Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
እኔ ግን ብዙ ጊዜ ቁርአን ይቀሩላቸው እስልምናን ይሰብኳቸው እንደ ነበር ተናግረዋል ይህ አይነት ድምጽ ደግሞ ሰይጣን አላህን አልታዘዝ ብሎ አላህ ሲረግመው መልኩና ድምጽ ሲቀየር የተቀየረው ወደ ደወል ድምጽነት እንደነበር እራሳቸው ተናግረዋል እንዲያውም ከላይ እንዳነበባችሁት ማንኛውም በምድር ላይ ያለ የደወል ድምጽ የሰይጣን ድምጽ የመባረክ ፍሬ ሳይሆን የእርግማን ፍሬ የሆነውን መጠቀም ደግሞ ለአላህ በመገዛት ላለ መልአክ የሚመጥን አይሆንም ገብርኤል ከሆነ የራሱን ድምጽ መጠቀም ያላስፈለገውና የሰይጣንን ለመጠቀም የተገደደው ለምንድን ነው። በትክክል የተገለጠላቸው መልአኩ ገብርኤል ለመሆኑ እርግጥ ያለው ማሳመኛ ምንድን ነው። አላህስ ቢሆን ላልተማረ ሰው እንደላከው አያውቅም ነበር። የአላህ ናችሁ እንዳንል ከቁርአኑ ባለቤትና ከነቢዩ ሙሐመድ ይልቅ በኢየሱስ ክርስቶስና በተከታዮቹ ሕይወትና አገልግሎት እስካሁን ድረስ ባለ ቁራኛ ሰይጣን ናቸው ይህ እየሆነ ያለው ነቢዩና ተከታዮቻቸው የማን ባሪያዎች ቢሆኑ ነው።
የሚል ጥያቄ ማንሳትና ትክክለኛ ምላሽ ማግኘት ይኖርባቸዋል የሰው ልጆች ግልጽ ጠላት የሆነው ሰይጣን ባለበት ሐሰት አለ ለእርሱና ለተከታዮቹ ገሃነምና የዘለአለም መከራ ከአላህ ዘንድ ተቀጥሯል ስለዚህ ከዚህ የሰው ልጆች ሁሉ ጠላት ከሆነው ጋር ለዘለአለም በገሃነም ላለመኖር ሰው አመንኩ ብሎ የሚከተለው ሃይማኖት እውነተኛ የአላህ መንገድ መሆኑን በጥንቃቄ ሊመረምርና ሊያረጋግጥ ይገባዋል እላለሁ የአንድ ነቢይ እውነተኛነት ከሚለካባቸው መንገዶች መካከል ስለ አላህና ስለ ሰይጣን እንዲሁም የራሱ የነቢዩ ሕይወትና አገልግሎት ከቀደሙት እውነተኛ ነቢያት ሕይወትና አገልግሎት ጋር ሲነጻጸር የሚገኘው ምስል አንዱ ነው ለዚህ ነው ነቢዩ ሙሐመድና ቁርአን ይህንን መለኪያ ያልፉት ይሆን። ፈያ ኤን ዜኀ ይ ነው ርሬርጋ ዖቃ ቹው ኃዴኝ ሶዴ ሙፈሲር ኢብን ካሲር ለዚህ የቁርአኑ አንቀጽ ማብራሪያ ተፍሲር ሲያዘጋጁ ለሰጡት ሃሳብ ማጠናከሪያ የሚከተለውን ሀዲስ አያይዘው አቅርበው እናገኛለን ተፍሲር ኢብን ካሲር ሱረቱል አልሒጅር ሳኢድ ቢን ጁቤይር ሲናገር አላህ ኢብሊስን ሰይጣንን በረገመው ጊዜ መልኩ ከመላዕክት ወደተለየ መልክ ተቀየረ ድምጹም እንደ ደወል ድምጽ ሆነ በዚህም ምድር ላይ እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ የሚሰማ ማንኛውም የደወል ድምጽ የዛው የሰይጣን ድምጽ አካል ነው ኢብን አቢ ሃቲም ያስተላለፈው ሃዲስ ነው ከዚህ በመነሳት ሐዲሳቱን ስንመረምር ደወልና ሰይጣን ያላቸው ግንኙነት ምን እንደሚመስል ከነቢዩ ሙሃመድ አንደበት ሰምተው ሱሃባዎቹ ያስተላለፉትን ደጋግመው ዘግበው እናገኛለን ከዛ እስቲ አንድ ሁለት ላስነብባችሁ ሳሂህ ሙስሊም የአላህ መልእክተኛ ሲናገሩ እንዲህአሉ ደወል የሰይጣን የሙዚቃ መሳሪያ ነው አቡ ሁሬይራ የዘገቡት ሃዲስ ነው ሳሂህ ሙስሊም የአላህ መልእክተኛ ሲናገሩ መልአክ ደወልና ውሻ ይዘው ከሚጓዙ ጋር አብሮ አይሄድም አቡ ሁሬይራ የተናገሩት ሃዲስ ሱና አቡ ዳውድ ኢብን አዝዙቤይር ሴት አገልጋዩን ሴት ልጁን ይዛ ወደ ኡመር እንድትሄድ ነገራት ልጅቷን እግሯ ላይ ደወል ያለበት አልቦ እንዳደረገች ወሰደቻት ኡመርም የአላህ መልእክተኛ ከእያንዳንዱ ደወል ጋር ሰይጣን አለ ሲሉ ሰምቻለሁ አለና አልቦውን ቆራርጦ ጣለው ኡመር ኢብን ኸታብ የተናገሩ ሃዲስ ነው ሰይጣን አላህ ለአደም ስገድ ሲለው ባለመታዘዙ ተረግሞ ከገነት በተባረረ ጊዜ በሰው ልጆች ሁሉ ላይ ፍጹም ጥላቻ ተሞልቶ የመጀመሪያው በእነርሱ ላይ በጠላትነት የተነሳ አካል እንደ ሆነ ቁርአንና የነቢዩ ሐዲሳት በአንድነት ይገልጻሉ አላህም እንዲህ በማለት የሰው ልጆችን በቁርአኑ አስጠንቅቋል ሱረቱል አልኢስራእ ንገረኝ ይህ ያ በኔላይ ያበለጥከው ነውን እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ብታቆየኝ ዘሮቹን ጥቂቶች ሲቀሩ ወደ ስህተት በእርግጥ እስባቸዋለሁ ጊዕ ጄኔ ዴጮኝ ሶ ኃቻ። ሂ ሰይጣን እና ተቀዳሚ አላማው ከላይ እንዳነበባችሁት ሰይጣን አላህ ለአደም ስገድ ሲለው አሻፈረኝ በማለቱ ትእዛዙ ትክክል ነው አይደለም እንዲህ አይነት ትእዛዝ አላህ ያዛል ወይንስ አያዝም የሚለውን ብርቱ ጥያቄ ሳናነሳ ማለቴ ነው ምህረት በሌለው እርግማን ለዘለአለም ተረግሞ ከገነት ተባሯል ሰይጣን ይህንን የመሰለ የፍርድ ውሳኔ በተላለፈበት ወቅት አላህን የለመነው የሰውን ልጆች እርሱን ከመከተል ለመመለስና ወደ ጀሃነመ እሳት ለመውሰድ ስለሚፈልግ ጊዜ እንዲሰጠው ብቻ ነበር እንጅ ጥፋተኛነቱን አምኖ ተውበት በማድረግ በሃጢያቱ ተጸጽቶ እርሱና ዘሮቹ ከገሃነመ እሳት የሚተርፉበትን መንገድ እንዲመራቸው አልነበረም ነገር ግን አንድ ነገር ብቻ እለምንሃለሁ አለ ገሃነምን በሰው ልጆች እስክሞላ ድረስ ጊዜ እንድትሰጠኝ ሰይጣን ለአላህ ያቀረበውን የልመናውን ቃል እስኪ ከቁርአኑ ውስጥ እንመልከት ሱረቱል አልሂጅር ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ ርግማን አለብህ ጌታዬ ሆይ እንግዲያውስ ሰዎች እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ አለ አላህም አለ አንተ ከሚቆዩት ነህ እስከ ታወቀው ወቅት ቀን ድረስ ኢብሊስም አለ ጌታየ ሆይ እኔን በማጥመምህ ይሁንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ ሯጢያትን እሸልምላቸዋለሁ መላቸውንም አጠማቸውም አለሁ ከሽ ጀን ተ ምጋ የገጢቢ ። ሠ ሬኔ ህ አላህ ሰይጣን ላቀረበውን ልመና ተቀብሎ ምላሽ በሰጠበት ወቅት ለሰይጣንና ለሰው ልጆች የሚከተለውን ጨምሮ ተናግሮ ቁርአን ውስጥ አንመለከታለን ሱረቱል ፋጢር ሰይጣን ለናንተ ጠላት ነው ስለዚህ ጠላት አድርጋችሁ ያዙት ተከታዮቹን የሚጠራው ከእሳት ጓዶች እንዲሆኑ ብቻ ነው ። ለሰይጣን ብቻ ሳይሆን ለነቢዩም የሚከተለውን ብሏቸዋል ሱረቱል አልነህል ቁርአንን ባነበብህ ጊዜ ርጉም ከሆነው ሰይጣን በአላህ ተጠበቅ እርሱ በነዚያ ባመኑትና በጌታቸው ላይ በተጠጉት ላይ ለርሱ ስልጣን የለውምና ስልጣኑ በነዚያ በሚታዘዙት ላይና በነዚያም እነርሱ በርሱ ምክንያት አጋሪዎች በሆኑት ላይ ብቻ ነው ዕቃ መቿ ጋ ህ አህ ህ ይሥ ሥ ጩህ ዶክተር ሳኢድ እስማኢል የተባሉ ኢስላማዊ ምሁር ፋት አልቀድዋ ወአልቀድር በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ አላህ የሰው ልጆችን እንዲሁም ሰይጣንንና ዘሮቹን ለምን እንደፈጠራቸውና በምድር ላይ የሚኖራቸውን ኃላፊነት ወይም ተጠያቂነት ሲጠቅሱ የሚከተለውን ነበር ያሉት የአዳምና ዘሮቹ ተቀዳሚ ተጠያቂነታቸው በምድር ላይ በጎ የሆነውን ነገር እንዲያስፋፉ ሲሆን ሰይጣንና ዘሮቹ ጂኖች ደግሞ ክፉ የሆነውን ነገር እንዲያስፋፉ ነው ይሁን እንጅ የአላህ ውሳኔ ለሁለቱም እኩል የሆነን የመምረጥን እድል ሰጥቷቸዋል የሰው ልጆች ከተፈጠሩበት አላማ ተመልሰው ወደ ጥመት መሄድን መምረጥ ይችላሉ ሰይጣንና ጂኖቹም እንዲሁ ተመልሰው በአላህ መመራትን መምረጥ ይችላሉ ልፐ ልሁ ጩልሀል ነሃሄልሁ ጩልሀልክ ሃ ኗልፎዬሀ እልርር ምንም የዶክተሩ አሳብ ከቁርአን ጋር እየተጣረሰ ቁርአንም እርስ በእርሱ እንዲጣረስ የሚያደርግ ነገር ቢታይበትም እርሱን ለጊዜው አቆይተነው በሁለቱ ወገኖች ላይ አላህ በሰጠው ኃላፊነት ላይ ትኩረታችንን እናድርግ አላህ እነዚህን ወገኖች ሲፈጥራቸው ከሰይጣንና ከዘሮቹ የሚጠብቀውና ተጠያቂ ያደረጋቸው ለክፋት ሲሆን ሰዎችን ደግሞ መልካሙን እንዲያደርጉ መሆኑ ከዶክተሩ ብቻ ሳይሆን ከላይ ከተጠቀሱት የቁርአኑ አያቶች ላይ ለመመልከት ችለናል እነዚህ ፍጥረታት ለፈጣሪያቸው ለአላህ መገዛታቸውን የሚያረጋግጡት ይህንን የሚጠበቅባቸውን ፈጽመው ከተገኙ ብቻ መሆኑ ግልጽ ነው ሰይጣን ክፋትን በማንገስ መገዛቱን ሲያሳይ የሰው ልጅ ደግሞ መልካም የሆነውን ብቻ በማድረግ መገዛቱን ያሳያል ማለት ነው ሁለቱም ወገኖች የተወሰነባቸውን ለመወጣት ሲንቀሳቀሱ በተለይ ሰይጣን የሰው ልጆችን በማጥመም ወደ ገሃነም እንዳይወስዳቸው አላህ በተለያየ ጊዜ የእርሱን መንገድ እንዲጠብቁ የሚመክሩና የሚያስጠነቅቁ ነቢያትን በየዘመናቱ ይልክ ነበር በመጨረሻ ነቢዩ ሙሃመድ ከአላህ በነቢይነት ቁርአኑ ተሰጥቷቸው እንደተላኩ በዛን ዘመን ለነበረው ህዝብ አበሰሩ ዛሬም ይኸው ብስራት ለተለያዩ ወገኖችና ዘሮች እየተበሰረ ይገኛል ሆኖም ማንኛውም ነቢይ ለነቢይነቱ ማስረጃ ቷ እንደሚያቀርበው ሁሉ የእርሳቸውን ነቢይነት ለማስረገጥ የሚሰጡት ማስረጃዎች ግን የነቢይነት ተልዕኳቸው ከአላህ ዘንድ ነው ብሎ አምኖ ለመቀበል እጅግ አስቸጋሪ እንዲሆን አድርገዋል እንግዲህ ገነት መግባት ስለምፈልግ ከሚሰጡት የነቢይነታቸው ማስረጃዎች የተነሳ ተልእኳቸውን በተመለከተ ውስጤ የተነሱትን ጥያቄዎች ለመመለስ ቁርአኑንና ሐዲሳቱን እንዲሁም በህይወት ታሪካቸው ዙሪያ የተጻፉትን የታሪክ መጽሐፍት ሳገላብጥ ከእነዚህ የእስልምና እውቅ መጽሐፍት ውስጥ ያገኘሁት መልስ ግን እንደተባለው ሳይሆን ነቢዩ ሙሃመድም ሆኑ ቁርአን የአላህ መልዕክትና መልእክተኛ አይደሉም የሜል ሆኗል እናንተም ይህንን ታረጋግጡ ዘንድ ተሳስቼም ከሆነ በአድራሻዬ እርማታችሁን ታደርሱኝ ዘንድ ትክክልም ከሆንኩ መንገዳችሁን ለትመርመር እንዲረዷችሁ የነቢዩን የተልእኮ አጀማመር ለማን እንደተላኩና መልእክቱ በምን ሁኔታ ይደርሳቸው እንደነበር የሚያትቱትን ሐዲሳትና የቁርአኑን አያቶች ላስነብባችሁ ከዛም በመቀጠል የነፍሴን ጥያቄዎች አቀርባለሁ ነቢዩ ሙሐመድ ስለ ተልዕኳቸው አጀማመር ሲናገሩ የነቢዩ ሙሐመድ ተልዕኮ የተጀመረው ማንኛውም የቁሬይሽ ጎሳ አባላት ያደርጉት እንደነበረው ለማድረግ በሂራ ዋሻ ውስጥ ለተመስጦ ለአንድ ወር በተቀመጡበት ወቅት እንደ ነበር ይነገራል በወርሃ ረመዳን በወሩ የመጨረሻ ቀናት ላይ ድንገት በሌሊት አንድ ማንነቱንና ምንነቱን የማያውቁት አካል መጥቶ ሱረቱል አልአለቅ ያለውን አያት እንዲቀሩ እንዳስገደዳቸውና አልተማርኩም እንኳን ሲሉት ከምንም ሳይቆጥር ፊደል ያልቆጠረን ሰው እንዴት ያደርጋቸው እንደ ነበር ሜስታቸው አኢሻ በሐዲሳቸው ተናግራለች እስኪ ሐዲሱን ላስነብባችሁ ተፍሲር ኢብኑ ካሲር ሱረቱል አልአለቅ በዋሻው ሳሉ መልአኩ ውደ እርሳቸው መጣና አንብብ አላቸው የአላህ መልእክተኛ ሲናገሩ እኔም ማንበብ አልችልም ስል መለስኩለት አለሉ ከዛም መልአኩ ጨመቀኝና የምሞት እስኪመስለኝ ድረስ እረገጠኝ ከዛም ለቀቀኝና አንብብ አለኝ እኔም መልሼ ማንበብ አልችልም አልኩት እርሱም ለሁለተኛ ጊዜ ጨመቀኝ እኔም የምሞት እስኪመስለኝ ድረስ እረገጠኝ ከዛም እንደገና ለቀቀኝና አንብብ አለኝ እኔም ማንበብ አልችልም አልኩት አሁንም ለሶስተኛ ጊዜ እየጨመቀ እረገጠኝ ከዛም ለቀቀኝና አለኝ ሱረቱል አልአለቅ አንብብ በዚያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ ጌታህ በጣም ቸር ሲሆን ያ በብዕር ያስተማረ ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲሆን እነዚህን አንቀጾች ይዘው ልባቸው እየተንቀጠቀጠ ወደ ቤት ወደ ኸድጃ መጡና ሸፍኑኝ ሸፍኑኝ አሉ እነርሱም ፍርሃቱ እስከሚለቃቸው ድረስ ሸፈኗቸው ከዛም በኋላ የተፈጠረውን ሁሉ ለኸድጃ ነገሯት እንዲህም አሏት ፈርቻለሁ የሆነ ነገር ሳልሆን አልቀረሁም ኸድጃም ከዋራቃ ኢብን ናኡፋል ጋር አገናኘቻቸው እርሱም እስልምና ገና ሳይመጣ ክርስትናን የተቀበለና አላህ እንዲጽፍ የፈቀደለትን ያክል ወንጌልን ከሂብሩ ወደ አረብኛ ተርጉሞ መጽሃፍ የጻፈ ሰው ነው ዋራቃ በጊዜው ሽምግሎና የአይን ብርሃኑን አጥቶ ነበር ኸድጃም ዋራቃን አጎቴ የወንድምህን ልጅ ታሪኩን አድምጠው አላቸው ዋራቃም የወንድሜ ልጅ ሆይ ያየኸው ምንድን ነው። ሲል ጠየቃቸው የአላህ መልእክተኛም ያዩትን ሁሉ ገለጹለት ዋራቃም እርሱማ አላህ ወደ ሙሴ ልኮት የነበረው አንናሙስ ገብርኤል ነው አላቸው ነቢዩ ሙሐመድ ለማን እንደተላኩ ነቢዩ ሙሃመድ ነቢይ ሆነው ከአላህ እንደተላኩ ሲያበስሩ የመልዕክቱ ተደራሾች እነማን ናቸው ሲባል አላህ በቁርአኑ አንቀጾች ለዓለማት እንደሆነ ተናግሯል ዓለማት የሜለው ቃል አላህ ለምን የመጀመሪያ አሳቡን እንደለወጠ ባይታወቅም ሰዎችንና ሰይጣናትን እንደሚያጠቃልል የቁርአኑ ሙፈሲሮች ይናገራሉ በሱረቱል አልጂን ላይም እነዚሁ ሰይጣናት ተልዕኳቸውንና ከአላህ የተቀበሉትን ኃላፊነት በሚቃረን ሁኔታ እኛም እስልምና እውነተኛ ስለሆነ ተቀበልን ሲሉም አንብበናል ይሁንና ቀጥዬ ስለ ነቢዩ ሙሐመድ ተልዕኮ የሚናገሩትን የቁርአኑን አንቀጸጾች እንዲሁም የኢብን አባስና የኢብን ካሲር ተፍሲሮች ስለዚሁ ምን እንደሚሉ ላስነብባችሁ ሱረቱል ዩሱፍ በርሱ በቁርአን ላይ ምንም ዋጋ አትጠይቃቸውም እርሱ የዓለማት ግሳጹ እንጅ ሌላ አይደለም ሥ። እርሳቸው ሲመልሱም መልአኩ አንዳንድ ጊዜ የደወል ድምጽ በሚመስል ድምጽ እየተናገረ ይመጣል ይህ አይነቱ የራዕዩ አወራረድ ለእኔ በጣም ልቋቋመው የማልችለው ከባዱ አይነት ነው ትቶኝ ከሄደ በኋላ መልአኩ የነገረኝን አስታውሰዋለሁ አንዳንዴ መልአኩ ሰው በመምሰል ወደ እኔ ይመጣና ያናግረኛል እኔም ምን እንዳለኝ እረዳለሁ አስታውሰዋለሁም አኢሻ አክላም እርሱ በእርሳቸው ላይ በወረደ ጊዜ ከባድ ብርድ እንደሚያንቀጠቅጠው ሰው ይንቀጠቀጣሉ ትቷቸው ሲሄድ ደግሞ ግንባራቸው ላብ በላብ ይሆናል አኢሻ የዘገበችው ሐዲስ ነው ነቢዩ ሙሐመድ ስለራሳቸውና ስለተከታዮቻቸው ሲናጉገሩ ጊዜው ሱረቱል አልፈለቅና ሱረቱል አልናስ የወረዱበት ሰአት ነበር ከእነዚህ ሁለት ሱራዎች በፊት መካ ላይ ሱራዎች ከወረዱ በኋላ በኛ እና ኛ ደረጃ ላይ የወረዱ ሱራዎች ናቸው የሩቅያህ ወይንም የመተት ሱራዎች ተብለው በሌላ ስምም ይጠራሉ ይህንን ስያሚ ለምን አገኙ የሜል ጥያቄ ያነሱ ይሆናል ነገሩ እንዲህ ነው በዛን ወቅት ላቢድ ቢን አሳም የሚባል አይሁዳዊ በነቢዩ ሙሐመድ የራሳቸው ጸጉርና በማበጠሪያቸው ላይ አስማት ያደርግምባቸውና ለአንድ አመት ያክል በጸና ይታመማሉ ህመም ከተባለ ማለቴ ነው ያኔ በዚሁ በተደረገባቸው አስማት ምክንያት ከሚስቶቻቸው ጋር ወሲብ የሚፈጽሙ እየመሰላቸው ከማያውቁት አካል ጋር ወሲብ ሲያስፈጽማቸው ይታይ ነበር ይህንን ዝም ብዬ የምናገር እንዳይመስላችሁ ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ላይ በተጨማሪ አስባቡ አል ኑዙል ሱራ እና ላይ መመልከት ትችላላችሁ ከሐዲሱ ቀንጭቤ ላስነብባችሁ ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ አይሻ ስትናገር የአላህ መልእክተኛ ላይ ድግምቱ ሰርቶባቸው ከሚስቶቻቸው ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲፈጽሙ እንደሚያደርጉት እንዲሁ ብቻቸውን ያደርጉ ጀመር እርሳቸው ከሚስታቸው ጋር እየፈጸሙ ይመስላቸዋል ግን አልነበረም ሌላዋ ሚስታቸው ሶፍያም እንዲህ አይነት ተግባር የሚያስተጽመው በጣም አደገኛው የድግምት አይነት ነው አለች ቷ ከዚህ ድግምት ገብርኤል ሩቅያህ መተት አድርጎላቸው ተፈወስኩ ባሉበት ወቅት በዙሪያቸው ለተሰበሰቡት ሱሃባዎች አንድ ነገር አሏቸው እናንተ ሁላችሁ ሰይጣን አለባችሁ ምን ይህ ብቻ እናንተው ከሐዲሱ አንብቡ እነሆ ሳሂህ ሙስሊም የአላህ መልእክተኛ ሲናገሩ እንዲህ አሉ ከእናንተ መካከል ሰይጣን ያልተመደበበት የለም ሱሃባዎቹም የአላህ መልእክተኛ ሆይ በእርሰዎም ላይ ሰይጣን ተመድቦበዎታልን። ስንል ጠየቅናቸው እርሳቸውም አዎን በእኔም ውስጥ ይሯሯጣል ነገር ግን አላህ በእርሱ ላይ እረዳኝና ተገዛልኝ አሉ ጃብር የተናገረው ሐዲስ ነው ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ የአላህ መልእክተኛ ከእናንተ የትኛውም ሰው ከመኝታው ሲነሳ ውዶ ያድርግ አፍንጫው ውስጥ ውሃ እያስገባ እያስወጣ ሶስቴ በመደጋገም ይጠበው ምክንያቱም ሰይጣን በአፍንጫው የላይኛው ክፍል ሌሊቱን ሙሉ አድሮ ሊሆን ይችላልና አሉ አቡ ሁሬይራ የዘገቡት ሐዲስ ነው አንዴ ነቢዩ ሙሐመድ መዲና ሲኖሩ ሳለ ደግሞ ጅኖች የአካባቢው ሙስሊሞች በሚፈጽሙባቸው ተግባር አዝነው ለነቢዩ ስሞታ አሰሙ ነቢዩም ጅኖቹ የነገሯቸውን ሰምተው ለሱሃባዎች ትእዛዝ አስተላልፈው ነበር በዛን ጊዜ ያስተላለፉት ትዕዛዝ እንዲህ የሚል ነበር ሱና ጃማኢ አትትርሚዝ ቅጽ ቁጥር የወንድሞቻችሁ የጅኖች ምግብ ነውና በአጥንትና በከብት ፋንድያ እስቲንጃ አታድርጉ አብደላ ኢብን መሱድ የተናገረው ሐዲስ ነው ሱና አቡ ዳውድ የጅን ባለስልጣናት ወይንም ወኪሎች ወደ ነቢዩ ሙሐመድ መጡና እንዲህ አሉ ሙሐመድ ሆይ ተከታዮችህን በአጥንት በኩበት ወይንም በከሰል እራቸውን ማጽዳታቸውን ሽሸንት ቤት ከተጠቀሙ በኋላ ማለት ነው ልትከለክላቸው ይገባል እነዚህ አላህ የወሰነልን ነገሮች ናቸው ሰለዚህ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ እንዳይደረግ ተከታዮቻቸውን ከለከሉ አብደላ ኢብን መሱድ የዘገበው ሐዲስ ነው በዚህ ብቻ ያበቃ መስሏችሁ ይሆን አላበቃም ነቢዩ ሙሃመድ በእነዚህ ሰይጣናት እየተጋበዙ ከእነርሱ ጋር ወደ መኖሪያቸው እየሄዱ ብዙ ጊዜ ቁርአን ይቀሩላቸው እስልምናን ይሰብኳቸው እንደ ነበር ሱሃባዎቻቸው ዘግበዋል ሳሂህ ሙስሊም አንድ ምሽት ከአላህ መልዕክተኛ ተከታዮች ጋር አብረን ነበርን እርሳቸው ግን ጠፉብን በሸለቆው በተራራው ሁሉ ፈለግናቸው ልናገኛቸው ግን አልቻልንም እንዲህም አልን ወይ በጅኖች ተወስደዋል ወይንም በሚስጢር ተገድለዋል አልን ሁላችንም በብዙ ድካም መጥፎ የሆነ ምሽት አሳለፍን ሲነጋጋ ሂን በሚባለው አካባቢ አቅጣጫ ሲመጡ አየናቸው እኛም የአላህ መልዕክተኛ ሆይ። ጠፍተውብን ስንፈልግ እጅግ ደክሞን በጣም መጥፎ የሆነ ምሽት አሳለፍን አልናቸው እርሳቸውም ከጅን ወገን የሆነና በእነርሱ የተወከለ ጅን ወደ እኔ መጣ እኔም ከእርሱ ጋር ሄድኩኝ በዛም ቁርአን ቀራሁላቸው አሉ እኛንም ይዘውን ሄዱና የእግራቸውን ኮቴና እሳት አንድደውበት የነበረውን ቦታ አሳዩን አብደላ ኢብኑ መሱድ የተናገረው ሐዲስ ነው ሱና አትትርሚዝ ቁጥር የአላህ መልዕክተኛ ወደ ተከታዮቻቸው መጡና ሱረቱል አልረህማንን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አነበቡት ከዛም ይህንን ሱራ በጅኖች ምሽት በጅኖች ፊት አንብቤው ነበር እነርሱ የሰጡት ምላሽ እናንተ ከሰጣችሁት ምላሽ በእጅጉ የተሻለ ነበር አሉ እንግዲህ ነገሩ እንዲህ ከሆነ ለእናንተ ለአንባቢዎቼ የማነሳቸው የነፍሴ ጥያቄዎች የሚከተሉት ናቸው ሁ የመጀመሪያው ጥያቄ በተገለጠላቸው አካል ማንነት ላይ ያተኩራል ራዕዩን ያመጣላቸውን አካል ማንነት ነቢዩ መጀመሪያ ማን እንደሆነ እንደማያውቁ በኋላ ግን ገብርኤል የተባለው መልአክ እንደሆነ በሰፊው ተነግሯል እንግዲህ እንደተባለው ገብርኤል ከሆነ ውድ ወገኖቼ እንደተባለው ወደ ነቢዩ ሙሐመድ የመጣው መልአኩ ገብርኤል ከሆነ ድምጹ ለምን እንደ ሰይጣን ድምጽ ሆኖ ተቀየረ። ለማነጻጸር ትችሉ ዘንድ ሐዲሱን ላስነብባችሁ ይገባልና እነሆ ሳሂህ ሙስሊም አቡ ሁሬይራ ከአላህ መልዕክተኛ ሰምቶ ያስተላለፈው ሐዲስ ነው የትንሳኤ ቀን እየተቃረበ ሲሄድ የአማኞች ራዕይ ሃሰተኛ ሊሆን ይችላል እውነተኛ ራዕይ የሚያይ በንግግሩ እውነተኛ የሆነ ሰው ብቻ ነው የሙስሊም ራዕይ አርባ አምስት እጁ ትንቢታዊ ነው ሶስት አይነት ራዕዮች አሉ አንዱ ምልካም ራዕይ ከአላህ የሆነ ነው ሁለተኛው አስጨናቂ የሆነ ክፉ ራዕይ ከሰይጣን የሆነና ሶስተኛው ከራሱ ከሰው አሳብ የሚወጣ ነው ሌላው አጠያያቂ ጉዳይ የአላህ ቃልና ትዕዛዙ መጣሳቸው ነው አላህ ሰይጣንን ከገነት ሲያባርረው እንዳይዳፈር የተከለከላቸውና እራሱም አምኖ የተቀበላቸው ትዕዛዛት እንደነበሩ ከላይ ማንበባችሁን ታስታውሳላችሁ ደግሞም መከልከል ብቻ ሳይሆን የተፈቀደለት ክልልም መኖሩን አንዘነጋም ይህ ሆኖ እያለ በነቢዩ ሙሃመድ የአላህ ነቢይነት ላይ ጥያቄ የሚሆነው አላህ ሰይጣንን እረግሞት ከገነት ሲያባርረው በባሮቹ ላይ ስልጣን እንደሌለውና እንዳይነካቸው ነግሮት እርሱም ላይነካ ምሉ መውጣቱን ቁርአን ነግሮናል ሆኖም ግን ነቢዩ ሙሐመድ በልባቸው ስይጣን እንዳለባቸውና ሰልሞላቸው መልካም እንዲያደርጉ እንደሚያዛቸው እንደተናገሩ አንብበናል እንዲህ ከሆነ ነቢዩ ሙሐመድ የማን ባሪያ ቢሆኑ ነው ሰይጣን መንካት አይደለም በልባቸው ቁጭ ብሎ ይህንን አድርግ ያንን አታድርግ የሚላቸው። ነኒይዩ ሙሐመድ ከአላህ ተቀበልኩ ብለው ያመጡት ቃል በራሳቸውና በተከታዮቻቸው ሕይወት ውስጥ ተግባራዊ ሆኖ የማይታይና የሰው ልጆች ሁሉ ጠላት ከሆነው ከሰይጣን እስራት ነጻ የማያወጣ ከሆነ ቁርአን ከአላህ የተላከ መልአኩ ገብርኤልም ያመጣው የአላህ ቃል ነው ብሎ ማመን ይቻላል አላህ በሱረቱል አልአንአም ላይ ነቢዩ ሙሐመድ የቀደሙትን ነቢያት ፈለግ እንዲከተሉ ቁርጥ ያለ ትዕዛዝ ደርሷቸዋል ሆኖም የታየው ተቃራኒው እንጅ የዚህ ትዕዛዝ ፍጻሜ አይደለም ነቢዩ ሙሐመድ የአላህ መልዕክተኛ ከሆኑና ቁርአን የአላህ ቃል ከሆነ ሁለቱ ለምን በተግባር ተለያዩ።