Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ብለው የሚጠይቁ አሉ አንዳንድ ጊዜ ዳኛው መሰረታዊ የሰብአዊ መብትንና ሰብአዊ ክብርን የሚጥሱ ህጎችን መሰረት አድርጎ የመወሰን አጣብቂኝ ውስጥ ሊገባ ይችላል እንዲህ ባለጊዜ አራሱን ከዳኝነት ሀላፊነት በማግለል ለፍትህና ለሰብአዊነት ያለውን ታማኝነት ማሳየት አለበት ምክንያቱም ዳኞች ወደዚህ ኃላፊነት በሚመጡበት ጊዜ ለፍትህና እውነት መከበር እንቆማለን ብለውና ምለው ነው ፍትህና አውነት ደግሞ የህግ የበላይነትና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ የተመሰረተባቸው ፅንሰ ሀሳቦች ናቸው ለነዚህም እሴቶችም ዳኞች በፅኑ መቆም የሚችሉት ለህግ መከበር ፍፁም ታማኝ ሲሆኑ ብቻ ነው ማከናወን ያለባቸውኞ በርግጥ በብዙ ሀገሮች የዐቃቢያነ ህግ ተቋማት በስራ አስፈፃሚነት የመንግስት አካል አንድ ጉዳይ ላይ ክስ መስርተህ ተከራከር የሚል የበላይ ትእዛዝ ቢመጣ ምን ማድረግ አለበት። ጉዳዩን ስለማውቀው ብሎ መዝገቡን መዝጋት ነው። ወይስ በጉዳዩ ላይ እኔ ክስ አልመሰርትም ብሎ መተው ነው።
ፍዐበፀ በቧሃ በወጩጪቧበ ሀዐኳ ዐህ በ ከፀሃ ዝብ ከ ክከ ርከ ህዐዝ ከ በ በሃከ ህከ ከከቨ ከ ከ ከርሃ ከ ርዐክከከሀ ዐ ከከፀ ፍኗሠ ዐ ልፍ ዝዩ ቪከዐዝ ኒ ከሀከሺ ሂከፀር ከ ፍጪበ ዐ ርዐከበሬርኒ ከዐቪከ ከ ዉበ ዐሀቪ ዐ ርዐክቪ ዝከርከ ር በኗዐበፀበ ሂዐ በበጠ ርዐክቨበፀከርፀ ከ ከከዐኗፀ ፀኗዐፀርከዐሽኗ አነዚህ ተቋማት ጥሩ ሥነምግባር በተላበሱ ሙያተኞች በሚገባ የተደራጁ ካልሆኑ ከአድሎ የጸዳና ፍትሃዊ አገልግሎት ሊያበረክቱ አይችሉም ቢችሉም እንኳን በህብረተሰቡ ዘንድ ካልታመኑ ብዙም ፋይዳ አይኖረውም ለዚህ ነው ፍትህ ማድረግ ብቻውን በቂ አይደለም ፍትህ መደረጉን ሌሎችም መገንዘብ መቻል አለባቸው የሚባለው የፍትህ ተቋማት ለአውነተኛ ፍትህ የቆሙ መሆኑን ህብረተሰቡ የሚረዳው በነዚህ ተቋማት ያሉ ሙያተኞች ሁሉ በሥነምግባራቸው ላቅ ያሉና ለሌሎችም አርአያ መሆን የሚችል ባህርይ ወይም በጎ ምግባር በሥራቸውና በሚሰጡት አገልግሉት ሄደት ሲያሳዩ ነው ስለዚህም ዜጎች በህግ ልእልና እንዲያምኑና በዴሞክራሲያዊ ባህል አለመግባባቶችን እንዲፈቱ የፍትህ ተቋማት ጥሩ ሥነምግባር ያላቸውን ሙያተኞች ለማፍራት ትኩረት አድርገው መንቀሳቀስ ይገባቸዋል ከዚህም የተነሳ የነዚህ ተቋማት ህልውናና ተቀባይነት በዳኞች ወይም አቃብያነ ሕግ መልካም ሥነምግባር ላይ የተመሰረተ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በ ባሰራጨው የሙስና ሁፄታ ሪፖርት ሙስና በአብዛኛው የአለማችን ሀገሮች ለፍትህ መዓደል በተለይም የወንጀል ሰለባዎችና የተከሰሱ ሰዎች ፍትዛዊና ከአድሎ ነጻ በሆነ መልኩ የመዳኘት መብት እንዳይከበር ምክንያት መሆኑን ያብራራል ይህ ሁኔታ በሀገራችንም ቢሆን ተመሣሣይ ገጽታ ያለው በመሆኑ ጥሩ ሥነምግባር ያላቸው የሕግ ሙያተኞችን በመፍጠር በፍትህ ተቋማት አካባቢ የሚታየውን ሙስናና ብልሹ አሠራር ከሥር መሠረቱ ማስወገድን ይጠይቃል በተለይም ዳኞች በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ የበጎ ምግባርና ግብረገብ መገለጫ እንደመሆናቸው መጠን ህብረተሰቡ መብቶቹ ሳይከበሩ ሲቀሩ ወደ ፍርድ ቤቶች የሚመጣ በመሆኑ ያለ አንዳች አድሎ በመሥራት በህብረተሰቡ ተአማኒነት ማግኘት ይገባቸዋል ህብረተሰቡ የፍትህ ተቋማት ከሙስና የፀዱ አይደሉም ብሎ ማመኑ በራሱ በጣም አደገኛ ነው በፍትህ ወይም በሕግ ልዕልና ላይ ህብረተሰቡ ጥርጣሬ ካሳደረ ልማትም ሆነ ዴሞክራሲ አይታሰብም ይልቁንም ሙስና ይንሰራፋል ለዚህ ነው የሙያ ሥነምግባር ለልማትም ሆነ ለዴሞክራሲ እንዲሁም ለመልካም አስተዳደር መረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው የሚባለው የዳኝነት ሥርዓቱ ባጠቃላይ የህዝብ አደራን የተሸከመ በመሆኑ በፍትህ አስተዳደር ሥራ ላይ የላቀ ሥነምግባር ባላቸው ሙያተኞች የተደራጀ መሆን ይገባዋል የሥነምግባር አስፈላጊነትም ከዚህ አንጻር ነው መመዘንና ትኩረት ማግኘት ያለበት ዳኞች እና አቃቤ ህጎች በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀጽ መሰረት ህገመንግስቱን የማክበርና የማስከበር ሀላፊነት አለባቸው ፐክኪርሃ ሀሀኳ በተለይም በአንቀጽ የተቀመጡትን መሰረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ከማክበር ባሻገር የማስከበር ሀላፊነት ስላላቸው ይህን ህገመንግስታዊ ግዴታዎችን በአግባቡ እንዲወጡ ይህንን ያለአግባቡ ሲሸራረፉ ወይም ስልጣናቸውን ያለአግባብ ሲጠቀሙና ፍርድን ሲያዛቡ ደግሞ ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማስቻል ሙያቸው የሚመራበትን የስነምግባር መርሆዎች ጠንቅቀው ማወቅና መተግበር ይጠበቅባቸዋል ክፍል ሁለት የዳኝነትዓቃብያነ ሕግ የሙያ ሥነምግባር በጠቅላላው ዝርዝር አላማዎች ሰልጣኞች ይህንን ክፍል ሲያጠናቅቁ የዳኞችንና የአቃቤ ህጎችን የሙያ ስነምግባር ለመወሰን በአለም አቀፍ ደረጃና በአገር ውስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና ክንዋኔዎችን ያስረዳሉ የዳኝነት ነጻነትን ለማረጋገጥ ከዳኞች የሚጠበቁ ሙያዊ ስነምግባራዊ ባህርያትን መለየትና ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ ከአድልዎ በጸዳ መልኩ ለመስራት የሚያስችለውን የዳኝነት ባህርይን መለየትና ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ የፍርድ ስራን በሀቀኝነት ለማከናወን ከዳኛው የሚጠበቁ ሙያዊ ስነምግባራዊ ባህርያትን ተረድተው ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ ዳኛው ሊያከብራቸው የሚገቡ የቅንነት ባህርይ መገለጫዎችን ተረድተው ተግባራ ማድረግ ይቸላሉ በዳኝነት ስራ የእኩልነት መርህን ተረድተው ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ በዳኝነት ስራ ትጋትና ጥረት ማሳየት አስፈላጊነትን ይረዳሉ በተግባራቸውም ለዚህ ዝግጁ ይሆናሉ አቃቤ ህግ አመዛዛኝና ከአድልዎ በጸዳ መልኩ መስራት እንደሚገባው ይረዳሉ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መነሳሳት ይኖራቸዋል ፍትሀዊነት የአቃቤህግ ሊያከብረው የሚገባ ባህርይ መሆኑን ተረድተው ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁ ይሆናሉ አቃቤ ህግ ስራውን ለማከናወን ነጻነት እንደሚያስፈልገውና ከነጻነት ጋር በተያያዘ ከአቃቤ ህግ የሚጠበቁ ባህርያትን ይገልጻሉ ከአቃቤ ህግ ስለሚጠበቅ ተጠያቂነት ይረዳሉ ምስጢር የመጠበቅ የአቃቤ ህግ ሀላፊነት መሆኑን ተረድተው ያውቃሉ የሙያ ብቃት ከአቃቤ ህግ የሚጠበቅ ባህርይ መሆኑን ይረዳሉ መግቢያ ሕግ እንደ አንድ የሙያ ዘርፍ በታሪክ ቀደምትነት ካላቸው ሙያዎች መካከል የሚመደብ ነው ታሪክ እንደሚያሳየን ከሆነ ሕግና የሕግ ሙያተኞች ከቀደምት ጊዜ ጀምሮ የተደራጁ ማህበረሰቦች ሁሉ ዓይነተኛ መገለጫ ሆነው መሰንበታቸውን ነው ዊድሮው ዊልሰን የተባሉ አንድ ምሁር ማንኛውም የፖሊስ ጥያቄ በሂደት የህግ ክርክር የሚያስነሳ ጭብጥ መሆኑ አይቀርም » ብለው የተናገሩት በተለይም ዛሬ የዓለም አቀፍ ህብረተሰብ ለሕግ ልዕልና መልካም አስተዳደርና ሰብዓዊ መብቶች መከበር ከሰጠው ትኩረት አንጻር ስንመዝነው ሕግና ፍትህ በታሪክ ብቻ ሳይሆን ዛሬም የሰው ልጆች መሠረታዊ እሴት መሆናቸውን ነው ፕሮፌሰር ሮናልድ አሮንሰንና ዶናልድ ዌክስቴይን የሕግ ሙያተኞች በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና ሲያብራሩ እንዲህ በማለት ነው ጪለነፎጩ በከህበበበ። ዝኒ ከማሁ አንቀጽ የባንግሎር የዳኞች ስነምግባር መርሆዎች ሀተታ ዘምክንያት ይመልከቱ የዓለም ክፍሎች ክፍለ አህጉራዊ የሆነ የዳኞች ነጻነትን በተመለከት የተደረሱ በርካታ ስምምነቶች እንዳሉ ሳንጠቅስ አናልፍም በተለያየ ጊዜያት በዚህ ረገድ ከተደረጉ ዓለምአቀፍ እንቅስቃሴዎች ሁሉ በተሟላ መልኩ ዳኞች የሚመሩባቸውን የሥነምግባር ደንቦች ለመጀመሪያ ጊዜ በዝርዝር ለማስቀመጥ የተሞከረው በባንግሎር የዳኞች ሥነምግባር መርሆዎች ላይ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል በአፕሪል ዓም የተባበሩት መንግሥታት አስረኛው የወንጀል መከላከልና የእስረኞች አያያዝ ኮንግረስ ጉባዔ በሚካሄድበት ወቅት በቪዬና ኦስትሪያ ከአፍሪካ ከኤሲያና ፓሲፊክ አካባቢ የተውጣጡ የ ሀገሮች የፍቤቶች ኃላፊዎችና ሲኒየር ዳኞች ተካፋይ በሆነበት ስብሰባ የራሳቸውን ተቋም ሥርዓት ለማስያዝና ተጠያቂነታቸውን ለማረጋገጥ ዳኞች የሚመሩባቸውን የሥነምግባር መርሆዎች በዓለምአቀፍ ደረጃ ማውጣቱ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ጁዲሺል ኢንቴግሪት ግሩፕ የሚባል ቡድን ተቋቁሞ ዓለምአቀፋዊ ይዘት ያለው ሰነድ አጥንቶ እንዲያቀርብ ኃላፊነት ተሰጥቷል ለዚህም ተግባር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ያነሳሳው ዋንኛው ነገር በተለያዩ ሀገሮች ሕዝቡ ከዳኝነት ተቋማት ላይ ያለው እምነት በሙስናና በአድሎዊ አሠራር ምክንያት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሸረሸረ መምጣቱን የሚያሳዩ የተለያዩ የጥናት ውጤቶች በመበራከታቸው እንደሆነ አንዳንድ ዋቢ ጽሁፎች ያስረዳሉ ጁዲሺያል ኢንቴግሪቲ ግሩፕ ተብሎ የሚጠራው ቡድንም እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በፌብሩዋሪ ዓም በህንድ ባንግሎር በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እስፖንሰር አድራጊነት ተሰብስቦ በሙያተኞች የቀረበለትን ረቂቅ ደንብ ከመረመረ በጊላ የሥነምግባር ደንቡን ዋንኛ እሴቶችና መርሆዎች በዝርዝር አስቀምጦ የመጀመሪያውን ረቂቅ የባንግሎር የዳኞች ሥነምግባር መርሆዎችን አጽድቋል ከዚህም በኋላ ይህ ረቂቅ ደንብ በጁን ዓለም በአውሮፖ ህብረት የዳኞች የጋራ የምክክር ጉባዔ ላይ ቀርቦ በውይይት እንዲዳብር ተደርጓል ከዚህም በተጨማሪ በኖቬምበር የኮንቲነንታል የሕግ ሥርዓትን የሚከተሉ ሀገሮችብራዚል ዝኒ ከማሁ ለምሳሌ ያህል የኦገስት ቱ የቤይጂንግ የዳኝነት ነጻነት መሰረታዊ መርሆዎች የላቲመር ሃውስ ጋይድላይንስ ተብሎ የሚጠራው ሰነድና የቱ የአውሮፓ ህብረት የዳኞች ቻርተር መጥቀስ ተገቢ ነው ቼክ ሪፐብሊክ ግብፅ ፈረንሳይ ሜክሲኮ ማዛንቢክ ሆላንድኖርዌይና ፊሊፒንስ የፍቤት ኃላፊዎች በተሳተፉበት መድረክ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል በዚህ ውይይትም በአብዛኛዎቹ የሥነምግባር ደንቡ አሴቶችና መርሆዎች ላይ የኮሞን ሉውና የኮንቲነንታል ሎው ሀገር ዳኞች ከስምምነት የደረሱ ሲሆን በጥቂት ጉዳዮች ላይ ብቻ መጠነኛ ልዩነቶች ተስተውሏል ከታዩት ልዩነቶች መካከል ለአብነት ለመጥቀስ ያህል የሥነምግባር መርሆዎቹ የቅደም ተከተል ሁፄታ የሥነምግባር ደንቡ መጠሪያ ኮድ መባል አንደሚገባው እንዲሁም በሰነዱ መግቢያ ላይ የዳኝነት ሥልጣን ምንጩ የህብረተሰቡ የዳኝነት ተቋሙን ሞራላዊ ሥልጣንና በሀቀኝነት የመዳኘት ሁኔታን የመቀበሉ ጉዳይ ነው የተባለው የዳኝነት ሥልጣን ምንጭ ሕገ መንግሥት ነው ተብሎ አንዲሻሻል የሲቪል ሎው የሕግ ሥርዓት የሚከተሉ ሀገሮች ዳኞች ጠይቀዋል ከዚህ በኋላ ነው የባንግሎር መርሆዎች የዳኝነት ነጻነትን ሚዛናዊነትን ምሉዕ ስብዕናን ቅንነትን እኩልነትን ብቃትና ትጋትን እና መሠረታዊ የሥነምግባር አሴቶች በማቀፍ የተቀረጸው ለማለት ይቻላል በአፕሪል ይህ ሰነድ ለተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ቀርቦ ሀገሮችና የተባበሩት መንግሥታት የተለያዩ ተቋማት የቀረበውን ረቂቅ ሰነድ እንዲያጤኑ ጋብዞ ነበር በአፕሪል ዓም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት የወንጀል መከላከልና የወንጀል አስተዳደር ኮሚሽን የተባበሩት መንግሥታት ኢኮኖሚና የማህበራዊ ጉዳዮች ካውንስል አባል አገራት ፍቤቶቻቸው ይህን ሰነድ መነሻ በማድረግ የዳኞችን የሥነምግባር ደንብ ከዚህ አንጻር በመቃኘት እንዲያወጡ ወይም እንዲያሻሽሉ የጠየቀ ሲሆን በዚህም መሠረት በጁላይ የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ካውንስልም የባንግሎር የዳኝነት ሥነምግባር መርሆዎችን በውሣኔ ቁጥር ጀዕዐዕዐር አጽድቋል ዝኒ ከማሁ የአቃብያነት ህግ ባለሙያዎችን በሚመለከት የዐቃብያነ ሕግ አደረጃጀትና በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና በየአገሩ የተለያየ ከመሆነ የተነሳ ረዘም ላለ ጊዜ አንድ ወጥ የሆነ ዓለምአቀፋዊ የሥነምግባር መርህን ለአቃብያነ ሕግ ማውጣቱ አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አቃብያነ ሕግ የሚመሩበት የሥነምግባር ደንብ እንዲወጣ የተለያዩ ግፊት የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የታዩ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ሁለቱን ለአብነት ያህል መጥቀስ ይቻላል በመጀመሪያ ደረጃ የተለያዩ የዓለም ሀገራት አለምዓቀፋዊ ሰብዓዊ መብት ስምምነቶችን መፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህ ስምምነቶችም በአግባቡ እንዲከበሩ የዐቃብያነ ሕግን የላቀ ተሳትፎና ሚና የሚጠይቁ ናቸው ከተባበሩት መንግሥታት ቻርተርና የሰብዓዊ መብቶች ሁሉ አቀፍ መግለጫ ባሻገር የዐቃብያነ ህግን ከፍተኛ ተሳትፎ የሚጠይቁ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶች የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለምአቀፍ ስምምነት ማሰቃየትንና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸው ሰብአዊነት የጎደላቸውና አዋራጅ የሆነ አያያዞችንና ቅጣቶችን ለማስቀረት የተደረገ ስምምነት የህጻናት ኮንቬንሽን ወዘተ መጥቀስ ይቻላል እነዚህ ስምምነቶች ለሰብዓዊ መብት አያያዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸውን ከፍርድ በፊት የተያዙና የተከሰሱ ሰዎችን መብት ይደነግጋሉ ለምሳሌ በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች በፍጥነት ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡየሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ እንዲሁም ፍትፃዊ በሆነ መልኩ የመዳኘትና ራስን የመከላከል መብትን የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ መጥቀስ ይቻላል ከዚህ በተጨማሪም ዐቃቤ ሕግ ገለልተኛ አካል እንደመሆኑ መጠን በወንጀል ምርመራ ሂደት የተያዙ ሰዎች ሰብዓዊ መብት በሚጣስበት ጊዜ የመርማሪ አካላትን ሕግ የተላለፈ ርምጃ የማረም ኃላፊነት እንዳለበት ይገነዘባሉ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ እና ሰብዓዊ መብት ሁሉን አቀፍ መግለጫ አንቀጽ እና ማሰቃየትንና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸው ሰብዓዊነት የጎደላቸውና አዋራጅ የሆኑ አያያዞችንና ቅጣቶችን ለማስቀረት የተደረገ ስምምነት አንቀጽ ከላይ የተዘረዘሩት የአስገዳጅነት ባህርይ ያላቸው ስምምነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች አለምዓቀፋዊ ይዘት ያላቸው አስገዳጅ ያልሆኑ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ልብ ማለት ያስፈልጋል ለምሳሌ አንደ አውሮፖ አቆጣጠር በ ዓም የፀደቀውን የተባበሩት መንግሥታት የዐቃብያነ ህግ ሚናን በተመለከተ የወጣውን መመሪያ መመልከት ይሻል ይህ መመሪያም ዓቃብያነ ህግ የሚመሩበትን የተግባር መርሆዎችና የሥነምግባር እሴቶችን የያዘ ነው በአርግጥ የዚህ መመሪያ ድንጋጌዎች በመንግሥታት ላይ የአስገዳጅነት ባህርይ ባይኖራቸውም የመንግሥታትን ሀሣብ ስለሚገልጹ በትብብርና በቅን ልቦና መንፈስ በመንግሥታት ላይ ኃላፊነት ሊያስከትሉ ይችላሉ በሁለተኛ ደረጃ ዐቃብያነ ሕግ አለም አቀፋዊ ጠባይ ያላቸውን የሥነምግባር ደንቦች ማውጣት አስፈላጊ ያደረገው በአሁኑ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣው ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ ወንጀሎች ናቸው እነዚህን የተደራጁ ወንጀሎች መከላከልም ሆነ መቆጣጠር በተለያዩ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ዐቃብያነ ሕግን ትብብር የሚጠይቁ በመሆኑ ለዚሁ ትግል ፍሬያማነትም የዐቃብያነ ህግን የሥነምግባር ደንብ በጋራ ማበጀቱ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ከዚህ ዓይነት አስተሳሰብም በመነሳት የአውሮፓ ህብረትም ክዕዐጠዘከበከከበ ዐበ ከ ዐ። ዳኛ ለሚሰጠው ውሳኔ በፍሬነገር በቀረበው ማስረጃና በህግ ላይ ብቻ ተመስርቶ መወሰን አለበት ይህ መሰረታዊ የሆነው የስነምግባር መለኪያው ነው የዳኝነት ነጻነት ማረጋገጫውም ይህ ነው ህገመንግስት አንቀጽ ዳኛ በህግ መሰረት ብቻ ይወስናል ይላል አንድ ዳኛ የዳኝነት ሥራውን በፍጹም ነጻነት የቀረበለትን ክርክር ፍሬ ነገር በህጉ አንጻር ብቻ በመመዘን ያለ አንዳች ቀጥተኛም ሆነ ቀጥተኛ ያልሆነ ውጪያዊ ተጽኖ ማባበያ ግፊት ማስፈራሪያ ወይም ጣልቃ ገብነት ሳይበገር በህጉ አግባብ መወሰን ይኖርበታል ከውጪ የሚመጡ ተጽኖዎች በምንም መልኩ የዳኛው ውሣኔ ላይ አሻራ ሊኖራቸው አይገባም ይህ የሚሆን ከሆነ ግን ህብረተሰቡ በዳኝነት ተቋሙ ገለልተኝነት ዙሪያ ያለው እምነት ስለሚሸረሽር የፍቤቶች ውሣኔዎች ፍትፃዊነት ከጥርጣሬ ይገባል ስለዚህም ዳኞች የፍቤት ውሣኔዎች በውጪያዊ ተጽእኖ የሚቃኙ መስለው ለህብረተሰቡ እንዳይታዩ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል ይህ በራሱ ህብረተሰቡ በፍትህ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲኖረው ከማድረጉም በላይ የዳኝነት አካሉን ነጻነትም ለማጠናከር የራሱ የሆነ በጎ ጎን አለው ይህ ማለት ዳኞች ለተለያየ ተጽእኖ አይጋለጡም ማለት አይደለም ቢሆንም የዳኞች ሊዐቨኪ ፐከፀ ዐፎር ዐ ሀከፀ ሀበርቋሃጋ ፀቧሀ ኗ ጠአዐበ ኳ ከፀ ርዐአበበቪኘ ዐከ ጪቧጪዐ ከርቨ ዐኳ ር ር ግዴታ ግን ህግን በአግባቡ ከቀረበላቸው የክርክር ጭብጥ አንጻር አመዛዝኖ ያለ አንዳች አድሎና ፍርሃት ወይም ውሣኔው ሰፊ ተቀባይነት ላያገኝ ይችላል ብለው ሳይሰጉ መወሰን መቻል ነው ዳኞች ከህብረተሰቡ ውዳሴ ለማግኘት ወይም ትችት እንዳይደርስባቸው በመስጋት ውሣኔዎችን ሊወስኑ አይገባም አንዳንድ ጊዜ በሚዲያ አማካይነት ዳኞች በያዚቸው ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ የሆነ ክርክር ሊነሳ ይችላል እነዚህ የሕዝብ ግፊቶችም አንዳንዴ ወደ አንድ ዓይነት ውሣኔ እንድንደርስ የሚገፋፉን ሊሆኑ ይችላሉ ነገር ግን ዳኛው በፍርድ አሰጣጥ ሄደት ከነዚህ የሕዝብ ግፊቶችና አስተያየቶች ራሱን በማግለል በነጻነት መወሰን ይገባዋል ከዚህ በላይ የተገለጸው ነገር እንደተጠበቀ ሆኖ አንድን የውጭ ድርጊት አንደተጽእኖ ወይም ግፊት ለመቁጠር ዳኛው በሚገባ የነገሩን ሁፄታ በማመዛዘን መለየት አለበት። ይህም ማለት በአንድ በኩል የዳኝነት ሥራን ከአላስፈላጊ ተጽኖዎች የመጠበቅ እና በሌላ በኩል ደግሞ በህብረተሰባዊ ጉዳዮች ላይ መንግሥትም ሆነ ፕሬሱ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ትችት ሊያቀርቡ እንደሚችሉና ዴሞክራሲያዊ ባህልም ይህንን እንደሚፈቅድ ዳኛው ከግምት ማስገባት ይኖርበታል ስለዚህም ዳኞች በሕግ አግባብ በውሣኔያቸው ይዘት በሰጡዋቸው ምክንያቶች ዙሪያ እንዲሁም በውሣኔ አሰጣጥ ፃዛደቱ ላይ ትችት ቢቀርብባቸው እንደተጽእኖ ሊቆጥሩት አይገባም በዳኞች ላይ የሚመጡ አንዳንዶቹ የግፊት ዓይነቶች የዕዝ ሰንሰለታቸውን ጠብቀው ህጋዊ ሊመስል በሚችልና በሚያሳስት መልኩ ሊቀርቡ ይችላሉ ስለዚህም ዳኞች በዚህ ረገድ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ተደጋጋሚ ተጽእኖ የመፍጠር ሙከራዎች ከተደረጉበት ዳኛው ለተገቢው አካል ሪፖርት ማድረግ ይገባዋል ዳኛው ባጠቃላይ ከህብረተሰቡና በተለይ ደግሞ ከተከራካሪ ወገኖች ጋር ገለልተኝነቱን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ግንኙነት መመስረት የለበትም በርግጥ እንዲህ ሲባል ከህብረተሰቡ ሙሉ በሙሉ ተነጥሎ ገዳም ውስጥ መኖር አለበት ማለት አይደለም ዳኛው ከጓደኞቹ ከስራ ባልደረቦቹና ከሚዲያ ጋር በሚያደርገው ግንኙነት ለተለያዩ አመለካከቶች የሚጋለጥበት ሁኔታ ይኖራል ይህ ደግሞ ዳኛው ከህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን ነገር እንዲረዳ እንዲያውቅና አእንዲላመዳቸው እንዲሁም ከነርሱ ጋር አብሮ እንዲኖር ይጠይቃሉ ዳኞች የተለያዩ አጨቃጫቂ ማህበራዊና የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን እንዲወስኑ ይጠየቃሉ ዳኛው ከማህበረሰቡ ተገልሎ በሚኖርበት ጊዜ የሕዝብ ጥቅምም ሆነ የዳኘው የግል ስብእና ዕድገት ይጠበቃል ብሉ ማሰብ የዋህነት ነው የተለያዩ የሕግ ድንጋጌዎችም ዳኛው የአንድ ምክንያታዊ ሰው አስተሳሰብን ከግምት በማስገባት ውሣኔዎችን አንዲሰጥ ይጠይቃሉ በዛሬው አለም ከማህበረሰቡ የተገለለ ዳኛ በፍርድ ሥራ ላይ ውጤታማ እንዲሆን የቀረበለትን ፍሬ ነገር መርምሮ ጭብጡን በማውጣት ወደ ውሳኔ ለሚደረግ ጉዞ ዳኛው ልምዱንና በልምድ የዳበረ ስሜቱን ርዐጠጠከ ከ በ ኦህፀበበር በመጠቀም ለቀረበለት ክርክር እልባት መስጠት ይገባዋል ስለዚህም ዳኛው ተገቢ በሆነ ደረጃ ከህብረተሰቡ ሳይርቅ የዳኝነት ተግባሩን ማከናወን ይኖርበታል ይሁንና አንድ ክርክር በሚያጋጥምበት ጊዜ ዳኛው አግባብነት ከሌላቸው አድሎአዊ አመለካከቶችና አስተሳሰቦች ነጻ መሆን ይኖርበታል በተለይም ፍትፃዊና ገለልተኛ የሆነ ፍርድ እንዳይሰጥ አክል የሚፈጥሩበትን ግንኙነቶች አድሎአዊ አስተሳሰቦችና አመለካከቶችን መጠንቀቅ አለበት ከዚህ አንጻር ተከራካሪ ወገኖች በግል ለመገናኘት የሚያቀርቡለትን ጥያቄ በተቻለ መጠን ከመቀበል መቆጠብ መቀበል አስፈላጊ መስሎ ከታየው ዳኛው ከመገናኘቱ በፊት የግንኙነቱ አላማ ምን እንደሆነ መጠየቅና ማጣራት ዳኛው በግንኙነቱ ጊዜ በክርክሩ ተከራካሪ የሆነ ወገኖች አቃቤ ህግ ጠበቃው እንዲገኙ ማድረግ ይኖርበታል የዳኝነት አካሉ ነጻ መሆን ብቻውን በቂ አይደለም ነጻ መሆኑ በሌሎች ዘንድም ግንዛቤ ሊወሰድበት የሚገባው ጉዳይ ነው ይህም ማለት አንድን የዳኝነት ተቋም ነጻ ሊያሰኙ የሚችሉ መሠረታዊ ነጥቦችን ያሟላ መሆኑ በሌሎችም ሊታመን ይገባል በእርግጥ የዳኝነት ነጻነት በተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ ወይም ዋስትናዎች ላይ የተመሰረተና የፍቤትን ነጻነት አስመልክቶ ያለ አዕምሮአዊ ሁኔታን የሚመለከት ቢሆንም አንድ የዳኝነት ተቋም ነጻ ነው ወይስ አይደለም ብሎ ለማለት ዋናው ቁም ነገር ምክንያታዊ የሆኑ ሌሎች ተመልካቾች በዚህ ረገድ ያላቸው አይታ ወይም ምልከታ ነው ሊባል ይችላል የዳኝነት ነጻነት መኖሩ ብቻ ሳይሆን የዳኝነት ነጻነት እንዳለ ህብረተሰቡ ሊያምነ ይገባል ስለሆነም ህብረተሰቡ በዳኝነት ነጻነት መኖር ላይ ምክንያታዊ የሆነ ጥርጣሬ እንዲያሳድር በር ከሚከፍቱ ባህርዮች ዳኛው አራሱን መጠበቅ ይኖርበታል ዳኛው ከህግ አውጪውና ከሥራ አስፈጻሚው አካል ጋር ተገቢ ያልሆነ ግንኙነት መመስረት የለበትም ከነቪህ አካላት ተጽእኖ የሚደረግበት መስሉ መታየትም አይኖርበትም ሁሉም የመንግሥት አካላት በተለይም የሥራ አስፈጻሚው ክፍል ህገመንግሥታዊ ድንጋጌዎችንና በአለም አቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ሰነዶች የተረጋገጡትን መብቶች አክብሮ መንቀሳቀሱን ፍቤቶች ሊያረጋግጡ ይገባል ፍቤቶች ነጻ መሆን ይገባቸዋል የሚለውም እነዚህን ወሳኝነት ያላቸውን ኃላፊነቶች በተገቢው ሁፄታ መወጣት ይችሉ ዘንድ ነው በጥቅሉ ሲታይ የዳኝነት ነጻነት የዳኝነት አካሉ ያለ አንዳች ተጽኖና አድሎአዊነት ተግባሩን እንዲያከናውን ወሳኝ ነው ከዚህ አንጻር ዳኛው ምን እንዲያደርግ ይጠበቃል። በአግባቡ ይህ በዳኝነት ነጻነት ላይ የሚደረግ ጣልቃ ገብነት መሆኑን መግለጽ ይገባዋል ከዚህ በተጨማሪም በመዝገቡ ውስጥ ስላሉ ዝርዝር ጉዳዮች ወይም በጉዳዩ ላይ ውሳኔ የሚሰጠው መቼ እንደሚሆን ሊገልጽ አይገባውም ይህንን ያደረገ ከሆነ ግን ፍርድ ቤቱ ነጻ አይደለም የሚል ምክንያታዊ ጥርጣሬ ለመፍጠር በር ይከፍታል የዳኛው የትዳር ጓደኛ ባልሚስት በፖለቲካ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ሊሆኑ ይችላሉ ዳኛው በዚህ ምክንያት የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ደጋፊ ተደርጎ ሊታይ ይችላል ይሁንና ፖለቲከኛ የሆነ የትዳር ጓደኛ ሊኖር አይገባም አይባልም ነገር ግን በምክንያታዊ ሰው አይታ የዳኛውን ነጻነት ጥርጣሬ ውስጥ ከሚያስገቡ ተግባራቶች መራቅ አለበት ከዚህ አንጻር የባንግሎር የዳኝነት ስነምግባር መርሆዎች ዳኛው የሚከተሉትን እንዲያደርግ ይመክራል የትዳር ጓደኛው በሚያደርገው ስብሰባዎች ከመገኘት አራሱን ማግለል በተቻለ መጠን በመኖሪያ ቤቱ ስብሰባ አንዳይደረግ ማድረግ በመኖሪያ ቤቱ ስብሰባ የሚደረግ ከሆነም እራሱ ከዚያ ውጭ መሆን ለአንድ የፖለቲካ ፖርቲ አጀንዳ መዋጮ ከማዋጣት መቆጠብ ወይም ከመቀስቀስ መቆጠብ ይሁንና የተወካዮች ምክር ቤት ሲከፈት በሚኖረው ስነስርአት ላይ ከትዳር ጌደኛ ጋር በስነስርአቱ ላይ መገኘትን አይከለክልም የዳኝጎት ሥራን በሚያከናውንበት ጊዜ ዳኛው ከሥራ ባልደረቦቹ ሊደርስበት ከሚችለው ተጽኖ ነጻ በመሆን የዳኝነት ውሣኔን በፍፁም ነጻነት መሰጠት ይኖርበታል የዳኝነት ተግባር ከሌሎች ተጽአኖ ነጻ መሆንና በራስ ህሊና መመራትን የሚጠይቅ እንደሆነ ይታወቃል ለዚህም ነው የዳኝነት ነጻነት የፍቤቶችን ተቋማዊ ነጻነት ብቻ ሳይሆን ዳኞችም ከባልደረቦቻቸው ሊደርስ ከሚችል ማንኛውም ተጽኖ ተጠብቀው በህጉና በህሊናቸው ብቻ በመመራት መወሰን እንደሚኖርባቸው የሚያስቀምጠው በሌላ አነጋገር የዳኝነት ነጻነት ከውጪ ሊመጣ ከሚችል ተጽኖ ፍቤትን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ከውስጥ ሊመጣ ከሚችል ማንኛውም ግፊትም ቢሆን ዳኞች ነጻ መሆን አለባቸው በተለይም ዳኞች በአንድ ችሎት ላይ ተሰይመው የሚሰሩ እንኳን ቢሆን አንዱ በሌላኛው ተጽእኖ ሥር ፈጽሞውኑ መውደቅ የለበትም አንድ ዳኛ የዳኝነት ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ ተቀጣሪ አድርጎ ራሱን በመውሰድ ከተቋሙ ኃላፊዎች ትዕዛዝ መጠበቅ የለበትም በፍቤቶች ዘንድ ያለው አደረጃጀት ተጠሪነት ላይ ያልተመሰረተና ዳኛው በያዘውና በቀረበለት ጉዳይ ላይ ራሱ የመጨረሻ ውሣኔ የመስጠት ሥልጣን ያለው መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ከዚህም የተነሳ የበላይ አካል አመራር ጠባቂነት ሊታይበት አይገባም በባንግሎር የዳኝነት ሥነምግባር ሀተታ ዘምክንያት ላይ ከዚህ በታች የሰፈረው አስተያየት ሁኔታውን በሚገባ የሚያብራራው ስለሆነ እንደሚከተለው እናስቀምጠዋለን ዚ ልበ ከ። በ ክዩ ከፅ ርሪፓርት የማቅረብ ግዴታ የለበትም ይሁን እንጂ ዳኛው ከወሰነው ውሳኔ ጋር በተያያዘ በዲሲኘሊን የሚያስጠይቅ ከሆነ በዚህን ጊዜ ዳኛው ስለሰጠው ውሳኔ ዝርዝር ፍሬ ነገር ጠቅሶ መልስ የሚሰጥበት አጋጣሚ ሊፈጠር ይችላል ነገር ግን ይህም ቢሆን ስለ ጉዳዩ ሪፖርት ማድረግ ሳይሆን ስለቀረበበት የዲሲፒሊን ክስ ወይም ምርመራ መልስ መስጠት ብቻ ነው ዳኞች የፍቤቶችን ተቋማዊ ነፃነት የሚጠብቁ አሰራሮችና ዋስትናዎች የመጠበቅና የመንከባከብ አንዲሁም የማጠናከር ግዴታ አለባቸው ተቋማ የዳኝነት ነፃነትን የሚፈታተኑ ሁኔታዎች በሚያጋጥሙበት ጊዜ እነዚህን ሁኔታዎች ለመቀነስ ወይም ለመከላከል ዳኞች ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል በርግጥ እንዲህ ሲባል የፍቤቶችን ተቋማዊ አደረጃጀትና አሰራር በመለወጥ ቀልጣፋ አንዲሆኑ ለማድረግ የሚቀርቡ የማሻሻያ ፃሳቦችን ሁልጊዜ በመቃወም የዳኝነት ነፃነትን ለትንሹም ለትልቁም ማንሳት ይገባቸዋል ማለት አይደለም ሆኖም ግን ዳኛው የፍቤትን ነፃነት ለማስከበር ሁሌም ቢሆን ራሱን ዝግጁ ማድረግ ይጠበቅበታል ህብረተሰቡ ስለ ዳኝነት ነፃነት ምንነትና ይዘት እንዲሁም አስፈላጊነት እንዲገነዘብ ማድረግ ለዳኝነት ነጻነት መከበር ወሳኝነት አለው በርግጥ የዳኝነት ነፃነት ሰፊ ዝኒ ከማሁ ገጽ ተቀባይነትና ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለው ፅንሰ ሀሳብ ቢሆንም የዳኝነት ነፃነትን እንዲሁም ይህ ነፃነት በዳኝነት ስራ ላይ የሚያስከትለውን አንድምታ ሁሉም ወገን ያውቀዋል ብሎ መደምደም ግን አይቻልም በመሆኑም ስለ ፍቤቶች ጠቅላላ አሰራርና የዳኝነት ነፃነት ህብረተሰብ እንዲገነዘብ ማድረግ የዳኝነት ተቋሙ ኃላፊነት መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል ይህ ካልሆነ ህብረተሰቡ በዳኝነት ተቋሙ ላይ አመኔታ ሊያሳድር አይችልምና ፍቤቶች ስለ ዳኝነት ነፃነት በቂ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ፈጥረው የህብረተሰቡን ግንዛቤ ካላዳበሩ በስተቀር ይህ ስራ ለሚዲያዎች ብቻ ከተተወ የዳኝነት ነፃነትን ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዳይረዳ ሊያደርጉ ይችላሉ ምክንያቱም ሚዲያዎች ብዙውን ጊዜ የሚያተኩሩት የዳኝነት ነፃነት ዳኞችን ለመከላከል የተወሰደ አቋም አድርገው ስለሚያስተጋቡ ነው ለዚህም ነው ጉዳዩ ለሚዲያዎች ብቻ ከተተወ ህብረተሰቡ ከዳኝነት ነፃነት አኳያ ሚዛናዊ መረጃና እውቀት ሊያገኝ አይችልም የሚባለው ስለዚህም ዳኞች የህዝብን ጥቅም ለማራመድ ሲባል ባገኙት መልካም አጋጣሚ ሁሉ የዳኝነት ነፃነት ምንነትንና አስፈላጊነትን ለህብረተሰቡ ለማስገንዘብ የተቻላቸውን ጥረት ሁሉ ማድረግ ይገባቸዋል ዳኞች ህብረተሰቡ በፍርድ ቤቶች ላይ ያለውን እምነት እንዲያጠናክር በማድረግ የዳኝነት አካላት ነፃነትን ለማጎልበት ከፍ ያለ ስነ ምግባር ሊኖራቸው ይገባል ህብረተሰቡ የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን የሚደግፈውና የሚቀበለው በዳኞች ስብዕናና ነፃነት በባመከ በዐ በዐዐበዐበር ላይ ሙሉ እምነት ሲኖረው ነው ዳኛው የተሟላ ስብዕና ያለውና ያለ አንዳች አይነት ተፅፅኖ የሚሰራ ነው ብሎ ህብረተሰቡ የሚያምነው ዳኛው በፍቤት መልካም ምግባር ሲያሳይ እንደሆነ አያጠያይቅም ስለዚህ ዳኛው የፍቤትን ነፃነት ለማጎልበት የመልካም ስነ ምግባር ባለቤት ለመሆን ተገቢውን ጥረት ማድረግ ይኖርበታል ዳኛው ከፍ ያለ ወይም መልካም ስነ ምግባር ሊኖረው ይገባል ሲባል ቢያንስ ፍትፃዊ ሊባል የሚችል የዳኝነት ስርዓት አካሄዶችን እብበባህጠ ባህዘበበከበ። በበ ሀ ሀከከ አፀር ከ ዐ ከ ከበርዘበ ዘባዐቭሃ ዐርህ ር ይህም በተዛቡ አመለካከቶች በመመራት ፍትፃዊ የሆነ ፍርድ ዳኞች መስጠት እንዳይችሉ የሚያደርግ የአዕምሮ ሁኔታ ማለት ነው ማለት ይቻላል አድሎአዊነት ዳኞች ኃላፊነታቸውን በትክክል አንዳይወጡ ከማድረጉም በላይ የህግ የበላይነት እንዳይሰፍን ያደርጋል ያለ አድሎ መስራት ከአንድ የዳኝነት አካል የሚጠበቅ መሰረታዊ አሴት ከመሆኑም በላይ የዳኝነት አካሉ ዋነኛ መገለጫ ባህሪይ ነው ያለ አድሎ መስራት በተጨባጭ ብቻ አይደለም መታየት የሚገባው ይልቁንም የዳኝነት ተቋሙ ያለ አድሎ እንደሚሰራ ሌሎችም መገንዘብ በሚችሉበት ሂሳብ ነው ተግባራዊ መደረግ ያለበት የዳኝነት ተቋሙ ያለ አድሎ የሚሰራ ተቋም አይደለም የሚል አመለካከት ሰዎች ዘንድ ከተስፋፋ ይህ በራሱ በፍቤቶች ላይ ቅሬታ አንዲኖር የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ፍትፃህዊነት ህብረተሰቡ እንዲጠራጠርና ብሉሎም በፍቤቶች ላይ ያለው እምነት እንዲሸረሽር ያደርጋል የዚህ አይነቱንም አመለካከትርሀከዐበ የምንለካው በምክንያታዊ ሰው አይታ መሆኑ ልብ ልንል ይገባል ማለትም አንድ ምክንያታዊ ነው ተብሎ የሚታሰብ ሰው የዳኝነት ተቋሙ ያለ አድሎ የሚሰራ አይደለም ብሉ እንዲያምን የሚያስገድዱት ሁኔታዎች ካሉ የዳኝነት ተቋሙ ያለ አድሎ ነው የሚሰራው ብሎ በአርግጠኝነት መናገር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች በጭፍን በአድሎ ተሰራ ብለው ፍርድ ቤትን ሊኮንኑ ይችላሉ ይህንን መከላከል ወይም ማቆም አይቻልም ዋናው ነገር ምክንያታዊ በሆነ ሰው አይታ ፍርድ ቤትን ያለ አድሎ አይሰራም የሚል ጥርጣሬ የሚፈጥር ሁኔታ እንዳይኖር መከላከል ነው ያለ አድሉ መስራት የራሱ የሆኑ መለያ ባህሪያት ያሉት እንደሆነ የአውሮፓ ህብረት ፍቤት ያትታል የመጀመሪያውና ዋንኛው ቁምነገርኗህቨርከሃ ባዐጸጺነ ሲሆን ይህም ማለት ችሎቱ ላይ የተሰየሙ ዳኞች በግላቸው ከተዛቡና አድሎአዊ ከሆኑ ዝኒ ከማሁ ገጽ ዝኒ ከማሁ ገጽ አመለካከቶች ነፃ መሆን ይገባቸዋል የሚለው ነው ሁለተኛው ቁምነገር ዐይርክህሃፀ ዘሞብዐልቨ ከካ ከሸከህበ ሲሆን ይህም ማለት አንድ ችሎት ለሌሎችም ሊታይና ግንዛቤ ሊወሰድበት በሚያስችል አኳቷን ከአድሎ የፀዳ ሊሆን ይገባል የሚል ነው ይህም ማለት ያለ አድሎ የሚሰራ መሆኑን ከጥርጣሬ የሚያስገቡ ሁኔታዎችን በማስወገድ እነዚህ ጥርጣሬዎች እንዳይኖሩ ዋስትና የሚሆኑ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት ይኖርበታል በሌላ አነጋገር ዳኛው በግሉ ከአድሎ የፀዳ አመለካከት ያለው መሆኑ ብቻውን በቂ አይደለም ይልቁንም ዳኛው ከአድሎ የፀዳ መሆኑን ከጥራጣሬ ላይ የሚጥሉ ኩነቶች ካሉ ችሉቱርክይርከህፀ ዘበዐጠልከ አለው ማለት አይቻልም እዚህ ላይ ሊሰመርበት የሚገባው ነጥብ የዳኝነት ተቋሙ ከአድሎ ነዛ በሆነ መልኩ መስራት መቻል ህብረተሰቡ በአንድ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ውስጥ በሚገኝ የዳኝነት አካል ላይ ፅኑ እምነት እንዲኖረው የሚያደርገው ሲሆን የዳኝነት ተቋሙ ከአድሎ ነባ ሆኖ መስራትን በሚመለከት ምክንያታዊ ጥርጣሬ ላይ ያለ እንደሆነ ግን ይህ ብቻውን በተቋሙ ላይ ህብረተሰቡ ያለውን እምነት ይሸረሽራል ዳኞች በፍቤት ውስጥም ሆነ ከፍቤት ውጪ በሚያሳዩዋቸው ባህሪያት የራሳቸውንና የፍቤቶችን ገለልተኝነትና ከአድሎአዊነት የፀዱ መሆንን በሚገባ በሚያረጋግጥ መልኩ ነው መንቀሳቀስ የሚገባቸው በተለይም የህብረተሰቡን የሌሎች ህግ ሙያተኞች እንዲሁም የተከራካሪ ወገኖችን እምነት ሊያገኙ በሚያስችላቸው መንገድ ነው የዳኝነት ተግባራቸው ማከናወን ያለባቸው ዳኞች በግላቸው የሚመርጡት የህግ አይዲዮሎጂ ወይም ፍልስፍና ሊከተሉ ይችላሉ ይህ ምርጫቸው በራሱ አድሎአዊ ናቸው አያሰኝም ዳኛው ከቀረበለት ጉዳይ ጭብጥ ጋር ተያያዥነት ባላቸው የህግና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አንዳች አይነት አቋም ወይም አመለካከት የሚያራምድ እንደሆነ ይህ ብቻውን አድሎአዊ ነው አሰኝቶት ያንን ጉዳይ እንዳያይ የሚያደርገው አይሆንም አዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ ዳኛው የአስተሳሰብ ነፃነት እስካለው ድረስ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የራሱ የሆነ አስተያየት ሊኖረው ይችላል ይህ አስተያየት ግን ከተዛባ አድሎአዊ አመለካከት የተለየ ነው ተቃራኒ ማስረጃ እስካልቀረበ ድረስ ማንኛውም ዳኛ አድሎአዊ ከሆኑ ግላዊ አመለካከቶች የፀዳ ነው ተብሎ ይገመታል ዳኞች ውሳኔ በሚሰጡበት ጊዜ የሚያቀርቧቸው ምክንያቶችና ሀተታዎች የተለየ አቋም በማንፀባረቅ የተፃፉ እንኳን ቢሆን እንደ ተዛባ አመለካከት ሊወሰዱ አይገባም አድሎአዊነት በምን ይገለፃል። አድሎአዊነት ተገቢ ያልሆነ ቃላትን በመጠቀም ሊገለጽ ይችላል ለምሳሌ አንድ ዳኛ በጾታበባህል በዘር በሃይማኖትላይ በመመስረት ተከራካሪ ወገኖች ላይ መድሎን የሚያመለክቱ ቃላት የተጠቀመ እንደሆነ ዳኛው አድሎአዊ ነው ለማለት አንችላለን ዳኞች በችሎት ላይ የሚያሳዩት ድርጊትና ባህሪይም አድሎአዊነት መኖሩን ሊያመለክት ይችላል ስለዚህም ዳኞች በተቻላቸው መጠን ሁሉ አድሎአዊ መስለው እንዲታዩ ከሚያደርጉዋቸው ባህሪያት መጠንቀቅ ይገባቸዋል የሚያሳዩት የአካል እንቅስቃሴም ሆነ ከፊታቸው ላይ የሚነበበው ስሜት አድሎ የሚያደርጉ እንዳይስመስላቸው ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይንገባል በከሳሽ ወይም በተከሳሽ ወይም ምስክር ክርክር ወይም ምስክርነት ላይ መሳቅ የመሰልቸት ምልክት ማሳየት በአንድ ወይም በሌላ መልኩ አንዱን ተከራካሪ የሚደግፍ ወይም የማይደግፍ መስሎ መታየት ተከራካሪዎች ከአድሎ የጸዳ ውሳኔ የሚያገኙ ለመሆኑ አንዲጠራጠሩ ያደርጋቸዋል ዳኛው ግልጽ ያልሆኑለትን ጥያቄዎች መጠየቅ ተገቢና ትክክልም ነው ይሁንና ዳኛው የአቃቤ ህጉን ሚና ወይም የጠበቃውን ሚና በሚጫወት በሚመስል መልኩ በክርክሩ ላይ ጥያቄ በመጠየቅ በማፋጠጥ የሚያስቸግር ከሆነና በራሱ ጥያቄ የተገኘውን ውጤት መሰረት አድርጎ የሚወስን ከሆነ ያለአድልዎ ነው የሰራው ለማለት ያስቸግራል ዳኞች የችሎትን ክብር የማስጠበቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሁሉ ችሎት ተደፍራል በሚል ሰበብ ለጥቃቅን ስህተቶች ተከራካሪዎችን ወይም ጠበቆቻቸውን መቅጣት የለባቸውም በተለይም የአስራት ቅጣትን እንደ መጨረሻ አማራጭ አድርገው ነው መጠቀም የሚገባቸው አለበለዚያ የዳኝነት አካሉ ገለልተኝነትና ያለ አድሎ መስራት ከጥርጣሬ ሊገባ ይችላል ይህንን ስልጣን ዳኞች ያለአግባብ የሚጠቀሙ እንደሆነ አድሎአዊነታቸውን ሊያረጋግጥ ይችላል ስለዚህም ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግና የህጉን መስፈርቶችና ስነስርዓቶች በመከተል ብቻ ነው ይህንን ስልጣን ዳኞች ሊጠቀሙበት የሚገባው ዳኞች የችሎት ሂደት ማስከበርና የተከራካሪዎችን የመናገር ነፃነት በማክበር የክርክራቸውን ጭብጥ በተገቢ ሁኔታ ለፍቤቱ እንዲያስረዱ በቂ እድል መስጠት ይኖርባቸዋል በተለይም ጠበቆችን ወይም ተከራካሪ ወገኖችን ያለአግባብ ከመዝለፍ ከመገሰፅ አድሎአዊነታቸውን ከሚያመለክቱ አስተያየቶች ከቁጣና ስሜታዊነት ሙሉ ለሙሉ ራሳቸውን ነፃ በማድረግ ፍፁም አድሎአዊነት እንደሌለባቸውና በገለልተኝነት የቀረበላቸውን ጉዳይ ተመልክተው በህጉ ብቻ አንደሚወሰኑ በተጨባጭ በሚያሳዩት ባህሪም ጭምር ማስመስከር ይኖርባቸዋል እንደዚሁም የግለሰቦች የግል ባህሪይ በችሎት ላይ በማንሳት ከተያዘው ጉዳይ ጭብጥ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ሳይኖረው ከተከራካሪዎች አንዳቸውን መዝለፍ ወይም መናገር በዳኛው በኩል አድሉሎአዊ አመለካከት መናሩን ያሳያል ከፍቤት ውጪም ቢሆን ዳኞች ከፍተኛ ጥንቃቄ ነው ማድረግ ያለባቸው በተለይም ያልሆኑ ቃላትን ከመጠቀም ተገቢ ያልሆኑ ባህሪያት ከማሳየት መቆጠብ ይኖርባቸዋል ከዚህም በተጨማሪ ዳኞች በግል ከተከራካሪ ወገኖች ከጠበቆቻቸው ከምስክሮቻቸው ወዘተ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ማድረግ የለባቸውም ከነዚህ ወገኖች ጋር የሚያደርጉት ግንኙነት ሁሉ በግልፅ ችሎት ተመዝግቦ የተደረገ መሆን ይገባዋል ከማንኛውም ሰው ጋር በሚያደርጉት ማህበራዊ ሆነ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት አድሎ የሚያደርጉ አስመስሉ ከሚያሳያቸው ማናቸውም አይነት እንቅስቃሴ መቆጠብ ይገባቸዋል ዳኞች ሊቀርብላቸው በሚችል ጉዳይ ላይ ቀድሞ አስተያየት በመስጠት ፍትዛዊ ዳኝነት መኖሩ ከጥርጣሬ ላይ እንዲወድቅ ከሚያደርግ ባህሪይ ራሳቸውን መጠበቅ አለባቸው የሚቀርብላቸው ጉዳይ ፍትፃዊ በሆነ መልኩ አንዳይታይ የሚያደርጉ አቋሞችን ቀድመው ማራመድ የለባቸውም አንደዚሁም አንድን ጉዳይ ወይም ግለሰብን በተመለከተ ቀድሞ አቋም በመያዝ ያ ጉዳይ ከአድሎ ነፃ በሆነ መልኩ መታየት እንዳይችል ከሚያደርጉ ምክንያቶች ራሳቸውን በሚገባ መጠበቅ ይኖርባቸዋል ይህ ማለት ክርክሩ አነርሱ ጋር ከቀረበ ጊዜ አንስቶ ውሳኔ አስኪያገኝ ድርስ ገለልተኛ ሆነው መቆየት ይኖርባቸዋል ማለት ነው ለምሳሌ አንድ በዜና ማሰራጫ ቅድሚያ ተሰጥቶት እየቀረበና ለፍርድ ሊቀርብ በሚችል ጉዳይ ላይ አንድ አቋም በመያዝ አስተያየት መስጠት ወይም አንድ ወንጀል እየተበራከተ በመምጣቱ ይህንን ችግር ለመግታት ዳኞች የዚህ ዓይነት ወንጀል ተፈፅሞ ቢገኝ ከዚህ አመት በታች ላለመቅጣት ተስማምተናል ብለው በአደባባይ ቢናገሩ ይህንን ወንጀል ፈፅመው በሚገኙ ግለሰቦች ላይ አቋም የያዙ መሆናቸውን ስለሚያመለክት አድሎአዊነታቸው ሊያሳይ ይችላል ስለዚህም ከዚህ አይነት እንቅስቃሴ ራሳቸውን መገደብ ይገባቸዋል አንድ ዳኛ በሰጣቸው ውሳኔዎች ላይ ከተከራካሪ ወገኖች አንደኛው ውሳኔውን በመተቸት ለዳኛው ተቃውሞ ቢፅፍ እንኳን ለዚህ ትችት መልስ መስጠት አይገባም የዳኞች ውሳኔ በሚዲያ በሚተችበት ጊዜም ለዚህ በጋዜጣም ሆነ በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች መልስ ለመስጠት መሞከር ተገቢ አይሆንም ይልቁኑ ዳኞች አስተያየታቸውን ሁሉ ማስፈር ያለባቸው በውሳኔዎቸቸው ውስጥ ነው በውሳኔዎቻቸው ውስጥ ፍርዱን የሰጡበት ምክንያት በግልፅ ማስፈር ስለሚችሉ ከዚህ ውጪ በመጓዝ በውሳኔዎቸቸው ላይ ለሚቀርቡ ትችቶች መልስ ለመስጠት ደፋ ቀና ማለት አይጠበቅባቸውም ሆኖም ግን የሚዲያ ሪፖርት የፍርድ ሂደቱንም ሆነ አንድን ውሳኔ ፍሬ ነገሮቹን በማዛባት የተሳሳተ ሪፖርት ያቀረበ እንደሆነ ይህንን ስህተት ለማረም ብቻ ለመገናኛ ብዙፃን ወይም ለጋዜጦች መግለጫ በሬጅስትራር በኩል ወይም እንደ ነገሩ ሁኔታ በፍቤቶች የህዝብ ግንኙነት በኩል ሊላክ ይችላል በመሆኑም ለሚዲያ መግለጫዎችን ከመስጠት ዳኞች መቆጠብ ይኖርባቸዋል በጥቅም ግጭት ምክንያት ከጉዳዩ አራስን የማግለል ሁኔታን ለመቀነስ ዳኞች ከኃላፊነታቸው ጋር የማይጣጣሙ የጥቅም ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ሾሼጠ። ፎቧከ ያዐ ርዐክበርቪ ነዛፒከ ቧርር ከ የዳኛው የቤተሰቦቹ ወይም የወዳጆቹን የግል ጥቅም ከያዘው የዳኝነት ኃላፊነት ጋር እንዳይጋጭ የጥቅም ግጭት ሊያስከትሉ የሚችሉ ምክንያቶችን ለመቀነስ ብሎም ለማጥፋት ጥረት ማሳየት ይገባል ከዚህም ባሻገር የቤተሰብ አባላቶቹ በርሱ ዳኝነት በመጠቀም ተገቢ ባልሆነ መልኩ ጥቅም አንዳያገኙ ክትትል ማድረግ ይኖርበታል በህግ በተደነገገ ጊዜ አንድ ዳኛ ስለ ራሱ ገቢዎችና የንግድ አንቅስቃሴዎች ለተገቢው አካል የማሳወቅ ግዴታ ሲኖርበት የቤተሰቦቹንም የንግድ አንቅስቃሴ በቅርበት በመከታተል የጥቅም ግጭት እንዳይፈጠር ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል ከዚሁ ጎን ለጎን ደግሞ የዳኛው ቤተሰባዊ ማህበራዊ ወይም ሌሉች ግንኙነቶች የዳኝነት ስራው ላይ ተፅዕኖ አንዳያሳርፉ መጠንቀቅ አለበት የዳኛው ቤተሰቦችየቅርብ ጓደኞችና የሙያ ባልደረቦች ከዳኛው ጋር ዘወትር የሚያደርጉት ግንኙነት በዳኛውና በነርሱ መካከል ያለውን መተማመን በመጠቀም ተገቢ ያልሆነ ተፅዕኖ በዳኛው ላይ በማድረስ የዳኛነት ስራውን ያለ አድሎ መስራት እንዳይችል ሊያደርጉት ስለሚችሉ ከዚህ አንፃር ዳኛው የዚህ አይነቱን ግንኙነት ሚዛናዊነት መጠበቅ ይኖርበታል ዳኛው ተገቢውን ጥንቃቄ ቢያደርግም የጥቅም ግጭት በሚኖርበት ጊዜ ደግሞ አንደዚህ አይነት ጉዳዮችን ከመመልከት ራሱን ማግለል አለበት ዳኛው ራሱ ተከራካሪ በሆነበት ጉዳይ ወይም ከክርክሩ ውጤት ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በሚያገኝባቸው ጉዳዮች ላይ ተሰይሞ ዳኛ መሆን አይችልም ይህም አንድ ሰው በራሱ ጉዳይ ራሱ ዳኛ መሆን አይገባውም ከሚለው መርህ የመነጨ ነው አንድ ዳኛ የቤተሰቡ አባል በህግ አማካሪነት አንድን ባለጉዳይ ወክሎ እርሱ በሚያስችልበት ፍርድ ቤት የቀረበ አንደሆነ ወይም በቤተሰቡ አባል ከቀረበው ጉዳይ ጋር አንዳች አይነት የሚያስተሳስረው የጥቅም ግንኙነት ያለው እንደሆነ ጉዳዮን ከማየት ራሱን ማግለል ይኖርበታል ምክንያቱም የዳኛው ገለልተኛው ጥርጣሬ ውስጥ ይወድቃልና ዳኛው ከጠበቃው ጋር የፍቅር ግንኙነት የመሰረተ እንደሆነ ይህ ጠበቃ የሚያቀርበው ጉዳይ ከሚመለከት ራሱን ማንሳት አለበት አንድ ዳኛና አንድ አቃቤ ህግ ወይም ጠበቃ ባለበት አካባቢ ዝኒ ከማሁ ገጽ ደግሞ ያ ጠበቃ ወይም አቃቤ ህግ የዳኛው የቅርብ ዘመድ እንደሆነ የዳኛው ገለልተኝነት አደጋ ላይ ሊወድቅ ስለሚችል እንደዚህ አይነት ጉዳዮችን ከማየት መቆጠብ ይኖርበታል ከዚሁ ጎን ለጎን ዳኛው የራሱን መኖሪያ ቤት ጠበቃ የሆነ ሰው ባለጉዳዮችን ተቀብሎ እንዲያነጋግርበት መፍቀድ የለበትም አውነተኛ የጥቅም ግጭት ሲኖር ብቻ ሳይሆን ዳኛው ያለ አድሎ መወሰን አይችልም ተብሎ ምክንያታዊ በሆነ አኳቷን በሚገመትበት ጊዜ እንዲህ አይነት ጉዳዮችን ከማየት ራሱን ማግለል አለበት ዳኛው ምንም አይነት ጥቅም ከጉዳዩ አወሳሰን የማያገኝ ከሆነና ከጉዳዮም ጋር የሚያያይዘው አንዳች ነገር ባይኖርም ዳኛው ካሳየው ድርጊት ወይም ከተናገረው ነገር ወይም ካሳየው ጠባይ በመነሳት ያንን ጉዳይ በፍፁም ገለልተኝነት ያለ አድሎ ሊያይ አይችልም ተብሎ በሚታመንበት ጊዜ ዳኛው እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ከማየት ራሱን ማግለል አለበት እንደዚህ አይነት ጥርጣሬ በዳኛው ላይ እንዲኖር ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል ለአብነት ያህል ከተከራካሪ ወገኖች መካከል አንደኛው የዳኛው የልብ ጓደኛ መሆን ወይም ለክርክር የቀረበው ጉዳይ ሳይቀርብ በፊት ዳኛው በአደባባይ አቋሙን መግለጽ ወይም ከተከራካሪ ወገኖች መካከል በአንደኛው ላይ የተዛባ አመለካከት እንዳለው በሚያሳይ መልኩ ዳኛው አስተያየት በችሎትም ሆነ ከፍቤት ዉጪ መስጠት ሊቀሱ የሚችሉ ናቸው ዳኛው ገለልተኝነቱን ከጥያቄ የሚያስገቡ ነጥቦች መኖራቸውን በተረዳ ጊዜ ተከራካሪ ወገኖች ጉዳዮን ማየት እንዲቀጥልበት ቢፈቅዱለትም እንኳ ጉዳዩን ከመመልከት ራሱን ማግለል ይገባዋል ዳኛው እንዴት መቼ ነው ራሱን በገለልተኝነት ለማየት ከማይችላቸው ጉዳዮች ራሱን የሚያገለው የሚለው ጥያቄ መልስ ማግኘት ያለበት ነው ዳኛው በገለልተኝነት አንድን ጉዳይ ማየት አልችልም ብሎ ምክንያታዊ በሆነ መልኩ የሚያሳምኑት ነጥቦች ካገኘዘቬዘበ ዐ በ ሀፀከፀበበ ራሱን ማግለል ይኖርበታል በርግጥም አንድ ዳኛ በተጨባጭ አድሎአዊነት ይታይበታል ብሎ የርሱን ርከል ማሳየት ይከብዳል ለዚህም ነው ህጉ አንድ ምራቁን የዋጠ ምክንያታዊ ሰው ዳኛው በገለልተኝነት አንድን ጉዳይ ማየት እንደሚሳነው የሚገምት ከሆነ ዳኛው ራሱን ማግለል ይገባዋል ፍትህ ያለ አድሎ በተጨባጭ መስጠት መቻል ብቻ አይደለም ቁምነገሩ ይልቁንም ፍትህ ያለ አድሎ ይደረጋል ተብሎ መታመንም አለበት ይህ ካልሆነ ግን የፍትህ አስተዳደሩ ሀቀኝነትና ገለልተኝነት ላይ ዜጎች አምነት መጣል አይችሉም ለህግ ልዕልናም ያላቸው ከበሬታ ይቀንሳል መወያያ ጥያቄዎች ዳኞች እንደማንኛውም ሰው ሰብአዊ መብት አላቸው የራሳቸውን እምነት የመከተል የራሳቸውን ሀሳብ የመግለጽ መብት አላቸው አንድ ዳኛ ሴቶች ከወንዶች እኩል አይደሉም ሴቶች ከወንዶች አኩል ማሰብ አይችሉም ሴቶች አይታመኑም የሚል አመለካከት ሊኖረው ይችላል ይህ የኔ አመለካከት ነው አመለካከቴን የመግለጽ ህገመንግስታዊ መብቴ ነው በማለት ሀሳቡን ከጓደኞቹ ጋር ሲገናኝም በመኖሪያ ቤቱ ውስጥም ይገልጻል ዳኛው ይህ መብቱ ነው ወይ። የሚለውንም አንስታችሁ ተወያዩበት ቅንነት ወፒነ ዳኞች የዳኝነት ስራን በሚያከናውኑበት ጊዜ ለገቡት ቃል ታማኝ በመሆን በፍፁም ቅንነት ማገልግል ይጠበቅባቸዋል ከዚህ አንፃር በዋነኛነት ዳኞች ቅንነታቸውን ከጥርጣሬ ከሚጥሉ ተገቢነት የሌላቸው ድርጊቶች መቆጠብ ይኖርባቸዋል የቅነነት መለኪያም አንድ ምክንያታዊ ሰው የዳኛውን ባህሪይ በማጤን ዳኛው ኃላፊነቱን በነፃነት በትጋት ያለ አድሎና በፍፁም ሀቀኝነት ሊያከናውን ይችላል ወይም አይችልም ብሎ በሚያስቀምጠው አስተያየት ነው ለምሳሌ ያህል አንድ ዳኛ ከባለጉዳዮች መካከል አንድን ባለስልጣን በተለየ ሁኔታ ያስተናገደ እንደሆነ ቅንነት የጎደለው ባህሪይ አሳይቷል ማለት ነው ከዚህ አንጻር የሚከተሉት ነጥቦች አንደመለኪያ ሊታዩ ይችላሉ ዳኞች ስራቸውን በሚያከናውኑበት በማህበረሰቡ ውስጥ በሚኖሩበት ጊዜ በኃላፊነታቸው ምክንያት የሚጣልባቸውን የስነ ምግባር ግዴታዎች በሙሉ ፈቃደኝነት በመቀበል ሊያጎለብቷቸውና ተግባራዊ ሊያደርጓቸው ይገባል እነዚህ ገደቦች ከከፍተኛ ኃላፊነታቸው የመነጨ መሆኑንም መገንዘብ ይኖርባቸዋል ዳኞች የህብረተሰቡ ዋልታዎች ተደርገው የሚቆጠሩ በመሆናቸው ከፍተኛ ስነ ምግባር የማሳየትና ባጠቃላይ ለህብረተሰቡ በመልካም ምግባራቸው ምሳሌዎች መሆን ይኖርባቸዋል በዚህ ረገድ የዳኝነት ክብርን ዝቅ ከሚያደርጉ ስፍራዎችና ድርጊቶች መቆጠብ አለባቸው በተለይም አዘወትረው በመጠጥ ቤቶች የቁማር ስፍራ መገኘትን በሚገባ ማጤንና ማስወገድ ያስፈልጋል ዳኛው በሚያስችልበት ፍቤት አዘውትረው የሚቀርቡና ጉዳይ ካላቸው ጠበቆች ወይም የህግ ባለሙያዎች ጋር ዳኛው ተገቢ ያልሆነና ለአድሉሎአዊነት በር የሚከፍት ግንኙነት ከማድረግ መቆጠብ ይናኖርበታል ይህ ማለት ዳኞች ባጠቃላይ ከሌሎች የህግ ሙያተኞች ጋር ግንኙነት እንዳያደርጉ የሚከለክል ሳይሆን ግንኙነቱ በጥንቃቄ አእየተፈሸ የዳኞችን ገለልተኝነት ከጥራጣሬ በማይከት መልኩ ሊሆን ይገባል ለማለት ተፈልጎ ነው ለምሳሌ ያህል አንድ ዝኒ ከማሁ ገጽ ዝኒ ከማሁ ገጽ ዳኛ በጠበቆች ወይም በህግ ሙያተኞች በተዘጋጀ የግብዣ ኘሮግራም ላይ ሊሳተፍ ይችላል ነገር ግን በያዘው ጉዳይ ላይ ውይይት እንዳይካሄድ ተገቢውን ጥንቃቄ ዳኛው ሊወስድ ይገባል ከዚህም በተጨማሪ ዳኛው እርሱ ዘንድ ጉዳይ ይዘው ከሚቀርቡ ጠበቆች ላይ ምንም አይነት ስጦታ መቀበል የለበትም ከዚሁ ጎን ለጎን አዘወትረው ከሚቀርቡ ተከራካሪዎች ጋርም ከልክ ያለፈ ማህበራዊ ግንኙነት መመስረት አይኖርበትም በአጠቃላይ አነጋገር ዳኞች ከባለጉዳዮች ከጠበቆችና ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በሚፈጥሩት ግንኙነት የዳኝነት ኃላፊነታቸውን በገለልተኝነት በሀቀኝነት ከማከናወን እንዳያደናቅፋቸው ከፍ ያለ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ዳኞች በተቻላቸው መጠን ሁሉ ተገቢ ያልሆኑ ግንኙነቶች ከሌሎች ጋር ከማድረግ መቆጠብ ይገባቸዋል ምክንያቱም ከሌሎች ጋር ከመጠን ያለፈ ግንኙነት በማድረግ ለአላስፈላጊ ተፅዕኖ ሊጋለጡ ይችላሉና ለምሳሌ አንድ ዳኛ አዘወትሮ በጠበቆች የግል መኪና የሚጠቀም ወይም ከፖሊሶች ጋር ግንኙነት የሚያዘወትር ከሆነ ወይም ከባለጉዳዮች ጋር በነርሱ መኪና በተደጋጋሚ ሁኔታ የሚጓጓዝ አእንደሆነ እነዚህ ድርጊቶች ተገቢ ያልሆኑና የዳኛውን ገለልተኝነት የሚፈታተኑ ናቸው ስለዚህ ዳኞች በስነምግባራቸው ከፍ ያለ ጠባይን በማሳየት በቅንነት በመስራት ለህብረተሰቡ አርአያ መሆን ይጠበቅባቸዋል ዳኞች እንደ ሌሎች ዜጎች ሁሉ ዛሳብን በነባነት የመግለፅየመደራጀትና የመሰብሰብ መሰረታዊ መብቶች አሏቸው ይሁን እንጂ እነዚህን መብቶች በሚጠቀሙበት ጊዜ የዳኝነት ስራቸው ዝቅ እንዳያረግ ገለልተኝነታቸውንና ነፃነታቸውን እንዳያደናቅፍ ከፍ ያለ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ዳኞች በህዝባዊ» ውይይቶች በሚሳተፉበት ወቅት አንደኛ ተሳትፏቸው በገለልታኝነታቸው ላይ አሉታዊ ገፅታ እንዳይፈጥር በሌላ በኩል ደግሞ የዳኛውን ፖለቲካዊ ወገንተኝነት እንዳያመለክት ተገቢው ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ከዚህ ባሻገር ዳኞች በህዝባዊ መድረኮች አከራካሪ በሆነ ጉዳዮች ላይ መከራከርም ሆነ አስተያየታቸውን መስጠት አይገባቸውም በዚህ ረገድ ዳኞች ቁጥብነትን ማሳየት የሚገባቸው ሲሆን ህግን ለማሻሻል ወይም የፍትህ አስተዳደርን በተመለከተ በሚጠሩ ህዝባዊ ውይይቶች ላይ መሳተፍ ይችላሉ ዳኞች የዳኝነት ስልጣናቸውን በተገቢ መልኩ ለህዝብ ጥቅም ብቻ ነው ሊገለገሉበት የሚገባው የዳኝነት ስልጣናቸውን የግል ጥቅሞቻቸውን ለማራመድ ወይም ሌሎችን ለመጉዳት ሊጠቀሙበት አይገባም ምንም ጊዜ ቢሆን ዳኞች ስልጣናቸውን በዘፈቀደ የግለ ጥቅሞቻቸውን ለማራመድ ወይም በአድሎአዊነት ነው የሚጠቀሙበት ተብሉ እንዳይወሰድ ጥርጣሬ የሚፈጥሩ ነገሮችን ሁሉ ለማስወገድ ብርቱ ጥረት ማሳየት አለባቸው ዳኞች ስልጣናቸውን ያለ አግባብ ይጠቀሙበታል የሚል አመለካከት በህብረተሰቡ ዘንድ ከተንሰራፋ የፍቤቶች ተዓማኒነት አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም አንድ ዳኛ የራሱን የግል ጥቅም ወይም የቤተሰቦቹን ጥቅም ለማስጠበቅ የዳኝነት ስልጣኑንና ክብሩን ያለአግባብ ሊጠቀምበት አይችልም ከዚህም ጎን ለጎን የዳኛውን ስልጣን መከታ በማድረግ ጥቅም ማግኘት የሚፈልጉ የቤተሰቦቹን አባላት በሚገባ በመከታተልና መከላከል ይኖርበታል ማንም ሰው ከዳኛው ጋር ባለው ቅርበት ምክንያት ዳኛው ላይ ተገቢ ያልሆነ ተፅእኖ መፍጠር እንደሚችል አድርጎ ሌሎችን አንዳይቀርብና እንዳይሳሳት ዳኛው ሁሌም ቢሆን ነቅቶ መጠበቅ አለበት የዳኝነት ስልጣኑን ተገቢ ያልሆነ የግል ጥቅሙን ለማራመድ መጠቀም የለበትም ሲባል ምን ማለት እንደሆነ ምሳሌ ወስደን አንመልከት ለምሳሌ ዳኛው የግል ቢዝነሱን በሚያካፄድበት ወቅት የዳኝነት መንበሩን በመጠቀም በፍርድ ቤቱ ደብዳቤ በመጠቀም መልዕክቶችን መለዋወጥ የለበትም አገልግሎት ፍለጋ የሆነ ቦታ ፄዶ ከቢሮክራሲያዊ አሰራሮች በማምለጥ በፍጥነት ለመስተናገድ ሲል ዳኛ መሆኑን በመግለፅ በተለየ ሁኔታ እንዲስተናገድ መጠየቅ የለበትም በርግጥ ዳኛው ዳኝነቱን ይደብቅ ለማለት ተፈልጎ ሳይሆን የዳኝነት መንበሩን ያለአግባብ የግል ጥቅሙን ለማስጠበቅ መጠቀም የለበትም ነው ለምሳሌ የዳኛውልጁ ወይም ባለቤቱ ወይም የቅርብ ዘመዱ ቢታሰር ዳኝነቱን በመጠቀም እነዚህ ሰዎች ከሌላው የተለየ መስተንግዶ ተደርጎላቸው እንዲፈቱ ወይም ጉዳያቸው በትኩረት እንዲታይ ግፊት መፍጠር የለበትም አንድ ዳኛ ለሌሎች ሰዎች የድጋፍ ደብዳቤ ሊፅፍላቸው ይችላል ሆኖም ግን በዚህ ረገድ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው ምክንያቱም የዳኝነት ኃላፊነቱ የተጎናፀፈውን ክብር በመጠቀም ሌሎች ሰዎች በርሱ የድጋፍ ደብዳቤ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም እንዳያገኙ ነው ። ዳኞች በወንጀል ጥፋተኛ ሆነው የተገኙ ሰዎችን በሚቀጡበት ጊዜ አንኳን ለተከሳሹ ተገቢውን ክብር መስጠታቸውን በሚያሳይ መልኩ አንጂ ተከሳሹን በሚያወግዝና በሚያወርድ አገላለፅ መጠቀም አይኖርባቸውም በርግጥ ተከሳሹ ወንጀል በመፈፀሙ ምክንያት ላደረሰው በደል የሕብረተሰቡን ቁጣ በሚያሳይ መጠን ብቻ መጠነኛ ተግሳፅ ማድረግ የዳኛው ኃላፊነት ቢሆንም ከመጠን ያለፈና አዋራጅ የሆነ የስድብ ቃላትን መጠቀም ተገቢነት የለውም ከዚህ በተጨማሪ ዳኞች ለእያንዳንዱ ሰው ማለትም ለሁሉም ተከራካሪዎችምስክሮችና የሕግ አማካሪዎቻቸው ተገቢውን ክብርና እኩል አንክብካቤ ማድረግ ይኖርባቸዋል በተለይም የፍርድ ሂደቱ ፍፁም ፍትፃሣዊና ሁሉንም ወገኖች በእኩልነት አይቶ የሚዳኝ መሆኑን በሚያሳይ መልኩ ነው ዳኞች መስራት የሚጠበቅባቸው በተከራካሪ ወገኖች መካከል ልዩነት የሚያደርጉ መስለው መታየትም የለባቸውም ለምሣሌ በችሎት ላይ ለአንደኛው ተከራካሪ ወገን ፃዘሌኔታን በገጽታም ሆነ በቃላት ማሳየት ለአንደኛው ወገን ረዘም ያለ የመናገር እድል መስጠትና ሌላውን መንፈግ ለአንደኛው ወገን ንግግር ወይም ዛሳብ ብቻ ትኩረት መደረጉን የሚያሳይ ገጽታ ወይም ድርጊት ማሳየት ወዘተ የዳኛውን አድሎአዊነት ሊያንፀባርቅ ስለሚችል በተቻለ መጠን መወገድ ያለበት ባህርይ ነው ከዚሁ ጋር በተያያዘ መልኩ የሁሉንም ተከራካሪ ወገኖች አስተያየትና ክርክር በጥሞና ማድመጥና በትኩረት መከታተል የሚያስፈልግ ሲሆን ለሁሉም ወገኖች አኩል ክብር መስጠትም በጣም አስፈላጊ ነው ዳኞች መድልዎን ከሚያራምዱ ድርጅቶች አባልነት መራቅ አለባቸው ዳኞች በተለያዩ የግብረ ሰናይ ስራዎች ሊሳተፉ ይችላሉ ይሁንና ገለልተኛ መሆናቸውን ጥያቀ ውስጥ ሊያስገባ በሚችል መልኩ ወይም ከዳኝነት ስራቸው ጋር በሚጋጭ መልኩ መሳተፍ የለባቸውም ለእንደዚህ አይነት ድርጅቶች ገንዘብ ለማሰባሰብ ከሚደረግ እንቅስቃሴ አራሳቸውን መቆጠብ ይኖርባቸዋል በፍርድቤት ክስ ሊኖረው ይችላል ብለው በሚገምቱት ድርጅት ተሳታፊ ከመሆን መታቀብ ይኖርባቸዋል መወያያ ጥያቄዎች ከእኩልነት መርህ ጋር የሚቃረን ዳኛው ከማድረግ ሊቆጠብባቸው የሚገቡ ባህርያትን አንስታችሁ ተወያዩበት ዳኛው በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች አርዳታ ለማሰባሰብ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራች ብቻ ሳይሆን እርዳታ ለማሰባሰብ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ላይ ንቁ ተሳታፊ መሆን ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር እንዴት ይታያል በዳኝነት ስራ ትጋትና ጥረት ማሳየት ፀህፀ በዩቨከርፀ ዳኛው በዳኝነት ስራው ላይ ተገቢውን ትጋትና ጥረት ማሳየት እንዲሁም ስለህግ ያለውን ዕውቀት ለማዳበር ዘወትር ጥረት ማድረግ አለበትኞ ዳኛው ማሳየት የሚገባው ጥረትና ትጋት በዕውቀት ክህሎት ጥልቀት ባለው አስተሳሰብና በቂ ዝግጅት የተደገፈ መሆን ይኖርበታል የዳኝነት ስራውን በሚያከናውንበት ጊዜ ዳኛው በበቂ የህግ ዕውቀት ላይ ተመስርቶ መሆን አለበት ዳኛው ለአልኮልና ለተለያዩ ሱሶች የተጋለጠ እንደሆነ የዳኝነት ስራ የሚጠይቀውን ትጋትና ጥረት ማሳየት ሊሳነው ይችላል በተጨማሪም ዳኛው የግል ባህሪይ የተረጋጋ ካልሆነና በቂ ልምድ የሚያንሰው ከሆነ የዳኝነት ስራ የሚጠይቀውን ብቃትና ችሉታ ሊጎድለው ይችላል ዳኛ የቀረበለት ጉዳይ በፍፁም ጥንቃቄ ማየትመመርመርና ያለ አድሎ መወሰን ሲኖርበት ይህም የዳኝነት ብቃት መገለጫ ነው እንዲሁም ዳኛው ህጎች በትክክል ተግባራዊ ማድረግ ያለበት ሲሆን በፍርድ ሂደትም ቢሆን የተከራካሪ ወገኖች መብት ሙሉ በሙሉ እንዲከበር የማድረግ ኃላፊነት አለበት ዝኒ ከማሁ ገጽ በተለይም የፍርድ ሂደቱ ፍትፃዊና ግልፅ አንዲሁም አግባብነት ያለው መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው በርግጥ የዳኛው ጥረትና ትጋት በተለያዩ ነገሮች ሊወሰን ይችላል ለምሳሌ ዳኛው ከፍተኛ የስራ ጫና ያለበት እንደሆነና ብቃት ባላቸው የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የማይደግፍ እንደሆነ እንዲሁም የዳኝነት ስራውን በተገቢ ሁኔታ ለመምራትና ለማሻሻል በቂ ሀብት ያልተመደበለት እንደሆነ ዞሮ ዞሮ የዳኝነት ስራውን በብቃትና በትጋት ለማከናወን የሚቸገር መሆኑ የሚያጠራጥር ነገር አይደለም ዳኞች ሁልጊዜም ቢሆን የስራ ሰአትን አክብረው በመገኘት አርአያነት ማሳየት ይገባቸዋል ዳኞች ስራቸውን በትጋት ማከናወን ይችሉ ዘንድ በቂ ዕረፍት ማግኘት ይገባቸዋል የዳኛው ማህበራዊ ህይወትና የቤተሰብ ኃላፊነት ከግምት ገብቶ በአመት ውስጥ በቂ ጊዜ በአረፍት ላይ መቆየት አለበት ይህ ዕረፍት ዳኛው በተሻለ ሁኔታ ጤንነቱ እንዲጠበቅና የአዕምሮ ዕረፍት እንዲያገኝ ነው ከዚህ ባሻገር ዳኛው የራሱን ክህሎትና ዕውቀት የሚያሻሻልበት ጊዜም ያስፈልገዋል የዳኝነት ስራ ከፍተኛ ጫናን የሚፈጥር በመሆኑ በዳኞች ላይ ጭንቀት ሊፈጥር እንደሚችል በሌሎች ሀገሮች የተደረጉ ምርምሮች ያሳያሉ ስለዚህም ዳኞች የምክር አገልግሎት ሊያስፈልጋቸው ይችላል የዳኞች ቀዳሚ ስራ የዳኝነት አገልግሎት በመሆኑ ዳኞች ከየትኛውም ተግባር የዳኝነት ስራቸውን በማስቀደም በከፍተኛ ትጋትና ጥረት ማከናወን ይጠበቅባቸዋል በተለይም የሚቀርቡላቸው ክርክሮች በአግባቡ ማስተናገድና ተገቢውን ፍርድ መስጠት የዳኞች ኃላፊነት ነው ከዚህም የተነሳ አንድ ዳኛ ሌሎች ኃላፊነቶች በመንግስት ተሰጥቶት ሌላ ስራ እንዲያከናውን ቢመድብም እንኳን በቅድሚያ ከፍቤቱ ኃላፊዎች ጋርና አብሯቸው ከሚሰራቸው ዳኞች ጋር በመመካከር የዳኝነት ስራው ወይም ተግባሩ እንዳይስተጓጎል ማድረግ ይኖርበታል ነገር ግን ኃላፊነት በመውሰዱ ምክንያት የዳኝነት ስራው የሚስተጓጉል እንደሆነ ዳኛው ሌላ ስራ ከመስራት መቆጠብ አለበት ዳኞች በትርፍ ጊዜያቸው ሌሎች ስራዎችን በማከናወን ገቢ የሚያገኙ እንደሆነ ይህ ሁፄታ ተፈታትኗቸው ለመደበኛ ስራቸው ትኩረት እንዲነፍጉ ሊያደርግ ዝኒ ከማሁ ይችላል ከዚህም አልፎ ዳኞች የያዙትን ከፍተኛ ኃላፊነት የህዝብ አገልጋይነት ወደ ጎን ትተው ገቢያቸውን ማዳበር ላይ ትኩረት ሊያደርጉ ይችላሉ የዳኝነት ስራ የህዝብ አገልጋይነትርዐጠዘህበቪሃ ከርፀ መሆኑን በመገንዘብ ዳኞች በመደበኛ ስራቸው ላይ ተገቢ ያልሆነ ጫናዎችን ከሚፈጥሩባቸው ሌሎች ስራዎች ራሳቸውን ማግለል ወይም መቆጠብ ይጠበቅባቸዋል አንድ ዳኛ ሙያዊ ዕውቀቱን ክህሎቱን ከዳኝነት ስራ በተለይም ውሳኔዎችን ከመስጠት ባሻገር የፍቤቱን የስራ አፈፃፀም ለማሻሻል የሚበጁ ሌሎች ተግባራት ላይም ማዋል ይጠበቅበታል ይህ ማለት ዳኞች ውሳኔ የመስጠት ወይም የፍርድ ስራን በአግባቡ የማከናወን ክህሎትና ችሎታ ብቻ አይደለም የሚያስፈልጋቸው ። በቦበክበ በመጨረሻም ዳኞች የዳኝነት ሥራን በትጋትና ጥረት እንዳያከናውኑ ከሚያደርጋቸውና አግባብነት ከጐደላቸው ድርጊቶች ሊታቀቡ ይገባል በተለይም መዝገቦችን ለዳኞች የማከፋፈል ኃላፊነት ያለበት ዳኛ የባለጉዳዮችን ወይም የጠበቆችን ወይም የሥራ አስፈጻሚውን የመንግሥት አካል ፍላጐት ብቻ ከግምት በማስገባት መዝገቦችን ለአንድ ችሎት ወይም ለሌላ ችሎት ማከፋፍል እያለበት አንድ ጠበቃ ወይም ባለጉዳይ ጉዳያቸውን እንዲያይ ለሚፈልጉት ዳኛ እንዲሰጥ ማድረግ ተገቢነት የለውም ምክንያቱም ጉዳዮች በተወሰኑ ዳኞች ወይም ችሎቶች አጅ ተከማችተው በፍጥነት እልባት እንዲያገኙና እንዳይቋጩ ሊያደርግ ከመቻሉም በላይ በጥቂት ዳኞች ላይ ተገቢ ያልሆነ የሥራ ጫና ሊፈጥር ይችላልና ስለዚህም የመዝገብ ክፍፍል በሚደረግበት ወቅት ከሁሉም ዳኞች ጋር ውይይት በማካፄድ ፍትፃዊ ፆ ዝኒ ከማሁ ገጽ እንዲሆን መጣር የሚያስፈልግ ሲሆን ክፍፍሉ በቁጥርም ሆነ በጉዳዩ ውስብስብነት ለሁሉም ዳኞች እኩል መከፋፈል ይኖርበታል አንድ ጉዳይ ለአንድ ዳኛ ከተሰጠ በኋላ በምንም ዓይነት ዳኛው በሕመም ምክንያት ወይም ከጥቅም ግጭት የተነሳ ጉዳዩን ለማየት የማይችል ካልሆነ በቀር ጉዳዩን አንዳያይ ለማድረግ መዝገቡ ከርሱ ሊወሰድ ወይም ሊነጠቅ አይገባም አንድን ጉዳይ አንዳይመለከት መደረግ የሚችለው አግባብ ያለውን የሕግ ሥነሥርዓት ተከትሎ ዳኛው ጉዳዩን ከማየት ራሱን ማንሳት ወይም ማግለል ካለበት ብቻ ነው የዚህ ዓይነቱም ውሣኔ ቢሆን በሌሎች የመንግሥት አካላት ጣልቃ ገብነት ወይም ተጽኖ ሊወሰን አይገባም ይልቁንም አግባብነት ያላቸውን ህጎችና ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ ተከትሎ ሊሆን ይገባል ከዚህ በተጨማሪ ዳኞች የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ያለአግባብ ከመደበኛው ሥራ ጋር ግንኙነት በሌላቸው ሁኔታዎች የተለያዩ ተግባራትን እንዲያከናውኑ ማስገደድና የሥራ ጫና እንዲበዛባቸው ማድረግ አይገባቸውም በተለይም የራሳቸውን የግል ሥራ አንዲሰሩ አላስፈላጊ ጫና እና ግፊት ማሳደር ተገቢነት የለውም መወያያ ጥያቄዎች በአንድ ችሎት በተያዘ ጉዳይ ዳኛው ውሳኔ ሲጽፍ ተከሳሽ ያቀረባቸውን የህግ ክርክሮች ለጉዳዩ አግባብነት የላቸውም ብሉ ስላመነ በቀረቡት የህግ ክርክሮች ላይ ሳይተችበት በተከሳሽ ላይ ውሳኔ ሰጠ ዳኛው ይህንን ማድረጉ ለከሳሽ ያደላ መሆኑን ያመለክታል በሚል በዳኛው ላይ ክስ ቀረበበት በአርግጥ ዳኛው አድልዎ ፈጽሟል ሊባል ይችላል። ፀሃበር ሀ ሀፀዉበክ ማድረግ ይኖርባቸዋል ምክንያቱም ዐቃብያነ ሕግ ለፍትህና አውነት ነው መቆም ያለባቸው እንጂ ተከሳሹን መርታትን እንደ ሙያቸው ግብ አድርገው መመልከት አይኖርባቸውምና በሌላ በኩል ዐቃብያነ ሕግ ሁልጊዜም ቢሆን የሕዝቡን ጥቅም ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ሊያደርጉ ይገባል ክስ ለመመስረትም ሆነ ላለመመስረትም ወይም ለፍርድ ቤት የቀረቡ ክሶችን ለማንሳት በሚወሰኑበት ጊዜ የሕብረተሰቡን ጥቅም ከግምት ማስገባት ይኖርባቸዋል ከዚህ በተጨማሪ ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩና አንዲጠበቁ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ያለባቸው ሲሆን የሙያ ግዴታቸውን በሚወጡበት ጊዜ የሰዎች ስብዕናክብርና መሰረታዊ ነፃነቶች እንዲጐለብቱ ብርቱ ጥረት ማድረግ አለባቸው ደሙዖ ዳታ ዐቃብያነ ሕግ ውጤታማና ፍትዛዊ በሆነ መንገድ እንዲሁም ያለ አንዳች አድሎ ገለልተኛ ሆነው ሥራቸውን ማከናወን የሚችሉት ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሊመጡ ከሚችሉ ተጽኖዎች ነፃ ሲሆኑ ብቻ ነው በዚህ ረገድ የዐቃብያነ ሕግን ሚና ለመወሰን በተባበሩት መንግሥታት የወጣው መመሪያና በዐቃብያነ ሕግ ዓለምአቀፍ ማህበር የወጣው የተግባር መመሪያ ሁሉም ሀገራት የዐቃብያነ ሕግን ሙያዊ ነፃነት ለማስጠበቅ ግዴታ እንዳለባቸውና ተጨባጭ ርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባቸው ነው መንግሥታት ዐቃብያነ ሕግ ሙያዊ ግዴታቸውን ያለ ማስፈራራት እክል ትንኮሳ አግባብ ያልሆነ ጣልቃ ገብነት ወይም ለምክንያት አልባ የፍትፃብሄር ዝኒ ከማሁ ለክዘ አዐድዞኮፎአዐፎክአርፎ ዐዞ ዞክዐፎርህፐርዌ ኮልሀህ እበ ዘእበከፀቦገ ዘበ ከ አሃ ርቪሸ ገጽ ይመልከቱ የወንጀል ወይም ሌላ ሃላፊነት ሳይጋለጡ መወጣት መቻላቸውን ማረጋገጥ አለባቸው የዐቃብያነ ሕግ የአገልግሎት ሁኔታዎች ደመወዝና የአገልግሎት ዘመን ገለልተኝነታቸውንና ነፃነታቸውን በሚያረጋግጥ መልኩ ነው መደራጀት የሚገባው ተገቢነት ያላቸው የዐቃብያነ ሕግ የአገልግሎት ሁኔታዎች በቂ ደመወዝ እንዲሁም አግባብነት ባለው ጊዜ የአገልግሎት ዘመን ጡረታና የጡረታ አድሜ በሕግ ሊደነገጉ ወይም በታተሙ ሕጐች ወይም ደንቦች ሊወጡ ይገባል ከዚህ በተጨማሪም ስርዓቱ በሚፈቅድበት ሁሉ የዐቃቤ ሕግ የሥራ ዕድገት በተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ በተመሰረተ ህግ በተለይም ሙያዊ ብቃትን ችሎታን ጠንካራ ስብዕናን አና ልምድን መሰረት ያደረገ ፍትሃዊና ገለልተኛ የሆነ ስነ ስርዓት ተከትሎ የሚወሰን መሆን አለበት ከዚሁ ጋር ተያይዞ ዐቃብያነ ህግ የመክሰስ ውሳኔን ለመስጠት ወይም ክስን ላለመመስረት ለመወሰን ዲስክሬሽን ባላቸው ጊዜ ውሳኔያቸውን በህግና በቀረቡላቸው ፍሬ ነገሮች ላይ በመመስረት አንጂ ከየትኛውም አቅጣጫ በሚመጣ ተዕኖ ወይም ግፊት መወሰን የለባቸውም በተለይም ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ዐቃብያነ ህግ ነፃ መሆን እንደሚገባቸው የአለም አቀፍ ዐቃብያነ ህግ ማህበር የተግባር መመሪያ አንቀፅ ያትታል ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ለዐቃብያነ ህግ ክስ እንዲመሰርቱ ወይም አንዳይመሰርቱ ትዕዛዝ ለመስጠት በህግ ስልጣን ያላቸው እንደሆነ እነዚህ የመንግስት አካላት ወይም ባለስልጣናት ይህንን ስልጣን ላይ ማዋል የሚገባቸው በግልፅነት ህጋዊ የስልጣን ገደባቸውን ሳይተላለፉና የዐቃብያነ ህግን የመወሰን ሙያዊ ነፃነት ሳይገፉ መሆን ይገባዋል የዐቃቤ ህግነት ስራን ያለ አድሎአዊነት ማከናወን ዐቃብያነ ህግ ስራቸውን ያለ አድሎ ፍትዛዊ ግልፅ በሆነ መንገድ እንዲያከናውኑ የዐቃቢያነ ህግን ሚና ለመወሰን በተባበሩት መንግስታት የወጣ መመሪያና የአለም አቀፍ የዐቃቢያነ ህግ ማህበር የተግባር መመሪያ ያስገነዝባሉ የተባበሩት መንግስታት የዐቃቢያነ ህግን ሚና ለመወሰን የወጣው መመሪያ ዐቃቢያነ ህግ በወንጀል ፍርድ ሂደት ፆ በዐቃብያነ ህግ ሚና ላይ የተባበሩት መንግሥታት መመሪያዎች አንቀፅ ን ይመልከቱ ዝኒ ካማሁ አንቀጽ ን ይመልከቱ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ልበ ዐ ፀበ የፀዐበቨቪነ ልበ ጠበ። አንቀፅ እና ይመልከቱ ውስጥ ስራቸውን ፍትዛሃዊ ወጥና ቀልጣፋ በሆነ መልኩ እአንዲወጡ ለሰብአዊ መብቶች መከበር እንዲቆሙና ስራቸውን በገለልተኝነት ያለ አንዳች አድሎ አእንዲያከናውኑ እንዲሁም በፖለቲካ በማህበራዊ አቋም በዛሃይማኖትበዘርበባህል ወይም በሌሎች ምክንያቶች አድሉአዊ ልዩነት ማድረግ አይገባቸውም ዐቃብያነ ህግ በሕጉ መሰረት ግዴታቸውን ፍትፃዊ በሆነ በአንድ ወጥና በቀልጣፋ ሁፄታ መወጣት አለባቸው እንዲሁም ሰብአዊ ክብርን መጠበቅ ሰብአዊ መብቶችን ማክበር በዚህም አግባብ ያለው የህግ አካፄድ አና እንከን የሌለው የወንጀል ፍትህ ስርዓት አሰራር አንዲኖር ለማስቻል የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ አለባቸው ከዚህም ባሻገር ስራቸውን ገለልተኛ በሆነ መልኩ ማከናወን አና ከማናቸውም የፖለቲካ ማህበራዊዛይማኖታዊየዘርባህላዊ የጾታ ወይም ሌላ ማናቸውም አይነት አድሎ ነፃ መሆን ይጠበቅባቸዋል የህዝብን ጥቅም መጠበቅበተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ መመስረት የተጠርጣሪውንና የተጠቂውን ሁኔታ በአግባቡ ከግምት ማስገባት ለተጠርጣሪው ጠቀሙም አልጠቀሙም ማናቸውንም አግባብ ያላቸውን ሁኔታዎች ማስተዋል አስፈላጊ ነው ገለልተኛ የሆነ ምርመራ ክሱ መሰረተ ቢስ መሆኑን ሲያሳይ ዐቃብያነ ህግ ክስ አይጀምሩም አይቀጥሉም ወይም ሄደቱ እንዲቆም የተቻላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ ዐቃብያነ ህግ ክስ የሚመሰርቱት የቀረበላቸው ማስረጃ አጥጋቢና አሳማኝ እንዲሁም ተዓማኒነት ያለው እንደሆነ ብቻ ነው ከዚሁ ጋር ተያያዞ የክሱ ማስረጃ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ የተሰበሰበ እንደሆነ ወይም የተከሳሹን መሰረታዊ መብቶች በመጣስ የተሰበሰበ ማስረጃ አንደሆነ የዚህ አይነቱ ማስረጃ ለሚቀርበው ክስ በማስረጃነት እንዲያገለግል ማድረግ የማይገባ ሲሆን የተከሳሹን መብቶች በመጣስ ማስረጃውን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ አንዲሰበስብ ባደረጉ አካላት ላይ ተገቢውን ማጣራት ተካሂዶ ለህግ እንዲቀርቡ ማድረግ የዐቃብያነ ህግ ግዴታ ነው ይህም ማለት ዐቃቢያነ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ የተጠርጣሪውን መብቶች በብርቱ በሚጥስ በተለይም ማሰቃየትጭካኔ የተሞላበት ኢሰብአዊ ወይም አዋራጅ አያያዝን ወይም ቅጣትን ወይም ሌላ የሰብአዊ መብት የዐቃቢያነ ህግ ሚና ለመወሰን በተባበሩት መንግስታት የወጣ መመሪያ አንቀፅ እና ሀ ይመልከቱ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ መጣስን በመጠቀም እንደተገኘ የሚያውቁትን ወይም በበቂ ምክንያት ይህ ስለመሆኑ የሚያምኑበትን በተጠርጣሪ ላይ የቀረበ ማስረጃ በድርጊቱ ፈፃሚዎች ላይ ካልሆነ በቀር በማንም ሰው ላይ ላለመጠቀም መወሰን ወይም ፍርድ ቤቱን ስለሁኔታው ማስረዳት እንዲሁም እንደዚህ ያለውን መንገድ የተጠቀሙ ሁሉ ለፍርድ እንዲቀርቡ አስፈላጊ የሆኑትን እርምጃዎች ሁሉ መውሰድ አለባቸው ዐቃቢያነ ህግ ስራቸውን ያለ አድሎ ለማከናወን ለሚከተሉት ነጥቦች ትኩረት ማድረግ ይኖርባቸዋል በግለሰቦች ወይም በተወሰኑ ቡድኖች ወይም በሚዲያና በህብረተሰብ ግፊት ስር ባለመውደቅ የህዝብን ጥቅም መጠበቅ ለተጠርጣሪው ጠቀሜታ ያላቸውም ሆነ አልሆኑ አግባብ ያላቸውን ሁኔታዎች ል። ርፐርህበበኗበር በአካባቢው ህግ የተፈቀደ እንደሆነ ወይም ፍትህፃዊ የፍርድ ዛደት እንዲኖር የሚያስፈልግ ከሆነ ደግሞ የተጠርጣሪውን ንፅህና ወይም ጥፋተኝነት በሚመለከት ተገቢው ምርመራ እንዲካሄድና የምርመራውም ውጤት ይፋ እንዲደረግ የማድረግ በህግና ርትዕ መሰረት በተከሳሹ በተጎጂውና በህብረተሰቡ መካከል ፍርድ ቤቶች ትክክለኛውን ፍትህ እንዲያደርጉና እውነትን እንዲያፈላልጉ ተገቢውን ጥረት ማድረግና ፍርድ ቤቶችን መርዳት ነው ዐቃቢያነ ህጎች በወንጀል የፍርድ ሂደት ሊኖራቸው የሚገባ ሚና የዓቃቤ ህግ ስራ ግልፅ በሆነ መንገድ ከዳኝነት ስራ መለየት ያለበት ሲሆን ክስ መመስረትን በህግ በተፈቀደ ወይም በአካባቢው አሰራር የተለመደ በሆነ ጊዜ ደግሞ የወንጀል ምርመራን የነዚህ ምርመራዎችን ህጋዊነት መቆጣጠርን የፍርድ ቤቶች ውሳኔ አፈፃፀምን መቆጣጠርን እንዲሁም የህዝብ ጥቅም በመወከል የሚፈፀሙ ሌሎች ስራዎችን ጨምሮ ዐቃብያነ ህግ በወንጀል የፍርድ ሄደት ውስጥ ንቁ ሚና መጫወት አለባቸውኞ የወንጀል ምርመራን በሚቆጣጠሩበትና በሚመሩበት ወቅት መርማሪ አካላት ህጉን አክብረው እንዲሁም የተጠርጣሪውን ሰብአዊ መብቶች ባረጋገጠ አኳቷን ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ እና ምርመራውን እንዲያከናውኑ ክትትል ማድረግ የሚገባቸው ሲሆን ለመርማሪ አካላት ምክር በሚለግሱበት ወቅትም ገለልተኝነትና ፍትፃህዊነትን ማሳየት ይጠበቅባቸዋል ክስ መመስረት ያለባቸው ደግሞ በቂና አስተማማኝ ማስረጃ ሲኖራቸው ብቻ መሆን አለበት ዐቃብያነ ህግ የወንጀል ፍርድ ሂደትም በተቻለው መጠን ሁሉ ፍትፃዊና ግልፅነት ያለው እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ አለባቸው በህግ በተፈቀደላቸው ጊዜ ወይም የአካባቢው አሰራር ልምድ በሚፈቅድላቸው ወቅት የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን አፈፃፀም በሚቆጣጠሩበት ጊዜ ወይም ሌሎች ተግባራትን በሚያከናውትበት ጊዜ የህዝብ ጥቅም መጠበቅ ቀዳሚ አላማቸው ሊያደርጉ ይገባል ከዚሁ በተጨማሪ ዐቃብያን ህግ በህዝብ ባለስልጣናት ለሚፈፀሙ በተለይም ሙስና በስልጣን አላአግባብ መገልገል ከባድ የሰብአዊ መብቶች ረገጣ አና ሌሎችም በአለም አቀፍ ህግ ለተደነገጉ ወንጀሎች የክስ ሂደት ተገቢውን ትኩረት ሊሰጡ ይገባል የግል ጥቅማቸው በሚነካበት ጊዜ የተጠቂዎችን አመለካከቶች ከግምት ማስገባት በወንጀልና በስልጣን አላአግባብ መገልግል ተጠቂዎች መሰረታዊ የፍትህ መርሆዎች ድንጋጌ መሰረት ተጠቂዎች ስለመብቶቻቸው እንዲያውቁ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል የተጠቂዎች መብት እንዲከበርም ተገቢውን ትኩረት ሰጥተው መስራት የሙያ ግዴታቸው ነው ። ርከ ዕዕበኗከህ ቪህዌ ዐ ርከ ከዌከበክፀከከ አንደዚህ ያለውን መንገድ በመጠቀም ማስረጃን በህገ ወጥ መልኩ ያሰባሰቡ መርማሪ አካላት ካሉ በነዚሁ ላይ ተገቢውን አርምጃ እንዲወሰድ ማድረግ ነው ከላይ ከተገለፁት ተግባራት ባሻገር ዐቃብያነ ህግ ብፄራዊ ህግን መሰረት በማድረግ ክስን ለመተው ያለምንም ቅድመ ሁኔታም ሆነ በቅድመ ሁኔታ ለማቋረጥ ወይም ከመደበኛው የፍትህ ስርዓት ጉዳዮችን በአማራጭ አልባት ወደሚያገኙበት መድረክ ለመምራት ተገቢውን ትኩረት መስጠት አለባቸው ይህንን ሲያደርጉ ግን የተጠርጣሪዎቹንና የተጠቂዎቹን መብቶች ሙሉ በሙሉ ማክበር ይገባቸዋል ለዚህም ሲባል የፍርድ ቤቶች የስራ ጫና ለማቃለል ብቻ ሳይሆን ቅድመ ክስ አስር መከሰስጥፋተኛ በመባሉ የሚያስከትለው የመገለል ስሜትና እስር ሊያስከትል የሚችለውን ፅኑ ውጤት ለማስቀረት መንግስታት በተቻላቸው አቅም አማራጮች እንዲያፈላልጉ ግፊት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ከሌሎች የፍትህ አካላት ጋር በቀና የትብብር መንፈስ ተቀናጅቶ ስለመስራት የክስ ሂደትን ፍትፃዊነትና ውጤታማነት ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ዐቃብያነ ህግ በተቻላቸው አቅም ከፖሊስ ፍርድ ቤቶችየህግ ባለሙያዎችተከላካይ ጠበቆችና ሌሎች የመንግስት አካላት ወይም ተቋማት ጋር ለመተባበር መሞከር አለባቸው ዐቃብያነ ህግ በሌሎች ሀገሮች ለሚገኙ የዐቃብያነ ህግ ተቋማትና የሙያ አጋሮቻቸው ጋርም ተባብረው መስራት አንደሚጠበቅባቸው ተመልክቷል ከሌሎች አካላት ጋር ዐቃብያነ ህግ በሚኖራቸው የስራ ግንኙነት የሙያ ነፃነታቸው በሚገባ እንዲጠበቅ የበኩላቸውን ጥረት ማድረግ ይጠቅባቸዋል በተለይም የዐቃቤ ህግነት ስራቸውን ከስራ አስፈፃሚ የመንግስት ተቋማትና ከህግ አውጪው ክፍል ተፅአኖ ሳይደረግባቸው በህግና በህጉ መሰረት ብቻ ነው ማከናወን ያለባቸውኞ በርግጥ በብዙ ሀገሮች የዐቃቢያነ ህግ ተቋማት በስራ አስፈፃሚነት የመንግስት አካል ስር የተደራጁና ተጠሪነታቸውም ለነዚሁ አካል ሲሆን የተባበሩት መንግስታት የዐቃብያነ ህግ ሚናን በተመለከተ የወጣው መመሪያም ሆነ የአለም አቀፍ ዐቃብያነ ህግ ማህበር የተግባር መመሪያ ይህንን አደረጃጀት መቀየር ላይ ሳይሆን ትኩረቱ ዐቃብያነ ህግ ከስራ አስፈፃሚ የመንግስት አካል አንድ ጉዳይ ላይ ክስ አንዳይቀርብ የሚያስተላልፈው ትዕዛዝ ገደብ ሊበጅለት አንደሚገባ ነው የአውሮፓ ህብረት አስተያየቶች የሚጠቁሙት ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ዐ ን ይመልከቱ በተጨማሪም የዓለም አቀፍና የዐቃብያነ ሐግ ማህበርን የተግባር መመሪያ አንቀጽ ን መመልከት ይቻላል ገዝፎ ልአ ኣዐጀኮኗአዐጀአርዩ ዕዞ ዞዕዐርዕህፐር ኮልሀ እከ አዐዘዚከፀጠ ዘልበ ከበሃ ር ገዕ ይመለከቱ የስራ አስፈፃሚው የመንግስት አካላት እንዲህ አይነቱን ስልጣን አልፎ አልፎ ብቻ መጠቀም እንደሚገባቸውና እንዲህ በሚደረግበት ጊዜ በግልፅነት በታወቁ መስፈርቶች ላይ መመስረት ወሳኝ እንደሆነ ነው ስልጣንና ተሰሚነት ዐቃብያነ ህግ ስራቸውን በፍፁም ነፃነትና ስለዐቃቤ ህግነት በወጡ አለም አቀፍ መርሆዎች መሰረት እንዲያከናውኑ ከሌሎች የመንግስት አካላት ጣልቃ ገብነት መጠበቅ ይኖርባቸዋል የዐቃቤ ህግነት ስልጣናቸውንም በህግ አግባብ ለህብረተሰቡ ጥቅምን በሚያስገኝ መልኩ ነው በትክክል ስራ ላይ ማዋል የሚያስፈልጋቸው በተለይም የዐቃቤ ህግነት ስልጣናቸውን ተግባራዊ በሚያደርጉበት ወቅት የሚከተሉት ጥበቃዎች ከመንግስት ሊደረግላቸው ይገባል የሙያ ግዴታቸውን ያለ ማስፈራራት እንቅፋትወከባ አግባብ ያልሆነ ጣልቃ ገብነት ለምክንያት አልባ የፍትህሃብፄር ወንጀል ወይም ሌላ ኃላፊነት ሳይጋለጡ እንዲወጡ ዋስትና መስጠት ዐቃብያነ ህግ የስራ ግዴታቸውን በሚወጡበት ወቅት የግል ደህንነታቸው አደጋ ላይ በወደቀ ጊዜ ከመንግስት ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው የአካላዊ ደህንነት ጥበቃን የማግኘት ከሚያከናውኑት ቁልፍ ተግባርና ኃላፊነት ጋር የሚመጣጠን የአገልግሉት ሁፄታተመጣጣኝ ክፍያና በቂ ደመወዝ እንዲሁም የአገልግሎት ዘመን በተቻለ መጠን ሁሉ የዐቃብያነ ህግ ምልመላና የስራ እድገት በተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ አንዲሆን ሙያዊ ብቃትን ችሉታን ጠንካራ ስብዕናንና ልምድን መሰረት ያደረገ ሆኖ ፍትዛዊና ገለልተኛ የሆነ ስርዓትሆጂ ልበ አጠሀቭ ኮርርርሀ ተከትሉ እንዲወሰን ዐቃብያነ ህግ ግልፅ በሆነ መንገድ ከሙያዊ ደረጃቸው ወሰን ዉጪ የሆነ ኢስነምግባራዊ ድርጊት ፈፅመዋል የሚል ቅሬታ በቀረበባቸው ጊዜ የዲስፒሊን ዝኒ ከማሁ ሀ ሃ ዐ ከከ ዐህከ ከ ዐ ዐር በዐሀሠመበ ከሃ ከፀ ዝቧከጠከዐከእቪ ላ ፊጪዐርከዐእ ዐ ጅዐፍፀርሀ። ዐኗ ዐከ ከፀ ከሆፀአቨ ከበ በሃ ዐ ለዝ ህርፀ ይመልከቱ ክስ ሂደቱን በፍጥነትና ፍትፃዊ በሆነ ሁኔታ አግባብ ባላቸው ስነ ስርዓቶች መሰረት እንዲታይ በዲስፒሊን ክስ ሂደት ዐቃብያነ ህግ ገለልተኛ በሆነ መንገድ የመሰማትና ፍትፃዊ ውሳኔ የማገኘት መብታቸውን ሊረጋገጥላቸው እንደሚገባ በዐቃቢያነ ህግ ላይ የሚደረግ የዲስፒሊን የክስ ሂደት ተጨባጭ ግምገማና ውሳኔ እንዲኖረው ማድረግ ተገቢነት ያለው ሲሆን ሂደቱም በህግ በሙያዊ ስነምግባርና በሌሎች ተቀባይነት ባገኙ የኖሩ ደንቦች ላይ የተመሰረተ መሆን ይገባዋል አንደ ሌሎች ዜጎች ሁሉ ዐቃብያነ ህግ ሃሳብን የመግለፅየእምነትየመደራጀትና የመሰብሰብ ነፃነት አላቸው በተለይም ህግን የፍትህ አስተዳደርን የሰብአዊ መብቶችን መስፋፋትና መጠበቅን በሚመለከቱ ህዝባዊ ሰብሰባዎች የመካፈል መብት አላቸው አነዚህን መብቶች በስራ ላይ በሚያውሉበት ጊዜ ሁሉ ዐቃብያነ ህግ ራሳቸውን ለህጉና በሙያቸው ለታወቁ መመዘኛዎችና ስርዓቶች ተገዢ ማድረግ ይኖርባቸዋል ከዚሁ ጋር ተያይዞ ዐቃብያነ ህግ የሙያ ማህበራቸውን ወይም ሌሎች ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁላቸው ድርጀቶችን በማቋቋምና አባል በመሆን ሙያዊ ስልጠናቸውን ለማስፋፋትና አቋማቸውን ለመጠበቅ የምንቀሳቀስ መብት አላቸው አቃቤ ህጎች አጠቃላይ በግል ኑሮአቸው ሊያከብሩት የሚገባ ስነምግባር አቃቤህግ ሰብአዊ መብቶችና ነጻነቶችን የጣሱ ሰዎችን ለፍርድ የሚያቀርብ ከመሆኑ አንጻር አሱም አራሱ በድርጊቱ ሰብአዊ መብቶችንና ነጻነቶችን የሚያከበርና አርአያ መሆን አለበት አቃቤ ህግ በግል አኗኗሩ ተቋሙን ጥያቄ ውስጥ ከሚከት አኗኗር መጠበቅ አለበት ተቋሙ ተገቢውን ክብርና ድጋፍ የሚያገኘው አቃቤ ህጉ በግል አኗኗሩ በሚያሳየው ባህርይ ነው አቃቤ ህግ የጥቅም ግጭት በሚፈጥር ስራ ውስጥ መግባት የለበትም ከሙያው ጋር የሚቃረን ተግባር ተሰማርቶ ገቢን ለማግኘት መሞከር የለበትም አቃቤ ህግ የፍርድ ቤቱን ነጻነት መቀበልና መጠበቅ አለበት የፍርድ ቤትን ውሳኔ ሊቃወመው የሚችለው ይግባኝ በማቅረብ ብቻ እንጂ በአደባባይ በመተቸት አይደለም መወያያ ጥያቄዎች አንድ የምርመራ መዝገብ ተጠናቆ የመጣለት አቃቤ ህግ የተሰባሰቡትን ማስረጃዎች ሲመረምር አንዳንዱ ተከሳሽን የሚጠቅም ሆኖ ያገኘዋል ስለሆነም ተከሳሽን የሚጠቅመውን ማስረጃ በማስቀረት በተከሳሽ ላይ ክሱን ለማስረዳት የሚጠቅመውን ማስረጃ ብቻ አያይዞ ክስ ይመሰርታል አቃቤ ህግ ተከሳሽን የሚጠቅም ማስረጃ ለተከሳሹ ማሳወቅና መስጠት ይገባው ነበር ይህንን ባለማድረጉ የሙያ ስነምግባሩን አላከበረም ይባላል። ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ን መመልከት ይቻላል ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ትን ይመልከቱ አንዲያገኙ መደረግ አለበትጭ በመንግስት የሚመደብላቸውም የህግ አማካሪ ከተከሰሱበት ጉዳይ ውስብስብነት ጋር በሚመጣጠን መልኩ በቂ ልምድና ችሉታ ያላቸው መሆን ይገባዋል ችሎታቸውና ልማዳቸው አምብዛም ያልሆነ የህግ አማካሪዎችን መመደብ በዚህ ረገድ በመንግስት ላይ የተጣለውን ኃላፊነት መንግስት በሚገባ አንዳልተወጣው ነው የሚያስቆጥረው በርግጥ በአብዛኛው በወንጀል ጉዳዮች ላይ ነው የመክፈል አቅም ለሌላቸው ግለሰቦች በመንግስት ወጪ ጠበቃን ማቆም የሚገባው ይሁን እንጂ ከወንጀል ጉዳይ ዉጪ በሆነ መልኩ ለተያዙ ግለሰቦች በመንግስት በነዓ ጠበቃ የማቆም ግዴታ እንዳለበት ነው ተደንግጎ የሚገኘው በአለም አቀፍ መርሆዎች የተደነገገው ደረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ በተለይም የተያዙ ሰዎች ጠበቃ የማቆም አቅም በማይኖራቸው ጊዜ መንግስት በተቻለው አቅም ሁሉ ከተያዙበት ጊዜ አንስቶ በ ሰዓታት ውስጥ ነው ነዛ የህግ አገልግሎት የሚሰጣቸውን የህግ አማካሪ ሊመደብላቸው የሚገባው ከዚህ የምንረዳው በሁሉም የፍርድ ሂደቶች ዜጎች በህግ አማካሪ ሳይወከሉ በፍርድ ሄደት እንዳያልፉ የሚደረግ መሆኑን የሚያመለክት ነው በሌላ አነጋገር አቅም ያጡ ግለሰቦች በድህነታቸው ምክንያት ብቻ የህግ ምክር ሳያገኙ በማንኛውም የፍርድ ሂደት እንዲሳተፉ ወይም ለፍርድ እንዲቀርቡ ከተደረገ የሁሉም ሰዎች ፍትፃዊሚዛናዊ ግልፅ የሆነ ዳኝነት የማግኘት መብት ተከብሯል ለማለት አያስደፍርንም የተያዙ ሰዎች በአስር ወቅት በመንግስት ከተመደበላቸው የህግ አማካሪ ጋር የሚገናኙበትና በነዛባነት የሚወያዩበት በቂ እድል ሊሰጣቸው ይገባል እነዚህ ሰዎች ከህግ አማካሪዎቻቸው ወይም ጠበቆቻቸው ጋር የሚያደርጉት ምክክርና ውይይት በየትኛውም መልኩ በህግ አስከባሪ ባለስልጣናት ሊደመጥና ይዘቱም ቅድመ ምርመራ ሊደረግበት አይገባም ጥብቅና ከፍተኛ ኃላፊነት የሚያስከትልና በፍትህ አስተዳደር ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው ሙያ በመሆኑ ከጠበቆች ከፍ ያለ ስነ ምግባር ነው የሚጠበቀው ከዚህም የተነሳ ጠበቆች በግል ህይወታቸውም ጭምር የሙያውን ክብርና ዝና ከሚያጎድፉ ባህሪያት ራሳቸውን ማግለልና በሚገባ መጠበቅ አለባቸው ከዚህም አልፍው የሙያ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ፀትን ይመልከቱ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ሃን መመልከት ይቻላል ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ተን ይመልከቱ ባልደረቦቻቸው የስነ ምግባር ጉድለት እንዳያሳዩ የመምከርና የስነ ምግባር ጉድለት ፈፅመው ሲገኙ ደግሞ ለተገቢው አካል የመጠቆም ኃላፊነት አለባቸው ለዚህ ነው ጠበቆች ሁሌም ቢሆን የሙያቸውን ክብርና ዝና በመጠበቅ የፍትህ አስተዳደሩ ዋልታ መሆን ይገባቸዋል የሚባለውኞ አንድ ጠበቃ የሙያውን ክብርና ዝና ለመጠበቅ የሚከተሉትን አሴቶች ማክበር በተግባርም ማሳየት ይኖርበታል ሙያዊ ነፃነትን ገለልተኝነትን ቅንነትን በስራው ላይ በተጨባጭ ማሳየት ጁዱ የባለጉዳዩን ምርጫ ፍላጎትን ጥቅም በማስቀደም በርሱ ፍላጎት መሰረት የጥብቅናውን ስራ ማከናወን ጁ የባለጉዳዩን ጥቅም በተቻለ መጠን ሁሉ ለማስጠበቅ ትጋት ማሳየትና ተገቢውን ጥረት ማድረግ የሙያውን ወይም የራሱን ክብና ዝና በሚያስጠብቅ መልኩ የግል ህይወቱን መምራት የጥብቅና ስራ የሚጠይቀውን ሙያዊ ኃላፊነትና የስራ ደረጃ አሟልቶ መገኘት ጁ በክርክር ሂደት ለዳኝነት አገልግሎቱ ውጤታማነት ሲባል ፍቤቶች ከፍትዛዊ ውሳኔ እንዲደርሱ ያለበትን ግዴታና ኃላፊነት መወጣት ናቸው ጠበቆች የባለጉዳዮች ወኪል ብቻ ሳይሆነ የፍትህ አስተዳደሩም ዋልታ በመሆናቸው ጭምር ፍርድ ቤቶች በእውነት ላይ እንዲያደርሱና ፍትሃዊና ሚዛናዊነትን የተላበሰ ውሳኔ እንዲሰጡ መርዳት አለባቸው ከዚህ አንፃር የፌዴራል ፍቤቶች ጠበቆች ስነ ምግባር ደንብ የሚከተሉትን ግዴታዎች በጠበቆች ላይ ጥሏል ጁ በምቀኝነት ወይም በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ሌላውን ወገን የሚጎዳ ክስ ወይም ክርክር አለማቅረብ ዱ ደንበኛው የወራዳነት ወይም የማጭበርበር ድርጊት እንዲፈፅም አለማበረታታት ወይም አለመፍቀድ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ የፌዴራል ነጋሪትጋዜጣ ኛ አመት ቁጥር የፌዴራል ፍቤቶች የጠበቆች የስነምግባር ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር አንቀጽ ይመልከቱ ዳኛን ወይም ሌላ የፍቤት ሰራተኛን በህግ መሰረት ከማሳመን ውጪ ሌላ ተገቢ ያልሆነ ማንኛውም አይነት ዘዴ በመጠቀም ተፅህኖ ለማሳደር አለመሞከር ወይም ሌላ ሰው እንዲሞክር አለመገፋፋት ዱ ሆነ ብሎ ፍቤትን የሚያሳስት የተጋነነ ፅሁፈ ንግግር ለፍርድ ቤት አለማቅረብ በምስክርነት ቃል ወይም የሰነድ ይዘት ላይ የሀሰት ድርጊት በመፈፀም ፍርድ ቤትን ለማሳሳት አለመሞከር በግልዕ ለጉዳዮ አግባብነት የሌለውን ማስረጃ አግባብነት ያለው አስመስሉ ለፍርድ ቤት አለማቅረብ ለጉዳዮ በምስክርነት መቅረብ የሚገባው ሰው ፍርድ ቤት አንዳይቀርብ አለማባበል ወይም አለመሞከር አንድን ምስክር ተገቢ ባልሆነ መንገድ አለማመናጨቅ አለማስጨነቅወይም አለማስፈራራት ናቸው በጥቅሉ የባለጉዳይን ጥቅም ከማስጠበቅ የተሻገረ ኃላፊነት አንዳለበት አውቆ ፍርድ ቤቱ ከአውነተኛና ፍትሃዊ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ የሚጠበቅበት ሲሆን የጥብቅና ስራውንም በቅን ልቦና ማከናወን ይጠበቅበታል ሌላኛውና ዋንኛው የጠበቆች የስነ ምግባር ግዴታ ጠበቆች ከደንበኞቻቸው አንፃር ያለባቸው ግዴታ ነውኞ በዚህ ረገድ የጠበቆች ዋንኛ ግዴታ የሚሆነው ባለጉዳዮች ዳኝነት ከጠየቁበት የክርክር ጭብጥ አንፃር ያላቸውን መብትና ግዴታ እንዲሁም መብታቸውን ለማስከበርና ግዴታቸውን ለመወጣት ህጉ የሚደነግጋቸውን አካሄዶችና ስነ ስርዓቶች እንዲያውቁ ማድረግ ነው ከዚሀ ጋር ተያይዞ የባለጉዳዮችን መብትና ጥቅም ለማስከበር እነርሱን ወክሎ ክርክር በማቅረብ መብታቸውና ጥቅማቸው እንዲከበር ዕውቀቱንና የስራ ልምዱን ስራ ላይ ማዋል ነው ከዚህም በላይ የደንበኛውን ጉዳይ ከመደበኛ ፍርድ ቤት ወይም አስተዳደራዊ የዳኝነት አካላት ዘንድ በመውሰድ የደንበኛውን ጉዳይ በትጋት መከታተል አፋጣኝና ፍትዛፃዊ ውሳኔ እንዲያገኝም ሙያዊ ጥንቃቄ ብርቱ ጥረት ማድረግ ይገባዋል በዚህ ሂደት ውስጥም ጉዳዩ የደረሰበትን ደረጃ በየጊዜው ለደንበኛው የማሳወቅ ግዴታ አለበት እንዴኤ አ በ የወጣውን የተባበሩት መንግስታት የህግ ሙያተኞችን ሚና መሰረታዊ መርሆዎች አንቀጽ ጠበቆች ሁሌም ቢሆን የደንበኞቻቸው ጥቅም ለማስጠበቅ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል ለደንበኞቻቸው ጥቅም መከበርም በፍፁም ታማኝነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋልፍ በዚህ ረገድ በጠበቃውና በደንበኛው ወይም በጠበቃው ዘመዶችና በደንበኛውወይም ጠበቃው በወከላቸው የተለያዩ ደንበኞች መካከል የጥቅም ግጭት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል እንዲሁም በጥብቅና አገልግሎቱ ምክንያት ያወቃቸውን የደንበኛውን የግል ወይም የስራ ሚስጥሮችን መጠበቅ አለበት ደንበኛው ሳይፈቅድለት በሙያው ምክንያት አጁ የገቡትን ማናቸውንም የደንበኛውን ሚስጥሮች ለሌላ አካል አሳልፎ ሊሰጥ አይችልም ራሱም ቢሆን በህግ በተፈቀዱለት ጥቂት ሁኔታዎች ካልሆነ በቀር ሊጠቀምበት አይችልም ከዚህም በተጨማሪ ጠበቆች ለሌሉች ሶስተኛ ወገኖችም ቅን የመሆን ግዴታ አለባቸው በተለይም ሌሎች ተከራካሪዎችን ለማጉላላት በማሰብ አከራካሪ የሆነ ጭብጥ ወይም በሌላኛው ተከራካሪ ላይ ኃላፊነትን ሊያስከትል የሚችል ውጤት የሌለ መሆኑ በግልፅ አኳኋን የሚታይበት ሁኔታ ቅንነትን በማጣት ተገቢ ያልሆነ ክርክር በተቃራኒ ወገኖች ላይ መጀመር የለበትም ከዚህ አንፃር በተለይም ከዚህ በታች ከተገለፁት ድርጊቶች መቆጠብ አለበት እነዚህም ተቃራኒ ወገን ማስረጃ እንዳያገኝ ማንኛውንም እንቅፋት መፍጠር ወይም ሌሉች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር ወይም መረዳት ማስረጃን ማሳሳት ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት አንዲፈፅሙ መሞከር መርዳት ጁ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌለው ወይም በማስረጀ ሊደገፍ የማይችል ነገር ማቅረብ በምስክርነት ካልቀረበ በቀር በግል የሚያውቀውን የጭብጥ ነገሮች መሰንዘር ወይም የጉዳዩን ፍትፃዊነት የአንድን ምስክር ተዓሚነት የተከሳሽን ጥፋተኛ ወይም ተጠያቂ መሆንና አለመሆን አስመልክቶ የግል አስተያየቱን መስጠት ደንበኛው ወይም ምስክርነታቸውን አንዲሰጡ የማይገደዱ ሰዎችን በተመለከተ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ማንኛውንም ሰው ለተቃራኒ ወገን የምስክርነት ቃሉን ወይም ሌላ አግባብነት ያለው ማስረጃ እንዳይሰጥ መገፋፋት ናቸው ዝኒ ከማሁ አንቀጽ የፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ኛ ዓመት ቁጥር የፌዴራል ፍቤቶች የጠበቆች የስነ ምግባር ደንብ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር አንቀፅ እና ን ይመልከቱ በመጨረሻም ጠበቆችም ፍትፃዊ ዳኝነት እንዲጎለብት እንዲሁም የደንበኞቻቸው መብትና ጥቅም እንዲጠበቅ የማድረግ ድርብ ኃላፊነት ሲኖርባቸው እነዚህን ኃላፊነቶች በተጣጣመ መልኩ ነው ማከናወን ያለባቸው ከዚህ አኳያ ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነፃነቶች መከበር በትጋት መቆምና መስራት ይኖርባቸዋል በዚህ ረገድ የደንበኛቸውን ጥቅም ማስጠበቅና ለፍትህ መከበርም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ መካከል የሚታየውን ክፍተት ለማጣጣመና ሚዛናዊ ለማድረግ መጣር አለባቸው ጠበቆች ሙያቸው የግለሰቦች መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች እንደከበሩና እንዲጐለብቱ የማድረግ ልዩ ኃላፊነት ወይም ግዴታ እንደጣለባቸው በመገንዘብ ይህንን ከፍተኛ የሙያ ግዴታ ለመወጣት ከፍተኛ ስነምግባር መላበስ ይጠበቅባቸዋል ለፍትህ ሥርዓቱ መጐልበትና ለሰብዓዊ መብቶች መከበርም ዘወትር የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት መሥራት እንደሚገባቸውና በዚህ ሂደት ውስጥም ለሙያቸው ስነምግባር መገዛት እንደሚጠበቅባቸው ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል የሕግ አስከባሪ አካላት የስነምግባር መመሪያዎችን በተመለከተ ያሉ ዓለምአቀፍ መርሆዎች በተባበሩት መንግሥታት የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የስነምግባር መመሪያ ላይ እንደተመለከተው ከሆነ የሕዝብን ደህንነትና ፀጥታ ለማስከበር የሚደረጉ የሕግ ማስከበር ስራዎች በግለሰቦችም ሆነ በህብረተሰቡ አኗኗር ላይ የሚያስከትሉትን ተፅዕኖ ከግምት በማስገባት የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የሰብዓዊ መብቶችን ጥበቃ መርሆዎች ተከትለው በጥንቃቄና ሰብዓዊ ክብር ባልተለየው ሁኔታ ሥራቸውን እንዲያከናውኑ ለማድረግ የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የሚመሩበትን የተግባር መመሪያ ማውጣት አስፈላጊ ነው በተለይም ከህግ አስከባሪ አካላት አገልግሎት የሚያገኙ ዜጐች መሰረታዊ መብቶች እንዲከበሩና ጥቅሞቻቸው እንዲጠበቁ በማድረግ ረገድ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው እንዴኤ አ በ የወጣውን የተባበሩት መንግስታት የህግ ሙያተኞችን ሜና መሰረታዊ መርሆዎች አንቀጽ በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ውሣኔ ቁጥር እኤአ ዲሴምበር ዓም የፀደቀውን የሕግ አስከባሪ አካላት የስነምግባር መመሪያ መግቢያ ፐራግራፍ እና ን ይመለከቱ የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት በስልጣናቸው ያለ አግባብ ሳይጠቀሙ የሕግ ማስከበር ኃላፊነታቸውን በአግባቡና ሰብዓዊ በሆነ አሰራር ለማከናወን አንዲችሉ የሚከተሉትን ርምጃዎች መውሰድ ጠቃሚነት አንዳለው ሊታወስ ይገባል የወንጀል ድርጊቶች ታይተውና ተመርመረው ውሣኔ የሚሰጥበት የፍትህ ስርዓት ተቋማት እንደሚያደርጉት ሁሉ እያንዳንዱ ሕግ ለማስከበር የሚደራጅ ተቋማት ሕብረተሰቡን በጠቅላላ አንዲወክል ለሕብረተሰቡ ችግሮች መፍትሄ የሚፈልግና ተጠሪነቱም ለሕብረተሰቡ እንዲሆን መደረግ አለበት የሕግ አስከባሪ ሃይሎችን የመንፈስ ልዕልና በተሳካ ሁኔታ ጠብቆ ማቆየት የሚቻለው መሰረቱ ትክክለኛ የሆነ ሕዝብ የተቀበለውና ሰብዓዊ የሆነ የሕግ ስርዓት እንዲኖር ሲደረግ ነው « አያንዳንዱ የሕግ አስከባሪ ባለስልጣን ዓላማው የወንጀል ድርጊቶችን ማስቆም እንዳይፈፀሙ ማድረግና መቆጣጠር እንደመሆኑ አንዲሁም የወንጀል ጉዳዮች የሚታዩበትና የሚመረመሩበት የፍትህ ሥርዓት አካል በመሆኑና የእያንዳንዱ በስርዓቱ ውስጥ የሚገኝ ባለስልጣን ስነምግባር በጠቅላላ በስርዓቱ ላይ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል መገመትና በዚህ ረገድ ሊፈጠር የሚችለውን አሉተዊ ተጽዕኖ ለመቀነስ ተጨባጭ ርመጃዎችን መውሰድ ተገቢ ነው የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት በሚወስዷቸው ርምጃዎች አንፃር በተባበሩት መንግሥታትን የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የተግባር መመሪያዎች መመራት ያለባቸው ከመሆኑም ባሻገር በእነዚህ አካላት የሚወሰዱ ርምጃዎች ላይ የሚቀርቡ ቅሬታዎች መታየት የሚኖርባቸው በቅሬታ ሰሚ ቦርድ በፍትህ ሚኒስቴር በፍርድ ቤቶች በዕንባ ጠባቂ ተቋም በዜጐች ኮሚቴ ወይም ከነዚህ አካላት ተውጣጥቶ በተቋቋመ አካል ሊሆን ይገባል የተባበሩት መንግሥታት የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የተግባር መመሪያዎች የሕግ አስከባሪ አካላት በዕለት ተዕለት ሥራቸው ውስጥ ተግባራዊ እንዲያደርጓቸው መንግሥታት እነዚህን የተግባር መመሪያዎች በብፄራዊ ሕጐቻቸው ሊያካትቷቸው ይገባል የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት ሕብረተሰቡን ለማገልገልና ሁሉንም ሰዎች ከሕገወጥ ድርጊቶች ለመጠበቅ በሕግ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነት ሁልጊዜም የሙያ ግዴታቸው በሚጠይቀው ሁኔታ ሊወጡ ይገባል ሙያቸው የሚጥልባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነት ለመወጣት ሁሌም ቢሆን ሁሉም ሰዎች ከሕገወጥ ድርጊት ወይም ጥቃት እንዲጠበቁ የማድረግ ልዩ ኃላፊነት አለባቸው የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የሕዝብ አገልጋዮች አንደመሆናቸው መጠን ሕብረተሰቡንና ግለሰቦችን ከማናቸውም ዓይነት ጥቃት መከላከል ይጠበቅባቸዋል የህግ አስከባሪ አካላት በምንልበት ጊዜ የፖሊስ ስልጣን የተሰጣቸው በተለይም የመያዝና የማሰር ስልጣንን ጨምሮ ስራቸውን በሚያከናውኑበት ወቅት አስፈላጊ ኃይል የመጠቀም ስልጣን ያላቸው ተሹዋሚዎች ወይም ተመራጮች ናቸው በአኛ ሀገር ሁኔታ የፖሊስ ተቋማትና ማረሚያ ቤቶችን ይጨምራል በርግጥ የፖሊስነት ስልጣን በተሰጣቸው ጊዜ የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የሚለው አገላለጽ የጦር ሠራዊትና የፀጥታ ኃይሎችንም ሊጨምር አንደሚችል ነው የተባበሩት መንግሥታት የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የስነምግባር መመሪያ የሚመለከተው አነዚህ አካላት ሕግን ከማስከበር አልፈው የተፈጥሮም ሆነ ሰው ሰራሽ አደጋ በአንድ ማህበረሰብ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት በሚያደርስበት ጊዜ ያንን ሕብረተሰብ ከአደጋ መታደግን ማዕከል ያደረገ ሕዝባዊ አገልግሎት ያበረክታሉ ለዚህም ነው እነሺህ አካላት ሕግ አስከባሪ ብቻ ሳይሆኑ ሕዝባዊ አገልግሎት ዕዐቦባጠህበቪሃ ከርዉ የሚሰጡ ተቋማት ናቸው የሚባለው ለሕብረተሰቡ የሚሰጥ አገልግሉት በተለይ የግል የኢኮኖሚ የማህበራዊና ሌሎች ድንገተኛ ችግሮች ለደረሰባቸው የሕብረተሰቡ አባላት የሚደረገውን ዕርዳታ ይጨምራል የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት ተግባራቸውን በሚያከናውኑበት ጊዜ የሁሉንም ሰዎች ሰብዓዊ ክብርንም ሆነ ሰብዓዊ መብቶችን ሊያከብሩ ይገባል በዚህ ረገድ የግለሰቦችን መሠረታዊ መብትና ነፃነት ከሚፃረር የኃይል ድርጊት መቆጠብ ይኖርባቸዋል በተለይም በብፄራዊ ሕጉችና ዓለምአቀፍ ሕጐች ጥበቃ ያገኙትን የሰብዓዊ መብቶች በሚገባ ማወቅና ማክበር አንዲሁም ማስከበር ከሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የሚጠበቅ ሙያዊ ግዴታ ነው ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ያንብቡ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ስለዚህም አንዱና ዋነኛውም የስነምግባር ግዴታቸው የሰዎችን ሰብዓዊ መብቶች ማክበርና መጠበቅ ነው ለማለት ይቻላል ለዚህም ሲባል የሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የሰብዓዊ መብቶችን ለይተው በማወቅ እንዲያከብሩና እንዲያስከብሩ ለማድረግ ስለ ሰብዓዊ መብቶች የተደነገጉ ሀገራዊ ክፍለ አህጉራዊና ዓለምአቀፋዊ ድንጋጌዎችንና በነዚህም ውስጥ የሰፈሩ መሰረታዊ መብቶችን እንዲያውቁ ማድረግ የመንግሥት ፃላፊነት መሆን አለበት ሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት የኃይል እርምጃን መጠቀም የሚችሉት እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ሁኔታዎች በሚፈጠሩበት ጊዜ ብቻ ሲሆን ይህም ለሥራው አፈፃፀም በሚያስፈልገው ኃይል ልክ የተወሰነ ይሆናልኞ ሕግ አስከባሪ ባለስልጣናት በኃይል ሊጠቀሙ የሚችሉት እጅግ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ልዩ ሁኔታ ሲያጋጥማቸው ብቻ ነው ይኸውም የወንጀል ድርጊት አንዳይፈፀም ለመከላከል ሲባል የወንጀል ድርጊት ፈፃሚዎችን ወይም ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን ሕግ በሚፈቅደው መሰረት ለመያዝ ወይም እንዲያዙ ለመርዳት ሕግ አስከባሪዎች ከሁኔታዎች ጋር የተመጣጠነ ሀይል ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ሕጉ ቢያመለክትም ሁፄታዎች ከሚጠይቁት መጠን ያለፈ ኃይል ግን ሊጠቀሙ አይችሉም ዐ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ን ይመልከቱ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ን ይመለከቱ በብዙ ሀገራት ብፄራዊ ሕጐች ላይ ሕግ አስከባሪዎች ሊጠቀሙ የሚገባውን ኃይል ተመጣጣኝ የሆነ በሚል ገደብ የተበጀለት ሲሆን ለዚህ ቃል የሚሰጠው ትርጓሜ በተቻለው መጠን ሁሉ ጠበብ ተደርጐ የሕጉን ዓላማ ለማስፈፀም በቂ የሆነውን ኃይል ለማለት እንደተፈለገ ተወስዶ የሕጉን ዓላማ ከማስፈፀም ጋር የማይመጣጠን የኃይል አጠቃቀምን እንደማይፈቅድ ሊታወቅ ይገባል ከዚህም በመነሳት የሕግ አስከባሪዎች ኃይልን መጠቀም የሚችሉት በጣም ውሱን በሆኑ ሁኔታዎች ብቻ ማለትም ወንጀልን ለመከላከል ወይም የወንጀል ድርጊት የፈፀሙ ግለሰቦችን ይዞ ለሕግ ለማቅረብ በሚያስፈለግበት ጊዜ ነው በጦር መሣሪያ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ መጠቀም ሌላ አማራጭ ሲጠፋ ሊወሰድ የሚገባው የመጨረሻ አማራጭ ነው ተደርጐ ሊወሰድ የሚገባው በተለይም በሕፃናት ላይ በጦር መሣሪያ መጠቀምን ለማስቀረት የሕግ አስከባሪዎች የተቻላቸውን ሁሉ ማድረግ አለባቸው የወንጀል ድርጊት ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች እንዳይያዙ በጦር መሣሪያ የሚከላከሉ ካልሆነ በስተቀር ወይም ለሌሎች ሕይወት አደገኛ ካልሆኑና አነስተኛ የኃይል አርምጃ ተወስዶ ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ ወይም ድርጊታቸውን ለመግታት የማይቻል ካልሆነ በስተቀር በጦር መሣሪያ መጠቀም ተገቢነት የለውም የሕግ አስከባሪዎች የጦር መሳሪያን ለመጠቀም የሚያስገድዳቸው ሁኔታ ከተፈጠረና የዚህ አይነቱንም እርምጃ የወሰዱ እንደሆነ ወዲያውኑ ለሚመለከታቸው ባለስልጣናት ስለሁኔታው ሪፖርት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል በህግ አስከባሪ ባለስልጣን ይዞታ ስር የሚገኙ ሚስጥርነት ያላቸው ጉዳዩች ግዴታን ለመወጣት ወይም ፍትህ የሚጠይቀውን ለማሟላት የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሚስጥርነታቸው እንደተጠበቀ ይቆያሉ ከያዙት የስራ ኃላፊነት የተነሳ የህግ አስከባሪዎች የሰዎችን የግል ህይወት የሚመለከቱ ወይም ለጥቅማቸውና ለመልካም ዝናቸው ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ መረጃዎችን ያገኛሉ እነዚህን መረጃዎች በከፍተኛ ጥንቃቄ ሊጠብቁ ይገባል ለሌሎች ወገኖች የሚገልፁትም የስራ ኃላፊነትን ለመወጣት ወይም ፍትህ ለማስፈን በጣም አስፈላጊ ሲሆን ብቻ ነው ስለዚህም የህግ አስከባሪዎች በስራ አጋጣሚ በአጃቸው የገቡትን መረጃዎች ሚስጥራዊነት በሚገባ መጠበቅ የሙያ ግዴታቸው ነው ማንኛውም የህግ አስከባሪ ባለስልጣን የማሰቃየትና ጭካኔ የተሞላበት ሰብአዊነት የሌለውና ሰብአዊ ክብርን የሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት ሊፈፅም ወይም አንዲፈፅም ማነሳሳት ወይም ሲፈፅም አይቶ ማለፍ የማይገባው ሲሆን ለዚህም በምክንያትነት የበላይ አካል ትፅዛዝንጦርነትንየጦርነትን ስጋትን የሀገር ፀጥታን መደፍረስን የውስጥ ፖለቲካ አለመረጋጋትን ወይም ማንኛውንም በህዝብ ደህንነትና ፀጥታ ላይ ሊፈጠሩ የሚችሉ አስቸኳይ ሁኔታወችን ቢያቀርብም ተቀባይነት የለውም እንደዚህ አይነቱን ድርጊት መፈፀም በሰብአዊ ክብር ላይ የወንጀል ድርጊት መፈፀም በመሆኑ የተባበሩት መንግስታት ቻርተርንና የተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችን የሚጥስ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ን ይመልከቱ ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ን ይመልከቱ ተግባር ነው በመሆኑም በጥብቅ የተወገዘ ነው እዚህ ላይ ልብ ሊባሉ የሚገባቸው ሁለት አገላለጻች ከህግ አስከባሪ ባለስልጣናት ግዴታ አንፃር ምን ማለት እንደሆነ በሚገባ ማጤን አስፈላጊ ነው ማሰቃየት ማለት ከራሱ ወይም ከሌላ ሶስተኛ ወገን መረጃ ለማግኘት ወይም ፈፅሟል የተባለውን ጥፋት ወይም ድርጊት እንዲናዘዝ ለማድረግ በአንድ ሰው ላይ ሆነ ብሎ የአካል ወይም የአእምሮ ስቃይ የሚያደርስ ድርጊት መፈፀም ራሱ ወይም ሌላ ሶስተኛ ወገን ለፈፀመው ወይም ፈፅሟል ተብሉ ለተጠረጠረው ድርጊት በማስፈራራት ወይም በማስገደድ በመንግስት ባለስልጣን ወይም የመንግስት ስልጣን ይዞ በሚሰራ ሰው ወይም በርሱ አነሳሽነት ስምምነት ወይም አውቆ እንዳላወቀ በመምሰል በሚፈፀም ማንኛውም የማሰቃየት ድርጊት ነው ጭካኔ የተሞላበት ሰብአዊነት የጎደለው ወይም ሰብአዊ ክብርን የሚያወርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የሚለው ሀረግ በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ የተለየ ትርጉም የተሰጠው ባይሆንም በስልጣን ያላአግባብ በመጠቀም በአካል ወይም በአዕምሮ ላይ የሚፈፀሙትን ጭካኔ የተሞላባቸውን ሰብአዓዊነት የጎደላቸውን ወይም ሰብአዊ ክብርን የሚያዋርዱ ድርጊቶች ሁሉ በተቻለ መጠን ለመከላከል እንዲያስችል ተደርጎ ነው ሊተረጎም የሚገባው ከዚህ ጋር ተያያዞ ግንዛቤ ሊወሰድበት የሚገባው ሌላው ቁምነገር በህግ አግባብ ወይም በፍርድ ቤቶች ውሳኔ ላይ ተመስርቶ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ በአስረኞች ላይ የሚፈፀመው የቅጣት እርምጃ አይጨምርም ህግ አስከባሪ ባለስልጣናት በቁጥጥራቸው ስር የሚገኙ ሰዎች ጤንነት መጠበቁንና ተገቢውን እንክብካቤ ማግኘታቸውን ያረጋግጣሉ በሚያስፈልግበት ጊዜ ሁሉ ወዲያውኑ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ያደርጋሉ የህግ አስከባሪዎች አስረኞች ወይም በህግ ቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች የህክምና አገልግሎት በጠየቁና ባስፈለጋቸው ጊዜ እንዲያገኙ እአአ በሴኘቴምበር ዐ ዓም በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ውሣኔ ቁጥር ተላልፎ በአባል ሀገራት የተፈረመው ማሰቃየትንና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸው ሰብዓዊነት የጐደላቸውና አዋራጅ የሆኑ አያያዞችንና ቅጣቶችን ለማስቀረት የተደረገውን ስምምነት አንቀጽ በዝርዝር እንዲመለከቱ ተጋብዘዋል በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ውሣኔ ቁጥር እአአ ዲሴመበር ዓም የፀደቀውን የሕግ አስከባሪ አካላት የስነምግባር መመሪያ አንቀጽ ን ይመልከቱ ማድረግ አለባቸው ከዚህም አልፈው የአስረኞች ጤንነት እንዲጠበቅ ተገቢውን አርምጃ ሁሉ መውሰድ ይገባቸዋል የህግ አስከባሪ ባለስለጣናት ከሙስና ነፃ ሊሆኑ ይገባል እንደዚህ አይነቱን ድርጊት በጥብቅ መቃወምና መዋጋት ይኖርባቸዋል የህግ አስከባሪዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነትና የህዝብ አደራ ከፍተኛ በመሆኑና ህግን ለማስፈፀምም ከየትኛውም የመንግስት አካል ይልቅ በዕለት ተፅለት ተግባራቸው ምክንያት ልዩ ቅርበት ስላላቸው ከሙስናና አድሎአዊ አሰራር መራቅ አለባቸው ይህንን የማያደርጉ እንደሆነ በህግ ልዕልና ላይ ዜጎች ፅኑ እምነት እንዳይኖራቸው ስለሚያደርግ የህግ ተገዢነትን በእጅጉ ይጎዳል ለስርዓት አልበኝነትም በር ሊከፍት ይችላል እንዲሁም መንግስታት በራሳቸው ባለስልጣናት በመዋቅራቸው ውስጥ ሊያከብሩት ያልቻሉትን ህግ ዜጎች አእንዲያከብሩላቸው መጠበቅ ስለሚገባቸው ህጉ ሙስና በሚፈፅሙ የህግ አስከባሪዎች ላይም በአኩል ደረጃ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል በሌላ አነጋገር ሙስና የህግ አስከባሪ ባለስልጣናት ካለባቸው የሙያ ግዴታና ከፍተኛ ኃላፊነት ጋር ስለማይጣጣም የህግ አስከባሪዎች ከሙስና አና አድሉሎአዊ አሰራር ነፃ መሆን አለባቸው ዝኒ ከማሁ አንቀጽ ዋቢ ጽሁፎች ክር። ዐፎሼ ሆእ ዐ ር ኋ ርበክ የ የተባበሩት መንግስታት የህግ ሙያተኞች ሚና መሰረታዊ መርሆዎች የፌዴራል ነጋሪትጋዜጣ ኛ አመት ቁጥር የፌዴራል ፍቤቶች የጠበቆች የስነምግባር ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የስነምግባር ስልጠና ማንዋልግንቦት አዲስ አበባ ፈስጸኮ የሙያ ስነምግባር ምንነት ያልታተመ የስነምግባር ማሻሻያ ንኡስ ፕሮግራም ሰነድ ቅጽ አባሪዎች አባሪ የፌዴራል ዳኞችን በተመለከተ አግባብነት ያላቸው ድንጋጌዎች አዋጅ ቁ አንቀጽ የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ዳኞች የሚመሩበትን የስነምግባር ደንብ ያወጣል አንቀጽ ለዳኝነት ለመመረጥ የሚያበቁ ሁኔታዎች ለህገመንግስቱ ታማኝ የሆነ በህግ ትምህርት የሰለጠነ ወይም በቂ እውቀት ያለው በታታሪነቱ በፍትሀዊነቱና በስነምግባሩ መልካም ስም ያተረፈ በዳኝነት ሙያ ለመስራት ፈቃደኛ የሆነ እና አድሜው ከ አመት ያላነሰ አንቀጽ ማንኛውም ሰው በመንግስት ህግ አውጪ ወይም አስፈጻሚ ውስጥ ወይም በማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት በአባልነት በሚያገለግልበት ጊዜ አጣምሮ የዳኝነት ስራ ሊሰራ አይችልም አንቀጽ ቃለ መሀላ ዳኞች ስራ ከመጀመራቸው በፊት የሚከተለውን ቃለ መሀላ ይፈጽማሉ እኔ በዛሬው አለት ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆን ተሸሜ ስራዬን ስጀምር የተጣለብኝን ከፍተኛ ሀላፊነት በታማኝነት ለመፈጸም ቃል እገባለሁ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ የዳኞች ከችሎት መነሳት አንድ የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛ ከዚህ ቀጥሉ ከተመለከቱት ምክንያቶች በአንዱ ከችሎት ይነሳል ሀ ዳኛው ከተከራካሪዎቹ ከአንደኛው ወገን ወይም ከጠበቃው ጋር የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ያለው እንደሆነ ለ ዳኞች ከተከራካሪዎች የአንደኛው ወገን ሞግዚት ነገረፈጅ ወይም ጠበቃ በሆነበት ጉዳይ ላይ የተነሳ ክርክር እንደሆነ ሐ ዳኛው ክርክር የተነሳበትን ጉዳይ አስቀድሞ በዳኝነት ወይም በእርቅ መንገድ ያየው ወይም የሚያውቀው ሆና የተገኘ እንደሆነ መ ዳኛው ከተከራካሪዎቹ ወገኖች ከአንደኛው ወይም ከጠበቃው ጋር በፍርድ ቤት የተያዘ ክርክር ወይም ሙግት ያለው እንደሆነ ሠ ከዚህ በላይ ከሀ እስከ መ ከተመለከቱት ምክንያቶች ውጪ ትክክለኛ ፍትህ አይሰጥም የሚያሰኝ ሌላ በቂ ምክንያት ሲኖር በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ መሰረት ዳኛው በችሎት ሊቀመጥ የማይገባው መሆኑን ሲያውቅ ከችሎት ተነስቶ ሌላ ዳኛ መተካት አለበት ጥር የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የወጣው የዳኞች ስነምግባር ደንብ አንቀጽ ህጎችን በትክክል ስራ ላይ ማዋል በሚሰጠው ፍርድ ውሳኔና ትእዛዝ ሁሉ በአገሪቱ የወጡት ህጎች በትክክል ስራ ላይ እንዲውሉ ማድረግ የዳኛ ተቀዳሚ ተግባሩ ነው በተለይም ወደነገሩ ከመግባቱ በፊት ስልጣኑ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ይገባዋል አንቀጽ የባለጉዳዮችን መብት በእኩልነት መጠበቅ ዳኛ ፍርድ ቤት የሚቀርቡለትን ተከራካሪዎች ሁሉ በእኩልነት ማየትና መብታቸውን በእኩልነት መጠበቅ አለበት ስለዚህም የቤተሰብ የሀይማኖት የብፄር የብሄረሰብ የፖለቲካ የማሕበራዊ ወይም ሌሎች ግንኙነቶቹ በዳኝነት ተግባሩ ላይ ተጽእኖ እንዲያሳድሩ መፍቀድ የለበትም አንቀጽ ትጋትና ጥረት ማሳየት ዳኛ በዳኝነት ስራው ላይ ተገቢውን ትጋትና ጥረት ማሳየት እንዲሁም ስለህግ ያለውን እውቀት ለማዳበር ዘወትር ጥረት ማድረግ አለበት አንቀጽ ቀጠሮ አለማብዛት ዳኛ የቀረበለትን ጉዳይ ሁሉ በተቻለ መፍጥነት መቁረጥ አለበት ስለዚህም በቂ ባልሆነ ምክንያት እንዲጓተት ማድረግ የለበትም አንቀጽ በአሰራሩ የፍርድ ቤቱን ክብር መጠበቅ ዳኛ በማናቸውም ጊዜ በአሰራሩና በችሎት አመራሩ የፍርድ ቤቱን ክብር መጠበቅ አለበት አንቀጽ ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ተግባብቶ መስራት ዳኛ አብረውት ከሚያስችሉት ዳኞች እና ከሌሎች የስራ ባልደረቦቹ ጋር ተግባብቶ ተባብሮና ተከባብሮ መስራት አለበት አንቀጽ በትእግስት ማዳመጥና ነገር ማስጨረስ ዳኛ በችሎት በስርአት የሚነጋገሩትን ጠበቆችና ተከራካሪዎች ሁሉ በትእግስት ማዳመጥና ለጉዳዩ አግባብ ያለው ክርክራቸውን ማስጨረስ አለበት የባለጉዳዮችን ሰብእና መብታቸውንና ክብራቸውን መጠበቅ ይኖርበታል አንቀጽ ተከራካሪዎችን መቆጣጠር ተከራካሪዎች ተገቢ ያልሆነ ጠባይ ሲያሳዩ ወይም ተገቢ ያልሆነ ድርጊት ሲፈጽሙ ወይም ሳይዘጋጁ ሲቀርቡና ያልረባ ምክንያት እየፈጠሩ ነገር እንዳይቆረጥ ለማድረግ ሲሞክሩ ዳኛው አጥፊዎችን በአግባቡ መገሰጽና ማረም አለበት አስፈላጊ ሲሆን ተገቢውን እርምጃ መውሰድ አለበት አንቀጽ ፍርድ አሰጣጥ ዳኛ የፍርድ ውሳኔ ወይም ትእዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ በስነስርአት ህጎቹ በተደነገገው መሰረት የነገሩን ጭብጥ የማስረጃውንና የክርክሩን ሁኔታ በመግለጽ አግባብ ያለውን ህግ ጠቅሶ ምክንያቱን በማብራራት መጻፍ አለበት አንቀጽ የጥፋተኝነትና የቅጣት አወሳሰን ዳኛ በወንጀል ጉዳይ የጥፋተኝነት ውሳኔ በሚጥበት ጊዜ ተከሳሹ በተከሰሰበት አንቀጽ ፈጸመ የተባለውን የወንጀል ድርጊት ድርጊቱን ለመፈጸም የቀረበውን ማስረጃና የተከሳሹን መከላከያ በብርቱ ጥንቃቄ መመዘን አለበት ዳኛ የቅጣት ውሳኔ በሚሰጥበት ጊዜ ቅጣቱን በዘፈቀደ ሳይሆን ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመበትን ሁኔታ ስለቅጣት አላማዎችና አወሳሰን እንዲሁም ስለቅጣት ማክበድና ማቅለል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ የተደነገጉት መርሆዎች በጥንቃቄ በመመዘን ለተከሳሹ ጥፋት ተገቢ የሆነውን ቅጣት መወሰን አለበት አንቀጽ በሀሳብ የመለየት ሁኔታ ዳኛ በሀሳብ መለየት መብቱ ቢሆንም የተፋጠነ ፍትህ ለመስጠት እንዲያስችል የልዩነት ሀሳቡን ያለመዘግየት ማስቀመጥ አለበት በሃሳብ ተለይቶ በሚጽፈውም አስተያየት ስለጉዳዩ ከመተቸት አልፎ የስራ ጓደኞቹን የሌሎች ግለሰቦችንም ሆነ የህብረተሰብ ክፍሎችን ስሜትም ሆነ ክብር ያለአግባብ የሚነካ አስተያየት መሰንዘር የለበትም አንቀጽ የችሎት ሰራተኞችን የስራ አፈጻጸም መቆጣጠር የችሎት ሰራተኞችን ስነስርአት እንዳያዓጓድሉ በስራቸው ላይ ቸልተኝነት አንዳያሳዩ ወይም ስራቸውን ለግል ፍላጎት መጠቀሚያ እንዳያውሉ ዳኛው መቆጣጠርና ተገቢውን ምክርና ተግሳጽ መስጠት ይገባዋል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ህጋዊ አርምጃ እንዲወሰድ ማድረግ አለበት ዳኛ የዳኝነቱን ተግባር በሚያከናውንበት ጊዜ ከንቱ ውዳሴን ሳይሻ በስሜትም ሳይመራ ያላንዳች ፍርሀትና ስጋት በህግ መስራት አለበት አንቀጽ የፍርድ ቤት ሰራተኞችን ስነምግባር መቆጣጠር ዳኛ በፍርድ ቤቱ ሰራተኞቹና በራሱ መካከል መናናቅን የሚፈጥሩ ግንኙነቶችን ከመመስረት መታቀብ አለበት እንዲሁም ሰራተኞቹ የፍርድ ቤቱን ክብር እንዲጠብቁና ለባለጉዳዮች ለምስክሮችና ለተገቢ ጉዳይ ወይም አላማ ወደፍርድ ቤቱ ለሚመጡ ሰዎች ሁሉ ትህትና እንዲያሳዩ ማድረግ ይጠበቅበታል አንቀጽ የስራ ሰአትን ማክበር ዳኛ የስራ ሰአትን በማክበር ለሌሎች አርአያ መሆን ስለሚገባው በቂ ምክንያት ሳይኖረው ወይም ፍቃድ ሳይቀበል ከስራ ገበታው መለየት የለበትም አንቀጽ በውሳኔ ያላለቁ ጉዳዮችን ምስጢራዊ ጠባይ መጠበቅ ዳኛ በቀረበለት ጉዳይ ላይ ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት አብረውት ከሚያስችሉት ዳኞች በስተቀር በዝርዝር ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሌላ ሰው ጋር በግል መወያየት ወይም በማናቸውም መገናኛ ብዙሀን መግለጫ ወይም አስተያየት መስጠት የለበትም አንቀጽ ከችሎት ስለመነሳት ዳኛ አንድን ጉዳይ እንዳያይ በህግ የተከለከለ ከሆነ ጉዳዩን ማየት የማይገባው መሆኑን እንዳወቀ መቃወሚያ እስኪቀርብበት ድረስ ሳይጠብቅ ምክንያቱን በሚገባ ገልጾ ከችሎት መነሳት አለበት ዳኛ ያለበቂ ምክንያት የቀረበለትን ጉዳይ አላይም ማለት የለበትም አንቀጽ መደለያ አለመቀበል ለዳኝነት በቀረበ ወይም በሚቀርብ ወይም ለዳኝነት ቀርቦ በተወሰነ ጉዳይ ምክንያት ዳኛ ጉቦ መደለያ ስጦታ ወይም ሌላ ጥቅም በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ ከባለጉዳይ ወይም ከሌላ ማንኛውም ሰው ላይ መቀበል የለበትም አንቀጽ በአማላጅ አለመስራት ዳኛ በአማላጅ መስራት ወይም አራሱ አማላጅ ሆኖ መቅረብ የለበትም አንቀጽ ስልጣንን ለግል ጥቅም አለማዋል ዳኛ የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ስልጣኑንና ክብሩን መሳሪያ ማድረግ የለበትም አንቀጽ የዳኝነትን ስራ ከግል ጥቅም ጋር አለማጋጨት ዳኛ ከዳኝነት ተግባር ክብሩ ጋር የሚጋጭ ወይም የሚቃረን ስራ መስራት አይገባውም አባሪ የአቃቤ ህግ የስነምግባር መርሆዎችን በተመለከተ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር የፌዴራል አቃቤያነ ህግ መተዳደሪያ ደንብ ላይ የተወሰዱ አግባብነት ያላቸው ድንጋጌዎች አንቀጽ ማንኛውም አቃቤ ህግ ሆኖ የሚሾም ሀ በዜግነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ ለ ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገመንግስት ታማኝ የሆነ ሐ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ በህግ ወይም በዲፕሉም የተመረቀ መ በታታሪነቱ በታማኝነቱ በፍትሀዊነቱና በስነምግባሩ መልካም ስም ያተረፈ እና ሠ አድሜው አመት ወይም ከዚያ በላይ የሆነ ስለአቃቤ ህግ ተጠሪነት አቃቤያነ ህግ ተጠሪነታቸው ለሚኒስትሩ ይሆናል በቢህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ በማንኛውም ደረጃ የሚገኝ አቃቤ ህግ ከእርሱ ለሚቀጥለው የበላይ ሀላፊ አቃቤ ህግ ተጠሪ ይሆናል አንቀጽ ቃለመሀላ እፄ ለሀገሬ ታማኝ በመሆን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገመንግስትንና ሌሎች ህጎችን ላከብርና ላስከበር በፌዴራሉ መንግስት የወጡና ወደፊት የሚወጡ ህጎችን በማስፈጸም የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ልሰራ የስራ ድርሻዬን ህግ በሚደነግገው መሰረት በመፈጸም የሰዎችን ክብርና ሰብአዊ መብት ላከብርና ላስጠብቅ የግል ጥቅም ሳልፈልግ ማንንም በመውደድ በመጥላት ወይም በሌላ በማንኛውም ምክንያት አድልዎ ሳላደርግ ማንኛውንም አይነት ተጽእኖ ሳልፈራ በፃቀኝነት በቅንነትና በትጋት ሀላፊነቴን ለመወጣት ቃል አገባለሁ አንቀጽ ከመደበኛ የስራ ሰአት በላይ መስራት ስራው የሚመለከተው የበላይ ሀላፊ በአዘዘ ጊዜ ማንኛውም አቃቤ ህግ ከመደበኛው የስራ ሰአት በላይ መስራት ግዴታው ነው ስለአቃቤያነ ህግ ግዴታ አንቀጽ ስለታማኝነት ማንኛውም አቃቤ ህግ መላ ጉልበቱንና ችሎታውን በታማኝነት ለመንግስትና ለህዝብ አገልግሎት ጥቅም ማዋል አለበት አንቀጽ ስለእያንዳንዱ አቃቤ ህግ ጠባይ ማንኛውም አቃቤ ህግ የህዝብን አክብሮትና አምነት እንዲያገኝ በመስሪያ ቤቱም ሆነ ከመስሪያ ቤቱ ውጭ በማናቸውም ጊዜ መልካም ጠባይና ስነምግባር እንዲኖረው ያስፈልጋል በማንኛውም ጊዜ የሙያውን ክብር ለማስጠበቅ የሚያስፈልገውን ሁሉ አሟልቶ መገኘት አለበት አንቀጽ ስለታዛዥነት ማንኛውም አቃቤ ህግ ስራውን ባለው ከፍተኛ አውቀትና ችሎታ መፈጸም አለበት የተመደበበትን መደበኛ ስራና ሌላውንም ተመሳሳይ ስራ መፈጸም ግዴታው ነው አቃቤ ህጉ ከበላይ ሀላፊው የሚሰጠው ትእዛዝ በግልጽ ከህግ ውጭ ካልሆነ በቀር አእንደትእአዛዙ መፈጸም አለበት በማንኛውም አኳእቷን የበላይ አቃቤ ህግ ለሚሰጠው ትእዛዝ ህጋዊነት ሀላፊ ነው አንቀጽ አቃቤ ህግ ከህዝብ ጋር ስላለው ግንኙነት አቃቤ ህግ የሚፈጽማቸው ተግባሮች በጠቅላለው የመላውን ህዝብ ጥቅም የሚመለከቱ መሆናቸውን ምን ጊዜም መዘንጋት የለበትም አቃቤ ህግ የሰዎችን ሰብአዊ መብትና ክብር መንካት የለበትም አንቀጽ ምስጢር ስለመጠበቅ ማንኛውም አቃቤ ህግ መረጃው ተራ ወይም በህዝብ ዘንድ የታወቀ ካልሆነ ወይም መደበኛ ስራውን በህጋዊ መንገድ ለመፈጸም አስፈላጊ ካልሆነ በቀር በስራው አጋጣሚ ወይም ምክንያት ወይም በሌላ አኳቷን ያገኘውን መረጃ ለማናቸውም ሰው መግለጽ የለበትም ስልጣን ባለው ሀላፊ በአግባቡ ካልታዘዘ በቀር በአሰራር ምስጢር የተባሉትን መረጃዎች ቃለጉባኤዎች የስራ እቅዶችና እነዚህን የመሳሰሉ ምስጢራዊ ጉዳዮች ሁሉ በስራው ላይ ሆነ ከስራ ውጪ ጉዳዩን አንዲያውቀው በደንቡ ለተፈቀደደለት ሰው ካልሆነ በቀር ለሌላ ማናቸውም ሰው መግለጽ የለበትም አንቀጽ ገንዘብ ስለመበደር አዘውትሮ ገንዘብ መበደር ክልክል ነው አቃቤ ህግ በስራው ምክንያት ከሚያጋጥመው ማናቸውም ሰው ገንዘብ መበደር ወይም ለመበደር መሞከር ፍጹም ክልክል ነው አንቀጽ ስለስጦታዎች ማንኛውም አቃቤ ህግ ከስራወ ጋር በተያያዘ ሁጌታ ስለሰጠው ወይም ወደፊት ስለሚሰጠው አገልግሎት ከማናቸውም ሰው ማናቸውም አይነት ስጦታ ወይም ዋጋ መጠየቅ ወይም መቀበል የለበትም አንቀጽ በመንግስት ስራና በግል ጉዳዮች ወይም ጥቅሞች መካከል ስለሚፈጠር ግጭት ማናቸውም አቃቤ ህግ የራሱ የዘመዶቹ ወይም የወዳጆቹ የግል ጉዳይ ወይም ጥቅም ከስራው ወይም በስራወ ምክንያት ከያዘው የህዝብ ወይም የግለሰብ ጉዳይ ጋር የሚጋጭ ሆኖ ሲገኝ ይህንነ ችግር ለበላይ ሀላፊው ወዲያውኑ በማሳወቅ ጉዳዩ በሌላ አቃቤ ህግ እንዲታይ ማመልከት አለበት ጉዳዩ የቀረበለት የበላይ አቃቤ ህግም አስፈላጊ የመሰለውን ውሳኔ መስጠት አለበት አንቀጽ ስለግል ደብዳቤዎች አቃቤያነ ህግ በመስሪያ ቤቱ አድራሻ የግል ደብዳቤ ሊጽፉ ወይም ከሌላ ሊጻፍላቸው ይትችላለ ስለዚህ ጉዳይ የሚያስፈልገውን የመላላክ ወጪ ጉዳዩ የሚመለከተው አቃቤ ህግ መክፈል አለበት በመስሪያ ቤቱ አድራሻ የተላከ የማንኛውም አቃቤ ህግ ደብዳቤ ጥቅል ወይም አቃ ቢጠፋ መስሪያ ቤቱ በሀላፊነት አይጠየቅም አንቀጽ በመስሪያ ቤቱ መገልገያዎች ስለመጠቀም አቃቤያነ ህግ ስራቸውን በሚገባ ለመፈጸም ያህል ብቻ በመስሪያቤቱ ልዩ ልዩ መገልገያዎች መጠቀም ይትላሉ አንቀጽ ለሌሎች መስሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ስለመስራት ማንኛውም አቃቤ ህግ ሀ በመደበኛ የስራ ሰአት መላ ጉልበቱን ችሎታውንና አሳቡን በደመወዝ በተመደበበት የመስሪያ ቤቱ ስራ ላይ ማዋል አለበት ሆኖም አቃቤ ህጉ በአግባቡ ሲታዘዝ ለሌላ መንግስት መስሪያ ቤት ወይም የመንግስት ልማት ድርጅት መስራት አለበት ለ ለመስሪያ ቤቱ የሚያበረክተውን አገልግሎት የሚያጓድል ወይም ለተሰጠው ስራና ሀላፊነት ተቃራኒ የሆነ ወይም ከስራውና ከሀላፊነቱ ወይም ከሙያ ስነምግባር ጋር የማይጣጣም ማናቸውንም የውጭ ስራ ሊሰራ አይችልም በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም አቃቤ ህግ የውጭ ስራ ለመስራት በቅድሚያ የሚኒስትሩን ፈቃድ ማግኘት አለበት አንቀጽ የዲሲፕሊን ጥፋቶች የሚከተሉት ከባድ የዲሲፕሊን ጥፋቶች ናቸው ሀ ጉቦ መቀበል ወይም እንዲሰጠው መጠየቅ ለ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራስ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ በአማላጅ መስራት ሐ ራስን ወይም ሶስተኛ ወገንን ለመጥቀም በጽሁፍ የሰፈረውን መረጃ ሆነ ብሎ ወደሀሰተኝነት መለወጥ መ ከስራ ጋር ግንኙነት ካላቸው ሰዎች ገንዘብ መበደር ሠ አግባብ ያለውን መረጃ ወይም ፍሬነገር ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ለሚመለከተው ባለማሳወቅ ወይም በመደቡት ውሳኔውን የሚያዛባ ሁኔታ መፍጠር ረ ያለበቂ ምክንያት ስራን በማዘግየት ባለጉዳይን ማጉላላት ሰ አአምሮን በሚያደነዝዝ ወይም ሱስ በሚያሲዝ ህገወጥ አጽ መጠቀም ሸ ሰክሮ በስራ ላይ መገኘት ወይም በአደባባይ በመታየት የሙያውን ስነምግባርና የመስሪያ ቤቱን ክብር ማጉደፍ ቀ ያለበቂ ምክንያት ወይም ያለፈቃድ አዘውትሮ ከስራ መቅረት በ በስራ ቦታ ላይ ለሞራልና ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈጸም ቸ ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት በመስሪያ ቤቱ ንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረስ ኅ ሌሎች በተመሳሳይ ደረጃ የሚታዩ ከባድ ጥፋቶች ነ በጽሁፍ ወይም በቃል ከመስሪያ ቤቱ ወይም ከበላይ ሀላፊው የተሰጠውን ግልጽና ህጋዊ ትአዛዝ አለመቀበል ወይም ተግባራዊ አለማድረግ የሚከተሉት ቀላል የዲሲፕሊን ጥፋቶች ናቸው ሀ በስራው ላይ ተገቢ ጥረትና ትጋት አለማሳየት ለ ከስራ ባልደረቦች ጋር በመግባባት ተባብሮ መስራት ባለመቻል በስራ ሂደት ላይ እንቅፋት መሆን ወይም ሐ አዘውትሮ መበደር መ ሌሎች በተመሳሳይ ደረጃ የሚታዩ ቀላል ጥፋቶችን መፈጸም።