ውስጥ ብዙ ፖለቲካዊ ጎዳዮች ስለተከናወኑ የተመረጡ ሰዎች ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር ተገናኝተው መምከር የአዲሱ የዴሞክራሲያዊ ፖለቲካ አንድ አካል መሆኑን ማሳየት አለብን የሚል ከመሠረታዊ የቅንጅቱ እምነቶች የመነጨ አቋምም ነበር በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ሕዝባዊ ስብሰባዎች በተቻለ መጠን በሁሉም ቅንጅቱ ባሸነፈባቸው ወረዳዎች እንዲጠሩ የየወረዳው ተመራጮች ስብስባውን እንዲያዘጋጁና እንዲመሩና የሰው እርዳታ የሚፈልጉ ወረዳዎች የነዛነት ገህ ሲቀደ እርዳታ እንዲሰጣቸው ተወሰነ በዚህን ጊዜ አቶ መለስ የምርጫው ዕለት ያወጀው የሰልፍ ክልከላ አዋጅ ተነስቶ ስለነበር ፈቃዱን ከማዘጋጃ ቤት ሁሉም ተመራጭ የስብሰባውን ቦታ እንዳወቀ አንዲያወጣ መመሪያ ተላልፏል ስብሰባዎቹም በአዲስ አበባና በየክልል ከተሞች እንዲሆኑም ተወስኗል የስብሰባዎቹም ዒባማ በአብዛኛው የሕዝቡን ሃሳብ ለመስማት ቢሆንም ለመግቢያ እንዲሆን ቅንጅቱ እስከ አሁን የወሰዳቸውን እርምጃዎችና ከኅብረት ጋር በመሆን ተደጋጋሚ የድርድር ጥያቄ ቢቀርብም መንግሥት አሻፈረኝ አንዳለ አሁንም ቅንጅቱ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ህጋዊና ሰላማዊ ትግሉን እንደሚቀጥል የፓርላማ መግባት አለመግባትን ጉዳይ በሚመለከት አሁን የደረስንበት ትግል ዋና ጉዳይ እንደሆነ የፓርላማው ጉዳይ ራሱ ከአጠቃላይ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጋር አብሮ የሚታይ እንጂ በተናጠል ማየቱ ፋይዳ እንደሌለው መግለጽ እንደሚገባ ነበር የተወሰነው ስብሰባዎች ለማድረግ አንደተወሰነ በአስደናቂ ፍጥነት የወረዳ ተመራጮች የመጀመሪያውን ስብሰባ በኢንጂነር ግዛቸው መሪነት ያደርጋሉ በዚህ የመጀመሪያው በችኮላ በተዘጋጀው ስብሰባ የተገኘው የሕዝብ ብዛት የነበረው ስሜት ከጠበቅነው በላይ ነበር ከሕዝብ የተነሳው ዋና አጀንዳም የፓርላማ መግባት ጉዳይ ነበር በዚህም ጉዳይ ላይ በጣም ጥቂት የሚባሉ ስዎች ፓርላማ መግባትና በተለይ ኢህአዴግ በመጨረሻ ያወጣው የፓርላማ ህግ ከተቀየረ ሁኔታውን ትንሽ አይቶ መውጣት ይገባል የሚል ሃሳብ ከመስጠታቸው በቀር እጅግ በጣም ብዙው ሕዝብ አንድም የሕዝቡ ድምጽ ተጭበርብሮ ፓርላማ መግባት ሕዝቡን መክዳት ነው አለበለዚያም ቢያንስ ተቃዋሚዎች ያነሷቸው የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደቶች ተቀባይነት ካላገኙ የስኔ አንዱ ጭፍጨፋ በገለልተኛ ወገን ተጣርቶ ወንጀለኞች ለፍርድ ካልቀረቡ ባጠቃላይ ግን ቅንጅቱና ኅብረቱ ያቀረቧቸውና ኢህአዴግም በአፉ ተስማምቼባቸዋለሁ ያላቸው ባለ ነጥብ ስምምነቶች በተግባር ካልዋሉ በምንም ዓይነት ፓርላማ መግባት የለባችሁም የሚል በጣም የክረረና ስሜታዊ አቋም ይዞ ነበር ይህ ስብሰባ በቪዲዮ ተቀድቶ ስለነበር የተወሰንን ሰዎች በቪዲዮ አይተነው ነበር ከዚህ የተረዳነው ሕዝቡ በጣም ስሜታዊ እንደሆነና ማረጋጋት እንደሚገባ የሕዝቡን ስሜት ማወቅ ለቅንጅቱ ውሳኔ በጣም ጠቃሚ የሆነውን ያክል የመጨረሻው የፖለቲካ ውሳኔ በቅንጅቱ አመራር እንደሚሰጥና ሕዝቡም የቅንጅቱ ውሳኔ ምንም ይሁን ምን በአመራሩ ግምት ከምንም በላይ የሕዝቡና የአገሪቱን ጥቅም መሠረት አድርጎ የሚወሰን ጾር ብርፃኑ ነጋ ስለሆነ ይህንን ውሳኔ እንዲያከብር ማሳመን እንደሚገባ በተቻለ መጠን በየስብሰባው ላይ ይህንን ማሳመን የሚችሉ ሰዎች መገኘት እንዳለባቸው አምነን የዚህን አጠቃላይ ቅኝት የተከተለ አንድ አጭር ጽሁፍ ተዘጋጅቶ በሁሉም ቦታ በመግቢያነት እንዲነበብና እንዲብራራ የሥራ አስፈፃሚው ይወስናል በዚህም መሠረት ለሚቀጥለው ሳምንት የሚደረጉ ስብሰባዎች የሚመሩ ሰዎች በአዲስ አበባ የዘመቻ ኮሚቴ ሊቀመንበር በዶር ኃይሉ አርአያ ይመደባሉ በዚህን ጊዜ የተከሰተ አንድ ግራ የሚያጋባ ሁኔታ አሁን ወደ ኋላ ሲታዩ ግራ አያጋባም ልደቱ በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ አልሳተፍም ማለቱ ነበር በሁኔታው የተገረምነው ሁሉ ለምን እንደማይሳተፍ ስንጠይቀው በመጀመሪያ በስብሰባው ስለማላምንበት ነው አለ ይህ ያስነሳውን ብዙ ጥያቄ መመለስ ሲቸግረው በጥቅሉ በግል ምክንያት አልሳተፍም አለ ሌሎች ወረዳዎች ለእርዳታ አልሄድም ካለ ምንም ማድረግ አይቻልም ግን ቢያንስ በራሱ ወረዳ የመረጠውን ሕዝብ ማናገር አለበት ቢባልም አሻፈረኝ አለ በመጨረሻ በእኔ ወረዳ የሚደረገውን ስብሰባ አዘጋጃለሁ ተናጋሪዎችም እኔ አመድባለሁ ብሎ በስብሰባው ሳይሳተፍ ቀረ በሚቀጥለው ሳምንት ቢያንስ በአሥር ወረዳዎች ሕዝባዊ ስብሰባዎች ተካሄዱ ስብሰባዎቹ የነበራቸው ሕዝባዊ ተሳትፎ በፍጹም ማመን የሚያቅት ነበር እኔ እራሴ በአንድ ቀን ሦስት ወረዳዎች ሄጀ ተሳትፌ ነበር በምርጫ ወቅት ከነበረውም የበለጠ ሕዝብ ነበር የተገኘ ው አደራሾች ሞልተው አዳራሾቹ ያሉባቸው ግቢዎች ሞልተው ሕዝቡ መንገድ ላይ ሳይቀር ነበር ከቦታ ቦታ መጠነኛ መለያየት ይኑረው እንጂ በየቦታው ከሕዝቡ የሚሰማው መልዕክት አንድ ነበር በምንም ዓይነት አሁን ባለው ሁኔታ ፓርላማ መግባት የለባችሁም የሚል የመረጥናችሁ ዴሞክራሲ ይኖራል ብለን እንጂ የቀድሞው የኢህአዴግ የጉልበትና የማጭበርበር አገዛዝ እንዲቀጥልና አሱን እንድታዳምቁ አይደለም ዝም ፉ ዝ ፖሥታ በመጨረሻ እኔ ያንሃረኝ ምፏዖታ ሪዕነኔታም ያነሃረ መሰፅኛጳሳ ይሀ ዕብኃሃ ቋፖኗኃማ መግጎታ ዙሪያ ቀጆታ እቋም ይወሰድ ያሬ መፕራ ቅኞቻራ የሚወሰደው ቋም ይ ጽኖ ያደር ዕወዕሃሃ በን ዕዝብፅዛሥሦሃ ንጠራ ፇ ይነዝሰዛው ዎና ዓማ ሕቋታ ማመሃ ይሆና ለሥጋ ፇሃ ሕዝሁ ለሦፇሁ ሳሪ ማሰቱ ሌይረሦን በ መጋገፉ ሰወሰጋ ቻቨሮ ውሰም ዖሚሰ ለቋም ለዳዕውታ በር ይህ ለመሪጓታሦ ፅሳደቱ ጋር ሳታ ይላመሰሃነ ሰይኑዶቻ ለቶ ነው እኛ ቦምናዕያው ዲታ ዴምዕራሲቷያቿ ፖያለቷጓ ይፖፅለስኞቻ ውዓኔ ይአዝህሃ ፍሳዕ ቦሚያጋሃርቅ መሆጋ ዳዳጎያ ሐቻህ ያሜቋውጋ ውጎኔ ዕፊሦ ማወ ይጠቅማሳ እጳፇጂ ዲይዕዳም ይሀ ደፇም ምኃም ዓይኑ «መሪነታኃ ለሰድ መሰጠቱ ዲይደፅም የነባነት ገህ ሲቀደ ኹዙጵጽፓ ንንን ። እነዚህም ቅንጅቱም በመንፈስ ብቻ ሳይሆን ዘተግባር የሚያዋህዱ አመራሮች ይሆናሉ ከውህደቱ በኋላም «የማዳላት» ሀሜትን ለማጥፋት እንኳን ባይቻል በእጅጉ ይቀንሰዋል የሚል ነበር ሆኖም በዚህ ፃሳብ ልደቱም ሆነ የመኢአድ ወኪሎች እምብዛም አልተደሰቱም በተለይ ልደቱ ሁሉም የአመራር ቦታዎች በድርጅቶች ድርድር መሞላት አለባችው አባሎቻቸውን የሚያውቁት ድርጅቶቹ ናቸው እንጂ «ቅንጅቱ» አይደለም የሚል በጣም ስሜታዊ ክርክር አቀረበ የመኢአድ ወኪሎችም «ሁሉንም» በምርጫ የሚለውን ነገር አልወደዱትም የቀስተደመናና የኢዴሊ ወኪሎች ግን አንድ ዓይነት ሁሉም የሚሳተፉበት ምርጫን ይደግፋሉ በተለይ የድርጅቱ ሊቀመንበርና ሌሎች ዋና ዋና መሪዎች መመረጥ አለባቸው የሚለው አቋማችን ጠንካራና በመርህ ደረጃ የያዝነው ነበር በመጨረሻ የተደረሰበት የማስማሚያ ሀሳብ ድርጅቶቹ በራሳቸው የላዕላይ ምክር ቤት ወኪሎቻቸውንና ከዚህ ውስጥ ደግሞ ወደ ሥራ አስፈፃሚ የሚሄዱትን አባሎቻቸውን እንዲመርጡ ነገር ግን የላዕላይ ምክር ቤቱ አባላት ከሥራ አስፈጻሚው ውስጥ አራቱን ማለትም ሊቀመንበር ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ምክትል ሲቀመንበርና ዋና ፀሐፊውን በምስጢር የድምጽ አሰጣጥ ሂደት እንዲመርጡ ነበር ከዚያ በተጨማሪ ግን ምርጫው እውነተኛና ከሁሉም የተውጣጣ እንዲሆን ለእያንዳንዱ የአመራር ቦታ አራቱም ድርጅቶች ከድርጅቱ የተጠቆሙ እጩዎችን እንዲያቀርቡ ሆኖም ግን ድርጅቶቹ ከሚያቀርቧቸው እጩዎች በተጨማሪ ማንኛውም የላዕላይ ምክር ቤት አባል እጩዎችን መጠቆም የሚችል እንደሆነና የተጠቆመው እጩ ደጋፊ እስካገኘ ፀበ የነባነት ገህ ሲቀድ ድረስ ለውድድር እንዲቀርብ ተወሰነ ይህ ሁሉ የሆነው ምርጫውን አውነተኛ ምርጫ ለማድረግና የተመራጮቹን ታማኝነት ለመጡበት ድርጅት ሳይሆን ለቅንጅቱ ለማድረግ ነው አንግዲህ እነዚህ ሁሉ ውሳኔዎች ከተወሰኑ በኋላ ነበር የቀስተ ደመናና የኢዴሊ ወኪሎች ለብቻቸው ወጥተው የመከሩትና የአመራሩን የመጨረሻ ስብጥር የወሰኑት ይህም ስብሰባ ቢሆን በቀላሉ ስምምነት የተደረሰበት አልነበረም «የእነዚህን ድርጅቶች ትልቅነትና ዕድሜጌ እንደምናከብር ማሳየት ካለብን ይህን ደግሞ የምናደርገው በላዕላይ ምክር ቤቱና በጉባዔው ላይ ያላቸውን ውክልና በመጨመር ነው ይህን ስናደርግ ግን ማንም ድርጅት ለብቻው የበላይነት የሚያገኝበትን መንገድ ሁሉ መዝጋት አለብን ስለ ማስማሚያ የመሰለኝን ሃሳብ አቀረብኩ በእኩልነት መርህ ቢሆን ይደርሰን የነበረውን የላዕላይ ምክር ቤት መቀመጫን ወደ አውርደን ለሁለቱ ድርጅቶች እኩል መቀመጫ እንስጣቸው አልኩኝ በውይይቱ ላይ ለዚህ ሃሳብ የነበረው ተቃውሞ መነሻ የመቀመጫ ቁጥራችን ለምን ያንሳል የሚል አልነበረም ትላልቆቹ ድርጅቶች የአባላት ብዛት ይኑራቸው እንጂ ባለፉት ወራት በተግባር አብረን በሰራንበት ጊዜ እንዳየነው ከፍተኛ የጥራት ችገር አለባቸው አዲሶቹ ድርጅቶች በተለያየ ምክንያት የተሻለ ጥራት ያላቸው ሰዎች በአጭር ጊዜ አባል ማድረግ ትለዋል እነዚህን አዳዲስ ሰዎች ወደ አመራር ቦታ ማምጣት ቅንጅቱን ያጠናክረዋል ያዘምነዋል የአመራሩን ብቃት ከፍ ያደርገዋል ስለዚህ በይሉኝታ ሳይሆን በእውነት ለቅንጅቱ እናስብ የምንል ከሆነ ይህን የማበላለጥ ሀሳብ መቀበል የለብንም የሚል ክርክር ከሁለቱም ድርጅቶች ወኪሉች ቀረቡ እኔ ያቀረብኩትን ፃሳብ የደገፉትም የሌላው ሀሳብ ትክክል መሆኑን ይቀበላሉ ግን ከአጀማመሩ አዲስ የመጡት ሰዎች ምንም ሳይሠሩና ሳይደክሙ የበላይነት ያዙ የሚለውን ሁኔታ ለማጥፋት የሚመጣው ለውጥም ድንገተኛ እንዳይሆንባቸው ቀስ በቀስ ማስለመዱ እንደሚሻል የተሻለ ጥራት ያላቸው ሰዎች ማቅረብ ከቻልን በሚቀጥለው ዓመት ምርጫ ላይ ሁሉም ሰው እንደ ግለሰብ በብቃቱ መወዳደር እንደሚችል በመከራከሬና ከሁሉም በላይ ግን ለቅንጅቱ ቀና ጅማሬ ሁሉም እንዲያስብ በመማፀን ምክክሩ በእኔ የቀረበውን ፃሳብ ተቀብሎ ወደ ስብሰባው ተመልሰን ውሳኔያችንን አሳወቅን ከዚያ በተጨማሪ ግን የጉባዔውን ውክልና በሚመለከት መኢአደ በምንም ዓይነት ላስቀራቸው የማልችላቸው የየዞኑ ተጠሪዎችና የማዕከላዊ ኮሚቴው አባሎች አሉኝ እነዚህ ደግሞ ከ በላይ ናቸው ብሎ አምርሮ ጠይቆ ጾር ብርፃኑ ነጋ ስለነበር በዚህ ላይ ብዙ ከመጨቃጨቅ ቁጥሩ ይጨመር ተብሎ እስከ እንዲጨመርና ሁለቱ ድርጅቶች እስከ ወኪሎች ይዘው እንዲመጡ ሌሎቹ የቀረውን ውክልና ለሁለት እኩል እንዲካፈሉ ተወስኖ በዚሁ አጠቃላይ ስምምነት ላይ ተደረሰ ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም ድርጅት ለላዕላይ ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ለሥራ አስፈፃሚ ደግሞ አንድ ሴት እንዲልክ ተወሰነ ከዚህ በኋላ ለውህደቱ የቀረው እነዚህን ስምምነቶች በተዘጋጁት ዶክመንቶች ላይ ማካተትና የጉባዔውን የሎጂስቲክ ሥራ መሥራት ነበር ከዚያም ሌላ ግን ሁሉም ድርጅት በየራሱ ለጉባዔው የሚመጡትን ሰዎች የላእላይ ምክር ቤቱንና የሥራ አስፈፃሚውን አባላት መምረጥና በጉባኤ ወይም በሚመለከተው አካል የቅንጅቱን ውህደት በየድርጅቱ ማስወሰን ይገባዋል ይህም በሁሉም ድርጅቶች በየተራ የተካሄደ ነበር ነገር ግን ቀላል ሥራ አልነበረም የቅንጅቱ መዋሀድ ግለ ድርጅቶችን ይገድላል ከምርጫው በኋላ ቅንጅቱ እውነተኛው ጠንካራ የተቃውሞ ድርጅት መሆኑ እየለየ ነበር ስለዚህም በተቃውሞው ፖለቲካ ሁነኛ ተሳትፎ ይኑረረኝ የሚል ማንኛውም ሰው እዚህ ውህድ ድርጅት አመራር ውስጥ ሁነኛ ቦታ እንዲኖረው ይሻል እንደከዚህ በፊቱ ከላይ ሌሎች ሰዎችን አስቀምጦ እውነተኛውን ሥልጣን ከኋላ ሆኖ ማሽከርከር እንደማይቻል ግልጽ ሆነ ስለዚህም እውነተኛ አመራሮች ወደፊት የሚወጡበት ጊዜ ነበር በሌላ በኩል ግን በቅንጅቱ ውስጥ ለረጅም ጊዜ አብረው ሲሰሩ የነበሩ ሰዎች ከራሳቸው ድርጅቶች በላይ ለቅንጅቱ ጠንካራ ወገንተኛነት አዳብረው ነበር በዚህም ምክንያት የየራሳቸው እናት ድርጅት ምን ያገኛል ወይም እንዴት ይወከላል ከሚለው ይልቅ ቅንጅቱ እንዴት የተሻለና ወደፊት ሊወስደው የሚያስችለው አመራር ያገኛል የሚለው ያስጨንቃቸዋል በዚህም ዙሪያ ቢሮ ውስጥ ብዙ ውይይቶች ይደረጉ ነበር አብዛኛው ሰው በየድርጅቱ ውስጥ ከሁሉም በላይ ይህ ስሜት የገነነ ነው የሚል አመለካከት ነበረው ይህ ግን የየድርጅቶቹን የዳበረ ውስጣዊ ባህል ከግምት ያስገባ አመለካከት አልነበረም ለላዕላይ ምክር ቤትና ለሥራ አስፈጻሚ ከየድርጅቱ የሚመጡ ወኪሎች አመራረጥ ላይ ችግር ሊኖር እንደሚችል መታየት የጀመረው በመጀመሪያ በኢዴሊ ዙሪያ ነበር የኢዴሊ ሊቀመንበር የነበረውና ለረጅም ጊዜ ከቅንጅቱ ጋር ይሠራ የነበረው ሰው በኢዴሊ ስብሰባ ለሥራ አስፈፃሚነት አለመመረጡን ሰማን ይልቁንም የድርጅቱ የበስተኋላ የነባነት ጎህ ሲቀደድ አሽከርካሪዎች ናቸው የሚባሉት ሰዎች አሁን ወደፊት መምጣታቸውን አወቅን ለዚህ አባለ አለመመረጥ ምክንያት ተብሎ የሰማነው ደግሞ በቅንጅቱ ውስጥ በሚሠራበት ጊዜ ከምንም በላይ ከኢዴሊም በላይ ለቅንድቱ ቅድሚያ በመስጠቱ ስለዚህም የእናት ድርጅቱን ጥቅም አላስጠበቀም የሚል ምክንያት ነው ቅንጅቱ አካባቢ የምንሠራ ሰዎች በዚህ ደስተኞች አልነበርንም እኛ ብቻ ሳንሆን ኢዴሊን ወክለው ቅንጅቱ ውስጥ የተሳተፉት አባሎች ተከፍተው ነበር በዚህን ጊዜ ኢዴሊ ውስጥ የሌለን ሰዎች በድርጅቱ የውስጥ ጉዳይ መግባት እንደማንችል ይታወቃል ነገር ግን የኢዴሊን የጊዜው አመራሮችን አንዳንድ ሰዎች እየደወሉ ቢቻል ፃሳባቸውን እንዲቀይሩና ይህንን ሰው ወደ ሥራ አስፈፃሚው እንዲያሳልፉት ይማጸናሉ በፓርቲው ውስጥም ከፍተኛ ችግር ይፈጠራል ለሥራ አስፈፃሚው ከተመረጡት ውስጥ አንዱ በገዛ ፈቃዱ ቦታውን ለዚህ ሰው ሊለቅለት እንደሚፈልግና ይህንንም ለማድረግ ከምርጫው ራሱን ሲያገል በቀጥታ በስድስተኛነት የተመረጠው ይህ ሰው ስለሆነ እሱ የሥራ አስፈፃሚው አባል ይሆናል ብሎ እንደሚያስብ ለአዲሱ አመራር ያቀርባል አዲሱ አመራር ግን ይህንንም አልቀበልም ብሎ እንዲያውም የዚህ ዓይነት ጫና የሚፈጠር ክሆነ እራሳችንን ከሂደቱ እናገላለን የሚል አቋም ይይዛል ምንም እንኳን ሁኔታው ባይጥመንምና ብዙዎቻችንን ቢያበሳጨንም ምንም ማድረግ አልቻልንም ማድረግ የምንችለው የቅንጅቱ አራቱ አመራሮች በሚመረጡበት ጊዜ በድምፃችን መቅጣት ብቻ ነበር ከኢዴሊም በላይ ግን በጣም ከፍተኛ ችግር እየተፈጠረ የነበረው በኢዴአፓመድህን ውስጥ ነበር ኢዴአፓመድህን ለላዕላይ ምክር ቤቱም ሆነ ለሥራ አስፈፃሚው የሚወክላቸው ሰዎች በሕገደንቡ መሠረት የሚመረጡት በማዕከላዊ ምክር ቤቱ ነው የውህደቱንም ጉዳይ የሚወስነው ይኸው ምክር ቤት ነው ይሁን እንጂ በድርጅቱ ውስጥ የበላይነቱን ለመያዝና ወደ ቅንጅቱ የሚመጡትን ሰዎች ለመወሰን ከፍተኛ ፉክክር እየተካሄደ ነበር አንዳንድ የኢዴፓ መሥራቾችና ዋና ሞተሮች ነን የሚሉ «ወጣቶች» በኋላ ለሕዝብ ተቀባይነት ያስፈልጉናል ብለው የአመራር ቦታ የሰጧቸውን እድሜያቸው ከ በላይ የሆኑ ሽማግሌዎች» በሚያሳፍር ጨቅላነት በጋዜጣ ላይ እየወጡ ያንቋሽዷቸውም ነበር የሚመስለው ግን በላዕላይ ምክር ቤቱም ሆነ በተለይ ከሥራ አስፈፃሚው ላይ የሚወከሉት ሰዎች እነዚህ «ወጣት» አመራሮች እንዲሆኑ የሚፈልግ በልደቱ የሚመራ ቡድን ከፍተኛ የውስጥ ድርጅት ቅስቀሳ ያካሂድ ነበር በዚያን ጊዜ የዚህ ጾር ብርዛኑ ነጋ ቡድን ዓላማ በቅንጅቱ ውስጥ ይገባኛል የሚለውን ቦታ ለመያዝ ይሁን ወይም በኋላ እንዳደረገው ቅንጅቱን ከውስጥ ገብቶ ለመበተን ማረጋገጥ አይቻልም በአጠቃላይ ግን በቅንጅቱ ውስጥ እየተፈጠረ ያለውና እያደር እየደነደነ የመጣው ከሁሉም ድርጅቶች በላይ የሆነ ቅንጅታዊ ስሜት ለነልደቱ በፍጹም አልጣማቸውም በዚህ አዲስ ቅንጅታዊ ስሜት ከሚጠረጠሩት ሰዎች መካከል ደግሞ በኢዴአፓመድህን ውስጥ ከፍተኛ ቦታ ያላቸው አዛውንት የአመራር አባላት ብቻ ሳይሆኑ ከድርጅቱ ምሥረታ ጀምሮ በውስጡ የነበሩና በድርጅቱ ውስጥ በነበረው መሰሪ አሠራር ደስተኛ ያልነበሩ ጠንካራ «ወጣቶች» ይገኙበታል ከዚህም በላይ ግን በአጠቃላይ በከተማም በክልልም ያሉ የኢዴአፓመድህን እጅግ በርካታ አባላት ከቅንጅት ውጪ ሌላ ድርጅት የማይታያቸው ነበሩ እነዚህና በተለይ በአመራር አካባቢ ያሉት ሰዎች የእነ ልደቱ አካፄድ በፍጹም አልገባ ብሏቸው ነበር ልደቱ በቅንጅቱ ውስጥ አይናቸው እያየ የፈፀማቸውን ተደጋጋሚ ስህተቶች እያስተዋሉ «ይህ ልጅ የምናውቀው ልጅ አይደለም የተቀየረ ነገር አለው» እያሉ በልደቱ ፀባይ ይገረሙ ነበር ለቅንጅቱ ውህድ አመራር ማን ይመረጥ በሚለው ላይ ደግሞ የራሳቸው አመሰካከት ነበራቸው ከረፈደ በኋላ የነ ልደቱን የውስጥ ቅስቀሳ አካሄድ ተገንዝበው እነሱም በበኩላቸው የራሳቸውን የውስጥ ቅስቀሳ ጀምረው ነበር በኢዴአፓመድህን የመጨረሻ ምርጫ ወቅት በተለይ በሥራ አስፈፃሚው ወኪሎች ምርጫ ላይ የነልደቱ ቡድን አሸንፎ ነበር ይህ የኢዴአፓመድህን ምርጫ ከመደረጉ በፊት ግን ነገሩ ትንሽ አሳስቦኝ ስለነበረ ሌላ ጊዜ እንደማደርገው ልደቱን በግል ሳር ቤቶች አካባቢ ቀጥሬ አነጋግሬው ነበር በዚህ ጊዜ በተለይ አራቱ የድርጅቱ መሪዎች እነማን ይሆናሉ። » የሚለውን ጥያቄ በአዎንታዊ መንገድ ለመመለስ ባለመቻላቸው የቅንጅቱን ፓርላማ መግባት የሚቃወሙ የላዕላይ ምክር ቤት አባሎችም ነበሩ በውጭ አገር የሚገኘው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ባጠቃላይና የቅንጅቱ ደጋፊዎች በተለይ ፓርቲው ፓርላማ መግባት የለበትም የሚለው አቋማቸው ጠንካራ ነበርፁ ኢንጅነር ኃይሉ ለህክምና በፄደበት በአሜሪካ ከኢትዮጵያውያን ጋር ባደረገው ውይይት ከነበረበት ግፊት የተነሳ ቅንጅቱ ገና ውሳኔ ሳይሰጥ «ቅንጅት ፓርላማ አይገባም» ሲል ተናግሮ አዲስ አበባ የነበረውን አመራር በጣም አበሳጭቶ ነበር በመጀመሪያ እንዲህ ዓይነት ውሳኔ የቅንጅቱ አመራር ባለው መዋቅር መሠረት ሳይወስን ይህን መግለጫ መስጠቱ በቅንጅቱ አካፄድ ተቀባይነት የሌለው ነበር ይህ ውሳኔ ለሚያስከትለው ውጤት ቅንጅቱ ሳይዘጋጅ በችኮላ ቢቀርብ ሊያስከትል የሚችለው የውስጥ አለመግባባት ቅንጅቱን ክፉኛ ይጎዳል የኢህአዴግ ፕሮፖጋንዲስቶች ይህንን የአቶ ኃይሉን ንግግር በአገር ውስጥ ሚዲያ እያራገቡ አንድም የቅንጅቱን ውሳኔ አቅጣጫ ለማስያዝ የበለጠ ደግሞ ቅንድቱን አቶ ኃይሉ እንደፈለገው የሚያሽከረክረው ለማስመሰል ተጠቅመውበታል ይህን የአቶ ኃይሉን ንግግር ማስተባበል ነበረበት ይህም ሲሆን ግን በቅንጅቱ ውስጥ ልዩነት ያለ እንዳያስመስል አቶ ኃይሉን የሚገስፅ ሳይሆን በእውነቱ በስብሰባው ላይ የነበረው ሁሉ መገሠፅ ነበር የፈለገው በዜና አቀራረቡ ያለመረዳት ችግር እንዳለ የሚገልፅ ማስተባበያ አዘጋጀን ማስተባበያውን በመግለጫ መልክ ከማውጣታችን በፊት ግን ለአቶ ኃይሉ ደውለን የተናገረው ስህተት እንደሆነ አመራሩን ችግር ውስጥ እንደከተተውና ከአሁን በኋላም በዚህ ጉዳይ «ቅንጅቱ ገና አልወሰነም» ከማለት በቀር ሌላ መናገር እንደሌለበት ተነጋግረን ጾር ብርሃኑ ነጋ የሚወጣውንም መግለጫ አንብበንለትና እሱም ተስማምቶ የማስተባበያ መግለጫው ወጣ በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያውያን ድረገጾች በተለይ ኢትዮጵያን ሪቪው በዚህ የቅንጅቱ መግለጫ ያለመደስታቸውን ገለፁ አንዳንዶች ይህ የኢህአዴግ የውስጥ አርበኛ የሆነው የብርሃኑ ሥራ ነው እሱ ቅንጅቱን ከውስጥ ሆኖ የሚቦረቡር ነው እንዴት አድርጎ የሊቀመንበሩን ሃሳብ ይቃረናል የሚል ወሬ ማናፈስ ጀመሩ በእርግጥ ቅንጅቱን በደንብ እንዳላወቁት ገብቶኛል ከዚህ ግርግር በኋላ ኢንጅነር ኃይሉም በፓርላማ ጉዳይ ላይ በሚወሰነው ውሳኔ ላይ መሳተፍ ስለምፈልግ ትንሸ አዘግዩት የሚል ጥያቄ ያዘለ ደብዳቤ ለሥራ አስፈፃሚው ላከ ከዚያም ውጭ በቅንጅቱ ስብሰባዎችና ውሳኔዎች ወቅት የመንግስት ደኅንነት ክትትል እያደረገ እንደሚቀዳን አውቀን ስለነበር ውሳኔውን እስከ መጨረሻው ቀን ድረስ መግፋት ነበረብን የፓርላማ ጉዳይን ለመወሰን ቅዳሜ ጠዋት መስከረም ቀን በኢዴአፓመድኅን ቢሮ ስንገናኝ ከሞላ ጎደል ሁሉም የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ተገኝተው ነበር ስብሰባው ውጥረትና ጭንቀት የነገሰበት ነበር ሁለት ተመጣጣኝ የሆኑ ነገር ግን በየራሳቸው አብዛኛውን ድምጽ ማግኘ ት ያልቻሉ ኃይሎች ውሳኔውን እነሱ በሚፈልጉት መልክ ለማስወሰን ተዘጋጅተው መጥተዋል ብዙኋኑ ግን የየራሱ ስሜት ቢኖረውም ጥሩ ምክንያት ካገኘ የቱንም አቅጣጫ ለመያዝ የሚጠበቅ ይመስላል ትግሉም ይህን የብዙኋን ድምጽ ለማግኘት ነበር የፓርላማ መግባት አለመግባት ውሳኔ በቅንጅቱ የውስጥ አንድነት ላይ ሊፈጥር የሚችለው ጫና ቀላል አልነበረም ከዚህ ውሳኔ በኋላ ኢህአዴግ ቅንጅቱን ለመከፋፈል ያለውን አቅም በሙሉ እንደሚጠቀም ቅንጅቱ በቅርብ ውህደቱን የፈፀመ ቢሆንም ገና መዋቅሩን ባለማዋሀዱና በዚህ ግርግር የራሳቸውን ጥቅም አስቀድመው ለኢህአዴግ መሣሪያ የሚሆኑ ሰዎች በቅንጅቱ ውስጥ ሊኖሩ እንደሚችሉ ምንም ጥርጥር አልነበረውም ኢህአዴግ በዚያው ሰሞን በኦብኮ ላይ የወሰደውን ዓይን ያወጣ የኃይል እርምጃና በጉልበት ድርጅቱን የመከፋፈል ሴራ ሁላችንም አይተነው ነበር ለዚህ ሥራው ደካማና ገብጋባ የሆነ የኦብኮ አባላትን ተጠቅሟል ይህንን በቅንጅቱ ላይ አንዴ ሞክረው በመኢአድ በኩል ባይሳካላቸውም እንደገና መሞከራቸው አይቀርም አገዛዝ ሥርዓቶች የሰዎችን ደካማ ጎን ፈልጎ እሱን ለፀረዴሞክራሲ ዓላማቸው መጠቀም የተካነበት ችሎታቸው ነው የማይወዱትን አልገዛም የሚልና ለእምነቱ የፀናን ዜጋ ነው ስለዚህ ይህ የነዛነት ገህ ሲቀደድ ውሳኔ ምንም ሆነ ምን ቅንጅቱ አንድነቱን ጠብቆ ውሳኔውን ለማስፈፀም በሚችልበት ሁኔታ መጠናቀቅ አለበት ይህን ከግምት በማስገባት ስብሰባው ሲጀመር በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ አንድ ሀሳብ አቀረብኩ ምንም እንኳን በሕገደንባችን መሠረት የላዕላይ ምክር ቤት ውሳኔ በአብላጫ ድምጽ የሚወሰን ቢሆንም ይህ ሁኔታ የተለየ ስለሆነና ውሳኔውንም ተግባራዊ ለማድረግ በቅንጅቱ ውስጥ ጠንካራ አንድነት እንዲኖር ስለሚያስፈልግ ማንኛውም ውሳኔ ቢያንስ ኛ ድምጽ ካገኘ ብቻ ተፈፃሚ ይሁን ይህን ካላገኘ ጉዳዩን መልሶ ለውይይት ማቅረብና ተጨማሪ ሰዎችን በክርክር ለማሳመን ይሞከር ሁለተኛ ሰው ስሜቱን ያለምንም መሸማቀቅ እንዲያቀርብ የድምፅ አሰጣጡ በምሥጢር ይሁን አልኩኝ በዚህ ፃሳብ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄደ ኛ ድምጽ ያግኝ የሚለው ብዙ ያከራከረ አልነበረም በዚህ ዙሪያ እንዲውም አንዳንድ አባሎች በሙሉ ድምጽ ይሁን ብለው ጠይቀው ነበር የበለጠ ያከራከረው የምሥጢር ድምፅ አሰጣጥ ይሁን የሚለው ዛሳብ ነበር በተቃራኒው የተነሳው ዋና ክርክር በግልፅ የሚሰጥ ውሳኔ ተጠያቂነት ያበረታታል የምሥጢር ድምጽ ግለሰቡ የሚፈልገውን እንዲወስን ያበረታታዋል ነገር ግን የቅንጅቱ መሪዎች በውሳኔያችን የምንፈራበት ምንም ምክንያት አይኖርም ለውሳኔያችንም በግልጽ ተጠያቂዎች መሆን አለብን የሚል መከራከሪያ ነበር የተነሳው አንዳንድ ግለሰቦች ይህንን የፓርላማ መግባት ውሳኔ በተመለከተ በሚሰማቸው ስሜት ላይ በመመርኮዝ ድምጽ ላይሰጡ ይችላሉ ተባለ እነዚህ ሰዎች ከእውነተኛ ስሜታቸው ይልቅ ሊጫወቱ የሚፈልጉት ጊዜያዊ የፖለቲካ ጨዋታ ሊኖር እንደሚችል ጥርጣሬ ውስጥ የተገባው አንድ የምክር ቤቱ አባል ባደረገው ንግግር ነበር ኢዴአፓመድኅን ለቅንጅቱ ላዕላይ ምክር ቤትና ለሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የሚሆኑትን ስዎች ለመወሰን በልደቱ ቡድንና በሌሎች ዘንድ ከፍተኛ ትግል አካሂዶ ነበር ከላይ የጠቀስኩት የምክር ቤት አባል የድርጅቱ የማዕከላዊ ምክር ቤት አባል የነበረና በተወሰኑ አባላት ዘንድ ድጋፍ የነበረው የነልደቱ ቡድን ቀርቦ ያናግረዋል ቡድኑም ይህ አባል ሊያልፈው የማይችል አጓጊ አማራጭ ቨከ ያቀርብለታል ከእነሱ ጋር ሆኖ ድምጽ ከሰጠና ሌሎቹንም ድጋፍ እንዲሰጡ ካስደረገ በቅንጅቱ ሥራ አስፈፃሚ ከሚወከሉት አምስት ሰዎች አንዱ እንደሚሆንና ከእሱ ጋር የሚመረጡትን ሌሎች አራት ሰዎች ስምም አብረው ይነግሩታል ይህ ሰው ይህንን አምኖ በማዕከላዊ ምክር ቤት ለነልደቱ ቡድን ለአዲሶቹ ጾር ብርፃኑ ነጋ አምስት ተመራጮች ያደርጋል የምርጫው ጊዜ ሲደርስ ግን እነ ልደቱ ከሱ ውጪ ቀድሞውኑ ያዘጋጁትን አምስት ሰዎች ያስመርጣሉ በዚህ በነልደቱ ቡድን ብልጠት እጅግ የቆሰለው ይህ ሰው የፓርላማ መግባት ውይይት ላይ ድምፅ ፊት ለፊት እንዲሰጥ አጥብቆ ይሟገታል ምክንያቱንም ሲያስረዳ እዚህ ቤት ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰዎች ለራሳቸው ጥቅም ቅንጅትን ፓርላማ እንዲገባ ማስወሰን ይፈልጋሉ ይህ ከተወሰነ በኋላ ግን ከሕዝቡ ጋር ላለመጣላትና ዋናው የሕዝብ ጥቅም አስጠባቂ ለመምሰል ብዙኃኑ እንግባ የሚል ድምጽ ሲሰጥ እኛ ይህንን ፓርላማ የመግባት ውሳኔ ተቃውመናል ብለው ለሕዝብ ለመፈከርና በሕዝብ ዘንድ በሀሰት አድናቆትን ለማግኘት ይሞክራሉ ይህ ዓላማ ያላቸው ሰዎች እንዳሉና እንዲህ ዓይነት የምሥጢር ድምፅ አሰጣጥ ለምን እንደተጎነጎነ አውቃለሁ ብሎ ተናገረ ስብሰባውም ላይ የነበረው ሰው በነገሩ በጣም ተገረመ ይህ ሰው የሚናገረው ስለ እነማን እንደሆነ ግልጽ ነበር ግን ወደዚህ ደረጃ መዝቀጥ ይችላሉ ወይ የሚለው ሁሉንም ያስደመመ ነበር ከዚህ ንግግር በኋላ የምሥጢር ድምጽ አሰጣጥ የሚለው ዛሳብ ተቀባይነት አላገኘም እኔም ያቀረብኩትን ሀሳብ ከዚያ በኋላ አልገፋሁበትም የውሳኔ አለጣጡም በፍፁም ቅርቃር ውስጥ ካልተገባ በስተቀር ኛ ድምጽ እንዲሆን በፍፁም የማይቻል ከሆነ ግን ከሦስት ሙከራ በኋላ ወደ አብላጫ ድምጽ ሊመለስ እንደሚል ተወስኖ ከሰዓት በኋላ በዋናው ፍሬ ነገር ላይ ውይይት ተጀመረ ስብሰባውን የምትመራው ወት ብርቱካን ነበረች ኢንጅነር ኃይሉ ገና ከውጭ መምጣቱ ነበር ከዚያም በላይ ግን በክርክሩ በቀጥታ መሳተፍ እፈልጋለሁ ስላለ ለስብሰባው አካሄድ እንዲያመች ሲባል ብርቱካን ተመረጠች ሁለቱም ወገኖች አቋማቸውን አጠንክረው ገለጹ ክርክሩ የሚካፄደው በስብሰባው ወቅት ብቻ ሳይሆን በእረፍት ሰዓትም ገና አልወሰኑም በሚባሉ ሰዎች ላይ ቅስቀሳ ይደረጋል የሚቀርቡት ክርክሮች የታወቁ ናቸው ፓርላማ መግባት የለብንም የሚሉት ከዚህ በፊት የጠቀስኳቸውን መከራከሪያዎች የሚቀርቡ ነበሩ በጥቅሉ በዚህ ሰዓት ፓርላማ መግባት ኢህአዴግ ለዘረፈው የሕዝብ ድምፅ እውቅና መስጠት ነው ከዚያም በላይ ግን ቅንጅቱ የተነሳበትን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዓላማ መካድ ነው ኢህአዴግ የሰረቀውን ሥልጣን እንኳን እንተውልህ ነገር ግን የወደፊቱ ሂደት ዴሞክራሲዊ መሆኑን በጋራ እናረጋግጥ ቢባል እምቢ ያለው ለአሁኑ ሥልጣኑ ፈርቶ አይደለም እሱንማ ያዘው ተብሏል የነፃነት ገህ ሲቀደድ ለወደፊቱም ቢሆን በምርጫ ሥልጣኔን አልለቅም እያለን ነው መልእክቱ ይህ ከሆነ ፓርላማ መግባታችን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው የሚፈይደው ነገር የለም እንዲያውም በተቃራኒው እያወቅን ለኢ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውቅናና ድጋፍ መስጠት ይሆናል ፓርላማ በመግባት የምናተርፈው ነገር ቢኖር ከኢህአዴግ የጉልበት እርምጃ ራሳችንን ማዳን ነው ያውም ምናልባት የተመረጥነውን ብቻ ሌሎች በተለይ በገጠር ያሉ አባሎቻችንን ማሰሩ ማንገላታቱ የሚቀጥል እንጂ የሚቀንስ አይሆንም የቅንጅቱንም አመራርና ተመራጮች ቢሆን ለጊዜው ይተውን እንደሆነ እንጂ ትንሽ ቆይቶ ሁኔታው ሲረጋጋለትና ሕዝቡም በቅንጅት ፓርላማ መግባት ተበሳጭቶና በእኛ ላይ ያለውን እምነት ካጣና ከተፋን በኋላ አይለቀንም የኢህአዴግ ዓይነት ቂመኛ መንግሥት በምርጫው ወቅት የደረሰበትን ውርደት እንዲሁ የሚረሳና የሚተው አይደለም ቅንጅቱ የፈጠረውን የነፃነት ስሜት ለማጥፋት ቅንጅቱን ማጥፋት አለብኝ ብሎ የሚያምን ድርጅት ነው ስለዚህ በመግባት የምናገኘው አጠቃላይ የፖለቲካ ክስረት እንጂ ጥቅም አይደለም ፓርላማ በመግባት የሚገኘው ትልቁ ነገር ደግሞ የህዝቡን እምነት ማጣት ነው በግንቦቱ ምርጫ ሕዝቡ በመጀመሪያ ጊዜ በፖለቲካና በፖለቲከኞች ላይ እምነት ያሳደረ ነበር ሕዝቡ ቅንጅቱን ለራሱ ጥቅም የሚታገል ሳይሆን ከሁሉም በላይ ለሕዝቡ ነፃነትና ለዴሞክራሲ የሚታገል እውነተኛ ድርጅት ነው ብሎ አምኗል ማመን ብቻ ሳይሆን ቅንጅቱ የዚህ የሕዝብ የነዛባነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት የሚንፀባረቅበት መንፈስ ሆኗል ቅንጅቱ ይህን የሕዝብ አመኔታ ትቶ አራሱን ለማዳን ብቻ ብሎ ፓርላማ ቢገባ የኢትዮጵያ ሕዝብ በፖለቲካና በፖለቲከኞች ላይ ያለውን እምነት አንቅሮ ይተፋል ይህ ደግሞ የሰላማዊና የዴሞክራሲያዊ ሽግግርን የጊዜ ሰሌዳ በብዙ ዓመታት ወደ ኃላ ይገፋዋል በአንፃሩ ፓርላማ አለመግባት በመጀመሪያ በመርህ ደረጃ ለኢህአዴግ እምቢታ አለመንበርከክን ያሳያል ቅንጅቱ መፍትሄ ፍለጋ ብዙ መጣሩን ማኅበረሰቡ ያውቃል ሁሌም ጉልበቱን ተማምኖ አምቢ ያለው ኢህአዴግ ነው በዚህ በመጨረሻ ሰዓት ራሱን ለብዙ አደጋ አጋልጦም ቢሆን በዴሞክራሲ ላይ ላለው እምነቱ መጽናቱ ለዘለቄታው ድርጅቱን እውነተኛ ዓላማ ያለው ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ያደርገዋል ከዚያም በላይ ውሳኔው ከሕዝቡ ፍላጎት ጋር አንድ አይነት ስለሆነ የሕዝቡን ስሜት የሚሰማ እውነተኛ የሕዝብ ድርጅት መሆኑን ያሳያል ፓርላማ ባለመግባት በኢህአዴግ በኩል ሊመጣ የሚችለውን ጥቃትም መከላከል ጾር ብርሃኑ ነጋ የምንችለው ከሕዝቡ ጋር በመሆን ብቻ ነው ሌላው ወሳኝ ነጥብ ደግሞ ለኢህአዴግ የማይገባውን የትክክለኛነት ገጽታ አለመስጠታችን ነው ይህም ይዘግይ እንጂ ኢህአዴግን ተመልሶ ድርድር ውስጥ እንዲገባ ማስገደዱ አይቀርም ይህ ሁሉ እንኳን ባይሆን በሚቀጥሉት ምርጫዎች ከሕዝቡ ጋር ሆነን ጠንካራ ግፊት መፍጠር እንችላለን የሚሉና የመሳሰሉ ጠንካራ ምክንያቶች በተለያዩ አለመግባባትን በሚደግፉ አባላት ቀርበዋል በዚያው መጠን ፓርላማ መግባትን የሚደግፉት ኃይሎች ያላቸውን መከራከሪያ አቅርበዋል መከራከሪያው በዋናነት ኢህአዴግ ሊወስድ የሚችለው እርምጃ ቅንጅቱን ይጎዳዋል ቅንጅቱ ያገኘውን የህዝብ ተቀባይነት ይዞ በፓርላማ ውስጥ የሕዝቡን ጩኸት እያሰማና አዲስ አበባን እያስተዳደረ ለሚቀጥለው የወረዳና የቀበሌ ምርጫ ቢዘጋጅ ይሻላል ኢህአዴግ አሁን የተደናገጠ አውሬ ነው ሥልጣኑን እንዳልተነካበት ሊያውቅ ትንሽ ቀይቶ ሊረጋጋ ይችላል አንዳንድ መጠኛ ለውጦችን ሊያደርግ ይችላል እርግጥ ምርጫው ተጭበርብሯል ሕዝቡም ድምጹ ይከበር እያለ እየጮኸ ነው ቅንጅቱም በትዕግስት ኢህአዴግን ለማግባባት ብዙ ጥሯል ሕዝቡም ይህንን ይረዳል ግን ኢህአዴግ በገባበት ቀውስ ተደናግጦ አገሪቱን ትርምስ ውስጥ ከሚከታት እኛ ሕዝቡን አረጋግተን ለሚቀጥለው ምርጫ ብናዘጋጀው ይሻላል የሚል ነበር የዚህ አቋም ድክመት ከዚህ ቀጥሎ የሚኖሩት ምርጫዎች ዴሞክራሲያዊ ይሆናሉ ብለን የምናምንበት ምክንያት ይኖራል። ይህን በማድረግም ሕጋዊ መሆን ብቻ ሳይሆን ከዚያም አልፎ ሌሎች ሕገወጦችና ፀረሰላም ወገኖች በሁኔታው ተጠቅመው የሕዝቡን ሰላም እንዳያውኩ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርጓል ከሁሉም በላይ ደግሞ የትግሉ ዒላማ ላይ ምንም ብዥታ እንዳይኖር በጥንቃቄና በዝርዝር ዒላማዎቹን ተንትኗል ዒላማዎቹ የአገሪቱን የዴሞክራሲ ሂደት ለጊዜያዊ ሥልጣን ብሎ እያበላሸ ያለው ገዢው ፓርቲ በተለይ ይህንን ኢዴሞክራሲያዊ አገዛዙን ለማስፈን የሚጠቀምባቸውን የፋይናንስ እና የፕሮፖጋንዳ ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ነበር ከየፓርቲው የንግድ ድርጅቶች ለሚገኝ ጥቅም ብሎ ከሆነ ዴሞክራሲው እየተረገጠ ከሆነ ከእነዚህ ተቋማት ጋር የኢኮኖሚ ግንኙነት ባለማድረግ ተቋማቱን ማዳከም እንደሚቻል ለማሳየት እነዚህን ተቋማት ዒላማው ያደርጋል የመንግሥትና የፓርቲ የፕሮፖጋንዳ መሣሪያዎች እውነት መናገር እስከሚጀምሩ ድረስ እነዚህን የፕሮፖጋንዳ መሣሪያዎች አለመስማት እና አለማየት መብት ነው ከዚያ በላይ የሕዝብን አመኔታን ዓይንና ጆር ያላገኙ የፕሮፖጋንዳ ተቋማት ለመንግሥትም ምንም ፋይዳ እንደሌላቸው ጾር ብርፃኑ ነጋ ማሳየት ይቻላል ሥራ ትቶ ለተወስኑ ቀናት ቤት በመቀመጥ የሕዝብ ትብብር የተነፈገው መንግሥት በሥልጣን ላይ እንኳን በጉልበቱ ቢቆይ አገርን ለመግዛት ምን ያህል እንደሚቸግረው ለማሳየትና በዚህም ግፊት ገዢዎቻችንን ወደ ልቦናቸው ለመመለስ ይቻል ይሆናል ተብሎ ተገምቷል ሌላው የትግሉ ዒላማ በግለሰብ ደረጃ ሕገወጦች ላይ ያነጣጠረ ነው የሕዝቡን መብት በሕገወጥ መንገድ የሚረግጡ ሕግ ከሰጣቸው ሥልጣንና ኃላፊነት ወጥተው ሕዝቡን የሚያሸብሩ ግለሰቦችን ከእኩይ ተግባራቸው እንዲታቀቡ የሚገፋፉ በመጀመሪያ በግልፅ ማስጠንቀቂያ መስጠትበዚህ ማስጠንቀቂያ ካልተመለሱ ግን ማኅበረሰቡ ከበዳዮቹ ጋር «ሁሉ ነገር አማን ነው» ብለው እንዳያስቡ የሚያደርግ የማኅበራዊ ማግለል ርምጃን እንዲያደርግ ይጠራል ይህን ሲያደርግ ግን ምንም ዓይነት የዒላማ መሳት እንዳይኖር ከሁለት ነገሮች የትግሉ ተሳታፊዎች እንዲጠነቀቁ እና በፍፁም እንዲታቀቡ ያስጠነቅቃል የመጀመሪያው እንዲህ ዓይነት ማግለል የሚደረግባቸው ግለሰቦች እንጂ ምንም ዓይነት ቡድኖቹ አንዳልሆኑ አጥብቆ ያሳስባል ይህ ከመስመር ወጥቶ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ሕዝቡ ሆን ብሎ ያንን ያደርጋል ተብሎ ተፈርቶ ሳይሆን በተለይ በምርጫው ጊዜና ከምርጫው በኋላ ሕዝቡን እርስ በእርሱ በዘርና በጎሳ ለመከፋፈል የሚደረገው እኩይ ተግባር ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሞ እንዳይባባስ ለመቆጣጠርና ሕዝቡም የትግሉ ዒላማ ማንኛውም ብሔር ብሔረሰብ ጎሳ ዘር ወይም የሃይማኖት ተከታይ ወይም የፖለቲካ ቡድን ላይ በጅምላ ያነጣጠረ እንዳልሆነ በግልፅ እንዲያውቀው ለማስተማርም የተደረገ ነበር የኢህአዴግን ፀረዴሞክራሲዊ ባሕርይ በመገንዘብ ኢህአዴግ የሆነ ሁሉ ጠላት ነው ብሎ እንዳያስብ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል ከኢህአዴግ ጋር ያለው የፖለቲካዊ አመለካከት ልዩነት በዴሞክራሲዊ ሥርዓት ተቀባይነት ያለውና በሁሉም በኩል የሚጠበቀው ያንን እምነት ይዞ ሰላማዊ የፖለቲካ ፉክክር ውስጥ መግባትና በመጨረሻም የሕዝቡን ፍርድ በምርጫ ቀን አሜን ብሎ መቀበል እንደሆነ ማስተማር ዘለቄታዊ ፋይዳ አለው ተብሎ ታምኗል ስለዚህም አንድ ሰው የኢህአዴግ አባል በመሆኑ ወይም የኢህአዴግን የፖለቲካ መስመር በመደገፉ ምንም ዓይነት ማኅበራዊ መገለል ሊደርስበት አይገባም ከዚያ በላይ ሄዶ ግን በንፁሀን ዜጎች ላይ ግፍ መሥራትባልሠሩት ወንጀል ማሳሰርና ማንገላታት ከሰውየው አመለካከት ባሻገር የገዢ ፓርቲ አባልነትን ወይም የመንግሥት ሥልጣንን ከሕግ ውጪ በመጠቀም የዜጎችን መብቶች መጋፋት በዴሞክራሲያዊ ኅብረተሰብ የነባነት ገህ ሲቀድ ወይም ዴሞክራሲን በሚሻ ማኅበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት እንደሌለው ተግባራዊ ትምህርት መስጠቱ ተገቢ የትግል መሳሪያ ነው ብሎ ጥሪው ያምናል በቅንጅት የተጠራው የትግል ጥሪ ዶክመንት ዶሴ ከዚያ የትግል ጥሪ ያለፈ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ታምኗል እስከ ዛሬ በኢትዮጵያ ፖለቲካ በሥልጣን ላይ የሚፈፀምን ግፍ መቋቋሚያ ተደርጎ የሚወሰደው የመሳሪያ ትግል ብቻ ነበር የግንቦት ምርጫ ከጠመንጃ ትግል ውጪ በሰላማዊ መንገድ እና በምርጫ መንግሥትን መለወጥ እንደሚቻል ለማሳየት የተደረገ አስገራሚ ትግል ነበር ይህ ትግል እንደ ወትሮው በጉልበት ሲቀለበስና የሕዝብ ድምፅ በጠራራ ፀሐይ ሲዘረፍ ብዙ ሕዝብ የ ወደ ቀድሞው እምነቱ በመመለስ ከእንዲህ ዓይነት የጉልበት አገዛዝ መገላገል የሚቻለው በጉልበት ብቻ ነው» ወደሚለው አመለካከቱ ሊሄድ ይችላል የቅንጅት የሰላማዊ ትግል ጥሪ ለአገዛዝ ሥርዓት መልሱ ዝም ብሎ ተገዝቶ መኖር ወይም ጠመንጃ መያዝ ብቻ እንዳልሆነ ለማሳየት ይሞክራል በመካከል ያለው የሰላማዊ ትግል በአገርና በሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሳያስከትል የሕዝብን ይሁንታ ያላገኘ መንግሥት አገርን ለማስተዳደር በእጅጉ እንደሚቸግረው የሚያሳይ የዜጎች በዕለት ተዕለት ሕይወታቸው ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ትብብር በማቆም ወይም በመቀነስ መንግሥትን ማንበርከክ እንደሚችሉ የሚያሳይ ለኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም ያልተገደበ ሥልጣንን የሚናፍቁና አንዴ ሥልጣን ላይ ከወጡ ሕዝቡን እንደፈለጉ መጋለብ የሚችሉ የሚመስላቸው የፖለቲካ ኃይሎች ካሉ እነሱንም ለማስጠንቀቅ የሚያስችል ፍቱን መሣሪያ መሆኑን ለማሳየት የሚሞክር የትግል ስልት ነው ለዚህም ነው የሰላማዊ ትግል ጥሪውን ቅንጅት አካባቢ ያሉ ሰዎች ያዩት አንድ ጊዜ ተደርጎ የሚያልቅ መሳሪያ አድርጎ ሳይሆን አጠቃላይ የአገሪቱን የፖለቲካ ትግል ስልት አቅጣጫ በዘላቂውም ሊቀይር የሚችል እንደ ቀድሞው በጉልበትና በገዳይ መሣሪያ የሚደረግ የአራዊት ጦርነት እንዳልሆነ የሚያስተምር አልፎ ተርፎም ሕዝብ ያለውን መብት እስከ መጨረሻው በመጠቀም የሥልጣን ምንጩ እሱና እሱ ብቻ መሆኑን የሚያስረግጥበትና የሰለጠነ መሣሪያ በእጁ የሚያስገባባት አጠቃላይ ቅንጅቱ የተነሳበት የዴሞክራሲያዊ ትግል አንድ አካል አድርጎ የወሰደው የትግል ጥሪ ነበር የፓርላማ አለመግባት ውሳኔ በተወሰነበትና የሰላማዊ ትግል ጥሪው ጾር ብርፃዛኑ ነጋ በተደረገበት ጊዜ መካከል የሦስት ሳምንታት ክፍተት ነበር ይህ ጊዜ ያለፈው በተለያዩ ምክንያቶች ነበር የመጀመሪያው ከላይ እንደተጠቀሰው የትግል ጥሪው እንደ ከዚህ በፊቱ በአጭር መግለጫ «ይህን አድርጉ» ተብሎ ሳይሆን የትግሉ ተሳታፊዎች ዓላማውንና ዒላማውን በደንብ እንዲያውቁት ለማድረግ ከነዝርዝር ምክንያቶቹ መቅረብ ነበረበት ይህንንም በማድረግ እግረ መንገዱን ሕዝቡን ስለ ሰላማዊ ትግል በዚያ ጥሪ ብቻ አንደማያቆም የሚገመተው ሥር የሰደደ ግንዛቤ ለመስጠት ያስችላል ከዚያም አልፎ ግን ከአመክኒዮት ከሎጂክ ጋር ያልተጣሉ አንዳንድ የኢህአዴግ ሰዎች ከተረፉም የቅንጅቱን ዓላማ ግልፅ በማድረግ ጥቂት የኢህአዴግ መሪዎች ድጋፍ ለማሰባሰብ ሲሉ ቅንጅቱን ጭራቅ አድርገው ለመሳል የሚያደርጉትን ከንቱ ፕሮፖጋንዳ ለማራክስ ይጠቅማል ከዚያም ውጪ ግን የኢህአዴግ መሪዎች ቅንጅቱን ለማጥፋት ያላቸውን ዓላማ ለማሳካት የፍትሕ ሥርዓቱን ለመጠቀም መሞከራቸው አይቀሬ ነውና በዚህ የትግል ጥሪ ምክንያት ሆን ብለው ቀስቅሰው ነገሩን ወደ አመፅ ለመለወጥ እና በዚህም የቅንጅቱን መሪዎች በፈጠራ ክስ ለመወንጀል ከፈለጉ ያንን ለማድረግ የሚያስችላቸው ምክንያት ይከለክላቸዋል ጥሪው እንዲዘገይ ግን ሌሎችም ምክንያቶች ነበሩ ጊዜው የረመዳን ፆም የሚካሄድበት ወር ነው በዚህ ትግል ውስጥ በተለይ በአዲስ አበባ የሁሉም የፃይማኖት ተከታዮች ይሳተፋሉ ተብሉ ይገመታል የረመዳን ፆም እየተካሄደ ባለበት ጊዜ የቤት ውስጥ መቆየት ጥሪ ማድረጉ ከፆም በኋላ በየመስጊዱ የሚደረገውን የሦላት ፕሮግራም ያስተዓጉላል የሚል ፍርሐት ነበር ስለዚህም ቢያንስ የቤት ውስጥ መቆየት አድማው ፆሙና በዓሉ ካለቀ በኋላ ማድረጉ የሙስሊሙን ማኅበረሰብ በትግሉ ውስጥ በሰፊው ለማካተት ይጠቅማል በዚህ ምክንያት በሚገኘው ተጨማሪ ጊዜ ደግሞ ምናልባት በኢህአዴግ በኩል አደብ ተገዝቶ ይህ ነገር ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት እንደገና ወደ ድርድር ለመግባት ይፈቅድ ይሆናል የሚል የተሟጠጠም ቢሆን ትንሽ የተስፋ ጭላንጭል ነበር ይህ ተስፋ በአጠቃላይ በጥሪው መዘግየት ብቻ የተገለፀ አልነበረም በጥሪው የእርምጃ ቀስ እያለ እያደጉ የሚሄዱ መሆን አንዴ እንቅስቃሴው ከተጀመረ በኋላም በመሐል ሊደረግ ለሚችል የሽምግልና ጣልቃ ገብነት በር መከፈቱን ያሳያል እንደሚታወቀው የጥሪው የመጨረሻ ትልቁ አካል በቤት ውስጥ መቆየት አድማው ሲሆን ይህ ደግሞ ተግባራዊ የሚሆነው ሌሎች ርምጃዎች መውሰድ ከተጀመሩ የጥሩንባ መንፋት የግዢ ዕቀባ ወዘተ ከ ቀናት የነፃነት ገህ ሲቀደ በኋላ ነበር ይህ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በዚህ ጊዜ ውስጥ ድርድር ማድረግ ለሚፈልግ ኃይል በር መክፈት ተብሉ ነው መቼም በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ አቅድ ማውጣትና በእቅዱ መሠረት ተግባራዊ ማድረግ ለየቅል ናቸው ተግባር ላይ በአቅዱ ጊዜ ከስሌት ውስጥ ያልገቡ ብዙ ነገሮች ይመጡና እቅዱን ያዛቡታል እቅዱን ከሚለወጡት ነገሮች አንዱና ዋናው የባላንጣን እንቅስቃሴ ማወቅ አለመቻል ነው ቅንጅት እስከ መጨረሻው ድረስ ሕግ በእንዲህ ዓይነት ተነጻጻሪ በሌለው መልክ ይረገጣል ብሎ ባለመጠበቁ ጥሪውን ራሱን መጥራት የፈለገው ክፍት የሆነ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ነበር ይህ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ የታሰበው ቅዳሜ ጥቅምት ወይም በማግስቱ አሁድ ነበር ሆኖም ልደቱን ከድርጅቱ ለማገድ ጋዜጣዊ መግለጫ በተሰጠበት አርብ ፅለት በታጣቂ የመንግሥት ኃይሎች በተሰብሳቢዎችና በጋዜጠኞች ላይ በተወሰደው የእብሪት ርምጃ የተነሳ ይህ ጥሪ ከመውጣቱ በፊት መንግሥት የቅንጅቱን ቢሮ በመዝጋት ምንም ዓይነት ሥራ እንዳይሠራ በጉልበት ሊከለክል ይችላል የሚል ፍርሐት ነበር ስለዚህ በዚያን ፅለት ማታ የትግል ጥሪውን ዋና ዋና ነጥቦች በማግስቱ ለሚወጡ ጋዜጦች እንዲሾልክ ተደረገ ይህ የተደረገው በጋዜጣ ላይ አንዴ ከወጣ አንዴ ለማስቆም ይቸግራቸዋል በሚል ነበር በቀጣዩ ቀን ጋዜጠኞች ዝርዝር ጥሪውን ከቅንጅቱ ቢሮ መጥተው እንዲወስዱና የእሁድ ጋዜጦች ቢቻል ዝርዝሩን እንዲያወጡትና የትግል ጥሪው አጠቃላይ ይዘት ማኅበረሰቡ ጋር አንዲደርስ ታቅዲል ክፍት የሆነ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠት የሜቻልበት ሁኔታ ቢኖር ኖሮ በማኅበረሰቡ ውስጥ ብዥታን ሏፈጥሩ የሚችሉ ነገሮች በጋዜጠኞች በኩል በጥያቄ ተነስተው ቅንጅቱ ዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት እንዲህ ዓይነት ብዥታዎች ለማጥራት እድል ይኖረው ነበር ኢህአዴግ ጥሪው መደረጉን ካወቀ ቀን ጀምሮ ግን ቀደም ብሎ የተዘጋጀበትን የአጠቃላይ አፈና መርሐ ግብር ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ ሰኞ የሰላማዊ ትግሉ የመጀመሪያ ቀን የነበረው ጥሪ ለሦስት ቀናት የሚቆይ የመኪና ጥሩንባ የማስማት ጥሪ ነበር ጥሩንባ የሚሰማው በቀን ለግማሽ ሰዓት ብቻ ነበር በመጀመሪያው ቀን በጥቂት ቦታዎች እንጂ የተጠበቀውን ያህል ውጤት አልተገኘም የማል ዘገባ ነበር የሰማነው በሁለተኛው ቀን ውጤቱ ከሰኞው የተሻለ እንደነበር ተነገረን በአዲስ ከተማ አካባቢ አንዳንድ ግጭቶች እንደነበሩ ሰማን የግጭቶቹ ምክንያቶች ጾር ብርዛኑ ነጋ ከየ ጨመ ምን እንደሆኑ አላወቅንም ሁኔታዎች ክፉ ሊሆኑ እንደሚችሉና የመንግስት ታጣቂዎችና የደኅንነት ሰዎች ሆን ብለው ግጭት እንዲፈጠር እየጋበዙ እንደሆነ በተለይ በመርካቶ አካባቢ ተሰምቶ ነበርሱ የአዲስ ከተማ ተማሪዎችን ያለሰዓታቸው በመልቀቅ ግጭት ውስጥ እንዲገቡ የማድረግ ርምጃዎች ይወስዳሉ የሚል ጭምጭምታዎች ይሰማ ስለነበር ቅንጅቱ ያንኑ ዕለት እንዲህ ዓይነት ሆን ብሉ ግጭት የመፍጠር ፍላጎት በመንግሥት ኃይሎች በኩል ሊኖር ስለሚችል ይህንን እኩይ ተግባር ለመቋቋም ሕዝቡ በምንም ዓይነት ለእንዲህ ዓይነት ጉንተላ እንዳይጋለጥ የሚጠይቅ አስቸኳይ መግለጫ አወጣ ሆኖም ሆን ብሎ ለረብሻ የተዘጋጀን የመንግሥት ኃይል ከእንዲህ ዓይነት የጥፋት ተግባሩ ለመመለስ የሚቻል አይደለም በራስ በኩል እንዲህ ዓይነት ግጭቶች እንዳይፈጠሩ መከላከል ይቻላል እስከ አፍንጫው የታጠቀና ያለውን የነፍጥ ኃይል በሰላማዊ ዜጎች ላይ ለመፈተን የሚጓጓን መንግሥት ለማስቆም የሚቻል አልነበረም ምንም ዓይነት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተዘጋጀ ድርጅት ሆን ብሉ ፀብ የፈለገን መንግሥት ከአመጽ መንገዱ ሊያስቆመው አይቻለውም መንግሥት የፈለገውን ግጭት ለማስቆም የሚቻለው ሁሉን ነገር አርግፍ አድርጎ ትቶ ለመንግሥት የእብሪት መንገድ አጎብድዶ በሰላማዊ መንገድ የሚደረገውን የነፃነትና የዴሞክራሲ ትግሉን በሙሉ አቁሞ እጅ ሰጥቶ በመቀመጥ ወይም ደግሞ ኢህአዴግ የሚወረውረውን «የዴሞክራሲ» ፍርፋሪ እየለቀሙ በኢህአዴግ የጊዜ ሰሌዳ «በሰላም» በመኖርና በዚህ ምክንያት የሚመጣውን ውጤት ለመቀበል ዝግጁ በመሆን ነው በቅንጅት ውስጥ ያሉ አንዳንድ ግለሰቦችን በተቃውሞ ስም ክራባታቸውን አስረው በየግብዣው በመዞር ብቻ «ተቃዋሚ ድርጅት ነን» ማለት ያጠግባቸው ይሆናል ይህ ለቅንጅቱ እንደ ድርጅትና የኢትዮጵያ ሕዝብ በግንቦቱ ምርጫ ለደረስበት የንቃተ ህሊና ደረጃ በፍጹም የሚመጥን አካሄድ አይደለም ከሁሉም በላይ ግን ለዚህ የኢህአዴግ የኃይል ርምጃ መስገድ በፍጹም ሰላምን የሚያመጣ አይደለም የቅንጅቱን ስምንት ጥያቂዎች በሰላማዊ መንገድ መመለሱ ይጠቅም የነበረው የግንቦቱ ምርጫ ይዞት የመጣውን የፖለቲካ ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ የመፍታትን ባህል ሥር እንዲሰድ ማድረግ ይችል ስለነበር ነው የኢህአዴግ ርምጃ የግንቦት ን ታሪካዊ አቅጣጫ ሰርኮ ማኅበረሰቡን ከዚህ በፊት ያውቅና ይረዳ ወደ ነበረው የፖለቲካ ችግሮችን በኃይል የመፍታት አካፄድ እንዲዞር በማድረግ የነፃነት ገህ ሲቀድ ግንቦት ን እንደ አንድ ትንሽ የታሪካችን የግርጌ ማስታወሻ አድርጎ ያስቀረዋል ይህ የኢህአዴግ የጥቅምት ርምጃ ከምንም በላይ አስክፊ ሁኔታ ሸህ ያደርገዋል ጥቅምት በኢትዮጵያ ፖለቲካ በምርጫበቡ መጭበርበር ምክንያት የተፈጠረው የረጅም ጊዜ ቀውስ የተፈታበት ቀን አቅጣጫው የታወቀ የነበረውን ነገር ግን በብዙ ኮረኮንቾች የታጀበውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ አውራ ጎዳና በቦምብ አዓራርሶ አቅጣጫወ ወዳልታወቀ ስምጥ ሸለቆነት የተቀየረበት ነው ጥቅምት በግንቦቱ ምርጫ ተቀባይነት ያገኘውን የሰላም ፖለቲካን መቆሚያ አሳጥቶ የአመፅ ፖለቲካን ከሰላማዊው ፖለቲካ በላይ አምክኀኖኒዮታዊ ያስመሰለ አሳዛኝ ርምጃ የተወሰደበት ቀን ነው ስዊዘርላንድ ኤምባሲ የነበረኝን ቀጠሮ ጨርሼ ወደ ቢሮ ልሂድ ወይስ ወደ ቤቴ እያልኩ ከራሴ ጋር ሳወራ ወደ ሰዓት አካባቢ ሞባይሌ ላይ አንድ የቅንድት አመራር ደውሉ ቡና አየጠጣን እናውራ ብሉ ፒያሳ አካባቢ ይተጥረኛል እሺ ብዬ በመስቀል አደባባይ በኩል ወደ ግዮን ሆቴል በሚወስደው መንገድ እየሄድኩ ሳለሁ ልክ ግዮን አካባቢ ካለው የኢዴአፓመድኀን ቢር አጠገብ ስደርስ በሦስት የፌዴራል ፖሊስ መኪኖች ተከበብኩ በተቀባበለ መሣሪያ አኔንም ሹፌሬንም ከመኪና እንድንወርድ ታዘዝን ምንም ሳያናግሩን አንደኛው ቶዮታ ላይ ሁለታችንንም ጭነው ወደ ቤተመንግሥት አቅጣጫ ወሰዱን ቤተ መንግሥት አጠገብ ስንደርስ ከመኪናው አስወርደው ሌላ የፈዴራል ፖሊስ መኪና ውስጥ አስገቡኝ ጋቢና ተቀምጩ በፖሊስ ኮፊያ እንድደበቅ ተደርጌ ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት በክፍተኛ ፍጥነት ተወሰድኩ ማዕከላዊ ስደርስ ወደ ሰዓት አካባቢ ነበር ተመዝግቤ ወደ ውስጥ ከመግባቴ በፊት ዶር ኃይሉ አርአያን ሲያስገቡት አየሁ ክዚያ ደቂቃ ጀምሮ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፍጹም አዲስና አሳዛኝ አቅጣጫ እንደያዘ ጥርጥር አልነበረኝም በዚያው ልክ ግን እንደ ቅንጅት የአመራር አባልነቴና እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በግንቦት ምርጫ በመሳተፌና አንደ ቅንጅት በወሰድናቸው የተለያዩ ውሳኔዎችና የዴሞክራሲ ትግሉ በሰላማዊ መንገድ እንዲሄድ ለተጫወትኩት ሚና ቅንጣት ታክል ቅሬታ አልነበረኝም ወደ እስር ቤት ስገባ የተሰማኝ ትልቅ ሸክም ከላዬ ላይ መነሳቱ ነበር ከአሁን በኋላ ለሚሆነው ሁሉ ተጠያቂው የኢህአዴግ መሪዎች ብቻ ዓቸው ትግሉ ይህን አቅጣጫ እንዲይዝ የተቻለንን ሞክረናል ከዚህ የተለየ ግን ልናደርግ የምንችለው ምንም ነገር አልነበረም የሚል ክፀፀት ነፃ የሆነ የእረፍት ስሜት ልቤን ሞላው ጾር ብርዛኑ ነጋ የክፍል ማጠቃለያ በዚህ ክፍል የቀረቡት የተለያዩ ምዕራፎች ከምርጫው ዕለት ጀምሮ የተፈጠሩ ክስተቶች እና ክስተቶቹን ቅንጅቱ ያየባቸውን መንገዶች የወሰናቸውን ውሳኔዎች እና ውሳኔዎቹን የገፋፏቸው ምክንያቶች አንዳንድ ጊዜም በቅንጅቱ ውስጥ የነበሩትን የአመለካከት ልዩነቶችና እነዚህ ልዩነቶች የተስተናገዱባቸውን መንገዶች ለማሳየት ተሞክሯል በዚህ ሂደት ውስጥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አሁን የደረሰበት አዘቅት ውስጥ እንዳይገባ በቅንጅቱ ውስጥ ይደረግ የነበረው ጥንቃቄ እስከ ምን ድረስ እንደ ሄዴ አሳይቷል ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ቅንድቱ ቀድሞውንም ሲፈራ የነበረውና እንዳይደርስ ሲጠነቀቅለት የነበረው ችግር እንደፈራው እየደረሰ ነው ይህ ቅንጅቱ ከወሰደው መስመር ሌላ አማራጭ መንገድ አልነበረም ወይ። የሚሉትንና ተመሳሳይ ጥያቄዎችን በዚህ አራተኛውና የዚህ ጽሑፍ ክፍል ለመመልከት ይሞከራል ይህ ክፍል ሦስት ምዕራፎችን ይይዛል ኢህአዴግ የወሰዳቸው ርምጃዎችን ዓይነት የሚነካካው ምዕራፍ የኢህአዴግን ስሌት ለመመልከት ይሞክራል ፀሐፊው ከኢህአዴግ እርምጃዎች በመነሳት የራሱን ግምት በመፍጠር የኢህአዴግ ስሌት የሚለውን ያቀርባል ይህን ስሌት በጽሑፍ የሚያሳይ የኢህአዴግ መረጃ አላገኘም ምዕራፍ የኢህአዴግ ስሌት ለምን እንደተሳሳተና ለምን ሰላምና መረጋጋትን ሊያመጣ እንደማይችል ለማሳየት ይሞክራል የዚህ ክፍልና የዚህ ጽሁፍ መጨረሻ የሆነው ምፅራፍ የኢህአዴግን ርምጃ ቅንጅቱ ከተከተለው የሰላማዊ ትግል አቅጣጫ ጋር በማያያዝ የአገራችንን የወደፊት ዕጣ ለመቃኘት ይሞክራል ጾር ብርሃኑ ነጋ ዴ ጥቅምት እና የኢህአዴግ ስሌት ኢህአዴግ የኃይልን መንገድ መርጦ የወሰደው ርምጃ ያስገኝልኛ ል ያለውን ውጤት በምን መንገድ ሊያሰላው እንደሚችል ያለኝን ግምት ከነምክንያቱ ከመስጠቴ በፊት የጥቅምት ርምጃ በራሱ በማን ላይ እንዳነጣጠረና በዚያ ርምጃ ይገኛል ተብሉ የታሰበውን የቅርብ ጊዜ ውጤት መመልክቱ ይጠቅማል በመጀመሪያ በተመለከተው የተወሰደው ርምጃ የቅንጅቱን ዋና ዋና አመራሮች ማሰር ስለነበር የተጠበቀው ውጤት ቅንጅቱን ቢቻል በነበረበት ሁኔታ ማጥፋት አሊያም በእጅጉ ማዳከም የሚኖርም ከሆነ ቅንጀቱን ኢህአዴግ በሚፈልገው መልክ ማዋቀር ይመስላል ይህንንም ሲያደርግ በዋናነት ቅንጅቱ የጠራውን የሰላማዊ ትግል ጥሪ ማኮላሸት የነባነት ገህ ሲቀድ ወዲያውኑ የሚገኝ ውጤት ይሆናል ብሎ ሊገምት ይችላል ነገር ግን አጠቃላይ የአፈናውን ዒላማዎች በጥንቃቄ ለተመለከተው ኢህአዴግ የወሰደው ርምጃ እንዲያስገኝ የተፈለገው ውጤት ብዙ የታሰበበትና ሩቅ ቦታ ይደርሳል ተብሎ የታለመለት መሆኑ ቀስ እያለ ግልጽ ይሆናል ብዙ ሰው እንደሚያስበው የኢህአዴግ ርምጃ ዋና ዓላማ ቅንጅቱን እንደ ድርጅት ማጥፋት ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ በዋናነት «የቅንጅትን መንፈስ» ማጥፋት ነበር በሌላ አነጋገር ዓላማው ትንሽ ያስቸገሩ «ነውጠኞችንጨ ለመቆጣጠርና አገሪቱን «ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት» ማመቻቸት ሳይሆን በተቻለ መጠን የእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ፍላጎት መግደል ነበር በተለይም በግንቦቱ ምርጫ የተፈጠረውን የሕዝቡን የነፃነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት አብሮ የመጣውን የነፃነት መንፈስና ከፍርፃት የመላቀቅ ስሜትን ለአንዴም ለሁሌም መጨፍለቅ ነበር ለዚህ ነው የኢህአዴግ ዓላማ በፍጹም የታለመለትን ግብ መምታት የማይችለው ይህንን ለመረዳት በመጀመሪያ መመልክት የሚያሻው የመንግሥት የጥቃት ሰለባ እንዲሆኑ የተመረጡትን ሰዎች ዝርዝርና ስብጥር ነው የተወሰነ መዘበራረቅ ቢኖርበትም ከቅንጅቱ አመራሮችና አባላት ውስጥ የታሠሩት ኢህአዴግ ቅንጅቱ በወሰዳቸው ርምጃዎች ተጠያቂ ይሆናሉ ብሎ ያመናቸውን ሰዎች አይደለም ይህ ቢሆን ኖር ከቅንጅት አመራር ውስጥ ውሳኔ ስጪዎቹን በሙሉ ያስር ነበር ወይም ያሰራቸው ውሳኔውን በተግባር የማዋል ሚና የነበራቸውን ሰዎች ነው እንዳይባል በእሱም መለኪያ ምንም የማይመለከታቸው በርካታ ሰዎች ታስረዋል ቅንጅቱ በወሰዳቸው አርምጃዎችና ውሳኔዎች ምንም ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ ሚና ያልነበራቸው ሰዎች በመጀመሪያ አመራር ከተባሉት ተከሳሾች ውስጥ በብዛት ይገኛሉ ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ በአንዱም የቅንጅቱ አመራር ስብሰባ ላይ ያልተሳተፉ ሰዎች ናቸው በአንፃሩ በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ ተሳትፈው ምንም ዓይነት እርምጃ ያልተወሰደባቸው ብዙ ሰዎች አሉ ስለዚህ ርምጃ አወሳሰዱ ባለፈው በሆነው ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሳይሆን ወደፊት እንዲሆን የሚፈለገውን ሁኔታ ለማመቻቸት ተብሎ የተወሰደ መሆኑን ያመላክታል ኢህአዴግ ክርምጃዎቹ በኋላ ሊሽከረከርበት ፅእዳዚሀ የቅፅቻ ሰዝቃባሥቻ ይ እነማጋ ለሄሀደሚሳታፉ ጴሀለዴፇና መሃፇግሥሦ ዲያውም ዖሚቋ ያዎህታኦ መቼም ማኃም ይኖረውም ያዎዕቻራ ይሥራ ዕፈፃሟም ያሆ ያጎሪጎሳይ ምኣረ ቤታ እ ማታ ዝቻ ይሆን ሰምን ሰብዕዛ ይ ማሃ ምኃ ለሐ ያሜሚሰውሃ ርር ቀደም ታም እድሚያውቀ ቋደንንነፉ ሰሰ ለ ሃጋዜጣማ ቋርረታኑ መረሻሥቅቻና ሰወዉውታ ሃባሥቻ ይ ማዖ ይቻጎፅ ጾር ብርሃኑ ነጋ በሚፈልገው የፖለቲካ ምህዋር እንዳይሾርበት እንቅፋት ሊሆነኑብኝ ይችላሉ ብሉ የገመታቸውን ሰዎች ነው በእኔ እምነት እነዚህ ሰዎች ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች» የሚፈልጋቸውን ሦስት ፀባዮች በበቂ አያሟሉም እነዚህ ሰዎች በገንዘብና በሥልጣን ተደልለው ዓላማቸውን ሙሉ በሙሉ አይሸጡም ዕምነታቸውን በቀላሉ አይለቁም በመንግስት በኩል ጫና ሲመጣ አንገታቸውን ደፍተው አርፈው ኑሯቸውን አይኖሩም ሦስተኛ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በውጭ እስካሉ ድረስ እናምንበታለን የሚሉትን ዓላማ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ መግፋታቸው አይቀርም ይህንን በማድረግም በጥንቃቄ የተዘጋጀውን የኢህአዴግ መሠሪ ፕላን ተግባራዊ በማድረግ ደረጃ የጀርባ ላይ ቅማል መሆናቸው አይቀርም ስለዚህ ለፕላኑ ተግባራዊነት እነዚህ ሰዎች ከጨዋታው መውጣት አለባቸው ኢህአዴግ ሊመሠርተው ያሰበው በእሱ ሙሉ ቁጥጥር ሥር የዋለ «የአንድ ፓርቲ የበላይነት ያለው ዴሞክራሲ» እዚህ ላይ ዴሞክራሲ የሚለውን እንዳለ እንውሰደው በእርግጥ ተግባራዊ እንዲሆን እንደ እነፒህ ዓይነት ጥቂት አስቸጋሪ ሰዎችን ማስወገድ እንደማይበቃ በሚገባ ያውቃል በአጠቃላይ እውነተኛ ዴሞክራሲ መመሥረት ይቻላል ይገባናልም ብለው የሚያምኑና ለዚህም ለመሥራት የቆረጡ ከፖለቲካ ፓርቲ ውጪ ያሉ ኃይሎችንም በቁጥጥር ሥር ማዋል ያስፈልጋል በቁጥጥር ሥር የሚውሉት ደግሞ ሁሉንም በማሠር ሳይሆን ይህንን ዓይነት ፀባይ ያንፀባረቁ ጥቂት ሰዎችን የእስር ሰለባ በማድረግ ለሌሎቹ የእኔን ያየህ ተቀጣ መልእክት ለማስተላለፍ ነው በዚህ ዙሪያ በእስሩና በክሱ የተካተቱት ከየትኛውም የቅንጅቱ ውሳኔ ወይም ርምጃ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸውን የግል ሚዲያ ጋዜጠኞች ባለቤቶችና የሲቪክ ማኅበረሰብ አባላት ይጠቅሳሉ በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው ርምጃ የግል ሚዲያው ወደፊት ለይስሙላ እንዲኖር ከ«ተፈቀደለት» እውነተኛ የመብቱን ልክ አውቆ በራሱ ላይ ቁጥጥር እንዲያደርግ ቨ በከሠ በአጠቃላይ ደግሞ በግል ሚዲያ የሚሰራ ማንኛውም ሰው አኗኗሩ በሰውነትም በኢኮኖሚም የሚወሰነው በመንግሥት ፈቃድ መሆኑን እንዲያውቀውና ፍርሃት በልቦናው እንዲሰርጽ ለማድረግ የተወሰደ ነውር ጋዜጠኞቹ ከዚህ በፊት በሠሩት ሥራ «ህገ ወጥነት» በመታየቱ ቢሆንማ ኖሮ እነዚህ የሚዲያ ሰዎች የኢህአዴግ መንግሥት ራሱ ባወጣው የፕሬስ ህግ መሠረት ይከሰሱ ነበር ዒላማው ያለፈው ሥራቸው ሳይሆን ሴክተሩ እንደ ሴክተር «በአዲሱ» የኢህአዴግ የነዛነት ገህ ሲቀደ ሥርዓት የሚኖረውን ሚና በግልጽና በማያሻማ መንገድ በህግ ሳይሆን በተግባር ማሳየት ነው ከሲቪክ ማኅበረሰቡም በተለይ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚያወሩትን መሆን አለባቸው ብለው ገንዘብ ለመጠየቅ ለመለመን በሚዘጋጅ ፕሮፖዛል ላይ «ዓላማችን ዴሞክራሲን መገንባት ነው» ሲሉ እያወሩ በተግባር ግን መሬት ጠብ የማይልና ለዴሞክራሲ ግንባታ ፋይዳ የሌለው ሥራ መሠራት የለበትም ብለውና የዴሞክራሲ ግንባታን ከምር ወስደው ትንሽ ለመፍጨርጨር የሞከሩትን ሰዎች መጀመሪያ በደኅንነት ጡንቻ ማስፈራራት አልሠራ ሲል ከሌላው ጋር ደምሮ «በዘር ማጥፋት» ወንጀል ትብብር መክሰስ ልክ አንደ ነፃው ፕሬስ ጠቅላላ የመያድ ማኅበረሰቡን ለማሸበርና በኢህአዴግ ከተቆረጠለት ሥራ ውጪ አልፍ እንዳይል ለማስጠንቀቅ የተዘየደ ነው በኢህአዴግ እምነት የሕዝቡን የዴሞክራሲ ፍላጎት ለመግደል ከዴሞክራሲ በመጀመሪያ ሊጠቀሙ ይችላሉ ተብለው የሚታመኑትን የንዑስ ከበርቴ ክፍል አባላት ከእንዲህ ዓይነት «ቅዝት» እንዲነቁና የአገሪቱን የሥልጣን እውነታ በደንብ እንዲያዩ ማድረግ ያስፈልጋል ስለዚህም ይህ ክፍል የኢህአዴግ ቀዳሚ ዒላማ መሆኑ የሚገርም አይደለም የሚጠበቅ እንጂ የኢህአዴግ ተግባር የታሰበበት መሆኑን በግለጽ የሚጠቁመው ሌላ ነገር አፈናው ዒላማ ያደረጋቸው በዚህ ምርጫ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ አስተዋጽዖ ሊኖራቸው ይችላል የተባሉ ከአገር ውጪም የሚኖሩ ዜጎችና ኢትዮጵያዊ ትውልድ ያላቸውን ጭምር መሆኑ ነው ኢህአዴግ በክሱ ወስጥ ያጠቃለላቸው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያዊ ትውልድ ያላቸው በአጠቃላይ «እኔን የማይወዱ» የሚላቸውን ነው ይህ መልዕክት በውጭ የምትኖሩም ብትሆኑ በሥልጣኔ ከመጣችሁ ሌላ ማድረግ ቢያቅተኝ አገራችሁ እንዳትመጡ ማድረግ እችላለሁ ስለዚህ አገራችሁ መጥታችሁ ሰርግ ማድረግ የምትፈልጉ ከሆነ ወይም ወላጆቻችሁ ሲሞቱ ለመቅበር መምጣት የምትፈልጉ ክከሆነ እኔን ከሚቃወሙ የፖለቲካ ኃይሎች ራቁ የሚል ነው አሊያማ ስለ ሕግ ትንሽ እውቀት ያለው ሰው የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኞችን በመንግሥት መገልበጥ» ወንጀል አይከስም በክሱ የተካተቱ አንዳንድ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ዝርዝር አተኩሮ ለተመለከተው ይህንን ሰፊ የመንግሥት ዓሳማ ለማሳካት እነማንን እንጨምር ተብሎ በአንዳንድ በውጭ አገር በሚኖሩ ወይም ኖረው በመጡ የመንግሥት ዘመነኛ አማካሪዎች የተቀናበረ ይመስላል ማንም ያዘጋጀው ማን በምንም ዓይነት የወንጀል ጭብጥ ተይዞ ወንጀለኛ ጾር ብርዛኑ ነጋ ን ለመቅጣት የተደረገ «የወንጀል ምርመራ ውጤት» አለመሆኑንና ይልቁንም ከሰዎቹ ማንነት ይልቅ አጠቃላይ የማስፈራራት ፍላጎቱ ቅድሚያ የተሰጠው መሆኑ ብዙም የሚያጠራጥር አይደለም ትንሸ የሚያሳፍር ነገር ሆኖባቸው አንጂ እንዲህ ዓይነት ነገር በመርህ ደረጃ መኖሩን የሚጠራጠሩ እንዳሉ አገምታለሁ በውጭ የሚገኙ ሌሎቹንም ኃይሎች ለማስፈራራት በክሱ ውስጥ ወሮ አና ጎሜዝን ቢያካትቱ የሚጠሉ አይመስሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአንድ ጋዜጣዊ መግለጫ «ወንጀለኛ» ብሏቸው የለ። የሚሉትን ጥያቄዎች አመርቂ መልስ የሚፈልጉ ናቸው ዝርዝር ምክንያቶችን ከመስጠቴ በፊት ግን እኔ ራሴና ኣብረውኝ በእስር የሚገኙ የቅንጅቱ አመራሮች የሚጋሩትን አጭር መልስ በማስቀመጥ ልጀምር በእኛ እምነት ሰላማዊ ትግል አሁንም ይቻላል ተገቢም ነው በእርግጥ ጥቅምት ሁኔታዎችን ለዚያ ዓይነት ትግል አስቸጋሪ አድርጎታል ነገር ግን በሰላማዊ ትግል ስልት ሥር የሚካተቱ በርካታ የመታገያ መንገዶች የሰላማዊ ትግል በሚጠይቀው የድርጅት መዋቅርና ስልቱ የሚጠይቀውን ሥነሥርዓት ነዘበፀ በደንብ ከተከተሉ አሁንም በጣም ጠንካራ መሳሪያ ናቸው ብለን እናምናለን ከዚያም ባሻገር ግን በውጤት ደረጃም ከላይ ኢህአዴግ ሀሳቡን ቀይሮ ለውይይትና ለድርድር ቢዘጋጅ ከሁሉም አማራጮች የተሻለው ውጤት ይመጣል ካልኩት አማራጭ ቀጥሎ ሁለተኛወ ተመራጭ ፀርዐሸ ከ መንገድ የሰላማዊ የትግል መንገድ ነው ብዬ አምናለሁ በዚህ ስልት የሚገኘው ውጤት ለምን ተመራጭ እንደሚሆን ከመዘርዘሬ በፊት ይህ ስልት ስለሚይዘው መልክና ለምን ይሰራል ብዬ እንደማምን በአጭሩ ልግለጽ በኢትዮጵያ የሰላማዊ ትግል ስልት በደንብ የሚታወቅ አይደለም የፖለቲካ ትግል ልምዳችን ሁሌም ኮጉልበት ጋር የተያያዘ ስለሆነና የገጠሙን መንግሥታት ባልታጠቁ ሰላማዊ ኃይሎች ላይ ኃይልን ለመጠቀም በፍጹም የማይራሩ ስለነበሩ መንግሥትን የሚቃወሙ ኃይሎችም በቶሎ የሚታያቸው የመንግሥትን ሽብር በሕዝብ የታጠቀ ኃይል መቋቋም ነው ከፖለቲካ ድርጅቶች ውጪ ያለው ሕዝብም ለተቃውሞ ሲዘጋጅና ሲሰለፍ የሚጠብቀው የመንግሥትን የኃይል እርምጃ ነው ምንም እንኳን ይህ በህግ የተፈቀደለት መብት መሆኑን ቢያውቅም የግንቦት የምርጫ ሂደት ይህን የተለምዶ አካሄድ ሊቀየር የሚችል መሆኑን በተለይ በምርጫው ወቅት በተደረጉት ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች አሳይቷል ከምርጫው በኋላ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተጀመረው የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ በመልሱ የመንግሥትን ዘግናኝ ዱላ ሲያገኝ በሰላማዊ ትግል ምክንያት ዙሪያ እየተቀየረ የነበረውን ሥነልቦና ተመልሶ ቀድሞ ወደነበረበት ጉልበትን የመጠበቅ ውስጥ እንዲገባ ሆኗል በዚህም ምክንያት ከዚያ በኋላ የተሞከሩ የነዓነት ገህ ሲቀደድ የሰላማዊ ትግል ሂደቶች በጣም በአጭር ጊዜ ወደ ግጭት የሚሄዱበት ሁኔታ ተፈጥሯል ከጥቅምት ቀን የተጠራውን የቅንጅቱን ሰላማዊ የትግል ጥሪ ብንመለከት በተቻለ መጠን ሕዝቡ ከመንግሥት ኃይሎች ጋር ፊት ለፊት የማይገናኝባቸውን የትግል አማራጮች በጣም በጥንቃቄ የመረጠ ነበር በኢኮኖሚ ማዕቀቦችና የግማሽ ሰዓት የጥሩንባ ማሰማት ሂደት ጀምሮ ቀስ እያለ እያደገ የቤት ውስጥ የመቆየት ትግል ላይ እንዲደርስ የተጠራው ጥሪ ወደ አጠቃላይ ግጭት የተቀየረው ገና የጥሩንባ ማሰማት ደረጃው ላይ እያለ ነው ይህ እንዴት እንደዚህ በቶሎ ሊቀየር እንደቻለ በጊዜው ስላልነበርኩ በእርግጠኛነት መናገር አልችልም የመጀመሪያውና ምናልባትም ዋነኛው ምክንያት መንግሥት ነገሩ እንዳይራዘምና ሊወስድ የፈለገውን እርምጃ ለመውሰድ እንዲያስችለው ሆን ብሎ ግጭቱን መተንኮሱ ነው ይህ ብዙው የአዲስ አበባ ሕዝብ የሚያምነውና እኔም የምጋራው ቅንጅቱም የዚህን የመንግሥት ሙከራ በ ተመልክቶ ሕዝቡ ከዚህ ጉንተላ እነዲጠነቀቅ በ ጠዋት መግለጫ ያወጣበት ጉዳይ ነው ነገር ግን ሸክሙን መንግሥት ላይ ብቻ በመጣል ልናልፈው አንችልም እንዲህ ዓይነት የመንግሥት ጉንተላ እንደሚኖር ማስጠንቀቂያ እየተሰጠም ነገሩ ወደ ግጭት መግባቱ ትግሉን በሚያካሂዱት ኃይሎች ዘንድ የትግሉን ይዘት ሙሉ ለሙሉ ያለመረዳት ችግር እንደነበረ ያመለክታል በተለይም የሰላማዊ ትግል መንገድ ተከታዮቹ በተቻለ መጠን እንዲህ ዓይነቱን የመንግሥት ትንኮሳ አስበው ትንኮሳው እንዳይሳካ ሆን ብሎ ግጭትን በሚፈልግ የመንግሥት አካል ባለበት ይህ በጣም ከባድ እንደሆነና እንደማይሳካ ይረዳኛል መጠንቀቅ እንዳለባቸው ያሳስባል የመንግሥት ኃይሎች ትንኮሳን ሲፈልጉ «በጀግንነት» መጋፈጥን ሳይሆን መሸሽ ለሰላማው ትግል የተሻለ አማራጭ ነው ይህ አለመሆኑ የሚያሳየው በህዝቡ መሀል የሰላማዊ ትግል መንገዶች ምንነት አለመታወቅ ብቻ ሳይሆን የዚህ ዓይነት ትግል የሚጠይቀው ሥነልቦናና መንፈስ ገና በደንብ አለመስረጽን ያሳያል የሰላማዊ ትግል መንገድ ተከታይ ከባላንጣው የሚበልጠው በጉልበቱ የሕዝብን ኃይል አሰባስቦም ቢሆን ሳይሆን በቸር መንፈሱ ነው ባላንጣውን የሚጥለው በአካል አ ነ የባላንጣውን የመንፈስ ደካማነትና አውሬነት በሰላማዊ ሰው ላይ ኃይልን በመጠቀሙ በማሳየት ነው ከባላንጣው በኩል ለሚመጣ ኃይል በአጸፋ ኃይል ድንጋይ መወርወርም ቢሆን ሲመልስ ይህንን የመንፈስና የሞራል የበላይነቱን ያዳክምበታል ጾር ብርሃኑ ነጋ ሌላው የሰላማዊ ትግል ስልትን ለየት የሚያደርገው የሚጠይቀው ትዕግስት ነው የችኮላ ውጤት የሚጠበቅበት የእልህ መንገድ አይደለም ቀስ በቀስ የባላንጣን የውስጥ ድክመት እያጋነነ ውጫዊ ኃይሉን የሚያሽመደምድ በባላንጣ ወገን ባለማወቅ የተሰለፉትን ግን መሰሪነት የሌለባቸውን ኃይሎች እያሸሸ የራሱን ወገን እያሰፋና እያጠናከረ የሚሄድ መንገድ ነው በመሠረቱ ለሰዎች የውስጥ ጥሩነት ትልቅ ክብር የሚሰጥ የሰውን ልጅ ከአውሬ የሚለዩት የማሰብና የማዘን ችሎታዎቹን በላቀ ቦታ የሚሰጥ አካሄድ ነው ስለዚህም ግጭት ሲተነኮስ ወዲያውኑ ለዚያ አፀፋ ለመስጠት አይቸኮልም በሌላ በሰለጠነ መንገድ እንደገና ይገጥመዋል እንጂ ከሁሉም በላይ ደግሞ የሰላማዊ መንገድ መንፈስ በፍጹም ከጥላቻ የራቀ ነው እንኳን ከመስመሩ ወጥቶ በባላንጣው ላይ አካላዊ ጉዳት ለማድረስ ቀርቶ እንዲህ ዓይነት አደጋ ሊያደርስበት የመጣውንም የሚቋቋመው በተቻለ መጠን ባላንጣው ላይ አደጋ ላለማድረስ በመጠንቀቅ ነው ራሱን እንኳን ከጥቃት ሲከላከል በተቻለው መጠን አጥቂውን እነዳይጎዳ መሞክር ይጠበቅበታል ስለዚህም አጥቂው ላይ ጥላቻ የለውም ግፋ ቢል ሀዘኔታ ዕርዜ ነው የሚኖረው ይህን ሲያደርግ ግን ለባላንጣው ብሎ ብቻ አይደለም ከሁሉም በሳይ ለራሱ ብሎ ነው ከባላንጣው በኩል ለሚመጣ ጥላቻ መልሱ ሌላ ጥላቻ ከሆነ በመንፈስ ደረጃ ባላንጣውን ሆነ ማለት ነው ባላንጣውን ከሆነ ደግሞ በትግሉ ተሸነፈ ማለት ነው የትግሉ ዓላማ ባላንጣውን አሸንፎ እንደ ባላንጣውም ለመሆን አይደለምና ከዚህ ውጪ ግን የሰላማዊ ትግል መንገድ በግድ ህጋዊ ይሆናል ማለት አይደለም እንደ ትግሉ ዒላማ ህጋዊ መንገድን ተፃርሮ ሊቆም ይችላል ኢፍትፃዊ ነው የሚባልን ህግ ህግ ሆኖ ስለተቀመጠ ብቻ መከበር አለበት ብሎ አያስተምርም የዚህ ትግል ስልት አባቶች የሚባሉ ለነፃነት የታገሉ እንደ ጋንዲና ማርቲን ሉተር ኪንግን የመሳሰሉ ሰዎች ሆን ብሎ ህግን መጣስ የትግላቸው አንድ አካል ያድርጉታል ጥቁር አሜሪካዊቷ ሮዛ ፓርክስ ከሥራ ደክማ ወደ ቤቷ ለመሄድ የተሳፈረችበት አውቶብስ ለሁለት ተከፍሎ ጥቆሮችና ነጮች የተለያዩ የመቀመጫ ቦታዎች ነበረው ይህች ሥራ ያደከማት ሴትዮ ባዶ ሆኖ ባገኘችው የነጮች መቀመጫ ቦታ ላይ ስትቀመጥ ይህ ስራሽ ሕገወጥ ነውና ተነሺ ስትባል እምቢ እንዲህ ዓይነት ዘረኛ ህግ አልቀበልም ብላ በመታሰሯ ነው የጥቁር አሜሪካ የእኩልነት ትግል የተቀጣጠለውና በመጨረሻ ያሸነፈው በደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ የጠመንጃ ትግል በማንዴላ መሪነት ከመምረጡ የነባነት ገህ ሲቀድ በፊትና ሰላማዊ ትግል ብቸኛው የትግል ስልቱ በነበረበት ጊዜ የዘረኛውን መንግሥት ሕዝብ ሆን ብሎ መጣስና በሺዎች ሆን ብሎ መታሰር አንዱና ትልቁ የትግል መሳሪያ ነበር ስለዚህ ሰላማዊ ማለት የግድ ህጋዊ አይደለም ከዚህ አንፃር ሰላማዊ መንገድ ዋነኛ ዒላማው ለመንግሥት የሕዝብን ትብብር መንፈግ ነው የሕዝብ ትብብር በፍጹም የተነፈገው መንግሥት በሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ያሉት የጦር ኃይል ቢኖረው በምንም ዓይነት በሥልጣን ማማ ላይ ለረጅም ጊዜ መቀጠል አይችልም ይህንንም በብዙ አገሮች ታሪክ ታይቷል በኢትዮጵያችንም በትክክል ከተጠቀምንበት ከመንግሥት ጋር ምንም ዓይነት የፊት ለፊት ግጭት ውስጥ ሳይገባ መንግሥትን በፍጹም ማሽመድመድ የሚቻልባቸው ብዙ መንገዶች አሉ የኢኮኖሚ ትብብር መንፈግ ከተወሰኑ ቦታዎችና ድርጅቶች ጋር የኢኮኖሚ ግንኙነት ማቋረጥ በሥራ ላይ መለገም አንዳንድ ጊዜ ሥራ አልስራም ማለት የመንግሥትን ፕሮፖጋንዳ በፍጹም አለመስማትና አፋኝ ከሆኑ የመንግሥት ተቋማት ጋር አለመተባበርና በእነዚህ ተቋማትም ለሥራ አለመቀጠር ወዘተ የመሳሰሉና በዚህ ስልት የተካኑ ጠበብት እንደሚጠቅሷቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የትግል ስልቶች አሉ በኢትዮጵያ ወደፊት እንዲቋቋም ለምንፈልገው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በመንግሥት በኩል የድርድሩ መንገድ አያስኬድም ተብሎ ከተረገጠና ያለው አማራጭ የሰላማዊ ትግል መንገድ ከሆነ የተፈለገለትን ውጤት እንዲያመጣ ግን በትግሉ የሚሳተፉ ኃይሎች የድርጅት አባላት ቀጥተኛ ደጋፊዎች ወይም አጠቃላይ ሕዝቡ የዚህን ትግል ምንነትና የሚሄድበትን መንገዶች ትግሉ የሚጠይቀውን የመንፈስ ጥንካሬ ከሁሉም በላይ ደግሞ እንዲህ ዓይነት ትግል ሲደረግ የሚጠበቀውን የመንግሥት የግጭት ጉንተላ መቋቋምን የሚያስችል ትምህርት ያስፈልጋቸዋል ከአሁን በኋላ የሚደረግ ሰላማዊ ትግል ከዚህ በፊት ከነበረው ይልቅ የተሻለ የተደራጀና በሥነሥርዓት የታነጸ ሲሆን ብቻ የማንፈልገውን የትጥቅ ትግል አስንቆ ውጤት ሲያገኝ የሚያስችል የተሻለ የትግል አቅጣጫ ሆኖ መዝለቅ ይችላል ይህም ትምህርት ተስ ሕዝቡም ለዚህ ዓይነት ትግል ዝግጁ ሆኖም ቢሆን የዚህ ዓይነት ትግል አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ አያዋጣም ወይም አይሠራም ስለዚህም የተሻለ አማራጭ የሚሆነው «ጉልበትን በጉልበት መቋቋም» ነው ብለው የሚያምኑ ኃይሎች እንዳሉ ይሰማኛል አሁን ያለው ሁኔታ በዚህ ከቀጠለ እያደር የበላይነት የሚይዝ ጾር ብርፃኑ ነጋ አስተሳሰብ ሊሆን እንደሚችልም ይገባኛል ይህንን ስለምፈራም ነው የለላማዊ ትግልን አማራጭ የተሻለ ነው ብዬ የምክራከረው ይህንን ክርክሬን ለማጠናከር ግን በውጤት ደረጃ በሰሳማዊ ትግል የሚገኝ ውጤት ከጉልበት መንገድ ለምን የተሻለ እንደሚሆን በአጭሩ ላቅርብ ኢህአዴግ በሰላማዊ ትግል ተንበርክኮ በዚህ ሽንፈቱ ምክንያተ የሚፈጠረው አዲስ ሥርዓት በአብዛኛው ኢህአዴግ ወደ ልቡናው ተመልሶ በድርድር ወደ ዴሞክራሲ ከሚደረገው ሽግግር ጋር ተመሳሳይ ውጤት አለው ምንም እንኳን በድርድር የሚገኘውን ያህል ያነሰ ባይሆንም አገሪቱን በሰው ሕይወትና በማቴሪያል ውድመት የሚያስከፍላት ዋጋ ዝቅተኛ ነው በተለይ በጦርነት ከሚመጣ ውጤት ጋር ሲነፃፀር በእንዲህ ዓይነት ሕዝባዊ ሰላማዊ ትግል በትግሉ ፃደት የሚፈጥረው የህዝብ ንጹህ የትብብር መንፈስ ከሽግግሩ በኋላ ለግንባታ ለሚያስፈልገው አብሮነት እርሾ ሆኖ የሚያገለግል ነው ድሉ የሚገኘው ሰላማዊ ትግል የሚፈልገው ከላይ የጠቀስኩት መንፈው ስር ከሰደደ በኋላ ከሆነ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እጅግ አስፈላጊ የሆነው የመቻቻል መንፈስና ከጥላቻ የራቀ ስሜት ገና ከወዲሁ ዳብሮ ስለሚቆይ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታውን በአንፃራዊነት ያቀለዋል በአጠቃላይ ግን በሰላማዊ የሕዝብ ትግል ኢህአዴግ ተሸንፎ የሚመሠረት ሥርዓት በአንፃራዊነት ከዋጋው ከፍ ማለትና ኢህአዴግ የመፍትፄው አካል ባለመሆኑ ምክንያት ከሚታጣው ሌላ በጥቅም በኩል በአብዛኛው እንደታየው ከመጀመሪያው አማራጭ ጋር የተመሳሰለ ነው በአንድ ነጥብ ላይ ከመጀመሪያውም መፍትፄ የላቀ ጥቅም እንዳለው እረዳለሁ የሰላማዊ ትግልን ከላይ በጠቀስኩት አካፄድና መንፈስ አስኪዶ ለውጤት ማብቃት ከተቻለ ሂደቱ በራሱ ለሕዝቡ የሚሰጠው የማይናቅ ኃይል አለ የሰላማዊ ትግል መሠረቱ የማኅበረሰቡን ትብብር ለመንግሥት በመንፈግ መንግሥትን ማሽመድመድ ክሆነ በዚህ ሂደት ውስጥ ኅብረተሰቡ እንዳለው የማያውቀው የነበረውን ትልቅ ኃይል እንዳለው ያውቃል ይህ የአገሪቱን የፖለቲካ ቀመር በሁለት መልኩ ይቀይረዋል በመጀመሪያ ሕዝቡ በሚገርም ደረጃ ትልቅ ሥልጣን ይሰጠዋል ይህ ሥልጣን ደግሞ በድምጽ መንግሥትን ሲመርጥ ከሚያገኘው ሥልጣን ያልተናነሰ ነው በምርጫ ጊዜ የፖለቲካ ኃይሎች መራጩን ሕዝብ ለማማለል ብዙ ጂምናስቲክ ይዉሠሩሉ አንዴ ከተመረጡ በኋላ እስከሚቀጥለው ምርጫ ድረስ ሥልጣን የሚሰጠው ትዕቢት ሊያበላሻቸው ይችላል በዚህ ሰላማዊ የትግል ስልት ልምድ ያገኘና የህዝብን ሥልጣን የነዓነት ገህ ሲቀድ ምንነት ዐዐክርጠር የተረዳ ሕዝብ በምርጫዎች መካከል ይህ የሰላማዊ ትግል መንገድ የመንግሥት ባለሥልጣኖች ከተፈቀደላቸው የሥልጣን ልክ በላይ እንዳይሄዱ መቆጣጠሪያ መሳሪያው ይሆናል ሁለተኛው ደረጃ በዚያው ልክ ለመንግሥት ሥልጣን የሚሻሙ የፖለቲካ ኃይሎች ክወዲሁ የሕዝብን ኃይልና የራሳቸውን የመንግሥትን የሥልጣን ልክ የሚረዱበት ክስተት ይሆናል ኢህአዴግን በሰሳማዊ መንገድ መጣል የቻለ የሕዝብ እንቅስቃሴ ከሥልጣን ገደቡ ለማለፍ የሞከረውን ማንኛውንም አዲስ ኃይል ቅንጅትን ሆነ ሌላ አዲስ የሚፈጠርንም ኃይል ለመጣል እንደሚችል በግልጽ ያሳያል ከዚያም አልፎ ግን የመንግሥት የጉልበት መሳሪያዎች የሆኑትን ተቋማት ከሕዝብ በታች መሆናቸውንና በግልጽ ህግ ከተሰጣቸው ሚና አልፈው ለሕዝብ መግዢያ መሳሪያ እንዳይሆኑ ያላቸውን የሥልጣን ልክ በመገደብ ሁሉም የሕዝብ አገልጋዮች መሆናቸውን ያስረግጣል ይህ ሁሉ ቀላል ውጤት አይደለም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ከተመሠረተም በኋላ በብዙ ጊዜና በብዙ ውጣ ውረድ የሚገኝ ውጤት ነው በሰላማዊ ትግል የሚገኝ ድል ግን በአጭር ጊዜና በተግባር ለሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች የማይረሳ ትምህርት የመስጠት ኃይል አለው ብዬ እገምታለሁ ይህም ጥቅም ኖሮት ግን ከሁለቱ መንገዶች የትኛው ይመረጣል ቢባል የመጀመሪያው አማራጭ እንደሆነ ለእኔ ግልጽ ነው ከላይ ስለሰላማዊ ትግል በገለጽኩበት ክፍል የዚህ ዓይነት ትግል በትግሉ ሂደትም በውጤቱም ሊያስገኝ የሚችለውን ጥቅም ዘርዝሬአለሁ በትግል ደረጃ ቅንጅቱ ከተቋቋመ ጀምሮ የሚያምንበትና የተከተለውም መስመር ይህ መሆኑን ድርጅቱ በግልጽ አስቀምጦታል አመራሩ ታስሮ ኢህአዴግ ቅንጅቱን ለማጥፋትም ያለ የሌለ አቅሙን ከተጠቀመም በቷላ ቅንጅቱና የቅንጅቱን መንፈስ ለማጥፋት አለመቻሉንም በተለያየ ቦታ ተጠቅሷል ቅንጅቱ አሁንም በጣም ብዙ አባሎችና ደጋፊዎች ያሉት ሰላማዊ ድርጅት ነው ይህ ሁሉ ግፍና በቀል ከደረሰበትም በኋላ የሚያስበው ያጠቁትን ኃይሎች እንዴት እንደሚበቀላቸው ሳይሆን እንዴት ወደ ልቦናቸው ተመልሰው አገሪቱን በጋራ ከጥፋት የምትድንበትን መንገድ ነው የቅንጅቱ አመራሮች በእስር ላይ ባለንበት ሁኔታ የተለያዩ የውጭ አገር ዲፕሎማቶች የቅንጅቱን አቋም ለማወቅም ሆነ ከዚህ አጣብቂኝ እንዴት መውጣት ይችላል ብሎ ለመማከር እሥር ቤት ድረስ መጥተው ሲያናግሩን ሁሌም በትዕዛዝ የወህኒ ቤቱ ሰዎች የቅንጅቱን አመራሮች በአንድ ላይ እንግዶችን እንዲያነጋግሩ አይፈቅዱም ከእንግዶች ጋር ጾር ብርሃኑ ነጋ ክዕኒት ት ጋ ክመ ርምምምምምምምሮፎምፎፎፎፎረፎጅውውፎው በተናጠል መነጋገር ብቻ ሳይሆን ከፍርድ ቤት ውጪ እርስ በእርስ በአንድ ላይ መገናኘትም አንችልም ከሁሉም የሚሰሙት ሁለት መሠረታዊ የቅንጅት አመራርን አቋም ነው የመጀመሪያው ከአመራሩ መታሰርና ካለንበት የእስር ሁኔታም በላይ የሚያሳስብን የአገራችን ሁኔታ እንደሆነና በጣም የሚያስፈራን የኢህአዴግ ኃላፊነት የጎደለው መንገድ አገሪቱን ወደ ጥፋት እየመራት መሆኑና ይህ በቶሎ ሩሬየሚገታበት መንገድ ካልተበጀ በቀር ጊዜው እያለፈ ሲሄድ ለሰላማዊ መፍትሄ አስቸጋሪ እየሆነ እንደሚሄድ ነው ሁለተኛው አጽንኦት የሚሰጠው አቋም ደግሞ ቅንጅቱ በምንም ጉዳይ ላይ ከኢህአዴግም ሆነ ከሌላ ማንም ኃይል ጋር ለመደራደር ዝግጁ አእንደሆነ የማይደራደርበት አንድ ጉዳይ ቢኖር በኢትዮጵያ እውተኛ ዴሞክራሲ የመፈጠሩ ጉዳይ ላይ እንደሆነ ነው ሰላማዊ ትግል አሁንም በኢትዮጵያ ይሠራል የተሻለ ውጤት ለማስገኘት ይችላል ብሎ ቅንጅቱ የሚያምነው ሌላ አማራጭም ስለሌለው ነው እንደ ድርጅት የሚያውቀው የሚያምንበትም ይህን የትግል ስልት ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሙሉ ለሙሉ አቅጣጫውን ቀይሮ ከሰላማዊ መንገድ በፍጹም የወጣ ቀን ቅንጅቱ ያለው የፖለቲካ ሚናም ቢያንስ አሁን በምናውቀው መልኩ በዚሁ ያበቃል የሰላማዊ ትግልን ትክከለኛነት ብቻ ሳይሆን አሁንም ኢትዮጵያ ላለችበት ሁኔታ ይሠራል የምንለው በእርግጥ ስለምናምንበት ብቻ አይደለም ድርጅቱ እንደ ድርጅት በፖለቲካ ሕይወቱ ለመቆየት ስለሚያስፈልገውም ነው ኢህአዴግ በድርድር በፍጹም የማይመለስ ከሆነና ከዚያም አልፎ ግን ሰላማዊ ሕዝባዊ ትግልን ፍጹም ቦታ ባለመስጠት ለማንኛውም ሰላማዊ ተቃውሞ መለሱ ጥይት ከሆነና ሕዝቡም የሰላማዊ ትግል የሚጠይቀውን ትዕግስትና መንፈስ አጥቶ በኢህአዴግም በሰላማዊ ትግልም ተስፋ ቢቆርጥ ያኔ ለዴሞክራሲ ሥርዓት የሚደረገው ትግል አቅጣጫው ይቀይራል ላለፉት ጥቂት ዓመታት በተለይም ከ ምርጫ መጀመር ጀምሮ በስልት ደረጃ የበላይነትን ይዞ የነበረው የሰላማዊ ትግል አብቅቶ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በድጋሚ በተለመደው የትጥቅ ፍልሚያ የሚፈታበት ሂደት ውስጥ ይገባል ይህ «ሊሆን ይችላል» ተብሎ የቀረበ የንድፈ ሀሳብ ትንተና አይደለም አሁንም እየሰማነው ያለነው እያደር እየበለጸገ የሚሄድ የሚመስል ሂደት ነው ይህን ጽሁፍ እየፃፍኩ እያለሁ በአንድ ሬዲዮ ጣቢያ ሁለት ተመራጭ የፓርላማ አባላት አንድ ከኦብኮ አንድ ከኦፌዴን ፓርላማውን ትተው የትጥቅ ትግል እንደ ተቀላቀሱ በቃለ መጠይቅ የነባነት ገህ ሲቀድ የሰጡትን መግለጫ እያዳመጥኩ ነበር በዚህ ቀን ሌሎች ወጣቶች ስማቸው ከነአያታቸው እየተጠቀሰ የትጥቅ ትግሉን መቀላቀላቸውን በሌላ ሬዲዮ ጣቢያ ስንሰማ ነበር ነገሮች በእስር ቤት ሲሆነ የመጋነን ስሜት አላቸው ካልተባለ በቀር በየጊዜው የምንሰማው ወሬ የአገሪቱን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚደረገው ጥረት እየሰለለ በአንፃሩ የትጥቅ ትግል ብቸኛው የመፍትፄ መንገድ ነው ብለው የሚያምኑት ኃይሎች የበለጠ እየተጠናከሩ እየፄዱ መሆናቸው ነው የወታደራዊ ኃይል ቀመሩ ምንም ሆነ ምን ኢህአዴግን በትጥቅ መታገል የተሻለው አማራጭ አይደለም ብሎ የሚያምነውና የሚከራከረው ኃይል እያደር የሞራል የበላይነቱን እያጣ እየሄደ እንደሆነ አሌ ማለት አይቻልም የሞራል ትክክለኛነት ኖረውም አልኖረው የትጥቅ ትግል ከሚያስከትለውም ጣጣ ብዛትና በሚፈለገው ውጤት ላይ ካለው አሉታዊ ተጽዕኖ አንፃር ተመራጭ መንገድ የማይሆንባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ የመጀመሪያው በትጥቅ ትግል የሚገኘው ድል በጣም ብዙ ዋጋ የተከፈለበት መሆኑ ነው ከሁሉም ተፋላሚ ወገኖች በኩል ከሚሞቱት የአንድ አገር ዜጎች በተጨማሪ ያልታሰበ ተጎጂ የሚሆነው የሲቪል ሕዝብ ብዛት በቀላሉ የሚቆጠር አይሆንም በተለይ ትግሉ ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ ከሆነ በሰው ኃይል ደረጃ ከሚሞተውና ከሚቆስለው ሕዝብ በተጨማሪ ከየቀየው የሚፈናቀለው ሕዝብ የትየለሌ ይሆናል ይህ ደግሞ በአጠቃላይ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ኑሮ ላይ የሚያመጣው መናጋት በቀላሉ የሚታይ አይደለም በእንዲህ ዓይነት ጦርነት ወቅት በቀጥታ የሚወድሙት የሕዝብ ሀብትና የመሠረተ ልማት መዋቅሮች እንደ ኢትዮጵያ ላለ ድሀ አገር ትንሽ ሊባሉ አይችሉም ጦርነት በቀጥታ ከሚያጠፋው ንብረት ባልተናነስ የጦርነት መኖር በራሱ የሚፈጥረው ሥኑልቦናዊ ሁኔታ በረጅም ጊዜ አገሪቱን የሚያስከፍለው ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዋጋ በጣም ብዙ ነው ጦርነት የሚፈጥረው አለመረጋጋት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንትን ያዳክማል ባለንብረቶች በአገሩ ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ ቢፈልጉ የሚሳተፉበት የስራ ዘርፍ በተቻለ መጠን በአጭር ጊዜ ምርቱንና ትርፉን ሊያዩ የሚችሉበት የሥራ መስክ ይሆናል ይህ ደግሞ ዘለቂታዊ እድገትን አያመጣም በደርግ ዘመን ክፉኛ ዳብሮ እስከ አሁን ልንላቀቀው ያልቻልነው በባለሀብቱ ዘንድ የሚፈጠር የአቋራጭ ትርፍ ፍለጋ እንቅስቃሴ አየር ባየር ዋናው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አካል ይሆናል በአጠቃላይ ሕዝቡም ዘንድ የሚፈጠረው ሥነልቦና ለእድገት ጾር ብርፃኑ ነጋ የሚመች አይሆንም አለመረጋጋት ሲኖር ትምህርት ቤቶች ሊዘጉ ይችላሉ የትምሀርት ሂደቱ ይቋረጣል ብዙ ወጣቶች የሚሠሩት ነገር ስለማይኖር ጦርነቱን የመቀላቀል እድላቸው በዚያው ልክ ይሰፋል ጦርነቱን የማይቀላቀሉት ደግሞ በሥራ መፍታት ምክንያት ብቻ ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታ በማዋል ፀረማኅበረሰብ የሆነ ፀባይ ያዳብራሉ ይህም ከቤተሰብ ጀምሮ በአጠቃላይ የማኅበረሰቡን ኑሮ ያውካል ወንጀልም ያስፋፋል ሁሉም ሰው ቢያንስ የሚጠብቀው በሰላም ወጥቶ መግባት እንኳ በጣም የማያስተማምን አድካሚ ሥራ ይሆናል በአጠቃላይ የእርስ በእርስ ጦርነት የሚኖረው ወይም የሚያስከትለው ጣጣ በጣም ብዙ እንደሆነ ስለሚታወቅ በመዘርዘር አንባቢውን ማድከም አያስፈልግም በትጥቅ ትግል የሚገኝን ድል የበለጠ ጥያቄ ውስጥ የሚከተው ከዚህ ሁሉ ወጪ በኋላ የሚገኘው ውጤት የተፈለገው ውጤት መሆኑን የምናረጋግጥበት መንገድ አለመኖሩ ነው መጀመሪያ ከአፈጣጠሩ የትጥቅ ትግል በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የታጠቁና ጉልበት አለን ብለው በሚያምኑ ኃይሎች መካከል የሚደረግ ፍልሚያ ነው በመሆነም አሸናፊውም ሌላ ጉልበተኛ ይሆንና ላገኘው ድል በዋናነት ተጠቃሽ የሚያደርገው የራሱን ኃይልና በሥሩ የተሰለፉት ታጋዮች ጀግንነት ነው ከዚህ ጋር አብሮ የሚመጣም ትዕቢት አለ ይህን ትዕቢት ያሸነፍኩት በጉልበቴ ብቻ ሳይሆን በአመራሬና በአመለካከቴ ትክክለኛነት ነው የሚል በጉልበት ብቻ ሳይሆን የአመሰካከት አዋቂነት የበላይነት አለኝ ከሚል ስሜት ይመነጫል ይህ ትዕቢት ሌሎችን የፖለቲካ ኃይሎች ተሸናፊውን ብቻ ሳይሆን ጠመንጃ ያልያዘውን ሁሉ በንቀት የመመልከትን አጉል ሥነልቦና በአሸናፊዎች ዘንድ ይፈጥራል ይህ ደግሞ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ለሚያስፈልግ በአኩልነት ላይ ለተመሠረተ የፖለቲካ ውይይትና ድርድር አሸናፊው መጪውን የፖለቲካ ምህዋር በድርድር ልመስርተው ብሉ እንኳን ቢወስን ማለት ነው የሚመች ሥነልቦናዊ ድባብ አይፈጥርም ለአጭር ጊዜም ቢሆን ሁኔታውን ለማረጋጋት በሚል የአገሪቱን የደህንነት ሁኔታ የሚቆጣጠረው አሸናፊው ኃይል መሆኑ በራሱ በሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች ላይ የሚፈጥረው ጫና ለንጹህ ውይይት የሚመች አይደለም በጠመንጃ ትግል የሚገኝ ድል ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት ሊሆን የሚችልበት ሌላም መንገድ አለ ቀደም ተብሎ እንደተጠቀሰው በጠመንጃ ትግል የሚገኝ ድል ብዙ መስዋዕትነት የነዛነት ገህ ሲቀድ ሕዴመመጮምምም የተከፈለበት ነው ከሁሉም ወገን ብዙ ሰው የሚሞተውና የሚቆስለውን ያህል በአሸናፊዎቹም ዘንድ ብዙ የደም ግብር ይከፈልበታል በዚህ መልክ ለአጭር ጊዜም ቢሆን በጉልበት የተገኘን ሥልጣን እንደዚሁ ዝም ብሎ «ለሕዝብ» ማስረከብ ቀላል አይሆንም ሌላው ቢቀር አዲስ በሚመሠረተው ሥርዓት ውስጥ የአመሰለካከቱን የበላይነት እንዲያገኝ በመፈለግም ሆነ ታግለው ለመጡት ሽልማት ለመስጠት አሸናፊው ኃይል ከሚመሰረተው መንግሥት ላይ የአንበሳውን ድርሻ መፈለጋቸው አይቀሬ ነው ይሆ ደግሞ የመንግሥት ተቋሞችን ክፉኛ ማናጋቱ አይቀርም የሲቪል ሰርቪሱ እንደገና የፖለቲካ አሸናፊዎች የሚቀራመቱት ሥልጣን እንጂ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንደሚፈልገው ታክስ የከፈለው ሕዝብ አገልግሎት የሚያገኝባቸው ይህን አገልግሎት ደግሞ በብቃት ለመሥራት የሚችሉና ሙያው ያላቸው ሰዎች በችሎታቸው እየተመዘኑ ቦታ የሚይዙባቸው ተቋማት አይሆኑም የተቋማቱ መዳከም ደግሞ የበለጠ ዘላቂ የኢኮኖሚና የአስተዳደር ቀውስ ያስከትላል ከዚህ በተጨማሪ እንዲህ ዓይነት የበላይነትን ለማግኘት በሚያደረገው ሙከራ ከሌሎች ተደራዳሪ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር የሚኖረው የመተማመን ስሜት ክፉኛ ይቀዘቅዛል በዚህ ምክንያት የምንጠብቀውን የተረጋጋ እና ሁሉም የተቀበለው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ያሰን እድል ሊስናክል ይችላል ሌሎቹ የፖለቲካ ኃይሎች የአሸናፊውን ኃይል አውቀውና ፈርተው አሸናፊው የሚያቀርባቸውን ተገቢ ያልሆኑ ሀሳቦች እንዲቀበሉ ቢገደዱ የሚቀበሉት ከቁጭት ጋር ስለሆን ጊዜውን ጠብቆ የሚቀሰቀስ ሴላ ችግር ከጅምሩ ይዞ ነው ይመጣል ይህ ደግሞ በምንም ዓይነት እውነተኛ ዴሞክራሲንም ሆነ ዘላቂ ሰላምን ሊያመጣ አይቻለውም እነዚህ ሁሉ ያነሳኋቸው ጥርጣሬዎች አሸናፊው ኃይል ለብቻው ሥልጣኑን መቆጣጠር አይፈልግም በተወሰነ ደረጃ ከተሸናፊው በመማር ከራሱ አስፍቶ ሌሎችንም የፖለቲካ ጋይሎች አዲስ በሚመሠረተው ሥርዓት ለማሳተፍ ይፈልጋል ከሚል ቸር አመለካከት የመነጩ ናቸው ለረጅም ጊዜ የታገልኩ ብዙ ጓዶቼ የተስዉለትበተከተልኩት መስመር ትክክለኛነትና «ዴሞክራሲያዊነት» ምክንያት የብዙኃኑን ሕዝብ ድጋፍ አግኝቼ ያሸነፍኩ መሆኔ ከግምት ገብቶ ሲታይና በተለይም ደግሞ ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች» የሚባሉት እንደ እኔ ቅንጣት ታህል ደም ሳያፈሉ እንዲያውም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከወደቀው መንግሥት ጋር ሲያብሩ የቆዩ ለምሳሌ መንግሥትን ዴሞክራሲያዊ ለማስመሰል በምርጫ ውስጥ ገብተው በመሳተፍና ፓርላማም በመግባት በመሆናቸው ጾር ብርፃኑ ነጋ በምንም ዓይነት በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ መሳተፍ የለባቸውም ብሎ ሊወስን ይችላል በዚህም የዴሞክራሲያዊ ሥርኣት ግንባታውን ሂደት ቢያንስ ሊያዘገየው ከከፋም ጭራሽኑ ላልተወሰነ ጊዜ አራዝሞ ሕዝቡን አዲስ ትግል ውስጥ ሊያስገባው ይችላል የታጠቁ የፖለቲካ ኃይሎች የግድ ካለፈው ታሪክ ይማራሉ ተምረውም የረጅም ጊዜ የአገርን ሰላምና ብልጽግና ከአጭር ጊዜ በሥልጣን ከሚገኝ ጥቅማ ጥቅም ያስቀድማሉ ብሎ መመኘት ጥሩ የሆነውን ያህል ተስፋ የለየለት የዋህነት እንዳይሆንም መጠንቀቅ ያሻል እነዚህ ከላይ ያቀረብኳቸው በትጥቅ ትግል የሚገኝ ድል አደጋዎች በትግሉ ሂደት የተፋለሙት ኃይሎች ሁለት ግልጽ ጎራ የለዩ የመንግሥትና የተቃዋሚ ኃይሎችን ብቻ ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ግልጽ ነው አሁን ባለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታና ባሉት የትጥቅ ትግል አካሂያጅ ኃይሎች ብዛትና ትግሉን የሚያካሂዱበት ዓላማ ልዩነት ምክንያት ከዚህም የከፋ አደጋ አገሪቱን ሊገጥማት እንደሚችል ማሰብ የትጥቅ ትግልን በከፍተኛ ናፍቆት ክ።