Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ት ርራ ረ ሩኘህ እጅዎ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ አንቀጽ መመሪያውን ስለማሻሻል ይህ መመሪያ ከመስከረም ቀን ዓም ጀምሮ የፀና ይሆናል።
ከፎዞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ መመሪያ ቁጥር ሳከትሚ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መስከረም ዓም አዲስ አበባ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ መግቢያ ትምህርት ለሀገር ብልፅግና ቁልፍ መሣሪያ ነው በዚህም ባለፉት ሶስት የኢንዱስትሪ አብዮቶች የሰው ልጆችን ኑሮ በማዘመንና በማቅለል ዓለም ወደ ደረሰበት ደረጃ ያሸጋገረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ዓለማችን ሰው ሰራሽ ብልህነትንና ናኖ ቴክኖሎጂን እየተገበረች ባለችበት በአራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ላይም የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል በመሆኑም ዓለም የደረሰበትን የሳይስንስና ቴክኖሎጂ ጥበብ በመጠቀም የህብረተሰብን ኑሮ ማሻሻል እንዲቻል በዕውቀትና በክህሎት የበለጸገ ዜጋ ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጆች ክብርና እና ብልጽግና ቅድሚያ የሚሰጥ በመልካም ስነ ምግባር የዳበረ ትውልድ ለማፍራት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያደርጉትን ጥረት መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው እናት ሀገራቸውና ቤተሰቦቻቸው የጣሉባቸውን ኃላፊነት በመገንዘብ ዝርዝር መብትና ግዴታቸውን አውቀው የግልና የጋራ ኃላፊነታቸውን በመወጣት ለሌሎች ወጣቶች መልካም አርዓያ እንዲሆኑ ለማስቻል ለተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመተሳሰብ የመከባበር የመቻቻልና በጋራ የመኖር ጥበብ ሥልጠና ማዕከል እንዲሆኑ ለማስቻል በተማሪዎች ላይ የስነ ልቦናም ይሁን አካላዊ ጉዳት እንዳይደርስባቸው ለመከላከል እንዲሁም ህጋዊና ፍትኃዊ የዲስፕሊን ጥሰት እርምጃ አወሳሰድ ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የተቋሙን ህግ የአካባቢውን ማህበረሰብ እሴቶች እና የሌሎችን ሰብኣዊና ዴሞክረሲያዊ መብቶችን እንዲያውቁ እንዲያከብሩ እና እንዲያስከብሩ ለማስቻል ሰላማዊ የመማር ማስተማርን ዛደትን ለማረጋገጥና ለማስቀጠል እንዲሁም መልካም አስተዳደርን ለማስፈን እንዲያግዝ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ወጥ የሆነ መመሪያና አተገባበር እንዲኖር ማድረግ በማስፈለጉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይህንን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ አውጥቷል ዕፐብሊ መ መፍ ከር ጨፍ ዒኾ ዴ« ትዮጵያ ፌ ኮንስና ክፍ ነ ጻዛ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ክፍል አንድ ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ አጭር ርዕስ ይህ መመሪያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል አንቀጽ ትርጓሜ የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ መሰረት ኒቨርሲቲ ማለት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የተቋቋመ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ነው ሴኔት ማለት በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት የተቋቋመና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ አካደሚክ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጭ አካል ነው ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ማለት በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ዩኒቨርሲቲውን በበላይነት እንዲመራ የተሾመ ነው አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ማለት በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት የተሾመና የዩኒቨርሲቲውን አካዳሚያዊ ጉዳዮች የሚመራ ነው የአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ማለት በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት የተሾመና የዩኒቨርሲቲውን አስተዳደራዊ ጉዳዮች የሚመራ ነው የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ማለት የዩኒቨርሲቷውን ተማሪዎች ሕብረት እንዲመራ በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የተመረጠ ተማሪ ነው ተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር ማለት በግቢው ለሚገኙ ተማሪዎች መሠረታዊ አገልግሎቶችን የሚሰጥ የሚያስተባብርና የሚያስተዳድር አካል ነው ተማሪ ማለት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በመደበኛ አና መደበኛ ባልሆኑ የትምህርት መርዛ ግብሮች ተመዝግቦ በመማር ወይም አጭር ስልጠና በመውሰድ ላይ ያለ ነው ዕጩ ተመራቂ ማለት ለመመረቅ የሚያስችሉ ሁሉንም ቅድመ ሁኔታዎች አሟልቶ የምረቃ ስነስርዓት እስኪከናወንና የትምህርት ማስረጃ ተሰጥቶት አስኪወጣ ያለ ነው የተማሪዎች የዲሲፕሊን ኮሚቴ ማለት በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የሚቋቋም ሆኖ በዲሲፕሊን ጥፋት የሚከሰስን ተማሪ ጉዳይን በዚህ የዲስፕሊን መመሪያ መሠረት እየመረመረ ጥፋቱን የሚመጥን የውሳኔ ፃሳብ ለአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት የሚያቀርብ አካል ነው አዋጅ ማለት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ቁጥር እና የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር ማለት ነው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ማህበረሰብ ማለት በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ና ከተገለጸው በተጨማሪ ተማሪዎችን እንዲሁም በግቢ ውስጥ የሚገኝን ከተቋሙ ጋር ግንኙነት ያለውን ማንኛውንም ሰው ይጨምራል ስነ ምግባር ማለት ማንኛውም በተቋሙ ወይም በተቋሙ ማህበረሰብ አባላት ወይም ከተቋሙ ውጭ ባለ ማህበረሰብ ላይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳርፍ የሚቸል ባህሪይ ሆኖ በማንኛውም ሁኔታ ሲገለጽ የሚችል ነው የተማሪዎች ህብረት ማለት በዩኒቨርሲቲው ወይም በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ወይም በሀገር አቀፍ የተማሪዎች ህብረት በሚወጣ ህግ መሠረት የተቋቋመ ገፅ ሀርቅ የከፍ ተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕ ሊን መመሪያ የተማሪዎች ክበብ ማለት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የግል ችሎታቸውን ለሌሎች በማካፈልና ከሌሎችም ለመማር የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ ለማገዝና ለማስተማር እንዲሁም ችግሮችን በጋራ ለመፍታት በተማሪዎች ፍላጎት የተቋቋመ የተጓዳኝ ትምህርት አካል ሆኖ በዩኒቨርሲቲው ዕውቅና ያገኘ ማለት ነው ማህበራዊ አገልግሎት ማለት ተማሪው በጥፋቱ የተነሳ የሚወሰንበት ቅጣት ሆኖ ተማሪው ያለ ክፍያ በተመደበበት በታ የሚሠራው የጉልበት ወይም የአዕምሮ ስራ ነው የዩኒቨርሲቲው ሀብት ማለት በዩኒቨርሲቲው ባለቤትነት ወይም በአደራ የተያዙ የተመዘገቡ ንብረቶችን ያጠቃልላል የዲሲኘሊን ጥፋት ማለት በዚህ መመሪያ ወይም በሌሎች አግባብነት ባላቸው ህጐች የተከለከለ ድርጊት መፈፀም ወይም መተባበር ወይም ሲፈጸም እያዩ በቸልተኝነት ማለፍ ነው የዲስፕሊን መመሪያ ማለት በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የወጣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስኘሊን መመሪያ ነው አነስተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች የሚባሉት ለዲስፕሊን ኮሚቴ ማቅረብ ሳያስፈልግ በዚህ መመሪያ መሠረት ኃላፊነት በተሰጠው አካል የምክር የቃል ወይም የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የሚያሰጡ የዲስፕሊን ጥፋቶች ናቸው ቀላል የዲስፕሊን ጥፋቶች የሚባሉት ከጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እስከ ከባድ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና እንደአስፈላጊነቱ ማህበራዊ አገልግሎት በመከጠት የሚያስቀጡ ዲስፕሊን ጥፋቶች ናቸው መካከለኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች ከአንድ ወሰነ ትምህርት እስከ ሁለት ዓመት የሚያስቀጡ ከትምህር ገበታ የሚያሳግዱ የዲስፕሊን ጥፋቶች ናቸው ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች የሚባሉት ከሁለት ዓመት እስከ ሶስት ዓመት የሚያስቀጡ ከትምህርት ገበታ የሚያሳግዱ የዲስፕሊን ጥፋቶች ናቸው በባጣም ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች የሚባሉት ከዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርነዛ ግብር ሙሉ በሙሉ መሰናበትን የሚያስከትሉ የዲስፕሊን ጥፋቶች ናቸው አንቀጽ የጾታ አገላለጽ በዚህ መመሪያ ውስጥ የቃሉ አግባብ ካላስገደደ በስተቀር በወንድ ፆታ የተገለፀው የሴትንም ፆታ ይጨምራል አንቀጽ የተፈፃሚነት ወሰን ይህ መመሪያ በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ባሉ በተለያዩ የትምህርት መርዛ ግብሮችና የቅበላ ዓይነቶች ተመዝግበው ትምህርታቸውን በሚከታተሉ ተማሪዎችና ዕጩ ተመራቂዎች ላይ ተፈዓሚ ይሆናል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ክፍል ሁለት መብቶችና ግዴታዎች በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር በአንቀጽ ና የተዘረዘሩትን እንዳሉ ሆነው በተጨማሪ የተማሪዎች መብቶችና ግዴታዎች በዚህ ክፍል ቀርበዋል አንቀጽ የተማሪዎች መብቶች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሴኔት ባወጣው የትምህርት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት በነጻነት የመማር የመጠየቅ የመመራመር የመረዳዳት የማወቅ ሳይንሳዊና ጥበባዊ ክህሎትን የማሳደግ ልቆ መገኘት በመማሪያ ክፍል በዩኒቨርሲቲ ግቢና በህብረተሰቡ ውስጥ ለመማር አመቺ ሁኔታን የማግኘትና የመጠቀም በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ህገመንግስታዊና ሰብዓዊ መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ የመኖር በዩኒቨርሲቲ ጉዳዮች ላይ በህጋዊና በሰላማዊ አግባብ አቋማቸውን በነጻነት የማራመድ ማንኛውንም አይነት አድሎ ወይም ትንኮሳ እንዳይደርስባቸው ህጋዊ ከለላን የማግኘት በማንኛውም የመምህርና የተማሪ ግንኙነት የፍትህና ፍትሃዊነት ተጠቃሚ የመሆንና ለመማር የሚያነሳሳ መልካም ተቋማዊ ድባብን የማግኘት ስለአካዳሚያዊ ብቃታቸው በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ በተደነገጉ መርሆዎችና በዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ መመዘኛዎች መሰረት የመመዘን ኢፍትኃዊ ምዘና ሲፈጸም ቅሬታን በዩኒቨርሲቲው ስርዓት መሠረት በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ የማቅረብና ፍትሕን የማግኘት ግልጽነት ባለው ስርዓት መሠረት የመምህራንንና ሌሎች አካዳሚክ ሰራተኞችን የስራ አፈጻጸም መሙላትና የአፈጻጸም ግምገማው ላይ በመሳተፍ አስተያየት የመስጠት በትምህርት ማህደራቸው ዉስጥ የሚቀመጡ መረጃዎች በሚስጢር ስለሚጠበቁበትና ለሌላ ወገን ስለሚገለጹበት ሁኔታ የሚወስን አስማማኝ ስርዓት ተጠቃሚ የመሆን የተማሪው የጋራ ጥቅሞችን በህጋዊ መንገድ እንዲጠበቁ ለማስቻል አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቋቋመና የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች በሙሉ በአባልነት በሚያቅፈው የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት አባል የመሆን በዩኒቨርሲቲው ደንብና ስርዓት መሠረት በግልም ሆነ በማህበራቸዉ አማካይነት በዩኒቨርሲቲው መገልገያዎች የመጠቀም በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ድንጋጌዎችና የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ በሚያወጣቸው መመሪያዎች መሠረት በማህበራቸው ወይም በተወካዮቻቸው አማካኝነት በተለያዩ የዩኒቨርሲቲው አካደምያዊና አስተዳደራዊ ስብሰባዎች ላይ የመሳተፍ የፈተና ውጤትን በወቅቱ የማየት ቅሬታ ካለ የማቅረብ የፈተና ውጤት ዐ ክፀቨ በወቅቱ የመቀበልና አስፈላጊ የሆኑ ማስረጃዎች በማቅረብ አግባብነት ያለው የትምህርት ማስረጃ በጊዜ የማግኘት የየሴሚስተሩን የመጨረሻ የፈተና ፕሮግራም በቂ በሆነ ጊዜ ቢያንስ ከአንድ ሳምንት በፊት የማወቅ ማንኛውም መደበኛ ተማሪ የወጭ መጋራት ውል ከፈረመ ወይም ለአገልግሎቱ የሚገባውን ክፍያ በቅድሚያ እስከ ፈፀመ ድረስ ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የምግብ የመኝታ የህክምናና የመዝናኛ አገልግሎቶችን የማግኘት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕ ሊን መመሪያ ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር ለሚፈጠሩ ማንኛውም የዲሲፕሊን ግድፈቶች አለመግባባቶች አግባብነት ያለው ፍትህ የማግኘት እና በተገቢው አካል የመዳኘት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚቋቋሙ የተማሪዎች ክበባትና ሌሎች አግባብነት ባላቸው አደረጃጀቶች ለምሳሌ የመኝታ ቤት የመኖሪያ ሕንፃባ የዲስኘሊን የመዝናኛ የምግብ ቤት የፀረኤድስ የጤና የአካባቢ የስፖርትና የመዝናኛ ወዘተ ውስጥ በአመራርነት ሆነ በአባልነት የመሳተፍ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጡ አገልግሎቶች በእኩልነትና በፍትፃዊነት የማግኘት በዩኒቨርሲቲው ህገ ደንብ ዐከዘበ የተካተቱትን መብቶች በአግባቡ የመጠቀም በጥፋተኝነት በሚከሰሱበት ጊዜ የተከሰሱበትን ወይም የተጠረጠሩበትን ጉዳይ በተመለከተ የበኩላቸውን ማስረጃና ክርክር የማቅረብ በአካዳሚክና በአስተዳደራዊ ነክ ጉዳዩች ዙሪያ በሰላማዊ ሁኔታ የመወያየትና ሐሳብ የመስጠት ብሎም ፓናል ውይይት የማዘጋጀት በሥራቸውና በችሎታቸው መሰረት ያለ ምንም አድልዎ የመገምገምና የግምገማ ውጤታቸውን የማወቅ ቅሬታ ካላቸውም ስርአትን ተከትሎ የፈተና ወረቀቶቻቸውና የተገመገሙባቸው ስራዎቻቸው እንደገና እንዲታይላቸው የማመልከት ውጤቱንም የማወቅ በዩኒቨርሲቲው ህገ ደንብ ከበ መሰረት በማንኛውም የመማር ማስተማርና አገልግሎት በሚሰጥበት መስክ በብሄር በጾታ በሃይማኖት በፖለቲካ ወይም በሌላ ወገንተኝነት ምክንያት አድልዎ የማይደረግባቸው መሆነን መረዳት ከተደረገባቸውም ለሚመለከተው የአመራር አካል ቅሬታቸውን የማቅረብና ምላሽ የማግኘት የምግብ አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲው የማይፈልጉ ተማሪዎች ማመልከቻ አቅርበው የሚመለከተው አካል ሲፈቅድ በወጪ መጋራት ደንብ መሰረት በወር ለምግብ የተበጀተውን ገንዘብ የመውሰድ መብት ቤተ ሙከራዎችና ወርክሾፖች አንዲሁም ሌሎች ትምርታቸውን ሊያግዙ የሚችሉ የዩኒቨርሲቲውን ወይም የሌሎች ተቋማትን በሚመለከትው አካል ክትትል የመጠቀም መብቶች አሏቸው አንቀጽ የተማሪዎች አጠቃላይ ግዴታዎች ትምህርት ይጀመራል በተባለው የጊዜ ገደብ በዩኒቨርሲቲው በአካል ተገኝቶ የመመዝገብና አስፈላጊውን ፎርማሊቲዎች አሟልቶ ትምህር የመጀመር በክፍል የመገኘትና ትምህርቱን በሚገባ የመከታተል የከፍተኛ ትምህርት ዓላማዎችንና የዩኒቨርሲቲውን መሪ እሴቶች የማወቅና የማራመድ አግባብነት ያላቸውን የሀገሪቱን ህጎች የዩኒቨርሲቲውን የተማሪዎች ዲስፕሊን መመሪያ የተቋሙን የሴኔት ደንብ እንደዚሁም ሌሎች ተፈፃሚነት ያላቸውን ህጎች የማወቅ የማክበርና የማስከበር በነሱም የመመራት ከማንኛውም ማህበረሰብ ጋር በሚኖረው ግንኙነት ሕገመንግስታዊ መብቶቻቸውን የማክበር የግልም ሆነ የጋራ የተማሪዎች ጥቅም አደጋ ላይ በሚወድቅበት ጊዜ ፍጹም ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ቅሬታን በማሰማት በጋራ መፍትሄ የመሻት ኛን የጋራም ይሁን የግል መገልገያ ንብረት በጥንቃቄ የመያዝና ምዝጅዓ ተብሎ ወይም በቸልተኝነት ምክንያት በዩኒቨርሲቲው ንብረት ላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ የመሆን እንደዚሁም የደረሰውን ጉዳት የመተካት ጥፋት ያደረሰውን አካል የማጋለጥ ዩኒቨርሲቲው ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች መከፈል የሚገባውን ክፍያ የመፈፀም ሁልጊዜ የመገልገያየመታወቂያ ካርድ መያዝና ለሌላ አካል አሳልፎ አለመስጠትና በሚመለከተው አካል ሲጠየቁ የማሳየት በተመዘገቡበት የትምህርት መስክ የተቀመጡ የብቃት መመዘኛዎችን ማሟላት የላቦራቶሪ ሪፖርቶችን እና ሌሎች በመምራን የተሰጡ ሥራዎችን በወቅቱ አጠናቆ ማሰረከብ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር ለእያንዳንዱ የትምህርት ኮርስ ዓይነት በሚወጣው ኘሮግራም መሰረት በሌክቸር በላቦራቶሪ በወርክሾኘና በመስክ በመገኘት ትምህርቱ የሚጠይቀውን ተግባራትን የማከናወን በዩኒቨርሲቲው የተደነገገውን የምሽት መግቢያና መውጫ ሰዓት ማክበር ማንኛውንም መምህር የአስተዳደር ሰራተኛ እንዲሁም የመማር ማስተማርንና የአስተዳደር ሂደቱን የመምራትና የመቆጣጠር ኃላፊነት ያለውን አካል የማክበር ሰልፍ ባለበት ቦታ ሁሉ ሰልፍን ጠብቆ መገልገል በማንኛውም ጊዜ ግቢውን ሲለቁ የተረከቡትን ንብረት በአግባቡ ቆጥሮ ማስረከብ ክሊራንስ በማውጣት ግቢውን በወቅቱ መልቀቅ ሉስ ከሚያስይዙ ጫት ሲጋራ አልኮል ሺሻና የመሳሰሉት ጎጂ ልማዶች ራስን መጠበቅ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የወጪ መጋራት ደንብ መሰረት ለትምህርትና ለአገልግሎት ተገቢውን ክፍያ መክፈል ወይም የወጪ መጋራትን ውል መፈረም ከዩኒቨርሲቲው ካምፓስ ውጪ ካለው ማህበረሰብ ጋር በሚኖረው ግንኙነት በመልካም ስነምግባር አርአያ መሆን የሌላውን ባህል ቋንቋ ዛይማኖት ወዘተ ማክበርና መጠበቅ ከማንኛውም ሕጉወወጥና ከስነምግባር ውጭ ከሆኑ ተግባራት የመቆጠብ ለምሳሌ ከስርቆት አላግባብ በመጮህ ሌላውን ከማወክ ለሕገወጥ ተግባር ሌሎችን ከማነሳሳት ሱስ ከሚያስይዙ ጫት ሲጋራ አልኮል ሺሻና የመሳሰሉት ጎጂ ልማዶች ወ ቬተ ራስንና ሌሎችን የመጠበቅ አንድ ተማሪ በተለያዩ ምክንያቶች መባረሩን ሲያውቅ ሰበብ አስባበብ ፈልጎ ሌላውን ተማሪ ይዞ ለመጥፋት ያልሆኑ ጥያቄዎችን ማንሳት ሌሎችንም ቀስቅሶ ረብሻ ለመፍጠር መሞክር በማንኛውም ምክንያት ከሌሎች ጋር መጣላትና የመሳሰሉትን ችግሮች ስለሚፈጥር እንደዚህ ዓይነት ተማሪዎችን ለሚመለከተው አካል ጥቆማ በመስጠት በጊዜ መፍትፄ እንዲፈለግላቸው የማድረግ ማንኛውም ተማሪ ከዶርሚተሪው ውጭ ፄዶ ያለመተኛት ሌላ ተማሪም አስደርቦ አለመገኘት ያለፈቃድ የመኝታ ክፍል አለመቀያየር ጀበመኝታ ቤት ምንም ዓይነት ተቀጣጣይ ነገሮችን ያለመያዝ ምግብ ማብሰልና ካውያ አለመጠቀም እና ምንም አይነት ሰው ሊጎዳ የሚችል መሳሪያ ይዞ አለመገኘት በሁለት ተማሪዎች መካከል የሚነሱ ግላዊ ጥሎችን ወደ ብሔርና ፃይማኖት በመለወጥ ግጭት ውስጥ አለመግባት የሚሰጡ የትምህርት የታ ለቻዩ ሥራዎችን በራስ ጥረት መሥራት የሌላ ሰው ሥራ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ክፍል ሶስት የተከለከሉ ተግባራት አንቀጽ ከላይ በአንቀጽ የተጠቀሱ ግዴታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በአጠቃላይ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የተከለከሉ ተግባራት በማንኛውም ሁኔታ በተቃራኒ ጾታ ላይ በደል ወይም ጾታዊ ትንኮሳ መፈፀም በግቢ ውስጥ በቡድን ሆኖ ማንኛውንም ዓይነት ኃይማኖታዊም ይሁን ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ሃይማኖትን ብሔርን ባህልንና ቋንቋን የሚያንቋሽሽ ማንኛውንም ንግግር ማድረግ መጻፍ ወይም ድርጊት መፈጸም ፖለቲካዊና ኃይማታዊ መልዕክት ያላቸውን አልባሳት ቅርጻ ቅርጾች ጌጣጌጦች የተለያዩ ቦርሳዎችና ፅቃ መያዣዎችን መጠቀም ወደ ግቢ ውስጥ ማንኛውም ዓይነት አደንዘዥ እፅ ማዛወር ማብቀልመትከል ይዞ ወይም ተጠቅሞ ወይም አልኮል ጠጥቶ ወይም ሰክሮ መግባት የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ሰራተኞችን በምንም ሁኔታ መሳደብ መዝለፍ ማንጓጠጥ ማስፈራራትና መዛት ያልተገባና ፀያፍ ንግግር መናገር የሌሎች ተማሪዎችን ማህበራዊ ኑሮ የሚያውኩ ድርጊቶችንና ንግግሮችን መፈፀም መረበሽ ቁማር መጫወት በግቢው ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን ፀብ ማንሳት ወይም መደባደብ ወይም በነዚህ መሠል ተግባራ መተባበር ማንኛውንም የስርቆት ተግባር መፈፀም አደዴጋ የሚያደርስ ማንኛውንም ነገር ለምሳሌ ስለት ያለው መሳሪያ መርዝ ይዞ ወደ ግቢ ወይም አግልግሎት መስጫ ቦታዎች መግባት በመማሪያ ክፍሎች እና በምግብ ቤት አዳራሾች እንዲሁም በመዝናኛና በክሊኒክ ቦታዎች በምንም መልኩ ያልተገባ ጩኸት ጠብ ግርግር መፍጠር መረበሽ ከመፀዳጃ ቤቶች ውጭ መፀዳዳት በማንኛውም አካል የሚለጠፉ ህጋዊ ማስታወቂያዎችን መገንጠል መቅደድና መሰረዝ በአገልግሎት ዙሪያ ቅሬታ ሲኖር ሰላማዊ እና ሕጋዊ መንገድን ተከትሎ መጠየቅ እንጂ አመፅ ማንሳት ማስነሳትና መተባበር በማኛውም የዩኒቨርሲቲው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ ፀጉርን በተመሰከተ ለወንዶች ከ ሴሜ ርዝመት ያልበለጠ ሆኖ ምንም ዓይነት ቅርጽ የሌለውና የተለየ ቀለም መቀባት ለሴቶች በአግባቡ የተሠራና ያልተንጨባረረ ሆኖ የተለየ ቀለም መቀባት አለባበስን በተመለከተ ለወንዶች የተቦጫጨቀ የተቀደደ ገላን የሚያሳይ ልብስ መልበስ ሱሪን ዝቅ በማድረግ የውስጥ ቁምጣ ማሳየትሌላን ሰው ሊረብሽ የሚችል ከፍተኛ ሽታ ያለው ሽቶ ዶዲራንትና ሌሎችም መጠቀም ከፍ ያለ ድምጽ የሚያወጡ ጫማዎችን መጫማት ለሴቶች የተቦጫጨቀ የተቀደደ ገላን የሚያሳይ ልብስ መልበስበማድረግ የውስጥ ቁምጣ ማሳየት ከጉልበት በላይ ያጠረ ቀሚስ መልበስ ሌላን ሰው ሮክር ቦፅ የር ኺዊሃ ን ይዴረጩጠ ኣዲ ዳኑ «ር ነሃ ም አላህም ሪ አ ሃሀ ናዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ሊረብሽ የሚችል ከፍተኛ ሽታ ያለው ሽቶ ዶዲራንትና ሌሎችም ኮስሞትክስ መጠቀም ከፍ ያለ ድምጽ የሚያወጡ ጫማዎችን መጫማት በግቢ ውስጥ ወሲብ መፈጸም ወይም ግቢ ውስጥ መውለድ ለሌላ ሰው ሊሰሙ የሚችሉ ድምጾችን በሞባይል መጠቀም ባልተፈቀደ በር ወይም አጥር ዘሎ መግባትና መውጣት የወል የጋራ መገልግያዎችን የግል ማድረግ በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ በወንጀለነት የተፈረጁ ድርጊቶችን መፈፀም አንቀጽ በተማሪዎች መኝታ ቤት የተከለከሉ የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆነ ወይም የተባረረ ተማሪ በመኝታ ቤት ማሳደር ማኖር ተደራራቢ አልጋዎችን መገንጠል ፍራሽ መሬት ላይ አውርዶ መተኛት የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጠልፎ ለሌላ አገልግሎት ማዋል በተቃራኒ ጾታ መኝታ ክፍል መግባት ማስገባት በህመም ምክንያት ካልተፈቀደ በስተቀር ምግቦችን ወደመኝታ ክፍል ይዞ መግባት የመኝታ ቤት ቁልፍ በሚመለከተው አካል ሳይፈቀድ ማስቀረጽ በአንድ አልጋ ላይ ከአንድ በላይ ሆኖ መቀመጥ መተኛት በመስኮት መውጣት ወይም መግባት ሽ በማንኛውም ጊዜ በመኝታ ክፍል ውስጥና አካባቢ ጫጫታና ረብሻ መፍጠር የሚረብሽ ድምጽ ሙዚቃ የሞባል መጥሪያ ማሰማት የሽንትና ሻወር ቤቶች የልብስና እጅ መታጠቢያ ገንዳዎችን ማስረጊያ ቀዳዳዎቹን አላስፈላጊ የሆኑ ፕላስቲክ ድንጋይ ጸጉር ጨርቅና ሞደስ ወዘተ ነገሮችን በመክተት እንዲዘጉ ማድረግ መብሳትና መቅደድ በመኝታ ክፍል ውስጥ አልጋን መጋረድ ቴንሽን ቦክስ መስራት ባልታወቀ ሁኔታና ሳይፈቀድ በዶርም ውስጥና አካባቢ ስብሰባ ማድረግና ሰፊ ቁጥር ይዞ በቡድን መንቀሳቀስ በዶርም ውስጥና አካባቢ በቡድን ሆኖ መጸልይ ወይም መስገድ በዶርም ውስጥ ምግብ ማብሰል ሻይና ቡና ማፍላት የመኝታና የፅዳት አገልግሎት ሰራተኞችን ማመናጨቅና መገላመጥ መሳደብ መዝለፍ ስም ማጥፋት ማስፈራራት ከተመደቡበት ዶርም ውጪ ያለፈቃድ መቀየር በሽንት ቤትና ሻወር ቤት ውስጥ ያልተገቡ ፅሑፎችን መጻፍ ወይም መለጠፍ የተመደቡበትን የመኝታ ክፍል ያለ ፈቃድ መቀየር ባልተመደቡበት መኝታ ክፍል ውስጥ ተዳብሎ መተኛት ወይም አዳብሎ ማስተኛት በግድግዳዎች መዝጊያዎች መስኮቶችና ቁም ሳጥኖች ላይ ማንኛውም ጽሁፍ መፃፍ ስዕል መሳልመለጠፍ ሚስማር መትከል መምታት በመኝታ ቤት ውስጥና አካባቢ ጫት ስጋራ አልኮሆል መጠጦችንና ሌሎች አደንዛዥ እፆችን ይዞ መግባት ወይም ሲጠቀሙ መገኘት የመኝታ ክፍልን በር የራስንም ሆነ የሌሎችን ያለፈቃድ መክፈትመስበር በእጅና ፊት መታጠቢያ ገንዳዎች እንዲሁም በዶርም ውስጥና ኮሊደር ልብስ ማጠብ ወዉመዕቃይወዕኸ ያ ይ ፆ » የ ሚ ኦ ። በግቢ ውስጥ ከፍተኛ ድምጽ ወይም ጩኸት በራስ ድምጽ ወይም በማንኛቸውም የኤልክትሮኒክስ መሣሪያዎች በማስጮህ የአካባቢን ፀጥታን ማደፍረስ በጫማም ይሁን በሌላ መንገድ አና ማስቲካ እያስጮኹ ማኘክ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ የተደነገገን የሰዓት ገደብ አለማክበር ሌሎች መሰል የስነ ምግባር ጥሰቶችን መፈጸም ህህርዮ ጄር ር ኾ አንቀጽ ቀላል የዲስፕሊን ጥፋቶች ከጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እስከ ከባድ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና እንደአስፈላጊነቱ ማህበራዊ አገልግሎት በመስጠት የሚያስቀጡ ዲስፕሊን ጥፋቶችን ያካትታል የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ወይም ከ ያላነሰ ከ ሰዓታት ያልበለጠ ማህበራዊ አገልግሎት የጉልበት ሥራ ወይም በሁለቱም ሊያስቀጡ የሚችሉ የዲስፕሊን ጥፋቶችን ከላይ በአንቀጽ በንዑስ አንቀጽ የተዘረዘሩትን የቃል ማስጠንቀቂያ ወይም ነጻ ማህበራዊ አገልግሎት የሚያሰጡ የዲስፕሊን ጥፋቶች መካከል አንዱን የዲስፕሊን ጥፋት ተፈፅሞ በተወሰደው ቅጣት መሻሻል ሳይታይና ያንኑ ወይም ተመሳሳይ የዲስፕሊን ጥፋት ደግሞ መፈጸም ኋበተራ ምድብ ወቅት የመኝታ ክፍልን መጸዳጃ ቤትን የመኖሪያ ሕንፃ ኮሪዶርን የመኖሪያ ሕንጻ አካባቢን አለማጽዳት የራስን አልጋ አለማንጠፍና የግል ንጽህናን አለመጠበቅ ግለሰቦችን ለተራ ጥል መጋበዝ ማጣላት ነገር መቆስቆስ ማጋጋል ጥል ሲነሳ አለመገላገል ወገን ለይቶ ማበር በነገር ማቆራቆስ ከተፈቀደ ቦታ ውጭ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ቆሻሻ መጣል በደኒቨርሲቲው ተገቢ አካል የተሰጠን ሕጋዊ ትእዛዝ አለማክበር ለጋራ ጤንነት አደገኛ የሆኑ ድርጊቶችን መፈጸም ግድግዳ በሚስማር ወይም በመሰል ነገር መብሳት ያለ ግለሰቡ ወይም ዩኒቨርሲቲው ፈቃድ የግለሰብ ወይም የዩኒቨርሲቲ ኝብረት መጠቀም ን የሌላ ሰው መታወቂያ ወይም የምግብ ካርድ መጠቀም የተማሪዎች አገልግሎት እና የተማሪዎች ህብረት ሳያውቁ በየትኛውም መንገድ ከተማሪዎች ገንዘብ መሰብሰብ የተማሪዎችን ትራንስፖርትና የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በማመቻቸት ሽፋን ለግል ጥቅም ሲባል ተማሪዎችን ከፍተኛ ክፊያ መጠየቅ ወይም እንዲጠየቁ መተባበር በተቋሙ ግቢ ውስጥ ሲጋራ ማጨስ ሌሎች አደንዛዥ ዕጾችን መጠቀም ወይም ይዞ መገኘት ሌሎችም አጭሰው ወይም ይዘው አያዩ ዝም ማለት የጋራ መገልገያዎችን አለአግባብ ለግል ጥቅም ማዋል በማንኛውም መልኩ በድጋሜ መመገብና ለመመገብ መሞከር አጭበርብሮ የገንዘብ ድጋፍ ከዩኒቨርሲቲው ለማግኘት መሞከር ምንም ውክልና ሳይኖር የተማሪዎች ህብረት አባል የክበብ ተጠሪ ነኝ ወዘተ በማለት ሰዎች መረጃ እንዲሰጡት መጠየቅ ወይም ፍቃድ ሳይሰጠው ስራ ለመስራት መሞከር ወይም መስራት ከባድ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና እንደአስፈላጊነቱ ማህበራዊ አገልግሎት በመስጠት የሚያስቀጡ የዲስፕሊን ጥፋቶች ከላይ በአንቀጽ በንኡስ አንቀጽ ከተዘረዘሩት የዲስፕሊን ጥፋቶች መካከል አንዱን ወይም ተመሳሳይ የዲስፕሊን ጥሰት ፈፅሞ በተወሰደው ቅጣት መሻሻል ሳያሳዩ ያንኑ ወይም ተመሳሳይ የዲስፕሊን ጥፋት ደግሞ መፈጸም በግቢው ውስጥ በተለይም በጋራ መገልገያ አካባቢዎች ማለትም በመኝታ በመመገቢያና በመማሪያ ክፍሎች በቤተ መፃዓህፍት በወርክሾፖች በቤተሙከራ ክከሊኒክና በዲኤስቲቪ ወዘተ አካባቢ ያልተገባ ጩኸት ማሰማት ሁከትና ለ ቀናት ከዩኒቨርስቲ ግቢ ውጭ ወጥቶ ካደረ እንዲሁም ለሶስት የአቴንዳንስ ክትትልና ቁጥጥር ቀናት ሪፖርት ካላደረገ በመጠጥ ሀይል ሰክሮ በግቢው ውስጥ ሁከት መፍጠር የአካባቢ ፀጥታን ማደፍረስ በተቃራኒ ፆታ መኝታ ህንፃ ውስጥ ያለ ፈቃድ ገብቶ መገኘት ፍራሽ ወይም ትራስ ወይም የፍራሽ ልብስ ቀዶ መገኘት ባለተፈቀደለት መኝታ ቤት ማደር ወይም የመኝታ ቦታን ያለፈቃድ መቀየር ያልተፈቀደለት ሰው በመኖሪያ ቦታ እንዲኖር እንዲዳበል ወይም እንዲያድር ማድረግ ያለፈቃድ የበሰለ ምግብ ከዳቦ ውጭ ከማንኛውም ቦታ ወደ ዶርም ይዞ ገብቶ ሲጠቀሙ መገኘት ማንኛውንም የዩኒቨርሲቲውን ንብረት በአግባቡ አለመጠቀም ማበላሸት ህጋዊ ባልሆነ መንገድ በአጥር ዘሎ ወይም ሾልኮ መግባትና መውጣት የስብሰባ የኮንሰርትና የፍልም ማስታወቂያዎችን ያለ ተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ጽቤት አውቅናና ፈቃድ መለጠፍ በመኝታ ክፍል ውስጥ ያልተፈቀዱ የኤሌክትሪክ አቃዎችን መጠቀም ለዩኒቨርሲቲው መምህራን ሰራተኞችና ሀላፊዎች ሥራው የሚጠይቀውን አስፈላጊውን ትብብር አለማድረግ በግቢ ውስጥ ሲጋራ ማጨስ ህጋዌዊ ያልሆነ ስብሰባ ወይም በተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር ወይም በዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር ፈቃድ ያላገኘ ትአይንት ማሳየት ወይም ለማሳየት መሞከር የራስን ዛሃይማኖት እምነትና የፖለቲካ አመለካከት ሌሎች እንዲቀበሉ ጫና መፍጠር መረበሽ በመግቢያ በርና በአገልግሎት መስጫዎች የመታወቂያ የመገልገያ ካርድ ሲጠየቅ ለማሣየት ፈቃደኛ አለመሆን ይማኖታዊ በአሎችንና ትዕይንቶችን በግቢው ውስጥ ማካፄድ እንዲካሄዱ መቀስቀስ ማነሳሳት መምራት ፀጉርን በተመሰከተ ለወንዶች ከ ሴሜ ያልበለጠ ሆኖ ምንም ዓይነት ቅርጽ የሌለውና የተለየ ቀለም መቀባት ለሴቶችኹ በአግባቡ የተሠራና ያልተንጨባረረ ሆኖ የተለየ ቀለም መቀባት አለባበስን በተመለከተ ለወንዶች የተቦጫጨቀ የተቀደደ ገላን የሚያሳይ ልብስ መልበስ ሱሪን ዝቅ በማድረግ የውስጥ ቁምጣ ማሳየትሌላን ሰው ሊረብሽ የሚችል ከፍተኛ ሽታ ያለው ሽቶ ዶዲራንትና ሌሎችም መጠቀም ከፍ ያለ ድምጽ የሚያወጡ ጫማዎችን መጫማት ለሴቶች የተቦጫጨቀ የተቀደደ ገላን የሚያሳይ ልብስ መልበስበማድረግ የውስጥ ቁምጣ ማሳየት ከጉልበት በላይ ያጠረ ቀሚስ መልበስ ሌላን ሰው ሊረብሽ የሚችል ከፍተኛ ሽታ ያለው ሽቶ ዶዲራንትና ሌሎችም ኮስሞትክስ መጠቀም ከፍ ያለ ድምጽ የሚያወጡ ጫማዎችን መጫማት ሎች መሰል የስነምግባር ጥፋቶችን መፈፀም ካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲሰፕ ሊን መመሪያ አንቀጽ መካከለኛ ዲስፕሊን ጥፋቶች ከአንድ ወሰነ ትምህርት እስከ ሁለት ዓመት የሚያስቀጡ የዲስፕሊን ጥፋቶች በዚህ ምድብ ይካተታሉ ለአንድ ወሰነ ትምህርት ከትምህርት ገበታ የሚያሳግዱ የዲስፕሊን ጥሰቶች በአንቀጽ በንኡስ አንቀጽ የተጠቀሱት ወይም ተመሳሳይ የዲስፕሊን ጥፋት በድጋሜ ፈጽሞ መገኘት ኋ ፈተና መስረቅ ወይም ፈተና መኮረጅ ወይም ማስኮረጅ የሌላ ሰው ሥራን የራስ አስመስሎ ማቅረብ ሴትም ሆነ ወንድ ተማሪዎችን በንግግር በጽሁፍ በስልክ ወዘተ ማስፈራራት ማስቸገር ማስጨነቅ መሳደብ የተለጠፉ ህጋዊ ማስታወቂያዎችን መገንጠል መቅደድ መደለዝ ወይም ማበላሸት በምንም ይሁን በምንም ሁኔታ ከተማሪ ጋር ጥል መፍጠር ለድብደባ መጋበዝ የዩኒቨርሲቲውን መምህር ሰራተኛ ወይም ሌሎችን መዝለፍ ማንጓጠጥ መሳደብ ለመምታት መጋበዝ ህጋዊ ፍቃድ የሌላቸው ስብሰባዎችንና ምክክሮችን በግቢው ውስጥ ማካሄድ መሳተፍ የራስ መታወቂያ ወይም የመመገቢያ ካርድን ለሌላ አካል አሳልፎ መስጠት በሌላ ተማሪ መታወቂያ ወይም መመገቢያ ርክ አገልግሎት ለማግኘት ማጭበርበር ሲመገቡ መገኘት ለተማሪዎች የትራንስፓርት አገልግሎት ለመስጠት በሚደረገው እንቅስቃሴ በማንኛውም ስም ከተመን በላይ ማስከፈል ለማስከፈል መሞከር ለማስከፈል ማስተባበር መተባበር የአንድን ተማሪ መታወቂያ ወይም የመመገቢያ ካርድ ወይም ሌሎች ንብረቶችን ገንዘብ ወይም ሌሎች ጥቅማ ጥቅም ለማግኘት በቅድመ ሁኔታነት መያዣ ማድረግ በተቋሙ ውስጥ የሚካፄድ አካዳሚያዊ አስተዳደራዊ ማህበራዊ ስፖርታዊ ወይም ሌሎች አንቅስቃሴዎችን መረበሽ ወይም ተገቢ ያልሆነ ጣልቃ ገብነት መፈጸም ከአንድ ዓመት አስከ ሁለት ዓመት የሚያስቀጡ የዲስፕሊን ጥፋቶች በዚህ ምድብ ይካተታሉ ሆን ብሎ የፈተና ወረቀት ሳያስረክብ ይዞ መውጣት የሌላ ተማሪ የታረመም ሆነ ያልታረመ የፈተና ወረቀት ለማጥፋት መሞከር ወይም ማጥፋት ወይም መቅደድ ኋበፈተና ወረቀቱ ላይ ስሙን ቀይሮ እንዲፈተንለት ሌላ ዲፓርትመንት ተማሪ ወይም ተማሪ ያልሆነ ሰው በራሱ ቦታ ማስፈተን አልኮልና ጫት ይዞ መግባት ለመግባት መሞከር መታወቂያና መመገቢያ ካርድ ሳይጠፋበት ጠፋኝ በሚል አመልክቶ ሁለተኛ ለማግኘት መሞከር ወይም አግኝቶ በሁለት ካርድ ሲጠቀም መገኘት በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ የአምልኮ ቦታ መጠየቅ ህንፃዎችን ለአምልኮ መጠቀም በግቢው ውስጥ በቡድን ተሰባስቦ ሐይማኖታዊ ስርዓት ማካሄድ በቤተ መጽሐፍት ወይም በሌሎች ክፍሎች ውስጥ ያሉ መጽሐፍትን ጆርናሎችን ወዘተ ገጽ መቅደድና መገንጠል ወይም መስረቅ መረጃ በሌለበት በአሉባልታ በመሰለኝና ባልታረጋገጠ ወሬ በስብሰባዎች ላይም ይሁን በሌሎች ሁነቶች የዩኒቨርሲቲውን ኃላፊዎች መምህራን የአስተዳደር ሠራተኞች ወይም ሌሎች ተማሪዎችን ማቃለል የፃሰት ንግግሮችን በማድረግ ክብር መንካት ስም ማጥፋትና የመሳሰሉ ድርጊቶችን መፈጽም በክፍል ውስጥ በዶርሚተሪ በቢሮ ወይም በሌላ የዩኒቨርሲቲው ግቢ ክልል ውስጥ በስምምነት ላይ የተመሠረተ የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም ወይም ለመፈፀም መሞከር የተማሪዎችን እንዲሁም የሌሎች አካላትን ንብረት መስረቅ ወይም መዝረፍ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባል ላይ የስነልቦና ጉዳት ማድረስ መሳደብ ማስፈራራት መዝለፍ መረበሽ ማስጨነቅ እንዲሁም አእምሮውን ማህበረሰባዊ ግንኙነቱን ህይወቱን ወይም አእንቅስቃሴውንና የስራ ሞራሉን ሊጐዱ የሚችሉ ዛፃይለ ቃሎችን መናገር በሥራው ላይ እንቅፋት የሚሆኑ ነገሮችን ማድረግ ሳይታመም የታመመ በማስመሰል ከክሊኒክ መድኃኒት አውጥቶ ሲሸጥ ወይም ለሌላ ሰው ሲሰጥ መገኘት መታወቂያ ካርዱን ወይም መመገቢያ ካርዱን የቤተመጽሐፍት መዋሻ ካርድ ወይም ሌላ የግል መሰያውን ለሌላ ተማሪ አሳልፎ በመስጠት ማስጠቀም ወይም ከሌላው ተቀብሎ መጠቀም የሌላ ተማሪ መመገቢያ ካርድ መታወቂያ ወይም ሌላ ዕቃ ሰርቆ ከወሰደ በኋላ እንዲመልስ ሲጠየቅ በገንዘብ ወይም በዓይነት ጥቅም ለማግኘት መደራደር ወይም ይህን ድርጊት ከሚፈጽም ሰው ጋር መተባበር በሆቴሎች በጭፈራ ቤቶች ወይም በሌሎች ቦታዎች በሴተኛ አዳሪነት ተሰማርቶ መገኘት ወይም እነዚህን የሚመስሉ ተግባራትን መፈጸም ወይም ይህን እንዲያደርጉ መገፋፋት እንደአገናኝ ማገልገል ያለግለሰቡ ፈቃድ ምስሉን ወይም ድምጹን በካሜራ ወይም በሞባይል ቀርፆ ለህዝብ ማሳየት ወይም ማሰማት ለማንኛውም ተግባር እንዲውል ማድርግ ለተማሪዎች ህብረት ስራ ማስኬጃ የተበጀተውን ገንዘብ ወይም የተማሪዎች ክበብ በድጋፍ ያገኘውን ወይም ከአባላት የተሰበሰበውን ገንዘብ የፋይናንስ የገቢና ወጭ ስርዓት ባልተከተለ መልኩ ማስኬድ መመዝበር ያለ ተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር እና ያለተማሪዎች ህብረት ፈቃድ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ በተመራቂ ተማሪዎች ኮሚቴም ሆነ በሌሎች ተማሪዎች አነሳሽነት ማንኛውም ተማሪ ብሔራዊም ሆኑ ብሔራዊ ያልሆኑ ሐይማኖታዊም ሆኑ ሐይማኖታዊ ያልሆኑ በአላትን በቡድን ማክበር በተማሪዎች ህብረት አባላት ላይ ሆን ብሎ ማመጽ ችግር መፍጠር ማዋከብ ብሔራቸውን ወይም ሌሎች ማንነታቸውን መሠረት አድርጎ ማጣጣል መስደብ ሌሎች እንዲነሱባቸው መቀስቀስ ችግር ያለባቸውን ለይቶ በህጋዊ መንገድ እንዲነሱ በመረጃ ላይ የተደገፈ ጥያቄ ማቅረብ እንደተጠበቀ ሆኖ በዩኒቨርሲቲ ሰራተኛ ወይም ተማሪ ላይ በማስፈራራት ወይም በመዛት የሆነ ነገር እንዲያደርግ ወይም እንዳያደርግ ማስገደድ አንቀጽ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕ ሊን መመሪያ የዲሲኘሊን ጉዳይ የሚያይ የኮሚቴ አባልን አመልካች ወይም ምስክር ሆኖ የቀረበ ሰውን የተከሳሹን ወይም መከላከያ ምስክሮቹን ማስፈራራትና ውሳኔ እንዳይተላለፍ የማድረግ ሙከራ ማጣራት በትክክልኛ መንገድ እንዳይካሄድ ማድረግ ሐይማኖትን መሠረት በማድረግ ለራሱና ተከታዮቹ ልዩ መመገቢያ አዳራሽና ምግብ መጠየቅ መመገቢያ አዳራሽ ውስጥ ከምግብ በፊትና በኋላ ፀሎት ሲያደርጉ ድምጽ ማሰማት በቡድን ድምጽ እያሰሙ መጸለይ ሌሎችን መረበሽ ሐይማኖትን መሠረት በማድረግ ለራሱና ተከታዮቹ ልዩ የመመገቢያ ሰዓትና ምግብ በመጠየቅ ሁከት አንዲፈጠር ማድረግ በተማሪዎች ህብረት አባልነት ስም ሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም በዩኒቨርሲቲው በሚሰጡ ፈተናዎች ለሌላ ተፈታኝ ተማሪ ወይም አካል ሲፈተን መገኘት የሌሎችን የፖለቲካ የኃይማኖት ብፄር ቋንቋ አመለካከት ባህልና እምነት ማንቋሸሽ ማንኳሰስ የፃይማኖት መጽሐፍት ማበላሸት ማቃጠል የበዓላት ቀናትን አሳብቆ መረበሽ ወዘተ በሌሎች ተማሪዎች ወይም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት ላይ የሞራል ችግር ሊያስከትሉ የሚችሉ ትዕይንቶችን እንቅስቃሴዎችን ፊልሞችንና የመሳሰሉ ነገሮችን ማሳየት ማቀነባበር ወይም ማሰራጨት ሌሎች በዚህ ምድብ ሊካተቱ የሚችሉ የዲስፕሊን ጥፋቶች ተብለው በዩኒቨርሲቲው በጽሑፍ የሚለዩ ጥፋቶች ሺክ ዩ ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች ከሁለት ዓመት እስከ ሶስት ዓመት የሚያስቀጡ ከትምህርት ገበታ የሚያሳግዱ የዲስፕሊን ጥፋቶች በዚህ ምድብ የሚካተቱ ይሆናል የዩኒቨርሲቲውን ህግና ደንብ ለመጣስ የአሰራር ስርአትና የሥራ አመራር ውሳኔ ለመቃዎም ተማሪዎችን ለአድማ ለአመጽና ለረብሻ ማነሳሳት ማስተባበር የፃሰት ወሬ መፍጠርና ማስፋፋት ለህገወጥ ሥራ ህብረት መፍጠር በማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይና በሌላ ቦታ ብጥብጥና ሁከት የሚያስከትል ያልተፈቀዱ ጽሁፎችን መለጠፍ በአግባቡ በመካፄድ ላይ ባለ የዲሲኘሊን ጥፋት ክርክር የመሰማት ዛደት ላይ ጣልቃ መግባትና ማደናቀፍ በስርዓቱ መሠረት ለመዳኘት የሚያመለክቱ ተማሪዎችንና ሠራተኞችን ማደናቀፍ በዲስኘሊን ኮሚቴዎች ላይ ወከባ በመፍጠር በገለልተኝነታቸው ላይ ተፅፅኖ ለመፍጠር መሞከር እንደ ማሪዋና ካናቢስ ሀሽሽ ኮኬይን ወዘተ ያሉ ዕፆችን መጠቀም በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ውስጥም ሆነ ከዚያ ውጭ ይዞ መገኘት ወይም በድብቅ ሲያዘዋውር ወይም ሲሸጥ መገኘት ሀሳቡን በነባነት የመግለጽ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ተማሪው የፖለቲካ ወይም የብሔር ምክንያቶችን በማንሳት ተገቢ ባልሆነ መንገድ ሰዎችን ለአመጽ ማነሳሳት ለመምህርም ሆነ ለሌላ አካል ሆን ብሎ የሌላ ተማሪን የስራ ውጤት መደበቅ ወይም ማጥፋት ገንዘብ ወይም ሌላ ዋጋ የሚያወጣ ነገር በመስጠት ያልተገባ የትምህርት ጥቅም ለማግኘት መሞከር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ዩኒቨርሲቲው በሚያወጣቸው ሕጎች ተገዢ ለመሆነ አለመፈለግ ያለበቂ ምክንያት የትምህት ፕሮግራሞች እንዲቀየሩ አመጽ ማስነሳት ሰላምን ማወክ በተደጋጋሚ እንደማይለወጡ ተነገሮ ለመቀበል ዝግጁ አለመሆን የሚኖርበትን ህንጻ አካባቢ ዶርሚተሪ ኮሪዶር ሽንት ቤትና ሻዎር እንዲያጸዳ ከጓደኞቹ ጋር ተመድቦ በተከታታይ ለሁለት ጊዜ ኃላፊነቱን ለመወጣት እምቢተኛ ሆኖ መገኘት አንቀጽ በጣም ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች ከዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርፃግብር ሙሉ በሙሉ መሰናበትን የሚያስከትሉ የዲስፕሊን ጥፋቶችን እንደሚከተለው ተመልክተዋል ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶቸን ፈጽሞ በተወሰደው እርምጃ መሻሻል ሳያሳይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋት ፈፅሞ መገኘት የሌሎችን ብሔር ወይም ኃይማኖት የሚጐዳ ድርጊት መፈፀም ለምሳሌ መንፈሳዊ መጽሐፍት ስዕሎችና ቅርፃዓቅርፆች ሐይማኖታዊ ምልክቶች እንዲቃጠሱ ወይም ቅርፃቸው እንዲጠፋ ማድረግ ድምጽ ባለው ወይም በሌለው መሣሪያ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ አባል ሆነ ከዩኒቨርሲቲው ውጭ ያሉ የማህበረሰብ አባላትን መጉዳት ወይም ለመጉዳት ሙከራ ማድረግ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ የአካል ጉዳት ወይም ሞት ሊያስከትሉ የ። ዖሂችሉ ስለታማና ተተኳሽ መሳሪያዎች ወይም መርዛማ ነገሮችን ይዞ መገኘት ለመግባት መሞከር አስገድዶ መድፈር ወይም የተቃራኒ ፆታውን የመከላከል አቅም በጉልበት ወይም በስነ ልቦና ጫና በማድከም ፆታዊ ጥቃት ማድረስ ወይም ለማድረስ መሞከር በጉልበት ገፍቶ ወደ ተቃራኒ ፆታ መኝታ ቤት መግባት በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ሆን ብሎ ወይም በቸለልተኛነት ወይም በጥንቃቄ ጉድለት ቃጠሎ ለማስነሳት መሞከር ወይም ማስነሳት በተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ተመዝግቦ መገኘት ፊርማን መኮረጅ ወይም ሰነድን መደለዝ በመሰረዝ ማጭበርበር ለማጭበርበር መሞከር በማስፈራራትና ጉልበት በመጠቀም የሌላ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ንብረት መውሰድ ወይም ለመውሰድ ሙከራ ማካሄድ ዘረፋ መፈፀም ተገቢውን ክፍያ ሳይፈጽም ወይም የወጭ መጋራት ውል ሳይፈርም መማር ወይም የአገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን መሞከር የሌሎች ተማሪዎችን ዓላማና ህይወት በሚያሰናክል ህገወጥ እንቅስቃሴ ላይ ተሰማርቶ መገኘት ለምሳሌ ያልተፈቀዱ የጭፈራ ሥርዓቶችንና በዓላትን በግቢው ውስጥም ሆነ ውጭ ማዘጋጀት ተባባሪ መሆን ለዝሙት ማቃጠር ማሻሻጥ ሀሽሽና ሌሎች አደንዛዥ አጾችን ተማሪዎችም ሆኑ ሌሎች እንዲጠቀሙ ማበረታታት ወዘተ ተመሳሳይ ጾታ ጋር ግንኙንት መፈጸም ያልሆኑ ከባህል ያፈነገጡ ነገሮችን ሲያደርጉ መገኘት የሌላ ተማሪን ቋንቋ ብሔር ሐይማኖት እና ማንነት ማንቋሸሸሽ ተማሪው ባገኘው ውጤት ቅር በመሰኘት በመምህሩና በመምህሩ ቤተሰብ ላይ ጉዳት ለማጅዷስ መሞከር ወይም ማድረስ ታደ የሰሪጋ በሏ ይክርልቤኾ ድ ለያ እ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ በመመገቢያ አዳራሽ አካባቢ ከምግብ ጋር አያይዞ ወይም በየትኛውም ምክንያት ዓመጽ ማስነሳት ወይም ለማስነሳት መሞከር በስራ ላይ ያሉ ስራተኞችን መደባደብ ጐበዝ ተማሪዎችን በጉልበት በማስፈራራት እንዲያሰቀዱ ማስገደድ ፈተና ክፍል ወስጥ ሁከት መፍጠር ሌሎች ከነዚህ ጋር ይመሳሰላሉ ብሎ ዩኒቨርሲቲው የሚጨምራቸው የዲስፕሊን ጥፋቶች አንቀጽ እጩ ምሩቃን የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽመው ሲገኙ የሚወሰዱ እርምጃዎች የመጨረሻውን የመመረቂያ የትምህርት ዓመት ፈተና ተፈትነውና ትምህርታቸውን አጠናቀው ለመመረቅ የተዘጋጁ እጩ ምሩቃን የዩኒቨርሲቲውን ህግ ወይም የስነምግባር ደንቦች በማክበር በኩል ለሌሎች ተማሪዎች አርአያ ሆነው መገኘት ሲገባቸው አልፎ አልፎ ቀላል ወይም ከባድ የስነምግባር ጥፋቶችን ሊፈጽሙ ይችላሉ ጥፋት ፈጽመው ሲገኙ ከሚጠብቃቸው ዛፃገራዊ ኃላፊነት አንፃር ሲታይ ያልተገባ በመሆኑ የጥፋታቸው ክብደት እየተመረመረ የዲስኘሊን እርምጃ በሚከተለው አግባብ አንዲወሰድ ይደረጋል ማንኛውም አጩ ምሩቅ አነስተኛ የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽሞ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ወራት ማንኛውም ዓይነት የትምህርት ማስረጃ ይያዝበታል ቀላል የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽሞ ከተገኘ ከሰባት ወራት እስከ ዘጠኝ ወራት የትምህርት ዓመት ማንኛውም ዓይነት የትምህርት ማስረጃ ይያዝበታል መካከለኛ የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽሞ ከተገኘ ከአስር እስከ አስራ አምስት ወራት ማንኛውም ዓይነት የትምህርት ማስረጃ ይያዝበታል ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽሞ ከተገኘ ከአስራ ስድስት ወራት እስከ ሁለት ዓመት ማንኛውም ዓይነት የትምህርት ማስረጃው ይያዝበታል በጣም ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽሞ ከተገኘ የትምህርት ማስረጃው በጭራሽ አይሰጥም አንቀጽ በተማሪ ውክልና የተለያየ ኃላፊነት ያለባቸው ተማሪዎች የዲስፕሊን ጥፋት ፈጽመው ሲገኙ የሚወሰዱ እርምጃዎች የተማሪዎች ህብረት አባል የክበብ መሪ የክፍል ተወካይ የብሎክ ተወካይ የፍሎር ተወካይ የዶርም ተወካይ ወይም በሌሎች በማንኛውም መንገድ የተማሪ ተወካይ ሆኖ ሲሰራ ተማሪዎች እኩል እንዳይሳተፉ በዘር በብሔር በሐይማኖት በቋንቋ በፖለቲካዊ አመለካከት ወዘተ ላይ የተመሰረተ አድሎ የፈፀመ ከሆነና በማስረጃ ከተረጋገጠ ወዲያውኑ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከተሰጠው ኃላፊነት እንዲነሳ ይደረጋል ከላይ ንዑስ አንቀጽ የተገለፀውን ቢኖርም በዚህ መመሪያ ቅጣት የተቀመጠለትን የዲሲኘሊን ጥፋት የሚፈጽም የህብረቱ አባል ወይም የክበቡ መሪ ወይም ማንኛውም የተማሪ ውክልና ኃላፊነት ያለበት ተማሪ እንደማንኛውም ተማሪ በመመሪያው መሠረት ይጠየቃል አንቀጽ የየዲስፕሊን ጥፋት ቅጣት ዓይነቶች በዚህ መመሪያ መሠረት የዲስፕሊን ጥፋት በፈጸመ ተማሪ ላይ ሊወሰድ የሚችል ቅጣትና እርምጃ የቃል ግሳጴ በጽሑፍ የሚሰጥ የቃል ማስጠንቀቂያ ሐ ስለ ጉዳዩ ለወላጆችለአሳዳጊዎች ማሳወቅ መ ማህበራዊ አገልግሎት የሚያሰጥ ቅጣት ሠ ጥፋት የፈፀመበትን ንብረት መውረስ ረ በዲስፕሊን ጥሰቱ የተጎዱ ወይም ዋጋቸው የቀነሰ ወይም ሙሉ በሙሉ የወደሙ ንብረቶች ወይም ሕንፃዎች ተገጣጣሚዎች ካሉ የሚተኩ ከሆኑ እንዲተኩ ማድረግ ካልሆነ ዩኒቨርሲቲው በባለሙያ አስጠንቶ በሚያቀርበው የወቅቱ የገበያ ዋጋ መሠረት ዋጋውን ማስከፈል ሰ የተወሰደ ንብረት ካለ ማስመለስ ከልሆነ የወቅቱን የገበያ ዋጋ ግምት በመንግስት ንብረት ህግ መሠረት በገንዘብ እንዲከፈል ማድረግ ሽ ለተወሰነ ጊዜ ከትምህርት ማገድ ቀ ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ማሰናበት በ የትምህርት ማስረጃውን ለተወሰነ ጊዜ መያዝ ተ የትምህርት ማስረጃ ፈጽሞ አለመስጠት ቸ ጉዳዩን በወንጀል ወይም በፍታብሔር ሕግ እንዲታይ ለሚመለከተው አካል ማስተላለፍ ክፍል ስድስት የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ አንቀጽ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ ስለማቋቋም የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ በየደረጃው በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የሚቋቋም ነው ሀ በትምህርት ክፍል ደረጃ ለ በኮሌጅ ወይም በፋኩልቲ ወይም በኢንስቲትዩት ደረጃ ሐ ከላይ በሀና ለ ላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ዩኒቨርሲቲው ፈጣን ጥራት ያለውና ፍትኃዊ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል ሆኖ ካገኘው ለዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ተጠሪ የሆነ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴን በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ወይም በከምፓስ ደረጃ ሊያቋቁም ይችላል አንቀጽ የዲስፕሊን ኮሚቴው ተጠሪነት ሀ በትምህርት ክፍል ደረጃ የተቋቋመ የተማሪዎች የዲስፕሲን ኮሚቴ ተጠሪነቱ ለኮሌጅ ወይም ለፋኩልቲ ወይም ለኢንስቲትዩት ዲንኃላፊ ይሆናል ለ በኮሌጅ ወይም በፋኩልቲ ወይም በኢንስቲትዩት ደረጃ የተቋቋመ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ ተጠሪነቱ ለአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ይሆናል ሕ ከዋና ከምፓስ ወጪ ባሉ ቅርጫፍ ከምፓስ ሶች በትምህርት ክፍል ደረጃ የተቋቋመ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ ተጠሪነቱ ለኮሌጅ ወይም ለፋኩልቲ ወይም ለኢንስቲትዩት ዲን ይሆናል በኮሌጅ ወይም በፋኩልቲ ወይም በኢንስቲትዩት የተቋቋመ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ ተጠርነቱ ለከምፓሱ አስተዳደር ዲን ይሆናል ስለሆነም ኮሚቴው ማንኛውንም የዲስፕሊን የውሳኔ ሐሳብ ተጠሪ ለሆኑበት አካላት በማቅረብ ያስጸድቃል ዩ ዘክርአነነው ይየ አ ታጅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕ ሊን መመሪያ አንቀጽ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ አባላት ስብጥሩም ከመምህራን ከተማሪዎች ህብረትና እንደአስፈላጊነቱ ከአስተዳደር ሠራተኞች የተውጣጡ አባላት ያሉት ይሆናል በትምህርት ክፍል ደረጃ የሚቋቋመው የዲስፕሊን ኮሚቴ አምስት አባላት ይኖሩታል እነርሱም ሀ ከትምህርት ክፍሉ አንድ ነባር መምህር ሰብሳቢ ለሊ የትምህርት ክፍሉ ሁለት የተማሪዎች ተወካዮች አንድ ወንድና አንድ ሴትአባል ሒ የትምህርት ክፍሉ የመምህራን ማህበር ተወካይ አባል መ ከትምህርት ክፍሉ አንድ የአስተዳደር ሠራተኛ አባልና ፀሐፊ በኮሌጅ ወይም በፋኩልቲ ወይም በኢንስቲትዩት ደረጃ የዲስፕሊን ኮሚቴ አምስት አባላት ይኖሩታል እነርሱም ሀ ከኮሌጅ ወይም ከፋኩልቲ ወይም ከኢንስቲትዩት አንድ ነባር መምህር ሰብሳቢ ለ የኮሌጅየፋኩልቲየኢንስቲትዩት ሁለት የተማሪዎች ህብረት ተወካዮች አንድ ወንድና አንድ ሴት ተ ተ ተ ተ ዚን ሄሄ ን አባል ሐ ከኮሌጅ ወይም ከፋኩልቲ ወይም ከኢንስቲትዩት የመምህራን ማህበር ተወካይአባል መ ከኮሌጅከፋኩልቲከኢንስቲትዩት አንድ የአስተዳደር ሠራተኛ አባልና ፀሐፊ ፐ ዝ ከላይ በና በ የተገለጹትን የኮሚቴ አባላት አሰያየም በተመለከተ ሀ የትምህርት ክፍል የተማሪዎች ዲስፕሊን ኮሚቴ አባላትን የትምህርት ክፍሉ ካውንስል ዐሀበጠፀበ። ዕዐሀከር ሀ መርጦ ሰብሳቢ ምሰብሳቢ ፀሐፊና አባላት ብሎ ለይቶ በፋኩልቲው አካደሚክ ኮሚሽን ለርፀጠር ርዐቨበ ልር አስጸድቆ ለፕሬዚዳንት ያቀርባል ለ የኮሌጅ ወይም የፋኩልቲ ወይም የኢንስቲትዩት የተማሪዎች ዲስፕሊን ኮሚቴ አባላትን የፋኩልቲው አካደሚክ ኮሚሽን ልርጠ ርጠበ ልዕር መርጦ ሰብሳቢ ምሰብሳቢ ፀሐፊና አባላት ብሎ ለይቶ ለፕሬዚዳንት ያቀርባል ሐ ከላይ በ በሀና ለ ላይ በተገጸው መሠረት የቀረቡትን የኮሚቴ አባላት ፕሬዚዳንቱ ተቀብሎ ሊያጸድቅ ወይም ሊቀይር ይችላል አንቀጽ የተማሪዎች ዲስፕሊን የኮሚቴ አባላት የሚከተሉትን ሊያሟሉ ይገባል ሀ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በስነስርዓት አክባሪነታቸው በታማኝነታቸውና በቁርጠኝነታቸው የሚታወቁና ፍትፃዊና ሚዛናዊ እይታ ያላቸው የማያዳሉ ለ በዲስፕሊን ጥፋት ተከሰውና ተቀጥተው የማያውቁ ሐ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በአብዛኛው ወገን ተቀባይነት ያላቸው መ በዩኒቨርሲቲው ቢያንስ የአንድ ዓመት ቆይታ ያላቸው ሠ ከላይ ከሀ አስከ መ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ አዲስ ዩኒቨርሲቲካምፓስ ሲቋቋም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የሚወስን ይሆናል አንቀጽ የኮሚቴው ሥልጣን ሀ ኮሚቴው የቀረበለትን የተማሪዎችን የዲስፕሊን ጥፋት ክስ በዚህ መመሪያ መሠረትና ማን በተማሪዎቹ ላይ ተፈፃሚነት ካላቸው ህጎች ጋር በማገናዘብ መርምሮ የውሳኔ አንቀጽ መሠረት ያቀርባል ገፅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ለሊ በትምህርት ክፍል ዲስፕሊን ኮሚቴ ታይቶ ውሳኔ ያገኘን ጉዳይ ለኮሌጁለፋኩልቲውለኢንስቲትዩቱ የዲስፕሊን ኮሚቴ በይግባኝ የቀረበ ከሆነ መርምሮ የውሳኔ ፃሳቡን ለአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ያቀርባል ሐ ክሱን በሚመለከት ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ማንኛውንም የሥራ ክፍል መረጃው ጠይቆ የመውሰድ ማንኛውንም አካል አስቀርቦ የመመርመር ሥልጣን ይኖረዋል የሥራ ክፍሎችም የመተባበር ግዴታ አለባቸው አንቀጽ የኮሚቴው አባላት መጓደል ከኮሚቴው ውስጥ አንድ አባል የተጓደለ ከሆነ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እንዲያውቀው ተደርጎ በኮሚቴው ሰብሳቢ አቅራቢነት ተጠሪ የሆኑበት የቅርብ ኃላፊ ተተኪ ይመድባል ከአንድ በላይ አባል ከሆነ ግን በአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ይፈጸማል አንቀጽ ከኮሚቴ አባልነት ስለመነሳት ሀ የኮሚቴው ሰብሳቢ ከሳሽ በሚሆንበት ጊዜ በአባላቱ ውሳኔ መሠረት ከአባላቱ መካከል አንዱ ሰብሳቢ ይሆናል ለ የኮሚቴው ሰብሳቢ ወይም ማንኛውም አባል ክስ ከቀረበበት ተማሪ ጋር የግል ጠብ ወይም የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ያለው መሆኑ ሲረጋገጥ ለዚህ ጉዳይ ብቻ በጊዜያዊነት ከሰብሳቢነቱ ወይም ከአባልነቱ እንዲነሳ ይደረጋል ሐ ማንኛውም የኮሚቴ አባል ራሱን ከጉዳይ በማግለል ብሌላው አባል ላይ ቱጽእኖ ለመፍጠር ወይም ችግር ውስጥ ለማስገባት ከባለጉዳይ ጋር እየተገናኘ ሚስጢር ያወጣ ወይም ቃለ ጉባኤዎችን መረጃዎችንና ጽሁፎችን ለባለጉዳይ ያሳየ ወይም የገለጸ ወይም የሰጠ እንደሆነ ከአባልነቱ ይነሳል በከፍተኛ የዲስፒሊን ጥፋትም በአባላቱ ወይም በሰብሳቢው ይከሰሳል አስፈላጊው አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል መ ማንኛውም የኮሚቴ አባል በተደጋጋሚ ያለ ማንም ፈቃድ የኮሚቴ ስብሰባ ጥሪ ሲደረግ የሚቀር ከሆነ የጽሑፍ ማብራሪያ እንዲያቀርብ ይደረጋል ጉዳዩም በፋይሉ ውስጥ እንዲያያዝ ይደርግና ከአባልነቱ እንዲነሳ ይደረጋል በዲስፕሊን ጥፋትም ሊጠየቅ ይችላል አንቀጽ የኮሚቴው ምልዓተ ጉባኤና ድምጽ አሰጣጥ ሀ በኮሚቴው ስብሰባ ላይ ግማሽ አባላት ከተገኙ ምልዓተ ጉባኤው ሙሉ ይሆናል ለ አከራካሪ ጉዳይ ሲያጋጥም የኮሚቴው አስተያየት የሚያልፈው በድምጽ ብልጫ ሲሆን እኩል በኩል ከሆነ ሰብሳቢው ባለበት ወገን የቀረበው ፃሳብ ይፀድቃል በሃሳብ የተለየ አባል ካለ የተለየበት ምክንያት በቃለ ጉባኤው ላይ ይሰፍራል ሐ ሰብሳቢው የክስ ዛደቱን በአግባቡ መምራት አለበት በክርክሩ ወቅት አንድ የኮሚቴ አባል የስነምግባር ግድፈት ካሳየ ከስብሰባው በጊዜያዊነት እንዲወጣ ማድረግ ይችላል ይህ ምልዓተ ጉባኤውን ሊያጎል የሚችል ከሆነ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲያውቀው በማድረግ የጎደለው አባል እንዲተካ ወይም ባሉት አባላት ውሳኔ እንዲሰጥ ሊፈቅድ ይችላል መ ማንኛውም የኮሚቴው አባል በስብሰባው ኖረም አልኖረም የዛሳብ ልዩነት ኖረውም አልኖረውም በቃለ ጉባኤው ላይ ይፈርማል ገፅ ደ ኢአ እ ሚዲ ው የርኣጤኔ ከ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ አንቀጽ የኮሚቴው የስብሰባ ጊዜና የአባላት ሰዓት አከባበር ሀ ኮሚቴው የሚሰበስብበትን ቀንና ሰዓት እንደየክሱ ጉዳይ አንገብጋቢነትና ብዛት እየታየ በኮሚቴው ሰብሳቢ ይወሰናል ቢያንስ ከአንድ ቀን በፊትም ለአባላቱ አመቺ በሆነ መንገድ የሚገለጽ ይሆናል ሊለ ማንኛውም የኮሚቴው አባል አስቀድሞ ሰብሰቢውን ሳያስፈቅድ አሳማኝ ባልሆነ ሰበብ አስባብ ለተደጋጋሚ ቀናት ቢቀር ወይም ስብሰባውን ቢያስተጓጉል ሰብሳቢው በሚያቀርበው ማስረጃ መሠረት በአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ለመምህራን በአካዳምክ ምፕሬዚዳንት በኩል ተገቢው አስተዳድራዊ እርምጃ ይወሰድበታል አንቀጽ የዲስፕሊን ኮሚቴው የስራ ዘመን የኮሚቴው የስራ ዘመን ሁለት ዓመት ይሆናል ሆኖም አባላት እንደገና ተመርጠው ለሁለት ዙር ብቻ ሊያገለግሉ ይችላሉ ክፍል ሰባት የሥነስርዓት ድንጋጌዎች አንቀጽ የዲስፕሊን ጥፋት ክስ አመሠራረት ማንኛውም ከመማር ማስተማር ጋር የተያያዙ ጥፋቶችን ተማሪዎች ፈጽመው ሲገኙ ተማሪው የተመዘገበበት የትምህርት ክፍል ኃላፊ በጽሑፍ የተደራጀ ክስ ይመሰርታል ይህም ከምዘናና ከፈተና አስተዳደር ከቤተ መጽሐፍቅ ከሪጅስትራር ከመማሪያ ክፍል ከዩኒቨርሲቲ ውስጥና ከዩኒቨርሲቲ ውጭ ባሉ ቤተ። በማ ባጠ ገፅ ኣውት ፈን ጧ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ ሲ ሌላ ተጨማሪ ማስረጃ ካለ ረ ተማሪው ከአንድ በላይ በሆነ የዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰ ከሆነ ለእያንዳንዱ ጥፋት ተለይቶ ከላይ ሀ ሰ በተመለከተው መሠረት መቅረብ አለበት ሺ በጋራ እና ተመሳሳይ ጥፋት የተሳተፈ ከሆነ በጣምራ ሊከሰሱ ይችላሉ አንቀጽ ክስ መመስረቻ ጊዜ ሀ የዲስፕሊን ጥፋቱ ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ በ የሥራ ቀናት ውስጥ መቅረብ አለበት ለ የዲስፕሊን ጥፋቱ አነስተኛ ከሆነና ለዲስፕሊን ኮሚቴ መቅረብ የሌለበት ከሆነ ሥልጣን የተሰጠው አካል ጥሰቱ በተፈጸመ በ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ እርምጃ ወስዶ ያሳውቃል ሐ ከላይ በሀና በለ የተደነገገው ቢኖርም በዚህ መሠረት ያልተፈጸመ ከሆነ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራር አካላት በየትኛውም ጊዜ ጉዳዩን ማንቀሳቀስ ይችላሉ አንቀጽ ክስን ስለማሻሻል ሀ በዲስፕሊን ጥፋት የክስ ጽሁፍ ውስጥ የተገለጸው ጥፋት ዝርዝር በሚመለከት መሠረታዊ በሆኑ ነጥቦች ላይ ስህተት ወይም ግድፈት መኖሩ ሲታወቅ የውሳኔ ሐሳብ ከመቅረቡ በፊት በማናቸውም ጊዜ ክሱን ማሻሻል ይቻላል ለ በንዑስ አንቀጽ ሀ መሠረት የዲስፕሊን ክሱ ሊሻሻል የሚችለው በከሳሹ አነሳሽነት ወይም ክሱን በሚያጣራው የዲስፕሊን ኮሚቴ ጥያቄ መሠረት ሊሆን ይችላል አንቀጽ ክስ ስለማቋረጥ ሀ የዲስፕሊን ጥፋት ክስ የቀረበበት ተማሪ በሞት ወይም በማናቸውም ሴላ ምክንያት ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያለው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ የተቋረጠ እንደሆነ ክሱ መታየት ያቆማል ለ ነገር ግን መካከለኛና ከዚያ በላይ የዲስፕሊን ጥፋት የፈጸመ ተማሪ በንዑስ አንቀጽ ሀ ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በማንኛውም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለመማር የተመዘገበ ከሆነ ክሱ መታየቱን ይቀጥላል ውሳኔውም ለመማር ወደተመዘገበበት ዩኒቨርሲቲ ለአፈጻጸም ይላካል ተማሪው የተመዘገበበትና ውሳኔውን የሚፈጽም ተቋም በዚህ መመሪያ መሠረት ውሳኔውን ያስፈጽማል ያልተረዳው የግንዛቤ ጉዳይ ካለ ውሳኔውን ያሳለፈውን ተቋም ማብራሪያ ሊጠይቅ ይችላል ሐ ከውሳኔ በፊት የዲስፕሊን ክስ የተመሠረተበት ተማሪ ዝውውር አይፈቀድም አንቀጽ ክስን ስለማሳወቅ ሀ የዲስፕሊን ኮሚቴ ክስ የቀረበበት ተማሪ መልሱን ይዞ እንዲቀርብ የክሱን ጽሑፍና ማስረጃዎች ቅጅ አባሪ በማድረግ የክስ ማስታወቂያ አስፈርሞ ይሰጠዋል ለ የክስ ማስታወቂያው ክሱ የሚሰማበትን ቦታ ቀንና ስዓት የሚገልጽ ሆኖ ክሱ ከሚሰማበት ቀን ቢያንስ ከሶስት የሥራ ቀናት በፊት ለተከሳሹ ተማሪ መድረስ አለበት ሐ ተማሪው ሊገኝ ባለመቻሉ ወይም ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆኑ የክስ ማስታወቂያውን ለመስጠት ያልተቻለ እንደሆነ ምግብ ቤት አዳራሽ መኖሪያ ሕንፃና ቤተመጽሐፍት ገሪ ሕንፃ እና በግልጽ በሚታይ የዩኒቨርሲቲው የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ተለጥፎ ለአምስት ተከታታይ ቀናት እንዲቆይ ይደረጋል አንቀጽ የክስ መልስ ስለማቅረብ ሀ ተከሳሽ የክስ መልሱን ማቅረብ ያለበት በጽሑፍ ነው ለ ተከሳሽ ተማሪ የተከሰሰበት ጉዳይ በዲስፕሊን ጥፋት የማያስከስሰው ከሆነ ወይም ቀደም ሲል ውሳኔ የተሰጠበት ከሆነ ክሱ ሊታይ አይገባውም የሜል የክስ መቃወሚያ የማቅረብ መብት አለው ከላይ እና መሠረት የቀረበውን መቃወሚ የዲስፕሊን ኮሚቴው የተቀበለው እንደሆነ ክሱ እንዲቋረጥ የውሳኔ ሀሳብ ያቀርባል መቃወሚያውን ያልተቀበለው ከሆነ በዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰው ተማሪ ለቀረበበት ክስ መልስ እንዲሰጥ ያዘዋል ሐ የዲስፕሊን ክስ የቀረበበት ተማሪ ክሱን በማመን ወይም በመካድ መልሱን ማቅረብና ሲጠራም በአካል በመቅረብ ለዲስፕሊን ኮሚቴው ስለጉዳዩ ማስረዳት ይኖርበታል መ የክስ መልሱ በክሱ ለተጠቀሰው ለአያንዳንዱ የዲስፕሊን ጥፋት የተሰጠውን ምላሽና ተከሳሹ የሚፈልጋቸውን የመከላከያ ማስረጃዎችን ዝርዝር የያዘ ሊሆን ይገባል ሠ የክስ መልሱ ተከሳሽ ከዘረዘራቸው የመከላከያ ማስረጃዎች መካከል በእጁ የሚገኙትን የጽሑፍ ማስረጃዎችን ቅጅ የያዘና የዲስፕሊን ኮሚቴው እንዲያስቀርብለት የሚጠይቃቸውን ማስረጃዎች የትና በማን እጅ እንዳሉ በግልጽ የሚያሳይ መሆን አለበት ረ በዲስፕሊን የተከሰሰ ተማሪ የመከላከያ ማስረጃዎችን አቅርቦ የማሰማት መብት ይኖረዋል ነገር ግን ቅረብ በተባለበት ዕለትና ሰዓት ባይቀርብ በቀረቡት ሪፖርቶችና ማስረጃዎች ላይ መሰረት ተደርጎ የቅጣት ውሳኔ ይተላለፍበታል ሰ በዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰው ተማሪ በማመን መልስ የሰጠ አንደሆነ ተጨማሪ ማጣራት አስፈላጊ ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር ክሱን ከዚህ መመሪያ ጋር በማገናዘብ የውሳኔ ሐሳብ ይቀርባል ሺ በዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰው ተማሪ በመካድ መልስ የሰጠ እንደሆነ ኮሚቴው የሁለቱንም ወገን ምስክሮች በመስማትና ሌሎች ማስረጃዎችን በመመርመር አጣርቶ የውሳኔ ሐሳቡን ያቀርባል አንቀጽ ምስክር ስለመጥራት ሀ የዲስፕሊን ኮሚቴው ምስክሮች ከሚፈለጉበት አንድ ቀን ቀደም ብሎ ቀርበው ቃላቸውን እንዲሰጡ መጥሪያ እንዲደርሳቸው ያደርሪጋል ለ በአንድ የዲስፕሊን ጥሰት ላይ የሚመሰክሩ ምስክሮች በአንድ ጊዜ ተጠርተው ተራ በተራ በኮሚቴው ፊት ቀርበው እንዲመሰክሩ ይደረጋል ሐ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ተጨማሪ ምስክሮችን ከሳሹ ወይም ኮሚቴው ሊያቀርቡና ምስክርነታቸውም ሊሰማ ይችላል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ አንቀጽ የምስክር ቃል ስለመስማት ሀ ምስክሮች ሲሰሙ በዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰው ተማሪና ክሱን ያቀረበው አካል ሁለቱም በተገኙበት ይሆናል ሆኖም ግን አንዱ ወገን ተነግሮት የቀረ እንደሆነ የምስክሮቹን ቃል ከመቀበል አያግድም ለ የምስክሮቹ መልስ ቃል በቃል የሚመዘገብ ይሆናል ሕ ተከራካሪ ወገኖች የቀረቡ ምስክሮችን ተጨማሪ ወይም መስቀለኛ ጥያቄዎችን መጠየቅና ይህም እንዲመዘገብላቸው ማድረግ ይችላሉ አንቀጽ በዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰው ተማሪ የመጨረሻ ቃል የዲስፕሊን ኮሚቴው የዲስፕሊን ጥፋቱን የማጣራት ሥራ ከማጠናቀቁ በፊት ተከሳሹ ተማሪ የመጨረሻ ሐሳቡን በተከሰሰበት ጉዳይ ላይ እንዲናገር ዕድል ይሰጠዋል ይህም ቃል በቃል ይመዘገባል በቅጣት አወሳሰንም ለቅጣት ማክበጃነት ወይም ማቅለያነት ሊያገለግል ይችላል አንቀጽ የውሳኔ ሐሳብ ስለማቅረብ ሀ የተማሪዎች ዲስፕሊን ኮሚቴ የዲስፕሊን ጥፋቱን አጣርቶ እንዳጠናቀቀ ወዲያውኑ የምርመራውን ውጤትና ሊወሰድ የሚገባውን የዲስፕሊን እርምጃ የሚያመላክት የውሳኔ ሐሳብ ፈርሞ ተጠሪ ለሆነበት ኃላፊ ትምህርት ክፍል ዲስፕሊን ኮሚቴ ከሆነ ለኮሌጅ ፋኩልቲ ኢንስቲትዩት ዲን ያቀርባል የኮሌጅፋኩልቲ ኢንስቲትዩት ኮሚቴ ከሆነ ለአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ያቀርባል ለ የኮሚቴው የውሳኔ ሐሳብ የሚከተሉትን ሊይዝ ይገባል » የተማሪውን ሙሉ ስም መለያ ቁጥር ትምህርት ክፍል የትምህርት ዓመት የሚኖርበት ሕንጻና ዶርም ቁጥር የተማሪውን የትምህርት ውጤት የተማሪውን የቀድሞ ሪከርድ » የዲስፕሊን ጥፋቱን ዝርዝር ደረጃና የተፈጸመበትን ሁኔታ » የተከሳሽ ምላሽ የምስክሮችን ቃል ዝርዝር የውሳኔ ሐሳብ የኮሚቴው አባላት ፊርማ ያለበት ቃለ ጉባኤ ከነአባሪ ማስረጃዎች ጋር የሰብሳቢው ፊርማ ያለበት ሸሺ ደብዳቤ ሐ በዲስፕሊን ጥፋት የተከሰሰ ተማሪ ተጣርቶ ከተከሰሰበት ጉዳይ ነጻ መሆኑ ሲረጋገጥ ይህንኑ የሚገልጽ የጽሑፍ መረጃ ይሰጠዋል አንቀጽ የአስተዳደር ፕሬዚዳንት ውሳኔ የዩኒቨርሲቲው ኮሌጅፋኩልቲኢንስቲትዩት ዲን ወይም አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ በዚህ መመሪያ መሠረት ከመረመረ በኃላ ሀ የኮሚቴውን የውሳኔ ሐሳብ ሙሉ በሙሉ የማጽደቅ ለ ኮሚቴው ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ የማሻሻል ው ከ ኮሚቴው ጉዳዩን እንደገና እንዲመረምር ምክንያቶችን ገልጾ የማዘዝ ሥልጠን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ በዩኒቨርሲቲው ኮሌጅፋኩልቲኢንስቲትዩት ዲን ወይም በአስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንቱ የጸደቀው የዲስፕሊን ውሳኔ ለተማሪው በጽሑፍ ይሰጠዋል ከከባድ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እና ከዚያ በላይ የዲስፕሊን እርምጃ የተወሰደበት ከሆነ ተመሳሳይ ቅጂ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ባሉ የማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይ ይለጠፋል አንቀጽ የውሳኔ አፈጻጸም ሀ የዲስፕሊን እርምጃ ውሳኔ ከጸደቀበት ቀን አንስቶ ተፈጻሚ ይሆናል ሆኖም ግን ተማሪው ከዩኒቨርሲቲው ግቢ የሚወጣ ከሆነ የ ሰዓታት ጊዜ ይሰጠዋል ይህም ማለት የተማሪነት መብቱን ማጣትን እንጂ እንደ አንድ ባለጉዳይ ከውጪ እየተመላለሰ መጨረስ ያለበት ጉዳይ ካለ የሚመለከተውን አካል አስፈቅዶ መጨረስ ይችላል ለ በንዑስ አንቀጽ ሀ ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ጉዳዩን ይግባኝ ብሎ ይግባኙ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ጥያቄ አቅርቦ ከተፈቀደለት በግቢ ውስጥ ሆኖ እየተማረና አገልግሎት እያገኘ ጉዳዩን መከታተል ይችላል አንቀጽ የተማሪዎች የዲሲኘሊን ጉዳይ ሰሚ ኮሚቴ የክስ አሰማም ዛደት ስነስርዓት ሰብሳቢው የኮሚቴውን ስብሰባ በሊቀመንበርነት ይመራል ሰብሳቢው በማይኖርበት ጊዜ ምክትሉ ኃላፊነቱን ይረከባል የኮሚቴውን ቃለ ጉባኤ ጸሐፊው ይይዛል ተከሳሹ ተማሪ በጽሑፍና በቃል መልስ የማቅረብ መብት እለው ከፍተኛና አሳማኝ በሆነ ምክንያት ተማሪው በክርክሩ ዛደት መሳተፍ ያልቻለ እንደሆነ ሲታመን እስከሚችልበት ቀን ድረስ ክርክሩ እንዲቆይ ይደረጋል ተከሳሹ ክሱን ለማስረዳት ከሳሽ ያቀረባቸውን ምስክሮች የመጠየቅ መብት አለው ከሳሽም ተከሳሽ ያቀረባቸውን የመከላከያ ምስክሮች የመጠየቅ መብት አለው ተከሳሹ ዝም የማለት መብት አለው ነገር ግን ዝምታው አምኖ እንደመቀበል ይቆጠራል ተከሳሹ አማርኛ የማይችል ከሆነ ሀሳቡን በእንግሊዘኛ የማቅረብ መብት ይኖረዋል ፎ ክፍል ስምንት የቅጣት አወሳሰን አንቀጽ ቅጣት ስለማቅለል ከዚህ ቀጥሎ የቀረቡት ምክንያቶች ለዲስፕሊን ጥፋቶች ለሚሰጡ ቅጣቶች የቅጣት ማቅለያ ሊሆኑ ይችላሉ ጥፋተኛው ከዚህ በፊት መልካም ስነ ምግባር የነበረው መሆኑ ከመዝገብ ሲረጋገጥና ከዚህ በኋላ የመድገም ሀሳብ የሌለው እንደሆነ በመፀፀት በጽሑፍ ያቀረበ ከሆነ ጥፋቱን የፈፀመው ከባድ አደጋ እየደረሰበት መስሎት ራሱን ለመከላከል በሚያደርገው ሙከራ ከሆነ ጥፋቱን እንዲፈፀም የተጐጅው እጅ ካለበት ጥፋቱን ሲፈጽም አጥፊው በከፍተኛ አካላዊና ስነልቦናዊ ጭንቀት ውስጥ ከነበረ ጥፋተኛው የሚጠበቅበትን ሁሉ በማድረግና ጥፋቱን በማመን ከፍተኛ የመፀፀት አዝማሚያ ያንፀባረቀ እንደሆነ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ አንቀጽ ቅጣት ስለማክበድ የዲስፕን ጥፋት በፈጸሙ ተማሪዎች የሚተላለፍ የቅጣት ውሳኔ ላይ ቅጣቱን ሊያከብዱ የሚችሉ ጉዳዮች አንደሚከተለው ቀርበዋል ተደጋጋሚ በሌሊት ወይም ጨለማን ተገን በማድረግ የጦር ወይም ሌላ አደገኛ መሳሪያ በመያዝ ከሆነ ጥፋቱን የፈፀመው ከሌሎች የወንጀለኞች ቡድን ጋር በመሆን በተለይ በመሪ ተዋናይነትና አደራጅነት ከሆነ ጥፋቱን የፈጸመው በቡድን በመሆን ጥፋቱ የከበደና በሌላው ላይ አስቦና ሆነ ብሎ ጉዳት ለማድረስ ከሆነ ጥፋቱን የፈፀመው በማናለብኝነት የተማሪውን አደራ ወደ ጐን በመተው ሆን ብሎ ለማጥፋት አስቦ ከሆነ ጥፋቱን የፈፀመው በከፍተኛ ጥላቻ በመነሳት ወይም ሆን ብሎ አስቦበት ከሆነ ጥፋቱን የፈፀመው ለጥል ባልተዘጋጁና ባላሰቡ ንጹሀን ተማሪዎች ወይም የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኃላፊዎች መምህራን ወይም በአስተዳደር ሠራተኞች ላይ ከሆነ አንቀጽ የዲስፕሊን ጥፋቱ በሪከርድነት በተያዘበት ወቅት ሲደገም ቀድሞ ውሳኔ የተሰጠበት የዲሲኘሊን ግድፈት አነስተኛ ግድፈት ሆኖ ውሰኔው የሚያበቃበት ጊዜ ሳይደርስ በተመሳሳይ ምድብ ውስት የሚገኝ የድስፕሊን ቸፋት ከተደገመ እስከ አንድ ወሰነ ትምህርት ከትምህርት ገበታ ያሳግዳል የተደገመው ግድፈት አነስተኛ የዲስፕሊን ጥፋት ካልሆነ ግን በአዲስ መልኩ ይታያል ቀድሞ ውሳኔ የተሰጠበት ጥፋት ቀላል ሆኖ በተመሳሳይ ምድብ ውስጥ የሚገኝ ጥፋት ወይም አነስተኛ ጥፋት ከተደገመ ከአንድ እስከ ሁለት ዓመት ከትምህርት ገበታ ያሳግዳል የተደገመው ጥፋት መካከለኛ ወይም ከፍተኛ ከሆነ ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ገበታ ያሰናብታል ቀድሞ ውሳኔ የተሰጠበት ጥፋት መካከለኛ ወይም ከፍተኛ ከሆነ የትኛውም ጥፋት ቢፈጽም ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ገበታ ያሰናብታል አንቀጽ ተደራራቢ የዲሲኘሊን ጥፋት ሲፈፀም የቅጣት አወሳሰን ተማሪው ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ከትምህርት ገበታ የሚያሳግዱ የዲሲኘሊን ግድፈቶች በአንድ ጊዜ ወይም በመጀመሪያ ለፈፀመው ጥፋት ውሳኔ ከማግኘቱ በፊት ፈጽሞ ከተገኘ ለአያንዳንዱ ጥፋት ቅጣት ከተቀመጠ በኋላ የሁሉንም ቅጣት በመደመር ይወሰናል የሁሉም ድምር ከሶሰት ዓመት ከበለጠ ሙሉ በሙሉ ከትምህርት የማስናበት ውሳኔ ይሰጣል አንቀጽ ውሳኔን ስለማሳወቅና ተያያዥ ጉዳዮች አፈጻጸም ኗ ከምክር ከግሳዔ በስተቀር ማንኛውም በተማሪ ላይ በዲስፕሊን ጥፋት የሚወሰድ አርምጃ ለተማሪው በጽሑፍ ሊሰጠው ይገባል በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በማንኛውም ደረጃ የሚወሰድ የዲስፕሊን ጥፋት አርምጃ ቢያንስ ለግቢ ደህንነትና ጥበቃ ለሚመለከተው የትምህርት ክፍል ኃላፊ ለሚመለከተው ን ዲን ለሪጅስትራር ለተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር ለአስተዳደር ፕሬዚዳንትና ለፕሬዚዳንት በግልባጭ ማሳወቅ ይገባል የተጠቀሱት በአግባቡ አደራጅቶ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዲስፕ ሲን መመሪድ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በሙሉ በግልጽ በሚታይ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በመለጠፍ ሌላው እንዲማርበት ይደረጋል ተማሪው ባጠፋው ጥፋት በጊዜያዊነትም ይሁን ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ገበታ በሚታገድበት ወቅት የታገደበት ምክንያት በጽሑፍ ይገለጽለታል በወቅቱ ተማሪው በግቢ ውስጥ ባለመገኘቱ ወይም አድራሻው ባለመታወቁ ወይም በሌላ ምክንያት በአካል ሳይገኝ በመቅረቱ ከትምህርት ገበታ የታገደበትን ውሳኔ ለራሱ መስጠት ካልተቻለ ውሳኔው በዩኒቨርሲቲው ማስታወቂያ ሰሌዳ ቢያንስ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ተለጥፎ እንዲቆይ ይደረጋል ተማሪው የተከሰሰበት የዲስፕሊን ጥፋት ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ገበታው እንዲታገድና የትምህርት ማስረጃው እንዳይሰጠው ካልተወሰነበት በስተቀር እስከ ዕግዱ ያለው የትምህርት ማስረጃ በዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ያቋረጠ መሆኑን ከሚገልጽ ሸፒ ደብዳቤ ጋር ይሰጠዋል የተማሪው በጊዜያዊነትም ይሁን ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ገበታው መታገድ ከዕግዱ ጋር ያልተያያዙ መብቶችንና ግዴታዎቹን ተፈጻሚነት አያስቀርም ውሳኔ ለመስጠትም ይሁን ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር እና የተማሪዎች ህብረት የውሣኔ መጓተት እንዳይፈጠር አፈፃፀሙን ይከታተላሉ አንቀጽ የዲስፕሊን ጥፋት ቅጣትን በሪከርድነት ስለመያዝ ማንኛውም ተማሪ የዲሲኘሊን ጥፋት የቅጣት ውሳኔ ከተላለደበት በኋላ በግል ፋይሉ ውስጥ ገብቶ በሪከርድነት ሊያዝበት የሚችለው ለአነስተኛና ቀላል የዲስፕሊን ጥፋቶች ቅጣት ከተላለፈበት ቀን ጀምሮ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚቆይ ሲሆን በተማሪው ማህደር ውስጥ ከአንድ ዓመት በላይ ተቀምጦ ቢገኝ ዋጋ አይኖረውም ለመካከለኛ ከፍተኛና በጣም ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች ውሳኔ ከተላለፈበት ቀን ጀምሮ ተማሪው ትምህርቱን እስካጠናቀቀበት ጊዜ ድረስ ሆኖ በሰነድነት ግን በተመራቂው ፋይል ውስጥ ሁሌም ይቀመጣል አንቀጽ የዲስፕሊን እርምጃ የመውሰድ ሥልጣንና ኃላፊነት የተሰጣቸው አካላት ማንኛውም ተማሪ አነስተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶችን በሚፈጽምበት ወቅት ጉዳዩን ለዲስፕሊን ኮሚቴ ማቅረብ ሳያስፈልግ ሀ የዲስፕሊን ጥፋቱ በተፈጸመበት ክፍል ኃላፊ ወይም ጥፋቱ በመማሪያ ክፍል በወርክሾፖችና በቤተ ሙከራ ክፍሎች ከሆነ በመምህሩ ከዚያ ውጭ ከሆነ የትምህርት ወይም የሥራ ክፍል ኃላፊ ምክር ወይም የቃል ማስጠንቀቂያ የመስጠት እና ይህንነ በመዝገብ መዝግቦ የመያዝ ኃላፊነት አላቸው ለ የትምህርት ክፍል ኃላፊ ኮሌጅፋኩልቲኢንስቲትዩት ዲንና የተማሪዎች ጉዳይ ዳይሬክተር የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የመስጠት ሥልጣንና ኃላፊነት አላቸው ማንኛውም ተማሪ ቀላል የዲስፕሊን ጥፋቶች የፈጸመ እንደሆነ ኮሌጅፋኩልቲኢንስቲትዩት ዲን በዚህ መመሪያ መሠረት በዲስፕሊን ኮሚቴ ተጣርቶ የውሳኔ ፃሳብ ሲቀርብለት በፋይል የሚቀመጥና በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የሚለጠፍ ከጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ወይምእና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሰጥ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣንና ኃላፊነት አለው ማንኛውም ተማሪ መካከለኛ ከፍተኛና በጣም ከፍተኛ የዲስፕሊን ጥፋቶች የፈጸመ ብ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት በዚህ መመሪያ መሠረት በዲስፕሊን ኮሚቴ ተጣርቶ የውሳኔ ፃሳብ ሲቀርብለት እንደጥፋቱ ክብደት በፋይል የሚቀመጥና በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የሚለጠፍ ከከባድ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ጀምሮ ከትምህርት ገበታ እስከማገድ ወይም ሙሉ በሙሉ እስከማሰናበት ሥልጣንና ኃላፊነት አለው ክፍል ዘጠኝ ልዩ የክርክር ሂደት አንቀጽ ኹ ጉዳዩ በሴኔት ስለመታየት ለሁለትና ከዚያ በላይ ዓመት ከትምህርት ገበታ ሊያስናብቱ የሚችሉ የዲስፕሊን ጥፋቶች ላይ በወቅቱ በተከሰተው ችግር አሳሳቢነት የተነሳ ሴኔቱ ማየት ሲፈልግ ጉዳዩን የመመርመር የማጣራትና ቀድሞ የተሰጠውን ውሳኔ በማጽደቅ በማሻሻል ወይም በመሻር ውሳኔ የመስጠት ስልጣን አለው ይህም የሚሆነው ጉዳዩ በሴኔት እንዲታይ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ሲወሰን ነው ክፍል አስር የይግባኝ ስነሥርዓት የይግበኝ ውሳኔ አሠጣጥ ሄደቱ ከዲስፕሊን ጥፋት ክስ አመሠራረት እስከ ውሳኔ አፈጻጸም ድረስ ካለው ጋር ተመሳሳይ ዛደትን የሚከተል ነው አንቀጽ የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ስለማቋቋም የዩኒቨርሲቲው ኘሬዚዳንት የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ያቋቁማል የኮሚቴው አባላት አንድ የሰኔት አባል የሆነ መምህር ሰብሳቢ አንድ የአስተዳደር ክፍል ፃላፊ አንድ የተማሪዎች ህብረት አባል አባል አንቀጽ ይግባኝ የማቅረብ መብት ሀ ጥፋተኝነት የተወሰነበት ተማሪ ቅሬታውን ይግባኙን ለይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ እንዲቀርብለት ለዩኒቨርሲቲው ኘሬዚዳንት ውሳኔው ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት አምስት የሥራ ቀናት ውስጥ በጽሁፍ ማመልከቻ የማቅረብ መብት አለው የይግባኝ ማመልከቻውም የሚከተሉትን መያዝ አለበት የይግባኝ አቅራቢ ስም መለያ ቁጥር ጾታና አድሜ የሚማርበት ፋካሊቲ ትምህርት ክፍልና የትምህርት ዓመት የቅሬታው መንስኤ ደጋፊ ማስረጃዎች ጣሉ አመልካች የሚሻው መፍትሄ ቀንና ፊርማ ለ የዩኒቨርሲቲው ኘሬዚዳንት በወቅቱ የቀረበውን ቅሬታ አይ ፕሬዚዳንቱ መጣራ አለበት ብሎ ስያምን የተጻፈውን ማመልከቻ ከአስፈላጊ መረጃ ጋር ለይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ልመራው ይችላል።