Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ይህ ጥናት በዚህ መልኩ እንዲሰናዳ እና ይህን መስመር ይይዝ ዘንድ ከእኔ ከታናሽህ ጎን ቆመህ ያላሰለሰ ደጋፊ አስተያየትህን ለሰጠኸኝ መምህሬ እና አማካሪየ ዶር አየነው ጓዱ ላቅ ያለ ምስጋናየ ይድረስልኝ ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው ድረስ የህይወት ስንቅ ይሆነኝ ዘንድ የዕውቀት ዘራችሁን በአዕምሮየ ላይ የዘራችሁልኝ መምህሮቼ ሁሉ ልባዊ ምስጋናየን እንኳችሁ ከዚህ በመቀጠል የእኔን ሀሴት እና ፍስሃ ለማየት እራስሽን ትተሽ ከእኔ በላይ ለእኔ ህላዌ ስትይ ብቻ ለምትኖሪው ውዷ ባለቤቴ ለምለም አረጋ ስቸገር እየረዳሽ ሲደክመኝ እያበረታሽ ያላንዳች እረፍት እየደከምሸ እዚህ አድርሰሽኛል እና እጅጉን አመሰግንሻለሁ በምክር በገንዘብ እና በጸሎት ለደገፋችሁኝ ውድ ቤተሰቦቼ እንዲሁም በሃሳብ ላጠናከራችሁኝ ጓደኞቼ እና የሥራ አጋሮቼ ሁሉ ምስጋናየ ለእናንተም ይሁንልኝ ሪዐዐርናዐዐሀ ማውጫ ይዘት ገጽ ምስጋና ከከ ከከ ከ ከ። ሦህህቪከ ቪ ዉርሃ በ ቨ ርየዘበ ካፀ በ ጠልበዖ በ። በባዐዘባ ቨዘጠ ህህዕዘፀ ህቪከ ሀከፀከሃ በ ዘፀጩጨጪሠህጩ እብ እና ፍጠ ፀዐህር ይህ የፍልስፍና ዘርፍ ከሥነጽሑፍ ጋር ስላለው ግንኙነት የሁሉም የዘርፉ ምሁራን ሃሳብ ነው ማለት ይቻላል ነገር ግን አንድን ሰፈር ተጋርተው ከመኖርም ባለፈ በእድሜ እኩያነትም ይሁን በሌሎች አዛማጅ ምክንያቶች እርስ በእርስ የተሳሰሩ እና በአንድ ላይ የተገመዱ ህብረወጣቶች ነበሩ ይሁን እንጅ በኋላ ግን ሁሉም ጌርሳሞትን የየግላቸው ለማድረግ አጥብቀው ከመፈለጋቸው የተነሳ አስበውትም ይሁን በአጋጣሚ በአራት በአምስት ሜትር ርቀት የተተከሉ አፍላ ዛፎች ሆነዋል ሁሉም ቅርንጫፎቻቸውን አስፍተው ጌርሳን ለማስጠለል የሚታትሩም ይመስላሉ የድር እና ማግ መረብ ሆነው ሁለቱ የድር የቀሩት የማግ ሆነው ፉክክርም ይመስሳል ፉክክር መጓተት ነውና መረቡን የማይመች ውጥር ያደርገዋል ምናልባት ወዳጅነታቸው ውስጥ የተገነባው ግን የተደበቀው ጊዜ የሚያወጣው የሕይወት ጉዞ በጨረፍታ እራሱን ሲያሳይ ሆናል ሁሉ ነገር ተለዋዋጭ ከሆነ በርሃው ካበበ ያበበው ከረገፈ የረገፈው ከፀደቀ እንዲህ የተሰበሰቡት ወጣቶች የማይበታተኑበት ምክንያት ኖራል። በ። በ ሦዐዉ። ልጠከጺበር ፀዉኪ ልከ ዐህፀከባፀነዘ ዐገጩ ዐ ድሀዐዐዌ ወመሰዐሃወፍ ህሃዐ ከ ዐር ሀ ሀፀል ከከካፀ እነፐዝ በ። ዕርዐበክዩበርፀ ዐ ጅ።ልበህ ዞኮ በቨኪበ ከ።
ጠ ዛህጠበአሸሸ ወይም ተመራማሪዎች ዘንድ ጥቅም ላይ የሚውሉ የመተንተኛ መነጽሮች ናቸው ሥነጽሑፋዊ ንድፈሃሳብ ዘርፈ ብዙ የሆነ ስያሜ በመሆኑ በሥነጽሑፍ እና በባህል ጥናት ሥራ ውስጥ ልዩልዩ ጽሁፋዊ አሃዶችን ለመለየት እና ለመተንተን ምቹ የሆኑ ንድፈሃሳቦችን ሁሉ አቅፎ የያዘ ሲሆን ይኸውም ለምሳሌ በስርዓተፆታ ተሟጋቾች ሮፀጠበ በማርክሳውያን እለ እንዲሁም ሥነጽሑፍን በሜያስተምሩ ነገርግን ሌላ ዝንባሌ ባላቸው የሥነልቦና እና የፍልስፍና ጥናቶች ውስጥ የሚያገለግሉ አተያዮችን ሁሉ ያካትታል ፈሀሀልበ ህሃቨቬሃ በተጨማሪም ዕርጩቬዐቫ ሥነጽሑፋዊ ንድፈሃሳብ በአዲስ ምዕራፍ ብቅ ያለው ከዎቹ ወዲህ መሆኑን ገልጸው ይኸውም የፍልስፍና የታሪክ የፖለቲካ እና የሥነልቦና ጭብጦችን የሚያስተዋውቁ እንዲሁም በማርክሲዝም በመዋቅራዊ ሂስ ዉከህርከዉበ በድህረመዋቅራዊ ሂስ ኮዐከህርከዉመበ በአንስታይ ሂስ በነገረ ባህላዊ ሂስ ርህዚህ ህነ በሃዲስ ታሪካዊ ሂስ ክፀለከበርዉመ እና በመሳሰሉት ንድፈሃሳባዊ ልማዶች መተንተን የሚሹ ሥነጽሑፋዊ ሥራዎች የፈለቁበት ወቅት እንደነበረ ያትታሉ ታዲያ እነዚህ እና ሌሎችም በቁጥር የበዙ እና የተለያየ አይነት ያላቸው ንድፈሃሳባዊ ልማዶች በአዲስ መልክ መምጣት የሥነጽሑፍንም ሆነ የንድፈሃሳቦችን ባህርይ እና ተፈጥሮ ለመረዳት ውስብስብ ተግዳሮቶችን እንደፈጠሩም ል ይገልጻሉ ስለሆነም እነዚህን ጨምሮ በዚህ ዘመን ያሉ ሌሎች ብዙ ቁጥር ያላቸውን ሥነጽሑፋዊ ንድፈሃሳቦች ሥርዓት ጽንሰሃሳብ አስፈላጊነት እና መርህ በውል መለየት እና መመርመር የሚሻ ጉዳይ መሆኑንም መገንዘብ ይቻላል የዚህ ጥናት ዋነኛ ትኩረት ደግሞ በአማርኛ ሥነጽሑፍ ላይ በመሆኑ ስለዚህ ጉዳይ ጥቂት ነገሮችን እንመልከት ይህን የአማርኛ ሥነጽሑፍ ጥናት አስመልክተው በአማርኛ ሥነጽሑፍ ጥናት ላይ ቅኝት ያደረጉት ታዬ አሰፋ እና ሽፈራው በቀለ የአማርኛ ሥነጽሁፍ ጥናት ከራሱ ከአማርኛ ሥነ ጽሁፍ መጀመር ጋር የተያያዘ ሆኖ በኢጣሊያን አጥሂዎች ግንባር ቀደምትነት በተለይም በአገራችን የዘመናዊ ሥነጽሑፍ ታሪክ የመጀመሪያው የአማርኛ ዘመናዊ ሥነጽሑፍ ሥራ የአፈወርቅ ገኢየሱስ ልቦለድልቦለድ ታሪክ ብቅ ካለበት ጌዜ ማለትም በፈረንጆች ገደማ ጀምሮ እንደተጀመረ እና ቀስ በቀስም በተለያዩ የሀገራችን ምሁራን አማካኝነት እያደገ መጥቶ ዛሬ ያለበትበት ደረጃ ላይ እንደደረሠ ያስረዳሉ በተመሳሳይ መልኩ ቴዎድሮስ ገብሬ ከሥነ ጽሑፍ ትይዩ እየሰፋ መጣ የተባለው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ጥናት በአንድ አይነት ደረጃ አንድ ጉዳይ ላይ አተኩሮ አንድ መስመር ተከትሎ እዚህ የደረሰ አይደለም በማለት የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ጥናት ወዲህ ከራሱ ከሥነጽሑፍ ዘርፍ መጀመር ጋር የተያያዘ እድሜ ያለው እና አብሮ እያደገ የመጣ እንደሆነ ወዲህ ደግሞ ጊዜተኮር እና ሁኔታተኮር ከመሆኑ የተነሳ በጊዜ ልዩነት ልዩ ልዩ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት ተግባር መሆኑን ያስረግጣሉ ስለዚህ ሥነ ጽሑፋዊ ጥናት የአማርኛን ጨምሮ የረጅም ዘመን ታሪክ ባለቤት ቀጣይነት ያለው እና ሥነጽሑፍ ባለበት ሁሉ የሚኖር ዘመን ተሻጋሪ ተግባር ነው ብሎ መደምደም ይቻላል ከፍ ሲል እንደተጠቆመው የአማርኛ ሥነጽሑፍ ጥናት ልክ እንደየትኛውም አይነት ሥነጽሑፋዊ ጥናት ሁሉ ይዞት የሚነሳውን ዋነኛ ጉዳይ ለመተንተን እና በተጨባጭ ለማሳየት የሚረዱ አሊያም ይዞት ከተነሳው ዓላማ አንፃር በሥነጽሑፋዊ ሥራዎች ላይ የሚቀርቡ ይዘቶችን ሊያጎሉ በሚችል መንገድ ልዩ ልዩ ሥነጽሑፋዊ ንድፈሃሳቦችን በሸፀጨሻቫ ከዘ ገርቶ እና አስማምቶ ይጠቀማል በዚህ መሰረት ይህ ጥናት የድህረ ጦርነት ክስተትን ተከትሎ በተለይም ከዘመናዊነት እሳቤ እፌሑጠ ትይዩ ብቅ እንዳለ እና በዚያው በኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሥነጽሑፋዊ ሽፋን እንዳገኘ የሚነገርለትን የነገረህላዌ ፍልስፍና አእጪጤበከበ በዋና ማናበቢያነት መርጦታል ነገረህሳዌ ፎበጠ የሚለው ቃል የተገኘው በዎቹ አጋማሽ በፈረንሳያዊው ፈላስፋ በ እር አማካኝነት እንደሆነ እና በሥራ ላይ መዋል የጀመረው ደግሞ በዚሁ ወቅት ላይ በጀርመናዊው ጸሐፊ እና ፈላስፋ ህቧኋበኮጸሀ አማካኝነት እንደሆነ ልከ እንዲህ ያስረዳሉ ፐከፀ ከክ ፔአፎጨከበቨበቿባ ዘባ ከህፀ ከፀከ ርዐበፀበ ከሃ ከፀ ዮጩበርከ ፀከኗሀፀከ። በ ሦቨ የጂጠ ልከከ በእርግጥ የነገረህላዌ ፍልስፍና ታሪክም ሆነ ብያኔ በተለያዩ የፍልስፍናው አራማጆች እና ተመራማሪዎች ዘንድ የተለያየ ስለመሆኑ የዘርፉ ተመራማሪዎች እና እራሳቸው ፈላስፋዎችም የሚጋሩት ሃሳብ ነው ይሁን እንጅ በዚህ ፍልስፍና ላይ የተሰማሩት ሁሉም አካላት ይህንኑ ፍልስፍናዊ እሳቤ በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ወይም ፍጹም የማይገናኝ ሃሳብ አላቸው ማለት እንዳለሆነ ልብ ይሏል እንዲያውም አብዛኛዎቹ ከሚጋሯቸው ጉዳዮች መካከል አንደኛው እና ዋናው የሁሉም የዘርፉ ፈላስፋዎች የፍልስፍናቸው ማዕከላዊ ጉዳይ የሰው ልጅ መሆኑ ነው ቴዎድሮስ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በሥራዎቻቸው ውስጥ ተመላልሰው የሚመጡ እና ደጋግመው የሚያነሷቸው ልዩ ልዩ የነገረ ህላዌ ጭብጦችም ነገረህላዌያኑ በዚሁ ፍልስፍና ላይ ያላቸውን ተቀራራቢ ወይም የጋራ ሃሳብ የሚያሳይ ሌላው ጉዳይ ነው ልከ እና ቴዎድሮስ ም በዚህ ጉዳይ ይስማማሉ መሠረቱ ከጥንታውያን ታላላቅ ፈላስፋዎች ቅዱሳን እና ትንቢተኞች እሳቤ ጋር እንደተቆራኘ የሚነገርለት ነገረህላዌ በተለያዩ የኪነጥበብ ሥራዎች ላይ በተለይም ደግሞ በሥነጽሑፍ ሲንጸባረቅ የቆየ እና ከሥነጽሑፍ ጋር የጠበቀ ዝምድና ያለው ፍልስፍናዊ እሳቤ ስለመሆኑ ብዙ ምሁራን ያትታሉ በዚህ መሠረት ቴዎድሮስ ጋ ይህ የህልውና ፍልስፍና ሁለንተናዊነት ያለው ማህበራዊ ክስተት በመሆኑ በየትኛውም ስፍራ በማንኛውም ዓውድ ሊነሳ የሚችል ማህበራዊ እና ሰብዓዊ የህልውና ጥያቄ መሆኑን ጠቅሰው ማንኛውም ህልው ሥርዓት ከዚህ የአስተሳሰብ ዘይቤ ሊወጣ እንደማይችል በአንክሮ ያስቀምጣሉ በዚህ ሃሳብ መነሻነትም ከሥነጽሑፍ ኪን ጋር ላለው ዝምድና ሁለት አበይት ምክንያቶችን ያስቀመጡ ሲሆን የመጀመሪያው የዘመናዊ የነገረ ህሳዌ ፍልስፍና መሠረት የተጣለው በራሱ በሥነጽሑፍ ኪን ውስጥ ነው የሜል ሲሆን የሁለተኛው ደግሞ ዓበይት የፍልስፍናው አቀንቃኞች የተለያዩ የሥነጽሑፍ ከያኒያን ከመሆናቸውም በላይ በተለያዩ የሥነጽሑፍ ሥራዎቻቸው ታላቅ ክብር እና ዝና የነበራቸው ታላላቅ ደራሲያን እና ጸሐፈ ተውኔቶች መሆናቸው ነው በማለት ከልከ እና ከነልከ ትንታኔ ጋር ተዛማጅ የሆነ ሃሳባቸውን ያራምዳሉ ከቴዎድሮስ ልከ እና ነሃህቨከ ማብረራሪያ መነሻውን ከአውሮፓ ያደረገው እና ሠፊ መጠነርዕይ ያለው የዘመናዊ የሰው ልጅ የህልውና ፍልስፍና እንደየትኛውም የዓለም አገራት ሁሉ በእኛ አገር የአማርኛ ሥነጽሑፍ ላይም የራሱን አሻራ ማሳረፉ አይቀርምና ይህ ጥናትም ይህን ከሥነጽሑፍ ጋር ያለውን ቅርብ ዝምድና ከግምት ውስጥ በማስገባት በዚህ ፍልስፍናዊ እሳቤ ዋነኛ የመተንተኛ መነጽርነት የሚጠቀም ይሆናል ይህ የነገረህላዌ ፍልስፍና ከሥነጽሑፍ ጋር ያለውን ጥብቅ ቁርኝት በተመለከተ ደግሞ ከላይ በጥቂቱ ጠቆም ያደረኩት የህልውና ጥያቄ በየትኛውም ሥፍራ በማንኛውም ዘመን ሊነሳ የሚችል ሰብዓዊ እና ማህበራዊ ጥያቄ በመሆኑ የትኛውም ህልው ሥርዓት ከዚህ አይነቱ የአስተሳሰብ ዘይቤ ውጭ ሊሆን አይችልም የሚለው የቴዎድሮስ ሐተታ በሚገባ ያጠነክረዋል ሁሉንም የሰው ልጆች የህልውና መልኮች አንድ በአንድ ለመዘርዘር አስቸጋሪ ቢሆንም አብዛኛዎቹ የፍልስፍናው አራማጆች ደጋግመው ከሚያነሷቸው እና ከተለመዱት የነገረ ህላዌ ጭብጦች መካከል ግን ከማንነት የቀደመ ህልውና ከር ዐር በር ነጻነት ምርጫ እና ኃላፊነት የቬዐጠ ርከዐርፀ በአ ክሀዐከከከ ሁኔታዊነት ሸህጩጨበዐበ ጭንቀት ስጋት እና ቀቢጸተስፋ ለበእከ በ ሀባ ባይታወርነት ልበከዐበ ነ ምንምነት። የሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ነው የህይወት ማሳያነቱ እና የይዘት ትኩረቱ ስፋት ደግሞ ይህን ዘውግ ለበርካታ ጥናቶች ማሄጃነት ተመራጭ እንዲሆን ያደርገዋል የሚል እምነትም አለኝ ለዚህም ነው ወደዚሁ ዘውግ ማዘንበሌ ይህ ከሥነ ጽሑፍ አብራክ የተወለደ የረጅም ልቦለድ ጥበብ በየዘመኑ የሚከሰቱ የሰው ልጆችን ፈርጀ ብዙ ጉዳዮች መነሻ በማድረግ ይቀነበባል የሚከየንበት ስልትም ቢሆን በደራሲው ዕውቀት ልምድ ችሎታ እና ፍልስፍና ልክ በመሆኑ ቀደም ብየ እንደጠቆምኩት ይህንን ዘውግ በቅርጽም ሆነ በይዘት በብዙ መልኩ ለምርምር ክፍት ሆኖ እናገኘዋለን በዚህ ጥናት ለምርመር የተመረጠው የደራሲ አዳም ረታ ሥራ የሆነው እና በቅርቡ ለንባብ የበቃው ሰፉ ረዐዐ ፍም የተስኘው ረጅም ልቦለድ ሲሆን ጥናቱም በዚሁ ልቦለድ ውስጥ የተንፀባረቁ ልዩልዩ የሰው ልጆችን ህልውናዊ ገፅታዎች በመፈተሽ ከላይ በተቀመጠው የነገረ ህላዌ ፍልስፍና ጽንሰሃሳብ መሠረት ተንትኖ ለማሳየት ብሎም ልቦለዱ ከዚሁ ከነገረህላዌዊ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት ለመግለጥ አልሞ የተነሳ ነው በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት እና ሌሎችም ተጨማሪ የነገረህላዊ ጭብጦች መካከል በልቦለዱ ውስጥ የቀረቡት ገናን ጭብጦች የትኞቹ እንደሆኑ የቀረቡበት ስልት ምን እንደሚመስል ብሎም እርስ በእርስ ያላቸው ዝምድን ምን እንደሚመስል ይዳስሳል የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት አንዳንድ የአማርኛ ሥነጽሑፍ ሥራዎች በተለይ ደግሞ ረጅም እና አጭር ልቦለዶች ከነገረሀላዌ ንድፈ ሃሳብ አንፃር በተለያዩ ጊዜያት እና በተለያዩ አካላት አማካኝነት ከዚህ ጥናት መካሄድ በፊት እንደተተነተኑ አጥሂፒው ባደረገው የቀደምት ጥናቶች ክለሳ አረጋግጧል በዚህም መሰረት ከዚህ ቀድሞ በአማርኛ ልቦለድ ላይ ከተካሄዱ የህልውናዊነት ጥናቶች መካከል የመሰለች ተሻገር በአለማየሁ ገሳጋይ ቀፅሪጎ እና ረሂሥ ልቦለዶች የቴዎድሮስ ገብሬ በፉፇርረ ጳዕ መቃሇሀረ ዳደፍረኃ ዖሥራሮዕ እና ዕሌድማዕ ፃፃረ የአክሊሉ ደሳለኝ በተመረጡ የአዳም ረታ ሥራዎች ራጫቃሎ ሌጴጳሃጨጳ ፅዕፊዕ ዕልደዳፓ ዖያዳያዐቻ ፖሥሪ ይሮቻ መዎሷሦ እና ኋመሪይቴ እንዲሁም የፀደይ ወንድሙ ሀጋዐዐዐሃገ በፉረ ኋዕ መቃዘረ ሕጴድማዕ ያሸሃና ጳኋጳኖ ሃራጫ ቃሎቻ ላይ የተካሄዱ ጥናቶች ይጠቀሳሉ በእነዚህ የአማርኛ የድርሰት ሥራዎች ላይ ይህን መሠል ህልውና ተኮር ጥናት መካሄዱ በእርግጥም ይህ የነገረህላዌዊ ንድፈ ሃሳብ ለአማርኛ ሥነጽሑፍ ዘርፍ እንግዳ ጉዳይ እንዳልሆነ እና ከዘርፉ ጋር ያለውን ዝምድናም ማሳያ ነው ማለት ይቻላል ከዚሁ ጋር በተያያዘ መልኩ በዚህ የሂስ መነፅርነት የደራሲ አዳም ረታ ቀደምት ሌሎች ሥራዎች ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ከአንድም ሁለት ጊዜ መተንተናቸው የደራሲው ሥራዎች ለነገረህላዌ ፍልስፍና ያላቸውን የበለጠ ቅርበት ሌላው አመላካች ጉዳይ ነው በዚህ መሰረት የዚሁ ደራሲ ሥራ የሆነው እና ለዚህ ጥናት የተመረጠው ለፉ ሪዐሃሪ ረጅም ልቦለድም ልዩልዩ ሰብዓዊ እና የህልውና ጉዳዮችን አቀናጅቶ የያዘ ሥራ መሆኑን አጥፒው ባደረገው ጥልቅ ንባብ አስተውሏል ፍ ረጅም ልቦለድ ምንም እንኳን ከሰውልጅ የህልውና ፍልስፍና ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እና ለምርምር ክፍት ቢሆንም እስከ አሁን ግን ምንም አይነት ጥናት እና ምርምር ያልተካሄደበት ወይም ደግሞ በየትኛውም አይነት የሂሳዊ ትንታኔ መነፅር ያልታየ ረቂቅ ሥራ ሆኖ የቆየ ስለመሆኑ የዚህ ጥናት አጠፒ ባደረገው ዳሰሳ ማረጋገጥ ችሏል ስለሆነም ይህን የተለያዩ ሰብዓዊ ጉዳዮች ማህደር የሆነ ልቦለዳዊ ሥራ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመተንተን ራሱን የልቦለድ አሃዱን ከሰው ልጅ የህልውና ፍልስፍና ጋር ያለውን ቀጥተኛ ግንኙነት አጉልቶ ለማሳየት መፈለግ እና በዚህ ልቦለድ ናሙናነት ደግሞ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ከህልውና ፍልስፍና ጋር ያለውን ተዛምዶ ለመግለጥ አብዝቶ መሻት ዋነኛው አነሳሽ ምክንያት ነው ጥናቱ የሚመልሳቸው ጥያቄዎች የዚህ ጥናት አብይ ጥያቄ ለምርምር የተመረጠው ጸፍ ፎዐጩ ረጅም ልቦለድ ከነገረህሳዌ ፍልስፍና ጋር ምን አይነት ግንኙነት አለው። የጥናቱ ዓላማዎች የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ ለምርምር የተመረጠው የአዳም ረታ ለፍ ፎዐሃሪ ረጅም ልቦለድ ከነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት መመርመር እና ማሳየት ነው ይህን አብይ ዓላማ ለማሳካት የሚያስችሉ የጥናቱ ዝርዝር ዓላማዎች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው በልቦለዱ ውስጥ የቀረቡት ገናን የነገረሀላዊ ጭብጦች የትኞቹ እንደሆኑ መፈከር በልቦለዱ ውስጥ የቀረቡት የነገረሀህሳላዌ ጭብጦች መነሻቸው ወይም መሠረታቸው ምን እነደሆነ ማብራራት በልቦለዱ ውስጥ የቀረቡት የነገረሀላዌ ጭብጦች የተገለፁበትን ስልት መመርመር በልቦለዱ ውስጥ የቀረቡትን የነገረህላዌ ጭብጦች የእርስ በእርስ ተዛምዶ ተንትኖ ማሳየት የጥናቱ ፋይዳ ይህ ጥናት ለምርምር በተመረጠው የአዳም ረታ ጸፉ ሪርዐወጋ ረጅም ልቦለድ ውስጥ የተንጸባረቁ የህልውናዊነት ጭብጦችን ለይቶ በማውጣት ተንትኖ የማሳየት እና ከነገረህሳዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት የመግለጥ አብይ ዓላማን አንግቦ የተነሳ በመሆኑ የሚከተሉት ጠቀሜታዎች እና ተጠቃሚዎች ይኖሩታል የልቦለዱን ሐተታ ወይም ጭብጥ ከነገረህላዌ ንድፈሃሳብ አንፃር በመተንተን እና በመግለጥ ልቦለዱ በዚህ ጥናት ለሚነሱት የህልውናዊነት ጭብጦች እና መሰል ሰብዓዊ ጉዳዮች ማህደር መሆኑን በመጠቆም እንዲሁም አንዳች ቁምነገር ያዘለ መሆኑን በማመላከት በሌሎች ተመራማሪዎች ዘንድ የተሻለ ዕይታ እንዲኖረው ያደርጋል ይኸውም ልቦለዱን ሌሎች ተመራማሪዎች ይህ ጥናት ባላየበት አቅጣጫ እንዲፈትሹት በማነቃቃት በአንድ በኩል እራሱ ልቦለዱ ለሌሎች የጥናት እና ምርምር መስኮች ክፍት መድረክ እንደሆነ ጥቆማ ይሰጣል በሌላ አንጻር እንዲመረመር በር ይከፍታል በሌላ በኩል ደግሞ ለተመራማሪዎች እንደ መነሻ ወይም መንደርደሪያ በመሆን ያገለግላል ማለት ነው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ንባብን ብሎም አጠቃላይ ዘርፉን ለሚያሳድጉ እና በተመሳሳይ መልኩ ለሚሠሩ ሌሎች ጥናቶች እንደማነቃቂያ ከመሆኑም ባሻገር በዘርፉ የእውቀት መስክ ላይ አንዳች ቁም ነገራዊ አሻራውንም በማሳረፍ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ዘርፍ እና የአማርኛ ሥነ ጽፋዊ ጥናት እድገት አንድ እርምጃ ከፍ እንዲል የራሱ የሆነ ትልቅ እና አዎንታዊ የሆነ ሚና ይኖረዋል ተደራሲያን ልቦለዱን በዚህ ጥናት መነሻነት ደጋግመው እንዲያነቡት እና እንዲያጣጥሙት በማድረግ አንድም የልቦለድ አሃዱን ተነባቢነት ከፍ ያደርጋል አንድም ደግሞ በልቦለዱ ብሎም በሥነ ጽሑፍ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ እና መረዳት በእጅጉ ይጨምራል ተብሎ ይታመናል በአጠቃላይ ይህ ጥናት ለሌሎች ተመራማሪዎች ይህን መሰል የጥናት አቅጣጫን የመጠቆም ለደራሲያን ተጨማሪ የይዘት ትኩረትን የማስተዋወቅ ለተደራሲያን የሥነ ጽሑፋዊ ግንዛቤ ማዳበሪያ የመሆን እንዲሁም ለሥነ ጽሑፍ እና ለሥነ ጽሑፋዊ ጥናት ዘርፎች ተጨማሪ የመረጃ ማዕከል የመሆን አይነተኛ አስተዋጽኦ አለው የሜል ጽኑ እምነት አለኝ የጥናቱ ገደብ እና ውስንነት ይህ ጥናት በዋናነት ለምርምር የተመረጠው ጸፉ ረጅም ልቦለድ ከነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት በመርመር በዚህ ናሙናነት ደግሞ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ከዚሁ የህልውና ፍልስፍና ጋር ያለውን ተዛሞዶ ለመግለጥ የሚሞክር ይሆናል በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ለምርምር በተመረጠው ረጅም ልቦለድ ውስጥ ተመላልሰው የሚከሰቱ ልዩ ልዩ የህልውና ገጽታዎች የነገረህላዌ ጭብጦች እነማን እንደሆኑ እነዚህ ጭብጦች ሪዐዐርናዐዐሀ እንዴት ባለ ስልት እንደቀረቡ መነሻ ምንጫቸው ምን እንደሆነ እና እርስ በእርስ ያላቸው ዝምድና ምን እንደሚመስል ይፈትሻል እነዚህን ጉዳዮች የነገረህላዊ ጭብጦች ለመፈተሽ ደግሞ የእውኑ አለም ነጸብራቅ የሆኑትን የገፀባህርያትን ህላዌ በጥልቀት እና በስፋት መቃኘትን ይጠይቃል ስለሆነም የገፀባህርያትን ህላዌ በተለያዩ አቅጣጫዎች በውል ለመቃኘት ያስችል ዘንድ ከበርካታ የሥነጽሑፍ ዘርፎች መካከል የአማርኛ ረጅም ልቦለድ ዘውግን ምርጫው አድርጓል ምክንያቱ ደግሞ ቀደም ሲል በጥናቱ ዳራ ላይ እንደተጠቆመው የእውኑን ዓለም ሰዎች ህላዌ በተመሳስሎ በመቅረፅ እና በስፋት በማሳየት ረገድ ከሌሎች የሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ይልቅ ልቦለድ በተለይም ደግሞ ረጅም ልቦለድ ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ የዚህ ጥናት አጥፒ በጽኑ ያምናልና ነው በዚህ መሠረት ይህ የምርምር ሥራ በዚሁ በረጅም ልቦለድ ዘውግ ላይ ብቻ በመወሰን ከበርካታ የአማርኛ ረጅም ልቦለዶች መካከል ደግሞ ጥናቱ አንግቦት የተነሳውን ዋነኛ ጉዳይ በተሻለ ያሳያል ተብሎ በታመነበት እና በ ዓም ለንባብ በበቃው የደራሲ አዳም ረታጸጳፉ ረጅም ልቦለድ ላይ ብቻ ትኩረቱን አሳርፏል ይህ ረጅም ልቦለድ ከዚህ አቀስድሞ ምንም አይነት ጥናት እና ምርምር ያልተካሄደበት ከመሆኑም በላይ ለዚህ ጥናት ዐውድ በይበልጥ አመቺ ሆኖ በመገኘቱ ጥናቱ በዚሁ ልቦለድ ላይ የተገደበ ሆኗል በሌላ አገላለጽ ሐፉ ሪዐሪ ረጅም ልቦለድ በዚህ ጥናት ዓብይ ጉዳይ አንጻርነት ወይም ደራሲው በዚሁ ረጅም ልቦለድ ውስጥ በጭብጥነት ባነሳቸው ልዩ ልዩ ህልውናዊ ፅንሰሃሳቦች እና ማህበራዊ እውነታዎች መሠረትነት የዚህ ጥናት ብቸኛ ምርጫ ሆኗል ማለት ነው እናም በዚህ ጥናት ውስጥ ለፍ ሪፎዐሃጋ ረጅም ልቦለድ የሚያትታቸውን ህልውናዊ መልኮች በነገረህላዌ ፍልስፍና ዋነኛ ማናበቢያነት በጥልቅ እና በተደጋጋሚ ንባብ በመፈተሽ ልዩ ልዩ የነገረሀላዌዊ ጭብጦች ተለይተው እና ተተንትነው ይቀርቡበታል ከዚህ አንጻር ደግሞ በዚህ ጥናት ውስጥ ለምርምር ለተመረጠው አፍ ረጅም ልቦለድ መተርጎሚያነት የሚውለው ንድፈሃሳባዊ አቅጣጫ የነገረህላዌ ፍልስፍና ርአበክጠ ይሆናል ማለት ነው ምክንያቱ ደግሞ ጥናቱ ለሜያነሳቸው ልዩ ልዩ የህልውናዊነት ጭብጦች መከሰቻቸው ይኸው የሰው ልጆች የህላዌ ፍልስፍና በመሆኑ እና የሚመዘዙትም ከዚሁ ፍልስፍና ስለሆነ በዚህ ፍልስፍዊ ንድፈሃሳብ መነፅርነት በጭብጦቹ ፍካሬ ላይ ያነጠጥራል የአንድን ልቦለድ ጭብጥ ለመተንተን ሲታሰብ በልቦለዱ ኪናዊ እሴት መታገጊያነት በርካታ ማህበረ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ማንሳት ይቻል ነበር ምንም እንኳን የዘመኑን እውነታ ቸል ብሎ በልቦለድ ኪናዊ እሴት ላይ ብቻ የሚያተኩር ጥናት ሙሉ ባይሆንም ቴዎድሮስ ይህ ጥናት ግን ለምርምር ማሄጃነት በተመረጠው ልቦለድ ውስጥ የተንጸባረቁ እና ልቦለዱ በተከየነበት ዘመን የሚቀነቀኑ ሌሎች ማህበራዊ ፖለቲካዊ ሥነልቦናዊ እና መሰል ጉዳዮችን አጉልቶ ከማሳየት ወይም የልቦለዱን ማህበረፖለቲካዊ ፋይዳ ከመመርመር ይልቅ በልቦለዱ ኪናዊ እሴት ላይ ማለትም ልቦለዱ በሚያትታቸው ህልውናዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ የተገደበ ሆኗል በሌላ አባባል እነዚህን ቀደም ሲል የተጠቆሙትን ዝርዝር ጉዳዮች ወይም የልቦለዱን ማህበረፖለቲካዊ ፋይዳ በግልጽ እና በስፋት ማሳየት ሳይቻል ቀርቷል ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ልቦለዱን ለግል ትርጓሜ ማጋለጥ እንዳይሆን በመስጋት ነው ታዲያ ይህ ጉዳይ ደግሞ የዚህ ጥናት የመጀመሪው ውሱንነት ተደርጎ ሊወሰድ ይችሳላል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ይህ ጥናት በአንድ ንድፈ ሃሳብ በነገረህላዌ ፍልስፍና ላይ ብቻ የተወሰነ እንደሆነ ከፍ ሲል ተገልጧል ይህ ደግሞ ተገቢነቱ እምብዛም ስለመሆኑ ቴዎድሮስ እንዲህ ያስነብቡናል በአንድ ፍጹም ነጠላ ንድፈ ሐሳብ ላይ ብቻ ተወስኖ ሥነ ጽሑፋዊ ምርምርን ለማካሄድ መሞከር ማለት በሥነ ጽሁፋዊ ትችት እና ንድፈ ሐሳብ ውስጥ ዘወትር ለሜወገዙ ሁለት ሕጸጾችን ከልክ ያለፈ የቆንጻይነት ሕጸጽ እና ቴክስትን የንድፈ ሐሳብ ባሪያ የማድረግ ሕጸጽ ለመፈፀም መፍቀድ ነው የሜሆነው ቢሆንም ይህ ጥናት ግን ለተመረጠው ቴክስት ማናበቢያነት ይሆኑ ዘንድ ሌሎች ተጨማሪ ንድፈ ሃሳቦችን አይጠቀምም ምክንያቱ ደግሞ አንደኛ ከላይ እንደተነሳው ለማናቢያነት የተመረጠው ብቸኛ ፍልስፍናዊ ንድፈሃሳብ በጥናቱ ውስጥ በዋናነት ከሚነሱት መሠረታዊ ጉዳዮች ጋር ካለው የጠበቀ ቁርኝት ወይም ከጥናቱ ዓላማ አንጻር ሲሆን ሌላው እና ሁለተኛው ደግሞ አጥሂው ሌሎችን ተጨማሪ ንድፈሃሳቦች እንዳስፈላጊነቱ ገርቶ እና አላምዶ በዚህ ጥናት ውስጥ ለመጠቀም አስቦ የነበረ ቢሆንም ካጋጠመው የጊዜ ውሱንነት አንጻር ይህን ማድረግ ሳይችል ቀርቷል ይህ ደግሞ ሌላው እና ሁተኛው የዚህ ጥናት ውሱንነት ነው ሪ። ዐዐርናዐዐሀ የጥናቱ ሥነዘዴ በዚህ ንዑስ ክፍል ውስጥ ደግሞ ረጅም ልቦለዱ የተመረጠበት መመዘኛ በጥናቱ ውስጥ መረጃ ለማሰባሰብ የሚረዱ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች የጥናቱ ዘዴ ስልት እና የመረጃ አተናተን ስልት እና ሂደት የሚሉት ጉዳዮች ይቀርቡበታል ረጅም ልቦለዱ የተመረጠበት መመዘኛ ይህ ጥናት በዋናነት ይዞት የተነሳው ዓብይ ጉዳይ የህልውናዊነት ጭብጦች ለጥናት በተመረጠው ረጅም ልቦለድ ውስጥ ያላቸውን የተሰጣቸውን ቦታ በመፈተሽ ልቦለዱ ከነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት መመርመር እና በዚህ ናሙናነት ደግሞ የአማርኛ ሥነጽሑፍ ከዚህ የህልውና ፍልስፍና ጋር ያለውን ዝምድና መግለጥ ነው በመሆኑም እነዚህ ጭብጦች በስፋት ተንጸባርቀውበታል ተብሎ የታመነበት እና ጭብጦቹንም ለይቶ ለማሳየት አመቺ ይሆናል ተብሎ የታሰበው ፅፉፍ ሪዐሃጋ ረጅም ልቦለድ ሲሆን ይኸውም የጥናቱን ዓላማ መሰረት አድርጎ ተመርጧል ስለዚህ ለዚህ ጥናት ማሄጃነት የተመረጠው ልቦለድ በውስጡ የያዛቸውን ህልውናዊ ይዘቶች መሰረት በማድረግ እነዚህን የህልውና ገጽታዎች ደግሞ ለይቶ እና ተንትኖ ለማሳየት ያስችላል በሜል እምነት በዓላማ ተኮር የንሞና ዘዴ ዞህዌዐከ ጠፀበባ በዉከ የተመረጠ ነው ማለት ነው በሌላ አባባል አጥሂው ይህን ልፉ ረጅም ልቦለድ ባነበበበት ወቅት በተዋቀረባቸው ታሪኮች እና በገፀ ባህርያቱ ኑባሬ ውስጥ ከዚህ አስቀድሞ ካነበባቸው ሌሎች ልቦለዶች በተሻለ ልዩ ልዩ ህልውናዊ ጉዳዮችን አስተውሷል ይሁን እና የዚህ ጥናት አጥፒሂ እስካሁን ድረስ እነዚህን ህልውናዊ ጉዳዮች እና ይህን ልቦለድ በናሙናነት ወስዶ ያጠና አንድም አካል አላገኘም በዚህም ምክንያት እነዚህን ህልውናዊ ጉዳዮች ተንትኖ በጉልህ ለማሳየት ካደረበት ጽኑ ፍላጎት አንጻር ይህን ለማድረግ ይረዳ ዘንድ ደግሞ ለፉ ረጅም ልቦለድን በናሙናነት መርጦታል የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ይህ ጥናት ለትንተናው ወሳኝ የሆኑ መረጃዎችን ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች የሚሰበስብ ሲሆን እነዚህ የመረጃ ምንጮች ደግሞ ለዚህ ጥናት ካላቸው ቅርበት አንጻር በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ተመድበዋል በዚህ መሰረት ለጥናቱ በአይነተኛ ማጠንጠኛነት የተመረጠው የአዳም ረታ ልፍ ረጅም ልቦለድ በቀዳማይ የመረጃ ምንጭነት የሚያገለግል ሲሆን ስለነገረህላዌ ፍልስፍና ጭብጦች እና መሰል ህልውናዊ ፅንሰሃሳቦች የሚያወሱ ሌሎች ልዩልዩ ድርሳናት እና መዛግብት እንዲሁም ከዚህ ጥናት ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተያያዥነት ያላቸው ቀደምት ጥናቶች ደግሞ ካልዓይ የመረጃ ምንጭ ሆነው አገልግለዋል እነዚህን በጽሑፍ የተሰነዱ ቀዳማይ እና ካልዓይ የመረጃ ምንጮች መዛግብት በምንባባዊ የትንታኔ ስልት አማካኝነት በተደጋጋሜ እና በጥልቀት በማንበብ ለጥናቱ ይበጃሉ ተብሎ የታመነባቸው መረጃዎች ሁሉ ተሰብስበዋል እንግዲህ ከዚህ አንጻር በዚህ ጥናት ውስጥ ሥራ ሳይ የሚውለው ምንባባዊ የትንታኔ ስልት ወይም የሰነድ ሀጠከእ ፍተሻ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ሆኗል ማለት ነው የጥናቱ ዘዴ ስልት የሰው ልጆች በህይወት ዘመናቸው ውስጥ ራሳቸውን ለማሻሻል ሲሉ በበርካታ ጉዳዮች ይጠመዳሉ ይለፋሉ ይደክማሉሌ የህልውና ጭብጣዊ ገጽታዎች የሚባሉትም እነዚሁ በሰው ልጅ ህልውና ላይ የተመሰረቱ እና በሰዎች ህላዌ ውስጥ ተመላልሰው የሚመጡ ሁነቶች ናቸው በአለም ላይ ካሉ እና ተፈጥሯዊ ከሆኑ ሌሎች ነገሮች ሁሉ ይልቅ ዋና ጉዳዩን በሰው ልጆች አጠቃላይ የህይወት ገጽታ ላይ በማድረግ የሚታወቀው እንደዚሁም እነዚህን የሰው ልጆች ራስን የማሻሻል ዑደታዊ የሆኑ ከፍተኛ ፍላጎቶች ለመመርመር የበለጠ ምቹ እና ተመራጭ የሚሆነው ንድፈሃሳብ ደግሞ የነገረህላዌ ፍልስፍና ፎበጠ ነው እነዚሁ የተለያዩ የህልውናዊነት ጭብጦችም የሚመዘዙት ከዚሁ የህልውና ፍልስፍና ውስጥ ነው ስለሆነም የህልውናዊነት ጭብጦች በአዳም ረታ ጸፍ ውስጥ የሚል ርዕስ ይዞ የተነሳው ይህ ጥናት ይህንኑ የነገረህላዊ ፍልስፍና በዋና መተንተኛነት በመጠቀም ለጥናት የተመረጠው ልቦለድ በፈጠረው ዓለም ውስጥ የሚኖሩ የሰው ልጅ ወኪል ገፀ ባህርያትን ህልውናዊ ሐተታዎች ለይቶ ተንትኗል የመረጃ አተናተን ስልት እና ሂደት በምርምር ሂደት ውስጥ ናሙና መምረጥ መረጃ መሰብሰብ እና የመረጃ መተንተኛ ዘዴን መወሰን ብቻውን ከግብ እንደማያደርስ በማመን ይህ የህልውናዊነት ጭብጦች በአዳም ረታ ፍ ውስጥ የተሰኘ አይነታዊ ጥናት በሚከተሉት ሂደቶች ውስጥ አልፏል ይህ ጥናት በቅድሚያ ለትንተናው ይበጃሉ ያላቸውን መረጃዎች ሁሉ በቤተመጻሕፍት ውስጥ አሊያም በመረጃነት ተሰንደው የሚገኙ ልዩ ልዩ መዛግብትን በማገላበጥ እና በጥልቀት በማንበብ ከያሉበት አፈላልጎ አሰባስቧል ታዲያ የተሰበሰቡት መረጃዎች ሁሉ ሙሉ በሙሉ ለትንተና ይቀርባሉ ወይም ይተነተናሉ ማለት አይደለምና ይህ ጥናት ላስቀመጠው ግብ ያላቸውን አስፈላጊነት በውል መዝኖ ከተሰበሰቡት መረጃዎች መካከል በጣም ወሳኝነት ያላቸውን ብቻ መርጧል እነዚህ የተመረጡት መረጃዎች ደግሞ ለጥናቱ መተንተኛ ይሆን ዘንድ ከተወሰነው ንድፈሃሳብ ወይም የመተንተኛ ስልት የየነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር በማናበብ እና በማገናዘብ በመልክበመልክ አደራጅቷል በመጨረሻም ግልጽ እና ተጨባጭ በሆነ መንገድ በመተንተን ለመሪ ጥያቄዎቹ ምላሽ ሰጥቷል አንግቦት የተነሳውን ዓላማም ማሳካት ችሏል የምዕራፍ አደረጃጀት ይህ ጥናት በአራት ዋና ዋና ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን ምዕራፍ አንድ የጥናቱን ዳራ የጥናቱን አነሳሽ ምክንያት የጥናቱን የምርምር ጥያቄዎች የጥናቱን ዓላማዎች የጥናቱን ጠቀሜታ ፋይዳ የጥናቱን ወሰን ገደብ እና ውስንነቶች እንዲሁም የጥናቱን ሥነ ዘዴ አካቶ ይዚል ምፅራፍ ሁለት ደግሞ በዋናነት የጥናቱ ማዕከላዊ ጉዳይ የሚተነተንበትን የንድፈ ሃሳባዊ ጽሑፍ ክለሳ እና የቀደምት ጥናቶች ክለሳን ያካተተ ሲሆን በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የነገረሀላዊ ንድፈ ሃሳብ እና የህልውናዊነት ጭብጦች ፅንሰ ሃሳባዊ ትንተና እንደዚሁም የቀደምት ጥናቶች ክለሳ የተካሄደባቸው ንዑሳን ርዕሶች ቀርበውበታል ምፅራፍ ሦስት የህልውናዊነት ጭብጦች ትንተና በፍ ውስጥ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ስር አምስት ንዑሳን ርዕሶች የተነሱ ሲሆን እነዚህም ነጻነት እና ኃላፊነት ኦናነት ሁኔታዊነት የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸ ተስፋ የሚሉት ናቸው ይኸውም ለትንተና በተመረጠው ፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ በተንፀባረቁት የህልውናዊነት ጭብጦች ላይ የተደረገውን ትንታኔ የያዘ ምዕራፍ ነው አራተኛው እና የመጨረሻው ምዕራፍ ደግሞ ከዚህ ምዕራፍ አሰቀድሞ በነበሩት ሦስት ምዕራፎች ውስጥ የተነሱት ጉዳዮች በማጠቃለያ የቀረበበት ክፍል ነው ምዕራፍ ሁለት የተዛማጅ ጽሑፍ ክለሳ የንድፈሃሳባዊ ጽሑፍ ክለሳ ነገረህሀላዌ ስለ ነገረህላዌ አጪበከበ ምንነት ቁርጥ ያለ እና ሁሉን አቀፍ የሆነ ትንታኔ ማግኘት በእጅጉ አስቸጋሪ ነው በርካታ ተመራማሪዎችም ስለዚህ ፍልስፍና ትርጓሜ ውስብስብነት ሲገልጹ ማስተዋል ብርቅ ነገር አይደለም እያንዳንዱ በዚህ የፍልስፍና ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ምሁራን ወይም ተመራማሪዎች እንደሚያገኙት የመረጃ ምንጭ እንዲሁም እንዳላቸው የግንዛቤ የአመለካከት የእምነት የፍልስፍና እና የዕውቀት ልክ በየወቅቱ የተለያዩ ሃሳቦችን ያራምዳሉ ለከነ በዚህ ምክንያት አብዛኛዎቹ ተመራማሪዎች ራሳቸው ስለዚህ ፍልስፍናዊ እሳቤ አንድ አይነት ትርጓሜ እና ታሪክ አለመኖር ያስቀምጣሉ የክጠብበ ይሁን እንጅ ስለዘርፉ የተሰነዘሩት ትርጓሜዎች ሁሉ ሙሉ በሙሉ የተራራቁ እና ምንም ግንኙነት የሌላቸው ናቸው ማለት በፍጹም አይደለም ይልቁንም ተቀራራቢ እና ወደ አንድ አይነት ፅንሰ ሃሳብ የሚመሩ ከመሆናቸውም የተነሳ ነገረሀላዌ በሰው ልጆች ሁለንተናዊ ህይወት ላይ መሰረት ያደረገ የህልውና ፍልስፍና ነው የሚለውን ብያኔ አብዛኛዎቹ ልሂቃን የሚጋሩት እና የሚያራምዱት ሃሳብ ነው ምክንያቱ ደግሞ ይህ የፍልስፍና እሳቤ በእያንዳንዱ ግለሰብ ህልውናዊ ሁኔታ ርዐበዐዘዚርከበ እበርፀ ዐ ካፅ በከህ ሀፀዐበ ስሜት ፀጠዐክበ ድርጊት ጸልርከበ ኃላፊነት ሀፀበከፎከ አስተሳሰብ በከዐህከእ እና በእያንዳንዱ የሰው ልጅ የህልውና ጥያቄ ላይ ያነጣጠረ ፍልስፍናዊ እሳቤ ስለመሆኑ ሁሌም እንደሚስማሙ ልከ ያስረዳሉ በተመሳሳይ መልኩ ቴዎድሮስ ገብሬ የነገረህላዌ ፍልስፍናን አስመልቶ የሚሰነዘሩ ሃሳቦች የተለያዩ ነገር ግን የማይራራቁ መሆናቸውን ገልጸው በዚህ ፍልስፍናዊ እሳቤ ላይ የተሰማሩ ፈላስፋዎችን እና የሚሰነዘሯቸውን የብያኔ ሃሳቦች ተመሳስሉ ያመለክታሉ ያሏቸውን ሦስት ዓበይት ጉዳች ያስቀምጣሉ በዚህ መሠረት የመጀመሪያው ከፍ ሲል እንደተጠቆመው የሁሉም የነገረህላዌ ፈላስፋዎች ማዕከላዊ ጉዳይ የሰው ልጅ መሆኑ ሲሆን በሁለተኛነት የሚያስቀምጡት ደግሞ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ሳቢያ ሰዎች ላጧቸው የጋራ ቁሳዊ እና መንፈሳዊ እሴቶች ምላሽ በሚሆኑ ጉዳዮች እና የወደፊት ዕጣ ፋንታን በመተንበይ ላይ ማተኮራቸው እንደሆነ ያብራራሉ ይኸውም አብዛኛዎቹ የዘርፉ ታላላቅ እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ፈላስፋዎች እና ጸሐፊያን ብቅ ያሉት የሁለተኛውን የዓለም ጦርነት ተከትለው መሆኑ እና በወቅቱ በሥራዎቻቸው ያስተጋቧቸው የነበሩ መልክዕቶች ደግሞ የጦርነቱን ክስተቶች የነበረ መሆኑን ለማመልከት ነው ሌላው እና ሦስተኛው ደግሞ የአብዛኛዎቹ ፈላስፋዎች የጭብጥ ምርጫ መመሳሰል መሆኑን ይገልጣሉሌ ልከቿ ም ቢሆኑ በቁጥር ወስነው አያስቀምጧቸው እንጅ እነዚህን ጉዳዮች ይጋራሉ ክዐቪቢ ዐዐበበከ ደግሞ አጽንኦቱን በህልውና ላይ ያደረገ ፍልስፍና ነው ካሉ በኋላ ህልውና ሲባል ደግሞ ከየትኛውም ረቂቅ እና ከሰው ውጭ ከሆኑ ነገሮች በተቃራኒ በሰው ልጅ ላይ ብቻ የተወሰነ ከመሆኑም ባለፈ ከእያንዳንዱ ሰው ተናጠላዊ ህልውና ላይ ብቻ ያነጣጠረ እንጅ ህብረህልውና እንዳልሆነ እንዲህ በሰፊው ያስነብቡናል ሺሸ ከፀ ፀከቨዐፍፀከሃ ዐሀ። በበ እልልክ ነገረህላዌዊ በግለሰቦች ትክክለኛ ህልውና ላይ ትኩረቱን በማሳረፍ የግለሰብዓዊነትን ገናንነት የሚያቀነቅን ብቸኛ የፍልስፍና መስክ ሊባል ይችላል በግለሰቦች አጠቃላይ ህልውና ላይ በማነጣጠር እና ግለሰብዓዊነትን ዋና ጉዳዩ በማድረግ የሚካሄድ የፍልስፍና ዘርፍ በመሆኑም የትክክለኛ ሰውነት ፍልስፍና ተብሎም ሊጠራ ይችላል በልከ እንግዲህ ይህ የነገረህላዌ ፍልስፍና የግለሰቦችን ነጻነት እና ምርጫ አስፈላጊነት አጉልቶ በማሳየት ለእያንዳንዱ ህልውና ነጻነት እና ምርጫ መከበር ዘብ የሚቆም ነው ማለት እንችላለን እንደዚህ ዘርፍ እሳቤ እያንዳንዱ ሰው ወይም ግለሰብ በህይወቱ ውስጥ የራሱን እድል እራሱ የመወሰን እና የማራመድ እንደዚሁም የህይወት ጎዳናውን በራሱ አቅጣጫ የመምራት አቅምም ሆነ ስልጣን አለው እያንዳንዱ የሰው ልጅ በተፈጥሮው ከሌሎች የተፈጥሮ አካላት በተለየ መልኩ ንቁ እና ፈጣሪ እንደዚሁም ተመራማሪ መሆኑ ለማናችንም የአደባባይ ምስጢር ነው በተቃራሂው ደግሞ ሌሎች የተፈጥሮ አካላት ከሰው ልጅ በተለየ መልኩ ቋሚ እና የማይለወጥ ማንነት ያላቸው ከመሆናቸውም በላይ ማድረግ የሚፈልጉትንም ይሁን የሚከውኑትን ማንኛውንም አይነት ድጊት የመምረጥ ነጻነት እና የራሳቸውን አለም እራሳቸው የመፍጠር ችሎታም ሆነ አቅም የላቸውም ስለዚህ ለነገረህላዌያን ፎአበ ለእነዚህ ሁሉ ጸጋዎች ብቸኛው ባለቤት የሰውልጅ ነው የሚል ዕኑ እምነት አላቸው በአጠቃላይ ነገረህላዌ በሰው ልጅ የህልውና ምርምር ላይ ልዩ ትኩረት ያደረገ እና ሰዎች በቁሳዊው አለም ሃህ ህዘበ ወይም ተፈጥሯዊ አለም ላይ ሲኖሩ እራሳቸውን ለማግኘት አለፍ ሲልም ህላዌያቸውን ለማሻሻል የሚያልፉባቸውን ውጣውረድ መንገዶች የሚያጠና የሚመረምር የኛው ክፍለዘመን የፍልስፍና ጉዞ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል ስለሆነም በቁሳዊው አለም ውስጥ እራስን የመፈለግ እና የማግኘት ወይም የህይወትን ትርጉም የመረዳት ፍልስፍና ነው ተብሎም ሊገለጽ ይችላል ይህ የፍልስፍና መስክ ማንኛውም ሰው በአለም ላይ ሲኖር ከየትኛውም አይነት የህግ የጎሳ ሥርዓት ወይም ማህበረባህላዊ ደንብ አስገዳጅነት አጋዥነት። ስፍር ቁጥር የሌለው ወይም ወሰን የለሽ ነው ነገር ግን እኛ መረዳት ወይም መገንዘብ የምንችለው የተወሰኑትን ብቻ ነው ስለዚህ እንደ አርስቶትላውያን እምነት ከሆነ ህልውና የሚባለው ጉዳይ ዛሬ ሳይ ካለው የግለሰባዊነት ህልውና ጉዳይ ይልቅ የአለምን የተፈጥሮን ህልውና ሁሉ የሚመለከት ነው ማለት ይቻላል በማለት ያትታሉ ታዲያ ከዚህ በተለየ መንገድ በኛው ክፍለዘመን ይኸው የነገረህላዌ ፍልስፍና ርዕዮተዓለሙን በማጥበብ ከአጠቃላዩ የሰው ልጅ የጋርዮሽ ህልውና በላቀ እና በረቀቀ መልኩ በእያንዳንዱ የሰው ልጅ ህላዌ ላይ እያነጣጠረ እና ፊቱን ወደዚሁ ተናጠላዊ ህሳዌ በማዞር ልዩ ልዩ ሰብዓዊ ጉዳዮችን የሚመለከት እሳቤ እየሆነ እንደመጣም ይጠቁማሉሌ ስለዚህ የዘመናችን የነገረህላዊ እሳቤ በዓለም ላይ ከሚገኙ እና እልቆቢስ ከሆኑ ህልው ነገሮች ሁሉ አንዱ ወደሆነው የሰው ልጅ ህላዌ ብሎም ከአጠቃላይ የሰው ልጅ ባህርይ በር ይልቅ ወደ እያንዳንዱ የህይወት ገጽታ ወይም ደግሞ ግለሰባዊ ጉዳይ የትኩረት አቅጣጫውን በማጥበብ ዛሬ ላይ የተለመደ የሰው ልጅ ተናጠላዊ ወይም ግለሰባዊ የህልውና ከዐከሀሟ በር ፍልስፍና ሆኗል ማለት ይቻላል በዚህ ጥናት የመግቢያ ክፍል ላይ እንደተጠቆመው ምንም እንኳን በኛው ክፍለዘመን ገረህላዌ የሚል ስያሜ አግቶ በአዲስ እና በዘመናዊ መንገድ በስፋት ቢቀነቀንም ይህ የህልውና ፍልስፍና ፅንሰሃሳብ ከ እስከ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ጀሞሮ በዘመኑ ታላላቅ ፈላስፋዎች ቅዱሳን እና ትንቢተኞች በእነር እና ኮ አማካኝነት እንደ ፈለቀ ብሎም በተለያዩ ሥራዎች ሲንንጸባረቅ የቆየ ስለመሆኑ ልከ ምስክር ናቸው በዘመኑም ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ልጅ እንደ ትክክለኛ የእውቀት እና የምርምር ባለቤት ተደርጎ የታየበት ወቅት ሲሆን በተለይም ዐርሀ የሰው ልጅ ለውጤታማ እና ትክክለኛ በህከ ዓለማዊ ኑባሬ የራስ ምርምር እና እውቀት ዙበበሀህሃ በ ዚበህ ሊኖረው ግድ ነው የሜል እምነት የነበረው ታላቅ ፈላስፋ ነው በሌላ በኩል ደግሞ የ ተከታይ የሆነው ሾኮከር በርካታ የነገረህሀላዌ ፍሬ ሃሳቦችን ያሰላስል እና በንግግሩ መካከልም የተለያዩ ህልውናዊ ቃላትን አካቶ ይጠቀም የነበረ ሌላው ግንባርቀደም ፈላስፋ ነው ከነዐርርጨ እና ኮር በተጨማሪ ደግሞ ፎሺ ልህሀሸበፀ በተናጠላዊ ህልውና ላይ በማተኮር የሰዎችን ውድቀት ከሃይማኖት መውጣት ሀሀሟ ክቨከጩመ እና የተለያዩ ህልውናዊ እንቅስቃሴዎችን ያራምድ የነበረ ወይም ህልውናዊ አተያይ የነበረው ቀደምት ፈላስፋ ስለመሆኑ ጠቅሰው እንዲያውም በኛው ክፍለዘመን እንደ አዲስ ብቅ ባሉት በእር እና በኋበፔ የነገረህላዌ እሳቤ ውስጥ የልህዐህበፀ ፅንሰሃሳብ በግልጽ እንደሚስተዋል ልረከ ያስረዳሉ እከፎ እና ኗባ ፀህ ነገረሀላዌ የታላቁን የሰው ልጅ እሳቤን ያህል የእድሜ ዘመን ያለው እና በፍልስፍናው በጥበባቱ እንደዚሁም በሥነ ጽሑፉ ዘርፍ የተንጸባረቀ የአስተሳሰብ ዘይቤ ነው በማለት ከ ህበበ ሃሳብ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ሐተታቸውን ያስቀምጣሉ ፐከ በጪ በከ ር። ሀሃርከርከሃ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ በከ ዘርፎች እና ወደሥነ ጽሑፋዊ ቨፎባ ሥነ ማህበረሰብዓዊ መደብ እንደዚሁም ወደ ፆታዊ በ ንድፈሃሳቦች በከበ የትኩረት አቅጣጫውን እያዞረ እና እየተከፋፈለ መጣ ከዚሁ ጋር በተገናኘ የነገረህላዌ ፍልስፍና ወደ ሥነጽሑፍ ንድፈሃሳብነት ሸዘፀዉቫ ከከፀባ እና ማህበራዊ የትችት አንጻርነት ር ርበክዉበ መስክ በመምጣት ተጽዕኖ መፍጠር የጀመረው ደግሞ በዎቹ እና በዎቹ ገደማ በዘ አመካኝነት ነው በማለት ዘህሀከቪበ በዌህ እና ከ ልሃአ የእቭርከጠበንን ሀሳብ ይጋራለ ልከ ደግሞ ለኛው ክፍለዘመን የነገረህላዌ ፍልስፍና የፈር ቀዳጅነት ሚናን ለልዘ እር እና ለህበኮጺሀ ያቀደጀቸዋል ከዚህ ባለፈ ግን ከላይ ካስቀመጧቸው ግንባርቀደም የፍልስፍና አባቶች በኋላ በተለይ በኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ እና በኛው ክፍለዘመን መባቻ አካባቢ እራሳቸውን እንደ ነገረህላዌ ፈላስፋ ይቆጥሩ የነበሩ በርካታ ዘመናዊ ፈላስፋዎች እና ጸሐፊያን በዚሁ የህልውና ፍልስፍና ላይ የየራሳቸውን ትላልቅ አሻራ ጥለው እንዳለፉ ያትታሉ ከእነዚህ መካከል ደግሞ የየክሃዐዐ ሀዕፀሃ ላዐፀ ያሀ ሀገዐወዌሪሀሪገሪ በዚህ የነገረህላዌ ፅንሰሃሳብ ላይ የተመሰረተ ፋናወጊ የሥነጽሑፍ ሥራ ነው ሀዐርህሃ በሥራዎቹ ውስጥ የሰዎችን ግለሰባዊ አመለካከት ሀክከ እና ነጻነት በጥልቀት መርምሮ ያሳየ ዘመናዊ ጸሐፊ እንደሆነም ኮጩፀጠፀሀበፀ በዐ ሀፀበ ን ዋቢ አድርገው ይገልጻሉ ይሁን እንጅ በዋናነት አዲስ መልክ ይዞ ብቅ ያለው ከመጀመሪያው የዓለም ጦርነት በኋላ ሲሆን ታላቅ እምርታ ያሳየው እና ተፅዕኖ መፍጠር የጀመረው ደግሞ የሁለተኛውን የአለም ጦርነት ተከትሎ ነው በወቅቱ በእነዚህ ታላላቅ ጦርነቶች ምክንያት የተከሰቱት ልዩ ልዩ ይዘት ያሳቸው አሰቃቂ የውድመት ክስተቶች በፈጠሩባቸው አካላዊ ማህበራዊ እና ሥነ ልቦናዊ ቀውሶች ሳቢያ የሰውልጆች በገዛ ህልውናቸው እርግጠኞች እንዳይሆኑ እና በየትኛውም ነገር ላይ አመኔታ እንዲያጡ ሆነዋል ሰዎች የተለያዩ መንፈሳዊም ሆኑ ቁሳዊ ሃብቶቻቸውን አጥተውባቸዋልና በራሳቸው ብሎም በፈጣሪያቸው በአምላካቸው የነበራቸው ተስፋ ሁሉ አብሮ ወድሞባቸዋል ምንም የማይሳነው ሁሉን አወቅ የመኖር ምስጢር እና የሰላም አምላክ አድርገው ይቆጥሩት የነበረው ፈጣሪያቸው ከመካከላቸው ተገኝቶ ከዚያ ሁሉ ጥፋት አላዳናቸውም የእርዳታ እጁንም አልዘረጋምና ህልው እንዳልሆነ እና እነርሱም እረዳት አልባ ፍጡራን እንደሆኑ ማሰብ ጀመሩ በዚህ ምክንያትም በህይወታቸው ለደህንነት ስጋት ለእርግጠኛነት እጦት እና ለህላዌ ትርጉም አልባነት በሽታዎች ተጋላጭ ሆኑ እናም ሰዎች በህይወታቸው ውስጥ አዲስ ዋጋ እና ትርጉም መፈለግ ሲጀምሩ ዘመናዊውን የነገረ ህላዌ ፍልስፍና ወደማግኘት እና መተርጎም መጡ ልከ የኛው ክፍለዘመን የነገረህላዌ ፍልስፍና ርአበክጠ የተቃውሞ ድምጽ እና ነጸብራቅ ሆኖ የተጀመረ ንቅናቄ ሲሆን ቀደም ባሉት ጊዜያት የነበረውን ማንኛውንም የእውናዊነት ከከሀ እና መላምታዊ ሀርሀሀሃፀ ፍልስፍና ለመቃወም ሲባል የተጀመረ እንቅስቃሴ ነው ፈለከር እንደ ልከ ትንታኔ በተለይ ደግሞ የዝበ የሄግሊያን ፍልስፍና ያነጣጥር የነበረው ዓለምን እንደ ፈጣሪ ስጦታ እና የሰው ልጆችን ደግሞ ረዳት የሌላቸው የትልቅ ሚስጥራዊ ድራማ ተዋናይ ወይም ገፀ ባህርያት አድረጎ ይቆጥር በነበረው የቁሳውያን እሳቤ ላይ ነበር ይሁን እንጅ ከዚህ አተያይ በተለየ መልኩ ነገረህላዌ የሰዎችን ሁኔታዊ አስተሳሰብ ወይም ግለሰባዊ ህላዌ እና የህላዌ ፍላጎትን የሚያጎላ ፍልስፍናዊ እሳቤ ነው ዘመናዊው የነገረህላዌዊ ፍልስፍና እንደ ፍቅር ወይም ጥልቅ የሆነ የፍቅር ስሜት ጸበ ደስታ ርሃ የውሳኔ ባለቤትነት ወይም ውሳኔ ሰጭነት ዐርዐበከልበ ጭንቀት ህመም በ ተስፋ መቁረጥ እና ሞት የመሳሰሉ የሰው ልጆችን ዋና ዋና የህልውና መልኮችን ቁብ ሳይሰጥ ከቆየው የጥንታዊው ርር ፍልስፍና በተለየ መልኩ እነዚህን ህልውናዊ ጉዳዮች የሚያጎላ ፍልስፍናዊ እሳቤ ነው በሌላ አባባል ይህ ዘመናዊ የህልውና ፍልስፍና በእያንዳንዱ ግለሰብ ሁኔታ በዐከሀ ቪህከዐበ የህልውና የትክክለኛነት እንዲሁም የሁለነንተናዊ ነጻነት ህበኩሼ። እና ባ ፀዐህ ያብራራሉ እንግዲህ ቀደም ብየ እንደጠቆምኩት ይህን የነገረህላዌ ፍልስፍናን አስመልክቶ በተለያዩ አካላት ከዚህ በላይ ባየነው መልኩ ታሪካዊ ዳራው መቀመጡ የዘርፉን ውስብስብነት እና ዘርፈ ብዙነት በጉልህ ከመግለጹም በላይ ዛሬም ድረስ ገና ሊጠና እና ሊመርመር የሚገባው ፍልስፍናዊ የእውቀት መስክ እንደሆነ አይነተኛ ማሳያ ነው ያም ይሁን ይህ ግን ይህ ፍልስፍና ከጥንት ጀምሮ የነበረ እና በተለይ ደግሞ ወደ ኛው እና ኛው ክፍለዘመናት በተለያዩ የኪነጥበብ ሥራዎች በተለይም ደግሞ በሥነጽሑፍ አማካኝነት በዘመናዊ መልክ እንዳንሰራራ ከፍ ሲል ከተቀመጡት መረጃዎች መገንዘብ ይቻላል የዚህን ፍልሥፍና ትክክለኛ ጽንሰሃሳባዊነት ወይም አሁናዊ መልክ በተመለከተ ቴዎድሮስ ገብሬ እነ ሾህጠበን እና ህዕከከ ከእርባህከን ዋቢ አድርገው የነገረ ህላዌ ፍልስፍና በረጅሙ የሰውልጅ የስልጣኔ ታሪክ ውስጥ ከሰው ልጅ ህልውና ጋር ተቆራኝቶ ዛሬን ጭምር የዘለቀ ርዕሰ ጉዳይ እና የአስተሳሰብ ዘይቤ መሆኑን ከጠቀሱ በኋላ ትክክለኛው የነገረ ህላዌ ዘመን ብለው የሚደመድሙት ግን የኛውን ክፍለ ዘመን ነው ስለሆነም አብዛኛዎቹ መረጃዎች ከሚያመለክቱት እና በርካታ ተመራማሪዎችም ከሚያስቀምጡት ፍንጭ አንጻር ይህ የሰው ልጆች የህልውና ፍልስፍና ጥንታዊ መሠረት ያለው እና በኛው እና በኛው ክፍለ ዘመናት ሠፊ ሽፋን የተሰጠው እሳቤ ነው ብሎ መደምደም ይቻላል የነገረህላዌ ፍልስፍና እና ሥነጽሑፍ ቀደም ባሉት ንዑሳን ክፍሎች የነገረ ህላዌን ፍልስፍና ምንነት እና ታሪካዊ እድገት በጥቂቱ ለማየት ሞክረናል ታዲያ በእነዚህ ንዑሳን ክፍሎች ውስጥ ይህ የነገረህሳዌ ፍልስፍና ከሥነጽሑፍ ጠቢባን ጋር የቆየ እና የጠበቀ ግንኙነት እንዳለው በግልጽም ይሁን በህቡዕ ተገልጧል ይህን ማለቴ ያለምክንያት ሳይሆን ይህ የህላዌ ፍልስፍና ከኪነጥበብ በተለይም ደግሞ ከሥነጽሑፍ ጋር ያለውን ዝምድና ለማጠየቅ ነው ይህ የፍልስፍና መስክ እንዲያንሰራራ የሆነውም በኪነጥበብ ጠበብቶች በተለይም ደግሞ በሥነጽሑፍ ባለሙያዎች መሆኑ ለእነዚህ ሁለት ሙያዎች መዛመድ ትልቅ ማሳያ እንደሆነ ልብ ይሷል በእርግጥም የፍልስፍናው ዋና ዋና አራማጆች ፈላስፋዎች ብቻ ሳይሆኑ የሁለቱም ታላላቅ ሙያዎች ማደሪያ ጭምር እንደነበሩ ከፍ ሲል በጥቂቱ ካየናቸው መረጃዎች መገንዘብ ይቻላል አፌ እና ጠ ዩፀዐህ። ስለዚህ አጋጣሚ ብሎ ነገር የለም አንድ ማህበራዊ ክስተት በድንገት ቢከሰት እና እኔን ያሳተፈ ቢሆን ክስተቱ ከውጭ ወይም ከሌላ የመጣ ሊሆን ፈጽሞ አይችልም ጦርነቱን ያንቀሳቀስኩት እኔ ደግሞ የራሴው ጦርነት የእኔ ሀሳብ እና ለእኔ የሚገባ የሆናል ለዚያውም በመጀመሪያ የችግሩ ሰለባ የምሆነው እኔው ነኝ ምክንያቱም ይህ ሁኔታ በታወሰኝ ቁጥር እራሴን ለማጥፋት በመሞከር ወይም እራሴን በመክዳት ነጻ ለመውጣት እሞክራለሁና አንድ ክስተት ትዝ ባለን ጊዜ የሚኖሩን የመጨረሻ አማራጮች እነዚህ ናቸውና ከሁኔታው ለመውጣት ወይም ለማምለጥ ስቸገርም የምመርጠው ይህንኑ ነው ነጻነት እና ኃላፊነት ጥብቅ የሆነ የምክንያት እና ውጤት ትስስር እንዳላቸው ከዚህ በላይ ከሰፈረው የሸዌጩ ሰፊ ትንታኔ መረዳት ይቻላል በነጻነት የምንመርጠው ምርጫ እና የምናስተላልፈው ውሳኔ እንደዚሁም የምንፈጽመው ድርጊት ሁሉ በሌሎች አካላት ዘንድ ባያስጠይቀን እንኳን ከራሳችን ንጹህ ህሊና የተፋታን ለሚመጣውም ተያያዥ ችግር ግንባር ቀደም ተጠቂ እንሆናለን ስለዚህ በህይወታችን ውስጥ እያንዳንዱ በነጻነት የሚከናወን ተግባር ውጤቱ ኃላፊነትን ይጠይቃል እንደ እምነት አለም የተፈጠረችው ከየትኛውም አይነት ልማዳዊ እና ሥነ ምግባራዊ እሴቶች ውጭ ነው ለእነዚህ ሁሉ የነገሮች መፈጠር ምክንያቱ የሰው ልጅ ነውና ተጠያቂውም ራሱ ነው ከእከባ እና ጠ ዞዐህ ም የህልውናዊነት ትልቁ እና ዋናው እሳቤ ጭብጣዊ ገጽታ የሰው ልጅ ነጻነት መሆኑን ጠቅሰው ይህን ነጻነት የሚያገኘው ደግሞ እራሱ ከመረጠው ኃይል ህ ነው ታዲያ የሰው ልጅ ለራሱ ባህርይ ከኋበ ንግግር ሀፀርከ እና ሃሳብ በከሀከ ሁሉ እራሱ ግለሰቡ ኃላፊነት አለበት በማለት የብጩቬን ሃሳብ ይደግፋሉ ስለዚህ ማንኛውም ሰው የራሱን ዓለም የመፍጠር እና የራሱን የህይወት መንገድ የመቀየስ ነጻነት አለው ሰው በራሱ ምንም በርከፀ ነው ማንነቱ የሚወሰነው እራሱ በሚፈጥረው የህይወቱ መልክ ነው እንደ ህልውናዊነት እሳቤም የሰው ልጆች ታሪካዊ ተፈጥሮ ከዘር ከህርጩ የላቸውም ይልቁንም ከሌሎች ፍጡራን ሁሉ በተለየ መልኩ ማንነታቸው በሥነ ህይወታዊ በታሪካዊ እና በባህላዊ ምርጫቸው የሚወሰን እና በራሳቸው የሜፈጠር ነው ለነገረ ህላዌ ልሂቃን ማንኛውም ሰው ያመነበትን ተግባር ሁሉ የመከወን ነጻነት አለው ስለሆነምከምንም ኃይል ተጽዕኖ ውጭ በሆነ መንገድ የራሱን እሴት ራሱ ግለሰቡ መፍጠር ይቻላል እንደ ዚሼዌ አባባል በሰዎች ምርጫ እና ውሳኔ ወይም ደግሞ ነጻነት ውስጥ የፈጣሪ ጣልቃ ገብነት እንኳን ቢሆን መኖር የለበትም ሰዎች የራሳቸውን እሴት እና አለማዊ ህይወት መፍጠር አለባቸው ገከቬ በ በ ነከ ዐር ። ርዐጠፀ ዐ ሀበርፀቪልባከ በ ሀበፀርቪሃ በበጪበፄ ሃ ጩም በበኩላሰው በህይወታችን ውስጥ ለምንወስነው ውሳኔ ዋስትና ማጣት እና በወደፊቱ ህይወታችን ብሩህነት እርግጠኛ አለመሆን ነው በማለት የተስፋ መቁረጥን ትርጓሜ እንደሚያስረግጡት ገበ ያስቀምጣሉ የቀደምት ጥናቶች ክለሳ በዚህ ንዑስ ክፍል ስር የነገረህላዊ የትችት አንጻርን በዋነኛ መነጽርነት በመጠቀም የተለያዩ ህልውናዊ ጭብጦችን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የዳሰሱ እና በአጠቃላይ ከዚህ ጥናት ጋር በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ዝምድና ያላቸው የምርምር ሥራዎች ከዚህ ጥናት ጋር ያላቸውን ተዛምዶ በሚያሳይ መልኩ ቅኝት ተደርጎበታል የነገረህላዌ የትችት አንጻርን ዋነኛ ማዕቀፍ በማድረግ የተለያዩ የህልውናዊነት ጉዳዮችን ለመተንተን የሞከሩ በርካታ የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ጥናቶች አሉ ይሁን እንጅ በዚህ ጥናት በተለይም ደግሞ በዚህ ንዑስ ክፍል ውስጥ ቅኝት የሚደረግባቸው የሃገር ውስጥ ጥናቶች ብቻ ናቸው ምክንያቱም የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ የህልውናዊነት ጭብጦች በፉፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ እንዴት እንደተገለጹ እና ምን አይነት ስፍራ እንደተሰጣቸው በመመርመር በዚህ ልቦለድ ናሙናነት ደግሞ የነገረህላዌ ፍልስፍና ከአማርኛ ሥነጽሑፍ ጋር ያለውን ዝምድና መግለጥ በመሆኑ ነው ስለዚህ በአገር ውስጥ እና በአማርኛ ሥነጽሑፍ ሥራዎች በተካሄዱ ጥናቶች ላይ ትኩረት ማድረጉ የተሻለ እና ተመራጭ ይሆናል በሜል ጽኑ እምነት ቅኝቱ በአራት የአማርኛ ሥነጽሑፍ ጥናቶች ላይ አነጣጥሯል ማለት ነው ታዲያ ይህ መጠነሰፊ ፍልስፍናዊ ንድፈሃሳብ እና ዘርፈብዙ ጭብጣዊ ገጽታዎቹ በሃገር ውስጥም ሆነ በሃገር ውጭ ጥናቶች በተለያዩ ጊዜያት የትኩረት ነጥብ መሆናቸው እነዚህ ህልውናዊ ጉዳዮች ከሥነጽሑፍ ጋር ያላቸውን ቁርኝት በድምቀት ማሳያ መሆኑንም ልብ ይሏል ለዚህ ጥናት በተመረጠው እና የደራሲ አዳም ረታ ሥራ በሆነው ጸፍ ረጅም ልቦለድ ላይ እስካሁን በተደረገ ፍተሻ መሠረት ምንም አይነት ጥናት ያልተካሄደበት መሆኑ ተረጋግጧል በሌሎቹ የደራሲው ሥራዎች ላይም ቢሆን የተካሄዱት ጥናቶች ከዚህ የምርምር ሥራ ጋር ምንም አይነት ዝምድና ከሌላቸው በዚህ ክፍል ውስጥ ክለሳ አይደረግባቸውም በዚህ መሠረት ከዚህ ጥናት ጋር ግንኙነት ያላቸው አራት ጥናቶች ብቻ ተመርጠው ካላቸው ዝምድና ወይም ቅርበት አንጻር በቅደም ተከተል እንደሚከተለው ቀርበዋል በመጀመሪያ ደረጃ ከዚህ ጥናት ጋር በእጅጉ ቀረቤታ ያለው የመሰለች ተሻገር የሰውልጅ ህልውና በቅበላ እና ኩርቢት ድርሰቶች ነገረህላዌ ንባብ የተሰኘው እና በነሃሴ ዓም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ዲግሪ ማሟያነት የቀረበው ጥናት ነው በዚህ ጥናት ውስጥም በርካታ የህልውናዊነት ጭብጦች ለጥናት ለተመረጡት ድርሰቶች ታሥሪ ናሃው ከሚል ድምዳሜ ላይ ተደርሷል ዓላማውም ቢሆን የኸው እንደሆነ በዚሁ ጥናት ውስጥ እንዲህ ተጽፎ አናነባለን የዚህ ጥናት አብይ ዓላማ በአለማየሁ ገላጋይ ቅበላ የድርሰት ስራ ውስጥ የተገለጸው ታሪክ የነገረህላዌ ታሪክ መሆኑን ፈክሮ ያሳያል ገጽ ከዚህ አንጻር በዓላማ አነዳደፍ ከዚህ ጥናት ጋር በተወሰነ መልኩም ቢሆን ልዩነት አለው የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ ለምርምር በተመረጠው የልቦለድ ሥራ ውስጥ የተገለጹ የህልውናዊነት ጭብጦችን ለይቶ በማውጣት እና ተንትኖ በለምርምር ተመረጠው ልቦለድ ከነገረህላዊ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት ማሳየት ሲሆን የመሰለች ጥናት ደግሞ ለምርምር የተመረጠው ጎ ልቦለድ ሙሉ በሙሉ የነገረህላዌ ታሪክ እንደሆነ ለማሳየት ያለመ ነው ለዚህም ነው በሁለታችን መካከል የዓላማ አነዳደፍ ልዩነት አለ ማለቴ የመሰለች ጥናት በደራሲ አለማየሁ ገላጋይ ሁለት የልቦለድ ሥራዎች እና ረሷያ ላይ ምርምር ለማድረግ ወሰኖ የተነሳ ይሁን እንጅ ከዓላማው ላይ የተካተተው ግን አንዱ ማለትም ቀፅጎ የተሰኘው ልቦለድ ብቻ ሆኖ እናነባለን ታዲያ በዚህ አኳኋን ለምርምር የተመረጡት ሁለቱ ልቦለዶች ሆነው ሳለ ዓላማው በአንዱ ልቦለድ ላይ ብቻ መወሰኑ ለምን እንደሆነ አልተገለጠልኝም በዚህ የመሰለች ጥናት ውስጥ ረዚሂ ልቦለድ ለርዕስ ማሟያነት ካልሆነ በስተቀር የጥናቱ አይነተኛ ናሙና አለመሆኑን ያስተውሏል የመሰለች ጥናት ምንም እንኳን ከዚህ በላይ ያስቀመጥኩትን ዋና ዓላማ አንግቦ የተነሳ ቢሆነም ጭንቀት ተስፋ መቁረጥ ነጻነት ከንቱነት ሞት በይታወርነት ትክክለኛነት እና ትክክለኛ አለመሆን እና ክስተት የተሰኙ ስምንት ያህል የህልውናዊ ጭብጣዊ ገጽታዎች ተተንትነውበታል ከዚህ አንጻር የጥናቱ ዓላማ ርዕሰጉዳዩ እና ተተንትኖ የቀረበበት መንገድ ዝምድናው አልታየኝም ምክንያቱም የጥናቱ ትንተና በዓላማው ላይ እንደተቀመጠው የድርሰቶቹን ሙሉ ታሪክ የህልውና ታሪክ መሆኑን ከማሳየት ይልቅ ከህልውናዊነት ጭብጦች ላይ ያነጣጠረ ነውና ማለትም ከፍ ሲል እንዳልኩት ዓላማው የድርሰቶቹን ታሪክ የህልውና ታሪክነት ማሳየት ሆኖ ሳለ የህልውና ጭብጦች መተንተናቸው የተቀመጠውን ዓላማ አሳክቷል ለማለት አያስደፍርም የሚል እምነት አለኝ ከትንተናው ላይም ቢሆን በዚሁ ክፍል ከቀረበው ሐተታ አንጻር በደፈናው ነገረህላዌ ትንተና ተብሎ ከሚቀመጥ ይልቅ የነገረህላዌ ጭብጦች ትንተና በሚል ቢስተካል የተሻለ ይመስለኛል ስለዚህ በአንድ በኩል ከአላማው እና ከቀረቡት ርዕሰነገሮች አንጻር የነገረ ህላዌ ንድፈሃሳብን ከልቦለዶቹ ታሪኮች ጋር ለማዛመድ የተሞከረበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በትንተናው ውስጥ የህልውናዊነት ጭብጦችን መሠረት ያደረገ መሆኑ የሥራውን ወጥነት አጠያያቂ ያደርገዋል ብየ አምናለሁ እንደ ዓላማው ከሆነ ደግሞ ጭብጦቹን በዋናነት ተንትኖ ማሳየት ነበረበት አሊያም እንደዚህ አይነቶቹ ጥቅል ርዕሰነገሮች እና የተነደፉት ዓላማዎች የነገረህላዌ ጭብጦችን ማሳየት መሆኑን በግልጽ ማሳየት ነበረባቸው የሆነው ሆኖ ይህ የመሰለች ጥናት ያታፉመረውፖ ያሥን ጽታፍ ለሃዶቻ ውኃዕዎ ያኋውኖን ሙዝቋጦቻ ማዖ ዖፇረያ ው ብንል እንኳን ከዚህ ጥናት ጋር በሚከተሉት ጉዳዮች ይለያያል ይህ ጥናት በዋናነት አምስት የህልውናዊነት ጭብጦችን የሚያነሳ ሲሆን ከመሰለች ጥናት ጋር የሚጋራው ፓዕፉ መቋረሪምዎ ሠሀወ የተሰኘውን ጭብጥ ነው ከዚህ ባለፈ ግን ሌሎቹ በዚህ ጥናት ውስጥ የተነሱት የርዕይ መነጠቅ ሁኔታዊነት እና ኦናነት የተሰኙት ሦስት ጭብጦች በመሰለች ጥናት ዉስጥ በፍጹም ያልታዩ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ያዳቅትም የሚባለው ጭብጥ ምረጫ ጳናኖ ውዓዕ ጋር በአንድነት በተደበላለቀ መልኩ ተተንትኗል ይሁን እንጅ ነጻነት እና ኃላፊነት ምንም ጊዜ የማይላቀቁ የህላዌ ጭብጦች በመሆናቸው በዚህ ጥናት ውስጥ ከመስለች በተለየ መልኩ በአንድ ላይ ተጣምረው እና ከምርጫ ርከር በተለየ መልኩ በስፋት ተተንትነዋል ምክንያቱም ምረ ጳኖ ውቆሪ ራሳቸውን የቻሉ ሌላ የህልውናዊነት ገጽታዎች እንጅ ከነጻነት ጋር በአንድነት የሚታዩ አይደሉም የሚል እምነት አለኝ ስለሆነም እነዚህ ጉዳዮች ይህን ጥናት ከመሰለች ጥናት የተለየ የሚያደርጉት ዋናዋና ቁምነገሮች ናቸው ከእነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪ ደግሞ ለጥናት ማሄጃነት የተመረጡት የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ናሙና ልቦለዶችም የተለያዩ ናቸው በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የቴዎድሮስ ገብሬ ሪፅ ዳፈፕፈኖሯቿ ያሥን ጽሑታፍፉ በሚል ርዕስ በ ዓም በታተመው መጽሐፍ ውስጥ ካሉት አራት ያህል መጣጥፎች መካከል የአማርኛ የርእይ መነጠቅ ልቦለዶች የሚል ርዕስ የተሰጠው መጣጥፍከዚህ ጥናት ጋር በእጅጉ ይዛመዳል በዚህ የቴዎድሮስ ገብሬ ጥናት ውስጥ እራሳቸው ቴዎድሮስ በአንድ ዘመን ተመሳሳይ ጭብጦችን ይዘው ብቅ ያሉ እና በአማርኛ ሥነጽሑፍ ዘርፍ እምብዛም አቻ የማይገኝላቸው ልሂቃን ሥራዎች ናቸውበሚሏቸው አራት የልቦለድ ሥራዎች ፉፇቀረ ጳፅያ መቃዝሀር ዖሥራጮሮሮዕ ዳደፍረዕ ዳና ጴድማዕ ሃር ውስጥ የተንጸባረቁ የጋራ የህልውና ትራጀዲያዊ ገጽታዎች ማለትም ሞት የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸተስፋ እና ግዞት የተሰኙ ሦስት ጭብጦች ከነገረህላዌ ንድፈሃሳብ አንጻር ተብራርተው ቀርበዋል የቴዎድሮስ ጥናት በአራት ልቦለዶች ላይ ያተኮረ ንጽጽራዊ ጥናት ርዕጠዐከሃ ህነ ሲሆን ይህጥናት ደግሞ በአንድ የልቦለድ ሥራ ላይ ብቻ በመወሰን እና ትኩረቱን በማሳረፍ በተመረጠው ድርሰት ውስጥ የተገለጹ ወይም የተንጸባረቁ የህልውናዊነት ጭብጦችን አጉልቶ ለማሳየት የሚደረግ ጥናት ነው ስለዚህ በዚህ መሰረት የናሙና ምርጫችን የተለያየ ነው ማለት ነው ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በቴዎድሮስ ጥናት ውስጥ ዖርሏይሪመዕጠዎ እና ፇፈጸፖዕፉ በአንድ ላይ ተጣምረው ቀርበዋል እርግጥ ነው የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸተስፋ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎቹም አብዛኛቹ የህልውናዊነት ጭብጦች እርስ በእርሳቸው ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ያላቸው ከመሆናቸውም በላይ አንዱ በሌላው ሳቢያ የሚፈጠሩ ክስተቶች ናቸው ማለት ይቻላል ማለትም እያንዳንዱ የህልውናዊነት ጭብጦች ተዛማጅ እና ተዋላጅ ናቸው ቴዎድሮስ ይህ ከሆነ ታዲያ ሁሉን በአንድ ላይ አቆራኝቶ ማየት ከነጻነት እና ኃላፊነት ውጭ የተለመደ አካሄድ ሆኖ አላገኘሁትም የተለመደ አካሄድ አለመሆን ብቻም አይደለም በእኔ የእምነት እና የእውቀት ልክ የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸተስፋ የተለያዩ እና ለየብቻቸው ተነጣጥለው ሊታዩ የሚሜገባቸው እንደዚሁም ለየራሳቸው መገለጫዎች ያሏቸው ሁለት የተለያዩ የህልውናዊነት ጭብጦች ናቸው ስለሆነም እነዚህ ሁለት የተለያዩ ጉዳዮች በዚህ ጥናት ውስጥ ለየብቻ ተነጣጥለው በስፋት ይተነተናሉ ከዚህ ውጭ ግን በሁለታችን ጥናቶች ውስጥ የተነሳ ወይም የጋራ የሆነ የህልውናዊነት ጭብጥ የለም በዚህ ረገድ በአንጻር ምርጫ እንመሳሰል እንጅ በምናነሳቸው ጭብጦች እንለያያለን ማለት ነው በሦስተኛ ደረጃ ከዚህ ጥናት ጋር የሚዛመደው ደግሞ የአክሊሉ ደሳለኝ ጄአበበበ በ ከፀ ርዌ ርሸ ህቨ ዐ ልበጠ ክቧኗ የተሰኘው እና በ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ዲግሪ መሟያ ይሆን ዘንድ ለእንግሊዝኛ ትምህርት ክፍል በአንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበ ጥናት ነው ይህ ጥናት ከአዳም ረታ ሥራዎች ውስጥ ግራሄ ቃሎቾቻ ረጅም ልቦለድ እና ሌልዛፊሬል ዕኃፊዕ ለሯድፓ ይዳዕቦቻ ታሥሪ ደድቻ መዎሷሥሦ ጳኖ ኋዳመይጭ ቦጐጃቋታሥ የተሰኙት አጫጭር ታሪኮች ላይ የተሰናዳ ሲሆን ይኸውም አዳምን የተጠናወቱትን የነገረህላዌያን ሃሳቦች ፎአሠበከ። የሚል ጥያቄ ፈጥሮብኛል ከዚሁ ጋር በተያያዘ የ በጩ አተያይ ብቸኛ ምርጫ የሆነበት ምክንያትም ቢሆን እንዲሁ ግልጽ አይደለም ከዚህ ባለፈ ግን ለምርምር የተመረጡት ሦስት መጻሕፍት ከ በዌ የነገረህላዌ እሳቤ አንጻር ብቻ በስፋት ተተንትነውበታል ይኸውም ልክ እንደ ቴዎድሮስ ገብሬ መጣጥፍ ሁሉ ትኩረቱን በሦስት ረጃጅም ለቦለዶች ልይ በማድረግ በድርሰቶቹ ገጸ ባህርያት አማካኝነት የተንጸባረቁ የህልውና ጉዳች ር እኗሼበር የተብራሩበት ንጽጽራዊ ጥናት ርዐጠፀከህ ህ ነው ማለት ይቻላል የሆነው ሆኖ በዓላማ እና ርዕሰ ጉዳይ አነዳደፍም ሆነ በአንጻር ምርጫ ይህ ጥናት ከጸደይ ጥናት በእጅጉም ባይሆን የተለያየ ነው የአንጻር ምርጫን በተመለከተ የ ዘጩን አተያይ ጨምሮ የሌሎችንም የነገረህላዌ ልሂቃን ሥራዎች እሳቤ ያካተተ ይሁን እንጅ አጠቃላይ ማዕቀፉ የነገረህላዌ ፍልስፍና መሆኑ ደግሞ ይህ ጥናት ከጸደይ ጥናት ጋር የሚጋራው ጉዳይ ነው ከዚህ ባለፈ ደግሞ ቀደም ብየ እንደጠቆምኩት የጸደይ ጥናት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበ መሆኑም ሌላው ከዚህ ጥናት የሚለየው ዓብይ ጉዳይ ነው ምዕራፍ ሦስት የህልውናዊነት ጭብጦች ትንተና በለልፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ በዚህ ምዕራፍ በምዕራፍ አንድ ስር በተገለጸው የመተንተኛ ወይም የመፈከሪያ ስልት እንደዚሁም በምዕራፍ ሁለት ስር በተደራጁት ንድፈሃሳባዊ ትንታኔዎች መሰረትነት በዚህ ጥናት ለትንታኔ በተመረጠው ጸናፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ የተንጸባረቁ ዋናዋና የህልውናዊነት ጭብጦች ተለይተው እና ተተንትነው የሚቀርቡ ይሆናል ከዚህ በፊት በሁለት ምዕራፎች በተደጋጋሚ እንደተነሳው የዚህ ጥናት መሰረታዊ ዓላማ ለምርምር የተመረጠው ልቦለድ ውስጥ የተገለጹትን የህልውናዊነት ጭብጦች በመለየት እና በመተንተን ልቦለዱ ከነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት መመርመር በመሆኑ ለትንታኔ በተመረጠው ጸፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ያሉትን ገፀ ባህርያት የእውኑ ዓለም ሰዎች ወኪሎች ህልውና በመመርመር ላይ ያነጣጥራል በዚህ ልቦለድ ውስጥ ያሉ ገፀ ባህርያት የየራሳቸውን ህላዌ ለማስቀጠል በግልጽም ሆነ በህቡዕ የሚታትሩ የየራሳቸውን የህይወት ፍልስፍና ተከትለው የሚነጉዱ አሊያም ደግሞ በቤተሰቦቻቸው በአካባቢያቸው ወይም በማህበረሰባቸው ደንብ እና ሥርዓት ውስጥ ሆነው በኗሪ አኗኗሪ ብሂል ውስጥ የሚዋልሉ የሁለት ዓለም የራሳቸው እና የሌሎች ሰዎች የየራሳቸውን ምርጫ እና ውሳኔ ያላስጠበቁ እና በአጋጣሚዎች በተሞላች ህይወት ውስጥ የሚዋኙ ሁሉም ማለት በሚቻል እረገድ ያቀዱትን የተመኙትን ያለሙትን ያላሳኩ በአንዱ ሲሞላ በሌላው ወገን የሚፈስባቸው በመጨረሻም የህይወት በአለም ትርጉም የጠፋባቸው የሰነቁትን ተስፋ የሚያጡ ሆነው ተቀርጸዋል በመሆኑም በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የእነዚህ ገፀ ባህርያት የህላዌ መልኮች በጥልቀት ይተነተናሉ በዚህ ጥናት ለትንተና የተመረጠው ጸፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ጌርሳሞት ዘሪሁን ገለታ ባካፋ እና አቡ ራሚሱ አቡ ቅጽል ስም የሚሉ ስያሜዎች የተሰጧቸው አምስት ዋና ገፀ ባህርያት እና በርካታ ንዑሳን ገፀ ሰዎች የተካተቱበት ሥራ ሲሆን በዚሁ ልቦለድ ውስጥ በዋናነት ተንጸባርቀዋል ተብለው የታመነባቸው አምስት ዋናዋና የህልውናዊነት ጭብጦች ማለትም ነፃነት እና ኃላፊነት ኦናነት ሁኔታዊነት የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸተስፋ የተሰኙ የሰው ልጅ ህልውናዊ ገጽታዎችን በልቦለዱ ውስጥ ባሉ ገፀ ባህርያት በተለይ ደግሞ በእነዚህ በአምስቱ ገፀ ሰዎች ህላዌ ናሙናነት እና ቀደም ሲል እንደተጠቆመው በምዕራፍ ሁለት ላይ የተነሱ ንድፈሃሳባዊ ሐተታዎችን መሰረት በማድረግ ከዚህ ጥናት ጋር ዝምድና ያላቸውን ደግሞ በማምጣት እና በማላመድ በልቦለዱ ታሪክ መንደርደሪያነት ትንታኔው ቀርቧል እነዚህ የህልውናዊነት ጭብጦች ደግሞ እርስ በእርስ ካላቸው ጥብቅ የሆነ ቁርኝት አንጻር ዝምድናቸው የምክንያት እና ውጤት ያህል ቅርበት ያለው ነው ማለት ይቻላል ይህን የህልውናዊነት ጭብጦች ተዛምዶ መደራረብ አስመልክተው ቴዎድሮስ ገብሬ እነዚህ ገጽታዎች አንዱ ከሌላው ይዛመዳሉ ይዋለዳሌ ተዋረዳዊ የሚመስልም ግንኙነት በመሃላቸው አለ በማለት ያብራራሉ በዚህ ጥናት ለናሙና በተመረጠው ፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ያሉት የዋና ገፀ ባህርያት ቁጥር እና በዋናነት የሚነሱት የህልውናዊነት ጭብጦች ቁጥር መመሳሰል ግን አጋጣሚያዊ እንጅ ሌላ አንዳችም ሚስጥር የለውም ስለሆነም ከእነዚህ ዋና ገፀ ባህርያት በተጨማሪ ሌሎች ንዑሳን ገፀ ባህርያትም እንዳስፈላጊነቱ በትንተናው ሂደት ውስጥ ሊካተቱ የሚችሉበት አጋጣሚ ብዙ እንደሚሆን ልብ ይሷል የሆነው ሆኖ በዚህ የትንታኔ ሂደት ደግሞ በዚሁ የጥናቱ የትንተና ምዕራፍ ውስጥ ለሚነሱ ዓበይት ጉዳዮች ማሳያ ይሆናሉ ተብለው የታመነባቸውን ሐተታዎች ከዚሁ ልቦለድ ውስጥ በተለያየ መጠን ቀንጨብ በማድረግ ጭብጦችን በጉልህ ለማሳየት ይሞከራል በዚህ መነሻነት ፃነት እና ኃላፊነት ኦናነት ሁኔታዊነት የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸተስፋ የተሰኙት ዋና ዋና የህልውናዊነት ጭብጦች ከዚህ በታች ባሉት ክፍሎች በቅደም ተከተል ቀርበዋል ነፃነት እና ኃላፊነት ቀደም ሲል ስማቸው ከተዘረዘሩት እና ለትንተና በተመረጠው ረጅም ልቦለድ ውስጥ ካሉት ገፀ ባህርያት መካከል ሁለቱ ዋና ዋና ገፀባህርያት ማለትም ራሚሟሱ እና ጌርሳሞት ለዚህ ክፍል ዋነኛ ማሳያዎች ተደርገው ተወስደዋል ራሚሱ ወይም በቤት ስሙ አቡ በትምህርት አቀባበሉ የተመሰከረለት እና በአካባቢው ዘንድ የት ይደርሳል የተባለለት ልጅ ነው በመጨረሻም ትምህርቱን በእንግሊዝኛ በዲግሪ ቋንቋ ጨርሶ ካገኛት ጋር እየተወዳጀ የመጠጥ እና የጫት ሱሶች ማደሪያ ሆኖ በአስራት ጉትጎታ በአንድ መስሪ ቤት በህዝብ ግንኙነት ሙያ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል ሥራ የገባውም ከፍቅረኛው ከአሥራት ጭቅጭቅ ለመዳን አለፍ ሲል ደግሞ ለሱሱ ማስታገሻ የማሆን ገንዘብ ያገኝ ዘንድ እንጅ የአሠሪ እና ሠራተኛ ህጉ ተመችቶት አይደለም በእርግጥ በእናቱ በኩል ሐኪም በአባቱ በኩል ደግሞ የዩኒቨረሲቲ መምህር ስለሆነ እና በአስተዳደጉ ምንም ሳይጎድልበት ስላደገ ይሆናል ይህን ያህል ወጣ ያለ አስተሳሰብ ያላበሰው ራሚሱ በባህሪው ከቤተሰቦቹ ብቻ ሳይሆ ከሰዎች የተለየ ገፀ ባህርይ ነው ስለሆም እያንዳንዷ ህልውናው በራሱ አና በራሱ ብቻ የተወሰነች ናት በህይወቱ ውስጥ እራሱ የፈለገውን ሁሉ ከማድረግ የሚያስቆመው ምንም ነገር የለም በሌላ በኩል ደግሞ ለቤተሰቦቿ አንድ የሆነችው በተለይ ለአባቷ ጌርሳሞት በተለይም የኛ ክፍል ተማሪ ከሆነች ጊዜ ጀምሮ አብዛኛዎቹን የሰፈሯን ጎረምሶች በከናፍሮቿ ውበት ያንበረከከች ውብ ገፀ ባህሪ ናት በትምህረቷ ደግሞ ገና የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ናት ጌርሳ የደን ልማት ባለሙያዋ እነቷ መግደላዊት አሊያም ደግሞ ሾፌሩ አባቷ አቶ ኮላሴ ከሚፈቅዱላት ውጭ የትም የማትንቀሳቀስ ምንም የማትሠራ እና በተቀመጠላት ሥርዓት ውስጥ ብቻ የምትኖር ገፀ ባህሪ ናት ከዚህ አንጻር በፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ የእነዚህን ሁለት ገጸባህርያት ህላዌ ፀፀፎፀበር የተመለከትን እንደሆነ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የሚቃረን ኑባሬን ሲመሩ እንታዘባለን አንዳቸው በሙሉ ነጻነት አንዳቸው ደግሞ በነጻነት ናፍቆት ለነገረ ህላዌያን ነጻነት ማለት የሰው ልጅ ያለምንም አይነት ማህበራዊም ሆነ መንፈሳዊ ደንብ እና ሥርዓት ጣልቃገብነት በራሱ እምነት እና ፍላጎት የትኛውንም ተግባር የመፈጸም ሂደት ነው ይህን የህልውናዊነት ማዕከላዊ ጭብጥ ደግሞ በዳፉፍ ረጅም ልቦለድ በሁለት መንገድ ማየት ይቻሳል የመጀመሪያው በዚህ አይነት ነጻነት ህልውናቸውን የሚመሩ ሰዎች የሚሄዱበት መንገድ ምን ይመስላል። አዳም ረታ መ ለጌርሳሞት ብልግና ማለት ሃሳብን በግልጽ መናገር መውደድን በነጻነት ማራመድ ነው ይህን ነው ቤተሰቧ ብሎም ማህበረሰቧ ያስተማራት አሁን ይህ ሥርዓት ለእሷ ሰብዓዊ ብቻም ሳይሆን ተፈጠሯዊም ጭምር ነው እንዲህ እንዲሆን መውደድ እና ፍርሃት እንዳዬላቀቁ ፈጣሪ ይሁን ብሎ ያበጀው የፈጠረው ይመስላት ጀምሯል አንድም ገና ከልጅነት ዕድሜዋ ጀምሮ ከእናቷ ጋር በመመላለስ በእምነት ተቋም ቤተክርስቲያን ቀኖና ውስጥ ያደገች በመሆኗ አንድም ደግሞ በተደጋጋሚ እንደተነሳው በልዩ ልዩ ማህብራዊ ሥርዓት ስለታጠረች ሳትወድ በግድ ስሜቷን እንድትደብቅ በእነዚህ ልማዶችም ቂም እንድትቋጥር ተገድዳለች አተኩራ በቅሬታ እና በፀፀት ዐይን አየችው ወንድ ልጅ መሆን ተመኘች የምትፈልገውን ልትጠይቀው ስለምትወደው ነገር ልታወራው የባጥ የቆጡን የሰማይ እና የመሬቱን አንድ እሁድ እለትም በህልሟ እዳየችው አዳም ረታ አሁን ጌርሳ በተፈጥሮ ጣልቃ መግባት ትዳዳለች ይህን ሁሉ ነጻነት የነፈገቻት ተፈጥሮ ትመስላት ጀምራለች እሷ የምታውቀው ፍቅርን ሳይፈራ መግለጽ የመሰለውን በግልጽ መናገር በአጠቃላይ ሙሉ ስሜቱን በነጻነት ማራመድ የሚችለው ወንድ ልጅ መሆኑን ነው ለእንደሷ አይነቷ ሴት የፍቅር ማህደር መሆን እንጅ ስሜትን እነደአትሮንስ ገልጦ ማሳየት ከቶውንም በቀላሉ የሚቻል አይመስላትም ጌርሳሞት ሌላው ሁሉ ቀርቶ አልባሳቶቿ እንኳን በብተሰቦቿ ምርጫ የሚወሰኑ ናቸው ጥሩ ነው ብላ ያሰበችውን እና የመረጠችውን ልብስ ስትለብስ ሐማረሇሃም ጳኖ ሐውመ ትባላለች ይህንን የአባቷን ግልምጫ ፈርታ አሮጌ ልብስ ስትቀይር ደግሞ ደሞዚ ያልተከፈላት ገረድ መስለሽ ሰሜን በክፉ ልታስነሺ ነው ትባላለች ታዲያ የመጨረሻው አማራጪ አበቷ የሚወደውን እና የአባቷ ምርጫ የሆነውን ብቻ መልበስ ትገደዳለች አዳም ረታ ፀ በአጠቃላይ ጌርሳሞት መሆን ያለባትን በሙሉ የሚወስኑት እና ህይወቷንም የምትመራው ቤተሰቦቿ ባስቀመጡላት የአድርጊአትድርጊ መርህ እና ሥርዓት ውስጥ ሆኖ እናገኛለን እያንዳንዱ የህይወት እንቅስቃሴዋ በቤተሰቦቿ የተወሰነላት በመሆኑ ይህንን ደንብ ተላልፋ የሆነ ድርጊት ብትፈጽም እንኳን የሚከተላት የባሰ ቁጣ እና ማስፈራሪያ አለፍ ሲልም ከአቅም በላይ ተንጠራርታ የጨበጠችውን መንጠላጠያ በመበጠስ ከነበረችበት በታች እንድትወረወር የሚጋብዝ ያልተመጣጠነ አጸፋ ይሆናል ከአንድም ሁለት ጊዜ የፍቅር ርዕዩዋን ያጣችውም በዚሁ ምክንያት ነው እንግዲህ እስካሁን እንዳየነው ነጻነት በፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ በሁለት መለኩ ተገልጧል ብሎ መደምደም ይቻላል ወዲህ እንደራሚሱ ወሰን በሌለው ነጻነት ወዲህ ደግሞ እንደ ጌርሳሞት በለከት አልባ የነጻነት ንፍገት ኦናነት ለዚህ ክፍል ብቸኛው ማሳያ ይሆን ዘንድ የተመረጠው ገፀ ባህርይ ራሚሱ ነው ራሚሱ ከዚህ ከፍ ብሎ በ ነጻነት እና ኃላፊነት ክፍል ውስጥ እንዳየነው የገደብ አልባ ነጻነት ባለቤት ነው ይህ ከመጠን ያለፈ ነጻነቱ ደግሞ አድጎ እና ተወሳስቦ ከኦናነት ውስጥ ይጥለዋል በዚህ ክፍል ውስጥም ይህ ጉዳይ እንደሚከተለው በስፋት ተተንትኖ ቀርቧል ኦናነት ከነገረህሳዌ ፍላስፍና አንጻር ሲታይ ከፈጣሪ የጸዳ ማንነትን መገንባት እንደሆነ ገፐዝበ በ ጨዌዌን ጠቅሰው ያብራራሉ በዚህ መሠረት በለልፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ካሉት ገፀ ባህሪያት መካከል ራሚሱ አቡ በዚህ እሳቤ ውስጥ ወድቆ እናስተውላለን ከላይ ባየነው ክፍል ውስጥ በተደጋጋሚ እንደተነሳው ራሚሱ ከልጅነት እስከ እውቀት ድረስ የገደብ አልባ ነጻነት ባለቤት እንደሆነ እንታዘባለን ይህ ወሰን የለሽ ነጻነቱ ደግሞ በስተመጨረሻ ከባዶነት ውስጥ ወስዶ ይጥለዋል ራሚሱ በህይወቱ ውስጥ ተስፋ የሚጥልበት ያግዘኛል ይረዳኛል ብሎ የሚያስበው አንዳችም አምላካዊ ሃይል የለውም ለእሱ ከሁሉም ነገር መሸሻው መደበቂያው የትንባሆ የመጠጥ የጫት እና የወሲብ ሱሶች ናቸው ምንም ያህል በህይወቱ ቢሰላች እና ቢማረር ከአነዚህ ነገሮች ያለፈ ተስፋ የሚጥልበት ልዕለ ተፈጣሮ ሃይል የለም ፈጣሪዎቹ እነሂህ ነገሮች ናቸው እራሱን በእነዚህ ተግባራት ለማግኘት ይኳትናል ከእነዚህ ተግባራት ውጭ ያለው ፍጡር ሁሉ ያስጠላዋል ታዲያ ይህን ጥላቻውን ደግሞ መልሶ በእነዚህ ውስጥ ይፈልጋል በሁሉ ነገር ይበሳጫል ከፈጠረው እግዚአብሔር እስከ ወለደው አባቱ ድረስ ያበሳጩታል በየመሃሉ ያለው ፍጡር እና ቁስ መአት ነው የሚያማርረውን ሁሉ በከፊል የሚረሳው ከወዳጆቹ ጋር ብቻ ሲሆን ነው አዳም ረታ ሪ ወዳጆቹ የተባሉት የሰፈር አብሮ ደጎቹን እነ ገለታ ዘሪሁን እና ባካፋን ነው ይሁን እንጅ አነሱም ቢሆን ከዚህ ሃሳቡ ጨርሰው ከቶውንም አያስጥሉትም እንዲያውም ከፍ እያሉ ሲሄዱ ሁሉም ጌርሳሞትን የየራሳቸው ለማድረግ የእርስ በእርስ ሽኩቻ ውስጥ ይገባሉ አቡ ደግሞ ለጓደኞቹ የሚሰጠው ከሱሶቹ የተረፈውን ጊዜ ብቻ ነው ወደዚች ምድር መጣሉ ያማርረዋል ያበሳጨዋል ይህን ምሬቱን እና ብሶቱን የሚጋራው ከዚህ የቁጣ መዓት ውስጥ የሚያወጣው ምንም ነገር እንደሌለ ያምናልና ተስፋ የሚጥልበት ፈጣሪ እንኳን የለውም እንደ ነገረ ህላዌያን እምነት ኦናነት ተስፋ የሚጣልበት መመኪያ የማሆን ሲቸግር የሚጠየቅ ሲሞላ የሚመሰገን አንዳችም ሃይል እንደሌለ ማመን እና የዚችን አለም ክስተት ሁሉ በገዛ እራስ መጋፈጥ መቻል ነው በ ታዲያ ይህ አይነቱ የህላዌ ሂደት በህይወት ውስጥ ምክንያት አልባም ያደርጋል ራሚሱም የሚመካበት ፈጣሪ የለውምና እንዴት እና ለምን እንደሚኖር አያውቅም ደስ ያለውን ብቻም ሳይሆን ያጋጠመውን ህይወት ነው የሚገፋው የመረጠውን ብቻ ሳይሆን ከፊቱ ያገኘውን ድርጊት ነው የሚፈጽመው አሁን አሁን ነጻነቱ አድጎ እና ተወሳስቦ የህይወት መስመሩ ተጣፍቶበት ግራ ያጋባው ያወዛግበው ይዚል ይህንን ተከትሎም አንዳንዴ በሀይወቱ ውስጥ ጭንቀት እና ስጋት ይጋረጥበት ጀምሯል አንዳንዴ ቁጭ ብዬ ሳስብ የምፈልገውን ሳላደርግ ምናልባት እተቀመጥኩበት ምናልባት እተኛሁበት ምናልባት ቢሮዬ ኩቢክል ውስጥ ተቀምጩ ሳንጋጥጥ ምናልባት የመጀመሪያዬን ቢራ ላጠናቅቅ ቡትሌ ሳጤስ ምናልባት ገና በምርቃና መፍሰስ ስጀምር ምናልባት ሽንቴን ልሸና የሱሪ ዚፔን ስፈታ ምናልባት ሳነጥስ ምናልባት በሹካዬ ጎንጉፔ ያነሳሁት የመጀመሪያ ፓስታ ጉርሻዬ አየር ላይ እያለ ምናልባት አርፌ እተኛሁበት ወይም ዝም ብሎ አሁን ከሩብ ሰዓት በኋላ የምሞት ይመስለኛል እግዜራችሁ የማልማት ብቻ ሳይሆን የማጥፋት ጥበበኛ ነውና ከዚህ ፍርሃት ምን እና ማን እንደሚያድነኝ ግን አለውቅምአዳም ረታ ጋ ኦናነት ከጭንቀት ጋር የተገናኘ ሲሆን ይኸውም የሰው ልጅ በዓለማዊ ህይወቱ ውስጥ የሚረዳው ወይም የሚያግዘው አንዳችም ሃይል በዙሪያው እንደሌለ በሚያምንበት ወቅት የሚፈጠር ስሜት እንደሆነ ከከ ያብራራሉ እንደ ነገረህላዌ ልሂቃን እምነት በገደብ የለሽ ነጻነት ውስጥ ያሉ ሰዎች ከእነርሱ የተሻለ እና ከራሳቸው በላይ የሆነ መሪ የሌላቸው ፍጡራን እንደሆኑ አድርገው እራሳቸውን ይቆጥራሉ በዚህ ሳቢያ ደግሞ ተስፋ ማጣት እና ጭንቀት ውስጥ ይገባሌሉ እንደ ከክ እምነት ለኦናነት የህልውናዊነት ገጽታ ዋና መከሰቻው ይህ አይነቱ ነጻነት ነውና ራሚሱ ፈጣሪን እንደ አጥፊ መንፈስ የጥፋት ሴራ ጠንሳሽ የህሳዌን ሰንሰለት ድንገት የሚበጥስ የሞት መልዓክ አድርጎ ይቆጥራል ከዚህ ባለፈ ግን የፈጣሪን እና የህይወትን መልካም ትስስር ከቶውንም አያምንም በእርሱ ህላዌ ውስጥ ፈጣሪ የሚባል እና እምነት የሚጥልበት ሠሪ መሪ አምላካዊ ሃይል የለውም የገዛ ህላዌውን እሱው እንደሚፈጥረው ያምናልና ዓለማዊ ህይወቱን በሙሉ በራሱ ምሕዋር ውስጥ ይገፋል እንጅ አለኝታ አያስፈልገውም ታዲያ ቆም ብሎ በሚያስብ ጊዜ በህይወት ጉዞው ውስጥ መቼ እና ምን አይነት አደጋ እንደሚገጥመው አያውቅም የህይወት አይቀሬ የአደጋ ዕጣ ሞት እንዳለ ቢያውቅም እንኳን ከዚህ ዕጣ ፋንታ ማን እንደሚያስጥለው እና በምን አይነት ሁኔታ እንደሚመጣበት ግራ ይጋባዋል ተስፋ የሚጥልበት ልዕለ ሃይል የለውምና እራሱው ይጨነቃል እርሱ በመረጠው ነጻነት እና ይህ ነጻነቱ በወለደው ጭንቀት መካከል ሆኖ እንደዚህ ሲያስብ የመኖር ትርጉሙ ተጣፍቶበት ባዶነቱ ትዝ ይለዋል እናም ህላዌውን በኦናነት ይፋለማል ለምን እንደምኖር አላውቅም ምን እንደምፈልግ አልውቅም በቆራጥነት የምጠጣው እና ጫት የምቅመው የመሞቻ ጊዜዬን ለማፋጠን ይመስለኛል ለመስከር የምጠጣው መዝናናቴ መስሎህ ልትቀናብኝ የልብህ ጥርስ የገጠጠ እውነት እውነት እልሃለሁ የምሰራው ስለጠፋኝ ነው አዳም ረታ ከፍ ሲል እንደተጠቆመው ራሚሱ ሁሉንም ነገር ትቶ ራሱን ከሱስ ጋር አላትሟል የአለምን ውስብስብ ጣጣ በመጠጥ ለማምለጥ ይታገላል ለእሱ አምላኩ ተስፋው ይኸው መጠጡ ብቻ ሆኗል የራሚሱ መጠጥ እንደ ማንኛውም ሰው የመጠጥ ናፍቆት የቅንጦት የተዝናኖት መጠጥ አይደለም የእሱ መጠጥ ስሜት እና ጥቅም አልባ ደመነፍሳዊነት ነው እርሱ እንደሚለው የሚሰራውን ወይም የሚፈልገውን በውል አይወቅ እንጅ ምናልባትም መጠጥ ለእርሱ ማምለጫው መደበቂያው ከሚጠላው ማህበራዊ ሱታፌ መሸሸጊያው አድርጎ መርጦታል ከአምላኩ የተሻለ ተስፋ ጥሎበታል ጊዜያዊ የጭንቀት መፈወሻ መድኃኒት ሆኖታል በሌላ በኩል ደግሞ ዘዝዐበ ነሃ ህ ሸን ዋቢ በማድረግ በእርግጥ ኦና በሆኑ ሰዎች ህልውና ውስጥ አምላክ የሚባል ሃይል የለም ስለዚህ ሰዎች ከአምላክ ጋርም ሆነ ከአምላክ ውጭ ሳይሆን አራሳቸውን ከሌላ ማንኛውም ነገር ጋር በማጣበቅ ከአምላክ ዘንድ ይገኛሉ የሚባሉ ቱሩፋቶችን እና መልካም የሚባሉ እሴቶችን ያጣሉ በዚህ ሳቢያ ደግሞ ለባይታወርነት ለከበ ይጋለጣሉ በማለት ያስረዳሉ በዚህ መሠረት እንደ እሳቤ ከሆነ ኦናነት ከባይታወርነት ጋር የተገናኘ ብቻም ሳይሆን ለባየታወርነት አንዱ መከሰቻውም ይኸው ኦናነት ነው ማለት ይቻላል ከዚህ አንጻር ሲታይ ራሚሱ በሃሳብም ይሁን በአጠቃላይ የህይወት ፍልስፍና ከእሱ ጋር የሚራመድ ሰው ይኖራል ብሎ ስለማያምን ብቸኝነትን የህይወት ምርጫው ካደረገ ውሎ አድሯል ቀደም ሲል እንደተነሳው እራሱን ከአምላክ ጋር ብቻ ሳይሆን ከመሰሎቹ ከሰዎችም አርቆ ተክሏል እሱ ማንንም ምንንም አይፈልግም ምክንያቱም በዚች ምድር ላይ ከእሱ ጋር ማንም ምንም አይገጥምም ስለሆነም ሰዎችን የሚጠጋቸው እሱ በሚፈልገው መንገድ ብቻ እንጅ እንደ እርሱ አይነት አሳቤን ስለሚያራምዱ ወይም ደግሞ የህይወት ፍልስፍናው ተጋሪ ስለሆኑ ከቶውንም አይደለም ለምሳሌ አሥራትን ይቀርባታል በሴትነቷ ጌርሳን መቅረብ ይፈልግ ነበር ለመቅረብም ሞክሯል እንዳሰበው ባይሳካለትም እሷንም በሴትነቷ እነ ገለታን ዘሪሁን እና ባካፋን ይቀርባቸው ነበር ህጻን ስለነበር ከዚህ ባለፈ ግን የትኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ለእሱ የሚመጥን አልሆነለትምና በመካከሉ መገኘቱን ይጠላል ይህን ባህሪውን በተመለከተ እንዲህ ሲተረክ እናነባለን በእሱ ፍቺ ሁለት አመታት ካምፓስ እያለ ያጋጠመው የዞረበት ሕዝብ ነው ይሄ አገር አማሃይ ያመልካል የአገራችን ፈጣሪ ፀጉሩን እንዳይረዝም እንዳያጥር አድረጎ የሚስተካከል አጎብዳጅ ነው ከእነዚህ ዜጎች ጋር መኖር እንደመረገም ነው ይላል አዳም ረታ ከዚሁ ጋር በተያያዘ መልኩ ራሚሱ የአገሩን አስተዳደራዊ ሥርዓት ሳይቀር አብዝቶ ይቃወማል በሥራ ሰበብ ሊያገኛቸው ከሚችሉ አካላት አስቀድሞ እራሱን ያሸሻል እራሱን በራሱ ፍልስፍና ብቻ አጥሮ ህይወቱን ለብቻው መኖር ይፈልጋል ከሆነ ከምጠላው ዩንቨርሲቲ ካልጠፋ ትምህርት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ዲግሪዬን ወስጄ በጥበቡ ያታለልኩት ወይም የመሰጥኩት ሰው የለም ምክንያቱም ስራ ሰርቼ አላውቅም እንዴት። በማለት ወንዙ ዳር ደረቅ ጥቁር ድንጋይ ለይ እየበረዳቸው አቅፈውት ተቀመጡ አቶ ባሪያው ማንም እንዳልመጣ ሲረዱ ልጁን በጋቢያቸው እንደጠቀለሉ እየተገላመጡ እያዩ ቤታቸው ገቡአዳም ረታ እንግዲህ የአቶ ኮላሴ ሰዋዊ ህልውና ከዚህ ይጀምራል አቶ ኮላሴ ከቀድሞ ዝርያዎቹ ከዝንጀሮዎች ተለይቶ በአቶ ባሪያው እጅ ስር እንዲያድግ ያደረገውን አጋጣሚ የልቦለዱ ታሪክ እንዲህ ከትቦ ይዚል አቶ ኮላሴ ገና በጨቅላነቱ በአንድ ገደላማ ጫካ ውስጥ እንደ ሌሎቹ ዝንጀሮዎች ሁሉ ከዛፍ ወደ ዛፍ እየዘለለ እና ቅጠሉን እየበላ ህልውናውን የሚገፋ የዱር የእንስሳ ነበር ታዲያ ከዕለታት በአንዱ ቀን ከአንዲት እንስት ዝንጀሮ ተጠግቶ በመገኘቱ በትልቅ ገመሬ ዝንጀሮ ተደብድቦ ቆሞበት ከነበረ ዛፍ ስር ወደሚገኝ ዥረታም ገደል ተወርውሮ እንዲወድቅ ተደረገ በዚህ ጊዜ አሳዳጊው የሆኑት እና በመሃንነት ሳቢያ የልጅ ስስት እድሜያቸውን ሁሉ ያሰቃያቸው አቶ ባሪያው በዙሪያው ባሉት ሌሎች ዝንጀሮዎች ጫጫታ ምክንያት ባጋጣሚ ተጠርተው በመሄድ ከላይ በቀጥታ እንደጠቀስኩት ለሌሎች ሰዎች አንዲት ዘመዳቸው ወልዳ እንደጣለችባቸው በማስወራት ከተጣለበት ገደል አንስተው ወስደው ክርሥትና ካስነሱት በኋላ አሳዳጊህ ነን ሳይሌ እንደ ጥሩ ወሳጅ ሆነው በታላቅ ፍቅር እና እንክብካቤ አሳደጉት በኋላም አሥራ ስምንት አመቱ ላይ እነዚሁ አባቱ እና እናቱ ቤታቸውን አውርሰው በሞት ተለዩት እርሱም በስማቸው እየተጠራ ቤቱን አከራይቶ እና የመንጃ ፈቃዱን አውጥቶ ሰዋዊ ህለውናውን መግፋት ጀመረ እንግዲህ ይህን የአቶ ኮላሴን የሰውነት መነሻ ታሪክ ላዕላይ ጎኑን የተመለከትን እደሆነ በመጀመሪያ ደርጃ እንደየትኛውም የሰው ልጅማሰብ ማገናዘብ የማይችል እናከእንስሳት ወገን የነበረ ፍጡር ነው ይሁን እንጅ ከሰዎች ጋር ከተቀላቀለበት ጊዜ ጀምሮ ሰዋዊ ሁነቶችን መላመድ ብሎም የተለያዩ ሰዋዊ ተግባራትን መፈጸም ጀምሯል ኮላሴን በህይወት ዘመኑ ውስጥ የእንስሳት ዘር ነህ የሚለው ማንም አልነበረም ምክንያቱ ደግሞ ሙሉ ኑባሬው ሠዋዊ ነውና ይህ ሰዋዊ ህልውናው የተቀዳው ደግሞ ካደገባቸው ቤተሰቦቹ ከእነ አቶ ባሪያው እና ምናልባትም በእነርሱ አካባቢ ካለው ማህበረሰብ ውስጥ እንጅ ሲፈጠር አብሮት የተፈጠረ ከቶውንም አይደለም ይኸውም ከነገረህላዌ እሳቤ አንጻር ሲታይ ማንኛውም የሰው ልጅ የሚፈጠረው ወደፊት የሚኖረውን ህልውና ይዞ ሳይሆን ባዶውን ነው ዓለማዊ ህልውናውን የሚፈጥረው እራሱ ግለሰቡ ወደምድር ከተቀላቀለ በኋላ ነው ይህንኑ መንደርደሪያ ጽንሰሃሳብ ይዘን ወደታሪኩ ታህታይ ምስጢራዊ ጉዳይ ስናመራ ደግሞ አቶ ኮላሴ የተወረወረው ከዛፍ ወደ ገደል ብቻ አይደለም የተወረወረው ሰው ካለመሆን ሰው ወደመሆን ከተፈጥሮ ወደ ዓለም ህላዌ ነው በልቦለዱ ውስጥ ከዛፍ ወደ ገደል እንደተወረወረ የተገለጸውም ይህንኑ ህልውናዊ መወርወርን ለማጠየቅ ይመስላል ምክንያቱም የዝንጀሮ ኑባሬ ሙሉ በሙሉ በዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን በምድርም ጭምር ሆኖ ሳለ የክስተቱ ጀርርከሰ መነሻ የሚጀምረው ደግሞ ከዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ነው ስለሆነም ካልጠፋ መልክዓ ምድር ከላይ ዛፍ ወደ ታች በደል እንደተጣለ ተደርጎ በመገለጹ ዛፉ ሰማያዊ ተፈጥሮን ገደሉ ደግሞ ዓለምን ወይም ሥነ ፍጥረትን መወከሉን እንድንገነዘብ ያደርገናል እንደ በዌ እምነት ከሆነ የሰውልጅ ወደ ዓለም የተወረወረ ለልበ ሸከጩነአጠ ህ ከ ሦሃርዘ ፍጡር ነው ኮለሴ ወደ ሰብዓዊ ዓለም ባዶውን የተጣለ እና ሰብዓዊና እንስሳዊ ህልውናን አቀናጅቶ የያዘ ባለ ውህድ ህልውና ነው ሁለመናው ራቁቱን የሆነ በሟል ከታሪኩም ላይ በግልጽ መስፈሩም ያለምክንያት አይደለም ይህንኑ ባዶ ህልውና ለማስተማሰል የቀረበ እንጂ አዎ ኮላሴ የተጣለው ራቁቱን ባዶውን ነበር ሰብዓዊ ካልነበረው የዝንጀሮዎች ህላዌ ወደ አዲስ ማንነት ወደ አዲስ የተቀዳ ህይወት መጥቷልና አሁን ኮለሴ ሰው እንጅ በፍጹም ዝንጀሮ አይደለም ሰውነትን ሰው መሆንንም ይዞት አልተወለደም ከተወለደ በኋላ አገኘው እንጂ ከዚሁ ጋር በተያያዘ መልኩ ይህ ታሪክ የሰውን ልጅ ሳይንሳዊ አመጣጥ ሥነ ህይወታዊ ልዋጤም በግልጽ ያስገነዝበናል የሰው ልጅ ሥነ ህይወታዊ ለውጥ ደግሞ በራሱ ሁኔታዊ ነው እንደ ዘ እምነት ማንኛውም ነጻነት ያለው ሰው እንኳን ቢሆን ህይወቱ የሚቀዳው ከአንድ የተወሰነ አውድ ውስጥ ነው ኑባሬውም አውዳዊ ነውና በሰው ልጅ ሥነ ህይወታዊ ለውጥ ውስጥ ደግሞ ማህበራዊነት አንዱ አካል ነውና በማህበራዊነት ውስጥም እንደዚሁ የጋራ የሆኑ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸው የሚሜያጠያይቅ አይደለም እንደዚህ አይነቶቹ ጉዳዮች ናቸው እንግዲህ የሰው ልጆችን ሁኔታዊ የሚያሰቸው ከዚህ በላይ ካየነው ታሪክ በኋላ አቶ ኮላሴ እንደማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር የተለያዩ ሰብዓዊ ተግባራትን ሲፈጽም እናስተውላለን ይኸውም በሾፌርነት ሙያ ተሰማርቶ ህልውናውን ከማስቀጠልም ባለፈ ሜስት አግብቶ ጌርሳሞትን የሚያክል የማራኪ ከናፍር ባለቤት የሆነች እና እንደዐይኑ የሚሳሳላት ልጅ እንደወለደ ልቦለዱ ያስነብበናል ከዚህ በተጨማሪም የሚወደውን መጽሔት የሚያነብ እና እንደማንኛውም ሰው ስታዲዮም ገብቶ ኳስ ጨዋታ ማየት የሚወድ እና የሚያዘወትር ገፀ ባህሪ ነው አባቴ ስታድዮም መሄድ ብዙ ፍራፍሬ መብላት ብዙ ሰላጣ ያውም ጥሬውን መቆርጠም አንድ ብቸኛ ናሽናል ጂኦግራፊክ መጽሔት ማንበብ እና በተለይ እንጀራ በጎመን ወጥ መብላት ይወድ ነበር አዳም ረታ ህ። እና የተቀበለው ማንነቶች ውህድ ነው የማሜለውን የየክጠበ ን ሃሳብ በድምቀት ያሳያል እንደ ክበበ እምነት አንድ ሰው በዘር በማህበራዊ ማንነት በቀደመ ምርጫ እና በመሳሰሉት ሁኔታዎች ውስጥ እራሱን በመዘፈቅ ቅይጥ የሆነ ህልውናን ይመሰርታልና የኮላሴ ህልውናም እንዲሁ ከእነዚህ ሁሉ ሁነቶች በአንዱ አሊያም በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ እራሱን በመንከር ከሰውነት እና ከእንስሳነት የተዳቀለ ቅይጥ ህልውና የሚመሰርት ገፀባህሪ ሆኖ እናስተውላለን ከዚህ በተጨማሪ በፉ ልቦለድ ውስጥ የምናገኘው ሌላው ሁኔታዊ ገፀባህሪ ደገግሞ ራሚሱ ሆኖ እናገኘዋለን ራሚሱ ወሰን የለሽ ነጻነት ያለው ገፀ ሰብ መሆኑን ከላይ በተደጋጋሚ አንስቻለሁ ነገር ግን ነገረህላዌያን እንደሚሉት የትኛው በነጻነት የሚኖር ሰው ምንም ያህል ነጻነት ቢኖረው ሙሉ በሙሉ ህልውናው ከሌሎች ሰዎች የተለየ ወይም ደግሞ ከሌሎች ሰዎች የአኗኗር አሊያም የህልውና ዘይቤ ተጽዕኖ ፈጽሞ የጸዳ አይደለምና ራሚሟሱም ከሌሎች ማህበረሰቦች የሚጋራቸው ጉዳዮች ጥቂት የሚባሉ አይደሉም በብዙ ጉዳዮች አማካኝነት ከማህበራዊነት ፈጽሞ ማምለጥ እንደማይቻልም በእራሱ አንደበት እንዲህ ይተርካል የግል ልምድን ወደ ማህበራዊ ውይይት ማምጣት የናሙና ህግ ማክበር ብቻ አይደለም አብረን እንዳለን ማሳያም ነው በዛ በኩል በዛች በቅሎ ደረትዎን ነፍተው ቢያልፉ እልዎታለሁ ያቺ የህያ ልጅ የጠጣችው ውሃ የወንዜ ነው የጋጠችው ከፍየሎቸ መንጋ ተጋፍታ ነው ፋንድያዋን እሳት ለኩሸበታለሁ ይሄ አሁን የማወራው ወሬ ደግሞ ወደዱም ጠሉም ሳሩን እኔን ፍየሌን እስዎን በቅሎዋን አባቷን ፈረስን ያያያዘን ናጥራን ነው ሙልጭ አድርገን ካልዋሸን በቀር ከዚህ ጉንጉን አናመልጥም ግን ሞላጫ በዛ አዳም ረታ ከዚህ በላይ ከተቀነጨበው የልቦለዱ ታሪክ የትኛውም ሰው ልጅ አብሮ እስከኖረ ጊዜ ድረስ ህልውናው ሰንሰለታዊ እንደሆነ በግልጽ እንረዳለን እናም ራሚሱ ህልውናውን በነጻነት የሚመራ እና በምንም ቅድመ ሁኔታ የሚገደብ ባይሆንም ኑባሬው ከሌሎች ሰዎች ጋር በአብሮነት ነውና ከሌሎች ጋር የሚጋራው የህላዌ ልምድ እንዳለ እንታዘባለን በየትኛውም ሰው ህላዌ ውስጥ የሚከወኑ ቋሚ ተግባራትን አብሮ ይከውናል ለምሳሌ ሌሎች የሚመገቡት ምግቡ ነው የሚጠጡት መጠጡ ነው የሚኖሩበት መኖሪያው ነው የሚለብሱት ልብሱ ነው ከዚህ አንጻር ደግሞ እሱ የሚለየው በአስተሳሰቡ በፍልስፍናው ወይም ደግሞ ለህይወት በሚሰጠው ትርጓሜ ብቻ ነው ማለት ይቻላል ስለሆነም እነዚህን የሌሎች ማህበረሰቦች የህልውና ልማዶች በሚኖርበት ማህበረሰብ ሥርዓት መሠረት ይፈጽማል ኑባሬውም በእነዚህ ሁነቶች መወሰኑ አይቀርም ግብዳ ግቢ የራሴው ምኝታ ክፍል እናት እና አባቴ የሚሰፍሩልኝ ቀለብ አፌ ውስጥ ደሞ የቁሞ ቀር ሴት የጡት ፍንጭ እንደ አብሲት አረፋ እየፈነዳ ጎዳናዬ ከዚህ አይወጣም አዳም ረታ ቁራሚሱ ምንም እንኳን ከሌሎች በዙሪያው ካሉ ሰዎች በተለየ የራሱን ህላዌ በራሱ የፈጠረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ግን ከእነርሱ ተጽዕኖ ሙሉ በሙሉ ሲያመልጥ አይስተዋልም ልክ እንደሌሎቹ በዙሪያው እንዳሉ ደደቦች እንዳላቸው ማህበረሰቦች ሁሉ እርሱም ለሌሎች ደስታ ሲል ብቻ ማስመሰሉ ፈፅሞ አልቀረም የውሸት ማንነት መገንባቱ ራሚሱ ከአሥራት ጋር የመሰረተው የፍቅር ጓደኝነት ለእርሷ ሲል እንጅ እርሱ ወዶ እና ፈቅዶ እንደዚሁም አምኖበት የገባበት ጉዳይ ከቶውንም አይደለም እንዲያውም በፍቅር ሰበብ መጠቀሚያ ባሪያዋ መሳሪያዋ ሆኗል ታዲያ በዚህ መሠረት የሌሎችን ማስመሰል አጥብቆ የሚያማርረው ራሚሱ ራሱም አስመሳይ ሆኗል ማለት ይቻላል ይህንን አስመሳይነት ደግሞ ምናልባትም በዙሪያው ካሉት እና ቀድሞ ሲታዘባቸው ከነበሩት ሰዎች የወረሰው ነው የቀረችኝ ይህቺ ካንጀቴ የማላፈቅራት ሴትዮ ናት የቀረኝ የማላፈቅረውን የማልወደውን ማስደሰት ነው አዳም ረታ ዐ እንግዲህ ራሚሟሱ ምንም ያህል ነጻ ቢሆንም በህይወቱ ውስጥ በትንሹም ቢሆን አውቆም ይሁን ሳያውቅ የሌሎች ሰዎች ሱታፌ መኖሩን መገንዘብ ይቻላል አሥራት የገቢ ምንጩ የሥራ ዕድሉ ናትና ሳይወድ በግድ እሷን ማስደሰት የዘወትር ተግባሩ ሆኗል ይህን ሳያደርግ ቢቀር ግን ያለምንም ነገር እንደሚቀር ያውቀዋልና አስመሳይነቱን እያወቀ ያስመስላል ሲመስለኝ ለአሥራት ምናልባት ከምናልባትም በላይድብርት መፈወሻ መድሐኒቷ ነኝ ፕሮዛክዋ ነኝ አንዳንዴም የማስታወቂያ ሰሌዳ የሆንኩ ይመስለኛል የእሷን ዳቦ የመሸሽ ነገር ሰፍቶ የአለምን ዳቦ መሸሸ እንዳይሆንብኝ ፈራሁ የአሥራት መሳሪያ ነኝ እኔም አስመስላለሁ አዳም ረታ ከዚህ አንጻር ደግሞ ይህ ገፀ ባህሪ ራሚሱ ነጻ ብቻ ሳይሆን ሁኔታዊም ጭምር ነው ብሎ መደምደም ይቻላል የርእይ መነጠቅ በፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ያሉ ገፀ ባህርያት ከሞላጎደል በተለያየ መጠን የርእይ መነጠቅ ሰለባዎች ሆነው እናገኛቸዋለን ይኸው የርእይ መነጠቅ ደግሞ በዋና ገፀ ባህርያት ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን የልቦለዱን ንዑሳን ገፀ ባህርያት ሁሉ የሚያካልል ነው ማለት ይቻላል በዚህ መሠረት በዚህ ክፍል ውስጥ አምስቱም ዋና ገፀ ባህርያት ማለትም ጌርሳሞት ገለታ ዘሪሁን ባካፋ እና ራሚሱ ለጭብጡ መተርጎሚያነት ተመርጠዋል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ከበርካታ ንዑሳን ገፀ ባህርያት መካከል ቢያንስ ከዋናዎቹ ጋር ቅርብ ዝምድና ያላቸው የጌርሳሞት እናት መግደላዊት የራሚሱ እናት ወሮ መቅረዝ እንዲሁም የገለታ እናት ወሮ ፎርቱና እንዳስፈላጊነቱ እየተጠሩ እንዲህ ሰፊ ትንታኔ ተደርጎባቸዋል በላይኛው ከንፈሩ የላይ ከንፈሯን ሊነካት በከፊል ድፍረት ሲሳብ ተረከዞቿ መሬት ለቀቁ ለመብረር እንደፈለገች ሁሉ ተንጠራርታ ቀረበችው ዳቦዋ እንደ አቃቂ መፍሰስ ጀምራለች በዚህ ስመት ባህር እንዳየች የ የማትዋኝበትን ስመቱ ምድራዊ አልነበረም የገለታን ስም ከግስ ጋር ልትጠራው ትፈልጋለች ቢቁነጠነጥም አፏ አንዲት ሆሄ ሳይወጣው ቃቅቶ ቀረ ከመሀል ከግንቡ አጥር ወዲያ አነፍናፊ እናቷ ጠራቻት ገለታ ቀና አድርጎ ወደ አፉ ሊያቀርባት ሲል ከእጁ ላይ ፊቷ እንደተነነ ሁሉ ጠፋ ገለታ ቆም ብሎ ሁኔታዋን ትንሽ ታዝቦ አንገቱን እንደሰበረ ከንፈሮቹን እየላሰ ወደ ደብዛዛው ጨለማ በቀስታ ሲራመድ ከእሷ እየሸሸ የሚሄደውን የእግሩን እና መሳም ያልደረሰውን የትንፋሹን ዳና በሃዘን ትዝታ እያዳመጠች ያን አስቀያሜ ቀዝቃዛ የብረት በር አንኳኳችአዳም ረታ እንግዲህ የእነዚህ የሁለቱ የመዋደድ ጥመኞች የከንቱ ፍቅር ናፋቂዎች ርእይ መነጠቅ የሚጀምረው ከዚህ ጀምሮ ነው ከአራቱ ጓደኛሞች ከባካፋ ከዘሪሁን ከራሚሱ እና ከገለታ መካከል ጌርሳሞት ገና ስታየው ልቧ በተለየ ይርድለት ሰውነቷ እንደ ተዓምራዊ ኪነተኛ ይንቀጠቀጥለት የስሜት ህዋሷ ሁሉ ይሳሳለት የነበረውን ገለታን ስለፍቅር ማሰብ ከጀመረች ጊዜ አንስቶ ስትመኘው የነበረውን ፍቅሯን በእዝነ ልቦናዋ ወይም በአይነ ህሊናዋ ከማየት እና ከመመኘት ተላቃ አሊያም ደግሞ በቃላት በሐረጋት እና በዓረፍተ ነገሮች ዘርዝራ ከመንገርም በላይ በከናፍራቸው ንክኪ ልታሳየው ለከት በሌለው መሳሟ የስሜቷን ጥልቀት ልታረጋግጥለት የልጅነት ድንበርን መራመደን ለመጀመሪያ ጊዜ ልትገልጥለት ጫፍ በደረሰችበት ቅጽበት በእናቷ ድንገቴ መብረቃዊ ጥሪ በአባቷ ሃይለኛ የማስፈራሪያ ትውስታ አማካኝነት በሰከንዶች ሽርፍራፊ ውስጥ ከንፈሯ ከከንፈሩ ሳይደርስ ሁለቱም ለመገናኘት በስስት በመሳሳብ ላይ ባሉበት አፍታ ሳይገናኙ ሳይነካኩ ለዚያች ቅጽበት ብቻ ሳይሆን ለዘለዓለሙ ተፋቱ ሁለቱም ደርሶ ሆኖ ማየት የናፈቁትን ቀን የቋመጡለትን የስሜት መግነጢሳዊ መዳረሻ በአይን እርግብግቦሽ ፍጥነት ለቀናት ለሳምንታት ለወራት ለዓመታት ብቻም ሳይሆን እስከ መጨረሻዋ የእስትንፋሳቸው ጠብታ ድረስ እንዳይገናኙ ተፈረደባቸው ፍርዳቸውንም ሳይወዱ በግድ እንዲቀበሉ ተገደዱ ይህ በብዙ የስሜት መሳሳብ በአድካሚ እና አስፈሪ የአቀራረብ ስልት በታላቅ የስሜት ስካር የታጀበው ቴያትር መድረክ ላይ ሳይታይ እንደታሰበ ብቻ ቀረ ይኸውም የህልም ትርኢት እንጅ የእውን አልነበረምና ለአንድ ቀን እንኳን ሳይደገም ከነአካቴው ዳግም ላይመለስ ለመጨረሻ ጊዜ ከሠመ እንደ ነገረህላዌ ልሂቃን እምነት ይህ አይነቱ አሳዶ የያዙትን ፈልጎ ያገኙትን የተመኙትን ያለሙትን ወዘተ ሁሉ በአንዳች ምክንያት ድንገት ከእጅ መመንተፍ ካጠገብ ማጣት የምኞት ከንቱ መቅረት የህልም ቅዥት መሆን የሰው ልጆችን የርእይ መነጠቅ ያጎላዋል እንደ ከእ ሃሳብ ሰዎች የህላዌ መሠረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ለማረጋገጥ ወይም ደግሞ የተሻለ እና ውጤታማ ለማድረግ በወቅቱ ካሉበት ቦታ የተሻለ እና ውጤታማ ያደርገኛል ብለው ወዳሰቡት ቦታ በመሰደድ በቦታ እና በጊዜ ልዩነት የተለየ ርእዮትን ሰንቀው ያሳድዳሉ ይፈልጋሉ በዚሁ መሠረት ገለታም ከሚኖርበት አካባቢ አዲስ አበባ ታቦት ማደሪያ አገር ለቆ መገለማመጥ መጠራጠር እና መናናቅ ባለበት ቦታ መኖር አይመቸኝም የሚለውን ብሂሉን እውን አደረገው ለመጀመሪያም መጨረሻም ጊዜ ወደ ውጭ ወጣ የትውልድ ሰፈሩን አካባቢውን አገሩን ጥሎ ተሰደደ አድራሻውንም በዚያው አጠፋ በዚህ ጊዜ የንጋት ወጋገኗን ብቻ ያሳየቻት የጌርሳሞት ጀምበር ሙሉ ብርሃኗን ለመጀመሪያ ጊዜ ነፈገቻት ዙሪያዋን ጨለማ ከበባት ከሚወዱት ሰው ውጭ የዓለም ከንቱነት ተገለጠላት እናም ጌርሳሞት ከዚያች ለአፍታ አይታ ካጣችባት የልቧን መሻት ከነጠቀቻት ቀን በኋላ ለብቻዋ ሆና ማልቀስን ያችን የዕውን ቅዥት ተዕይንት በአዕምሮዋ ማመላለስን በምናብ ወደኋላ እየተመለሱ ከንቱ የቀረ ህልምን ማንሰላሰልን ህልሟን የነጠቋትን ሁነቶች ሁሉ እያሰበች መርገምን የዘወትር ሥራዋ አደረገች የቅልልቦሽ መጫወቻነቷ እና አይቶ ማጣቷም ከዚያች ቅጽበት ጀመረ ከገለታ ጋር በመለያየቷ ምክንያት የዋጣት ጨለማ ለዘለዓለም እንደማይነጋ እያሰበች ሁነቱን ሁሉ እንደዓለም ፍጻሜ መቁጠር ጀምራለች ወደ ትምህርት ቤት ወደ ገበያ ወደ ሲኒማ ወደ የትም ስትሄድ ዛላው ህሊናዋ ውስጥ አለ ተብታባነቱም ቀጫጫነቱም የአንዳንድ እንጉርጉሮውም ወዝ ወደ ጥልቁ ቀደ አይቶ መነፈግ ባዶ ጉድጓድ አፍጣ አንገቷን ሰበር አድርጋ የብር ሃብልዋ ደረቷ መሃል እንደ ደራጎን እንባ እየፈለቀ የቀሯትን ቃላቶች ኃደታ ይሙታ አዳም ረታ ጌርሳሞት ያጣችው የገለታን ፍቅር ብቻም አይደለም ከገለታ መሄድ በኋላ ሌላ አለም እንዳለ ላሳይሽ ብሎ በቅልብልብ ምላሱ ያሳመናትን እና የገለታን በውጥን የቀረ ፍቅር ያስረሳኛል ብላ ያሰበችውን ራሚሱ አቡንም ጭምር ነው በእርግጥ ከአቡ ጋር እዚህ ግባ የሚባል የትዝታ ጊዜ እንዳላሳለፉ ታሪኩ ራሱ ይነግረናል ነገር ግን አግኝታው ካወራት ጊዜ ጀምሮ ደጋግማ ስለእሱ ማሰቧን ቀጥላለች ለዚያም ነው ስልኩ ላይ ደጋግማ ስትደውል የነበረው ታዲያ ጣጣ ያለዘለበቱ አይመጣም እንዲሉ ይህ ደጋግማ ለራሚሱ መደወሏሷ ደግሞ እስከመጨረሻው እንድታጣው ምክንያት የሚሆን ሌላ መዘዝ ገና ከጅምሩ ይዞ ብቅ አለ ታሪኩ እንዲህ ነው ከራሚሟሱ ጋር ስልክ ስታወራ የሰማችው እናቷ መግደላዊት ስልኳን ከእጄ ላይ መንጥቃ የራሚሱን ሰልክ ከማጥፋቷም በላይ ባለቤቷን እና የጌርሳን አባት ግስላውን አቶ ኮላሴን ከቤቱ ድረስ ልካ እንዲያስፈራራው አድርጋለች እሱም ከቤቱ ድረስ ገብቶ እሳት በላሰ ድንፋታው አስፈራርቶ እና የማስጠንቀቂያ መልዕክት አስተላልፎ ወጥቷል ታዲያ ጌርሳ መልሳ ለመደወል ብትፈልግ እንኳን ስልኩን ከወዴት። ገ ከዛ አቋቋማቸው ይሄ የተፈጥሮ ሕግ እንዳለ መጠርጠርን ይገፋፋል አዳም ረታ ቀድሞ በነበራቸው በተቀራረበ እና ዝግ በሆነ ጥግግታቸው መካከል በተፈጥሮ የስሜት ልዋጤ ሕግ ሽፋን ተጠቅልላ ጌርሳሞት የተባለች አጥር ተገንብታ አራርቃ ተክላቸዋለች ከፍ ሲል እንደተነሳው እርሷም በመንገዷ ላይ እዚህም እዚያም ስታገኛቸው ከአንዱ ተነስታ ከሌላው ጥላ ስር ታርፋለች ደግሞ በሚገባ ሳትጠለል ወዲያው ወደ ሌላው ትሻገራለች ይሁን እንጅ ሁሉም በሙቀት ከሚያንገበግባት ጨረር ሙሉ በሙሉ አላሳጣሏትምና በመጨረሻም የአራቱንም ጥላ ጨርሳ ምንም ከሌለበት ምድረበዳ ላይ በሐሩር ትቃጠላለች በሌላ በኩል ደግሞ በልቦለዱ ውስጥ ካሉት በርካታ ንዑሳን ገፀ ባህሪያት መካከል በተለይ ከዓበይት ገፀ ባህሪያት ጋር የጠበቀ ዝምድና ያላቸውን ገፀ ሰዎች ህልውናዊ ርእይ የተመለከትን እንደሆነ የጌርሳሞት እናት መግደላዊት በመጀመሪያ የልጅነት ተስፋዋን በአባት እና እናት አልባነት የተነጠቀች ያለ እናት እና አባት በሌሎች ዘመዶቿ መደፈር መነሳት እና መጣል የልጅነት ብሩህነቷን ያጣች በኋላ ደግሞ ከተጣለችበት ያነሳትን እና ከሰው እኩል ያናገራትን ባሏን እና የልጅ አባቷን አቶ ኮላሴን ገና በህይወቷ አጋማሽ በድንገት የተመነተፈች ባለከንቱ ህልም ናት መግደላዊትን ያለ ኮላሴ ከሦስት ወር በለይ መኖሯ እንደጎዳት ገጽዋ ላይ ተጽፎአል ይሙት ይኑር ፖሊስ መርምሮ ባደርስበትም ጥቁር ቀሚስ ለብሳለች ጥቁር ሻሽ አስራለች ኩልዬን አልረሳሁትም ለማለት መኪናው ተበላሽታ የቆመችበት አካባቢ ወንዝ ዳር የተገኘውን መስታወቱ የተሰባበረ የማይሰራ ካሲዮ ኤሌክትሮኒክስ የእጅ ሰዓቱን በቀኝ እጃ ላይ አስራለች አዳም ረታ ሌላዋ የርእይ መነጠቅ ሰለባ የሆኑት ንዑስ ገፀ ባህሪ ደግሞ የራሚሱ እናት ወይዘሮ መቅረዝ ናቸው ወይዘሮ መቅረዝ በመጀመሪያ ደረጃ ልክ እንደ ጌርሳሞት ሁሉ በድንገት እና ለጊዜው ቀላል በመሰለ አደጋ አካላቸውን አጥተዋል ይህን የተጎዳ አካላቸውን በህክምና ወደነበረበት ጤናማነት ለመመለስ ያላሰለሰ ጥረት ቢያደርጉም ብዙ ብዙ መስዋዕትነት ቢከፍሉም ሳይሳካላቸው ቀርቶ ዘለአለማዊ በሽተኛ ሆነው አርፈዋል የአቡ እናት ወይዘሮ መቅረዝ የአንገት በላይ ሃኪም ሆነው አለርት ሆስፒታል ለአስርታት ሰርተዋል አንድ ቀን እዛው ሆስፒታል ውስጥ ሊኖሊየም ወለል ላይ የፈሰሰ ሇራራ ቫዝሊን እረግጠው ሲወድቁ የብረት ጠረሌሴዛ ጠርዝ አገጫቸውን ገጭቷቸው መንጋጋቸው ተሰበረ ስብራቱ ሊስተካከልላቸው ስላልቻለ ያለማቋረጥ ለሃጭ ይወርዳቸው ጀመር ማስክ ለብሶ መስራት አማሯቸው ስራ አቋርጠው ጡረታ ወጡ አዳም ረታ ወይዘሮ መቅረዝ ከአካላቸውም ሌላ ለአሠርታት የደከሙለትን እና የሚወዱትን የህክምና ሙያቸውን በዚሁ በአካል ጉዳተኝነታቸው ሳቢያ ባደረባቸው ሥነ ልቦናዊ ቀውስ የህይወት ስንቅ ይሆነኛል ያሉትን ሙያቸውን ሳይወዱ በግድ ባጋጣሚ ተገደው አጥተውታል ድካማቸው ህልማቸው ሁሉ ከንቱ ሆኗል ከልጅነታቸው ጀምሮ ከተማሩት የሕክምና ሳይንስ ራቁ ሃያ ስድስት አመታት የተማሩት እና ለሃያ ስድስት አመታት የሰሩበት ሳይንስ የተሰበረአገጫቸውን ሊያድናቸው አልቻለምና ቁም ያዙበት አዳም ረታ ሃፋጋ ከዚህ አንጻር ጠቅለል ባለ መልኩ ሲገለጽ ወይዘሮ መቅረዝ ወዲህ አካላቸውን አፋቸውን ጤናቸውን አጥተዋል ወዲህ ደግሞ ሥራቸውን እንጀራቸውን በአደጋ ሰበብ ተቀምተዋል እድሜ ዘመናቸውን ለፍተው ያገኙትን የህይወት ዘመን ራዕያቸው የሆነውን ሙያቸውን እና በሙያቸው ሠርተው የመብላት ርእያቸውን ተነጥቀዋል በአጠቃላይ ከፍ ሲል እንደተጠቆመው በ ለፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ያሉ ገፀ ባህርያት አንዳንዶቹ በከባድ ህመም አንዳንዶቹ በሞት ሌሎቹ ደግሞ በስደት እና መሰል ምክንያቶች ካለሙት ሳይደርሱ የሳሱለትን ሳይቀምሱ የተመኙትን ሳያሳኩ የፈለጉትን ሣያገኙ ወይም ያገኙትን ሳይጠቀሙ ሃሳባቸው ህልማቸው ምኞታቸው ዕቅዳቸው እውን ሳይሆን ቅዥት ሆኖ የቀረባቸው ስኬትን ጨብጠው ድንገት የለቀቁ ብቅ ያለችላቸው ፀሐይ ድንገት ከመንገድ ላይ እያሉ የጠለቀችባቸው በእጃቸው የያዙትን ሙዳ በቅፅበት በጭልፊት የተመነተፉ በጥቅሉ የተለያዩ ርዕዮቶቻቸውን በተለያየ መጠን እና ሰበብ ያጡ ገፀ ሰዎች ናቸው ብሎ መደምደም ይቻላል ቀቢጸ ተስፋ ከሁሉ በፊት የህልውናዊነት ጭብጦች በግልጽም ይሁን በህቡዕ የሚዛመዱ እና የሚዋለዱ ከመሆናቸው የተነሳ አንዱ የሌላው መንስኤ ወይም አንዱ የሌላው ውጤት እንዲሁም አንዱ ከሌላው ጎን የተቆረሰ ሊሆን እንደሚችል በምዕራፍ ሁለት ላይ ተነስቷል ይህን የህልውናዊነት ጭብጦች ተዋላጅነት እና ተዛማጅነት ቴዎድሮስ ገብሬ ዐዐም ይጋሩታል በዚህ መሠረት እንግዲህ ቀቢጸ ተስፋ የሚባለው ህልውናዊ ገጽታ ከአጠቃላይ የማንነት መበጥበጥ ወይም መታወክ ጋር የተገናኘ እንሆነ የነገረህላዌ ልሂቃን ያትታሉ እንደ ነገረ ህላዌያን እምነት ሰዎች በህይወታቸው ውስጥ ከራሳቸው ጋር የሚፈጥሩት አለመግባባት ወይም እሰጥ አገባ ከዚሁ ተስፋ መቁረጥ ላይ ያደርሳቸዋል ይህ ከራስ ጋር የሚደረግ ግጭት ደግሞ ምንጩ ከምኞት ከንቱነት ወይም ከርእይ መነጠቅ አለፍ ሲልም ከባዶነት ስሜት ባሕር ውስጥ ሊቀዳ ይችላል በዳፍ ልቦለድ ውስጥ የምናገኘው ራሚሱ ህልውናውን ሙሉ በርካታ ተግባራትን በነጻነት እንዳከናወነ አልቀረም ይልቁንም የሚከተለው ነጻ አስተሳሰቡ ይዞበት የሚመጣውን ውጤት ሁሉ ብቸኛ ተቋዳሽ ሆነ እንጂ ስለሆነም በስተመጨረሻ በዙሪያው ባሉ ነገሮች ሁሉ ተስፋ ቆረጧል ነገር ግን አሁንም ድረስ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆኖም ቢሆን ህይወቱን ይገፋል ምናልባትም ከዚህ የተስፋ መቁረጥ አረንቋ ውስጥ የሚያወጣው የጫት እና የመጠጥ ሱሱ ብቻ ነው ወደዚህ መደበቂያው ሱስ የገባውም ከሚኖርበት ዓለም ውስጥ የሚጠብቀውን በማጣቱ እንጅ መዝናናት ፈልጎ እንዳለሆነ ኦሖናንፖ በተሰኘው ክፍል ውስጥም አንስቻለሁ ከዚህ ባለፈ ደግሞ ራማሚሱ እንደ እርሱ አባባል እውቀት ሊሰብክ አስቦ በር የተባለ መፅሔት ከጓደኞቹ ጋር በአንድነት ያቋቁማል ይሁን እንጅ በተለያዩ መንግስታዊ አካላት ተቃውሞ ምክንያት ሃሳቡ እንዳቀደው እውን ሳይሆን ቀርቶ በአንድነት ሊጽፉ የተሰባሰቡት ጓደኞቹ ሁሉ ወደየብትውናቸው ይበተናሉ ታዲያ ከዚህ በኋላ የሚሰራው ጠፍቶበት ሞራሉ ሁሉ ወድቆ ብቻ በሁሉም ነገር ተስፋ ቆርጦ በልቦለዱ ታሪክ ውስጥ እናነባለንጉ በዚህ ምክንያት በተማረበት የሙያ መስክ ያገኘውን ሥራ እንዳይሰራ እንኳን በዘመኑ ያለው የአሰራር ሥርዓት ሁሉ ያስጠላዋል አስተማሪነት እንዳልገባ የተማሪ ፊት ያስጠላኛል እንደገናስ በበርጫ ያበጠ የጎረምሳ ዐይን ልይ። አዳም ረታ በሌላ በኩል ደግሞ ገለታ በአገሩ ውስጥ ያለው እና በየትኛውም ቦታ የተሰራጨው የምን አገባኝነት ስሜት እና ስር የሰደደ ድንቁርና ተስፋ አስቆርጦት ወደ ውጭ እንዲሰደድ ምክንያት እንደሆነው የልቦለዱ ታሪክ ያትታል ገለታ ይህ በአገሩ ላይ የተንሰራፋ ጭፍን የሆነ የሰዎች እውቀት እና አስተሳሰብ መቼውንም ቢሆን ይቀረፋል የሚል ተስፋ አላደረበትምና ሽሽትን ስደትን መርጧል ከቆመበት ትንሽ ቦታ ጀምሮ እስከዛ አድማስ ድረስሊዋጋው የማይችል ስር የሰደደ ድንቁርና እንደሰፈረ ሲገባው አፉን ለክርክር ሳይከፈት መታዘቡን ቀጠለ ይህንን በዝምታ መከታተል ስላደከመው ከዚህ አገር መሸሽ ነበረበት ከአገር ወጣ አዳም ረታ በተጨማሪም የገለታን መንገድ ዳር ሞቶ የመገኘት ጉዳይ እዲያጣራ የታዘዘው ደቡብ አፍሪካዊው ፖሊስ ሰርጀንት መቶ አለቃ ዴላኒ በአገሩ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ የዴሞክራሲ የሠላም የብልጽግና እና የእኩልነት አዎንታዊ ልዋጤ መኖሩን በሰዎች በጋዜጦች በመጽሔቶች በሬዲዮ በቴሌቭዥን በአጠቃላይ በብዙሃን መገናኛዎች ሁሉ ሲሰማ ከእውነታ የራቀ ሆኖ በእጅጉ እንዳሰላቸው የልቦለዱ ታሪክ ያወሳል ምክንያቱም አገሪቱን የሚያዝዛት ገንዘብ እና ወንጀል እንደሆነ አሳምሮ ያውቃልና ዴላኒ በእነዚህ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከእራሱ በላይ ምንም አይነት ምስክር አያሻውም በአገሪቱ ውስጥ የሚፈጸሙት ቁጥር ስፍር የሌላቸው ውስብስብ ወንጀሎችን ሙያው አስተዋውቆታል በስተመጨረሻም እነዚህ በመዓልትም ሆነ በሌሊት በሥራው ላይ በተደጋጋሚ የሚያጋጥሙት በርካታ ቁጥር ያላቸው ውስብስብ ወንጀሎች ተስፋ አስቆርጠውታል ህይወቱን ለማቆየት ብቻ ሲል ሥራውን መሥራቱን ይቀጥል እንጅ የአገሩ የፖለቲካ ሽፋን እና እውናዊው ሁነት አልጣጣም ብሎት በህላዌው ሲሰላች እና ተስፋ ቢስ ሲሆን እንታዘባለን የሚገባው ነገር የየቀኑ ሕይወቱ በሽብር መሞላቱ ነው የሚበላው ቢያገኝ ድንጋይ እንኳን ቢሆንና ቢስማማው ስራውን ትቶ እሱን እየቆረጠመ በርሃ ለብቻው ለመኖር ይሰደዳል ሞቱ ከደረሰ እንቅልፍ ሲወስደው ቢሆን ይመርጣል አሁን እንደሚሆን ቢረዳ ቢሞት ቅር አይለውም አዳም ረታ ዐፀ ለድኦዕፖ ሃሄራፖኘግሂታል በየቀኑ የሚያጋጥመው የወንጀል መዓት በህይወቱ ውስጥ ተስፋ አስቆርጦታልና ብቸኛ የበርሃ መራር ሕይወትን ሲከፋም ሞቱን አስመኝቶታል ዴላኒ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ውስብስብ ወንጀሎች እና ወንጀለኞች በአለቆቹ ተዕዛዝ መሠረት በማሳደድ በተደጋጋሚ ከቁጥጥር ስር እንዲውሉ ቢያደርግም በስልታዊ የውሸት ጭምብል በመሸፋፈን እራሱኑ መልሰው እንደወንጀለኛ እየቆጠሩ ሚያደርሱበትን ጭቆና እና በደል ሲያስብ መሸከም ያቅተውና በሃሳብ ብቻ ይናውዛል ይህን መሰሉን የግፈኞች ከባድ ቀንበር ለመሸከም የዴላኒ ትክሻ አቅም አነሰው በመጨረሻም የወንጀለኞችን ርዕዮተዓለም ከነጭራሹ ማምከን ከቶውንም የማይታሰብ እንደሆነ በመገንዘብ ትክክለኛውን የወንጀል ማነፍነፍ ሥራውን እርግፍ አድርጎ ለመተው ተገዷል በአገሩ ውስጥ ወንጀል ተሸጋጋሪ እና ምንም አይነት ቀኖና ሊገድበው የማይችል ተግባር መሆኑ ገብቶታል ስለዚህ ወንጀልን የመታገል ራዕዩ መቼውንም የማይፈጸም ትንቢት ሆኖበት ባይመቸውም በዘመኑ ባህሪ ውስጥ እራሱን ደብቆ ለመኖር ወስኗል የወንጀል ድርጊትን እስከ መጨረሻው ድረስ የማድረቅ ተስፋው ተሟጧል ሕግ ጠባቂ ቢሆንም ሕግ እራሱን አይጠብቀውም አስከፊ ሆነ አልሆነ የወንጀለኞቹን ባህርይ ሁሉም ሰው በቀላሉ የሚሜገለብጠው እና የዘላለማዊነት ተስፋ ያለው ነው እና ወያምቻ ዎፉ ማለት አጉል ህልም ነው ዴላኒ መሞከር ካቆመ ሰነበተ አዳም ረታ ዐወ ምዕራፍ አራት ማጠቃለያ ይህ ጥናት የነገረህላዌ ፍልስፍናን መሠረት በማድረግ በለፉ ረጅም ልቦለድ ውስጥ የተንፀባረቁ እና ጎልተው የወጡ የህልውናዊነት ጭብጣዊ ጉዳዮችን በመለየት እና ተንትኖ በማሳየት ለምርምር የተመረጠው ልቦለድ ከነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ግንኙነት ለመመርመር የተደረገ ሙከራ ነው ይህንን ለማድረግ ያነሳሳው ዋነኛው ምክንያት ደግሞ የልቦለዱን ብሎም በልቦለዱ ናሙናነት አጠቃላዩን የአማርኛ ሥነ ጽሑፍን እና የሰው ልጅ የህልውና ፍልስፍናን ተዛምዶ ለመግለጥ መሻት ነው ከዚህ ባሻገር ደግሞ ይህ ጥናት ከላይ የተቀመጠውን ዓብይ ዓላማ ለማሳካት ማለትም በዚሁ የልቦለድ ሥራ ውስጥ የተንፀባረቁ የህልውናዊነት ጭብጦችን በመለየት እና ተንትኖ በማሳየት ከነገረህላዌ ፍልስፍና ጋር ያለውን ዝምድና ለመግለጥ እራሱን የነገረህላዌ ፍልስፍናን ንድፈሃሳብን ለተመረጠው ልቦለድ መተርጎሚሜሚያነት ተጠቅሟል በዚህም መሠረት በዚህ ጥናት ለምርምር በተመረጠው ጸፉ ረጅም ልቦለድ ውስጥ ተንፀባርቀዋል ተብለው የታመነባቸው አምስት ያህል የህልውናዊነት ጭብጦች ተለይተው እና በስፋት ተተንትነው ቀርበዋል በዚህ ጥናት ለትንተና በተመረጠው ጸፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ የሚገኙትን ከዓበይት እስከ ንዑሳን ገፀ ባህርያት እንዳስፈላጊነቱ በመውሰድ ዓለማዊ ኑባሬያቸው ምን እንደሚመስል እና በህይወታቸው ውስጥ ያለፉባቸው ገናን የህላዌ ክስተቶች የትኞቹ እንደሆኑ በመፈተሽ ነው የህልውናዊነት ጭብጦቹ ተለይተው እና ተተንትነው የቀረቡት በዚህም መሠረት በዚህ ልቦለድ ከተቀረጹት ገፀ ባህርያት መካከል አንዳንዶቹ በነጻነት የሚሜቦርቁ አንዳንዶቹ ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ የህላዌ እስትንፋሳቸው ሁሉ በሌሎች ማህበራዊ እና ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች የተሸበበባቸው የቁም እስረኞች ሆነው እናስተውሳላለን ስለሆነም በዚህ ልቦለድ ውስጥ ነጻነት እና ኃላፊነት ከነጻነት እጦት ጋር ፊት ለፊት ተገልጸው ይገኛሌሉ ይህ የህላዌ ሁነት ደግሞ በሁለቱ ዓበይት ገፀ ባህርያት ማለትም በራሚሱ አቡ እና በጌርሳሞት ላይ በስፋት የሚስተዋል ሲሆን በአንደኛው ጽንፍ ራሚሱ ከምንም አይነት ማህበራዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ሥርዓት ውጭ ሆኖ ተገልጧል ስለሆነም እራሱ ባመነው እና ባሰበው ልክ ራሱን የሚመራ ፍፁም ነጻ ገፀ ባህሪ ሆኖ እናገኘዋለን ራሚሱ በእያንዳንዱ የነጻነት ህላዌው ውስጥ የሚመጣበትን ኃላፊነትም ለመሸከም ትክሻውን ቀድሞ ያደነደነ ገፀ ባህሪ ነው ከዚህ በመነሳት ራሚሱ ነፃ እና የራሱን ዓለም የራሱን ማንነት በጥቅሉ ራሱን በራሱ የፈጠረ ገፀ ባህሪ ነው የትኛውንም አይነት ደንባዊ ሥርዓት ከመቃወም እና ከዚህ ሥርዓት እራሱን ከማራቅ ባለፈ ስርዓቱን ሊቀይረው ባይችልም የእራሱን ህልውና ፈጥሮ በራሱ አቅጣጫ ሲጓዝ እና ከማንም ጣልቃ ነጻ የሆነ ህላዌን ግን ሲመራ እንታዘባለን ስለዚህ ነጻ የሆዌ ገፀ ሰብ የሚል ትርጓሜ ተሰጥቶታል ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ ወዲህ በማህበረባህሉ ወግ ወዲህ በሃይማኖታዊ አስተምህሮው ወዲህ ደግሞ በቤተሰባዊ ደንብ እና ሥርዓቱ በሦስት በአራት ገመድ የታሰረችውን ጌርሳሞትን እናገኛለን ከዚህ አንጻር ነጻነት ይሉት ነገር ለጌርሳሞት የሚታለም እንጅ የሚደረስበት አልሆን እንዳላት በተደጋጋሚ እናስተውሳላለን ጌርሳሞት ሁለንተናዊ ህይወቷን አይደለም የምትለብሳቸውን አልባሳት ሁሉ የማህበረሰቧ ብሎም የቤተሰቧ ህግ አስቀምጦላታል ከዚህ ህግ የምታመልጥበት ደግሞ አንዳችም ቀዳዳ የለም የማምለጫ መንገዱ ሁሉ በቤተሰቦቿ ግልምጫ እና ማስፈራሪያ ብሎም በማህበረሰቡ ይሉኝታ የተዘጋ ነው በዚህም ምክንያት ጌርሳሞት በተከለለላት አጥር ስር ብቻ ተወስና የምትኖር እንስት ገፀ ሰብዕ ሆናለች በሌላ በኩል ደግሞ የራሚሜሱ ገደብ አልባ ነጻነት በህይወቱ ውስጥ መመኪያ መጠለያ ተስፋ መጣያ እንዲያጣ ምክንያት ሲሆነው እና ህልውናው ባዶ ኦና ሲሆን ተመልክተናል ራሚሱ በየትኛውም አይነት ሃይማኖታዊም ሆነ ባህላዊ ሥርዓት የሚያምን አይደለምና በስተመጨረሻ በዙሪያው ያሉትን ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ተግባራትን አለፍ ሲልም ሥነ ፍጥረታትን ሁሉ ይጠላል ራሱንም ጨምሮ ስለዚህ የመጨሻ ዕጣው ትርጉም አልባ ህልውናን መምራት እና ከማንም እና ከምንም ነገር ውጭ የሆነ ኑባሬን መከተል ሆኗል እናም ለዚህ አይነቱ ኑባሬው የህልውና ኦናነት የሚል ትርጓሜ ተሰጥቶታል በቋፍ ልቦለድ ውስጥ የውህድ ማንነት የድብልቅ ባህርያት ባለቤቱ የጌርሳሞት አባት አቶ ኮላሴ ደግሞ የሁኔታዊነትን ጽንሰ ሃሳብ የሚያጎላ ገፀ ባህሪ ነው አቶ ኮላሴ በተፈጥሮው ዝንጀሮ ሆኖ የተወለደ በኋላ ግን በኑረቱ ሁኔታ ምክንያት ሰው የሆነ ሰውም ዝንጀሮም ሁለቱንም የሆነ ምትሃታዊ ተፈጥሮ ነው ይኸውም በዚህ ጥናት ውስጥ የህልውና ሁኔታዊነት የሜል ፍቺ ይዚል ኮላሴ በህይወት ዘመኑ ውስጥ የሰዎችንም የዝንጀሮችንም ተግባራት በጥምረት ይፈጽማል እንደሰውዙ ጋዜጣ ማንበብ እና ስቴዲዮም ገብቶ ኳስ መመልከት የሚያዘወትር በመኪና ማሸከርከር የሙያ መስክ ተሰማርቶ መሰረታዊ ህላዌውን የሚመራ አለፍ ሲል ደግሞ ከወየዘሮ መግደላዊት ጋር ትዳር በመመስረት ጌርሳን የመሰለች ተወዳጅ ልጅ የወለደ እና ሌላም ሌላም በርካታ ሰዋዊ ተግባራቶችን እና ሁነቶችን የሚፈጽም ገፀ ባህሪ ነው እንደ ዝንጀሮ ደግሞ አመጋገቡ ጥሬ ሰላጣ እና ጎመን ባህሪው ደግሞ ተደባዳቢ እና ብጥብጥ የሚቀናው በተግባሩ ደግሞ ከዛፍ ዛፍ ከገደል ገደል በቀላሉ መዝለል የሚችል ተዓምራዊ ፍጡር ነው ከአቶ ኮላሴ ሌላ ግን ራሚሱም ፍጹም ከሆነው ነጻነቱ ጀርባ አንዳንድ ሁኔታዊ የህልውና ተግባራትን ሲፈፅም እንታዘባለን እንደ ነገረህላዌያን እምነት ማንኛውም ሰው ምንም ያክል ነጻ ቢሆንም ከሚኖርበት ማህበረሰብ የሚቀስመው ኑረት አይጠፋምና ራሚሱ በጥቂቱም ቢሆን ማስመሰልን ለሰው ሲሉ መኖርን በዙሪያው ካሉ ሌሎች ማህበረሰቦች ወርሷል በአፍ ልቦለድ ውስጥ ትልቁን እና ዋናውን ሃሳብ የሚሸፍነው ህልውናዊ ጉዳይ የርእይ መነጠቅ ነው መጠኑ ይለያይ እንጅ ከዚህ ልቦለድ ውስጥ በዚህ የህልውና ገጽታ የማያልፍ ገፀ ባህሪ አለ ማለት አይቻልም ይልቁንም ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ገፀ ባህርያቱ ከሞላ ጎደል ርእያቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ያጡ ናቸው በዚህ መሠረት ከዋና ገፀ ባህርያት ብንነሳ እንኳን ገለታ ባካፋ ዘሪሁን እና ራሚሱ ቢያንስ ሁሉንም አንድ የሚያደርጋቸውን የጌርሳን ፍቅር በተለያዩ ወቅቶች እና ምክንያቶች አጥተዋል ጌርሳሞትም የእነርሱን ፍቅር እንደዚሁ ከዚህ ባሻገር ግን ገለታ ውጭ አገር ሄዶ በድሎት ለመኖር ያለመውን ህልም በሞት ተነጥቋል ባካፋ ደግሞ ከኬንያ ባመጣው የምግብ መመረዝ እና ሌሎች ተደራራቢ በሽታዎች ሳቢያ ጤናውን አጥቷል ጌርሳሞትም ብትሆን ከእነዚህ አራት አብሮ አደጎች ፍቅር በተጨማሪ የአፏን ውበት እና ጤናዋን እንዲሁም አባቷን በድንገት ተነጥቃለች ወደ ንዑሳን ገፀ ባህርያት ስንመጣ ደግሞ የጌርሳ እናት መግደላዊት ባሏን አቶ ኮላሴን በገድንገት አጥታለች እንደዚሁም የአቡ እናት ወይዘሮ መቅረዝ እንደጌርሳሞት ሁሉ የአፏን ጤንነት ብሎም የረጅም ጊዜ የልፋት ውጤቷ የሆነውን ሥራዋን በድንገት ለቃለች በተጨማሪም የገለታ እናት ወይዘሮ ፎርቱና በልጃቸው ገለታ መጥፋት አለኝታቸውን የወደፊት ምርኩዛቸውን ተነጥቀዋል በመጨረሻም ከዚህ በላይ ርእያቸውን የተነጠቁ ገፀ ባህርያት በህይወታቸው እና በተለያዩ ሁነቶች ተስፋ ይቆርጣሉ የያዙት ሲያመልጣቸው የጨበጡት ሲወድቅ በአንድ በኩል የያዙት በሌላ በኩል ሲፈስባቸው እርግጠኛ የሆኑባቸው ጉዳዮች ድንገት ከአጠገባቸው ሲሰወሩባቸው ተስፋ የጣሉባቸው ዕምነታቸውን ሲያጎድሉባቸው የሰጧቸውን አደራ ሲበሉባቸው ወዘተ ወዘተ በህላዌያቸው ተሰላችተዋል ተማረዋል በስተመጨረሻም ተስፋ ቢስ ሆነዋል ጌርሳሞት በከንፈሯ መበላሸት እና በአፏ ቁስለት ምክንያት የወደፊት ጤንነቷ ብሎም የደም ግባቷ ነገር ተስፋ የምታሳድርበት አልሆን ብሏታል ተስፋዋ ተሟጧል በራስ መተማመኗን ሁሉ አጥፍቶባታል ወይዘሮ መቅረዝም እንደዚሁ የነበረው ጤናዋ እንደማይመለስ ታውቃለችና ዘመናዊ የህክምና ሙያዋን ትታ ወደ ባህል መድሃኒት ቅመማ ፊቷን መልሳለች በሌላ በኩል ደግሞ ራሚሱ ለመተዳደሪያ ብሎም ለእውቀት እና ስልጣኔ መስበኪያ ያሰበው ር መጽሔት በመንግስታዊ አካላት አማካኝነት ሲታገድበት ተስፋ በመቁረጥ ከሌላ ሥራ ከሰብዓዊ ፍጡር እና ከሌሎችም ሥነ ፍጥረታት ሁሉ እራሱን አርቆ የጫት ጓደኛ ብቻ አበጅቷል ገለታንም ቢሆን ለስደት የዳረገው በአካባቢው ባለው ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ሥርዓት ተስፋ መቁረጡ ነው በተመሳሳይ መልኩ በአገሩ የፖለቲካ ሥርዓት በእጅጉ የተማረረው እና በዚሁ ጉዳይ ተስፋ የቆረጠው ሌላው ገፀ ሰብዕ ደግሞ ደቡብ አፍሪካዊው ፖሊስ ፅኃሪጀኃ ዴላኒ ነው በአጠቃላይ በዚህ ጥናት በቋፍ ረጅም ልቦለድ ውስጥ የተንጸባረቁ እና ጎልተው የወጡ ህልውናዊ ጉዳዮች ማለትም ነጻነት እና ኃላፊነት ኦናነት ሁኔታዊነት የርእይ መነጠቅ እና ቀቢጸ ተስፋ የሚሉት የህልውናዊነት ጭብጦች ተለይተው እና በስፋት ተተንትነው ቀርበውበታል ብሎ መደምደም ይቻላል ዋቢ ጽሑፎች መሠለች ተሻገር የሰው ልጅ ህልውና በቅበላ እና ኩርቢት ድርሰቶች ነገረህለዌ ንባብ የሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ ጽሑፍ ባሕር ዳር ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሰብለ ወልደኪዳን የእኔነት ሐተታ በተመረጡ የአማርኛ ረጅም ልቦለዶች የፒኤችዲ ማሟያ የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ አዲስ አበባ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ብሌን ፊ ያዲሦዶጮሕዖ ደራሷዖ ማሠርረ ቦፆሥንኃ ጽታፍ መድይፊፖ ቅ ቁ ነሐሴ አዲስ አበባ ኤክሊፕስ ማተሚያ ድርጅት ኢደማ ቴዎድሮስ ገብሬ ሃይፀቋ ፕሷኖፎ ቦሮሥሪን ጽሑታፍ ሠ አዲስ አበባ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲፕረስ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ኑፊ መሯጽጋ«ራ ፇዕው ወሃቨግዕ ወመሀፇ ቃጎፖ ጋዳቋፅኃ አዲስ አበባ አርቲስቲክ ማተሚያ ቤትአዳም ረታ ዳፉፍ አዲስ አበባ ሃሳብ አሳታሚ ዘሪሁን አስፋው ።