Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ያ ለክርስቶስ ውሳኔ አድርጓል የተባለው ሰው በመለወጥ ውስጥ ያሉት ዋና ቁልፍ ነገሮች ሁሉ መምጣት ያለባቸው በሁለተኛ ደረጃ ላይ ነው። ብለን አራሳችንን መጠየቅ አለብን እነዚህ ምልክቶች ለእኛ በጣም የሚያስፈልጉን ማበረታቻዎች ናቸው በሌሎችም ሕይወት የጌታን ሥራ ለመለየት የምንፈልግ ከሆነ እነዚህን ምልክቶች በሚገባ ማወቅ ያስፈልገናል ከዚያም ያለማመንታት በቃላችን እያስታወስን ልንጠቀምባቸው እንችላለን ሰባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች እንዳሉሱሉ በሚገባ ተጠቅሷል ነገር ግን ይህ ጥናት ያተኮረው ወይም የተወሰነው በጣም በቀላሉ ሊታወቁ በሚችሉት ላይ ብቻ ነው ነገሮችን ለማሳጠር ሲባል ወደዚህ ያሳለፍነው ሌላ ጠቃሚ የሆነ ምልክት በሐዋርያት ሥራ ሁለት ላይ አለ ሉቃስ እንደመዘገበው በጳንጠቆስጤ ቀን የተለወጡት በሐዋርያት ትምህርትና ፅንዳራውንሥ መቀረሰ ስብርው ጸተጉ ነበር ሐዋ እውነተኛ አማኞች በእውነት ጌታን ማምለካቸውና ለሱ ያላቸውን ፍቅር ማሳየታቸው ሌላው የመለወጥ የጸጋ ምልክት ነው። የቤተክርስትያን አባልነትስ ምን ማለት ነው።
ንስሐ ኃይለኛ ስሜትን ያስከትላል አንድ ሰው ስለኃጢአቱ በጥልቅ ሲያስብና የእግዚአብሔርን ምሕረት በጣም ሲፈልግ ብቻ ነው የእግዚአብሔር የጸጋ ሥራ በልቡ ውስጥ ተከናውኗል ብለን ተስፋ የማድ ረግ መሠረት የሚኖረን ምንም ዓይነት ንስሐንና በኃጢአት ማዘንን የማያካትቱ ምስክርነቶች አስከመጨረሻው ድረስ መጠርጠር አለባቸው ብዙ ጊዜ በቀልድና በግልብ ቋንቋ የተነገሩት የኮከብ ዘፋኞችና ተዋንያን ጭሁ የመለወጥ ታሪኮች መለወጥን ልብ የማይነካና ስሜት የሌለው እንዲሁም በጣም ጠቃሚውን የመለወጥ የጸጋ ምልክት ማለትም ኃጢአተኝነትን አምኖ መቀበልን የጎድለው አድርገውታል ሰዎችም ሕይወትን መቋቋም ሲያቅታቸው ኢየሱስን እንዲቆጣጠርላቸው ሲጠይቁትና በውጤቱም አሁን በነሱ ጎን በተ ውኔት መድረክ ላይ ሳይቀር እንዲቆምና ሕይወታቸውን ዓለማዊውንና ያልተ ለወጠውን የበለጠ ስኬታማ እንዲያደርግላቸው ብዙ ጊዜ ሲናገሩ እንሰማለን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለአንድ ሰው ሌላ ምንም ነገር ከመሆኑ በፊት ከኃጢአት ላ አዳኝ መሆን አለበት ሰው በውስጡ እንዲያው ባዶነት በተሰማው ወቅት ክርስቶስን ሊቀበል ይችላል የሚለው ሐሳብ አሳዛኝ ስህተት የሞላበትና ከመጽሐፍ ቅዱሳዊው መለወጥ ጋር ተመሳሳይነት የሌለው ነው ስለዚህም አንድ ሰው በእውነተኛ የኃጢአተኝነት መረዳት በእግዚአብሔር ፊት አዝኖ በእውነት ዝቅ ለማለቱ እንዲሁም ይቅርታንና አዲስ ሕይወትን ለመቀበል ጥልቅና እውነተኛ ፍላጎት ያለው ለመሆኑ አንዳንድ ምልክቶችን መመልከት አለብን በአንዳንድ ክርስትያኖች ሕይወት ታሪክ ወይም በታላላቅ የሪቫይቫል ታሪኮች ውስጥ ተጽፎ እንዳነበብነው ዓይነት የጠለቀ ሐፍረትና ነፍስን ለንስሐ የሚያነሳሳ ኀዘን አሁን ጌታን ከሚፈልጉት ባንጠብቅም ልምዳቸው የተወሰነ መጠን ያለው ኀዘኔታ በእግዚአብሔር ፊት መዋረድና በእግዚአብሔር ምሕረት መቅለጥን ማሳየት አለበት ለኃጢአት ይቅርታም በቀራንዮው ክርስቶስ ብቻ የሚታመን የተዋረደና የተሰበረ ልብ ያላቸው መሆኑን በሆነ በአንድ መንገድም ቢሆን ማሳየት ይኖርባቸዋል ስባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች ንስሐ መቀየር ወይም የአመለካከት ለውጥ አድርጎ ከኃጢአት ወደ እግዚአብሔር መመለስ ማለት ነው በመሆኑም ንስሐ ሁለት ነገሮችን ያካትታል እነሱም ለኃጢአት እና ለእግዚአብሔር ያሉን አመለካካቶች ናቸው ኃጢአተኛ መሆናችንን በምንገነዘብበት ጊዜ ኃጢአተኛ በመሆናችን ብቻ አንሸማቀቅም ነገር ግን ለኃጢአት ያለንንም ፍቅር እንጥላለን ኃጢአትንም ለመተውና ልዩ ለመሆን እንናፍቃለን በተጨማሪም ስለጌታ ያለንን አመለካከት እንቀይራለን እሱንም እንደ ብቸኛ የግል አዳኛችን እንፈልገዋለን ደግሞም የሕይወታችን ፍጹም ገዢ አድርገን እንወስደዋለን በአሁኑ ጊዜ የመጽሐፍ ቅዱስ ክርስትያኖች ነን ብለው ራሳቸውን የሚጠሩ ብዙ ሰዎች ይህን ግልጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የመለወጥ ትምህርት በርዘውታል በመሆኑም ከአሮጌው ሕይወት ማለትም ከዓለማዊው የሕይወት ልምድ ጋር ፍጹም የሆነ መቆራረጥ አያስፈልግም ይላሉ እነሱ እንደሚሉት ንስሐ ስለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የአዕምሮ ለውጥን ማድረግ ብቻ ነው ነገሮችን የበለጠ ሲያበላሹም በሕይወት ላይ የክርስቶስ ጌትነት ለደኅንነት ያለውን አስፈላጊነት ይክዳሉ በሌላ አነጋገር ንስሐን ምንም ወደማይጠቅም ደረጃ አውርደውታል ስለዚህም በነሱ አገልግሎት የተለወጡት አዳዲስ ሰዎች የነሱን ዓለማዊ ልምምድና ሕይወት ቢይዙ ምንም አያስደንቅም በአዲስ ኪዳን ምሳሌ መሠረት ሲታይ ይህ እውነተኛ ለውጥ አይደለም ጉዳዩን እንደሚከተለው በሚገባ ልናጠቃልለው እንችላለን ጸጸትና ኀዘን ከሌለ መለወጥ የለም በቀራንዮው ሥራ ላይ ብቻ መታመን ከሌለ መለወጥ የለም ከአሮጌው ሕይወት መለያየት ከሌለ መለወጥ የለም ከዓለም መለየት ከሌለ መለወጥ የለም ክርስቶስ በሕይወት ውስጥ ንጉሥ ካልሆነ መለወጥ የለም በመሆኑም መልሳቸውን ልናውቅ የሚገቡን ጥቂት ቁልፍ ጥያቄዎች እነዚህ ናቸው ጌታን ለመፈለግ የመጡት በቅዱስ እግዚአብሔር ፊት ሲቀርቡ በኃጢአታቸው ሐፍረትና መዋረድ እንዲሁም የልብ መሰበር ተሰምቷቸዋልን። እንዲሁም በጸሎታቸው ጌታን በጣም ያመሰግናሉ ነገር ግን ሰዎች ተለውጠናል ብለው ከተናገሩ በኋላ ወደ ሕይወታቸው በሚመጣው ጥቃቅኑ ፈተና ሁሉ በመፍራትና በመጨነቅ የሚወድቁ ከሆነ ይህ ጠቃሚና የከበረ የጸጋ ምልክት በሕይወታቸው በጭራሽ እንዳልታየ ነው የቆዩና እውነተኛ የሆኑ አማኞች ከጸሎት ልምምድ ተንሸራትተው ሊሆን ይችላል ይህም ለነሱ ለጉዳታቸውና ለሐፍረታቸው ነው ነገር ግን ሐዋርያት ሥራ እንደሚያሳየው ጸሎትን መገንዘብ በክርስትና ሕይወት ልምምድ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ እውነተኛ የመለወጥ የጸጋ ምልክት ነውፁ ይህም የሚያመለክተው እውነተኛ የሆኑ አማኞች ችግራቸውን ወደ ጌታ በጸሎት የማምጣት ውስጣዊ ተፈጥሮ ያላቸው መሆኑን ነው አዳዲሶቹ አማኞች ይህን በሚያደርጉበት ጊዜ እኛ የምንረዳው ነገር ቢኖር በእርግጥ ጌታን ማግኘታቸውን ው ደ አዲስ ልብ ሌላው ጠቃሚ የጸጋ ምልክት በሐዋርያትፉፁፌ ላይ ግልጥ ሆኖ ተ ጠቅሷል በጳንጠቆስጤ ዕለት የተለወጡት ሰዎች በአውነተኛ በማያመቻምች መሰጠትና የልብ ታማኝነት ይታወቁ እንደነበር በክፍሉ ተነግሮናል ይህም የተ ገለፀው ሄ ሪያ ተብሎ ነው በአዲሱ ትርጉም በቀና ልብ ተብሏል በሌላ አነጋገር በተለወጠው ሰው ውስጣዊ አሳብና ስሜት ውስጥ ታላቅ የሆነ ለውጥ ተክከናውኗል ይህም ለአግዚአብሔር ነገር በጣም ግልጥ ወደ መሆን ይመራዋል ለጌታም ነገር የመሰጠትና ንጹህ ዝንባሌ ይኖረዋል በአውነት የተ ለወጡ ሰዎች እግዚአብሔርን ለማስደሰትና የሕይወታቸውን መስመር ለመለወጥ በጣም ዝግጁ ናቸው መንፈሳዊ በረከትንና ዓለማዊ ዝናን በአንድ ጊዜ የመፈለግ ሁለት አሳብ የላቸውም። በመሆኑም በመንፈሳዊ ነገር ወዲያውኑ ይነካሉ የሚታዘዝ ልብ አግኝተው ለእግዚአብሔር ፈቃድና ለክርስትያናዊ ተግባራቸው በመንፈስ የነቁ ይሆናሉ አዲስ ዝንባሌ አመለካከትና አሳብ በልባቸው ገብቷል እንዲሁም አዲስ የሆነ የባሕርይ ተቋም ሁሉን ነገር ተረክቦታል ዓለምና በውስጧ ያለው የኃጢአት ደስታ በሙሉ ለጣዕማቸው ጎምዛዛ ይሆንባቸዋል ስለዚህም አሁን በጣም የሚወዱት ነገር በሙሉ ከእግዚአብሔር ጋር የተገናኘውን ብቻ ነው ምክንያቱም መቸቻ ያያሃቶ ሪባቸኦ ደሃም ስሰደያ ደያኘሪኛ ታቻ የሚለው ሰባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች የክርስቶስ ቃል እውነት ነውና ለመለወጥ የሚፈልገውን ሰው መንፈሳዊ ሁኔታ ለመለየት ስንፈልግ ልናይ የሚገባን ትክክለኛ የሆነውን የመለወጥን ምልክት ማለትም የባሕርይና የአመለካከት ለውጥን ነው እውነተኛ አዲስ አማኝ በግልጥና በሚታወቅ መልኩ የሚማርና የሚቀረፅ ነውፅ ቀደም ብሎ ትዕቢተኛና ጉረኛ የነበረው ሰው ሲለወጥ በድንገት ለመንፈሳዊ ጉዞው ርዳታና ምሪት ይፈልጋል በሰዎች ሕይወት በሚሆነው መለወጥ ብዙ ጊዜ እንደነቃለን ልባቸው ሙሉ በሙሉ ይለወጥና ትክክለኛ የሆነውን ነገር ለመሥራት እጅግ በጣም ይፈልጋሉ በአንዳንድ ሁኔታዎች አሁንም ግትርነትና ነገሮችን ያሰመቀበል አቋም ይኖራቸው ይሆናል ነገር ግን አጠቃላይ በሆነ መልኩ ግልጥ የሆነ የመማርና የመታዘዝ ምልክት ይታይባቸዋል አንድ ኩራተኛና ራሱን ከፍ አድርጎ ያይ የነበረ ሰው በድንገት ትሁት የሚቀርብና የሚማር ሆኖ መለወጡ በጣም ኃይለኛ የሆነ የመለወጥ የጸጋ ምልክት ነው። ያ እውነተኛ መለወጥ ነው በሌላ ጎኑ ተለወጡ የተባሉት ለዓለማዊ ንብረት ምኞት ፋሽን እና ሙዚቃ ሱሰኛ ሆነው ባልተለወጡ ጊዜና ከእግዚአብሔር ቃል አኳያ ተከታታይ ምክር ሲሰጣቸው የማይንቀሳቀሱ ወይም የማይነኩ ከሆነ አዲስ ልብ የመቀበላቸውን ነገር ፍጽም ልንጠራጠረው ይገባናል ይህ አዲስ ልብ ለጌታ ትልቅ አክብሮትና አድናቆት የያዘ ዝንባሌንና እንዲሁም የጠለቀ ፍቅር ይኖረን ዘንድ ያደርጋል በዚህ በያዝነው ክፍል ማለትም በሐዋ የምናነበው ፀሰዕው ይፉ ዩርሃቶ ያዮ የሚለውም ቃል የሚያመለክተው የአክብሮትን ወይም የመደነቅን ፍርዛት ነው አዲሱ ልብ ጌታን ለመታዘዝ በጣም ጠንቃቃና የሱን መገኘት ቅድስናና ኃይል በሚገባ የሚያውቅ ነው ሆኖም ምንም ጥንቃቄ የማያደርግና እንዲያውም አጂፊ የሆነ አማኝ ምናልባትም አዲስ ልብ በጭራሽ አልተቀበለ ይሆናል የክርስቶስ አምባሳደርነትን ባሕርይ ይዘው ሳይሆን ሥርዓት የለሽ በሆነና እግዚአብሔራዊ አክብሮት ፍጹም በሌለበት የታይታ ነጋዴነት ባሕርይ አንዳንድ የክርስትያን ስብሰባን ብዙ ጊዜ ሲመሩ የምናገኛቸው ሰዎችም ጉዳይ እንዲሁ ነው ጊዜ ባለፈ መጠን አማኞች የመጀመሪያ ፍቅራቸውን ይጥሉና በሚያሳዝን ሁኔታ በቀዘቀዘና ባለመታዘዝ ወራት ያልፉ ይሆናል ይህ በጣም ከባድ መንፈስ ቅዱስንም የሚያስቆጣ ስህተት ነው ነገር ግን በክርስትና ሕይወት መጀመሪያ ላይ የሚታየው ሞቅ ያለ ግልጥ ምላሽ የሚሰጥና ታዛዥ ልብ መታየቱ በጣም ግልፅ ነገር ነው በመሆኑም እንደ ዋነኛ የጸጋ ምልክት ሊቆጠር ይገባዋል ፊ የመጀመሪያው የደኅንነት ርግጠኝነት ሐዋብ የሚገልፀው በክርስትና ሕይወት የመጀመሪያ ልምምዳቸው ግልጽ የሆነ የደኅንነት ማረጋገጫ ወይም ርግጠኝነት ያገኙ ሰዎችን ነው በቁ የነሱ ደፅሃኝኑሦ በቁ ሰዌርያን ማወሰቸው እንዲሁም ፍቅራቸውና መሰጠታቸው ይህን ይጠቁማል ምንም እንኳ በሰይጣን ውጊያ ሰባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች በሚቀሰቀስ ጥርጥር የተነሳ ቢደበዝዝም እውነተኛ አማኞች በሙሉ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ የመሆናቸውን የመጀመሪያውን የአዲስ ሕይወት የደኅንነት ማረጋገጫ በረከት ይለማመዳሉ መጽሐፍ ቅዱስ በመለወጥ ጊዜ ለሁሉም ክርስትያኖች ስለሚሰጥ የማረጋገጫ ማኅተም ይናገራል ስለዚህም በኤፌ ላይ እንዲህ ይላል ሰናንቀም ዳግሞ ዖስው። ለማኝ ይሂያ ሰኗይ ዕመሆኑ በፊታ ዝብ ፈፇፆይና ታበ ፈሥናሥቻ ጋረ ቷሷጋጭ ይጾጎፅ መንፈሳዊ አማካሪዎች የደኅንነትን እርግጠኝነት በማጣት ለተቸገሩ አማኞች እግዚአብሔር አስቀድሞ ለነፍሳቸው ያደረገላቸው ምን እንደሆነ ኦንዴት ማሳየት እንዳሰባቸው ሊያውቁ ይገባቸዋል እነዚህ የተጠራጠሩና በፍርፃት ውስጥ ያሉ አማኞች እግዚአብሔር በነፍሳቸው ውስጥ የመሥራቱን ርግጠኝነትና መጽናናት የነዚህ መሠረቶች ካሉ ግልጥ በሆነ ማስረጃ ያገኙ ዘንድ አማካሪዎቹ እነዚህን የጸጋ ምልክቶች ከእነሱ ጋር አብሮ ለማየት መዘጋጀት አለባቸው የሰይጣን ውጊያ ምንም እንኳ በሐዋርያት ሥራ ሁለት ላይ ባይጠቀስም ሰይጣን በአዲሱ አማኝ ላይ ያለው ጥላቻ ተጨማሪና ጠቃሚ የደኅንነት ምልክት ነው ጠላት ሰይጣን ሁልጊዜ የሚንበለበሉትን የሱን ፍላዓዎች ማለትም ጥርጥርንና ፍርሃትን ወደ እውነተኛው አማኝ አዕምሮ ይተኩሳል አማኞች ስለወንጌል እውነትና ስለራሳቸው መንፈሳዊ እድገት በጥርጥር ተሞልተው ራሳቸውጎ በሚያገኙበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በልባቸው ውስጥ በጸጋው እየሠራ የመሆት ቀና ምልክት እንደሆነ መረዳት አለባቸው ያልዳነው ሰው በመንፈሳዊ እስራት ውስጥ ስላለ ብዙውን ጊዜ በሰይጣን ፍርዛትና ጥርጥር ውስጥ አይቸገርም ጌታ ኢየሱስ ይህን በሉቃስ ላይ አስተምሮታል ያኛ ቋው ጦሂ ይፆ ያራታን በሸቋቀ ያዘው ንዘሁ ዘያናም በሆናዕ በዚህ ቁጥር በታጠቀ ኃይለኛ ሰው የተ መሰለው ሰይጣን ነው እሱም የሚታየው ባሪያዎቹ በራሱ ቅጥር ግቢ ውስጥ እስከኖሩ ድረስ ሳያስጨንቃቸው ወይም ሳይጎዳቸው በደህና ጠብቆ እንደሚይዛቸው ተደርጎ ነው ዌስትሚኒስቴር ኮንፌሽን በሀሀ የወንጌላውያን አማኞች የእምነት አቋማቸውንና አንቀፃቸውን በጽሑፍ እንዲያዘጋጁ የእንግሊዝ ፓርላማ በ በሕግ ወሰነ በዚህ ውሳኔ መሠረት ጥልቅ የእግዚአብሔር ቃል ኦውቀት ያላቸው የእግዚአብሔር ሰዎች እንዲሁም ከስልሳ እስክ ሰማንያ የሚደርሱ አማኞች በተሳታፊነት ይገኙ በነበረበትና ሐምሌ ጀምሮ አምስት ዓመት ከስድስት ወር ከዛያ ሁለት ቀናት በፈጀ ጊዜ በዚያው በዌስትሚኒስቴር የእንግሊዝ ፓርላማ ውስጥ በተደረጉ ስብሰባዎች የተዘጋጀ የአቋመ እምነት ነው ይህ ኮንፌሽን አቋመ እምነት የእምነት አንቀፆችን የያዘና በእግዚአብሔር ቃል መሠረት በጥንቃቄ የተዘጋጀ ነው ስቋመ እምነቱ በዌስትሚኒስቴር ፓርላማ ውስጥ በተደረጉት ጉባኤዎች በመዘጋጀቱ ስሙን ያገኘው ከዚያ ነው ይህንን አቋመ እምነት በመላው ዓለም ያሉ የፕሪስቢተሪያን ቤተክርስትያን አማኞችና የታወቁት የፕሪስቢተሪያን መንፈሳዊ ኮሌጆች የክርስትና አምነት አጠቃላይ አስተምህሮን መመሪያ የያዘ መሠረታዊ ሰነድ አድርገው የሚጠቀሙበት ሲሆን ሌሎች ፕሮቴስታንቶችም እንደ ዋና የእምነት አስተምህሮ ማገናዘቢያነትና መመሪያ አድርገው በአክብሮት ይቀበሉታል ሰባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች ሆኖም እውነተኛ አማኞች ከእንግዲህ ወዲህ በሰይጣን ግዛት ውስጥ አይደሉም እነሱ ነዓ ወጥተዋል በመሆኑም አሁን ታላቅ ጦርነት በነሱ ላይ ተ ጀምሯል አሁን እነሱ መቋቸው ስዘቋያቆቸ ስሥዕጣሃቶ ስጸህም ስጩዘማ ፅም ቻፆቸ በያሚያዊም ፅዩራ ሳበ ስስፍተ መንሬቀጩያን ቓሠራዊቶ ነውሌ ፊራያሠጋ ስለዚህ የሚቸገሩበት የአአምሮ ነውጥ በጣም የሚጠሉት የጥርጥር ሐሳብ ብዙ ጊዜ የሚሰማቸው የእርግጠኝነት ማጣት እነዚህ ሁሉ ጌታ በእርግጥ ያዳናቸው ለመሆኑ ማስረጃዎች ሊሆኑ ይችላሉ በመሆኑም እነሱ አሁን በጦር ሜዳ ላይ ናቸው በአዳዲስ አማኞች ላይ ሰይጣን ጥቃቱን መክፈቱ በአንድ በኩል ብዙ ሞክሮ ያልተሳካለት ወይም የተሸነፈ መሆኑን የሚያረጋግጥና የሚያሳይ ተጨማሪ ማስ ርግጠኝነትና እነሱንም ለመዋጋት ምክንያት ያሰው መሆኑን ያረጋግጥላቸዋል ሰዎች እስከሚለወጡ ድረስ ምንም ያለማድረግ የጦርነት ሥልቱ በክርስትያን ቤተሰብ ውስጥ ባደጉ ሰዎች የሕይወት ልምድ ውስጥ ማለትም በእውነት ከመለወጣቸው በፊት የስም ክርስትያን ሆነው ዘመናቸውን ባሳለፉ ሰዎች ሕይወት ውስጥ ይታያል እነሱም ባለመለወጥ ዘመናቸው የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪካዊ ድርጊቶች ወይም የጌታ ኢየሱስን ሥራና አገልግሎት ብዙም ሳይጠራጠሩ ኖረዋል በእውነት ወደ ጌታ በተመለሱበት ሰዓት ግን መጠራጠር ይጀምራሉ። ይላል አዲስ አማኞች ስለሕይወታቸው በአውነት መዳን ወይም አለመዳን በተ መሰከተ የሚያደርጉት የመጨነቃቸው እውነት ራሱ የመለወጥ እርግጠኝነት ማስረጃ ነው እውነተኛ አማኞች ከሆኑ በነሱ ሕይወት ውስጥ በጣም ጠቃሚው ነገር የነፍሳቸው ጉዳይ ነው ለነሱ የመንፈሳዊ አቋማቸው ሁኔታ በጣም ጠቃሚ ነው በመሆኑም መጨነቃቸው በእርግጥ የእግዚአብሔር ልጅ መሆናቸውን ያረጋግጣል ያልተለወጡ ሰዎች ለመንፈሳዊ ሕይወት አቋማቸው ጉዳይ በጥልቅ ተጨንቀው ሲመላለሱ አይታዩም እነሱ ብዙ የሚያስቡት ለዚህ ዓለም ጉዳይ ነው ጥሪታኖች እንደሚጠሩት ቅዱስ ጭንቀት የሰውየው መዝገብ አሁን በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ለመሆኑ ጥሩ ማስረጃ ነው ሰባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች የምልክቶቹ ማጠቃለያ አውነተኛ ንስሐ ተከናውኗል ስለዚህም የተሰበረውና የተዋረደው ልብ ለምሕረትና ለጸጋ ወደ እግዚአብሔር ይመለከታል የእግዚአብሔር ቃል አዲስ መረዳትና ለቃሉ ሥልጣን መገዛት ጀምሯል ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገራችንን የምናውቅበት ከአግዚአብሔር ሕዝብ ጋር የመዋደድና የወገናዊነት ኃይለኛ ስሜት ተፈጥሯል ምስጋናና መንፈሳዊ መቃተት የተካተተበት አስደናቂ የሆነ የመጸለይ አዲስ ችሎታ ተጀምሯል ጸሎቶችም መልስ ተሰጥቷቸዋል ከአዲስ ደስታ ባሕርይ ልምምድና መሻት ጋር አዲስ የሆነ ልብ ተገኝቷል ምክንያቱም አዲሱ አማኝ ከዓለማዊ ሕይወት ነፃ ወጥቶ ወደ እግዚአብሔር ነገር ተመርቷልና ከአዲስ ልብ ጋር የቅድስና ሕይወት ጀምሯል ይህም እግዚአብሔርን የመታዘዝና የማስደሰት ፍላጎት ነው የእግዚአብሔር ሰላምና የእግዚአብሔር የመሆን የእርግጠኝነት የመጀመሪያ ስሜት በመንፈስ ቅዱስ መኖር አማካኝነት በልብ ውስጥ ተቀምጧል የዲያቢሎስ ጥቃቶች በአዳዲስ ፈተናዎች እንዲሁም ጥርጥርና ፍርሀት ስሜታቸው አሁን ጀምሯል ወይም ታውቋል መንፈሳዊ ጦርነቱ ጀምሯል የመለወጥ ምልክቶቹ በአንድ ጊዜ ይክሰታሉን። በጣም ብዙ ጊዜ በወንጌል ስብከት ስብሰባዎች ሰዎች ቀላል ውሳኔ እንዲወስኑ ወይም ለወንጌል ስብከቱ ቀላል የሆነ የአዕምሮ መስማማት እንዲያደርጉ ይገፋፋሉ ለዚህም ምላሽ ከሰጡ ወዲያውኑ እንደ ዳኑ ይነገራቸዋል ይህም የሚሆነው በአብዛኛው ጊዜ ከሚሰማቸው ስሜት ውጭ ነው አንድ ሰባኪ ወይም አገልጋይ ጌታን መቀበል እፈልጋለሁ ላለ አንድ ሰው ነፍስህ ድኗል ብሎ አጥብቆ ማረጋገጫ ይስጠው ብለን እናስብ ይህም ምንም ዓይነት የደኅንነት እውነተኛ ምልክት ሳይታይበት ነው ይህ ጌታን ፈላጊ ሰው በሕይወቱ መጠነኛ የሆነ ትህትና ያለው ቢሆንም እንኳ ጌታ ግን ገና የዳግም ልደትን በረከት ግንዛቤ አልሰጠውም ምክንያቱም ንስሐው ጥልቅ ስላይደለ ብለን ደግሞ እናስብ መንፈስ ግን በሰውየው ሕይወት ውስጥ እየሠራ ከሆነ ያን ጊዜ ውኑ ስለኃጢአቱ በጥልቅ እንዲያስብና እንዲስማው ከቪያም በጣም ትርጉም ባለው መልኩ እንዲናዝዝ ያደርገዋል ሆኖም በዚህ በኩል ክርስትያን አገልጋዩ የሰጠው ትክክለኛ ያልሆነው ማረጋገጫ ጌታን በሚፈልገው ሰው ሕይወት መንፈሳዊ እድገት ላይ ከፍተኛ የሆነ የጣልቃ ገብነት ተጽእኖ ያመጣል ምክንያቱም እንደ ዳነ ያስባልና ቀናትም እያለፉ በፄዱ ቁጥር ጌታን በሚፈልገው ሰው ሕይወት ውስጥ ምንም ለውጥ ያለመከናወኑ እውነታ ሰውየውን እያሳሰበው ይመጣል ምክንያቱም ሰባኪው ወይም መንፈሳዊው አማካሪ ተለውጠሀል ብለው ገፋፍተውታል ሌላም ሊያደርገው የሚገባ ነገር እንደሌለ በእርግጠኝነት ነግረውታል እሱ እራሱ ከሚስማው ስሜት ውጭ የተ ለወጠ ሰው መሆኑን ነግረውታል ይህም ነገር ሌላ ችግርን ያመጣል በውጤ ቱም ይህ ስው የተምታታበት ይሆንና በመንፈሳዊ ረዳቶቹ ሳይና ለጊዜውም እንኳን ቢሆን በወንጌሉ መልእክት ላይ ጭምር አመኔታ ያጣል ከዚህ የምናገኘው ትምህርት ጌታን ለመቀበል የሚፈልጉትን በምንረዳበት ወይም በምናማክርበት ጊዜ ልክ በሚከተለው የእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ብትዬፅጉት ታገኙታባችሁ በፍዜም ዕባችኩና ከዬዜም ነዬፍሳችኩ ከዩበጋችሁት ታገኙታሳችኩ ዜና ተብሎ በግልጥ እንደተቀመጠው የደኅንነት የተስፋ ቃል ኪዳን ሁል ጊዜ ብቃት ወይም ችሎታ ያለው መሆኑን በማረጋገጥ መሆን አለበት ቁልፍ የሆኑት ቃላትም ብቭትሄስጉት እና በፍዜም ናቸው ሰባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች በዚህ ሁኔታ ሰባኪው ወይም አማካሪው ጌታን ለሚፈልገው ሰው ንስሐ እንዲገባና በክርስቶስ እንዲሆን በቀላል መንገድ በግልጥ ካስረዱት ይህንንም በሙሉ ልቡ ቢያደርገው አንደሚድን በተጨማሪ ከነገሩት ምንም ዓይነት መምታታት አይኖርበትምፎ ሰባኪው ወይም መንፈሳዊ አማካሪው ጌታን ፈላጊውን ወዲያውኑ ሙሉ ለሙሉ ድነሀል ብለው ካላሉት በሚቀጥሉት ቀናት እሱን ለመርዳት የሚያስችልን ዕድል ጠብቀዋል ማለት ነው ጌታን ለመቀበል ፈላጊው አሁንም ገና ያልተባረከ መሆኑን ሲገነዘብ ከጌታ ጋር ያለውን አቀራረብ እንደገና ለመመርመር ዝግጁ ይሆንና መንፈሳዊ ርዳታ ለማግኘት ወደ ሰባኪው ወይም አማካሪው በሚገባ ይመለሳል ያን ጊዜ የእግዚአብሔር አገልጋይ ጌታን ፈላጊዎቹ ወደ እግዚአብሔር ሲቀርቡ ያደረጉትን አንዳንድ ስሀተቶች ለማብራራት ዕድል ያገኛል ጌታን ለመቀበል ፈላጊው እሱ ለራሱ ደኅንነት ሊጨምረው የሚችለው ምንም ነገር እንደሌለው አውቆ በቀራንዮ መስቀል በተሠራው ሥራ ብቻ ተማምኖ እንደሆነ ሊጠይቀው መቻል አለበት ጌታን ፈላጊው የራሱን ምኞትና ፈቃድ ክዶ ለጌታ ትእዛዝና ሥልጣን ራሱን መስጠቱንና አለመስጠቱን ሊጠይቀው መቻል አለበት ጌታን ፈላጊው ስለገባው ንስሐ እውነተኛነት እና የደበቀው የኃጢአት ባሕርይ ላለመኖሩና እነሱንም ሳይናዘዝና ሳይተው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የመግባት ተስፋ ሊኖር እንደማይችል በግልጥ ሊነግረው መቻል አለበት በእርግጥ ብልህ አማካሪ ወደ ኃጢአተኛው ዝርዝር የኃጢአት ምርመራ ውስጥ አይገባም ነገር ግን በአጠቃላይ ከሚታወቁት ኃጢአቶች ሁሉና ከጣዖታት የመመለስን አስፈላጊነት ያስረዳል ዝርዝር ምርመራ ውስጥ መግባት የንስሐ ወይም የነፍስ አባት የመሆን ጨዋታ ውስጥ መግባት ነው ይህም ወደ ሁለት ጎጂ ውጤቶች ይመራል አንደኛውሱ ሰውየው ለሰባኪው በመናዘዙ ኃጢአተኛ ሕሊናው እረፍት ያገኝና ከዚያ በኋላ ኃጢአቱን ለክርስቶስ የመናዘዝዙ አስፈላጊነት እንደሚገባ ላይሰማው ይችላል ሁለተኛው ደግሞነ ሰውየው ኃጢአቱን ለሰባኪው ወይም ለመንፈሳዊው አማካሪ በመናገሩ በጣም ያዝንና ከፍተኛ ሐፍ ረት ተሰምቶት ጭራሽ ወደ ቤተክርስትያን ላይመለስ ይችላል የሚያሳዝነው ነገር እነዚህ ሁለት ውጤቶች የኃጢአትን ዝርዝር በሚሰሙና ሞኝ በሆኑ መንፈሳዊ አማካሪዎች ሁል ጊዜ የሚታዩ መሆናቸው ነው ብልህ የሆኑ መንፈሳዊ አማካሪዎች ለነዚህ ደኅንነት ፈላጊዎች ነፍስ በተለያየ መንገድ የእግዚአብሔር መሣሪያዎች ወይም መጠቀሚያዎች በመሆን መቀጠል አለባቸው። ሰዎችን መለወጥ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው በመሆኑም የእግዚአብሔር አገልጋዮች ጉዳዩን ቶሎ ለመጨረስ በመሞከርና በጥድፊያ የእሱን ሥራ በፍጹም መቅደም አይኖርባቸውም ተቃራኒውን ስህተትም ስለመስራት ደግሞ በእርግጥ ልናስብ ይገባናል አንድ ሰው በእውነት ኃጢአተኝነቱ ተሰምቶት እውነተኛ ንስሐ ገብቶና ሙሉ ልቡን ለጌታ ሰጥቷል ብለን እናስብ በመሆኑም ይህ ሰው የእግዚአብሔርን እውነተኛ የመለወጥ የጸጋ ልምምድ አግኝቷል ሆኖም ይህ እውነተኛ አማኝ ከጥቂት ጊዜ ያት በኋላ የደኅንነት ርግጠኝነቱን በማጣት ይቸገራል ወይም ይሰቃያል ወዲያው ወይም ቆይቶ ይህንን ችግሩንና ጥርጥሩን ለመግለጥ ወደ ፓስተሩ ወይም ወደ ቆየው አማኝ ጋ ይቀርባል ይህ በችግር ውስጥ ያለ አማኝ ስባቱ ርግጠኛ የመለወጥ ምልክቶች ክርስትያናዊ ካልሆነ ሁኔታ ከሌላ ኃይማኖት የመጣ ከሆነ መንፈሳዊ ነገርን በተምታታ መልኩ ሊገልጥ ይችላል በመሆኑም መንፈሳዊው አማካሪ አልተ ለወጠም ብሎ ይገምትና እንደገና ወደ ቀራንዮው መስቀል ሥራ ተመልሶ በመሄድ የተናዘዘውን ሁሉ እንዲናዘዝ ይመክረዋል በግድ የለሽነት ምክር እውነተኛው የሰውየው መለወጥ ሳይታይ ቀርቶ እጅግ ብዙ የሆነ የልብ መሰበር ተከስቶ ያውቃል እንደዚሁም እውነተኛ አማኝ ሆኖ ለመዳኑ ርግጠኛ ያልሆነው ከዳኑት ኅብረት ውጭ እንዲወረወር ተደርጓል የደኅንነቱን ማረጋገጫ ባጣው ሰው ሕይወት ውስጥ የመለወጡ ማስረጃዎች መኖራቸውን ማረጋገጥ በአገልጋዮች እጅ ውስጥ የተጣለ ለመሆኑ ቀደም ብለን አይተናል በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ የመለወጥ ምልክት ካለ የኛ ሥራ የሚሆነው ለዚያ ተጠራጣሪ ነፍስ ይህንን ማስረጃ መግለጥና ማሳየት ነው ጌታ በሕይወቱቷ በግልጥና በሚገባ ከሠራው ሥራ ተነስተን ወደዚያ ሰው ወይም ሴት ሕይ ውስጥ ርግጠኛነትንና መበረታታትን በማምጣት ልንረዳቸው ያስፈልገናል ለእንደነዚህ ዓይነት ሰዎች ልናሳይ የሚያስፈልገን ሌላው ነገር ጌታ ለእውነተኛ አማኞች ለሠራው ለያንዳንዱ የጸጋ ሥራ ምስጋና አለመስጠት ስህተት መሆኑንና ከጌታ ምስጋና መስረቅ እንደሌለብን ጭምር ነው ለሌሎች ብቃት ያለን መንፈሳዊ ረዳት ለመሆን እንችል ዘንድ የመለወጥ ምልክቶቹን ማወቅ እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው መጽሐፍ ቅዱሳዊውን ኃላፊነታችንን ለመወጣት በአጥቢያ ቤተክርስትያናችንም ውስጥ ዳግም የተወለዱ አባላት እንዲኖሩ ለማድረግ ይህን መረዳት በጣም ጠቃሚ ነው።