Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convertir en PDF
  • Liste de lecture
  • Abrégé
  • Livre audio
  • Chercher
  • Télécharger
  • myzon
  • S'identifier
  • registre
English  አማርኛ  Français  العربية
Livre du jour

የመንግስታት_ግንኙነት_ስርዓትን_ለመወሰን_የወጣ_አዋጅ.pdf


  • word cloud

የመንግስታት_ግንኙነት_ስርዓትን_ለመወሰን_የወጣ_አዋጅ.pdf
  • Extraction Summary

  • Cosine Similarity

አዋጅ ቁጥር ዓም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመንግስታት ግንኙነት ስርዓትን ለመወሰን የወጣ አዋጅ ረቂቅ የመንግስታት ግንኙነት ስርዓትን ለመወሰን የወጣ አዋጅ ሀገራችን ኢትዮጵያ ፌደራላዊና ዴሞክራሲያዊ የመንግስት አደረጃጀት ስርአትን የምትከተል እንደመሆኗ መጠን ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ዋስትና ያለው ዴሞክራሲን ለማረጋገጥ ፈጣን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማስቀጠልና አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብን ለመገንባት ይቻል ዘንድ ከተናጠል ጥረቶች ይልቅ የየእርከኑን አካላት አቅሞች በተገቢው መንገድ አቀናጅቶና አዋህዶ ዘርፈብዙ የልማትም ሆነ የመልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማከናወን የሚያስችሉ መደበኛ የመንግስታት ግንኙነቶችን በግልፅ መደንገግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በስራ ላይ ባለው ፌደራላዊ የመንግስት አደረጃጀት ውስጥ የፌደራልም ሆነ የክልል መንግስታት የተናጠልና የወል ስልጣንና ሀላፊነቶች በህገመንግስቱ ተለይተው የተቀመጡ ቢሆንም የየእርከኑ መንግስታት በወል ከተሰጣቸው ሀላፊነት ባሻገር በተናጠል በየተመደቡላቸው ስልጣንና ተግባራት ተቀራርቦና እርስ በርስ ተናቦ መስራትና ተገቢ ሆኖ ሲገኝ የጋራ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ነድፎ በዉጤታማነት ለመንቀሳቀስ የሚያግዝ ትብብራዊ የግንኙነት ማዕቀፍ እንደ ሚያስፈልጋቸው በመታመኑ በፌደራላዊ ስርዓተመንግስት ውስጥ በመንግስታት መካከል የሚካሄዱ የእርስ በርስ ምክክሮችና የሚደረጉ የትብብር ስምምነቶች ከስርዓቱ ባህርይ የሚመነጩ እንደ መሆናቸው መጠን ለስርዓቱ ዘለቄታ ተፈላጊ የሆኑ የጋራ አስተሳሰቦችን በመያዝና በማጠናከር ስርዓቱ በየጊዜው እየጎለበተ የሚሄድበትን አሰራር መዘርጋት በማስፈለጉ በፌደራልና በክልል መንግስታት እንዲሁም በራሳቸው በክልሎች መካከል እርስ በርስ ሲካፄዱ በቆዩ ግንኙነቶች አስከ አሁን የታዩትን ጥንካሬዎች ለማስቀጠልና ያጋጠሙ ወይም ወደፊት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ክፍተቶችን ለመሙላት ፌደራላዊ ስርዓቱንም ሆነ የሀገሪቱን ዲሞክራሲያዊ አንድነት ለማጠናከር ብሉም በየእርከነ መንግስታትና አቻ ተቋማቱ መካከል በመርህ ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የትብብር ስርዓት መፍጠር ለፌደራላዊ ስርዓቱ ጤናማነትና ቀጣይነት ጉልህ ድርሻ ያለው በመሆኑ አያንዳንዱ መንግስት የተሰጠውን ስልጣንና ፃላፊነት ለመወጣት የራሱን ዕቅድ በሚነድፍበትና በሚፈጽምበት ጊዜ በተናጠል ከመስራቱ የተነሳ የወጪ መደራረብና የጊዜ ብክነት እንዳይደርስና ከተገልጋዮች ፍላጎት መለዋወጥና ማደግ ጋር በተያያዘም የአገልግሉት አሰጣጥ ስታንዳርዶችን በጋራ በመንደፍና አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት እንዲሁም በክልሎች መካከል የልምድ ልውውጦችን በማካሄድ በመካከላቸው የሚታየውን ወጣገባነትና የጥራት ልዩነቶችን ማጥበብና ተቀራራቢ አፈፃፀም እንዲኖር ማድረግ ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ ለዚሁ ያመች ዘንድም የመንግስታት ግንኙነት ስርዓት የሚመራበት ራሱን የቻለ ህግ ማውጣትና ገቢራዊ ማድረግ በማስፈለጉ ይህ አዋጅ ታውዷል ክፍል አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አጭርርዕስ ይህ አዋጅ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመንግሥታት ግንኙነት ስርዓት መወሰኛ አዋጅ ቁጥር ዓም ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ትርጓሜ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ አዋጅ ውስጥ ክልል ማለት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገመንግስት አንቀፅ ስር የተጠቀሱት ሲሆን ለዚህ አዋጅ ዓላማ ሲባል በሕግ የተሰጣቸው ስልጣን እንደተጠበቀ ሆኖ የአዲስ አበባ ከተማና የድሬዳዋ አስተዳደሮችን ይጨምራል መንግስት ወይም መንግስታት ማለት እንደ አግባብነቱ የፌደራልና ወይም የክልል መንግስታትን ይገልጻል የመንግስታት ግንኙነት ስርዓት ማለት ይህንን አዋጅ በመከተል እንዳስፈላጊነቱ የፌደራልና የክልል መንግስታት በመካከላቸው አንዲሁም የክልል መንግሥታት በጋራ ወይም በጣምራ በተሰጣቸው ስልጣንና በሚያገናኙዋቸው ጉዳዮች ላይ የሚመሰርቱት የቀጥታ ወይም የጎንዮሽ ግንኙነት ሲሆን ግንኙነቶቹ የሚመሩበትን መርሆዎች አሰራሮችና አደረጃጀቶችን የሚያካትት ነው ግንኙነት መድረክ ማለት እንዳግባብነቱ ሀገርአቀፉ የህግ አዉጪ አካላት ግንኙነት መድረክ አገርአቀፉ የህግ አስፈፃሚዎች ግንኙነት መድረክ አገርአቀፉ የዳኝነት አካላት ግንኙነት መድረክ ሀገርአቀፉ የአስፈፃሚዎች ዘርፋዊ ግንኙነት መድረኮች የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የክልሎች ግንኙነት መድረክ ወይም የክልል መንግስታት ግንኙነት መድረክ ነው ሀገርአቀፍ የአስፈፃሚዎች ዘርፋዊ የግንኙነት መድረኮች የሚለው ሀረግ የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶችን ጨምሮ ማናቸውም የፌዴራልና አቻ ክልላዊ የዘርፍ አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የህግ አስከባሪና በፌዴራልና በክልል መንግስታት አወቃቀር ውስጥ ተመሳሳይ ተግባራትን የሚያከናዉኑ ሌሎች የዘርፍ መስሪያ ቤቶች በጋራና በሚያገናጃቸው ጉዳዮች ላይ ለመምከር በዚህ አዋጅ መሰረት የተቋቋመን መድረክ የሚያጠቃልል ነው የማፅቀፍ ስልጣን ማለት በአንዳንድ የስልጣን ዘርፎች ለፌደራልና ለክልል መንግሥታት ተመሳሳይ ስልጣንና ሀላፊነት የተሰጠበት የስልጣን ክፍፍል ስርዓት ሆኖ ክልሎች በዘርፉ የሚያወጧቸው መንግስታዊ ፖሊሲዎችና ሕጎች ከፌደራሉ መንግስት ፖሊሲዎችና ሕጎች ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ በማዕቀፍነት የሚያገለግል ስልጣን ነው ሴክሬታሪያት ማለት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመንግሥታት ግንኙነትን የሚመለከቱ ተግባራትን ለማስተባበርና ለማሳለጥ አስተዳደራዊና ቴክኒካዊ ጉዳዮችን እንዲያከናውን ዛላፊነት የተሰጠው አካል ነው ማንኛውም በወንድ ፆታ የተገለፀው የሴትንም ፆታ ይጨምራል የተፈጻሚነት ወሰን ይህ አዋጅ በፌደራልና በክልል መንግሥታት እንዲሁም በራሳቸው በክልል መንግሥታት መካከል በጋራ እና በጣምራ በተሰጣቸው ስልጣኖች ዙሪያ በሚካሄዱ ግንኙነቶች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ ስር የሰፈረው አጠቃላይ ድንጋጌ አንደተጠበቀ ሆኖ አዋጁ በተለይ ተፈጻሚ የሚሆንባቸው ቁልፍ የመንግስታት ግንኙነቶችና ተቋማት ከዚህ በታች የተመለከቱት ይሆናሉ ሀ በሀገርአቀፉ የህግ አውጪዎች ግንኙነት መድረክ አማካኝነት በፌደራልና በክልል መንግስታት መካከል የሚካሄድ ቀጥታ ግንኙነት ለ በሀገርአቀፉ የህግ አስፈጻሚዎች ግንኙነት መድረክ አማካኝነት በፌደራልና በክልል መንግሥታት መካከል የሚካፄድ ቀጥታ ግንኙነት ሐ በሀገርአቀፉ የሕግ ተርዓሚዎችግንኙነት መድረክ አማካኝነት በፌደራልና በክልል የዳኝነት አካላት መካከል የሚካፄድ ቀጥታ ግንኙነት መ የፌደራልና የክልል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶችን ጨምሮ በሀገርአቀፉ የዘርፍ አስፈፃሚ መድረኮች አማካኝነት በፌደራሉ መንግስት አስፈጻሚ አካላትና በክልል አቻዎቻቸው መካከል በተናጠል የሚካሄድ ከዘርፍተኮር ግንኙነት ሠ አንደ አጀንዳዎቹ ስፋትና ጥልቀት ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ወይም በሁሉም የክልል መንግሥታት የተናጠል ወይም የጋራ መድረኮች አማካኝነት የሚካፄድ ሁሉንአቀፍ ወይም ከዘርፍተኮር የጎንዮሽ ግንኙነት ረ በፌደሬሽን ምክር ቤትና በክልሎች መድረክ አማካኝነት የሚካፄድ የፌደራልና የክልል መንግስታት ግንኙነት ሰ እንደ አስፈላጊነቱ በዚህ አዋጅ መሰረት የሚካሄዱ ሌሎች ግንኙነቶች የሚደራጁ የጋራ መድረኮችና በተናጠልም ሆነ በጋራ የሚዋቀሩ የዚሁ ግንኙነት አሳላጭ ተጨማሪ አደረጃጾጀቶች ክፍል ሁለት መሰረታዊ መርሆዎች መስረታዊ መርሆዎች በዚህ አዋጅ መሰረት የፌደራልና የክልል መንግስታት እንዲሁም የክልሉች የርስበርስ ግንኙነቶች የሚከተሉትን መርሆዎች በጥብቅ በማክበርና በመከተል ይካሄፄዳሉ የሕገመንግሥትን የበላይነት ማክበር እኩልነትና የርስበርስ መከባበር ምክክርና ድርድር ሀገራዊ ራዕዮችንና ዕሴቶችን ማጎልበት ግልፅነትና ተጠያቂነት አሳታፊነትና ውጤታማነት ትብብርና የጋራ መግባባት ክፍል ሶስት ስለመንግስታት ግንኙነቶች ስርአት አመሰራረት ተቋማዊ አደረጃጀትና ተግባር ስለምስረ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መደበኛ የመንግስታት ግንኙነት ስርዓት ከዚህ በኋላ የመንግስታት ግንኙነት ስርዓት ተብሎ የሚጠራው በዚህ አዋጅ ተመስርቷል የመንግስታት ግንኙነት አደረጃጀት የመንግስታት ግንኙነት መድረኮች የሚከተሉት ናቸው ሀገርአቀፉ የሕግ አውጭዎች ግንኙነት መድረክ ሀገርአቀፉ የሕግ አስፈጻሚዎች ግንኙነት መድረክ ሀገርአቀፉ የህግ ተርጓሚዎች ግንኙነት መድረክ ሀገርአቀፉ የአስፈፃሚዎች ዘርፋዊ ግንኙነት መድረክ የፌደሬሽን ምክር ቤትና የክልሎች ግንኙነት መድረክና የክልል መንግሥታት የግንኙነት መድረኮች ንኡስ ክፍል አንድ ስለ ሀገርአቀፉ የሕግ አውጪዎች የግንኙነት መድረክ የመድረኩ አባላት ተዋጽኦ ሀገርአቀፉ የህግ አዉጪዎች የግንኙነት መድረክ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ለ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ጠ የየክልሉየአዲስ አበባ ከተማና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤቶች አፈጉባኤዎች መ የደቡብ ክልል ብሄፄሮችብሄረሰቦችና ህዝቦች ምክር ቤት አፈጉባኤ መድረኩ አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የፌደራልም ሆነ የክልል ምክር ቤቶች ቋሚ ኮሚቴዎች ሰብሳቢዎችና ሌሎች አካላት እንደ ተገቢነታቸው በአባልነት ወይም በአስረጂነት እንዲሳተፉ ሊጋብዝ ይችላል የመድረኩ ተግባርና ኃላፊነት ሀገርአቀፉ የህግ አዉጪዎች ግንኙነት መድረክ በዚህ አዋጅ መሰረትየሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶችይኖሩታል በሕገመንግስቱ ለፌደራልና ክልል መንግስታት በጋራ የተሰጡ ስልጣንና ኃላፊነቶችን ተፈፃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ እርስበርስ የተጣጣሙና የተመጋገቡ ሕጎች እንዲያወጡ ምክክር ያደርጋል አፈፃፀማቸውን ይከታተላል ይገመግማል በሕገመንግስቱ በተናጠል ህግ የማውጣት ስልጣን እንደተጠበቀ ሆኖ በየደረጃው የሚገኙ ምክርቤቶችይህንን ተግባራዊ ከማድረጋቸው በፊት ሌላኛውን የስልጣን እርከን በአሉታዊ መንገድ የማይጎዳ ስለመሆኑ ይመክራል መግባባት እንዲፈጠር ይጥራል ይኸው በተግባር ላይ መዋሉን ይከታተላል ፃሃገራዊ እንድምታ ባላቸው ጉዳዮች ላይ በመምከር የህዝቡን የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሕጎች እንዲወጡ ይመክራል አብሮነትን ያጠናክራል የፃገር ግንባታን ለማሳካት የተደነገጉ ሕጎችን አፈፃፀም በቅርብ ይከታተላል እንዲሁም በፌደራልና በክልል መንግሥታት የወጡ ወይም ወደፊት የሚወጡ ህጎችን ተቃርኖ በማስተካከል አንደኛው ከሌላው ጋር እንዲጣጣሙ የሚያደርጉ ተግባራትን ያከናውናል በፌደራሉ መንግስት ፖሊሲዎች ሕጎችና ስትራቴጂዎች ላይ ተቀራራቢ የአፈፃፀም ደረጃ እንዲኖር የጋራ መግባባት ይፈጥራል በአስፈፃሚ አካላት መካከል የተደረሱ ስምምነቶች ሕገመንግስታዊ ድንጋጌዎችን የተከተሉ ስለመሆናቸው በጋራ ይመክራሉ በአስፈፃሚዎች የጋራ ስምምነቶች ተግባራዊነትና አፈፃፀም ላይ ክትትል ያደርጋል የእርምት አርምጃዎች እንዲወሰዱ ይመክራሉ የሕዝብ ተወካዮችና የክልል ምክር ቤቶች አባላት የህዝብ ውክልና ግዴታቸውን ለመወጣት ወደመረጣቸው ህዝብ ወርደው ተግባርና ሀላፊነቶቻቸውን በጋራና በተቀናጀ መንገድ እንዲፈዕሙ ያስተባብራል አፈጻጸሙን ይከታተላል ንኡስ ክፍል ሁለት ስለ ሀገርአቀፉ የሕግ አስፈጻሚዎች የግንኙነት መድረክ የመድረኩ አባላት ተዋጽኦ ሀገርአቀፉ የህግ አስፈፃሚዎች የግንኙነት መድረክ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ለ የሁሉም ክልሎች ርአሳነመስተዳድሮች ሐ የአዲስ አበባ ከተማና የድሬዳዋ አስተዳደሮች ከንቲባዎች መድረኩ አስፈላጊ ነው ብሎ ያመነባቸው ሌሎች የፌደራል ወይም የክልል ተቋማት ኃላፊዎች እንደ ተገቢነታቸው በአባልነት ወይም በአስረጂነት እንዲሳተፉ ሊጋብዝ ይችላል የመድረኩ ተግባርና ኃላፊነት ሀገርአቀፉ የህግ አስፈፃሚ አካላት ግንኙነት መድረክ በዚህ አዋጅ መሰረት የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይኖሩታል የፌደራሉ መንግስትና የክልል አስፈፃሚ አካላት ግንኙነቶች የበላይ አካል ሆኖ ሁለቱንም የመንግስት እርከኖች በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ምክክሮችን ያደርጋል በሀገርአቀፍ የፖሊሲ ሀሳቦችና አጠቃላይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ዉይይትና ምክክሮችን ያካሂዳል በሀገርአቀፍ ፖሊሲዎች ስትራቴጂዎች ፕሮግራሞችና ፅቅዶች ላይ ውይይቶችን ያካሂዳል ይመካከራል ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት እንዲፈጠር ያደርጋል የተደረሰባቸውን የመግባቢያ ስምምነቶች አፈፃፀም በተቀናጀ መንገድ ይከታተላል ይገመግማል ይመራል ሀገራዊ አንድምታ ባላቸው የዘላቂ ሰላም የዲሞክራሲ የመልካም አስተዳደር እንዲሁም ፈጣንና ፍትዛዊ የማህበረኢኮኖሚያዊ ልማት ጉዳዮች ላይ ይመክራል በሚያጋጥሙ ችግሮች ዙሪያ የመፍትሄ ፃሳቦችን ያመነጫል በሕገመንግስቱ ለፌደራል መንግስቱና ለክልሎች በጋራ የተሰጡ ስልጣንና ኃላፊነቶችን ተፈፃሚ ለማድረግ የጋራ አፈፃፀም ስልት ይነድፋል ይገመግማል ይመራል የፌደራል መንግስት ስልጣንና ፃላፊነቱን በክልሎች ተግባራዊ ሲያደርግ ከክልሎች ጋር ይመክራል አስተያየቶቻቸውን ያዳምጣል በዘርፋዊ የአስፈፃሚ መድረኮች ደረጃ ዕልባት ያላገኙና ዘርፍ ተሻጋሪ የሆኑ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በነዚሁ ላይ ይመክራል ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ፃገርአቀፍ አገልግሎት በሚሰጡ ተቋማት የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ምክክር ያደርጋል እንዲሁም ክልሎች በውክልና በሚያከናዉኗቸው የፌደራሉ መንግሥት ስራዎች ላይ የወጪ አሸፋፈንን በተመለከተ ውይይትና ምክክር ያካሂዳል መመሪያዎችን ይሠጣል በመንግስታት ግንኙነት የፖሊሲ አፈጻጸምና ስትራቴጅያዊ ጉዳዮች ላይ ይወያያል ምክክሮችን ያካሂዳል መግባባት ላይ ይደርሳል አስፈላጊ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ስርዓተፆታ በሁሉም የመንግስታት ግንኙነቶች ተገቢውን ትኩረት ማግኘቱን ይከታተላል ንኡስ ክፍል ሶስት ስለሀገርአቀፉ የህግ ተርጓሚዎች የግንኙነት መድረክ የመድረኩ አባላት ተዋጽኦ ሀገርአቀፉ የህግ ተርጓሚዎች የግንኙነት መድረክ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ሰ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዚደንቶች መድረኩ አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የፌደራልም ሆነ የክልል የዳኝነት አካላት ወይም ሌሎች ተቋማት ባልደረቦች እንደ ተገቢነቱ በአባልነት ወይም በአስረጂነት እንዲሳተፉ ሊጋብዝ ይችላል የመድረኩ ተግባርና ሀላፊነት በሕገመንግስቱ አንቀፅ ስር የተደነገገውን የፍርድ ቤቶች ጣምራነትና የዉክልና ጉዳይ አስመልክቶ ቀደም ሲል ተቋቁመው በመስራት ላይ ያሉት ፍትህና ዳኝነትነክ የምክክር አካላት ባሉበት ሁኔታ ተጠናክረው የሚቀጥሉ ሲሆን በዚህ አዋጅ የተደራጀው መድረክ የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይኖሩታል የዳኝነት አካሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ተደራሽ ቀልጣፋና የተገልጋዩን ህብረተሰብ እርካታ በየጊዜው እየፈተሸና እያሳደገ በሚኬድባቸው አግባቦች ላይ ይመክራል የጋራ ስልቶችን ይነድፋል የሕግ የበላይነትና ፍትሃዊነት በሚረጋገጥባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ያካሂዳል አፈጻጸማቸውን በቅርብ ይከታተላል የፌደራል ሕጎች በክልል ደረጃ የተቀራረበ አተረጓጎም እንዲኖራቸው ምክክር ያደርጋል የመፍትሄ እርምጃዎችን ይወስዳል ነፃና ገለልተኛ የሆነና የሕዝብ አመኔታን ያተረፈ የዳኝነት ሥርዓት እንዲገነባ ይጥራል በውክልና በሚሰጥ የፌደራል የዳኝነት ስልጣንና ተያያዥነት ባላቸው ሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ያካሂዳል የአፈጻጸም ስልት ይቀይሳል ከዳኝነት ስርዓቱ ጋር በተገናኙ ጉዳዮች ላይ የአቅም ግንባታና ሌሎች የለዉጥ ፕሮግራሞች ተቀናጅተው እንዲፈፀሙ ያደርጋል መመሪያዎችን ይሰጣል የፍትህና የዳኝነት ስርአቱን ይበልጥ በሚያጎለብቱ ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ይወያያል ንኡስ ክፍል አራት ስለ ሀገርአቀፉ የአስፈቀፃሚዎች ዘርፋዊ የግንኙነት መድረክ የመድረኩ አባላት ተዋጽኦ ሀገርአቀፉ የህግ አስፈፃሚዎች ዘርፋዊ የግንኙነት መድረክ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ የየዘርፉ የፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች የበላይ ሀላፊዎች ለ የዘጠኙ ክልሎች እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማና የድሬዳዋ አስተዳደሮች የየዘርፉ መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎች መድረኩ አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የሌሎች አካላት ወይም ተቋማት ተወካዮች በስብሰባው ላይ በአባልነት ወይም በአስረጂነት እንዲሳተፉ ሊጋብዝ ይችላል የመድረኩ ተግባርና ኃላፊነት መድረኩ በዚህ አዋጅ መሰረት የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይኖሩታል በየዘርፉሀገርአቀፍ ጥቅሞችን በሚመለከቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በጋራ ይመክራል የክልሎችን ስልጣን ጥቅሞችና ፍላጎቶች በሚመለከቱ የፌዴራል መንግስት ዘርፍ ተኮር ፖሊሲዎች ስትራቴጂዎችና ዕቅዶች ዝግጅትና አፈፃፀም ላይ ይመክራል ክልሎች የሚሰጧቸውን ዛፃሳቦችና አስተያየቶች ያዳምጣል በጋራና በማዕቀፍ ስልጣኖች አተገባበር ዙሪያ የሚዘጋጁ የረዥም የመካከለኛና የአጭር ጊዜ ዕቅዶችና ፕሮግራሞች የሚቀናጁበትንና የሚተሳሰሩበትን ስርዓት ይፈጥራል በጋራ እንዲፈጸም ያደርጋል በየዘርፎቹ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና የአፈፃፀም ደረጃ ዙሪያ ውይይቶችን ያካሂዳል የጋራ ስልቶችን ይነድፋል በክልል ደረጃ በሚተገበሩ ዘርፍተኮር ሀገራዊ ዕቅዶችና ፕሮግራሞች ዝግጀት አፈጻፀም ክትትልና ግምገማ ላይ ይመክራል የምርጥ ተሞክሮዎች ልዉዉጥ የሚካፄድበትና ወደ ተቀራራቢ የአፈጻጸም ደረጃ የሚደረስበትን መንገድ በጋራ ይቀይሳል ይመክራል አፈጻጸሙን ይከታተላል በየክልሉ የሚመዘገቡትን የስራ አፈጻጸም ዉጤቶች ወደ ተመሳሳይ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የአቻ ግምገማ ሥርዓት በጋራ ይቀይሳል ተግባራዊ በሚሆንበት አግባብ ላይ ምክክር ያደርጋል አፈጻጸሙንም ይከታተላል የአስፈጻሚዉን ዘርፋዊ ተግባራት በሚያጠናክሩ ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ እንዳስፈላጊነቱ ይወያያል መመሪያዎችን ይሰጣል የጋራ ጉባኤ ስለማቋቋም ሁለትና ከዚያ በላይ የሆኑ ዘርፋዊ የአስፈፃሚ አካላት የግንኙነት መድረኮች አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኙት በጋራ የሚታቀፉበት አቢይ መድረክ ወይም ጉባኤ የማቋቋም መብት አላቸው ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቱንም የዚህን አዋጅ ድንጋጌዎች መንፈስ ተከትለው ሊወስኑ ይችላሉ ንኡስ ክፍል አምስት ስለፌደሬሽን ምክር ቤትና የክልሎች ግንኙነት መድረክ የመድረኩ አባላት ተዋጽኦ የፌደሬሽን ምክር ቤትና የክልሎች ግንኙነት መድረክ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ለ የየክልሉ ምክር ቤት አፈጉባዬዎች ሐ የየክልሉ ርዕሳነመስተዳድሮች መ የአዲስ አበባ ከተማና የድሬዳዋ አስተዳደሮች ከንቲባዎች ሠ የገንዘብ ሚኒስቴር ረ የሰላም ሜኒስትር ሰ የገቢዎች ሚኒስቴር መድረኩ አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የሌሎች አካላት ወይም ተቋማት ተወካዮች በስብሰባው ላይ በአባልነት ወይም በአስረጂነት እንዲሳተፉ ሊጋብዝ ይችላል የመድረኩ ተግባርና ኃላፊነት የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የክልሎች ግንኙነት መድረክ በዚህ አዋጅ መሰረት የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይኖሩታል የፌደራሉ መንግሥት ለክልሎች በሚሰጠው ድጎማ ቋትና ክፍፍል እንዲሁም በሕገ መንግስቱ ለፌደራልመንግሥቱና ለክልል መንግሥታት በተሰጡ የጋራ ገቢዎች ክፍፍል ላይይወያያልበመካከላቸው የርስበርስ መግባባት የሚፈጠርበትን ሁኔታ ያመቻቻል የብፄሮች ብሄረሰቦችና የህዝቦችን አብሮነትና የጋራ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በሚያስችሉ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይይመክራል እንዲሁምበመካከላቸው በሚታዩ የግንኙነት አዝማሚያዎች ላይ አስቀድሞ በመወያየት በየደረጃው ለሚገኙ አስፈፃሚ አካላት የሚጠቅሙ ምክረፃሳቦችን ይሰጣል በብፄርብፄረሰቦችና ህዝቦች በተለይም አናሳ ቁጥር ባላቸው ማህበረሰቦች አያያዝ ላይ ውይይቶችን ያካሂዳል ምርጥ ልምዶችን ያስፋፋል በአያያዝ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች ቢኖሩ በአፋጣኝ የሚፈቱባቸውን ስልቶች ይቀይሳል አፈጻጸማቸውንም በቅርብ ይከታተላል ይደግፋል በክልሎችና በተለያዩ ማህበረሰቦች መካከል ለግጭት መንስኤ በሚሆኑ ጉዳዮችና አፈታታቸው ላይ ምክክር ያደርጋልየተከሰቱና የተፈቱ ግጭቶችና አለመግባባቶች ቀጣይነት ያለው ቅራኔ በማይፈጥርና ወንድማማቻዊ ትስስሮችን ይበልጥ በሚያጎለብት መንገድ ለማስተካከል የሚያስችል ስልት ይነድፋል አፈጻጸሙን ይከታተላል ንኡስ ክፍል ስድስት ስለክልል መንግሥታት የግንኙነት መድረክ የመድረኩ አባላት ተዋጽኦ የክልል መንግሥታት የጋራ ግንኙነት መድረክ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ የየክልሉ ምክር ቤት አፈጉባዬዎች ለ የሁሉም ክልሎች ርፅዕሳነመስተዳድሮች ለ የአዲስ አበባ ከተማና የድሬዳዋ አስተዳደሮች አፈጉባዔዎች አና ከንቲባዎች መድረኩ አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የሌሎች አካላት ወይም ተቋማት ባልደረቦች በስብሰባው ላይ በአባልነት ወይም በአስረጂነት እንዲሳተፉ ሊጋብዝ ይችላል የመድረኩ ተግባርና ሃላፊነት የክልል መንግሥታት የጋራ ግንኙነት መድረክ በዚህ አዋጅ መሰረት የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይኖሩታል የሀገርአቀፍ ፖሊሲዎች ስትራተጂዎችና ዕቅዶች አፈፃፀም በክልሎች ላይ ያሳደራቸውን ወይም የሚያሳድራቸውን በጎና አሉታዊ ተፅእኖዎች ይገመግማል እንዳስፈላጊነቱ የማሻሻያ ሃሳቦችን ለፌደራል መንግሥቱ ያቀርባል በአንድ ክልል ውሳኔ ያገኘ ጉዳይ በሌሎች ክልሎች ተፈፃሚነት እንዲኖረው የጋራ መግባባት የሚደረስበትን አሰራር ይዘረጋል አተገባበሩን ይከታተላል በለልማት በመልካም አስተዳደርና በመሰረታዊ ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች አያያዝና አጠባበቅ ረገድ ተቀራራቢ አፈፃፀም አንዲኖር የጋራ ስልት ይቀይሳል የተሞክሮ ልውውጥ እንዲደረግ ሁኔታዎችን ያመቻቻል የፌደራል መንግሥቱን ልዩ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ይመክራል የተደረሰበትን የጋራ አቋም ለሚመለከተው አካል ያሳውቃል አፈጻጸሙንም ይከታተላል ክልሎችን በጋራ የማስተሳሰር ፋይዳ ያላቸውና ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች እንዲነደፉ ያደርጋል በተነደፉት ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች ጠቀሜታ ላይ ይወያያል የውሳኔ አስተያየቱን አግባብ ላለው አካል ያስተላልፋል የተለያዩ መድረኮችን ስለማቋቋም ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ተጎራባች ክልሎች እንዳስፈላጊነቱ ርአሳነመስተዳድሮችን ወይም የዘርፍ አስፈፃሚ አካላት የበላይ ፃላፊዎችን ያቀፉ የጋራ መድረኮችን የማቋቋም መብት አላቸው የነዚህ መድረኮች ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይህንን አዋጅ መሰረት አድርጎ በሚወጣ መመሪያ ይወሰናል ክፍል አራት የመንግሥታት ግንኙነት የስብሰባና የአሰራር ስነስርዓት የግንኙነት ትስስር የመንግሥታት ግንኙነት አደረጃጀቶችና ተግባራት ተቀናጅተው የሚመሩት በሚከተለው የአሰራር ስርዓት ይሆናል ሀገርአቀፍ የሕግ አስፈፃሚው እና የሕግ ተርጓሚው አካላት የግንኙነት መድረኮች አፈፃፀማቸውን ያጋጠሟቸውን ችግሮችና ሕግ እንዲወጣላቸውየሚፈልጓቸውን ጉዳዮች በሚመለከት ለሕግ አውጪው የግንኙነትመድረክ ያቀርባሉ ሀገርአቀፉ የአስፈፃሚዎች ግንኙነት መድረክም ከሴክሬታሪያቱ በሚቀርብለት ሪፖርት ላይ ከተወያየ በኋላ ውጤቱን ለሀገርአቀፉ የሕግ አውጭዎች ግንኙነት መድረክ ያስተላልፋል ሥ ሀገርአቀፉ የሕግ አውጪዎች ግንኙነት መድረክ በበኩሉ ከሀገርአቀፉ የአስፈፃሚዎች ግንኙነት መድረክ የተላለፈለት ሪፖርት የዳኝነት ስርአቱን የሚመለከት ሆኖ ያገኘው እንደሆነ ለሀገርአቀፉ የሕግ ተርጓሚ አካላት ግንኙነት መድረክ እንዲደርስ ያደርጋል ስለግልፅነትና የተጠያቂነት አሰራር በዚህ አዋጅ መሰረት የሚካፄዱ የመንግሥታት ግንኙነቶች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ዘዴዎች ተግባራዊ ያደርጋሉ የመንግስታት ግንኙነት መድረኮች ግንኙነት የተደረገባቸውን ጉዳዮች በሚመለከት በብዙሃን መገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት ለህዝብ ይፋዊ መግለጫዎችን ይሰጣሉ የመንግሥታት ግንኙነት መድረኮች የርስበርስ ምክክሮችን ካካሄፄዱ በላ ወሳኝ በሆኑ የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ የሚደርሱባቸውን ስምምነቶች ያሳለፏቸውን ውሳኔዎችና አፈፃፀማቸዉን የሚያሳዩ የመግባቢያ ሰነዶች ይፈራረማሉ ስምምነቶቹንም ለየምክር ቤቶቻቸው ያሳውቃሉ የአስፈፃሚዎች ዘርፋዊ የግንኙነት መድረኮች አፈፃፀማቸውን በተመለከተ ለሀገር አቀፉ የአስፈፃሚዎች ግንኙነት መድረክ ሪፖርት ያቀርባሉ የመንግስታት ግንኙነት መድረኮች በየደረጃው የሚያሳልፏቸውን ውሳኔዎች ተፈጻሚ በማያደርጉ አካላት ላይ እንዳግባብነቱ በትይዩ ለሚገኙ የክልል ርዕሳነመስተዳድሮችና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት በማድረግ ተገቢው የእርምት እርምጃ በወቅቱ አንዲወሰድ ያደርጋሉ ጉዳዩንም በብዙሀን መገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት ያጋልጣሉ ስለመወያያ አጀንዳዎች አቀራረፅና አቀራረብ በመንግሥታት ግንኙነት መድረኮች ውይይት የሚደረግባቸው ርዕሰጉዳዮች በሚመለከታቸው የመድረኩ አባላት ስምምነት ላይ የተደረሰባቸው ይሆናሉ የፌደራልም ሆኑ የክልል አካላት በመወያያ አጀንዳዎች አቀራረፅ ወቅት አኩል የመሳተፍ ዕድል ይኖራቸዋል አጀንዳ የመቅረፁን ሂደት የየመድረኮቹ ሴክሬታሪያቶች ያስተባብራሉ ስለ ስብሰባ አመራር የትኛውም የመንግስታት ግንኙነት መድረክ ስብሰባ በጋራ አመራር ይካሄዳል የፌደራል መንግስቱ የስራ ዛፃላፊዎች ሰብሳቢና የክልል አቻዎቻቸው በዙር በምክትል ሰብሳቢነት ይመራሉ ስለ ስብሰባ ጊዜና የውሳኔ አሰጣጥ ስነስርዓት የመንግሥታት ግንኙነቶች መድረክ መደበኛ ስብሰባውን በስድስት ወር አንድ ጊዜ ያካሂዳል ሆኖም እንዳስፈላጊነቱ አስቸኳይ ስብሰባዎችን ከማካፄድ በዚህ ድንጋጌ አይታገድም ከመድረኩ አባላት መካከል ኛ የሚሆኑት በስብሰባው ላይ ከተገኙ ምልአተጉባኤ ይሆናል ለግንኙነት መድረኮች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸውና ውሳኔ የሚሹ ጉዳዮች በተቻለ መጠን በስምምነት እና በድርድር አልባት እንዲያገኙ ይደረጋል ማናቸውም የውሳኔ ሃሳብ በስምምነትም ሆነ በድርድር የማይቋጭ ሆኖ የተገኘ እንደሆነ በስብሰባው ላይ በተገኙት የመድረኩ አባላት ሶስትአራተኛ ድምጽ የመጨረሻ ውሳኔ ያገኛል ክፍል አምስት ስለሀገርአቀፍፉ የመንግስታት ግንኙነት ሴክሬታሪያትና ሌሎች ፅህፈት ቤቶች መቋቋምና ተግባር ስለ ሴክሬታሪያቱ መቋቋምና ተጠሪነት በሀገርአቀፍ ደረጃ የመንግስታት ግንኙነትን የሚያስተባብር ህጋዊ ሰውነት ያለው ከዚህ በኋላ ሴክሬታሪያቱ እየተባለ የሚጠራ አካል በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል የሴክሬታሪያቱ ተጠሪነት ለሀገርአቀፉ የሕግ አስፈፃሚዎች የግንኙነት መድረክ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል የፌደራልና የክልል መንግሥታት በጋራ ተስማምተው ሴክሬታሪያቱን የሚመሩ ተዷሚዎችን ይመድባሉ ሴክሬታሪያቱ ለስራው አስፈላጊ ባለሙያዎችና ሌሎች ሰራተኞች ይኖሩታል ለሴክሬታሪያቱ ስራ ማስኬጃ የሚያስፈልገዉን በጀት የፌደራልና የክልል መንግሥታት በማዋጣት በጋራ ይመድባሉ ዝርዝሩ ይህንን አዋጅ ለማስፈፀም በሚወጣ ደንብ ይወሰናል የበጀት አፈፃፀሙን ኦዲት በተመለከተ ክልሎችና የፌደራሉ መንግሥት በጋራ ተስማምተው በሚሰይሙት አካል እንዲከናወን ሊያደርጉ ይችላሉ የሴክሬታሪያቱ ተግባርና ኃላፊነት ሴክሬታሪያቱ በዚህ አዋጅ መሰረት የሚከተሉት ተግባርና ፃላፊነቶች ይኖሩታል መንግሥታቱ በጋራ የነደፏቸውን ፕሮግራሞች ዕቅዶችና የደረሱባቸዉን ስምምነቶች አፈፃፀም ይከታተላል የመንግሥታት ግንኙነትን የሚመለከቱ ተግባራትን የማስተባበርና የማሳለጥ እንዲሁም ሙያዊና ቴክኒካዊ ስራዎችን ያከናውናል ግንኙነቶቹ ለስርዓቱ መጎልበት ለህብረቱ መጠናከርና ለህዝቦች ወዳጃዊ ትስስር የሚያስገኙትን ፋይዳ ያጠናል መድረኮቹ በሀብት አጠቃቀምና በጥራት ረገድ ውጤታማ እንዲሆኑ ይሰራል የየመድረኮቹን ውጤታማነት በመከታተል በግንኙነቶቹ ዙሪያ የሚታዩትን ክፍተቶች በጥናት ላይ ተመስርቶ ይለያል ግንኙነቶችን የተመለከቱ የዳሰሳ ጥናቶችን በማካሄፄድ የአፈፃፀም ሪፖርቶችን የመፍትፄ ፃሳቦችን እያዘጋጀ ለሀገርአቀፉ የአስፈፃሚዎች ግንኙነት መድረክ ያቀርባል አለመግባባቶችንና ግጭቶችን ሊፈጥሩ የሚችሉ ጉዳዮችን አስቀድሞ በመለየት የመድረኩ የትኩረት አጀንዳዎች እንዲሆኑ ያደርጋል በመንግሥታቱ መካከል የመረጃ ልውውጡ ሳይቋረጥ እንዲሳለጥ ይሰራል በተመሳሳይ ጉዳዮች የሌሎች ፌደሬሽኖች ልምዶችን በመቀመርና ከሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር በማጣጣም በጥቅም ላይ እንዲውሉ ፃሳብ ያቀርባል ሲወሰንም ይህንኑ ተከታትሎ ያስፈጽማል በመንግሥታት ግንኙነቶች ዙሪያ የሚታዩ የግንዛቤ ክፍተቶች እንዲቀረፉ ትምህርታዊ ማብራሪያዎችን ይሰጣል በየደረጃሻው የተቋቋሙ መድረኮችና ሌሎች አደረጃጀቶች እንዲጠናከሩ ሙያዊ ድጋፍ ይሰጣል ግንኙነቶቹን የሚያጠናክሩና በሀገርአቀፉ የአስፈጻሚዎች ግንኙነት መድረክ የሚሰጡትን ሌሉች ተዛማች ተግባራት ያከናውናል ስለ ሌሎች ፅህፈት ቤቶች መቋቋም በዚህ አዋጅ መሰረት የተቋቋሙትን የቀጥታም ሆነ የጎንዮሽ መንግሥታዊ ግንኙነቶችና በየዘርፉ የተደራጁትን መድረኮች የሚያስተባብሩ የተለያዩ ጽህፈት ቤቶች እንዳስፈላጊነቱ ሊቋቋሙ ይችላሉ የክልሎችና የሌሎች መድረኮች ፅህፈት ቤቶች ተግባርና ኃላፊነት በዚህ አዋጅ መሰረት የተቋቋሙ የክልልና የዘርፍ መድረኮች ጽህፈት ቤቶች የሚከተሉት ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች ይኖራቸዋል የመንግሥታት ግንኙነት ስርዓቱን አጠቃላይ ጤናማነትና ውጤታማነት ይከታተላሉ በመንግሥታቱ ግንኙነቶች ዙሪያ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ያካሂዳሉ ግንኙነቶችን የሚመለከቱ የአፈፃፀም ሪፖርቶችን እያዘጋጁ ለጋራ መድረኮች ያቀርባሉ ግንኙነቶችን የሚመለከቱ የድጋፍ አገልግሎቶችን ይሰጣሉ የግንኙነቶቹን አካፄድና ውጤታማነት በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሀንና ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ወቅታዊ መረጃዎችንና ማብራሪያዎችን ይሰጣሉ የየመድረኮቹን ስብሰባዎች ያመቻቻሉ የመንግሥታት ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን ያከናዉናሉ ስለ ሌሎች ኮሚቴዎች የመንግሥታት ግንኙነት መድረኮች ስራዎቻቸዉን ለማሳለጥ የሚያግዙ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን እንዳስፈላጊነቱ ሊያቋቁሙ ይችላሉ የኮሚቴዎቹ ተጠሪነት ለያቋቋሟቸው የግንኙነት መድረኮች ይሆናል የነዚህ ኮሚቴዎች ዝርዝር ተግባርና ሀላፊነቶች በያቋቋሟቸው አካላት ይወሰናሉ ክፍል ስድስት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት ስለማይኖራቸው ህጎች ይህንን አዋጅ የሚቃረን ማናቸውም ህግ ደንብ መመሪያ ወይም የተለመደ አሰራር በዚህ አዋጅ ውስጥ በተሸፈኑት ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት አይኖረውም መመሪያ የማውጣት ስልጣን ሀገርአቀፉ የህግ አስፈጻሚዎች የግንኙነት መድረክ ይህንን አዋጅ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉትን መመሪያ የማውጣት ስልጣን አለው ይህንን አዋጅና በአዋጁ መሰረት የሚወጡትን ዝርዝር መመሪያዎችን በአዋጁ የተቋቋሙትና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሌሎች የመንግሥታት ግንኙነት መድረኮች ሊያወጡ ይችላሉ አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ በፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል አዲስ አበባ ቀን ዓም ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ ፕሬዚደንት።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Commentaires:


memezon

Options de téléchargement | Convertir en PDF | Livre du jour

© dirzon | Conditions d'utilisation | Intimité | Sur | Services | Contact