Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ለሚለው ጥያቄ ሁላችንም ምላሹን ማወቅ ይኖርብናል በመሠረቱ ከጥንት ጀምሮ ሳያቋርጥ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የቤተ ክርስቲያን ሀብት ነው ስለዚህ ዛሬ ሐዋርያዊ መንበር ባላቸው በጥንት አብ ያተ ክርስቲያናት ይህ የተቀደሰው ትውፊት እየተሠራበት ይገኛል መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ።
መግቢያ ጸሎተ ሃይማኖትና አምስቱ አዕማደ ምሥጢር በክፍል አንድ የምንማረው የሃይማኖት ትምህርት በጸሎተ ሃይማኖት ላይ የተመሠረተ ነው ጸሎተ ሃይማኖት ታሪካዊ አነሣሙ ምንም እንኳ መናፍቃንን ለመለየትና ምእመናንም በትክክለኛው ሃይማኖት እንዳጸኑ ለማድረግ ታስቦ በጉባኤ ኒቂያ ዓም እና በጉባኤ ቁስጥንጥንያ ዓ ም የተወሰነ ቀኖና ሕገ ሃይማኖት ቢሆንም የትምህርቱ ይዘት ግን ከጥንት ጀምሮ በጌታና በሐዋርያት ትምህርት ውሰጥ የነበረ ነው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንደ ዛሬው ሳይከፋፈሉና ሳይወጋገዙ በኅብረትና በአንድነት በሚሠሩበት ጊዜ የነበሩ መንፈሳውያን የሃይማኖት መሪዎችና ሊቃውንት አኣባ ቶች ይህን ጸሎተ ሃይማኖት ከቅዱሳት መጻሕፍት አውጣጥተው በ አንቀጸች ከፍለው በማዘጋጀት የክርስትና መሠረተ እምነት ሆኖ እንዲሠራበት በውሳኔአ ቸው ለአብያተ ክርስቲያናትና ለምእመናን ሁሉ አስታውቀዋል አውጀዋል ጸሎተ ሃይማናኖት ልዩ ልዩ አንቀጸ ሃይማኖትን ዶግማን ማለት ምሥጢረ ሥላሴን የወልድ አምላክነትን የመንፈስ ቅዱስ አምላክነትን ምሥጢረ ሥጋዌንና የማዳን ሥራን» ጥምቀትን ትንሣኤ ሙታንን የሚመጣውንም ሕይወትና የመሳሰሉትን ያካትታል ፒከ ፎ ዐበበ ሃ ደከ ህርከ ቪኪኪ ከፎ ርከር ሂከዕ ዐኪ ከ ርከር ዐ ከፍ ኩ ቪ ከፎ በርየበከክ ፎበኪ ቢ ክፎ ጀፎኗየፎርኪ ከ ፍ ዕጠ ዐኮ ከፍህ ከፎ ርሂዩርበ ፎከ ዴጽክበ ሟ አከ ሀ እነዚህን እውነተኛ ዓለም ኣቀፍ የኣብያተ ክርስቲያናት ጉባኤያትንና የተቀደሰውን የሃይማኖት ውሳ ፄሄያቸውን ታላቅነት በማሰብ ጉባኤ ኒቲቂያ መስከረም ቀን ጉባኤ ቁሰጥንጥንያ የካቲት ቀን በቤተ ክርስቲያናችን ተከብሮ ይውላል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲፀናዊ ሕጾዉት ጸሎተ ሃይማኖትን መሠረት በማድረግ የሀገራችን ሊቃውንት ከብሉያትና ከሐዲሳት እንዲሁም ከሊቃውንት መጻሕፍት በማውጣጣት አምስቱ ኣዕማደ ምሥጢርን አዘጋጅተውልናል እነርሱም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን መሠረት ስለሆኑ ለጸሎተ ሃይማኖትና ለምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ትምህርታችን አዕማድ ምሰሶዎሺፒሚ ናቸው ስለዚህ አሥራ ሁለቱን የጸሎተ ሃይማኖት አንቀጸች በኣራት ምዕራፎች መድበን በአጭር በአጭሩ እናጠናቸዋለን መጀመሪያ የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት እንዲሁም ፈጣሪነቱን የምንማርበትን ምሥጢረ ሥላሴንና ሥነ ፍጥረትን እናስሰቀድማለን ሁለተኛው የእግዚአብሔር ፍቅርና የማዳን ሥራው የተገለጠበትን የምሥጢረ ሥጋዌና የነገረ መሰቀልን ትምህርት እንቀጥላለን ሦስተኛው ሰለ መንፈስ ቅዱስና ቤተ ክርስቲያን ሲሆን በዚህ ምዕራፍ የመዳናችንና የመቀደሳችን ምሥጢር እንዴት እንደሆነ ይገለጻል አራተኛው የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል በማሰመልከት ስለ ምሥጢረ ትንሣኤና ስለ ዘላለም ሕይወት ስለ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት ይሆናልፈ ምሥጢረ ጥምቀትና ምሥጢረ ቁርባን በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክፍል ሁለት ተገልጠዋል በዚህ አንቀጸ ሃይማኖት ሥር የሚገኙትን አርእስተ ትምህርት እርስ በርሳቸው ውስጥ ውስጡን በማገናኘት እንደ ሠንሠለት የሚያያይዝልን ለትም ህርተ ሃይማኖታችን በአጠቃላይ ለክርሰትና እምነታችን ተሰፋችንና ፍቅራችን ለክርስቲያናዊ ሕይወታችንና ምግባራችን ሁሉ ማዕከልና መሠረት የሆነን ርእሰ ትምህርት የእግዚአብሔር ፍቅርና የማዳን ሥራው ነው ይህም አዲስ ትምህርት ሳይሆን በቅዱሳን ሐዋርያት በተለይም በሐዋርያውና በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ አድኅኖና ሕገ ተፋቅሮ ላይ የተመሠረተ ነው ዮሐ ዮሐ ቆሮ በመሆኑም ይህን ርእሰ ትምህርት በትክክል ማወቅና ማመን ለሁላችንም አሰፈላጊና ግዴታም ነው ስለዚህ እግዚአብሔር ሰውን በመውደዱ ሰውን ለማዳን የፈጸመው ታሪክ ከምዕራፍ አንድ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ድረስ በልዩ ልዩ መንገድ እንደ አን ቀጽ ሁኔታ አርእስተ ትምህርቱ በሚፈቅደው መሠረት በመጠን በመጠኑ ለመግለጽ ተሞክሯል በሥነ ፍጥረት ታሪክ መጨረሻ በክብር የተፈጠረው ሰው የፈጣሪውን ትእዛዝ በማፍረስ እርሱ ራሱ ወዶ ፈቅዶ በፈጸመው በደል ምክንያት በሥጋውም በነፍሱም በመከራና በችግር ውስጥ በወደቀ ጊዜ እግዚአብሔር ከታላቅ ፍቅሩና ቸርነቱ የተነሣ የመዳንን ተሰፋ ሰጠው ዘፍ እና ራእይ የአዳምም ተስፋ በምሥጢረ ሥጋዌ በክርስቶስ የማዳን ሥራ ማለት በሕማሙና በሞቱ በትንሣኤውና በዕርገቱ ተፈጽሟል ይህም በመስቀል ላይ በዕለተ ዓርብ አንድ ጊዜ የተፈጸመው የማዳን ሥራውና ጸጋው ለፍጥረት ሁሉ እንዲዳረስ ለማድረግ እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያኑን አዘጋጅቷል ስለዚህ በክርስቶስ በማጩን ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኘው የመዳንና የመቀደስ ጸጋ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በየጊዜው ለሚ ነሙት አማኞች ሁሉ በቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናት በሚፈጸመው የጸሎትና የቃሉ አገልግሎት በተለይም ፀምመሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አማካኝ ነት ይሰጣቸዋል በክርስቶስ ድኅነተ ጸጋ ያገኙትና በበጐ ሥራ እስከ መጨረሻው የጸኑት ሁሉ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ በአፀደ ነፍስ ለጊዜው በሀገረ ሕይወት በገነት ይኖራሉ ከዚያም በኋላ በዓለም ፍጻሜ የዘላለም ሕይወትና የክብር ትንሣኤን በመቀዳጀት በመንግሥተ ሰማያት የመዳናቸው ተስፋ ምሥጪር ሙሉ በሙሉ ይገለጣል ይፈጸማል እንግዲህ ከላይ የተጠቀሱትን ሁሉ በትክክል ለማስረዳት አቅማችንም ሆነ ሁኔታችን ባይፈቅድልንም ኣሥራ ሁለቱን የጸሎተ ሃይማኖት አንቀጸች ኃይለ ቃል በመከተል የተወሰኑትን አርእስተ ትምህርት ብቻ በመምረጥ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛዩመኖትና ክርስቲያናዊ ሕዷዌዉት ከብዙው በጥቂቱ ከረጂሙ ባጭሩ እግዚአብሔር በቸርነቱ በለገሠን ጊዜና ባደረገልን ርዳታ ተደግፈን በአፍ በመጣፍ የተማርነውን በክርስቲያናዊ ሕይወታችን በተመክሮ ያገኘነውን በቅዱስ መጽሐፍ መሠረትነት በሐዋርያዊ ትውፊት መሪነት በጽሑፍ ለመግለጽ ሞክረናል በዚህ ላይ ልናክለው የሚያስፈልግ ትምህርት ቢኖር ለእግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብን መማር ነው የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ ከማስተዋል ጋር ስለ ሁሉም ለሁሉም ነገር በክርስቶስ ሰም እግዚአብሔር አምላካችንና አባታችንን ሁልጊዜ ማመስገን ይገባናል ኤፌ ከዚህ ቀጥሎ ወደ ትምህርቱ ከመግባታችን በፊት ትምህርቱን ለመከታተል እንድንችል በቅድሚያ ጸሎተ ሃይማኖትን አንቀጽ በአንቀጽ ማወቅ ትምህርታዊ ግዴታችን ነው ስለዚህ ጸሎተ ሃይማኖትን ምእመናን ሁሉ በቃል አጥንተው በግል ጸሎት እንዲደግሙት ያስፈልጋል ይልቁንም በቤት ክርስቲያን ውስጥ በጊዜ ቅዳሴ ዲያቆኑ ንበል ኩልነ በጥበበ እግዚአብሔር ጸሎተ ሃይማኖት በእግዚአ ብሔር ጥበብ ሁነን ሁላችን የሃይማኖትን ጸሎት እንበል በሚልበት ጊዜ ቀዳሾችም አስቀዳሾችም ሁሉ ድምፃቸውን አሰምተው እንደ አቡነ ዘበሰማያት ጸሎት በአንድነት ሆነው ሊጸልዩት ይገባል ሥርዓተ ቅዳሴ የአማኞች ጸሎተ ቅዳሴ ፍሬ ቅዳሴ የሚጀመረው በመላ በቤተ ክርስቲያን ያሉት ሁሉ የኦርቶዶክስ ጸሎት ሃይማኖትን በኃይልና ከልብ በሆነ አኳኋን ድምፃቸውን አሰምተው በአንድነት በማለት በመድገም ነው በፍሬ ቅዳሴ መጀመሪያ ላይ የኦርቶዶክስ ጸሎተ ሃይማኖትን መድገም እኛ እግዚአብሔርን ለማስደሰታችን የሚያረጋግጥ እጅግ ትልቅ ቁም ነገር ነው ያለ እምነት እርሱን ለማስደሰት አይቻልምና ዕብ የኦርቶዶክስ ጸሎተ ሃይማኖትን በመድገም የአንድ አምላክ የቅድስት ሥላሴን በአንድ የእግዚአብሔር ልጁ የተፈጸመውን የማዳን ሥራውን እና በመንፈስ ቅዱስ የተሠራውን የመቀደሳችንና የመንጻታችንን ነገር በመግለጽ እም ነታችንን እናስታውቃለን ወዳጆቼ ሆይ የኦርቶዶክስ ጸሎተ ሃይማኖትን ከመላው ቤተ ክርስቲያን ማለት ከጉባኤው ጋር ሆናችሁ በጥንቃቄ በሉት ድገሙት በመንፈስ ቅዱስ በተመሩ በታላላቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶች የተመሠረቱት የታላላቆቹ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤዎች የሥራ ፍሬ እንደ መሆኑ መጠን እያንዳንዱን ቃል እመኑ ከዚህ በታች ለጥናት እንዲያመች ታስቦ ጸሎሉተ ሃይማኖት ኣንቀጽ በአንቀጽ ተዘርዝሮ በግዕዝና በአማርኛ እንደሚከተለው ቀርቧል ፕከ ህፎሃ የ ከፎ ቨርሃፎ ክፎፎነበ ዛክ ከፍ ዚ ክጄ ፍርቨፎ ከሃ ዚክር ህህከር ርከህየርከ ጸህከሃ በ ከ ክ ሃፎ በ ዩርኣሃርቪህ ከብ ወቨርር። ተያዢ እንዲሆን ጥፋተኛ ያልሆነ ጻድቅ ሰው ይፈለግ እንዳይባል ሁሉም በደለኛ ሆኗል ከዓለመ መላእክትም ማለት ንጹሕ ፍጥረት ከሚባሉትም ውስጥ እንዳይፈለግ ጥፋቱ የተፈጸመበት ቦታ ከዚህ ዓለም ሰለሆነ ጥፋተኛውም ሰው በመሆኑ የሌላ ፍጥረት አዳኝነትን ማሰብ የማይሆን ነገር ነው ለዚህ አዳጋች ነገር መልስ ሊገኝ የሚችለው ከራሱ ከእግዚአብሔር ብቻ ነው እርሱም የመረጠው ትክክለኛ መንገድ ኃጢአት የሌለበት ንጹሕ ሥጋና ነፍስን በመዋሐድና ሰው በመሆን በበደላቸው ለተከሰሱትና ለተፈረደባቸው ሁሉ ተያዥ ብቻ ሳይሆን በእነርሱ እግር ተተክቶ በእነርሱ ወን ጀልና ኃጢአት ተከሥሶ የሞትን ፍርድ በመቀበል ማዳን ነበር ስለዚህ ነው ቅዱስ አቡሊዲስ ዘሮም መልአክን ወይም ነቢይን በመላክ ሳይሆን እርሱ ራሱ እግዚአብሔር ቃል ወደ እኛ መጥቶ ሰው ሆኖ እንዳዳነን በኛ ድርሳኑ የጓፈው እንግዲህ የዚህን መለኮታዊ አሠራር በጽሞና እናስተውል ሞትን ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማኖትና ክርስቲፀናዊ ሕደወት ትሞታለህ በማለት የተወሰነው መለኮታዊ ቃል ሳይሻር ወልደ አግዚአብሔር ቃል በሥጋው በመሞቱ የእግዚአብሔርን ትክክለኛ ፍርድ በአዳም ተገብቶ ፈጽሞታል በዚሁም ሰውን ከሞት አድኖ አዲስ ፍጥረት አድርጉታል የዘላለም ሕይወትን ሰጥቶታል አሁንም ልብ እናኖናድርግ የእግዚአብሔር ትክክለኛና እውነተኛ ፍርድ ተፈዳሜነት እንዲኖረውና እንደዚሁም እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለው ፍቅር እንዲገለጽ ለማድረግ በመስቀል ላይ ሁለቱም ማለት ፍርዱና ፍቅሩ ምሕረቱ በክርስቶስ ሞት ተፈጽመዋል ፍርድ ሰንል በኃጢአት ላይ የተወሰደውን አርምጃ ማለት በበደል ላይ የተወሰነውን የሞት ቅጣት የሚያመለክተን ነው ይህም የእግዚአብሔር የባሕር ዩ የሆነውን ትክክለኛ ዳኝነቱን ይገልጽልናል በሌሳ በኩል ደግሞ ኃጢአት የሌለበት ክርስቶስ ኃጢአተኛውን ከዘላለም የሞት ፍርድ ለማዳን በኃጢአተኛው ምትክ ሞትን በፈቃዱ በመቀበሉ የእግዚአብሔርን የፍቅሩንና የምሕረቱን ታላቅ ነት ያሰረዳናል እንግዲህ ሰለዚህ ነው የእግዚአብሔር ፍርዱና ፍቅሩ በአንድ ነት በክርሰቶስ መሥዋዕትነት በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ ተፈጸሙ የምን ሰው አዳም መለኮታዊ ሕግን በመተላለፉ በደል በመፈጸጩ የሞት ቅጣት ተፈርዶበታል አዳም ከዚህ ዘላለማዊ ቅጣት ለመዳን የሚችለው በፍርድ መን ገድ እንጂ በሌላ ሁኔታ መዳን አይቻልም ቅጣቱ በፍርድ እንደ ሆነ መዳኑም በፍርድ ይፈጸማል ስለዚህ ነው ጌታ ሥጋ ለብሶ ማለት ሰው ሆኖ የኣዳምን የሞት ፍርድ በራሱ ሰውነት ተቀብሎ ያዳነው ወአድኃነነ በፍትሕ ጽድቅ ወርትዕ ተብሎ እንደ ተጓፈው መዳናችን በፍርድ እንደሆነ እናሰተውል መቅድመ ወንጌል ፍርድም የተፈጸመው በመሰቀል ላይ ነው እንግዲህ በመስቀል የመዳናችን ነገር አማራጭ የሌለው በእግዚአብሔር የተመረጠ ብቸኛ የጽድቅና የፍትሕ የርትዕ መንገድ እንደሆነ እናምናለን ከመሰቀል ሌላ የመዳን አማራጭ ኣለ ብሎ ማሰብ ከእውነትና ከእግዚአ ብሔር ፈቃድ ውጭ መሆንን ያመለክታል መስቀል ኣያስፈልገንም ክነ ኃጢአ ታችን ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ እንችላለን ማለት ዘበት ነው ሐሰት ነው ከእግዚአብሔር ተለይቶ መቅረት ካልሆነ በስተቀር የእግዚአብሔር የቅድስና መለኮታዊ ባሕርዩ የሚያቃጥል እሳት ሰለሆነ በክርስቶስ መስቀል በኩል ካልሆ ነ ማንም ሊድንና ወደ እግዚአብሔር ሊቀርብ አይችልም ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው እግዚአብሔር አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና ዕብ ፊ ደም ካልፈሰሰ የኃጢአት ሥርየት የለም ፅብ። እንዲሞት ከተፈረደበት ከሰው ዘር እንደሆነ በእርግጥ ሰዎች ያውቁ ነበር እርሱም የሰው ልጅ ወልደ እጓለ እመሕያው ነው እርሱም ከቅድስት ድንግል የሚወለደው መድኃኒታችን እንደሆነ ታወቀ እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙን አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ኢሳ እነዚህና ሌሎችም የትንቢት ቃል እውነተኛውና ንጽሕ አማናዊው መሥዋዕት ክርስቶስ እንደሆነ ይመሰክራሉ እንግዲህ እስካሁን ከተቁ የተመለከትነው ከጥንት ጆምሮ ሰዎች በፈጸሙት በደል ምክንያት ከእግዚአብሔር ስለተለዩ ለኃጢአታቸው ሥርየት ለበደላቸው ምሕረት የሚያገኙበትን መንገድ ሰውን ወዳጅ እግዚአብሔር በታሪክና በምሳሌ አስተምሯቸዋል በነቢያቱም አስረድቷቸዋል ይህም መን ገድ የመዳናቸውን ምሥጢር በእንስሳት መሥዋዕት በምሳሌ ሲሠራበት ኖሮ ኖ ሮ በዘመኑ ፍጻሜ በአማናዊው መሥዋዕት በክርስቶስ መስቀል ተደምድሟል መሥዋዕት አያስፈልግም ለሚሉት የሃይማኖት ወገኖች ከዚህ በላይ የተመለከት ነው የእግዚአብሔር ቃል ይመሰክርባቸዋል እኛስ የእግዚአብሔርን ቃል ምስክርነት እንቀበላለን እንደ ትንቢቱም ቃል ክርስቶስ ለኃጢአታችን ቤዛ ሆኖ አድኖናል ሉቱ ስብሐት እንግዲህ ሁሉም ሰው በራሱ ወንጀል እጅ ከፍንጅ በመያዙ ሁሉም በእግዚአብሔር ሕግና ፍርድ ሥር ስለነበር ክርስቶስ እኛ በበደልን እርሱ ክሦ የኃጢአታችንን ዋጋ ሞታችንን በሞቱ ሽሮ እዳችንን በወርቀ ደሙ ከፍሎ አ ድኖናል ይህንንም ለማድረግ በመጀመሪያ ሰው ሆነ ከሰውም ጋር ተዛመደ የሥጋንና የነፍስን ባሕርይ ገንዘብ አደረገ ቃል ሥጋ ሆነ ዮሐ ከኃጢአት በስተቀር ከእኛም እንደ አንዱ ሆነ የመለኮቱ ባሕርይ ሳይለወጥ ሳ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛዘይመኖትና ክርሰቲያናዌቹ ሕፀጠት ይቀላቀል ሳይለያይና ሳይከፋፈል ከሥጋ ጋር ተዋሐደ ሥግው ቃል ማለት ሰው የሆነ ቃል መለኮትና ትሰብእት ተዋሕደው ኣንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆኑ ማለት ነው በዚህም አባባል ክርሰቶስ ማለት ፈጣሪና ፍጡር አን ድ አካል አንድ ባሕርይ ፀመሆን አንድ ሆነ ማለት ነው ሲል የኑሲሰ ኤሏስ ቆጸጳሰ ቅዱስ ንጎርጎርዮስፅ ጽፏል ገለዳውንም በመቀጠል እንዲህ ብሷል ዓ ለም ሳይፈጠር የነበረ ለዘላለሙ የሚሜኖር ለውን ሁሉ የፈጠረ እርሱ ነውና ሰለእሱ ስንናገር ያልተፈጠረ ነው እንላለን መዝ ዕፅ ሰው ነው ያልነውም ሰለ እኛ ባደረገው ተዋሕዶ ደካማ ባሕርያችንን ስለ ተዋሐደ ነው ሃይማኖተ ኣበው ገጽ እንግዲህ ክርሰቶስ በቃልነቱ በመለኮቱ ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ከእግዚአብሔርም የተገኘ አምላክ ወልደ አምሳክ እንደሆነ ባለፉት ኣንቀጸች ተመልክተናል በሥጋው ደግሞ ከአዳም ተገኝቷል እኛን ሰዎችን ለማዳን ከእኛ ጋር ዝምድናን መሥርቷል ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ዐመንፈሰ ቅዱስ ግብር ሰው በመሆኑና በመወለዱ ከኣዳም ልጆች ጋር ያለውን ዝምድና በተዋሐደው ሥጋ ልጽንቶታል ከቅድስት ድን ግል ማርያም በመወለዱ የእግዚኣብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆሩናል እርሷም የእግዚኣብሔርን ልጅ አክርሰቶሰን በመውለጳ የአምላክ አናት ሆናለች ለለዚህ ክርሰቶስ ሁለት ልደት እንዳለው እናምናለን ቅድጩ ዓለም ከኣብ ያለ እናት መወለዱ አንድ ልደት ድኅረ ዓለም ከእመቤታችን ያለ አባት መወለዱ ሁለት ልደት ወልደ ኣብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ ከበረ በማለት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን እንገልዳለን ከዚህ ቀጥሎ ሰለ ጌታችን ሁለተኛ ልደት ከመግለዳጻችን በፊት መጀመሪያ በሥጋ ስላሰገኘችው ስለ ወላጅ እናቱ በጥቂቱም ቢሆን ማወቅ ይገባናል ምክንያቱም የሥጋዌ ምሥጢር በድንግል እናቱ አማካይነት የተጀመረ ስለሆነ ነው ቃል ሥጋ የሆነው ከእርሷ ነውና ሐ ሰለ ቅድስት ድንግል ሃርያም ወላዲተ አምላክ ሠጋን ኣዘጋጀህልኝ ዕብ ከላይ እንደ ተመለከትነው እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን ሰው ለመሆን ስላሰበ በሥጋም በነፍሰም ኃጢኣት የሌለበትን ንጹሕ ሰውነት ይፈልጋል ኃጢኣተኛ ሰው ለኃጢአተኞች መድኅን ሊሆን አይችልም በራሱ ኃጢኣት ዶሞታል እንጂ ለኃጢአተኞች ተላልፎ ሊሰጥ የሚችል በእግዚኣብሔር ዘንድ ተቀባይነት ያለው መሥዋዕት ንጽሕ ቅዱስ መሆን አለበት የኦሪት መሥዋዕ ትም የእንሰሳት መሥዋዕት ሰለሆነ የሰውን ልጅ ከኃጢአትና ከሞት ሊያድ ማመም አፍ ሰለ ክርሰቶስ ባሕርይ የሚከተለው የስምምነት ታል ተዘጋጅቷል ጌታችን አምሳካችን ጩድኃ ኒታችን ኢየሱሰ ክርስቶሰ ሥግው ቃል በአምላክነቱ ፍጹም በሰውነቱም ፍጹም መሆኑን ኣናምናለን ያለ መቀሳቀል ያለ መዳበል ያለ መደባለቅ ሰውነቱን ከመለኮቱ ጋር አንድ ኣደረዝገ መለኮቱ ከሰውነቱ ለአንድ አፍታ ወይም የዓይን ጥቅሻ ያህል እንኳ ኣልተለየም የሁለቱን የንሰጥሮሰንና የአውጣኪን ትምህርቶች ኣናወግዛለን ልጄርርርበ ሁጠርበ ክ ከ ህፍ ከፎቨይሃዩ ሀከጭ ዐዚዣ የሷ ር ሺ ሀ ከቨሺ ከፍ ከየከ ሀዩር በ ከበዚሃ ዞፍ ዌክ ህጠመክዜዜ ሸ ቭሀበቪ በዩ ኣቭከ ዛ ኬክዚቨሃ ክዘክሄ ኢእብጻ ከዘፍ ክር አብክበዷ ክር ዐክኪ ኪ ከብክቨ በር በ ተህበክቪሃ ዩነርክ የ ክባክገፎበ ዐዘ አባክኤቨከደ ክ ላበ የክር ገር በፎ ህፎ ጸክከወበከሯፎ ሀካሬ ርዘር ዐየኮ እሀ ዘ ህከርከፎ ኮሀ ከርበህ ከር ካጸከዙር ዐያ ከ ፐኮ ኢክጻከቧ ይዞባበሂኒ እየሸርከ ሀ ጠር ዮር ርያ ርከ ዝነገነገርህኽ ትምህርተ ዛይመሻትና ክርስቲያናዊ ሕፎዩዉት ነው አልቻለም ስለዚህም የኦሪትን መሥዋዕትንና መብዐን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ ተብሎ እንደ ተጓፈው ኣካላዊ ቃል ወልድ የሚዋሐደውን ንጹሕ ሥጋ ከየትና እንዴት እንደሚያገኝ እርሱ ባወቀ ሥጋን አዘጋጅቷል ዕብ ይችውም ከጥንት ጆምሮ በልበ አምላክ የታሰበች አዲስቱ ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያም ነበረች የመጀመሪያይቱ ሔዋን በኃጢአቷ ወድቃ ተረግማ እንዳትቀር ያሳታትን ጠላቷን የሰይጣንን ራስ የሚቀጠቅጥላት እርሷንም የሚያድናት ከዘርዋ እንደሚመጣ እግዚአብሔር ተስፋ ሰጥቷት ነበር ዘፍ። ቅድስት ኤልሳቤጥ ስለ እመቤታችን ከተናገረችው አንዱ ይህ ነበር በኤልሳቤጥም መንፈሰ ቅዱሰ ሞላባት በታላቅ ድምጽም ጮኻ እንዲህ አለች » ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት ሉቃ እንግዲህ እንድታምነው ከጌታ የተነገረላት ቃል ምንድነው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በድንግልና ወንድ ልጅ እንደ ምትወልድ እርሱም የልዑል ልጅ እንደ ሚባል በሰማች ጊዜ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር እንደሌለ አምና መቀበሏን የሚያመለክት ቃል ነው እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ በማለቷ እመቤታችን በታላቅ ሃይማኖትዋና ትሕትናዋ ለክርስቲያኖች ሁሉ አርአያ ሆኖለች ሉቃ ስለዚህ እመቤታችን በእናትነትዋ ብቻ ሳይሆን በታላቅ እምነቷና ፍቅሯ ትሕትናዋና በጎ ምግባሯ በሁሉ ዘንድ የተመሰገነች ብፅዕት ናት እንግዲህ የእመቤታችን ክብርና ምስጋና በመሳእክትና በቅዱሳን መካከል እጅግ ከፍ ያለ ነው ስለዚህም በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እንበላት ሉቃ እንደ ቅድሰት ኤልሣቤጥም የጌታዬ እናት እያልን እናክብራት እናመሰግናትም ሉቃ እግዚአብሔር ለእመቤታችን ታላቅ ሥራ አድርጎላታልና ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሏታል ሉቃ ላቲ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወለወልዳ አምልኮ ወስግደት በምድር ወበ ሰማያት በባሕር ወበቀላያት ለዓለመ ዓለም አሜን ለእርሷ ክብርና ምስጋና ለልጂም አምልኮና ስግደት ይገባል እንደ ተባለው ከልጂ ቀጥለን ለእርሷ ከፍተኛ ምስጋና እናቀርባለን የእርሷ ማዕረግ ከጌታችን በታች ከመላእክትና ከቅዱሳን ሁሉ በላይ ስለሆነ ለእርሷ የሚቀርበው ክብርና ምስጋና በዚሁ መጠን ከፍ ያለ ነው መ ጌታ ሰው ስለ መሆኑ የቅዱስ ገብርኤል ምሥራች በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፈጽሞ ሰው ሆነ በማለት ከላይ በአንቀጹ የተገለጸው የእግዚአብሔር ልጅ ያለ አዳም ኃጢአትና ያለ ዘርዐ ብአሲ ስለ እኛ ስለ መዳናችን ሲል እንደ እኛ ፈጽሞ ሰው መሆኑን የምንመሰክርበት የሃይማኖት ድንጋጌ ነው ከሁለት ነገሮች በስተቀር እንደ እኛ እንደ ሰው በመሆኑ ከሰውነት ባሕርይ የጐደለው ነገር የለም የመጀመሪያው ሰው ኣዳም ከሁለቱ በስተቀር ማለት ያለ ዘርዐ ብእሲና ያሊ ኃጢአት ተፈጥሯል ክርስቶስም ያለ ዘርዐ ብአእሲና ያለ ኃጢአት ከአመቤታችን ተወልጳል ሰለዚህም ክርስቶስ በሰውነቱ ዳግማዊ አዳም ይባላል በሥጋም በነፍስም ከበደል በፊት እንደ ነበረው እንደ መጀመሪያው ሰው ነው ከኃጢአት በስተቀር ፈጽሞ እንደ እኛ ሰው ሆነ ትእዛዙንና ቃል ኪዳኑን በማፍረሳችን የአግዚአብሔር ጠላቶች ሰንሆን እርሱ ግን እኛን ከመውደዱ የተነሣ ከእኛ ጋር ወዳጅነትን መሠረተ በሥጋም በነፍስም እንድን ዛመደው ፈቃዱ ሆነ ከገነት የተባረሩት አዳምና ሔዋን ልጆቻቸውም ወደ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛክይመሟናትና ክርስቲወናዊ ሕይጾወዉት ሚኖሩበት ዓለም ጌታ እንደ ሚመጣና የማዳኑንም የተስፋ ቃል እንደ ሚፈጽም ገና ከመጆመሪያው አስታውቋቸው ነበር በነቢያቱም አድሮ ከሴቲቱ ዘር የሚገኘው የእባብን ራስ የሚቀቃጠቅጠውና ሰውንም የሚያድነው ጌታ እርሱ ለመሆኑ እንድናውቀው ምልክትን አዘጋጅቷል ምልክቱም ከድንግል ያለ ዘርዐ ብእሲ መወለዱን ያሳያል ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል ተብሎ እንደ ተጓፈ ኣእነሆኛ ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልቿም ትወልዳለች ስሙን ም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች በማለት ጌታ ሰው የመሆኑን ነገር በዚህና በሌሎችም የትንቢት ቃል በማያሳስት ምልክት አረጋግጧል ኢሳ በተስፋም የተሰጠው የሴቲቱ ዘር ለአብርሃምና ለዘሩ በተነገረው ትን ቢት መሠረት ጊዜው ሲደርስ እኛን ለማዳን ወደዚህ ዓለም መጣ ገላ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም እንደ ጻፈው የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ሳላከ እን ደ ልጆች እንሆን ዘንድና ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ በማለት በመርገም ሥር ለሚገኘው ዓለም ቤዛ ለመሆን ጌታ ሰው መሆኑን ያስረዳናል ገላ ዔዱዔታም ወደዚህ ዓለም ከመምጣቱ አስቀድሞ መንገዱን የሚያዘጋጅለት ሰው መሆኑን የሚመሰክርለትና ከፊት ከፊቱ የሚሄድ የአዋጅ ነጋሪ ቃል ነቢየ ልዑል ዮሐንስ መጥምቅ እንደ ሚወለድ ምሥራቹን ለዘካርያስ እንዲነግር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተልኮ ነበር ይህም እንደ ተፈጸመ በስድስቴቱኛው ወር ይኸው መልአክ ስለጌታ ሰው መሆን እንዲያበሥራት ወደ አመቤታችን ተላከ እኛን ለማዳን ጌታ ሰው ለመሆኑ የተነገረው የቅዱስ ገብርኤል የምሥራች ቃል እንደ ሚከተለው ተጽፏል ይህ ቃል በቤተ ክርስቲያን ደንብ መሠረት የጸሎታችን አንዱ ክፍል ነው በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደ ምትባል ወደ ገሊላ ከተማ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ ደስ ይበልሽ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ጌታ ከአን ቺ ጋር ነው አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው። መልአኩም ቅዱስ ዮሴፍ ጠባቂዋ መሆኑን ስለ ሚያውቅ ይህንን ነገር አላነሣውም እርሷ ግን ለዘላለሙ ወንድ የማታውቅ የዘላለም ድንግል ናት ቅዱስ ዮሴፍም የእመቤታችን ንጽሕናና ድንግልና የተገለጠለትና በጌታ መልአክም ትእዛዝና መመሪያ መሠረት የሚኖርና የሚመራ ጻድቅ ሰው እንደ ነበረ ተጽፏል የትውፊቱን ሳንቆጥር በማቴዎስ ወንጌል ብቻ የጌታ መልአክ ለዮሴፍ አራት ጊዜ ተገልጦ ስለ ሜያደርገው ነገር ሁሉ መመሪያ እንደሰጠው እናነባለን ማቴ እና ከዚህ ቀጥሎ የምንመለከተው ሁለተኛው ነገር ድንግል ማርያም ያለ ዘር ዐ ብእሲ ጌታን መፅነሷን ነው የቅዱስ ገብርኤል የምሥራች ቃል ይህንኑ ያረጋግጥልናል በመንፈስ ቅዱስ ግብር እንደ ፀነሰች እናምናለን ወንጌላዊ ማቴዎስም እንደ ጻፈው እመቤታችን በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች በማለት ያእግዚአብሔርን ተአምራዊ ሥራ ይመሰክራል ማቴ መልአኩም መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ማለቱ እመቤታችን በድንግልና እንደ ፀነሰች ያስረዳናል ይጸልልሻል ማለትም እመቤታችን ከሴቶች ልማድና ግዳጅ በልዑል እግዚአብሔር ኃይል ነፃ መሆኗን ያመለክታል የጌታ ኃይል ይጸልልላታል ማለት ይከልልላታል ወይም ይጋርድላታል ማለት ነው ይኽውም በሔዋን ላይ የነበረው መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ በእመቤታችን ላይ አለመኖሩን ያረጋግጥልናል በእርሷም ምክን ያት በሰዎች ልጆች ላይ የነበረች የመጀመሪያዋ መርገም ተሽራለች ምክን ያቱም ጌታ ከእርሷ በነሣው ማለት በወሰደው ሥጋ ሞትንና እርግማንን አ ጥፍቶልናልና ሔዋን በሕማምና በችግር በልቡናም ኀዘን ትወልድ ነበር እመቤታችን ግን የሔዋን ኃጢአትና መርገም ስለሌለባት በድንግልና ፀንሳ በድን ግልና ወለደች ይኸም የሆነው ከመፈጠሯ ጆምሮ የልዑል መድ ይጸልልላትና ይጠብቃት ስለነበር ነው ስለዚህም የደኅንነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችንም መሠረት ሆነች በመጨረሻ የምንመለከተው ሦስተኛው ትምህርት እመቤታችን በት ኅትናና በአዎንታ ለቅዱስ ገብርኤል ስለ ሰጠችው የመጨረሻ ቃል ነው መልአኩም ኤልሳቤጥ መኻን መሆኗን ብቻ ሳይሆን በእርጅናዋ ጊዜ የመፅነሷን ታሪክ አንሥቶ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር እንደሌለ ለእመቤታችን ከገለጸላት በኋላ ቃሉን ተቀበለች እንዲህም አለች እነሆኝ የጌታ ባሪያ እን ደቃልህ ይሁንልኝ አለች ወዲያውኑ ኣካላዊ ቃል በእርሷ አኣደረ ቃልም ሥጋ ሆነ ዮሐ አካላዊ ቃል ወልደ አምላክ ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን በመንሣት ማለት በመውሰድ መለኮትና ትስብእት በማኅፀኗ ተዋሐዱ አንድ አካልና አንድ ባሕርይ በመሆን ያለ መለወጥ ያለ መለያየትሸ ያለ መቀላቀል ያለ መከፋፈል ተዋሐዱ ሥግው ቃል ማለት ሰው የሆነ ቃል በድንግል ማኅፀን ተፀነሰ የዕለት ፅንስም ሆነ ይህም ዕለት እጅግ ታላቅ ስለሆነ በቤተ ክርስቲያናችን መጋቢት ቀን በየዓመቱ ይከበራል በዓሉም በዓለ ትስብእት ይባላል ትስብእት ማለትም ሰው መሆን ማለት ነው የትስብእት በዓልም በድንግል ማኅፀን አምላክ ፍጽም ሰው የሆ ነበትን የመጀመሪያውን ዕለት ያመለክታል ብሥራተ ገብርኤልም ታኅሣሥ ቀን በየዓመቱ ታስቦ ይከበራል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀይማናኖትና ክርስቲፀደናዊ ሕይዉት ትህርት ይ መ መ ጌታ በሥጋ ስለ መገለጡልደቱ ነበልባል በለምለሙ ቁጥቋጦ ውስጥ መጋቷየቱ በአንቀጸ ሃይማኖት ውስጥ ፈጽሞ ሰው ሆነ ሲባል በመጀመሪያ በፅን ሰቱ በኋላም በልደቱ አምላክ ወልደ አምላክ በሥጋ መገለጡን ያመለክታል በድንግል ማኅፀን ሳለ ጥቂት ቅዱሳን ብቻ ያውቁ ነበር ከልደቱ በኋላ ግን ለዓ ለም ሁሉ ተገለጠ ሕዝብ አሕዛብም የሚያዩት የሚዳስሱት ሰውነት ያለው ሆኖ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ እንደ ሰው ተገልጧል የአሁን አ መጣጡ በሥጋ በመገለጥ ነው የቀድሞው አመጣጡ ግን በመለኮታዊ እሳት አ ምሳል ስለነበር ማንም ሊቀርበው አይችልም ነበር ያን ጊዜ የእግዚአብሔር መገለጥ በሚታይ በነበልባል ውስጥ ነበር በእሾህ ቁጥቋጦ መካከል በሚነደው እሳት የተገለጠው ኣምላክ ለሙሴ ብቻ ነበር። ለወፎች ጐጆ ለቀበሮችም ጉድጓድ አላቸው ለ ሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት ስፍራ የለውም የተባለውን ያስታውሰናል ማቴ እርሱ የጌቶች ጌታ ሲሆን በዝቅተኛ ስፍራ በመገኘት የድሆች ድሀ በመሆን በአንድ ትንሽ ሕፃን መልክ በጨርቅ ተጠቅልሎ በበረት ተጥሎ የተገለጠበት ምክንያት ከቶ ምን ይሆን መልሱም እንደ ሚከተለው ነው የወደቀውንና የተዋረደውን የጠፋውን አዳምን በመፈለግ እርሱን መስሎ እር ሱን አኽሎ የፍጡርን ሥጋ ለብሶ ወደዚህ ዓለም የመጣው እርሱንና ልጆቹን ለማዳን ነው ከገነት በመውጣቱ በልቡ ያዘነውንና የተከዘውን አዳምን ወደ ቀደመው ክብሩ ጌታ ሊመልሰው ስለ ወደደ የእርሱንና የልጆቹን ውርደትና ኃጢአት ተሸክሞ ሊያድናቸው ከሰማየ ሰማያት ወረደ ከበረት ውስጥ ተወለደ የሰው ልጆችን ልቡና ለመንካት በእንዴት ያለ ትኅትና በዝቅተኛ ሁኔታ እንደ ተወለደ ተመልከቱ ይህንንም ያደረገበት ምክንያቱ የወደቀውን የሰው ልቡና ለማደስና ለማንሣት ነው አዲስ ልቡናን ሊፈጥርልን ትንሣኤ ልቡናን ሊሰጠን ፈልጐ በሥጋ ተገለጠ እኛ የእርሱን ቅዱስ መንፈስ ለመቀበል እን ድንችል እርሱ የእኛን ሥጋ ወሰደ የእርሱን ልዕልና እንድንወርስ ሕይወትም እንድናገኝ እርሱ የእኛን ውርደትና ሞት በሥጋው ተሸከመ እንደዚህም በማድረጉ ሁላችንንም አዲስ ፍጥረት አደረገን ስለዚህ ነው በማዳን ሥራው ሁላችንን እንደገና ሊፈጥረን አስቦ ጌታ ሥራውን ሁሉ ከመጀመሩ በፊት ጥበብን ፈጠረ ተብሎ በቅድሚያ በመጽሐፈ ምሳሌ የተነገረው ይህም ማለት በሥጋ መወለዱን ለማብሠር ነው ምሳ ግዕዙን ከነትርጓሜው ተመልከት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛክማናትና ክርስቲይናዌ ሕይወት ዖሄፖ ልጳድፖ ፅዳኋቋሪ ሪኃቋ መሃሰው ቀጥሎ የምንማረው ሁለተኛ ትምህርት ይህን የጌታ ልደት የሰው ልጆች በተአምራዊ ሁኔታ እንዲያውቁትና እንዲያምኑት መደረጉ ነው ፀጥ ባለው ሌሊት በሜዳ ላይ ለሚገኙ እረኞች ጨለማውን አርቆ ከሰማይ የወረደላቸው ብርሃን የጌታን ክብርና ልዕልና የሚያስረዳ ሲሆን የጌታ መልአ ክም ተገልጾ ነቢይና ሐዋርያ በመሆን ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆነውን ታላቅ ደስታ አ ብሥሯቸዋል ለእነርሱ መዳን ሲል የመጣውን ጌታ ክርስቶስ በዳዊት ከተማ መወለዱን ነገራቸው ሄደውም ለማየት እንዲችሉ ሕፃኑ በጨርቅ ተጠቅልሎ በግርግም ላይ ተኝቶ ታገኙታላችሁ በማለት ምልክቱን አስታወቃቸው የጌታን ልዕልናና ትኅትና በአንድ ጊዜ ለማየት የሚችሉ በድንገት ብዙ ሠራዊተ መላእክት ተገልጠው ጌታን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመንበሩ ላይ ሆኖ በሰማያት ስላዩት ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም በሰማያት ይሁን አሉ ደግሞም ከታች በትኅትና በምድር ላይ ሆኖ በግርግም ላይ ተኝቶ በማየታቸው ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ በማለት ለጌታ ልደት የሚገባ ምስጋናና መዝሙር አቅርበዋል ዛሬም በቤተ ክርስቲያናችን ይህ ምስጋና ዘወትር በቅዳ ሴ ሰዓት በዜማ ይባላል እረኞችም ይህንን ሁሉ ታላቅ ታምራት አይተውና ሰምተው ዝም አኣ ላሉም በተሰጣቸው ምልክት መሠረት ከቤተ ልሔም ፈጥነው በመሄድ እንደ ተጻፈው ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ እረኞችም እንደ ተባለላቸው ስለ ሰሙትና ሰላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ ተመለሱ ሉቃ እነርሱም በጌታ መልአክ የተሰበኩ የመጆመሪያው አማኞች ነበሩ ያዩትንና የሰሙትን ሁሉ ለሰዎች በመንገራቸው ለጌታ ልደት ምስክሮች ሆነዋል እኛም ለሰዎች መዳን ይህን ታላቅ ተአምር ያደረገውን በሥጋና በደም የተገለጠውን ጌታ ከቤተልሔም ማለት ከቤተ ክርስቲያን ሄደን እን ፈልገው ሥጋውንና ደሙን በመቀበል እንወቀው እንመነውም እናክብረውም ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ በማለት ሁል ጊዜ በጸሎተ ቅዳሴ እናመስግነው ታሪ ህልሷኋ ስለ ጌታ ልደት በማቴዎስ ወንጌል የተጻፈውን መሠረት በማድረግ ሦስተኛውን ትምህርት እንቀጥላለን ማቴኑፁ ጌታ በተወለደ ጊዜ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም ላይ አዲስ ተአምር ታየ ለዓለሙ ሁሉ የሚታይ አዲስ ኮከብ ተወለደ የጌታ መልአክ ለእረኞቹ ስለ ጌታ ልደት እን ደ ነገራቸው እንደዚሁም ኮከብ በመታየቱ ብቻ ለአሕዛብ ሁሉ ልደቱን አ በሠረ በኮከቡም እየተመሩ ሰብአ ሰገል የተባሉ የምሥራቅ ጠቢባን ነገሥታት ኢየሩሳሌም ደረሱ የአይሁድ ንጉሥ የት እንደ ተወለደ በመጠየቃቸው በዘመት የነበረው ንጉሥ ሄሮድስና የኢየሩሳሌም ከተማ ሁሉ በ ሰሙት አዲስ ዜና ተደናገጡ በትንቢት እንደ ተነገረው ከቤተ ልሔም እንደ ሚወለድ ስለ ተረዱ ሰብአ ሰገል ከቤተ ልሔም ከተማ ገቡ ያዩትም ኮከብ ሕፃ ኑ እስከ ሚገኝበት ቦታ ድረስ መራቸው ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅ እና ዕጣን ከርቤም አቀረቡለት ማቴ የስጦ ታዎቹም ትርጉም ወርቅ የጌታችንን ንጉሥነት ዕጣን ክህነቱን ከርቤ ክቡር ሞቱን የሚያስታውቀን መሆኑን የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስተምሩናል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናኖትና ክርስቲቓይናዊ ሕይጠት ሪኃቋ ሄፖ ጩዌድደ ዕፅ መሪድኗደድ ከሰብአ ሰገል ታሪክ ቀጥሎ የምንማረው አራተኛው የትምህርት ርእስ ስለ ጌታችን ወደ ግብፅ መሰደድ ነው ከማቴዎስ ወንጌል እንደ ምናነበው ታላቁ ሄሮድስ የአይሁድ ንጉሥ የጌታችንን በቤተ ልሔም መወለድ በምሥጢር እንደ ተረዳ ሊገድለው አስቦ በቤተ ልሔም ኣካባቢ የሚገኙትን ሕፃናት ሁሉ አ ስገደለ ነገር ግን ቅዱስ ዮሴፍ ቀደም ብሎ በጌታ መልአክ ትእዛዝ መሠረት ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብጽ ሸሸ ከዚያም ወደ ናዝሬት እስኪመለሱ ድረስ ስደተኛ በመሆን ቆይተዋል ማቴ በስደታቸውም ጊዜ ብዙ መከራና ችግር ደርሶባቸዋል እንግዲህ ወልደ እግዚአብሔር ፍጽም ሰው በመሆን ገና በበረት ከመወለዱ ጆምሮ በኋላም በስደቱ መከራ መቀበሉ ስለ እኛ ስለ ሰዎች ደኅንነት መሆኑን ማስታወስ ይኖርብናል በቤተ ክርስቲያናችንም የሕፃኑንና የእናቱን የስደት መከራ ለማስታወስ በየዓመቱ ከመስከረም ቀን ጀምሮ እስከ ኅዳር ቀን ድረስ ይታሰባል ካህናቱም እሑድ እሑድ በማኅሌተ ጽጌ ያከብሩታል ምእመናንም በየዓመቱ ይህንን ዘመነ ጽጌ ተብሎ የሚታወቀውን ጊዜ በማስታወስ የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ተሳታፊነታቸውን በበጎ ምግባራቸው ይገልጻሉ የጠፋውን አዳም ሊፈልግና ሊያድነው ሰው ሆኖ የመጣው ክርስቶሰ በመጆመሪያ የደረሰበትን ችግርና መከራ በጽሞና በማሰብ ትሩፋትን የሚያዘወትሩ ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ሕይወት ጋር ያላቸውን አንድነት ለመግለጽ በጸም በጸሎት ይተጋሉ ጋ ወቧይሄሯፎና ይጋ መድፉ ከጌታ ልደትና የሕፃንነት ታሪክ ጋር አያይዘን የምንማራቸው ሁለት ነገ ሮች አሉ በመጀመሪያ በአንቀጸ ሃይማኖት ላይ እንደ ተገለጸው ጌታ ፈጽሞ ሰው ሆነ የተባለውን የምንረዳው ሕግ ጠባይዓዊን እየፈጸመ ቀስ በቀስ ማደጉን የሚያመለክት ነው ሕግ ጠባይዓዊ ማለት የሰውነትንና የተፈጥሮን ሕግጋት በመጠበቅ ከመፀነስና ከመወለድ ጀምሮ ሕፃን ሆኖ ጡት እየጠቡ ቀስ በቀስ ማደግንና እስከ አቅመ አዳም መድረስን መራብና መጠማትን መከራና ኀዘንን መብላትና መጠጣትን መተኛትና መነሣትን መድከምና መበርታትን ሌሎችንም የመሳሰሉትን ሁሉ ያጠቃልላል ምንም ያለ ዘርዐ ብእ ሲ ቢፀነስም ሥጋን በመዋሐዱ ጌታ ሕግ ጠባይዓዊን ከኃጢአት በቀር በየደረጃ ው ፈጽሞታል ሁለተኛው ሕግ መጽሐፋዊ ይባላል ይህም ማለት ጌታችን ሕገ ኦሪትን እየፈጸመ ማደጉን የሚያስረዳን ነው በስምንተኛው ቀን መገረዝን በአርባኛው ቀን ቤተ መቅደስ መግባትን በዓመት ሦስት ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም መሄድንና ሌሎችንም የኦሪት ትእዛዛት ሁሉ ጌታችን እንደ ፈጸማቸው ተጽፏል ሉቃ ጌታ ሕግን ሁሉ የፈጸመው እኛ ሕግ አፍራሾችን በእርሱ እምነትና ጸጋ ሥር ያለነውን በእርሱ መንፈስ የምንመላለሰውን ሁሉ እንደ ሕግ ፈጻሚዎች ሊቆጥረን ኣስቦ ነው ሮሜ እንዲህም በማድረጉ በሕግ አፍራሽነታችን ከሚመጣብን ፍርድና ኩነኔ ነፃ አውጥቶናል አድኖናል ቤተ ክርስቲያናችን ጌታ የተወለደበትን ታኅሣሥ ቀን መነሻ በማድረግ በስምንተኛው ቀን ግዝረትን ጥር ቀን በአርባኛው ቤተ መቅደስ የገባበትን የካቲት ቀን በየዓመቱ ታከብራለች እነዚህን በዓላት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲፀናዌ ሕፎዩዉጠት በምናከብርበት ጊዜ ጌታ ስለ እኛ ሰው ሆኖ ሕግጋትን በመፈጸሙ እንዳዳነን ማስታወስ ለአማኞች ሁሉ አስፈላጊ ነገር ነው ወንዶች ልጆች በአርባ ቀናቸው ሴቶች ሕፃናት በሰማንያ ቀናቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ የጥምቀትን ሕግ መፈጸማቸው ከዚሁ ታሪክ ጋር የተያያዘ መሆኑን እንረዳለን ረ ጌታ በውኃና በመንፈስ ስለ መምጣቱጥምቀቴ በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ በውኃና በደም በመንፈስ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ የጻፈውን መነሻ በማድረግ ስለ ጌታ ጥምቀት ዓላማ ለማስረዳት እን ጀምራለን ኛዮሐ። እንግዲህ ክርስቶስ በአ ብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድን መላለስከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትን ሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን ሮሜ እንግዲህ ክርስቶስ ተጠምቆ እንድንጠመቅ ያደረገን ከሞቱና ከትን ሣኤው ተሳታፊዎች እንድንሆን ነው ጌታ በጥምቀቱ ለሰዎች ልጆች ሁሉ ኃጢአት በመስቀል ላይ መሞቱን ያስረዳናል እኛም በጥምቀታችን ከጌታ ጋር ተባባሪ ስንሆን ለኃጢአት መሞታችንን ማለት ከክፉ ሥራ መለየታችንን ለመን ፈስ ቅዱስ መገዛታችንን በአናናራችን የምንመሰክርበት ነው ከኃጢአት ሕይወት ወደ ጸጋ ሕይወት የምንተላለፍበት አውነተኛ መንገድ ነው ኢያሱ ዮርዳኖስን ተሻግሮ እሥራኤልን ሁሉ እንዳሻገረና ምድረ ርስትን እንዳወረሳቸው እንዲሁም ጌታችን ተጠምቆ እንድንጠመቅ በማድረጉ ከሞት ወደ ሕይወት አ ሻግሮናል ገነት መንግሥተ ሰማያትን አውርሶናል በተጨማሪ በክፍል ሁለት ስለ ጥምቀት የተጻፈውን ተመልከት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕፎጾዉት አንቀጽ ጁ ሰው ሆኖ በጳንጤናዊ በሏላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ ታመመ ሞተ ተቀበረም በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈ በዚህ አንቀጽ ውስጥ የጴላጦስ ስም የተጠቀሰበት ምክንያት የጌታ ሞትና ትንሣኤ የተፈጸመበትን ዘመን ለማመልከት የድርጊቱን ታሪካዊነትና እውነተኛነት ለመግለጽ ነው እሥራኤል የሮማ ቅኝ ግዛት በነበረችበት ዘመን የጢባርዮስ ቄሣር እንደራሴ ጳንጤናዊ ጺሏላጦስ አገሪቱን ይገዛ በነበረ ጊዜ የጌታችን ሕማምና ሞት በእርሱ ዳኝነት ተፈጸመ ይህ ታላቅ ነገር በዓለማችን ውስጥ በአንድ ክፍለ ዘመን በአንድ ክፍለ ሀገር የተከናወነ እውነተኛ ታሪክ መሆኑን እንገነዘባለን የክርስትና አጀማመር በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ላይ የተመሠረተ ነው በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ኣ ዲስ የታሪክ ምዕራፍን ከፍቷል ከጳንጤናዊ ጴላጦስ ጀምሮ የዚህ ዓለም ገዢዎች ክርስትናን ወይም ቤተ ክርስቲያንን በዓይነ ቁራኛ ይመለከቷታል ክርስቲያን መሪዎች እንኳ ቢሆኑ ለራሳቸው ጥቅምና አገልግሎት እንድትውል ያደርጓታል ሌሎች ደግሞ ይፈርዱባታል ያሳድዷታልም እግዚአብሔር ግን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ይጠብቃታል በአንቀጽ ውስጥ የምንማረው በመጀመሪያ ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሕማማትንና ሞትን መቀበሉን ሁለተኛ ጌታ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ ነፍሳትን እንዳዳነ ሦስተኛ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ሲሆን በመጨረሻ ስለ ቅዱሳ ት መጻሕፍት በአጭሩ እንመለከታለን ሀ ጌታ ስለ ኃጢአታችን በሥጋ ስለ መሞቱ ጌታ በመስቀል ላይ ሲሞት በለበሰው ሥጋ እንጂ በመለኮቱ አይደለም ክርስቶስ በአምላክነቱ ሞት የለበትም ኛጴጥ ጌታችን ሰው የሆነው የሰውን ኃጢአትና ሞት ለማሰወገድ ነው ስለዚህም ጌታችን በለበሰው ሥጋ እንደ ሚታረድ በግ ለኃጢአታችን መሥዋዕት ሆኗል እነሆ የእግዚአብሔር በግ የዓለምን ሁሉ ኃጢአት የሚያስወግድ በማለት ስለ ክርስቶስ ተጽፏል ዮሐ ስለዚህም ክርስቶስ የዓለምን ሁሉ ኃጢአት በመሸከም በእኛ እግር ተተክቶ በመስቀል ላይ ሞቶልናል አዳም በበደለ መድኃኔ ዓለም ካሠ የተባለው እውነት ነው አዳም የፈጠረውንና የሚወደውን አምላኩን በመበደሉና ትእዛዙን በመጣሱ ከእግዚአብሔር ተጣልቶና ተለይቶ ይኖር ነበር በዚህም የተነሣ ውርደትና ውድቀት ደረሰበት የእግዚአብሔርም ቁጣና እርግማን በበደለኛው በአዳምና በልጆቹ ላይ ማለት በኃጢአተኞች ሁሉ ላይ ስለነበረ የሞት ሞት ተፈረደባቸው በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ትልቅ የጥል ግርግዳ ተፈጠረ ሰውም የእግዚአብሔር ጸጋና ረድኤት ስለ ተለየው በመከራና በፈተና በሞትና በሕይወት መካከል በችግርና በስቃይ የሚኖር ሀሆነ እን ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲወናቫዊ ሕይዉት ግዲህ ወደ እግዚአብሔር ማን ይቀርባልን ማንስ ያስታርቃል። ነውና በእርሱ በኩል ካልሆነ ወደ አብ የሚመጣ የለም ዮሐ የተባለው በእርሱ ሥጋዌ በማመን እርሱ በከፈተው የጽድቅ መንገድ እርሱ በመስቀሉ ባስገኘው ቤዛ ካልሆነ በቀር በገሐድ በሥጋዌ ያልተገለጠውን አብን የሚያገኘው የለም ማለት ነው አንድም የለ እኔ ወደ አብ የሚመጣ የለም እኔን ተወሳዲ ካላለ አብን ወላዲ የሚለው የለም ማለት ነው ዮሐ ትርጓሜውን ተመልከት በመሠረቱ ሰው ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የሚችለው ሰው በሆነው ብክርስቶስ በኩል ነው ከዚያ በፊት ግን ሰው መጀመሪያ ወደ ክርስቶስ ለመ ቅረብና እርሱን ለማመን የሚችለው የእግዚአብሔር ረድኤት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ወደ ክርስቶስ ሲስበው ነው በመሆኑም ክርስቶስ አልቦ ዘይክል መጺአ ኀቤየ እመ ኢሰሐቦ አብ ዘፈነወኒ የላከኝ አባቴ በሀብት ስቦ በረድኤት አ ቅርቦ ካልሰጠኝ በኔ ማመን የሚቻለው የለም ብሏል ዮሐ ትርጓሜውን ተመልከት እንግዲህ ራሱ እግዚአብሔር እኛ ሰዎችን ኃጢአተኞችን ከራሱ ጋር ለማስታረቅና ለማቅረብ ያሰበውና ያዘጋጀው የጽድቅ መንገድ የሕይወት መንገድ በልጁ ሰው መሆን ማለት በምሥጢረ ሥጋዌና በነገረ መስቀል እንደ ተገለጸው ተፈጽሟል በሥጋዌ ወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስ የሰውን ባሕርይ ባሕርዩ በማድረጉ ያን ጊዜ ባሕርያችንን ከእግዚአብሔር ጋር አኣስታርቋል ስለዚህ ነው የአብ ሊቀ ካህናት የሚሆን እርሱ የሰውን ባሕርይ ከእግዚአ ብሔር ጋር አስታረቀ እያልን በሐዋርያት አመክንዮ እምነታችንን የምንገልጸው ሥርዓተ ቅዳሴ ቁጥር ተመልከት በመስቀሉ ደግሞ ነፍሱን ሰለ ሁላችን ቤዛ አድርጎ በመሰጠቱ ሰውን ከእግዚአብሔር አጣልቶና አርቆት የነበረውን ኃጢአትን አስወግዶ እርቅና ሰላምን አስገኝቶልናል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን መሥዋዕት በመሆኑ እውነተኛ አስታራቂያችን ሆኗል ቤተ ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሰን አማናዊው መንገድ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት የተባለው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው እግዚአብሔር ወደ አለበት ወደ ቅድስት ለመግባት የምንችለው በክርስቶስ ሥጋ በኩል እንደ ሆ ነ ቅዱስ ጳውሎስ ለዕብራውያን ክርስቲያኖች ሲጽፍ እንግዲህ ወንድሞች ሆይ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት እንዳላን ና እንዲሁም በእግዚአብሔርም ቤት ላይ የሆነ ታላቅ ካህን እንዳለን ገልጸልናል ወዶ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን የሚለውን የሐዋርያውን ቃል ትርጉም ወይም ምሥጢር የምንገነዘበው ሰው በሠራው በደልና ኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይቶ በፍርሃትና በጭንቀት ሲኖር ሳለ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ደመን አፍስሶ ኃጢአቱን አስወግዶ ከራሱ ጋር አስታርቆ ወደ ቅድስት የሚወስደው መንገድ እንዲከፈት አድርጉ ወደ ሰማያዊው መቅደስ ወደ ጸጋው ዙፋን ወደ እግዚአ ብሔር ለመምጣት ለመግባት መብትን ድፍረትን እንዲሁም የጸጋ ልጅነትን እንዲያገኝ ሥልጣንን አንደ ሰጠው በማመን ነው ብ ዮሐ የቀድሞው የብሉይ ኪዳን መንገድ ወይም ሥርዓት የሰውን ኃጢአት ስለ ማያስወግድ ከእግዚአብሔርም ስለ ማያስታርቅ እግዚአብሔር በፈቀደውና በወደደው በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ እርሱ እንድንመጣ አድርጉናል ይኸውም መንገድ በኦሪቱ ሊቀ ካህናትና በእንስሳት መሥዋዕት በኩል ሳይሆን ክርስቶስ በሰውነቱ በሥጋው በኩል በፈጸመው መሥዋዕትነትና ሊቀ ካህናትነት እንደሆነ ሐዋርያው ለዕብራውያን በጻፈው መልእክቱ አረጋግሖጦልናል እንግዲህ ወደ ቅድስት የሚወስደው መንገድ ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሰው መንገድ በኦሪቱ ሥርዓት በቤተ መቅደሱ መጋረጃ ተዘግቶ የነበረውን በዕለተ ዓርብ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ በሥጋው በፈጸመው መሥዋዕትነትና አስታራቂነት አስወግዶታል ያን ጊዜ መጋረጃው ተቀጻጳል ማቴ በክርስቶስ ለሚያምኑት ሁሉ ወደ ፈጣሪያቸው የሚደርሱበት የእርቅና የሰላም የጽድቅና የሕይወት መንገድ ተከፍቶላቸዋል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛማናኖትና ክርስቲያናዊ ሕይወት ክርስቲያንም በእርሱ ስም በእርሱ መሥዋዕት የማስታረቁን ሥራ እርሱ ዳግመኛ እስኪመጣ ድረስ በኃላፊነት እንድትሠራ ታዛለች ቆሮ ቆሮ ማቴ ስለዚህ ነው ክርስቶስ ከጥንት ጀም ሮ እስክ ዘላለሙ ድረስ አስታራቂ ሆነን ተብሎ የተጻፈው ሄኖክ «እንደ መልከ ጹዴቅ ባለ ሹመት የዓለም ካህን እንደ ሆንክ» የተባለለት «እሱ ለዘለዓለም ይኖራል ክህነቱ አይሻርምና ዘወትር በእሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡትን ሊያድናቸው ይቻለዋል ለዘለዓለም ሕያው ነውና ያስታርቃቸዋል እንዲህ ያለ የካህናት አለቃ ይገባናል ከሰማያት በላይ የሆ ነ ኦሪትስ የሚሞት ሰውን ሊቀ ካህናት አድርጋ ትሾማለች ከኦሪት በኋላ የመጣው የአግዚአብሔር የመሐሳ ቃሉ ግን ዘለዓለም የማይለወጥ ፍጹም ወልድን ካህን አድርጎ ሾመልን» ዕብዐ የግዕዙን ትርጉም ተመልከት ክርስቶስ መካከለኛ የተባለበት አዳምና ልጆቹ ሁሉ በኃጢአት ምክን ያት ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተው ተለይተውና ርቀው የነበሩትን በማስታረቁና በማቅረቡ ነው ወኮነ ዐራቄ ለሐዲስ ኪዳን በውጊዘ ደሙ ቅዱስ አንጽሖሙ ለመሃይምናን ወለሕዝብ ንጹሐን እንዲል ለወንጌል ሊቀ ካህናት ለመንግሥተ ሰማያት አስታራቂ ሆነ በከበረ ደሙ ፈሳሽነት በዓ ለመ ሥጋ በዓለመ ነፍስ ያሉትን አዳናቸው አነጻቸው ወደ ቅዱስ እግዚአ ብሔርም አቀረባቸው ዕብ እና የእሑድ ውዳሴ ማርያም ትርጉም ተመልክት በቅድሚያ እርሱ ራሱ በተዘምዶት ሥጋ ማለት ሰው በመሆኑ ወደ እኛ ቀርቧል ከእኛም ጋር ታርቋል እንግዲህ እርሱ ራሱ በሰውነቱ ቀርቦ አቅርቦናል ታርቆ አስታርቆናል ፇሪ መሪፇሷጳ ክርስቶስ የአዳምን ዘር ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት አድርጐ ነው ያስታረቀው። ለሚለው ጥያቄ መልሱ ወደ ነገረ መስቀል ይወሰስደናል ነገረ መስቀልን ለማወቅ የመስቀሉን ነገር ለመረዳት የክርስቲያንን ሃይማኖት መሠረታዊ ምሥጢር መመርመር ያስፈልጋል የምሥጢረ ሥጋዌም ዓላማ በነገረ መስቀል ይተረጐማል እንግዲህ ከሁሉ በፊት መረዳት ያለብን ከጥንተ ፍጥረት የነበረውን የፈጣሪንና የፍጡሩን የሰውን ግንኙነት ነው እግዚአብሔር በቸርነቱ ሰውን ከሁሉ ፍጥረት ኣልቆ በራሱ አኣ ርአያና አምሳል ፈጥሮ ገነትን ያህል ቦታ አዘጋጅቶ በተድላ በደስታ እንዲኖርና ሌሎች ፍጥረታትንም እንዲገዛ ሥልጣንም ጭምር ሰጥቶት ነበርዘፍ አዳም ግን የእግዚአብሔርን ሕግ በማፍረስ በደለ ከፈጣሪውም ጋር ራሱን ለማስተካከል በማሰቡ ይቅርታ የማይገባውን ዓመፅ ፈጸመ እንደዚህ በማድረጉ ከእግዚአብሔር ተጣላ ከፊቱም ተባረረ ከገነትም ወጣ ሁለት ዓይ ነት ሞት ተፈረደበት በሥጋው ወደ መቃብር በነፍሱ ወደ ሲኦል ወረደ እግዚአብሔር ርኅሩኅ ስለሆነ የፍጡሩ የሰው ሥቃይ ስላሳዘነው ከራሱ ጋር የሚታረቅበትን መንገድ አዘጋጀ ስለዚህም የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዓለም መጣ ቃሉም ሥጋ ሆነ ሁለተኛው አዳም በመባል ክርስቶስ ኃጢአት በሌለበት ሰውነቱ የመጀመሪያውን አዳም ኃጢኣት ተሸክሞ የርሱን ሞት ሞቶ በመስቀል ላይ የሕይወት መሥዋዕት በመክፈል ከራሱ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አስታርቆታል ከነልጆቹም ከሲኦል አውጥቶ ገነት አኣስገብቶታል እንግዲህ በክርስቶስ መስቀል ለሰዎች ሁሉ እርቅና ሰላም እንደ ወረደ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕይወት እናስተውላለን ቆላ ክርስቶስ በአዳም ምትክ ባይሞት ኖሮ የአዳም ኃጢኣት እንደ ተያዘ የሞት ፍርዱም እንደ ጸና ለዘላለም ይቀር ነበር ነገረ መስቀልን አንዳንድ ወገኖች ለመረዳት ኣስቸጋሪ ይሆንባቸዋል እን ደ እነርሱ አስተሳሰብ እግዚአብሔር ከሰማይ እንዳለ በቃሉ ብቻ በመናገር ለሰ ዎች ልጆች የኃጢአት ሥርየትንየምሕረት ጸጋን ሊሰጥ ይችላል በማለት ይናገራሉ ነገር ግን የሰው ሐሳብና የእግዚአብሔር ሐሳብ የተለየ ነው እግዚአብሔር የተሻለውንና የሚገባውን መንገድ መርጧል አሁንም ቢሆን ምሕረትን ያገኘነው በእግዚአብሔር ቃል ነው የእግዚኣብሔር ቃል ሥጋን ለብሶ ሰው ሆኖ የምሕረትን ጸጋ ሰጠን የምሕረቱ አዋጅ በንግግር ብቻ ከሚገለጽ ይልቅ ሰው በሆነው በእግዚአብሔር ቃል በሥጋና በደም ኪዳን መጽናቱ እጅግ የበለጠ ነው መለኮታዊ ቃሉ ሰው ሆኖ በሰው መካከል በመ መላለስ የእግዚአብሔርን ጸጋና ምሕረት በማብሠር የእግዚኣብሔር ፍቅር በሰ ዎች ልቡና በጋለ ስሜት እንዲመሠረት አድርጓል በሩቅ ከመናገር ይልቅ ሰውን መስሎ ሰውን አህሎ እንደባልንጀራ ሆኖ በቅርቡ በመነጋገር ሥግው ቃል ክርስቶስ አዲስ ልቡና አዲስ መንፈስን ለሰው ልጆች ሊሰጥ አስችሎታል እስከ ሞት ድረስ ሰውን መውደዱን በሰውነቱ ገልጸታል በንግግር ብቻ ቢሆን ነቢያት ሁሉ የተናገሩትና የአስተማሩት በቂ በሆነ ነበር ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ይህ በቂ አልነበረም ለሚመጣው እውነተኛ ነገር መንገድ የሚያዘጋጅ ነበር እንጂ እውነተኛው ነገር አካላዊ ቃል ሰው በሆነ ጊዜ ሰው ሁሉ ሙሉ ምሕረትንና ደኅንነትን አግኝቷል የሰ ውንም ሕማምና ሞት ተቀብሎ ትንሣኤ ሙታንን በተጨባጭ ለማብሠር የቻለው በለበሰው ሥጋ ነው እንግዲህ የእግዚአብሔር ቃል በነቢያት አማካኝነት ስለ ኃጢአት ሥርየትና ስለ ዘላለም ሕይወት በቃል ብቻ ተነግሮ ከሚቀርና የእግዚአ ብሔር አካላዊ ቃል ሥጋ ለብሶ ሰው ሆኖ የሰውን መከራና ሞት ቀምሶ በመጨረሻም ከሞት ተነሥቶ በድርጊት ከማሳየት የቱ ይበልጣል። ጴላጦስ ግን አንድ በደል ስንኳ አላገኘሁበትም በማለት ወደ ሄጄ ሮድስ ላከው እርሱም ከሠራዊቱ ጋር ናቀው ዘበተበትም የጌጥ ልብስም አ ልብሶ ወደ ኢሏላጦስ መልሶ ሰደደው ሉቃ ከጺላጦስ ፍርድ ችሎት ሁለተኛ በቀረበ ጊዜ ሊቃነ ካህናቱና ሕዝቡ ስቀለው ስቀለው እያሉ ጩኸት ስላበዙ ክርስቶስ በጅራፍ ተገርፎ በራሱ ላይ የእሾህ አክሊል ተደፍቶ ከለሜዳ ቀይ ልብስ ለብሶ እንዲሰቀል ኢሏላጦስ አሳልፎ ለአይሁድ ሰጣቸው ጌታችንንም የሚሰቀልበትን መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ኮረብታ እንዲወጣ አደረጉት ከዚያም እግሩንና እጁን በቀኖት በምስማር ከመስቀሉ ጋር ቸንክረው በሁለት ወንበዴዎች መካከል ሰቀሉት የክሱ ጽሕፈትም በመስቀሉ ራስ ላይ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ በማለት በሦስት ቋንቋ ማለት በዕብራይስጥ በሮማይስጥና በግሪክ ፊደል ተጽፎ ነበር ማር ዮሐ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ተብሎ በጥምቀቱ ጊዜ የተነገረው በመስቀል ላይ ለተሰቀለው ለኢየሱስ ክርስቶስ ነው ዮሐ የጌታ ጥምቀቱ የሞቱ ምሳሌ ነበርና ሉቃ እርሱ ለበደላችን ካሣ ለዓለም ቤዛ ሆኖ ክቡር ሕይወቱን ሠውቷል ክቡር ደሙን አ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደይማናትና ክርስቲያናዊ ሕይደዉት ፍስስል ለሰቀሉት አይሁድ እንኳ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ማራቸው በማለት ይቅርታን ለምኖላቸዋል ሉቃ ክርስቶስ ለመሥዋዕት እንደ ቀረበው እንደ እግዚአብሔር በግ ብቻ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔርም ሊቀ ካ ህናት በመሆን ራሱን እንደ መሥዋዕት አቅራቢ ሆኖ ለዓለም ሁሉ የኃጢአት ሥርየትን አስገኝቷል ሰውን ከእግዚአብሐር ጋር አስታርቋል ይኽም ሲባል ሰውን ከራሱ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በሞቱ ማስታረቁን ማስተዋል ይገባል በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ያለው መካከለኛ የተባለው እርሱ ሰው የሆነ ክርስቶስ ነው ራሱን ለሁሉም ቤዛ የሰጠ ኛጢሞ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣበትን ሥጋ የለበሰበትን ዓላማና ተግባር የፈጸመው የኃጢአት መሥዋዕት በመሆን በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ ነው ስለዚህ ነው በመስቀል ላይ ሆኖ ተፈጸመ በማለት የሞትን ጽዋ የተቀበለው ራሱን ኣዘን ብሎ ነፍሱን አሳልፎ የሰጠው ዮሐ እንግዲህ ክርስቶስ በእግዚአብሔርና በ ሰው መካከለኛ እንደ መሆኑ ስለ ኃጢአት ምሕረትን የመለመንና የማስታረቅ ሥራውን አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ መሥዋዕት በመሆን ፈጽሞታል ዕብራ ይህ ይቅርታን የመለመንና የማስታረቅ ሥራ ከትንሣኤ በኋ ላም የክርስቶስ አካል በሆነችው በቤተ ክርስቲያን ጸሎትና ምልጃ እንደዚሁም በምታ ቀርበው መሥዋዕተ ቁርባን አማካኝነት ቀጥሏል ዛሬም ይህ የማማለድና የማስታረቅ ሥራ በሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ይሠራበታል ስለ ክርስቶስ መልእክተኛ በመሆን ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ እያለች ሰዎችን ትለምናለች እግዚአብሔ ርንም ታማልዳለች ምክንያቱም የማስታረቁ አገልግሎት ለእርሷ ከእግዚአብሔር ስለ ተሰጣት ነው ኛቆሮ ከክርስቶስ ጐን በወጣው ንጹሕ ውኃና ደም የዓለም ሁሉ ኃጢአት ተወ ግዲል ይህም ውኃና ደም ዛሬም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ረድኤት በምሥጢረ ጥምቀትና በምሥጢረ ቁርባን አማካኝነት ይገኛል አምነው ለተቀበ ሉትና ለፈጸሙት ሁሉ የኃጢአት ሥርየትንና የዘላለም ሕይወትን ይሰጣል ቤተ ክርስቲያን በምሥጢራት አማካኝነት በዕለተ ዓርብ በክርስቶስ መሥዋዕትነት የተገኘውን የደኅንነትና የሕይወት ጸጋ ወደ እርሷ ለሚመጡት ሁሉ በነፃ ትሰጣለች ይህንንም ጸጋ እንዲቀበሉ ጥሪ ታደርጋለች በጸሎተ ቅዳሴዋም ፈያታዊ ዘየማንን እን ዳሰብከው አቤቱ እኛንም በመንግሥትህ አስበን እያለች ለሁላችንም ታማልዳለች የደኅንነታችን ጸጋ ምንጭ የሆነውን ለሁላችንም የተሠዋውን የእግዚአብሔርን በግ ከሰማይ ሠራዊት ጋር በመሆን ቤተ ክርስቲያን እንዲህ እያለች አዲሱን ቅኔ ትዘምራለች ታርደሃልና በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው የታረደው በግ ኃይልና ባለጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል ራእይ ከሰባቱ አጽርሐ መስቀልኞ አንዱ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ ። ይበቃናል ሌላ ነገር አያስፈልገንም የሚሉት ወገኖች እንኳ ከቤተ ክርስቲያን ትውፊት ሙሉ በሙሉ የተለዩ አይመስሉም ምክንያቱም እነርሱ የተለዩዋትን ቤተ ክርስቲያን በመቃወም ኣንፃር ይቁሙ እንጂ በመጠኑም ቢሆን የትውፊቱ ተካፋዮች እንደ ሆኑ በአንዳንድ ሁኔታዎች ይታወቃል እንዲያውም ከመካከላቸው ቤተ ክርስቲያን ከመከፋፈሏ በፊት የነበረውን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ሁሉ የማሜደግፉ አሉ እነርሱ በአጠቃላይ ሲገልጹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የተጋነነውንና የተትረፈረፈውን ትምህርትና ሥርዓት ትሕርምት የበዛበትን መንፈሳዊ አኗኗርም በኋላ ዘመን እንደ መጣ እንደፈሪሳዊ ወግ ይቆጥራሉ እንደዚህ ያሉበትም ምክንያት የወንጌልን ሕግና ሥርዓት የጣሰ ስለመሰላቸው ይሆናል ስለዚህ ትውፊት ብለን ስንናገር ሕገ እግዚአብሔርን የሚያስተው መሰሎ ይታያቸዋል ነገር ግን ትውፊትና መጽሐፍ ቅዱስ ከላይ እንደ ጠቀስነው ከአንድ ምንጭ የፈለቁ ስለሆነ ይተባበራሉ እንጂ አይጣሉም ሁለቱንም ከጌታና ከሐዋርያት የተቀበልናቸው ሰለሆ ነ ሁለቱንም አክብረን እንይዛቸዋለን እንጂ አንዱን ብቻ ይዘን ሌላውን የምን ተውበት ምክንያት የለንም ሐዋርያት ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንደ ሚተጉ እንጀራንም አ ብረው እንደ ሚቆርሱና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንንም እንደ ሚፈጽሙ ተጽፏል የሐዋ ቆሮ ይህም ማለት ለመጆ መሪያዎቹ ምእመናን በሐዋርያት የሚሰጠው ኣገልግሎት ቃሉን መስበክ ብቻ ሳይሆን የምሥጢራት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎትም እንደሚሰጥ እን ረዳለን ከዚህ ጋር ልዩ ልዩ ጸሎት በተወሰነ ሰዓት እንደሚደርስ የታወቀ ነው እነዚህና የመሳሰሉት ሁሉ ቀድሞ በሐዋርያት የተፈጸሙ ዛሬም በቤተ ክርስቲያናችን የሚፈጸሙት ከሐዋርያዊ ትውፊት የተገኙ ናቸው መጽሐፍ ቅዱስን መስበክ ከዚህ ውስጥ አንዱ የትውፊት ክፍል ነው እንግዲህ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ይበቃናል እርሱን ብቻ ካስተማርንም ሌላ ነገር አያስፈልግም በማለት እጅ እግርን አጣምሮ መቀመጥ አኣይገባንም ምክንያቱም ከሐዋርያት የወረስነው ሰብከተ ወንጌል ብቻ አይደለም እንደ ሐዋርያት በየጊዜው ተሰብስቦ ጸሎት ማድረስ መባና መሥዋዕትን ማቅረብ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን መፈጸም ለተቸገሩ መርዳትና የመሳሰሉትን ሁሉ ማድረግ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ መብትና ግዴታ ነው ይህንን የማትፈጽም ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊት አይደለችም የተቀደሰውም የትውፊት ርቱዕነት እውነተኝነት መመዘኛው ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ባለው ስምምነት ነው ስለ ትውፊት ስንናገር በሰዎች የተዘጋጁትን ሐሰተኛ ትውፊቶች ወጐች ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትን ወይም መንፈስን የሚቃወሙትን ማለታችን አይደለም ጤነኛ እውነተኛ ትውፊት በሚከተሉት ተራ ቁጥር የተጻፉትን ማሟላት አለበት ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የማይቃረን ገላ ከሌላ የቤተ ክርስቲያን ትውፊቶች ጋር የማይቃረን በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት ያለው ኮዕክ ከዕከህ ክዐጸየክቨሃር ፔከዐኗሂ ር የ ፐፍኮ ጸዝበ ክ ሃ ኮዩ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፎማናትና ክርስቲናዌ ሕፎዩዉጠት ትውፊት ከእርሷ ዘንድ አይገኝም ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር የተቀደሰው ሐዋርያዊ ትውፊት ለቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖቷን ብቻ ሳይሆን ሥርዓተ አምልኮትዋንና በጐ አ ድራጐትዋን አኗኗርዋንና ሥነ ምግባሯን የሚገልጽና የሚወስን የሚመራም ስለሆነ ለሚቀበሉት ሁሉ የተሟላ መንፈሳዊ ሕይወትን ይሰጣል ምክንያቱም የመለኮታዊ መገለጥ እውቀት በምልዐት የተላለፈው በዚሁ መንገድ ሰለሆ ነ ነው ከሐዋርያዊ ትውፊት ተከፍሎ የመጣውን ቅዱሳት መጻሕፍትን እንደ ተቀበልን እንዲሁም ከሐዋርያት በቃል ለተላለፈው ትውፊት መታዘዝ ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለተሰሎንቄ ሰዎች እን ደ ጻፈው መልእክቱን ብቻ ሳይሆን በቃልም በተግባርም ያስተላለፈውን ወግ ማለት ትውፊት ሁሉ አጥብቀው እንዲይዙ ከምክርና ከአደራ ጋር አ ስታውቋቸዋል ኛተሰ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስን በምናጠናበት ጊዜ መላውን ሐዋርያዊ ትውፊት አብሮ መማር ይኖርብናል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኘውን ሐዋርያዊ ትውፊት ብንማረውና ብንመራበት በመንፈስ ቅዱስ ረድኤት መጽሐፍ ቅዱስን አንብበን በትክክል ለመረዳት እንችላለን መጽሐፍ ቅዱስን በእውነት መረዳት የሚቻለውና እርሱም የሚገኝ በት ቦታ የተቀደሰው ትውፊትና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት በሚጠበቅበት በቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው በማለት ቅዱስ ሄሬኒዎስ ያረጋግጣል ቀጥሎም ቤተ ክርስቲያን እንደ ገነት በዚህ ዓለም ውስጥ ተተክላለች ሰለዚህም መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ይላል ከአትክልት ቦታ ከሚገኘው ከማንኛውም ዛፍ በነፃ ብላ ዘፍ ይህም ማለት ከማንኛውም ከጌታ ቅዱሳት መጻሕፍት ብላ ነገር ግን በትዕቢት በተወጠረ ልቡና አትብላ የትኛውንም መናፍቃዊ ቅራኔን አ ትንካ ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች እነሱ ራሳቸው የደግና የክፉ እውቀት ባለቤቶች እንደ ሆኑ ይናገራሉና ነው እንደዚሁም የራሳቸው የሆነውን አምልኮ ቢስ ልቡናቸውን ከፈጠራቸው ከእግዚአብሔር በላይ አድርገዋልና ሲል ይህ በሁለተኛው ክፍለ ዘመን የነበረ የቤተ ክርስቲያን አባት መናፍቃንን በመቃወም የጻፈውን በመጥቀስ አባ ታድሮስ ማላትይ የግብፅ ኦርቶዶክስ መምህር በእንግሊዝኛ በጻፉት መጽሐፋቸው ገልጠውታልላ ቀሽ ኙ ፐ ኘእነ ለበሰ በከዐኗሂ ፎ ርሀቨ ከህ ዩ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛዩማናትና ክርስቲፀናዊ ሕጾፎዉት አንቀጽ ሟ በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛ ሕያዋንን ሙታንንም ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም ከልደት እስከ መቃብር ጌታችን ፈተናና ኀዘን መከራና ሕማም አል ተለየውም ነበር ከትንሣኤው በኋላ ግን ሕማምና ሞት ፈጽሞ አያገኙትም እርሱ ለዘላለም ሕያው ሆኖ በደስታና በክብር ይኖራል በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ ስንል ጌታችን በሚያስደንቅ ተአምራዊ ሁኔታ ከመሬት ከፍ ከፍ በማለት ወደ ሰማይ ወጣ ከብሩህ ደመና ውስጥ ገባ ከዓይንም ተሰወረ ማለታችን ነው እንደ ሄኖክ በመሰወር እንደ ኤልያስም በእሳት ሠረገሳ ሳይሆን በራሱ መለኮታዊ ሥልጣን በተዋሐደው ሥጋ ዐርጓል ብለን እናምናለን እንደዚህም በማድረጉ ከአብ የተላከበትን ዓላማ ታላቁን የማዳን ሥራ በመስቀል ላይ ፈጽሞ ወደ አብ መመለሱን እንገነዘባለን ጌታ በቀደመው ክብሩ በሰማያዊ መንበሩ ተቀምጧል ከአብ ዘንድ ክብርንና ምስጋናን አግኝቷል የተባለበትም ምክንያት ጌታ ለዘላለም የተዋሐደው ሥጋ መለኮታዊ ክብርን ማግኘቱን ለመግለጽ ነው ዮሐ ጴጥ ዳግመኛ ሕያዋንን ሙታንንም ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም ተብሎ የተገለጸው ቃለ ሃይማኖት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሁለተኛ ወደዚህ ዓለም መምጣት ያስረዳናል ዳግመኛ ይመጣል የተባለውም ከዚህ ቀደም መጥቶ እንደ ነበር ያመለክተናል ያንጊዜ ደዌያችንንና ሕማማችንን በመሸከም እኛን ለማዳን የባሪያውን መልክ ይዞ ራ ሱን ዝቅ አድርጐ መጥቶ ነበር የአሁኑ አመጣጥ ደግሞ ሰዎችን ሁሉ ለመግ ዛትና በዓለምም ላይ ፍርድ ለመስጠት በታላቅ ክብርና ጌትነት ይሆናል ይህቺ ቀን ለፍጥረት ሁሉ የምታስጨንቅና እጅግም የምታስፈራ ጊዜ ነች በነቢያትም በሐዋርያትም የተተነበየላት ታላቅ የፍርድ ቀን መሆኗ የታወቀ ነው ስለዚህም የሰው ልጆች መጨረሻ የሕይወት ሁሉ መዳረሻ ይህ ስለሆነ በምድር የሚገኝ ማንኛውም ሰው የኑሮውን ዓላማ በምርና በቁም ነገር ማሰብ ይኖርበታል ምክንያቱም የሃይማኖት ወገኖች ብቻ ሳይሆኑ በሃይማኖትም የማይኖሩት አሕዛብም ሁሉ ከዚያች የፍርድ ቀን የማያመልጡ ስለሆነ ነው ስለዚህ ነው ሕያዋንንና ሙታንን ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል የተባለው ሕያዋን የተባሉት ሕያው እምነትና በጎ ምግባር ያላቸው ሲሆኑ ሙታን የተባሉት ደግሞ እምነት የሌላቸው ብቻ ሳይሆኑ እምነት ኖሯቸው በጐ ምግባር የሌላቸው በተለይም እውነትንና የጽድቅ ሥራን የሚጠሉና በአመፅ ሥራ ላይ የተሰለፉት ሁሉ ናቸው ሌላው ትርጉም ደግሞ ሕያዋን የሚባሉት በዕለተ ምጽአት በምድር ላይ የሚገኙት በአፀደ ሥጋ ያሉትን ሕዝብና አሕዛብን ሁሉ ያመለክታል ሙታን የተባለው ቃል ደግሞ ከአዳም ጀምሮ እስከ ምጽአት ድረስ ያሉትን በመቃብር የሚገኙትን ሁሉ ያጠቃልላል ዮሐ ኛተሰሎ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይመናትና ክርስቲይናዊ ሕፎዉት ያሟመጋሟው ሪዕታፇረ ያዖጃሟመማሟያታምሠ ፇሠ ያዖሟያውቃ ያቋም ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆ ኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም ጊዜው መቼ እንዲሆን አ ታውቁምና ተጠንቀቁ ጸልዩም ለእናንተም የምነግራችሁን ለሁሉ እላለሁ ትጉ በማለት ክርስቶስ ለዚያች ቀን በጸሎት ተግተን በንስሐ ተዘጋጅተን እንድንጠብቀው ሐዋርያትን ብቻ ሳይሆን ሁላችንም እንድንጠነቀቅ ያስተምረናል ማር ያችን ቀን ማወቅ የእግዚአብሔር ድርሻ ነው የእኛ ፈንታ ግን ተዘጋጅቶ መኖር መሆኑን እንረዳለን እርሱ ለሁለተኛ ጊዜ ከአብ ዘንድ የሚመጣው ክርስቶስ ያችን ቀን ያውቃታል ሌሎች ግን መላእክትም ቢሆኑ የሰው ልጆችም ቢሆኑ አ ያውቋትም እርሱ ተመልሶ የሚመጣው ክርስቶስ የሚመጣበትን ጊዜ ምልክቶቹን ሁሉ አስታውቋቸዋል በቅድሚያም ሁሉን ነግሯቸዋል ማር ክርስቶስ ሁሉን ነገር የሚያውቅ ሲሆን ሁሉንም ምሥጢር አል ነገራቸውም። ምክንያቱም አንዳንድ መገለጽ የማይገባቸው ነገሮች ሰውን ስለ ሚጉጐዱ አይነገሩም አንዳንድ ነገሮች ደግሞ ቢነገሩ አድማጮች ሊቀበሉት የማይችሉት ወይም ለአእምሯቸው የማይስማማ ሆኖ ሊከብዳቸው ይችላል ስለዚህ ነው ጌታ ሐዋርያትን የምነግራችሁ ገና ብዙ ኣለኝ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም ብሎ ያላቸው ዮሐ እንግዲህ ያችን ሰዓት ልጅም ቢሆን ከአብ በቀር የሚያውቅ የለም ብሎ ጌታችን የተናገረው ዓለምንና ጊዜያትን ሁሉ የፈጠረና በኋላም ሊያሳ ልፋቸው የሚችል ፈጣሪ ብቻ ሁሉን የማወቅ ሥልጣን እንዳለው ሊገልጽልን አ ስቦ ነው ጌታም ከአብ ጋር አንድ ስለሆነና የአብ የሆነው ሁሉ እውቀትም ሥልጣንም የእርሱ ስለሆነ ሰለዚያች ቀን እርሱም ያውቃል ምክንያቱም ወልድ በመለኮቱ ከአብ ጋር እኩል ነውና እንግዲህ ክርስቶስ ሁሉን እያወቀ ራሱን ከአብ ለይቶ ያችን ቀን እንደማያውቅ የተናገረበት ምክንያት እርሱ ከአብ ተለይቶ ማለት ወልድ በተለየ አካሉ ቅድመ ተዋሕዶ የነበረ አላዋቂ ሥጋን እን ደ ተዋሐደ ለማስረዳት ነው ይህም ማለት ክርስቶስ ፍጹም ሰው በመሆኑ ለ ሰው ልጆች ሁሉ ወገናዊነቱን ያመለክተናል ከእኛ ጋር ያለውን ዝምድና ይገልጻል እርሱ ሰው ሆኗልና የሰው ልጅም ተብሏልና ክርስቶስ ፍጹም ሰውና ፍጹም አምላክ በመሆኑ በመለኮቱ ከአብ ጋር አንድ ሲሆን በሰውነቱ ደግሞ ከሰዎች ጋር አንድ ሆኗል ስለዚህም ዳግማዊ አዳም ተብሏል ምክን ያቱም እርሱ የአዳምን ሥጋና ነፍስ የተዋሐደ ፍጹም ኣምላክ ነውና የክርስቶስ ዳግመኛ መምጣት ታላቁ ፍርድ መቼ እንደሚሆን በማን ኛውም ክፍለ ዘመን የሚኖር ትውልድ ሁሉ ሊያውቀው አይችልም ሆኖም በአንዳንድ ሀገርና ዘመን የነበሩና ዛሬም ያሉ ሐሰተኞች ነቢያት ክርስቶስ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይመማኖትና ክርስቲያናዊ ሕይወት የሚመጣበትን ቀን ወስነው በሐሰት በመናገራቸው ብዙ ወገኖች በችግር ውስጥ እንደ ወደቁ እንሰማለን በሐዋርያት ዘመን የነበሩ የተሰሎንቄ ሰዎችም ዳግም ምጽአት በዘመናቸው እንደሚፈጸም በማሰብ ተሸብረው ነበር ሐዋርያው ውሎስ ግን አእምሯቸው እንዳይታወክ የሚከተሉትን የምክር ቃላት ጽፎላቸዋል ወንድሞች ሆይ ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣትና ወደ እርሱ ስለ መሰብሰባችን በመንፈስ ወይም በቃል ወይም ከእኛ እንደሚመጣ በመልእክት የጌታ ቀን ደርሷል ብላችሁ ከአእምሯችሁ ቶሎ እንዳትናወጡ እንዳትደነግጡም እንለምኖችኋለን ማንም በማናቸውም መንገድ አያስታችሁ ክህደቱ አስቀድሞ ሳይመጣና የአመዕ ሰው እርሱም የጥፋት ልጅ ሳይገለጥ አ ይደርስምና እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ አዋጅ እየነገረ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እስኪቀመጥ ድረስ አምላክ ከተባለው ሁሉ ሰዎችም ከሚያመልኩት ሁሉ በላይ ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርገው ተቃዋሚ እርሱ ነው የዓመዕ ምሥጢር አሁን ይሠራልና ብቻ ከመንገድ እስኪወገድ ድረስ አሁን የሚከለክል አለ በዚያን ጊዜ ጌታ ኢየሱስ በአፉ መንፈስ የሚያጠፋው ሲመጣም በመገለጡ የሚሽረው ዓመፀኛ ይገለጣል ይድኑ ዘንድ የእውነትን ፍቅር ስላልተቀበሉ ለሚጠፋየእርሱ የዓመፀኛው መምጣት በተአምራት ሁሉና በምልክቶች በሐሰተቅኛ ችም በዓመጽም መታለል ሁሉ እንደ ሰይጣን አ ሠራር ነው ተሰሎ እንግዲህ በዚህ ቃል መሠረት ሐዋርያው እንዳስተማረንና እንደ መከረን ስለ ጌታ ቀን መድረስ ሳንደናገጥ ራሳችንን በእውነትና በመልካም ሥራ ኣዘጋጅተን እንድንኖር ያስፈልገናል ምክንያቱም ከላይ እንደ ተጠቀሰው እንደ ሰይጣን ሥራ የረቀቀው የዓመፅ ምሥጢር ኣሁን በሥራ ላይ ስለሆነ በሐ ሰት ምልክቶችና ድንቆች ሊያስተን እየተዘጋጀና ብዙዎችንም ከእውነተኛው መንገድ እያወጣቸው በመሆኑ ነው ስለዚህ በሚያባብለው በሰይጣን ሽንገላ ሳን ታለልና ከዓመፀኞችም የስውር ሥራ ሳንተባበር እንደ ጌታ ቀን የሚያስፈራውን ና በድንገትም የሚመጣውን ዕለተ ሞታችንን እያሰብን በእውነተኛው ሃይ ማኖትና በጉ ምግባር ጸንተን ለመገኘት ዘወትር ተግተን መጸለይ ይኖርብናል ሄታ ፅማዎ መፇሃሃፇሃሥታ ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም ተብሎ በአንቀጸ ሃይማኖት የተገለጸው ቃል የክርስቶስን ዘላለማዊ መንግሥት የሜያመለክት ነው ሥጋ ለብሶ በዕ ለተ ዓርብ መሥዋዕት ሆኖ በደሙ ያዳናቸውን የሰውን ልጆች ሁሉ ከሰይጣን ግዛት አውጥቶ ለእግዚአብሔር መንግሥት እንዲገዙ አድርጓቸዋል ከአባቱም ጋር የሰውን ልጆች በማስታረቅ ለአባቱ ተገዢዎች እንዲሆኑ ሰጥቷቸዋል በዕ ለተ ዓርብ ከሲኦል ያወጣቸውን ነፍሳት ሁሉ ለመንግሥተ እግዚአብሔር የተጠበቁ ሆነው እንዲቆዩ ከገነት አኑሯቸዋል ከዚያም በኋላ እስከ ምጽአት ድረስ በክርስቶስ አማካኝነት የዳኑት ሁሉ የአባቱ ቡሩካን ተብለው ለአባቱ የተጠበቁ ይሆናሉ በመጨረሻም በጌታ አገዛዝ ሥር የሆኑትን በእርሱ መን ግሥት የሚተዳደሩትን ሁሉ ማለት ተገዢዎቹንም ግዛቱንም ለአባቱ ይሰጣል ይህም ከአብ የተላከበትን ሰው የሆነበትን ዓላማ ከግቡ መድረሱንና የዕለተ ዓ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛጣናትና ክርስቲያናዊ ሕፀዐት ርቡም ተልእኮ ፍጻሜ ማግኘቱን ያስረዳናል ወልድ ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ የመጨረሻውን ጠላት ሞትን ደምስሶ ከአበቃ በኋላ በመጨረሻ እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ የራሱ የሆነውን ሁሉ ለአባቱ ያስገዛል እርሱም ከአባቱ ጋር በአንድነት ይገዛል ለመን ግሥቱም ፍጻሜ የለውም ተብሉ እንደ ተጻፈ ወልድ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይገዛል ፍርድንና ግዛትን አብ ለልጄ ሰጥቷልና ኢሷ ዮሒ ስለዚህ ነው ሃመጨረሻውን ነገር በተመለከተ ስለ ክርስቶስ እንዲህ ተብሉ የተጻፈው በኋላም መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ እሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዚ ፍዳሜ ይሆናል ጠላቶቹን ሁሉ ከአግሩ በታች አሰኪያደርግ ድረሰ ሊነግሥ ይገበዋልና የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቷልና ነገር ግን ሁሉ ተገዝቷል ሲል ሁሉን ካሰገዛለት በቀር መሆ ኑ ግልጥ ነው ሁሉ ከተዝለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል ኛቆሮ ክርስቶስ ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል የተባለው መገዛቱ ለማን እንደሆነ» መቼ እንደ ሆነ።