Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
በ ሀከልዐ በወንጀል ጉዳይ ወንጀል የተፈፀመበት መሳሪያ ወይም የወንጀል ውጤት የሆነ ነገር በማስረጃነት ሳይቀርብ ሊታለፍ ይችላል ወይም ምስክሮች ሳይገልፁት ሊያልፉ ይችላሉ ወይም ድርጊቱን ፈፀመ በሚል ስሙን የገለፁትን ሰው እንዲያሳዩ ሲጠየቁ ማሳየት ሊያቅታቸው ይችላል ይህ በምስክሮች ቃል ምዘና ላይ የሚያስከትለው ተፅዕኖ ምንድ ነው። ይላዲሦ ኔቾደ«ቻ ምሃና ቦሟመሰቋገራ ሦጨማሪ ኃጎሪጋቻ የገንዘብ ወይም የንብረት ጉድለትን ለማስረዳት የኦዲት ምርመራ ውጤቶች በማስረጃነት የሚቀርቡበት አጋጣሚ በርካታ ነው እነዚህ ጽሁፎች ውስጥ የተጠቀሱትና ማስረጃ ናቸው የተባሉት ፍሬ ነገሮችን በማመን ወይም በማስተባበል መልስ ያልተሰጠባቸው መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ው እንዲሁም ከችሎት ውጪ የታመነ ፍሬ ነገር ከተከሳሹና መከላከያ ማስረጃዎች አንፃር መመዘን አለበት በመጨረሻም ታምኖአል ወይም አልታመነም በሚል ለመወሰን የታመነ ነው በሚል የተሰጠው ቃል አስረጅነት በተያዘው የፍትሐብሔር ጉዳይ የአስረጅት መመዘኛ ደረጃ አንፃር መታየት አለበት መመዉደዖ ሜምጭዎሥቻ በፍብሥሥህቁ ላይ በግልፅ የተካደ ባይሆንም በአነጋገሩ ስልት እንደተካደ የሚቆጠር ሲባል ምን ማለት ነው። በዚሁ በቁጥር ላይ ፍርድ ቤቱ አስፈላጊና ተገቢ ሆኖ የሚያገኘው መቼ ነው።
ሳይጠቀሱ የታለፉ ፍሬ ነገሮች የሚያስከትሉት ዉጤት ጥቅም ያላቸው ምስክሮች የምስክርነት ቃል ምዘና የሰነዶችንና ኤግዚቢት ማስረጃዎችን አስረጂነት ስለመመዘከን የጽሁፍ ሰነድ ማስረጃዎች ምዘና ህህ ንን ንዓ ንዓ ንን ሄን ሄሄ ቴቴ ሄቴ ንዓ መ እ እ እ ከን ተ ከ ከ ከ ተ ተ ተ ተ ተ ተ ዜን ን ን ተን ሄሄ ንቴ ንቴ ቆቴ ንቴ ሄሄ ፋፋ ቆቴ ፋቀ ቀራን የእምነት ቃል አስረጂነትን ስለመመዘን ራነሑ « ሄለን ሄ ሄሄ ቴሄዜዜሄዜቴዜን መግቢያ በፍርድ ቤት ክርክር የሚደረግባቸው ጉዳዮች ሁሉ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ማስረጃን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን የሚያስነሱ ናቸው ለማለት ይቻላል ውሳኔ ሊሰጥባቸው የተፈለጉት ጭብጦች ህግን የሚመለከቱ ቢሆኑ እንኳ ወደ ህግ ጭብጥነት ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ፍሬ ነገሮችን የሚመለከቱ ጭብጦችን እንደሚያስተናግዱ የሚታወቅ ነው ፍሬ ነገሮቹን የሚመለከቱት ጭብጦች የሚረጋገጡት ወይም የሚሰተባበሉት ደግሞ በማስረጃ አማካኝነት ነው በሌላ በኩል ደግሞ የፍሬ ነገሮችን መኖር ወይም የመደምደሚያን ትክክለኝነት ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ያስችላል ተብሎ የቀረበ ማስረጃ ሁሉ እንደተባለው ያረጋግጣል ወይም ያሰተባብላል ለማለት እይቻልም በሥራ ሂደት ትልቅ ችግር ሆኖ የሚታየው ማስረጃን የመመዘን ጉዳይ ነዉ የቀረበዉ ማስረጃ እውነተኛ ወይም ትክክለኛ ላይሆን ይችላል ወይም እውነተኛ ወይም ትከክለኛ ቢሆን አንኳን ያስረዳዋል ወይም ያስተባብለዋል የተባለውን ፍሬ ነገር ወይም የተደረሰ መደምደሚያ በተፈለገው ደረጃ ላያስረዳ ይችላል ስለዚህም ማስረጃውን የሚቀበለው ፍርድ ቤት የቀረበለትን ማስረጃ የመመዘን ኃላፊነት ይወድቅበታል የሚመዝነው ደግሞ በአንድ በኩል በማስረጃነት የተገለፀው ፍሬ ነገር እውነተኛ ወይም ትከክለኛ መሆን አለመሆኑን ለማጣራት ነው ማለትም ውሳኔ ለመስጠት ተገቢ የሆነውን ፍሬ ነገር መኖር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል በማስረጃነት የቀረበው ፍሬ ነገር እውነት ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ያጣራል በሌላ በኩልም የተባለው ማስጃ እውነተኛ ወይም ትክክለኛ ነው ቢባል ውሳኔ ለመስጠት ተፊላጊ የሆነውን ፍሬ ነገር ወይም ጭብጥ በሚፈለገው ደረጃ ማስረዳቱን ወይም ማስተባበሉን ያጣራል ስለዚህም የቀረበው ማስረጃ በሚፈለገው ደረጃ አስረድቷል ወይስ አላስረዳም ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ የማስረጃ ምዘና ተግባራትን ማከናወን ይጠበቅበታል የዚህ ፅሁፍ ዝግጅት ዋነኛ ትኩረትም ማስረጃዎችን በዓይነት ለይተዉ አዉቀዉ በሥራ ወቅት በወንጀልና በፍትሐብሔር ጉዳዮች የማስረጃ ምዘና ሲከናወን ግምት ውስጥ ሊገቡ የሚገባቸውን መሠረታዊ ነጥቦችን በማንሳት የሰልጣኞችን ግንዛቤ በማስፋት ወደሥራ በሚገቡበት ወቅት ሳይቸገሩ ኃላፊነታቸዉን እንዲወጡ ለማስቻል ነዉ ሠልጣኞች ከቅርብ አሰልጣኞቻቸዉ ጋር በመሆን ብዙ ነጥቦችን በዉይይት እንደሚያዳብሩም ይጠበቃል በዚህም መሠረት ማስረጃ ሲመዘን ከቀረበው ማስረጃ እና ከጉዳዩ ዓይነት አንፃር የማስረጃውን እውነተኛነት ወይም ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ምንምን ነገሮችን ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባ እንዲሁም ለጉዳዩ አግባብነት ካለው የአስረጅነት ደረጃ አንፃር የቀረበው ማስረጃ ተፈላጊውን ፍሬ ነገር አስረድቷል ለማለት የሚበቃው ምን ዓይነት መመዘኛዎችን ሲያሟላ እንደሆነ የፍርድ ቤት መዘግብትን እና ተሞክሮዎችን መሠረት በማድረግ ይገለጳል ዝግጅቱ በሦስት ክፍሎችና በዘጠኝ ምዕራፎች የተከፋፈለ ነው በክፍል አንድ ሥር የተካተቱት ሁለት ምዕራፎች ምዕራፍ እና ማስረጃን በሚመለከት አጠቃላይ ግንዛቤ የሚሰጡ ናቸው ማስረጃ ምን ማለት አንደሆነ ለምን እንደሚያስፈልግ ዓይነቶቹን በልዩ ሁኔታ ማስረጃ ማቅረብ የማያስፈልጋቸው ፍሬ ነገሮች በአጭሩ ይገለፃሉ በክፍል ሁለት ሥር የተካተቱት ሦሰት ምዕሪፎች ከምዕራፍ የማስረጃ አቀራረብን የሚመለከቱ ሲሆን ለፍርድ ቤት መቅረብ የሚችሉት ምን ዓይነት ማስረጃዎች እንደሆኑ ማን እና እንዴት እንደሚያቀርባቸው እንዲሁም ችሎት የቀረቡት ማስረጃዎች የገለፀት ፍሬ ነገር እንዴት እንደሚሰበሰብ መሠረታዊ ነጥቦች ይገለፀሉ ሦሰተኛውና የጽሁፉ አብይ ክፍል ማስረጃ መመዘንን የሚመለከት ሆኖ በዚህ ሥር ከተጠቃለሉ አራት ምዕራፎች በመጀመሪያው ምዕራፍ ሥር በወንጀልና በፍትሐብሔር ጉዳዮች ላይ ያስረዳል ተብሎ የሚቀርብ ማስረጃ አስረድቷል ለማለት ማሟላት የሚጠበቅበት ተፈላጊው የአስረጅነት ደረጃ ምን እንደሆነ የሚገልፅ ሲሆን በተከታዮቹ ሦስት ምፅራፎች ደግሞ በምዕራፍ ላይ የተገለፀውን የአስረጅነት ደረጃ ማሟላት አለማሟላታቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ዐይነት ማስረጀዎች እንዴት ሊመዘኑ አንደሚገባ እና ማስረጃዎቹ ሲመዘኑ ግምት ውስጥ መግባት የሚኖርባቸው ጉዳዮች ይገለፃሉ ሲሆን ዓላማቸውም የሥልጠናው ተካፋዮች እነዚህን ጥያቄዎች መሠረት በማድረግ የቡድን ውይይት አንዲያደርጉና ልምድ አንዲለዋወጡ ማስቻል ነው አጠቃላይ የስልጠናው አላማ የትምህርቱ ዓላማ የፍትህ ሥርዓቱን በዳኝነትን በዐቃቤ ህግነት ለሚያገለግሉ ባለሙያዎች በማስረጃ ህግ በቂ ግንዛቤና ተግባርን ያተኮረ ክህሎት ማዳበር በመሆኑ ስልጠናዉ ሲጠናቀቅ ስለማስረጃ ሕግ ፅንሰ ሀሳብ በቂ ግንዛቤ ይኖራቸዋል በወንጀልን በፍታብሔር ጉዳዮች የማስረጃን ተቀባይነት አግባብነትና አቀራረብ በተመለከተ በቂ እዉቀት ያገኛሉ የተለያዩ ዓይነት ማሰረጃዎች በወንጀል እና በፍታብሔር ጉዳዮች እንዴት እንደሚመዘኑ ተገቢ ክህሎት ያዳብራሉ ዝርዝር ዓላማዎች የማስረጃ ዓይነቶችን ልዩነቶችን እና አስፈላጊነትን ለይተዉ ይገልፃሉ ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የሚሆንባቸዉን ጉዳዮች እና አስፈላጊ የማይሆንባቸዉን ጉዳዮች ለይተዉ ያዉቃሉ ሥራ ላይ ያዉላሉ የተለያዩ የህግ ሥርዓቶች የሚከተሉ አገሮች ማስረጃ እንዴት እንደሚመዝኑ በቂ ግንዛቤ ይጨብጣሉ ከአገራችን አፈፃፀም ጋር ማዛመድ ይችላሉ ጻ በወንጀልም ሆነ በፍታብሔር ጉዳዮች ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ ቢሆንም እንኳ መቅረብ የሚገባቸዉ አግባብነት እና ተቀባይነት ያላቸዉ ማስረጃዎች ብቻ መሆናቸዉን ምን ዓይነት ማስረጃዎች አግባብነት እንዳላቸዉ እና ለፍርድ ቤት እንዴት መቅረብ እንዳለባቸዉ ለይተዉ አዉቀዉ በተግባር ሥራ ላይ ማዋል ይችላሉ በወንጀልም ሆነ በፍታብሔር ጉዳዮች ማስረጃ ማን መቼ እና እንዴት ማቅረብ እንደሚገባቸዉ ያዉቃሉ ተግባራዊ ልምምድ በማድረግ በዚሁ መሠረት መሥራት ይችላሉ የማስረጃ አስረጅነት መመዘኛዎችን እንዲሁም በፍታብሔርና በወንጀል ጉዳየች መካከላ ያለዉን የመመዘኛ ልዩነት ያዉቃሉ ይህንን የሚመለከቱ መመዘኛ ጉዳዮችን በተግባር ሥራ ላይ ያዉላሉ በተለይ በወንጀልና በፍትብሔር ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ ማስረጃዎች ሲመዘኑ ትኩረት ዉስጥ መግባት ስለሚያስፈልጋቸዉ መሠረታዊ መርሆዎች ያዉቃሉ በፍታብሔርም ሆነ በወንጀል ጉዳይ የቀረቡ ምስክሮችን የመመርመር ክህሎት ያዳብራሉ የተለያዩ ዓይነት ማስረጃዎችን በወንጀልም ሆነ በፍታብፄር ጉዳይ ሲቀርቡ መዝነዉ አሳማኝነታቸዉን በመለየት መጠቀም ይችላሉ ክፍል አንድ ስለማስረጃ አጠቃላይ ግንዛቤ ምዕራፍ የማስረጃ ጽንሰ ሐሳብ አስፈላጊነትና ዓይነቶች ዝርዝር አላማዎች ሰልጣኞች ይህንን ምእራፍ ሲያጠናቅቁ የማስረጃን ፅንሰ ሀሳብ ይረዳሉ የማስረጃ ዓይነቶችን የመለየት ጠቀሜታ ከህግ ሥርዓቶች ተሞክሮ አንፃር ጠንቅቀዉ ያዉቃታሉ በአገራችን ያለዉን ተግባራዊ አፈፃፀም ፈትሸዉ አዉቀዉ በሥራ ላይ ተገቢዉን ጥንቃቄ ያደርጋሉ ያማዕረያጽያኀጎያ ዉድ ሰልጣኞች ማስረጃ ምንድነው። በ ሀ ርበርህቨበ የሚረዳ በመሆኑ ነው በዚህም መሠረት ከማስረጃ ምንነት ጋር በተያያዘ የሚከተሉትን ማስተዋል ተገቢ ነው በመጀመሪያ ደረጃ ፍሬ ነገርን ወይም መደምደሚያን ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ ይሁን እንጂ ማስረጃ ራሱ ፍሬ ነገር መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ይህም ማለት ማስረጃ የፍሬ ነገርን መኖር ወይም መደምደሚያን ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ እንጂ የህግ ጉዳይን ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ አይደለም ሕግን የሚመለከት ክርክር የተነሳ እንደሆነ ውሳኔ የሚያገኘው ሕጉን በመመርመር ነው እንጂ ማስረጃ በማቅረብ አይደለም ማስረጃ የህግ ክርክርን ለማስረዳት የሚቀርብ አይደለም በሁለተኛ ደረጃ ማስረጃን ለማስረዳት ከምንጠቀምባቸው ዘዴዎች መለየት ያስፈልጋል ከላይ እንደተገለፀው ማስረጃ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም የመደምደሚያን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ሲሆን በኋላ እንደሚገለፀው ይህንን ፍሬ ነገር ለፍርድ ቤት ለመግለፅ የምንጠቀምባቸው መንገዶች ወይም ዘዴዎች ምስክር አቅርቦ ማሰማት ወይም ሰነድ አቅርቦ ይዘቱን ማሳየት ወይም አንድ ፅቃ አቅርቦ ፍርድ ቤት ግንዛቤ እንዲወሰድበት ማድረግ ሊሆኑ ይችላሉ ለፍርድ ቤቱ የተገለፀው ወይም ፍርድ ቤቱ አይቶ የተገነዘበው ፍሬ ነገር ምሰክሩ የተናገረው ቃል ወይም የሰነዱ ይዘት ወይም መልዕክት ወይም ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ዕቃ አይቶ የወሰደው ግንዛቤ ማስረጃ ፎህበር ሲሆን ይህንን ማስረጃ ፍርድ ቤቱ አንዲያውቀው ለማድረግ የቀረቡት ምስክሮች ሰነዶች ወይም ዕቃዎች ወዘተ ደግሞ ዘዴዎች ዞበ ይባላሉ በአንግሊዝ አሜሪካ በህንድ የማስረጃ ህጐችና ሰለማስረጃ የተፃፉ ጽሑፎች ላይ ማስረጃን ዐበር ከዘዴው ዞከ ለይቶ መጠቀም የተለመደ ሲሆን የአገራችን ህጐችም ይህንን ልዩነት ግምት ውሰጥ ያስገቡ የሚመስሉ ድንጋጌዎችን ይዘዋል ለምሳሌ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዐት ቁጥር ርዕስ ማስረጃን በመዝገብ ስለመፃፍ ይልና ዝርዝሩ ሲታይም ማስረጃ ተብሎ በመዝገቡ ውስጥ የሚፃፈው ምስክሮች የተናገሩት ቃል መሆኑን ይገልባል ሌሎችም በርካታ ልዩነቱን አመልካች የሆኑ ድንጋጌዎች ይኖራሉ በፍርድ ቤቶችና በዐቃቤ ህግ መስሪያቤቶች ያለው ልማድ ሲታይ ግን ማስረጃ የሚለውን ቃል ፍሬ ነገሩንና የተጠቀምንበትን ዘዴ እንዲገልፅ በመለዋወጥ መጠቀም የተለመደ በመሆኑ በዚህ ጽሑፍም በዚሁ በተለመደው መልክ በተለዋዋጭነት መጠቀሙ የሚቀጥል ሲሆን የትኛውን ሐሳብ ለማመልከት አንደተፈለገ ከቃሉ አገባብ በቀላሉ መለየት ይቻላል መ ያማዕረያይኑዶቻ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም የመደምደሚያን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ከሚቻልባቸው ዘዴዎች እና ማስረዳት ከሚፈለገው ፍሬ ነገር ወይም መደምደሚያ ጋር ማስረጃው የሚኖረውን ግንኙነት መሠረት በማድረግ ማስረጃን በተለያዩ መንገዶች ክፋፍሎ መረዳት ይቻላል ፍሬ ነገርን ለማስረዳት ከምንጠቀምበት ዘዴ አንፃር ማስረጃን የምስከርነት ማስረጃ ከጠዐበከ። ዐበር ነው የሚባለው የሰሚ ሰሚ ማስረጃን ቀጥተኛ ያልሆነ የሚያሰኘው ማስረጃው ፍሬ ነገሩን የሚገልፀው ራሱ በቀጥታ እንዳወቀው ሳይሆን ከሌላ ሰው የሰማው ወይም ከሰነድ ያነበበው በመሆኑ ነው በሰነድ ማስረጃም በኩል የሰሚ ሰሚ የሚያሰኘው ማስረጃ ሆኖ የቀረበው ሰነድ ላይ የተገለፀው ፍሬ ነገር ስለዚህ ፍሬ ነገር አውቃለሁ በሚል ሌላ ሰው የተዘጋጀ መሆኑ ነው ሁለተኛው ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ ነው የሚባልበት ሁኔታ የሚያጋጥመው አከባቢያዊ ማስረጃ ርቭርህበበቨበቨጪቨ ጅሯህበር የቀረበ እንደሆነ ነው አከባቢያዊ ማስረጃ በጭብጥ ስለተያዘው ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር በቀጥታ አይነግረንም ይልቁንም የተወሰኑ ፍሬ ነገሮችን መኖር ወይም አለመኖር በማረጋገጥ ከዚህ ተነስተን በጭብጥ የተያዘውን ፍሬ ነገር በተመለከተ አንድ አይነት መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ የሚያደርግ ነው ጠመንጃ ተኩሶ ሰው ገድሏል በሚል ዐቃቤ ህግ ላቀረበው ክስ የቀረቡት ማስረጃዎች የሚገልፁት ተከሳሹ ተኩሶ ስለመግደሉ ሳይሆን ተከሳሹ ከሟች ጋር ፀብ እንደነበረው ሟች ከመሞቱ ጥቂት ጊዜ አስቀድሞ ተከሳሹ ከብት ሸጦ ጠመንጃ እንደገዛ ሟች ተገደለ ከተባለ በኋላ ተከሳሹ ከአካባቢው ተሰውሮ ቆይቶ በፖሊስ ክትትል መያዙን ቢሆን ስለዋናው ክስ ጉዳይ በቀጥታ አይናገሩም ስለአከባቢያዊው ሁኔታ ይናገራሉ እነዚህ ማስረጃዎች ከራሳቸው ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን ውሳኔ ስለሚሰጥባቸው ፍሬ ነገሮች መኖር ወይም አለመኖር አንድ ዓይነት ግምት ለመውሰድ ያስችላሉ ለማጠቃለል አካባቢያዊ ማስረጃን ቀጥተኛ ያልሆነ የሚያሰኘው በማስረጃነት የተገለፀው ፍሬ ነገር በጭብጥ ስለተያዘው ፍሬ ነገር በቀጥታ የሚናገር ወይም የሚገልፅ ሳይሆን ሌሎች ፍሬ ነገሮችን በመግለፅ በጭብጥ ስለተያዘው ፍሬ ነገር ግምት እንዲወሰድ የሚያደርግ መሆኑ ነው ማስረጃን ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆነ በሚል ከፋፍሎ ማየት ለምን አስፈለገ። በመሠረታዊነት የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ማረጋገጥ የሚቻለዉ ማስረጃ በማቅረብ ነዉ ነገር ግን ይህ መሠረታዊ መርህ የማይመለከታቸው ልዩ ሁኔታዎች አሉ ማለት ከፍሬ ነገሮቹ የተለየ ባህሪይ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸው ሁኔታዎች አሉ እነዚህም ሩ ፍርድ ቤት ግንዛቤ ሊወሰድባቸው የሚችሉ ወይም የሚገቡ ፍሬ ነገሮች እንዲሁም ሩ በፍርድ ቤት በሚደረግ የክርክር ሒደት በተከራካሪ ወገን የታመኑ ፍሬ ነገሮች ናቸው እነዚህን ሁኔታዎች በቅድሚያ መረዳት የተያዘውን ጉዳይ በአግባቡ ለመወሰን አስፈላጊ ነው አንድ ፍርድ ቤት ማስረጃ መቀበል ሳያስፈልገው ለጉዳዩ አወሳሰን ተገቢ የሆነውን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ግንዛቤ ሊወስድበት የሚገባ ነው ወይም የታመነ ነው የሚል አቋም መውሰድ እንዲችል ማድረግ ያስፈለገውም በተለያዩ ምክንያቶች ነው በመጀመሪያ ደረጃ በታወቀ ፍሬ ነገር ወይም አከራካሪ ያልሆኑ ማረጋገጫዎች በመመልከት መወሰን በሚቻል ፍሬ ነገር ላይ ማስረጃ መቀበሉ ትርጉም ስለማይኖረው ነው በይፋ የታወቀ ወይም አከራካሪ ያልሆነ ማረጋገጫን መሠረት በማድረግ በቀላሉ ሊረጋገጥ የሚችል ሆኖ እያለ ተከራካሪዎች ግን ሊካካዱበት ይችላሉ ይህንን መከልከል አይቻልም ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ራሱ ግንዛቤ ሊወሰድበት የሚችል ወይም የታመኑ ምንጮችን መሠረት በማድረግ መደምደሚያ ላይ መድረስ እየቻለ ተከራካሪ ወገኖችን ማስረጃ አቅርቡ ማለት ጊዜና ገንዘብ ከማባከን ሌላ የሚጨምረው ነገር የለም እንዲሁም የፍሬ ነገሩ መኖር ወይም አለመኖር ወይም የመደምደሚያው ትክክለኛነት በችሎት በተደረገ ክርክር ወይም መግለጫ የታመነ በሆነበት ሁኔታ ማስረጃ መቀበል የሚሰጠው አገልግሉት የለም ማስረጃ የሚቀርበው ተከራካሪ ወገኖች በተካካዱበት እና ጭብጥ ብለን የምንጠራው በተያዘበት ሁኔታ መሆኑ እየታወቀ ፍሬ ነገሩ ባልተካደበት ጭብጥ ባለተያዘበት ማስረጃ ቢቀርብም የሚያስረዳው ነገር የለም ከወጭና ጊዜን ከማባከን ውጭ የሚሰጠው ጥቅም የለም በዚሀ ምዕራፍ የሚገለፁትም እነዚህ ልዩ ሁኔታዎች ናቸው ነገር ግን ወደዝርዝር ውስጥ ከመግባት አስቀድሞ በአብዛኛው የቀድሞ የማስረጃ ሕግ ጽሑፎች ላይ ኛው አይነት ማስረጃ ማቅረብ የማያስፈልገው ፍሬ ነገር ስለሚባለውና በሕግ ግምት ዎሞጩህከፀዘበ ላይ መጠነኛ መግለጫ መስጠት ያስፈልጋል አንድ ፍሬ ነገር በህግ ግምት እንዲረጋገጥ ህግ በደነገገ ጊዜ ይህ ፍሬ ነገር ህግ በሚወሰነው ግምት መሠረት አንደሚረጋገጥ ይታወቃል በዚህም መሠረት ሩ ከአንድ ከተረጋገጠ ፍሬ ነገር ዞሾጸር በመነሳት ሌላ ፍሬ ነገርን ወይም መደምደሚያን ዞቬህበ ርከ ትክክለኛነት መገመት እንደሚገባነገር ግን ይህ ግምት መውሰዱ የሚጉዳው ሰው ተቃራኒ ማስረጃ በማቅረብ ማስተባበል እንደሚችል ህግ ሊደነግግ የችላል ይህም ሊስተባበል የሚችል የህግ ግምት ሀ ፀፀሀከባዐክከ ይባላል ቀሩ እንዲሁም ከአንድ ከተረጋገጠ ፍሬ ነገር ርእ በመነሳቱ ሌላ ፍሬ ነገርን ወይም መደምደሚያን ሀበ ዉኗርእ ትክክለኛነት መገመት እንደሚገባና ይህንን ህግ የወሰደውን ግምት ግን ተቃራኒ ማስረጃ በማቅረብ ማስተባበል እንደማይቻል ህግ ሊደነገግ ይችላል ይህም ሊስተባብል የማይችል የህግ ግምት ዘሀከከ ቨ ርዐበርህክፀ ፀጨፀሀበህቨበ ይባላል ግምት የሚወስድበት ፍሬ ነገር በጥልቀት ከታየ ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ ያልሆነበት ሁኔታ አለ ለማለት አይቻልም በርግጥ ማስረጃው የሚቀርበው ግምት የሚወሰድበትን ፍሬ ነገር መኖር ወይም መደምደሚያ ትክክለኘነት ለማረጋገጥ አይደለም ነገር ግን ለህግ ግምት መሠረት የሚሆነውን ፍሬ ነገር ለማስረዳት ማስረጃ ሊቀርብበት የሚገባ ነው ለምሳሌ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር የልጅ መፀነስ ጊዜ የሚቆጠረው ልጁ ከተወለደበት በፊት ካለው ከሦስት መቶኛው ቀን ወዲህ ነው ይላል በዚህም መሠረት ልጁ የተፀነሰበትን ቀን ለመወሰን የሚቻለው ልጁ የተወለደበትን ቀን ለማስረዳት ከሚቀርበው ማስረጃ በሚወሰድ ግምት ነው ልጁ የተወለደበትን ቀን የሚያስረዳ ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ ነው ይህ ልጁ የተፀነሰበትን ጊዜ ለመገመት መሠረት ነው ከዚህ አንፃር ምንም እንኳን ልጅ የተፀነሰበትን ቀን ለማስረዳት ማስረጃ ባይቀርብም የተወለደበትን ቀን ለማስረዳት ግን ማስረጃ መቅረቡ አይቀርም ስለዚህ ግምት የሚወሰድበት ፍሬ ነገር መኖርን ለመገመት መንደርደሪያ የሆነውን ፍሬ ነገር ለማስረዳት ማስረጃ የሚቀርብ በመሆኑ ይህ ግምት የሚወሰድበት ፍሬ ነገር በራሱ ብቻውን ሊቆም የማይችል በመሆኑ ማስረጃ ሳያስፈልገው ስለሚረጋገጥ ፍሬ ነገር በሚል በተጠቀሰው በዚህ ምፅራፍ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው አይደለም በዚህም መሠረት ቀጥሎ በፍርድ ቤት ግንዛቤ ስለሚወሰድባቸው እና ስለታመኑ ፍሬ ነገሮች ይገለፃል መወያያ ጥያቄዎች በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር ላይ የሚከተለው ተደንግጐአል አንድ ሰው ደንበኛ የመኖሪያ ስፍራው አንድ በሆነ ጊዜ በዚሁ ስፍራ በነዋሪ አኳኋን ለመኖር አሳብ እንዳለው ይገመታል ይህ የተባለው ሰው የገለፀው ተቃራኒ ሐሳብ ቢኖር አሳቡ በቂ በሆነ አነጋገር የተለየ ካልሆነና ውጤትም የሚኖረው እንደነገሩ ደንበኛ ሁኔታ ወደፊት ለመድረስ የሚችል አንድ ሁኔታ ከደረሰ በጐላ የሚሆን ካልሆነ በቀር በደንበኛው የነገሮቹ መንገድ ወደ ፍፃሜ ደርሶ መታየት ያለበት ተቃራኒው አሳብ ከቁም ነገር አይቆጠርም በዚህ መሠረት ሀ ማስረጃ ሊቀርብብት የሚገባው ፍሬ ነገር የትኛው ነው። ከጠቅላይ ፍርድ ቤት የወይመቁጥር በላይ በማስተካከል የተወሰደ ኖዎቻሥፖ ዕልታመጵ ፉሪ ነሮፖሮቻ ጽንሰ ሐሳቡ አንድ ፍሬ ነገር መኖሩ ወይም አለመኖሩ ታምኗል የሚባለው በተከራካሪ ወገኖች በአንደኛው ስለዚህ ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር የተገለፀውን ሌላኛው ወገን አምኖ ሲቀበለው ወይም ስምምነቱን ሲገልፅ ነው በዚህም መሠረት የታመነውን ፍሬ ነገር በተመለከተ የታመነለት ሰው ማስረጃው አድርጐ እንዲጠቀምበት ወይም ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልገው በፍርድ ቤት የተረጋገጠ ፍሬ ነገር ተደርጐ አንዲወሰድ የማድረግ ውጤት አለው የፅምነት ቃል አሰጣጡን በተመለከተም ክርክሩ ከመጀመሩ በፊት ማለትም ከፍቤት ውጭ የተሰጠና የማስረጃነት ዋጋ ያለው ፎበከቫ ልበጠዕርበ ወይም ከፍቤት ከተጀመረ ክርክር ሒደት ማለትም በፍርድ ቤት ውስጥ የተሰጠ የዕምነት ቃል ህሀርጪ ልዐጠወዐበሊሆን ይችላል ከፍርድ ቤት ውጭ የተሰጡ የዕምነት ቃሎች ፍሬ ነገርን ለማስረዳት በማስረጃነት ሊቀርቡ የሚችሉ ናቸው የማስረጃ ተቀባይነትን የሚመለከቱ ደንቦችን እስከ አሟሉ ድረስ ማለት ነው ከነዚህም መካከል በወንጀል ጉዳይ የወንጀሉ ድርጊት መፈፀሙን በማመን በተከሳሹ ለመርማሪ ፖሊስ ወይም ለምርመራ ቃል ተቀባይ ፍርድ ቤት የሚሰጡ የዕምነት ቃሉች ሩ በፍትሐብሔር ጉዳይ ዕዳን በማመን ከፍርድ ቤት ውጭ የተሰጡ መተማመኛዎች ተጠቃሽ ሲሆኑ እነዚህም በማስረጃነት ሊቀርቡ ይችላሉ ነገር ግን አምኖአል የተባለው ሰው ማስረጃ በማቅረብ ማስተባበል ይችላል በፍርድ ቤት ውስጥ የተሰጡ የዕምነት ቃሎች የተለያዩ ዓይነት አላቸው ለምሳሌ ያህልም ሩሩ በወንጀል ጉዳይ ተከስሶ ፍርድ ቤት የቀረበ ተከሳሽ ክሱ ተነብቦለት ከተረዳው በኃላ የፅምነት ክህደት ቃሉን አንዲሰጥ ሲጠየቅ ወንጀሉን በማመን የሚሰጠው የዕምነት ቃል ሩ በፍትሐብሔር ጉዳይ የተከሰሰው ሰው ለፍርድ ቤት በሰጠው መልስ ወይም በክርክሩ ሒደት በቃል በጽሑፍ የሰጠው የዕምነት ቃል በጽሁፍ የሰጠው የዕምነት ቃል ተጠቃሽ ናቸው በፍርድ ቤት ውስጥ የተደረገ የማመን ቃል እንደሁኔታው የማስረጃነት ወይንም ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ እንደተረጋገጠ ፍሬ ነገር የመወሰድ ውጤት ያስከትላል ከላይ ከተመለከተው መረዳት የሚቻለው ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈለግ ፍሬ ነገሩ የተረጋገጠ ተደርጐ እንዲወሰድ የማስደረግ ውጤት ሊኖረው የሚችለው በፍርድ ቤት ውስጥ የተደረገ ማመን ነው ከፍርድ ቤት ውጪ የተደረገ ዕምነት ግን በማስረጃነት የሚቀርብና ማስተባበያ ማስረጃም ሊቀርብበት የሚችል በመሆኑ ማስረጃ የማያስፈልጋቸው ፍሬ ነገሮች በሚለው በዚህ ምዕራፍ ሥር የሚሸፈን አይደለም በዚህ ምዕራፍ የሚታየው በፍርድ ቤት የተደረገ የእምነት ቃል ሲሆን በፍትሐብሔር እና በወንጀል ጉዳዮች የተለያየ አፈፃፀም ስለአለው ለያይቶ መመርመሩ አስፈላጊ ነው በወንጀል ጉደይ በችሎት የታመኑ ፍሬ ነገሮች በወንጀል ጉዳይ በፍርድ ቤት የታመኑ ፍሬ ነገሮች ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ የተረጋገጡ ተደርገው የሚወሰዱበት ዕድል በጣም ጠባብ ነው በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት ቁጥር ላይ እንደተመለከተው እንደተረጋገጡ ፍሬ ነገሮች ተደረገው የሚወሰዱት ተከሳሹ በክሱ ማመልከቻ ላይ የተዘረዘረውን ወንጀል ለመስራቱ በሙሉ ያመነ እንደሆነ ነው ከዚህ ጋር በተያያዘ በወንጀል ጉዳይ ፍሩ የፅምነት ቃል ሰጠ የሚባለው ተከሳሹ ራሱ ነው እንደፍትሐብሔር ጉዳይ ከሳሹ ተከሳሹ በመልስ ላይ የገለፀውን ከሳሽ ሊያምን ይችላል ወይም ጠበቃ ሞግዚቱ እንደራሴውወዘክተ ስለተከሳሽ ሆነው የዕምነት ቃል ሊሰጡ አይችሉም ተከሳሹም ቢሆን በመሠረቱ አመነ ለመባል በክሱ ማመልከቻ ላይ የተዘረዘረውን ወንጀል ለመስራቱ በሙሉ ያመነ መሆኑ መረጋገጥ አለበት እንደፍትሐብሔር ጉዳይ በዝምታ ወይም በግልፅ እና በዝርዝር ባለማስተባበል መነሻ አምኖአል አይባልም የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነሥርዓት ቁጥር ድንጋጌን ከፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ጋር አገናዝብ ተከሳሹ ራሱ በክሱ ላይ የተዘረዘረውን ወንጀል ለመስሪቱ በሙሉ ያመነ ሆኖ እያለ ፍርድ ቤቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ዐቃቤ ሕጉ ለክሱ የሚደግፈውን ማስረጃ እንዲያቀርብ ለማዝዝና ተከሳሹም የመከላከያ ማስረጃውን እንዲያቀርብ ለመፍቀድ ይችላል የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ው ው ሆኖም ቃሉ የዕምነት ቃል የሚለውን የአሟላ ሆኖ ከተገኘና ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ህግንና የመከላከያ ማስረጃን መቀበል አስፈላጊ ሆኖ ባላገኘው ጊዜ የታመነው ፍሬ ነገር እንደተረጋገጠ ተቆጥሮ የጥፋተኛነት ውሳኔ ይሰጣል ይህም ማለት ሩሩ ፍሬ ነገሩን ለማስረዳት ማስረጃ ማቅረብን አላስፈላጊ ያደርገዋል ስለዚህም ዐቃቤ ህጉም ሆነ ተከሳሹ ማስረጃ አያቀርቡም ሩ በቅጣቱ ላይ ካልሆነ በስተቀር ጥፋተኝነትን ባቋቋሙት ፍሬ ነገሮች ላይ ይግባኝ መጠየቅ አይፈቀድም በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሥነ ሥርዓት ቁጥር በፍትሐብሔር ጉዳይ በችሎት የታመኑ ፍሬ ነገሮች በፍርድ ቤት ውስጥ በችሎት የታመኑ ፍሬ ነገሮች ማስረጃ ሳያስፈልጋቸው ውሳኔ ለማሰጠት የሚችሉት በዋነኛነት በፍትሐብሔር ጉዳዮች ነው በፍትሐብሔር ጉዳይ በችሎት የተሰጡ ናቸው የሚባሉት የፅምነት ቃሎችተከራካሪ ወገኖች የሚያቀርቡአቸው የአቤቱታ ጽሑፎች እንዲሁም እነዚህ ወገኖች በፍርድ ቤት ለሚደረግ የቃል ክርክር በሚሰጡዋቸው መልሶች ሊገለፁ ይችላሉ በዚህ መንገድ የተሰጡትን ቃሎች የዕምነት ቃል የሚያደርጋቸው ሩ ተከራካሪ ወገኖች ወይም ወኪሉቻቸው በግልፅ ማመናቸው ሩ በዝምታ ማለፋቸው ወይም ፍሩ በአነጋገር ወይም በአገላለፅ ዘይቤ ማመናቸው ተደርጐ እንዲወሰድ ማድረጋቸው ሊሆን ይችላል የፍትሐብሐር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር በተጨማሪም የፍትሐብሔር ጉዳይ እንደወንጀል ጉዳይ በሙሉ ማመንን በግዴታ የሚጠይቅ አይደለም በዚህም መሠረት የዕምነት ቃሉ ሩ በግልፅም በዝምታ ወይም በአነጋገር ዘይቤ በሙሉ የታመነ በመሆኑ የታመነውፍሬ ነገር በሙሉ ማስረጃ ማቅረብ የማያስፈልገው ወይም ሩሩ በግልፅም በዝምታ ወይም በአነጋገር ዘይቤ በከፊል የታመነ ሆኖ የታመነው ክፍል ብቻ ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ ውሳኔ ሊያሰጥ የሚያስችል ሊሆን ይችላል መወያያ ጥያቄዎች በወንጀል ጉዳይ ተከሳሹ በክሱ ማመልከቻ ላይ የተረዘረዘውን ወንጀል ለመስራቱ በሙሉ አምኖ እያለ ፍርድ ቤቱ ማስረጃ እንዲቀርብ ትዕዛዝ የሚሰጠው ምን ምን ነገሮችን ግምት ውስጥ በማስገባት ነው። ክፍል ሁለት ማስረጃን ለፍርድ ቤት ስለማቅረብ ምዕራፍ ስለማስረጃ ተቀባይነት ዝርዝር አላማዎች ሰልጣኞች ይህንን ምእራፍ ሲያጠናቅቁ በወንጀል ጉዳይም ሆነ በፍታብሔር ስለማስረጃ ተቀባይነት እና አግባብነት በቂ ግንዛቤ በመጨበጥ በተግባር ላይ ማዋል ይችላሉ ተቀባይነት ያላቸዉን ማስረጃዎች ተቀባይነት ከሌላቸዉ የመለየት ብቃት ያዳብራሉ ጋፇጎጎ ዉድ ሠልጣኞች ባለፉት ምዕራፎች ውስጥ አንደተገለፀው በተወሰኑ ልዩ ሁኔታዎች ካልሆነ በስተቀር የአንድን ፍሬ ነገር መኖር በመጥቀስ በፍቤት የሚከራከር ሰው ወይም አንድ ዓይነት መደምደሚያ ላይ ሊደርስ ይገባል በሚል የሚከራከር ሰው ማስረጃ በማቅረብ የፍሬነገሩን መኖር ወይም የመደምደሚያውን ትክክለኛነት ማስረዳት ይገባዋል የተባለው ፍሬ ነገር አለመኖሩን ወይም የተጠቀሰው መደምደሚያ ትክክለኛ አይደለም የሚል ሰውም ማስረጃ በማቅረብ ይህንኑ የማስተባበያ አቋሙን ማስረዳት አለበት ዉድ ሠልጣኞች ለሚከተሉት ሁለት ቃላት ከማስረጃ መርህ አንፃር ትርጉም ስጡ ተዛምዷቸዉንም አስረዱ ተቀባይነት አግባብነት የአንድ ፍሬ ነገርን መኖር ወይም የመደምደሚያን ትክክለኛነት ለማስረዳት ወይም ለማስተባበል የተፈለገው ማስረጃ በዘፈቀደ ወይም ማስረጃ አቅራቢው ስለፈለገው ብቻ ይቀርባል ማለት አይደለም ማስረጃው ሊቀርብ የሚችለው ተቀባይነት ሲኖረው ብቻ ነው ተቀባይነት የሌለው ማስረጃ ሊቀርብ አይችልም የማስረጃው ተቀባይነት የሚወሰነው ደግሞ በሁለት መንገዶች ነው የመጀመሪያው የማስረጃ ተቀባይነት ቀዳሚ ደንብ የማስረጃን አግባብነት የሚመለከተው ነው ማለትም እንዲቀርብ የተጠየቀው ማስረጃ ያስረዳዋል ለተባለው ፍሬ ነገር አግባብነት ሊኖረው ይገባል በወመህሥሥ ቁጥር ላይ በዋናው ጥያቄ የሚቀርቡ ጥያቄዎች ውሳኔ ስለሚሰጥበት ፍሬ ነገር ተገቢ የሆኑትና ምስክሩ በቀጥታም ሆነ ቀጥታ ባልሆነ መንገድ የሚያውቀውን ፍሬ ነገር ብቻ ነው በሚል ሲደነገግ ተገቢ የሆኑትና የሚለው ምስክሮች የሚያስረዱት ፍሬ ነገር ውሳኔ ለሚሰጥበት ፍሬ ነገር አግባብነት ያለው መሆን እንዳለበት የሚያመለክት ነው ብቻ የሚለው ቃል ደግሞ ህጉ አግባብነት ያላቸውን ብቻ ለመቀበል መቁረጡንና አግባብነት የሌላቸውን ደግሞ ላለመቀበል መወሰኑን ያመለክታል በፍብሥሥ ሕጉም በቁጥር ላይ የተደነገገውም ከ ወመሕሥሥ ድንጋጌው ጋር ተመሳሳይ ነው እነዚህ ድንጋጌዎች ምስክሮችን የሚመለከቱ ይሁኑ እንጂ የማስረጃው ዓይነት ሰነድም ይሁን ሌላ አግባብነት የሌላቸው ማስረጃዎች ለፍቤት አይቀርቡም ለዚህም የወመሕሥሥ ቁጥር እና የፍብሥሥ ሕግ ቁጥር እና ድንጋጌዎችን መመልከት ይቻላል በሌላ በኩል ማስረጃው ውሳኔ ለመስጠት ተገቢነት ቢኖረው እንኳ እንዳይቀርብ የሚያግድ በህግ የተደነገገ ክልከላ ካለ አይቀርብም ማስረጃ ሊቀርብ የሚችለው ውሳኔ ሊሰጥበት ለተፈለገው ፍሬ ነገር አግባብነት ስላለው ብቻ ሳይሆን ህግ እንዳይቀርብ ያልከለከለው በመሆኑ ጭምር ነው ስለዚህ ሕግ እንዳይቀርብ የከለከለው ማስረጃ አግባብነት ቢኖረው እንኳን ሊቀርብ አይችልም በዚህም መሠረት የማስረጃ ተቀባይነትን በተመለከተ ከላይ ከተገለፁት ሐሳቦች መረዳት የሚቻለው ሃሦ ማንኛውም ማስረጃ ሊቀርብ የሚችለው ያስረዳዋል ለተባለው ፍሬ ነገር አግባብነት ያለው መሆኑ ሲረጋገጥ ነው ሃሦ በተጨማሪም ማስረጃው ሊቀርብ የሚችለው በህግ አንዳይቀርብ ያልተከለከለ እንደሆነ ነው የማስረጃ ተቀባይነት ጉዳይ ብቸኛ ባይሆንም መሠረታዊ የማስረጃ ህግ ደንብ ነው ለማለት ይቻላል ይህም በበቂ ምክንያቶች ላይ የተመሰረተ ነው አግባባነት የሌለው ማስረጃ ሊቀርብ አይገባም የሚባለው የተያዘውን ክርክር ወይም ጭብጥ ለመወሰን ስለማይጠቅም ነው ስለዚህም አግባብነት የሌለውን ማስረጃ እንዳይቀርብ ማገድ የማያስፈልገው ማንኛውም እቃ ግን ደረሰኝ በመቀበል ለተወሰደበት ሰው ተመላሽ ይሆናል ፍርድ ቤቱ ለክርክሩ አግባብ ያልሆነውን ወይም ከነገሩ ጋር ግንኙነት የሌለውን ማንኛውንም ጽሁና በማናቸውም ጊዜ እንዳይቀርብ ለማገድ ይችላል ይህንንም ሲወስን ምክንያቱን በመዝገቡ ላይ መግለጽ አለበት ስለጽሁፍ ሰነዶች አቀራራብ በዚህ ምእራፍ ውስጥ የተነገረው ድንጋጌ እንደነገሩ አካባቢ ሁኔታ በማስረጃነት በሚቀርቡ ግዙፍ ነገሮች ላይም ተፈጻሚ ይሆናል የፍቤቱ እና የተከራካሪ ወገኖችን ጊዜና ወጪ ከመቆጠቡም በላይ የፍርድ ሒደት ሥርዓት ይዞ እንዲጓዝ ያደርጋል ለተያዘው ጭብጥ በማይጠቅሙ ማስረጃዎች ክምችት ምክንያት የውሳኔ አሰጣጥ እንዳይወሳሰብም ያደርጋል ከዚህ በተጨማሪም ማስረጃው አግባብነት ቢኖረው እንኳን ሕግ ተቀባይነት ያላቸው ማስረጃዎች በተለያዩ ምክንያቶች ሊሆን ይችላል ለምሳሌ ፍሬ ነገሩን በተሻለ ሁኔታ የሚያስረዳ ሌላ ማስረጃ በመኖሩ የሰነድ ማስረጃ ካለ ከምስክር በተሻለ ሁኔታ ያስረዳል ወይም ሚዛናዊ ዳኝነት እንዳይሰጥ የሚያደርግ በመሆኑ በወንጀል ጉዳይ ከጥፋተኛነት በፊት የተሰጠ ሌላ የጥፋተኛነት ውሳኔ ወይም መሠረታዊ የህግ መርህ ወይም የሰው ልጆችን መብት የሚፃዛረርበነፃ ፈቃድ ያልተገኘ የዕምነት ቃልን በመሆኑ ምክንያት ሊሆን ይችላል በአገራችን የማስረጃ ተቀባይነትን የሚመለከቱ ደንቦች በተለያዩ ሕጐች ውስጥ ተሰበጣጥረው ይገኛሉ ከዚህ አንፃር አግባብነት የሌላቸው ማስረጃዎች የሚለዩት በማስረጃነት ሊገለፅ በተፈለገው ፍሬ ነገር እና ያስረዳዋል ወይም ያስተባብለዋል በተባለው ፍሬ ነገር ወይም መደምደሚያ መካከል በሚኖር ግንኙነት መሠረት ሲሆን ህግ አይቀርቡም የሚላቸው ማስረጃዎች የትኞቹ እንደሆኑ ደግሞ ህጐችን በመፈተሽ የሚገኝ ነው በተግባር እንደሚታየውም በበርካታ የፍትሐብሔር እና የወንጀል ጉዳዮች ላይ የማስረጃ ተቀባይነትን የሚመለከቱ ክርክሮች የሚቀርቡ ሲሆን ፍቤቶች ደግሞ ህጐችን በመመርመር ተገቢውን ብይን መስጠት ይገባቸዋል ዕታማዕረያሮህሦ ጽያራሳዮ ዉድ ሠልጣኞች ከላይ እንደተገለፀው የማስረጃ አግባብነት የሚወሰነው በሁለት ፍሬ ነገሮች መካከል በሚኖር ግንኙነት መነሻ ነው እነዚህ ፍሬ ነገሮችም ማስረጃው ይገልፀዋል የሚገልጸው ፍሬነገርና ማስረጃው ያስረዳዋል ወይም ያስተባብለዋል የተባለው ፍሬ ነገር ናቸው ከዚህ አንፃር ትኩረት ሊሰጥባቸው የሚገቡ ነጥቦች የማስረጃው አግባብነት የሚወሰነው ይህ ማስረጃው ይገልፀዋል የተባለው ፍሬ ነገር ማስረጃው ሊያስረዳው ወይም ሊያስተባብለው ከሚፈልገው ፍሬ ነገር ጋር ያለው ትስስር በነገሮች አመክኖአዊ ግንኙነት ርዐበበርቪበ ወይም ህግ በፈጠረው ትስስር ለምሳሌ ህፃኑ የተፀነሰበት ቀን ከዚህ በኃላ ነው ብሎ ለመገመት የተወለደበትን ቀን የሚመለከት ፍሬ ነገር መነሻ ሊሆን ይችላል ሃ ማስረጃው ያስረዳዋል ወይም ግምቱ እንዲወሰድ ያስችለዋል ወይም ያስተባብለዋል የተባለው ፍሬ ነገር በፍቤት ክርክር ረገድ በጭብጥ የተያዘ ፍሬ ነገር ር። ኗር ሊሆን ይችላል የማስረጃ አግባብነት በወንጀል ጉዳዮች በወንጀል ጉዳዮች የሚቀርቡ ማስረጃዎች ውሳኔ ለሚሰጥበት ፍሬ ነገር አግባብነት ሊኖራቸው እንደሚገባ ይህም በወመህሥሥእንደተደነገገ ቀደም ሲል ተገልፆአል የአግባብነት ድንጋጌው ተፈፃሚ የሚሆነውም በዐቃቤ ሕግ በኩል ለሚቀርቡ ማስረጃዎች ብቻ ሳይሆን በተከሳሹ በኩል ለሚቀርቡ የመከላከያ ማስረጃዎች ጭምር ነው ሊቀርብ የተፈለገው ማስረጃ ውሳኔ ሊሰጥበት ለተፈለገው ፍሬ ነገር አግባብነት ያለው መሆኑ ወይም አለመሆኑ በሁለቱ ፍሬ ነገሮች መካከል ባለው ግንኙነት ወይም ትስስር የሚወሰን ሆኖ የዚህን ግንኙነት መኖር ለማረጋገጥ ደግሞ ሦ በክስ ማመልከቻው ላይ የተገለፀውና ተላለፈ በተባለው የወንጀል ህግ ድንጋጌ ወንጀሉን ያቋቁማሉ በሚል የደነገጋቸው ፍሬ ነገሮች ሊመረመሩ ይገባል በጭብጥ የሚያዘውን ፍሬ ነገር ለማወቅ ይረዱናል ሃሦ ጮማስረጃው ይገልፀዋል የተባለውን ፍሬ ነገር ደግሞ ግራቀኝ ተከራካሪ ወገኖች ዐቃቤ ህጉና ተከሳሹ ማስረጃውን ከማሰማታቸው በፊት ስለማስረጃው አይነትና ይገልፀዋል ስለተባለው ፍሬ ነገር ከሚሰጡት መግለጫ ለመረዳት ይቻላል የወመህሥሥ ቁጥሮች እና ፍርድ ቤቱ ይህንን መግለጫ ካደመጠ በኃላ ማስረጃውን ከመቀበሉ በፊት በአግባቡ ላይ ሊወሰን ይገባል በወንጀል ጉዳይ የማስረጃ አግባብነት ሲወሰን ከጭብጥ ወይም በወንጀል ህጉ ላይ ከተጠቀሰው እና ተከሳሹ ተላለፈ የተባለውን ወንጀል ያቋቁማሉ ተብለው ከተገለፁት ፍሬ ነገሮች እና በከስ ማመልከቻው ላይ ከተጠቀሱት ፍሬ ነገሮች አንዛር የሚታዩ መሆኑ ግልፅ ነው ነገር ግን ሊቀርብ የተፈለገው ማስረጃ የግዴታ ከእነዚህ ፍሬ ነገሮች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ሊኖረው ይገባል ብሎ መደምደም ስህተት ነው ሊቀርብ የተፈለገው ማስረጃ ከጭብጡ ጋር በቀጥታ ባይገናኝም እንኳን የወንጀሉን አፈፃፀም አካባቢያዊ ሁኔታ የሚያስረዳ ከሆነ አግባብነት ሊኖረው ይችላል እንደነዚህ ያሉ ቀጥተኛ ሳይሆን ቀጥተኛ ያልሆኑ ማስረጃዎች በተናጠል ሲታዩ ጭብጡን የሚያስረዱ ባይሆኑም ተጠረቃቅመው ሲገናዘቡ ግን ሊያስረዱ ይችላሉ ከላይ እንደተመለከተው የማስረጃ አግባብነት የሚለካው በጭብጥነት ከተያዘው ፍሬ ነገር ወይም ለዚህ ፍሬ ነገር አግባብነት አለው ከተባለ ፍሬ ነገር ጋር ካለው አግባብነት ነው የሚባለውም ለዚህ ነው እንግሊዝና ህንድን በመሳሰሉ አገሮችም በወንጀል ጉዳይ ማስረጃ አግባብነት አለው ከሚባልባቸው ምክንያቶች መካከል በጭብጥ ለተያዘው ፍሬ ነገር ወይም ለዚህ ፍሬ ነገር አግባብነት ላለው ፍሬ ነገር ሃ አንድ አካል ወይም አንድ ክፍል የሆኑ ፍሬ ነገሮች አጋጣሚ መንስኤ ወይም ውጤት የሆኑ ፍሬ ነገሮች አመቺ ሁኔታዎችን የፈጠሩ ፍሬ ነገሮች ሃ ያነሳሱ ዝግጅነትን የሚያሳዩ እንዲሁም ከድርጊቱ በፊትና በኃላ የታዩ ባህርያት ይገኙበታል ልሃ ዞኮ በእኛ አገርም ተፈፃሚነት ሊኖራቸው ይችላል የማስረጃ አግባብነት በፍትሐብሔር ጉዳዮች በፍትሐብሔር ጉዳዮች የማስረጃ አግባብነትን ለመወሰን ዋነኛው መመዘኛ ማስረጃው ይገልፀዋል በተባለው ፍሬ ነገር እና በጭብጥ በተያዘው ፍሬ ነገር መካከል ያለው ትስስር ወይም ግንኙነት ነው ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በህግ የሚወሰንበት ሁኔታም አለ ሕጉ የማስረጃውን አግባብነት የሚወሰነውም ሦ ሕጉ በፍሬ ነገሮች መካከል ያለውን ትስስር ሊወሰን ይችላል ለምሳሌ የህፃኑ መፀነስ ከመቼ ጀምሮ ነው። የሚለውን ለማስረዳት የተወለደበትን ቀን ማስረዳት ይገባል በሚል በተፀነሰበት እና በተወለደበት ቀን መካከል ትስስር እንደፈጠረው ማለት ነው እንደህ ዓይነት ትስስር የሚታይባቸው በርካታ ድንጋጌዎች አሉ ሃ ሕጉ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ለማስረዳት አግባብነት ያላቸው የተወሰኑ ፍሬ ነገሮች ብቻ ናቸው በሚል የሚደነግግበት ሁኔታ አለ በፍብሕ ቁ ላይ እንደተመለከተው ማስገደድ ስህተት እና ማታለል ማለት ነው ስለሆነም የሚቀርበው ማስረጃ ማስገደድ ስህተት ወይም ማታለል መፈጸሙን የሚያስረዳ መሆን አለበት ነው ሃ እንዲሁም ሕጉ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ለማስረዳት አግባብነት የላቸውም በሚል የተወሰኑ ፍሬ ነገሮችን ከማስረጃነት ያስወገደበት ሁኔታም ይኖራል በፍብህቁ በሞት ምክንያት የሚሰጥ ካሳ የዉርስ ሀብት ክፍል አለመሆን ቁጥር የወራሽ ፆታ እድሜ ዜግነት በዉርሱ ላይ ምንም ልዩነት ያለማምጣት ቁጥር ተንቀሳቃሽ ነገሮችን የወሰደ ሰው ንብረቱን የወሰደው ንብረቱን ለማስተላለፍ መብት በሌለው ሰው መሆኑን ንብረቱን ከወሰደ በኃላ ቢያውቅ ጉዳት እንደማይደርስበት ቁጥር የአንሰሳት ልጆች ባለሀብትነትን በሚመለከት ባለሀብትነቱ እንስቲቱን የሚከተል መሆኑንና የመሳሰሉት ማለት ነው ማስረጃው ሊገልፀው የፈለገው እና ያስረዳዋል የተባለው ፍሬ ነገር ሊገኝ የሚችለውም የተከራካሪዎች አቤቱታ ጽሁፍን ግራ ቀኙ በክርክር ሂደት ከገለፁዋቸው ነገሮችን እና ማስረጃ ሊያቀርቡ ማስረሻው ስለሚገልፀው ፍሬ ነገር የሚሰጡት መግለጫን በመመርመር ነው ማዕረኛታፇፀኑሦ ጳኖረው ያፖዕያሚሟደድኔታ ይታ የማስረጃ ተቀባይነት በሚመለከት በቅድሚያ የሚቀመጠው መሰረታዊ መርህ ማስረጃ በተለይ እንዳይቀርብ በህግ ካልተከለከለ በቀር ተቀባይነት ሊኖረው ይገባል የሚለው ነው በዚህም መሠረት አግባብነት ያለው ሆኖ ተቀባይነትን የሚያጣው ሕጉ የከለከለው አንደሆነ ብቻ ነው በሕንድ እና በእንግሊዝ የማስረጃ ሕግ መሠረት ማስረጃ ተቀባይነት ከሚያጣባቸው ሁኔታዎች መካከል ሃ የሰሚ ሰሚ ማስረጃ ሃ በግዴታ የተሰጠ የዕምነት ቃል ሃ የምስክር አስተያየት የሚሰጥበት ማስረጃ ሃ ፀባይን የሚመለከት ማስረጃ ሃ የትዳር የሥራ ሚስጢርን የሚመለከቱ ማስረጃዎች ይገኙበታልበዉሃ ዞፀፀ በአገራችን ግን የሰሚ ሰሚ ማስረጃ እና በትዳር ጓደኛ ላይ የሚሰጥ ምስክርነት በማስረጃነት እንዳይቀርብ የሚከላከል ሕግ የለም የምስከር አስተያየት የሚሰጥበት ማስረጃን በተመለከተም ምንም እንኳን አይቀርብም በሚል የተደነገገ ነገር ባይኖርም ምስክር የሚቀርበው ፍሬ ነገሮችን ብቻ ለመግለፅ በመሆኑ በተለይ የባለሞያ ማስረጃ ሆኖ እንዲቀርብ ፍቤት የሚያዝዝ ካልሆነ በቀር አይቀርብም ይህ አንደጠበቀ ሆኖ የህጐቻችን ድንጋጌዎች ሲፈተሹ ሃ ፍሬ ነገሩን ለማስረዳት ተገቢ የሆነውን የማስረጃ ዓይነት ሃ ፍሬ ነገሩ ማስረጃው ራሱ ፍቤት እንዳይቀርብ በሚል ወይም ሃ ማስረጃው የተገኘበት መንገድ ተገቢ ባለመሆኑ ምክንያት ማስረጃ ተቀባይነት እንዳይኖረው ሊደረግ ይችላል ከማስረጃ አይነት አንፃር የፍትሐብሔር ህግ ድንጋጌዎች አንዳንድ ፍሬ ነገሮችን ለማስረዳት ወይም ለማስተባበል ሰነዶች ብቻ ሊቀርቡ እንደሚገባ እና ምስክሮች ሊቀርቡ አንደማይችሉ ያስረዳሉ በዚህም መሠረት ሃ የፍብሕቁጥር ላይ ውል በጽሑፍ እንደሆነ ህግ በአዘዘ ጊዜ ውሉ የተሰረቀ የጠፋ መሆኑ ካልተረጋገጠ በቀር ውሉን በምስክር ወይም በህሊና ግምት ማስረዳት አይቻልም በሚል ተደንግጉአል ስለዚህ አንድ ውል በጽሑፍ እንዲሆን ሕግ በአዘዘ ጊዜ ውሉን ማስረዳት የሚቻለው የጽሑፍ ሰነድን በማቅረብ ነው ጽሑፍ ከሌለ በምስክር ማስረዳት አይቻልም በጽሑፍ ውል የተደረገ ከሆነም ውሉ የተሰረቀ ወይም የጠፋ መሆኑ ካልተረጋገጠ በስተቀር ምስክር ማቅረብ አይቻልም በማስረጃነት የቀረበ የውል ሰነድ ላይ የተገለፁ ፍሬ ነገሮችን ማስረዳት የሚቻለው በሰነዱ ብቻ ነው ኑዛዜን በተመለከተም በግልፅ ወይም በተናዛዥ ጽሑፍ የተደረገ ኑዛዜ መኖሩንና በኑዛዜው ላይ የሰፈረውን ቃል ማስረዳት የሚቻለው በኑዛዜው ሰነድ ብቻ ነው ቁጥር ፁ መወያያ ጥያቄዎች በጽሑፍ የሚደረግ ውል በሁለት ምስክሮች ፊት ካልተረጋገጠ በስተቀር እንደማይፀና በፍብህቁ ላይ እንዲሁም በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ በአራት ምስክሮች ፊት ካልተረጋገጠ ፈራሽ እንደሚሆን በዚሁ ህግ በቁጥር ላይ ተደንግጓል በጽሑፍ የተደረገ ውልን ወይም ኑዛዜ በምስክር ማስረዳት አይቻልም ከሚለው አንፃር የምስክሮች መኖር ፋይዳው ምንድ ነው። የሚለውን ጥያቄ የሚመለከት ነው ይህም በሚከተለው አጠቃላይ መርህ የሚመራ ነው ይኸውም ማስረጃ ሊቀርብበት በሚያስፈልገው አንድ ፍሬ ነገር ላይ ማስረጃ ማቅረብ የሚገባው ማስረጃ ሳይቀርብ ቢቀር በክርክሩ ተሸናፊ የሚሆነው ወገን ነው በወንጀል ጉዳይ ሲሆን ማስረጃ የማቅረብ ግዴታ የሚወድቀው በእምነት መሠረት ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ ውሳኔ የሚሰጥበት ሁኔታ ከሌለ ማለት ነው በከሳሽ ዐቃቤ ህግ ላይ ነው ተከሳሹ ማስረጃ ሊያቀርብ የሚገደደው ዐቃቤ ህጉ ማስረጃ አቅርቦ ካሳመነ ፍርድ ቤቱም በበቂ ሁኔታ አስረድቷል የሚል መደምደሚያ ላይ ከደረሰ በጐላ ነው በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር ላይ ዐቃቤ ህግ ክሱን ሲከፍት የሚለው አገላለፅ እንዲሁም በቁጥር ላይ ዐቃቤ ህጉ ማስረጃውን አስምቶ ከጨረሰ በኃላ የሚለው ይህንን ያረጋግጣል ስለዚህ በወንጀል ጉዳይ ማስረጃ በቅድሚያ የማቅረብ ግዴታ ምን ጊዜም የዐቃቤ ህጉ ነው በወንጀል ጉዳይ የማስረዳት ሽክም ወደ ተከሳሹ የሚዞርበት ሁኔታ የለም በተለይ የማስረዳት ሽክም ወደ ተከሳሹ የሚዞርበት ሁኔታ በወንጀል ጉዳይ ማለት ነው የተደነገገው በፌዴራል የፀረ ሙስና ሥነ ሥርዓት የማስረጃ ህግ አዋጅ ቁጥር ላይ ነው በፍትሐብሔር ጉዳይ ማስረጃ የማቅረብ ግዴታን የሚመራው ከላይ የተገለፀው መርህ የተፃሚነት አለው በመሠረቱ ማስረጃ በመጀመሪያ በማቅረብ ማስረዳት የሚገባው ምንም ማስረጃ ባያቀርብ ተሸናፊ የሚሆነው ወገን ነው ማስረጃ ማቅረብ የሚገባው ማን ነው የሚለውን በተመለከተም በፍብህ ላይ በየቦታው ተሰበጣጥረው የተቀመጡ ድንጋጌዎችን እናገኛለን ለምሳሌ ያህል በቁጥር አና ላይ የተደነገገውን መመልከት ይቻላል ለምሳሌ ኑዛዜ አለኝ የሚል ወገን ይህ ኑዛዜ መኖሩና ይዘቱንም በተመለከተ የማስረዳት ሽክም አለበት ውል አለ የሚል ወገንም ውሉ መኖሩን የማስረዳት ሽክም አለበት በተጨማሪም በፍትሐብሔር ጉዳይ ማስረጃ የማቅረብ ሽክም ሁል ጊዜ ተሸካሚ የሚሆነው ከሳሽ ነው ማለት አይቻልም በዚህም መሰረት ሩ ተከሳሽ ያቀረበበትን ክስ ተከሳሽ አምኖ ነገር ግን ህጋዊ መከላከያ የአቀረበ እንደሆነ ማስረጃ የማቅረብ ሽክሙ ወደ ተከሳሹ ይዞራል የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር ከሳሽ ለአቀረበው ክስ ተከሳሹ ክሱን አምኖ የማቻቻያ ጥያቂ የአቀረበ አንደሆነ የማቻቻያ ጥያቄውን በሚመለከት ከሳሹም የማቻቻያ ጥያቄውን የተቀበለው ካልሆነ በቀር የማስረደት ሽክሙ የተከሳሹ ይሆናል ፍሩ ከሳሹ ክሱን ሲያቀርብ ያስረዱልኛል በሚል የዘረዘራቸው ሰነዶች በተከሳሹ እጅ የሚገኙ መሆናቸውን ጠቅሶ እያለ ተከሳሹ ማስረጃው በእጁ መኖሩን ሳይክድ ነገር ግን ለማቅረብ ፈቃደኛ ካልሆነ የማስረዳት ሽክሙ ወደርሱ ይዞራል ፈ ማዕረያዕሐሟፇረሀያፖ ፊና ሥራኔታ « ያምዕያጵሮቻ ሰፇራረ አጠቃላይ በሆነ አገላለፅ በማስረጃነት የሚቀርቡ ምስክሮች የሚሰጡት የምስክርነት ቃል በጭብጥ ለተያዘው ፍሬ ነገር ወይም ለዚህ ፍሬ ነገር አግባብነት ላለው ሌላ ፍሬ ነገር አግባበነት እስከአለው ድረስ የመመስከር ብቃት አላቸው የአንግሎ አሜሪካ የህግ ሥርዓት በሚከተሉ አገሮች ውስጥ የተደነገጉት ማስረጃን ብቃት የለውም የሚያሰኙ የተለያዩ ምክንያቶችን በአገራችን በቀጥታ ተፈፃሚነት ይኖራቸዋል ማለት አይቻልም ዋናው ነገር ምስክሩ ሊመሠክር ስለመጣበት ጉዳይና ስለሚጠየቀው ጥያቄ የመረዳት ችሎታው ነው በአዕምሮ መናወጽ በአካል ላይ በደረሰ ጉዳት የተነሳ ለመረዳት አለመቻል ወይም ተፈላጊውን ፍሬ ነገር ለመግለፅ ባለመቻል በንግግርም ሆነ በምልክት መግለፅ የማይቻል ካልሆነ በቀር መመስከር ይችላል ስለዚህም አዘውትረው በመቃወሚያነት የሚቀርቡት ሩ ህፃናት ስለሆኑ ሊመሰክሩ አይገባም የዉልና የኑዛዜ ጉዳዮች የተጠበቁ ሆነዉ ፍሩ ከተከራካሪ ወገኖች ጋር ፀብ ወይም ዝምድና ያላቸው ስለሆነ ሊመሰክሩ አይገባም አብረን በግብር አበርነት የተከሰስን በመሆነ ለመመስከር ብቁ አይደሉም የሚሉ መቃወሚያዎች ተቀባይነት የላቸውም እነዚህ የመቃወሚያ ነጥቦች ማስረጃን በመመዘን ረገድ የራሳቸው ድርሻ የሚኖራቸው ቢሆንም ይህም በምዕራፍ ላይ እንመለከተዋለን ማስረጃዎች ብቃት የላቸውም ለማስባል ግን አይችሉም ይህ አጠቃላይ አነጋገር አንደተጠበቀ ሆኖ ግን በህጋችን የተደነገጉትን የሚከተሉት ነጥቦች ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል በወንጀል ሕግ ላይ እንደተደነገገው አንድ ሰው በፈፀመው ወንጀል ምክንያት የጥፋተኝነት ውሳኔ ከተላለፈበት ፍርድ ቤቱ ከሚወስነው መደበኛ ቅጣት በተጨማሪ የምስክርነት መብቱን ሊያግደው የሚችል ሲሆን ፍርድ ቤቱ አንዲህ አይነት ቅጣትን ሲወስን ምስክሩ የመመስከር ብቃቱን ያጣል ሩ በምስክርነት የተቆጠሩት ሰዎች ልዩ እውቀት ያላቸው ኤክስፐርቶች ከሆኑ ለምስክርነት ሊቆሙ የሚችሉት ተፈላጊው ዕውቀት አንዳላቸው ማረጋገጫ ሲገኝ ነው ማረጋገጫው የእውቀት ደረጃቸውን አስከምን ደረጃ ድረስ እንደሆነ ሊያረጋግጥ ይገባል የሚለው እንደተያዘው ጉዳይ የሚለያይ ሲሆን ነገር ግን ባለሞያ ያስረዳዋል በተባለው ፍሬ ነገር ወይም ይገልፃዋል ከተባለው አስተያያት አኳያ የባለሞያነት ማረጋገጫ ከሌለው ምስክር ለመሆን ብቃት የለውም ለማለት ይቻላል በወንጀልም ሆነ በፍትሐብሔር ምስክሮች መቼ ይቀርባሉ ለሚለው ጥያቄ መልሱ ተመሳሳይ ነው ለማለት ይቻላል በወንጀል ጉዳይ ዐቃቤ ህጉ ክስ ሲያቀርብ ያስረዱልኛል የሚላቸውን ምስክሮች ስም ዝርዝር አያይዞ ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን በፍትሐብሄር ጉዳይም ከሳሽ ክሱን ሲያቀርብ የምስክሮቹን ስም ዝርዝር ከክሱ ጋር አባሪ በሆነ ጽሑፍ ገልፃ ማቅረብ ይገባዋል ተከሳሹም እንዲሁ መልሱን ሲያቀርብ ከመልሱ ጋር አባሪ በሆነ ጽሑፍ ያስረዱልኛል የሚላቸውን ምስክሮች ስም ዝርዝር ገለጾ ማቅረብ አለብት የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሥነ ሥርዓት ቁጥር የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር በዚህም መሠረት በህግ በተፈቀደ ልዩ ሁኔታ ካልሆነ በቀር የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር እና የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር በመጀመሪያ ዝርዝራቸው ለፍርድ ቤቱ ገቢ ያልተደረገ ምስክሮች ሊቀርቡ አይገባም ለማጠቃለል ጉዳዩ ወንጀልም ሆነ ፍትሐብሔር ዝርዝሩ ማስረጃ ከመስማቱ በፊት ለፍርድ ቤቱ ሊቀርብ ይገባል ፍሩ ነገሩ ሲሰማ ማለትም ማስረጃ ሊሰማ በተቀጠረበት ቀን ግራ ቀኙ ለቆጠሯራቸው ምስክሮች መጥሪያ አውጥተው አድርሰው አቅርበው ማሰማት ይገባቸዋል ሩ መጥሪያ ደርሶአቸው ያልቀረቡ ምስክሮች ፍርድ ቤቱ በሚሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ተገድደው ቀርበው የምስክርነት ቃላቸውን አንዲሰጡ ይደረጋል ቀሩ በዝርዝሩ ያልተጠቀሱ ምስክሮች እንዲቀርቡ እንደመብት መጠየቅ የማይቻል ሲሆን ሊፈቀድ የሚቻለው መቅረባቸው ለትክክለኛ ፍርድ አስፈላጊ መሆኑን ፍርድ ቤቱ አምኖ የፈቀደ እንደሆነ ነው መመዉሮዖ ሜምጭዎሥቻ የሚከተለውን ጉዳይ መርምራችሁ አስተያየት ስጡበት ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ ሰውን በግፍ ገድሎአል በሚል ለአቀረበው ክስ ሰባት ሰዎች በምስክርነት በመጥራት ዝርዝራቸውን የአቀረበ ሲሆን ምስክሮች እንዲቀርቡ በተቀጠረበት ዕለት ሁለቱ ቀርበው ድርጊቱ ሲፈፀም አልነበርንም አናውቅምም በማለት መስክረዋል ዐቃቤ ህጉ ቀሪዎቹን ፈልገን ማግኘት ስላልቻልን ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ እንድናቀርብ ይታዘዝልን በማለት ጠይቋል በዚሁ መሠረት ለተለዋጩ ቀጠሮ ቀሪዎችን ምስክሮች አንዲያቀርብ ትፅዛዝ የተሰጠ ቢሆንም በተለዋጩ ቀጠሮም ምንም ምስክር አልቀረበም ዐቃቤ ሕጉ ተመሳሳይ ምክንያት በመስጠት ለኛ ጊዜ አንድናቀርብ ይታዘዝልኝ ሲል የጠየቀ ሲሆን ተከሳሹ በበኩሉ ለረጅም ጊዜ ታስሮ መቆየቱን በመጥቀስ በተሰማው ምስከር ብቻ ብይን እንዲሰጥ ጠይቋል ከጠቅላይ ፍርድ ቤት የወይመቁ የተወሰደ ፍርድ ቤቱ ምን ዓይነት ትዕዛዝ ሊሰጥ ይገባል። ለሚለው ደግሞ ቁጥር መልስ ይሰጣል ቁጥር መረጃዎች ኢግዚቪቶች እና የተከሳሽነት እና የምስክር ቃሎች ፍርድ ቤት መዝገብ ቤት ቀርበው መዝገብ ቤቱ ተረክቦ ቁጥርና ምልክት እንደሚያደረግባቸው ከዚያም በፍርድ ቤት መዝገብ ቤት በተጠበቀ ሥፍራ እንደሚጠበቁ የሚወጡትም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብቻ እንደሆነ ይገልፃል እነዚህ መረጃዎች የተሰጣቸውን ቁጥርም በወንጀል መዝገቡ ውስጥ አንደሚመዘገብ ቁጥር በ ያመለክታል በዚህም መሠረት ሩ ሰነዶች እጅግ ቢዘገይ የክስ ማመልከቻው ፍርድ ቤት ሲቀርብ አብረው መቅረብና መዝገብ ቤት መቀመጥ የሚገባቸው ሲሆን ለማስረጃነት ሲፈለጉም በዳኞች ትዕዛዝ ወጪ ይደረጋሉ ሩ ኢግዚቪቶችም አስቀድመው ፍርድ ቤት ቀርበው በተጠበቀ ስፍራ መቀመጥ የሚገባቸው ሲሆን ለማስረጃነት ሲፈልጉም የሚቀርቡት ከዚሁ ነው በፍትሐብሔር ጉዳይም ተከራካሪ ወገኖች ይጠቅመኛል ወይም ያስረዳልኛል የሚሉትን ሰነድ ከአቤቱታዎቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይገባቸዋል የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር ለ በልዩ ሁኔታ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ካልፈቀደ በስተቀር ቁጥር ዘግይተው ሊቀርቡ አይችሉም ማስረጃው በእጅ የማይገኝ ከሆነ በትዕዛዝ እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱን መጠየቅ የሚቻል ሲሆን ቁጥር ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ለተከሳሹ መጥሪያ ከመስጠቱ በፊት ይህ ማስረጃ እንዲቀርብ ትዕዛዝ መስጠት ይንገባዋል በትዕዛዝ እንዲቀርብለት የጠየቀው ተከሳሹ ከሆነም መልሱን ከመስጠቱ በፊት ፍርድ ቤቱ ትፅዛዝ ሰጥቶ ማስረጃውን አእንዲያስቀርብለት መጠየቅ ይኖርበታል ፍርድ ቤቱም በዚሁ መሠረት ማስረጃው እንዲቀርብ ትዕዛዝ እንደሚሰጥ ይጠበቃል ምዕራፍ ምስክሮችን ስለመመርመር ዝርዝር አላማዎች ስልጣኞች ይህንን ምእራፍ ሲያጠናቅቁ ስለምስክሮች ምርመራ በቂ እዉቀት አግኝተዉ ሥራ ላይ ያዉላሉ ምስክሮች ስለሚመረመሩበት ሥርዓት በቂ ግንዛቡ አዳብረዉ ሥራ ላይ ያዉላሉ ምስክሮች በሚመረመሩበት ወቅት ሊወሰድ ስለሚገባዉን ጥንቃቄ ተረድተዉ ሥራ ላይ ያዉሉታል ዋና ጥያቄ መስቀለኛ ጥያቄ እና ድጋሚ ጥያቄ የሚቀርብበትንና የሚጠየቅበትን ሥርዓት አዉቀዉ ተግባር ላይ ያዉላሉ ፊይ ጋፇጎጎ ዉድ ሠልጣኞች ባለፈው ምዕራፍ ውስጥ ውሳኔ ለመስጠት አስፈላጊ በሆነው ፍሬ ነገር ላይ ሊያስረዱ የሚችሉ ማስረጃዎች ፍርድ ቤት የሚቀርቡበት ሁኔታ ተገልፆአል ማስረጃን ማን እንዴትና መቼ ማቅረብ እንደሚገባውም ተጠቅሶአል በዚህ ምዕራፍ ደግሞ የቀረቡት ማስረጃዎች እንዴት አንደሚመረመሩ ማለትም ተፈላጊውን ፍሬ ነገር ለፍርድ ቤቱ እንዴት እንደሚያስረዱ ይገልፃል በመሠረቱ ፍሬ ነገርን ለማስረዳት የሚቀርቡት ምስክሮች ብቻ ሳይሆኑ ሰነዶች እና ሌሎች ገላጭ ማስረጃዎች ጭምር ቢሆኑም ነገር ግን ምስክሮች የሚመረመሩበት ሥርዓት ለየት ያለ በመሆኑ በምስክሮች ቃል አቀባበል ሁኔታ ላይ ይህ ምዕራፍ እንዲያተኩር ተደርጐአል ምስክሮች በማስረጃነት ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ማስረጃ ተብሉ የሚቆጠረው በችሎት የሰጡት ቃል በመሆኑና በውሳኔ ጊዜም የሚመረመረው ይኸው ምስክሮች የሰጡት ቃል በመሆኑ የምስክሮች ቃል አቀባበል መሠረታዊ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው ችሎአል ወደ ዋናው ጉዳይ ከመገባቱ በፊት ግን የሚከተሉት ሁለት ነጥቦች ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል ቀሩ በወንጀልም ሆነ በፍትሐብሔር ጉዳይ ምስክሮች የሚመረመሩበት ሁኔታ የተወሰነ ልዩነት ቢኖረውም በአብዛኛው ተመሳሳይ ነው ለማለት ይቻላል በሁለቱም ጉዳዮች ምስክሮች ዋና ጥያቄ መስቀለኛ ጥያቄ እና ድጋሚ ጥያቄ ይጠየቃሉ ዳኞችም አስፈላጊ በሆነ ጉዜ በፍትሀብፄርም በወንጀል ክስ ለምስክሮች ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ ሩ በኢትዮጵያ የወንጀልም ሆነ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጐች መሠረት ምስክሮችን ችሎት የማቅረብ የቀረቡት ምስክሮች የሚያስረዱትን ፍሬ ነገር የማስመዝገብ እና የመመርመር ወይም የመጠየቅ መብቱም ግዴታውም የተከራካሪ ወገኖች ነው ፍርድቤቱ አስፈላጊ በሆነ ጊዜ በራሱ አነሳሽነት ማስረጃ የማስቀረብና ራሱም ሆነ ተከራካሪ ወገኖች ያቀረቡአቸውን ምስክሮች የመጠየቅ ሥልጣን ቢኖረውም ዋነኛው ግዴታ የሚወድቀው ግን በተከራካሪ ወገኖች ላይ ነው ስለዚህ የኢትዮጵያ የወንጀል ሥነ ሥርዓት ህግ የአንግሉ አሜሪካን የወንጀል ሥነ ሥርዓት አካሔድ ልሰህዘ ኮየርዐሀ የሚከተል ነው ማለት ይቻላል ይሪ ምዕያጡሮቻ ያታዕራትሪ ወፖኖቻ ፊፖ ፇረሃጃጃታ መመሰርያዖፇያፖው ቋሪመፖቅ ምስክሮች ቃላቸውን የሚሰጡበትና የሚመረመሩት ተከራካሪ ወገኖች ባሉበት መሆኑ የታወቀ ነው ጉዳዩ ወንጀልም ሆነ ፍትሐብሔር በመሠረቱ ልዩነት የለውም ተከሳሹ በሌለበት ጉዳዩ አንዲሰማ የታዘዘ በሆነ ጊዜየፍብሥሥሕቁሀ እና የወመህሥሥቁጥር ይመለከታል ምስክሮች ተከሳሽ በሌለበት ሊቀርቡ የሚችሉ ቢሆንም ነገር ግን ችሎት ቀርበው ቃላቸውን መስጠት ይኖርባቸዋል ይህ የሆነበት ምክንያትም አንድ ምስክር የሰጠው የምሰክርነት ቃል እውነተኛነት ወይም ሐሰተኛነቱ አርግጠኛነቱ ወይም አጠራጣሪነቱ የሚፈተነው በሚቀርብለት መስቀልኛ ጥያቄ በመሆኑና ይህ ሊፈፀም የሚችለውም ምስክር በችሉት የቀረበ ከሆነ ብቻ በመሆኑ ነው በተጨማሪም በወንጀል ጉዳይ ሊመሠከሩበት የቀረቡበትን ምስክሮች መመርመር የተከሳሹ ህገመንገሥታዊ መብት በመሆኑ ነውየኢፌዴሪሕገመንግስት አንቀጽ ስለዚህ ምስከር ተከራካሪ ወገን ባለበት ቀርቦ ማንነቱን አረጋግጦ የምስክርነት ቃሉን ሊሰጥ ይገባዋል በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል ጉዳይ በዐቃቤ ህግ በኩል የተቆጠረ ምስክር በተከሳሹ ፊት ቀርቦ የምስክርነት ቃሉን መስጠቱ ወይም የቀረበ ቢሆን እንኳ ማንነቱንና አድራሻውን በተከሳሹ ፊት መግለፁ ለደህንነቱ አላስፈላጊ ሁኔታ የሚፈጥርበት ቢሆንሰ። የቁጥር ድንጋጌን አተረጓጐም በተመለከተ የአገራችን ፍርድ ቤቶች በአብዛኛው የሚቀበሉት ጥርጣሬ በማያስነሳ ሁኔታ ማስረዳትን ነው በበርካታ የፍርድ ቤት ውሳፄዎች ላይ አንደሚታየው ዐቃቤ ህግ በሚያቀርበው ማስረጃ ተከሳሹ ወንጀሉን ስለመፈፀሙ ጥርጣሬ በማያስነሳ ሁኔታ ማስረዳት እንደሚገባው አቋም ይያዛል ለምሳሌ ሆኖም በወመህሥሥህቁ ላይ የተደነገገው በቂ የሚለው ቃል ምንም ጥርጣሬ በማያስነሳ ሁኔታ ማስረዳትን የሚመለከት አይደለም በቂ የሚለው ቃል ፍፁም የተሟላ የሚለውን ያመለክታል ለማለት አስቸጋሪ ነው በዚህም መሠረት በቁጥር መሠረት በቁ ነው የሚለው መመዘኛ በአንግሎ አሜሪካ የህግ ስርዓት በወንጀል ጉዳይ ተፈላጊው የሆነውን ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ የማስረዳት መመዘኛ ይመለከታል ለማለት አይቻልም ከላይ እንደተጠቀሰው ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ ሲባል የአስረጂነት ደረጃው ወደ መቶ በመቶ የተጠጋ እውነተኛነቱ የተረጋገጠን ማስረጃ የሚመለከት ሲሆን ይህ ደግሞ ከበቂ በላይ እንጂ በቂ ለማለት የማይቻል ነው ቁጥር ግን አስረጅነቱ በቂ እንዲሆን አንጂ ከበቂ በላይ ይሁን በማለት አይናገርም ከውሳጌ በፊት ጥፋተኛ ሆኖ ያለመቆጠር መብት በኢትዮጵያ ህግ ውስጥም የተካተተ ቢሆንም ይህ ማለት ግን ከኛ ህግ አኳያ ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ ማስረዳትን አይመለከትም ሁ እንዲሁም በቁጥር መሠረት ማስረጃው በቂ ለመሆን በአንግሎ አሜሪካ የህግ ስርዓት ተከታይ አገሮች ለአብዛኛው የፍትሐብሔር ጉዳዮች አስረጅነት በመመዘኛነት የሚያገለግለውን በይመስላል ወይም በተሻለ አስረድቷል ልበርፀ ዐ ዞኮዕኩቪሃ ዞዌፀዐበበር ያመለክታል ለማለት አይቻልም ለወንጀል ጉዳይ እንዲህ ዓይነት መመዘኛ የማይታወቅ ሲሆን ቁጥር ላይ ይህን መመዘኛ ለማንፀባረቅ ተፈልጐ ቢሆን ኖሮ ማፍረሻ ማስረጃ ሳያስፈልግ ተከሳሹን ጥፋተኛ የሚያደርገው ሆኖ ባልተገኘ ጊዜ ተከሳሽ በነዓ እንዲለቀቅ ፍቤቱ ያዝዛል ማለት ብቻ ይበቃ ነበርፊ ይህም ይበዛል ህጉ ግን ከዚህ በተጨማሪ እና ማስረጃው በቂ ሆኖ ሳያገኘው ሲቀር የሚል ጨምሮበታል ስለዚህ ያስረዳ ይመስላል የሚል መመዘኛ መጠቀም አንችልም ሁ ይልቁንም ቁጥር የሚቀርበው በአንግሎ አሜሪካን የህግ ስርዓት ተከታይ አገሮች ለምሰሌ በአሜሪካ በጣም ለተወሰኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮች ብቻ የሚውለው በሲቪል ህግ ሥርዓት ደግሞ ለፍትሐብሔርና ለወንጀል ጉዳዮችም ተመሳሳይ አገልግሎት ያለው ግልፅና አሳማኝ ማስረጃ በማቅረብ የማስረዳት መመዘኛ ነው ለማለት ይቻላል ስለዚህ በኛ አገር የወንጀል ጉዳይ የአስረጅነት ደረጃው ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ ወንጀሉን ስለመፈፀሙ ግልፅና ፍርድ ቤቱን የሚያሳምን ማስረጃ በማቅረብ ማስረዳት አለበት የሚለው ነው ይህ መመዘኛ በእኛ ህግ ተፈፃሚነት ካለው ሁ ዐቃቤ ህግ የአቀረበው ማስረጀ ተከሳሹ የተከሰሰበትን ወንጀል ለማቋቋም አስፈላጊ የሆኑን ነገሮች ሁሉንም በበቂ ሁኔታ ከላይ የተጠቀሰው መመዘኛ ማለት ነው ማስረዳት የሚጠበቅበት ሲሆን ከነዚህ መካከል አንዱን እነኳን ግልፅና አሳማኝ በሆነ ሁንታ ማስረዳት ካልቻለ መመዘኛውን አላሟላም ማለት ነው ሁ ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ምስክር በቀረበለት መስቀልኛ ጥያቄ ወይም በተከሳሽ መከላከያ ማስረጀ አማካኝነት ክብደት ከአጣ አሳማኝ ካልሆነ ማስረጃው በቂ ነው ለማለት አይቻልም ምክንያቱም ክብደት የአጣ ማስረጃ በሚያሳምን ሁኔታ ሊያስረዳ አይችልምና ሁ እንዲሁም ዐቃቤ ህጉ የአቀረበው ማስረጃ በግልፅ በሚታይ ሁኔታ የማይታመን በመሆኑ የተነሳ የጥፋተኛነት ውሳኔ ለመስጠት የማያስችል ሲሆን በለከበ ከ ፀኣዛብቁፀበርፀ ህር ከሃ ከ ዐየዕርህቨበ በበባበቨቪሃ ሀበከ በቂ ነው ለማለት አንችልም ከር ሾ ያፍሥፖለጩጨረ ፖዳፅ በኢትዮጵያ የፍትሐብሔርን ጉዳይ ለማስረዳት የቀረበ ማስረጃ አስረድቷል ለማለት መመዘኛው ምንድነው። ፖፈ ያምዕሮቻ ቃሷኋ መሳጎሷፀታፖ ዕለሟጸጳነያፖሐው ዉጨ የምስክሮች ቃል ዕርስ በርስ ሲገናዘብ ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፍተኛ ደረጃ ተመሳሳይ መሆኑ የሚደገፍ ነው ነገር ግን ምስክሮች የሰጡት የምስክርነት ቃል ሙሉ ለሙሉ መመሳሰል የምስክሮች ቃል ምንም የማይወጣለት እውነት ነው ብሎ በርግጠኛነት መደምደም አይቻልም ስለዚህም ማስረጃው ተመሳሳይ ሆኖ ቢገኝ አንኳን መገምገምና መመዘን አስፈላጊ ነው የአገራችን ፍቤቶች ማስረጃ ተመሳሳይ በሆነ ጊዜ የሚወሰዱት አቋም ሲታይ በአብዛኛው የማስረጃው ግምገማ የሚያተኩረው በመከላከያ ማስረጃዎች የምስክርነት ቃል ላይ ነው የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ቃል ተመሳሳይ ሲሆን ልዩነት በሌለው ሁኔታ አስረድቷል የሚል መደምደሚያ ሲሰጡ የመከላከያ ማስረጃ ቃል ተመሳሳይ ሲሆን ደግሞ የመከላከያ ምስክሮች የሰጡት ቃል ተመሳሳይነት ቢኖረውም በጥናት ላይ የተመሠረተ ነው በማለት ውድቅ ሲያደርጉት ይስተዋላል ይህ እንደአቋም መወሰድ የሌለበት ነው የምስክርነት ቃሉ ተመሳሳይነት ቢኖረውም የተለያዩ የመመዘኛ ስልቶችን በመከተል አውነትነቱ ሊጣራ የሚገባው መሆኑ አንደተጠበቀ ሆኖ ምዘናው ግን የዐቃቤ ህግንም ሆነ የመከላከያ ማስረጃን የሚያጠቃልል ነው በዚህም መሠረት እንዲህ ዓይነት የምስክርነት ቃል ሲመዘን የምስክሮቹ ቃል ትክክለኛነት ሊያስረዱ ከቀረቡበት ጭብጥና ከተከሰተበት ጊዜና ቦታ አንፃር ሊመዘን ይገባል ምስክሮች በዚያ ጊዜና ቦታ ለመገኘት ያላቸው አጋጣሚ ይመረመራል ምስክሮች ያስረዱበታል የተባለው ድርጊት ተከሰተ በተባለበት እና ምስክሮቹ ችሎት ቀርበው በመሰከሩበት ጊዜ መካከል ያለው ርቀት ግምት ውስጥ ሊገባ ይገባል ልዩነቱሰፊ በሆነ መጠን በተመሳሳይ ሁኔታ የማስታወስ ዕድል እየጠበበ ይሄዳል ማስረጃው ሊያስረዳ የቀረበበት ፍሬ ነገር ዓይነት ግምት ውስጥ ሊገባ ይችላል አደጋን ሐይማኖታዊ በዓላትን በሚገባ በማስተዋል ከረጅም ጊዜ በጊላም ለማስታወስ የሚቻል ሲሆን ተራ ክስተቶችን ግን ብዙ ሰዎች በተመሳሳይ ሁኔታ ከረጅም ጊዜም በኋላም ለማስታወስ ይከብዳቸዋል ምስክሮች የመሠከሩበትን ፍሬ ነገር አንድ ላይ ሆነው እንዴት ለመከታተል እንደቻሉ መመርመር አለበት ምስክሮች ከምስክር አቅራቢው ሰው የዐህግ ምስክር ከሆነ ከግል ተበዳይ ጋር ያላቸው የግል ወይም ማህበራዊ ግንኙነቶች ሊታዩ ይገባል በዝምድና በወዳጅነት የሚተሳሰሩ ምስክሮች ከማይተዋወቁ ምስክሮች የተሻለ የመጠናናት ዕድልና ፍላጐት ሊኖራቸው ይችላልና ፖ ኋይመፇታ ደታሪፉ ፉሪ ሮሪሮቻዐዘዝዐ ሮጄባነያፖታፖ ዉጨጨፖ ስለ አንድ ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ለማስረዳት የቀረቡ ምስክሮች በቂና የተሟላ መረጃ ቢሰጡ ምስክሮች የሰጡት ቃል የአስረጅነት መመዘኛውን ማሟላት አለሟሟላቱን ለመወሰን የበለጠ እንደሚረዳ የሚታወቅ ነው ሆኖም የቀረቡት ምስክሮች ሳይጠየቁ በመቅረታቸው ወይም ተጠይቀውም ማስታወስ ባለመቻላቸው ምክንያት ያልተጠቀሱ ነገሮች ይኖራሉ ከዚህ አንፃር ሳይጠቀሱ የታለፉ ነገሮች በማስረጃ ምዘና ላይ የሚያሳድሩት ተፅፅኖ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ጉዳዩ ወንጀል ወይም ፍትሐብሔር መሆኑ ልዩነት ሊፈጥር የሚችል ቢሆንም ሳይጠቀሱ የሚታለፍ ፍሬ ነገሮች በሁለቱም ጉዳዮች ላይ ተፅዕኖ ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ማወቅ ይገባል ሳይጠቀሱ ወይም ሳይገለፁ ወይም ሳይቀርቡ የሚታለፉ ፍሬ ነገሮች በመሠረቱ ምስክሮች በሰጡት ቃል ውስጥ የሚንፀባረቁ ቢሆኑም ከዚህ አልፎም ሌሎች ማስረጃዎችንም ሊመለከቱ ይችላሉ ከዚህ አንፃር አስተማማኝ መደምደሚያ ለመስጠት የሚያስችሉ ሌሎች ማስረጃዎች አለመቅረብም አብሮ ሊታየ የሚገባው ነው በዚህም መሠረት ሃሦ ድርጊቱን ለመፈፀም ያነሳሳ ምክንያት ጠዐርከህ ሳይገለፅ ቢቀር ድርጊቱ መፈፀሙን ወይም ተፈፅሞም ከሆነ የምክንያትና ውጤት ግንኙነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ማስረጃ አለመቅረብ የህክምና ማስረጃ አለመቅረብ ድርጊት የተፈፀመበት መሳሪያ አለመቅረብ ወይም አለመታወቅ ሃ ጊዜና ቦታው አለመገለፅ አዘውትረው የሚያጋጥሙ ሲሆኑ ዋና ዋናዎቹ ማለትም መነሻ ምክንያት አለመገለፅ የሀኪምና ማስረጃ አለመቅረብና ድርጊቶች የተፈፀሙበት መሳሪያ አለመቅረብ የምስክሮችን ቃል በመመዘን ረገድ የሚያስከትለውን አስተዋጽኦ ቀጥሎ ይንገለፃል ድረመሟፖ ሐመፈጮም ያሃዕጎሳጎ ምችዖትቻ ዕጋዐዕህህ ለሪመሪ ማስረጃ ሊያስረዳበት የቀረበው ጭብጥ ወይም ፍሬ ነገር አንድ አድራጐትን የሚመለከት የሆነ እንደሆነ ይህንን ድርጊት ለመፈፀም ያነሳሳ ምክንያቶች መታወቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው በተለይ በወንጀል ጉዳይ ላይ ይህ መታወቁ አስፈላጊነቱ ከፍተኛ ነው የጥፋተኛነት ውሳኔን ከማስገኘት አንፃር ወንጀሉን የሚያቋቁመውን የሀሳብ ክፍል ለማረጋጥ ድርጊቱን ለመፈፀም ያነሳሳው ምክንያት መታወቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው በሌላ በኩል ደግሞ የቀረበው ማስረጃ ድርጊቱን መፈፀሙን ቢያስረዳም ለመፈፀም ምክንያት የሆነውን ፍሬ ነገር አለመጥቀሱ ማስረጃውን ሁል ጊዜም ሚዛን ያሳጠዋል ለማለት አይቻልም በብዙ የወንጀል ጉዳዮች ላይ ድርጊቱን ለመፈፀም ያነሳሳ ምክንያት ከሀሳብ ክፍሉ ጋር የማይገናኝ ሊሆን አንደሚችል መታወቅ አለበት ለምሳሌ በቸልተኛነት ለሚፈፀም ወንጀል የሀሳብ ክፍሉ ተገቢ ጥንቃቄ አለማድረግ ስለሚሆን ከዚህ አልፎ ድርጊቱን ለመፈፀም ያነሳሳው ምክንያት ጠዐከህ መረጋገጥ አለበት የሚል አቋም መውሰድ አይገባም በተጨማሪም የድርጊቱን አፈፃፀም የሚያስረዳ ማስረጃ እግረ መንገዱን ምክንያቱን ለማረጋገጥ ሊረዳ ይቻላል ከባለቤቱ ፈቃድ ውጭ የሰው ቤት ዘው ብሎ ገብቶ ዕቃ ወስዶ የተገለገለበት እንደሆነ ንብረቱን የወሰደው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት በማሰብ መሆኑን ድርጊቱ ራሱ ያረጋግጥልናል ስለዚህም ድርጊቱን ለመፈፀም መነሻ ምክንያት መጠየቅ አስፈላጊ መሆኑን አስቀድሞ መመርመር ያስፈልጋል ድርጊቱን ለመፈፀም ምክንያቱ ከድርጊቱ አፈፃፀም ሊታወቅ የሚችልበት ሁኔታ ሊኖር አንደሚችል ማወቅ ያስፈልጋል ሃሦ ይኸው ምክንያት አስፈላጊ መሆኑ ተረጋግጦ ነገር ግን የቀረበው ማስረጃ ላይ ያልተገለፀና ከተጠቀሰው የማስረጃ ቃልም የማይገኝ ከሆነ በውሳኔ አሰጣጥ ላይ የሚያስከትለውን ውጤት ከድርጊቱ አፈፃፀም አካባቢያዊ ሁኔታዎች ጋር በማገናዘብ መመርመር ያስፈልጋል ፖልጋ ያሀቪቋምና ማዕረያ ሰሐመቃዎረሀ በአካል ወይም በህይወት ላይ በደረሰ ጉዳት ምክንያት ለሚቀርብ የወንጀል ወይም የፍትሐብሔር የጉዳት ካሳ ክስ ጉዳይ የህክምና ማስረጃ መቅረቡ የሚሰጠው አገልግሎት ከፍተኛ ነው ይህ ማስረጃ መቅረቡ ሃ በምክንያትና በውጤት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማረጋገጥ ያስችላል የተከሰሰው ሰው ፈፀመው የተባለውና በምስክሮች የተናገረው ድርጊት ግድያ ወይም አካል ማጉደል በርግጥም የተፈፀመ መሆኑን ለማረጋገጥ የጉዳቱን ደረጃና መጠን ለማወቅ በወንጀል ከባድ የአካል ጉዳት ነው ወይስ ቀላል የሚለውን ለማወቅ በፍትሐብሔር ደግሞ የጉዳቱን ደረጃና የካሳውን መጠን ለመወሰን ያገለግላል በሌላ በኩል ደግሞ ተፈላጊው ፍሬ ነገር መኖሩን ወይም አለመኖሩን ለማረጋገጥ የህክምና ማስረጃ የግዴታ መቅረብ አለበት መባል የለበትም ሰው ሲሞት ወይም የአካል ጉዳት ሲደርስበት በሐኪም መመርመር አለበት የሚል አስገዳጅ ደንብ በሌለበት ሁኔታ ህክምና ለማግኘት የማይቻልበት በርካታ ምክንያት መኖሩ እየታወቀ ፍሬ ነገሩ መኖሩ ወይም አለመኖሩ በህክምና ማስረጃ አልተረጋገጠም ወይም አልተደገፈም በሚል ምክንያት የምስክሮችን ቃል ማጣጣል ተገቢ አይደለም የህክምና ማስረጃ ሊቀርብ ያልቻለበትን ምክንያት መጠየቅ ተገቢ ይሆናል ነገር ግን ይህ ማስረጃ ባይኖርም ምስክሮች የሰጡትን ቃል መመዘንና ይኸው ቃል በራሱ ፍሬ ነገሩ መኖሩን የሚያረጋግጥ ከሆነ ወደዚህ መደምደሚያ ላይ መድረስ ይገባል ስለዚህ ጠንካራ መሠረት ያለው የምስክርነት ቃል በህክምና ማስረጃ አልተደገፈም ተብሎ ውድቅ ሊደረግ አይገባም ፖይዉ ታዎ ይሳፖያጵ ፉሬ ሮሪሮቻ መፀም ማዕረጀመምቻ በወንጀል ጉዳይ ወንጀል የተፈፀመበት መሳሪያ ወይም የወንጀል ውጤት የሆነ ነገር በማስረጃነት ሳይቀርብ ሊታለፍ ይችላል ወይም ምስክሮች ሳይገልፁት ሊያልፉ ይችላሉ ወይም ቀርቦ እያለ ምስክሮች ለይቶ ለማመልከት ሊቸገሩ ይችላሉ ወይም ድርጊቱን ፈፀመ በሚል ስሙን የገለፁትን ሰው እንዲያሳዩ ሲጠየቁ ማሳየት ሊያቅታቸው ይችላል ይህ በምስክሮች ቃል ምዘና ላይ የሚያስከትለው ተፅዕኖ ምንድ ነው። ሥ ፓ»ቃምያጎፖው ምዕሮቻ ደምዕረን ቃሳ ምሃና በወንጀልም ሆነ በፍትሐብሔር ጉዳይ የአስረጅነት ደረጃው እና በማስረጃ ምዘና ሂደት የሚሰጠው ክብደት የተለያየ ቢሆንም በምስክርነት የሚቀርቡ ሰዎች በሚመሠከሩበት ጉዳይ አወሳሰን ላይ የተለየ ጥቅም ወይም ፍላጐት ሊኖራቸው ይችላል ተከራካሪ ወገኖች በራሳቸው ጉዳይ ምስክር በመሆን በወንጀል ጉዳይ የግል ተበዳዩን ይጨምራል ወይም ምስክሮቹ ከተከራካሪ ወገኖች ጋር ባላቸው ፀብ ዝምድና ወይም የተለየ የጥቅም ተጋሪነት ወይም ወዳጅነት መነሻ ወገንተኛነት በማሳየት በጉዳዩ አወሳሰን የተለየ ፍላጐት ሊኖራቸው ይችላል ወይም ደግሞ አብረው በግብረ አበርነት ከተከሰሱት መካከል ወይም በፍትሐብሔር ጉዳይ ተጣምረው ከከሰሱት መካከል አንደኛው በሌላኛው ላይ ወይም ሌላኛው ምስክር ሆነው ሊቀርቡ ይችላሉ በዚህ ሁኔታ ግንኙነት ያላቸው አና ወገንተኛ ይሆናሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች የተለየ ጥቅም ያላቸው ምስክሮች በበጤጪጨ ክቪበ የሚባሉ ሲሆን የምስክርነት ቃላቸው ሲመዘን ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው በዚህ ክፍል እንደነዚህ ዓይነት ምስክሮች የሚሰጡት ቃል ሲመዘን ግምት ውስጥ ማስገባት የሚገቡ ነገሮች በአጭሩ ይገለፃሉ ልዉ ያያ ዉይም ምድና ምስክሮች ከተከራካሪ ወገኖች ጋር ፀብ ወይም ዝምድና ቢኖራቸውም ከመመስከር ሊከለከሉ አይችሉም ሆኖም ፀብ ወይም ዝምድና መኖሩ ከታወቀ የምስክርነት ቃላቸው አውነተኛ መሆኑ ወይም ደግሞ በዚህ ፀብ ወይም ዝምድና መነሻ የተፈጠረ የተጋነነ ወይም የተምታታ መሆኑ በጥንቃቄ ሊመዘን ይገባዋል ፀብ ወይም ዝምድና መኖሩ አስቀድሞ ሊረጋገጥ የሚገባው ነገር ነው ዝምድና ትርጉሙ ሊሰፋም ሊጠብም የሚችል መሆኑ መታወቅ አለበት በጐሳ ላይ የተመሠረተ ዝምድና ሊጠቀስ የሚችለውን ያህል ቅርብ የሥጋ ወይም የጋብቻ ዝምድናም ከዝምድና የማይቆጠርበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል ፀብን በተመለከተም ማናቸውም ዓይነት አለመግባባት ፀብ ያሰኛል ማለት አይቻልም የሆነ ሆኖ ፍቤቱ የምስክርነት ቃሉን ሲመዝን ይመሠክሩበታል ከተባለው ፍሬ ነገር ወይም ጭብጥ አካባቢያዊ ሁኔታ አንፃር ማየትና የተሰጠው የምስክርነት ቃል አውነተኛ መሆኑን ወይም ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት በማሰብ የተቀነባበረ የተጋነነ ወይም የወረደ መሆኑን ግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል ፖልጋ ያዖዖፅዕራጓሪ ወ ምዕረንፖ በወንጀልም ሆነ በፍትሐብሔር ተከራካሪ ወገኖች በራሳቸው ጉዳይ የምስክርነት ቃል ሊሰጡ ይችላሉ በወንጀል ጉዳይ የግል ተበዳዩ በከሳሽ ዐቃቤ ህግ በኩል እና ተከሳሹ በፍትሐብሔር ጉዳይ ደግሞ ከሳሽና ተከሳሽ ለራሳቸው ጉዳይ ምስክር መሆን ይችላሉ በሌላ በኩል ደግሞ አነዚህ ምስክሮች በጉዳዩ አወሳሰን የተለየ ፍላጐት ሊኖራቸው እንደሚችልና እንደሚጠበቅም መታወቅ አለበት ከዚህ አንዛር ከግል ተበዳይ ውጭ ያሉ ከሳሽም ሆነ ተከሳሽ የሚሰጡት ቃል ክርክራቸውን የሚያጠናክር በመሆኑ ምስክርነታቸው ክብደት ሊሰጠው አይገባም ው በወንጀል ጉዳይ የግል ተበዳይ ምስክር ሆኖ በራሱ ላይ ስለአደረሰው ጉዳት የሚሰጠው የምስክርነት ቃል እውነተኛነቱ ተፈፀመ ከተባለው ድርጊት ከባድነት እና ከአፈፃፀሙ አካባቢያዊ ሁኔታ አንፃር ሊገመገም ይችላል ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰበትና ለምሳሌ አይን መጥፋት ይህንን ለማስረዳት የመጣ የግል ተበዳይ አይኑ መጥፋቱ እስከተረጋገጠ ድረስ አይኑን ያጠፋውን ሰው ትቶ ሌላ ሰው ይወነጅላል ለማለት አዳጋች ሊሆን ይችላል በዚህ ጊዜ ዋናው መመዘኛ ምስክሩ ድርጊቱን የፈፀመው ተከሳሽ መሆኑን ሊያረጋግጥ የቻለበት ሁኔታ ነው በሌላ በኩል ቀላል ጉዳት ወይም የእጅ አልፊት ወይም ስም ማጥፋትን ለማስረዳት የሚቀርብ የግል ተበዳይ የሚሰጠው የምስክርነት ቃል ከሆነ እውነቱ በከፍተኛ ጥንቃቄ ሊመረመር ይገባል ሀበሀ ልበ ሀከሟ ገፅ እንዲሁም አንዳንድ ወንጀሎች በባህሪያቸው ከግል ተበዳይ ሌላ ማስረጃ ሊገኝ የማይችልባቸው ወይም የግል ተበዳይ በርግጥ ካልተፈፀመበት በስተቀር አደባባይ የማያወጣቸው ሊሆኑ ስለሚችሉ ይህም በማስረጃ ምዘና ግምት ውስጥ ሊገባ ይገባል ለምሳሌ በአብዛኛው የመድፈር ወንጀል የሚፈፀመው ከግል ተበዳይ ውጭ ሌላ ሰው በሌለበት ሁኔታ ሲሆን ተደፍራለች የተባለችው ሴትም መደፈርዋ እርግጥ ካልሆነ በስተቀር አንዳንዴ ተደፍሬያለሁ የሚባልበት የተለየ ምክንያት ቢያጋጥምም ተደፍሬያለሁ ብላ አደባባይ ስለማትወጣ ማስረጃው ክብደት ሊሰጠው ይገባል በሌላ ደጋፊ ማስረጃ አላስረዳህም በሚል ውድቅ ማድረግም አይገባም ፖዉዉ ያፇረ ፀር ምዕረን በመሠረቱ ግብረ አበር የሆነ ሰው አብሮት በተከሰሰው ላይም ሆነ ለዚሁ ሰው ምስክር አንዳይሆን የሚከላከል ህግ የለም በፍትሐብሔር ጉዳይ በጣምራ የከሰሱ ወይም የተከሰሱ ሰዎችም አንደኛው ለሌላኛው ሊመሰክሩ ይችላሉ ያም ሆኖ ግን አብሮት ለከሰሰው ወይም ለተከሰሰው ሰው በመርዳት ወይም ኃላፊነቱን ከራሱ አውርዶ አብሮት የተከሰሰው ሰው ኃላፊነቱን እንዲሸከም በማድረግ ዓላማ በመጉዳት የምስክርነት ቃሉን ፀ ሊሰጥ ይችላል ስለዚህ የምስክርነት ቃላቸው ሲመዘን በዋናነት ለመመስከር የተነሳሱበት ምክንያት ግምት ውስጥ መግባት አለበት ፖፖ ሳጾዶመደሀያጎፖው ምዕዕሮፖዎቃጳ ምኖና ፖፖ ያሀፃናኖ ምዕዳረንፖ ቃሳ ምሃና ህፃናት የሚጠየቁትን ጥያቄ መገንዘብና መልስ መስጠት እስከቻሉ ድረስ በምስክርነት ከመቅረብ እንደማይከለከሉ አስቀድሞ ተገልያአል ነገር ግን የሚሰጡት የምስክርነት ቃል በጥንቃቄ ሊመዘን ይገባዋል በጥንቃቄ ሊመዘን ይገባል የተባለውም ህፃናት ማስረጃ ስለሚሆነበት ጉዳይ በሌሎች ሰዎች ተፅዕኖ ስር በቀላሉ ሊወድቁ ስለሚችሉና ሊደለሉም ስለሚችሉ ከተገነዘቡት ፍሬ ነገር ውጭ በሰዎች ግፊት ትክክለኛ ያልሆነ ምስክርነት ይሰጣሉ የሚል ስጋት ስላለ ነው ነሃ ፀ በዚህም መሠረት የህፃናት የምስክርነት ቃል ሲመዘን ው ፅድሜያቸው ግምት ወስጥ ሊገባ ይገባል ዕድሜያቸው ትንሽ በሆነ መጠን የመደለል ወይም በሌላ ተፅፅኖ ሥር የመውደቅ ዕድላቸው የሰፋ ሊሆን ይችላል ው የሰጡት የምስክርነት ቃል ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር ያለው አንድነትና ልዩነት መገናዘብ ይኖርበታል ው ይመሠከሩበታል የተባለው ፍሬ ነገር በተከሰተበትና ቀርበው በመሠከሩበት ጊዜ መካከል ያለው ልዩነት ግምት ውስጥ ሊገባ ይገባል ጊዜው ሰፊ በሆነ ቁጥር የማስታወሱ ሁኔታ እየደከመ ይሄዳል ተብሎ ይገመታል በ ዞ ፖፖፎጆ ሪድማሜ ያፉ ይነነ ዉይም ሰሪምሮ ፇሦድፅቋፖ ያጎያምው ምዕሮቻ ቃሰ ምሃና በማስረጃነት የቀረቡት ምስክሮች የዕድሜ መግፋት የተነሳ የማስታወስ ችሎታቸው የጠፋ ባይሆንም የደከመ ሊሆን ይችላል ወይም በአዕምሮ ወይም በአካል ጉዳት የተነሳ ምስክርነታቸው የተሟላ ላይሆን ይችላል ያም ሆነ ይህ በምስክርነት እስከቀረቡና ቃላቸውን እስከሰጡ ድረስ የሰጡት የምስክርነት ቃል ሊመዘን ይገባዋል እነዚህ ምስክሮች የሰጡት የምስክርነት ቃልም በሌላ ደጋፊ ማስረጃ መታገዝ አለመታገዙን ማረጋገጥ ጠቃሚ ነው ፖፖዉ ያይሌዕሃፖ ማዕረ ምሃና ኤክስፐርቶች ወይም ልዩ አዋቂዎች ችሎት ቀርበው የምስክርነት ቃላቸውን በሚሰጡበት ጊዜ ምስክርነታቸው ሳይመዘን በቀጥታ አስረጅነትን ያገኛል ማለት አይቻልም ኤክስፐርት የሰጠው ምስክርነት ነው ስለተባለ ፍቤቱ እንዳለ በጥሬው መቀበል አይገባውም ከሌሎች ማስረጃዎች የተለየ ክብደት ይሰጠዋል ማለትም አይደለም አለማየሁ ኃይሌ ገፅ ስለዚህም ፍርድ ቤቶች የኤክስፐርት ማስረጃን እንዳለቀ ነገር አድርገው ለመቀበል የማይገደዱ ሲሆን ይህንን ማስረጃ ስለተሰጠው የኤክስፐርት አስተያየት ትክክለኛነት የቀረቡ ማረጋገጫዎችን ኤክስፐርቱ አስተያየቱን ወይም መደምደሚያውን የሰጠው የራሱን እውቀትና ምርመራ ተጠቅሞ ወይም ሌላ ባለሞያነቱን ፍቤቱ ያላረጋገጠውን ሰው ጠይቆ ያገኘውን መረጃ መሠረት በማድረግ መሆኑን ው ኤክስፐርቱ በተያዘው ጉዳይ ላይ ያለውን ገለልተኛነት ማለትም ኤክስፐርቱ የተጠራው በማን ወገን ነው ከጉዳዩ ጋር ያለው የግል ግንኙነትስ ምን ይመስላል ከሚሉት ጥያቄዎች አንፃዛር ኤክስፐርቱ እንዲያረጋግጥ ወይም አስተያየት እንዲሰጥ ከተሰጠው መመሪያ ወይም ጥያቄ ጋር የሰጠው አስተያየት ያለውን ግንኙነትወዘተ መሠረት በማድረግ ሊገመግመው ይገባል ዓለማየሁ ኃይሌ ገፅ የጠፍቤት ፍይመቁ ኹ ምዕራፍ የሰነዶችንና ኤግዚቢት ማስረጃዎችን አስረጂነት ስለመመዘን ዝርዝር አላማዎች ሰልጣኞች ይህንን ምእራፍ ሲያጠናቅቁ ማስረጃዉን ለመስጠት ያላቸዉን ብቃትና ቅርበት መሠረት አድርገዉ የጽሁፍ ማስረጃዎችን የመመዘን ክህሉት ያገኛሉ የፅሁፍ ሰነዶች በሚቃረኑበት ጊዜ እንዴት ማስረጃን መመዘን እንዳለባቸዉ በቂ ግንዛቤ ያገኛሉ ተግባር ላይም ያዉላሉ በኦዲት ማስረጃዎች ላይ የሚቀርቡ መቃወሚያዎችን በአግባቡ በማስተናገድ መመዘን ይችላሉ የህትመት ዉጤቶችን የቴፕና የቪዲዮ ካሴቶችን የፎቶግራፍ ማስረጃዎችንና የኤግዚቢት ማስረጃዎችን የመመዘን ክህሎት ይረዳሉ ተግባር ላይም ያዉላሉ ጋፇጎጎ ዉድ ሠልጣኞች በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ጉዳይ ፍሬ ነገርን ለማስረዳት ወይም ለማስተባበል ሰነዶችና ኤግዚቢቶች በማስረጃነት ሊቀርቡ እንደሚችሉ በማስረጃነት ሲቀርቡ ግን አግባብነት አንዳላቸውና መቅረባቸውን የሚከላከል ህግ አለመኖሩ ሊረጋገጥ አንደሚገባ በምዕራፍ ላይ ተጠቅሶአል የአንዳንድ ፍሬ ነገሮችን መኖር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሰነድ ማስረጃዎች ብቻ ሊቀርቡ እንደሚገባ ህግ የሚደነግግበት ሁኔታ መኖሩን ተመልክቶአል ዉድ ሠልጣኞች እነዚህን ጥያቄዎች በግላችሁ ሞክራቸዉ ሀ የጽሁፍ ማስረጃዎች እንዴት ሊመዘኑ ይችላሉ። በዚህ ምፅራፍ የምንመለከተው የሰነድ ማስረጃዎች ወይም ኤግዚቢቶች ማስረጃ ሆነው ከቀረቡ በኋላ የሚመዘነበት ሁኔታ ነው ማለትም የሰነድ ማስረጃ ወይም ኢግዚቢት የተፈለገውን ፍሬ ነገር መኖር ማስረጃነቱን ወይም ማስተባበሉን ለመወሰን የማስረጃ ምዘና ተግባር ሲከናወን ግምት ውስጥ ሊገቡ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ትኩረት ይሰጣል ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ከመገባቱ አስቀድሞ ግን የሚከተለው ሐሳብ በማስታወሻነት ሊያዝ ይገባዋል ይኸውም ሰነዶችና ኤግዚቢቶች አግባብነት አላቸው የተባሉትን ፍሬ ነገሮች ከማስረዳት አንፃር አስተማማኝ ቢመስሉም ነገር ግን በጥልቀት ሲመረመሩ እና ሲመዘኑ አስተማማኝነታቸው ከምስክሮች ቃል የተሻለ ላይሆን ይችላል የጽሁፍ ሰነድ ወይም ካሴት ወይም ፎቶ ግራፍ ወዘተ ቀረበ ስለተባለ ከምስክር ቃል የበለጠ በአስተማማኝነት የሚያስረዳ መስሎ ቢታይም ነገር ግን አስተማማኝነቱን ሊሸረሸሩ ለሚችሉ በርካታ ጥያቄዎች የተጋለጠ ነው ምስክሮች የፈለገ ተዘጋጅተው ቢቀርቡ ችሎት ላይ ከሚከናወን መስቀልኛ ጥያቄ ጋር ፊት ለፊት ስለሚጋፈጡ የሰጡት መልስ እውነተኛነት ወይም ሐሰተኛነት ተአማኒነት ወይም አጠራጣሪነት በቀላሉ ሊታወቅ ይችላል ችሎት የምስክሮች እውነተኛነትና ሐሰተኛነት ማረጋገጫ መድረክ ነው በሰነድ ላይ የተገለፀ ፍሬ ነገር ግን ከችሎት ውጭ የተፈጠረ አንደመሆኑ ማን አንደፈጠረው መቼ አንደፈጠረው እና ለምን ዓላማ እንደፈጠረው ሰነዱ ራሱ አይናገርም ወይም ቢናገርም አስተማማኝነቱ ጥያቄ ሊያስነሳ የሚችል ነው እነዚህን ለመሠሉ ጥያቄዎች የሚሰጠው መልስ በሌላ ደጋፊ ማስረጃ ላይ የተመረኮዘ ነው ስለዚህ የሰነድ ማስረጃ ቀረበ ማለት በሰነዱ ላይ የተገለፀው ፍሬ ነገርን ባለቀለት ሁኔታ አስረዳ ማለት አይደለም በሚገባ ሊመዘን ይገባዋል ከላይ ከተገለፀው በተጨማሪም የሰነድ ወይም ኤግዚቢት ማስረጃዎች ምዘና በማስረጃው አይነት የተነሳ የተለየ ምዘና ሂደት የሚከተል ቢሆንም ከምስክሮች ምዘና ጋር በተያያዙ የተገለፁት ማስረጃው ያስረዳቸዋል የተባሉትን ፍሬ ነገሮች በሚገባ የመለየት ው በምክንያትና በውጤት መካከል ያለውን ግንኙነት በሚገባ የመለየት እንዲሁም ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ ምዘና ዘዴዎች በሰነድና ኤግዚቢት ማስረጃ ምዘና ላይም እንደ አግባብነታቸው ተፈፃሚ ይሆናሉ አስቀድሞ እንደተገለፀው የዚህ ምፅራፍ ትኩረት የሰነድ እና ኢግዚቢት ማስረጃዎች ምዘና ነው ከዚህ አንፃር የሰነድ ማስረጃ ምዘና የሚመለከታቸው በጽሁፍ የቀረቡ ሰነዶች የቴፕና የቪዲዮ ካሴቶች የፎቶ ግራፍ ማስረጃዎች ወዘተ ሲሆኑ ኤግዚቢቶች ተብለው የሚገለፁት ደግሞ ፍሬ ነገርን ያስረዳሉ ተብለው የቀረቡ ነገሮች ዕቃዎች መሳሪያዎች ናቸው በዚህ ምዕራፍ ትኩረት የሚሰጥባቸውም በሥራ አጋጣሚ አዘውትረው በማስረጃነት ሲቀርቡ የሚስተዋሉት በጽሁፍ የተደረጉ ሰነዶች እና የቴፕና የቪዲዮ ካሴት እንዲሁም የፎቶግራፍ ማስረጃዎች ሲሆኑ በምዕራፉ የተገለፁት ሀሳቦች ከፍርድ ውሳኔዎችና ከሌሎች አገሮች ህጐች ወይም ጽሁፎች እንዲስማሙ ተደርገው የተወሰዱ ናቸው ገለፃውም በአጠቃላይ ነጥቦች ላይ ብቻ የሚያተኩር ነው ያጽሥፍዕይድ ማዕረፍምቻምቭሃና ዝቃታና ቀረያታፖ መሥረፖ ይሮደረሃ ምሃና የሰነድ ማስረጃ ሲመዘን ትኩረት ሊደረግባቸው ከሚገቡ ጉዳዮች አንዱ ማስረጃውን ያዘጋጀው ወይም የሰጠው አካል ይህንን ለመፈፀም ያለው ብቃት ወይም ቅርበት ነው የጽሑፍ ሰነዱ ያዘለው ፍሬ ነገር ውሳኔ ለመስጠት አስፈላጊ የሆነውን ፍሬ ነገር ያስረዳ ይሆናል ነገር ግን ፍሬ ነገሩ ተፈላጊውን ፍሬ ነገር ወይም ጭብጥ ያስረዳል ስለተባለ ብቻ ክብደት ይሰጠዋል ማለት አይቻልም ሟች የሞተበትን ምክንያት ለማወቅ የህክምና ማስረጃ አስፈላጊ የመሆኑን ያህል በማስረጃነት የቀረበው ሰነድም ሟች የሞተበትን ምክንያት የመግለፁን ያህል ይህንን ያረጋገጠው ሰው ወይም ድርጀት ማስረጃውን ለመስጠት የሙያ ብቃት ከሌለው በሰነዱ ላይ ለተጠቀሰውና ስለሟች ሞት ምክንያት ለሚናገረው ክብደት ሊሰጠው አይችልም ስለዚህም የሰነድ ማስረጃ ሲመዘን ው ማስረጃ ሰጭው ተፈላጊውን ማስረጃ ለመስጠት ሥልጣን አለው ወይ። ፅ የመሆን ዕድሉ የሰፋ በመሆኑ አስረጅነቱ ሲመዘን ከተቀዳው ወይም ከተቀረፀው ድምፅ ወይም ምስል ሙሉ ይዘት የንግግሩ ወይም ድርጊቱ ዓላማ አንፃር በማገናዘብ መመዘን ያስፈልጋል ለሃ ፀ ፀዉፈ ያፎፇ ራፍፉ ማሰዕረደምቻፅሰረሯድኑሦፖ ምና ፎቶ ግራፍ የአንድን ሰው ማንነት ዐበከከ ወይም የተጐጂውን የአካል ጉዳት ወይም የተሰረቀውን ንብረት ወይም ወንጀል የተፈፀመበትን ቦታ የሚመለከት ሊሆን ይኝላል ያም ሆኖ ግን የፎቶግራፍ ማስረጃ ሲመዘን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል በመሠረቱ ስለቴፕና ቪዲዮ ካሴቶች ከላይ የተገለፁት ለፎቶ ግራፍ ማስረጃዎች ምዘናም አግባብነት አላቸው በተጨማሪም በማስረጃነት የቀረበው ፎቶግራፍ የታተመው ከመጀመሪያው ምንጭ እህ መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ይሆናል እሃ ሀ በአጠቃላይም የህትመት ውጤቶችን የቴፕና የቪዲዮ ካሴቶችን እና ፎቶግራፎችን አስረጅነት ለማረጋገጥ የሚደረግን ጥብቅ የማስረጃ ምዘናን በተለይ በወንጀል ጉዳይ ፍቤቱ የሚከተለው ፍርድ ቤት እውነትን ይገልፃል ብሎ በማያምንበት ማስረጃ ላይ በመመስረት ውሳኔ መስጠት የለበትም የቀረበው ማስረጃ በተቻለ መጠን እውነቱን የሚያረጋግጥ መሆን አለበት በሚለው ምክንያት መነሻ ነው እሃ ፀ ሯግ ይፈ ይእቪሂደፈፖ ማዕረያሰሰረሯቻንታ ምሃና የኤግዚቢት ማስረጃ ዋነኛ አስተወጽኦው አካባቢያዊ ማስረጃ በመሆን ስለተፈለገው ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ግንዛቤ እንዲወስድ ማድረግ ነው ስለዚህ የኤግዚቢት ማስረጃ በሌላ ማስረጃ የተነገረውን በመደገፍ ቨከዐሀበ ማገልገል እንጂ ሌላ ማስረጃ በሌለበት በራሱ ተፈላጊው ፍሬ ነገር መኖሩን ወይም አለመኖሩን ያረጋግጣል ማለት አዳጋች ነው ያም ሆኖ ግን ሌሎች ማስረጃዎችን የማጠናከር አስተዋጽኦው ከተፍተኛ ነው ለምሳሌ በወንጀል ጉዳይ ተሰረቀ የተባለውን ዕቃ በማየት በምስክሮች ጤት ገብቶ ዕቃውን ካወጣ በላ ተሸክሞ ሲሮጥ አይቻለሁ በሚል ከተነገረው ቃል ጋር በማገናዘብ ዕቃውን ሰው ተሸክሞት ሊሮጥ የሚችል መሆን አለመሆኑን ፍቤቱ ሊረዳው ይችላል ግድያ ለመፈፀም አገልግሎት ላይ የዋለ ነው በሚል የቀረበን ዱላ በማየት ዱላው ሰው መግደል የሚያስችል መሆን አለመሆኑን ለመገንዘብና ተከሳሹ ደበደበ በሚል በተናገሩት ቃሎችና ሞተ በተባለው ሰው ሞት መካከል የምክንያትና የውጤት ግንኙነት እንዳለና እንደሌለ ለመገመት ያስችላል በአጠቃላይ የኤግዚቢት ማስረጃ ምዘና በሌላ ማስረጃ የተናገረውን ፍሬ ነገር ትክክለኛነትን ወይም ተዓማኒነት በመገንባት ወይም በማፍረስ ላይ ያተኮረ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ምዕራፍ የእምነት ቃል አስረጂነትን ስለመመዘን ዝርዝር አላማዎች ሰልጣኞች ይህንን ምእራፍ ሲያጠናቅቁ በፍርድ ቤት እና ከፍርድ ቤት ውጪ የሚሰጡ የእምነት ቃሎችን ይለያሉ የእምነት ቃል አስረጅነት በፍትሀብፄሄርና በወንጀል ጉዳይ መመዘን ክህሎት ያዳብራሉ ጋቃጎጎ በምዕራፍ ላይ ማስረጃ ማቅረብ ስለማያስፈልጋቸው ፍሬ ነገሮች በሚል ርዕስ ስር ከተጠቀሱት ጉዳዮች መካከል የታመኑ ፍሬ ነገሮች እንደሚገኙበት የታመኑ ፍሬ ነገሮችን ከፍቤት ውጪ እና ከፍቤት ውስጥ በሚል ከፋፍሎ ማየት እንደሚቻል ከነዚህ ውስጥም ከፍቤት ውጪ የታመኑ ፍሬነገሮች ተፈላጊውን ፍሬ ነገር በተመለከተ በራሳቸው ማስረጃዎች ሲሆኑት ነገር ግን ማስተባበያ ማስረጃ ሊቀርብባቸው አእንደሚችል በፍቤት ውስጥ የታመኑ ፍሬ ነገሮች የሚባሉት ደግሞ በፍትሐብሔር ጉዳይ ማስተባበያ ማስረጃ ሳይቀርብባቸው ለታመነው ፍሬ ነገር መኖር ማረጋገጫ ተደርገው ሊወሰዱየወንጀል ጉዳይ ከሆነ ግን እንደሁኔታው በከሳሽ ማስረጃነት ከመቆጠር እና በሌላ ማስረጃ ከመደገፍ አልፈው ማስተባበያ ማስረጃ ሊቀርብባቸው አንደሚችል ወይም እንዳለቁ ፍሬ ነገሮች ተቆጥረው ማስተባበያ ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ የጥፋተኛነት ውሳኔ ሊያሰጡ እንደሚችሉ ተገልፆአል በሌላ በኩል ደግሞ የታመኑ ፍሬ ነገሮች ላይ ማስረጃ ማቅረብ አያስፈልግም ቢባልም አንዲህ ዓይነት መደምደሚያ ላይ ለመድረስ ፍሬ ነገሮቹ በርግጥ ታምነዋል ወይ። በሚል መጠየቅና መመዘን ተገቢ ነው ከዚህ አንፃር በተከሳሽ የተሰጡ ቃሎች ላይ ላዩን ሲታዩ የታመኑ ፍሬ ነገሮችን የሚመለከቱ ቢመስሉም ነገር ግን ከተፈላጊው ጭብጥ ወይም ፍሬ ነገር አንፃር ሲገናዛዘቡ ታምኗል የማያስብሉ ይሆናሉ ተከሳሹ ሾፌር ሆኖ ሳለ ከሙያው አንፃር ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ሲገባው በቸልተኛነት ሰው ገጭቶ ገድሏል በሚል ለቀረበበት ክስ በሰጠው ቃል መስመሬን ጠብቄ እየነዳሁ አያለ ሟች መኪና ተከልሎ በድንገት ገብቶብኝ ሊገጭ ችሏል ቢል ይህ በግርድፉ ሲታይ የአመነ ቢመስልም ነገር ግን ጠበቅ ተብሎ ሲመረመር ድርጊቱ የተፈፀመው በቸልተኛነት ይሁን በአጋጣሚ ለመለየት አያስችልም ስለዚህም ይህንን ቃል በእምነት ቃልነት ከመውሰድ ይልቅ ድርጊቱ ስለተፈፀመበት አካባቢያዊ ሁኔታ ማለትም የተከሳሹን ፍጥነት መጠንና የተፈቀደውን የፍጥነት መጠን ሟች ተከልሎበታል የተባለው መኪና አይታን የሚከላከል መሆን አለመሆኑ ሟች ወደ መኪና መንገድ የገባበት ሁኔታ በማስረጃ ሊረጋገጥ ይገባዋል የዚህ ምዕራፍ ትኩረትም የተቀባይነትን መመዘኛ የአሟላ የፅምነት ቃል ነው የተባለ ቃል በርግጥም የዕምነት ቃል መሆኑ ወይም አለመሆኑን የሚመዘንበትን መሠረታዊ ነጥቦች መግለፅ ነው በመጨረሻም ወደ ዝርዝር ነጥቦች ከመግባት አስቀድሞ የታመነ ፍሬ ነገር ነው የተባለ ቃል አመዛዘን ከወንጀልና ከፍትሐብሔር ጉዳዮች አንፃር ያለው ልዩነት ሊታወቅ ይገባል በምዕራፍ ስር እንደተጠቀሰው አንድ ፍሬ ነገር ታምኗል የሚባልበት መመዘኛና የሚያስከትለውም ውጤት እንደጉዳዩ ፍትሐብሔር ወይም ወንጀል መሆን የሚለያይ በመሆኑ በዚህ ምፅራፍ ስለታመኑ ፍሬ ነገሮች አስረጅነት የሚገለፀውም ይህንን መሠረት በአደረገ ሁኔታ ይሆናል ወደሳ ሦዳፀ ደታመት ፉሪ ጋሮቻ ሰዕሬድታ ምሃና በወንጀል ጉዳይ የታመኑ ፍሬ ነገሮች ብለን የምንመድባቸው በወመህሥሥቁ አና ወይም በቁጥር መሠረት ለመርማሪ ፖሊስ ወይም በምርመራ ጊዜ ቃል ለተቀበለ ፍቤት የተሰጡ ቃሎች እና ከቁጥር ላይ በተደነገገው መሠረት ክስ ችሎት ቀርቦ ተነብቦ ተከሳሹ እምነት ክህደት ሲጠየቅ የሰጠው ቃል ናቸው የመጀመሪያው በቁጥር እና ወይም መሠረት የተሰጠው ቃል የዕምነት ቃል ነው በሚል ከመደምደምና ክሱን አስረድቷል ከማለት በፊት ወንጀሉን የሚያቋቁሙትን ፍሬ ነገሮች ድርጊቱና የሀሳብ ክፍሉን እንዲሁም አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ድርጊቱን ለመፈፀም ያነሳሳ ምክንያት እርከከህ ተሟልቶ የታመነ መሆኑን ው ተፈላጊው የምክንያትና ውጤት ግንኙነት የተሟላ መሆኑን የተሰጠው ቃል የመከላከያ ጭብጥ የሌለበት መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል በተጨማሪም በተሞክሮ እንደሚታየው ሰዎች ወንጀል መፈፀማቸውን አምነው ቃላቸውን እንዲሰጡም ባልተገደዱበት ሁኔታ በተለያዩ ምክንያቶች ለምሳሌ የምርመራውን ትክክለኛ አቅጣጫ ለማሳትና ሌሎች ሰዎችን በወንጀል ከመጠየቅ ለማዳን ወይም የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት ማህበራዊ ተቀባይነትን ለማግኘት ወይም ከማይፈልጉት ግዴታ ለመዳን ያልፈፀሙትን ወንጀል ፈፅመናል በማለት ቃላቸውን ሊሰጡ ይችላሉ መዝገቡ ምትኬ ገፅ በዚህም መሠረት ምንም እንኳን የሰጡት ቃል የዕምነት ቃል የሚያስብል ቢሆንም ቃል ለመስጠት የተገደዱ ባይሆኑ አንኳን የሰጡትን ቃል ከሌሎች ደጋፊ ማስረጃዎች ጋር በማገናዘብ የተሰጠው ቃል በትክክልም የዕምነት ቃል መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው እንዲሁም ተከሳሹ የመከላከያ ማስረጃ የአቀረበ ከሆነ የዕምነት ቃሉ እና የመከላከያ ማስረጃዎቹ የገለፁዋቸው ፍሬ ነገሮች ተገናዝበው ሊመረመሩ ይገባል የፅምነት ቃሉ የተሰጠው በፍቤት ክሱ ተነብቦ ካበቃና ተከሳሹ እንዲረዳው ከተደረገ በኋላ ለተጠየቀው የፅምነት ክህደት በመልስነት ተከሳሹ ያስመዘገበው ከሆነም ከላይ በመግቢያዉ የተጠቀሱት የመመዘኛ ነጥቦች ተፈፃሚነት አላቸው የወመህሥሥቁ ላይ እንደተገለፀው ተከሳሹ አመነ ለመባል በክሱ ማመልከቻው ላይ የተዘረዘረውን ወንጀል ለመስራቱ በሙሉ ያመነ መሆኑ መረጋገጥ አለበት ስለዚህ በከፊል የሚሰጥ የዕምነት ቃል የሚባል ነገር የለም በክሱ ማመልከቻው ላይ የተገለፀውን በሙሉ ሊያምን ይገባልና ው ተሰጠ በተባለው የዕምነት ቃል ውስጥ ከፊሉን ማለትም ተከሳሹን የሚያስጠይቀውን ብቻ ነጥሎ ወስዶ ጥፋተኛ ነህ ማለት አይገባም የሚሦጐዳውም የሚጠቅመውም ቃል አንድ ላይ ተወስዶ ከቀረበው ክስ አንፃር የዕምነት ቃል ነው ለማለት ያስችላል።