Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ቃ ፋ ቁ ጸሐፊዉ ከእግዚአብሔር ባሪያ አንዱ በኢሜል ሐምሌ ዓም የሚሰራጭ የ የጨስማዉ ገዝ ስገስጋዩ የዘኑትገ ካድረዎች ስባስ በሚያደርጉ መገፈሳዊ ማኅበራት ሳይ የከገዚስብሔርንገ መስከክት ስገቀበፅም ባስ ሰዎች ሳይ ጋብቻቸዉን በስሕዛብ ሥርዓት በሚፈጽመት ሳይ ነፍስ ክዎጋ ክተስየች በኋሳ ምኘም ስታዉቅም ክሞት በኋላ ሕደወት የስም ዋጋ መቀበስና መክፈስ የሰም ብሰዉ በሚሟያምነት ሳደ ባጠቃሳይ በቁስስካሳዉያኘ ሳይ በምገ መስኩ ከገዳሳገጠባቸዉና ከገዚስብሔር ደገሞ ከከርሱ የሆነዉን ከዉነት ከንደናዉቅ ያደረገዉኀ የሟገፀበጽ «የጨለማዉ ገዥ ዉዶቼን ካድሬዎችን እናንተም አየመለመላችሁ አባልና ደጋፊ በማድረግ የምታሳምጹብኝ ሰዎች ወዮላችሁ። ምን እናወራለን። የገቢ ምንጫችን ስለሆነ እንዴት ከዚህ ታላቅ ተግባር እንለያለን። » በማለት አፋቸዉን አዘጉ እኔም ከጎናችሁ ቆሜ ጥብቅና እቆምላችኃለሁ እናንተ ከበላችሁ ከጠጣችሁ ከተዝናናችሁ ከጨፈራችሁ ከዘፈናችሁ ከሰከራችሁ እንደፈለጋችሁ ከሆናችሁ ሌላዉ ቢራብ ቢጠማ ቢታረዝ ቢያዝን መከራና ችግር ቢደርስበት ምን ቸገራችሁ።
» በማለት በትሕትና ከመጀመሪያዉ እስከ መጨረሻዉ ድረስ በተረጋጋ መንፈስ ዉስጥ ሆነን እናንበዉ አንብቡት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ግልጽ ካልሆነላችሁ ደግሞ በጸሎት አምላካችሁን በመጠየቅ ደጋግማችሁ አንብቡት ከዚያም ዲያብሎስ አድርጉ» የሚላችሁንና ደስ የሚሰኝበትን አታድርጉ እርሱ የማይፈልገዉንና የሚጠላዉን ደግሞ አድርጉ ጸሐፊዉ የራሱ ስራና ፈጠራ ስላልሆነ እንደ ማንኛዉ ሰዉ ጽሑፉን ያነባል በሚያስለቅሰዉ ቦታ ላይም ያለቅሳል በሚያሳዝነዉ ቦታ ላይም ያዝናል በሚያስቆጨዉ ቦታ ላይም ይቆጫል በታላቅ ተስፋዉ ደግሞ እጅግ ይጽናናል ማንነቱንም በደንብ አዉቆ እንደማንነቱና እንደተራነቱ ራሱን በአምላኩና በፈጣሪዉ ፊት ዝቅ አድርጎ ይኖራል በእዉነትና በመንፈስ አምላኩን ያመልካል የተለያዩ አዉቀቶችንም ከመጽሐፉ አግኝቷል ሌላዉ ጸሐፊዉ የራሱን ሆነ የእያንዳንዱን ሰዉ ያደፈና የጎደፈ ባሕርይ አንዲሁም ጎሰቋላ ኑሮና ሕይወት በደንብ ስላስተዋለ እያንዳንዱን ሰዉ የሚመለከተዉ እግዚአብሔር እንዲያይበት በሰጠዉ ዐይን ነዉ እንጂ ማንም እንዲታይበት በሚፈልገዉ መልኩ አይደለም ለሰዉ ዐይን ሲታዩ ለዐይን የማይገቡ ምስኪኖች የሆኑ እዉነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋዮችን ግን የመመልከቱ አቅምና ብቃት የሌለዉ ስለሆነ አነሱ እንዲመለከቱት የሚመኝ ሰዉ ነዉ ከዚህ በተጨማሪ ማንንም ሰዉ በቀለሙ በነገዱ በዘሩ በቋንቋዉ በሃይማኖቱ ምክንያት የማይጠላና ልዩነት የማያደርግ «ሁሉም ሰዉ የአዳም ዘር ነዉ አባቴ እናቴ ወንድሜ እህቴ ልጄ ናቸዉ ብሎ የሚያምን ነዉ እያንዳንዱ ሰዉ ለእግዚብሔር መንግሥት የታጨ ነዉ እንደ እግዚአብሔር ቃል ሆኖ ከተገኘ እንደ ምርጫዉ ሕያዉ ሆኖ እንደ ቅዱሳን መላእክት በገነትና በሰማያት ዉስጥ ይኖራል በተቃራኒዉ ደግሞ የዲያብሎስን ፈቃድ ነዉ የምፈጽመዉ ካለ እንደ ምርጫዉ በሲኦልና በገፃነመ እሳት ዉስጥ ይኖራል ብሎ በእምነት ብቻ ሳይሆን በእርግጠኝነት ያምናል ስለዚህ እያንዳንዱ ሰዉ ተስፋዉን ሰማያዊ አድርጎ እዉነትን ሳይሸራርፍ ሙሉ በሙሉ ተቀብሎ አንድነቱንና ኅብረቱን ከአምላኩ ጋር ብቻ እድርጎ እንዲኖር ጸሐፊዉ የሚቀበለዉና የሚሰማዉ ሰዉ ካለ ራሱን ዝቅ አድርጎና ተንበርክኮ ትዉልዱን ይለምናል «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር መግቢያ አግዚአብሔር ላለፉት ዘመናት መልእክቶቹን በተለያየ መንገድ ያደረሰ ሲሆን በዚኛዉ መልእክት ደግሞ ከዚህ በፊት ባልተሞከረበት መልክ ነዉ ያቀረበዉ ይኸዉም ትዉልዱ ከአግዚአብሔር የሆነዉን ከመስማትና ከመፈጸም ይልቅ በጨለማዉ ገዥና መንፈስ የሚመሩትን ሰዎች የሚሰማና የሚሉትንም ስለሚፈጽም «እስቲ ትዉልዱ በሚሰማዉና በሚፈጽመዉ መልክ የጨለማዉ ገዥና በእርሱ መንፈስ የሚመሩ ሰዎች የሚሰሩትን የሚናገሩትን የሚያስቡትን በሚገባቸዉ ቋንቋ ይቅረብላቸዉና «በግልጽ ዲያብሎስ ይሻለናል የሚናገረዉንና የሚመክረዉን ተግባራዊ እናደርጋለን አንጂ እግዚአብሔር የሚደሰትበትንና የሚፈቅደዉን አንፈጽምም» ካሉ ደግሞ የባሰዉን ዋጋ ይከፍሉበታል በተቃራኒዉ ደግሞ አኔን አግዚአብሔርን የሚሉ ከሆነ ደግሞ ዲያብሎስ የሚመክረዉንና የሚደግፈዉን አይፈጽሙ ይልቁኑ አርሱ ከሚለዉ በተቃራኒ በመሰለፍ እኔን ደስ በሚያሰኝ ሕይወት ይመላለሱ» በማለት ነዉ በዚህ መልኩ መልእክቱ ለትዉልዱ እንዲደርስ ያደረገዉ በክፍል አንድ የጨለማዉ ገዥ አንዳች እንዳይቀባጥር በእሳት ሰንሰለት ተጠፍሮ «አናንተ የአዳምና ሔዋን ዘሮች» እያለ ተግባሩን ንግግሩን አስተሳሰቡንና ምክሩን ያቀርባል «አናንተ አስመሳዮች ለእኔ ደግሞ ምርጦች» አያለ ይናገራል እንዲሁም አናንተ ምርጦቼ እንደራሴዎቼ መሪዎች ባለሟሎቼ ባለሥልጣናት ዉዶቼ ካድሬዎች» እያለ ያለዉን እዉነታ ዘክዝኮ ይናገራል ከነዚህ በተጨማሪ በእርሱ መንፈስ በበላይ መሪነትና በሸዋጅ መንፈስነቱ ስንቶቹን እዉነተኛ የሚመስሉ ነገር ግን የአርሱ አገልጋዮች መሆናቸዉን ይመሰክርባቸዋል በዘጠኝ ምዕራፍ የተከፋፈለ ነዉ በክፍል ሁለት ደግሞ ያልታሰቡትና ያልተገመቱት ሰዎች ከእዉነተኛዉ የሕይወት መንገድ ወስጥ ካሉት ሰዎች ይልቅ ተመርጠዉ ከእዉነተኛዉ ከአግዚአብሔር አገልጋይ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ልዩ ዉይይት በተለየ ስፍራ አዉነትን የጠየቁ ሰዎች ስለእአዉነት ምን እንደተባሉ እንዲሁም ከተለያየ ጉዳዮች ጋር የተያያዙና የተከደነዉ የተገለጸላቸዉ የተሰወረዉ እንዲያዉቁት የተደረገበትን ያሳየናል በሰባት ምዕራፍ የተከፋፈለ ነዉ ክፍል ሦስት የተለያዩ መሪዎችና ባለሥልጣናት እንዲሁም የእግዚአብሔር ልዩ ባለሟሎችና መልእክተኞች ያደረጉት ታሪካዊ ንግግርና ከፓለቲካ ጋር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በተያያዘ ብዙ ጉዳዮች ቀርበዉበታል እንዲሁም የተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮችንና የጨለማዉ ገዥ ለሮድ ዘመን ያጠናቸዉ ጥናቶች ተገዶ እንዲገልጽ የተደረገዉ ቀርቦበታል በዘጠኝ ምዕራፍ የተከፋፈለ ነዉ ክፍል አራት ደግሞ የጨለማዉ ገዥ በክፍል አንድ አድበስብሷቸዉና በዝርዝር ያልገለጻቸዉ ጉዳዮችንና አዉነታዎችን ለመግለጽ ባይፈልግም በእሳት ሰንሰለት ተጠፍሮ እየተቀጣ ሁሉንም ጉዳዮች በግልጽ ለአዳም ዘሮች ገልጂል በአስራ አንድ ምዕራፍ የተከፋፈለ ነዉ ስለዚህ የተከበራችሁ የአዳምና ሔዋን ዘሮች እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ ምድራዊዉም ሰማያዊዉም ምሥጢር ግልጽ ባለ መልኩ እንዲቀርብ ያደረገ ስለሆነ ከመጀመሪያዉ እስከ መጨረሻዉ በትዕግሥት በቅንነት አንብበን እግዚአብሔር በሚፈቅደዉ ሕይወት እንመላለስ ገበናችን የተጋለጠብን ሰዎች ደግሞ ፈጥነን አዉነተኛ ንስሐ አንግባ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሊያደርግ ያሰበዉን ከማድረግ ወደ ኋላ የማይመለስና ማንም ፍጡር ዕቅዱንና ሓሳቡን ሊያስቀር ሆነ ሊያዘገይ ስለማይችል ባለችዉ አጭር ጊዜያት እጃችንን ለእግዚአብሔርና ለአዉነተኛ እንደራሴዎቹ ሰተን ፈቃዱን ብቻ ለመፈጸምና ለማስፈጸም መሰለፍ ይኖርብናል እንጂ ከሚጠረጉትና ከምድር ከሚጸዱት የዓመፃ ልጆች ጋር አንዳች አንድነትና ኅብረት ፈጥረን በእግዚአብሔር እዉነታ ላይ ልንቃወምና እግዚአብሔርን ልንገዳደር አይገባም እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ በዚህ መጽሐፍ ዉስጥ የተናገረዉ ቃል አንዷ እንኳ አትቀርም አሁንም አየተፈጸመ ነዉ ለወደፊትም በባሰ ሁኔታ ይፈጸማል ስለዚህ እንክርዳድ ያልተደባለቀበትን ከንቱ ሥጋዉ መጠበብ የማይታይበተን የሥጋና የደም ስሜት የልተጨመረበትን ባጠቃላይ ለሥጋችንም ለነፍሳችንም በሚጠቅመን እዉነት ስር ሆነን እንመላለስ እንኑር አግዚአብሔር ከመጭዉ የጥፋትና የጠረጋ ቁጣዉ ጠብቆን አዉነት ለምትነግሥበት ለመልካሙ ዘመን ለኢትጵዮጵያ ትንሣኤ ያድርሰን ይላል የእግዚአብሔርን መልእክት አምጪዉ ታናሹ ልጃችሁና ወንድማችሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ለኢትዮጵያዉያንና ለዓለም ሕዝብ የተገለጸ የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር። እናንተ ለመሰበክም ለምስጋናም ለትምህርትም ለጸሎትም ወረተኞች ሆናችሁ እንደ ሥጋና ደም ስሜታችሁ የምትንቀሳቀሱ ለእኔ ምቹ ለስላሳ መሬት የሆናችሁልኝ ሰዎች በዚህ ወረተኛነታችሁ አስከ መጨረሻዉ እንድትጸኑ በጨለማዉ ስሜ እመክራችኋለሁ ታዲያ አንዳንድ ለእኔ የማይመቹኝ ራሳቸዉን የሚገዙና በስሜት የማይመላለሱ ሰዎች የሚሉትን አትስሙ ይኸዉም « የእግዚአብሔር ቃል ሁሌም አዲስ ነዉ ሌት ተቀን ሰይጣን እንደሚፈታተናችሁና እንደሚያዳክማችሁ ሁሉ እናንተም ሁል ጊዜ በአግዚአብሔር ቃል ልትታደሱና ልትጠነክሩ ይገባል ኃይልን የምትጎናጸፉት በአግዚአብሔር ቃልና ጸሉሎት ነዉ አንደ ዓለማዊ ሕይወት ለጊዜ ማሳለፊያና መደበሪያ የምትተቀሙበት አይደለም ካለ እግዚአብሔር ቃልና ካለ ጸሎት በመብላትና በመጠጣት ብቻ የምትመላለሱ ከሆነ እንኳን ለነፍሳችሁ አይደለም ለሥጋችሁም ኃይል አታገኙም በማለት የሚያስተምሩትንና የሚናገሩትን አንዳች እንዳትሰሙ የሚሏችሁን እንዳትፈጽመ እነሱ የጨለማ ግዛቴን አሰራር ያልገባቸዉና በኅሊናችሁ ሰልጥቼኝ እናንተ «ድብርት ዱካክ ጭንቀት» እያላችሁ ብትሰይሙኝም የማዳከምና የማስጨነቅ ስሜቶችን በመፍጠር እንደማልከሰክሳችሁ አንደማስረክሳችሁእንደማስከፋችሁ እንደማማርራችሁ ባጠቃላይ ፍዳና መከራ እነደማደርስባችሁ ያልተረዱ ስለሆነ ነዉ እነሱ የኅሊና ሰላማቸዉና እርካታቸዉ ቢጠበቅ ኖሮ እንደእናንተ በተረጋጋ ባልተቅበዘበዘና ወረተኛ ባልሆነ ሕይወት ይመላለሱ ነበር ነገር ግን እንደእናንተ የረካ ሰላም የሞላዉ ጽናት ያለዉ ኅሊና በማጣታቸዉ ምክንያት ይኸዉ ለእግዚአብሔር ቃል ትኩረት በመስጠጥ ሌት ተቀን በጸሎት በጾም በስግደት በምስጋና በቅን ሓሳብ በመልካም ተግባር በእዉነተኛ ሕይወት ፍዳዬን እያሳዩኝ ያሰቃዩኛል ያቃጥሉኛል ያበሳጩኛል ያነዱኛል ስለዚህ ከንደነዚህ ካሉት የእኔን አንድነትና ኅብረት ከማይፈልጉት «ኅሊናቸዉን በቀላሉ አልሸጥም አልቦዝንም ወረተኛ አልሆንም አረክስም አልልከሰከስም አልከፋም አልጨክንም» ከሚሉት ሰዎች እኔን ካስቸገሩ ለእናንተም ወደ ኋላ ከማይሉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ራሳችሁን አግላችሁ በሥጋና በደም ስሜታችሁ ብቻ እንደፈለጋችሁ ብትኖሩ የሚሻላችሁ መሆኑን ደግሜ ደጋግሜ በጨለማዉ ስሜ አመክራችኋለሆ እናንተ በዚህ ምድር ቆይታችሁ ዉስጥ ራሳችንን ማወቅ ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ የሰራነዉን የተናገርነዉንና ያሰብነዉን የኃጢአት ተግባር ንግግርና ሓሳብ እኛ ከረሳናቸዉ እግዚአብሔር አያስታዉሳቸዉም» ብላችሁ የምታምኑና ነፍሳችን ከሥጋ ከተለየች በኋላ ምንም የምታዉቀዉ የምትረዳዉ የምታስተዉለዉ ነገር የለም የምትሉ ሊቀምሁራን ለዚህ ታላቅ አስተሳሰባችሁና እዉቀታችሁ በጨለማዉ ስሜ አደንቃችኋለሁ ታዲያ አንዳንድ አዉቀት የሌላቸዉ አላዋቂ ሰዎች ነፍስ ካወቅን ጀምሮ የሰራነዉ የተናገርነዉ ያሰብነዉ ሳይቀር አግዚአብሔር በባሕርይዉ መዝገብ ላይ ልክ በኮምፒተር የምንመዘግባቸዉ የተለያዩ መረጃዎች ተመዝግበዉ እንደሚቀመጡ ሁሉ ተመዝግቦ ይቀመጣል ልክ በኮምፒተር የተመዘገ እንዲጠፋ እስካልተደረገ ድረስ ማንኛዉንም መረጃዳታ መዝግቦ እስከመጨረሻዉ እንደሚቆይና እንዲጠፋ ዲሌት ካልተደረገ በስተቀር እንደማይጠፋ ሁሉ በእግዚአብሔር የባሕርይ መዝገብ ላይ የተመዘገበዉ ኃጢአት በእዉነተኛ ንስሐ እንዲደመሰስ ወይን እንዲጠፋ ካልተደረገ በስተቀር ነፍስ ከሥጋ ስትለይ የተረሱት ሆነ ያልተረሱት የኃጢአት ተግባር ንግግር ሓሳብ ጭምር ነፍሳችን በምትገለጽበት ረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ሆና እያስታወሰች እስከ መጨረሻዉ ፍርድ ቀን ሁሉ ትዝ እያላት በሲኦል ዉስጥ ትጨነቃለች ትሰቃያለ «ምን ዓይነት የመጨረሻ ፍርድ ነዉ የሚጠብቀኝ እያለች ታወጣለች ታወርዳለች በዚህም ምክንያት ካለዕረፍት አንቅልፍ በዚያ የለምና እጅግ ትጨነቃለች በተቃራኒዉ ደግሞ እዉነተኛ ንስሐ ገብተዉ ስለ ኃጢአት ተግባራቸዉና ንግግራቸዉ ሓሳባቸዉ ጭምር ተጸጽተዉ የኢየሱስ ክርስቶስን መለኮት የተዋሓደዉን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደሙን የተቀበሉ የሚያስታዉሱትም የማያስታዉሱትም ኃጢአት ሁሉ ከእግዚአብሔር ባሕርይ መዝገብ ላይ ስለሚደመሰስ ነናስ ከሥጋቸዉ ስትለይ ልክ በሕጻንነት ዕድሜያችን የምንፈጽመዉ ተግባርና ንግግር ትዝ እንደማይለን ሁሉ አንዳች ትዝ የሚላቸዉ ኃጢአት የለም ንጹህ ኅሊና ብቻ ይዘዉ በገነት ዉስጥ በመግባት በሰማያዊ መላእክት አኗኗን ይኖራሉ እንጂ በምድራዊ ሕይወታቸዉ በሥጋ በመገለጻቸዉ ምክንያት የሚያጋጥማቸዉ ያደፈና የጎደፈ ባሕርይ የሆኑት ዓይነ ምድር ሽንት ላበት ንፍጥ አክታ የመሳሰሉትና የጎሰቆለ ባሕርይ የሆኑት ድካም ማንቀላፋት ማዘን ማልቀስ መተከዝ መናደድ መበሳጨት መታመም መቸገር መዉጣት መዉረድ ምድራዊ መብልና መጠጣት መብላት መጠጣት በጨለማና በብርሃነን በሙቀትና በቅዝቃዜ በተፈራረቀ ሕይወት መኖር ከሌለበት ከሙቀት ከቅዝቃዜ ከዝናም ለመከላከል ቤት መጠለያ መስራት በማያስፈልግበት ሰዎች በራሳቸዉ ጊዜ የፈጠሩት ጉስቁልና ሕይወትና ጠባይ የሆኑት ጥል ጦርነት ግድያ ስርቆት ዝሙት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አመንዝራነት ዘፈን ዳንኪራ ዘረኝነት ጎጠኝነት ባዕድና ጣዖት አምልኮ ጥንቆላ መተት አስማት ሟርት ክፋት ተንኮል ቅናት ምቀኝነት ጥል ቂም በቀል አድማ መከፋፈል መለያየት ስስት ራስ ወዳድነት ስግብግብነት ወዘተ የመሳሰሉት ከማይታዩበትና ከማይታሰቡበት ባጠቃላይ አዳምና ሔዋን በገነት ኑሮ ዉስጥ አያሉ «እግዚአብሔር አትብሉ» ብሎ ያዘዛቸዉን ትዕዛዝ ተላልፈዉ የዲያብሎስን የክፋትና ተንኮል ምክር ሰምተዉ በራሳቸዉ ምኞትና ፍላጎት ተገፋፍተዉ በድፍረት ከምሳሌያዊ ባሕርይ የተፈጠረችዉን ፍሬ በመብላታቸዉ ምክንያት የተገለጹበት ረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ወደ አለመኖር አልፎ ይህ ግዙፉ ሥጋ መብላትና መጠጣት የግድ የሚያስፈልገዉ አካል በምድር ዉስጥ የሚያስፈልጉት የሚታዩና የማይታዩ ፍጥረቶች የሆኑት ፀሐይ አየር ጨረቃ ከዋክብት እንስሳት ፅፀዋት አእዋፋት መሬት ዉኃ ወዘተ የመሳሰሉት ተዘጋጅቶለት በመጨረሻዉ ቀን በዕለተ ዓርብ ከአፈር ከመሬት ተበጅቶ አማናዊዋ ፍጥረት በገነት የነበረችዉ ነፍስ እንድትዋሓደዉ ተደርጎ በመፈጠሩና በዚህ ምድር ዉስጥ ነፍሳት የሚጠሩበት የሚነጥሩበት የሚቀጡበት ሆኖ በመዘጋጀቱ ምክንያት ላደፈና ለተጎሳቆለ ባሕርይ እንዲሁም ለጎስቋላ ኑሮና ሕይወት በመዳረጉ ምክንያት የተከሰቱት ባሕርያትና ሕይወት ጠባይ የማይከሰትበትን ሕይወትና ኑሮ ይኖራሉ ፈተናና መከራ ካለባት ከጎስቋላ ምድር መመጣታቸዉን እንጂ አንዳች የምድራዊ የኃጢአት ተግባራቸዉ ንግግራቸዉ ሓሳባቸዉ ትዝ የማይላቸዉ የጉስቁልናና የፈተና ኑሮዋቸዉ የነበረዉ አንዳች ስሜት የማይሰጣቸዉ ይሆናል በቅድስናና በደስታ ሕይወት ብቻ ይኖራሉ ለአዳም ዘር ወገኖቻቸዉ ደግሞ ያስባሉ ይጸልያሉ ስለዚህ እደነዚህ ጻድቃን እድል እንዲያጋጥመን ሕይወታችንን በንስሐና በቅዱስ ቁርባን በመምራት ልንመላለስ ይገባል» በማለት የሚያስተምሩትንና የሚናገሩትን ተረት ተረት አንዳች እንዳትሰሙ እንዳትቀበሉ እንኳን ፍጡሮቹን ሰዎች አይደለም እግዚአብሔር ተገልጦ ቢያስተምራችሁ ቢናገራችሁ ወይንም እኔ የጨለማዉ ገዥ ሳት ብሎኝ በጸሎቱና በጸበሉ ተቃጥዬና ታስሬ ብለፈልፍ እንኳ አኛ እግዚአብሔርንም ሰይጣናትንንም አናዉቅም እኛ የተገኘነዉ ከተፈጥሮ ከጦጣ መሰል እንስሳ በቀስ በቀስ እድገትና ለዉጥ በኢኮልሽን አማካይነት ነዉ ከቁስ አካል የተገኘን ስለሆነ በቅርቡ ተፈጥሮን በቁጥጥራችን ዉስጥ አዉለን እንደፈለግነዉ እንሆናለን የሐሳብያዉያን ከንቱ እምነት ምን እንደሆነ እድሜ ለማርክስ ለኤንግልስ ለሌኒን ለቻርልስ ዳርዊንናና ለተለያዩ ፈላስፋዎች አዉቀናል በማለት ለማንኛዉም ሰዉ ምላሽ ሰታችሁ አፋቸዉን አዘ። እንላለን በንግግራችሁና በድርጊታችሁ ሁል ጊዜ እንታዘባችኋለን ይኸዉም ከራሳችሁ ሆነ ካለፉት ሰዎች ዕጣ ፈንታ መማር ተስኗችሁ ቀደም ያሉት የፈጸሙትን ግፍ ጭከና በደል አድሎ ተንኮል ደባ ብቻ ምኑ ተነግሮ ያልቃል እናንተም ትደግማላችሁ እነሱ የዘሩትን ፍሬ መራራም ቢሆን ሳይፈልጉት ጠጥተዉት ማለፋቸዉን እያወቃችሁ ነግ በኔ » ሳትሉና «አኛም የዘራነዉን እናጭዳለን መራራም ከሆነ መራራዉን ነዉ የምንጠጣዉ ብላችሁ መልካም ፍሬ ከማፍራት ይልቅ ለክህደት ለዓመጻ ለርኩሰት ለጭካኔ ተግባር ታጥቃችሁ ትሰለፋላችሁ አምላካችሁንም ዕለት ዕለት ታስቆጣላችሁ ታዲያ እንዲህ ስላችሁ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑሩ በቅንነትና በእዉነት ሕዝቡን ምሩ አገልግሉ ተስፋችሁን ሰማያዊ አድርጋችሁ በሰማያዊ ሥርዓት ተመላለሱ በሥጋችሁም በነፍሳችሁም የምትጠቀሙበትን ተግባር ፈጽሙ «የዘራነዉን አናጭዳለን ብላችሁ ፍሩ «ለሰራነዉ ግፍና በደል ዋጋ እንከፍልበታለን ብላችሁ ስጉ «መልካም ከሰራን በሥጋችንም በነፍሳችንም ዋጋ እናገኝበታለን ብላችሁ አስቡ ስላለፈዉ ኃጢአታችሁ ንስሐ ግቡ ከዚህ በኋላ ወደ ልባችሁ ተመልሳችሁ እግዚአብሔር በሚደሰትበት ሕይወት ተመላለሱ» ለማለት ፈልጌ እንዳልሆነ በተለይ እንደራሴዎቼ መሪዎችና ባለሟሎቹ ባለስልጣናት እንዲሁም ዉዶቼ ካድሬዎች በደንብ ታዉቃላችሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በመሆኑም ከላይ የዘረዘርኩትን መልካም ተግባራት ከፈጸማችሁ እነዚያ የቀደሙት እንደወደቁት አይወድቁ አወዳደቅ ነዉ የምትወድቁትና የታላላቅ መሪዎችና ባለሥልጣናት ፅጣ ፈንታ ነዉ የሚደርስባችሁ ስለዚህ ሕዝቡን በኃይልና በጭከና ንድታስተዳድሩ ራሳችሁን ብ በለጸጋችሁ ሕዝቡን እንድታደኸዩ በክፋት በተንኮል በዓመጻና በክህደት በርኩሰት በጭከና በበደል በግፍ በጭቆና በዘረኝነትና በጎጠኝነት ሕይወታችሁ እሰከመጨረሻዉ እንድትጸኑ ነዉ የጨለማዉ ምክሬ ባጠቃላይ አኔን በሚያስደስት እግዚአብሔርን በሚያስቆጣ ተግባርና ንግግር ላይ እንድትተጉ በመጨረሻም የእኔን ጨለማ ግዛት መንግሥቴን እንድትወርሱ ነዉ ፍላጎቴና ምኛቴ የዚህ ምፅራፍ ማጠቃለያዬ ከሕፃንነታሁ ጀምርሮ ነፍስ ከሥጋችሁ እስከምትለይ እናንተ ከዓለም ዉጣ ዉረድ ከእኔ ፈተና የምትገላገሉበትን ያ የምትፈሩት ሞት እስኪመጣባችሁ ድረስ የምፈታተናችሁ የማጎሳቁላችሁ መሆኑን በዚህ ምድር ቆይታችሁ ሌት ተቀን የእኔን የጨለማዉ ገዥ ፈቃድ ለመፈጸም ለማስፈጸም የምትተጉ በዚህም ድርጊታችሁ ሲኦልና ገዛነመ እሳትን እንደምትወርሱ በምድርም የስራችሁን እንደምታገኙና ዋጋም እንደምትከፍሉበት ባጠቃላይ ጎስቋላ ኑሮና ሕይወታችሁን እንድታዉቁ እንድታስተዉሉ በግልጽ ያስቀመጥኩላችሁ ከንቱነታችሁን አስተዉላችሁ ራሳችሁን በአግዚአብሔር ፊት አዋርዳችሁና ዝቅ አድርጋችሁ እንድትኖሩ ለሰዉ ልጆችም ቅን እንድታስቡ መልካም አንድትሰሩ በበደል ዉስጥ ያላችሁትም ንስሐ ገብታችሁ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋና ደም ተቀብላችሁ ለሰማያዊ መንግሥት እንድትበቁ ፈልጌ ሳይሆን የልባችሁን ደንዳናነት አዉቃለሁና እንኳን የእኔን የፍጡሩን ለዚያዉም የጨለማዉ ገዥ የዲያብሎስን ቃልና ንግግር ሰምታችሁ መቀበልና መለወጥ ቀርቶ ፈጣሪ አምላካችሁ በሥጋ ተገልጾ የተለያየ ፈዉስና ተአምራት በማድረግ በትህትና ያስተማራችሁን የተናገራችሁን ሕያዉ ቃል ተቀብላችሁ ተግባራዊ አላደረጋችሁም ይልቁኑ ሰደባችሁት አዋረዳችሁት ወነጀላችሁት ተፋችሁበት ገረፋችሁት አንገላታችሁት ተሳለቃችሁበት ዘበታችሁበት አዳፋችሁት ሰቀላችሁት በመስቀል ላይ ሆኖ «ተጠማሁ» ቢላችሁ አንኳ ሳትራሩለትና ሳታዝኑለት መራራ ሐሞትን አቀረባችሁለት ባጠቃላይ እንኳን ለመጋቢያችሁና ለአጠጫችሁ እግዚአብሔር ቀርቶ ለእኔ ለጠላታችሁ ዲያብሎስ መደረግ የሌለበትን ድርጊት ፈጸማችሁ ሁለት ሺህ ዘመን አልፎ እንኳ እስካሁን ድረስ አላመናችሁበትም እንደ ቃሉ ሆናችሁ አልተገኛችሁም ከሃዲዎችና አስመሳዮች ናችሁ ታዲያ እንዲህ ስላችሁ እመኑበት ትዕዛዙንና ሕጉን በመጠበቅ እንደ ቃሉ ሆናችሁ ተገኙ በአዉነትና በመንፈስ አምልኩት ማለቴ ሳይሆን ማንነታችሁንና ድርጊታችሁን እወቁ እኔ ከአናንተ በመቶ አጥፍ ስለምሻል ለእፄ ፍርዱ ይቀልልኛል በአናንተ ላይ ፍርዱ እጅግ ይብሳል ስለዚህ ፍርዱን እንዳቀልልላችሁ ሌት ተቀን እኔን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የጨለማዉን ገዥ ዲያብሎስን በደንብ አምልኩኝ ፈቃዴን ለመፈጸምና ለማስፈጸም ትጉ የስራችሁን ዋጋ አሰጣችኋለሁ መንግሥቴንም አወርሳችኋለሁ ለማለት ፈልጌ መሆኑን እናንተ የአዳም ዘሮች በደንብ ታዉቃላችሁ ብዬ ነዉ ባጠቃላይ የእኔን ጨካኝነት የአምላካችሁን ፍቅርና ትዕግስት በደንብ የዘረዘርኩላችሁ እኔን ጨካኙና ክፉዉን የግብር አባታችሁን እንድትጠሉ እዉነተኛ አባታችሁን አግዚአብሔርን እንድትወዱና ፈቃዱን አናንተም ፈጽማችሁ ሌላዉንም በማስፈጸም መንግሥቱን እንድትወርሱ ፈልጌ ሳይሆን እኛ ሰይጣናት እንደ እናንተ አምላክ ተገልጦልን «ይህን አታድርጉ ይህን ካደረጋችሁ ይቅር እላችኋለሁ ወደ መጀመሪያዉ መኖሪያችሁ መንግሥተ ሰማያት አስገባችኋለሁ» ብሎ አስተምሮንና ተስፋ ሰቶን ቢሆን ኖሮ እንኳን በዓመጻና በክህደት መመላለስ ቀርቶ ምድራዊ ዘመናችንን በመቸገርና በኀዘን በእንባ ብናሳልፍ ምርጫችን ነዉ ነገር ግን ለእናንተ የተሰጠ እድል ለእኛ አልተሰጠም ለዚህም ነዉ በዓመጻችንና በክህደታችን የጸናነዉና እናንተንም ከአምላካችሁ ጋር በማጣላትና በማስቆጣት ተግባርና ሓሳብ ላይ እንድትሰለፉ ሌት ተቀን የምንፈታተናችሁና ለዓይን ቅጽበት እንኳ የማንለያችሁ እናንተንም በተግባራችሁና በንግግራችሁ ብቻ አይደለም ሓሳባችሁን የምንከታተልና እንደ ዉሎዋችሁና አዳራችሁ በተለያየ ፈተና ለመጣል የምንተጋዉ እናንተ ግን እንኳን ስለእዉነት ራሳችሁን ክዳችሁ በእዉነት በመኖር የተለያዩ ፈተናዎችን መታገሥና ስለነገረ መስቀሉ ማንባት ቀርቶ የምትበሉትን የምትጠጡትን ሳያጎልባችሁና የመዳኛን መንገድ አቅልሎላችሁ «ሥጋዬን ከበላችሁ ደሜን ከጠጣችሁ ሕያዉ ሆናችሁ በመንግሥቴ ትኖራላችሁ ምንም ከማይጠቅማችሁ ከክፋት ከተንኮል ከምቀኝነት ከቅናት ከትዕቢት ከዓመጻ ከክህደት ከጥንቆላ ከመተት ከአስማት ከድግምት ከተለያዩ ባፅድና ከጣዖት አምልኮ ከግድያ ከስርቆት ከበደል ከግፍ ከዝሙት ከአመንዝረኛነት ከዘረኝነት ከጎጠኝነት ከዘፋኝነት ከዳንኪራ ከሚርት ከቂም በቀል ከጥላቻና ከጥል ባጠቃላይ ከሚያረክሱና ከሚጎዳችሁ ተግባር ተለዩ ቅን አስቡ መልካም ስሩ ከዘልማድ ሕይወት ወታችሁ በእዉነትና በመንፈስ አምልኩኝ ያለዉን የሚጠቅማችሁን ትዕዛዝ «አንፈጽምም» ብላችሁ ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን በሚያስቆጣ እኔን ዲያብሎስን በሚያስደስት ተግባርና ድርጊት ላይ ተሰማርታችሁ ትዉላላችሁ ታድራላችሁ ታዲያ እንዲህ ስላችሁ እኔን አታስደስቱ አግዚእሔርንም አታስቀጡ ለማለት ፈልጌ ሳይሆን «ምርጫ እናዉቃለን በትክክለኛዉ መንገዳችንም እንጓዛለን አዋቂዎች ምሁር ነን » ብላችሁ ራሳችሁን ስለምታመጻድቁ ምርጫችሁና መንገዳችሁ ምን እንደሚመስል እንድታዉቁትና የእኔ መንገድ ተመራጭ ያደረጋችሁ የአዋቂዎች አዋቂ መሆናችሁን ልመሰክርባችሁ ነዉ በመጨረሻ የእኔ የጨለማ ገዥ ወዳጅና ባሪያ የሆነ ሰዉ የምጠይቀዉ ሴት ተቀን ለመፈታተንና ለማጥቃት ስቀርባቸዉ እንደ ኳስ አእያነጠሩኝ የሚመልሱኝ ያስቸገሩኝን በዓለት ላይ የታነጹ በቅን ሓሳብ በመልካም ተግባር በእዉነተኛ አምልኮ ዉስጥ ሆነዉ በጸሉት በጾም በስግደት የሚያቃጥሉኝና ጉዳት ላደርስባቸዉ ያልቻልኩትን እንደ ግድግዳ የሆኑብኝን ሰዎች ከእኔ ግዛት ትለዩልኝ ዘንድ ነዉ በዚህ ድርጊታችሁም የምትመኙትንና ሌት ተቀን የምትጋደሉለትን ጨለማዉ ግዛቴን ሲኦልን በኋላም የጋራ መንግሥታችንን ታላቁን መንግሥተ ገዛነመ እሳትን አወርሰዋለሁ » ይላል ሓሳቹና ጨካኙ የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ ከነሠራዊቱ ሰይጣናት ጭምር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምዕራፍ « አናንተ የአዳም ዘሮች የመጀመሪያ የገነት አኗኗራችሁን ባለማየታችሁ ፅድለኞች ናችሁ ይኸዉም እንደ ቅዱሳን መላእክት በረቂቂ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ የተገለጻችሁበትን እንደዚህ ምድራዊ ኑሮ መብላት መጠጣት የሌለበትን በመብላታችሁ በመጠጣታችሁ ምክንያት የተከሰተባችሁ ያደፈና የጎደፈ ባሕርይ የሆኑት ዓይነምድር ሽንት ላበት መሽተት የሌለባችሁን ለመኖር ስትሉ መዉጣትና መዉረድ የሌለባችሁን ዝናብ ፀሐይ ሙቀት ቅዝቀዜ ለመከላከል መጠለያ የማያስፈልጋችሁና የማይፈራረቁባችሁን ስራችሁ የነበረዉ አንደ ቅዱሳን መላእክት ለፈጣሪያችሁ ምስጋና ማቅረብ ብቻ መሆኑን በዚያም እዉነተኛ ደስታንና እርካታን የምታገኙ እንደነበረ የዚህ ምድራዊ ኑሮ አኗኗር ሥርዓት አለመኖሩን ብርፃንና ጨለማ እንደ ማይፈራረቅባሁችሁ ሁሌ በማይጠፋ በእዉነተኛ ምሳሌያዊ ብርፃን ዉስጥ ትኖሩ የነበረዉን ቀን ከሌሊት በእኔ የማትፈተነበትን ሕይወት ሁል ጊዜ በሰላም በደስታ በእርካታና በቅድስና ሕይወት ብቻ መኖሩን እንዲሁም ጎስቋላ ባሕርይ የሆኑት ማልቀስ ማማጥ መዳህ ማዘን መቸገር መተከዝ መራብ መጠማት መታመም መሞት የመሳሰሉት እንደማይከሰትባችሁ በራስ ተነሳሽነትና ፈቃደኛነት የተፈጠሩ የማይገቡ ባሕርያትና ጠባይ የሆኑት መለያየት መጠላላት መበቃቀል መከፋፈል አድሎ በደል ግፍ ጭከና ጭቆና ግድያ ጦርነት ልዩነት ክፋት ተንኮል ምቀኝነት ቅናት ጣዖትና ባዕድ አምላኮት ክህደት ዓመጻ ዝሙት አመንዘረኛነት ዘረኝነት ጎጠኝነት ዘፋኝነት ዳንኪርተኛነት የተለያዩ ርኩሰት ተግባር የመሳሰሉት የማይታዩበትን ባጠቃላይ ያደፈ የጎደፈ የጎሰቆለ ባሕርያት እንደሌሉባችሁ አዉቃችሁና አስተዉላችሁ ቢሆን ኖሮ እንኳን እርስ በአርስ መገዳደል መጨካከን መከፋፋት ራስ ወዳድነት ስግብግብነት አድሎ በደል ዓመጻና ክህደት የተለያዩ የርኩሰት ተግባርን መፈጸም ቀርቶ በኅሊናችሁ አታስቡትም ነበር አንዲት ቀን በዚህች ምድር ዉስጥ መኖርን አትመርጡም ነበር ለክፋትና ለተንኮል ተግባር አትሰለፉም ነበር በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት ዉስጥ አትኖሩም ነበር ባጠቃላይ ተስፋችሁን ሰማያዊ በማድረግ እግዚአብሔርን በመፍራት ትኖሩ ነበር አንዳንድ ቀን ወደ ልቤ ስመለስ የእግዚአብሔርን ፍርድ አደንቃለዉ ይኸዉም « እነዚህ የአዳም ዘሮች ይህ ሁሉ ያደፈ የጎደፈ የጎሰቆለ ባሕርያትን ተላብሰዉ እደዚህ በከፋና በከረፋ የዓመጽ የክህደትና ርኩሰት ተግባርና ሕይወት ይመላለሳሉ እርስ በእርስ ይገዳደላለሁይመቀኛኛሉ ይጣላሉይከፋፈላሉ ይለያያሉፎ ሌት ተቀን አምላካቸዉን በሚያስቆጣ ተግባርና ንግግር ላይ ይሰማራሉ ስለዚህ በዚህች ምድር ዉስጥ በዚህ ጎስቋላ ኑሮና ሕይወት መኖራቸዉ ሲያንሳቸዉ ነዉ እኛ ሰይጣናት እንኳ እርስ በእርስ አንጣላ አንገዳደል አንከፋፈል በአንድነትና በኅብረት ሆነን የአዳም ዘርን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር መፈታተንና ማጎሳቆል ነዉ ተግባራችን በእኛ ሰንድ ተስፋ መቁረጥና ስንፍና የለም እስከመጨረሻዉ ነፍስ ከሥጋችሁ አስከመትለይ ድረስ በትጋትና በቆራጥነት የአዳም ዘርን ከመፈታተንና ከማጎሳቆል ወደ ኋላ አንልም በእኛ ዘንድ እርስ በእርስ ምቀኝነት ተንኮል ቅናት መጠላለፍ የለም በአንድ ዓላማ በአዳም ዘር ላይ ዘመቻ ማድረግ ነዉ ሌት ተቀን እቅዳችንና ተግባራችን አግዚአብሔር ግን በአዳምና ሔዋን በዓመጻቸዉ መጸጸትና እንዲሁም እናንተ ልጆቻቸዉ ባላወቃችሁትና ባልፈጸማችሁት ዓመጻ ምክንያት በቅን ሓሳብና በመልካም ተግባር እንዲሁም በእዉነትና በመንፈስ በምትፈጽሙት እዉነተኛ አምልኮ አማካይነት ዳግም ወደ ገነትና ከፍርድ ቀን በኋላ ደግሞ ወደ መንግሥተ ሰማያት የመግባት እድል ሰጣችሁ እናንተ ደግሞ ከአዳምና ሔዋን ብሳችሁ አንድ ትዕዛዝ መሻርና መጣስ አይደለም አንዱን ቀላል ትዕዛዝ መፈጸም ያልቻላችሁ የዓመጸኞች ዋና ዓመጸኛ ናችሁ የከፃድያንም ዋና ከፃዲ ናችሁ ምክንያቱም እኔ ዓመጸኛና ከፃዲ የተባልኩት ዲያብሎስ እንኳ የእናንተ የአዳም ዘር ያህል በእግዚአብሔር ላይ የሚያስቆጣ ተግባር አልፈጸምኩም አልፈጽምም እኛ ሰይጣናት እንደ እናንተ ዳግም ወደ መንግሥተ ሰማያት ወደ መጀመሪያ መኖሪያችን የመመለስ ዕድል ቢሰጠን ኖሮ ሌት ተቀን አግዚአብሔር ደስ በሚሰኝበት ተግባርና ሓሳብ ዉስጥ በተመላለስን ነበር። ታድያ እንዲህ ስላችሁ የእግዚአብሔርን ፍርድ እንድትፈሩና እዉነትን እንድትቀበሉ ከአዉነት ጋር እንድትሰለፉ ለማሳሰብ ሳይሆን የእግዚአብሔር ፍርድ ጥብቅ መሆኑን እንድታዉቁና ተስፋ ቆርጣችሁ እንደእኔና ሠራዊቶቼ ሰይጣናት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በዓመጻና በክህደት ተግባራችሁና ንግግራችሁ እንድትጸኑ በመንግሥቴም አንደምራራላችሁ ለመግለጽ ያህል ነዉ ሌላዉ ቢሰማችሁም ባይሰማችሁም አንድ እዉነት እነግራችኋለሁ ይኸዉም እኔ ዲያብሎስ የሰይጣናት አለቃና ሠራዊቴ ሰይጣናት በእምነት ደረጃ ከእናንተ የሰዉ ሰሮች ከዘጠና እጅ ፐርሰንት በላይ ከሆናችሁት በመቶ አጥፍ እንበልጣችኋለን በዚህም ፍርዱ ለእኛ ይቀላል ምክንያቱም አኛ በአግዚአብሔር ላይ ብናምጽም ህልዉናዉን መኖሩን አልካዳንም ከዚያም በላይ ሰዉ ሆኖ ከአመቤታችሁ ከንግሥታችሁ ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆኖ ፍጹም ሰዉ ፍጹም አምላክ ሆኖ በዚህ ምድር ለሠላሳ ሶስት ዘመን ኖሮ የተለያየ መከራ ተቀብሎ ተሰቅሉሎ ሞቶ መነሳቱን እናዉቃለን እናምናለን ለእኛ ግን ምናችንም ስላልሆነ ብናዉቅም ብናምንም አንዳች የንስሐ ሆነ መልካም ተግባር ምልክት አላሳየንም አናሳይምም እናንተ ግን እጅግ ብዙዎቻችሁ የእግዚአብሔርን ህልዉና የማትቀበሉ በቁስ አካል የምታምኑ በቀስ በቀስ እድገትና ለዉጥ በኢኮልሽን አማካይነት ከጦጣ መሰል እንስሳ ወደ ሰዉ ተለወጥን የምትሉ አሳፋሪና ከእብደት ያልተለየ ኅሊና የያዛችሁ ናችሁ እንዲሁም እምነት አለን» የምትሉት ደግሞ በተለያዩ አማልክት የምታምኑና የማታዉቁትን አምላክ የምታመልኩ የኢየሱስ ክርስቶስን አግዚአብሔርነትና ፈጣሪነት የካዳችሁና ያልተቀበላችሁ ናችዉ ከዚህ በተጨማሪም በእግዚአብሔርነቱ ያመናችሁትም በስሙ ትነግዱበታላችሁ እንጂ እንደ ቃሉ የማትኖሩ ትዕዛዙንና ሕጉን የማትጠብቁ አስመሳዮች ምግባር የሌላችሁ ናችሁ በዚህ ብቻ የምንቀጣበት ቦታ ገዛነመ እሳት ቢሆንም የቅጣቱ ደረጃ ለእኛ እንደሚቀልልን እንተማመናለን ይኸዉም እኛ በዓመጻችንና በክህደታችን ብንጸናም እንደእናንተ የመዳን እድል ስለሌለን ነዉ እንዲሁም ምግባር ባይኖረንም የእግዚአብሔርን ህልዉናና ፈጣሪነት አልካድንም «ኢየሱስ ክርስቶስም እግዚአብሔር አምላክ ፈጣሪ አይደለም» ብለን አልካድንም ነገር ግን እንዳትድኑ ምቀኞች ነንና በኅሊናችሁ «እግዚአብሔር አይደለም ፍጡር ነዉ አማላጅ ነዉ ነቢይ ነዉ ሓሳች ነዉ ለማለት ግን አልተከለከልንም የምንላችሁን መቀበል አለመቀበል ደግሞ ሙሉ ነጻነት ያላት የኅሊናችሁነፍሳችሁ ድርሻ ነዉ ታዲያ ይህን እዉነት መመስከሬ እዉነቱን እንድታዉቁና ከአዉነት ጋር እንድትሰለፉ ለመምከር ሳይሆን እናንተ ብቻ ሳትሆኑ አዉነት መስካሪ ልመስክር ካልኩ እኔም እዉነትን መናገር እንደምችል እንድታዉቁና እንደእናንተ የምታስብ ሕያዉ የሆነች ነፍስ አንዳለኝ እንድታዉቁና ራሳችሁን የተለየ አድርጋችሁ እንዳትቆጥሩ እንዲሁም ማንነታችሁን አንድታዉቁ ለማሳሰብ ያህል ብቻ ነዉ እናንተ የአዳም ዘሮች በኃጢአት መልከስከሳችሁና በዓመጻ ሕይወት መጽናታችሁ ከእኔ ታላቅ ዋጋ የሚያሰጣችሁ ቢሆን ኖሮና እናንተም አሁን እንደሚታየዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ተግባር ንግግር ስድብ ላይ መሰለፋችሁና ምሴን ብታቀርቡልኝ ብዙ አያስደንቀኝም እኔን የሚያስደንቀኝ ነገር እኔ የጨለማዉ ገዥ በሥጋችሁም እንድትጎሳቆሉ በነፍሳችሁም የዘላለም ሞት እንድታገኙ ቀን ከሌሊት የምፈታተናችሁ ዋንኛ ጠላታችሁን ለማስደሰት እጅጉን መትጋታችሁ ነዉ ይህ ነዉ በአኔ ዘንድ ሳይቀር ትዝብት ዉስጥ የጣላችሁ በሥጋችሁ ቢመቻችላችሁ ብዙ እንዳማያስጨንቀኝ ሳልገልጽላችሁ ማለፍ አልፈልግም ምክንያቱም በዚህች ምድር የተገለጻችሁበት የዚህ ቅርፊት ሥጋ ምድራዊ ክብሩንና መጨረሻዉን እኔም እናተም ጠንቅቀን እናዉቀዋለን ዋናዉ ፍላጎቴና ትግሌ ነፍሳችሁን አሳምዖ ለገሃነመ እሳት ፍርድ ማቅረብ ነዉ ለዚህ አይደል እናንተ ኢትዮጵያዉያን እንደመንግሥተ ሰማያትና እንደ ገነት የምትቆጥሯቸዉና ሌት ተቀን ወደእነሱ ለመሄድ በምኞት የምትቃጠሉባቸዉ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሬ ዉስጥ ያስገባዋቸዉን ልዩ አገሮቼን አሜሪካን አዉሮፓን ኤሽያን አብለጭልጩ የማጓጓችሁ «እኛ በሚታይና በሚዳሰስ ነገር እንጂ በምናባዊ ሓሳብ አናምንም ማቴሪያሊስት ነን በማለት ለነፍሳችሁ አንዳች ቦታ አለምስጠታችሁ የአዉቀታችሁን ምጥቀት የሚያሳይ በመሆኑ መቼም እኔም የማልታይና የማልዳሰስ በመሆኔ ከአኔ የሆነዉን ለመቀበልና ለመስማት ወደ ኋለ የምትሉ መሆኑን የኅሊናችሁን ሓሳብና ምጥቀት ስለማዉቅ ስለታላቅነታችሁ ምስክርነት ሳልሰጥ ባልፍ ኅሊናዬ ይወቅሰኛል ሌላዉ ቢቀር «አኛ የሰዉ ዘሮች ከጦጣ ከእንስሳነት በቀስ በቀስ ለዉጥና ዕድገትበኢኮሊሽንን አማካይነት ነዉ የተለያዩ ዕድገቶችን አልፈን ለአሁኑ ሰብእና የበቃነዉ» በማለት ማንነታችሁን መግለጻችሁና በትምህርት ተቋማችሁ ይህንኑ ከሕፃን እስከ አዋቂዉ ድረስ እንዲማርና በዚህ አስተሳሰብ ተስፋዉን ምድራዊ ብቻ አድርጎ እንዲኖር ተረት ተረት የሆነዉን «መንግሥተ ሰማያት ገነት ሲኦል ፈጣሪ እግዚአብሔር ሰይጣናት ወዘተ» የሚባለዉን አስተምሮ መሰረዛችሁና ማስቀረታችሁ ዋናዉ የታላቅነታችሁና የምሁርነታችሁ መገለጫ በመሆኑ በራሴዉ በጨለማዉ ስም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ እናንተ ኢትዮጵያዉን በችግርና በመከራ ዉስጥ እያላችሁ እንኳ «እግዚአብሔርን» ብላችሁ ሙጭጭ ብላችኋል ታዲያ እንደ አሜሪካን ጃፓን ቻይና ህንድአዉሮፓ ኤሽያ መካከለኛዉ ምስራቅ ወዘተ አገራት በሥጋችሁ ብትበለጽጉማ ለእኔ አንዳች ቀዳዳ አንዳማትከፍቱልኝና ርኅራጌቴ እንደማታሳዩኝ አዉቃለሁና ለዚህም ነዉ በችግር እየገባዉና በምርጥ እንደራሴዎቼ አማካይነት ከሕይወት መንገድ እያወጣሁ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት ያሰለፍኳችሁ በቅርብ ጊዜ ዉስጥ ደግሞ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሬ ዉስጥ አእንደማዉላችሁ ተገንዝባችሁ ከወዲሁ አጃችሁን ብትሰጡኝና የተሟላ አምልኮቴን ብታቀርቡልኝ የተሻለ መሆኑን በጨለማዉ ስሜ እመክራችኋለሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የእኔ ተስፋና ምኞት የእናንተን ዉድቀትና ጥፋት ማየት ነዉ ምክንያቱም እስከአሁን ለእኔ ያስቸገራችሁና እጅ አንሰጥም ብላችሁ የምትጋደሉት እናንተና አገራችሁ ኢትዮጵያ ናት ለአፄ አስቸግረዉኝ ለአናንተ ጥብቅና የሚቆሙ ከእናንተዉ ወተዉ በቅድስና ሕይወት የሚመላለሱት ብቻ ሳይሆን ሰማያዉያን ቅዱሳን መላእክት ጻድቃን ሰማዕታት ነቢያትና ሐዋርያት ጭምር በመሆኑ ነዉ አቅመቢስነቴና ልምሾነቴ እየባሰ ኃይሌ እየተዳከመ ያለዉ ከሁሉ በላይ ያማረረችኝና ፍዳዬን የምታሳየኝ ስሟ እንኳ እንዲነሳ የማልፈልገዉ ያች የምትመኩባት የአደራ እናታችሁ «ቅድስት ድንግል ማርያም» የምትባለዉ ናት ከግዛቴ ወዴት እንድሄድላት ነዉ የምትፈልገዉ። ቀደም ብሎ የሰራችሁት ኃጢአታችሁ ስለማይደመሰስ ዞሮ ዞሮ መምጫችሁ ወደ እኔ መንግሥት ስለሆነ በመንግሥቴ በገዛፃዛነመ እሳት ዉስጥ አይቀጡ አቀጣጥ ነዉ የምቀጣችሁ ስለዚህ አርፋችሁ በኃጢአት ተግባራችሁ እስከመጨረሻዉ ድረስ ጸንታችሁ በበደልና በዓመጻ ሕይወታችሁ እንድትኖሩ ታላቅ ምክሬን እመክራችኋለሁ ምናልባት አንዳንድ ሐሰተኛ መምህራን «ዳዊት እግዚአብሔርን የሚፈራ ቅን ቆራጥ ጀግና ስለነበረ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አድርጎት ንጉሥ አደረገዉ ለተወሰነ ጊዜ አምላኩን በተግባር በንግግር በሓሳብ ሳይቀር በመፍራትና ደስ በሚያሰኝ ሕይወት ዉስጥ ከኖረ በኋላ ምቾትና ድሎት ሲበዛበት ኅሊናዉ ደነደነና ያ ከበግ አረኝነት አንስቶ ለንጉሥነት የቀባዉንና ያበቃዉን አምላክ መርሳት ጀመረ አንኳን በሓሳብና በንግግሩ ሊፈራዉ ቀርቶ በተግባር የባለሟሉን ሚስት ደፈረ ታማኝ አገልጋዩንም አስገደለ ታዲያ ፍርዱ ጥብቅ የሆነዉ አምላክ ነቢዩን ናታንን ላከበት አስገሰጸዉ ለመማማሪያም ይሆን ዘንድ በተለያየ መንገድ ቀጣዉ አዋረደዉ ስለኃጢአቱ ዋጋን አስከፈለዉ ይሁንና ገር የንስሐ ልቦና ያላዉ ንጉሥ ዳዊት በበደሉና በኃጢአቱ እጅጉን አዘነ አለቀሰ አልጋዉን በእንባ አራሰ በእዉነት ተጸጸቶ አምላኩን ይቅርታ ጠየቀ ርኅራጌዉም እጅግ የበዛ ይቅርባይ አምላክም ይቅር አለዉ በቀሪ ዘመኑ ባሳየዉ የንጽህናና የቅድስና ተግባርእንደ ልቤ አለዉ የቅድስና የጻድቅነት ማዕረግ ሰጠወዉ በመሆኑም በኃጢአት የወደቃችሁ በእዉነተኛ ንስሐ ኃጢአታችሁ ከሰማያዊ መዝገብ ላይ ይደመሰስላችኋል ንስሐ በገባችሁበትና በተጸጸታችሁበት ኃጢአት ዳግም አንዳች አትጠየቁም ስለዚህ አንዳች ተስፋ ሳትቆርጡ ስላለፈዉ ዓመጻችሁና ክህደታችሁ ርኩሰት ተግባራችሁ ንስሐ ግቡ በቀሪ ሕይወታችሁም እግዚአብሔር ደስ በሚሰኝበት ኑሮ ኑሩ እንጂ «አግዚአብሔር የእኔን በደል ይቅር አይልም» የምትሉና ተስፋ የምትቆርጡ ከሆነ ዲያብሎስ ደስ ይለዋል ይህን አቋም ይፈልገዋል የእርሱ ባሪያ ሆናችሁ አርሱ በሚቀጣበት በገሃነመ አሳት ቦታ እናንተም ትቀጣላችሁ በማለት የሚያስተምሩትን ትምህርት አንዳች እንዳትቀበሉ እኔ ከአናንተ በላይ ቂመኛና ተበቃይ ስለሆንኩ ንስሐ ከገባችሁና በበደላችሁ በዓመጻችሁ ከተጸጸታችሁ ከእኔ ጋር የመጨረሻ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ጥል ነዉ የምታደርጉት እፄ ይቅር አልላችሁም እንደከዳችሁኝ እክዳችኋለሁ ለመንግሥቴም አትበቁም ይህንንም በታላቁ ጨለማዉ ስሜ አረጋግጥላችኋኃለሁ እናንተ ጸሎታችሁን በዘልማድ የምታነበንቡ በሓሳባችሁ የተለያየ ጉዳዮችና ቦታዎች ላይ የምትነጉዱ አዛኝ ሰዎች ስለርኅሩነታችሁ እያመሰገንኩ ለወደፊት ደግሞ ጸሎቱን ሙሉ በሙሉ አንድትተዉት አሳስባችኋለሁ ሙሉ በሙሉ ከተዋችሁት ለመበቀል የወሰንኩባቸዉ ሰዎች ዕድል አያጋጥማችሁም ይኸዉም እነዚህ ሌት ተቀን አንደብረምጣድ በአሳት መፃል ጥደዉኝ ኅሊናቸዉን በመሰብሰብና በተመስጦ ጸሉት አሳቱን ከመሃል እያፋፋሙ ያነደዱኝን ያቃጠሉኝን በተለመደዉ በባዶ ጉራ አንደበቴ አይቀጡ አቀጣጥ እቀጣቸዋለሁ ታዲያ እናንተም መፃል ለመፃል ባይሆንም ዳር ዳሩን እያቀጣጠላችሁ በወላፈኑ በመጠኑም ቢሆን ስለምትለበልቡኝ ሙሉ በሙሉ ጸሉታችሁን ማቆም አለባችሁ ያለበለዚያ እኔም በገዛነመ አሳት ዉስጥ አልራራላችሁም እነሱ ግን የእኔን አድል እንዳያገኙ መንገዱን ሁሉ እዘጋባቸዋለሁ ለአናንተ ግን ሰፊ መንገድን አሳያችኋለሁ የትምህርት መመሪያዉ ፖሊሲ በእኔ ቁጥጥር ዉስጥና በክህደት እምነት ዙሪያ ዉስጥ ስለሚከናወን የሥጋዊ ጥበብና አዉቀት በመገኘቱ ምንም እንኳን ሰዎች ከጉስቁልና ሕይወት መለየታቸዉ ባያስደስተኝም አንዳች ቅናት ግን የለብኝም ዋናዉ ዓላማዬ ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት እስከ ከፍተኛ ትምህርት ደረጃ ድረስ በየተቋማቱ «ሰዉ የተገኘዉ ከተፈጥሮ በቀስ በቀስ እድገትና ለዉጥበኢኮልሽን አማካይነት ከጦጣ መሰል እንስሳ ነዉ በሚለዉ የትምህርት አቅጣጫ ስለሚመራ ለእኔ ለጨለማዉ ገዥ «የተፈጥሮ ባለቤት ፈጣሪ እግዚአብሔር የለም የሚለዉ የክህደት ትምህርቴ በቂዬ ነዉ የገረመኝና የታዘብኩት ግን ሌላዉ የዓለም ሕዝብ በዚህ የክህደት ትምህርትና አስተሳሰብ ቢሄዱ ብዙም አያስገርመኝም አያስደንቀኝም ምክንያቱም ክህደቱ ከእነሱ ስለፈለቀ እኔን የገረመኝ ገና ከሕፃንነት አድሜያቸዉ በዓርባና በሰማኒያ ቀን በጥምቀት ከእግዚአብሔር ልጅነትን አግኝተዉ ማርያም ማርያም» እየተባለ ተወልደዉ ከሕፃን አስከ ምሁሩ ድረስ በዚህ በክህደት ትምህርቴ መመራታቸዉና የቅሬተ አፅም አጥኝዎችም ከዉጭ የከሃዲያን ጌቶቻቸዉን ትምህርት ተከትለዉ ለሰዉ ልጆች አድሜና ለተፈጥሮ ተረት ተረት ትምህርቴን በሚሊዮንና በቢሊዮን አድሜ እየሰጡ ነጭ ዉሸቱን ለአገራቸዉና ለዓለም ሕዝብ ማቅረባቸዉ ነዉ ምንም እንኳን የሰዉ ዝር የተገኘባት ከገነት የተሰደዱት አዳምና ሔዋን በመባል የሚታወቁት ሁለቱ ነፍሳት በዚህች ምድር የተገለጹበት ሥጋ የተበጀዉ ከዚህችዉ ኢትዮጵያ ዔደን ገነት ከተባለችዉ ምድርመሬት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ግዮን የዓባይ መነሻ አገር መሆኑን እኔ ፈጡሩ የጨለማዉ ገዥ ብቻ አይደለም መሪያቸዉ መንፈስ ቅዱስ የሆኑ ሁሉ ያዉቃሉ ታዲያ የዚህ ታሪክ ባለቤቶች የሆኑት ኢትዮጵያዉያን ዐሥር ሺህ አድሜ እንኳ የማይሞላትን ሚጢጢዋን ምድር ዓለም እንደሌሎቹ አገሮች ዓመጻና ክህደትን በመፈጸም ከእግዚአብሔር ለማስካድ በሚሊዮንና በቢሊዮን አድሜ ይሰጣሉ በየትምህርት ተቋማቱ ለትዉልዱ ያስተምራሉ በዚህም ተደፋፍረዉ ትዉልዱም «ተፈጥሮን እንቆጣጠራለን» በማለት ሌት ተቀን ይታበያሉ እዚህ ላይ የእኔ ተግባር በዓመጻና በክህደቱ እንዲሰለፉ በኅሊናቸዉ ሹክ ማለት እንጂ ማንንም አስገድጄ ወይንም በግልጽ አዝዝ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ተግባር ዉስጥ እንዲሰለፉ አላደረኩም እያንዳንዱ ሰዉ በነጻ ኅሊናዉ ተመርቶ ነዉ በተግባርም በንግግርም በሓሳብም ኃጢአት የሚፈጽመዉ እንጂ የእግዚአብሔርን ድምፅ ለይቶ መልካም መስራትና ቀና ማሰብ የእያንዳንዱ ሰዉ የራሱ ምርጫ ነዉ እንዲሁም በተፈጥሮ ባሕርይዉ መልካም መስራትና ቀና ማሰብ የራሱ ፈቃድ ነዉ በተቃራኒዉ ደግሞ ኅሊናዉሃፍሱ የእኔን የጨለማዉ ገዥ ድምፅ ሰምታ የተባለዉን ወደ ተግባርና ንግግር በመለወጥ ኃጢአት ለመስራት የራሷ ፍላጎትና ዉሳኔ ነዉ ማንም አስገድዷት ኃጢአት የሚያስፈጽም አካል ስለሌለ በእኔ ላይ አንድ ሰዉ እንዳያላክክ ስለ ድርጊቱ ዋጋ የሚቀበለዉም ወይንም በተቃራኒዉ ዋጋ የሚከፍለዉም በነጻ ኅሊናዉ ተመርቶ የሚሰራዉ ራሱ የአዳም ዘር ብቻ ነዉ እኔ የጨለማዉ ገዥ ተስፋ በመቁረጥና የመዳን ተስፋ ስለሌለኝ ነዉ ሌት ተቀን የአዳም ዘርን ለመፈታተንና ለማጎሳቆል እንዲሁም መከራና ስቃይ ለማድረስ የምተጋዉና ርካታም የማገኘዉ ይህ አቅዴና ምኞቴ ሲሳካልኝ ብቻ ነዉ የእናንተ የአዳም ዘር ለኃጢአት ተግባር መነሳሳት ግን ግራ ገብቶኛል ምናልባት ለአኔ አዝናችሁልኝ «ዲያብሎስ ከነሠራዊቱ ሰይጣናት ጋር ብቻቸዉን ለምን ገዛነመ አሳት ዉስጥ ይኖራሉ። ነገር ግን በዚሁ አቋማችሁ እስከመጨረሻዉ እንድትጸኑ አስጠነቅቃችኋለሁ ከእግዚአብሔር የታዘዛችሁትና የተማራችሁት ግን ስለ እዉነትና ስለ አግዚአብሔር መንግሥት እንኳን እኔን በዓይናችሁ የማታዩኝን የጨለማ ገዥን ቀርቶ በዓይናችሁ የምታያቸዉን ምድራዊ ሰዎች ነገሥታቱን ፕሬዘዳንቶቹን ጠቅላይ ሜኒስትሮችን ባለሥልጣናቱን የጦር አዛገዝፐቹን የተለያዩ ኃላፊዎችን ወዘተ ሳትፈሩና ኅሊናችሁን ሳትሸጡ ስለ እዉነት እንድትመሰክሩና በእዉነትም እንድትኖሩ ነበር እንኳን «ለዘሬ ለጎጤ ለዘመዴለቤተሰቤለወላጆቼ ለልጆቼ ወዘተ» በማለት ኅሊናችሁን መሸጥና በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት መመላለስ ቀርቶ የራሳችሁን ማንነት እንኳ ንቃችሁና ክዳችሁ አዉነተኛ አገልጋይና አማኝ መሆን ይጠበቅባችሁ ነበር እናንተ ግን እንኳን በአዉነትና በመንፈስ እግዚአብሔርን ማመንና ማገልገል እንዲሁም በመልካም ተግባርና በቅን አሳብ ተመላልሳችሁ ተስፋችሁን ገነትና መንግሥተ ሰማያትን አድርጋችሁ መኖር አይደልም የሚጎዳችሁን የኃጢአት ተግባር ለመፈጸምና እኔን ጠላታችሁን ዲያብሎስን ደስ በሚለኝ ሕይወት ለመኖር የምትተጉ ናችሁ የሚያሳዝነዉ ግን እናንተ አንደምትወዱኝ እኔ አልወዳችሁም ለዚህም ነዉ በምትሰሩት ኃጢአት ምላሼ ደስታን እርካታን ሰላምን ከመስጠት ይልቅ ኅሊናችሁ ደስታንና እርካታን እንዲሁም ሰላም እንዳያገኝ አድርጌ ተስፋቢስ ሕይወት እንድትኖሩ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የተቅበዘበዛችሁ እንድትሆኑና ባዶነት እንዲሰማችሁ የማደርገዉ ከዚህ በተጨማሪም በተለያየ በሸታ እንድትያዙ በማድረግ የተለያየ ችግርና መከራ በማምጣት ተቃራኒ መልስ ነዉ የምሰጣችሁ በመጨረሻም ንስሐ ሳትገቡ በክፉ አሟሟት እንዲትሞቱ በማድረግ ለሲኦልና ለገፃነመ እሳት ፍርድ አሳልፈን የምንሰጣችሁ ታዲያ እናንተ እንዲህ እንደምንጨክንባቸሁ እያወቃችሁ በፍቅር በቸርነት በርኅራጌ በበረከት በጸጋ የሚያስተዳድራችሁንና በኋላም በመንግሥቱ ሕያዉ ሆናችሁ እንድትኖሩ ፈቃዱ የሆነዉን እግዚአብሔርን አኛ አንተን አንፈልግም ፈቃድህንም አንፈጽምም በሕያዉ መንግሥትህም መኖር አንመርጥም ማለታችሁ ክብር የማይወድላችሁ መሆኑን እያስመሰከራችሁ እንደሆነ እንኳን በፈጣሪያችሁና በቅዱሳኑ ዘንድ አይደለም በእኔ ርኩሱ ዲያብሎስ ዘንድ የታወቀ ነዉ ይሁንና ስለደንዳናነታችሁ የጨለማዉ መንግሥቴ ወራሽ ስለምትሆኑና መጨረሻችሁ እንደእኔ ያማረ ስለሚሆን በዚህ እንደምትጽናኑ ተስፋ አደርጋለሁ የእግዚአብሔር ፍርድ ከዓለም ዕልፈት በኋላ ብቻ አይደለም በዚህች ምድር ዉስጥ እናንተ የአዳም ዘሮች ሆናችሁ እኛ ሰይጣናት ርኩሳን መናፍስት እንደ ዓመጻ ደረጃችን እንቀጣለን ፍዳችንን እናገኛለን ቀድሞ ይህች ዓለም ሳትፈጠር በፊት በመጀመሪያዉ ፍጥረት ምሳሌያዊ ባሕርይ ቦታ በሰማያት ዉስጥ ይህን አታድርጉ» ሳንባል አፄ ሳጥናኤል የተገለጥኩበት አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ከሌሎቹ መናፍስት መላአክት የበለጠ ስለነበረ ከሁሉ በፊት የነበርኩ ዓይነት ስሜት ተሰምቶኝ አፄ ነኝ የፈጠርኳችሁ እኔን አምልኩ በምልበት ጊዜ አጅግ የብዙ ብዙ መናፍስት መላእክት ያልተቀበሉኝና በሰዉ ዘንድ ብዙ የሆኑ ነገር ግን ካልተቀበሉኝ መናፍስት ቁጥር አንጻር አንድ መቶኛ የማይሞሉ አልፍ አእላፋት መናፍስት አምነዉብኝና የተወሰኑት ደግሞ በጥርጣሬ ተቀብለዉኛል ይሁንና «አልቀበልም» ካሉኝ መናፍስት ጋር ጥል ስንፈጥር በተለይ ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ኃይለኛ ትንቅንቅ በምናደርግበት ወቅት ቀድሞ የማናዉቀዉና ያላየነዉ ነገር ግን ከእኛ በላይ የሆነ አንዳለ ኅሊናችን የሚመሰክርብን የሁላችን ፈጣሪ በብርፃናዊ ባሕርይ ተገልጾ ታየን የእኔንና ከእኔ ጋር ኅብረት የፈጠሩ እንዲሁም በዉስጣቸዉ «ፈጣሪያችን ሊሆን ይችላል በማለት በጥርጣሬ የተቀበሉኝን ጭምር እንደ ዓመጻችን ደረጃ ጸጋችንን ገፎ አዋርዶን ጎስቋላ ባሕርይ እንድንለብስ አድርጎ «ርኩሳን መናፍስት» የሚል ስያሜ ሰቶን እኔንም «የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ» ብሎኝ ከሰማያት ቀጥላ የተፈጠረችሁ ሁለተኛዋ ምሳሌያዊ ቦታ ትልቋ ዓለም ዉስጥ አነስ ያለች ምድር በዉስጧ ፈጥሮና በድቅድቅ ጨለማ እንድትሞላ በማድረግ ወደዚህች ምድር ተጣልን በተቃራኒዉ ደግሞ አኛን የተቃወሙ እንደ ጽናታቸዉ ደረጃ የተለያየ ሹመትና የክብር ጸጋ ተሰቷቸዉ በሰማያት ዉስጥ አምላካቸዉ በብርሃናዊ ባሕርይ ተገልጾ መመለክ ጀመረ እንዲሁም በእኛ ዓመጸኞች መናፍስት ምትክ ሌላ ሕያዉ ፍጥረት ካለመኖር ወደ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር መኖር ለማምጣት ፈልጎ በሁለተኛዋ ምሳሌያዊ ቦታ ዓለም ዉስጥ ከምድር በስተቀኝ የምትገኝ ገነት የተባለች ምድር ቦታ አዘጋጅቶ ሁለት ሕያዋን ፍጥረቶች ከባሕርይዉ እንዲሰርጹ እንዲወጡና በምስሌያዊ ባሕርይ ረቂቅ አካል እንዲገለጹ በማድረግ በገነት አኖራቸዉ እኛ እንደተሳሳትነዉና እንዳመፅነዉ እንዳያምፁና በግልጽ ተገዥነታቸዉን እንዲያረጋግጡ አንዲት ከምሳሌያዊ ባሕርይ ፍሬ አዘጋጅቶ እንዳይበሏት አዘዛቸዉ ከበሉ ግን የሞት ሞትን እንደሚሞቱ ጭምር አስጠነቀቃቸዉ ስራቸዉ አሱን ማመስገንና በቅድስና በደስታ ኑሮ ብቻ እንዲኖሩ እንዲሁም ሌሎች አንደነሱ የሆኑ ሕያዋን ፍጥረቶች በእነሱ ምሳሊያዊ ባሕርይ ግንኙነት ብቻ ካለመኖር ወደ መኖር እንደሚመጡና የሁሉም ወላጆች አንደሚሆኑ ተነግሯራቸዉ ነበር በመጨረሻም ቁጥራቸዉ ከእኛ ርኩሳን መናፍስት አኩል በሚሆንበት ሰዓትና ባቀደዉ ዘመን ወደ ሰማያት ዉስጥ በማስገባት በቅዱሳን መላአክት ሥርዓት ሊያኖራቸዉ ነበር እቅዱ እኛም ዓመጸኞቹ ርኩሳን መናፍስት እነሱ ወደ ሰማያት ዉስጥ እስከሚገቡ ድረስ በዚህች ቀድሞ ድቅድቅ ጨለማ ብቻ በነበረችዉ ምድር ወስጥ እየተቀጣንና እየተሰቃየን እንድንኖር ለማድረግና በኋላም እነሱ ወደ ሰማያት ዉስጥ ሲገቡ ህልዉናችንን አጥፍቶ በአንድ ቦታ ሳናስተዉልና ሳናዉቅ እንድንኖር ለማድረግና በመጨረሻም ዓለምን ከመኖር ወደ አለመኖር ለማሳለፍ ነበር እቅዱ ይሁንና ገና አንድ ሕያዉ ፍጥረትነፍስ በምሳሌያዊ ባሕርይ ግንኙነት ካለመኖር ወደ መኖር ሳይመጣ አኔ የጨለማዉ ገዥና ሠራዊቶቼ ሰይጣናት በእኛ ምትክ ሌላ ሕያዉ ፍጥረት መፈጠሩ ገባንና ቅናትና ምቀኝነት አደረብን ከዚያም እኔ ክፋትና ተንኮል የሞላብኝ የጨለማዉ ገዥና ጌታ ወደ ገነት እንድገባ ተፈቅዶልኝ ሔዋን በመባል የምትታወቀዉን ሕያዉ ፍጥረት ነፍስ የገነት አኗኗራቸዉን ጠየኳት እሷም እንደሷ በምሳሌያዊ ባህርይ በረቂቅ አካል የተገለጽኩ ነበርኩና አንዳች ጥርጣሬ ሳያድርባት የተባሉትን ሁሉ ዘክዝካ ነገረችኝ እፄም ዉድቀታቸዉንና ጥፋታቸዉን አፈልገዉ ነበርና ምክንያቱም በእኛ ምትክ ስለተፈጠሩ ቅናት አድሮብናልና እንዲሁም አነሱ አምላካቸዉ ላይ ካመጹ ለእኛ ምሕረት ይደረግልናል በሚል ግምት «አትብሉ የተባላችሁትን ፍሬ ከበላችሁ እንደእርሱ ሁሉን አዋቂ ፈጣሪ ስለምትሆኑ ነዉ አትብሉ ያላችሁ» በማለት የዓመጻ ምክሬን መከርኳት ለካስ የእምነት ጽናታቸዉ ይታይ ዘንድና በነጻ ኅሊናቸዉ በእዉነትና በመንፈስ እንደሚያመልኩትና የታዘዙትንም ትዕዛዝ «እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ያየናልና ትዕዛዙን መጠበቅ አለብን ብለዉ ትዕዛዙን እንደሚጠብቁና እንደማይጠብቁ ለማየት ነዉና እኔም ወደ ገነት እንድግባ የተፈቀደልኝ ልክ ክፉ ምክሬን አንደመከርኩ ከገነት እንድወጣ ተገድጄ ወዲያዉ ወደዚህች ምድር ተመለስኩ ምክሬን ተግባራዊ ያድርጉ አያድርጉ በወቅቱ ያላወኩ ሲሆን ለካስ ምክሬን በመቀበል በምኞት ተቃጥላ ኖሯልና ያቺ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ያልተፈቀደችላቸዉን ፍሬ በመጀመሪያ ሔዋን በመቀጠልም አዳም በመባል የሚታወቀዉ በላ ወዲያዉ ከአግዚአብሔር ጸጋ ተለዩ ባዶነት ተሰማቸዉ ያ ለታላቅ ዓላማ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣቸዉ አምላክ እንደበፊቱ በብርፃናዊ ባሕርይ ተገልጾ ያልተፈቀደላቸዉን ፍሬ ለምን እንደበሉ ጠየቃቸዉ አዳምም በሔዋን አሳበበ ሔዋንም በእኔ አሳበበች ይሁንና ሁሉቱም ማንም ሳያስገድዳቸዉ በነጻ ኅሊናቸዉ ተመርተዉ ነጻ ፈቃዳቸዉን ተጠቅመዉ በምኞት ተሸንፈዉ የበሉ በመሆናቸዉ ምንም አስተያየት ሳይደረግላቸዉ ይህች የእኛ መኖሪያ ብቻ የነበረችዉ በድቅድቅ ጨለማ ተሞልታ የነበረች ምድር አሁን የምታያቸዉና በሥጋዊ ዓይናችሁ የማታያቸዉ ፍጥረቶች ሁሉ ተፈጥሮላቸዉ በመጨረሻ ይቀጡበት ይጠሩበትና ይነጥሩበት ዘንድ ይህ የለበሳችሁትን ሥጋ ከመሬት አዘጋጅቶ ቀድሞ በገነት ዉስጥ ተገልጠዉበት የነበረዉን ረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ወደ አለመኖር አሳልፎት ይህን ግዙፉን ምሳሌያዊ ፍጥረት የሆነዉን ሥጋ ነፍሳቸዉ ተዋሕዳ እንድትገለጽበት አደረገ አዳምን በወንድ ጾታ ሔዋንን በሴት ጾታ እንዲገለጹና ቀድሞ በእነሱ አማካይነት በምሳሌያዊ ባሕርይ ግንኙነት ብቻ ሌሎች ነፍሳት ካለመኖር ወደመኖር አንዲመጡ ያዘዘዉን ሽሮ እነሱና የልጅ ልጆቻቸዉ ሁሉ በምሳሌያዊ ፍጥረት ግንኙነት በወንድና በሴት ጾታ ግንኙነት አማካይነት እንደሚወልዱ ገልጾላቸዉ እነሱም በዚህ ምድር ቆይታቸዉ እኔን የጨለማዉን ገዥ ክፉ ምክር ሰምተዉ ነዉና ያመጹት እኔ ገዥያቸዉ እንደምሆን ሌት ተቀን እንደምፈታተናቸዉና እንደምቀጠቅጣቸዉ ከዚህ ከሚቀጡበት ለመኖር ግድ መብላትና መጠጣት ካለበት ሥጋቸዉ ሲለዩ ደግም ድቅድቅ ጨለማ ቦታ ሲኦል እንደሚጠብቃቸዉ ምንም ሳይለፉ ሳይወጡ ሳይወርዱ የሚኖሩበትን ገነትን ስለናቁና ስላመጹ በዚህች ምድር ወተዉ ወርደዉ በድካማቸዉ እንደሚኖሩ ሔዋንም የመጀመሪያ ክፉ ምክር ተቀባይና የዓመጻ ፈጻሚ በመሆኗ በገነት በምሳሌያዊ ባሕርይ ግንኙነት አማካይነት እንኳን ምጥና ጭንቀት አይደለም መዉለዷን እንኳ አንዳች የተለየ ስሜት በማይሰማት መልክ ከእግዚአብሔር ባሕርይ የሚሠርጹትን ሕያዋን ነፍሳት የሆኑት አማናዊ ፍጥረቶች ሁሉንም የሰዉ ዘሮች በእናትነት ካለመኖር ወደ መኖር የሚመጡባትን ባለመፈለጓ በምጥና በጭንቅ እንድትወልድና ዘሮዎቿም እንደእሷ እንደሚወልዱ ነግሯቸዉ ተለያቸዉ እነሱም ባደፈ በጎደፈ በጎሰቆለ ባሕርይ መኖር ጀመሩ በእኔም ሌት ተቀን መፈተንና መቀጥቀጥ ደረሰባቸዉ ይሁንና ለዚህ ሕይወት በመዳረጋቸዉና አምላካቸዉ ላይ በማመጻቸዉ ምክንያት እጀግ ያዝኑ ይተክዙ ጀመር አምላካቸዉንም በእንባና በለቅሶ በጸጸት ይቅርታ ሁሉ ጊዜ ይጠይቁት ነበር አምላካቸዉም ርኅሩኅ ነዉና ጎዘናቸዉንና እንባቸዉን ተመልክቶ ስለሁለት ነገር ንሰሐቸዉን ተቀበለ አንደኛዉ እዉነተኛ ንስሐ ስለገቡ ሁለተኛ እናንተ የእነሱ ዘሮች ባላወቃችሁትና ባላመጻችሁት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ዓመጻ በእነሱ ላይ የተፈረደዉ ፍርድ ሁሉ በእናንተም ላይ ስለጸና እናንተም ስላሳዘናችሁት የእናንተ የሰዎች ነፍስ ከእኛ ሰይጣናት ቁጥር እስኪሞላ ድረስ ያሉትን ነፍሳት ከባሕርይዉ አሥርጾ ለቅጽበት ያህል በነጻ ኅሊናችሁ ያሳያችሁትን የእምነት ጽናትና አምላካችሁን የመፈለግ ብቃታችሁን ተመለከተ በዕይታዉ ዉስጥም አጅግ ብዙዎቻችሁ አሱ ከሚጠብቀዉ ደረጃ ዝቅ ብላችሁ ቀላችሁ ነዉ የተገኛችሁት ጥቂቶች ደግሞ ከመቅለል አልፈዉ እንደእኔና አንደ ሌሎች ሰይጣናት የማይገባ ሓሳብ በዚያች ቅጽበት በማሰባቸዉ እንደኛ ሆነዉ ነዉ ያገኛቸዉ የተወሰኑት ደግሞ የሚፈልገዉን ደረጃ አሟልተዉ በምርጥ ነፍሳትነት ደረጃ ያገኘዉ ጥቂቶች ደግሞ ከሚጠብቀዉ ደረጃ ልቀዉ በብቃት ነፍስነት ነዉ ያገኘዉ አንዲት ነፍስ ደግሞ ከሁላችሁ እጅግ ልቃና በቅታ ነዉ ያገኘዉ በነጥብ ደረጃ ሲታይ እጅግ በቅታ የታየችዉ ከመቶ መቶ ነጥብ ያገኘች ስትሆን ሌሉች የበቁ ነፍሳት ደግሞ ከ እስከ ነጥብ ምርጥ ነፍሳት ደግሞ ከ እስከ ነጥብ የቀለሉ ነፍሳት ደግሞ ከ እስከ ነጥብ ከመቅለል አልፈዉ በእኛ ደረጃ የታዩት ደግሞ ከ እስከ ነጥብ ያገኙ ናቸዉ ለአዳምም እጅግ ልቃና በቅታ የተገኘችሁ ነፍስ ስትወለድ «ከእርሷ ተወልጄ አድንፃለዉ ወደ ቀደመ ግዛትህ ገነትና ወደ መጀመሪያ ወደተፈጠርክበት ዓላማ ሰማያት ዉስጥም አስገባፃለዉ በማለት ቃል ገብቶለት አጽናናቸዉ አኔ የጨለማዉ ገዥና ጭፍሮቼ ሰይጣናት ግን አጅጉን ተናደድን ተባሳጨን የሚቻለን ቢሆን ኖሮ በዚያች ቅጽበት ዉስጥ ታንቀን ራሳችንን ብናጠፋ ምርጫችን ነበር ነገር ግን እንደ እናንተ በግዙፍ ሥጋ ስላልተገለጽን አልተቻለንም ከዚያች ጊዜ ጀምሮ በተጠናከረ መልኩ አዳምንና ዘሮቹን ሁሉ በመፈታተንና ዓመጻ ክህደት ርኩሰት እንዲፈጽሙ በማድረግ ወደ ገነት ሆነ መንግሥተ ሰማያት እንዳይገቡ መፈታተንን ጀመርን የመጀመሪያዉ ጥረቴ ተሳክቶልኝ ምስኪኑ አቤል በወንድሙ ቃኤል እንዲገደል በማድረግ ከገነት ውድቀታቸዉ በኋላ ከትልቋ ዓለም ዉጭና አጠገብ የተፈጠረችዉ ሲኦል ዉስጥ እንዲጋዝ አደረኩ ምንም እንኳ በሲኦል ዉስጥ የመጀመሪያዉ ነፍስ በምሳሌያዊ ባሕርይ በረቂቅ አካል ተገልጻ ብትገባም ጻድቅ ነፍስ ነበረችና በእግዚአብሔር ረድኤት ስለምትጠበቅ አንዳች የጭንቅ ሆነ የመከራ ሕይወት አላጋጠማትም ይልቁኑ ካደፈና ከጎሰቆለ ባሕርይ ተለይታ በተረጋጋና በረካ ሕይወት ዉስጥ ነበር የምትኖረዉ ታዲያ ለ ዘመን ነፍሳት ወደ ሲኦል ሲጋዙ እግዚአብሔርን በመፍራት ይመላለሱ የነበሩ ሰዎች ነፍሳቸዉ በሲኦል ዉስጥ ብትኖርም የሲኦል ሕይወት አይከብዳቸዉም ነበር። አያሉ እንደ ኃጢአታቸዉ ደረጃ በሲኦል ዉስጥ በስጋትና በጭንቀት ይሰቃዩ ነበር ዘመን ሲያልቅ ያቺ የሰዉ ዘሮች መዳኛ ምክንያት የሆነችዉና ትጠበቅ የነበረችዉ ነፍስ ኢያቄምና ሃና ከሚባሉ አግዚአብሔርን በመፍራት ከሚኖሩ ቤተሰቦች ተወልዳ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ ያ ለአዳም « ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንዛለዉ ብሎ ቃል የገባለት አልፋና ዖሜጋ ፍጥረታት ከመፈጠራቸዉ በፊት በአማናዊ ሕዋ ዉስጥ አንደ አማናዊ ባሕርይዉ የነበረ በሕያዉነት ዘመን ዉስጥ ከዛሬ ድጽ ዓመት በፊት ሰማያትንና አልፍ አእላፋት ወትአልፊት መናፍስትን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ በኋላም ዓለምንና በዉስጧ የሚታዩትንና የማይታዩትን ፍጥረቶች ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ከፈለገም በዓይን ቅጽበት ዉስጥ አሁን ካላዉ ፍጥረት በእልፍ አእላፋት አጥፍ ካለመኖር ወደ መኖር ማምጣት የሚችል ከፈለገም የሚታየዉንም የማይታየዉን ዓለም በዓይን ቅጽበት ጊዜ ዉስጥ ከመኖር ወደ አለመኖር ማሳለፍ የሚችል ካለአእርሱ ፈቃድ አንዳች ሊሆን ሆነ ሊኮን የማይቻል ሁሉን የሚመለከትና የሚቆጣጠር ያልኖረበትና የማይኖርበት ጊዜ የሌለ ለእያንዳንዱ እንደ ስራዉና እምነቱ የሚፈርድለትና የሚፈርድበት እዉነተኛ ፈጣሪ አምላክ አግዚአብሔር ከአማናዊ ሕዋ ዉስጥ ሳይጎል ከሰማያት ሳይጎል ከዓለም መግቦቱ ሳይጎል ባጠቃላይ በሁሉ ቦታ ምሉዕ እንደሆነ ባሕርይዉን ብቻ ዝቅ አድርጎ ከእመቤታችሁ ከመዳኛችሁ ምክንያት ከአደራ እናታችሁ ከእኔ ደግሞ ከዘመናት ደመኛዬና ጠላቴ ከሆነችዉ ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ በመሆን በተዋሕዶ ፍጹም ሰዉ ፍጹም አምላክ ሆና ተወለደ አኔም የጨለማዉ ገዥ ታወኩ ተሸበርኩ ተጨነኩ በሄሮድስ አማካይነት ለማስገደል ብሞክርም አልቻልኩምፈ በሥጋ ከተገለጸ ሠላሳ ዓመት ሲሞላዉ በሚያስተምርበት በሚፈዉስበት ተአምራትን በሚያደርግበት ጊዜ ሰዎችን በተለይ «የእግዚአብሔር አገልጋይ ነን የሚሉትን የልባቸዉን ክፋት ትዕቢት ቅናት ዓመጻ አዉቃለሁና በተለያየ ጊዜ ጥቃት አንዲፈጽሙበት ባነሳሳም ሳይሳካልኝ ቀርቶ ራሱ በፈቀደዉ ጊዜ የተለያዩ መከራዎችን ተቀብሎ በመስቀል ላይ በመሰቀል ነፍሱን ከሥጋዉ ሲለይ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ሄዶ እሰከዚያች ሰዓት ድረስ በሲኦል በረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ተገልጸዉ ይኖሩ የነበሩትን ነፍሳት ሁሉንም ነጻነትን አዉጆላቸዉ በምድራዊ ሕይወት ዘመናቸዉ ለገነት የሚያበቃ የጽድቅ ስራ የነበራቸዉን ይኸዉም በምድራዊ ዘመናቸዉ በኪዳነ ልቦና ተመርተዉ መልካም የሰሩትና በኃጢአት ሲወድቁም በኅሊናቸዉ ጸጸት ያደረጉ እንዲሁም በኪዳነ ኦሪት ተመርተዉ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ የጠበቁና በኃጢአት ሲወድቁም የኃጢአት ስረየት የተደረገላቸዉ ነፍሳት በቀጥታ ወደ ገነት የገቡ ሲሆን ሌሎቹ ነፍሳት ግን በሲኦልና በዓለም አጠገብ በተፈጠረችሁ አራተኛዋ ምሳሌያዊ ባሕርይ ቦታ ወደ ማረፊያ ቦታ ነዉ የገቡትፊ እነዚህ ነፍሳት የእግዚአብሔር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የኢየሱስ ክርስቶስን የመጨረሻዉን ፍርድ ለማግኘት የዓለም ዕልፈትን ቀን እየተጠባበቁ ይገኛል በማረፊያ ቦታም ከሲኦል ድቅድቅ ጨለማ ኑሮ ተገላገሉ እንጂ በምድር ዉስጥ እንደፈጸሙት ዓመጻ ክህደት ርኩሰት ደረጃ ነፍሳቸዉ እየተቀጣች ነዉ የሚገኘዉ ከክርስቶስ ስቅለት በኋላ የሚሞቱት ሰዎች ነፍስ ከሥጋቸዉ ተለይታ በረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ስትገለጽ የሚገቡት ወደ ገነት ማረፊያ ቦታና ሲኦል ዉስጥ ነዉ ወደ ገነት የሚገቡት በእርሱ በኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔርነቱ አምነዉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቁ መለኮት በተዋሓደዉ በክርስቶስ ሥጋና ደም የታተሙ መልካም ምግባር ያላቸዉ በኃጢአት ሲወድቁ ደግሞ እዉነተኛ ንስሐ ገብተዉ መለኮት የተዋሓደዉን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበሉ ክርስቲያኖች ብቻ ናቸዉ ወደ ሰኦል የሚገቡት ደግሞ በኪዳነ ልቦና ወይም በኪዳነ ኦሪት ወይንም በኪዳነ ወንጌል ተመርተዉ መልካም ያልሰሩ በኃጢአት የኖሩ ስለ ኃጢአታቸዉ ያልተጸጸቱና ንስሐ ያልገቡ ባጠቃላይ ዳግም ፍርድ የማያስፈልጋቸዉ በፍርድ ቀን በቀጥታ ወደ ገዛፃነመ እሳት ዉስጥ ከእኔ ከጨለማዉ ገዥና ከሠራዊቴ ሰይጣናት ጋር አብረዉ የሚጣሉ ዓመጸኛና ከፃዛዲ ሰዎች ነፍሳት ናቸዉ ወደ ማረፊያ ቦታ የሚገቡና የመጨረሻ የክርስቶስን ፍርድ የሚጠባበቁት ሰዎች ደግሞ በምድራዊ ሕይወት ዘመናቸዉ በመሰላቸዉ ሕይወት ዉስጥ በመልካም ተግባርና በቅን ሓሳብ የተመላለሱና ኃጢአት ሲፈጽሙ የኅሊና ጸጸት ያደረጉ ነገር ግን በእአዉነተኛዉ የሕይወት መንገድ ዉስጥ ያልተመላለሱ እንዲሁም በምድራዊ ሕይወት ቆይታቸዉ ነፍሳቸዉ የእምነትና የምግባር ደረጃዋ ያልታየ ሕፃናትና ተመሳሳይ ሕይወት የሚታይባቸዉ ነፍሳት ናቸዉ እነዚህ በማረፍያ ቦታ ቆይታ በሚያሳዩትና በሚያቀርቡት የእዉነትና የመንፈስ አምልኮ ለመንግሥተ ሰማያት የሚያበቃ ብቃት ላይ ከደረሱ በፍርድ ቀን ወደ መንግሥተ ሰማያት የመግባት እድል አላቸዉ አሁን የእኛ ሰይጣናት የዓመጻ ተግባር ነጻነት የሚገደበዉ የእናንተ የሰዉ ዘሮች በገነት በሲኦል በማረፊያ ቦታ በዚህች ምድር እንዲሁም ነፍሳቸዉን እጅግ ብቃት ደረጃ ላይ በማድረሳቸዉ ምክንያት እግዚአብሔር በመለኮታዊ ሥልጣኑ ወደ ሰማያት ያስገባቸዉና የሚያስገባቸዉ ቅዱሳን ነፍሳት ቁጥር ጠቅላላ ድምር ከእኛ ሰይጣናት ቁጥር እኩል በሚሆንበት ወቅት ነዉ በዚያን ጊዜ በዚህች ዓለም ዉስጥ ያሉት በዓይን የሚታዩትም የማይታዩትም ከመኖር ወደ አለመኖር ያልፋሉ እኛና በዚህች ምድር ዉስጥ የሚኖሩት ሰዎች ኃጢአተኛ ሰዎች በመቅሰፍት ሞት ጻድቃን ደግሞ በምሕረት ሞት ነፍስ ከሥጋቸዉ ትለይና ምሳሌያዊ ባሕርይ ረቂቅ አካል ትለብስና በቀጥታ ከዓለም ዉጭ ወዳለችዉ ማረፊያ ቦታ ለመጨረሻ ፍርድ ይቀርባሉ በዚህች ዓለም ዉስጥ በገነት ያሉት ጻድቃን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ነፍሳት የማረፊያ ቦታ የመጨረሻዉን ፍርድ ተመልክተዉ በቀጥታ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ በሲኦል ያሉት ነፍሳት ደግሞ የመጨረሻ ፍርዳቸዉን ተቀብለዉ ወደ ገነነመ እሳት ከኛ ሰይጣናት ጋር አብረዉ ይጣላሉፈ በማረፊያ ቦታ ቆይታቸዉ ለመንግሥተ ሰማያት የሚያበቃ ብቃት ላይ የሚደርሱት ነፍሳት ደግሞ ከገነት ከነበሩት ነፍሳት ጋር በቀጥታ የመጨረሻ ፍረድ ተፈርዶላቸዉ እንደቅዱሳን መላእክት በሰማያዊ ሥርዓት ለመኖር ወደ ሰማያት ዉስጥ ይገባሉ እንዲሁም በመጨረሻዉ የዓለም ዕልፈት ወቅት በኃጢአታቸዉ በመቅሰፍት ሞት ወደ ማረፊያ ቦታ የተጠሩት ነፍሳት ደግሞ ከእኔ ፈቃዴን ከፈጸሙልኝ ከጨለማዉ ገ ወደ ገሃነመ እሳት ዉስጥ ይጣላሉ በተቃራኒዉ ደግሞ በምሕረት ሞት ወደ ማረፊያ ቦታ የተጠሩት ነፍሳት ደግሞ ከወዳጆቻቸዉ ጻድቃን ጋር ወደ ሰማያት ይገባሉ በመጨረሻም ሲኦልም ማረፊያ ቦታም ዓለምም ምሳሌያዊ ባሕርይ ናቸዉና ከመኖር ወደ አለመኖር ያልፋሉ መጀመሪያና መጨረሻ በሌለዉ አማናዊ ሕዋ ዉስጥ ሁለቱ ምሳሌያዊ ቦታ ሰማያትና ገፃነመ እሳት ብቻ ይቀራሉ እኛ ሰይጣናትና እናንተ ርኩሳን ነፍሳት ዓመጸኛ ሰዎች ነፍሳችን በረቂቅ አካል በምሳሌያዊ ባሕርይ ሆና እሳቱ በማይጠፋ ምሳሌያዊ ባሕርይና ትሉ በማይሞት ምሳሌያዊ ባሕርይ በተሞላ በገፃነመ እሳት ዉስጥ እንደ ዓመጻችን ደረጃ እየተቀጣን ለሕያዉነት ዘመን እንኖራለን በዚህ አጋጣሚ በኖኅ ዘመን የነበሩት ዓመጸኛና ርኩሳን ሰዎችን በጨለማዉ ስሜ ላመስገናቸዉ እፈልጋለሁ ምክንያቱም በዚያን ወቅት እጅግ የከፋና የከረፋ የዓመጻ ተግባር ባይፈጽሙና ከምድር ባይደመሰሱ ኖሮ የሰዎች ነፍስ ቁጥር ገና ዱሮ ከእኛ ሰይጣናት ቁጥር እኩል ስለሚሆን ነጻነታችን ተገድቦ ገና ዱሮ ነበር ወደ ገሃነመ እሳት ዉስጥ የምንጣል የነበረዉ አሁንም ምኞታችን እናንተ የአዳም ዘሮች ኃጢአታችሁ እጅግ ከፍቶ ከምድር ትደመሱሱና እንደኖኅና ቤተሰቡ ዓይነቶች ብቻ ቀርተዉ የምድራዊ ዘመናችን እድሜ እንዲራዘም የእናንተም ምድራዊ ቅጣት ዘመን እንዲራዘም ስለምንፈልግ ነዉ ሌላዉ ቅሬታዬን በእናንተም ሆነ በእኔ ፈጣሪ ላይ አቀርባለሁ ይኸዉም እኔ የመዳን እድል ሳይሰጠኝ ዋጋ ሳይከፈልልኝ ስላመጽኩ ነዉ ወደ ገፃነመ እሳት ዉስጥ እንድጣል የሚፈረድብኝ እናንተ የአዳም ዘሮች የመዳን እድል ተሰቷችሁ በመስቀል ላይ ታላቅ ዋጋ ተከፍሎላችሁ «እኛ በእግዚአብሔር መንግሥት መኖር አንፈልግም በመስቀል ላይ የተሰቀለዉና ዋጋ የከፈለልንን አምላክ አንፈልገዉም አናምንበትም » ብላችሁ ነዉ በኃጢአት ተግባር የጸናችሁና ከእኔ ከጨለማዉ ገዥ ዓመጻና ክህደት በላቀ ደረጃ ላይ ተገኝታችሁ «እንዴት እኩል በገፃነመ እሳት ቦታ ላይ ይፈረድብናል። ይኸዉም ዘመናችሁን ሁሉ የእኔን ፈቃድ እየፈጸማችሁና እያስፈጸማችሁ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት በጭከና በግፍ በዘረኝነት በጎጠኝነት በዘፋኝነት በዳንኪርተኛነት በዝሙት በባዕድና ጣዖት አምልኮ ወዘተ አእየተመላለሳችሁ በማይቀረዉ ሥጋ ሞት ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደተዘጋጀላት ቦታ ይግባኝ ይቅርታ ንስሐ የማይባልበትና ዋጋዋን እንደ ዐመጻዋ ደረጃ የምትቀበልበት ቦታ ተጠርታ ስትሄድ ሰማዕት ጀግና ንጉሥ ንግስት ወዘተ» የመሳሰለት ስያሜ ሲሰጣት ስሰማና በተቃራኒዉ ደግሞ ስለ እዉነት መስክረዉ በእዉነት ኖረዉ እግዚአብሔርን ደስ በሚሰኝበት ሕይወት ተመላልሰዉ ስለ እዉነት ራሳቸዉን ክደዉ በመመስከራቸዉ ምክንያት በዐመጻ ልጆች በግፍና በጭከና ተገለዉ ወደ አምላካቸዉ እቅፍ የፄዱትን እንደ ቅዱሳን መላእክት በቅድስናና በፍጹም ደስታ ሕይወት የኖሩትንና የሚኖሩትን ለታላቅ ክብርና ሽልማት የበቁትንና የሚበቁትን ደግሞ «ዐመጸኞች ከፃዲያን» በማለት ስም ስታወጡላቸዉ በመስማቴና በመመልከቴ ነዉ ይላል ለማንም ፍጡር አንዳች ርኅራጌ የሌለዉ ዋናዉ ዓመጸኛዉና ከፃሃዲዉ ዲያብሎስ ከጭፍሮቹ ሰይጣናት ጭምር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምዕራፍ « አናንተ በምርጥ አንደራሴዎቼ መሪዎቻችሁና በባለሟል አገልጋዮቼ ባለሥልጣናት አንዲሁም በዉዶቼ ካድሬዎች ኅሊናችሁ ተመርኮዞ ጥላቻና በቀል ተሞልቶ በዘረኝነትና በጎጠኝነት ሕይወት ያላችሁ መልካም ፍሬዎቼ በመጀመሪያ አገልጋዮቼን በቶሎ አሳብባችሁ ለፍሬ በማድረሳችሁ በጨለማዉ ስሜ እያመሰገንኳቸዉ አናንተም በዘረኝነትና በጎጠኝነት የተበከለ ኅሊና የያዛችሁ ሰዎች የምጸየፈዉን ስያሜ « ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለዉን ንቃችሁና ተጸይፋችሁ የምፈልገዉንና የምወደዉን « እኔ ትግሬ ነኝ እኔ ኦሮሞ ነኝ እኔ አማራ ነኝ እኔ አፋር ነኝ እኔ ሱማሌ ነኝ እኔ ጋምቤላ ነኝ እኔ አኙዋክ ነኝ እኔ ቤንሻንጉል ነኝ እኔ ጉሙዝ ነኘ እኔ ሐረሪ ነኝ እኔ ፃድያ ነኝ እኔ ወላይታ ነኝ እኔ ሲዳማ ነኝ እኔ ከፊቾ ነኝ እኔ ስልጤ ነኝ ወዘተ» በማለት በጎጣችሁ መጠራትን የመረጣችሁ እንኳን ለዚህ ማዕረግ በቃችሁ እያልኩ በቅርቡ ደግሞ በናፍቆት እየተጠባበቃችሁት ያለዉን የዜግነት ስማችሁን ትግራዉያን ትግራዋይ ኦሮሚያዉያን አማራዉያን አፋርያዉያን ሱማሌያዉያን ቁጥር ሁለት ጋምቤላዉያን አኙዋክያዉያን ቤንሻንጉሊያዉያን ጉሙዝያዉያን ሐረሪያዉያን ፃዲያዉያን ወላይታዉያን ሲዳማዉያን ከፊቸኛዉያን ስልጤያዉያን ወዘተ» በማለት በሰማኒያዉ በብሔር ብሔረሰቡ ስም የተለያዩ ነጻ መንግሥታትን መስርታችሁ በዜግነት ስማችሁ ስትጠሩ እኛ ሰይጣናት ለማየት ያብቃን የኢትዮጵያዊነት የዜግነት መለያ በዓለም ላይ ተሰርዞ ለማየት ያድላችሁ ታላቁን የእኔን የጨለማዉ ገዥና የመሪዎቻችሁን ምኛት ያሳካላችሁ ያሳካልን በአንድ ላይ እንላለን ታዲያ አንዳንድ ከእንስሳ መሰል ከጦጣ በቀስ በቀስ ለዉጥና እድገት በኢኮልሽን አማካይነት አሁን ላሉበት ሰብእና መብቃታቸዉን የማያምኑ ሰዎች « የእግዚአብሔር ፍጥረት የሆን ሕያዋን ፍጥረት በአግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ የተፈጠርን የአግዚአብሔር ልጆች ነን የአዳምና ሔዋን ዘሮች ነን የኖኀ ልጆች የካም የሴም የያፌት ዘሮች ነን ከሁሉም በላይ ደግሞ የሦስቱ ነገድ ዉሕድ የሆነዉ ዘር ኢትዮጵያዊ ነን » በማለት የእግዚአብሔር ሕያዋን ፍጥረቶች መሆናቸዉንና የቅዱሱ ኪዳን ሕዝብ ኢትዮጵያዊ መሆናቸዉን የሚመሰክሩትንና የሚናገሩትን አትስሙ አነሱ ሐሳብያዉያን ናቸዉ እናንተ ግን ቁሳዉያን ተፈጥሮን ልትቆጣጠሩ የደረሳችሁ አዋቂዎችና ምሁራን ናችሁ በዚህ የክህደትና የዓመጻ ሕይወታችሁ ከጸናችሁ ጨለማዉ መንግሥቴን እንደማወርሳችሁ አንዳች ጥርጣሬ እንዳይገባችሁ እናንተ ምርጦቼ አንደራሴዎቼ መሪዎችና ባለሟሎቼ ባለሥልጣናት እንዲሁም ዉዶቼ ካድሬዎች ላለዉ ይጨመርለታል የሌለዉ ያዉ ያለዉ ይወሰድበታል » የሚለዉን ቃል ለመፈጸም ሌት ተቀን የምትተጉ አገልጋዮቼ የዕለት ኑሮዋቸዉን ለማሸነፍና ለመደጎም በትንንሽ ንግድ ሰራ ላይ ተሰማርተዉ የነበሩትን ምስኪኖች ያተረፉትን ብቻ አይደለም ዋናቸዉን ጭመር እንዲገብሩ አድርጋችሁ ስራቸዉን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ያዚጋችሁና ያስመረራችሁ በተቃራኒዉ ደግሞ ሚሊዮነሮችን ባላቸዉ ላይ ገንዘቡንም መሬቱንም ንብረቱን በላይ በላይ እንዲጨመርላቸዉ በማድረግ የፖለቲካ ደጋፊዎቻችሁንና አባሎቻችሁን ያናጠጣችሁ በመሆኑ ቃሉን በራሳችሁ አተረጓጎም ተግባራዊ አድርጋችኋልና ያለኝን አድናቆት ልገልጽላችሁ እአወዳለሁ ሌሎቹንም አባባሎች በራሳችሁ እየተረጎማችሁ ለሥልጣን ቁጥጥራችሁ ያመቻችሁ ዘንድ «ለባለሥልጣናት ታዘዙ ተገኩዙ»እ ተብሏልና ሕዝቡን ኅሊናዉን እንዲሸጥ በማስደረግ አናንተ ኢትዮጵያዉያን ለሕገ መንግሥታችን ብቻ አይደለም ለምንናገረዉ ንግግሮችና አባባሎች ሁሉ ተገዙ ስንሰድባችሁና ስናዋርዳችሁም «አዎን ስድባችሁ ለእኛ ምርቃት ነዉ ጭከናችሁም ለእኛ የርኅራጌዔቴ መገለጫ ነዉ ግፋችሁም ለእኛ የቸረነት ስራ ነዉ አንዲሉ አድርጉ እናንተ ሕዝቡን በባዶ ተስፋ የምትሞሉ ኅሊናችሁ እዉነቱን እያወቀ የማይሆነዉን ይሆናል የሆነዉን አዉነት እንዳልሆነ ያልተደረገዉን እንደተደረገ አድርጋችሁ የጌቶቻችሁን ገበና በሐሰት ሸፋፍናችሁ በተለያየ መገናኛ ብዙኃን ማስ ሚድያ በተለያዩ ሕትመቶች የምታቀርቡ ዘጋቢዎች የእንደራሴዎቼ መሪዎችና የባለሟሎቼን ባለሥልጣናት ፈቃድ ፈጻሚና አስፈጻሚ በሞሆናችሁ በጨለማዉ ስሜ እያመሰገንኳችሁ ለወደፊት ሕዝቡን « ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አለይ እስከሚል ድረስ በባዶ ተስፋ ኅሊናቸዉን ሞልታችሁ ጌቶቻችሁን ተስፋ እንዲያደርጉና እንዲያመልኩ አድርጉ የጌቶቻችሁን ግፍ ዓመጻ ክህደት በደል አድሎ ርኩሰት ክፋትና ክርፋት ተግባራቸዉን ደግሞ በደንብ አድርጋችሁ ሸፋፍኑ በተለይ እዉነተኞችና ንጹፃን ኅሊናችንን አንሸጥም ከነፈሰዉ ጋር አንነፍስም ብለዉ ለኅሊናቸዉ የቆሙትንና ስለ እዉነት በሚመሰክሩት ሰዎች ላይ የሐሰት ምስክር አቀነባብራችሁና ማስተባበያ የሚሰጡ ኃላፊዎችን አዘጋጅታችሁ በተለያየ ወንጀል እንዲከሰሱ አድርጉ ታዲያ አንዳንድ ተስፈኞች «አንድ ቀን እዉነት ትነግሥና ሐሰትን ታጋልጣለችታዋርዳለች» በማለት የሚናገሩትን አትስሙ አንዳችም ሥጋት አይግባችሁ ከአኔ ከጨለማዉ ገዥ አዉቀት ዉጭ በዚህ ዓለም ሌላ እዉቀት የለም የሚሆነዉን ሁሉ ስለማዉቅ አንዲህ ሊፈጠር ይችላል የአሁኖቹ መሪዎች ሆኑ ባለሥልጣናት ከወንበራቸዉ ሊቆረጡ ይችላሉ የዘሩትን የዓመጻና የክህደት ፍሬ ሊያጭዱ ይችላሉ» የሚል ስጋት አንዳች አይግባችሁ አስከ ሺህ ዘመን ድረስ ትዉልዳቸዉን ብቻ አነግሥላችኃለሁ እናንተ ስም አወጣጥና ስያሜ የምታዉቁ አዋቂዎች በዚህ ስም አወጣጣችሁ አድናቆቴንና ሙገሳዬን እገልጽላችኋለሆ ይኸዉም አገር በመገንጠል በማስገንጠል እንዲሁም ዘረኝነትንና ጎጠኝነትን በማስፋፋት የሞቱትን አገልጋዮቼን ጀግኖች «ሰማዕታት ታላቅ ታሪክ ሰሪዎች» እያላችሁ በመሰየማችሁና መታሰቢያም በማድረጋችሁ ነዉ በተቃራኒዉ ደግሞ ለአገራቸዉና ለሕዝባቸዉ ታሪክ ሰርተዉ ያለፉትን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ኢትዮጵያዉያንን በጥላቻ በቂም በቀልነት ተነሳስታችሁ ስማቸዉን በማጥፋታችሁና መታሰቢያቸዉን በመደምሰሳችሁ ጭምር ነዉ ለወደፊቱ ደግሞ ይህን ታላቅ ተግባራችሁን በማጠናከር ለእናት አገራቸዉ ኢትዮጵያ ታሪክ የሰሩትን ብቻ ሳይሆን «ጻድቃን ቅዱሳን » የሚባሉትን ሁሉ መታሰቢያቸዉን ከምድረ ገጽ እንድታጠፉልኝ በጨለማዉ ስሜ አዛችኋለሁ በዚህ ድርጊታችሁ ደግሞ የመረጣችሁትን መንግሥቴን አወርሳችኋኃለሁ እናንተ ኢትዮጵያዉያን ተራማጅ ኃይሎች የሶሻሊስት የአብዮታዊ ዲሞክራሲ የካፒታሊስት የመሳሰሉት አግዚአብሔር የለሽ ሥርዓቶች ለመቀበልና አሜሪካዊ አዉሮፓዊ አረባዊ ሥርዓት ለመዘርጋት ወደ ኋላ የማትሉና የራሳችሁን ኢትዮጵያዊ ሥርዓት ለመዘርጋት ፈቃደኛ ያልሆናችሁ ስለ ታለቅ አስተሳሰባችሁና ቆራጥነታችሁ እንዲሁም እንደማንነታችሁ ለመኖር አለመፈለጋችሁ ያለኝን አድናቆቴን በጨለማዉ ስሜ እያቀረብኩ ለወደፊትም በምንም መልኩ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራዉን ቤተ ሕዝቡ ቤተ ክህነቱ ቤተ መንግሥቱ በአንድ የሚመራበትን የእግዚአብሔር መንግሥት ሥርዓት እንዳትዘረጉ የምትዘረጉ ከሆነ ግን ከአኔ ምድራዊ መንግሥት የምትለዩና ያጎናጸፍኳችሁን ርኩሰት ዓመጻ ክህደት የምትፈጽሙበትን ዴሞክራሲ መብታችሁን አሳጣችኋለዉ ከክፋት ከተንኮል ከምቀኝነት ከትፅቢት ከዝሙት ከባዕፅድ አምልኮ ከዘፋኝነት ከዳንኪርተኛነት ከአመንዝራነት ከጥላቻና ከጥል ከቂምና ከበቀል ከበደልና ከአድሎ ከስግብግብነትና ከስስት ከራስ ወዳድነት ባጠቃላይ በዚህች አገር ካነገሣችሁት ከአኔ ታላቅ ስራ እለያችኋለሁ ስለዚህ ከነዚህ መልካም ፍሬ አንዳትለዩ የጨለማ ሥርዓቴን ለመጠበቅ ታጥቃችሁ እንድትነሱ በዚህ አጋጣሚ አሳስባችኋለሁ እናንተ በተለየዩ መገናኛ ብዙኃን በሆኑት በነፋስ ሥዕልቴሌቨዥን በነፋስ ድምጽበሬድዮን በጦማረ ሕዝብበጋዜጣ በመጽሔት በመጽሐፍ በድረ ገጽ በኢንተርኔት በመሳሰሉት የጊዜ ማባከኛና ማጥፊያ ወሬና የተለያዩ ማደንዘዣ ትዕይንቶች እንዲሁም ርኩሰት የተሞሉ ፊልሞች የምታስተላልፉና ትዉልዱም ሌት ተቀን ስለ ዘፈን ስለዳንኪራ ስለአገዳደል ስለ አደባደብ ስለዝሙት ስለስርቆት ስለመሳሰሉት ተግባር እንዲያስብ በማድረጋችሁ በጨለማዉ ስሜ ምስጋና አቸራችኃለሁ ከዚህ በተጨማሪ ሕዝቡን ለጦርነት ለጥላቻ ለበቀል ለግድያ ለዓመጽ ለክህደት ለርኩሰት በማነሳሳታችሁ እንዲሁም የክህደትና የመናፍቅነት እምነት እንዲስፋፋ የክህደት ፍልስፍና እንዲነግሥ በማድረጋችሁ ስለ መልካም አገልግሎታችሁ በድጋሜ በጨለማዉ ስሜ አመሰግናችኋኃለሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በተለይ በዚህ መልኩ የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተግባርና ንግግር እንዲተላለፍ ላደረጋችሁ ታላላቅና ለአናሳ መንግሥታቶቼ መሪዎችና ባለሥልጣናት እንዲሁም እንደማዕረጋችሁ ለካድሬዎቼ በጨላማዉ ስሜ ደግሜ ደጋግሜ አመሰግናችኋለሁ በዚሁ አጋጣሚ እነዚህ መገናኛ ብዙኃን ዋናዉ መሳሪያዬና በቀላሉ ተግባሬና ንግግሬን የማስተላልፍበት ቅስቀሳ የማደርግበት ጥሩ ዉጤት ያስገኘልኝ በመሆኑ ይህን ታላቅ መሳሪያ በምንም መልኩ ለማይታወቀዉ «መንግሥተ ሰማያት» ለሚባለዉ ዓለም አገልግሎት እንዳይሰጥበት እያስጠነቀኩ እዉነታ የሚባል ነገር ቢተላለፍበት ከወንበራችሁ የምቆርጣችሁና ከአገልግሎቴም የምሽራችሁ መሆኔን አግልጽላችኋለሁ ስለዚህ ለሥጋችሁ ሆነ ለነፍሳችሁ የሚጠቅም ነገር ብታስተላልፉበትና ሕዝቡ ተስፋዉን ሰማያዊ አድርጎ መኖር ቢጀምር ጦርነት ቢቆም ርኩሰት ባይታይበት ሕይወት የሆነዉና የእርካታ የደስታ ምንጭ የሆነዉ ኮንደም ሰንሴሽን ባይተዋወቅበት ሰዎች ለበቅልና ለጥላቻ እንዲነሳሱበት ባይደግበት ክፋት ተንኮል ዓመጻ ክህደት ባይስፋፋበት ዘፈንና ዳንኪራ ባይታይበት ጊዜ ማባከኛና ማጥፊያ እንዲሁም የኅሊና ማደንዘዣ ወሬና ትዕይንቶች ባይተላለፍበት ባጠቃላይ ሐሰት ባይነግሥበትና ለእዉነት ቦታ ከተሰጠዉ በሕገ መንግሥቴ ዐዋጅ መሰረት በዓመጻና በክህደት በወንጀል የምጠይቃችሁና ከመንግሥቴም የምሽራችሁና በመንግሥቴም የማላኖራችሁ መሆኑን ከወዲሁ እንድታዉቁ አቋሜን እነግራችኋለሁ በተቃራኒዉ ደግሞ ለመንግሥታቶቼ ታማኝ አገልጋይ ሆናችሁ የሐሰት ዘገባና እዉነተኞቹን በሐሰት መረጃ በመወንጀል ለዓለም የምታሳጡ ጋዜጠኞች በወደፊቱ መንግሥቴ መገናኛ ብዙኃን ዘርፍ በሚንስትርነትና በከፍተኛ ባለሥልጣንነት ማዕረግ እንደምሾማችሁ ቃል እገባላችኋለሁ በተለይ እናንተ ኢትዮጵያዉያን አድናቆቴን ልቸራችሁ እወዳለዉ ምክንያቱም የራሱን ታሪክና ማንነት በራሱ አንደበት የሚያጥላላና የሚደመስስ የአገሪቱና የሕዝቡ ጥፋትን የሚፈልጉ ግለሰቦችና ቡድኖች የጻፉትን የክህደትና የሐሰት የፈጠራ ታሪክ ወደ አዉነትነት ለዉጦ አገሩንና ሕዝቡን ለማጥፋት የተሰለፈ የራስ መንግሥትና የራስ አገልጋይ በዓለም ላይ እስከአሁን ድረስ ባለማየቴ ነዉ ይልቁነ ሌላዉ ዓለም የሌለዉን ታሪክ እንኳ እየፈጠረ ማንነቱን ከፍ ከፍ የሚያደርግና የሚያገን ሆኖ ስመለከት እናንተ ደግሞ ማንነታችሁን እያጠፋችሁ ዕንቁ ታሪካችሁን እምነታችሁን ባህላችሁን ደብቃችሁና አጥፍታችሁ የሌሎች አገራትን የሐሰት ታሪክ የክህደት እምነት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የርኩሰት ባህል እያሳያችሁና እያስፋፋችሁ በመሆኑ የአድናቆት አድናቆቴን ልገልጽላችሁ እወዳለሁ ከዚህ በተጨማሪ ለዓለም ሕዝብ እናንተ የዓለም ሕዝቦች ሆይ። ሁሉም በአኔ መንገድና ምክር ተጉዘዉ ነዉ ለዚህ ደረጃ የበቁትፅ ስለዚህ እናንተም እንደነሱ ለመሆን ከፈለጋችሁ ታላቁን የጨለማ ምክሬን ልትሰሙ ይገባችኋል እናንተ ተስፋችሁን ምድራዊ አድርጋችሁ የታላቅነታችሁ መገላጫ በሆነዉ በአብሪትና በትዕቢት መናገራችሁና መደንፋታችሁበኃይላችሁና በጦራችሁ መመካታችሁ በካድሬዎቻችሁና በደኅንነታችሁ መተማመናችሁ አንዲሁም በእአዉቀታችሁና በጥበባችሁ መታበያችሁ በሀብታችሁና በብልጽግናችሁ መመካታችሁ ከዚህ በተጨማሪ ባማረዉ ገላችሁ ተመክታችሁ ሰዉነታችሁን በመገላለጥና በተወጣጠረ ልብስ አካላችሁን የምታስመልኩ ባጠቃላይ ተፈጥሮ በለገሰቻችሁ የሰላ አንደበት ልኬት በሌላዉ እዉቀትና ጥበብ አብሯችሁ በሚኖር ሀብት ንብርት ብልሽት በማይታይበት ገላችሁ ተመክታችሁ የዓመጻ ስራ የምትፈጽሙና የምታስፈጽሙ ሰዎች በመጀመሪያ ደረጃ እኔ የጨለማዉ ገዥ ስለታላቅነታችሁ አመሰክርላችኃኋለሁ በማስከተል ደግሞ አንዳንድ አላዊቂዎችና ተስፋቸዉን የማይታየዉን ሰማያዊ መንግሥት አድርገዉ የሚመላለሱት ሰዎች የሚሉትን እንዳትሰሙ እመክራችኃለሁ ይኸዉም እነዚህ ራሳቸዉን በማስታበይና በዕብሪት ሌት ተቀን የሚደነፉ የሚያስፈራሩ በደልን አድሎ ግፍ የሚፈጽሙ በትዕቢትና በዓመጻ ሕይወት የሚመላለሱ በኃይላቸዉ በጦራቸዉ በካድሬዎቻቸዉ በደኅንነታቸዉ በሀብትና ንብረታቸዉ በብልጽግናቸዉ በአዉቀታቸዉ በጥበባቸዉ በገላቸዉ ወዘተ የሚመኩና የሚታበዩ በእግዚአብሔር ቦታ ላይ ሆነዉ መመሰለክንና መግነንን የሚፈልጉ ነጥብ በማትሞላ እዉቀታቸዉና ጥበባቸዉ የሚመኩና የሚመጻደቁ ለደቂቃ እንኳ በራሳቸዉ ሥልጣን በምድር መቆየት የማይችሉ በዓይን ቅጽበት ዉስጥ ከመኖር ወደ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አለመኖር በሚያልፍ እንዳልነበረ በሚሆን ኮልኮሌ የሚመኩ በሰከንድ ዉስጥ በሚበላሽና በሚፈረካከስ ገላቸዉ የሚመኩና ራሳቸዉን የተለየ አድርገዉ በመቁጠር ቅርፊት ሥጋቸዉን የሚያስመልኩ ባጠቃላይ ይህ በሥጋዊ ዐይን በሚታየዉ ምሳሌያዊ ፍጥረት በሆነዉ ጥንት ባልነበረዉ ቁሳቁስ ነገር የሚታበዩና የሚመኩ ሰዎች ምድራዊ ክብራቸዉን ቢያዉቁና ቢያስተዉሉ እንኳን ራሳቸዉን የተለየ አድርገዉ ሊቆጥሩና ሊታበዩ በራሳቸዉና ባላቸዉ ሊመኩ በእግዚአብሔር ቦታ ላይ ተቀምጠዉ ራሳቸዉን ሊያስመልኩና ሊያገኑ እንዲሁም ቅርፊት ሥጋቸዉን ሊያስመልኩ ቀርቶ አንዲት ቀንን በዚህ ምድር ዉስጥ መቆየትን አይፈልጉም ነበር ምክንያቱም እንደዚህ የሚታበዩትም ሆኑ በራሳቸዉና ባላቸዉ የሚመኩት እንዲሁም ራሳቸዉን የሚያመጻድቁትም ሆኑ የሚያስመልኩት ሰዎች ቀድሞ በገነት አኗኗር ዉስጥ ያልነበረዉና የማይከሰተዉ በአዳምና ሔዋን ዓመጻ ምክንያትና በስደት ወደዚህች ምድር ዉስጥ በመግባታቸዉ ምክንያት በሰዉ ዘሮች ላይ ከተከሰተዉ ያደፈና የጎደፈ ባሕርይ ከሆነዉ ከዓይነ ምድር ከሽንት ከሽታ ከላበት ከንፍጥ ከአክት ሕይወት ያልተለዩ የጎሰቆሉ ባሕርያት ከሆኑት ከመድከም ከማልቀስ ከማዘን ከማንቀላፋት ከመቁሰል ከመድማት ከመዳህ ከማማጥ ከመቅበዝበዝ ከስጋት ከሓሳብ ኑሮን ለማሸነፍ ከመዉጣት ከመዉረድ ከመታመም ከማርጀት በሥጋ ከመሞት በነፍስ ደግሞ አዉነተኛ ፍርድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ከመቀበል ወዘተ መለየት ያልቻሉ አንዲሁም ጉስቁልና ኑሮና ሕይወት ከሆኑት በፀሐይ በሙቀት በቅዝቀዜ በተፈራረቀ አየር ጠባይ ዉስጥ ከመመላለስ ዝናብ ብርድ ሙቀት ለመከላከል መጠለያና ማረፍያ ከመስራት ሌት ተቀን በሰይጣናት ከመፈተንና ሰይጣናት ከኅሊናና ከአካል ዉስጥ ሲወጡ ከሚገለጽበት ከማፋሸክ ከማስነጠስ ከመሳል ከማግሳት ከማሳከክ ከመንጠራራት ከፈስ ያልተላቀቁ ከዚህ በተጨማሪ ሰዎች ወደዚህች ምድር ከገቡ በኋላ በራሳቸዉ ጊዜ በፈጠሩት የስግብግብነት የራስ ወዳድነት የጥላቻ የወገንተኝነት የዘረኝነት የጎጠኝነት የክፋት የተንኮል የምቀኝነት የጦርነት የግድያ የስርቆት የጥንቆላ የአስማት የመተት የዝሙት የዘፋኝነት የዳንኪርተኛነት የመከፋፈል የቂም በቀል የዕብሪት የትዕቢት የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ወዘተ ሕይወት ዉስጥ የሚመላለሱ በመሆኑ ነዉ በዚህም ምክንያት የዚህች ምድራዊ ሕይወት ሕይወት ሳይሆን ነፍሳት በሥጋቸዉ የሚቀጡበትና እንደ ነጻ ምርጫቸዉ እግዚአብሔርን ከመረጡ ፈቃዱን ፈጽመዉ እጅግ እጅግ እጅግ አጭር የሆነችዉን ዘመናቸዉን ከዚህች ምድራዊ ዘመን በኋላ የማይኖሩበት ጊዜ ስለማይኖር ሕያዉ ሆነዉ ስለሚኖሩ የምድራዊ ቆይታቸዉ ጊዜ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የዓይን ቅጽበት እድሜ ያህል አንኳ ርዝመት ስለሌለዉ ነዉ ወደ አዉነተኛ መኖሪያቸዉ ገነት ከፍርድ ቀን በኋላ ደግሞ ቅዱሳን መላእክት ባሉበት ሰማያት ዉስጥ የሚገቡበት ነዉ በተቃራኒ ደግሞ በሥጋ ከተገለጹ በኋላ በዓመጻና በክህደት እንዲሁም በርኩሰት ሕይወት ዉስጥ የሚጸኑት ሰዎች ደግሞ ነፍሳቸዉ በምሳሌያዊ ባሕርይ እንደ ሰይጣናት ተገልጻ ነጻነቷም ተገድቦ በባሰ ሁኔታ የምትቀጣበት ቦታ ዉስጥ ሲኦል ከፍርድ ቀን በኋላ ደግሞ አሳቱ ከማይጠፋበት ትሉ ከማያንቀላፋበት ገፃነመ እሳት ዉስጥ በመግባት ለሕያዉነት ዘመን እንደ ዓመጻዋ ደረጃ ከሰይጣናት ጋር ይቀጣሉኤ በማለት ከእኔ ከጨለማዉ ገዥ ፈቃድ አስፈጻሚነትና ፈጻሚነት ሊለያችሁ የሚፈልጉትን በእኔ ላይ ፅለት ዕለት ዓመጻና ክህደት እየፈጸሙ የሚያስቸግሩኝን አንዲሁም አንዳች ርኅራቴ ሳያደርጉልኝ ሌት ተቀን ፍዳዬን የሚያሳዩኝን የሚያሰቃዩን ሰዎች አንዳች አትስሙ ይልቁኑ በቅን ሓሳብ በእዉነተኛ ሕይወት በመልካም ተግባር በጸሎት በጾም በስግደት እያሰቃዩንና መከራ እያደረሱብ ስለሆነ ተበቀሉልኝ እናንተ ግን ታላቅ ሰዎችና ባለችሁ አጭር ዘመን ዉስጥ አኔን ደስ ለማሰኘት የምትተጉ ለአኔ ምርጦችና ወዳጆች መሆናችሁን ደግሜ አመሰክርላችኋለሁ እናንተ «ሞተን በስብሰን እንቀራለን ብትሉም አኔ ግን ሞታችሁና በስብሳችሁ አንደማትቀሩ ሕያዋን አንደምትሆኑ ሙሉ ዋስትናና ለወደፊት ደግሞ እኔን እንደማስደሰታችሁ ደረጃ የሚያምረዉንና እጀግ መዝናናትን በማደርግበት መንግሥቴ የመኖር ዕድል አንደምሰጣችሁ በጨለማዉ ስሜ ቃል እገባላችኃለሁ እናንተ «ፖለቲካ ዴሞክራሲ» የሚለዉ ልዩ ቋንቋይ ስያሜ ያልገባችሁና በተደጋጋሚ ማብራሪያ እንድሰጥበት እየጠየቃችሁ የምታስቸግሩኝ ሰዎች አሁን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ምላሼንና ማብራራዬን እኔ የጨለማዉ ገዥ እሰጣችኃለሁ ፖለቲካ የሚለዉ ስያሜ የተፈለሰፈዉ በቀጥታ እዉነታ የሚለዉ የእግዚአብሔር እዉነትን ለመቃወምና ስያሜዉንም ጭምር ለመተካት ታስቦ በእግዚአብሔር ተቃራኒ መንፈስ አሳሳቢነትና መሪነት የተፈጠረ ታላቅ ቃል ነዉ በዚህም ምክንያት ሰዎች የዓመጻ የክህደት የርኩሰት አስተሳሰብን ኅሊናቸዉ በቀላሉ እአንዲቀበለዉና ወደ ተግባርም ለመፈጸም እንዲቻል እንደ ዶግማና ቀኖና በርዕዮተ ዓለም መልክ አንዲቀበሉት የተደረገ ነዉ ልዩ ጥበብና ፍልስፍ እንዲጨመርበትና ወርቃማ ቃላቶች እንዲካተቱበት የተደረገዉ ሰዎች ተታለዉ ለእኔ ለጨለማዉ ገዥ ፈቃድ ፈጻሚዎችና አስፈጻሚዎች እንዲሆኑበነጻ ፈቃዳቸዉ እንዲቀበሉት እንዲመሩበት እንዲተዳደሩበት እንዲታገሉበት እንዲጋደሉበት እንዲፋጩበት እንዲገዳደሉበት እንዲጨካክከነበት አንዲከፋፈሉበትና እንዲለያዩበት አንድ እንዳይሆኑበት ባጠቃላይ ተስፋቸዉን ምድር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አድርገዉ እንዲመላለሱበት ለማስቻልና በመጨረሻም ለታላቁ ለጨለማዉ መንግሥቴ ለማብቃት ታስቦ ነዉ በመሆኑም የምርጦቼ እንደራሴዎቹ መሪዎች ሆነ የባለሟሎቼ ባለሥልጣናት የዉዶቼ ካድሬዎች እንዲሁም ተጠባባቂ እጭዎቼ አስተሳሰብና ዓላማ እግዚአብሔር መፍራት ያለበትንና ፈቃዱን የሚፈጽሙበትንንና የሚያስፈጽሙበትን ሥርዓት መዘርጋትና ሕዝቡ ምድራዊ በረከት እንዲያገኝ አድርገዉ ለሰማያዊ ሕያዉ ሕይወት ለማብቃት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ህልዉና በመካድ «ሰዉ የተገኘዉ ከተፈጥሮ ነዉ በቀስ በቀስ ዕድገትና ለዉጥ በኢሾኮልሽን አማካይነት ከጦጣ መሰል እንስሳ ወደ ሰዉ ተለዉጦ ነዉ ጽድቅና ኩነኔ የሚባል ነገር የለም ሰዉ በዚህች ምድር ሞቶ በስብሶ ይቀራል እንጂ ትንሣኤ ገነት መንግሥተ ሰማያት የሚባል ነገር የለም ወዘተ በማለት በእኔ በጨለማዉ ገዥ ፍልስፍና የሚመሩ ፍጹም ለእኔ ታማኝ ሆነዉ ባሪያዎቼ የሆኑና ሕዝቡም ባሪያዎቼ እንዲሆኑ ሌት ተቀን የሚተጉልኝ የምርጦቼ ምርጥ መሆናቸዉን በዚሁ አጋጣሚ እመሰክርላቸዋለሁ ታዲያ በዚህ ፍልስፍናዬ የተለያዩ ዛሃይማኖቶችና እምነቶችን እንዲሁም የተለያዩ ርዕዮተ ዓለሞች በየጊዜዉ እንደ ፋብሪካ ምርት እንዲመረቱና ሕዝቡም እንዲከፋፈል እንዲለያይ በጥላቻ እንዲተያይ እንዲጣላ እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንዳይሆን አድርጌ ሙሉ በሙሉ በጨለማ ሥርዓቴ እንዲመላለሱ አድርጌያለሁ ስለዚህ ፖለቲካ የምለዉ ቋንቋዬ እጅግ ፍሬ ያፈረሁበት ለሕዝቡም ፍትህ እኩልነት ነጻነት አንድነት ክብር ታላቅነት ብልጽግና ሰላም ዲሞክራሲ ወዘተ ባጠቃላይ ወርቃማ የሆኑ ነገር ግን ወደ ተግባር የማይለወጡ አባባሎችንና ቃላቶችን አጎናጽፌዋለሁፎ ስለዚህ እያንዳንዱ አባሌና ተከታዬ እንዲሁም ደጋፊዬ ዉለታዬን አሰቦ በየቦታዉ ሐዉልት አቁሞልኝ ሊያመልከኝ እንደሚገባ በዚሁ ትዕዛዝና መመሪያዬን ለእንደራሴዎቼና ለባለሟሎቼ ለዉዶቼ አስተላልፋለሁ ታዲያ አደራ የምላችሁ እዉነታ የምትባለዉን ሥርዓት ቤተ ሕዝቡ ቤተ ክህነቱ ቤተ መንግሥቱ በአንድ መንፈስ ቅዱስ የሚመሩበትና ወደ ተግባር ተለዉጦ ሕዝቡ በፍቅር በሰላም በአንድነት በቅን ሓሳብ በአዉነተኛ ሕይወት በመልካም ተግባር እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ በሚሆኑበት ባጠቃላይ እግዚአብሔር ደስ በሚሰኝበትና ምድራዊ በረከት በሚያገኙበት ለሰማይዊ መንግሥት በሚበቁበት ሕይወት እንዲመላለሱ እንዳታደርጉ ይልቁኑ ዴሞክራሲ መብታቸዉን ተጠቅመዉ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት የሚመላለሱበትን እንዲሁም አድሎ በደልግፍ ጭከና ወዘተ የሚፈጸምበትን የበለጠዉን ሥርዓት አዘጋጁላቸዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሌላዉ ጥያቄያችሁ ስለ ዴሞክራሲ ምንነትና መገለጫዉ ሲሆን ዴሞክራሲ ልክ እንደፖለቲካዉ እዉነታን ለመቃረንና ሰማያዊ ሥርዓትን ለመተካት ያዘጋጀሁት ልዩ ፍልስፍና ቋንቋዬ ነዉር ይህም መሪዎች ሆኑ ባለሥልጣናት እንዲሁም ካድሬዎች እንደ ዶግማና ቀኖና ተመልክተዉት ኅሊናቸዉን የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተግባር ለመፈጸምና ለማስፈጸም አእንዲቀበለዉ በርዕዮተ ዓለም መልኩ ያዘጋጀዉላቸዉ ሲሆን ዉጤቱም ሕዝቡ በሙሉ ነጻነቱ ተጠቅሞ ከፈለገ «አግዚአብሔር የለም» ከፈለገ «እግዚአብሔር አለ» ብሎ በክፋት በተንኮል በምቀኝነት በትዕቢት በዓመጻ በዝሙት በግብረ ሰዶም በዘፈን በዳንኪራ በጣዖትና ባዕድ አምልኮ በዘረኝነት በጎጠኝነት በአስማት በጥንቆላ በመተት ወዘተ ሕይወት ዉስጥ ምንም ሳይፈራና ሳይሸማቀቅ እንዲመላለስ በማድረግ ለታላቅ ክብር ለማብቃት በማሰብ ነዉ በበላይ ሆፔ ዴሞክራሲ ሥርዓት የዘረጋዉላችሁ ታዲያ ይህን የተጎናጸፋችሁትን ዴሞክራሲ መብታችሁን ለመገደብና ብሉም ለማስቀረት ሰማያዊ ሥርዓት ናፋቂዎችን አንዳች እንዳትቀበሉ እንዳትሰሙ እነሱ ከዚህ ከሚጣፍጠዉ ሕይወት ሊለያችሁና እግዚአብሔርን በመፍራትና በማስደሰት እንድትኖሩ አድርገዉ ከስስት ከስግብግብነት ከራስ ወዳድነት ሕይወት ለይተዉ በመተሳሰብመረዳዳት በመተዛዘን እንድትኖሩና ሕይወታችሁም በቅድስና እንድትመላለስ ሊያደርጉ ስለሆነ አንዳች እንዳትሰሟቸዉ የሚሉትንም እንዳትፈጽሙ ይልቁኑ ሌት ተቀን ኮንደሙን በቴሌቨዥንና በሬድዮን በስብሰባ እያስተዋወቃችሁ ዝሙትን አስፋፉ ከሕፃን እስከ አዋቂዉ ድረስ ነፍሱን በማሳበድ ሌት ተቀን በዘፈኑና በዳንኪራዉ አስጨፍሩት በተለያዩ ትዕይንቶችና ወሬዎች ኅሊናዉን አደንዝዙ ብቻ ምን እኔ እነግራችኋለሁ እናንተ ከእኔ በላይ ሕዝቡ ማድረግ ያለበትን ታዉቃላችሁና እንደማሳስባችሁና እንደምመራችሁ ሁሉን አስፈጽሙልኝ ለጠቅላላ አዉቀት ስለ ፖለቲካና ዴሞክራሲ የዚህን ያህል ካልኳችሁ ለወደፊቱ በዋናዉ መንግሥታችን የበለጠ ማብራሪያ አንደምሰጣችሁ በጨለማዉ ስሜ ቃል አገባላችኋለሁ ዋናዉ ለዚያ መንግሥት ያብቃችሁ እላለሁ እናንተ ኢትዮጵያዉያን ተራማጅ ኃይሎች የሶሻሊስት የአብዮታዊ ዲሞክራሲ የካፒታሊስት የኢምፔሪያሊስት ወዘተ እግዚአብሔር የለሽ ሥርዓቶችን ለመቀበልና አዉሮፓዊ አሜሪካዊ ኤሽያዊ አረባዊ ሥርዓት ለመዘርጋት ወደ ኋላ የማትሉ የራሳችሁን ኢትዮጵያዊ ሥርዓት ለመዘርጋት ፈቃደኛ ያልሆናችሁ ስለተራማጅ አስተሳሰባችሁና እንደማንነታችሁ ለመሆን አለመፈለጋችሁ ያለኝን አድናቆት እኔ የጨለማዉ ገዥ ልገልጽላችሁ አወዳለሁ ለወደፊትም በምንም መልኩ ቤተ ሕዝቡ ቤተ ክህነቱ ቤተ ምልክናዉ አንድ ሆነዉ በሚመሩበት የእግዚአብሔር መንግሥት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሥርዓት እንዳትዘረጉ ከዘረጋችሁ ግን ከእኔ መንግሥት የምትለዩና የፈለጋችሁትን የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተግባር መፈጸም እንደማትችሉ አሁኑን እንድታዉቁ እፈልጋለሁ በዚህም ምክንያት ኃጢአትን ማንገስ ስለማትችሉ የእግዚአብሔር ባሪያ ሆናችሁ የምትቀሩና የአኔን የጨለማ መንግሥት ማግኘት ተስኗችሁ ሰማያዊ መንግሥት ልትገቡ እንደምትችሉ አዉቃችሁ ከእኔ እንዳትለዩ አስከመጨረሻዉ አንድነታችሁንና ኅብረታችሁን ለአፄ ብቻ መግለጽ ይጠበቅባችኋል ያፄ ከአንዱ ወደ አንዱ ወንበር አሸጋግራችኋለሁ ኅሊናችሁን በምታገለባብጡት ብቃት ደረጃ እኔም በዚያኑ ልክ እያገለባበጥኩ ወደፈለጋችሁት ወንበር አደርሳችኋለሁ ታዲያ በእኔ ታቃራኒ መንፈስ የሚመሩ ኢትዮጵያ የአግዚአብሔር መንግሥት ናት እያሉ ስለ ሰባቱ ቅዱሳት ኪዳናት የሚናገሩትን አትስሙ የእናንተ የኢትዮጵያ ታሪክ እንኳን ድድጽ አይደለም ቋ እንኳ አይሆንም ምርጥ እንደራሴዎቼ መሪዎቻችሁና ባለሟሎቼ ባለሥልጣናት እንዲሁም ዉዶቼን ካድሬዎች መጠየቅ ትችላላችሁ በአስተያየት የአንድ መቶ ዓመት ታሪክ አላችሁ ቢባልም ዋናዉ ታሪካችሁ የጀመረዉ በአዲሲቷ ኢትዮጵያ ዘመን ስለሆነ ታሪካችሁ ገና ፃያ ዓመትን አስቆጥሯል እናንተ የአዳም ዘሮች አኔ የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ አንደ እናንተዉ ሕያዉ የሆንኩ ፍጥረት ነኝ እንደእናንተዉ የማልሞት ከመኖር ወደ አለመኖር የማላልፍ እንደ እናንተዉ የሚያስብ ኅሊና ያለኝ ዘመዳችሁ ነኝ ታዲያ እኔ የሚያስገርሙኝና የሚያስደንቁኝ ጥያቄዎች ሁሉ ጊዜ በኅሊናዬ ይመላለሳሉ ለምሳሌ ያህል እኔ ምን አድርጌላችሁ ነዉ ሌት ተቀን እኔ የጨለማዉ ገዥ ደስ በምሰኝበት ሕይወት የምትመላለሱት። » በማለት ለጠየቃችሁት እናንተ እንዳላችሁት ፈጣሪ አንድ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ነዉ አሱም ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበትም ጊዜ የማይኖር ፍጥረታትን ሁሉ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ከፈለገም በዓይን ቅጽበት ዉስጥ ከመኖር ወደ አለመኖር ማሳለፍ የሚችል እንዲሁም አሁን ከሚታየዉ ፍጥረታት በእልፍ አአላፋት እጥፍ ካለመኖር ወደ መኖር ማምጣት የሚችል ምንም የማይሳነዉ ሁሉ በኃይሉ ስለተፈጠረ ኃይሉ ደግሞ በእርሱ ቁጥጥር ዉስጥ በመሆኑ ሳያዉቀዉና ሳይፈቅደዉ አንዳች ነገር ሊሆን የማይችልና አንዳችም ማድረግ የማይቻል መጀመሪያና መጨረሻ በሌለዉ አማናዊ ሕዋ ዉስጥ እንደ አማናዊ ባሕርይዉ ያለ በሰማያት ዉስጥ በአልፍ አአላፋት ወትአእልፊት ቅዱሳን መላአክት በብርፃናዊ ባሕርይዉ የሚመለክ ባጠቃላይ አሱን ለመግለጽ የምንችልበት አንደበትና ቃላት የሌለን ኃያል ገናና ርኅሩኅ ደግ አፍቃሪ አምላክ ነዉ ታዲያ ይህ እዉነተኛ አምላክና አባታችን ሊታወቅ ሆነ ልንረዳዉ የምንችለዉ በእዉነትና በመንፈስ ስናመልከዉ በስራችን በንግግራችንና በሓሳባችን ጭምር እሱን በመፍራት ስንመላለስ በትህትናና በፍቅር ሆነን ፈቃዱን ስንፈጽምና ስናስፈጽም ብቻ ነዉ ያለዉ እዉነታ ደግሞ ተቃራኒ ነዉ ይኸዉም እጅግ ብዙዎቻችን አምልኮታችን በዘልማድ ነዉ እንጂ በሚያመዛዝነዉና በሚያገናዝበዉ ኅሊናችን ተመርተን በእዉነትና በእምነት አናመልከዉም በዚህም ምክንያት የተለያዩ ሃይማኖቶችና አምልኮዎች ሊፈጠሩ ችሏል እልፍ አእላፋት ወትአልፊት መላእክት ሲፈጠሩ የነበረ አዳምና ሔዋን ሲፈጠሩ የነበረ በብሉይ ዘመን በኪዳነ ልቦናን በኪዳነ ኦሪት ይመለክ የነበረ አሁን በሐዲስ ዘመን ደግሞ በኪዳነ ወንጌል የሚመለከዉ ያዉ የነበረዉ ያለዉ የሚኖረዉ ሕያዉ አግዚአብሔር አንዱ አምላክ ነዉ የእናንተ ሙስሊሞች ሆነ የእኛ ክርስቲያኖች ፈጣሪ አንድ ብቻ ነዉ እሱም «አዶናይ ኤልሻዳይ ያህዌህ ጸባዎት» በመባል የሚታወቀዉ የአብርዛም የይስሐቅ የያዕቆብ አምላክ ነዉ ይሁንና ሰዎች በራሳቸዉ ሥጋና ደም ሓሳብ ተመርተዉ በፈጠሩት ዛይማኖት ስያሜ ይኸዉ ለዘመናት ተለያይተን እአእንገኛለን እናንተ ግን በቅንነት በየዋህነት በግልጽነት ተነሳስታችሁ ልዩነቱን ለማወቅ በመነሳታችሁ እግዚአብሔር የዋህና ቅን ልቦናችሁን ተመልክቶ አዉነቱን ሊያሳዉቃችሁ እንደወደደ አምናለሁ እኔም እዉነቱን ፍርጥርጥ አድርጌ እነግራችኋለሁ እንኳን እናንተ የምታመልኩት አምላክና እኛ የምናመልከዉ አምላክ አንድ ዓይነት ሊሆን ቀርቶ ክርስቲያኖች የምንባባለዉ እንኳ የምናመልከዉ አምላክ ይለያያል ይኸዉም ለምሳሌ «ፕሮቴስታንት» የሚባሉት በክርስትና ስም የሚጠሩት አጅግ ብዙ የተከፋፈሉ የአምነት ድርጅቶች ሳታዉቁና ሳትሰሙ አይቀርም ባገራችን እንኳ በአብዛኛዉ ኅብረተሰብ «ጴንጤ» ነዉ የሚባሉት በዓለም ዉስጥ በአስራ ሺህ ስም ይታወቃሉ ታዲያ ብዙዎቹ ክርስቲያን የሚለዉን ስያሜ ነዉ የሚጠቀሙት ነገር ግን እነሱ የሚያመልኩት አምላክና እኛ የኢትዮጵያ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ተዋሕዶ ዛይማኖት ተከተያ ክርስቲያኖች አምላክ የሰማይና የመሬት ያህል ልዩነት አለዉ ብዙዎች ግን በክርስትና ስም ስለሚጠሩ አንድ ዓይነት ይመስላቸዋል እኛ የምናመልከዉ አምላክ ቀደም ብዬ የጠቀስኩላችሁ ፈጣሪ ያልኳችሁ የመልከጴጹዴቅ የአብርፃም የሙሴ የነቢያት የሐዋርያት የሰማዕታት የጻድቃን አምላክ ነዉ ይህ አምላክ በብሉይ ዘመን በተለያየ መልኩ ሲመለክ ሲገለጽ የነበረ ነቢያትንና መምህራንን እያስነሳ ሕዝቡን ያስተምር ሲያጠፉም ይንገስጽ ነበር አዳምና ሔዋን በዓመጻቸዉ ምክንያት ይኸዉም አትብሉት የተባሉትን ፍሬ የሰይጣንን ክፉና ሐሰት ምክር ሰምተዉ በመብላታቸዉ ምክንያት ከገነት ተባረዉ ወደዚህች ሰይጣናት መኖሪያና መቀጫ ምድር ሲገቡ እዉነተኛ ንስሐ ስለገቡና በዓመጻቸዉም አጅግ ስለተጸጸቱ አንዲሁም እኛ ልጆቻቸዉ ባላወቅነዉና ባልፈጸምነዉ ዓመጻ በእነሱ ምክንያት የዚህች ምድርና የሲኦል ቅጣት ስለተፈረደብን እያንዳንዱ የአዳምና ሔዋን ዘር በነጻ ኅሊናዉ በሚፈጽመዉ እዉነተኛ አምልኮና መልካም ምግባር ያጣዉን መንግሥት ገነትን እንዲሁም ከፍርድ ቀን በኋላ መንግሥተ ሰማያትን እንዲወርስ ለማስቻል አዳምን «ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንፃለዉ ባለዉ ቃል ኪዳን መሰረት ያ ሁሉን በራሱ ሥልጣን ማድረግ የሚችለዉ ምንም የማይሳነዉ የሁሉ ፈጣሪ አምላክ የሆነዉ እግዚአብሔር መጀመሪያና መጨረሻ በሌለዉ አማናዊ ሕዋ ዉስጥ ሳይጎል ከሰማያት ዉስጥ ሳይጎል ከዓለም መግቦቱ ሳይጎል እንዲሁም ፍጥረታቱን ከመቆጣጠርና ከመጠበቅ ሳይለይ መለኮታዊ ባሕርይዉን ብቻ ዝቅ አድርጎ አዳምና ሔዋን ንስሐ በገቡበት ወቅት የሰዎች ነፍስ በዚህች ምድር ዉስጥ ካሉት ሰይጣናት ቁጥር አኩል እስከሚሆን ድረስ አስቀድመዉ በአዳምና ሔዋን ምሳሌያዊ ባሕርይ ግንኙነት አማካይነት እንዲወለዱ በእግዚአብሔር እቅድ ዉስጥ የነበሩ ነፍሳት በቅጽበት ከባሕርይዉ አስርጾ ካለመኖር ወደ መኖር በማምጣት በራሳቸዉ ህልዉና በነጻ ኅሊናቸዉ በዚያች ቅጽበት ዉስጥ ያሳዩትን የአምነት ብቃት በባሕርይዉ ተመልክቶና አዉቆ እጅግ የብቃት ቅድስናና እምነት የታየባት አንዲት ነፍስ ተመልክቶ አዳምን «አሷ ስትወለድ ሰዉ ሆፔጌ አድንዛለዉ ብሎ ቃል በገባለት መሰረት ያቺ የበቃች ነፍስ ሰዉ ሆና ተወልዳ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ መላኩን ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ የእግዚአብሔር ልጅ የተባለዉን ኢየሱስ ክርስቶስን በድንግልና ጸንሳ እንደምትወልድ ተነግሯት ባመነች ጊዜ ያ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለዉ መለኮት ባሕርይዉን ወስኖ ከእመቤታችን ከአደራ እናታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽህይተ ንጹሃፃን ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ በመሆን በተዋሕዶ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰዉ ሆኖ ተወልዶ የተለያዩ ተአምራትንና ፈዉስን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አድርጎ በመጨረሻም የተለያየ ጸዋትዎ መከራ ተቀብሎ በመስቀል ላይ የተሰቀለዉን አምላክ ነዉ የምናመልከዉ ይህ አዉነተኛ ፈጣሪ አምላክ ነዉ አኛ ሥላሴ ወይንም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በመባል የሚታወቁትን በመለኮት በህልዉና በአገዛዝ በመፍጠር ባጠቃላይ በባሕርይ አንድ የሆነዉን በስም በአካል በግብር ሦስት የሆነዉን የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት በግልጽ ያሳወቀን ታዲያ የእናንተ ሄፃይማኖት መስራች የሆነዉ «ነቢያችን» የምትሉት መሐመድ ይህ ምሥጢር ስለረቀቀበት ነዉ «እግዚአብሔር አይወርድም አይወለድም» ብሎ ያስተማረዉና በዓለም ላይ ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብ በትዉልዱ ኅሊና እንዲሰርጽ ያደረገዉ እናንተ ከቅርቦቹ አባቶቻችሁና እናቶቻችሁ በወረሳችሁት ዛይማኖት አስተሳሰብ እምነት ያላችሁ ሲሆን አኔ የሚገርመኝና የሚያሳዝነኝ በመጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ በግልጽ ኢየሱስ ክርስቶስ አግዚአብሔር አምላክ አልፋና ዖሜጋ ፈጣሪ መጀመሪያዉና መጨረሻዉ ሁሉ በእርሱ ለእርሱ መሆኑን እያነበቡ መጽሐፍ ቅዱስ ነዉ መመሪያችን» እያሉ ይህን እዉነተኛ አምላክ «አማላጅ ነዉ ፍጡር ነዉ የሚሉት የተለያዩ የፕሮቴስታን አምነት ድርጅቶች አባላት ናቸዉ አብዛኛዎቹም ከእዉነተኛዉ ፃይማኖታቸዉ «ኢየሱስ ክርስቶስን ተማላጅ ዳኛ ፈራጅ ፈጣሪ ነዉ ብላ ከምታስተምረዉ ከኢትዮጵያ ተዋሕዶ ዛይማኖት ኮብልለዉ የወጡ ናቸዉ ለዚህም ነዉ ድርጊታቸዉ አስገራሚና አሳዛኝ ነዉ ያልኩት ከእርሱ በላይ አሱን የሚያዝ አምላክ የለም ከእርሱ ጋር የሚስተካከሉትና በመለኮታዊ ባሕርይ አንድ የሆኑትን አብና መንፈስ ቅዱስ በመባል የሚታወቁትን ሁለት አካላት እርሱ ወልድ በመባል የሚታወቀዉ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ነዉ በሥጋ ተገልጦ ያስተዋወቀን ከነዚህ ሦስት አካላት ዉጭ ያሉት ሁሉ የአነሱ ፍጥረቶች ናቸዉ የፕሮቴስታንቱ እምነት ልክ እናንተ «ኢሳ ኢየሱስ እግዚአብሔር ሳይሆን ነቢይ ፍጡር ነዉ እንደምትሉ እነሱም «የእግዚአብሔር መልአክተኛ ፍጡር ነዉ አማላጅ ነዉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድ ንታ ነዉ ወዘተ» የሚል ስያሜ ነዉ የሚሰጡት ስለዚህ «መልእክተኛም አማላጅ ጌታ ነዉ ፍጡር ነዉ። እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ ድረስ አምላኩን አስደስቷልፎ በዚህም ምክንያት «እንደ ልቤ» ተባለ የጽድቅና የቅድስና ማዕረግ አገኘ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በአሁን ትዉልድ ቢሆን ኖሮ አስተሳሰባችን ሰይጣናዊ ስለሆነና እንደ አግዚአብሔር ስላልሆነ በነቢዩ በንጉሥ ዳዊት ሕይወት ላይ የስም ማጥፋትና ዉንጀላ ነበር የምናደርገዉ አንጂ ከዉድቀቱ በእዉነተኛ ንስሐ መነሳቱንና እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ አምላኩን ደስ አሰኝቶ ጻድቅና ቅዱስ መባሉን አንመሰክርም ምክንያቱ እንኳን እንዲህ የገዘፈ ኃጢአት በሰዉ ላይ ተገኝቶ አይደለም የሰዎችን እንከን እየፈለግንና ቃላት እየሰነጠቅን ቅኖችንና አዉነተኛ ሰዎችን የምንወነጅል ስለሆነ ነዉ በሌላ በኩል ደግሞ እንኳን የንጉሥን ገበና እንዲህ ለመማማሪያ በጽሑፍ ማዉጣት ቀርቶ በአንደበት እንኳ ሰዎች አይናገሩም ኃጢአቱ አንኳ ተፈጽሞ በዓለም ቢታወቅ አንኳ ምንም በማያዉቀዉ ሰዉ ይላከካል በሐሰት ምስኪኑ ይወነጀላል እንጂ «ንጉሥ ሆይ እግዚአብሔር የማይወደዉን ተግባር ፈጽማዛል» ብሎ የሚገስጽ እዉነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋይ በአሁን ጊዜ ያለ አይመስለኝም ይልቁን በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ተግባርህ በርታ ከጎንህ አለን አስፈጻሚዎችህ ነን» በማለት የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተባባሪ ነዉ የሚሆኑት ከላይ ከተገለጹት የምንረዳዉ እግዚአብሔር አዉነተኛ ፍርድ እምደሚሰጥና እዉነተኛ ንስሐ ለሚገቡትም ፍጹም ይቅርታ እንደሚያደርግና ለታላቅ ክብር እንደሚያበቃ ነዉ ስለዚህ እናንተ ለጥላቻና ለበቀል የሚያነሳሳዉ ያ ክፉ ጠላት ዲያብሎስ መሆኑን አዉቃችሁ እግዚአብሔር ይበቀል ይፍረድ እንጂ እንኳን የቅርብ ወገኖቻችሁን ኢትዮጵያዉያንን አይደለም ሌሎች ወገኖቻችሁ የአዳምና ሔዋን ዘሮች ላይ ለበቀል መነሳሳት የለባችሁም ሌላዉ የምመክራችሁ ያላየነዉን ትዉልድ የዱሮዉን እያነሱ አርስ በእርስ ተፋቅረንና በአንድነት ከመኖር ይልቅ እንድንጣላ እንድንገዳደል እንድንበቃቀል እንድንከፋፈል የሚያደርጉ ሰዎች መሪያቸዉ መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን ርኩስ መንፈስ መሆኑን ልናዉቅ ይገባል ዱሮ ሰዎች በነበራቸዉ አስተሳሰብና ንቃተ ኅሊና እርስ በእርስ ተጣልተዉ ተገዳድለዉ ተበቃቅለዉ ሊሆን ይችላል ከአምላክም እዉነተኛ ፍርድ እንደተቀበሉ ምንም ጥርጥር የለዉም ስለአዉነት ብቻ መከራን የተቀበሉ የተገደሉ በአግዚአብሔር ዘንድ ትልቅ ቦታ እንደሚጠብቃቸዉና ግፈኞችና ዓመጸኞች አጅግ የባሰ ፍርድ ዉስጥ እንደሚገኙ በአምነት ለምንመላለስ የታወቀ ነዉ በምድራዊ ዘመናችን ዉስጥ በዓመጻና በክህደት ሕይወት ዉስጥ ለተመላለሱና ለሚመላሰሱ ሰዎች ዘመዴ ዘሬ ጎጤ ባለዉለታዬ በሚል ስሜት ለግለሰቦች ክብርና ዝና ጥብቅና መቆም የለብንም ሁሌም ስለአዉነት ነዉ ልንመሰክር የሚገባዉ እንጂ በቅንነትና በእዉነተኛነት ተመርቶ እንኳን የሌላ ሰዉ የራሳችንን ገበና ድክመት ስህተት ቢጋለጥብንና ቢነገረን ትምህርት ልንወስድበትና ልንታረምበት ልንስተካከልበት ይገባል «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሌላዉ ማወቅ ያለባችሁ እግዚአብሔር በእዉነት ለሚገዛለት ትዉልድ ሕዝብ መልካም እረኛ ይሰጠዋል በተቃራኒዉ ለዓመጸኛና ለከሃዲ ትዉልድ የሚቀጣዉ ጨካኝና ከሃዲ መሪ ይሰጠዋል ይህም የሚሳየዉ አግዚአብሔር ለሕዝቡ አንደምርጫዉና ፍላጎቱ ነዉ የሚሰጠዉ ጥቂት እዉነተኞች ተገኝተዉ በቅንነትና በእዉነት እግዚአብሔርን በመፍራት የሚመላለሱ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ የሚፈጽሙ የሚያስፈጽሙ መልካም እረኛ እግዚአብሔር እንዲሰጣቸዉ ከጠየቁ ስለ አነሱ ሲል ከመዛከላቸዉ መልካም እረኛ አስነስቶ ለእዉነተኛ አገልግሎት ይሾምላቸዋል ስለዚህ እናንተም ሆናችሁ እኛ ፈጣሪ አምላካችን አንድ ስለሆነ ያ አዉነተኛ አምላክ የእርሱ የሆነዉን መንግሥት እንዲሰጠንና የእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ እንዲፈጸም ልንጸልይና ሁሉን ለእርሱ አሳልፈን መስጠት ይጠበቅብናል እንጂ በሰይፍና በጦር መሳሪያ የሚመጣ መንግሥት በዚያዉ በመጣበት ሰይፍና ጦር መሳሪያ እንዲሁም በእግዚአብሔር ቁጣ ስለሚወገድ እደዚህ ዓይነቱን መንግሥት በምንም ሁኔታ መጠበቅ የለብንም እግዚአብሔር ፈቃዱ ከሆነ በአንድ ጊዜ የዓመጻ ልጆችን እንዳልነበሩ አድርጎ ሰማያዊ ሥርዓት ሊዘረጋ ይችላል በመሆኑም አሁን እንደምናየዉ በጦር መሳሪያ ተመክተዉና ሕዝቡን አስፈራርተዉ በደኀንነት እያሰለሉና በካድሬዎቻቸዉ ቅስቀሳ እያደረጉ ለይስሙላ በካርድ ተመረጥን ለማለት በሥጋዊ ምርጫ የሚመሩትን ተከትለን እኛም የእነሱ አጫፋሪና አጃቢ ከሆን በተዝዋዋሪ «እግዚአብሔር ሆይ እኛ የምንፈልገዉ የዲያብሎስን ሥርዓት ነዉ የምንመርጠዉም የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ስራ አስፈጻሚዎችን ነዉ እነሱ ይንገሠብን የአንተን ንግሥና አንፈልግም ማለታችን እንደሆነ ሊገባን ይገባል ወደ ሰማያዊዉና አሁን ወዳለንበት እዉነታ ስንመጣ ደግሞ እግዚአብሔር የሚወደዉ እርስ በእርስ ለምንቀያየምበት ለምንጣላበት ይቅር ተባብለን ከጥላቻና ከበቀል ሕይወት ስንወጣ ነዉና የበደልነዉን ክስን የተበደልን ይቅር ብለን ተሳስበን ተቻችለን ተፋቅረን ስንኖር ነዉ ከዚያ ዉጭ «ባለ ጊዜና ባለ ወንበር ነኝ» በሚል ስሜት በደልና ግፍ አድሎና በቀል የምንፈጽም ከሆነ በዚህ ምድር ላይ ሳይቀር ዋጋ እንከፍልበታለን እንኳን መግደልና ግፍ መፈጸም አይደለም አንድ ወገናችንን በድህነቱና ችግሩ ምክንያት «አንተ ደህ መናጢ ቡቱታም ጨርቃም» ብለን ብንሰድበዉ ለዚሁ ንቀትና ትምክህት ስድባችን ወደ ምድራዊ ፍርድ ቤት ቀርበን ሊፈረድብን እንደሚገባ ነዉ ቃሉ የሚያስተምረን እንዲሁም እንኳን በተግባር በወገናችን ላይ የምንፈጽመዉ የኃጢአት ተግባር አይደለም እኛ እንደቀላል የምንቆጥረዉ ስድብ አንድ ምንም የማይሰማ ደንቆሮን አይሰማም ብለን ደንቆሮ» ብለን ብንሰድበዉና አንድ ዓይነ ስዉር አያይም ብለን የማይገባ ነገር ብናደርግበት ወይንም ብናሾፍበት ፈጣሪን እንደሰደብንና እንዳቃለልን ስለሚቆጠር ይኸዉም እነሱ ባይሰሙና ባይመለከቱ እግዚአብሔር ሆነ ሌላ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሰዉ ይሰማል ይመለከታልና እንዲህ ያደረጉ ደግሞ በምድራዊ ፍርድ ብቻ የሚታለፉ ሳይሆኑ እዉነተኛ ንስሐ ካልገቡ የገፃነመ እሳት ፍርድ እንደሚጠብቃቸዉ ነዉ ቃሉ የሚያስረዳን ይህም የሚያሳየዉ የእግዚአብሔር ፍርድ በምድርም በሰማይም ምን ያህል ጥብቅ መሆኑን ነዉ በዚህ ምድርም በወገኑ ላይ ኢሰብአዊ ተግባር የሚፈጽም ሰዉ ሆነ አግባብ የሆኑ ሕጎችን የሚጥስ በምድራዊ ፍርድ ወንበር ቀርቦ እስርና የተለያየ ቅጣት እንደሚደርስበት ይታወቃል በእግዚአብ ንድ ደግሞ እንኳን በተግባር ለሚፈጸም አት ሆነ ወንጀል አይደለም በንግግርና በሓሳብ የሚፈጸም ኃጢአት ያስጠይቃል በምድራዊ ሕይወታችን ቆይታ በተግባራችን በንግግራችን በሓሳባችን ጭምር እግዚአብሔርን በመፍራት የምንመላለስ ከሆነ በምድራዊ ሕግ ሆነ በሰማያዊ ፍርድ አንጠየቅም ምናልባት «ኅሊናችንን አንበጥም የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተግባር ተባባሪና አስፈጻሚ አንሆንም» በማለታችን በሐሰት ብንወነጀል እንኳ በእግዚአብሔር ዘንድ ለታላቅ ክብር የምንበቃበትና ዋጋ የምናገኝበት ይሆናል እንጂ በነፍሳችን አንዳች አንጎዳበትም ሌላዉ ስለ አዉነት በመመስከራችሁና ከነፈሰዉ ጋር አንነፍስምእንደ ቦይ ዉፃ አንነዳም ከእዉነት ጋር ነዉ አንድነትና ኅብረት ያለን» በማለታችሁ ፈተና ችግር እስር ግድያ ቢመጣባችሁ የሚታደጋችሁና የሚጠብቃችሁ የእዉነት አምላክ ስለሆነ እስከ መጨረሻዉ ስለ እዉነት መጽናት አለባችሁ እንጂ ግፈኞችንና ሐሰተኞችን ፈርታችሁ የዓመጻና የሐሰት ተባባሪ ከሆናችሁ እነዚያ የፈራችዋቸዉ መሪዎችና ባለሥልጣናት አንዲሁም ካድሬዎች የዓመጻ ጽዋቸዉ ሲሞላ አግዚአብሔር በቁጣዉ አንዳልነበሩ ስለሚያደርጋቸዉ እናንተም ሰለተባባሪነታችሁና ስለአስፈጻሚነታችሁ በምድርም በሰማይም ዋጋ መክፈላችሁ አይቀርም ስለዚህ በምድርም በሰማይም ዋጋ እንድታገኙ እስከ ዕለተ ሞታችሁ ሕያዉ ነፍሳችሁ ከዚህ ከተገለጻችሁበት ሥጋ እስከምትለይ ድረስ አንድነታችሁና ኅብረታችሁ ከእዉነት አምላክ ጋር ብቻ ማድረግና እግዚአብሔርን በመፍራት ልትመላለሱ ይገባል በዚሁ አጋጣም ስለተለያዩ የሰዉ ልጆች ባሕርይና ጠባይ ልንገራችሁ በዚህ ምድር ዉስጥ አምስት የተለያየ ጠባይ ያላቸዉ ሰዎች አሉ የመጀመሪያዎቹ አንደማንኛዉም ሰዉ በሥጋ የተገለጽና በነጻ ኅሊናቸዉ ተመርተዉ መልካም ሆነ መጥፎ የመስራት ሙሉ ፈቃድና ነጻነት ያላቸዉ ሲሆን ነገር ግን ነጻ ኅሊናቸዉንና ፈቃዳቸዉን ለትዕፅቢት ለክህደት ለዓመጻ የሚያዉሉ ዓይነታቸዉ ሦስት የሆነ ነዉ ሀ ትፅቢት የተባለዉ ሰዉ ፈርኦንን የሚመራዉ የነበረ ርኩስ መንፈስ ሰይጣናት የሚመራቸዉ ዉስጣቸዉ ትዕቢት የተሞላ ሰዎች ናቸዉ እነዚህ ሰዎች «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በኃይላቸዉ በአዉቀታቸዉ በሀብታቸዉ በሥልጣናቸዉ ስለሚመኩ እግዚአብሔር መፍራት በዉስጣቸዉ አንዳች የሌለባቸዉ ልበደንዳናና ዕብሪተኛ ናቸዉ ለ ክፋት የተባለዉ ሰዉ ይሁዳን ይመራዉ የነበረ ርኩስ መንፈስ ሰይጣናት የሚመራቸዉ ዉስጣቸዉ ክፋትና ተንኮል ምቀኝነት የሞላባቸዉ ሌት ተቀን ለራሳቸዉ ጥቅም ብቻ የቆቁሙ ጥቅማቸዉን ለማግኘት ሰዎችን በሐሰት በተንኮል በክፋት በምቀኝነት ለማጥፋት ሆነ ግፍ ለመፈጸም አንዲሁም በደል ለማድረስ ወደ ኋላ የማይሉ ኅሊናቸዉ እንኳ ስህተታቸዉን ቢመሰክርባቸዉ የማይሰሙትና የማይቀበሉት ኅሊናቸዉን ያደነደኑ ሰዎች ናቸዉ ሒ ዓመጻ የተባለዉ ሰዉ አርዮስን ይመራዉ የነበረ ርኩስ መንፈስ ሰይጣናት የሚመራቸዉ ዉስጣቸዉ ለራሳቸዉ ሥጋና ደም ስሜት ተግባርና እምነት የቆመ ከአግዚአብሔር የሆነዉን አዉነት ለመቀበል ፈቃደኛ የማይሆኑ ቢቀበሉት እንኳ «ጥቅም እናገኝበታለን በሚል እምነት እንጂ ከኅሊናቸዉ አምነዉበት የማይቀበሉ ባገኙት አጋጣሚ ለራሳቸዉ ዓመጻ ስራ የሚነሳሱ በሥጋና ደም ስሜታቸዉ ብቻ የሚንቀሳቀሱና በደመ ነፍሳቸዉ የሚመሩ ሰዎች ናቸዉ ሁለተኛዎቹ ሰዎች አእምሮ ቀላል የሚባሉት ናቸዉ እነዚህ ሰዎች በአብዛኛዉ ጊዜ ኅሊናቸዉን ለመገለባበጥ ወደ ኋላ የማይሉ በሥጋና ደም ስሜታቸዉ የሚመሩ ለጥቅማቸዉ ሲሉ የዲያብሎስ ፈቃድ የሚያስፈጽሙና የሚፈጽሙ ሥጋዉያን መሪዎችንና ባለሥልጣናትን ተከትለዉ «አድርጉ ፈጽሙ የሚሏቸዉን ሁሉ ሰዉን አእሰከመግደልና አእሰከማሰቃየት የሚደርሱ ሆዳቸዉና ጥቅማቸዉ አምላካቸዉ የሆነ ከነፈሰዉ ጋር የሚነፍሱ እንደ ቦይ ዉኃ ወደወሰዷቸዉ የሚሄዱ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት የሚመላለሱ ሰዎች ናቸዉ ሦስተኛዉ ሰዎች አእምሮ ሕፃን የሚባሉ ናቸዉ እነዚህ በሥጋቸዉ አዋቂዎች ቢሆኑም ራሳቸዉን በሚገባ ያልገዙ የሥጋና የደም ስሜታቸዉ የሚያይልባቸዉና የሚያሸንፋቸዉ ነዉ ኅሊናቸዉ እዉነትን ቢያዉቅና ቢመርጥም ፈተናዉን ችግሩን በጽናት ለማሳለፍ ራሳቸዉን የማያዘጋጁ ቆራጥነት የሚጎላቸዉ ሰዎች ናቸዉ በዚህም ምክንያት በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት ለጥቅማቸዉ ሲሉ ለመመላለስ ወደ ኋላ የማይሉ ናቸዉ አራተኛዉ ሰዎች አአምሮ አዋቂዎች የሚባሉ ናቸዉ እነዚህ ሥጋዊ ሆነ መንፈሳዊ ትምህርት ቢማሩም ባይማሩም ነገሮችን በሚገባ የማስተዋልና የማመዛዘን ችሎታ ያላቸዉ ሁሉ በትክክል ቢመራ የሚመርጡ ሲሆን ነገር ግን ትክክል ያልሆነዉን «ትክክል አይደለም የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተግባር ነዉ» ለማለት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የማይደፍሩ ስለ እዉነት ራሳቸዉን መካድ የማይፈልጉ ቆራጥነትና ጽናት የሚጎላቸዉ ኑሮ በመመሳሰል የሚለዉን ፈሊጥ የሚከተሉ ሰዎች ናቸዉ አምስተኛዉ ሰዉ አእምሮ ጽኑአን የሚባሉ ናቸዉ እነዚህ ትክክለኛዉንና አዉነቱን ማወቅ ብቻ አይደለም ሰዎች ሁሉ በትክክለኛዉ መንገድ እንዲፄዱ የሚፈልጉና ለዚያም ማንኛዉን ዋጋ ለመክፈል ቆራጦች የሆኑ ራሳቸዉንም ለመካድ የማይከብዳቸዉ ኅሊናቸዉን በቀላሉ ለመገለባበጥ የማይቻል ያላመነበትንና ያልተቀበሉትን በተጽህኖ ሆነ በግዳጅ እንዲቀበሉ ቢደረግ ለመቀበል ፈቃደኛ የማይሆኑ ስለ እዉነት ማንኛዉንም ችግርና መከራ ለመቀበል ዝግጁ የሆኑ እስከ ሞት ድረስ ራሳቸዉን አሳልፈዉ የሚሰጡ ለእግዚአብሔር አገልግሎት ምቹ የሆኑ ሰዎች ናቸዉ ስለዚህ በዚህ በተለያየ ዓይነት ሰዎች የተሞላች ምድር አግባብ የሆነ ሕግና ሥርዓት ለሰዉ ልጆች ያስፈልጋል ማንም ሰዉ ኃይል ጉልበት ሥልጣን ሀብት ወገን ዘመድ አለኝ ብሎ ሌላዉን መጉዳትና ማጥቃት የማይችልበት አንዲሁም በተቃራኒዉ ሌላዉ ሰዉ ኃይል ጉልበት ሥልጣን ሀብት ወገን ዘመድ የለኝም ብሎ አድሎና በደል ግፍ ጥቃት እንዳይፈጸምበት ሁሉ ሰዉ በእኩልነት የሚመራበትና የሚዳኝበት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የተዘጋጀ ሕግና ሥርዓት ሊኖር ይገባል አሁን ያለዉ ሕግናሥርዓት የይስሙላና ለማስመሰል በሸዋጁ መንፈስ መሪነት የተዘጋጀ በወረቀት ላይ ነዉ የሰፈረዉ እንጂ ተግባራዊ የማይሆን ሰዎች ሥልጣናቸዉንና ኃይላቸዉን ተመክተዉ በፈለጉት ጊዜ የሚሽሩት የሚጠቅማቸዉ ከሆነ ደግም እንደፈለጉት አድርገዉ የሚጠቀሙበት ለመበቀልም ከፈለጉ ለራሳቸዉ እነደሚመች አድርገዉ የሚበቀሉበት ባጠቃላይ በሥጋና ደም ስሜት የተዘጋጀ ስለሆነ ሰዎች በሥጋና ደም ስሜታቸዉ ተግባራዊ የሚያደርጉት ለእዉነት ያልቆመ የእዉነታ ተቃራኒ በሆነዉ በፓለቲካ ስሜት የተዘጋጀ በተዝዋወሪ የዲያብሎስ ፈቃድ የሚፈጸምበት የእግዚአብሔር ሰማያዊ ሥርዓት ተቃራኒ የሆነዉ በዴሞክራሲ ሽፋን የተቀመረ የአምባገነኖች ሕግና ሥርዓትነዉ በዚህም ምክንያት እንኳን ለነፍሳችን አይደለም ለሥጋችን የማይጠቅም የአሕዛብ አግዚአብሔርን የማያምኑና የካዱ ሰዎች ስብስብ በዲያብሎስ መንፈስ መሪነት የተዘጋጀ ሕዝቡን ለማታለልና ኅሊናዉን ለማሸጥ አልፎ አልፎ ወርቃማ ቃላቶችና አባባሎች ያሉበት ነዉ በመሆኑን በትክክል ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ ቅንነትና አዉነተኛነት የተላበሱ ለምድራዊዉም ለሰማያዊዉም ሕይወት የሚጠቅሙ እግዚአብሔር የሚከብርበትና የሚመሰገንበት ሕግና መመሪያ እንዲሁም ሥርዓት ነዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የሚያስፈልገን እንጂ በአገር ዉስጥ ሆነ በዉጭዉ ዓለም ያለዉ የአሕዛብ ሕግናሥርዓት ወደ ሞትና መቀመቅ የሚወስደንና በሥጋችንም በነፍሳችንም የማንጠቀምበት ነዉ የአሕዛብን ሕገ መንግሥትና ሥርዓት እንደምናየዉ ሕዝቡ ከፈለገ ዲያብሎስን እንዲያመልክ ከፈለገም የተለያዩ አማልክት እንዲያመልክ ከፈለገም በባዕድና በጣዖት አምልኮ እንዲመላለስ የሚፈቅድ ራሱ መሪዉና ባለሥልጣናቱ ከእግዚአብሔር መቀባትንና መመረጥን የማይፈልጉ በተዝዋዋሪ የጨለማዉ ገዥን ፈቃድ የሚፈጽሙና የሚያስፈጽሙ በዲያብሎስ የተቀቡ ናቸዉ በእግዚአብሔር መንግሥት ግን ቤተ ሕዝቡ ቤተ ክህነቱ ቤተ ምልክናዉ በአንድላይ በመንፈስ ቅዱስ ስለሚመራ የእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ ነዉ ከታች እስከ ላይ የሚፈጸመዉ ከላይ እስከታች ያሉ የእግዚአብሔር እንደራሴዎችና የሕዝብ ጠባቂዎች የሕዝቡ አገልጋዮችና እረኞች ናቸዉ እንጂ በሕዝብ ስም እየነገዱ ሕዝቡን የሚያሰቃዩ የሚያጉላሉ ችግርና መከራ የሚያመጡበት ለእስራትና ለግድያ እንዲሁም ለስደት የሚዳርጉት አይደለም ራሳቸዉን በአምላክና በሕዝብ ፊት ዝቅ አድርገዉ በሥጋዉም በነፍሱም የሚጠቀምበትን ተግባር ለመፈጸምና ለማስፈጸም የሚተጉ ናቸዉ እንጂ ሕዝቡን የሚከፋፍሉ የሚለያዩ የሚያጣሉ ለጥላቻና ለበቀል ያሚያነሳሱ ዘረኝነትንና ጎጠኝነትን የሚያነግሥ ባዕድና ጣዖት አምልኮ የሚያስፋፉ የሕይወትን መንገድ አያጠፉ ክህደትንና መናፍቅነትን የሚዘሩ ዓመጻንና ርኩሰትን የሚያስፈጽሙ አይደለም በእዉነት የሚኖሩ ስለአዉነት ራሳቸዉን ክደዉ የሚመሰክሩ መልካም እረኝነታቸዉንና አገልጋይነታቸዉ ለእግዚአብሔርም ለሕዝብም የሚያሳዩ ናቸዉ ሕዝቡን ለነጣቂ ተኩላና ለጨካኞች ለግፈኞች አሳልፈዉ የማይሰጡ መስዋዕት ለመሆን እንደ አምላካቸዉ ራሳቸዉን የሚያስቀድሙ ናቸዉ እንጂ ምንደኛ ቅጥረኞች ሕዝቡን ለዲያብሎስ እንደራሴዎች አሳልፈዉ ሰተዉ ራሳቸዉን የሚያድኑ አይደሉም አዚህ ላይ የአንዳንዶቹን ሥጋዉያንና መንፈሳዉያን ፍጽም ከእዉነት የራቀ አስተሳሰባቸዉን ልገልጽላችሁ እዉዳለዉ ይኸዉም አስተሳሰባቸዉ የእዉነታ ፍጹም ተቃራኒ በሆነዉ በፖለቲካ ኅሊናቸዉ የተበከለና የተመረዘ ስለሆነ የአግዚአብሔር ፍጥረቶችና ልጆች የሆኑት የአዳም ዘሮች «ለዲያብሎስ ሥርዓት መገዛትና ፈቃዱንም መፈጸምና ማስፈጸም አለባቸዉ ብለዉ የሚያምኑና ሳያፍሩና ሳይሸማቀቁ በድፍረት የሚናገሩ ናቸዉ አብዛኛዎቹ ደግሞ በዚሁ በዲያብሎሳዊ ሥርዓት ዉስጥ ቁልፍ ቦታ ይዘዉ የክህደት የዓመጻ የርኩሰት ተዋናይ ሆነዉ የምታገጃቸዉ እነ ሆዱ አምላኩና እነ ጥቅማቸዉና ክብራቸዉ ዝናቸዉ ከኅሊናቸዉ በላይ የሆኑ ሰዎች ናቸዉ እነዚህ በብልጣብልጥነት የእግዚአብሔርን መንግሥት መዉረስ አንደሚችሉ አድርገዉ የሚያስቡ ከንቱ ሥጋዊ መጠበብ የሚያደርጉ በእግዚአብሔር ስምና በቃሉ የሚነግዱ አስመሳይ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አገልጋዮችና አማኞች ናቸዉ እንጂ ፍጹም ኅሊናዉ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመራ ሰዉ በተቃራኒ መንፈስ ከሚመራ ሰዉ ጋር ሆነ ድርጅት ወይንም ቡድን አንድነትና ኅብረት ሊኖረዉ አይችልም አሁን ወዳለዉ የኢትዮጵያ መንግሥት እዉነታ ስንመጣ ደግሞ « ከዚህ በፈት እንዲህ አልተደረገላችሁም እኛ ግን እንዲህ ሰራንላችሁ እንዲህ አደረግንላችሁ እንዲህ እናደርግላችኋለንጊ ወዘተ» በማለት ራሳቸዉን ባያመጻድቁና በአጉል ተስፋ ሕዝቡን እየሞሉ ኅሊናዉን ባያደነዝዙ እንዲሁም በአቅማቸዉ ለአገራቸዉና ለሕዝባቸዉ አገልግለዉ ያለፉትን እየኮነኑ ራሳቸዉን ታላቅ ለማድረግ ኅሊናቸዉን ባይሸጡ ይልቁኑ «እኛ መስራት ከሚጠበቅብን ያነሰ ነዉ የሰራነዉ ብንሰራም መስራት ያለብንን ነዉ የሰራነዉ ለወደፊት ደግሞ እግዚአብሔር ባሳሰበንና በረዳን መጠን የበለጠዉን እንሰራለን » ቢሉና «በሕዝብ ስም የተበደርነዉን የተረዳነዉን እንዲሁም ከሕዝብ የሰበሰብነዉን ሙሉ በሙሉ በአግባቡ በልማት ላይ ማዋል ተስኖን የተወሰኑ ግለሰቦች እንዲጠቀሙበትና በአቋራጭ መንገድ እንዲከብሩበት በማድረጋችን በዘመድ አዝማድ በጎጥ ተቧድነን ሕዝቡን በረፃብና በችግር ባንቀጣዉ ኖሮ አሁን ከተሰራዉ ግንባታ በላይ ብዙ ግንባታዎችን እናከናዉን ነበር በማለት ንስሐ ቢገቡ ከዚህ በተጨማሪም «ግንባታዉንና ልማቱን ያከናወነዉና የምናከናዉነዉ አስተሳሰባችንና መመሪያችን አገራዊ ራአይ ይዘን በኢትዮጵያዊነት ብሔር ሳይሆን በጎጣዊ ስሜት ለወደፊት ኢትዮጵያ የምትባል አገር ተከፋፍላና ተበታትና ህልዉናዋን ስታጣ ክልል መንግሥታት የራሳቸዉን ነጻ መንግሥትነት ሲያዉጁ ተጠቃሚ በምንሆንበት መልኩ አድሉና በቀል በተሞላበት አስተሳሰብ ስለሆነ ይህንን በክፋትና በተንኮል የተሞላዉ አስተሳሰባችንን ትተን በአራቱም ማዕዘን ያሉት «ኢትዮጵያዉያን ወንድምና እህቶቻችን እናትና አባቶቻችን ናቸዉኹ ብለን ከእንግዲህ ካለ አድሎና በቀል በእኩልነት እናገለግላለን በማለት የዘረኝነትንና ጎጠኝነት አስተሳሰባቸዉን ቢተዉ ማንም ሰዉ ከተመቻቸለትና ገንዘብ እርዳታ ካገኘ ሊሰራቸዉ የሚችለዉን መንገዶች ሕንጻዎች ግድቦች የመብራትና የስልክ አዉታሮች ፋብሪካዎች የትራንስፓርት ዘርፎች ወዘተ እና « ለፖለቲካ ዓላማችን ነዉ የሰራነዉ» በማለት በራሳቸዉ ጎጣዊ አስተሳሰብ ባይመሩ ኖሮ ለተሰሩት የትምህርት የጤና የሕንጻ የዉዛቀ ወዘተ ግንባታዎችና አገልግሎቶች እንዲሁም ለፓለቲካዊ ድጋፍና ለካድሬነት ምልመላ ባይጠቀሙበትና የራሳቸዉን ሰዉ ብቻ ባያበለጽጉበትና «ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ናቸዉ የስራ እድል እንፍጠርላቸዉ ራሳቸዉንም ቤተሰባቸዉንም ይርዱ ለእናት አገራቸዉም የራሳቸዉን አስተዋጽኦ ያድርጉ በሚል አስተሳሰብ ተደራጅቶ ቢሆን ኖሮ ስለ አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት ባጠቃላይ ለሥጋዊ ሕይወታችን ጥቅም ስለሚሰጡን ሁሉ የእግዚአብሔር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ስም እንዲጠራ ባይፈልጉም እግዚአብሔር ይስጣችሁ አገራችሁንና ሕዝባችሁን በቅንነትና በእዉነት የምታገለግሉበትን ልቦና ያድላችሁ ለንስሐና ለእግዚአብሔር መንግሥት ያብቃችሁ ብለን አእንመርቃቸዉ ነበር እንዲሁም በጨለማዉ ገዥ ገላጭነትና አሳሳቢነት በፈጠሩት «ብሔር ብሔረሰቦች» ቋንቋ ኢትዮጵያዉያንን በዘር በጎጥ በቋንቋ ከፋፍለዉ እርስ በአርሱ በጥላቻና በንቀት እንዲተያዩ እንዲከፋፈል እንዲለያዩ ራሳቸዉን የተለየ አድርገዉ እንዲቆጥሩ እንዲገዳደሉ እንዲበቃቀሉ ቂምና በቀል እንዲያረግዙ ለጥፋትና ለበቀል ጊዜ እንዲጠብቁ እንዲጨካከኑ አንዱ በአንዱ አንዲነሳሳ ባጠቃላይ የበላይ መሪያቸዉ የጨለማዉ ገዥ መንፈስ ያሳሰባቸዉን የዓመጻና የክህደት ፍሬዎችን ባያፈሩ በእግዚአብሔር እዉነት በኢትዮጵያዊነት በሰንደቅ ዓለማ ላይ ዓመጻና ክህደት ባይፈጽሙና ባያስፈጽሙ ከሕፃን እስከ አዋቂ ድረስ «ብሔር ብሔረሰቦች» በሚል ሽፋን በዘፈንና በዳንኪራ ባያሳብዷቸዉና የጨለማን ስራ ባያሰራቸዉ «በብሔር ብሔረሰብ» ስም የራሳቸዉን መሰሪ ተግባር ባይፈጽሙና በሕዝቡም ስም ባይነግዱ ኖሮ በየበረፃዉ በየገጠሩ በየጫካዉ የተረሱና ትኩረት ያልተሰጣቸዉ ወገኖቻችን ኢትዮጵያዉያን እንዲታወቁ በመደረጉና ራሳቸዉን የሚያመጻድቁና በዘራቸዉ በጎጣቸዉ የሚመኩ ሰዎች ደግሞ በበረፃ ሆነ በጫካ እንዲሁም በገጠር የሚኖሩ ሰዎች እንደማንኛዉ ኢትዮጵያዊ እኩል መሆናቸዉን እንዲያዉቁ በመደረጉና ትኩረት ስለተሰጣቸዉ እግዚአብሔር ለሙሉ እዉቀትና ለአዉነተኛ እረኛነት ያብቃችሁ በማለት እንመርቃቸዉ ነበር ከዚህ በተጨማሪም የእግዚአብሔር እዉነታን እንኳን ኢትዮጵያዉያን አይደለም ሌላዉ የዓለም ሕዝብ ሁሉ የአንዱ እግዚአብሔር ፍጥረቶችና የአዳም ዘሮች ናቸዉ የአግዚአብሔር ልጅ መሆን ከፈለጉ ደግሞ ማንኛዉም ሰዉ በጥምቀት በመንፈስ ከእግዚአብሔር ተወልዶ ለሰማያዊ ሆነ ምድራዊ የእግዚአብሔር መንግሥት ሊበቃና አገልጋይ ሊሆን ይችላልር ማንም ሰዉ በዘሩ በጎጡ በቋንቋ የበላይ አይደለም እንዲሁም የበታች አይደለም ሁሉ ሰዉ በአግዚአብሔር ፍጥረትነቱ ካመነ በአግዚአብሔር ዘንድ እኩል ነዉ እግዚአብሔርን ከካደና ዓመጻና ክህደት እንዲሁም ርኩሰት ከፈጸመ እዉነተኛ ንስሐ ገብቶ ከአምላኩ እስከሚታረቅ ድረሰ እርሱ እንደ ሰይጣናት በእግዚአብሔር እዉነታ ላይ ያመጸ በመሆኑ ዓመጸኛና ከዛዲ ስለሆነ እንደ ማንኛዉ ሰዉ በሰዉነቱ አኩል ቢሆንም ስለዓመጸኛነቱ ግን ባዶና ተራ የሆነ አሳዛኝ ፍጥረት መሆኑን ማስተዋል ይኖርበታል ሰዎች በቋንቋ በባህል በሃይማናት የተለያዩት በኃጢአታቸዉ ምክንያት ነዉ እንጂ በጽድቅ ስራቸዉ አይደለም ሰዎች ራሳቸዉን ለማምለክና ለማስመለክ እንዲሁም «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ለማግነንና የበላይ ለመሆን ነዉ ልዩነትን እየፈጠሩ ክፍፍልና መለያየት የሚያደርጉት አንጂ እግዚአብሔር አንድ እንደሆነ ሁሉ ለእግዚአብሔር መንግሥትም የሚያበቃ አንድ የሕይወት መንገድ ብቻ ነዉ ያለዉና ሕያዉ ሆኖ በእግዚአብሔር መንግሥት ዉስጥ መኖር የሚፈልግ ሰዉ በአንዱ እዉነተኛ ዛይማኖት ሊመላለስ ይገባዋል «አይ የራሴን የሥጋና የደም ስሜት ፈቃዴን ነዉ የምከተለዉ ራሴነዉ የማገነዉና የማስመልከዉ የሚል ሰዉ ካለ ስለ ዓመጻዉ እንደ ሰይጣናት በምድራዊ ሕይወቱም ዘመንና ከሁሉ በላይ ደግሞ ነፍሱ ከቅርፊት ሥጋዉ ስትለይ ለሕያዉነት ዘመን የባሰ ዋጋ እንደሚከፍልበት እያወቀ እንደ ማንኛዉ ሰዉ ምድራዊ ኑሮዉን መኖር ይችላል እግዚአብሔርን የሚል ሰዉ ደግሞ ከአሕዛብአግዚአብሔርን ከማያምኑ ሰዎች የተወረሰዉን የአሕዛብ ባህልና ልማድ አርግፍ አድርጎ በመተዉ ለእግዚአብሔር አገልግሎትና መንግሥት የሚያበቃዉን ባህልና ሥርዓት ሊከተል ይገባዋል «አይ እኔ እግዚአብሔር የሚባል ነገር አላዉቅም ዝርያዎቼም ጦጣዎች ናቸዉ ተፈጥሮ ናት ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣችኝ» የሚል ዓመጸኛና ከፃዲ ሰዉ ካለ በግል ሕይወቱ በዓመጻዉና በክህደቱ ሊጸና ይችላል ነገር ግን ዋጋ እንደሚከፍልበትና ሌላዉን የእግዚአብሔርን ሕዝብ ግን ሊያሳምጽና ሊያስክድ እንደማይችል ማወቅ ይኖርበታል ባጠቃላይ እያንዳንዱ ሰዉ በግል ሕይወቱ እግዚአብሔርን ሊክድና ላያምን ቢችልም በእግዚአብሔር እዉነታ ላይ ግን ዓመጻንና ክህደትን መፈጸምና ማስፈጸም እንደማይችል ሊረዳ ይገባዋል ምክንያቱም አያንዳንዱ ሰዉ ለማንኛዉ ሰዉ የሚፈቀደዉ ሙሉ ነጻነት በግል ሕይወቱ የሚፈቀድለት ቢሆንም በአግዚአብሔር ፍጹም አውነታ ላይ ማንንም ሊያሳምጽ ሆነ ሊያስክድ አይችልም እንኳን በእግዚአብሔር እዉነታ ላይ ቀርቶ የጨለማዉ ገዥ እንደራሴዎች በእርሱ አሳሳቢነትና መሪነት ባዘጋጁት ሕገ መንግሥት ላይ ዓመጻና ክህደት ሲፈጸም ዋጋ እንደሚከፈልበት ይታወቃል በእግዚአብሔር ሕገ መንግሥት ላይማ እንዴት በምድርም በሰማይም የበለጠዉ ዋጋ አይከፈልበት። እጅግ ይከፈልበታል በማለት እንነግራቸዉ ነበር የጨለማዉ ገዥ እንደራሴና አገልጋይ የሆኑት ሰዎች ለራሳቸዉ መሰሪ ዓላማ የፈጸሙት አንዳንድ ተግባሮች እግዚአብሔር ለበጎ ያዉለዋል እነሱ ግን ሕዝብን ለመሸንግል የሥልጣን አድሜያቸዉን ለማስረዘም ትዉልዱ ኅሊናዉን እንዲሸጥና በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት ዉስጥ እንዲመላለስ በማድረግ ከአምላካቸዉ አጣሉት ለእግዚአብሔር ቁጣም አሳልፈዉ ሰጡት ማስተዋሉን አጡ እንጂ ራሳቸዉን በእግዚአብሔርና በሕዝብ ፊት ዝቅ አድርገዉ ቢመላለሱና በቅንነትና በእዉነት ቢያገለግሉ ኖሮ እንኳን በምድር ብቻ አይደለም በሰማይም ይገኑ ይከበሩ ይሸለሙ ነበር በዚህች ምድር የተፈቀደላቸዉን የሥልጣን ዘመንም ማንም ሊያሳጥርባቸዉ ሆነ ሊያስረዝምላቸዉ እንደማይችል ቢያዉቁና አስተዉለዉ ቢሆን ኖሮ በተፈቀደላቸዉ ዘመን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር እግዚአብሔር ደስ በሚሰኝበት ሕይወት በመመላለስ ፈቃዱን ፈጽመዉና አስፈጽመዉ ወደ አምላካቸዉ እቅፍ ይሄዱ ነበር አሁን ግን እንኳን ፈቃዱን መፈጸምና ማስፈጸም አይደለም ራሳቸዉን ከዓመጻ ከክህደት ከርኩሰት ተግባር መለየት አልቻሉም ሕዝቡንም ከማሳመጽ ከማስካድ ከማስረከስና የአምልኮ ምንዝርና ከማስፈጸም አልተመለሱም በመሆኑም በሥጋቸዉ ሆነ በነፍሳቸዉ ላይ በራሳቸዉ ነጻ ፈቃድ ታላቅ መከራና ቅጣት አያመጡ መሆኑን መገንዘብ ይገባቸዋል እግዚአብሔር አንደ ፍጡር የዓመታት ወይንም የወራት ዝግጅት አያስፈልገዉም የፈለገዉን በፈለገዉ ቀንና ሰዓት ማከናወን ይችላል ዛሬ ከወንበራቸዉ ማንሳት ከፈለገ ዛሬዉኑ በፈለገዉ መንገድ ከወንበራቸዉ ሊቆርጣቸዉ ይችላል በተቃራኒዉ ደግሞ ቀኑ ካልደረሰ የዓለም ሕዝብ ተባብሮ ከወንበራቸዉ ሊያነሳቸዉ ቢጥር ሊያነሳቸዉ አይችልም የተፈቀደላቸዉ ቀን ሊረዝም የሚችለዉ ቀና ካሰቡ መልካም ከሰሩ በእዉነት ከኖሩ ብቻ ነዉ በተቃራኒዉ የተፈቀደላቸዉ ቀን ሊያጥር የሚችለዉ ዓመጻቸዉ ክህደታቸዉ ርኩሰታቸዉ ሲከፋ ግፍና ጭካፄኔያቸዉ ሲያይል ነዉፁ ከዚያ ዉጭ ግን በተቆረጠላቸዉ ቀን በአንድም ይሁን በተለያየ መንገድ ከወንበራቸዉ ተቆርጠዉ ወንበሩ ለባለተረኛዉ ተላልፎ ይሰጣል ታዲያ እነሱም ሆኑ እኛ ሰዉ በራሱ ኃይልና ሥልጣን ወደ ወንበር የሚመጣ ይመስለናል እንጂ እግዚአብሔር ባወቀና በፈቀደዉ መንገድ አይመስለንም እንዲሁም ወንበሩ የሚጸናዉ በራስ ኃይልና ሥልጣን ይመስለናል እንጂ በእግዚአብሔር ቸርነትና ጥበቃ መሆኑን አይገባንም እዉነታዉ ግን ሁሉ በእግዚአብሔር ቁጥጥርና እዉቅና የሚከናወን ነዉ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር የሆነ መልካም ሥርዓትን ከፈለገና ከጠየቀ እንደጥያቄዉና ምርጫዉ መልካም ሥርዓትን ይሰጠዋል በተቃራኒዉ ደግሞ የዓመጻና የክህደት አንዲሁም የርኩሰት ሥርዓት ከፈለገ የሚቀጣበትንና ዋጋ የሚከፍልበትን ሥርዓት ይሰጠዋል እግዚአብሔር እንደ ሕዝቡ ፍላጎትና ጥያቄ ነዉ ደግ መሪ ወይንም ጨካኝ መሪ የሚሰጠዉ አንዳንድ ምሳሌ ብንመለከት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የነበሩት አጹ ኃይለ ሥላሴ የሥርዓት ማብቂያቸዉ በደረሰ ወቅት አሳቸዉም ሆኑ ሌላዉ ሰዉ ባላሰበዉና ባልጠበቀዉ መንገድ ከወንበራቸዉ ሊቆረጡና አሳቸዉም ባለሥልጣኖቻቸዉም የተለያየ መከራና ግድያ ሊደርስባቸዉ ችሏል ከዚያም የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ሥርዓት ማብቂያ ላይም ባልታሰበና ባልተጠበቀ ጊዜ ከወንበራቸዉ ተቆርጠዉ አሳቸዉም ለስደት ባለሥልጣኖቻቸዉም ለችግርና ለአስር ተዳርገዋል አሁንም ባለተረኛዉ አቶ መለስ ዜናዊ የሥርዓታቸዉ ማብቂያ መዳረሱ ቢታወቅም በምን መልኩ ከወንበራቸዉ እንደሚቆረጡና እሳቸውም ሆኑ ባለሥልጣኖቻቸዉ ስለ ዓመጻ ክህደት ርኩሰት ተግባራቸዉ ምን ዋጋ እንደሚከፍሉ ቸሩ መድኃኔዓለም አንድዬ ነዉ የሚያዉቀዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር እኛ ግን የአዳም ዘሮች ወንድምና እህቶቻችን ናቸዉና ስለ ዓመጻ ስለክህደት ስለርኩሰት ተግባራቸዉ ንስሐ ገብተዉ ለእግዚአብሔር እጃቸዉን ሰተዉ በሰዉ ሳይሆን በራሱ ጊዜ እንዲጠራቸዉ ነዉ ምኞታችንና ጸሉሎታችን የማንንም ጥፋትና ዉድቀት አንመኝም በዉድቀታቸዉና በጥፋታቸዉም አንደሰትም ምክንያቱም አንድነታቸዉንና ኅብረታቸዉን ከአምላካቸዉ ጋር ካደረጉ ሁላችንም በእግዚአብሔር መንግሥት እዉነተኛ አምላካችንን በመስቀል ላይ ዋጋ የከፈለልንን በአዉነትና በመንፈስ እያመለክነዉ ሕያዉ ሆነን በመንግሥቱ መኖር ነዉ ፍላጎታችንና ልመናችን በዚሁ አጋጣሚ ስለ ነፍሳቸዉ የሚያስብላቸዉ ሰዉ ካለና እነሱም ለመስማት ፈቃደኛ ከሆኑ ማንም ይሁን ማን በዚህ ምድር የዘራዉን ፍሬ ማጨዱና መራራዉን ፍሬ መጠጣቱ ስለማይቀር በአዉነተኛ ንስሐ ቢመለሱና መልካም ፍሬ ማፍራት ባለመቻለቸዉ ምክንያት መልካም ፍሬ ለሚያፈሩትና የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ ለሚፈጽሙና ለሚያስፈጽሙ ለተመረጡትና ለተቀቡት ለኢትዮጵያዉያኑ ለሥጋዊዉ ሆነ ለመንፈሳዊዉ ወንበር ለታጩት እዉነተኛ እንደራሴዎች ወንበሩን ቢለቁ የተሻለና የሚበጃቸዉ እንደሚሆን እንዲነግሯቸዉና እንዲያስረዲቸዉ እፈልጋለሁ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሊያደርግ ያሰበዉንና የወሰነዉን ማንም ፍጡር ሊያስቀረዉ ሆነ ሊያዘገየዉ ስለማይችል መራራዉን ጽዋ ጠጥተዉ ከምድሩም ከሰማዩም ሳይሆኑ ቀርተዉ ዳግም የንስሐ እድል ወደ ማይገኝበት ቦታ ከፄዱ ፍርዱ እጅግ ይብስባቸዋልና ነዉ ከዉጭዎቹ ምሳሌ ብንመለከት ደግሞ የኢራቁ መሪ ሳዳም ሁሴንና የሊቢያዉ መሪ ሙሐመድ ጋዳፍ «ማንም አይነካቸዉም ከወንበራቸዉም ማንም አይነቀንቃቸዉም» ሲባል የተቆረጠባቸዉ ቀን ሲደርስ ባላሰቡትና ባልጠበቁት መንገድ ከወንበራቸዉ ሊቆረጡና የዉርደት ሞት ሊሞቱ ችለዋል የግብጹ መሪም ሆሲን ሙባረክ ብንመለከት ባለሰቡበትና ባልጠበቁበት ቀን በተከበሩበትና በገነኑበት አገርና ሕዝብ በራሳቸዉ ሕዝብ ተዋርደዉ ከወንበራቸዉ መቆረጣቸዉና የቁም ስቃያቸዉን እያዩ መሆኑን እናዉቃለን ታዲያ በዚህ አጋጣሚ ለሌሎች የዓለም መንግሥታት መሪዎች የሚነግራቸዉ ካለና እነሱም ለመስማት ፈቃደኛ ከሆኑ «ነግ በእኔነብለዉ ከመዉደቃቸዉና ከመዋረዳቸዉ በፊት ለአግዚአብሔር እጃቸዉን እንዲሰጡና ወንበሩንም የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ ለሚፈጽሙትና ለሚያሰፈጽሙት ለኢትዮጵያዉያኑ ለተመረጡትና ለተቀቡት እዉነተኛ ለእግዚአብሔርና ለአመቤታችን ድንግል ማሪያም ባለሟሎችና እንደራሴዎች አሳልፈዉ ቢሰጡ የተሻለና የሚበጃቸዉ እንደሚሆን እንዲነግሯቸዉና እንዲያስረዲቸዉ እፈልጋለሁ ምክንያቱም አግዚአብሔር ለዓለም መንግሥታት መዉደቅም መነሳትም ምክንያት የምትሆነዉን ኢትዮጵያን የሚጎበኝበት ወራት ደርሷልና በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ ለሚቋቋመዉ የእግዚአብሔር መንግሥት እጁን የማይሰጥ መንግሥት ሆነ ቡድን እንዲሁም ግለሰብ ዳግም የንስሐ እድሜ ሳያገኝ በእግዚአብሔር ቁጣ ከምድር ይጠረጋልና «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ነዉ ጥቅሙ ለራሳቸዉ ነዉ እንጂ እግዚአብሔር አደርገዋለዉ ያለዉን የዓለም ሕዝብ በአንድላይ ቢሰለፍ ሊያስቀረዉ ሆነ ሊያዘገየዉ አይችልምና ወደ ነፍስ ጉዳያችን ስንመጣ ደግሞ አሁን ያለዉ የኢትየጵያ መንግሥት እንደ ሌሎቹ አገራት መንግሥት ሕዝቡንና ምእመኑን ሙሉ በሙሉ ገሏል ከእግዚአብሔር ፈቃድ ተቃራኒ ተግባር አየፈጸመ የተመረጠዉን የእግዚአብሔርን ሕዝብ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት እንዲመላለሱ በማድረግ የኃጢአትን ተግባር አንግሷል ክህደትንና መናፍቅነትን አሳፋፍቷል የእአዉነትን መንገድ አጥፍቷል ዳንኪራንና ዘፈንን ከሕጻን ኅሊና እስከ አዋቂ ኅሊና ዉስጥ በማሥረጽ ነፍሳትን አሳብዷል ባጠቃላይ በእግዚአብሔር እዉነታ ሲታይ ፍጹም የዲያብሎስን ሥርዓት ዘርግቶ የእርሱን ፈቃድ እየፈጸመና አያስፈጸመ ነዉ ለዚህ ምስክሩ በቴሌቨዥን በሬድዮ በተለያዩ ኅትመቶች የሚታየዉና የሚደመጠዉ የሚነበበዉ ይህንኑ የዲያብሎስን ስራ ያሳያል ሕዝቡም የአምልኮ ምንዝርና እንዲፈጽምና በርኩሰት ሕይወት እንዲመላለሱ በማድረጉ በራሱ ላይም በሕዝቡ ላይም የእግዚአብሔርን የከፋዉን ቁጣ እንደሚያመጣ በእምነት ዉስጥ ያለ ሰዉ ይረዳዋል ታዲያ ይህን በመናገሬ ነገ የሚደርስብኝን ፈተና መከራ ስደት እስራት ግድያ ሳልገምት ቀርቼ አይምሰላችሁ ቢበዛ ሊጎዱት ሆነ ሊገሉት የሚችሉት ይህን የተገለጽኩበትን ቅርፊት ሥጋ እንጂ ነፍሴን እንኳን ሊጎዱ አይደለም ይልቁኑ ለታላቅ ክብርና ሽልማት ያበቋታል ተስፋዬ ምድራዊ ቢሆን ኖሮ ለጊዜያዊ ሥልጣን ክብር ጥቅም ዝና ድሎትና ምቾት ስል እንደሌሎቹ ወገኖቼ ኅሊናዬን በመሸጥና በማገለባበጥ የኢህአዴግ ወይን አጋር ድርጅት ዉስጥ አባልና የጨለማዉ ገዥ አገልጋይ መሆን አችል ነበር እንዲሁም በወገኖቼ አናት ላይም ተረማምጀጄ ወንበር ላይ አወጣ ነበር ነገር ግን ሁሉ ተራና ኃላፊ ስለሆነ ስለ እዉነት ከመመስከር ዉጭ ከነችግሬና ከሚመጣብኝ ፈተና ጋር ለመኖር ራሴን ያዘጋጀዉት ወደ ኢትዮጵያዊነትና ወደ ሕዝቡ ስንመጣ ይህ የኢሕአዴግ መንግሥት በጣት የሚቆጠሩትን አጅግ ጥቂት ሰዎች በዘመድ አዝማድና በጎጥ ተቧድነዉ አንዲሁም አንዳንዶችን በአቋራጭ መንገድ ዉስጥ በጉቦ በትዉዉቅ በጥቅማ ጥቅም ወዘተ አንዲገቡ አድረጎ ቢያበለጽግም እጅግ እጅግ ብዙዎቹን ኢትዮጵያዉያንን ግን በድህነት አረንቋ ዉስጥ እንዲማቅቁ የቀሩት ደግሞ በየመንገዱና በየእምነት ተቋማት ዙሪያ እንዲወድቁ ለልመናና ለችግር ለሮሮ እንዲዳረጉ ያደረገ አንዳች ለሕዝብ ርኅራቴ የሌለዉ ጨካኝ መንግሥት መሆኑ ይታወቃል ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ልክ እንደ ነፍሳችን ሙሉ በሙሉ አጥፍተዋል ደምስሰዋል ዘረኝነትንና ጎጠኝነትን በማስፋፋት ኢትዮጵያዊነት ሃይማኖትን ክደዋል «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሕዝቡን አስክደዋል የከፋና የከረፋ ተግባራቸዉ ዉጤት በእናንተ ላይ እንኳ ብንመሰከት ከአራቱም ማዕዘን ከኢትዮጵያ ምድር የመጣችሁ ኢትዮጵያዉያን መሆናችሁ ቢታወቅም «አይደለንም ብትሉ» እንኳ መልካችሁ የሚፈርድባችሁ ሲሆን ይኸዉም በነቢዩ ኤርምያስ እንደተነገረዉ ትንቢተ ኤርምያስ ም «በዉኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን ወይስ ነብር ዥንጉርጉርነቱን ሊለዉጥ ይችላልን። » በማለት ያቀረበችዉን ምልጃዋን ሰምቶ ነዉ እዉነትን ሊያሳዉቃችሁ የወደደዉ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ ብዙ ባለማወቅ በተሳሳተ እምነትና ሕይወት የሚመላለሱ ቅኖችና የዋሃን አሉ እነሱም በሂደት ወደ አዉነታዉ ይመጣሉ ለዚህም ነዉ ነፍሳትን ከአሳትና ከጥፋት አያወጣች ወደ ሕይወት ስለምታመጣ ዲያብሎስ ከነጭፍሮቹ ሰይጣናት ጋር በመሆን ቀን ከሌሊት ትዉልዱን ከድንግል ማርያም ለመለየት የሞት ሽረት ጦርነት የሚያደርገዉ ዲያብሎስ ትዉልዱን ከእርሷ ለየ ማለት ከአምላካቸዉ መለየቱን እርግጠኛ ነዉ የሚሆነዉ ምክንያቱም ከእርሷ የተለየዉ ትዉልድ ነዉ አምላኩን አማላጅፍጡር እያለ የሚክደዉና የሚሳደበዉ እንዲሁም ቅዱሳንን እያቃለለ የሚያዋርደዉ አዚህ ላይ አንድ ያላወቃችሁትንና ያላስተዋላችሁትን እዉነታ እነግራችኋለሁ ይኸዉም አመ አምላክ ድንግል ማርያም በሰማያት ከብራና ገና በፍጹም ደስታ መኖር ስትችል እርሷ ግን የመረጠችዉ ስለ አደራ ልጆቿ የአዳም ዘር ስትል ከመክበርና ከመግነን ይልቅ ኀዘንተኛ መሆንን መርጣለች ምክንያቱም የአዳም ዘር ጥፋት አላስቻላትምና ነገር ግን ስለ እርሷና ስለቅዱሳን እንዲሁም በዚህች ምድር ስለ እዉነት ስለሚያዝኑ ሲል እግዚአብሔር በአራቱም ማዕዘን ያሉ ነፍሳትየሰዉ ዘሮች የሚድኑበትን ሰማያዊ ሥርዓት በቅርቡ ይዘረጋል ለዚህ ሰማያዊ ሥርዓት ኅሊናቸዉን አደንድነዉ አንቅፋት የሚሆኑትን የዓመጻ ልጆችን ደግሞ እጃቸዉን ለአምላክ ለመስጠት ፈቃደኛ አይደሉምና ከምድሪቱ በእግዚአብሔር ቁጣ ይጠረጋሉ ሌላዉ ማወቅ ያለባችሁ የእኛ የዓመጻ የክህደትና የርኩሰት ተግባር የረበሸዉና ያወከዉ የቅዱሳንና የጻድቃን ደስታን ብቻ ሳይሆን እርሱን ባለቤቱን እግዚአብሔርን ኀዘንተኛ አድርገነዋል ምክንያቱም እንኳን በተግባራችንና በንግግራችን ብቻ አይደለም በሓሳብ ጭምር የምንረክሰዉና የምናምጸዉን በመላዉ ዓለም እያንዳንዱ ሰዉ የሚፈጽመዉን እየተመለከተና እየሰማ እንዳያጠፋን ሕያዉ ፍጥረቶቹና ልጆቹ ስለሆን ባሕርይዉ ይገድበዋል ፍቅሩና ርኅራዔዉ እጅግ ያይልበታል ዝም ብሎ እንዳይምረን ደግሞ እንዲሁ ባሕርይዉ ይገድበዋል ይልቁኑ ፍርዱ ጥብቅ እንዲሆን ያደርገዋል «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በዚህ ምክንያት አሱም እንደቅዱሳንና ጻድቃን ስለ እዉነት ኀዘንተኛ እንዲሆን አድርገነዋል ነገር ግን ከፍርድ ቀን በኋላ ግን እያንዳንዱ አንደ ስራዉና እምነቱ ስለሚፈረድለትና ስለሚፈረድበት ቅዱሳን ሆኑ ጻድቃን ፍጹም በሆነ ደስታ በመንግሥቱ ሕያዉ ሆነዉ ይኖራሉ ማንም ፍጡር በአዉነተኞች ላይ በደል ሆነ ግፍ አድሎ መፈጸም አይችልም በተቃራኒዉ ደግሞ በምድራዊ ሕይወት ዘመናቸዉ በእዉነተኛ አገልጋዮችና ምእመን ላይ ግፍ በደል አድሎ የፈጸመና የሚፈጽም ግፈኛና ጨካኝ ሰዉ ነፍስ ከሥጋዉ አንደተለየች ስለዓመጻዉና ጭከናዉ በመቶ አጥፍ ዋጋ ይከፍልበታል በዚህ ምድርም የዓመጻዉና የግፍ ጽዋዉ ሲሞላ ፍዳዉን ያገኛል የአመቤታችን እዉነተኛ ወዳጅ ቢወድቅ ይነሳል ቢደክም ያበረታል ተስፋ ቢቆርጥ ተስፋዉ ይለመለማል ቢገፋ ይነሳል ቢያዝን ይጽናናልቢደኸይ ይበለጽጋል ቢሞት ሕያዉ ይሆናል ሌላዉ ማወቅ ያለባችሁ በመጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ከዘፍጥረት ጀምሮ እስከ ዮሐንሰ ራአይ ድረስ በግልጽና በምሳሌ በተለያየ መልኩ ተገልጻለች ከአምላክ ማዳን ተግባር ጋር ፍጽም ልተለይ የማትችል የድኅነታችን ምክንያት መሆኗን በሚገባ ልታዉቁ ይገባል እዚህ ላይ ታዲያ በስሟ የሚነግዱ አገልጋዮችና ምእመናን እንዳሉ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ አነዚህ አስመሳዮች ለአግዚአብሔር ትዕዛዝና ሕግ አንዳች ደንታ የሌላቸዉ ለሆዳቸዉና ለክብራቸዉ የቆሙ ስለ ነፍሳት መዳን አንዳች ስሜት የሌላቸዉ ሲፈልጉ ለኃጢአታቸዉ ሽፋን እሷን የሚያደርጉ ትዉልዱ ከንስሐ ከሥጋና ደሙ የሚለዩ እነሱ የማይሸከሙትና የማይፈጽሙትን ሸክም በምእመን ላይ ጭነዉ ምእመኑን የሚያስጨንቁ የሚያስቸግሩ ናቸዉ እነዚህን እግዚአብሔር ብቻ ሳይሆን አመ አምላክም ቅዱሳንም ስለሚያዉቋቸዉ አላጋጩ ዲያብሎስ እንዳላገጠባቸዉ ለንስሐ ሳይበቁ ከነዓመጻቸዉና ርኩሰታቸዉ በሥጋ ሞት ተጠርተዉ የባሰዉን ፍርድ የሚቀበሉ ናቸዉ እዉነተኛ ወዳጆቿ ግን በሥጋ ድካም በኃጢአት ቢወድቁ እንኳ ለንስሐ ለሥጋና ደሙ አብቅታቸዉ ለሰማያዊ መንግሥት ታጫቸዋለች በአሁን ሰዓት ቤተክርስቲያን በዉጭም በዉስጥም እየተፈተነች ትገኛለች ይኸዉም አንዳንድ አንደ ሥጋና ደም ስሜታቸዉ የሚንቀሳቀሱ አታላዩ ሸዋጁ የፕሮቴስታን መንፈስ ራሱን በማሻሻልና በመሰወር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ፃይማኖት ለቤተክርስቲያን ተቆርቋሪና አገልጋይ በመምሰል ከቤተክህነቱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ድረስ በተደራጀና በጥቅማ ጥቅም በተሳሰረ መንገድ የቤተክርስቲያኒቱን እምነት ሥርዓት አስተምሮ ትዉፊት ለመለወጥና ለቅርፊት ሥጋ የሚመች ሥርዓትና አስተምህሮ በምእመኑ ኅሊና ለማስረጽ ሌት ተቀን የሚተጉ ተኩላዎች አሉ የሚገርመዉና የሚያሳዝነዉ ደግሞ ሽፋንና ድጋፍ አድርገዉ የሚመላለሱት ዋና የፃይማኖት መሪ የተባሉትንና የእሳቸዉን ጋሻ ጃግሬ መከታ አድርገዉ ነዉ እነዚህ ስብከቱን መናፍቅ መናፍቅ አድርገዉ ያሸተቱ መዝሙሩን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ዘፈንና ዳንኪራ ያደረጉ ናቸዉር ምእመኑ የአመቤታችን ፍቅር በልቡ የታተመ ስለሆነ በቀላሉ መመንገል አንደማይችሉ በመረዳታቸዉ ከልባቸዉ ሳይሆን ለማስመሰል ስለ አርሷ አንክርዳድ በተደባለቀ መልኩ ያስተምራሉ ሲፈልጉ ደግሞ በክብር አንዳትጠረ ልክ ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብርና አንደ እግዚአብሔርነቱ አንዳይጠራ ልክ አንደ ፕሮቴስታንቱ « የሱሴ ወይንም ኢየሱስ» እንዲባል አሷንም አመ አምላክ እመቤታችን ቅድሰት ድንግል እመ ብርሃነን ብለን በክብር አንዳንጠራት «ማርያም ብቻ» እንድንላት በየመድረኩ አያለማመዱን ነዉ ታዲያ ከእንደነዚህ ዓይነቶቹ ጋር ባለማወቅ በየዋህነትና በቅንነት የሚመላለሱትን እግዚአብሔር አጥርቷቸዉ ለእዉነተኛ አገልግሎት ያሰልፋቸዋል ነገር ግን በዓለማ የሚንቀሳቀሱትን ደግሞ ኅሊቸዉን አንደ ትዕቢትፈርኦንን ይመራዉ የነበረዉ የትዕቢት መንፈስ ክፋት ይሁዳን ይመራዉ የነበረዉ የክፋትና የተንኮል መንፈስ ዓመጻ አርዮስን ይመራዉ የነበረዉ ሸዋጁ መንፈስ የደነደነ ወደ ንስሐ የማይቀርቡና እዉነተኛ ንስሐ የማይገቡ እንኳን ፍጡሮቹ የሆኑት አገልጋዮቹን ሊሰሙ ቀርቶ አምላክ በሥጋ ተገልጾ ቢናገራቸዉ ተአምራትንና ፈዉስ ቢያደርግ የማይቀበሉት እጅግ የታበየና በዓመጽ የተሞላ ሕይወት ስለያዙ እግዚአብሔር ያበጥራቸዋል ከስንዴዉ ይለያቸዋል እንደ እንክርዳድነታቸዉ እንደ ቆሻሻ ተቆጥረዉ ከሌሎች የዓመጻ ልጆች ጋር ይጠርጋቸዋል እነዚህን ብቻ አይደለም እዉቀታቸዉን አምልከዉና አስመልከዉ ያሉ «ከእግዚአብሔር የሆነዉን ሙሉ እዉነታ አንቀበልም ከእኛ እዉቀትና አስተሳሰብ ዉጭ ያለዉን አንቀበልም አንመራበትም» ብለዉ እግዚአብሔርን በራሳቸዉ እዉቀትና በጠባብ አእምሮዋቸዉ የሚወስኑትን የሚቃወሙትን የጸሐፎችና የፈሪሳዉያን እንዲሁም የአይሁድ ካህናት አለቆች ሕይወት የያዙትን ደንዳና አገልጋዮችንም የሚጠራ ልብ ያላቸዉን ያጠራቸዋል ለእዉነተኛ ምሉዕ አገልግሎት ያበቃቸዋል እብሪተኞቹንና ዓመጸኞቹን ደግሞ ያበጥራቸዋል ከስንዴዉ ይለያቸዋል ይጠርጋቸዋል ቀደም ብዬ እንደገለጽኩላችሁ ሥርዓት ለማሻሻል የሚችለዉ እዉነተኛ የእግዚአብሔር እንደራሴዎችና አገልጋዮች ብቻ ናቸዉ እንጂ እንደ እኔ ዓይነቱ እንደ እግዚአብሔር ቃል ሆና የማይገኝ ኅሊናዉን የሚያገለባብጥና የሚሸጥ ለሥጋ ፈቃዱ የሚያደላ ቢሆንለት ሰባቱ አጺማት ተሽረዉለት ዓመቱን ሙሉ የፈለገዉን ለመብላት የሚመኝ በዳንኪራዉና በዘፈኑ ሌት ተቀን ኅሊናዉ ስላበደ ደስ ብሎት እንዲሰማዉና እንዲዝናናበት ሲያስፈልገዉም እንዲጨፍርበት ልክ እንደ ፕሮቴስታንቱ የእግዚአብሔርን ቃል መጫወቻና ማላገጫ እንዳደረጉት ዘፈን መሰል መዝሙር በኦርጋን በጊታር በሳክስፎን በጃስ ታጅቦ እንዲቀርብለት የሚፈልግ እንዲሁም ስብከቱን ሆነ መዝሙሩን እንደ ንግድ ስራ ቆጥሮ የቤተክርስቲያኒቱን እምነት ሥርዓት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አስተምህሮ ትዉፊት ባልጠበቀ መልኩ የእግዚአብሔርን ቃል መሸቀጫ የሚያደርግ በአናቱ ላይ ለጥቅሙና ለሥልጣኑ ብቻ ሲል ቆብ ደፍቶ ስዉር ዓመጻዉንና ርኩሰቱን ለመፈጸም ደግሞ ሽጉጥ ታጥቆ የሚሄድ በዘመድ አዝማድ በጎጥ ተቧድኖ በእግዚአብሔር ቤት ዓመጻ ክህደት ርኩስት የሚፈጽም ከዓመጻ ልጆች ጋር አንድነትና ኅብረት ፈጥሮ ምእመኑን የሚያሳምጽ ስለ እዉነት ራሱን ክዶ መመስከር የማይችል ለሥልጣኑ ለክብሩ ለጥቅሙ ለዝናዉ ያደረ ሆዱ ከሞላ ክብሩ ከተጠበቀ በቤተክርሰቲያን ላይ ደባ ሲፈጸም ዝም የሚል ተስፋዉን ምድራዊ አድርጎ የሚመላለስ ባዶ ቀፎ የሆነ ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ የእግዚአብሔር ቃል አሳምሮ ብቻ የሚናገርና ለራሱ ሥጋዊ ፈቃድ የሚያዉል እንደቃሉ ሆና የማይገኝ ምእመኑ በዘልማድ እንዲመላለሱ የሚያደርግ እዚህ መታችሁ ስላጨበጨባችሁና እልል ስላላችሁ ብቻ መንግሥተ ሰማያት ትወርሳላችሁ እያለ ምእመኑን ከንስሐና ከቅዱስ ቁርባን የሚለይ በባዶ ሕይወት በትዕቢትና በዕብሪት የሚያስተምር እንደ ቦይ ዉፃ ወደ ወሰዱት አቅጣጫ የሚፄድና የዲያብሎስን ሥርዓት ለመጠበቅና ለማስጠበቅ ምእመኑንም ለማሳመጽ ሌት ተቀን የሚተጋ የካድሬነት ተግባር የሚፈጽም የዓመጻን ስራ የማያወግዝ ራሱ የማይሸከመዉን ሸክምና የማይፈጽመዉን ትብታብ በሰዎች ጫንቃ ላይ የሚጭንና የሚተበትብ የወንጌል እንቅፋት የሆነ ባጠቃላይ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ ለመፈጸምና ለማስፈጸም አንዳች ብቃቱ የሌለዉ እንደእኔ ዓይነቱ አገልጋይ ሆነ ምእመን እንኳን ሥርዓት ሊያሻሽል ቀርቶ ከሚያገለግልበት ወንበር ሊነሳና ራሱን በእዉነተኛ ንስሐ አጥቦ ከአዉነት ጋር ሊሰለፍ እንዲሁም በእዉነትና በመንፈስ ብቻ አምልኮቱን ሊፈጽምና ሊመላለስ ይገባዋል እዚህ ላይ አንዳንዴ ከጥያቄያችሁ ወጣ እያልኩ የምናገራችሁ ከሥጋና ደም ሓሳቤ ሳይሆን እኔም ሳለስበዉ መንፈስ ቅዱስ እንድናገር እያደረገ ነዉ እንጂ ለጥያቄያችሁ በቀጥታ ቃል በቃል እግዚአብሔር የሚያናግረኝን እመልስላችሁ ነበር ነገር ግን ግድ ይገለጽ ዘንድ ያስፈልጋልና ከጥያቄዎቻችሁ መልስ ዉስጥ የሚገቡትን እዉነታዎች እንድታዉቁና ልብ እንድትሉት ለወደፊት ሸዋጁ መንፈስ በኅሊናቸዉ የሚፈነጭባቸዉ «አገልጋይ ነን ሰባኪ ነን ዘማሪ ነን » በሚሉ ሰዎች እንዳትበከሉና እንዳትመረዙ ፈልጎ ነዉእግዚአብሔር አስቀድሞያለዉን አዉነታእንድታዉቁ ያደረገዉና የሚያደርገዉ ወደ ቀደመ ነገሬ ልመለስና አንዳንድ ምእመናን ሆኑ አገልጋዮች በሽተኛን ሰዉ እንዲሁም የተለያየ ቁስል ያለበትን ሰዉ ጠበሉን እንዲጠጣ ሲያደርጉ ወር አበባ የታያትን ሴት እንደርኩስ ቆጥረዉ ብትታመም እንኳ እንድትጠጣ አይፈቅዱላትም «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ይህም የሚያሳያዉ የቀድሞዎች ጸሐፍት ፈሪሳዉያን አይሁድ ካህናት ርኩሰቱንና ርኩሰት ያልሆነዉን መለየት የተሳናቸዉ ወጋቸዉንና ልማዳቸዉን እንደ እግዚአብሔር ሕግ የሚቆጥሩ ሰዎችን ሕይወት የተላበስን መሆኑን ነዉ የሚያሳያን በዚህ አጋጣሚ ከንጽህና ጋር የታዘብኩትን ልንገራችሁ እናንተ ወደ መስገጃ ቦታ ስትገቡ የእግራቸሁን ንጽህና ሳይቀር ጠብቃችሁ በፍርፃት ስትገቡ በእኛ ቤተክርስቲያን ግን ብዙዎቻችን በዘልማድ ስለማምንመላለስ አንኳን ንጽህናችንን ጠብቀን ወደ ቤተክርስቲያን ዉስጥ ልንገባ ቀርቶ በዋልንበትና በከረምንበት ካልሲ ከነሽታዉ ስንገባ አንዳች ፃፍረት አይሰማንም ነገር ግን አንድ ሰርግ መርሐግብር ላይ ብንጠራ ሰዉነታችንንም ታጥበን ያማረዉን ልብስ ለብሰን ነዉ የምንገኘዉ በዚሁ አንዳንድ አገልጋዮች ራሳቸዉ የማይፈጽሙትንና የማያደርጉትን የዋሁ ምእመናን ላይ ጭነዉ ባልና ሚስትን የሚያጣሉ ልዩነት የሚፈጥሩበትን ትምህርት ልንገራችሁ ይኸዉም ምእመኑ የዋህ ቅን ስለሆነ አንድ መምህር ሆነ ካህን የሚለዉን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ስለሚነሳ አንድ ቀን አንዱ መምህር በጾም ወቅት የግብረ ሥጋ ግንኙነት አታድርጉ በማለት ያስተማረዉን ትምህርት አንድ እህት ይዛ ከባለቤቷ ጋር መጣላት ደረጃ ላይ ደርሳ ነበር ይሁንና አንድ እዉነተኛ የነፍስ እረኛ አግኝተዉ ስለ ጾም ሆነ ስለ ግብረ ሥጋ ግንኙነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት በመስጠት ሊያስታርቋቸዉ ችለዋል የጾም ሥርዓት በአዋጅ የተደነገገ ሲሆን ማንም ሰዉ በራሱ ሥልጣን ሊያሻሸለዉ ሊቀንሰዉ ሊጨምርበት አይችልም ነገር ግን እያንዳንዱ ሰዉ በሥርዓቱ መሰረት ከጾመ ከአግዚአብሔር ጸጋ የሚያገኝበትና ለአዉነተኛ ሕይወት የሚበቃበት ነዉ ስንፍና ካድረገ ደግሞ የሚፈልገዉን ጸጋ የማያገኝበት ለሰይጣን ፈተና የሚጋለጥበት ነዉ ሰዉ በራሱ ፈቃድ የአዋጅ ጾምን ብቻ አይደለም የግሉን ጾም ቢጾም የበለጠ ጸጋ ያገኝበታል እንጂ «ለምን ከአዋጅ ጾም ዉጭ ጾምክ» የሚለዉ ሰዉ የለም ከዓመት ዓመት በቆሉና በሽንብራ ሊኖር ይችላል በጾም ወቅት ባልና ሚሰት ሁለቱም ፈቃደኛ ሆነዉ ከግብረ ሥጋ ተከልክለዉ እዉነተኛ ጾም ከጾሙ የበለጠዉን ጸጋ ያገኛሉ ነገር ግን አንዳቸዉ እንኳ ስሜታቸዉን መቆጣጠር ካልቻሉና የሚፈተኑ ከሆነ ግንኙነት ቢያደርጉ ኃጤአትነት የለዉም ታዲያ «ያ ግብረ ሥጋ ግንኙነት» አታድርጉ ብሎ የሚያስተምረዉ «መምህር ነኝ» ባዩ እንኳን በሰባቱ አጺሟት ከግንኙነት ሊከለከል ቀርቶ ትልቁ የጌታችን ጾም በሆነዉ ዐብይ ጾምና ከሕጻን እስከአዋቂ ድረስ ሱባኤ የሚገቡበትና መሬት ላይ ወርዶዉ በሚተኙበት በእመቤታችን ፍልሰታ ጾም እንዲሁም ሁሉም አምልኮቱን ለመፈጸም ወደ ቤተክርሰቲያን በሚሄድበት በዕለት ሰንበት እሁድና በዐበይት በዓላት እንኳ ግንኙነት ይፈጽማል ይህ የሚያሳየዉ ታዲያ አስመሳይ የአፍ አገልጋይ መሆኑን እንጂ አዉነተኛ አገልጋይና እረኛ አይደለም አንዳንድ አገልጋዮች ቢያንስ አርአያና ምሳሌ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ለመሆን ግድ መፈጸም ያለባቸዉን እንኳ ሳይፈጽሙ እነሱ የማይፈጽሙትንና ሊያደርጉት ፈቃደኛ ያልሆኑትን ሰዎች እንዲያደርጉትና እንዲፈጽሙት ያደርጋሉ ያስገድዳሉ በማለት ከአራቱም ማእዘን ለተሰባሰቡት ለእስልምና እምነት ተከታይ ሴቶች ከተናገሩ በኋላ በመጨረሻ እኛ አባት የእአግዚአብሔር ፍጥረቶችና ልጆች በመቶና በሺዎች ኪሎሜትር አቋርጣችሁ መምጣታችሁ ነፍሳችሁ አዉነትን የተራበችና የምትፈልግ መሆኑን ይገልጻል ስለዚህ ከሥጋና ከደም ስሜት ርቃችሁ ሙሉ እዉነትን ለማግኘት ፈቃደኛ ከሆናችሁ ያልጠየቃችሁትንም ሙሉ እዉነታ ልንገራችሁ። በሚል ርእስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በመስከረም ወር በ ዓም የተጻፈዉን የመጀመሪያዉን የእግዚአብሔር መልአክት መጽሐፍ ማንበብና በፊት ለፊት ሽፋን ላይ በሥዕላዊ መግለጫ ቦታዎቹ ስለተገለጹ መመልከት ትችላላችሁ በዚህች ምድር በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወት እየተመላለሱ ደስተኛ ነኝ የሚል ሰዉ ካለ እሱ ራሱን እያታለለ ያለ ሐሰተኛ ሰዉ ነዉ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጸጋ በራቅን ቁጥር የሰይጣናት መንፈስ በኅሊናችንና በአካላችን ስለሚሰለጥን እርካታን ያጣን ሰላም የሌለን ተቅበዝባዥ ነዉ የምንሆነዉ ሌላዉ በዚህች ምድር ትልቁም ትንሹም የተማረዉም ያልተማረዉም አማኙም ከዛዲዉም እዉነተኛዉም ሐሰተኛዉም ዛብታሙም ደዛዉም መሪዉም ተመሪዉም አለቃዉም ተከታዩም ቀዩም ጥቁሩም ነጩም ጠይሙም ረጅሙም አጭሩም መልከ ቀናዉም መልከ ጥፉም ባጠቃላይ የአዳም ዘር ሁሉ በአዳምና ሔዋን ኃጢአት ምክንያት ባደፈ በጎደፈ በጎሰቆለ ባሕርያት ዉስጥ ነዉ የሚመላለሰዉፁ እንዲሁም በጉስቁልና ኑሮና «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሕይወት ዉስጥ ነዉ የሚወጣዉ የሚወርደዉ ከዚህ ዉጭ ሰዎች የሚለያዩት በሚታየዉ ኮልኮሌ ቁሳቁስ ነዉ ዛብታም ደዛ ተብሎ በልዩነት ሕይወት ዉስጥ የሚኖረዉ እንጂ ከላይ ከተገለጹት ሕይወት ዉጭ የሚኖር ሰዉ የለም ታዲያ ምን የሞላልን ሰዎች ብንሆን እንኳ የምድራዊዉ ሕይወት «ሕይወት ነዉ» ብለን አንድ ቀን በዚህ ምድር መኖርን አያስመኝም ነገር ግን በነጻ ኅሊናችን ተመርተን በምንፈጽመዉ ተግባር እንመዘን ዘንድ በምድር ዉስጥ መቆየት ግድ ነዉና ለመጥራትና ለመንጠር እንዲሁም በአዳምና ሔዋን ዓመጻ ምክንያት ልንቀጣ እርሱ እስከፈቀደዉ ቀን ድረስ በዚህች ምድር እንቆያለን ስለዚህ ከእኛ ከአዳም ዘሮች የሚጠበቀዉ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ በቅንነት በእዉነት በመልካም ተግባር መመላለስ ብቻ ነዉ ፈጣሪ አምላካችንን በአዉነትና በመንፈስ ስናመልከዉ ያኔ ምድራዊ ኑሮዋችንን በሰማያዊ ሕይወት ስለምንመራ ይህች ምድርን የእግዚአብሔር መንግሥት ምሳሌ አድርገን ልንኖርባት እንችላለን በሥጋ ሞት ስንጠራ ይህንኑ የተቀደሰ ሕይወት እንደያዝን በቀጥታ ወደ እዉነተኛ መኖሪያ ቦታችን እንሄዳለን ከዚያ ዉጭ ነፍሳችን አዚህ ምድር ዉስጥ ከአምላኳ ጋር ሳትታረቅና አንድነትና ኅብረት ሳትፈጥር በክፋት በተንኮል በትዕቢት በክህደት በርኩሰት ባጠቃላይ በኃጢአት ሕይወት ብትኖር እንደ ምድራዊ ዓመጻ ሕይወቷ የባሰ ስቃይና መከራ ጭንቀት ወዳለበት ድቅድቅ ጨለማ ቦታ ሲኦል በኋላም ወደ ገፃነመ እሳት ዉስጥ ነዉ የምትገባዉ ስለዚህ ያለዉ እዉነታ ይህን ይመስላልና ለወደፊት ከምንኖረዉ ዘመን አንጻር ምድራዊ ዘመናችን የዓይን ቅጽበት እድሜ እንኳ ያህል ስላልሆነ በምድር ዉስጥ ያለዉን ጉስቁልና ባሕርይና ኑሮ በትእግሥትና በጽናት እያለፋችሁ ከእንግዲህ በኋላ ስለ አዉነት ራሳችሁን መካድና በእዉነት መኖር ይጠበቅባችኋል ወደመጣችሁበት ቦታ ስትመለሱ በተረጋጋና በጸና ስሜት ቀስ ብላችሁ ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዛፃይማኖት ካህናት ዘንድ ቀርባችሁ ያለዉን ሁኔታ አስረድታችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ በሥላሴ ስም ተጠምቃችሁ ከአግዚአብሔር በመንፈስ ልትወለዱና አዉነተኛ ልጆቹ ልትሆኑ አንዲሁም በቅዱስ ሥጋዉና በክቡር ደሙ ልትታተሙ ይገባችኋኃል እስከዛዉ ድረስ ግን በልቦናችሁ ጌታችን መድኃኒታን ኢየሱስ ክርስቶስን «ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ። ነገር ግን በሥጋዊ ዓይናችን ስለምንመለከት እዉነተኛዉ ዓይነ ኅሊናችን ስላልተከፈተልንና በምድራዊ ነገር ብቻ ስለደነዘዝን ታላቁ ማንነታችንና ክብራችንን አላስተዋልንም አቃለነዋል አጥላልተነዋል ክደነዋል ወደ ጥያቄያችሁ ስመለስ እግዚአብሔር «በዚህ ቀን እንዲህ ይሆናልና ተዘጋጁ ዓለም በዚህ ቀን ታልፋለችና ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ » በማለት ለፍጥረቱ ዓመቱን ወሩን ቀኑን ገልጾ አይናገርም ምክንያቱም ሰዎች በነጻ ኅሊናቸዉ በነጻነት ተመላልሰዉ ሁሉ ጊዜ ለእግዚአብሔር የሚመች ሕይወት ይዘዉ እንዲገኙና ሁል ጊዜ በንስሐ እየጸዱ በንጽህናና በቅድስና ሕይወት እንዲኖሩ ነዉ ፈቃዱ እንጂ ይህን ጊዜ ስላለህ እስከዚያ ጊዜ እንደፈለከዉ ሁን ቀኑ ሲደርስ ግን እኔን በመፍራትና ለእኔ በመገዛት ኑር ብሎ ፍጥረቱን አያዝም ለዚህም ነዉ በሥጋ የምንሞትባት ቀን ሳናዉቅ ሞታችንን ተሸክመን የምንዞረዉ ስለዚህ እኛ ሁል ጊዜ እግዚአብሔርን በእዉነትና በመንፈስ እያመለክነዉ በንስሐ በሥጋና ደሙ ተወስነን ነዉ መኖር ያለብን እንጂ «በዚህ ዓመት በዚህ ወር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በዚህ ቀን» እንዲህ ይሆናል ብለን በአጉል ተስፋ ዉስጥ መመላለስና መጨነቅ የለብንም «ዓለም በዚህ ቀን ታልፋለች የሚሉ ሰዎች በራሳቸዉ የፈጠሩት ወይንም ሸዋጁ መንፈስ በኅሊናቸዉ እንዲፈነጭባቸዉ ስላደረጉ እየተጫወተባቸዉ መሆኑን ነዉ የሚያሳየዉ አግዚአብሔር ስለ ዓለም ዕልፈት የተናገረዉ ከእንግዲህ በኋላ ሦስት ዋንኛ ትንቢቶች ናቸዉ የሚቀሩጎ የዓለም ሕዝብ በዓመጻዉና በክህደቱ እንዲሁም በርኩሰቱ ተግባርና ንግግር እግዚአብሔርን እጅግ ስላስቆጣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እንደምታዩትና እንደምተሰሙት የተለያዩ የእግዚአብሔር ቁጣ መገለጫ የሆኑት እግዚአብሔር የለሹ ትዉልድ «የተፈጥሮ አደጋ» የሚላቸዉ የተላያዩ መቅሰፍቶችና ቅጣቶች በዚህ ትዉልድ ላይ ይመጣል በተለያየ መንገድ እያንዳንዱ አገርመንግሥት ቡድን ድርጅት ግለሰብ የዘራዉን የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ፍሬዉን መራራ ቢሆንም ያጭዳል ጽዋዉንም ይጠጣል የዲያብሎስ እንደራሴ ሆነዉ የእርሱን ፈቃድ የሚያስፈጽሙትና የሚፈጽሙት « የዓመጻ ልጆች» የተባሉት ሁሉ ከዚህች ምድር ከተጠረጉና ምድሪቱም ከሕዝብ ደም መጣጮችና ጨቋኞች እንዲሁም ከበደለኞች ከግፈኞች ከዓመጸኞች ከጸዳች በኋላ ኢትዮጵያም ሆነች ሌላዉ የዓለም አገራት ሁሉ በእግዚአብሔርና በእመቤታችን ድንግል ማርያም ዘንድ ሞገስን ያገኙ ለተመረጡና ለተቀቡ ለሁለት ኢትዮጵያዉያን ሥጋዊዉም መንፈሳዊዉም ወንበር ተላልፎ ይሰጣልፁኹ አነሱም በሥጋዊዉም በመንፈሳዊዉም ሕይወት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ አየፈጸሙ እያስፈጸሙ በዓለም ዘንድ በረዛብ በልመና በድርቅ በጦርነት በስደት በችግር የምትታወቀዉን እናት አገራቸዉን ኢትዮጵያን በእዉነትና በመንፈስ ብቻ በማገልገል በኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥት ሥርዓት እንዲዘረጋ አድርገዉ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያዉያን ብቻ አይደለም የዓለም የሥጋዊዉም የመንፈሳዊዉም መሪና አገልጋይ ሆና በእግዚአብሔር እንደራሴ መንግሥትነቷ ህልዉናዋ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ይቆያል እግዚአብሔር እስከመጨረሻዉ ድረስ ከአርሷ ጋር ነዉና ማንም ምንም ሊያደርጋት ስለማይችል ስንዱ እመቤት ሆና አስከመጨረሻዉዓለም ፍጻሜ ድረስ በእግዚአብሔር መንግሥትነቷ ትኖራለች ይ በዚህች ምድር ዉስጥ ያሉት ከቁጥር በላይ የሆኑት ርኩሳን መናፍስትሰይጣናት ቁጥር በዚህች ምድር ዉስጥ በገነት ዉስጥ በማረፊያ ቦታ ዉስጥ በሲኦልና በሰማያት ዉስጥ ከሚኖሩት ሰዎችነፍሳት ጠቅላላ ድምር ቁጥር ጋር ሲቀራረብ በቅርቡ የሚከሰተዉንና የሚታየዉን የእግዚአብሔርን ማጥሪያና ማበጠሪያ ኃይሉን የሚዘነጋና የሚክድ እንዲሁም ከማጥሪያዉና ከማበጠሪያዉ ወቅት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በኋላ የሚፈጠረዉን መልካም ዘመን የኢትዮጵያ ትንሣኤ የሚታይበትን ዘመን የሚዘነጋ ትዉልድ በዓለም በዚህች ምድር ዉስጥ ይወለዳሉ በዚያን ዘመን ዋናዉ የዓመጻ ልጅ የተባለዉ ሐሳዌ መሲህ ሐሳዌ ክርስቶስ ሐሳዌ አምላክ በዓለም ዉስጥ ይወለዳል በዚያን ጊዜ ትዕቢት ክፋት ዓመጻ የተባሉት የፈርዖን የይሁዳ የአርዮስ ወንድምና እህቶች ዋና ተከታዮቹና ስራ አስፈጻሚዎቹ እንዲሁም አጫፋሪዎቹ ይሆናሉ በዚያን ጊዜም ዓመጻ ክህደት ርኩሰት አሁን ካለዉና ከሚታየዉ በባሰ መልኩ ይነግሣል ዋናዉ የዓመጻ ልጅ ሐሳዌ መሲህ ከኅሊና በላይ በሆነዉ ተአምራቱና ኃይሉ እንዲሁም ቅጣቱ ምክንያት አእምሮ ሕጻናትና አእምሮ ቀላሎች ተከታዮቹ ይሆናሉ አእምሮ አዋቂዎችም የተባሉት ምርጥ ነፍሳት ለጥቅማቸዉ ለክብራቸዉ ለሥልጣናቸዉ ለዝናቸዉ ለብልጽግናቸዉ ሲሉ በጽናት ስለ እዉነት ከመቆምና ከመመስከር ይልቅ ልክ እንደአሁን ዘመን ያሉ ሰዎች ለእግዚአብሔር እዉነት ይቆማሉ ብለን ስንገምት ከዲያብሎስ እንደራሴዎች ጋር ሽር ጉድ ሲሉ የፖለቲካ አስፈጻሚ ሲሆነ እንደምንመለከተዉ በባሰ ሁፄታ የዲያብሎስ በሥጋ የሚገለጸዉ የዋናዉ የዓመጻ ልጅ ስራ ፈጻሚና አስፈጻሚ በመሆን ተሰናክለዉ ይቀበሉትል አአምሮ ጽኑአን የሚባለት የበቁ ነፍሳት ግን በተለያየ ድንቃድቅ ተአምራቱና በቁጣዉ ቢፈተኑም እስከመጨረሻዉ ድረስ የአግዚአብሔር አገልጋይና አማኝ ሆነዉ በመጽናት ይቃወሙታል እንጂ አይቀበሉትም ለሦስት ዓመት ተኩል ዋናዉ የዓመጻ ልጅና የአጫፋሪዎቹ እንዲሁም የተባባሪዎቹ የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ጽዋ ሲሞላና በምድር ዉስጥ ያሉት የሰይጣናት ቁጥርና በምድር ዉስጥና ከምድር ዉጭ ባሉት ቦታዎች ያሉት የሰዉ ዘሮች ነፍሳት ቁጥር እኩል በሚሆንበት ዘመን የዓመጻ ልጆች ባለጊዜነት ይሻራል በዚያን ዘመን የዓመጻ ልጆች በምድር ላይ ለወራቶች ያህል በተለያየ መቅሰፍት ይሰቃያሉ በመጨረሻም በመቅሰፍት ሞት ወደ ማረፊያ ቦታ ይጠራሉ በእግዚአብሔር የታመኑት እዉነተኛ አገልጋዮችና አማኞች ደግሞ በምሕረት ሞት ወደ ማረፊያ ቦታ ይጠራሉ አግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስም ከእልፍ አእላፋት ቅዱሳን መላአክትና ከበቁ ነፍሳት ጋር ከሰማያት በታችና ከዓለምና ከሲዖል በላይ ወደ ሆነችዉ እንዲሁም በመጨረሻ ዘመን ከምትዘጋጀዉ ከገዛነመ አሳት ጎን በምትሆነዉ ማረፊያ ቦታ ላይ የመጨረሻ ፍርድ ለመስጠት ይገኛል በዚህች ምድረ ዉስጥ ያሉት ሰይጣናትርኩሳን መናፍስት ከመሪያቸዉ ዲያብሎስ ጋር ወደ ማረፊያ ቦታ መተዉ በቀጥታ ዐወደ ገፃነመ አሳት ዉስጥ ይጣላሉ በዚህች ትልቋ ዓለም ዉስጥ ከምድርከትንጂ ዓለም ጎን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በስተቀኝ በምትገኘዉ ገነት ዉስጥ ያሉት ነፍሳት ወደ ማረፊያ ቦታ ተጠርተዉ በቀጥታ ወደ ሰማያት ዉስጥ ይገባሉ ከትልቋ ዓለም ጎን በስተግራ በምትገኘዉ ሲኦል ዉስጥ የሚገኙት ነፍሳት ወደ ማረፊያ ቦታ ተጠርተዉ በቀጥታ ወደ ገፃነመ አሳት ዉስጥ ይጣላሉ በማረፊያ ቦታ የተገኙት ነፍሳት እንደ ነፍስ ብቃታቸዉ ለሰማያዊ መንግሥት የሚያበቃ ሕይወት የያዙት ተፈርዶላቸዉ ወደ ሰማያት ሲገቡ ለሰማያዊ መንግሥት የሚያበቃ ሕይወት ያልያዙት ደግሞ እንደ ዓመጻ ደረጃቸዉ ፍዳቸዉን ለመቀበል ወደ ገፃነመ እሳት ዉስጥ ይጣላሉ በዚህ መልክ ለእያንዳንዱ ሕያዋን ፍጥረት እንደ ስራዉና እምነቱ ተፈርዶለትና ተፈርዶበት ትልቋ ዓለም ሲኦል ማረፊያ ቦታ ከመኖር ወደ አለመኖር ያልፋሉ በቦታዉ አማናዊ ሕዋ ይተካል ሰማያትና ገፃነመ እሳት ቦታ ብቻ በአማናዊ ሕዋ ዉስጥ ይቀራሉ በሰማያት ዉስጥ የሚገቡት ሰዎችነፍሳት እንደ ጽድቅና ቅድስና ብቃታቸዉ ክብርንና ጸጋን አግኝተዉ እስከ ሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን ድረስ ከቅዱሳን መላእክት ጋር እግዚአብሔርን እያመለኩ በፍጹም ቅድስናና ደስታ ሕይወት ብቻ ይኖራሉ ቅዱሳን መላእክት ሁሉም ቅዱስ ቢባሉም ሥልጣናቸዉና ክብራቸዉ እንደ እምነት ጽናታቸዉና ብቃታቸዉ ይለያያል ይኸዉም ዲያብሎስ ጥንት በሰማያት ዉስጥ «እኔ ነኝ አምላካችሁ እኔን አምልኩ በማለት ዓመጻና ክህደት ሲፈጽም እንደመቃወማቸዉና እንደአለመቀበላቸዉ አምነትና ጽናት ነጥብ ተሰቷቸዉ ነዉ በሰማያት ዉስጥ የተለያየ ሥልጣንና ክብር ያገኙት ለምሳሌ ቅዱስ ሚካኤል በዲያብሎስ ላይ ባሳየዉ የተቃዉሞና ለአምላኩ በታመነዉ እምነትና ጽናት የቅዱሳን መላእክት ሁሉ አለቃ እንዲሆን ተሹሟል በዚህም በሥልጣንና በክብር ከሁሉም መላእክት ይበልጣል በመቀጠል ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል ባሳየዉ የተቃዉሞና ለአምላኩ በታመነዉ እምነትና ጽናት የቅዱሳን መላእክት ሁሉ ሁለተኛ አለቃ ሁኖ ተሹሟል ሌሎቹም እልፍ አአላፋት ወትእልፊት መላእክት እንድ እምነታቸዉና እንዳሳዩት ጽናት ደረጃ ነዉ በሰማያት ዉስጥ ሥልጣንና ክብር አግኝተዉ የኖሩትና የሚኖሩት በዚሁ መልክ ነዉ ሰዎች በምድራዊ ዘመናቸዉ በሚያሳዩት የእምነትና የምግባር ብቃት በሰማያት ዉስጥ ሥልጣንና ክብር የሚያገኙት ጓ ነጥብ ያገኘዉ ጻድቅ ሆነ ነጥብ ያገኘዉ ቅዱስቅድስት ነፍሳት ተብለዉ በሰማያት ዉስጥ ቢገቡም የሚያገኙት ክብር እንደ ነጥባቸዉ ይለያያል በሰማያት ዉስጥ የሚኖሩት ቅዱሳን መላእክት ሆኑ ቅዱሳን ሰዎችነፍሳት የሚገለጹት በረቂቅ አካል በምሳሌያዊ ባሕርይ ሲሆን ከቅዱሳን መላእክት ሆነ ከቅዱሳን ነፍሳት በእምነቷና በሕይወቷ እጅግ በቅታ የተገኘችዉ የእግዚአብሔር እናት ለመሆን የበቃችሁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን በሰማያት ዉስጥ አሁንም የተገለጸችበት ወደፊትም የምትገለጽበት አካል «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር እንደ ልጂ መድኃኔለም በብርፃናዊ ባሕርይ ነዉ እንጂ እንደ መላእክትና ነፍሳት በምሳሌያዊ ባሕርይ አይደለም በዚህም ምክንያት ከፈጣሪ ከልጂ ከኢየሱስ ክርስቶስ በታች ከፍጡራን በላይ ሆና ትከብራለች ትመሰገናለች እስከ ሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን ድረስ በሰማያት ዉስጥ ቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ነፍሳት አምላካቸዉን በእዉነትና በመንፈስ እያመለኩ በቅድስናና በደስታ ሕይወት ከኖሩ በኋላ ጸጋቸዉ አጅግ ይበዛል በዚህም ምክንያት ሁሉም ቅዱሳን መናፍስትና ቅዱሳን ነፍሳት የመጨረሻዉን ቅድስና ብቃት ላይ ስለሚደርሱ ብርዛናዊ ባሕርይ አንዲለብሱ ተደረጎ ተገልጸዉበት የነበረዉ ፍጥረት የሆነዉ ረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ከመኖር ወደ ወደ አለመኖር ያልፋል የመጀመሪያዉ ምሳሌያዊ ባሕርይ ቦታ የሆነዉ ሰማያት በአማናዊ ሕዋ ይተካል ምሳሌያዊ ባሕርይ የሆነዉ የመጀመሪያዉ ፍጥረት ቦታ ሰማያት ዉስጡ ያለዉ ፍጥረት ሙሉ በሙሉ ከመኖር ወደ አለማኖር ያልፋል ከዚያም አግዚአብሔር ጥንት እንደነበረዉ አኗኗር እንደ አማናዊ ባሕርይዉ መጀመሪያና መጨረሻ በሌለዉ አማናዊ ሕዋ ዉስጥ ሕያዉ ሆኖ ይኖራል ቀድሞ ያልነበሩት ከሕያዉነት ዘመን በኋላ ካለመኖር ወደ መኖር የመጡት ቅዱሳን መናፍስትና ቅዱሳን ነፍሳት እንደ አማናዊ ባሕርያቸዉ በብርፃናዊ ባሕርይ ተገልጸዉ ለሕያዉነት ዘመን ከፈጣሪያቸዉ ከእግዚአብሔር ጋር ሕያዉ ሆነዉ ይኖራሉ እንደ አምላካቸዉና እንደ እዉነተኛ አባታቸዉ የማይኖሩበት ጊዜ አይኖርም ከሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን በኃላ በአኛ በሰዎች ኅሊና ቁጥር ለሕያዉነት ዘመን ቢባል የሚቀል ሲሆን ምክንያቱም ከዛሬ አስከ እግዚአብሔር መጀመሪያ ከሌለዉ ጥንት ያልኖረበት ጊዜ የሌለ ጊዜ ድረስ ያለዉን ዘመን በእኛ አእምሮ ወይንም በፍጡር አእምሮ ደረጃ ልናሰለዉ ሆነ ልንገምተዉ እንደማንችል ሁሉ ከሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን ድረስ ያለዉን ዘመን ማለት የዘመኑን መጠን በፍጡር አአምሮ እንዲሁ ልናሰላዉና ልንገምተዉ አንችልም ይኸዉም በሂሳብ ስሌት ሲታይ ከኔጌቲቨ ኢንፊኒቲር እስከ አሁን ያለዉ ዘመን ኢንፊኒቲ ስለሆነ ከፍርድ ቀን አስከ ሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን ድረስ የተባለዉም ለእኛ ኅሊና መጨረሻ የሌለዉ ኢንፊኒቲር ነዉ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ዘመኑ ይታወቃል በምሳሌ ብቻ ብንገልጽ ኳትሪሊዮንን ቁጥር ኳትሪሊዮን ጊዜ እየተደጋገመ ቢባዘ ወይንም ዐዐ ከሚሰጠን ቁጥረ እጅግ እጅግ ለሚበልጥ ዘመን ማለት ነዉ ይህ በእኛ ኅሊና ለሕያዉነት ዘመን ብለን ብንናገረዉ የሚቀል ነዉ በዚህ ዘመን ማለትም ከሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን በኋላ ቅዱሳን መናፍስትና ቅዱሳን ነፍሳት እንደአማናዊ ባሕርይ አንደ ነፍሳቸዉ ባሕርይ ብቻ በአማናዊ ሕዋ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ዉስጥ መኖር ሲጀምሩ በገሃነመ አሳት ዉስጥ በተገለጹበት ረቂቅ አካልምሳሌያዊ ባሕርይ እንደ ኃጢአታቸዉ ደረጃ እየተቀጡና እየተሰቃዩ የሚኖሩት ርኩሳን መናፍስትና ርኩሳን ነፍሳት ለሕያዉነት ዘመን ፍዳቸዉን ከተቀበሉ በኋላ የአግዚአብሔር ቸርነት ይበዛል በዚህም ምክንያት ልክ ነፍሳችን ሕያዉ ብትሆንም በምናቀላፋበት ወቅት አንዳች አንደማታስተዉልና አንደማታዉቅ ሁሉ አነዚህ ዓመጸኛና ከፃዲ የሆኑት ርኩሳን መናፍስትና ርኩሳን ነፍሳት ምንም እንዳያዉቁና እንዳያስተዉሉ ተደረጎ ህልዉናቸዉን ያጣሉ ምሳሌያዊ ባሕርይ የሆነችሁ አምስተኛዉ ቦታ ገዛነመ አሳት ዉስጡ ካሉት ምሳሌያዊ ባሕርይ ፍጥረቶች ጋር ከመኖር ወደ አለመኖር ያልፋል በአማናዊ ሕዋ ይተካል በመጨረሻም መጀመሪያና መጨረሻ የሌለዉ አማናዊ ሕዋና ርኩሳን መናፍስትና ርኩሳት ነፍሳት ህልዉናቸዉን አተዉ የሚኖሩበት ነጥብ ቦታ ብቻ ይቀራል እግዚአብሔርና ቅዱሳን መናፍስትና ቅዱሳን ነፍሳት ብቻ ሕያዉ ሆነዉ በአማናዊ ሕዋ ዉስጥ ይኖራሉ ልክ ምሳሌያዊ ፍጥረት ወይንም በዚህ በሥጋዊ ዓይናችን የምናያቸዉ ፍጥረቶች በዓለም ፍጻሜ ጊዜ ከመኖር ወደ አለመኖር አልፈዉ ምሳሌያዊ ባሕርይ ብቻ በሰማያትና በገዛሃነመ እሳት ዉስጥ እንደሚቀር ሁሉ ከሕያዉነት ዘመን አንድ ቀን በኋላ ፍጥረት የሚባል ወይንም ምሳሌያዊ ባሕርይ ከመኖር ወደ አለመኖር አልፎ የቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳንጻድቃን ሰዎች ነፍስ እንደ አማናዊ ባሕርያዋ የመጨረሻዉን ቅድስናና ደስታ አግኝታ በብርፃናዊ ባሕርይ ብቻ ተገልጻ ከአዉነተኛ አባቷ ከእግዚአብሔር ጋር በአማናዊ ሕዋ ዉስጥ ሕያዉ ሆና ስትኖር ሰይጣናትና የተኮነኑ ሰዎች የተገለጹበት ምሳሌያዊ ባሕርይ ከመኖር ወደ አለመኖር ያልፍና ምንም አንዳያዉቁና እንዳያስተዉሉ ተደርጎ የራሳቸዉን ህልዉና እንዲያጡ ከተደረገ በኋላ በብርፃናዊ ባሕርይ ተሸፍነዉ በነጥብ ቦታ በአማናዊ ሕዋ ዉስጥ ለሕያዉነት ዘመን በበድን ሕይወት ይኖራሉ ይኸዉም በእናቱ ማሕፀን ዉስጥ ያለ ሕፃን እንደማንኛዉም ሰዉ ሕያዉ ፍጥረት ቢሆንም አንዳች የሚያዉቀዉና የሚያስተዉለዉ ነገር እንደሌለና አንዳች እንደማይሰማዉ ሁሉ እነዚህ ዓመጸኛ ነፍሳትም ለሕያዉነት ዘመን ፍዳቸዉን ከጨረሱ በኋላ በዚህ መልክ በነጥብ ቦታ በዚህ መልኩ ይኖራሉ እንግዲያ የእኛ የሰዉ ዘሮች ተስፋ እጅግ እጅግ የላቀ በአንደበት የማይገለጽ መሆኑ በዚህ ይታወቃል ነገር ግን ይህን ታላቅ ተስፋችንን ትተን የከፋዉንና የከረፋዉን የሸተተዉንና የጠነባዉን ዓለም ሙጭጭ አድርገን ይዘን በከፋ በከረፋ በሸተተ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ባጠቃላይ በኃጢአት ሕይወት እንመላለሳለን ሌት ተቀን የምንወጣዉ የምንወርደዉ ለዚህ ቅርፊት ሥጋችን ለአፈር አስረክበን ለምንሄደዉ መሆኑን ሳስብ ነፍሴ እጅጉን ታዝናለች ታነባለች እናንተ እግዚአብሔር መርጧችኋልና ያልጠየቃችሁትን ምስጢር ሁሉ ነዉ እግዚአብሔር ያሳወቃችሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምክንያቱም እኔም እንደእናንተ ፍጡር የሆንኩ ሥጋ ለባሽ ነኝና ይህን ምስጢር ቀድሞ አለዉቀዉም ነበር አሁን ነዉ እንደእናንተ የተነገረኝና የተገለጸልኝ ከእንግዲህ ነፍሳችሁን ወደ ኋላ የሚያስቀርና የሚያዳክም ኃይል የሚኖር አይመስለኝም ለመፈታተን የሚመጣዉ የዲያብሎስን ኃይል በተማራችሁት መሰረት ድል እንደምታደርጉ ጥርጥር የለኝም ታዲያ ከላይ በተገለጸላችሁ መሰረት ስለ ዓለም ፍጻሜ ምልክቱ ነዉ የተነገራችሁ እንጂ «በዚህ ዓመተ ምሕረት በዚህ ወራት በዚህ ቀን ተብሎ አንድም ቦታ አልተገለጸም ስለዚህ እናንተ ዓለም በዚህ ቀን ታልፋለች ብላችሁ አንዳች መጨነቅ ሆነ ማሰብ የለባችሁም የእያንዳንዳችን የዓለም እልፈት ቀን አለተ ሞታችን ስለሆነ ይኸዉም ዳግም የንስሐ እድል ስለማናገኝና ዕለተ ሞታችንን ስለማናዉቅ ሁል ጊዜ ዝግጅዎች ሆነን መገኘት ይኖርብናል ሌላዉ በኅሊናችሁ «ይህች ደኃ ኋላ ቀር የተባለች አገር አሁን ደግሞ በጎጥና በቋንቋ ተከፋፍላ ዘፈኑና ዳንኪራዉ ክፋትና ተንኮሉ ዓመጻዉና ክህደቱ ርኩሰቱ የነገሠባት አገር ኢትዮጵያ እንዴት ቤተሕዝቡ ቤተክህነቱ ቤተምልክናዉ በአንድ መንፈስ ቅዱስ ተዋሕዶ በእግዚአብሔር መንግሥትነት ትገለጻለች። ፉ ዕፅሥሳዕ ፅርጴሲማ ምሳል ቦዖፇፈጠራቻሯቻ ሕያዋን ፍጥረቶች የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁ እግዚአብሔርን እንድትመስሉ ያደረጋችሁ በሥጋዊ ዐይናችን የምናየዉ ፍጡሩና ደካማዉ ጎስቋላዉ ሥጋችሁ ሳይሆን የእግዚአብሔርን ባሕርይ የተላበሰችዉ ነፍሳችሁ ናት የምትገኘዉም ከግንባራችሁ ፊት ለፊት በአንጎላችሁ ዉስጥ ነዉ አእምሮ ኅሊና እያልን በተለምዶ የምንጠራት እርሷ ናት ከእርሷ በሚወጠዉ ኃይል ይህን ሥጋችን ተዋሕዳ ስለምትገኝ በሥጋችን ላይ የሚደርሰዉ ጉዳት ሁሉ ይሰማታል የምታወራዉ የምትሰራዉ የምትንቀሳቀሰዉ አርሷ ናት አንጂ ይህ ሥጋ ከእርሷ ሕይወት ባያገኝ ኖሮ በድን ነዉ የሚሆነዉ የሕጻናት የወጣቶች የጎልማሳላሳ የአዛዉንት ነፍስ አንድ ዓይነት ነዉ ይህም ማለት ነፍስ እንደ ሥጋ አታድግም አትወፍርም አትከሳም አታረጅም አትሞትም ቢበዛ በሥጋ ድካም ምክንያት በተጽህኖ ዉስጥ ትወድቃለች እንጂ እግዚአብሔር በፈቀደላት መጠን ታስተዉሳላለች ታዉቃለች እንጂ ሰዉ በራሱ ተጠቦ የተለየ ምሥጢር ሆነ አዉቀት ሊያመጣ አይችልም እግዚአብሔር ሲፈቅድ ብቻ ነዉ ምሥጢራትም ጥበብም እዉቀትም የሚገለጸዉ ሰዉ ግን በተሰጠዉ እዉቀት ጥበብ ምሥጢራት በነጻ ኅሊናዉ በመልካም ነገር መጠቀምን ትቶ ለጥፋትና ለክህደት እንዲሁም ለርኩሰት ቢያዉለዉ የሚጠየቅበት በዓመጻ የተሰማራዉ ሰዉ ነዉ እንጂ የሰዉ ልጆች እንዲጠቀሙበት እግዚአብሔር የገለጸለት ሰዉ አይደለም የተገለጸለት ሰዉ ለመጥፎ ነገር ካዋለዉ ደግሞ ከማንም በላይ የሚጠየቅበትና ፍዳዉን የሚቀበል ይሆናል አንዳንዴ ይህ ሥጋዊ ዐይናችን የሚመለከት ቢመስልም አንጎል ዉስጥ ያለችዉ ነፍስ ካልተመለከተች ሥጋዊዉ ዐይን አያስተዉልም አይረዳም አያይም በሥጋዊ ዐይናቸዉ እዉርነት ምክንያት ምሳሌያዊ የሆኑ ፍጥረቶችን የማይመለከቱት ዓይነ ስዉራን ነፍሳቸዉ ግን ትመለከታለች በተገለጸችቸበት ሥጋ ስለተገደበች ነዉ እንጂ እንኳን ምድራዊዉን ቀርቶ ከተፈቀደላት ሰማያዊዉን ምሥጢርንና ረቂቃኖቹን ሰይጣናትን ጭምር ልትመለከት ትችላለች እግዚአብሔር ምክንያት ስላለዉ ነዉ እነዚህ ሰዎች ነፍሳቸዉ በሥጋዊዉ ዐይናቸዉ አማካይነት እንዳትመለከት ያደረገዉ እንጂ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ነፍሳቸዉ ሁል ጊዜ የምትመለከት ናት ነፍስ የማታረጅ በመሆኗ ሰዉ ምን ያህል እድሜዉ ቢገፋ እንኳ ምላሱ አይደክምም ምክንያቱም ተናጋሪዋ የማታረጀዉና የማትደክመዉ ነፍስ ናት እንጂ ምላስ ወይንም አፍ አይደለም ምላስንም አፍንም የምታንቀሳቅስ እርሷ በአንጎል ዉስጥ በአካል ደረጃ የተቀመጠችዉ ሕያዊት ነፍስ ናት አንዳንዴ በሕጻንነት አድሜ ያለ ሰዉ በአድሜዉ እንደጎለመሰ ሰዉ ነገሮችን የሚያዉቀዉና የሚያስተዉለዉ አእምሮዉ ቶሎ እንዲከፈትለት በመደረጉ ነዉ እንጂ ልዩ ፍጡር ሆኖ አይደለም ለዚህም ነዉ በአንዳንድ ገድላትና ተአምራት ላይ እግዚአብሔር ለተለየ ዓላማዉ ከማሕጸን ጀምሮ የመረጣቸዉ ጻድቃን በተወለዱ በሦስተኛዉ ቀን ለአምላካቸዉ ምስጋና በማቅረብ ልዩ ምልክት የሚታይባቸዉ እንኳን የተወለደ ሕጻን አይደለም በማሕጸን ዉስጥ ያለ ሰዉ የሕያዊት ነፍስ ባለቤት ነዉና በማሕጸን ዉስጥ ሆኖ የተለያየ ተአምራትና ምልክትን ሊያደርግ ይችላል እንኳን እነዚህ ቀላል ነገሮች አይደለም ከኅሊናችን በላይ የሆነ ተአምራትን አግዚአብሔር በተመረጡት ላይ አድሮ ሊሰራ ይችላል ዋናዉ ተአምርም ሆነ ምልክት እንዲሁም ፈዉስ የሚያደርገዉ ፍጹም እግዚአብሔር መሆኑን አዉቀን ልናመልከዉና ልናገነዉ አንዲሁም ልናመሰግነዉ የሚጋበዉ እርሱ ባለቤቱን እግዚአብሔርን እንጂ ፍጡሩን ሰዉ መሆን እንደሌለበት ልናዉቅ ይገባል ምንም እንኳን የእግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳንና ጻድቃንን መለያቸዉ የቅድስናና የጽድቅ ስራቸዉ እንዳይታወቅ እግዚአብሔር ብቻ ከፍ ከፍ እንዲል ቢሆንም አግዚአብሔር ግን እኛ የአዳም ዘሮች የበረከታቸዉና የጸጋቸዉ ተካፋይ እንድንሆን ለእኛዉ ጥቅም ሲል ነፍስ ከሥጋቸዉ ከተለየችና እስከመጨረሻዉ ጥሪ ድረስ የሚጠበቅባትን ኃላፊነት ተወታ ወደ አርሱ እቅፍ ስትሄድ በተለየ ሁኔታ መታሰቢያ ተደርጎላቸዉ እንዲዘከሩና እንዲከበሩ ፈቃዱ ነዉ እግዚአብሔር ከፈለገ ሰዎች ሥጋዊዉን ሞት ሳይሞቱ ነፍሳትን ሊወስድ ይችላል ከፈለገ ደግሞ ለብዙ መቶ ዓመታት አንዳች ሳይሆኑ በምድር እንዲመላለሱ ሊያደርግ ይችላል ከፈለገም በሕጻንነት አድሜ ሊጠራ ይችላል ከፈለገም በሰማዕትነት ሊጠራ ይችላል ስለዚህ ከእኛ የሚጠበቀዉ እንደ ፈቃዱ መመላለስ ብቻ ነዉ ሌላዉ ግን የእግዚአብሔር ድርሻ ነዉ ሰይጣናት ደግሞ በረቂቅ አካልበምሳሌያዊ ባሕርይ ተገልጸዉ ነዉ በዚህች ምድር እየተቀጡ ያሉት እግዚአብሔር በግልጽ ሳይገለጽላቸዉና ሳይታያቸዉ በፊት በነጻ ኅሊናቸዉ ተመርተዉ ዓመጻና ክህደት ስለፈጸሙ ፍርዱ ቀሎላቸዉ በጎሰቆለ ባሕርይ ብቻ ማለትም ሰላምና እርካታ የሌላቸዉ ቅብዝብዝ እረፍት የሌላቸዉ በስጋትና በጭንቀተ ዉስጥ የሚመላለሱ ሆነዉ ነዉ በዚህች ምድር ዉስጥ የሚኖሩት እኛ የአዳምና ሔዋን ዘሮች ግን እግዚአብሔር በግልጽ ለአዳምና ሔዋን በብርሃናዊ ባሕርይዉ ተገልጾላቸዉ «ይህን ፍሬ እንዳትበሉ ከበላችሁት ግን የሞት ሞትን ትሞታላችሁ ብሎ አዚቸዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የዲያብሎስን ፈተና ማለፍ ተስኗቸዉ በድፍረት «አትብሉ» የተባሉትን ከምሳሌያዊ ባሕርይ በገነት የተፈጠረችዉን ፍሬ በመብላታቸዉ ምክንያት ዓመጻንና ክህደትን ፈጽመዉ ከገነት ወደዚህች ምድር ስለተባረሩ ይህች ምድር ቀድሞ ድቅድቅ ጨለማ የሞላባት የሰይጣናት መቀጫ ነበረችና ለተከታዮቹ ዓማጽያን ነፍሳት መቀጫ ትሆን ዘንድ አሁን በዐይናችን የምናያቸዉም የማናያቸዉም የተለያየ ፍጥረታት በዚህች ምድር ተፈጥረዉ በገነት ተገልጸዉበት የነበረ ረቂቅ አካልምሳሌያዊ ባሕርይ ወደ አለመኖር አልፎ ስለመብል ነዉና ነፍሳቸዉ ያመጸችበት በመብል እንድትቀጣ ታስቦ ይህን ያደፈ የጎደፈ የጎሰጎለ ባሕርይ የተላበሰዉን ሥጋ በዚህች ምድር ከዓመጻ በኋላ ከተፈጠረዉ መሬት ተበጅቶ እንድትዋሓደዉ ተደርጎ ይኸዉ እኛ ዘሮቻቸዉ ጭመር እየተቀጣን አንገኛለን የዲያብሎስን የሽንገላና የማስመሰል ስብከት ሰምተን ነዉና ከገነት የወጣነዉ ይኸዉ በዓለም ዉስጥ የዲያብሎስ ፈቃድ ገኖና ተቀባይነትን አግኝቶ ሌት ተቀን በዓመጻ ሕይወት ዉስጥ እንመላለሳለን ከሰይጣናት የተሻለ እድል ያገኘነዉ ደግሞ እኛ ነን ይኸዉም በንስሐ ወደ ቀድሞ ቦታችን ገነትና ወደተፈጠርንበት ዓላማ ወደ መንግሥተ ሰማያት የመግባት እድል በማግኘታችን ነዉ ይኽም የሆነበት ዋንኛዉ ምክንያት አዳምና ሔዋን አዉነተኛ ንስሐ ስለገቡ እንዲሁም አኛ ዘሮቻቸዉ ባለወቅነዉና ባልፈጸምነዉ ዓመጻ ምክንያት ፍርዱ በእኛ ላይም ስለጸና ነዉ ይህ ደግሞ ለእኛ አጅግ ትልቅ እድል ነዉ ስለዚህ ከአግዚአብሔር በጥምቀት ዳግም ተወልደን በሥጋና ደሙ ታትመን ወደገነትና መንግሥት ሰማያት የመግባት እድል አለን ወደ ገነት ስንመለስም ቀድሞ አዳምና ሔዋን ሲፈጠሩ የተገለጽበትን ረቂቅ አካልምሳሌያዊ ባሕርይ ለብሰን የምንኖር ሲሆን ከፍርድ ቀን በኋላ ደግሞ እንደቅዱሳን መላእክት የበለጠዉን ረቂቅ አካልምሳሌያዊ ባሕርይ ለብሰን ነዉ ወደ ሰማያት ዉስጥ የምንገባዉ በዚህች ምድር ዉስጥ የሰይጣናት ዋና ስራቸዉ ሌት ተቀን እኛን የአዳም ዘሮችን መፈታተንና ኃጢአት በማሰራት ለገሃነመ እሳት መዳረግ ነዉ ምክንያቱም የእነሱን ቃል ሰምተን በዓመጻ ስለወደቅናና በእነሱ ምትክ የተፈጠርን ስለሆነ ኃይለኛ ቅናት ስላደረባቸዉ በምቀኝነት ሕይወት ስለሚመላለሱ ነዉ የእነሱ እርካታ የእኛ የአዳም ዘሮች ዉድቀትና ጉስቁልና ማየት ነዉ ስለዚህ ሁሉ ጊዜ የእነሱን ክፋትና ተንኮል አዉቀን በቅን ሓሳብ በአዉነተኛ ሕይወት በመልካም ተግባር መመላለስ አምላክንም በስራችን በንግግራችንበሓሳባችን ጭመር ልንፈራና ባጠቃላይ ፍጹም እግዚአብሔር በሚደሰትበት ሕይወት ብቻ መመላለስ ነዉ የሚጠበቅብን በዚህ ሥጋዊ ዐይናችን አናያቸዉም እንጂ አልፍ አአላፋት ነዉ ቁጥራቸዉ በዚህች ምድር የሌሉበት ቦታ የለም የሚመቻቸዉ ሰዉ ካገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩት በአንድ ሰዉ ላይ ሊያድሩና ሊያሰቃዩት እንዲሁም ከሰዉነት ማዕረግ ሊያሶጡት ይችላሉ የዚህን ያህል ነዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ጭከናቸዉ እንዲሁም ጻድቁን ሆነ ኃጢአተኛዉን ከመፈታተን ወደ ኋላ የማይሉ ባገኙት አጋጣሚ ኃጢአት ለማስፈጸምና ከአምላካችን ጋር ለማጣለት ለዓይን ቅጽበት ያህል እንኳ ከሰዉ ዘሮች ኅሊናና አካል የማይለዩ ናቸዉ ስለዚህ በዋናነት ከኃጢአት መጠበቅ ያለብን ከሓሳባችን ነዉነ ምክንያቱም ሰይጣናት እያሰብን ያለዉን ሁሉ ስለሚያዉቁና ስለሚሰሙ የክፋት ሆነ የርኩሰት ሓሳብ ቢመጣብን እንኳ ወዲያዉ ልንቃወመዉና መንገዱን ልንዘጋባቸዉ ይገባል ያለበለዚያ ያንን የክፋትና የርኩሰት ሓሳብ በኅሊናችን በመደጋገም ሹክ እያሉን ለኃጢአት ስራ ሊያሰልፉንና ወደ ተግበር እንድንለዉጠዉ ሊፈታተኑን ይችላሉ እነሱ በእርግጠኝነት የማያዉቁት እያሰብን ካለነዉ ዉጭ የወደፊቱን ሓሳብ ተግባር ንግግር ጭምር ነዉ ነገር ግን እንደ ማንኛዉም ሰዉ አቋማችንን በመመልከት ስለ ወደፊቱ በራሳቸዉ ግምት እየሰጡ በምን መንገድ እንደሚያሰናክሉንና በፈተና እንደሚጥሉን ይራቀቁብናል እኛም ታዲያ ንጹህ ኅሊና በመያዝ እነሱን የምናሳፍርበትና ድል የምናደርግበትን ከዚያም አልፎ ሌተ ተቀን የምንቀጣበትንና የምናቃጥልበትን የተለያዩ መሳሪያዎችን ጸሎት ጾም ስግደት ምጽዋት መያዝ ይኖርብናል ረቂቃን ስለሆኑ ወደማንኛዉም ሰዉ ኅሊናና አካል ይገባሉ ይወጣሉ ይህ ሥጋችን ለእነሱ ሰፋፊ ወንፊት ነዉ በዚህች ምድር ዉስጥ ሊገድባቸዉ የሚችል ምሳሌያዊ ፍጥረት ሆነ ምስሌያዊ ባሕርይ የለም እንኳን የእኛ አካል ቀርቶ መስታወት ለእነሱ በጣም ሰፋፊ ወንፊት ያህል ነዉ የሚታየዉ በዉሎዋችንና በአዳራችን ከእኛ እንደማይለዩን ለማወቅ ከፈለጋችሁ ወደ ኅሊናችንና አካላችን አኛን ለመፈታተንና ለማዳከም የሚገቡት ረቂቃን ርኩሳን መናፍስት በአፋችን በኩል በማስፋሸክና በማዛጋት ይወጣሉ በአፍንጫችን በኩል ደግሞ በማስነጠስ ይወጣሉ በጉሮሯችንና በአፋችን በኩል በማሳል ይወጣሉ በቆዳችን በኩል በማሳከክ ይወጣሉ በመገጣጠሚያችን በኩል በማንጠራራት ይወጣሉ በፊንጢጣችን በኩል በማስፈሳት ይወጣሉ ከእግዚአብሔር ጸጋ የተለዩ ጎስቋሎች ስለሆኑ እኛ በምንጸየፈዉ አነሱ ደግሞ ዙፋን መቀመጫቸዉ በሆነዉ ዓይነምድርና ሽንት እንዲሁም ንፍጥና አክታ ላይ አድረዉ አብረዉ ይወጣሉ በእግዚአብሔር መንፈስ ምንም ምልክት ሳያሳዩ ከኅሊናችን ሆነ ከአካላችን ተቃጥለዉ ብን ብለዉ ይወጣሉ ይህም የሚያሳየዉ ከእግዚአብሔር ጸጋ መለየት ለእንደዚህ ለተጎሳቆለና ለተዋረደ ሕይወት እንደሚዳርግ ነዉ እዚህ ላይ የምነግራችሁ ሰይጣናት ወደ ኅሊናችን ሆነ አካላችን ቢገቡም ቢወጡም ነፍሳችንን ሆነ ሥጋችንን በራሳቸዉ ሥልጣን አንዳች ጉዳት ሆነ ጥቃት ሊፈጽሙ አይችሉም ሊጎዱ ሆነ ሊያጠቁ የሚችሉት ለእነሱ በኃጢአት ባሪያ የሆነዉን ሰዉ ነዉ ፈቃዳቸዉን የምንፈጽም ከሆነ በነፍሳችን ሆነ በሥጋችን ላይ ሊሰለጥኑ ይችላሉ ከዚያ ዉጭ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሚመላለሱትን ሰዎች አንዳች «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የመጉዳትና የማጥቃት ሥልጣን የላቸዉምፁ ይልቁኑ ለመፈታተን ወደ ኅሊናችንና አካላችን ሲገቡ እየተቃጠሉ እየተሰቃዩ እየነደዱ ይወጣሉ ይኖራሉ ለመጉዳት እንኳ ቢያስቡ የእግዚአብሔር መላእክት ካሉበት ከሰማያት ከኅሊናችን ርቀት በላይ የሆነዉን ርዝማኔ ከዓይን ቅጽበት ባነስ ጊዜ ዉስጥ አቋርጠዉ በመምጣት ርምጃ ይወስዱባቸዋል አይቀጡ አቀጣት ይቀጧቸዋል ስለዚህ ሰይጣናት እንዲህ ያደርጉናል » ብለን አንዳች ልንሰጋና ልንፈራ አይገባም አቅማቸዉንና በቅዱሳን መላአክት እንደምንጠበቅ ስለሚያዉቁና እኛን በቀጥታ ሊጎዱን ስለማይችሉ ሊያጠቁንና ሊጎዱን የሚችሉት ለዚያዉም ዋጋ እንድናገኝበት እግዚአብሔር ከፈቀደ ብቻ በሰዎች ኅሊና ላይ በማደር የክፋትና ጥላቻ ስሜት በኅሊናቸዉ በመፍጠር በመገፋፋትና በመፈታተን ለጥቃት በማነሳሳት ነዉ ይህም የሚሆነዉ ምንም እንኳን የሰዎች ነፍስ ነጻ ፈቃድ ያላት ቢሆንም ኃይሏ ግን የተገደበ ነዉ ለክፋት ሆነ ለጥፋት ከመሰማራቷ በፊት ከዓይን ቅጽበት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ አግዚአብሔር ካለበት ቦታ አርምጃ ሊወስድባት ወይን በቅዱሳን መላአክት ርምጃ ሊያስወስድባት ይችላል በመሆኑም ሰዎች የአግዚአብሔርን ምርጦችን ካልተፈቀደላቸዉ በስተቀር አንኳን መግደልና ጉዳት ማድረስ ቀርቶ አንዲቱን ጸጉር እንኳ የመንቀል ኃይልና ሥልጣን የላቸዉም ነቢያት ሐዋርያት ሰማዕታት ጻድቃን የተለያዩ መከራና ስቃይ የደረሰባቸዉ አግዚአብሔር ለታላቁ ሰማያዊ ክብርና ሽልማት ሊያበቃቸዉና ትዉልዱም ስለ እዉነት ራሱን በመካድ እስከመጨረሻዉ አቅታ ድረስ እንዲጸና ትምህርት እንዲወስድበት ነዉ አንጂ እነዚያን ዓመጸኞችንና ግፈኞችን በዓይን ቅጽበት ጊዜ ዉስጥ እንዳልነበሩ ሊያደርጋቸዉ ይችል ነበር አንኳን ፍጡሮቹ ሰዎች አይደለም እርሱ ፈጣሪ አግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዉ ሆና በዚህች ምድር በተመላለሰበት ዘመን ከኅሊናችን በላይ የተለያየ መከራና ስቃይ ደርሶበታል ስለዚህ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ የተለያየ መከራና ስቃይ ቢመጣብን እስከመጨረሻዉ ድረስ ከእዉነት ጋር መቆም ነዉ ያለብን እንጂ ቅርፊት ሥጋ ለባሾችን ፈርተን የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ተግባር ፈጻሚና ተባባሪ መሆን የለብንም ግፈኞችና ዓመጸኞች ሰዎች የግፍና የዓመጻ ጽዋቸዉ ሲሞላ በአንድም ይሁን በተለያየ መንገድ በዚህች ምድርም ፍዳቸዉን ተቀብለዉ ነዉ ወደ ይግባኝና ንስሐ አድል ወደሌለበት የመቀጫ ቦታ የሚሄዱት እኛ ግን መቼም ይሁን መች በምድራዊ ሕይወት ዘመናችን ሁሉ ስለ ሰዎች ስንል እግዚአብሔር የማይፈቅደዉንና የማይወደዉን ስራ መስራት የለብንም እንዲሁም ሰዉን በመፍራት የእግዚአብሔርን ሕግና ትዕዛዝ በመጣስ እግዚአብሔርን መካድ የለብንም በመንፈሳዊ ሕይወት ጉዚችሁ የምታቀርቡት ጸሎት ጾም ስግደት እንዲሁም ምጽዋት በግብታዊነትና በስሜት መሆን እንደሌለበት ላሳስባችሁ እወዳለሁ ምክንያቱም «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሰይጣናት ቅናተኞች ስለሆኑ ከአቅማችሁ በላይ እንድትፈጽሙ በማድረግ ለተለያየ ፈተናና ለወረተኛነት ሕይወት ሊዳርጓችሁ ይችላሉ ስለዚህ ጸሎታችሁን ከአቡነ ዘበሰማያትና በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል ትጀምሩና የዘወትር ጸሎት በማስከተል ወደ የየዕለቱን ዉዳሴ ማርያምና ይዌድስዋ መልአክትን መጸለይ እየጠነከራችሁና ጸጋዉ እየበዛላችሁ ሲሄድ ደግሞ አንቀጸ ብርፃንን መዝገበ ጸሎት ላይ ያለዉን ወዳሴ አምላክ የየዕለቱን እንዲሁም መልክአ ኤዶም ከዕለት ዕለት ስትጠነክሩ ደግሞ ወርዛዊ መታሰቢያ የሚደረግላቸዉ ከሥላሴ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም ከአመቤታችን ድንግል ማርያም በመነሳት የቅዱሳንና የጻድቃንን መልክአ መልክ በመታሰቢያቸዉ ቀን ሲሆንላችሁ ደግሞ ዲያብሎስ የሚዳመጥበትን የእመቤታችን ዉዳሴ የያዘዉ መጽሐፈ አርጋኖን ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ እፄ ያልጠቀስኳቸዉ የጸሎትና የምስጋና መጻሓፍቶችን ልትጸልዩ ትችላላችሁ እነዚህ ጸሎቶች ላይ ለመድረስ ዓመታትና ዐሥራ ዓመታት ሊፈጅባችሁ ይችላል ነገር ግን እንደ ተሰጣችሁ ጸጋ መትጋት ይገባችኋል ቢያንስ ቢያንስ ግን ለሰይጣናት ኃይል ማዳከሚያ ዋና መሳሪያ የሆነዉን የእመቤታችንን ወዳሴ ማርያም የየዕለቱን ማድረስ ይጠበቅባችኋል አዚህ ላይ የማስታዉሳችሁ ትዉልዱ እስከ አሁን ድረስ ችላ ያለዉን የኢትዮጵያዉያን የቅዱሱ ኪዳን ጸሎት የሆነዉን የኢትዮጵያዉያን ቃል ኪዳን ጸሎት ልክ እንደ ጸሎተ ፃዛይማኖት ከጸሎታችሁ መጨረሻ ላይ ሁል ጊዜ ልትጸልዩት ይገባል አምላካችን ሰዉ ሆኖ በምድር በተገለጸበት ዘመን በመዋዕለ ሥጋዌዉ ያስተማረን ጸሎትና በአርሱ መንፈስ በተመሩት ቅዱሳን ያዘጋጁልን ሁል ጊዜ የሚጸለየዉ ጸሎት በግእዝ ቋንቋችን «አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ትምጻእ መንግሥትከ ወይኩን ፈቃድከ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር ሲሳየነ ዘለለ ዕለትነ ሀበነ ዮም ኅድግ ለነ አበሳነ ወጌጋየነ ከመ ንሕነኒ ንኅድግ ለዘአበሰ ለነ ኢትአብአነ እግዚኦ ዉስተ መንሱት አላ አድኅነነ ወባልሐነ እምኩሉ አኩይ እስመ ዚአከ ይእቲ መንግሥት ኃይል ወስብሓት ለዓለም ዓለም በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ ኦ እግዝእትየ ማርያም ሰላም ለኪ ድንግል በኅሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ እመ እግዚአብሔር ጸባዖት ሰላም ለኪ ቡርክት አንቲ አምአንስት ወቡሩክ ፍሬ ከርሥኪ ተፈሥሒ ፍሥሕት ኦ ምልእተ ጸጋ እግዚአብሔር ምስለኪ ሰአሊ ወጸልዩ ኀበ ፍቁር ወልድኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይስረይ ለነ ንጣዉኢነ በኢትዮጵያዉኛአማርኛ ቋንቋችን ሲተረጎም ደግሞ «አባታችን ሆይ በሰማይ የምትኖር ስምህ ይቀደስ መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁም በምድር ትሁን የዕለት እንጀራችንን ስጠን ዛሬ በደላችንንም ይቅር በለን እኛ የበደሉንን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ይቅር እንደምንል ወደ ፈተናም አታግባን ከክፉ አድነን እንጂ መንግሥት ያንተናትና ኃይል ምስጋናም ለዘላለሙ አሜን አመቤቴ ማርያም ሆይ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም አእልሻለሁ በሓሳብሽ ድንግል ነሽ በሥጋሽም ድንግል ነሽ የአቸናፊዉ የእግዚአብሔር እናት ሆይ ላንች ሰላምታ ይገባል ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽና የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነዉ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነዉና ከተወደደዉ ልጅሽ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ይቅርታንና ምሕረትን ለምኝልን ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ለዘላለሙ አሜን የሚል ነዉ የፃይማኖት ጸሎት እኛ ኢትዮጵያውያን ኹሉን በያዘ ሰማይንና ምድርን የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ አንድ አምላክ በሚኾን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ አንድ የአብ ልጅ አንድ ጌታ በሚኾን በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን እርሱም ከብርፃን የተገኘ ብርዛን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ በመለኮቱ ከአብ ጋራ የሚተካከል ኹሉ በአርሱ የኾነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በሰማይ ካለው በምድርም ካለወ ያለእርሱ ምንም ምን የኾነ የለም ስለእኛ ስለሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ፍጹም ሰውን ኾነ በዴንጤናዊው ዲላጦስ ዘመን ስለእኛ መከራን ተቀበለ ተሰቀለ ሞተ ተቀበረ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በክብር በምስጋና ወደሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ በዙፋኑ ተቀመጠ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ በምስጋና ይመለሳል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን እርሱም ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረፀና በነቢያት አድሮ የተናገረው በሐዋርያት ላይ የወረደውና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት ዓለሙን በጸጋው የሞላው ቅድሱ የእውነት መንፈስ ነው ለእርሱም ከአብና ከወልድ ጋራ በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለንም ኢየሱስ ክርስቶስ በአበው ልቦና በመሠረታት በነቢያት ቃል ባጸናትና በሐዋርያት ጉባኤ በፈጸማት የእርሱ ሥጋና ደም ለመሥዋዕትነት በሚቀርብባትና የመንፈስ ቅዱስ ጸጋዎች በሚሰጡባት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን ኃጢአት በሚሠረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን በሙታን ትንሣኤ በሚመጣውም ሕይወት እናምናለን ለዘለዓለሙ አሜን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የኢትዮጵያውያን የቃል ኪዳን ጸሎት ደግሞ እኛ ኢትዮጵያውያን እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጣቸውን ቃል ኪዳናት ጠብቆ በኖረው በቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያዊነታችን እናምናለን አምላካችን ይህን ኢትዮጵያዊ ሰውነት በመጀመሪያዉ የአበው ዘመን በአዳምና ሔዋን ሥርዓተ ጋብቻ በኪዳነ ልቦና መሥርተው ከዚያም በኖኀ ቀስተ ደመና በመልከ ጴዴቅ ቁርባንና በአብርፃም ግርዛት ገንብቶ አሳደገው በመካከለኛውም የሕግ ዘመን በሙሴ ጽላትና በዳዊት ዙፋን አዋቅሮ የኢትዮጵያዊቷን ንግሥት የማክዳንና የእሥራኤላዊውን ንጉሥ የሰለሞንን የዘር ሐረጎች በማዋሓድ በኪዳነ ኦሪት አከናወነው በመጨረሻውም የሕይወት ዘመን ከዚህ ምሉዕ ትውልድ ከተገኘችው ከድንግል ማርያም በተወለደው ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም አጽንቶና ዘለዓማዊውን ዘውድ አቀዳጅቶ በኪዳነ መንፈስ ቅዱስ ፈጸመውኢትዮጵያ እንዲህ በቀጠለው በቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያዊው ሰውነት ቤተ ሕዝቧን ቤተ ክህነቷንና ቤተ ምልክናዋን አንድ አድርጋ የኖረች የእግዚአብሔር መንግሥት እንደኾነች እናምናለን እርሱ ክርስቶስ ተብሎ እኛን ክርስቲያን ያሰኘን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀደመው ዘመን ምሳሌው ኾኖ በተገለጠው በመልከ ጴዴቅ ኢትዮጵያዊነትና ሹመት ከሴም ከካምና ከያፌት ዘሮች ተወልዶ የዘለዓለም ካህናችንና ንጉሣችን እንደኾነ እናምናለን እርሷ ኢትዮጵያ ተብላ እኛን ኢትዮጵያውያን ያሰኘችን ድንግል ማርያም አምላክን በመውለዲ አማናዊቷ የሕያዋን እናትና ዘለዓለማዊቷ ታቦተ ጽዮን የሰማይና የምድር ንግሥትም እንደኾነች እናምናለን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የኾነው የቀስተ ደመና ምልክት በኖኀ አማካኝነት ከእግዚአብሔር የተቀበልነው የዘለዓለም ሰንደቅ ዓላማችን እንደኾነ እናምናለን የቅዱሱ ኪዳን ፍጻሜ ለኾነው ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረው ሞአ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ የሚለው መለኮታዊ ቃልና ለድንግል ማርያም የተነገረው ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊፃዛ ኀበ እግዚአብሔር የሚለው ትንቢታዊ ቃል ከአምላካችን ያገኘነው የዘለዓለም ማኀተማችን እንደኾነ እናምናለን በቅዱሱ ኪዳን ጸጋ ከእግዚአብሔር በመንፈስ የመወለደን ክብር ስላገኘን በዚህ በልጅነታችን የእግዚአብሔር መንግሥት ወራሾችና አገልጋዮች እንደኾንን እናምናለን ይህን ልጅነታችንን አጽንተን ለመጠበቅ የመንግሥቱ ወራሽነታችንን ለማረጋገጥና ንጹሕ አገልግሎታችንን ለመቀጠል ኃጢአታችንን ዘወትር በንስሐ እያጠራንና የክርስቶስን ሥጋና ደም እየተቀበልን መኖር እንዳለብን እናምናለን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የኢትዮጵያዊነት ዛይማኖታችን በይፋ የሚገለጠውና ተለይቶ የሚታወቀው በኢየሱስ ክርስቶስና በድንግል ማርያም ፍቅር ኾነን በምንፈጽመው የኢትዮጵያዊነት ምግባራችን እንደኾነ እናምናለን የቅዱስ ኪዳን ኢትዮጵያዊነታችንን በየልቦናችን ጽፎ ያስተማረን ጠብቀነው አንድንኖር ያደረገም እንደ ቃል ኪዳኑ አግዚአብሔር እንደኾነ አናምናለን ለዘለዓለሙ አሜን ሌላዉ አደራ የምላችሁ ጸሎታችሁ ትጠርም ትርዘምም የምትጸልዩትን በማስተዋል እየተረዳችሁ ልተጸልዩ ይገባል እንጂ በዘልማድ የምታነበንቡ ከሆነ ላትጠቀሙበት ትችላላችሁ ጸሎታችንን ወደ ፈጣሪ ስናቀርብ ሰይጣንን በምጣድ ላይ ጥደነዉ ከስር እሳት አያነደድንበትና አያቃጠልነዉ መሆኑን ልናስተዉል ይገባል በተመስጦ ስንጸልይ ሰይጣን መፃል ለመፃል በተፋፋመ እሳት ዉስጥ እየነደደ መሆኑን ልናዉቅ ይገባል ሓሳባችንን የሚሰርቅብን ከሆነ ግን ከቃጠሎዉ ለመዳን ሲል ዳር ዳሩን ብቻ አሳቱን አንደምንቆሰቁስበትና ፍሙ ሳይሆን ዳር ዳር ላይ የተቆሰቆሰዉ አሳት ብቻ መጠነኛ መለብለብ የሚደርስበት መሆኑን ልንረዳ ይገባል ስለዚህ ጸሎታችንን በተመስጦ ጾማችንን በትጋት ስግደታንን በጽናት በምናቀርብበት ጊዜ ሰይጣናት እጅግ ስለሚቃጠሉ ከእኛ ይርቃሉ ኃይላቸዉ ስለሚዳከም የእግዚአብሔር ጸጋ ይበዛልናል ነፍሳችን በሥጋችን ላይ የበላይነትን ትጎናጸፋለች በዚህም ምክንያት ራሳችንን እንገዛለን ስሜታችንንም እንቆጣጠራለን ዋናዉ መንፈሳዊነት መገለጫ የሆነዉ ራስን መግዛት ነዉና ይህ ደግሞ የሚሆነዉ ነፍሳችን በሥጋችን ላይ የበላይነትን ስትጎናጸፍ ነዉ ጾሙም ዋንኛ የሰይጣናት ድል መንሻና ራስን መግዣ መሳሪያ መሆኑን ተረድታችሁ ለዚህ ሥጋችሁ ሳትሳሱ ልትጾሙ ይገባል ሥጋችሁ ሁል ጊዜ ያማረዉንና የፈለገዉን መብላትና መጠጣት ነዉ የሚፈልገዉ ነፍሳችሁ ደግሞ ሥጋችሁ እንደፈለገዉ ከሆነ ልትቆጣጠረዉና ልትመራዉ አቅምና ኃይል ያንሳታል ስለዚህ ጾም ዋና የነፍሳችሁ መሳሪያ መሆኑን ልታዉቁ ይገባል ጾሙንም ስትጀምሩ በመጀመሪያ ከጥሉላት ምግብ ከሥጋዉ ከቅቤዉ ከእንቁላሉ ከወተቱ ወዘተ ከመሳሰሉት ተከልከሉ ከዚያም ለተወሰነ ሰዓታት ካለመብልና ካለመጠጥ መቆየትን ልመዱ ያፄ የጾሙ ጥቅም ስለሚገባችሁ ማንም ሳያዛችሁ በራሳችሁ ጊዜ የጾሙን ሰዓት ከዕለት ዕለት እየጨመራችሁ ትሄዳላችሁ «ጥቅሙን ስትረዱ ለምን ቀኑን ሙሉ አንጾምም። በማለት ለኅሊናቸዉ ተናግረዉ እስከ ዕለተ ሞታቸዉ ድረስ አንዳች ምስጋናን ሆነ ሽልማት ሳይፈልጉ በንጽህናና በቅድስና ሕይወት ለመኖር የወሰኑ ሲሆን እፄ የጨለማዉ ገዥ ግን በአቋማቸዉ አልተደሰትኩም ምክንያቱን ስንቱን በከንቱ ዉዳሴ ጥያለሁና እንዲሁም ስንቱን ራሱን እንደተለየ አድርጎ እንዲቆጥር አድርጌ በዓመፃና በክህደት እንዲሁም በርኩሰትና በትዕቢት ሕይወት አሰልፌዋለሁና ነዉ እናንተ «የእግዚአብሔር አገልጋይ ነን መንፈሳዊ ነን እያላችሁ የነቢያት የሐዋርያት የሰማዕታት የጻድቃን ተጋድሎ ብቻ በአንደበታችሁ ሌት ተቀን የምታወሩ የእነሱን ታጋድሎ ግን አንደ አስረኛዉን እንኳ ለመፈጸም ፈቃደኞች ያልሆናችሁ በስማቸዉ የምትነግዱ የእናንተ ሆድ ከሞላ ከተከበራችሁ «ቅዱስ ቅዱስ ብፁዕ ብፁዕ መምህር መምህር ሊቅ ሊቅ አባት አባት» ከተባላችሁ ከተመቻቸላችሁ ምእመኑ እዉነትን አወቀ አላወቀ ደንታ የሌላችሁ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ተጠበቀ አልተጠበቀ ግድ የማይላችሁ ወንጌል ተሰበከ አልተሰበከ አንዳች ስሜት የማይሰጣችሁ የእግዚአብሔር ሕግና ሥርዓት ተጠበቀ አልተጠበቀ ከግል ጥቅማችሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አንጻር ብቻ የምትመለከቱ ሕግና ሥርዐት በመጣስ ጥቅም የሚገኝበት ከሆነ ዋና ተባባሪና አስፈጻሚ የምትሆኑ በእግዚአብሔር ቃል የምትነግዱ ስለ አዉነት ራሳችሁን ክዳችሁ መመስከር አይደለም የእኔ የጨለማዉ ገዥ አእንደራሴዎቼና ባለማሎቼ አንዳች ሳያዚችሁና ሳያስገድዷችሁ በጸበል ላይ እንደሚለፈልፍ «እኛ የዲያብሎስ እንደራሴዎችና ባለሟሎች ጉዳይ አስፈጻሚ ነን የሕይወት መንገድ የሆነችዉን ተዋሕዶ ዛይማኖት ለማጥፋትና ክህደትና መናፍቅነት ለማስፋፋት የሚተጋ መንግሥትድርጅት አባላትና የዓመጻ የክህደት እንዲሁም የርኩሰት ተግባራቸዉን የምናስፈጽም ካድሬዎች ነን ቀሪዎቻችንም የዚሁ የዓመጻ ድርጅትርድን ደጋፊ ነን የምትሉ እኔ «ኅሊናችሁን ሽጡልኝ የእኔን ስራ እንደጥሩ አድርጋችሁ መስክሩልኝ» ሳልላችሁ እናንተ ግን ከእኔ ከጨለማዉ ገዥ ሽልማት የምታገኙ ይመስል አንዳችሁ አዳችሁን ለመቅደም በቴሌቨዥን በሬድዮ በመጽሔት በጋዜጣ በኢንተርኔት ባጠቃላይ መገናኛ ብዙኃን በወርቃማ ቃላትና አባባል ታጅባችሁ ምስክርነትን ትሰጡልኛላችሁ እኔ የጨለማዉ ገዥ ለዘመናት ያየሁትና የማዉቀዉ እናንተ ነቢያት ሐዋርያት ሰማዕታት ጻድቃን ቅዱሳን» የምትሏቸዉ በዚህች ምድር ቆይታቸዉ ምንም ሳይባሉ ኅሊናቸዉን መሸጥ አይደለም በተቃራኒዉ ስለ ኅሊናቸዉ ራሳቸዉን በመካድ ስለ አዉነት በመመስከራቸዉና በእዉነት በመኖራቸዉ ምክንያት የተለያየ ፈተናና መከራ ደርሶባቸዉ ወደ አምላካቸዉ እቅፍ ሲሄዱ ነዉ እንጂ « ቅዱስ ብፁዕ መልአክ ሊቅ ጻድቅ» ተብለዉ በምድራዊ ሕይወት ዘመናቸዉ ሲጠሩ አልሰማሁም አላየሁም ይላል ከተራዉ እስከ ታላቅ እስከተባሉት ሰዎች ድረስ ለመገንደስና ለማዋረድ እንዲሁም ኃጢአት ለማስፈጸም ከፈጣሪ ለማጣላት ወደ ኋላ የማይለዉ ጨካኙ የጨለማዉ ጌታና ገዥ ዲያብሎስ ከሰይጣናት ጋር በመሆን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ክፍል ሦስት ምዕራፍ «በኢትዮጵያ ከሰማኒያ በላይ ቋንቋ የሚናገሩ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ተወካይ የተለያዩ ሃይማኖት አባቶች የተለያዩ አገራት ተወካዮች የአዲስቷ የፌደራላዊ ዴሞክራሲ ሪፐብሊክ ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሜኒስትርና ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ካድሬዎቻቸዉ የብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታት ፕሬዘዳንቶችና ከፍተኛ አመራሮቻቸዉ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች አባላትና ደጋፊዎችየአገር ሽማግሌዎች የጎሳ መሪዎች እንዲሁም ከተባበሩት መንግሥታት የየአገሩ መሪዎች ተወካይ ከአፍሪካ ኅብረትና ከአዉሮፓ ኅብረት በታዛቢነት በተገኙበት ባጠቃላይ የተለያዩ አካላትን የሚወክሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ከአገር ዉስጥም ከዉጭ አገርም ታላቅ የዉይያት መድረክ ተፈጥሮላቸዉ ታሪካዊ ስብሰባ በኢትዮጵያ ምድር በተመረጠዉና በተለየዉ ቦታ ላይ ተደርጓል በመጀመሪያ ንግግር እንዲያደርጉ እድል የተሰጣቸዉ ከሰማኒያ በላይ ቋንቋ ተናጋሪዎች የሆኑት የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ተወካዮች ሲሆኑ እነሱም የተከበሩ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ከአገር ዉስጥና ከዉጭ የተጋበዛችሁ አንግዶች በሙሉ እኛ አሁን የምናቀርበዉ ጥያቄና አስተየያት ባስተማራችሁንና በሰበካችሁን ትምህርት ተነስተን ነዉ ይኸዉም እናንተ የእግዚአብሔር ፍጥረቶች አይደላችሁም የገዥ መደቦች ለመጨቆን አእንዲያመቻቸዉና እናንተን አስፈራርተዉ እንድትገዙላቸዉ ለማድረግ «እግዚአብሔር ምንትስዬ» እያሉ ተፈጥሮ የለገሰቻችሁን በአግባቡ እንዳትጠቀሙ ለማድረግ ነዉ እንጂ ዘሮቻችሁ እንስሳ መሰል ጦጣዎች የሆኑ እናንተም በቀስ በቀስ ዕድገትና ለዉጥ በኢሾልሽን አማካይነት አሁን ላላችሁበት ሰብእና የበቃችሁት ናችሁ «የአዳም ዘሮች ናችሁ አንድ ወገን አንድ ቤተሰብ ናችሁወዘተ» የሚባለዉ ተረት ተረት ነዉ እያላችሁ ነዉ በዚሁ ትምህርታችሁ መሰረት ይኸዉ ተፈጥሮ ባደለችንና የመጨረሻዉ ሰብእና ብቃት ደረጃ መድረሳችን በሚያሳየዉ የአፍ መፍቻ ቋንቋችን እንድንናገርና ሁላችንንም በአንድነት ሊያዋሕደንና ሊያግባባን የነበረዉን የነፍጠኞችንና የትምክህተኞችን ቋንቋ የሆነዉን አማርኛ ቋንቋ ከመነጋገሪያነት ከመማሪያነት ከመስሪያነት ባጠቃላይ ከጫንቃችን ላይ አሽቀንጥራችሁ ስለጣላችሁልን በመጀመሪያ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ስም እናመሰግናችኋለን ነገር ግን በስራ ቦታ በትምህርት ቤት በተለያዩ የእምነት ተቋማት በገበያዉ በዕድሩ ሳይቀር በአኗኗራችን ተቸግረናል ይኸዉም የአንዱ ብሔር ቋንቋ በአንድ በኩል የአንዱ ብሔር ቋንቋ በሌላ በኩል ባጠቃላይ በአራቱም አቅጣጫ ተከፋፍሎ ልንደማመጥና ልንሰማማ ልንግባባ አልቻልንም ለሁላችንም አስተርጓሚ እያስፈለገን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ነዉ ስለዚህ ሁላችንም ልንደማመጥበትና ልንግባባበት የምንችልበትን ቋንቋ ከብሔር ብሔረሰቡ እንደ ሕዝቡ ብዛት ተዋጽኦ አየተወጣጣ ቃላት ተፈጥሮልን በአንድነት የምንናገረዉ የምንማርበት የምንሰራበት ባጠቃላይ በአራቱም ማዕዘን ልንግባባበትና ልንነጋገርበት ልንማርበትና ልንሰራበት የምንችለዉን ቋንቋ በአምስቱ ዓመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን እንድታዘጋጁልን አንጠይቃለን «የአፍ መፍቻ ቋንቋችሁ የማንነታችሁና የታላቅነታችሁ መለያ ነዉ ። » ብለዉ እአስከሚቸገሩ ድረስ ቤተክርስቲያናችንንና አምልኮታችንን በማመሳሰል ብዙ ነፍሳትን በቀላሉ መማረክ ችለናል ምእመኑንም ከኃለ ቀር አለባበስ ለይተነዉ በዘመናዊ ደስ ባለዉ አለባበስ እንዲመላለስና የጾምና የጸሎት ሸክም አቅለንለት እንደ ሥጋዊ ፍላጎቱና ምርጫዉ አምልኮቱን እንዲፈጽም አድርገናል መንግሥትም የኦርቶዶክስ አማኞችን በቀላሉ ወደ በረታችን ዉስጥ ለማስገባት እንድንችል መንገዱን በደንብ ስላመቻቸልን ዛሬም ዘወትርም እናመሰግነዋለን» በማለት ንግግራቸዉን እንዳቀረቡ የተለመደዉ ጭብጨባ ስለቀጠለ ለቀጣይ ተናጋሪዎች ማኅፀናቸዉ ከአምስት መቶ ዓመት በፊት ለፈለፈለቻቸዉ ለልጆቻቸዉ ለፕሮቴስታንት ክፍልፋይ ድርጅቶች ተወካይ ሰተዋል ተወካዩም እኛ የመንግሥታችንን ታላቅነት ለመናገር አንደበት ያጥረናል ብቻ ዝም ብለን «ዕፁብ ዕፁብ ፅፁብ ብንል የሚቀል ይመስለኛል ለእኛ ያወጣልንን ፀሐይ ለሌላ አልወጣም ብንል ማጋነን አይሆንብንም ዱሮ በቁጥር ይታወቁ የነበሩት የእምነት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ድርጅቶቻችን አሁን እንደ አሜሪካ አገር ለቁጥር የሚታክቱ ድርጅቶች ተፈጥረዋል ዱሮ ለመግባት እንቸገርባቸዉ የነበሩ ክልሎችና ብሔር ብሔረሰቦች ክፍት ሆነዉልን እንዲሁም ዋና መሪዎች ሆነዉልን በአራቱም ማዕዘን በተለያዩ ስያሜዎች ገብተን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዛይማኖትን እያዳከምንና ምእመኑንም ከእናታችን ከካቶሊክ በላይ ወደ እኛ እያስገባን እንገኛለን ምክያቱም እንኳን ምእመኑ አይደለም አገልጋዮቹ ሳይቀር በጾምና በጸሎት ስለተመረሩ እንቅልፋቸዉን አተዉ በማገልገላቸዉ ነፍሳቸዉ እረፍት በማጣቷ አረፍት ስለምትፈልግ ጥሩ መዝናኛ የሚፈልጉ ምአመናን ደግሞ በፈለጋቸዉ አለባበስ ከፈለጉ ደረትና ጡታቸዉን ገላልጠዉ ከፈለጉ በተወጣጠረ ሱሬ መላ አካላቸዉን አያሳዩ በመዝሙር የሚዘፍኑበትንና የሚጨፍሩበትን አዳራሽ ስለተዘጋጀላቸዉ አንዲሁም እኛ ጋር መተዉ የሱስን ከተቀበሉ ምግባር ኖራቸዉ አልኖራቸዉ ስለ መጽደቃቸዉ ዋስትና ስለምንሰጣቸዉ ባጠቃላይ ጠባቡን መንገድ አስወግደንና ንደን ሳይጨናነቁና ሳይጋፉ በሰፊዉ መንገድ ወደ መንግሥተ ሰማያት እንዲገቡ ስለምናደርግ ምርጫቸዉን አኛን ንጹዛንንና ቅዱሳንን ስለሚያደርጉ ነዉ አንዲሁም በቀንና በሌሊት መንፈሳችንን ስለምንልክላቸዉ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ሙሉ በሙሉ ወደ አኛ ይገባሉ ብለን እንገምታለን ለዚህ ነጻነትና አኩልነት ብቃት ላበቃን መንግሥታችን አሌ ሉዣ እንላለን በማለት ሲናገሩ የተለመደዉ ጭብጨባ ቀርቶ ሁሉም ሳያስቡት የተናጋሪዉ መንፈስ አሸንፏቸዉ «የሱስ ጌታ ነዉ አሜን ሀለ ሉዣ የሱስ ጌታ ነዉ አሜን ሀለ ሉዣ የሱስ ጌታ ነዉ አሜን ሀለ ሉዣ ኦ የሱስ ኦ የሱስ ኦ የሱስ አያሉ ለብዙ ደቂቃዎች እንደለፈለፉ የተወሰኑት መሬት ላይ ተንፈራግጠዉ «መንፈስ ተሞላን በማለት ምስክርነትን ሰተዋል በማስከተል የባህላዊ እምነት ተከታዮች ተወካይ መንግሥታችን የአማልክቶቻችን ጸጋና በረከት ይድረሰዉ» በማለት ከመረቁ በኋላ እኛ ለዘመናት አምልኮታችንን በስዉር በሽርኩቻዉ ተደብቀንተሸማቀን ነበር ስንፈጽም የነበረዉ አድሜ ለዴሞክራሳዊ መንግሠታችን ይኸዉ በየአደባባዩና በየወንዛወንዙ በግልጽ እዉቅና ተሰቶን አምልኮታችንን እንፈጽማለን «ባዕድ አምልኮ» እየተባልን ከሌሎች ፃይማኖቶችና አምላኮች ዝቅ ይሉ የነበረዉ አማልአክቶቻችን ይኸዉ አሁን በአገር አቀፍ ደረጃ እየተከበሩና እየተመሰገኑ ናቸዉ ይኸም ባለ ጊዜ የመሆን አድል እአንዳጋጠመንና የአኛ መንፈስ የበላይነትን የተጎናጸፈ መሆኑን ያሳያል ሕዝቡም ከፈለገ በቤቱ በጨሌዉ በቦረንትቻዉ በአርሲዋ አመቤት በወሎ መጀን በታዬ ከራማ በጠንቋዩ በአስማተኛዉ በመተተኛዉ መንፈስ አየተለማመነ አምልኮቱን በነጻነትና በእኩልነት በመፈጸም ላይ በመሆኑ ትልቋን ፀሐይ ለእኛ በተለየ ሁኔታ እንዳወጣችሁልን ነዉ የምናምነዉ ለዚህም እንደ አማልክቶቻችን አግራችሁ ስር ወድቀን ብናመሰግናችሁ ደስ ይለናል» በማለት በጠቅላይ ሚኒስትሩና በባለሥልጣናቱ እግር ስር ወደቁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ወዲያ በቅናት የተቃጠለዉ የቀጥተኛዉ አዉሬ መንፈስ ተወካይ « እናንተ ያለቦታዉ የወደቃችሁ ተነሱ» በማለት የባህላዊ እምነት ተወካዮችን እንዲነሱ ካዘዘ በኃላ በመጀመሪያ የጨለማዉ ገዥ ጌታችንን ዲያብሎስን እንድናመሰግን ሁላችሁም ተነሱ በማለት ሲናገር ተሰብሳቢዎቹ የዲያብሎስ ስም በመጠራቱ ተደናግጠዉ ባሉበት ፈዘዙ ወዲያዉ ተወካዩ በእርግጥ እስከአሁን ድረስ በሥጋ የተገለጡ ወኪሎቻችንን ሲሆኑ ያዳመጣችሁት ሁሉም የእኛን ፈቃድ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ምስክርነትን ስለሰጡና ለመንግሥታችንም ታላቅ ምስጋናንና አድናቆትን ስላቀረባችሁ በጊቢሁ አጋጣሚ በጨለማዉ ስማችን እናመሰግናችኃለን ለወደፊት ደግሞ ኅሊናችንን አንሸጥም ከነፈሰዉ ጋር አንነፍስም በማለት የእኛ ተቀዋሚ በሆነዉ መንፈስ የሚመሩና «የምናመልከዉ አምላክ አንድ አምላክ ነዉ እርሱም አልፋና ዖሜጋ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለዉ የፍጥረታት ጌታና ፈጣሪ የሆነ ሁሉ በእርሱ ለእርሱ የተፈጠረ በአንድነትና በሦስትነት የሚመለክ አንድነቱንና ሦስትነቱንም የገለጸዉ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ በመሆን በተዋሕዶ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰዉ በሆነዉ በመስቀል ላይ በተሰቀለዉ አምላክ በጌቶች ጌታ በነገሥታን ንጉሥ በሆነዉ በኢየሱስ ክርሰቶስ ብቻ ነዉበማለት የእኛን የተለያዩ አማልክቶችን የሚቃወሙና የሱስን የማይቀበሉትን ምእመናንና አገልጋዮችን በግድም ይሁን በዉድ እንደ አሁኑ ዓይነት የምስክርነት አደባባይ አዘጋጅታችሁ አሁን የተሰጠዉን ምስክርነት እነሱም እንዲሰጡ አድርጉ ይህ ካልሆነ ግን በአጭር ጊዜ ዉስጥ በሥጋዊዉም ሆነ በመንፈሳዊዉም ወንበር ላይ የተቀመጣችሁ ሥልጣናችሁ እንደሚሻርና ለሌላ ለተሻለ ብቃት ላላቸዉ ምርጥ ባለሟሉሎቼ ወንበሩን አሳልፌ እንደምሰጥ በታላቁ የግብር አባታችሁ ዲያብሎስ ስም አምላለሁ ብዬ እኔ የጨለማዉ ገዥ ተሰወርኩ በመቀጠል የአገሪቱ መሪ « በአርግጥ ይህች ቀን የተመረጠች ብዙ ድንቃድንቅ ያልተጠበቁ ንግግሮችና ተአምራቶች የታዩበት ነዉ ትንሽ የሚከብደዉ በመጨረሻ የታዘዝነዉን ተግባራዊ ማድረግ ላይ ቢሆንም በአምስቱ ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን የሽግግር ዓመት ዉስጥ ጎን ለጎን ተግባራዊ ለማድረግ እንድንችል እዚህ የተገኛችሁ ባለሥልጣናትና የኢህአዴግ አባላት እንዲሁም አጋር ድርጅቶች የተለያዩ የፃሃይማኖትና እምነት ተወካዮች በጋራ መሰለፍ ይጠበቅባችኋል ምክንያቱም ለህልዉናችን የመሪያችንን ፈቃድ ግድ መፈጸም አለብን ያለበለዚያ ከወንበራችን እንቆረጣለን እንደመሰሳለን መታሰቢያችንም ለዘለዓለም ይጠፋል በመሆኑም እንደ በፊቱ ንግግሬ «መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ» የምል አይደለም ተግባራዊ ለማድረግ የሞት ሽረት ልናደርግ እንደሚገባ ከልመና ጋር ነዉ የምማጸናችሁ በማለት የተለያዩ ዛይማኖቶች የተለያዩ ባህላዊ አምነት ተከታዮች ተወካይ ዉይይቱ በምርቃት እንዲዘጋ በማድረግ በቤት ስራ ተለያይተዋል እኔም የጨለማዉ ገዥ ትዕዛዜ ተግባራዊ እንደሚሆንና እንደማይሆን መጨረሻቸዉን እየተጠባበኩ ነዉ ይላል የጨለማዉ ገዥ አታላዩ በሰዉ ኅሊና በመንገሥ የዓመጻና የክህደት ስራ የሚያሰራዉ ሸዋጁ መንፈስ ዲያብሎስ ከጭፍሮቹ ጋር በመሆን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምዕራፍ « አንዳንድ ሌት ተቀን በመንፈሳዊ አገልግሎትና አምልኮ የሚመላለሱ አገልጋዮችና ምእመናን አኔን የጨለማዉ ገዥ በሚያስቆጣ ተግባርና ንግግር ዉስጥ በመግባት ጥያቄያቸዉን ለተለያዩ አካላት አቀረቡ ይኸዉም «እኛ አገልጋዮችና ምእመናን በሕገ መንግሥቱ ጣልቃ እንዳትገቡ ብላችሁ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ መስጠታችሁና እናንተም በመንፈሳዊ አገልግሎትና አምልኮ ዉስጥ ጣልቃ እንደማትገቡ ገልጻችሁ ነበር ምንም እንኳን በሕገ መንግሥቱ የሰፈረዉ ለደንቡና ለማስመሰ ንጂ ተግባራ እንደማይሆን ብናዉቅም አሁን የሕግ ጥሰቱ ከልክ በማለፉና ሊሆን የማይችለዉ ሲሆንና ሲደረግ በማየታችን ነዉ የፈቀደዉ ይምጣ ብለን ወደ እናንተ ቅሬታችንን ለማሰማት የመጣነዉ በዝርዝር ለማቅረብ እናንተ በግልጽና በተዝዋዋሪ መንገድ በሥጋዊ ወንበር ላይ የተቀመጣችሁት የሥጋ ፈቃዳችሁን ለመፈጸምና ለማስፈጸም ዝሙት ጣዖትና ባዕድ አምልኮ ዓመጻ ክህደት ርኩሰት ዘረኝነት ጎጠኝነት ዘፈን ዳንኪራ ለማስፋፋት የብሔር ብሔረሰቦች መብትና ነጻነት አስከመገንጠል ድረስ ለማስጠበቅ ስግብግብነትን ራስ ወዳድነትን አድሉሎን በደልን ጥላቻን በቀልን ጭከናን ግፍን የመሳሰሉትን በአንድም ይሁን በተለያየ መንገድ የዲያብሎስ ፍሬዎችን ለማፍራትና ተግባራዊነቱንም ለማፋጠንሙሉ ዴሞክራሲ ለመስጠት መሆት እየታወቀ እኛን የተወሰን አገልጋዮችንንና ምእመናንን የሚወክሉ ተጠሪዎቻችንንና አለቆቻችንን በራሳቸዉ አንደበት «አብዛኛዎቻችን ከላይ የተገለጹትን ተግባራት ለማስፈጸም የተሰለፍንና ቀሪዎቻችንም ደግሞ የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ፈጻሚዎችንና አስፈጸሚዎችን የምንደግፍ ነን በማለት መግለጫ አንዲሰጡ ማስደረጋችሁና ያለዉ እዉነታ ደግሞ ተቃራኒ መሆኑንን አያወቃችሁ ማስተባበያ መስጠት አለመቻላችሁ ቅር አስኝቶን ነዉ ወደ እናንተ ሥጋዊና መንፈሳዊ መሪዎች የመጣነዉ በማለት ቅሬታቸዉን አሰምተዋል በመጀመሪያ ምላሽ የሰጡት በሥጋዊ ወንበር ላይ ያሉት መሪዎችና ባለሥልጣናት ሲሆኑ ይኸዉም «በእርግጥ ሕገ መንግሥታችን የሕዝቦችን ነጻነት ያወጀ የብሔር ብሔረሰቦችን መብት የሚያስከብር ቋንቋቸዉን ባህላቸዉን አምልኮታቸዉን በፈለጉት መልኩ እንዲፈጽሙ ከፈለጉም ከፌደራል መንግሥቱ ራሳቸውን በመገንጠል ነጻ መንግሥትን መመስረት እንደሚችሉና ከፈለጉም በነጻ መንግሥታቸዉ ዉስጥ ብሔራዊ ፃይማኖት ሊመሰርቱ እንደሚችሉ የራሳቸው ሉዐላዊነት መንግሥት መገለጫ የሆነዉ ሰንደቅ ዓላማቸዉን በክልላዊ መንግሥታቸዉ ከፍ አድርገዉ እንዲያዉለበልቡ ባጠቃላይ የብሔር ብሔረሰቦች ለዘመናት በጭቆና የነበሩበትን ሥርዓት አስወግደን ስር ነቀል ለዉጥና ነጻነት ያጎናጸፍናቸዉ መሆኑ ይታወቃል «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አዚህ ላይ በደንብ መታወቅ ያለበት ሕገ መንግሥቱ ሙሉ ነጻነትን ይሰጣል አንጂ በግድ ዘሙቱ አመንዝሩ ጣዖትና ባዕድ አምልኮ ፈጽሙ ዝፈኑ ጨፍሩ ዘረኛ ጎጠኛ ሁኑ ዓመጻና ክህደት ፈጽሙ ወዘተ የማይልና እንደ ታላቁ መሪያችን የጨለማዉ ገዥ ማንንም አስገድደን አናስፈጽምም አንዳንዴ የበቀልና የግፍ አርምጃ የምንወስደዉም ያጎናጸፍናቸዉን ዴሞክራሲ መብት አንጠቀምም ኅሊናችንን አንሸጥም ለኅሊናችን ነዉ የምናድረዉ ወዘተ በማለታቸዉ ነዉ እንጂ አንደኛና መሰሎቻችን ፅያዖሄዉ ሰአቋማፖቻዉ ፈጎያጩውና «አድርጉ » የተባለዉን ቢያደርጉ «አታድርጉ» የተባለዉን ባያደርጉ ማንንም ቢሆን አናስርም አንገልም አናሳድድም አንወነጅልም ሀብትና ንብረቱን አናዘርፍም አንወስድም ታዲያ አሁንም እናንተን እንወክላለን ያሉ አለቆቻችሁ ነጻ ዴሞክራሲ መብታቸዉን ተጠቅመዉ ነዉ እንጂ ማንም በሉ» ብሎ ሳያስገድዳቸዉ ኅሊናቸዉን የማገለባበጥና የመሸጥ መብታቸዉንና ነጻነታቸዉን ተጠቅመዉ ነዉ «እኛ አብዛኛዎቻችን የኢሕአዴግ አባላትና ደጋፊ ነን ያሉት እንጂ አኛ አስገድደን ወይንም አዘናቸዉ አይደለም ለዚህም ከፈለጋችሁ የእናንተ አምላክ ወይንም የእኛ አምላክ የጨለማዉ ገዥ ሊመሰክር ይችላል ስለዚህ ዴሞክራሲ መብታቸዉንና ነጻነታቸዉን ተጠቅመዉ የፈጸሙትን የምትተቹና የምትቃወሙ ከሆነ ይልቁኑ እናንተ ናችሁ ሕገ መንግሥቱን የጣሳችሁት እንጂ እኛ አይደለንም እንደ እዉነቱ ከሆነ ደግሞ እኛ በጥርጣሬና በዓይነ ቁራኛ የምናያችሁ ስለነበረ ይህን መግለጫችሁን ስንሰማ በመጀመሪያ ደረጃ የገመገምነዉ የእኛን የጨለማዉ ጌታንና የእናንተንም ጌታ የሚያገለግሉ ዉዶቻችንን ሲሆን እነሱ ግን «ወደ ምትፈልጉት አቅጣጫ ለመምራትና ለእናንተም ጌታ አገልጋይ እንዲሆኑ የተደረገ ታላቅ መስዋዕትነት ስለሆነ ልንሸለምና ልንመሰገን ሲገባ መገምገማችን ተገቢ አይደለም በማለት ቅሬታ ያቀረቡብን ቢሆንም «እኛ የገመገምናችሁ በአንደበታችሁ ብቻ በመናገር በተግባር ባለመፈጸሙና የሽወዳና የሽንገላ ንግግር ስለመሰለን ነዉ እንጂ እኛም ያልጠበቅነዉ ሲሳይ ነዉ» ብለን አጽናንተናቸዋል አንዲሁም « ምንም እንኳ ለጊዜዉ ከእኛ ጋር ኅብረትና አንድነቱ የጠበቀ መሆኑን በመገለጹ ያስደሰተን ቢሆንም በአብዮታዊ ዲሞክራሲና በአምስቱ ዓመት እድገትና ትራንስፎርሜሽን ዉስጥ የበለጠ ተሳታፊ ሆነዉ እንዲያገለግሉና ብሔር ብሔረሰቦችን እንዲያነቁ አንድታደርጉ አንዳንድ ጥሩ ጅማሮች በማሳየታችሁ ተደስተናል ይኸዉም «ብሔር ብሔረሰቦች በራሳቸዉ አፍ መፍቻ ቋንቋ ባህል አምልኮና ፊደል ሊማሩ ሊገለገሉ ይገባል» ብላችሁ ይህን የነፍጠኞችንና የትምክህተኞችን ፊደል የሆነዉን የአማርኛ ፊደል አስወግዳችሁ በላቲን ፊደል መጻሓፍትንና ጽሑፎችን አዘጋጅታችሁ የላቲኑን ፊደል በደንብ ለሚያነበዉ በገጠር ላለዉ ገበሬና አርብቶ አደር ማቅረባችሁና «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የአማርኛ ፊደል ለማንበብ ለሚቸግረዉ ለተማረ ክፍል ማቅረባችሁ አርቆ አሳቢነታችሁንና አስተዋይ መሆናችሁን ያስመሰክራል ከተወሰነ ዓመት ወዲህ ተመሳስለህ ኑር ፖሊሲን ተግባራዊ ማድረግ የጀመራችሁና የብሔር ብሔረሰቦች መብትና ነጻነት እስከ መገንጠል ድረስ ያለዉን ሕገ መንግሥታችንን በደንብ መጠበቅና ማስጠበቅ ስለጀመራችሁ ያ የማይጠቅማችሁን ግትርነትና ቆራጥነት ከራሳችሁ ማስወገዳችሁ ጥሩ ጅማሮ መሆኑን እንገልጽላችኋለን በቀጣይ ደግሞ በየብሔራዊ ክልላቱ መንግሥታት በሰማኒያዉም ብሔር ብሔረሰቦች ቋንቋና በላቲንና በዓረብኛ ፊደላቸዉ ድጓዉን አቋቋሙን ሰዓታቱን ቅዳሴዉን ኪዳኑን ቅኔዉን እንደምታቀርቡና እንደምታጽፉ ተስፋ እናደርጋለን እንዲሁም የብሔር ብሔረሰቡን ባህልና አምልኮ በጠበቀ መልኩ በየወንዛወንዙ በየጥንቆላዉ በየዛሩ ቦታ ጎን ለጎን ማስፈጸም ይጠበቅባችኋል በእኛና በጨለማዉ ገዥ ዘንድ የተሸራረፈ ዴሞክራሲና ነጻነት ዋጋ የለዉም በዚሁ አጋጣሚ «እኛ ለእዉነተኛዉ መንግሥታችንና ለፀሐዩ ንጉሣችን ማንኛዉንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጆዎች ነን ለሕዳሴዉ ግድብ በመስሪያ ቤት ያዋጣነዉ ገንዘብ ስለማይበቃ በተጨማሪ በማኀበራችን ስም የአንደ ወር ደሞዛችንን ከአራት መቶ ሺህ ብር በላይና እንዲሁም ከአገልግሎታችን የተትረፈረፈዉን ገንዘብ ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ ቦንድ እንገዛበታለን በማለት በቴሌቨዥን በሬድዮን በኅትመት ዉጤቶች ላይ በግልጽ ስላስነገራችሁ አድናቆታችንን እንገልጽላችኋለን ለወደፊትም ለወንበራችን አደገኛ የሚሆኑ አካላት ቢነሱ ማንኛዉንም መሳሪያ በመጠቀም ደጀን እንደምትሆኑን እንተማመንባችኋለን በማለት ለሁለት ጌታዎች ለሚያገለገሉ ዉዶቻችን ከመናገር ዉጭ አሁን ላቀረባችሁት ቅሬታ ግን ማንንም አስገድደን ሆነ መሳሪያ ደግነንበት መግለጫ አላሰጠንም በማለት ምላሽ ሰተዋል በመቀጠል በመንፈሳዊ ወንበር ላይ የተተመጡት መሪዎችና ኃላፊዎች «ልጆቻችን። የአናንተ አካሄድ አሳፋሪ ቢሆንም አኛ የአዳምና ሔዋን ዘሮች የአንዱ አግዚአብሔር ፍጥረቶችና ልጆቹ ነን ወንድና ሴት የሚል ልዩነት ያለዉ በተገለጽንበት ሥጋችን እንጂ በነፍሳችን አንዳች የጾታ ልዩነት የሌለን ሕያዋን ፍጥረት ነን የአግዚአብሔር ልጆች ያስባለችን የነፍሳችን ባሕርይ ነዉ እንጂ ይህ የጾታ ልዩነት የፈጠረብን ሟች ፈራሽ በስባሽ ሥጋችን አይደለም በዚህች ምድር ቆይታችን ዉስጥ ወንድ የራሱ ድርሻ ብቻ የሆነ ስራ አለዉሱ ሴትም የራሷ ብቻ የሆነ የስራ ድርሻ አላት ከዚያ ዉጭ ግን በመማር በማስተማር በማሰብ በመናገር በመስራት በማሰራት በኃላፊነት በአስተዳዳሪነት በመሪነት ከወንዱ እኩል የሆን ነን አንዳች በሴትነት ጾታችን «ለዚህ ኃላፊነትና ስራ ብቁ ልትሆኑ አትችሉም» ያማንባል ተስፋችንም ሰማያዊ የሆነ የቅዱሳን መላእክት አኗኗር የምንናፍቅና «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የምንጠባበቅ ነን እንጂ እናንተ ኅሊናችሁን መርዛችሁና አጥባችሁ እንደምታስቡት አይደለንም እናንተ ግን ለፓለቲካችሁና ለሥልጣናችሁ ለጥቅማችሁ ስትሉ «ለፍልፉ» የምትባሉትን የምትለፈልፉ «ቀባጥሩ» የምትባሉትን የምትቀባጥሩ ለኅሊናችሁ ያልቆማችሁ ተስፋችሁን ምድራዊ አድርጋችሁ የምትመላለሱ ይህን ቅርፊት ሥጋችሁን የምታመልኩና የምታስመልኩ ናችሁ በማለት ሓሳባቸዉንና አቋማቸዉን አቅርበዋል የሴቶች ጉዳይ ኃላፊዎችም እኛ የምንሰማዉ በሕገ መንግሥታችን እኩልነታችንን ያረጋገጠልን መንግሥታችንን ነዉ እንጂ እናንተ ጤንነታችሁ በሚያጠራጥር መልክ የምታናገሩትን አይደለም ምናባዊ አስተሳሰባችሁ በእኛ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ በምናምን ሴቶች ዘንድ ተቀባይነትና ቦታ የለዉምፅ ንግግራችሁ ሁሉ እኩልነታችሁን ያረጋገጠላችሁንና ያጎናጸፋችሁን ዴሞክራት መንግሥታችንን ለመቃወም ለማጣጣል እንዲሁም ለማንቋሸሽ አስባችሁ መሆኑንና የአንዳንድ የፓለቲካ ድርጅቶች ቅጥረኞች መሆናችሁን ይገልጻል እኛ ግን ከአሕዛብ መንግሥታችን ጎን በመሰለፍ የሴቶች እኩልነትን አስከመጨረሻዉ አእናረጋግጣለን በማለት ምላሽ የሰጡ ስለሆነ እኔም የጨለማዉ ገዥ በምላሻቸዉ ስለተደሰትኩ ለበለጠ ለታላቅ ሹመት አብቅቻቸዋለሁ በማግስቱ ደግሞ አንዳንድ በዝሙት የሚተዳደሩ ሴተኛ አዳሪዎች በሴቶች ጉዳይ ዘርፈ የሴተኛ አዳሪዎች ችግር አስወጋጅ ዲያሬክተር ለሆኑት ጉዳያቸዉን አቅርበዋል ይኸዉም «እናንተ ለሴቶች ነዉ የቆምነዉ ለእኩልነታችሁና ለዴሞክራሲ መብታችሁ እንታገላለን» ፖፇቻፆሯ ነገር ግን አንድ ቀን የእኛ ሕይወት አሳስቧችሁ አያዉቅም እናንተ ለፖለቲካችሁ ብቻ ሌት ተቀን የምትሯሯጡ ናችሁ እንጂ ነዚህ እህቶቻችን በምድራዊ ኑሮዋቸዉም በሚያጎሳቁልና በሚያዋርድ ሕይወት ዉስጥ ይኖራሉ በእግዚአብሔር ዘንድም የኃጢአት ተግባር እየፈጸሙ ነዉ ስለዚህ ከዚህ ሕይወት ልናላቅቃቸዉና ራሳቸዉን የሚረዱበትን ስራ ልንፈጥርላቸዉ ይገባል ብላችሁ አንድ ቀን እንኳ ለሥጋችን ሆነ ለነፍሳችን አስባችሁልን አታዉቁም ይልቁኑ እግዚአብሔርን በሚያስቆጣ ተግባር የተሰለፈዉና ለእኛም ሕይወት አንዳች ስሜት የሌለዉ መንግሥታችሁ በዝሙት ሕይወታችን እንድንገፋበት የሚያበረታታ ማስታወቂያዎችን በቴሌቨዥንና በሬዲዮን አንዲሁም በኅትመት ዉጤቶች ላይ አያወጣ ሲያስፈልገዉ «ሕይወት የሆነዉን ኮንደም ተጠቀሙ ኤድስ የሚባል ነገር አይደርስባችሁም ይላል ሲያስፈልገዉ ደግሞ «የደስታና የእርካታ ምንጭ የሆነዉን ሰንሴሽን ተጠቀሙ አያለ በብሔር ብሔረሰቦች ዘፈንና ዳንኪራ እያጀበ ትዉልዱን ለዝሙት እያነሳሳና እያገፋፋ እንዲሁም እያደፋፈረ ነዉ ምንም የማያዉቁት ሴቶችና ወንዶች ቢያንስ የእግዚአብሔር ቁጣ የሆነዉን ኤድስ በሽታ እንኳ እንዳይፈሩ « ኮንደም ኤድስን የመከላከል ብቃት አለዉና ዝሙትን አትፍሩ ድፈሩ አያለ ሌት ተቀን የሚለፍፍ ነዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የሚገርመዉና የሚያሳዝነዉ ደግም የዛይማኖት አባቶችና የእምነት ተቋማት ይህ በግልጽ የዲያብሎስ ስራ የሆነዉን የርኩሰት ማስታወቂያ ሊያስቆሙና ሊያወግዙ ሲገባ የርኩሰት ስራ አስፈጻሚ ከሆነዉ መንግሥት ጋር እጅና ጓንት በመሆን በዓመጻዉ ስራ ተሰልፈዋልር እርዳታንና ገንዘብን ለማግኘት ሲሉ በአጭሩ «አታመንዝር አትዘሙት» በሚለዉ የእግዚአብሔር ሕግ መፍትሔ ሊያገኝ የሚችለዉን ችግርና በሽተኞቹንም «ንስሐ ግቡ ቅዱስ ቁርባንን ተቀበሉ ጠበሉንና እምነቱን ተጠቀሙ ራሳችሁን ጠብቁ» በማለት መምከርና ማጽናናት ሲገባቸዉ አንዲሁም ሕዝቡንም «በኤድስ የተያዘዉን ሆነ በሌላ በሽታ የተያዘዉን ሰዉ አድሎና መገለል አታድርጉ ወገኖቻችሁ ናቸዉና እርዷቸዉ ተንከባከቧቸዉ አፍቅሯቸዉ በማለት ሊያስተምሩ ሲገባ በጨለማዉ ገዥ በሚመራዉ ሥርዓት ዉስጥ በመመላለስ አብረዉ ከመንግሥት ጋር በመሰለፍ እንድ ትልቅ ስራ «ኤድስን እንከላከል የአባላዘር በሽታ እንከላከል» እያሉ ወሬ በማራገብ በእግዚአብሔር ቁጣ ላይ ከንቱ ሥጋዊ መጠበብ የሚያደርጉና በተዝዋዋሪ ዝሙት የሚስፋፋበትን መንገድ የሚደግፉና የሚያበረታቱ እንዲሁም ግብረ ሰዶምነትን ጭምር በይሉኝታና በጥቅም ኅሊናቸዉን አሳዉረዉ ማዉገዝ ያልቻሉ ለሥልጣናቸዉና ለሥጋዊ ክብራቸዉ የቆሙ ናቸዉ እኛ ግን ከምድሩም ሳይደላን ከሰማዩም ሳንሆን ለሥጋችንና ለነፍሳችን የሚያስብልን ግለሰብና አካል አተን በአየር ላይ ተንሳፈን የቀረን ምስኪኖች ነን አናንተ በእዉነት ለሴቶች የምታስቡ ቢሆን ኖሮ የፖለቲካ ወሬያችሁን ትታችሁ ከዚህ ሰቆቃ ሕይወት የምንገላገልበትን ኑሮ ታመቻቹልን ነበርፈ መንግሥታችሁ ደግሞ «የዴሞክራሲ መብታችሁን ስላጎናጸፍናችሁ ማንኛዉንም መብታችሁን በመጠቀም ማመንዘርና መዘሞት ቀርቶ በግልጽ የሥራ መተዳደሪያና የገቢ ማግኛ ልታደርጉት ትችላላችሁ ብሎ የሕግ ሽፋን ስለሰጠን ሳንፈራና ሳንሸማቀቅ በግልጽ እንደ ስራ መስክ ቆጥረነዉ ገላችንን እንሸጣለን በሕግ እንኳ ብንገደብ ሌሎች አማራጭ ስራዎችን እንፈልግና ሕይወታችንን አንለዉጥ ነበር እናንተም ሆናችሁ መንግሥታችሁ ሌት ተቀን የምትሯሯጡት የሰዎችን ኅሊና አደንዝዛችሁ የራሳችሁን መሰሪ ዓለማ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ነዉ እንጂ የሰዉ ሕይወት አንዳች የሚያሳስባችሁ አይደለም ከዚያም አልፎ አንዳንዶች ባለሥልጣናትና ካድሬዎች ዉሏቸዉንና አዳራቸዉን ከእኛጋ እያደረጉ ዝሙት ስራችንን ያበረታታሉ ይደግፋሉ» በማለት በምሬት ብሶታቸዉን አቅርበዋል ዲያሬክተሯም ፃፍረትና ኀዘን ተሰምቷቸዉ ወደ ልባቸዉ በመመለስ ለካስ መንግሥታችን ሕዝቡን ብቻ ሳይሆን እኛን ካድሬዎቹን ጭምር አደንዝዞናል ከዚህ በኃላ እነዚህን እህቶቻችንን ከዚህ ጎስቋላና መከራ ሕይወት ልናወጣቸዉና የስሜት ጉዳታቸዉንም ልንክሳቸዉ ይገባል በየቦታዉ የወደቁ ወገኖቻችን የሆኑትን አባቶቻችንን እናቶቻችንን ወንድምና እህቶቻችንን ልናስባቸዉ ይገባል እንጂ ነጋ ጠባ የፖለቲካ ስራ መስራት የለብንም በማለት ለኅሊናቸዉ በመናገር አህቶቼ ንግግራችሁ ዐይኔን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ከፍቶልኛል ለወደፊት ምን ማድረግ እንዳለብኝ አስተምራችሁኛል እስከአሁን ድረስ ሴቶች እያልን በስማችሁ በመነገዳችን ይቅርታ አድርጉልኝ ከዚህ ሕይወት የምትለዩበትን መንገድ እናመቻቻለን በማለት የሚያጽናና መልስ የሰጡ ሲሆን እኔ የጨለማዉ ገዥ ለኅሊናቸዉ የነገሩትንም አዛዉ ኅሊናቸዉ ጋር ሆፔጄ በደንብ አዳምጫለሁና ከዚያ በተጨማሪ መልካም ምላሽ በመስጠታቸዉና ለእንደራሴዎቼ ዘብ ሆነዉ የሚያሳፍርና የሚያዋርድ መልስ ባለመስጠታቸዉ ተናድጄ ስለነበር በታማኝ ካድሬዎቼ አማካይነት ከበላይ ላሉት ባለሥልጣናት ሪፓርት አስደርጌ ከወንበራቸዉ እንዲሻሩና ታማኝ ዉዶቼ እንዲመደቡ አስደርጌያለሁ አንዳንድ አገርና ወገን ወዳድ እንዲሁም የዓለም ምሁራን አንድ ላይ ሆነዉ ለሚመለከተዉ የተባበሩት መንግሥታት ተወካይ ቅሬታቸዉን አቀረቡ ይኸዉም የእኛ ፍላጎትና ምኞት ቴክኖሎጂዉ እዉቀቱ ጥበቡ ፍልስፍናዉ ሁሉ የአዳምና የሔዋን ዘሮችን የሚጠቅም ከጉስቁልና ኑሮና ሕይወት የሚለይ ረዛብ ችግር ስቃይ ሕመም ድንቁርና እርዛት ባጠቃላይ ሰዎች ሁሉ እደሰዉነታቸዉ ብቻ ተከብረዉ ተፈቅረዉ በልተዉ ጠጥተዉ ተምረዉ መጠለያና መጠጊያ አግኝተዉ አንዲኖሩ ነዉ እንጂ ለብዙ ሰዎች ለችግር ማቃለያና ለመርጃ የሚጠቅመዉ በቢሊዮንና በትሪሊዮን የሚቆጠር ብር ፈሰስ እየተደረገ ለተለያዩ ጦር መሳሪያና ለሕዋ ምርምር መደረጉ አግባብነት የሌለዉና ለእነዚህ የሚወጣዉ ገንዘብ ለልማት ስራ ቢዉል ኖሮ በምድራችን ረፃብ ችግር ሰቆቃ የሚባለዉ ቀርቶ ስማቸዉ እንኳ አይታወቅም ነበር የየአገራቱ መሪዎች ሆኑ ባለሥልጣናት ለክብራቸዉ ለጥቅማቸዉ ለዝናቸዉ ለታላቅነታቸዉ ለሥልጣናቸዉ የቆሙ አምባገነን ናቸዉ የወገናቸዉ የአዳም ዘር ሰቆቃና ችግር አንዳች አይሰማቸዉም እነሱ ከገነኑ ከተመሰገኑ ከበሉ ከጠጡ ከተዝናኑ ከጨፈሩ ከዘፈኑ ከተመለኩ ሁሉ በእነሱ ቁጥጥር ዉስጥ ከሆነላቸዉ ለሌላዉ ወገናቸዉ አንዳች ስሜት የሌላቸዉ ናቸዉ ከዚያም አልፈዉ በዕብሪትና በትዕቢት ከእኛ በላይ ማንም የለም ቀና ብትሉ ጣርና ጣሪያ ነዉ» አያሉ የሚደነፉ ሕዝብን የሚያስጨንቁና ግፍ የሚፈጽሙ ናቸዉ የሚገርመዉና የሚያሳዝነዉ ደግሞ ወደ ተግባር የማይለዉጡትን ለመሸንገያና ኅሊናን ለማሸጫ ለመጠቀም «አኛ ለሰላም ለፍትህ ለዴሞክራሲ ለእኩልነት ለነጻነት ለብልጽግና የቆምን ነን» ይላሉ ተግባራቸዉ ግን ጦረኝነትና ግፈኝነት አድሎና በደል ነዉ ስለዚህ አላስፈላጊ ለሆነዉ የተለያዩ ጦር መሳሪያና ለተለያዩ ፕላኔቶች ግኝት የሚወጣዉ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ለሕዝብ አገልግሎት ለትምህርት ለጤና ለመኖሪያ ቤት ለመስኖ ለትራንስፖርት ለመብራት ለስልክ ወዘተ ለመሳሰሉት አገልግሎት ላይ እንዲዉል አንጠይቃለን በማለት አስተያየታቸዉንና ጥያቄያቸዉን አቅርበዋል ኢትዮጵያዊዉ ምሁር ተጨማሪ አስተያየት አለኝ ብለዉ« እኛ የሰዉ ዘሮች የፈጠረን አምላክ ረስተን እኛ ሳናስተዉለዉ ለጨለማዉ ገዥ ለዲያብሎስ ባሪያዎች ሆነን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሌት ተቀን ፈቃዱ በሚፈጸምበት የጨለማ ሥርዓት ዉስጥ በመመላለሳችን ነዉ መንግሥታት ሆኑ ባለሥልጣናት እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን መልካም ተግባር መፈጸምና ማስፈጸም ተስኗቸዉ ሕዝቡን ለጦርነት የሚያነሳሱትና ሀብትና ንብረት በጥቂት ሰዎች ቁጥጥር ዉስጥ እንዲሆን አድርገዉ በረፃብና በችግር እየቀጡት ያለዉ ታዲያ የሕዝብ እንባ አንድ ቀን እንደ ጎርፍ ሆና እንዳይጠራርጋቸዉ እሰጋለሁሆ እንደ እኔ አስተያየት ለሁሉም መፍትሔ የሚሆነዉ በዲያብሎስ መንፈስ የሚመሩ መንግሥታት ሆኑ ባለሥልጣናት በምንም መልኩ ኅሊናቸዉን የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ሊያደርጉትና የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሊፈጽሙና ሊያስፈጽሙ ስለማይችሉ ይህ አሁን በዓለም ላይ የሚታየዉ የዲያብሎስ ሥርዓት ሊወገድና በምድራዊ ሕይታችንም የምንጠቀምበት ለሰማያዊ ሕይወታችንም በአግዚአብሔር መንግሥት ሕያዉ ሆነን የምንኖርበት ሰማያዊ ሥርዓት ልንዘረጋና ከላይ የተገለጹትና መልካም ተግባራትን ልንፈጽም ይገባል ነገር ግን አሁንም «በዲያብሎስ ሥርዓት እንመራኔ ከተባለ ይህ ቅርፊት ሥጋዉን የሚያመልክና የሚያስመልክ አንዲሁም ተስፋዉን ምድራዊ ያደረገ ትዉልድ ከላይ የተገለጹትን መልካም ተግባሮች ለመተግበር እንደሚቸገር ለመግለጽ እወዳለሁ» በማለት አስተያየታቸዉንና ስጋታቸዉን ገልጸዋል የመንግሥታቱም ተወካይ « በአርግጥ አስተሳሰባችሁና አስተያየታችሁ ጥሩ ቢሆንም ለዚህ ምላሽ መስጠት የሚችሉት አምስቱ ኃያላን አገራት የተባሉት አሜሪካ እንግሊዝ ፈረንሳይ ሩሲያና ቻይና ናቸዉ ዓለምን እንደፈለጉ አያሽከረከሩት ያሉት እነሱ ስለሆኑ አሁን ባለሁ ሁኔታ የሚሰማችሁና የሚቀበላችሁ ግለሰብ ሆነ አካል ያለ አይመስለኝም ምናልባት ለወደፊት የአዳም ዘር ሁሉ የዓለም ሕዝብ ሁሉ ወገኔ አባቴ እናቴ ወንድሜ እህቴ ልጆቼ ናቸዉ የሚል ትዉልድ የሚፈጠርበት አገር ካለ ያኔ ሓሳባችሁና ጥያቄያችሁ ተቀባይነት ሊያገኝ ይችላል እንጂ አሁን ይህን ሓሳብ ብታቀርቡ የእብድ አስተሳሰብ አድርገዉ ነዉ የሚቆጥሩት በማለት ስለመለሱላቸዉ ጥያቄያቸዉ ዋጋ ቢስ ሆኖ ቀርቷል እኔም የጨለማዉ ገዥ ማን ጀግና ደፋር ነዉ ይህን መልካም ተግባር ሊፈጽምና ሰማያዊ ሥርዓት ሊዘረጋ የሚችል። » በማለት ለዉይይት አቅርበዉታል ከተሰብሳቢዎቹ መካከል የግንባታ ግብአቶችን የሚያቀርቡና የሚያመርቱ አካላት «እንግዲህ ሁላችንም የአገረና የወገን ፍቅር አስገድዶን ነዉ በራሳችን ፈቃድ የተሰባሰብነዉ ስለዚህ ስለማንም ሳይሆን ለኅሊናችንና ስለ አገራችን ስንል ያለዉን ችግር በግልጽ ልንወያይና የራሳችን ችግር ካለም በግልጽ ማስቀመጥ ይኖርብናል ለምሳሌ በእኛ በኩል በአጭር ጊዜ ዉስጥ ከእኛ በላይ እንደሆኑት ሀብታሞች ለመሆንና ለመክበር ስለምንፈልግ ጥራት የጎደለዉና ደረጃዉን ያልጠበቀ ግብአት እናመርታለን እናቀርባለን በዚህም ምክንያት ወደ ግንባታ ሲለወጡ በሂደት በግንባታዉ ላይ የጥራት መጓደልና መበላሸት ይታያል» በማለት አስተያየት ሰተዋል በማስከተል ከስራ ተቋራጮች« በአርግጥ በግልጽ እንነጋገር ተብሏልና እኛም ስራ ተቋራጮች በአጭር ጊዜ ዉስጥ ለመክበርና ለመበልጸግ ካለን ፍላጎትና ከእኛ በላይ የሆኑት ባለጸጋዎች ላይ ለመድረስ ከዚያም ለመብለጥ ካለን ምኞት የተነሳ ከፍ ያለ ትርፍ ማግኘታችንን እንጂ ግንባታዉ በጥራት ደረጃዉን በጠበቀ መልኩ እንደራሳችን ሕንጻ በመመልከት አይደለም የምንሰራዉ የዱሮዎቹ ተቋራጮች ሆኑ ባለሙያተኞች ከገንዘብ ፍቅር ይልቅ ለስማቸዉ ቅድሚያ ስለሚሰጡ ከራሳቸዉ ጥቅም ይልቅ የአገራቸዉንና የሕዝባቸዉን ጥቅም ነዉ የሚያስቀድሙት የነበረዉ ለዚያም ይመስለናል በድሮ ስራዎች ላይ ብዙ ብልሽትና ጉድለት የማይታየዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር አሁን ያለነዉ ነጋዴዎች እንደአጠቃላይ ሲታይ ራስ ወዳዶች ስግብግቦች ስለሆን በሀብት ላይ ሀብት በሕንጻ ላይ ሕንጻ በንብረት ላይ ንብረት እንዲኖረን ነዉ የምንፈልገዉ እንጂ አገራዊና ሕዝባዊ አስተሳሰብ የለንም ማለት ይቻላል ስለዚህ ይህ አስተሳሰባችን በመጀመሪያ ደረጃ ሊታደስ ይገባል ያኔ ለአገርና ለወገን ማሰብ አንጀምራለን መስገብገብና ራስ ወዳድነት አይደለም ከገንዘባችን በተጨማሪ ለአገራችንና ለሕዝባችን አንደ ቀደሙት አባቶቻችንና እናቶቻችን ደማችንን ጭምር መስዋዕት ከማድረግ አንመለስም አሁን ባለን አስተሳሰብ ግን የዓለም ሕዝብ ሀብቱና ንብረቱ የእኛ ብቻ ቢሆንና እኛን ሌት ተቀን ደጅ ቢጠናን ምርጫችን ነዉ በማለት አስተያየታቸዉን ሰተዋል አርክቴክቶች መሐንዲሶችና የተለያዩ ባለሙያተኞች «ጥንት ኢትዮጵያዉያን በራሳቸዉ ልጆች ለዓለም የሚያስደንቅ የጥበብ ስራና ግንባታ አሳይተዋል ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ደግሞ እነዚያ ጥበበኛ ኢትዮጵያዉያን ጠፍተዉ ኢትዮጵያዉያን ባልሆኑ ባለሙያተኛ ነበር የዲዛይኑና የቁጥጥሩ ስራ ይከናወን የነበረዉ አሁን ደግሞ ብዙ ባለሙያተኞችን አገሪቷ አፍርታ ሳለ ከዱር በበለጠ የተሻለና ጥራቱን የጠበቀ ሕንጻ መንገድ የመሳሰሉት ሊኖረን ሲገባ ከዱሮ ያነሰና የሚያስተቸን ሆኗል ይህም የሙያ ስነምግባር ጠብቀን ስለማንሰራና ከሥራ ተቋራጩ ጋር ተሻርከን እኛም ገቢያችንን ከና ለማድረግና በኋላም ሥራ ተቋራጭና አማካሪ ለመሆን ነዉ የምንሰራዉ እንጂ ለስራዉ ጥራት ትኩረት ስለማንሰጥና በአቋራጭ ለመክበር ስለምንፈልግ ግንባታዉን በጥራት መቆጣጠር አልቻልንም» በማለት አስታያየታቸዉን ሰተዋል በመቀጠል የኮንስትራክሽን ግንባታና ቁጥጥር አማካሪ ድርጅቶችም « በሥራ ተቋራጭ ሆነ በዕቃ አቅራቢዎችና አምራቾች ዘንድ ችግር ቢኖር እንኳ በእኛ በኩል በአግባቡ በመቆጣጠር የግንባታ ጥራቱንና ደረጃዉን ጠብቆ እንዲሰራ ማድረግ ሲጠበቅብን በአግባቡ የስራ ድርሻችንን ስላለተወጣን አኛም ለስራዉ ጥራት መዓደልና መበላሸት አስተዋጽኦ አድርገናል ይህም የሆነበት ዋንኛ ምክንያት እያንዳንዳችን ባለሙያተኞች ከጥናት ከዲዛይን ከግንባታ ክትትልና ቁጥጥር ጀምሮ ስራችንን እንደ ትርፍ ስራ ሁለተኛ ስራ አድርገን እየተመለከትን ስለምንሰራና በጋራ ተቀናጅተን ጥራቱንና ደረጃዉን በጠበቀ መልኩ እንዲሰራ ለአንድ ዓላማ መቆም ስላልቻልን ነዉ ይባስ ብሎ በሙያችን እየተከፋፈልንና እየተቧደን እርስ በእርስ የምንተቻች የምንጠላለፍ አገራዊና ሕዝባዊ አስተሳሰብ የሌለን የራሳችንን ሙያ ብቻ ከፍ እያደረግን የሌላዉን የምናጥላላና የምናኳስስ የአንድ አካል የተለያዩ ብልቶች መሆናችንን የዘነጋን ጆሮ በዐይን ላይ አጅ በአግር ላይ ጥሩ አመለካከት የሌለዉ የአንዱ ዉድቀትና መበላሻት ለሌላዉም እንደሚተርፍ ያላስተዋልን ነን ባጠቃላይ ለአንድ ዓላማ መቆም ያልቻልን ለጥራት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ስራ አንዳች የማንቆረቆር ደሞዛችንን በየወሩ ከመዉስድ ዉጭ አንዳች አገራዊና ወገናዊ ፍቅር ተሰምቶን ለግንባታ ጥራትና ዕድገት ስሜት አልባ በመሆናችን ምክንያት ነዉ ጥራቱ ሆነ ደረጃዉን ያልጠበቀ ስራ ሊሰራ ያቻለዉ በማለት አስተያየታቸዉን ሰተዋል በመጨረሻም ሁሉም የራሳቸዉ ጉድለት አምነዉ በቀጣይ ለአንድ ዓላማ በተቀናጀ መልኩ ጥራት ላለዉ ግንባታ በመሰለፍ የበደሉትና አገርና ሕዝብ ለመካስ ቆርጠዉ የተነሱ መሆናቸዉን በመግለጽ ለሚመለከተዉ አካል አቋማቸዉን ለማሳወቅ እየተዘጋጁ ሳላ እኔ የጨለማዉ ገዥ የመልካም ነገር ተቃራኒ ነኝና አንድ ልብ እንዳይሆኑ በቨዘር በጎጥ በቋንቋ በሃይማኖት ከፋፍዬ ዉይይቱንም በካድሬዎቼ አማካይነት ከፖለቲካ ጋር እንዲያያዝ አድርጌ መልካም ሓሳባቸዉንና ዕቅዳቸዉን አኮላሽቻለሁሆ አንዳንድ የጤና ባለሙያተኞች በአገር ዉስጥ ስለሚሰጠዉ የጤና አሰጣጥ ድክመትና ሥነ ምግባራዊ ባልሆነ መንገድ የሚሰሩ ስራዎችን በተመለከት ዉይይትና አቋም መዉሰዳቸዉ ታዉቃል ይኸዉም በዉይይታቸዉ አኛ ሐኪሞች ጤና መኮንኖች ነርሶች ጤና ረዳቶች የላብራቶሪ ቴክኒሺያኖች እንዲሁም ተዛማችነት ባለዉ ስራ በጋራ የምንሰራ ሰራተኞች ሕዝቡን ቃል በገባነዉ መሰረት በትህትናና በቅንነት ማገልገል ሲገባን በአግባቡ ማስተናገድና አገልግሎት መስጠት አልቻልንም ምክንያቱም አኛ አገልጋይ መሆናችንን በመዘንጋት ገና በሽተኛዉ ሲመጣ የምናመናጭቅና ሌላ ያላሰበዉን በሽታ የምንጨምርበት ሆነን ተገኝተናልፈ ከዚህ በተጨማሪ ቀልጠፍ ያለ አገልግሎት መስጠትና ጥንቃቄ የመላበት ሕክምና መስጠት ሲገባን የምናጉላላና ጥንቃቄ የጎደለዉ የቸልተኛነት ስራ በመስራታችን አንዳንዶቹ ለሞትና ለከፋ ጉዳት ዳርገናቸዋል ስለዚህ በተለያየ መልክ ሕዝቡ ስለተማረረብን በመልካም ሥነምግባር እንደ ወላጆቻችንና ቤተሰቦቻችን በመመልከት ልናስተናግዳቸዉና ልናገለግላቻዉ ይገባል በማለት በጋራ ተወያይተዋል በማስከተል በግል ሕክምና የሚሰሩት ደግሞ አኛ በግል ሕክምና የምንሰራ ባለሙያተኞች ከፍ ያለ ገቢ ለማስገኘትና በአጭር ጊዜ ዉስጥ ለመክበር እንዲሁም በአጭር ጊዜ ዉስጥ የራሳችን የንግድ ሆስፒታል ለመክፈት ስንል ሥነ ምግባር በጎደለዉ መልኩ ምርመራ ሊደረግበት የማይገባዉን የተለያየ ምርመራ ዉጤት እንዲቀርብ በማዘዝ የማያስፈልግ ወጭ በሕዝቡ ላይ ጭነናል ሙያችንን ልክ እንደ ንግድ ስራ በመመልከት በአንዴ የምነበለጽግበትን መንገድ ነዉ የምንፈልገዉ እንጂ ወገናችንንና ቤተሰባችንን የምናክም መሆኑን ዘንግተነዋል በመሆኑም ከእንግዲህ ታካሚዎችን እንደ አባቶቻችን እናቶቻችን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በመቁጠር በቅንነትና በእዉነት ለማገልገል ቃል እንገባለን በማለት በመንግሥትና በግል የሕክምና ተቋም የሚሰሩ የተለያዩ የጤና ባለሙያተኞች ስምምነት ያደረጉ ቢሆንም እፄ የጨለማዉ ገዥ የቅንና የእዉነት ተግባር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ተቃዋሚ ነኝና የአፍ ዉይይት ብቻ እንዲሆን አድርጌ አስከአሁን ድረስ ተግባራዊ እንዳይሆንና ሕመምተኛዉም እንዲማረር አድርጌያለሁ በሌላ ጊዜ ደግሞ በየትምህርት ተቋሙ ያሉ መምህራን በትምህርት አሰጣጥና በተማሪዎች ጉዳይ በጋራ ተሰብስበዉ ዉይይት ያደረጉ ሲሆን በዉይይታቸዉም «እኛ መምህራን ከማንኛዉም ሙያ በላይ ትዉልዱን በእዉነተኛ አስተሳሰብና ሕይወት ልንቀርጸዉ የሚገባና አገራዊና ዓለማቀፋዊ አስተሳሰብ እንዲኖረዉ እንዲሁም አግዚአብሔር መፍራት ባለበት ሕይወት እንዲመላለስ ማድረግ ሲገባን የመንግሥትን ፖሊሲና ፖለቲካ ተግባር ለማስፈጸም ስንል ኅሊናችን ሳይፈቅድ በዉስጣችን በተሰገሰጉ ካድሬዎች አማካይነት በተቃራኒዉ ተግባር ተሰልፈናል ይኸዉም ገና ከሕጻንነት እድሜ ጀምሮ ትዉልዱ በዘረኝነትና በጎጠኝነት አስተሳሰብ እንዲያድግ አለቆቻችን ባመጡልን በዓለም ላይ ተሰምቶም ታይቶም የማይታወቀዉን «ብሔር ብሔረሰቦች» የሚለዉን ኅሊና ማሸጫ ቋንቋና የአባልነት ማጥመቂያ መንፈስ ኅሊናቸዉ ዉስጥ እየዘከራን በዘፈንና በዳንኪራ እያሳበድን ይኸዉ በአገሩ ላይ በሰንደቅ ዓላማ ላይ በአምላኩ ላይ ዓመጻና ክህደት የሚፈጥር ርኩሰትን የሚያነግሥ ትዉልድ አፍርተናል አሳዛኙና አስገራሚዉ ደግሞ ተማርን ተመራመርን የተባልን ሰዎች ነን ከታች ከመዋዕለ ሕጻናት ጀምር እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ያለን መምህራን የመንግሥት እንደራሴ ሆነን የመሪያችንን አንደበት አንደበት መንፈሱን መንፈስ አድርገን ለዓመጻ ለክህደት ለርኩሰት እንዲመች አድርገን ትዉልዱን እየቀረጽን ያለነዉ ወላጆቻችን አንዳች ሳይማሩ እናት አገራቸዉን ኢትዮጵያን የተቀደሰዉን ሰንደቅ ዓላማቸዉን ፈጣሪቸዉን አላስካዱም አላጥላሉም ዓመጻም አላስፈጸሙም እኛ ግን የዓመጸኛዉና የከሄሃዲዉ መንግሥት አገልጋይ ሆነን በየትምህርት ተቋሙ ትዉልዱን ከእዉነት አርቀነዋል የፈጠረዉን አምላክ አስክደነዉ የዘር ሐረጎችህ አዳምና ሔዋን አይደሉም ፈጣሪህም አንዱ እግዚአብሔር አይደለም ከጦጣ መሰል እንስሳ በቀስ በቀስ እድገትና ለዉጥ በኢሾልሽን አማካይነት ነዉ አሁን ላለህበት ደረጃ የበቃኸዉ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣችህ ተፈጥሮ ነች እንደፈለክ በዚህ ምድር ላይ ተመላለስ እንጂ «መንግሥተ ሰማያት ገነት ሲኦል ገፃነመ እሳት» የሚባሉት የገዥ መደቦች ለመጨቆኛ ያመጡት ነዉ» በማለት ከሰዉነት ባሕርይ አስወጥተነዋል በዚህም ምክንያት ክብሩ ታላቅ የነበረዉ የመምህርነት ሙያችን ሞገሱ ተገፎ እኛም በተማሪዎቻችን እየተናቅን እንገኛለን ስለዚህ ከእንግዲህ መንግሥት ከፈለገ ለአሱ ጨለማ አገዛዝ የሚመች ትዉልድ ካገኘ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቷቸዉ የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ትምህርት ያስተምራቸዉ እንጂ የቅዱስ ኪዳኗን ኢትዮጵያ ሕዝቦችን ከእንግዲህ አናሳምፅም እግዚአብሔር መፍራት ያለበትን ትምህርት እንዲሁም በሥጋቸዉም በነፍሳቸዉም የሚጠቀሙበትን እዉቀትና ጥበብ ብቻ ነዉ የምናስተምረዉ እንጂ ዳግም የካድሬነት ተግባር አንፈጽም በማለት በአንድ አቋም የተስማሙ ቢሆንም እኔ የጨለማዉ ገዥ ስለ ድፍረት ዉይይታቸዉና እንደራሴዎቹ የሆኑትን መሪዎች ባለሟሌ የሆኑትን ባለሥልጣናት አንዲሁም ዉዶቼ የሆኑትን ካድሬዎች ስላጣጣሉብኝና ስለናቁብኝ እንዲሁም የጨለማዉ ተግባሬን አናስፈጽምም በማለታቸዉ ዋንኛ አስተባባሪዎችን ለአለቆቻቸዉ በዉዶቼ አሳሳቢነት ወደ እስርና ስደት ዳርጌያቸዋለሁ ይላል ዓለምን እንደፈለገዉ እያሸረከረ ያለዉ የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ ከነሠራዊቱ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምዕራፍ « ስለ እዉነት እንኳን እኔን ዲያብሎስን ቀርቶ እዉነተኛ አምላካችሁን የማትሰሙና የማትፈሩ ደንዳኖችና ቆራጥ ጀግኖች በመሆናችሁ የሮድደ ዘመን የጥናቴን ግኝት በምሥጢር ለአናንተ ለምርጦቼ መሪዎችና ለባለሟሎቼ ባለሥልጣናት እንዲሁም ለዉዶቼ ካድሬዎች ብቻ አቀርባለሆ አደራ የምላችሁ ይህን ምሥጢሬን ብዙ የደከምኩበት ስለሆነ ከቢጤዎቻችሁ በስተቀር በአኔ ላይ አድማና ዓመጻ ለፈጸሙብኝና ለሚፈጽመብኝ በአገር ዉስጥ ሆነ በዉጭ አገር ላሉ ጠላቶቼ እንዳትገልጹ አናንተ ብቻ በጸጋዬ ተጠቀሙ ለረጅም ዘመን ባጠናሁት ጥናቴ እያንዳንዱ መንግሥት ቡድን ግለሰብ የዘራዉን የዓመጻ የክህደት የርኩሰት የክፋት የተንኮል ፍሬዉን አጭዶና መራራ ቢሆንም ጭልት አድርጎ በመጠጣት ያልፋል እንጂ ማንም ይሁን ማን ከተፈቀደለትና ከተቆረጠበት ቀን አንድ ቀን እንኳ በራሱ ሥልጣንና ኃይል የሥልጣን እድሜዉን አያስረዝምም ታዲያ እንዲህ ስላችሁ «በተፈቀደልን አድሜ ቀና እናስብ መልካም እአእንስራ እዉነተኞች እንሁን አግዚአብሔርንም በእዉነትና በመንፈስ አምልከን ራሳችንን ለሰማያዊ መንግሥት እናብቃ ስላለፈዉ ዓመጻችንና ክህደታችን ንስሐ አንግባ» እንድትሉ አይደለም ይልቁኑ እንደታላቁ ፈርኦን «እግዚአብሔርንም አናዉቅም ለሕዝቡም አንራራም በዓመጻና በክህደት ሕይወታችን እንጸናለን አንድነታችንና ኅብረታችን ከጨለማ ገዥ ከዲያብሎስ ከግብር አባታችን ጋር ነዉ እንድትሉና አስከመጨረሻዉ ዕቅታ ድረስ ታማኝነታችሁን እንድትገልጹልኝ ነዉ እግዚአብሔር የፈለገዉን ለማድረግ እንደ ሰዉ ወይንም እንደ እኔና እንደ እናንተ የዓመታት የወራቶች የቀናት ዝግጅት እንደማያስፈልገዉና የፈለገዉን በፈለገዉ መንገድና ቀን ማድረግ እንደሚቸልና ካለ እርሱ ፈቃድ በባለሟሎቹ ላይ ማንም ይሁን ማን አንዳች የማድረግ ሥልጣን እንደሌለዉ ነዉ እንኳን ግዙፉ ነገር ቀርቶ እናንተ በሳይንሱ «አተም» የምትሉት ረቂቅ ነገር በአርሱ ዕይታና ቁጥጥር ዉስጥ ስለሆነ ከእርሱ ፈቃድ ዉጭ አንዳች ሊሆን ሆነ ሊደረግ አይችልም ታዲያ እንዲህ ስላችሁ ተስፋ ቆርጣችሁ እጃችሁን ለእግዚአብሔር እነድትሰጡና ከእዉነት ጋር አንድነትና ኅብረት እንድትፈጠሩ ሳይሆን ይልቁኑ በበደል ላይ በደል በዓመጻ ላይ ዓመጻ በርኩሰት ላይ ርኩሰት በእጥፍ በእጥፍ እንድትጨምሩና ማንም የማያገኘዉን የሚጣፍጠዉን የግፋችሁንና የጭከናችሁን ጽዋ እንድትጠጡ ነዉ እስካዉን ድረስ የራሱን አገርና ሃይማኖት ለማጥፋትና ሕዝቡንም ለዓመጻ ለክህደት ለርኩሰት ለጥላቻ ለበቀልለዘረኝነት ለጎጠኝነት ያሰለፈ እንደልቤ የሆነ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በዓለም ላይ አንደ ወያኔ ወይንም ኢሕአዴግ መንግሥት አላጋጠመኝም በዚሁ አጋጣም ለአባላቱና ለደጋፊዎቹ በተለይ ለመሪዎቹ ታላቅ ምስጋናዬንና እስከአሁን ድረስ ላደረጋችሁልኝ እንደልብ መታዘዘ አድናቆቴን ልገልጽላችሁ እወዳለሁ ለታላላቅ ባለሟሎቼ እንኳ የዓመታት አይደለም የአንዲት ቀን ዋስትና መስጠት አለመቻሌንና አቅመቢስነቴን ተረድቻለሁ ታዲያ አንዲህ ስላችሁ ኃይል የለኝም የፈለኩትን ለፈለኩት መስጠጥ አልችልም ከጥፋትና ከዉድቀት መታደግ አይቻለኝም ለማለት ፈልጌ ሳይሆን መቼስ ስለ እዉነት መሸነፍን ሆነ እዉነትን መቀበል ዉርደት መሆኑን ከእኔ በላይ እናንተ ሳታዉቁ አይቀርም ብዬ እገምታለዉና አቅማችሁን እንኳ ብታስተዉሉ በአንደበታችሁ ኃያል መሆናችሁን መግለጽና ማንኛዉንም ሰዉ በተለያየ መንገድ ማስፈራራት ማስጨነቅ አለባችሁ እንጂ በእአግዚአብሔር ጭብጥ ዉስጥ ነኝ አጥብቆ ቢይዘኝ የምጨፈለቅ ጨክኖ ቢለቀኝ ብትንትኔ የሚወጣ ነዉ እንኳን በራሴ ሥልጣን ልሰራና ልናገር ቀርቶ ማሰብ የማልችል ደካማ ነኝ» ብላችሁ ራሳችሁን ዝቅ አድራገችሁ ዉርደት በሆነዉ በትህትና ሕይወት እንዳትኖሩ ለማሳሰብ ነዉ እናንተ የዓለም ሕዝቦች በተለይ ኢትዮጵያዉያን የቅዱሱ ኪዳን ሕዝቦች» የምትባሉ ለወደፊቱ «አንድ በእግዚአብሔር የተቀባ አዉነተኛ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ «ቴዎድሮስ» የሚባል ይነግሣል በዚያን ዘመን እዉነተኛ ሰላም ፍቅር ፍትህ አኩልነት ነጻነት ብልጽግና አንድነት ይሆናል ምድሪቱም ከሕዝብ ደም መጣጮችና ተባዮች ትጸዳለች ሀገረ እግዚአብሔር የተባለች ኢትዮጵያ የድንግል ማርያም አስራት አገርን ሊያጠፏት የተነሱና የሚነሱ መንግሥታት ቡድኖች ድርጅቶች ግለሰቦች በእግዚአብሔር ቁጣ ይጠፋሉ አገሪቱና ቀሪዉ ዓለም አገራት በእግዚአብሔር በተመረጡና በተቀቡ በአንድ ንጉሠ ነገሥትና በአንድ አጨጌ ይመራሉ ከምድረ ገጽ እንድትጠፋ የተፈለገችዉ ታላቋ ኢትዮጵያ በአዉነተኛ ልጆቿ በዓለም ትገናለች ማንም ምንም ሊያደርጋት አይችልምና ስንዱ እመቤት ሆና ከፍ ከፍ ትላለች ቤተሕዝቡ ቤተክህነቱና ቤተምልክናዉ በአንድ ላይ ሆነዉ በመንፈስ ቅዱስ ይመራሉ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥት ትሆናለች የሚባል ንግርት አለና ይህ የሚጣፍጠዉ የዓመጻ የክህደት የርኩሰት የክፋት የተንኮል ተግባራችሁ ሳይቆምና ሳያልቅ ቶሎ ቶሎ እንድትበሉትና እንድትጠጡት አሳስባችኋለሁሆ መቼም ይህን ንግርት ከተረት ተረት ዉጭ አድርጋችሁ የማታዩ በእዉቀታችሁና በኃይላችሁ የታበያችሁ መሆኑን ስለማዉቅ ነዉ በጥናቴ ላይ ያሰፈረኩት እንጂ ለድሾ ዘመን የተቅቐጣጠርኩትን መንግሥቴን ለማንም አሳልፌ እንደማልሰጥና ዲያብሎሳዊ ሥርዓቴ የሆነዉን ሕዝቡ ሲፈልግ እኔን እንዲያገለግልና እንዲያመልክ ሲፈልግ የራሱን አምላክ እንዲያመልክ ሙሉ ዴሞክራሲ መብቱን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ያጎናጸፍኩትን ታማኝ ጌታዉን ክዶ መቼም ለእግዚአብሔርና ለእንደራሴዎቹ ይታዘዛል የሚል አንዳች እምነት የለኝም እነሱን የሚቀበል ከሆነ ደግሞ ጣዖታትንና ባዕድ አምልኮ እንዳይፈጽም አግደዋለዉ በዝሙትና በአመዝራነት ሕይወት እንዳይኖር ተጽህኖ አደርስበታለዉ ዘፈኑንና ዳንኪራዉን በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እንዲያቀርብ እድል አልሰጠዉም ጥላቻና ም በቀ ንዳይፈጽም ን አሳጠዋለሁ በተንኮል በክፋት በግፍ በአድሎ በስረቆት በዉንብድና በጭቆና በበደል ሕይወት ዉስት እንዳይኖር መንገዶቹን ሁሉ እዚጋበታለሁ እንዳያዉቀዉና እንዳያስተዉለዉ አድርጌ ያደነዘዝኩትን ኅሊናዉን ከፍቼለት ይህን ያደፈ የጎደፈ የጎስቆለ ባሕርይዉንና ጎስቋላ ኑሮዉንና ሕይወቱን እንዲያስተዉ አድርጌ ምድራዊ ሕይወቱን እንዲንቅና በዐይኑ ያላየዉን ሌላ ዓለም እንዲመኝ አደርገዋለሁ ባጠቃላይ እንደፈለገዉ የሚፈጽመዉን የኃጢአት ተግባርና ንግግር እገድብበታለሁ ይህንንም በታላቁ ስሜ ዲያብሎስ በመማል አረጋግጣለሁሆ በተለይ እናንተ እንደልቤ የሆናችሁ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክና የብሔር ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግሥታት መሪዎችና ባለሥልጣናት ከሁሉ በላይ የእኔ ስጦታ የሚቀርባችሁ እናንተ ስለሆናችሁ ኃይላችሁን የተለያዩትን ስሜን አርማችሁን ደግሞ ኮኮቤን አድርጋችሁ እስከመጨረሻ ዕቅታችሁ ድረስ እንድትፋለሙና በጽናት እንድትቆሙ እያልኩ ለወደፊትም ታላቁን የጨላማ መንግሥቴን የምትወርሱና ሺህሞታችሁንም በዚያ የማጸናላችሁ መሆኑን በዚሁ ቃል እገባላችኋለሁ። የሆነ የተታለልነዉና የሳትነዉ አዉነት አለ ብሉ የሚጠይቅና እዉነትን የሚፈልግ የለም ሁሉም ለቅርፊት ሥጋዉ በሚመች ሕይወትና ሥርዓት መመላለስ ስለሆነ ምርጫዉ በአንደበቱ «እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስ ወንጌል» እያለ በሞት መንገድ ዉስጥ እንዲመላለሱ በማድረጌ አንደኛዉን የሚሊኒየም ግቤን አሳክቻለሁ ታዲያ ብዙ ተከታይ እንዲያገኙ እኔን «ዲያብሎስ» እያሉ እንዲያጥላሉኝና እንዲረግሙኝ ሙሉ ነጻነትንና ፈቃድ ሰጥቻቸዋለሁ ልክ እንደዘመኑ አንዳንድ «ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ነን በማለት የመንግሥት መሳሪያ የሆኑና ተቃዋሚ ለማስመሰልና ደጋፊ ለማግኝት ሲሉ አንዳንዴ መንግሥትን ሲቃወሙና ሲኮንኑ መንግሥት የራሱ ተለጣፊ መሆናቸዉን ስለሚያዉቅ አንዳች እንደማይላቸዉና ቂም ይዞባቸዉ እንደማይበቀላቸዉ ሁሉ እኔም የጨላማዉ ገዥ እነዚህ በእግዚአብሔር ሆነ በኢየሱስ ስም የሚነገዱ አገልጋዮቼ በእኔ ቁጥጥር ዉስጥ ስለሆኑ ቢሰድቡኝ ሆነ ቢረግሙኝ አንዳች የማይሰማኝ ሲሆን ዋናዉ ፍላጎቴ በእዉነተኛዉ አምልኮና አምነት ዉስጥ ያሉ ምአመናን እግዚአብሔር «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የሚሰበክበትና ዲያብሎስ የሚረገምበት አዳራሽ ነዉ» በማለት ወደ እኔ ጨለማዉ ገዥ የእምነት ድርጅቴ ዉስጥ እንዲመጡ ነዉ ኅሊናቸዉን በራሳቸዉ ጊዜ አደነደኑት አንጂ መሪያቸዉ መንፈስ ቅዱስ ቢሆን ኖር እንኳን አስራ ሺህ ቤት ድርጅት ሊቋቋም ቀርቶ ሁለት የተለያዩ ተቋም አይሆኑም ነበር ነገር ግን ምርጫቸዉን እኔን ስላደረጉና ሁሉም ድርጅቶች በበላይ የምመራቸዉና የማሳስባቸዉ እኔ ስለሆንኩ እያንዳንዱን የድርጅቴን አባል እንደ ኳስ ልጫወትበትና ከአዉነት ላርቀዉ ችያለሁ የሚያሳዝነዉና የሚገረመዉ ደግሞ ከእዉነተኛነት ከቅንነት ከየዋህነት ከልባምነት ሕይወት መራቃቸዉና በደመ ነፍስ በመመላለስ በክህደትና በዓመጻ መኖራቸዉ ሳያንሳቸዉ እኔ አንኳ የማልዳፈረዉን በትዕቢትና ዕብሪት በሞላዉ ንግግር ቅዱሳን መላእክትን ነቢያትን ሐዋርያትን ሰማዕታትን ጻድቃንን ከሁሉ በላይ ደግሞ የአደራ እናታቸዉን ለሰዉ ዘሮች ደኅንነት ሁል ጊዜ ኀዘንተኛ መሆንን የመረጠችሁንና ለሰዉ ዘር በሙሉ ጥብቅና የምትቆመዉን ድንግል ማርያምን ያዋርዳሉ ያቃልላሉ ይሰድባሉ በዚህ ብቻ ሳያቆሙ ዕለት ዕለት እዉነተኛዉን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስን «አማላጅ ነዉ ፍጡር ነዉ » እያሉ ይሰድባሉ ያዋርዳሉ ታዲያ ይህን ድርጊታችሁን ማቅረቤ ማንነታችሁን ለመግለጽና ወደ አዉነተኛ የሕይወት መንገድ ዉስጥ በንስሐ እንድትመለሱ ፈልጌ ሳይሆን ከእኔ በላይ የሆነዉን ድፍረታሁንና ጀግንነታችሁን ለማድነቅ ፈለጌ መሆኑን እናንተም የምትረዱት ይመስለኛል እናንተ ኢትዮጵያዉያንና የዓለም ሕዝቦች አንደራሴዎቼ መሪዎቻችሁ ባለሟሎቼ ባለሥልጣናት ዉዶቼ ካድሬዎች እንዲሁም ጠንቋዮች አስማተኞች መተተኞች ባለዛሮች ወዘተ ያመጡላችሁን የባህልና የክህደት የርኩሰት አምልኮና ሥርዓት ርግፍ አድርጋችሁ በመተዉ በአዉነተኛ ንስሐ የቀደሙ ወላጆቻችሁ ያመጡላችሁን በብሉይ ዘመን በእዉነትና በመንፈስ የሚከናወነዉን ኪዳነ ልቦና በኋላም በሙሴ አማካይነት የመጣዉን ኪዳነ ኦሪት በመጨረሻም የካም የሴም የያፌት ነገድ ዉሕድ ዘር ከሆነችዉ ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰዉ የሆነዉ አምላክ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በመሰረተዉ ኪዳነ መንፈስ ቅዱስ ተመርታችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በመጠመቅ ከእግዚአብሔር እዉነተኛ ልጅነትን ብታገኙ ሕያዉ ሆናችሁ በመንግሥተ ሰማያት እንድትኖሩ የሚያስደርገዉንና ኃጢአታችሁን ከአግዚአብሔር ባሕርይ መዝገብ ላይ የሚደመስስላችሁን ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን ብትቀበሉ በእዉነተኛነት በቅንነት በየዋህነት በልባምነት ሕይወት ብትመላለሱ እኔ የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ ደስ የማይለኝ ስለሆነ ከእኔ ጋር ያላችሁን ወዳጅነት ሆነ አንድነት ወዲያዉ አንድታቋርጡ የማደርግ መሆኑን በጥብቅ አሳዉቃችኃለሁ ስለዚህ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ሕይወታችሁ እስከመጨረሻዉ አንድትጸኑ አሳስባችኃለሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ሌላዉ አደራ የምለዉ ሰባቱ ቅዱሳት ኪዳናት የተባሉትን መመሪያችሁ አድርጋችሁ ብትኖሩ በምድራዊ ሕይወት ዘመናችሁ በረከት ሰላም ፍቅር አርካታ አንድነት ቅድስና በተሞላዉ ኑሮና ሕይወት እንድትመላለሱና ከሥጋ ሞት በኋላ ደግሞ በእግዚአብሔር መንግሥት ሕያዉ ሆናችሁ በቅዱሳን መላእክት ሕይወት ዓይነት አኗኗር በቅድስናና በደስታ ሕይወት ብቻ እንድትኖሩ ስለሚያደርግ ይህ ድርጊታችሁ ደግሞ በእኔ ላይ ክህደትና ዓመጻ እንደፈጸማችሁ ሰለሚያስቆጥር የክህደትና የሽብርተኛነት ዐዋጅ አስወጥቼ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ሆነ ለማጥቃት እንዳልችል ልምሾ ብታደርጉኝም እንዲሁም ሌት ተቀን አረፍት ነስታችሁኝ በመከራ በስቃይ በምሬት ሕይወት ዉስጥ አንድኖር ብታስገድዱኝም እናንተን እስከ መጨረሻዉ እቅታ ድረስ ልበቀላችሁ ወደ ኋላ የማልል መሆኔን በተለመደዉ ጉራ ዕብሪትና ባዶነት በተሞላዉ አንደበቴ አስጠነቅቃችኋለሁ መቼስ እኔ የማዝንለት ግለሰብ ሆነ ቡድን መንግሥት የእምነት ተቋም የሌለ ቢሆንም «ግድ አዘንላቸዉ» ብባል የሚያሳዝኑኝ ሙስሊም ወገኖቻችሁ ናቸዉፀ ዉዱ ባለዉለታዬ የሆነዉ ፍጹም አግዚአብሔር የሆነዉን አምላክ በድፍረት «ኢየሱስ ኢሳ አንደ አኔ ነቢይ ነዉ እንጂ አምላክ አይደለም በማለት ትዉልዱ በክህደት እምነት አንዲመላለሱ በማድረጉ ምክንያትና በአምነቱ ዉስጥም «ሰዉ ሰዉን ገሉሎ ግፍና ጭከናን ፈጽሞ ገነት ይገባል» የሚል አሰተምሮ ስላለዉ በአራቱም ማዕዘን ፈቃዴን ለማስፈጽም አጅግ ስላመቻቸልኝ በዚሁ አጋጣሚ በጨለማዉ ስሜ ባለበት ቦታ አመሰግነዋለሁ ታዲያ አሳዛኞቹ ደግሞ በእምነቱ ዉስጥ ባለዉ አንዳንድ አዉነት ማስመሰያ አስተምሮ አምላካቸዉን በመፍራት በጾሙ በጸሎቱ በስግደቱ በምጽዋዕቱ ወዘተ የሚመላለሱ ከአሕዛብ የራቁትነት አለባበስ ራሳቸዉን ለይተዉ እግዚአብሔር መፍራት ያለበት የጨዋ አለባበስ የሚለብሱ ከዳንኪራዉ ከዘፈኑ ራሳቸዉን የለዩ ከሱስና ከስካር የራቁ የአሜሪካንና የአዉሮፓን የአሕዛብ ባህል የማይከተሉ ሌሎች ወገኖቻቸዉን የሚወዱና የሚያከብሩ ባጠቃላይ እኔ የጨለማዉ ገዥ ደስ በማይለኝ ሕይወት የሚኖሩት በአምነቱ ዉስጥ የሚመላለሱት ሰዎች ናቸዉ ዞሮ ዞሮ የሕይወት መንገድን ስለሳቱልኝ ፍርዱ ቢቀልላቸዉም እንደ እግዚአብሔር ቃል «በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ በሥላሴ ስም ተጠምቆ ከእግዚአብሔር ልጅነትን ያላገኘና መለኮት የተዋሓደዉን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ያልተቀበለ የእግዚአብሔር መንግሥት አይወርሱም በሚለዉ የፍርድ ቃል እጽናናለሁ ምክንያቱም እግዚአብሔር ወልድ በሥጋ ማርያም ተገልጾ የተናገረዉ ስለሆነና «ቃሌ ከሚያልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል በማለት ቃሉ ምን ያህል ጥብቅ መሆኑን ለአዳም ዘር ስለገለጸ ለእኔም ሆነ ለእናንተ አንዳች አድሎ እንደማያደርግ የታወቀ ነዉናነፁ ስለዚህ ከተፈረደባችሁ አይቀር እኔ ደስ በምሰኝበት የኃጢአት ተግባርና ሕይወት ብትመላለሱ የተሻለ መሆኑን እመክራችኋለሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በዚሁ አጋጣሚ አንድ ሥጋቴን አገልጽላችኋለሁ ይከዝዉም የቅዱሱ ኪዳን ሕዝብ ለማጥፋትና ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለመደምሰስ የተሰለፋችሁ የጥፋት ሰዎችና የዓመጻ ልጆች የሆናችሁ ዉዶቼ የዓመጻ የክህደት የርኩሰት ጽዋችሁ ሲሞላ የመጨረሻ ዕጣ ፈንታችሁ የሚሆነዉ በዚህች ምድርም መዋረድ መከራና ስቃይን መቀበል በመጨረሻም መጠረግና በቀጥታ ካለምንም ጥያቄ ወደ ጨለማዉ ቦታ ሲኦል መግባት መሆኑን አዉቃችሁ እጃችሁን ለእግዚአብሔር ትሰጣላችሁ የሚል ነወዉ ታዲያ አንዳንዶች የአኔን አሰራር ያልተረዱ ባለሟሎቼና ዉዶቼ ያልገለጽኩላቸዉን ምሥጢር አሁን ብገልጽላቸዉ ምን እንደሚሉ ባላዉቅም የጥፋት ሰዎችና የዓመጻ ልጆች ለእኔ ዉዶቼ የሆናችሁ ግን ትምህርት እንዲወስዱ ቀኝ ገዢዎች ከእናት አገራቸዉ ለይተዉ «ሱማሊያ» የሚል ስያሜ አዘጋጅተዉ የዓመጻና የክህደት ተግባር ሲያስፈጽሟቸዉ የደረሰባቸዉንና እየደረሰ ያለባቸዉን ችግርና መከራ ዓለም ስለሚያዉቀዉ ብዙ አልናገርም በተዝዋዋሪ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተሰለፉት የኢራቁና የሊብያዉ መሪ ምን ዓይነት እድል እንደገጠማቸዉ ዓለም ስለሚያዉቅ ስለዚህም አልናገርም ስለ ሁለተኛዉ ዓለም ጦርነትም ማስታወስ አልፈልግም እኔ የምናገረዉ በአንድም ይሁን በተለያየ መንገድ የተቀደሰችዉን አገር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ለማጥፋት የተሰለፉ መንግሥታት ቡድኖችሮፎርጅቶች ግለሰቦች ካለፉት መማር አልቻሉምና በእግዚአብሔር ቁጣ እንዳልነበሩ ቢሆኑና ቢጠረጉ እኔ አንዳች እንደማልጠየቅ እየገለጽኩ በመጨረሻ ግን አናንተ ዉዶቼንና ባለሟሎቼን እናንተን የማጣ ከሆነ ኀዘንተኛ እንደምሆን አዉቃችሁ አሁን ባለቀለት ሰዓት ቢሆንም «ምናለ ብታጽናኑኝና ብታስደስቱኝ። የዚህን ሥጋችሁን ምድራዊ ክብሩን አስተዉላችሁና የነፍሳችሁን ማንነት አዉቃችሁ ቢሆን ኖሮ ራሳችሁን በራሳችሁ እጅግ ትታዘቡና የአዳም ዘር ሁሉ ወንድምና አህታችሁ መሆናቸዉን አስተዉላችሁ በዚህች በኮንትራት አገራችሁና ዘመናችሁ ተፋቅራችሁ ተሳስባችሁ ተረዳድታችሁ ተቻችላችሁ በአንድነት በእዉነት በሰላም በፍቅር በእርካታ ትኖሩ ነበር ተስፋችሁንም ሰማያዊ አድርጋችሁ በቅን ሓሳብ በእዉነተኛ ሕይወት በመልካም ምግባር ትመላለሱ ነበር አንድነታችሁንና ኅብረታችሁን ከአምላካችሁ ጋር በመፍጠር ከዚህች ምድር የምትገላገሉበትን ቀን በናፍቆት ትጠባበቁ ነበር ነገር ግን እድሜ ለእንደራሴ መንግሥታትና ባለሥልጣናት እንዲሁም ካድሬዎቼ በቀለም በነገድ በዘር በቋንቋ በሃይማኖት እንድትለያዩ እንድትከፋፈሉ እርስ በእርስ እንድትባሉ እንድትገዳደሉ አንድትጣሉ በጥላቻ እንድትተያዩ አድርገዉልኝ ለጨለማዉ መንግሥቴ ይገብሯችኋል እኔም የጨለማዉ ገዥ ለዉለታቸዉ በሥልጣን ላይ ሥልጣን በገንዘብ ላይ ገንዘብ በሹመት ላይ ሹመት እየጨመርኩላቸዉ ለመጨረሻዉ የጨለማ ግዛቴ ለታላቅ ኃላፊነት አጫቸዋለሁ እሳቱን መንግሥቴን ሌሎችን የሚያቃጥለዉን እናሱን ግን እንደ ወርቅ የሚያጠራዉን እንዳች ጉዳት የማያመጣባቸዉን አወርሳቸዋለሁ አሁን አሁን ደግሞ ሥጋዊዉን መድረክ ሙሉ በሙሉ ስለተቆጣጠርኩ ወደ መንፈሳዊ መድረክ ሙሉ ኃይሌን አሰማርቼ ጉደኛ ትዕይንት እያሰራዉ እገኛለሁ ዋና «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ዓላማዬ ተዋሕዶ ሃይማኖትን ለማጥፋት ነዉ በዚህ ምክንያት የተለየ ቡድን አቋቁሜ በየአብያተክርስቲያኑ አገልግሎት ዉስጥ ሰግስጌ ክፍፍሉን በሃይማኖት አባቶች ዘንድ ጭምር በሰፊዉ እያስፋፋዉ እገኛለሁ እነዚህ ምርጥ ባለሟሎቼ ብልጥ ናቸዉና በዋና ጉባኤና የሃይማኖት አባቶች ባሉበት « አመቤታችን ቅዱሳን» እያሉ የሚጠሩ በራሳቸዉ ልዩ ጉባኤ ደግሞ እንኳን ድንግል ማርያምንና ቅዱሳንን በክብር ሊጠሩ ቀርቶ እዉነተኛዉን አምላክ እግዚአብሔርን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ፕሮቴስታንቱ አማላጁ የሱስ በተዝዋዋሪ ወደ እኔ ጨለማዉ ጌታ የሰሱ ለመለወጥና የሱሴ የሱሴ ከማለት የማይመለሱ ድንግል ማርያምንም ስንት የክብር ስሟን አስወግደዉ ማርያም አያሉ የሚጠሩ ቅዱሳንንም እንደ ቆሎ ጓደኛቸዉ ገብርኤል ጳዉሎስ ጊዮርጊስ እያሉ ከመጥራት የማይመለሱ ቆራጥና ደፋሮች ናቸዉ አንዳንዴም ሞቅ ሲላቸዉ ኢየሱስን «እግዚአብሔር አትበሉ» ቅድስት ድንግል ማርያምንም «ወላዲተ እግዚአብሔር አትበሉ» ከማለት ወደ ኋላ የማይመለሱ የጀግኖች ጀግኖች ናቸዉ ይህን የዋህ ምእመንን አያታለሉትና እየሸወዱት ወደፈለጉት አቅጣጫ ለመዉሰድ የሞት ሽረት እያደረጉልኝ ይገኛሉ ለዚህ ታላቅ ተጋድሏቸዉ በጨለማዉ ስሜ በዚህ አጋጣሚ አመሰግናቸዋለሆ ትዉልዱም ቀን ከሌሊት ኅሊናዉ በዘፈንና በዳንኪራ ስለደነዘዘ በዚሁ መልኩ ለኅሊናዉ ምቹ የሆነዉን የዘፈንና የዳንኪራ «መዝሙር» የክህደትና የጥርጥር ስብከት» እንዲያወጡ እያደረኩ እንደ ፕሮቴስታንት ድርጅቴ አባላቶቼ እነሱ ማሪያን የሚሏቸዉ ምርጥ ዘፋኛቼና «ሰባኪያን ወንድሞቼ» የሚሏቸዉን ምርጥ ምስክሮቼን ተከትለዉ ያዳጳሂዚቋጩጨረ ቃሰ መጫወቻና መታኛ ሕድረግዉልኋቻልሳ ታዲያ አንዳንድ ምአመናንና አገልጋይ ይህን ዘፈን ዘፈን የሚለዉን መዝሙርና በድንፋታና በዕብሪት የተሞላዉ ስብከታቸዉን እንደኔ ሲደሰቱበትና ሲዝናኑበት እጅጉን እረካለሁ እኔ የምጠላዉ መዝሙርና ስብከት የሰዎች ነፍስ ወደ ሰማየ ሰማያት የምትመጥቅበትና ራሷን ለንስሐ የምታዘጋጀጅበትን ነዉ እድሜ ለምርጥ አገልጋዮቼና ባላሟሎቼ ይኸዉ በአግዚአብሔር ቃል እያስጨፈሩልኝ እያዝናኑልኝ ነዉ ከዚህ በተጨማሪ ለጫት መቃሚያም እያዋሉልኝ ነዉ የእኔን ታላቅነት የሚያስመሰክር ያላሰብኩት ሲሳይ በ ዓም ወደ ማለቂያዉ ወራቶች ላይ ገጥሞኛል ይኸዉም ለአሰራ ዘጠኝ ዓመት በቀላሉ ኅሊናቸዉን አልሸጥም እያሉ ሲያስቸግሩኝ የነበሩ የእኔን ምርጥ አገልጋዮችና ባለሟሉችን ገበናቸዉን እያጋለጡ ሲያሳቸግሩኝ የነበረ ቤተክርስቲያናቸዉን ለብዙ ዓመታት በትጋትና በመንፈሳዊ ቅናት ሲያገለግሉ የነበሩ ባለቀለት ሰዓት ዘረኝነትና ጎጠኝነት እያስፋፋ ክህደትን ዓመጻን ርኩሰትን እየፈጸመና እያስፈጸመ ያለ መንግሥቴን እንደ ሌሎቹ መንግሥታቴ ዘፈኑንና ዳንኪራዊን ያነገሠልኝን ዉዴ የሆነዉ ኢሕአዴግ ድርጅቴ የእነሱም ማኅበራት አብዛኛዉ አባላት ከላይ የተገለጹትን ፈጻሚና አስፈጻሚ የሆኑና «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር እንዲሁም ቀሪዎቹ ደግሞ ደጋፊና ድርጊቱን ባያስፈጽሙም በመፈጸሙ ድጋፍ የሚያደርጉ መሆናቸዉን ለዓለም ያስተዋወቁበት በመሆኑ ነዉ መቼስ እአዉነታቸዉን ከሆነ አብዛኛዉ አባላት የኢሕአዴግ አባልና ደጋፊ ከሆኑ ለስራ አስፈጻሚነት ሆነ ለአመራርነት ሊመርጧቸዉ የሚችሉት የኢሕአዴግን አባላትና የኢህዴግ ደጋፊ የሆኑ ሰዎችን መሆኑን ምንም ጥርጥር የለዉም ምክንያቱም አባልና ደጋፊ ሆኖ የሚቃወምን ወይንም ገለልተኛን የሚመርጥ በዓለም ላይ እስከ አሁን ባለኝ ድኗር ዓመት ጥናቴ ዉስጥ አልተመለከትኩም ቢበዛ በጥናቴ የታየዉ ሰዎች ራሳቸዉን ለማዳን ከመጥፋትና ከመጠረግ ራሳቸዉን እንኳ የማያድኑትን ደካማና ዓመጸኛ የክህደትና የርኩሰት ጽዋቸዉ የሞላባቸዉን ሰዎች « እኛን ያድኑናል ከለላ አምባ መጠጊያ ይሆኑናል » ብለዉ ያልሆኑትን «ነን» ሲሉ ብቻ ነዉ ታዲያ በዚህ ክፍተት ገብቼ የአስራ ዘጠኙን ዓመት ብስጭቴን ለመበቀልና አንዳልነበሩ ለማድረግ ብነሳም ያቺ የዘመናት ደመኛዬና ጠላቴ ሁልጊዜ አባላቱ ስሟን የሚጠሩ የሚዘክሩ የሚያመሰግኑ «ድንግል ማርያም» የምታባለዉ ከዉድቀትና ከጥፋት ታደገቻቸዉፁ ያ የሚመኩበት አምላከ ኢትዮጵያን ትተዉ ምስጥ በልቶት ሊገነደስ የደረሰን ዛፍ መጠጊያና መከለያ የሚደርጉ ከሆነም ምሳር እንደሚበዛባቸዉ ማስጠንቀቂያ ደረሳቸዉ እኔ ግን የቤተክርስቲያኒቱንና የኢትዮጵያን ተዋሕዶ ዛይማኖት እምነቷን ሥርዓቷን ዜማዋን ቋንቋዋን ባህሏን ትዉፊቷን ባጠቃላይ የቀደሙት አባቶቻቸዉና እናቶቻቸዉ ያወረሷቸዉም ከእግዚአብሔር የሆነዉን እምነትና ቅርስ ለቀጣይ ትዉልድ ለማስተላለፍ ሌት ተቀን የሚተጉ መሆናቸዉን ስለማዉቅ መቼም ቢሆን እነሱንና መሰሎሉቻቸዉን ለማጥፋ ወደ ኋላ የማልል መሆኑን በተለመደዉ በጉራና በዕብሪት በባዶ ሕይወት በተሞላዉ አንደበቴ ዓለም በዚሁ አጋጣሚ እንዲያዉቅልኝ አፈልጋለሁ ሌላዉ የረሳሁት ደግሞ እናንተ የፃይማኖት መሪዎችና የእግዚአብሔር አገልጋይ ነን» የምትሉ የአገራት መሪዎች እንደራሴዎቼን ምርጥ ባለሟሎቼን ባለሥልጣናትን አንዲሁም ዉዶቼ ካድሬዎችን ተከትላችሁ በቴሌቨዥኑ በሬድዮኑ በተለያዩ የኅትመት ዉጤቶችና በድረ ገጾች ወዘተ የሚተዋወቁትን ለዝሙት የሚያነሳሱና ለኃጢአት ተግባር የሚያሰለፉ ማስታወቂያዎችን ይኸዉም «ሕይወት የሆነዉን ኮንደም ተጠቀሙ የደስታና የእርካታ ምንጭ የሆነዉን ሰንሴሽን ኮንደም ተጠቀሙ ታላቅ ርካታ የምታገኙበትን ኮንደም ወይንም ሰንሴሽን በቀላል ዋጋ እየተጠቀማችሁ ተደሰቱ ወዘተ እያሉ ፈቃዴን የሚፈጽሙትን ሥጋዉያንን ተከትላችሁና የእነሱ ተባባሪ ሆናችሁ በእግዚአብሔር ቁጣ ላይ መገዳደራችሁን በዚሁ አጋጣሚ እመሰክርባችኋለሁ በእርግጥ እናንተ ሆናችሁ እነሱ ለአግዚአብሔር ትዕዛዝ ደንታ የሌላችሁ መሆኑን ባዉቅም «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ገንዘቡን ጥቅማጥቅሙን ለማግኘት እንደምትተጉ የእግዚአብሔርን ሕግ ለማስጠበቅ አለመትጋታችሁና ተቃራኒዉን ተግባር ከሚያስፈጽሙ እንደራሴዎቼ ጋር እጅን ጓንት ሆናችሁ በጋራ መሰለፋችሁ ምን ያህል ኅሊናችሁን ያደነደናችሁ ቆራጥና ጀግና መሆናችሁን በዚሁ ታላቅነታችሁን እመሰክርባችኋለሁ ታዲያ አንዳንድ ያልገባቸዉ ሰዎች እነዚህ የዛይማኖት መሪና አገልጋይ ነን» የሚሉ ሰዎች ከቻሉ ይህን ማስታወቂያ ማዉገዝና ማስቆም ሲገባቸዉ ካልሆነላቸዉ ደግሞ «ዓመጻና ርኩሰትን ከሚያስፈጽሙ የዓመጻ ልጆች ጋር አንድነትና ኅብረት የለንም በእግዚአብሔር ሕግና ሥርዓት ላይ አናምጽም» በማለት ከእዉነት ጋር መሰለፍ ሲገባቸዉና «ኤድስ ሆነ የአባላዘር በሽታ የመጣዉ በኃጢአታችን ምክንያት ነዉ ካልደረሱበት አይደርስም ስለዚህ ከዝሙትና ከአመንዝራነት ሕይወት እንዲሁም ከግብረ ሰዶም ተለዩ በበሽታዉም የተያዛችሁ ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙን ተቀበሉ እምነቱን ጠበሉን ተጠቀሙ ሌሎቻችሁም ደግሞ በኤድስ ሆነ በማንኛዉም ዓይነት በሽታ የተያዘን ሰዉ አታግሉ አድሎና መገለል አትፈጽሙ እርዱ ተንከባከቡ አግዙ ሁሉንም አፍቅሩነ በማለት በግልጽ ማስተማርና በሽተኞችንም ማጽናናትና በሕክምና ሆነ በተለያየ መንገድ መርዳት ሲገባ እንደ ዓለማዉያትኑና ሌት ተቀን ስለገንዘብ የሚያስቡ እርዳታን ለማግኘትና በአቋራጭ መንገድ ገንዘቡን ለመበልጸጊያ እንደሚጠቀሙ ሰዎች ስለ እግዚአብሔር ትዕዛዝ መጠበቅ ደንታ ሳይኖራቸዉ እንደ ሥጋዉያኑ አካፄድ ነዉ የሚሄዱት» እያሉ የሚተቿችሁን አንዳች አትስመ አነሱ ተስፋቸዉ ሰማያዊ አገልግሎታቸዉም አዉነተኛ መንፈሳዊ ስለሆነና የእኔን የጌታችሁን አካሄድ ስላላወቁ ለእናንተም ለእኔም የሚያስቸግሩ የእግዚአብሔር እዉነተኛ አገልጋዮች ስለሆኑ ነዉ እናንተ ግን በመንፈሳዊ ሽፋን የሥጋ ፈቃዳችሁን የምትፈጽሙ ምድራዊ ክብርን ጥቅምን ሥልጣንን ዝናን ድሎትንና ምቾትን የምትፈልጉ መሆኑን በደንብ አስረዲቸዉ የአኔን ወዳድነት ከፈለጉ የእናንተን ፈለግ ተከትለዉ በእኔ አታላዩርሸዋጁ መንፈስ ተመርተዉ ፈቃዴን ይፈጽሙ ያስፈጽሙ ያኔ ከእኔ ዘንድ እንደአናንተ ሞገስ አግኝተዉ ለታላቅ አገልግሎት አሰልፋቸዋለሁ ይላል ትዉልዱን በቀለም በነገድ በዘር በጎጥ በቋንቋ በሃይማኖት ከፋፍሎ እያጣላዉና እያባላዉ እንዲሁም በጊዜያዊ ጥቅምና ድሎት ዓይነ ኅሊናዉን በማሳወር ለዓመጻና ለርኩሰት ሕይወት የዳረገዉ የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ ከሠራዊቱ ሰይጣናት ጋር በመሆን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምዕራፍ « እናንተ ኢትዮጵያዉያን መሪዎች ባለሥልጣናት እንዲሁም የተለያዩ የሃይማኖት መሪዎች ወደ ትዝብቴ ከመግባቴ በፊት በመጀመሪያ እንኳን ለታላቁ በአሌና በአላችሁ ለአስራ ስድስተኛዉ ዓለም አቀፍ የኤች አይቪ ኤድስና አባላዘር በሽታ አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ ወደ ትዝብቴ እአገባለሁ ይኸዉም እንደራሴዎቼ ሥጋዉያን መሪዎቻችሁና ባለሟሉሎቼ ባለሥልጣናት በዓም ወደ ወንበር ሳመጣቸዉ በዓለም ዘንድ ሞገስ ካገኙባቸዉ አገራት አንዷ የሆነችዉ የአሜሪካ የታላቋ ባቢሎን መሪ የነበሩት ለዚሁ ታላቅ ክብረ በኣሌ «ሀገረ እግዚአብሔር» ወደተባለች ወደተቀደሰችዉ አገር ኢትዮጵያ ሲመጡ ከሰማይ መልአክ አንደመጣ ቆጥራችሁ ዳግም ሞገስን ለማግኘት እንደ ሕጻን ልጅ ከኋላ ኋላ ድክ ድክ እያላችሁ ስትሯሯጡ በመመልከቴ ነዉ ይህ ደግሞ የሆነበት ዋንኛ ምክንያት ከጸጋ እግዚአብሔር መራቃችሁና ነዉራችሁን ክብራችሁ በማድረጋችሁ ምክንያት ከእግዚአብሔር የምታገኙት ግርማና ሞገስ ከእናንተ ተወስዶ ማፈሪያ እንድትሆኑ ለሌላ በመሰጠቱ ነዉ አስቲ አንዲት ጥያቂ ልጠይቃችሁ። » እያልን ፈጣሪን እንዲያጠፋን እያስገደድነዉ መሆኑን ኢትዮጵያዉያን ሆኑ ዓለም ሊያዉቅ ይገባዋል በማለት የሚናገሩትን አትስሙ እነሱ የዚህችን ዓለም ጣፋጭነት ያልተረዱ በዝሙት በግብረ ሰዶም የሚገኘዉን ደስታና ሕይወት ያላወቁ መአትን ብቻ በማዉራት ዘመናቸዉን ከሰላም ከአዉነተኛ አርካታ ከጤና የራቁ ናቸዉ አምላካቸዉንም የመአት አምላክ አድርገዉ የሚቆጥሩ ናቸዉ እናንተ ግን አምላካችሁ የምሕረት አምላክ ስለሆነ እንኳን ይህን ቀላል ተግባር ቀርቶ በግልጽ ዝሙቱን ሆነ ሌላዉን ብትፈጽሙ ከመንግሥቱ አይለያችሁም የገዛነመ አሳት ፍርድም አያመጣባችሁም ታዲያ አንዳንዶች የንስሐ ምሥጢር ያልገባቸዉ ሰዎች የሚሉትን አትስሙ ይኸዉም የንንስሐ አድል የሚያገኙትና ወደ ልባቸዉ ተመልሰዉ ከእግዚአብሔር ጋር አንድነትና ኅብረት ሊፈጥሩ የሚችሉ ሰዎች ባለማወቅና በሥጋ ድካም በኃጢአት የወደቁ ሰዎች ናቸዉ እንጂ ኅሊናቸዉ እያወቀና እየተቃወማቸዉ በድንዳኔ ኃጢአት የሚፈጽሙ ሰዎች የንስሐ እድል አያገኙም ነፍሳችዉም ወደ ልቧ ተመልሳ ከአምላኳ የመታረቅና አንድነት የመፍጠር እድል አታገኝም ምክንያቱም የድፍረት ድፍረት ኃጢአት ስለሚፈጽሙና የመንፈስ ቅዱስን ስራ በድፍረት ስለሚቃወሙ ነዉ በዚህም ምክንያት ከማንም በላይ የባሰዉ ፍርድ እንደ ፈርኦን ይሁዳ አርዮስና መሰሎቻቸዉ እንደሚጠብቃቸዉ ማወቅ አለባቸዉ በማለት የሚናገሩትን ነዉ ምክንያቱም እናንተ በተለያየ አቋራጭ መንገድ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምትገቡበትን በር ስላዘጋጃችሁና መንገዱንም አስፍታችሁ እንደልባችሁ የምትወጡበት የምትገቡበት ስላደረጋችሁ አንዳች ስጋት አይግባችሁ በዚህ አጋጣሚ በግልጽ ኃጢአትን ለምትፈጽሙ አንድ መልእክት አለኝ ይኸዉም እናንተ እዉነተኛ ርካታ ጤና ሰላም ደስታ ቅድስና ያላችሁ ስለሆነ ከቻላችሁ አንድ ለአንድ ተወሰኑ ብዬ ባልመክርም በሕይወት ትረስ ኮንደምና የደስታ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምንጭ በሆነዉ በቀላል ዋጋ በምታገኙት ሰንሴሽን ተጠቅማችሁ ዝሙትን ፈጽሙ ተዝናኑ ዝፈኑ ጨፍሩ ምክንያቱም የእናንተ ህልዉና የሚያበቃዉ በዚህች ምድር ስለሆነ አንዳች የሲኦል ሆነ የገዛፃነመ አሳት ነገር አያሳስባችሁ እነዚያ ሞኞች ያላዩትን ገነትና መንግሥተ ሰማያትን ተስፋ የሚያደርጉትን አትከተሉአትስመሙ እናንተ ኢትዮጵያዉያን የዉጭዉን የባዕዳንን ወይንም የኢትዮጵያዉያን ያልሆነዉን ሕይወትና ባህል አንደ ታላቅ መሆን ቆጥራችሁ ይህን ቅርፊት ሥጋችሁን ለማስመለክ ሌት ተቀን መትጋታችሁ እኔን የጨለማዉን ገዥ ቢያስደስትም አግዚአብሔርንና ቅዱሳንን ማሳዘኑን ልገልጽላችሁ እወዳለሁ ይኸዉም ጡታችሁንና ደረታችሁን አምብርታችሁን ቂጣችሁን ዳሌና ታፋችሁን ገላልጦ በሚያሳይ አለባበሳችሁና በተወጣጠረ ሱሬና ልብስ ይህን ዘለዓለማዊ ሐዉልት ሆኖ የሚቆየዉን የማይፈርስ አካላችሁን ለዝሙት ማነሳሻ በመጠቀማችሁና መንገደኛዉን ሁሉ በኅሊናዉ ስላስረከሳችሁልኝ ነዉ «ወደ ሴት አይቶ ለዝሙት የተመኘ ሁሉ እንዳመነዘረ ይቆጠራል የተባለዉን ቃል ተፈጻሚ እንዳስደረጋችሁ ሁሉ ማሰናከያ ለሚያመጣ ሁሉ ወዮለትከኩ የተባለዉ ደግሞ በእናንተ ተፈጻሚ ስለሚሆን በመፃል በሁለታችሁም ዉድቀት ተጠቃሚዉ እኔዉ የጨለማዉ ገዥ በመሆኔ የአድለኞች እድለኛ መሆኔን በዚሁ አጋጣሚ ልገልጽላችሁ እወዳለሆ በራቁትነት ማሳበደ የቀረችን ይህች «የእግዚአብሔር አገር » የተባለች ኢትዮጵያ ነበረች እድሜ ለአእንደራሴዎቼ መሪዎችና ለዴሞክራሲ ፍልስፍናዬ ይኸዉ በሥልጣኔና በባህል ሽፋን ርኩሰትን አንግሼባታለሁ ከዚህ በኋላ ጥፋታችሁን እንጂ « ይህን ሳለደርግ ቀረሁ» ብዬ አንዳች የምቆጭበት ነገር እንደሌለም አኔ የጨለማዉ ገዥ ላሳዉቃችሁ እወዳለሁ የደረቱን የጡቱን የታፋና የዳሌ ባጠቃላይ የከበረዉን ገላ ወደ ተራነት ለዉጣችሁ በየአደባባዩና በየመንገዱ ገላልጣችሁ ለአላፊ አግዳሚዉ ስታሳዩ ትዝ ያለኝ ከዛሬ ሶስት ሺህ ዓመት በፊት እስራኤላዉያን ከግብጽ ባርነት ነጻ ወተዉ ወደ ከንዓን ሲጓዙ በሞአብ ንጉሥ ትዕዛዝ የሞአብ ሴቶች የእስራኤልን ወንዶች ለመማረክና በዝሙት ለመጣል በኋላም አግዚአብሔር እንዲያጠፋቸዉና አንዲቀስፋቸዉ ለማድረግ ለበልዐም የመከርኩትንና ያሳሰብኩትን ክፉ ሓሳብ ተግባራዊ ያስደረገልኝን ነዉ የአሁኖቹ ግን አዛዥ ንጉሥ ሳይኖርባቸዉ ሳይገደዱ ሳይመከሩ በነጻ ኅሊናቸዉና ፈቃዳቸዉ ተመርተዉ በአካል በቴሌቨዥን በፊልም በማስታወቂያ ወዘተ በመሳሰሉት የከበረዉን ገላ አራክሰዉና ገላልጠዉ በማሳየት ትዉልዱ በፍትወት እንዲቃጠል በተግባር በንግግር በሓሳብ እንዲረክስ በማድረጋቸዉ በዚሁ አጋጣሚ የጥንቶቹንም የበለጠ ደግሞ ካለምንም ተጽህኖ በራሳችሁ ነጻ ፈቃድ ፈቃዴን እየፈጸማችሁልኝ ያላችሁትን የአሁኖቹ ዘመናይ ሰዎችን በጨለማዉ ስሜ አመሰግናችኋለሁ እናንተ ኢትዮጵያዉያን ሆናችሁ ሌሎች የዓለም ሕዝቦች ዘፈኑንና ዳንኪራዉን እንደምትመለከቱት ባለመድረኮቹ ጥቂቶች ናቸዉ አጫፋሪዎቹና የድርጊቱ ተቀባዮች «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር የአዳም ዘሮች ናቸዉ ዘፋኞቹንና ዳንኪርተኞቹን ሙሉ በሙሉ ኅሊናቸዉን ስለምቆጣጠር እነሱ «ጥበብ አርት ነዉ» ብለዉ ራሳቸዉንም አርቲስትና ጥበበኛ ነን በማለት ስለሰየሙ ትዕይንቱን ሲያቀርቡ ነፍሳቸዉ በዚያች ወቅት እያበደችና ሌሎችንም አእሳበደች መሆኑን አያስተዉሉም ዱሮ በየጠንቋዩ በየዛሩ በየሚርቱ ቤት የሚቀርብልኝ ምሴን አሁን ደግሞ በዘመናዊ መልክ ሲቀርብልኝ ለጊዜዉ በኅሊናቸዉ የምፈታተነዉንና የማስጨንቀዉን ፈተናዬን ገታ አደርግና ተያያዥ የሆኑትን የርኩሰት አሳቦች በወንዱም በሴቱም አመጣለሁ ይኸዉም ስካሩን ዝሙቱን ሴሰኝነቱም ወዘተ በማሳሰብ ወደ ሞትና ጉስቁልና ሕይወት አመራቸዋለሁ በመጨረሻም ሰላማቸዉን አእርካታቸዉን ነስቼ ለማይገባ ባሕርይና ጠባይ በመዳረግ ሙሉ በሙሉ ኅሊናቸዉን በመቆጣጠር እንደ ሱሰኞች ባሮቼ አደርጋቸዋለሁ አንዳንዶች ግን ወደ ልባቸዉ ተመልሰዉ ከዚህ ተግባር ራሳቸዉን ከለዩ በኋላ የቀድሞ የእብደት ተግባራቸዉን ሲያስተዉሉ ለወገኖቻቸዉ ያዝናሉ እነሱ የተከፈተላቸዉ ዐይን ለወገኖቻቸዉም እንዲከፈትላቸዉ ይጸልያሉ ይለምናሉ ምክንያቱም አምላካቸዉን ራቁቱን ሰቅለዉ ራሳቸዉን በማታለልና በማጃጃል « ዘፈኑና ዳንኪራዉ የደስታ ምንጭ ነዉ» በማለት ተታለዉ ነፍሳቸዉን አእያሳበዱ በዓመጻ ሕይወት መመላለሳቸዉን በማስተዋላቸዉ ነዉ እኔ የጨለማዉ ገዥ ግን ምሴ ስለሆነ ከፈለጋችሁ «ባህል ነዉ» በሉ ከፈለጋችሁ «የብሔር ብሔረሰቦች መገለጫ ነዉ» በሉት ከፈለጋችሁ «ጥበብ ነዉ» በሉ ምሴን እንዳታቋርጡ ነፍሳችሁንም ከማሳበድ ወደ ኋላ እንዳትሉ ሌላዉ ደግሞ ዱሮ ጥንት በአሕዛብ ነገሥታትና ባለሥልጣናት አማካይነት ሰዎችን ከአራዊት ጋር አያታገልኩና አያጋጠምኩ እዝናና ነበር አሁን ደግሞ በዘመናዊ መልክ ሰዉን ከሰዉ ቡድንን ከቡድ እያጋጠምኩ ኳስ እያስረገጥኩ ትዉልዱ ስለ እዉነትና ስለ ነገረ መስቀሉ እንዳይሰማና እንዳያስተዉል እንዲሁም ለነፍሱና ለሥጋዉ አንዳች ጥቅም በማያገኝበት ሕይወት ዉስጥ እንዲመላለስ በማድረግ አእምሮዉን ተቆጣጥሬ አድንዝዝዋለሁ ትዉልዱ ነጋ ጠባ « ሉ እገሌ አሸነፈ አገሌ ይህን ያህል ጎል አገባ እገሌ ድንቅ ተጨዋች ነዉ አገሌ በዚህን ያህል ብር ተሸጠ አገሌ ከእገሌ ጋር ተጣላ ወዘተ» እያለ ቅርፊት ሥጋ ለባሽን እያገነነና አያመለከ ስለ ሕያዊት ነፍሱ አንዳች እንዳያስብ አድርጌ ከሕይወት መንገድ አስርቄዋለሁ ታዲያ በራሱ ነጻ ፍቃድ የመረጠዉና የሚፈጽመዉ እያንዳንዱ ግለሰብና ቡድን ስለሆነ የሚጠየቀዉ እኔ የጨለማዉ ገዥ በዚህ የምጠየቅበት አንዳች ነገር የሌለ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ አሳዉቃችኋኃለሁ አናንተ ኢትዮጵያዉያን ዶሮ ከሃያ ዓመት በፈት «ወንበዴ እያላችሁ የምትሰድቧቸዉና አገር ገንጣጥ አስገንጣይ እያላችሁ ካለስማቸዉ ስም የሰጣችኋቸዉ ምርጥ እንደራሴዎቼና ባለሟሎቼ ወያኔዎችኢሕአዴግ በዚህ አጋጣሚ በዚህ ስም ልጠራቸዉ የቻልኩት እነሱም የሚመኩበት የሚመጻደቁበት የሚታበዩበት የሚወዱት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ስም ስለሆነ ነዉ እንጂ እኔ የጨለማዉ ገዥ ልክ እንደ ኢሕአዴግ ልዩ ስም ልሰጣቸዉ ነበር ፍላጎቴና ምኞቴ የነበረዉ ነገር ግን የባለማሎቼን ምርጫ አከብራለሁ ያወጣሁትን ዴሞክራሲ መብት አጠብቃለሁ ታዲያ አሁን ላሉበት ሥልጣንና ክብር ያበቃዋቸዉ ከጫካ ጀምሮ ታማኝነታቸዉን ስላረጋገጡልኝና የተነሱበት ዓላማ በሚገባ ስላሳኩልኝ ነዉ ይኸዉም ገና ከመሰረቱ እግዚአብሔር የለሽ ሥርዓት ሶሻሊዝምን በማርክዚስት ሌኒዝስት ፍልስፍና ለመመራትና ዓላማቸዉንም ለመፈጸምና ለማስፈጸም ልክ ክርስቲያኖች ኃይል እንዲሆናቸዉ አርማቸዉን መስቀል እንደሚያደርጉ ሁሉ አነሱም እኔ የጨለማዉ ገዥ ኃይል እንድሆናቸዉ አርማዬን ኮኮብ በማንሳት ስለተዋጉልኝ በአግባቡ አርማዬን ያላስከበረዉን ደርግኢሠፓ ድል አድርገዉ ወደ ወንበር ሊመጡ ችለዋል በኋላም ዉለታዬን ሳይዘነጉ ኃይል የሆናቸዉን አርማዬን ከድርጅታቸዉ አርማ በተጨማሪ ለወደፊት ነጻ መንግሥታቸዉ ለአሁኑ ለብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታቸዉ ለትግራይ ለትግሬ መንግሥታቸዉ ሰንደቅ ዓላማ አዉለዉታል በማስከተል ለወደፊቱ ነጻ መንግሥት ለአሁኑ ለብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታቸዉ ለአማሪያ ለአማራ መንግሥታቸዉ ሰንደቅ ዓላማ አዉለዉታል በመቀጠልም ለወደፊቱ ነጻ መንግሥት ለአሁኑ ለብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታቸዉ ለአፋሪያ ለአፋር መንግሥታቸዉ ሰንደቅ ዓላማ አዉለዉታል በማያያዝም ለወደፊቱ ነጻ መንግሥት ለአሁኑ ለብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታቸዉ ለጋንቤሊያ ለጋንቤላ መንግሥታቸዉ ሰንደቅ ዓላማ አዉለዉታል በመጨረሻም በሕገ በዐዋጅ አጽድቀዉ በኢትዮጵያ ምድርና በአራቱም ማዕዘንና በመላዉ ዓለም ከፍ ብሎ እንዲዉለበለብ አድርገዉልኛል ይህ ብቻ አይደለም እዉነተኛዉን የኢትዮጵያ ሰንድቅ ዓላማ የሆነዉ ኢትዮጵያዉያን በአባታቸዉ ኖኅ አማካይነት ከአግዚአብሔር የተቀበሉትና ዘላለማዊ ሰንደቅ ዓላማ ቃልኪዳን የሆነዉን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ኮኮብ አርማዬ የሌለበትን ከና ብሎ አይደለም ዝቅ ተደርጎ እንኳ የሚያዉለበልብ ከተገኘ በወንጀል እንዲቀጣ ማድረጋቸዉ ለእኔ ለጨለማዉ ገዥ ምን ያህል ታማኝነታቸዉን እንዳረጋገጡልኝ ነዉ የሚያሳየዉ በዚሁ አጋጣሚ አድናቆቴን ልገልጽላቸዉ የምፈልገዉ የእነዚህን ምርጥ ባለሟሎቼን ሓሳብ ተቀብለዉ ተግባራዊ ያደረጉና ያጸደቁ ዉድ ባለሟሎቼን የተወካይ ምክር ቤት አባላትንና በአገርና በዉጭ አገር ያሉ ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የተጉ ዉዶቼን ጭምር ነዉ ከሁሉ በላይ ሙገሳዬን የምገልጽላቸዉ ደግሞ ያለፈዉ ባለሟሌ መንግሥት ያስወገደልኝን የምጸየፈዉና የምጠላዉ ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረዉን «ሞአ አንበሳ» በሚል ሲያሜ የሚታወቀዉን መለኮታዊ አርማ ለማስወገድ ወደ ኋላ ያላሉት የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ዛይማኖት መሪዎችና አገልጋዮችን ነዉ ምክንያቱም አሁን ደግሞ ባስወገዱት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር መለኮታዊ አርማ ምትክ «ወያኔኢሕአዴግ ያመጣልን ዲያብሎሳዊ አርማ ኮኮብ የአሸናፊዎች አሸናፊ ስለሆነ አሱን ነዉ ከፍ አድርገን የምናዉለበልበዉ» በማለት በየአብያተክርስቲያኑ እንዲዉለበለብ ስላደረጉልኝ ነዉ ለቅዱሱ ኪዳን ፍጻሜ ለሆነዉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ የተነገረዉ «ሞአ አንበሳ ዘምነገደ ይሁዳ የሚለዉ መለኮታዊዉ አርማ የምቃጠልበትና የምዋረድበት ስለሆነ እንኳን ከፍ ብሎ እንዲዉለበለብ አይደለም በወረቀት ላይ እንኳ አንዲታይ አልፈልግም ታዲያ ዋናዉ ባለቤቶቹ ሲያቃልሉልኝና ሲያስወግዱልኝ እንዴት ምስጋናና አድናቆት አልቸራቸዉ። » ብላችሁኝ እንደማትጠይቁኝ እገምታለሁ ምክንያቱም ለዚህ ሥልጣን አድሜ ያበቃችሁ ይህ ስም ኃይላችሁ ሆኖ ልክ እንደ ብሔር ብሔረሰቦች ቋንቋዬ ልዩነት ለመፍጠርና እርስ በእርስ ደም ለማፋሰስ ለማጣላት ለመከፋፈል ለማገዳደል የረዳችሁ ታላቅ ባለዉለተኛ ስያሜ መሆኑን ከእኔ በላይ እናንተ እንደምታዉቁ እገምታለሁ ስለዚህ እናንተን የሚያዋጣችሁ ነጋ ጠባ በየቴሌቨዥኑ በየሬዲዮኑ በየኀኅትመት ዉጤቶች «ብሔር ብሔረሰቦች ነፍጠኞች ትምክህተኞች» እያላችሁ ጥላቻ መፍጠርና መከፋፈል እንጂ «የሰንደቅ ዓላማ ቀን የሕዳሴ ግድብ የአምስት ዓመቱ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ወዘተ» የሚሉት ለእኔ የጨለማዉ ገዥ የማይመቹኝና ሕዝቡ ወደ አንድነት የሚያሰባስብ የዘረኝነትና የጎጠኝነትን መሪያችሁን መንፈስ የሚፈታተን ስለሆነ በቀደመዉ የጨለማ መንፈሴ ብቻ መመራት እንዳለባችሁ አሳስባችኋለሁ እንዲሁም «አንድነት አገር ምንትስዬ» የምትሉትን የማስመሰል አባባላችሁን ብታቆሙ ለረጅም ዕድሜያችሁ የሚሻላችሁ እንደሆነ በጨለማዉ ስሜ አመክራችኋለሁ» ይላል እዉነትን ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳዉ የጨለማዉ ገዥ ዲያብሎስ ከግብር አበሮቹ ጋር በመሆን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ምዕራፍ « አናንተ «ጸሎተኛ ነን» አያላችሁ በዘልማድ ብቻ የምታነበንቡ ከመልካም ምግባር የተለያችሁ እንዲሁም «ቆራቢ ነን እያላችሁ በክፋት በተንኮል በምቀኝነት በትዕፅቢት በርኩሰት በጥላቻ በቂም በቀል በዘረኝነት በጎጠኝነት በዘፋኝነት በዳንኪርተኛነት በአምልኮ ምንዝርና በስካር ወዘተ በመሳሰሉት ሕይወት የምትኖሩ ሰዎች መቼስ በዚህ ሕይወታችሁ መንግሥተ ሰማያትን የምትወርሱ ከሆነ እኔም የጨለማዉ ገዥ ከመንግሥተ ሰማያት በላይ የሆነ ቦታ እንደሚዘጋጅልኝ ተስፋ አደርጋለሁ ምክንያቱም በዚህች ምድር ላይ እንዲህ የምታስመስል ዓመጸኛ ነፍስ ከሥጋዋ ስትለይ የምትገለጽበትን ረቂቅ አካል ምሳሌያዊ ባሕርይ ብቻ ትለብሳለች እንጂ በዚህ ምድር ላይ ያላት ባሕርይና ሕይወት አብሯት ስለሚሆን ከእኔ ዓመጻ በላይ ዓመጸኛ ሆና ይኸዉም በመስቀል ላይ የተከፈለላትን ታላቅ ዋጋ ከንቱ አድርጋ ይልቁንም በማስመሰል ሕይወት እያላገጠችና እየተሳለቀች ገነት መንግሥተ ሰማያት የምትገባ ከሆነ እግዚአብሔር በባሕርይዉ አድሎ ስለማያደርግና ፍትሐዊ ፍርድ ስለሚሰጥ እኔንና ሠራዊቶቼን ሰይጣናትን ያላስመሰልነዉና ያላላገጥነዉን አንዲሁም አንዳች ዋጋ ያልተከፈለልንን ዓመጸኞችን ወደመንግሥቱ ቅድሚያ ሰቶን ሰተት አድርጎ እንደሚያስገባን እናምናለን ታዲያ በእናንተ ሕይወት በደንብ አንድንጽናና ኃጢአታችሁን በላቀ መልኩ አጠናክራችሁ ቀጥሉበት እያልን በጨለማዉ ስማችን አንመክራችኋለን እናንተ «በምድር ዉስጥ በተዘረጋዉ የጨለማዉ መንግሥትና ሥርዓት የዲያብሎስ ነዉና አንመራበትም እኛ የምንመራዉና የምንመላለሰዉ በእግዚአብሔር መንግሥት ቤተ ሕዝቡ ቤተ ክህነቱ ቤተ ምልክናዉ በአንድላይ በመንፈስ ቅዱስ ብቻ በሚመራበት ሥርዓት ነዉ» የምትሉና በእኔ በጨለማዉ ገዥ በዲያብሎስ ላይ ዓመጻ በመፈጸም ያንተን ፈቃድ አንፈጽምም አናስፈጽምም» በማለት ላንተ አንገዛም አንታዘዝም ከፃዲ ዓመጸኛ ርኩስ ነህ» እያላችሁ የምታወግዙኝና እግዚአብሔር በሰጣችሁ መሳሪያ ሌት ተቀን የምታቃጥሉኝ የምታስሩኝ የምታበሳጨኝ የምታናድዱኝ ባጠቃላይ ፍዳዬን የምታሳዩኝ ሰዎች ሁሉ እኔን የማትከተሉና ፈቃዴን የማትፈጽሙ ከሆነ እንደበገናችሁ እንዳዘናችሁ ምድሬን ለቃችሁ ወደ ምትሄዱበት ትሄዳላችሁ እንጂ ለምርጥ ባለሟሎቼ የማድለዉን ሥልጣንና ብልጽግና በተለመደዉ በባዶ ቀፎ በሆነዉ አንደበቴ አልሰጣችሁም በእኔ ዘንድ ርኅራጌ ይሉኝታ የሚባል ነገር የለም ከአዳም ዘር የባስኩ ጨካኝ ነኝ ስለዚህ የመጨረሻ አንድ እድል እአሰጣችኃለሁ ምድራዊ የጨለመዉ መንግሥቴና ሥርዓት አክብራችሁ የምትኖሩ ከሆነ በምድሬ መኖር ትችላላችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንመሰርታለን የእሱን ፈቃድ ብቻ እየፈጸምን ሕዝቡንም እናስፈጽማለን የምትሉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ከሆነ ከዚህች ምድሬ ለቃችሁ ወደምትፄዱበት እንድትሄዱ በጥብቅ እነግራችኋለሁ የጨለማዉ ገዥ እናንተ ከምትመሩበት መንፈስ አንድነትና ኅብረት ስለሌለዉ በኅብረትና በአንድነት የምድሪቱን መንግሥቴን ለማገልገል እንደማይቻል ከእኔ ከጨለማዉ ገዥ በላይ እናንተ የምታዉቁ ይመስለኛልና በእኔ ዘንድ አንዳች ድርሻ የሌላችሁ መሆኑን በተለመደዉ ተራና ባዶ በሆነዉ ፉከራዬ እንድታዉቁ ለመግለጽ እወዳለሆ እናንተ «ለመንፈሳዊ አገልግሎት የተሰለፍን ነን» ብላችሁ የእኔን የጨለማዉ ገዥ ዉዶቼን ካድሬዎችን እናንተም አየመለመላችሁ አባልና ደጋፊ በማድረግ የምታሳምጹብኝ ሰዎች ወዮላችሁ። እግዚአብሔር በተለያየ ዘመናትና ዓመታት መልእክቱን በተለያዩ አገልጋዮቹ ቢያስተላልፍም «አንቀበልም አንፈጽምም እጃችንንም ለእግዚአብሔር አንሰጥም» በማለት የታበያችሁና ያመፃችሁ በመሆኑ ክብር ስላልወደደላችሁ በቁጣዉ እናንተ ሳታስተዉሉትና ሳትጠብቁት በተለያየ መንገድ ከምድር መጠረጋችሁና መጽዳታችሁ ስለማይቀር ነጻነታችሁ ተገድቦ ወደ ሲኦል እንደምትጋዙ ቢታወቅም የመጨረሻዉ የጨለማ ምክሬ ግን ተጠርጋችሁ እስከምትሄዱ ድረስ በዓመጻ በክህደት በርኩሰት ባጠቃላይ በኃጢአት ተግባራችሁና ንግግራችሁ እንዲሁም ሓሳባችሁ ጽኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እጅ በመስጠት ንስሐ እንዳትገቡ እንዲሁም በተመረጠችዉና በተቀደሰችዉ አገር ኢትዮጵያ ለሚመሰረተዉ የእግዚአብሔር መንግሥት ሆነ ለቅዱስ ኪዳኗ ፃኝይማኖት ለተዋሕዶ እጃችሁን እንዳትስጡ ምክንያቱም ሰላምፍቅር አእረፍት በረከት እርካታ የምታገኙት አግዚአብሔር ለሚመሰርተዉ መንግሥት እጃችሁን ከሰጣችሁና በኢትዮጵያ ተዋሕዶ ሃይማኖት አማካይነት ከእግዚአብሔር ልጅነትን ካገኛችሁ ብቻ ነዉና እናንተ ግን ምርጫችሁ ጦርነት ግድያ ስርቆት ክፋት ተንኮል ምቀኝነት ዘረኝነት ጎጠኝነት ትዕቢት ዓመጻ ክህደት ርኩሰት ግፍ ጭከና በደል አድሎ ምኑ ተነግሮ ያዉቃል የእኔን የጨለማዉ ገዥ ፈቃድ ስለሆነ ነዉ እናንተ የቀደሙት የጸሐፍት ፈሪሳዉያንና የአይሁድ ካህናት ሕይወት የያዛችሁና በአግዚአብሔር ስም የምትነግዱና የምታስመስሉ አገልጋዮችና ምእመን ነን » የምትሉ ዋናዉን የኃጢአት ስራ ከቁም ነገር ሳትቆጥሩ ወጋችሁንና ልማዳችሁን እንደ ሕግ የምትቆጥሩና ምእመኑ በእዉነትና በመንፈስ አምላኩን እንዳያመልክ እንቅፋትና ማሰናከያ የሆናችሁ ሰዎች የራሳችሁን የኃጢአት ስራ ያማትመለከቱና የሌላዉን እንደ ኃጢአት እንኳ የማይቆጠረዉን የምታራግቡና የምታብጠለጥሉ ባጠቃላይ በዘልማድ ሕይወት የምታገለግሉና የምትመላለሱ እንዲሁም ለእኔ ለጨለማዉ ገዥ እንደ ልቤ የሆናችሁ ወዳጆቼና አገልጋዮቼ በያዛችሁት አቋምና ሕይወት እንድትቀጥሉበት እመክራችኋለሁ መቼስ ለድርጊታችሁ ሆነ ለንግግራችሁ ምክንያትና መረጃ ማዘጋጀትና መፍጠር የማይሳናችሁ ብቃታችሁ ከእኔ አንዳንዴ የሚልቅ ነዉና ለእያንዳንዱ የማስመሰልና የባዶነት እንዲሁም የግብዝነት ተግባራችሁና ንግግራችሁ ተቀባይነት እንዲኖረዉ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ከቅዱሳትና ከአዋልድ መጻሕፍት እየጠቃቀሳችሁ ማሳመን አለባችሁ አእንጂ ትዉልዱ ከእናንተ የነቃና የመጠቀ ስለሆነ እንደ ቀድሞ በቁጣና በማስፈራራት ብትናገሩት አይሰማችሁም አያምናችሁም ስለዚህ ለምሳሌ ክርስቶስ ኦሪትና ነቢያትን ለመሻር አልመጣሁም ልፈጽም ነዉ እንጂ» ብሏልና ሙሴ ያወጣዉን የተለያዩ ፍርዶችና ሥርዓት ተግባራዊ አድርጉ ለምሳሌ የገደለ ይገደል የሰረቀ አጁ ይቆረጥ ዐይን ያወጣ ዐይኑ ይዉጣ ያመነዘረች ወይን ያመነዘረ ተወግራ ወይንም ተወግሮ ትገደል ወይንም ይገደል በሰንበት የዘረጋዉን እግር ያጠፈ የተፈወሰበትን አልጋ ተሸክሞ የሄደ በሽተኛን ይዞ የተንቀሳቀሰ ምግቡን አብስሎ የበላ መጠጡን አሙቆ የጠጣ ወዮለት ይኮነናል ወር አበባ የታያት ሴት ርኩስ ናት የወለደች ሴት ርኩስ ናት ወደ መቃበር የፄዱ ሰዎች ርኩሶች ናቸዉ ሚስቱ ወይንም ባሏ የደበረችዉ ወይንም የደበራት የሰለቸችዉ ወይንም የሰለቻት የፍቺ ወረቀት እተሰጣጡ ይፋቱ እንደገና ደግሞ የፈለጉትን ያግቡ ለዚህች አጭር ዘመናቸዉ ምን አጨናነቃቸዉ ባልታጠበ እጅ የሚበላ ሰዉ ርኩስ ነዉ ኃጢአትን ፈጽሟል ለታይታ ብቻ በየመንገዱና በየቦታዉ የማይጸልይና በእዉነትና በመንፈስ ብቻ የሚጸልይ ሰዉ ጸሎቱ በፈጣሪ አይሰማም የብሉይ ዘመን ሕግና ሥርዓት ይጠበቅ የእንሳሱት መስዋዕት ይፈጸም ወዘተ በማለት ባጠቃላይ በሙሴ ዘመን እንደነበሩት ሰዎች ሕይወት የአሁኑ የሐዲስ ዘመን ሰዎችም በዚያ ሕይወት ይመላለሱ በማለት የጨለማዉን የብሉይ ዘመን ሕይወት ተግባራዊ አድርጉ አስደርጉ ይህን በማድረጋችሁና በማስደረጋችሁ እንደ ጸሐፍት ፈሪሳዉያን አይሁድ ካህናትና አለቆች የተለየ የከበሬታ ወንበር ታገኛለችሁ ትመሰገናላችሁ ትከብራላችሁ ትገናላችሁ ታዲያ አንዳንድ ያልገባቸዉ ሰዎች በሐዲስ ዘመን ሁሉ በእዉነትና በመንፈስ ነዉ የሚፈጸመዉ የብሉይ ዘመን የአምልኮት ሥርዓትና የፍርድ አፈጻጻም የወጣዉ በወቅቱ ካለዉ ትዉልድ አስተሳሰብና ንቃተ ኅሊና እንዲሁም ደንዳናነትና ዓመፃ በመነሳት ነዉ እያንዳንዱ የብሉይ ዘመን ሥርዓትና ፍርድ ከዘመኑ አንጻር ምክንያት የነበረዉና በዘመኑ ለነበሩ ሰዎች የሚገባ ነዉ ሰዎች በራሳቸዉ ሥጋና ደም ስሜት የፈጠሩት ወግና ልማድ ግን እንደ እምነትና አምልኮ ሥርዓት የሚታይ አይደለም በሐዲስ ዘመን ራሱ ባለቤቱ እግዚአብሔር በሥጋ ተገልጾ ዐሥርቱን ትዕዛዛትን በማጽናት ሌሎች ሥርዓቶችና ፍርዶችን በከፊልና ሙሉ በሙሉ ያሻሻለዉና የለወጠዉ አንዲሁም ሰዎች ስለ ወጋቸዉና ልማዳቸዉ የአግዚአብሔርን ሕግና ሥርዓት እያሻሩ ስለነበረ ገስቧቸዋል እንጂ ወግና ልማዳቸዉ አንደ ሕግና ሥርዓት እንዲታይ አላደረገም ስለሆነ በክርስቲያናዊ ሥርዓትና ልማድ ሕይወት ነዉ የምንመላለሰዉ እንጂ በጨለማዉ ሕይወትና ልማድ አንመላለስም ኢየሱስ ክርስቶስ የባርነት ቀንበራችንን ሰብሮልናልሸክማችንን አቃሎልናል ለሕያዉነት ሕይወት የሚሆነን መብልና መጠጥ ራሱ ተሰዎቶልን ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን ሰቶናልዕለት ዕለት ሕይወታችንን «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በንስሐ እየመረመርን እንበለዋለን አንጠጣዋለን አንድነታችንን ከአርሱ ጋር አንፈጥራለን በተለያየ መንገድ ተተብትበን የነበረዉን እስራት ፈቶልናልና በግብዝነትና በባዶ ቀፎ ሕይወት አንመላለስም አግዚአብሔር ሰንበትን አንድናርና ያዘዘዉ የተለየ ጥቅም ሊያገኝበት ፈልጎ ሳይሆን እኛ የአዳም ዘሮች ነፍሳችን ዕረፍት አንድታገኝበትና ለሰማያዊ ሕይወት የሚረዳትን ሰማያዊ መብልና መጠጥ እንድትበላበት እንድትጠጣበት ፈልጎ ለእኛዉ ፍጥረቶቹና ልጆቹ አዝኖልን ነዉ ጋብቻንም በተመለከተ አንድ ወንድ ለአንድ ሴት ብቻ ያጸናልንና ማንም ይሁን ማን በክሳት በሕመም በችግር በጉስቁልና ባጠቃላይ በምድር ላይ በተለያየ ምክንያት ሊከሰት በሚችል ክስተት ምክንያት ማንም ሰዉ ሚስቱን ሆነ ባሉን መፍታት እንደማይችልና ካደረገ ደግሞ በእግዚአብሔር ሕግ ላይ ዓመጻ እንደ ፈጸመ እንደሚቆጠርበት በግልጽ አስተምሮናል ባጠቃላይ እስከ ዕለተ ሞታችን ድረስ አግዚአብሔርን በስራችን በንግግራችን በሓሳባችን ጭምር እርሱን በመፍራትና አሱ ደስ በሚሰኝበት ሕይወት ብቻ እንመላለሳለን እንኖራለን ወዘተ » በማለት የሚናገሩትንና የሚያስተምሩትን አንዳች እንዳትሰሙ እነሱ ነፍሳቸዉ በሚመቻት ሥርዓትና ሕይወት ለመመላለስ የሚፈልጉ ናቸዉ እንጂ ለሥጋቸዉ አንዳች አያስቡለትም መመስገንና መግነን አንዲሁም መመለክን የማይፈልጉ እግዚአብሔርንና ምእመኑን በቅንነትና በእዉነት ለማገልገል የሚፈልጉ ተስፋቸዉን ሰማያዊ አድርገዉ የሚኖሩ ስለ እዉነት ራሳችዉን ክደዉ የሚመሰክሩና በእዉነት የሚኖሩ ስለሆነ ለእናንተ ሕይወትና አገልግሎት ስለማይመቹ ከእነሱ ጋር አንዳች ኅብረትና አንድነት እንዳትፈጥሩ በጨለማዉ ስሜ አደራ እላችኃለሁ አንዲሁም አንዳንድ አገልጋዮችና ምእመናን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ሆዳቸዉ አምላካችዉ የሆነና ከንቱ ሥጋዊ መጠበብ አድርገዉ በተለያዩ አዋልድ መጻሕፍትና የእዉቀት መጻሕፍት ወስጥ የሥጋና ደም ሓሳቸዉና ፍላጎታቸዉን በማስገባት ምእመኑ ለእግዚአብሔር ትዕዛዝና ሕግ ቦታ እንዳይሰጥ መለኮት ከተዋሓደዉ ከቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ እንዲርቅ በእዉነትና በመንፈስ እንዳያመልክ መልካም ምግባር ሳይኖረዉና ስለ ኃጢአቱ እዉነተኛ ንስሐ ሳይገባ በዘልማድና በማስመሰል ሕይወት እንዲመላለስ የሚያስተምሩትን ትምህርት ተቀበሉ አንደ ሥጋ ፈቃዳችሁ ብትመላለሱም ራሳችሁን ለንስሐ ባታበቁም ወደ ሥጋዉና ደሙ ባትቀርቡም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምትገቡበት የተለያዩ ሰፋፊ መንገዶች አሉና ነፍሳችሁን አንዳች አታስጨንቁ «አንኮነናለን» ብላችሁ አንዳች ስጋት አይግባችሁ እንኳን እናንተ ልትኮነኑ ቀርተ በሲኦል ያሉትን ነፍሳት ከፈለጋችሁ ዘመዶቻችሁን ከፈለጋችሁ ጓደኞቻችሁን ከፈለጋችሁ የማታዉቁትን ሰዉ ጭመር እዚሁ ምድር ላይ እያላችሁ ወደ ገነት ሰተት ብለዉ እንዲገቡ ማድረግ ትችላላችሁ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ስለዚህ በምድራዊ ሕይወታችሁ ዘመን ዘና ብላችሁ ስትፈልጉ ትዕዛዙን መጠበቅ ስትፈልጉ ትዕዛዝን በመሻር የሥጋ ፍላጎታችሁንና ስሜታችሁን በማርካት ልትኖሩ ትችላላችሁ ለዚህም እኔ የጨለማዉ ገዥ ሙሉ ዋስትና እሰጣችኃለሁ ታዲያ አንዳንድ የእኔን የጨለማዉ ገዥ ድንቅ ስራ ያልገባቸዉ ሰዎች «ማንም ይሁን ማን ከሥላሴ በጥምቀት ልጅነትን ካላገኝ ሕይወት የሚሆነዉን መለኮት የተዋሓደዉን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደሙን ካልበላና ካልጠጣ በምድራዊ ዘመኑም መልካም ስራ ካልሰራ እንዲሁም በኃጢአት ሲወድቅ እዉነተኛ ንስሐ ካልገባና ኃጢአቱ ከሰማያዊ መዝገብ ላይ እንዲደመሰስለት ቅዱሰ ቁርባን ካልተቀበለ በስተቀር በዘልማድና በማስመሰል እንዲሁም በዓመፃና በክህደት በርኩሰት ሕይወት እያለ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም በማለት የሚያስተምሩትን ሰዎች አንዳች እንዳትሰሙ አነሱ ከምትደሰቱበትና ከምትዝናነኑበት የኃጢአት ሕይወት ሙሉ በሙሉ ሊለያችሁና ከእኔ አራርቀዉና አጣልተዉ ለእግዚአብሔር ብቻ እንድትገዙ ለማድረግ ቆርጠዉ የተነሱ የእኔ የጨለማዉ ገዥ ተቃዋሚና ጠላቶች ናቸዉ አኔ አዝጌላችሁ በዚህ ምድር አንደፈለጋችሁት ሆናችሁ ወደ አግዚአብሔር መንግሥት ለማስገባት ከፍተኛ ትግል እያደረኩ እነሱ ግን ከእኔ ተቃራኒ በመቆም ሥጋችሁን ሊጎዱና ነፍሳችሁን ብቻ ሊጠቅሙ ይሯራራጣሉ ስለዚህ እንናተ መምረጥ ያለባችሁ ኃጢአት እየፈጸማችሁ እንዲሁም በዓመፃና በክህደት ሕይወት አየተመላለሳችሁ በቀላሉ ጻድቃን የገቡበት ገነትና መንግሥተ ሰማያት ዉስጥ ለመግባት የሚያስችላችሁን መንገድ እንጂ ሥጋችሁ የሚጎዳበትና ነፍሳችሁ ብቻዋን የምትጠቀምበትን መንገድ በምንም መልኩ እንዳትመርጡ በጨለማዉ ስሜ እመክራችኋለሆ እናንተ ቆብ በመድፋታችሁ ብቻ አግዚአብሔርና ምእመኑ በእዉነት የሚገለገሉበትን ወንበር ተቆጣጥራችሁ «አዉነተኛና ብቸኛ የሕይወት መንገድ» ተብላ የተመሰከረላትን የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ሃይማኖትን ለዘመናት ሳትበረዝና ሳትደለዝ ተጠብቃ ለአሁን ትዉልድ እንድትደርስ ያደረጉትን መምህራንና ሊቃዉንትን አግልላችሁና አርቃችሁ ሥልጣኑን በመቆጣጥር የሥጋ ፈቃዳችሁን የምትፈጽሙና የምታስፈጽሙ ምእመኑንም ለተኩላና ለወንበዴ አሳልፋችሁ የሰጣችሁ « አዉነተኛ አረኞች እኛ ብቻ ነን» በማለት ምአመትኑን ለዓመፃና ለክህደት ሕይወት የዳረጋችሁ ለሥጋዊ ጥቅም ለክብር ለዝናና ለግላችሁ ሥጋዊ ብልጽግና ታላቅ ተጋድሎ የምታደርጉ በተለያየ የቅድስናና የመልአክ ስም የምትጠሩ ልዩ አገልጋዮቼ። እያለች ታስባለች ታወጣለች ታወርዳለች በዚህም ምክንያት ካለ ዕረፍት ትጨነቃላችእንደ ምድራዊ ዘመኗ እንኳ በማንቀላፋት አታርፍም «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በተቃራኒዉ ደግሞ ስለ ኃጢአታቸዉ እዉነተኛ ንስሐ የገቡና ስለ ኃጢአታቸዉ የተጸጸቱ ሰዎች መለኮት የተዋሓደዉን የክርስቶስን ሥጋና ደም ሲቀበሉ በተግባርም በንግግርም በሓሳብም የፈጸሙት ኃጢአት ሁሉ ከአግዚአብሔር ባሕርይ መዝገብ ላይ ሙሉ በሙሉ ይደመሰሳል በምድር ያልረሱትም ኃጢአት ሆነ የረሱት ኃጢአት ልክ ሕጻን ልጅ በልጅነቱ የሰራዉን ድርጊት ንግግር ያሰበዉን ሓሳብ እንደማያስታዉስ ሁሉ ነፍሳቸዉ ከሥጋቸዉ ስትለይ አንዳች አያስታዉሱትም ያለፉበት የመከራና የፈታና ሕይወት አይታወሳቸዉም ነገር ግን መከራና ስቃይ ከነበረበት ዓለም መምጣታቸዉን ልብ ይላሉ በንስሐ መታደሳቸዉን ያስተዉላሉ ኑሮዋቸዉም ቀደም ካሉ ጻድቃን ጋር በንጹህ ኅሊና በመሆን ይቀላቀላሉ አምላካቸዉንም በእዉነትና በመንፈስ ብቻ ያመልካሉ በመጨረሻዉ ፍርድ ቀንም በማረፊያ ቦታ የሚካሄደዉን የመጨረሻ ፍርድ እንደ ቅዱሳን መላእክት ተመልክተዉ በቀጥታ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ በሰማያዉያን መላአክት አኗኗር በረቂቅ አካላቸዉ ሕያዉ ሆነዉ ይኖራሉ እንኳን የምድሩን የስቃይ ኑሮ ቀርቶ የገነቱን አኗኗር ረስተዉ በአዲስ ልዩ ብቃት በተሞላዉ ሕይወት በቅድስናና በደስታ ሕይወት ብቻ ይኖራሉ በዚህ ምድር ዉስጥ እምነትና ምግባራቸዉ ያልታየና ያልጠሩና ያልነጠሩ የሕጻናት ነፍስ እንዲሁም በነጻ ኅሊናቸዉ ብቻ ተመርተዉ በቅን ሓሳብ በመልካም ተግባር ሕይወታቸዉን ያሳለፉ ነገር ግን በእዉነተኛዉ አምልኮ ዉስጥ ያልተመላለሱ ወይንም ከሰብአዊነት አንጻር ብቻ በቅን ሓሳብና በመልካም ሕይወት የተመለለሱ ሰዎች ነፍስ ከሥጋቸዉ ስትለይ በቀጥታ ከዓለም ዉጭ ከሲኦል አጠገብ ወዳለችሁ ወደ ማረፊያ ቦታ ነዉ የሚገቡት በዚያ በሚኖራቸዉ ዉስጣዊ የአምነት ብቃት ደረጃ በፍርድ ቀን ተፈርዶላቸዉ ወደ መንግሥተሰማያት የመግባት እድል አላቸዉ በነጻ ኅሊናቸዉ ተመርተዉ የሚፈለገዉ የእምነት ብቃት ደረጃ ላይ ያልደረሱ ነፍሳት ደግሞ በሲኦል ካሉት ጋር ወደ ገፃነመ አሳት ዉስጥ ይጣላሉ በዚያም አንደ ዓመጻና ክህደት ደረጃቸዉ ይቀጣሉ በመጨረሻዉ የዓለም ፍጻሜ ዘመን የሚኖሩት ጻድቃን ሰዎች ደግሞ በምሕረት ሞት በቀጥታ ወደ ማረፊያ ቦታ ይጠራሉ ኃጢአተኞችና ዓመጸኛ ከሃዲዎች ሰዎች በመቅሰፍት ሞት ወደ ማረፊያ ቦታ ይመጣሉ ጻድቃን በገነት ከነበሩት ጋር በአንድላይ ወደ መንግሥተ ሰማያት ሲገቡ ኃጥአን ደግሞ «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር ለዘመናት በምድር ዉስጥ በዓመጻና በክህደት ሕይወት ከኖሩት ሰይጣናትና ከአለቃቸዉ ዲያብሎስ ጋር ወደ ገዛነመ አሳት ዉስጥ ይጣላሉ በዚያም ያለዉ ቅጣታቸዉ በምድር ቆይታቸዉ እንደፈጸሙት የኃጢአት ደረጃ ቅጣታቸዉ የሚለያይ ሲሆን አጅግ የከፋ ኃጢአት የፈጸሙ እጀግ ሊቋቋሙት የማይችሉት ስቃይ ይጠብቃቸዋል አነስ ያለ ኃጢአት የፈጸሙ በዚያዉ ልክ ቅጣቱ ይቀልልላቸዋል ልክ ሰዎች በተመሳሳይ ሥጋ አካል የተገለጹ ቢሆንም ደገኛዉ ሰዉ ወደ በረፃ እንዲኖር ቢደረግ በረፃ ከሚኖረዉ ሰዉ ይልቅ የሙቀቱና የቃጠሎዉ ስቃይ እንደሚበረታበትና መቋቋም አንደሚያቅተዉ ሁሉ ለሁሉም ዓመጸኞች የመቀጫዉ ቦታ ገሃነመ አሳት ቢሆንም ሰይጣናት ሆኑ ሰዎች የሚቀጡበት ደረጃ አንደ ምድራዊ ዓመጻና ክህደት ሕይወታቸዉ ይለያያል እንኳን በገዛፃነመ እሳት አይደለም በመንግሥተ ሰማያት የሚገቡት የጸደቁ ነፍሳት በተመሳሳይ ረቂቅ አካል ቢገለጹጽም የሚያገኙት ደስታና እርካታ እንዲሁም ክብር እንደምድራዊ የቅድስና ብቃታቸዉ ይለያያል ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ለመሆን የበቃችሁ እመ አምላክ ድንግል ማርያም ከቅዱሳን መላእክት ሆነ ከጸደቁ ሰዎችሰፍሳት በተለየ መልኩ በምሳሌያዊ ባሕርይ በረቂቅ አካል ሳይሆን የምትገለጸዉ እንደ ልጂና አምላኳ በብርፃናዊ ባሕርይ ነዉ ተገልጻ በንግሥትነት ከአማነዊዉ ንጉሠ ነገሥት ከጌታችን ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በሰማያት ዉስጥ የምትኖረዉ አዚህ ምድር ጸጋዉ የተሰጠዉ ሰዉ ልክ የሩቆቹን ከዋክብት በሥጋዊ ዐይን አዚህ ሆና ማየት አንደሚቻል ሁሉ ነፍሳችንም እዚሁ ሆና ከምድር ጎን ያለችዉን ገነት ከዓለም ዉጭ ያሉትን ሲኦልና ማረፊያ ቦታ እንዲሁም አልፍ አአላፋት ወትአልፊት የሆኑት ቅዱሳን መላእክት የሚኖሩበትን ሰማያትን መመልከት ይችላሉ ከተፈቀደላቸዉ ደግሞ በዚያ የሚከናወነዉን ሥርዓትና ሕይወት መመልከት ይትላሉ በፍርድ ቀን በምድር ዉስጥ ያሉ በእምነታቸዉና በምግባራቸዉ የጸኑት ሰዎችበአሁን ሰዓት ማንም ሰዉ በሥጋዊ ዐይኑ ፀሐይን መመልከት እንደማይችል በዚያን ዘመን ግን አርሱ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ዉስጥ ከእልፍ አእላፋት ቅዱሳን መላእክት ጋር ሆኖ ሲመጣ ከዓለም ዉጭ ከሲኦል ከፍ ብላ ከሰማያት ዝቅ ብላ ያለችዉን ማረፊያ ቦታ ከዚህ ዓለም ጋር በምትነካካበት አቅጣጭ በግልጽ እንደ ፀሐይ እየታያቻቸዉ በምሕረት ሞት «የጨለማዉ ገዥ ተግባርና ንግግር በቀጥታ ነፍሳቸዉ በረቂቅ አካል በምሳሌያዊ ባሕርይ ተገልጻ ወደዛ ቦታ ይነጠቃሉ በተቃራኒዉ ደግሞ ዓመጸኛ ሰዎች ሆኑ ርኩሳን መናፍስት ሰይጣናት በመቅሰፍት ቅጣት ከዚህ ምድር ተለይተዉ ከማረፊያ ቦታ ዝቅ ተደርጎ ከሲኦል አጠገብ የሚዘጋጀዉ እሳቱ የማይጠፋበትን ትሉ የማያንቀላፋበትን ገፃነመ እሳትን እየተመለከቱ ነዉ ወደ ማረፊያ ቦታ ተጠርተዉ በቀጥታ የመጨረሻዉን ፍርድ ተቀብለዉ ወደ ገፃነመ አሳት ዉስጥ የሚጣሉት በማለት ተረተ ተረት የሚናገሩትን ሰዎች አንዳች እንዳትሰሙ ይልቁኑ «እኛ እግዚአብሔርንም አናዉቅም የሰይጣንንም ህልዉና አናምንም ተፈጥሮ ናት ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣችንና ያስገኘችንሞተን በስብሰንየምንቀር ነን ዝርያዎቻችንም ጦጣዎች ናቸዉ በቀስ በቀስ እድገትና ለዉጥ በኢሾኮልሽን አማካይነት ነዉ ተለዉጠንና የክሮማግነንና የኒያንደርታን ሰዉነት ዕድገት ደረጃ አልፈን አሁን ላለንበት ሰብእና የበቃነዉ» በማለት አሳፍሯቸዉ የእኔን የጨለማዉ ገዥ ህልዉና ካዳችሁ ብዬ አንዳች ቂም አልይዝባችሁም በቁስአካላዊ አስተሳሰባችሁ እስከመጨረሻዉ ጽኑ እነዚህ ሐሳብያዉያን «ከቁስ አካል በፊት መንፈስ አለሁሉ የተፈጠረዉ በመንፈስ ኃይል ነዉ ሁሉ በእርሱ ቁጥጥር ዉስጥ ነዉ በማለት አዋቂነታችሁንና ምሁርነታችሁን ዝቅ ሊያደርጉ ነዉና ትግላቸዉ እናንተ በቅሬተ አፅም ጥናታችሁ በሚሊዮንና በቢሊዮን የሚቆጠር አድሜ አየሰጣችሁ ትዉልዱን በእግዚአብሔር ላይ ያለዉን አምነት እንዲጠራጠርና እንዲክድ እንድታደርጉ የጨለማዉ ምክሬን አለግሳችኋለሁ በዚህ ዉለታችሁም አናንተ ባታምኑኝም ቸርነትን አድርጌ አኔ የምወርሰዉን መንግሥት አወርሳችኃኋለሁ ይላል የጨለማዉ ገዥ ትዉልዱን በተለያየ የክህደት ትምህርትና ትዕይንት አደንዝዞ ወደ ሞትና መቀመቅ በመዉስድ ላይ ያለዉ ዲያብሎስ ከሠራዊቱ ሰይጣናት ጋር በመሆን።