Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
በአዲስ አበባ ከተማና ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ የሚገኝ ማንኛውም የመኖሪያ ቤት የኪራይ ውሎች ናሙና ከዚህ መመሪያ ጋር አባሪ ሆኖ እንዲያያዝ ይደረጋል ። ተከራይ ውል ገብቶ በተከራየው ቤት የተወሰነውን ወርሃዊ ክፍያ ወር በገባ በአስር ቀናት ውስጥ በወረዳ አነስተኛ ግብር ከፋዩች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጥያቄውን አቅርቦ ማስፈቀድ ይኖርበታል በዚህ አንቀጽ ከተገለጸው ውጭ ማብሰያና የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ገንብቶ ከተገኘ በራሱ ወጪ እንዲያፈርስ ይደረጋል ።
ደባል ማለት ተከራይ ቤቱን መጀመሪያ ከመንግስት ሲከራይ በደባልነት የተመዘገበና በወቅቱም በቤቱ ውስጥ እየኖረ ያለ ወይም የቤት ችግራቸውን ከማቃለል አንፃር በወረዳ አስተዳደር ትዕዛዝ በደባልነት ውሳኔ አግኝተው እስካሁን በቤቱ ውስጥ በመኖር ላይ ያሉ እና የቤት ኪራይ ዉሉ በደባሎቹ ስም የሆነ ማለት ነው የኪራይ ተመን ማለት የከተማው አስተዳደር ለሚያከራየው መኖሪያና ንግድ ቤቶች በሚያውጣው የኪራይ ተመን መሠረት በየወሩ ሊከፈል የሚገባ የገንዘብ መጠን ነው ሷው ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው ተደራሽ ቤት ማለት ከንግድ ቤት ውጭ ያሉ በህንፃው የምድር ቤት ወይም በአንፃራዊነት ከሌሎች ወለሎች ከመሬት አነስተኛ ከፍታ ላይ የሚገኝ ወለል ያለው ሆኖ ለመኖሪያ የሚያገለግል እንዲሁም ለአካል ጉዳተኛዉ በአንጻራዊነት ካሉት ቤቶች መካከል የመግቢያና እና የመውጫ መንገዶቹ ምቹ የሆነ ቤት ማለት ነው አካል ጉዳተኛ ማለት በተፈጥሮ ወይም ሰው ሰራሽ በሆነ አደጋ ምክንያት በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የአካል የአእምሮ ወይም የስሜት ሕዋሳት ጉዳት ምክንያት ማከናወን የሚገባውን መደበኛ ተግባር ማከናወን ሳይችል ቀርቶ በሌላ አካል ወይም ድጋፍ ሰጪ መሳሪያ የሚጠቀም ግለሰብ ነው ጌተሰብ ማለት ባል ሚስት ልጆች እንዲሁም በህጋዊ ጉዲፈቻ ያደጉ ልጆችን ይጨምራል ተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋዎች የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ማለት ከቤታቸው በጐርፍ በእሳት በመሬት መንቀጥቀጥና በሌሎች አደጋዎች ቤት አልባ የሆኑ የከተማው ነዋሪዎች ናቸው ዋቤት ኪራይ ዉል ማለት በአከራይ የመንግስት አካልና በተከራዩ ሰው መካከል ለተወሰነ ጊዜ ወይንም ውሉ ለጸናበት ዘመን ብቻ የሚያገለግል ሰነድ ነው ግግድ ቤት ማለት ለንግድ አገልግሎት እየዋለ ያለ እና የጸና የንግድ ቤት የኪራይ ውል ያለው ቤት ነዉ ዋጨረታ መነሻ ዋጋ ማለት በቢሮው የተመን ቀመር መሰረት ቤቱ በጨረታ ወይም በጨረታ መነሻ እንዲከራይ ሲወሰን የሚኖረው የመነሻ ወይንም የወለል ዋጋ ነዉ መንግስት ቤቶች ይዞታ ማለት በይዞታ አስተዳደር የሽግግር ጊዜ መስተንግዶ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት መመሪያ መሰረት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የወጣላቸው እና ለወደፊት የሚወጣላቸው የመንግስት ቤቶች የሚደርሳቸው የቦታ ስፋት ነው ዋመንግስት ሥራ ኃላፊዎች ማለት በከተማ አስተዳደሩ ተሹመው የመንግስት ቤት እንዲሠጣቸው የተፈቀደላቸው የሥራ ኃላፊዎች ናቸው ጅ የጾታ አገላለጽ በዚህ መመሪያ ውስጥ በወንድ ፆታ የተገለፀው የሴትንም ፆታ ያካትታል የተፈጻሚነት ወሰን በአዋጁ የተወረሱና የከተማው አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው ቤቶች የከተማው አስተዳደር የሰራቸውና የሚያስተዳድራቸው ቤቶች ወይም በህጋዊ መንገድ የተያዙ ሌሎች ቤቶች እና እነዚህ የሚገኙበት ይዞታ ላይ ተፈጻሚ ይሆናል መርሆዎች ግልፅነት ተጠያቂነት ፍትሐዊ እና ደረጃውን የጠበቀ የቤት አስተዳደር ስርዓት መፍጠር የቤት አስተዳደር ስርዓቱ የከተማውን የልማት እና የመልካም አስተዳደር እንቅስቃሴ በሚደግፍ መልኩ መምራት የቤት አስተዳደሩ በዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት የተደራጀ እና ለህብረተሰቡ ተስማሚነት እንዲኖረው ማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍል ከቤት አስተዳደር ሥርዓቱ ይበልጥ ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥ አሰራር መፍጠር የሴቶችንና ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን የአካል ጉዳተኞችን ልዩ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በየደረጃው የመረጃ ተደራሽነትን ማረጋገጥ በመንግስት ቤቶች ላይ የሚፈጸሙ ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን በነዋሪው እና በባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ተሳትፎ እና ጥረት ማስወገድ የከተማ አስተዳደሩን ሥራ አጥነትና ድህነት ቅነሳ እንቅስቃሴው ላይ አዎንታዊ አስተዋፅኦ የሚያደርግ የቤት አስተዳደር ስርዓት ማረጋገጥ የመንግስት ቤቶችን ይዞታ አጠቃቀም ውጤታማነት በማሳደግ በዝቅተኛ ኪራይ የሚቀርቡ ቤቶችን ብዛት መጨመር የመመሪያው አላማ መመሪያው የሚከተሉት ዓላማዎች ይኖሩታል በከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች የሚደረገውን የመኖሪያና መስሪያ ቦታ አቅርቦት ጥረት በቤት ኪራይ አማራጭ የሚደረገውን አበርክቶ ስርዓት አሻሽሎ ማስቀጠል ጅ በቢሮዉ የቤት መረጃ አያያዝ የማከራየት ሂደት የቤት አሰጣጥ የቤት ቅያሬ የቤት የኪራይ አከፋፈል የቤት ጥገና እና በሚወጡት አሰራሮች ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚለቀቁ ክፍት ቤቶችን ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ለማከራየት የሚያስችል ስርዓት ለመዘርጋት ቢሮዉ በቤቶች ላይ የሚፈጸሙትን ህገወጥ ተግባራት ለመከላከልና በህገወጦች ላይ ህጋዊ እርምጃ አወሳሰድ ስርዓት ለመዘርጋት ከአቅም በታች አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የመንግስት ቤቶችን ቦታ በዳግም ልማት ወይም ጥገና ተጨማሪ የቤት አቅርቦት እንዲሰፋ ለማስቻል ክፍል ሁለት መረጃ ስለማደራጀት በአዋጅ የተወረሱ ቤቶች መረጃ ማደራጀት ቢሮው በአዋጁ የተወረሱ ቤቶችን ቆጠራ በማካሄድ ያሉና የፈረሱ ቤቶችን እንዲሁም ለባለቤቶቹ የተመለሱትን በመለየት መረጃ በአግባቡ ያደራጃል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሠረት የተለዩ ቤቶችን የተከራይ መረጃን የቤቱን ዓይነትና ደረጃ እንዲሁም የግልና የጋራ መገልገያ ቤቶችን እና ክፍት ቤቶችን በቋሚ መዝገብ ይመዘግባል ያደራጃል እንዲሁም የፈረሱ ቤቶችን መፍረሳቸውን በማረጋገጥ ከቋሚ መዝገብ እንዲሰረዝ ያደርጋል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ እና የተለዩና የተደራጁ ቤቶችን በአድራሻና በቤት ቁጥር ከለየ በኋላ በዘመናዊ መረጃ አደራጅቶ በሶፍትና በሀርድ ኮፒ እንዲሁም እንደሁኔታው የምስል መረጃ መያዝ ይኖርበታል ቢሮው የቤቶችን መረጃ በገፀምድር መረጃ ጭምር በማደራጀት ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርአት እንዲኖር ማድረግ ይኖርበታል የቤት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የሚሰራላቸውን ቤቶች እና ይዞታዎችን መረጃ በማደራጀት ለሚመለከተው አካል መረጃውን በመላክ ካርታው ተሰርቶ ሲጠናቀቅ አስፈላጊውን ርክክብ ያደርጋል የቤቶችና ይዞታዎች ካርታ እንዲሰራላቸው በማድረግ መረጃው አደራጅቶ ያስቀምጣል ከአዋጁ በኋላ በአስተዳደሩ የተገነቡ ቤቶችን በተመለከተ በከተማው አስተደዳር ውስጥ በተለያየ ጊዜ አስተዳደሩ የገነባቸውን ቤቶች ቆጠራ በማካሄድ ያሉና የፈረሱ ቤቶችን ይለያል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሠረት የተለዩ ቤቶችን የተከራይ ማንነት የቤቱን ዓይነትና ደረጃ እንዲሁም የግልና የጋራ መገልገያ ቤቶችን በቋሚ መዝገብ ይመዘግባል ያደራጃል በልማት ወይም በእርጅና የፈረሱ ቤቶችን መፍረሳቸውን እያረጋገጠ ከቋሚ መዝገብ እንዲሰረዝ ይደረጋል የተሰረዙትን ቤቶች በቃለ ጉባኤ በመያዝ በወረዳው ካቢኔ ቤቶቹ በልማት ወይም በአርጅና የፈረሱ ስለመሆናቸው ተወስኖ መረጃውን ይይዛል ለበላይ አካላትም ሪፖርት ይደረጋል አስተዳደሩ ገንብቷቸው ነገር ግን ቢሮው የማያስተዳደራቸው ቤቶችን ባለቤትን ለመወሰን የሚያስችሉ ቤቶችን መረጃ አደራጅቶ ለሚመለከተው አካል ለውሳኔ ያቀርባል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ እና የተለዩና የተደራጁ ቤቶችን በአድራሻና በቤት ቁጥር ከለየ በኋላ በዘመናዊ መረጃ አደራጅቶ በሶፍትና በሀርድ ኮፒ ይይዛል ከላይ በክፍል ሁለት አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው በዚህም አንቀጽ ተፈጻሚ ይሆናል ከአዋጁ በኋላ በመንግስታዊ ድርጅት መንግስታዊ ባልሆኑ እና በግል ድርጅቶች የተገነቡ እና መንግስት የሚያስተዳድራቸው እና ሊያስተዳድራቸው ስለሚገባ ቤቶችን በተመለከተ ቢሮው በከተማው አስተዳደር ውስጥ በተለያዩ ጊዜ መንግስታዊ ባልሆኑ የግል እና የመንግስት ድርጅቶች የተገነቡና የከተማው አስተዳደር የሚያስተዳድራቸውና ሊያስተዳድራቸው የሚገባ ቤቶችን ቢያንስ በሁለት አመት አንድ ጊዜ ቆጠራ ያካሂዳል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሠረት ቆጠራው ሲከናወን በቤቱ ውስጥ እየኖሩ ያሉት ነዋሪዎች ቤቱን በምን አግባብ እንዳገኙት ቤቱን ከመያዛቸው በፊት ይኖሩበት የነበረበት ሁኔታ እና በአሁኑ ጊዜ ቤቱ በማን ባለቤትነት እንደተያዘና ባለቤትነቱም በግለሰብ ከሆነ የተላለፈበትን ሁኔታ በዘመናዊ መረጃ አደራጅቶ በሶፍትና በሀርድ ኮፒ መያዝ አለበት በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሠረት የተለዩ ቤቶችን በቤት ዓይነትና ደረጃ እንዲሁም የግልና የጋራ መገልገያ ቤቶችን መረጃ መዝግቦ አደራጅቶ ይይዛል በተለያየ ጊዜ መንግስታዊ ያልሆኑ እና የግል እንዲሁም የመንግስት ድርጅቶች ቤቶቹን ገንብተው ነገር ግን ቢሮው የማያስተዳድራቸውን ቤቶች ባለቤትን ለመወሰን የሚያስችሉ የቤቶቹን መረጃ አደራጅቶ ለሚመለከተው አካል ለውሳኔ ያቀርባል መንግስታዊ ባልሆኑ እና የግል እንዲሁም የመንግስት ድርጅቶች በወረዳው አስተዳደር ውስጥ ተገንብተው ርክክብ የተደረገባቸው እንዲሁም ለወረዳው አስተዳደር በስጦታ ወይም በማናቸውም ህጋዊ መንገድ የተላለፉለትን ቤቶች የወረዳው አስተዳደር ወዲያውኑ በክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት በኩል ለቢሮው የማሳወቅ ግዴታ አለበት በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ መሰረት የመንግስት ቤት እንዲሆኑ የተወሰነባቸው ቤቶችና ይዞታዎች እንዲሁም በንዑስ አንቀፅ መሰረት ርክክብ የተፈፀመባቸው ቤቶችና ይዞታዎች የመረጃ ማደራጀቱ ስራ ከላይ በአንቀፅ የተደነገገው በእዚህም አንቀጽ ተግባራዊ ይሆናል ሪ ። መ ለህመምተኞች እንደየህመማቸው አስከፊነት ደሀ ደሀ ሆነው በእድሜ ለገፉ ደሃ ደሃ በመሆናቸው በአቅም ማነስ የከፋ የቤት ችግር ላለባቸው ሠ ከቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለተፃፈላቸው ረ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መ እና ሠ የተገለጸው አሰጣጥ ለሴቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ይሆናል ሰ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሀ እስከ ሠ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ቢሮው አሳማኝ ሁኔታ ሲያጋጥም በልዩ ሁኔታ ቅድሚያ እንዲሰጥ ሊያደርግ ይችላል የመንግስት መኖሪያ ቤት በኪራይ የሚሰጠዉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ላለው ወይም በከተማው ውስጥ በቋሚነት ነዋሪ ለሆነ የኢትዮጵያ ተወላጅ ዜጎችን በትውልድ አገራቸዉ የተለያዩ መብቶች ተጠቃሚ ለማድረግ የወጣ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት የጸና የኢትዮጵያ ተወላጅነት መታወቂያ ካርድ ያለዉ ማንኛውም የውጪ ሃገር ዜጋ ነው በአዋጁ ተወርስው ለአንድ ጊዜም ቢሆን በመንግስት ቤትነት ኪራይ የተከፈለበት ቤት በመንግስት ቤትነት ይቀጥላል ማንኛውም የመንግስት የቀበሌ ቤት ህጋዊ ተከራይ የጋራ መኖሪያ ቤት የግል ቤት ወይም በማንኛውም ሁኔታ የመኖሪያ ቤትና የቤት መስሪያ ቦታ ያለው ወይም ያገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ በእጁ ያለውን የመንግስት መኖሪያ ቤት በነበረበት ሁኔታ ለአከራይ የማስረከብ ግዴታ አለበት ነገር ግን እድሜዉ ከ ዓመት በላይ ሆኖ ቤተሰብ መስርቶ ከቤተሰቦቹ ጋር ተጠግቶ ይኖር የነበረ ልጅ የቤት ችግር ካለበት ከታች በተዘረዘሩት ንዑሳን አንቀፆች መሰረት እየተመዘነ በአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይስተናገዳል ሀ እድሜው ከ አመት በላይ ሆኖ ባለፉት አመታት ቤተሰብ መስርቶ ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ችግረኛ ከሆነ ለ ከቀጠና ጀምሮ በሜሚደራጅ የድሀ ድሀ ኮሚቴ ችግረኛነቱ ቅድሚያ የሚያሰጥ ሆኖ ሲገኝ ባለበት ቤት እንዲተች ተደርጎ በ የስራ ቀናት ውስጥ በወረዳው እና ክፍለ ከተማው ካቢኔ ውሳኔ መሰረት ተግባራዊ ይሆናል ሐ የቀጠናና የወረዳ ህዝብ አደረጃጃት እንዲሁም የወረዳው ካቢኔ ባፀደቀለት የድህነትችግረኛነት ደረጃ መሰረት ቀዳሚ ከሆነ በያዘው ቤት ይዋዋላል ነገር ግን የሚቀደም ከሆነ ለሌላ አካል ለቆ በደረጃው መሰረት ይስተናገዳል መ በዚህ አንቀፅ መሰረት በአንድ ቤተስብ ውስጥ ተጠቃሚ ሊሆን የሚችለው ችግረኛ ቤተሰብ የመሰረተ ሰው ከአንድ መብለጥ የለበትም ከላይ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ ሆ የተቀመጡት መስፈርቶች ሲሟሉ አንድና ከዚያ በላይ ተቀፅላ ፊደሎችን ሸንሸኖ በመስጠት የተወሰነለት ሰው የሚኖርበትን ቤት ብቻ እንዲዋዋል ተደርጎ ቀሪው ለሌላ የሚገባው አካል በኪራይ ይሰጣል በመንግስት ቤቶች ቦታ ውስጥ ከዋናው ቤት ተቀጥለው የተሰሩ ቤቶች የዋናው ቤት አካል ተደርገው ስለሚቆጠሩ ዋናው ቤት ሲለቀቅ አብረው ለመንግስት ተመላሸ ይደረጋል በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው የከተማው ነዋሪዎች ቤት ስለመመደብ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው የከተማ ነዋሪዎች ዝርዝር ቀደም ብሎ ይዘውት የነበረውን የመኖሪያ ቤት ክፍል ብዛት እና የቤተሰብ ብዛት መረጃ በወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት አደራጅቶ በላከለትና የሚመለከተው የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ባረጋገጠለት መሠረት የክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት በክፍለ ከተማው ካቢኔ አስወስኖ ክፍት ቤት ካለ ያስመድባል ክፍት ቤት ከሌለው ለቢሮ ያሳውቃል ቢሮው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ከክፍለ ከተማ የተላከለትን የድጋፍ ጥያቄ መነሻ በማድረግ ክፍት ቤት ባለበት ክፍለ ከተማ ቤት እንዲሰጥ ይወስናል ቢሮው በወሰነው መሠረት ክፍለ ከተማው በክፍትነት ከያዛቸው ቤቶች ጋር በማጣጣም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው የከተማ ነዋሪዎች እንደሁኔታው ቤት ይመድባል በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ጉዳት ከደረሰባቸው የከተማ ነዋሪዎች መካከል በደባልነት እየኖሩ ለሚገኙ ተፈናቃዮች በቢሮው ወይም ቀደም ብሎ የወረዳው ቤቶች አስተዳዳር ጽህፈት ቤት በደባልነት የመዘገባቸውና የቤት ኪራይ ውል ያላቸው ከሆኑ ለደባሎቹ በየስማቸው የተፈቀደላቸውን ምትክ ቤት እንዲያገኙ ይደረጋል ለመንግስት የስራ ኃላፊዎች ቤት ስለመመደብ ለከተማው አስተዳደር ስራ አስፈላጊ የሆኑ ኃላፊዎች ከክልል ከፌደራል መንግስት ወይም ከአስተዳደሩ የተለያዩ መስሪያ ቤቶች በቋሚነት በኃላፊነት ወደ ከተማው አስተዳደር መመደቡን የሚያረጋግጥ የሹመት ደብዳቤ ሲደርሰው በስሙም ሆነ በትዳር አጋሩ ስም በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ የግልም ሆነ የመንግስት ቤት የሌለዉ መሆኑ ተረጋግጦ ካለው ክፍት የመኖሪያ ቤት በስሙ ውል እንዲፈፅም ይፈቅድለታል በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው ቢኖርም ለተሺሚዎች ቤት ለመስጠት ሲባል ነዋሪዎችን ማፈናቀል አይፈቀድም የዚህ አንቀጽ ድንጋጌ ቢኖርም የመንግስትየቀበሌ ቤት በኪራይ ሊሰጣቸው የሚችሉ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ደንብ ቁጥር መሠረት ይሆናል የቀበሌ መኖሪያ ቤት የኪራይ ተመን አወሳሰን እና የቤት ቁጥር አሰጣጥ የቀበሌ መኖሪያ ቤት ኪራይ ተመን ጥናትን መሰረት አድርጎ አዲስ ማሻሻያ እስካልተደረገ ድረስ ቀደም ሲል በነበረው የኪራይ ተመን የሚቀጥል ይሆናል በከተማው አስተዳደር ውስጥ ቀደም ሲል ለመኖሪያ ቤትነት ተከራይተው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች ወርሃዊ የኪራይ ተመን በነበረው የኪራይ ተመን መሠረት ይቀጥላል ሆኖም የኪራይ ተመኑ በቢሮውና በፋይናስና ቢሮ በሚያቀርቡት ጥናት ላይ ተመስርቶ በከተማው አስተዳደር ውሳኔ መሰረት ሊሻሻል ይችላል የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ሆነው የቤት ቁጥር የሌላቸው ቤቶች መረጃን የወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህበት ቤት በመለየት ለክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት የሚያሳውቅ ሲሆን የክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤትና የይዞታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት በጋራ ተጠንቶ በክፍለ ከተማው ካቢኔ ፀድቆ እንዲመዘገብ ያደርጋል ዝርዝሩን ለቢሮው ያሳውቃል « በተለያዩ ምክንያት የቀበሌ መኖሪያ ቤቶችን ይዘው ነገር ግን የቤት ኪራይ ተመን ያልወጣላቸውና ኪራይ የማይከፈልባቸውን ቤቶች የኪራይ ተመን አወሳሰን በተመለከተ በአካባቢ የሚገኙ የቀበሌ መኖሪያ ቤቶችን ማእከል ያደረገ ሆኖ ቤቱ የሚገኝበትን አጎራባች ግራና ቀኝ ወርሃዊ የቤት ኪራይ አማካኝ ዋጋ መሰረት ያደረገ ይሆናል የመኖሪያ ቤት የኪራይ ውል ቀደም ሲል የቀበሌ መኖሪያ ቤት ተከራይተው የሜገኙና ወደፊትም አግባብ ባለው አካል እንዲከራይ የሚፈቀድለት ማንኛውም ሰው ከቢሮው እና ቢሮ ውክልና ከሰጠው አካል ጋር የቤት ኪራይ ውል እንዲዋዋል ይደረጋል የኪራይ ውል ያልፈጸመ ማንኛውም አካል ሕጋዊ ተከራይ ሆኖ አይቆጠርም የኪራይ ውል በሕጋዊ መንገድ ማደስ ሲገባቸው በወቅቱ ውላቸውን ያላደሱትን በተመለከተ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውል እንዲያድሱ ይደረጋል ከዚህ በላይ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት በተሰጠዉ ማስጠንቀቂያ ቀርበው ውላቸውን በወቅቱ ያላደሱት ውሉን በማቋረጥ ቤቱን አከራይ ቤቱን ይረከባል የመንግስት መኖሪያ ቤት ተከራዮች በየአመቱ ከሃምሌ እስከ ታህሳስ የቤት ኪራይ ውላቸውን ማደስ አለባቸው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የኪራይ ውል ያላደሱ ተከራዮች ከጥር ጀምሮ እስከ ሰኔ ድረስ ላለው እያንዳንዱ ወር የቤት ኪራይ ፐርሰንት በወርሃዊ ክፍያው ላይ ተቀጥተው እንዲያድሱ ይደረጋል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና መሰረት ቀርቦ በበጀት አመቱ ውሉን ማደስ ያልቻለ ተከራይ በገዛ ፈቃዱ ውሉን እንዳፈረሰ ተቆጥሮ ቤቱን አስተዳደሩ ይረከበዋል ቢሮው ከተከራይ ጋር የሚያደርጋቸው የመኖሪያ ቤት የኪራይ ውሎች ናሙና ከዚህ መመሪያ ጋር አባሪ ሆኖ እንዲያያዝ ይደረጋል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት በተዘጋጀው የቤት ኪራይ ውል ፎርማት መሰረት ቢሮው ወይም በሚወክለው አካል ከተከራዮች ጋር ውል ይዋዋላል ከነባር ተከራዮች ጋርም ያለውን ውል ያድሳል በየዓመቱ ተከራይ የኪራይ ውል ባለማደሱ ምክንያት በሚሰጠው ማስጠንቀቂያ እና በሚወሰነው ጊዜ ውስጥ ቤቱን ለአከራይ ባለማስረከቡ ምክንያት በአከራይ ላይ ለሚያደርሰው ወጪና ጉዳት ሁሉ ኃላፊነቱን ራሱ ተከራይ ይወስዳል የኪራይ አሰባሰብ እና አከፋፈል በዚህ መመሪያ ክፍል ሁለት መሰረት የተደራጀ የቤቶች መረጃን መሰረት በማድረግ አስተዳደሩ በኪራይ ያስተላለፋቸውንና የሚያስተላልፋቸውን የመንግስት መኖሪያ ቤቶች ኪራይ መረጃ በቤት ብዛት በኪራይ ተመን የከፈለውንና ያልከፈለውን እንዲሁም አጠቃላይ ወርሃዊ ገቢ በመለየት መረጃውን አደራጅቶ መያዝ ይኖርበታል መረጃውን የማደራጀት ስራው በክፍለ ከተማ እና በወረዳ በኩል የሚፈጸም ይሆናል ቢሮው ወይም ቢሮ የወከላቸው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የተሰበሰውን መረጃ በተከራይ ስም ወርሃዊ የኪራይ ክፍያ እና ቅጣት መኖሩን አጣርቶ አጠቃላይ ክፍያውን አስልቶ ለወረዳ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኪራይ እንዲከፈል ያስተላልፋል ተከራዩም ስለመክፈሉ የተሰጠውን ደረሰኝ ኮፒ ለቢሮው ወይም ቢሮ ለወከላቸው እንዲያቀርብ ተደርጎ ይመዘገባል ተከራይ ውል ገብቶ በተከራየው ቤት የተወሰነውን ወርሃዊ ክፍያ ወር በገባ በአስር የስራ ቀናት ውስጥ በወረዳ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የመክፈል ግዴታ አለበት ከበቂ ምክንያት ጋር በሕመም በመንግስት ግዳጅ በሌሎች ከአቅም በላይ በሆኑ ጉዳዮች ሕጋዊ ማስረጃ ካላቀረበ በቀር ተከራይ በተከታታይ ለ ወራት ኪራይ ያልከፈለ እንደሆነ ቢሮው ቤቱን ይረከባል የቀበሌ መኖሪያ ቤት ለሶስተኛ ወገን ስለማስተላለፍ የቀበሌ ቤትን የተከራየ ማንኛውም ሰው በሞት ሲለይ ወይም ከአካባቢው በተለያየ ምክንያት ሲለቅ ቤቱን ለቢሮው እንዲመልስ ይደረጋል ሆኖም ሟች በተከራየው ቤት ውስጥ የሚከተሉት ሀ የተከራይ ባል ወይም ሚስት ለመሆኑ ህጋዊ የጋብቻ ማስረጃ ሲቀርብ ለ የተከራይ ልጆችና በህጋዊ መንገድ በጉዲፈቻ ያደጉ ልጆች በቤት ውስጥ እየኖሩ መሆናቸው በወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሲረጋገጥ ሐ እድሜያቸው ከ ዓመት በታች ሆነው በቤቱ ውስጥ መኖር የጀመሩና ሟች እስከሞተበት ቀን ድረስ በቤት ውስጥ ከወላጆቻቸዉ ተለይተው እንደ ልጅ መኖራቸው በወረዳው የቤተሰብ አባላት መመዝገቢያ ቅጽ ዉስጥ መመዝገቡ ሲረጋገጥ እና የወረዳው አስተዳደርም እንደ ልጅ ቤት ውስጥ ማደጉን ማረጋገጫ ሲሰጥ የቤት ኪራይ ውል እንዲዋዋሉ ይደረጋል መ በችግር ምክንያት ከተከራይ ጋር በጥገኝነት የሚኖሩ የባል ወይም የሚስት እናት ወይም አባት ለመሆናቸው በወረዳ ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ሲረጋገጥ ሠ ከላይ ከተራ ቁጥር ሀ እስከ መ የተገለፁ ሁሉም ወራሾች ስለመሆናቸው እና በስማቸው ወይም በትዳር አጋራቸው ስም የጋራ መኖሪያ ቤት የግል መኖሪያ ቤት ወይም የቤት መስሪያ ቦታ ወይም ከመንግስት የተከራዩት ቤት የሌላቸው ወይም ከ ዓም በኋላ በሽያጭ ወይንም በስጦታ ያላስተላለፉ መሆኑ በማስረጃ ሲረጋገጥ ቤቱን በቀድሞ የኪራይ ተመን መሰረት በአዲስ ውል እንዲከራዩ ይፈቀድላቸዋል ረ በዚህ አንቀጽ ከንኡስ አንቀጽ ሀ እስከ መ ለሶስተኛ ወገን ቤትን ማስተላለፍን በተመለከተ ተፈጻሚነት የሚኖረዉ እንደቅደም ተከተላቸው ብቻ ይሆናል። ከዚህ በላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በፍርድ ቤት ወይም በቢሮ ውሳኔ ሲሰጥበት ለሌላ ሶስተኛ ወገን ሊተላለፍ ይችላል ተከራይ ለሚስትለባል ለልጅ ለሞግዚት የኪራይ ውል በስሙ እንድያድሱለት ህጋዊ ውክልና መስጠት ይችላል በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ከተጠቀሱት አካላት ዉጪ ለሌላ ወገን በውክልና ስም አስተላልፎ አምስት ዓመት እና ከዚያ በላይ በውጭ አገር ከኖረ የቤት ኪራይ ውሉ እንዲቋረጥ በማድረግ መንግስት ቤቱን ይረከባል የቀበሌ ቤት ተከራይ በሕግ ጥላ ስር በመሆኑ የቤት ክራይ ውል ማደስ ያልቻለ ከሆነ ከማረሚያ ቤት በሚሰጥ ማስረጃ በህጋዊ ወኪሉ በውክልና የቤት ኪራይ ውል ማደስ ይችላል በአእምሮ መዛባት ምክንያት ንብረቱን ማስተዳደር የማይችል ህጋዊ ተከራይ ከሚመለከተዉ አካል ማስረጃ ሲያቀርብ በሞግዝቱ ወይም በአስተዳዳሪዉ በኩል የቤት ኪራይ ዉሉ በስሙ ይታደሳል የመንግስት ቤት ተከራይ ከሆኑት ባልና ሚስት አንደኛዉ ወገን በሞት ቢለይ ሟች በህይወት በነበሩበት ጊዜ የተመዘገበዉ የኮንዶሚንየም ቤት እጣ ደርሶት በህይወት ያለው ወገን የእድሉ ተጠቃሜ ከሆነ ወይም የግል ቤት በማናቸውም መንገድ ካገኘ የሟች ልጆች ሟችን ተክቶ የመንግስትን ቤት የተከራይነት መብት ሊጠይቁ አይችሉም ስለ ደባልነት ከደባሎች አንዱ በሞት ቢለይ የቤቱ ግማሸ ለወራሾች እንዲተላለፍ ይደረጋል ሆኖም የሟች ህጋዊ ወራሸ የሌሉ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ቀሪዉ ደባል የቤቱ የሙሉ መብት ተከራይ ይሆናል ከደባሎች መካከል አንዱ የግል ቤቱን ሰርቶ ኮንዶሚኒየም ደርሶት ወይም በተለያየ ምክንያት ቤቱን ሲለቅ ቀሪዉ ደባል የቤቱ የሙሉ መብት ተከራይ ይሆናል ሪ ክፍል አራት ስለ መንግስትቀበሌ ንግድ ቤቶች አስተዳደር ለተጠቃሚው ስለሚሰጡበት ሁኔታና የኪራይ ውል የመንግስትቀበሌ ንግድ ቤት ስለሚሰጥበት ሁኔታ ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው ህጋዊ አካል በክፍትነት የተያዙና እና ወደፊት የሚለቀቁ የቀበሌ ንግድ ቤቶችን ዝርዝር መረጃ አደራጅቶ መያዝ ይኖርበታል የቀበሌ ንግድ ቤት በኪራይ ሊሰጥ የሚችለው ጨረታን መሰረት በማድረግ ብቻ ይሆናል ሆኖም ግን ከንቲባው እንዳስፈላጊነቱ በምደባ በአከባቢዉ የንግድ ቤት ጨረታ መነሻ ዋጋ እንዲተላለፍ ሊያደርግ ይችላል የቀበሌ ንግድ ቤትን በአካባቢው መነሻ ዋጋ በማህበር ለተደራጁ ስራ አጦች እንዲከራይ የክፍለ ከተማው ስራ እድል ፈጠራና በኢንተርፕራይዝ ልማት ጽቤት ጥያቄ ሲያቀርብ የክፍለ ከተማው ካቢኔ ምቹነቱን አረጋግጦ ይወስናል የክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ውል አዋውሎ ለቢሮው ያሳውቃል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተገለፀው መሠረት ማህበራቱ በሚሰጣቸው ንግድ ቤት ላይ ከቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ጋር የንግድ ቤት ኪራይ ውል መፈፀም ይኖርባቸዋል በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው የመንግስት ንግድ ቤት የተከራዩ ማህበራት ቤቱን ሊገለገሉበት የሚችሉት ለአምስት አመታት ብቻ ሆኖ የቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ውል በማቋረጥ ቤቱን ተረክቦ በመመሪያው መሰረት ያስተላልፋል የጨረታ አወጣጥ ሂደት ቢሮው የሚወክለው ህጋዊ አካል የንግድ ቤቶችን ጨረታ ለማውጣት በቅድሚያ የጨረታ መነሻ ዋጋ ቀደም ሲል ቤቱ ለጨረታ ከመቅረቡ በፊት ይከፈል የነበረው የኪራይ ተመን ሲሆን ጨረታውን የሚያወጣው አካል ነባራዊ ሁኔታውን ግምት ውስጥ በማስገባት እንደአስፈላጊነቱ ሊያሻሽለው ይችላል ወ ወ ጅ መሬ መ የንግድ ቤቶች ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያና የተጫራቾች መመሪያ የጨረታ ሀሳብ መልስ ማቅረቢያ እና የንግድ ቤት ሽያጭ ውል ናሙና ሰነድ ማዘጋጀት የጨረታ ኮሜቴ መሰየም የጨረታ ሳጥን እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶች ማዘጋጀት ጨረታውን ማሳወቅ ወይም ጥሪ ማድረግ የጨረታ ሰነድ መሸጥ የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ እና ሌሎች በጨረታ ማስታወቂያና መመሪያ መሠረት አስፈላጊ ሰነዶችን መቀበል ጨረታውን ለማከሄድ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል ከላይ የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ የጨረታ ሂደቱ የመንግስት የግዥ መመሪያን የተከተለ መሆን ይኖርበታል የንግድ ቤቶች ሽያጭ ጨረታ ሰነድ ይዘት ቢሮው የጨረታ ሰነዱን በሚያዘጋጅበት ወቅት ይዘቱን በተመለከተ በዚህ መመሪያ አባሪ ሆነው የሚወጡ ሲሆን በዋናነት ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት ስምና አድራሻ ከመያዙም በተጨማሪ በፋይናንስ ግዥ መመሪያ መሠረት ያደረገ ስለመሆኑና መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይዘትን ያገናዘበ የጨረታ መርህ መከተል አለበት ለጨረታ የሜቀርበው ንግድ ቤት ሙሉ አድራሻ እና የአከባቢው ልዩ ስምና ምልክት እንዲሁም የቤቱ ስፋት በካሬ ሜትር የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ለጨረታ የቀረቡ የንግድ ቤቶች ዝርዝር በክፍለ ከተማ በወረዳ ወይም በቀበሌ እና በቤት ቁጥር እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን መያዝ ይኖርበታል የንግድ ቤቶች ሽያጭ ጨረታ ኮሚቴ አሰያየም የቢሮው እና ቢሮዉ የሚወክለዉ አካል የንግድ ቤቶች ሽያጭ ጨረታ ኮሚቴ አምስት አባላት የሚኖሩት ሲሆን በወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት የሚሰየም ሁለት አባላት የወረዳው የገቢዎች ጽህፈት ቤት አባል በወረዳ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሚሰየም ሰብሳቢ የወረዳው የፋይናንስ ጽህፈትቤት ኃላፊተወካይ ። ተከራይ ውል ገብቶ በተከራየው ቤት የተወሰነውን ወርሃዊ ክፍያ ወር በገባ በአስር ቀናት ውስጥ በወረዳ አነስተኛ ግብር ከፋዩች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ቀርቦ የመክፈል ግዴታ አለበት በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት የመክፈያ ጊዜ ካሳለፈ በመቶ መቀጮ ተጨምሮ እንዲከፍል ይደረጋል በተደጋጋሚ ጊዜ የቤት ኪራይ ክፍያቸውን የማይከፍሉትን ተከራዮች የንግድ ቤቱን ውል እስከ ማቋረጥ የሚደርስ እርምጃ ቢሮው ይወስዳል የቀበሌ ንግድ ቤት የኪራይ ተመን አወሳሰን እና የቤት ቁጥር አሰጣጥ በከተማው አስተዳደር ውስጥ ቀደም ሲል ለንግድ ቤትነት ተከራይተው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የቀበሌ ንግድ ቤቶች ወርሃዊ የኪራይ ተመን ጥናትን መሰረት አድርጎ አዲስ ማሻሻያ እስካልተደረገ ድረስ በነበረው የኪራይ ተመን መሠረት ይቀጥላል ሆኖም የኪራይ ተመኑ በቢሮውና በፋይናስና ቢሮ በሚያቀርቡት ጥናት ላይ ተመስርቶ በከተማው አስተዳደር ውሳኔ መሰረት ሊሻሻል ይችላል የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቤቶች ሆነው የቤት ቁጥር የሌላቸው ቤቶች መረጃን የወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት በመለየት ለክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ያሳውቃል የክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ከክልለ ከተማው ይዞታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ጋር በጋራ በማጥናት በክፍለ ከተማው ካቢኔ ፀድቆ እንዲመዘገብ ያደርጋል ዝርዝሩንም ለቢሮው ያሳውቃል የቀበሌ ንግድ ቤቶችን ይዘው ነገር ግን የቤት ኪራይ ተመን ያልወጣላቸውና ኪራይ የማይከፈልባቸውን ቤቶች የኪራይ ተመን በግራና በቀኝ የሚገኙ ንግድ ቤቶች አማካይ ተመን እንዲከፍል ይደረጋል የከተማ አስተዳደሩ የንግድ ቤቶች ለአካባቢው በተቀመጠው የመንግስት ቤቶች የጨረታ መነሻ ዋጋ መሠረት ይተላለፍላቸዋል የቀበሌ ንግድ ቤት ለሶስተኛ ወገን ስለማስተላለፍ የቀበሌ ንግድ ቤትን በኪራይ የመጠቀም መብት ለሌላ ሶስተኛ ወገን ሊተላለፍ የሚችለው ከዚህ በታች በተቀመጠው አግባብ ብቻ ይሆናል ። ክፍል ስምንት የቤት ክፍፍል ልዉዉጥ እና የአገልግሎት ለውጥ ስለማድረግ የቀበሌ መኖሪያ እና ንግድ ቤትን ስለማካፈል በባልና ሚስት መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ በፍርድ ቤት ውሳኔ ፍቺ ከተፈፀመ እና ቤቱን ተካፍሎ ለመኖር በአንዳቸው አቤቱታ ሲቀርብ እና ቤቱ ሊካፈል የሚችል ሲሆን ቢሮው ወይም ቢሮዉ የወከለዉ አካል ቤቱን ሀሆ እና ለ በሚል ቁጥር በመስጠት ቤቱን በእጣ ወይም በስምምነት ያካፍላል የቤቱን ኪራይ ተመን በተመለከተ ቀደም ሲል ሲከፈልበት የነበረውን ክፍያ ለሁለት በመክፍል የቤት ኪራይ ውል በየስማቸው እንደ አዲስ እንዲዋዋሉ ይደረጋል ባልና ሚስት ፍቻቸው በፍርድ ቤት ውሳኔ ካገኘበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ፍች የፈፅሙበትን የፍርድ ቤት ውሳኔ ለወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ማሳወቅ ይኖርባቸዋል ነገር ግን በተገለፅው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማያሳውቁ ከሆነ የቤት ይካፈልልኝ መብት መጠየቅ አይችሉም ፍች የፈፅሙ ባልና ሚስት የሚከፈለውን ቤት ድርሻ አንዳቸው ለአንዳቸው መልቀቅ ይችላሉ ነግር ግን ድርሻውን የለቀቀው ወገን በማንኛውም ሁኔታ ተመልሶ ድርሻቸውን መጠየቅ አይችልም ቢሮው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በ እና ሯ መሠረት ለሁለት የተከፈለውን ቤት በቋሚ ንብረት መዝገብ እንዲመዘገብ ያደርጋል ከአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ከአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በ ዉጪ የመንግስት ቤቶችን መሸንሸንም ሆነ ማካፈል አይቻልም የቤት ቅያሬ እና የልዉዉጥ ጥያቄን በተመለከተ ማንኛውም ተከራይ ለመኖሪያ ቤትነት የተከራየውን ቤት ከሌላ ተከራይ ጋራ ለመለዋወጥ ከፈለገ ለመለወጥ ምክንያት የሆነውን ጥያቄ በወረዳና በክፍለ ከተማ ዉስጥ ከሆነ መለወጥ የሚችለዉ የክፍለ ከተማዉ ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ይሆናል ከክፍለ ከተማ ክከተማ ከሆነ ለቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በማቅረብ ፈቃድ ማግኘት ይኖርበታል ቹ የመኖሪያ ቤት ለመለወጥ የሚፈለጉ ተከራዮች ስምምነታቸውን የሚገልጽ የፍላጎት ማሳወቂያ ማመልከቻ ለቢሮው ወይም ቢሮዉ ለሚወክለዉ አካል በጽሁፍ ማቅረብ አለባቸው በዚሁ መሠረት ውሳኔ ካገኘ ልውውጡ መከናወን ይችላል የቤት ልውውጡ ከመከናወኑ በፊትም የቤት ኪራይ ውዝፍ እና ሌሎች ከቢሮው ወይም ቢሮው ከሚወክለው አካል ጋር የገባቸው ግዴታዎች መሟላቱን በማረጋገጥ የቤት ኪራይ ውሉ በተለዋወጡት ቤት ተከራይ ስም ውል እንዲዋዋሉ በማድረግ ቤቱን እንዲረከቡ ይደረጋል ልውውጡን የሚያደርጉት ሌላ መኖሪያ ቤት ቦታ የሌላቸው መሆኑን ቤታቸው በአንፃራዊ ተመጣጣኝ መሆኑና የቁልፍ ሽያጭ አለመሆኑ ተረጋግጦና የግዴታ ዉል ገብቶ ይፈጸማል ቤት ሊቀየር የሚችለዉ በጎርፍ አደጋ በእሳት አደጋ እና በሌሎች ድንደተኛ ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ሲሆን ከዚህ ዉጪ በልዩ ሁኔታ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ካመነበት ሊፈቅድ ይችላል በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እንደተጠበቀ ሆኖ የቤት ቅያሬ ጥያቄዎች ቀርበዉ ሊሰተናገዱ የሚችሉት የወረዳዉ አስተዳደር የዉሳኔ ሃሳብ ለክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ሲያቀርብ እና የክፍለ ከተማዉ የቤቶች አሰተዳደር ጽቤት ሲወስን ተፈጻሚ ይሆናል በህገዐወጥ የተያዙ የመንግስት ቤቶችን ማስለቀቅን በተመለከተ በህገወጥ መንገድ የመግስት ቤት የያዙ ኮንዶሚኒየም ቤት ደርሶአቸው ወይም በተለያየ ምክንያት ሌላ ቤት ኖሯቸው የቀበሌ ቤቱን ያለቀቁ ግለሰቦችን ለማስለቀቅ የሚቋቋመው ግብረ ሃይል አባላት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰብሳቢ የወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊፈዐኃፊ የወረዳው ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፈ አባል የወረዳው የመሰረተ ልማት ቅንጅትግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ጽህፈት ቤት ኃላፊአባል የወረዳው ንግድ እና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት አባል እንደአስፈላጊነቱ በወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ የሚሰየሙ አካላት አባል ቹ የግብረ ሃይሉ ተግባርና ኃላፊነታቸው ሀ በህገወጥ ተይዘዉ በግብረሃይል መለቀቅ ያለባቸውን ቤቶች መረጃ ከቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽህፈት ቤት ተቀብሎ ያደራጃል ለ በቀረበለት መረጃ መሰረት ፕሮግራም በማዉጣት በህገወጦች የተያዙ ቤቶችን ያስለቅቃል ቤቱንም ያሽጋል እንዲሁም ሂደቱንም በቃለ ጉባኤ ይይዛል ሐ በህገወጥ የተያዙ ቤቶችን ለማሸግ ቤቱ ዉስጥ ያለዉን ንብረት በቅድሚያ ግለሰቡ በራሱ ከቤቱ እና ከግቢ ዉስጥ እንዲያወጣ ያደርጋል ነገር ግን ፈቃደኛ ካልሆነ ንብረቶቹን በመመዝገብ የወረዳዉ አስተዳደር በሚያዘጋጀው ቦታ ንብረቱ እንዲቀመጥ በማድረግ ቤቱን ያሸሽጋል መ ግለሰቡ ንብረቱ እንዲመለስለት በጽሁፍ ሲጠይቅ አስተዳደሩ የመዘገበውና የያዘውን ንብረት ከመመለሱ በፊት አስተዳደሩ ያወጣውን ወጪ ግለሰቡ እንዲሸፍን በማድረግ ንብረቱ ይመለስለታል ሠ በግብረ ሃይሉ የተለቀቁትን ቤቶች ዝርዝር ለወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ወዲያውኑ ሪፖርት ያደርጋል ረ ህገ ወጥ ቤት በማስለቀቅ ሂደቱ የህግ የበላይነት ከማስከበር አንፃር የፖሊስ ኃይልን ማሳተፍ ይችላል የመንግስት ቤት አገልግሎት ለውጥ ስለማድረግ የንግድ ቤትን በከፊልም ይሁን በሙሉ ወደ መኖሪያ ቤት አገልግሎት መለወጥ አይፈቀድም ተከራይ ሙሉ በሙሉ በኪራይ የተሰጠውን የመንግስት መኖሪያ ቤት ወደ ንግድ ቤት መቀየር አይቻልም ከላይ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው ቢኖርም ቢሮው በጥናት ላይ በመመርኮዝ መኖሪያ ቤቱ ለመኖሪያነት ምቹ አለመሆኑን ሲያረጋግጥ ለተከራይ ምትክ ቤት በመስጠት ቤቱን ወደ ንግድ ቤት ቀይሮ የንግድ ቤትን ስለመስጠት በተደነገገው አግባብ ያስተላልፋል ከላይ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ስራ ፈጠራን ከማበረታት አንፃር የሚከተሉት ጉዳዮች ሲሟሉ በከፊል የመኖሪያ ቤትን ወደ ንግድ ቤት መቀየር ይቸላል ሀ የመኖሪያ ቤቱ በከፊል ወደ ንግድ አገልግሎት ለመለወጥ ፍላጎት ያለው ተከራይ ፍላጎቱን እና ሊሠራበት ስላሰበው የንግድ ሥራ ዘርፍ በጽሁፍ ለወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ማቅረብ ይኖርበታል ለ ማንኛውም ተከራይ ለመኖሪያ ቤትነት የተከራየውን ቤት ከፊሉን ወደ ንግድ ቤት ለመቀየር በቅድሚያ ለወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ማመልከቻ አቅርቦ ጽህፈት ቤቱ ለወረዳው ካቢኔ በማቅረብ ማስወስን ይጠበቅበታል ሐ ወረዳው የቀረበለትን ከፊል የቤት አገልግሎት ለውጥ ጥያቄ መነሻ በማድረግ ለንግድ የታሰበው ቤት ለተጠየቀው ንግድ ዘርፍ አመቺ መሆኑንና የአካባቢውን ነዋሪ ጸጥታ የማይረብሽ መሆኑን በየደረጃው ካሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት በቅድሚያ ስምምነቱን ማግኘት ይኖርበታል መ መኖሪያና ንግድ ቤት በሚል የሚከፈለው ቤት ሁለቱም ቤቶች የየራሳቸው ወደ ውጭ መዉጫና መግቢያ በር ሊኖራቸው ይገባል ሠ በክፍፍሉ ወቅት የመኖሪያ ቤቱ ድርሻ ለመኖሪያነት ምቹ ለማድረግ ሲባል የንግድ ቤት የሚሆነው ቤት ስፋት ከአጠቃላይ የቤቱ ስፋት ከ በላይ መሆን የለበትም ረ ለሶሰተኛ ወገን ተላፎ ቢገኝ ይቀማል ሰ የወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ወቅታዊ መረጃ ለክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሪፖርት ያደርጋል በባል ስም የነበረው መኖሪያ ቤት ለመኖሪያና ለንግድ ቤት እንዲውል ከተፈቀደ በኋላ በባልና ሚስት ስምምነት በከፊል ወደ ንግድ የተቀየረው ቤት የንግድ ቤት ኪራይ ውል በሚስት ስም መፈፀም ይቻላል ቭ« ክፍል ዘጠኝ የመንግስት ቤቶችን ይዞታ ስለማስተዳደር የመንግስት ቤቶች ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ስለማውጣት ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው የሚያስተዳድራቸውን እና በቀጣይ በተለያየ መንገድ ወደ ቢሮው የሚገቡ ቤቶችን ይዞታ በሙሉ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ እንዲወጣሳቸው መረጃ አደራጅቶ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ለሚሰጠው አካል ያቀርባል ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው የመንግስት ቤቶችን እና ይዞታውን ካርታ ለማውጣት የሚያስፈልጉ ሰነዶችን ያሰባስባል የተሰበሰበውን መረጃ በመያዝ ቤቶቹ በሙሉ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲኖራቸው ከክፍለ ከተሞች ጋር በመገናኘት ካርታዎቹ እንዲዘጋጅ ያደርጋል ተከታትሎም ይረከባል የወረዳው የቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ካርታ የወጣሳቸው ቤቶች የካርታውን ኮፒ በየአንዳንዱ የሚመለከታቸው ቤቶች ማህደር ውስጥ እንዲያዝ ያደርጋል ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው አካል ካርታ የተዘጋጀላቸውን ቤቶች የመሬት ምዝገባ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲዘጋጅ ክትትል ያደርጋል ስለ መንግስት ቤቶች ይዞታ መረጃ አደረጃጀትና አያያዝ በተመለከተ የተዘጋጀው ኦርጅናል የመንግስት ቤት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቤቱ በሚገኝበት ወረዳ ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ተደራጅቶ መቀመጥ ይኖርበታል አንድ ኮፒ በክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት እና አንድ ኮፒ በቢሮው ይቀመጣል የቤት ቁጥር መረጃ ችግር ያለባቸውን እና የቤት ቁጥር የሌላቸውን ቤቶች እንዲሁም የአድራሻ ችግር ያለባቸውን ይዞታዎች የወረዳው የቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ለይቶ ለሚመለከተው አካል በማቅረብ መረጃው እንዲስተካከል ያደርጋል የመንግስት ቤቶችን ይዞታ ስለማስተዳደር በእድሜ ብዛት እና በለተያዩ አደጋዎች የፈረሱ ቤቶችን የወረዳዉ ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ቤቶቹን በመለየት ወደ አገልግሎት መመለስ የሚችሉትን ዌ በመጠገን ለአገልግሎት ማዋል አለበት ነገር ግን ወደ አገልግሎት መመለስ የማይችሉ ቤቶችን ቦታዉን በማጽዳት መረጃውን አጠናቅሮ ለክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ያስተላፋል የክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ከቢሮው ጋር በመነጋገር የግንባታ ፈቃድ በማውጣት ቤቶችን ዳግም በማስገንባት ወደ ኪራይ አስገብቶ ያስተዳድራል ካርታ ወጥቶላቸው በመልሶ ማልማት ሙሉ በሙሌና በከፊል የፈረሱ ቤቶች ለይቶ መረጃውን ይይዛል በየደረጃው ሪፖርት ያደርጋል ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው አካል ከተለያዩ አካላት ለሚቀርቡ የይገባኛል ጥያቄዎች የድንበር ክርክር እና መሰል ጥያቄዎች ባገኘው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ መሰረት እንዲከበር ያደርጋል በየደረጃው ሪፖርት ያደርጋል በመንግስት ቤቶች ይዞታና ለሌሎች አጎራባቾች መካከል የወሰን ይከበርልኝ ጥያቄ ሲኖር የወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት መረጃውን አደራጅቶ ለክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደርጽህፈት ቤት ይልካል አፈፃፀሙን ይከታላል ሲወሰንም ተግባራዊ ያደርጋል ከላይ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ በተደነነገው መሰረት የክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት የቀረበለትን መረጃ መሰረት በማደረግ የቢሮውን መብት ያስጠብቃል ውሳኔውንም ለወረዳውና ለቢሮው ያሳውቃል በመሬት አስተዳደር ህግ መሰረት የይዞታ ይከፈለልኝ ጥያቄ እና የግንባታየእድሳት ፈቃድ ጥያቄ ሲኖር የወረዳው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት ቢሮውን ወክሎ ይገኛል የቢሮው መብት መከበሩን ያረጋግጣል ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው አካል ኩታ ገጠም የመንግስት ቤት ይዞታዎች ላይ የሚገኙ ቤቶችን ለጥገና ወይም ዳግም ልማት ሲፈልግ የይዞታ ይቀላቀልልኝ ጥያቄ ያቀርባል አፈፃፀሙን ይከታተላል ክፍል አስር የአስተዳደሩን ቤት ስለማስረከብ ክልከላ ውል ስለማቋረጥ ተጠያቂነት እና አቤቱታ አቀራረብ የቀበሌ መኖሪያ ወይም ንግድ ቤት ወይም የአስተዳደሩን ቤት ስለማስረከብ የቀበሌ መኖሪያ ወይም ንግድ ቤት ወይም የአስተዳደሩን ቤት ከቢሮው የተከራየ ሰው በስሙም ሆነ በትዳር አጋሩ ስም የራሱን ቤት ከገነባ ወይም የጋራ ህንፃ ቤት ከገዛ ወይም የመንግስት ቤቶች ኮርፖሬሽን ቤት ካገኘ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት ቤቱን የለቀቀ ከሆነ ቤቱን ባለበት ሁኔታ ለቢሮው ወይም ቢሮዉ ለሚወክለዉ አካል ማስረከብ ይኖርበታል ቢሮው ወይም ቢሮዉ የሚወክለዉ አካል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ቤቱን ሲረከብ ተከራይ መሸኛ ወይም ማስረጃ እንዲሰጠው ሲጠይቅ ውዝፍ ዕዳ የሌለበት መሆኑ እና ቤቱ ጉዳት ሳያደርስ በነበረበት ሁኔታ ማስረከቡ ተረጋግጦ መሸኛ እንዲሰጠው ይደረጋል የተከለከሉ ድርጊቶች ማንኛውም ተከራይ ወይም ይህን መመሪያ የሚያስፈጽም አካል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ተግባሮች ማከናወን የተከለከለ ነው ማንኛውም ሰው በህጋዊ መንገድ በተከራየው ቤት ውስጥ ባለ ክፍት ቦታም ሆነ በቤቱ አካል ላይ ካለ አስተዳደደሩ ፈቃድ ግንባታ መገንባት ክልክል ነው በዚህ መመሪያ ከተፈቀደው አግባብ ካልሆነ በቀር ከኪራይ ውሉ ውጭ የቤቱን አገልግሎት መለወጥ የተከለከለ ነው ከቢሮው ወይም ቢሮዉ ከሚወክለዉ አካል የተከራየውን የመንግስት ቤት በዚህ መመሪያ ዉስጥ ከተጠቀሰዉ አሰራር ዉጪ ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት የተከለከለ ነው ተከራይ ከአስተዳደሩ የተከራየውን ቤት ለሌላ ሶስተኛ ወገን ማከራየት የተከለከለ ነው ማንኛውም ተከራይ ከተሰጠው የእድሳት ወይም ጥገና ፈቃድ ውጭ የቤቱን ቅርጽ እና ስፋት መቀየር አይችልም በሕገወጥ መንገድ የተያዙ መኖሪያና ንግድ ቤቶች ላይ የወረዳዉ አስተዳደር እርምጃ ሳይወስድ ማስቀመጥ የተከለከለ ነዉ « የመንግስት ቤትን በህገወጥ መንገድ ያለኪራይ ውል መያዝ የተከለከለ ነው ከቢሮው ወይም ቢሮዉ ከሚወክለዉ አካል የተከራየውን የቀበሌ ወይም የመንግስት ቤት ወይም ህንፃ ዲዛይን መቀየር የተከለከለ ነው የቢሮው ሠራተኞች በማንኛውም ወቅት ስለቤቱ ቁጥጥርና መረጃ ለመጠየቅ ለስራ ጉዳይ ሲንቀሳቀሱ ተከራዩ የመተባበርና ስለቤቱ ትክክለኛ መረጃ የመስጠት ግዴታ አለበት ተከራይ የተከራየውን ቤት ኪራይ ሳይከፍሉና የኪራይ ውል ሳያሳድስ መገልገል የተከለከለ ነው ቢሮው የመንግስት ቤቶችን ምዝገባ ለማካሄድ ለሚያደርገው ጥረት መረጃ አለመስጠት ወይም መደበቅ የተከለከለ ድርጊት ነው ማንኛውም ሰው በዚህ መመሪያ ከሚፈቀደው ውጭ የመንግስት ቤትን ማከራየት መጠቀም ማስተላለፍ ኪራይ መሰብሰብ ክልክል ነውቤቱ በኪራይ ከተላለፈ በኋላ ተከራዩ ከ ወር በላይ ዘግቶ ማስቀመጥ አይፈቀድም ተከራይ ቤቱን ሲለቅ የውኃ የመብራትና የስልክ የተጠቀሙበትን ለየተቋሙ በመክፈል የከፈለበትን የመጨረሻ ወር ደረሰኝ ለወረዳዉ ቤቶች አስተዳደር ጽቤት ሳያስረክብ መሄድ የተከለከለ ነዉ አንድን የመንግስት ቤት መመሪያዉ ሳይ ከተፈቀደዉ ዉጪ መሸንሸንም ሆነ የቤት ቁጥር መስጠት የተከለከለ ነዉ ማንኛዉም የመንግስት ቤት ተከራይ የቤት ኪራይ ዉል ሳይኖረዉ ወይም ሳያድስ ኪራይ መክፈል የተከለከለ ነዉ በቂ መረጃ ባልተገኘበት አንድን የመንግስት ቤትይዞታ የመንግስት ቤትይዞታ አይደለም ብሎ ምላሽ መስጠት የተከለከለ ነዉ የመንግስት መኖሪያ ቤትን ወደ ንግድ ቤትነት ሙሉ በሙሉ መቀየር የተከለከለ ነው የቀበሌ ንግድ ቤትን ወደ መኖሪያ ቤት መቀየር የተከለከለ ነው ቹ ውል ስለማቋረጥ ተከራይ በዚህ መመሪያ ከተገለፀው ውጭ ቤቱን ለሶሶስተኛ ወገን ያስተላለፈ እንደሆነ ህገወጥ ግንባታ ከገነባ ቢሮዉን ሳያስፈቅድ የአገልግሎትና የዘርፍ ለውጥ ካደረገ እና በዚህ መመሪያ ከተፈቀደው ውጪ የህብረተሰቡን ደህንነትና ጤንነት የሚጎዳ ተግባር ማከናወኑ ሲረጋገጥ ውሉ ሊቋረጥ ይችላል ማንኛውም ተከራይ ለተከታታይ ወራት የቤት ኪራዩን ባይከፍል ቢሮው ወይም ቢሮዉ የሚወክለዉ አካል ውሉን ያቋርጣል ሆኖም ውል ከመቋረጡ በፊት ለተከራይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሊደርሰው ይገባል ማንኛውም ተከራይ ለኛ ወገን ካስተላለፈ የውል ዕድሳት ያላደረገ ሁለት የመንግስት ቤት የያዘ በስሙ ወይም በትዳር አጋሩ ስም የግል ቤት እያለው የመንግስት ቤት የያዘና በመንግስት ቤትቦታ ካርታ ያወጣ የመንግስት ቤቶችን ያለ አገልግሎት ዘግቶ ያስቀመጠ የውል ዘመን ሲፈጸም ቤቱ ሲፈርስ ከሃገር ውጭ የወጣና እንደማይመጣ ሲረጋገጥና ሌሎች የውል ግዴታዎችን አለመወጣት ሲያጋጥም የኪራይ ውሉ ይቋረጣል ቤቱንም ይረከባል ተከራይ ከባል ከሜሚስት ከልጅ ከሞግዚት ውጭ ለሌላ ወገን በውክልና ስም አስተላልፎ አምስት አመት እና ከዚያ በላይ ውጭ አገር ከኖረ የቤት ኪራይ ውሉ ይቋረጣል መንግስትም ቤቱን ይረከባል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና መሰረት ውል የተቋረጠበትን ተከራይ ውዝፍ የቤት ኪራይ ዕዳ እና ሌሎች ቢሮው ያወጣቸውን ወጪዎች በሕግ ጠይቆ እንዲከፈለው ያደርጋል ሆኖም ቢሮው ወይም ቢሮው የሚወክለው አካል የውል ማቋረጥ ውሳኔ ከማስተላለፉ በፊት ተከራይ ያለበትን መሰረታዊ ችግሮች ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የተከራይን ውል ማቋረጥ ከህብረተሰብ ሞራል ጋር ተቃራኒ ሆኖ ካገኘው እና ተከራይን ለከባድ ችግር የሚያጋልጥ ከሆነ ውዝፍ እዳውን ከስድስት ወር በማይበልጥ ጊዜ ውስጥ እንዲከፍል ጊዜ ሊሰጠው ይችላል የመንግስት መኖሪያ ቤትን መንግስት ሲፈለግ ምትክ መኖሪያ ቤት በመስጠት የቤት ኪራይ ውሉን ያቋርጣል በተመሳሳይ መልኩ የንግድ ቤትን መንግስት ሲፈልግ ባለው አሠራር መሠረት ምትክ በመስጠት ቤቱን ይረከባል የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ከ እስከ ተገባራዊ ከመሆኑ በፊት አከራይ ለተከራይ የ ቀናት ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የቤት ኪራይ ውሉን በማቋረጥ ቤቱን ይረከባል ተጠያቂነት ማንኛውም ሰው የዚህን መመሪያ ድንጋጌ ተላልፎ ቢገኝ በወንጀልም ሆነ በፍትሐ ብሔር ሕግ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል ከመንግስት ቤቶች አስተዳደርና ተያያዥ ስራዎችን የሚሰራ ማንኛውም አስፈፃሚና ፈፃሚ ሠራተኛ ወይም የስራኃላፊ በዚህ መመሪያ የተደነገጉ ግዴታዎችና ክልከላዎችን ተላልፎ ከተገኘ በወንጀልና በፍትሐብሔር ሕግ መሠረት ተጠያቂነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር መሠረት ተጠያቂ ይሆናል አቤቱታ ስለማቅረብ ማንኛውም ተከራይ ከመንግስት ቤት አስተዳደር በጨረታም ሆነ በልዩ ሁኔታ ቤት ሊተላለፍልኝ ሲገባ መብቴን አላግባብ እንዳጣ ተደርጌአለሁ ወይም በደልም ደርሶብኛል ወይም በንግድ ቤት ጨረታ ውጤት ላይ ቅሬታ አለኝ ወይም ውል ያለአግባብ ፈርሶብኛል ወይም ከቤቶች አስተዳደር ጋር ቅሬታ አለኝ የሟል ከሆነ አቤቱታውን በየደረጃው ለሚገኘው አቤቱታና ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የማቅረብ መብት አለው የአቤቱታና ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ አደረጃጀት እና አፈጻጸም በየደረጃዉ ለተሰየመዉ የአቤቱታ እና ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ በዚህ መመሪያ መሠረት የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የሚመለከት ይሆናል ስለአቤቱታና ቅሬታ አቀራረብ ሥነሥርዓት አቤቱታ ወይም ቅሬታ ያለው ባለጉዳይ አቤቱታውን ወይም ቅሬታውን ራሱ ወይም በህጋዊ ወኪሉ አማካኝነት በፅሁፍ በየደረጃዉ ላሉ የቤቶች አስተዳደር ጽቤት እና ለቢሮው ሊያቀርብ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ አቤቱታው ወይም ቅሬታው የቀረበለት አካል አቤቱታውን ወይም ቅሬታውን ለአጣሪው ኮሚቴ እንዲታይ ወዲያውኑ ይመራል የቅሬታ ወይም አቤቱታ አቀራረብ በጹሑፍ ሆኖ ቅሬታው ወይም አቤቱታዉ የቀረበበትን ዋና ጉዳይ ባለጉዳዩ እንዲሰጠው የሚፈለገውን መፍትሄ ደጋፊ ሇ« ማስረጃዎች ካሉ የባለጉዳይ ሙሉ ስምና አድራሻ እና መንስኤ የሆነው ድርጊት የተፈፀመበትን ቀን መያዝ ይኖርበታል ስለአቤቱታና ቅሬታ መልስ አሰጣጥ ኮሚቴው አቤቱታ ወይም ቅሬታ ያቀረበው ተገልጋይ ደረሰብኝ ያለውን በደል ባለው አሰራር መሰረት በመመርመር የተደረሰበትን ግኝትና ውሳኔ በአምስት ቀናት ውስጥ ለባለጉዳዩ ምላሽ መስጠት ይኖርበታል አቤቱታው ወይም ቅሬታው ተገቢነት ከሌለው ያቀረበው ሀሳብ ትክከለኛ አለመሆኑን ካረጋገጠ በሰብሳቢው በኩል ለባለጉዳዩ በጽሁፍ ያስታውቃል በግልባጭም እንደ አግባብነቱ ለቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ወይም ለክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት እንዲያውቀው ያደርጋል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና መሰረት አቤቱታ አቅራቢው ኮሚቴው በሰጠው መልስ ወይም በተሰጠው ማብራሪያ ካልረካ ቅሬታውን እንደ አግባብነቱ ለቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ወይም ለክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት በሰባት የስራ ቀን ውስጥ ማቅረብ ይኖርበታል የቀረበው አቤቱታ ከኮሚቴው አቅም በሳይ ከሆነ የውሳኔ ሀሳቡን በከተማ ደረጃ ለቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወይም ጉዳዩ የሚታየው በክፍለ ከተማው ደረጃ ከሆነ ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤት በጽሁፍ ያሳውቃል የክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽህፈት ቤትም ጉዳዩን አይቶ ከአቅም በላይ ከሆነ ለቢሮው ሃላፊ በጽሁፍ ያሳውቃል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በ እስከ በተዘረዘሩት መሰረት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ይግባኝ ወይም ክስ ስለማቅረብ ቢሮው በሚሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ሰው የይግባኝ አቤቱታውን ለከተማው የሕዝብ ቅሬታና አቤቱታ ማስተናገጃ ጽሕፈት ቤት በማቅረብ የመጨረሻዉን ዉሳኔ ያገኛል « ክፍል አስራ አንድ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ውክልና ስለመስጠት ቢሮው ይህን መመሪያ ለማስፈጸም ለክፍለ ከተማና ወረዳ የቤቶች አስተዳደር ጽቤት እንዲሁም ለሌሎች አስፈላጊ ተቋማት ውክልና ሊሰጥ ይችላል የመተባበር ግዴታ ማንኛውም ሰው ይህን መመሪያ ከማስፈጸም አኳያ የመተባበር ግዴታ አለበት መመሪያውን ስለማሻሻል ይህን መመሪያ ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊሻሻል ይችላል የተሻሩና ተፈፃሚነት ስለማይኖራቸው መመሪያዎች የመንግስት ቤቶች አስተዳደር መመሪያ ቁጥር በዚህ መመሪያ ተሽሯል ከዚህ መመሪያ ጋር የሚቃረን ማንኛውም መመሪያ ወይም ልማዳዊ አሰራር በዚህ መመሪያ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ ይህ መመሪያ ከነሐሴ ወር ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል ሰናይት ዳምጠዉ ኢር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ።