Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
አንደም የዘዘሮጭዝብ ሹም ፊት በመቅረብ አባት መሆኑን በመግለፅ ልጅነትን ለመቀበል ይችላል ጐዮር አንቀጽ ስለውክልና አካለ መጠን ያልደረሰው ልጅ ጥቅም የማይጓደልበትን አሠራር ብቻ መከተል እንጂ የቀረቡለትን ሀሳቦች የመቀበል ግዴታ አይኖርበትም አንቀጽ ሥራው ያለ ክፍያ የሚከናወን ስለመሆኑ የአሳዳሪነትና የሞግዚትነት ሥራ የሚከናወነው ማናቸ ውም ዋጋ ሳይከፈልበት በነፃ ነው ሆኖም አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ በፈፀመው የሥራ አካፄድ ጉድለት ብቻ ነው።
ምዕራፍ ስድስት በጋብቻ ውስጥ የሚነሠሁ ክርክሮችን ስለመወሰን ቻ ለመኖሩ ስለሚቀርብ ክርክር አንቀጽ የሚፀና ጋብቻ ስለመኖሩ ጋብቻ በዚህ ሕግ ምዕራፍ እና በተደነገገው መሠረት ጋብቻ ለመፈፀሙ ወይም የሚዐና ጋብቻ ስለመኖሩ ክርክር የተነሣ እንደሆነ ጉዳዩን አጣርቶ ውሣኔ እንዲሰጥ ተጋቢዎች ጥያቄያቸውን ለፍርድ ቤት ሊያቀርቡ ይችላሉ አንቀጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ጋብቻ ለመፈፀሙ ወይም የሚዐና ጋብቻ ስለመኖሩ የሚነሣውን ክርክር አይቶ ለመወሰን ሥልጣን የሚኖረው ፍርድ ቤት ብቻ ነው ፍርድ ቤቱም በአንቀጽ መሠረት የሚቀርብለትን ጥያቄ በዚህ ህግ አንቀጽ መሠረት በሚቀርቡለት ማስ ረጃዎች እያጣራ አስፈላጊውን ውሣኔ ይሰጣል የዚህ አንቀጽ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ በፍቺ ክርክር ውስጥ ሊነ ለሚችሉ የጋብቻ መፈፀም ወይም የሚፀና ጋብቻ መኖር ጥያቄዎችም እንደየአግባቡ ተፈፃ ሚነት ይኖረዋል አንቀጽ ብቻ ለመፈፀሙ ስለሚቀርብ ማስረጃ የጋብ ያምስክር ወረቀት ጋብቻ መፈፀሙን ለማስረዳት የሚቻለው ጋብቻው በተፈፀመበት ፅለት ወይም ከዚያ በኋላ በሕጉ መሠረት ተዘጋጅቶ የተሰጠውን የጋብቻ የምስክር ወረቀት ወይም የጋብቻውን መዝገብ የተረጋገጠ ግልባጭ በማቅረብ ነው አንቀጽ የጋብቻ ምስክር ወረቀት በሌለ ጊዜ ስለሚቀርብ ማስረጃ የጋብቻ ምዝገባ ሳይደረግ የቀረ ወይም መዝገቡ በመ ጥፋቱ ምክንያት ጋብቻ መፈፀሙን በጋብቻ ምስክር ወረቀት ለማስረዳት ያልተቻለ እንደሆነ ጋብቻ ለመፈፀሙ አሳማኝና በቂ ማስረጃ በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት አንድ ሰው በራሱና ከእርሱ ጋር ጋብቻ አለኝ የሚለው ወገን ጋር ጋብቻ መፈጸሙን ማስረዳት የቻለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ጋብቻ ተፈጽሟል ሲል የሕግ ግምት ይወስዳል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተውን ግምት ጋብቻው አለመፈፀሙን ማናቸውንም ዓይነት አስተ ማማኝ ማስረጃ በማቅረብ ለማፍረስ ይቻላል ክፍል ከፍቺ በመለስ ን ስለመወሰን አንቀጽ በጋብቻ ውስጥ ስለሚፈጠሩ አለመግባባቶች በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከተው እንደተጠበቀ ሆኖ ባል ወይም ሚስት ወይም ሁለቱም በአንድነት ከፍቺ በመለስ የሆኑ በጋብቻ ውስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን አስመልክተው አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤት ሊያቀርቡ ይችላሉ አንቀጽ የፍርድ ቤቱ ሥልጣን ፍርድ ቤቱ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ጥያቂ ሲቀርብለት ባልና ሚስቱን በተናጠልም ሆነ በአንድነት በማነጋገር አለመግባባቱን በስምምነት መፍታት የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንዲችሉ ያግባባቸዋል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሠረት ሞክሮ ውጤት ያላገኘ እንደሆነ ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ውጤት የማያገኝ መስሎ የታየው እንደሆነ ባልና ሚስቱ ከፍርድ ቤት ውጭ ራሳቸው በሚመርጧቸው ሽማግሌዎች አማካይነት በስምምነት እንዲጨርሱ ከሁለት ወር ያልበለጠ ጊዜ በመወሰን ያሰናብታቸዋል በሽማግሌዎቹ በሚቀርብ የማስማሚያ ፃሳብ ያልተስማማ ወገን አቤቱታውን ለፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል ፈ ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን አቤቱታ መርምሮ በሽማግሌዎቹ የተሰጠውን የማስማሚያ ፃሳብ ሊያዐና ሊያሻሸል ወይም ሊሽር ይችላል የሚሰጠውም ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል ምዕራፍ ሰባት የጋብቻ መፍረስና የሚያስከትለው ውጤት ክፍል ጠቅላላ አንቀጽ በማናቸውም ዓይነት የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓት የተቋቋሙ ጋብቻዎች አኩል ስለመሆናቸው ጋብቻው የተፈጸመበት ሥርዓት ማናቸውም ዓይነት ቢሆን የጋብቻው መፍረስና የሚያስከትለው ውጤት በተመለከተ ምንም ዓይነት ልዩነት አይደረግበትም ስንቀጽ ጋብቻ ስለ ስባቸው ቶች ጋብቻ ቦሚፈርሰው በሚአተፅተ ምክንያቶቸ ነው ሀ ከተጋቢዎቹ አንዱ ሲሞት ወይም በፍርድ ቤት የመዊፈፉት ውሳኔ ሲሰጥ ወይም ለሌ ጋብቻ ለመፈፀም መሟላት ካለባቸው ሁኔታዎች አንዱ በመጣሱ ምክንያት በሕግ መሠረት ጋብቻው እንዲፈርስ ሲወሰን ወይም ሒየፍቺ ውሳኔ ሲሰጥ አንቀጽ ስለፍቺና ስለ ፍቺ ውጤቶች የመወሰን ስልጣን የፍቺ ስምምነትን የማጽደቅ ወይም ፍቺን የመወሰን ወይም በዚህ ሕግ አንቀጽ በተደነገገው መሠረት የፍቺ ውጤቶችን በተመለከተ ውሳኔ የመስጠት ወይም የማጽደቅ ሥልጣን የፍርድ ቤት ብቻ ነው ክፍል በስምምነት ስለመፋታት አንቀጽ ፍቺ በስምምነት ስለሚወሰንበት ሁኔታ ጋብቻ በስምምነት እንዲፈርስ ሲወሰን የሚችለውባልና ሚስት በስምምነት ለመፋታት ሲወስኑና ይህንኑ ለፍርድ ቤት አቅርበው ውሳኔያቸው ተቀባይነት ሲያገኝ ነው አንቀጽ በስምምነት ለመፋታት ስለሚቀርብ ጥያቄ ባልና ሚስት በስምምነት ለመፋታት የወሰኑ እንደሆነ የፍቺ ስምምነታቸውንና ፍቺው የሚያስከትለውን ውጤት በጽሑፍ ለፍርድቤት በማቅረብ ፍቺው እንዲፀድቅላቸው መጠየቅ ይችላሉ በቪህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ቢኖርም ተጋብተው ስድስት ወር ያልሞላቸው ባልና ሚስት በስምምነት ለመፋታት አይፈቀድላቸውም ለመፍታት የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንዲችሉ ያግባባቸዋል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሠረት ሞክሮ ውጤት ያላገኘ እንደሆነ ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ውጤት የማያገኝ መስሎ የታየው እንደሆነ ባልና ሚስቱ ከፍርድ ቤት ውጭ ራሳቸው በሚመርጧቸው ሽማግሌዎች አማካይነት ጉዳያቸውን በፅርቅ እንዲጨርሱ ይጠይቃቸዋል ባለና ሚስቱ ጉዳያቸውን በሽማግሌ አማካይነት በዕርቅ ለመጨረስ ያልተስማሙ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ከሦስት ወር ያልበለጠ የማሰላሰያ ጊዜ በመወሰን ሊያሰናብታቸው ይችላል የፍቺ አቤቱታው እንደቀረበ ፍርድ ቤቱ ወዲያውኑ ባልና ሚስቱ ስለሚተዳደሩበትና ስለሚኖሩበት ሁኔታ ስለል ጆቻቸው አጠባበቅ ስለሚኖሩበት ስፍራና ስለአናኗራቸው እንዲሁም ስለንብረታቸው አስተዳደር ተገቢ መስሎ የታየውን ትዕዛዝ ይሰጣል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፊ በተመለከተው መሠረት ትዕዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ ከሁለቱ ተጋቢዎች የአንዳቸው ከጋራ መኖሪያቸው መውጣት የግድ ሆኖ የተገኘ እንደሆነ የጋራ መኖሪያቸውን ለቆ ቢወጣ የባሰ ጉዳት የሚደርስበት ወገን የትኛው መሆኑን እንዲሁም የልጆቻቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ አመቺ የሚሆነውን ሁኔታ ሁሉ ከግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል አንቀጽ ስለዕርቅ አስታራቂ ሽማግሌዎችን ስለመምረጥ በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ባልና ሚስት ጉዳያቸውን በዕርቅ ለመጨረስ በወሰኑ ጊዜ አመቺ ሆኖ በሚያገኙት መንገድ አንድ ወይም ቁጥራቸው ከአንድ በላይ የሆኑ ሽማግሌዎችን በመምረጥ ሽማግሌ እንዲ መርጡ ከተነገራቸው ቀን አንስቶ በ ቀናት ውስጥ የሽማግሌዎቹን ስም ዝርዝር ለፍርድ ቤቱ ማሳወቅ ይኖርባቸዋል ሂካ ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በበ መሠረት የሽማግሌዎች ስም ዝርዝር ስቀርብለት ወይም ሽማግሌዎቹ እንደቀረቡ ወዲያውኑ መዝግቦ ዕርቅ የሚከናወንበትን የመፍትሔ አቅጣጫ የሚጠቁም ምክርና መመሪያ በመስጠት ወይም እንዲደርሳቸው በማድረግ የዕርቁ ወይም የፅርቁ ሙከራ ውጤት በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ እንዲቀርብለት ያዛል የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ቢኖርም ፍርድ ቤቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የዕርቁ ሂደት የደረሰበትን ደረጃ በየጊዜው ለመመርመርና ወቅታዊ ሪፖርት እንዲቀርብለት ማዘዝ ይችላል አንቀጽ ስለተጨማሪ ጊዜ ከፅርቅ ሙከራው ሂደት አኳያ ባልና ሚስት ያለመግባባታቸውን በዕርቅ ሊጨርሱ ይችላሉ የሚል ግምት ያለው እንደሆነፍርድ ቤቱ በዚህ ሕግ አንቀጽ በተመለከተው ጊዜ ሳይገደብ ከአንድ ወር ያልበለጠ ተጨማሪ ጊዜ በመስጠት የፅርቅ ሙከራው እንዲቀጥል ሊያዝ ይችላል አንቀጽ የአስታራቂ ሽማግሌዎች ኃላፊነት አስታራቂ ሽማግሌዎች ባልና ሚስቱ የመፋታት ፃላባቸውን እንዲተውና ጉዳያቸውን በመግባባት እንዲጨርሱ ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ አለባቸው አስታራቂ ሽማግሌዎቹ ጉዳዩ ከፍቺ በመለስ ሊፈታ አንደማይችል የተረዱ እንደሆነ ተጨማሪ ጊዜ ሳያስፈልጋቸው ስለደረሱበት ውጤት ለፍርድ ቤቱ ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው አስታራቂ ሽማግሌዎች ጉዳዩን ከፍቺ በመለስ በማግባባት ለመፍታት ከመጣር አልፈው ባልና ሚስቱን የሚመለከት ማናቸውንም ትዕዛዝም ሆነ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን አይኖራቸውም አንቀጽ ብ የሪፖርት አለመቅረብ በዚህ ሕግ አንቀጽ እና መሠረት አስታራቂዎቹ ሪፖርት ሳያቀርቡ የቀሩ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን ይዘጋዋል መዝገቡ በተዘጋ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ባልና ሚስቱ ወይም ከሁለቱ አንዳቸው ጉዳያቸውን በዕርቅ አለመጨረሳቸውንና ሪፖርት በወቅቱ ያልቀረበበትን ምክንያት በመግለጽ ጉዳያቸው እንዲንቀሳቀስላቸው የጠየቁ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ጥያቄያቸው ተገቢ ሆኖ ካገኘው መዝገቡን በመክፈት በሕጉ መሠረት የራሱን ውሳኔ ይሰጣል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት የሚሰጠው መዝገቡን የመዝጋት ውሳኔ ባልና ሚስቱ ወይም ከሁለቱ አንዳቸው አዲስ አቤቱታ በማቅረብ ጉዳያቸው እንዲታይላቸው ከመጠየቅ የሚያግዳቸው አይሆንም አንቀጽ ፍቺና የፍቺ ውጤቶችን ስለመወሰን ከዚህ በላይ በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት ተገቢውን ሁሉ አድርጐ ጥረቱ ውጤት ያላስገኘ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የአስታራቂ ሽማግሌዎች ሪፖርት ከደረሰው ወይም እንደሁኔታው ለተጋቢዎቹ የተወሰነው የማሰላሰያ ጊዜ ከአበቃበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የፍቺ ውሳኔ ይሰጣል በዚህ ክፍል መሠረት ጋብቻው በፍቺ የፈረሰ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ፍቺው ስለሚያስከትለው ውጤት እንዲስማሙ ባልና ሚስቱን ይጠይቃቸዋል ባለና ሚስቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረትለመስማማት ያልፈለጉ ወይም ለመስማማት ሞክረው ስምምነት ላይ ለመድረስ ያልቻሉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በራሱ ወይም በሽማግሌዎች ወይም ፍርድ ቤቱ በሚሾማቸው ባለሞያዎች አማካይነት ወይም አመቺ መስሎ በሚታየው በማናቸውም ዘዴ የፍቺውን ውጤት ይወስናል ፈ ፍርድ ቤቱ የፍቺውን ውጤት በሚወሰንበት ጊዜ ከተጋቢዎች ያንደኛው ጥፋት የሆነ ከባድ ምክንያት መኖሩን ወይም ያለመኖሩን ከግምት በማስገባት ይሆናል የፍቺ ውጤት በስምምነት በሚያልቅበት ወይም በሸማግሌዎች ወይም በባለሞያዎች በሚወሰንበት ጊዜ ውሳኔው ተፈፃሚነት የሚኖረው ለፍርድ ቤቱ ቀርቦ ተቀባይነት ሲያገኝ ብቻ ነው ፍርድ ቤቱ ፍቺውን አስቀድሞ በመወሰን የፍቺውን ውጤት በተመለከተ የሚሰጠውን ውሳኔ እንደሁኔታው ከፍቺ በኋላ ከ ወር ላልበለጠ ጊዜ ሊያዘገየው ይችላል ከባልና ከሚስት ባንዱ የተፈጸመውና ለፍቺው ምክንያት ሆኖ የተገኘው ጥፋት በሌላው ተጋቢ ላይ ጉዳት አስከትሎ ከተገኘ በዳዩ ላደረሰው ጉዳት ተመጣጣኝ የሆነ ካሣ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ይወስናል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት ከጋራ ንብረት በካሣ መልክ ያንደኛውን ተጋቢ ድርሻ አብዛኛውን ወይም ሙሉውን በደል ለተፈፀመበት ወገን ሊሰጥ ይችላል መፋታቱ የተወሰነው የሁለቱም ወገኖች ጥፋት ባልሆነ ምክንያት የሆነ እንደሆነ ከላይ የተመለከቱት ቅጣቶች በሁለቱም ላይ አይፈፀምባቸውም ረ ከፍል የባልና ሚስትን ሀብት ስለማጣራት አንቀጽ የባልና ሚስትን ሀብት በስምምነት ስለማጣራት በዚህ ሕግ ስለካሣ ክፍያ የተደነገጉት እንደተጠበቁ ሆነው ጋብቻው በቪህ ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት የፈረሰ እንደሆነ ባልና ሚስቱ የጋብቻቸው መፍረስ በንበረት በኩል የሚያስከትለውን ውጤት አስመልክተው በሚያደርጉት ስምምነት ወይም በጋብቻ ውላቸው መሠረት ይጣራል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው የጋብቻ ውል ወይም ሌላ ስምምነት የሌለ ወይም በሕግ ፊት የማይፀና ሆኖ የተገኘ እንደሆነ የባልና ሚስት ሀብት በሚከተሉት ድንጋጌዎች መሠረት ይጣራል አንቀጽ የግል ሀብትን መልሶ ስለመውሰድ ባለ ወይም ሚስት የግሉ መሆኑን በማስረዳት የግል ሀብቱ የሆነውን ንብረቱን መልሶ የመውሰድ መብት ይኖረዋል ከባልና ሚስቱ አንደኛው የግል ሀብቱ የሆነ ማናቸውም ንብረት ለሌላ ሰው የተላለፈ መሆኑንና ከዚሁ ግብይት የተገኘውም ገንዘብ ከጋራ ሀብታቸው ጋር የተቀላቀለ መሆኑን ያስረዳ እንደሆነ ከዚህ ንብረት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ገንዘብ ወይም ንብረት ከጋራ ሀብታቸው በቅድሚያ የማንሳት መብት ይኖረዋል ባለና ሚስት የየግል ሀብታቸውን የሚያነሱበት ሁኔታ ሲኖር ሁለቱም በመጨረሻ ከተገኘው የንብረት መጠን እንደየአስተዋጽኦዋቸው ሲደርሳቸው የሚችለውን ያህል የማንሳት መብት ይኖራቸዋል አንቀጽ ስለካሳ በዚህ ሕግ መሠረት የጋራ ንብረቱን ወይም የሌላኛውን ተጋቢ ንብረት በብቸኝነት እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተጋቢ ከተሰጠው ሥልጣን ውጪ በፈፀማቸው ድርጊቶች ምክንያት ወይም ከብልሹ አስተዳደር የተነሳ ወይም የካሳ ጠያቂውን መብት በማታለል ድርጊቱ የጎዳ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በተበዳዩ ጥያቄ ሲቀርብለት ተገቢ የጉዳት ካሳ እንዲከፈለው ሊያዝ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሠረት የሚቀርብ የካሳ ጥያቄ ተፈፀመ የተባለው ድርጊት ጋብቻው ከመፍረሱ ሦስት ዓመት በፊት የሆነ እንደሆነ ተቀባይነት አይኖ ረውም አንቀጽ ያለአግባብ ስሰመበልጸግ ባልና ሚስት ተቃራኒ ስምምነት ካላደረጉ በስተቀር ከባልና ሚስት የአንደኛው የግል ሀብት ከሆነ ንብረት የሌላኛው የግል ሀብት ወይም የጋራ ሀብታቸው ያለአግባብ መበልጸጉን ያስረዳ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ተገቢ ካሳ እንዲከፈለው ሊያዝ ይችላል አንቀጽ የዕዳ ጠያቂዎችን መብት ስለማስከበር ከባልና ሚስት አንደኛው ወይም ሁለቱም በጋራ በፍርድ የተረጋገጠባቸው ወይም ሁለቱም ያመኑት ዕዳ መኖሩ የታወቀ እንደሆነ ይኸው ዕዳ የባልና ሚስት ሀብት ከመከፋፈሉ በፊት ተቀንሶ የሚከፈል ይሆናል አንቀጽ የ ት ፈ ከዚህ በላይ የተመለከቱትና የባልና ሚስት ሀብትን በስምምነት ስለማከፋፈል የተደነገጉት እንደተጠበቁ ሆነው የባልና ሚስት የጋራ ሀብት ለሁለቱም እኩል የሚከፋፈል ይሆናል አንቀጽ የባልና ሚስት ሀብት በዓይነት የሚከፋፈል ስለመሆኑ በመሠረቱ እያንዳንዱ ተጋቢ ከጋራ ሀብቱ የተወሰነ ንብረት እንዲደርሰው በማድረግ የጋራ ሀብቱ በዓይነት እንዲከፋፈል ይደረጋል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው አኳኋን እኩል ለማከፋፈል የማይቻል ሆኖ የተገኘ እንደሆነ ልዩነቱ በገንዘብ እንዲካካስ ይደረጋል የሀብት ክፍፍሉ በሚደረግበት ጊዜ እያንዳንዱ ተጋቢ ይበልጥ ጠቃሚነት ያላቸውን ንብረቶች እንዲያገኝ ለማድረግ ጥረት መደረግ ይኖርበታል አንቀጽ ለማከፋፈል አዳጋች ስለሆኑ ንብረቶች ንብረቱ ለክፍፍል የማያመች ወይም ለማከፋፈል የማይቻል ሆኖ የተገኘ እንደሆነና ባልና ሚስቱን ንብረቱ ከሁለቱ ለአንዳቸው እንዲሰጥ ለማስማማት ሳይቻል የቀረ አንደሆነ ንብረቱ ተሽጦ የተገኘውን ገንዘብ እንዲከፋፈሉ ይደረጋል ስለአሻሻጡ ሁኔታ ባልና ሚስቱ ሳይስማሙ ቀርተው አንደኛው ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ሽያጩ የሚደረገው በጨረታ ይሆናል አንቀጽ ጋብቻው ከፈረሰ በኋላ ከባልና ከሚስት ስለሚጠየቅ ዕዳ ጋብቻው ከፈረሰና የባልና ሚስት ሀብት ከተከፋፈለ በኋላ የሚጠየቅ ዕዳ በጋራ መከፈል የነበረበት በሆነ ጊዜ ስለዕዳው አከፋፈል ሁለቱም በየድርሻቸው መጠን ተጠያቂ ይሆናሉ ዕዳው የሚመለከተው አንደኛውን ተጋቢ በሆነ ጊዜ የዕዳው ክፍያ ሊጠየቅ የሚችለው ባለዕዳ ከሆነው ተጋቢ ብቻ ይሆናል ክፍል የክርክሮች ሂደትና አወሳሰን አንቀጽ ተፈጻሚነት ስለሚኖረው ሕግ በዚህ ሕግ የተመለከቱት የሥነ ሥርዓት ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው በዚህ ሕግ ውስጥ በተመለከቱት ጉዳዮች ላይ ለሚነሱ ክርክሮች የኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች እና የክልሉ መንግስት የፍትሐብሔር ሥነሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል አንቀጽ የባለና ሚስትን ዛሃብት ስለማጣራት የተደነገጉት ተፈጻሚ ስለመሆናቸው ጋብቻው የፈረሰው በፍቺ ባይሆንም የባልና ሚስትን ሀብት ስለማጣራት በዚህ በምዕራፍ ክፍል የተደነገጉት እንደየአግባብነታቸው ተፈጻሚ ይሆናሉ በተለይም ጋብቻው የፈረሰው በሞት በሆነ ጊዜ በሕይወት ባለው ተጋቢ እና በሟች ወራሾች መካከል የንብረት ክፍፍልን በተመለከተ ክርክር የተነሳ አንደሆነ የባልና ሚሜስትን ሀብት ስለማጣራት በዚህ ምዕራፍ ክፍል የተደነገጉት እንደዚሁ እንደየአግባብነታቸው ተፈጻሚ ይሆናሉ አንቀጽ የጋብቻ ሁኔታዎች መጓደል በዚህ ሕግ ምዕራፍ ሁለት ከአንቀጽ እስከ በተመለከተው መሠረት የጋብቻ ሁኔታዎች ከመጓደላቸው የተነሣ የጋብቻ መፍረስ በሚወሰንበት ጊዜ ፍርድ ቤት መፍረሱ የሚያስከትለውን ውጤት በርትዕ ይወሰናል አንቀጽ የባልና ሚስት ክርክር ስለሚታይበት ሁኔታ ፍርድ ቤት የባልና ሚስትን ክርክር በሚያይበት ጊዜ እንደነገሩ ሁኔታ አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው ባልና ሚስቱን በአንድነት ወይም በተናጠል ሲያነጋግር ወይም ጉዳዩን ሲመረምርና ምስክር ሲሰማ በዝግ ያስችላል አንቀጽ ስለ ውሳኔ አሰጣጥ ፍርድ ቤቱ አስፈላጊና ተገቢ ሆኖ ሲያገኘው ፍቺ በሚወሰንበት ጊዜ የተጋቢዎችን ወይም የቤተዘክመዶቻቸውን መልካም ስም ለመጠበቅ ዝርዝር ጉዳዩችን ከመተቸት በመቆጠብ ፍቺውን ለመወሰን የሚያስችሉ ምክንያቶች መኖራቸውን ብቻ በውሳኔው ላይ ሊያሰፍር ይችላል አንቀጽ ስለ ይግባኝ ፍርድ ቤቱ ፍቺ መወሰኑን ብቻ መሠረት በማድረግ ይግባኝ መጠየቅ አይቻልም አንቀጽ የልጆችን አጠባበቅና አያያዝ በሚመለከት ፍርድ ቤቱ ስለሚሰጠው ውሳኔ ፍርድ ቤቱ ጋብቻው እንዲፈርስ ሲወስን ልጆች ከማን ጋር ሊኖሩ እንደሚገባ ስለትምህርታቸው እና ስለጤናቸው አጠባበቅ ስለቀለባቸውና ባጠቃላይ ስለአፍኗራቸው እንዲሁም ወላጆችና ልጆቻቸው ለመጠያየቅ ስላላቸው መብት መወሰን አለበት ፍርድ ቤቱ ከዚህ በላይ በተመለከተው ሁኔታ ውሳኔ በሚሰጥበት ጊዜ የወላጆች የገቢ የዕድሜ የጤና እና የአኗኗር ሁኔታ አንዲሁም የልጆቹን ዕድሜ ጥቅማቸውና ፍላጐታቸው የሚጠበቅበትን ሁኔታ ማገናዘብ ይኖር በታል የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እንደተጠበቀ ሆኖ ተቃራኒ ውሣኔ የሚያሰጥ የተረጋገጠ ምክንያት በሌላኛው ወገን እስካልቀረበ በቀር ዕድሜአቸው ከአምስት አመት በታች የሆኑ ሕፃናት ከእናታቸው ጋር እንዲቆዩ ይደረጋል በቪህ አንቀጽ መሰረት ስለልጆች አጠባበቅና እንክብካቤ ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው ውሳኔ የሁኔታ ለውጥ ምክንያት በማድረግ በሚቀረበው ጥያቄ ማሻሻል ወይም መለወጥ ይችላል ምዕራፍ ስምንት ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ ስለመኖር አንቀጽ ትርጓሜ ጋብቻ ሳይፈፅሙ እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድና አንዲት ሴት በሕግ በሚፀና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈጽሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው ፊ አንቀጽ ማብራሪያ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት አብረው ኖሩ ለማለት ወንድየውና ሴትየዋ የሚያሳዩት ሁኔታ በሕግ እንደተጋቡ ሰዎች ዓይነት መሆኑ አስፈላጊና በቂ ነው ለሶስተኛ ወገኖች እንደተጋቡ ሆነው መቅረብ አስፈላጊ አይደለም አንድ ወንድና አንዲት ሴት በታወቀና በተደጋገመ ሁኔታ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈፀማቸው ብቻ በሁለቱ መካከል ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት ግንኙነት አላቸው ለማለት በቂ ምክንያት አይደለም አንቀጽ የጋብቻ ዝምድና የማያስከትል ስለመሆነ ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር በወንድየውና በሴቲቱ የሥጋ ዘመዶች መካከል እንዲሁም በሴትየዋና በወንድየው የሥጋ ዘመዶች መካከል አንዳችም የጋብቻ ዝምድና አያስከትልም ሆኖም የጋብቻ ዝምድና ባለ ጊዜ ጋብቻን የሚከለክሉ ድንጋጌዎች ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር ባለ ጊዜ ተፈፃሚ ይሆናል አንቀጽ የጋራ ኑሮ ወጪዎችን ስለመሸፈን ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ሰዎች የጋራ ኑሮአቸውን ወጪ ለመሸፈን እያንዳንዳቸው እንደየአቅማቸውና ችሎታቸው አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው አንቀጽ ስለ ጋራ ሀብት የንብረትአስተዳደራቸውን አስመልክቶ የሚያደርጉትን ውል እንደተጠበቀ ሆኖ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ሰዎች ከሶስት ዓመት ላላነሰ ጊዜ አብረው ከኖሩ በግንኙነት ውስጥ እያሉ ያፈሩዋቸው ንብረቶች የጋራ ሀብታቸው ይሆናሉ ተቃራኒ ማስረጃ አስካልቀረበ ድረስ አብረው በመኖሩ ወንድና ሴት የሚገሯቸው ንብረቶች በግንኙነቱ ውስጥ የተፈሩ ሀብቶች ተደርገው ይቆጠራሉ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ወንድና ሴት የሚገቧቸው ዕዳዎች አብረው የሚኖሩበት ጊዜ ለጋራ ኑሮአቸው ወይም የግንኙነቱ የተወለዱ ልጆችን መሠረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት ሲባል የተገቡ ዕዳዎች ሲሆን ለፅዳዎቹ አከፋፈል ሁለቱም በአንድነትና በነጠላ ኃላፊዎች ይሆናሉ አንቀጽ የጋራ ንብረት ስለሚያስከትለው ውጤት በዚህ ሕግ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በተመለከተው መሠረት በጋራ ሀብት የሚፈጠርበት ጊዜ ስለንብረቱ አስተዳደር የሶስተኛ ወገን ዕዳ አከፋፈልና ንብረት ማጣራት ሂደት በዚህ ሕግ በጋብቻ ስለሚፈጠር የጋራ ንብረትና የማጣራት ሂደት የተነገሩት ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል አንቀጽ አንቀጽ የልጆች መወለድ ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብረው ከሚኖሩ ወንድና ሴት የተወለዱት ልጆች ተወላጅነታቸው የሚረጋገጠው በዚህ ሕግ ስለመወለድ በተባለው ምዕራፍ ውስጥ በተደነገገው መሠረት ይሆናል አንቀጽ የግንኙነት መቋረጥ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ወንድና ሴት በማንኛውም ጊዜ ግንኙነታቸው እንዲቋረጥ ማድረግ ይችላሉ በዚህ ሕግ አንቀጽ ስለጋራ ሀብት የተነገረው እንደተጠበቀ ሆኖ ግንኙነቱ እንዲቋረጥ ያደረገው ወገን ጥፋት ካልፈጸመ በስተቀር ካሳ እንዲከፍል አይገደድም አንቀጽ የግንኙነቱ ማስረጃ ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖርን የግንኙነቱ ሁኔታ መኖሩን በማረጋገጥ ማስረዳት ይቻጓላል አንድ ወንድና አንዲት ሴት ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት አብረው ይኖራሉ የሚባለው ምንም እንኳን በሕግ የተጋቡ ባይሆኑም የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ ሲያሳዩና ቤተዘመዶቻቸውና ማኅበረሰቡ እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ ናቸው ብለው ሲገምቸው ነው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ሁኔታ መኖሩን አንደኛው ወገን ለማስረዳት የቻለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ናቸው ሲል የሕግ ግምት ይወስዳል ከዚህ በላይ የተመለከተውን የሕግ ግምት ማናቸውንም ዓይነት አስተማማኝ ማስረጃ በማቅረብ ግንኙነት ያለመ ኖሩን በማስረዳት ማፍረስ ይቻላል አንቀጽ የክርክሮች ሂደትና አወሳሰንዐ ሥልጣን ስላለው አካል በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ የመኖር ግንኙነት ስለመኖሩ ክርክር የተነሳ እንደሆነ ጉዳዩን አይቶ ለመወሰን ሥልጣን የሚኖረው ፍርድ ቤት ብቻ ነው አንቀጽ ተፈፃሚነት ስለሚኖረው ሕግ በዚህ ሕግ ከአንቀጽ እስከ የክርክሮችን ሂደትና አወሳሰን በሚመለከት የተደነገጉት ድንጋጌዎች እንደአ ግባብነታቸው ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ በመኖር ግንኙነት ውስጥ በሚነ ክርክሮችም እንደየአግባብነታቸው ተፈፃሚ ይሆናሉ ቀጽ ብቻ ሳይፈጸም የ ከጋብቻ ሥርዓት ወይም ጋብቻ ሳይፈጸም እንደባልና ሚስት አብሮ ከመኖር ውጪ በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል የሚደረጉ ሌሎች ግንኙነቶች በሕግ ፊት ምንም ውጤት አይኖራቸውም በዚህ ሕግ ስለ ጉዲፈቻ ልጅ ወይም ልጅነትን ስለመቀበል የተወሰኑት ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ከእንደዚህ ያለ ግንኙነት የተወለዱ ልጆች ከእናታቸው በስተቀር ከሌላ ሰለው ጋር ማናቸውም ዓይነት ህጋዊ ግንኙነት አይኖ ራቸውም ምዕራፍ ዘጠኝ ስለ መወለድ ክፍል አባትነትንና እናትነትን ስለማወቅ ንዑስ ክፍል አጠቃላይ ድንጋጌዎች አንቀጽ የሕጉ ድንጋጌዎች አስገዳጅ ስለመሆናቸው ሕጉ በግልጽ የሚፈቅድ ካልሆነ በስተቀር አባትነትና እናትነትን ስለማወቅ የተመለከቱት የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች በስምምነት ሊለወጡ አይችሉም አንቀጽ ስለእናትነት እናት የተባለችው ሴት ልጁን የወለደችው በመሆንዋ ብቻ እናትነትዋ ይታወቃል አንቀጽ ስለ አባትነት ልጅ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ በእናትየዋና በአንድ ወንድ መካከል በሕግ የታወቀ ግንኙነት መኖሩ በመረጋገጡ ምክንያት አባትነት ይታወቃል አባትየው ልጁን ልጄ ነው ሲል በመቀበሉ ምክንያትም አባትነት ሊታወቅ ይችላል በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔም አባትነት እንዲታወቅ ሊደረግ ይችላል ንዑስ ክፍል አባትነት በሕግ ግምት የሚታወቅ ስለመሆኑ አንቀጽ ባል አባት ነው ተብሎ የሚገመት ስለመሆኑ በጋብቻ ውስጥ የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ አባቱ ነው የሚባለው ባልየው ነው አንቀጽ የግምቱ አጠቃላይነት ከልጁ ጋር ያለው የእናት ግንኙነት በየትኛውም ዘዴ የተረጋገጠ ቢሆንም በአንቀፅ የተመለከተው ድንጋጌ ተፈፃሚነት ይኖረዋል የልጁ የልደት ምስክር ወረቀት ባልየው አባት ያለመሆኑን ወይም የልጁ አባት ሌላ ሰው መሆኑን የሚያመለክት ቢሆንም እንኳን ይኸው ድንጋጌ ተፈፃሚነት ይኖረዋል ከዚህ በላይ የተመለከተው ሁኔታ ባጋጠመ ጊዜ የልደት ምስክር ወረቀቱ እንዲታረም ይደረጋል አንቀጽ እርግዝናው ስለሚቆይበት ጊዜ ጋብቻው ከተፈፀመ ከ ቀናት በኋላ ወይም ጋብቻው በፈረሰ በ ቀናት ውስጥ የተወለደ እንደሆነ ልጁ በጋብቻው ውስጥ እንደተፀነሰ ይቆጠራል ለዚህተቃራኒ የሆነ ማስረጃ ተቀባይነት አይኖረውም አንቀጽ የባለየው መጥፋት በዚህ ሕግ ስለአባትነት የተደነገጉት የሕግ ግምቶች በሕግ አባት ነው የሚባለው ሰው መጥፋቱ በተነገረበት ፍርድ ላይ ስለመኖሩ ወሬ የተሰማበት የመጨረሻ ቀን ነው ከተባለበት ከ ቀናት በኋላ ለተወለደ ልጅ ተፈዓሚነት አይኖረውም አንቀጽ ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብር መኖር ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብረው በሚኖሩበት ጊዜ የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ አባት በዚሁ ግንኙነት ከእናትየዋ ጋር አብር የሚኖረው ሰው ነው በዚህ ሕግ አንቀጽ እና ስለግምቱ አጠቃላይነትና እርግዝናው ስለሚቆይበት ጊዜ የተመለከቱት ድንጋጌዎች በዚህ አንቀጽ ለተመ ለከተው የሕግ ግምትም ተፈፃሚነት ይኖራቸዋል ንዑስ ክፍል ን ስለመ አንቀጽ መሠረቱ ከዚህ በላይ በተመለከቱት ድንጋጌዎች መሠረት የልጁ አባት ሊታወቅ ያልቻለ እንደሆነ አባትየው ልጄ ነው ሲል በመቀበሉ ሊታወቅ ይቸላል አንቀጽ ትርጎሜ አንድ ሰው አንድን የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ የእርሱ ልጅ መሆኑን አምኖ በመቀበል ቃሉን የሰጠ እንደሆነ የልጁ አባት መሆኑን ተቀበለ ይባላል አንቀጽ ሥርዓት ፎርም አንድ ሰው የክብር መዝገብ ሹም ፊት በመቅረብ አባት መሆኑን በመግለፅ በሚሰጠው ቃል ወይም በጽሑፍ በሚያደርገው ትዛዜ ወይም በሌላ በማናቸውም ሥልጣን በተሰጠው ባለሥልጣን በተረጋገጠ ሰነድ አማካይነት አባት መሆኑን በመግለፅ ልጅነትን ለመቀበል ይችላል ጐዮር አንቀጽ ስለውክልና አካለ መጠን ያልደረሰ ቢሆንም እንኳን ልጄ ነው ሲል ቃል ለመስጠት የሚችለው አባት ብቻ ነው ቃሉን ሌላሰው እንዲሰጥለት ማድረግ የሚችለው በፍርድ ቤት የፀደቀ ልዩ የውክልና ሥልጣን በመስጠት ብቻ ይሆናል በፍርድ የተከለከለ ሰው ቃሉን በራሱ ወይም ፍርድ ቤት ሲፈቅድ በእርሱ ስም በሕጋዊ ወኪሉ አማካይነት ሊሰጥ ይችላል። አንቀጽ መሠረቱ በእናት በኩል ያለው ተወላጅነት በማንኛውም ባለጉዳይ በማንኛውም ጊዜ ሁሉ ክርክር ሊደረግበት ይችላል አንቀጽ ክስን ስለመቀበል በተወላጅነት ላይ ስለሚደረገው ክርክር የሚቀርበው ክስ ፍርድ ቤት ካልፈቀደ በስተቀር ሊቀርብ አይ ችልም በተወላጅነት ላይ ክርክር ለማድረግ ለሚቀርበው ክስ ፈቃድ የሚሰጠው ፍርድ ቤቱ ክሱን እንዲቀ በል የሚያደርጉት ተጨባጭነት ካላቸው ተግባ ራት የሚመነጩ ግምቶች ወይም ምልክቶች ሲኖሩ ብቻ ነው አንቀጽ ላለመቀበል ልጁ ተወላጅነቱን የሚያረጋግጥ የልደት ምስክር ወረቀትና ከዚህ ጋር የሚስማማ የልጅነት ሁኔታ ያለው እንደሆነ በተወላጅነቱ ላይ ለመከራከር ፈቃድ አይሰጥም አንቀጽ ስለ ክስ በተወላጅነት ምክንያት የሚቀርበው ክስ በተወሳጅነቱ ላይ ክርክር በተነሳበት ሰው ላይ ወይም በወራሾቹ ላይ ይመሰረታል የልጁን እናት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም የልጁን አባት ክርክሩ ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ አስፈላጊ ነው ን ፍል ስለ መካድ አንቀጽ መሠረቱ በአባት በኩል ያለውን መወለድ መቃወም የሚቻለው የመካድ ክስ በማቅረብ ብቻ ነው አንቀጽ ከልጁ እናት ጋር የሩካቤ ሥጋ ግን ኙነት ስላለመኖር መሠረቱ የልጁ አባት ነህ ተብሎ በህግ አባትነት የሚሰጠው ሰው ልጁ ከመወለዱ በፊት በኛውና በኛው ቀናት መካከል ባለሀ ጊዜ ውስጥ ከልጁ እናት ጋር የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት ላለመፈፀሙ በማያጠራጥር ሁኔታ ያስረዳ እንደሆነ የተባለውን ልጅ ልጄ አይደለም ለማለት ይችላል አንቀጽ የሕግ ግምት ከሁለቱ አንዱ ባቀረበው የመፋታት ጥያቂ መሠረት ወይም በሁለቱ መካከል በተደረገው የመለያየት ስምምነት ምክንያት ባልና ሚስቱ በእውነት ተለያይተው በነበሩበት ጊዜ በመካ ከላቸው የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት እንዳልተደረገ ይገ መታል ለዚህ ተቃራኒ ሆኖ የሚቀርበው ማስረጃ በማናቸውም ምክንያቶች ቢሆን ይሰማል አንቀጽ አባት ለመሆን ስለአለመቻሉ በ መሠረቱ በሕግ የልጁ አባት ነህ የተባለው ሰው የዚሁ ልጅ አባት ሊሆን አለመቻሉን በማያጠራጥር አኳኋን በማስረዳት ለመካድ ይችላል አንቀጽ ክስን ለመቀበል ስለመቻል ከዚህ በላይ በተመለከተው አንቀጽ መሠረት የሚቀርበው የመካድ ክስ ፍርድ ቤት ካልፈቀደ በስተ ቀር ሊቀርብ አይችልም ፈቃዱም የሚሰጠው ፍርድ ቤት ክሱን እንዲቀበል የሚያደርገው በቂና አስተማማኝ ከሆነ መረጃ የሚ መነጭ የህሊና ግምት ወይም ከባድ ምልክት ሲኖር ብቻ ነው አንቀጽ ስለ ህሊና ግምቶችና ከባድ ምልክቶች የህሊና ግምቶችና ከባድ ምልክቶች የሚባሉት ልጅህ ነው ከተባለው ሰው አባትነት ጋር የማይስማሙ ለመሆናቸው በሳይንስ እውቀት ተለይተው የማታዩ ተጨባጭ መረጃዎች ሊሆኑ ይችላሉ እንዲሁም እነዚህ ነገሮች ሴቲቱ በሰውየው አባትነት ላይ ጥርጣሬ በሚያሳድር አኳኋን የልጁን መወለድ ወይም እርግዝናዋን ከሰውየው ከደበቀችው ነው አንቀጽ ብ ስለ ሴሰኝነት በባል ላይ ስለሚደረግ ዝሙት ወይም ስለ እናቲቱ ማመን እናቲቱ በባልዋ ላይ ያደረገችው የሴሰኝነት የዝሙት ሥራ ወይም ልጁ የሌላ ሰው ለመሆኑ የምትሰጠው የአምነት ቃል ብቻ እንደ ከባድ ምክንያት ሊቆጠሩ አይችሉም አንቀጽ ስለ ከሳሽ የአኔ ልጅ አይደለም ብሎ የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚችለው የልጁ አባት ነህ ተብሎ በህግ ግምት የሚሰጠው ሰው ብቻ ነው በዚህ ጉዳይ በተለይ እናቲቱ አባት ነኝ ባዩ ዐቃቤ ሕግ ወይም ልጁ ራሱ ክስ ሊያቀርቡ አይችሉም አንቀጽ በፍርድ የተከለከለ ሰው በፍርድ የተከለከለ ሰው ፍርድ ቤትን አስፈቅዶ የመካድ ክስ ለማቅረብ ይችላል እንዲሁም በፍርድ የተከለከለው ሰው አሳዳሪ ይህንኑ የፍርድ ቤት ፈቃድ ከተቀበለ በኋላ በፍርድ በተከለከለው ሰው ስም ሆኖ የመካድ ክስ ለማቅረብ ይችላል አንቀጽ ክስ ስለሚቀርብበት ጊዜ መሠረቱ የእኔ ልጅ አይደለም የሚል የመካድ ክስ የልጁን መወለድ ካወቀበት ወይም ማወቅ ከሚገባው ቀን ጀምሮ በ ቀናት ውስጥ መቅረብ አለበት እናትነት የተወሰነው ተወላጅነትን ለማረጋገጥ በቀረበ ክስ ሲሆን የመካድ ክስ የሚቀርበው ተወላጅነትን ለማረጋገጥ የቀረበውን ክስ የሚወስን የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠ ጀምሮ ባሉት ቀናት ውስጥ ነው አንቀጽ ልዩ ሁኔታ በሕግ ግምት የልጁ አባት ነህ የሚባለው ሰው የሞተ ወይም የመካድ ክስ ለማቅረብ በተወሰነው ጊዜ ውስጥ ችሎታውን ያጣ እንደሆነ ከተወላጆቹ አንዱ በርሱ ፋንታ ሆኖ የመካድ ክስ ሊያቀርብ ይችላል ተወላጆቹ የሌሉ እንደሆነ አባትና እናቱ እነቪህም የሌሉ እንደሆነ ወደ ላይ ከሚቆጠሩ ወላጆቹ አንዱ መብቱን ሊሰራበት ይችላል ወደ ላይ የሚቆጠሩ ወላጆች የሌሉ እንደሆነ የተባለውን መብት ማንኛውንም ሌላ ወራሽ ወይም ወኪልን ሳይ ጨምር ከወንድሞቹ ወይም ከእህቶቹ አንዱ ሊሰራበት ይችላል አንቀጽ ክስን ስላለመቀበል ባልየው በጽሁፍ በሰጠው ፈቃድ መሠረት ልጁ በሰው ሰራሽ ዘዴ የተፀነሰ ለመሆኑ የተረጋገጠ እንደሆነ የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚቀርብ ጥያቄ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም አንቀ ለ ሾ የመካድ ክስ በልጁ ላይ አርሱም ሞቶ እንደሆነ በወራሾቹ ላይ ያቀርባል የልጁን እናት በሚቀርበው ክስ ውስጥ እንድትገባ ማድረግ ያስፈልጋል ልጁ አካለመጠን ያልደረሰ ከሆነ ፍርድ ቤት በተለይ ለዚህ ጉዳይ የመረጠው ሞግዚት ወኪል ይሆነዋል ምፅራፍ አሥር ስለ ጉዲፈቻ አንቀጽ ስለጉዲፈቻ ዝምድና መሠረቱ በሕዝቡ ልማድ መሠረት ወይም በአንድ ሰውና በአንድ ልጅ መካከል በሚደረግ ስምምነት የጉዲፈቻ ዝምድና ሊፈጠር ይችላል አንቀጽ ውጤቱ በዚህ ሕግ አንቀጽ የተመለከቱት ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው የጉዲፈቻ ልጅ በማናቸውም ረገድ ቢሆን እንደ ጉዲፈቻ አድራጊው ልጅ ይቆጠራል አንቀጽ ልዩ ሁኔታ ጉዲፈቻ የጉዲፈቻውን ስምምነት በግልጽ የተቃ ወሙትን ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆችን ወይም ወደጐን የሚቆጠሩ ዘመዶችን በሚመለከት ውጤት አይኖረውም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ተቃውሞ ስምምነቱ በፍርድ ቤት መጽደቁ በታወቀ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በፍርድ ቤት መዝገብ ካልተመዘገበ በስተቀር አይፀናም አንቀጽ ዐ የጉዲፈቻ ልጅ ከቀደምት ቤተሰቦቹ ጋር ስለሚ ኖረው ግንኙነት የጉዲፈቻ ልጅ ከቀደምት ቤተሰቦቹ ጋር ያለው የዝምድና ግንኙነት እንደተጠበቀ ይቆያል የጉዲፈቻ ልጅየው ሚስትባል እና ተወላጆችም ከቀደምት ቤተሰቦቹ ጋር የዝምድና ግንኙነት ይኖራቸ ዋል በቀደምት ቤተሰቦቹና በጉዲፈቻ ቤተሰቦቹ መካከል መምረጥ አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ለጉዲፈቻ ቤተ ሰቦቹ ቅድሚያ ይሰጣል አንቀጽ የጉዲፈ ው ዕድሜ ፅድሜው ከ ዓመት ያላነሰ ማንኛውም ሰው የጉዲፈቻ አድራጊ ሊሆን ይችላል ጉዲፈቻ አድራጊዎች ባልና ሚስት በሆኑ ጊዜ የአንዳቸው ፅድሜ ዓመት የሞላ ከሆነ በቂ ነው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ እና ላይ የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ዕድሜው ዓመት የሞላው ሰው ፍርድ ቤቱ የልጁን ጥቅም በጥሩ ሁኔታ ለመጠበቅ ይችላል ብሎ ካመነበት ጉዲፈቻ አድራጊ ሊሆን ይችላል ቀጽ የጉ ጅ ዕድሜ ፅድሜው ከ ዓመት በታች የሆነና ከሞግዚት አስተዳደር ነፃ ያልወጣ ማንኛውም ሰው የጉዲፈቻ ልጅ ለመሆን ይችላል አንቀጽ ገባ ሰው ስለ ገው ጉዲፈ ጉዲፈቻ አድራጊው ያገባ በሚሆንበት ጊዜ ባልና ሚስቱ በጋራ ልጁን የጉዲፈቻ ልጃቸው የሚያደርጉት ካልሆነ በስተቀር ጉዲፈቻ ማድረግ አይ ቻልም የጉዲፈቻው ልጅ የጉዲፈቻ አድራጊው ባል ወይም ሚስት ልጅ በሆነ ጊዜ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ ተፈፃሚነት አይኖረውም እንዲሁም ከባል እና ከሚስት አንደኛው ፈቃዱን ለመስጠት የማይችል ሲሆን ተፈፃሚነት አይኖረውም የተፀነሰን ልጅ የጉዲፈቻ ልጅ ማድረግ ይቻላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ቢኖርም ልጁ በተወለደ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ እናቲቱ ስምምነቱን በገዛ ፈቃድዋ ብቻ ለመሠረዝ ትችላለች አንቀጽ ስለ ጉዲፈቻው አድራጊው ልጆች ጉዲፈቻ አድራጊው ከአብራኩ የተገኙ ልጆች ያሉት መሆኑ ጉዲፈቻ ከማድረግ የሚያግደው አይሆንም የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በ ድንጋጌ ቢኖርም ፍርድ ቤቱ በአንቀጽ መሠረት ጉዲፈቻ ከማጽደቁ አስቀድሞ ጉዲፈቻ አድራጊው ከአብራኩ የተገኙ ልጆች ያሉት መሆኑ በጉዲፈቻ ልጁ መልካም አስተዳደግና ጥቅም ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተፅዕኖ ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት አንቀጽ አንድ ልጅ ከአንድ በላይ ጉዲፈቻ አድራጊ ሲኖረው የማይችል ስለመሆኑ ባለና ሚስት ካልሆኑ በስተቀር ማንኛውም ልጅ ለብኩዙ ሰዎች የጉዲፈቻ ልጅ ሊሆን አይችልም ጉዲፈቻ አድራጊው የሞተ እንደሆነ ግን አዲስ ጉዲፈቻ ማድረግ ይቻላል ልጅየው የባልና ሚስት የጉዲፈቻ ልጅ ከሆነና ከባልና ሚስቱ አንደኛው የሞተ እንደሆነ በሕይወት ካለው ሰው ጋር የሚጋባው አዲስ ተጋቢ የጉዲፈቻ ልጅ ሊያደ ርገው ይችላል አንቀጽ ስምምነቱን ስለሚያደርጉ ወገኖች የጉዲፈቻው ስምምነት በጉዲፈቻ አድራጊውና በልጁ አሳዳሪ መካከል ይደረጋል አንቀጽ የጉ ው ልጅ ወላጆች ፈቃድ የልጁ አባትና እናት በሕይወት ያሉና የታወቁ ከሆነ ልጁ የጉዲፈቻ ልጅ እንዲሆን ፈቃዳቸውን እንዲሰጡ ያስፈልጋል ከወላጆቹ አንደኛው የሞተ የጠፋ የማይታወቅ እንደሆነ ወይም ፈቃዱን ለመስጠት የማይችል ሲሆን ሌላኛው ወላጅ ፈቃዱን ይስሰጣል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው ቢኖርም ከወላጆቹ አንዱ ፈቃዱን ለመስጠት ያልፈለገ እንደሆነና የልጁ ዕድሜ ዓመትና ከዚያ በላይ ከሆነ ፍርድ ቤቱ ያንደኛውን ወላጅ ፈቃድና የልጁን አስተያየት በመጠየቅ ጉዲፈቻውን ሊያፀድቀው ይችላል ፋፈ ልጁ ፈቃዱን ለመስጠት የሚችል ወደላይ የሚቆጠር ወላጆ የሌለው እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ለልጁ ያለውን ጠቃሚነት ግምት ውስጥ በማስገባት ጉዲፈቻውን ሊያ ፀድቀው ይችላል አንቀጽ ስለመንግሥት ወይም የግል ዕጎለማውታን አሳዳጊ ተቋሞች የመንግሥት ወይም የግል ዕጎለማውታን አሳዳጊ ተቋሞች እያሳደጉት ያሉትን ማንኛውንም ልጅ ለጉዲፈቻ አድራጊዎች በስምምነት ለመስጠት ይችላሉ ከዚህ በላይ የተጠቀሱት ተቋሞች አንድን ልጅ በስምምነት ከመስጠታቸው በፊት የሕፃናትን ደህንነት ለመከ ታተል ሥልጣን ለተሰጠው የመንግሥት አካል ስለልጁ ማንነት ተቋሙ በምን ሁኔታ እንደተረከበውና ስለጉዲፈቻ አድራጊው ግላዊ ማኀበራዊና ኢኩኖሚያዊ አቋም መግለጫ ማቅረብ አለባቸው አንቀጽ ፈቻ አድራጊው የውጭ ሲሆን ጉዲፈቻ አድራጊው የውጭ ዜጋ ሲሆን የሕፃናትን ደህንነት ለመከታተል ሥልጣን የተሰጠው አካል ስለጉዲፈቻ አድራጊው ግላዊማኀበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቋም አግባብ ያላቸውን መረጃዎች በማጠናቀርና በመመርመር ስምምነቱ ቢደረግ ለልጁ ጠቃሚነት ይኖረዋል ሲል አስተያየቱን ካልሰጠ በስተቀር የጉዲ ፈቻውን ስምምነት ፍርድ ቤት ሊያፀድቀው አይችልም ሪ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ቢኖርም ፍርድ ቤቱ ስምምነቱ ለልጁ ጠቃሚነት አይኖረውም ሲል የገመተ እንደሆነ የባለሥልጣኑን አስተያየት ባለመ ቀበል ስምምነቱን ላያፀድቀው ይችላል ፍርድ ቤቱ ከባለሥልጣኑ የቀረበለት መረጃ በቂ መስሎ ያልታየው እንደሆነ አዲስ ምርመራ በማከናወን ተጨማሪ መረጃ እንዲቀርብለት ባለሥልጣኑን ለማዘዝ እንዲሁም ሴሎች ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች አስፈላጊ መስሎ የሚታያቸውንና በእጃቸው የሚገኘውን መረጃ እንዲያቀርቡ ወይም እንደአስፈላጊነቱ የምስ ክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ለማዘዝ ይችላል አንቀጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን በዘልማድ ወይም በውል የተገባ የጉዲፈቻ ስምምነት ፍርድ ቤት ካላፀደቀው በስተቀር ውጤት አይ ኖረወም ፍርድ ቤቱ ጉዲፈቻ ከማጽደቁ አስቀድሞ በወሳኝ መልኩ ለልጁ መልካም አስተዳደግና ጥቅም የሚበጅ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት በዚህ ሕግ በአንቀጽ እና የተመለከቱትና የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ አጠቃላይ አነጋገር እንደ ተጠበቀ ሆኖ ፍርድ ቤቱ የጉዲፈቻ ስምምነቱን ከማጽደቁ በፊት የሚከተሉትን ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት ሀ ልጅየው ስለጉዲፈቻ ስምምነቱ ያለውን አስተያየት ለአስቀድሞ ፈቃዱን ያልሰጠ ከሆነም የአሳዳ ሪውን አስተያየት ሒ ጉዲፈቻ አድራጊው ልጁን ለማሳደግና ለመንከባከብ ያለውን ብቃት መ ጉዲፈቻ አድራጊው የውጭ ዜጋ ሲሆን ልጅየው ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያድግበት ሁኔታ አለመኖሩን መሥ ጉዲፈቻ አድራጊው እንደልጁ አድርጐ እንደ ሚያሳድገውና አላግባብ መጠቀሚያ እንደማያደ ርገው ለመገመት የሚያስችል መረጃ መኖሩን ፈ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በፊደል ተራ ሠ የተመለከተውን በሚያጣራበት ጊዜ ጉዲፈቻ አድራጊው የውጭ ዜጋ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ልዩ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል አንቀጽ የጉዲፈቻ ስምምነት የማይሰረዝ ስለመሆኑ የጉዲፈቻ ስምምነት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ከተመለከተው ሁኔታ ውጪ ሊሰረዝ አይችልም ጉዲፈቻ አድራጊው በጉዲፈቻ የተቀበለውን ልጅ እንደልጁ በማሳደግ ፋንታ በባርነት ወይም ባርነትን በሚመስል ሁኔታ ወይም ከግብረ ገብ ውጪ በሆኑ ተግባሮች እንዲሠማራ በማድረግ መጠቀሚያ ያደረገው እንደሆነ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ የልጁን የወደፊት ሕይወት ክፉኛ በሚጐዳ አኳኋን የያዘው መሆኑን የተረዳ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የጉዲፈቻ ስምምነቱን ለመሠረዝ ይችላል ። አንቀጽ ጉዲፈቻ እንዲሰረዝ አቤቱታ ስለማቅረብ የጉዲፈቻው ልጅ ራሱ የሕጻናትን ደኀንነት ለመከታተል ሥልጣን የተሰጠው የመንግሥት አካል ወይም በጉዳዩ ያገባኛል የሚል ማንኛውም ሰው ከዚህ በላይ በተመለከ ተው አንቀጽ የተደነገገውን መሠረት በማድረግ ጉዲፈቻው እንዲሰረዝ አቤቱታ ለማቅረብ ይችላል በዚህ አንቀጽ ንዑስ መንቀጽ መሠረት አቤቱታ ሲቀርብለት ፍርድ ቤቱ ጉዲፈቻ አድራጊውን ከማስቀ ረቡ በፊት ለአቤቱታው ምክንያት ናቸው የተባሉት መረ ጃዎች እውነት ሆነው ቢገኙ ጉዲፈቻውን ለማፍረስ በቂ መሆናቸውን ማረጋገጥ አለበት ምዕራፍ አሥራ አንድ ቀለብ የመስጠት ግዴታ አንቀጽ ስለግዴታው ይዘት በዚህ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌዎች መሠረት ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለበት ሰው እንደ ባለጉዳዮቹ ሁኔታና እንደ አካባቢው ልማድ የሚስማማውን በመከተል ለቀለብ ተቀባዩ ምግብ መኖሪያ ልብስ ጤናውን እንደሁኔታው ለትምህርት አስፈላጊ የሆነውን ነገር መስጠት አለበት አንቀጽ ግዴታው በእነማን መካከል ስለመሆኑ ቹ በዚህ ሕግ አንቀጽ ፅ ንዑስ አንቀፍ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ቀለብ የመስጠት ግዴታ የሚኖረው በቀጥታ ወላጆችና ተወላጆች ወይም በቀጥታ የጋብቻ ዘመዳሞች መካከል ነው እንዲሁም በወንደማማቾች እና እህትማማቾች መካከል ቀለብ የመስጠት ግዴታ ይኖራል አንቀጽ ግዴታው ስለሚቀርበት ሁኔታ ጋብቻ የፈረሰው በሞት ምክንያት ካልሆነ በስተቀር በጋብቻ ዘመዳሞች መካከል ያለው ቀለብ የመስጠት ግዴታ ከጋብቻ መፍረስ በኋላ ቀሪ ይሆናል አንቀጽ ቀለብ ተቀባዩ መብቱን ስለሚያጣበት ሁኔታ ቀለብ ተቀባዩ በቀለብ ሰጪው ወይም በዚህ ሰው ወደሳይና ወደታች በሚቀቆጠሩ ወላጆች ወይም ተወላጆች ወይም ባል ወይም ሚስት ሕይወት ወይም ንብረት ላይ የወንጀል ተግባር የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ እንደሆነ ቀለብ የመቀበል መብቱን ያጣል አንቀጽ ግዴታው እንዲኖር አስፈላጊ ሁኔታዎች ቀለብ የመስጠት ግዴታ ተፈጻሚ የሚሆነው ቀለብ ጠያቂው ሠርቶ ለኑሮው አስፈላጊ የሆነ ገቢ ለማግኘት አቅም የሌለውና በችግር ላይ የወደቀ ሲሆን ብቻ ነው አንቀጽ ስለግዴታው አፈጻጸም በመሠረቱ ቀለብ የመስጠት ግዴታ የሚፈጸመው ቀለብ ሰጪው ለቀለብ ተቀባዩ የቀለቡን ገንክብ በመስጠት ነው የቀለኩቡ መጠን የሚወሰነው ቀለብ ጠያቂው ያለበትን ችግር እና የቀለብ ሰጪውን አቅም በማመዛዘን ነው አንቀጽ ውሳኔውን ማሻሻል የሚቻል ስለመሆኑ ቀለብ ሰጪው ወይም ተቀባዩ የሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት ስለቀለቡ መጠን ወይም ስለቀለብ ተቀባዩ መኖሪያ የተሰጠውን ውሳኔ በማናቸውም ጊዜ ማሻሻል ይቻላል አንቀጽ ቀለቡ ስለሚከፈልበት ቦታ ቀለቡ የሚከፈለው በተቻለ መጠን ለቀለብ ተቀባዩ በሚያመቸው ቦታ ይሆናል አንቀጽ የቀለብ ገንዘብ ሊተላለፍና ሊያዝ የማይችል ለመሆኑ ለቀለብ የሚከፈል ገንዘብ ሊተላለፍ ወይም ሊያዝ አይችልም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው ቢኖርም ለቀለብ የሚከፈል ገንዘብ የሚከፈልበት ጊዜ ከመድረሱ አስቀድሞ ለዕርዳታ ለተቋቋሙ ድርጅቶች ሊተላለፍ ይችላል እንዲሁም የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ለቀለብ ተቀባዩ ኑሮ አስፈላጊ የሆነውን ነገር ያበ ደሩ ሌሎች ሰዎችን በተመለከተ ተፈጻሚነት አይኖረውም አንቀጽ የቀለብ ገንዘብ የማይጠራቀም ስለመሆነ ቀለብ ተቀባዩ ለኑሮው አስፈላጊ መሆኑን ካላረጋገጠ በስተቀር የቀለቡን ገንዘብ መቀበል ካለበት ቀን ጀምሮ በተከታዮቹ ሦሥት ወራት ውስጥ ያልተቀበለው ወይም ሳይጠይቀው የቀረ እንደሆነ የተጠራቀመው ቀለብ እንዲሰጠው መጠየቅ አይችልም አንቀጽ ቀለብ ተቀባዩን በቀለብ ሰጪው ቤት ሰማኖር ስለመቻል ቀለብ ሰጪው ቀለብ ተቀባዩን በመኖሪያ ቤቱ ተቀብሎ በማስቀመጥ ቀለብ የመስጠት ግዴታውን ሊፈጽም ይችላል ክዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ሰለተመለከተው ጉዳይ ክርክር የተነሳ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የነገሩን የአካባቢ ሁኔታዎች በመመልከት ተገቢ መስሎ የታየውን ይወ ስናል ቀለብ ሰጪው ቀለብ ተቀባዩን በመኖሪያ ቤቱ እንዳ ያስቀምጥ ምንጊዜም ቢሆን አይገደድም ንቀጽ ስለቀለብ ሰጪዎች ብዛት መሠረት ለቀለብ ተቀባዩ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ሰዎች ብዙ የሆኑ እንደሆነ ቀለብ ተቀባዩ ከእነርሱ መካከል አንዱ ቀለቡን እንዲሰጠው ሊጠይቀው ይችላል አንቀጽ ስለ አቤቱታ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ሰዎች ብዙ ሆነው ከአነርሱ መካከል አንድ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑት ቀለቡን የከፈሉ እንደሆነ ሳይከፍሉ የቀሩት ድርሻቸውን እንዲከፍሏቸው ለመጠየቅ ይችላሉ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ስለተመለከተው ጉዳይ ክርክር የተነሳ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ተካሳሾቹ ያላቸውን ሀብትና ከከሳሽ ጋር ያላቸውን የሥጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ደረጃ በማመዛዘን ተከሳሾቹ የቀለቡን ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲከፍሉ ሊወስንባቸው ይችላል አንቀጽ ለቀለብ ሰጪዎች የሚሰጥ የከፋይነት ተራ በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ሰዎች ቅደም ተከተል ፅ ሀ በመጀመሪያ ደረጃ ባል ወይም ሚስት ለ በሁለተኛ ደረጃ ተወላጆች እንደየደረጃቸው ሐ በሦስተኛ ደረጃ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች እን ደየደረጃቸው መ በአራተኛ ደረጃ ወንድማማችና አህትማማቾች ሠ በአምስተኛ ደረጃ የጋብቻ ተወላጆች እንደየደረ ጃቸው ረ በስድስተኛ ደረጃ የጋብቻ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላ ጆች እንደየደረጃቸው አንቀጽ ራ ቀለ ች መካ የሚደረግ ስምምነት የጋራ ቀለብ ሰጪዎች እርስ በእርሳቸው ስለአላቸው ግንኙነት ለጋራ ቀለብ ተቀባያቸው ከእነርሱ መካከል አንድ ቀለቡን እንዲሰጠው በማለት የሚፀና ስምምነት ለማድረግ ይችላሉ ቀለብ ተቀባዩ ስምምነቱን ወዶ የተቀበለ እንደሆነ ይህንን ስምምነት የማያከብርበት ከባድ ምክንያት ካልተገኘ በስተቀር ቀለቡን ከሌሎቹ ቀለብ ሰጪዎች መጠየቅ አይችልም አንቀጽ ስለ ጉዲፈቻ ልጅ ልዩ ሁኔታ የጉዲፈቻ ልጅ ባል ወይም ሚስትና የቀጥታ መስመር ተወላጆች የጉዲፈቻ አድራጊው ቤተዘመዶች ቀለቡን መስጠት በማይችሉበት ሁኔታ ካልተገኙ በስተቀር የሥር ወላጆቹን ቤተዘመዶች ቀለብ ለመጠየቅ አይችሉም የቀደምት ቤተሰቦቹ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ቀለብ ለማግኘት ከዘመዶቻቸው አንዱን ለመጠየቅ የማይችሉ ካልሆነ በስተቀር በጉዲፈቻ የሰጡትን ልጅ ቀለብ ሊጠ ይቁት አይችሉም አንቀጽ ስለ ሥርዓተ ቀብር ወጪ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለበት ሰው ለዚህ ለተባለው ለሰው ሥርዓተ ቀብር የወጣውንም ወጪ ለመክፈል ይገደዳል ይህን ወጪ ያደረገው ሰው ወጪውን እንዲተካለት ቀለብ ሰጪውን ለመጠየቅ ይችላል አንቀ ዩ ስምምነቶ ልዩ ስምምነቶችን በማድረግ በዚህ ምዕራፍ የተጻፉትን ድንጋጌዎች ለመለወጥ አይፈቀድም ምዕራፍ አሥራ ሁለት አካለ መጠን ስላልደረሱ ሰዎች ክፍል ጠቅላላ ድንጋጌዎች አንቀጽ ትርጓሜ አካለ መጠን ያልደረሰ ሰው ማለት ጾታ ሳይለይ ዕድሜው አሥራ ስምንት ዓመት ያልሞላው ሰው ነው አንቀጽ ለ መጠን ያልደረሰ ሎ ለው ስለመሆኑ አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ ስለመልካም አስተዳደጉና ደህንነቱ ጉዳይ በአንድ አሳዳሪው እየተጠበቀ ይቆያል ንብረት ነክ ጥቅሞቹንና በአጠቃላይ የንብረቱን አስተዳደር በሚመለከት በሞግዚቱ ይወከላል በሕግ በግልጽ ለተመለከቱ ጉዳዮች ካልሆነ በስተቀር አካለ መጠን ያልደረሰ ሰው ሕጋዊ ድርጊቶችን ለመፈፀም አይችልም አንቀጽ የዕድሜ ማስረጃ የአንድ ሰው ዕድሜ የሚረጋገጠው በልደት ምስክር ወረቀት ነው የልደት ምስክር ወረቀት የሌለ እንደሆነ ዕድሜውን በአስተማማኝነት ለማረጋገጥ ያስችላሉ በሚባሉ ሰነዶች ወይም ከሁለት ያላነሱ ምስክሮችን ቃል መሠረት በማድረግ ፍርድ ቤት ዕድሜውን ይወስናል አንቀጽ ውሳኔ ሰጪ አካላት መከተል ስላለባቸው መርህ በዚህ ምዕራፍ መሠረት በሚቀርቡ ጉዳዮች ላይ የሚሰጡ ውሳኔዎች ሁሉ ለልጆች ደህንነትና መልካም አስተዳደግ የሚበጁ መሆን ይኖርባቸዋል ልን መ ረሰን ልጅ ስለ ቁ ተቋሞ አንቀጽ የወላጆች ሥልጣን አባትና እናት ጋብቻቸው ንቶ ባለበት ጊዜ ሁሉ አካለመጠን ላለደረሱት ልጆቻቸው የአሳዳሪነትና የሞግዚትነት የጋራ ሥልጣን ይኖራቸዋል አንቀጽ ከወላጆቹ አንዱ ብቁ አለመሆን ከወላጆቹ አንዱ የሞተ ችሎታ ያጣ የተገቢነት መብት ያጣ ወይም የቤተሰብ አስተዳዳሪነት መብቱ የታገደ እንደሆነ የአሳዳሪነትና ሞግዚትነት ሥልጣኑን ይዞ የሚቆየው አንደኛው ወገን ብቻ ይሆናል አንዲሁም የልጁ አባት ያልታወቀ በሆነ ጊዜ የዚህን ሥልጣን ሥራ የምትፈፅመው እናቱ ብቻ ትሆናለች አንቀጽ የልጁ አባትና እናት መፋታት በዚህ ሕግ አንቀጽ መሠረት ባልና ሚስት በስምምነት ሲፋቱ የልጆቻቸውን አሳዳሪነትና ሞግዚትነት በተመለከተ በስምምነት ይወስናሉ በማናቸውም የፍቺ ሁኔታ የልጆቻቸውን አሳዳሪነትና ሞግዚትነት ባልና ሚስቱ በስምምነት ሊወስኑ ካልቻሉ ፍቺውን የወሰነው ፍርድ ቤት ስለልጆቹ አሳዳሪና ሞግዚትም አብሮ ይወስናል አን የተመ ወ ሞግዚት መሠ አካለ መጠን ያልደረሰው ልጅ በህይወት ያለው ወላጅ ከጊዜ ሞቱ በኋላ ልጁን የሚያስተዳድር ወይም ለልጁ ሞግዚት የሚሆነውን ሰው በመጨረሻ የኑዛዜ ቃል ለመምረጥ ይችላል እንዲሁም የአሳዳሪውን ወይም የሞግዚቱን ሥልጣን ለመወሰንና የአሳዳጊነቱን የሥራ አመራር ሥልጣን በተወሰነ ሁኔታ ብቻ ለመስጠት ይችላል አንቀጽ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት ለመሾም የሚፈፀም ግዴታ አባት ወይም እናት በህይወት ሳለ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ የአሳዳሪነት ወይም ሞግዚትነት ሥራ ያካሂድ የነበረ ካልሆነና በዚሁም ጊዜ በገዛ ፈቃድ ሥልጣኑን አውቆ የተወ ከልሆነ በስተቀር በዚህ ሕግ አንቀጽ ለአባት ወይም ለእናት የተሰጠውን መብት አይኖረውም አንቀጽ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ስለማቅረብ አካለ መጠን ያልደረሰው ልጅ ጥቅም የሚያስገድድ ሆኖ የተገኘ አንደሆነ ስለ አሳዳሪው ወይም ስለሞግዚቱ አባቱ ያደረጉትን ውሳኔ ፍርድ ቤት ሊሽረው ወይም ሊያሻሸለው ይችላል አንቀጽ የልጅን አሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥልጣን ሊይዙ የሚገባቸው ዘመዶች ሊከተሉት የሚገባ ቅደም ተከተል አንድ ልጅ አባትና እናት የሌለው እንደሆነና ከሁለቱ በመጨረሻ የሞተው ወላጅ በሚገባ ሁኔታ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት ሳያደርግለት ቀርቶ እንደሆነ ለልጁ አሳዳሪነት ወይም ሞግዚትነት በሕጉ መሠረት የሚመረጡና ይህ ሥልጣን የሚሰጣቸው በዚህ ቀጥሎ የተመለከቱት ሰዎች ናቸው ሀ የልጁ ወደ ላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ሊለ እነዚህ በሌሉ ጊዜ አካለመጠን የደረሱ የልጁ ወንድሞች ወይም እህቶች ሒ እነዚህ በሌሉ ጊዜ የልጁ አጎት ወይም አክስት አንቀጽ ይህ ቅደም ተከተል ስለሚለወጥበት ሁኔታ ከዚህ በላይ በተመለከተው መሠረት ሥልጣን በሚሰጠው ሰው ምትክ ለልጁ የሥጋ ዝምድና ወይም የጋብቻ ዝምድና ያለው ማንኛውም ሰው የአሳዳሪነቱ ወይም የሞግዚትነቱ ሥልጣን ይሰጠኝ ሲል ጥያቄ ለማቅረብ ይችላል ይህም ጥያቄ መቅረብ የሚገባው ቅደም ተከተሉ ለሚመለከታቸው ዘመዶች ሲሆን ስምምነት ካልተገኘ ግን ጉዳዩ ለፍርድ ቤት ይቀርባል ጥያቄው መቅረብ ያለበት አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ ይህን ሥልጣን መያዙ ከታወቀበት ቀን ጀምሮ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ይሆናል ፈ ጥያቄውን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል መሠረት የሚሆነው የልጁ ደህንነትና ጥቅም ሊሆን ይገባል አንቀጽ በሕግ የሚመረጡ ዘመዶች መታጣት ከዚህ በላይ ባሉት አንቀጾች የተመለከተውን መሠረት በማድረግ በልጁ አንድ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት ለማግኘት ያልተቻለ አንደሆነ ይህ ሥራና ሥልጣን ፍርድ ቤት ለመረጠው ሰው ሊሰጥ ይችላል ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ ለመወሰን የልጁ ዘመድ በሆነ ወይም ባልሆነ ያገባኛል ባይ በሚቀርብ ጥያቄ ሊመሰረት ይችላል የህፃናትን ደህንነት ለመከታተል ሥልጣን የተሰጠው የመንግሥት አካልም ጉዳዩን ለፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል አንቀጽ የፍርድ ቤት ምርጫ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ የሥጋ ወዉ ብቻ ዘመዶች ፍርድ ቤት ለልጁ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት እንዲሆን የሚመርጠውና ይህን ሥልጠን የሚሰጠው የልጁ የቅርብ የሥጋ ዘመድ የሆነን ወይም የጋብቻ ዝምድና ያለውንና በተቻለም መጠን ይህን ሥራ ለማከናወን ችሎታና ፈቃደኛነት ያለውን ሰው ነው አንቀጽ የበጐ አድራጐት ድርጅት ፍርድ ቤቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነቱን ሥልጣን ለዚህ ዓይነት ጉዳይ ለተቋቋመ የበጐ አድራጎት ድርጅት ሊሰጥ ይችላል አንቀጽ ተመሳሳይ ሁኔታዎች ከዚህ በላይ ለተዓፋት ድንጋጌዎች አፈፃፀም አንድ ሰው በሕግ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ተግባሮችን ለማከናወን የማይችል እንደሆነ እንደሌለ ይቆጠራል አንቀጽ የአሳዳሪው ወይም የሞግዚቱ መታወቂያ በመሠረቱ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ አሳዳሪ እንዲሆን ሥልጣን ተሰጥቶት የልጁን አሳዳሪነት የተቀበለው ሰው ሞግዚቱም ነው የነገሩ ሁኔታ ተቃራኒ ትርጉም የሚያሰጥ ካልሆነ በስተቀር በህይወት ያለው አባት ወይም እናት ወይም ፍርድ ቤት ለልጁ የሚሾሙት ሞግዚት ወይም አሳዳሪ ሁለቱንም ሥልጣን እንደያዘ ይቆጠራል አንቀጽ ለአባትና ለእናት የተሰጠ መብት አባት ወይም እናት ጉዳዩ ጠቃሚ መስሎ የታያቸው እንደሆነ የልጃቸውን የአሳዳሪነት ሥልጣን ራሳቸው ይዘው ሞግዚት ለመሾም ይችላሉ አንቀጽ ለፍርድ ቤት የተሰጠ ሥልጣን ፍርድ ቤት የልጁን አሳዳሪና ሞግዚት የመሾም ሥልጣን በያዘበት ጊዜና ይህን ለማድረግ አሳማኝ ምክንያት ሲኖር ከአሳዳሪው በተጨማሪ ሌላ ሞግዚት ለመሾም ይችላል አንቀጽ ምትክ ሞግዚት በሞግዚቱና አካለመጠን ባልደረሰው ልጅመ ስለሚነሳ የጥቅም ግጭት በሞግዚቱና አካለመጠን ባልደረሰው ልጅ መካከል የጥቅም ግጭት የተነሳ እንደሆነ ፍርድ ቤት አካለመጠን ላልደረሰው ልድ ምትክ ሞግዚት ይሾምለታል ምትክ ሞግዚት የሚመረጠው በሞግዚቱ ወይም ወደ ላይ ከሚቆጠሩ የልጁ ወላጆች ወይም አካለመጠን ከደረሱ ወንድሞቹና እህቶቹ በአንዳቸው ጥያቄ አቅራቢነት ነው አንቀጽ አካለመጠን ባልደረሱ በብዙ ልጆች መካከል ስለሚነሳ የጥቅም ግጭት አካለመጠን ባልደረሱ በብዙ ልጆች መካከል የጥቅም ግጭት የተፈጠረ እንደሆነና የነዚህም ተጠሪ ወኪል አንድ የጋራ ሞግዚት ብቻ በሆነ ጊዜ ከዚህ በላይ የተመለከተው ድንጋጌ ተፈዓሚ ይሆናልአንቀጽ የጥቅም ግጭቱ የሚፈታውም በሞግዚቱና በምትክ ሞግዚት መካከል በሚደረግ ስምምነት መሠረት ይሆናል አንቀጽ የሥራ አጀማመር የአሳዳሪነቱ ወይም የሞግዚትነቱ ሥራ የሚጀመረው አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ በሕጉ መሠረት ወይም በፍርድ ውሳኔ ተመርጠው እንደተሾሙ ወዲያውኑ ነው ሆኖም የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥራ የተሰጠው መሆኑን ከማወቁ በፊት አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ ይህን ሥራውን ሳይጀምር ለደረሰው ጉዳት ሁሉ በኃላፊነት ሊጠየቅ አይችልም አንቀጽ ሥራው የግዴታ ስለመሆኑ የአሳዳሪነትን ወይም የሞግዚትነትን ሥራዎች እንዲያከናውን ተመርጦ የተሾመው ሰው ሥራውን የማከናወን ግዴታ አለበት አንቀጽ ሥራው እንዲቀርለት የሚቀርብ ጥያቄ አንድ ሰው የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ተግባርን ማከናወን በራሱ ላይ ከበድ ያሉ ችግሮችን በአጠቃላይ ኑሮውም ላይ እንቅፋት የሚያስከትልበት ከሆነ ሥራው እንዲቀርለት ፍርድ ቤትን ሊጠይቅ ይችላል እንዲሁም በተመሳሳይ ሁኔታ አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ ከተሰጠው የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥራው እንዲሻር ጥያቄ ማቅረብ ይችላል አንቀጽ ሥራው እንዲቀርለት በሕግ አግባብ የሚሰጥ ልዩ እስ ። ተ ያየ በዚህ ሕግ መሠረት ለአሳዳሪነት ወይም ለሞግዚትነት ስለሚመረጡ ሰዎች የተደነገገው ቢኖርም ከዚህ የሚከተሉት ሰዎች በአሳዳሪነት ወይም በሞግዚትነት እንዳይሾሙ ወይም እንዲሻሩ ጥያቄ ካቀረቡና ይህም ጥያቄ የራሳቸውን ልጆች የሚመለከት ካልሆነ በስተቀር የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥራ እንዲሰሩ አይገደዱም ሀ ዕድሜው ስድሳ አምስት ዓመት የሞላው ሰው ሊለ በውትድርና የተሰማሩ ሰዎቹች አንቀጽ ለጊዜው ሥራውን የማከናወን ግዴታ የልጁ አሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥራ ችግር ያደርስብኛል ብሎ ምክንያት በማቅረብ ይህ ኃላፊነት እንዲወገድለት የሚጠይቅ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት በዚህ ሥራ ሌላ አሳዳሪ ወይም ሞጊዚት ተወክሎ ሥልጣኑን እስከሚረከብ ድረስ የተሰጠውን ሥራ ለጊዜው የማከናወን ግዴታ አለበት እንዲሁም በሹመቱ ላይ ተቃውሞ የተነሳበት አሳዳሪ ወይም ሞግዚትም ተመሳሳይ ግዴታ ይኖርበታል አንቀጽ ስለ ሥራው መቅረት የአሳዳሪው ወይም የሞግዚቱ ሥራ ቀሪ የሚሆነው የሚጠበቀው ልጅ የሞተ እንደሆነ ወይም አካለመጠን በደረሰ ጊዜ ወይም ከሞግዚት አስተዳዳር ነፃ በወጣ ጊዜ ነው እንዲሁም አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ ሲሞት ወይም ችሎታ ሲያጣ ወይም ብቁ ያለመሆኑ ሲገለጽ ወይም ከሥራው ሲሻር ቀሪ ይሆናል አዲስ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ ሲሾምለትም የቀድሞዎቹ ተጂሚዎችኃላፊነት ያበቃል አንቀጽ ሎታ ማጣተ አካለመ ሰልጅ የራሱን ልጆች በሚመለከት ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ የአሳዳሪነት ወይም ሞግዚትነት ሥራን ለማካሄድ ችሎታ የለውም አንቀጽ በፍርድ የተከለከሉ በፍርድ የተከለከለ ማንኛውም ሰው የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥራን ለማከናወን አይችልም ይህን ሥራ ያከናውን የነበረ አንድ ሰው ችሎታ ያጣ መሆኑ በፍርድ ቤት ውሳኔ የተገለጸ እንደሆነ የዚህ ሰው ሞግዚት በሕግ መሠረት የተከለከለውን ሰው ሥራ ተረክቦ በምትክነት ማካሄድ ለሚገባው ሰው ወዲያውኑ ማስታወቅ አለበት እንዲህ ያለ ሰው የሌለም እንደሆነ በፍርድ የተከለከለው ሰው ምትክ እንዲደረግለት ሞግዚቱ ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረብ አለበት አንቀጽ ብቁ ስላለመሆን አንድ ሰው የአሳዳሪነት ወይም የሞግዚትነት ሥራን ለማካሄድ ብቁ አይደለም ብሎ ፍርድ ቤት ለመወሰን የሚችለው የወንጀል ተግባር በመፈጸሙ የግል ነፃነትን የሚከለከል የእስራት ወይም የሞት ቅጣት የተፈረደበት ሲሆን ነው ፍርድ ቤት የዚህን ዓይነት ቅጣት በአንድ ሰው ላይ በሚወስንበት ጊዜ ነገሩ ተገቢ መሆኑን የገመተ እንደሆነ የተፈረደበት ሰው ለዚህ ሥራ ብቁ አለመሆኑን ጭምር ለመወሰን ይችላል አንቀጽ የአሳዳሪው መሻር አካለመጠን ላልደረሰ ልጅ አሳዳሪው እንዲሆን የተሾመ ሰው ልጁ ለኑሮው አስፈላጊ የሆነውን ጥበቃ ሳያገኝ ወይም ከሞራል ጋር የሚስማማ የአእምሮ አስተዳደግ ወይም ከችሎታው ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ትምህርት እንዲያገኝ ሳያደርግለት የቀረ እንደሆነ አሳዳሪው እንዲሻር ፍርድ ቤት ሊወስን ይችላል ይህንንም ውሳኔ ለመስጠት አሳዳሪው የሚኖርበትን የአካባቢ ሁኔታና ጊዜውንም መመርመርና መሠረት ማድረግ አስፈላጊ ነው በተለይም ፍርድ ቤቱ አሳዳሪውን ለመሻር የሚችለው አካለ መጠን ያልደረሰው ልጅ ወንጀል መስራቱ የተረጋገጠ ሲሆንና ይህንንም ወንጀል የፈፀመው በመጥፎ አስተዳደግ ወይም በአሳዳሪው ጉድለት ተገቢውን የግብረ ገብ ትምህርት ለማግኘት ካለመቻሉ የሆነ እንደሆነ ነው አንቀጽ የሞግዚት መሻር አካለመጠን ላልደረሰ ልጅ ሞግዚት የሆነ ሰው እንዲሻር ፍርድ ቤት የሚወስነው ሞግዚቱ የልጁን ንብረትና ሀብት በመጥፎ ሁኔታ ያስተዳደረና አጠባበቁም በቂ ያልሆነ እንደሆነ ወይም ልጁን በሞግዚትነት እንዲያስተዳድር ሥልጣን የሰጠው ሰው ወይም አካል የሰጠውን መመሪያና የንብረት አስተዳደር ሥርዓት ሳይጠብቅና ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ ወይም ዕዳ ለመክፈል ያለመቻሉ በፍርድ ውሳኔ የተረጋገጠ እንደሆነ ነው አንቀጽ የወላጆች መሻር የልጁ አባት ወይም እናት ወይም ሌሎች ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆቹ ከልጃቸው አሳዳሪነት ወይም ሞግዚ ትነት ስራቸው እንዲሻሩ መወሰን ሲያስፈልግ ፍርድ ቤቱ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅበታል ፍርድ ቤቱ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠውን ውሳኔ በቲሻረው ወገን ጠያቂነት በማንኛውም ጊዜ እንደገና ሊመረምረው ይችላል ንቀጽ ሥነ ሥርዓት አንድ አሳዳሪ ወይም ሞግዚት እንዲሻር የሚቀርበው ጥያቄ በማናቸውም በጉዳዩ ያገባኛል ባይ ወገን ወይም በዐቃቤ ሕግ በኩል ሊቀርብ ይችላል ፍርድ ቤቱ አሳዳሪውን ወይም ሞግዚቱን በመሻር ከመወሰኑ በፊት በርሱ በኩል ያለውን ሀሳብ ሊያዳምጠው ይገባል ሆኖም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተውን ሲያከናውን በልጁ ደህንነት ወይም ሀብት ላይ ተጨማሪ ጉዳት ይደርሳል ተብሎ የሚገመት ከሆነ ፍርድ ቤቱ ተገቢ መስሎ የታየውን ጊዜያዊ ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል አንቀጽ የፍርድ ቤት ኃላፊነት ፍርድ ቤት አንድን ሰው አካለመጠን ላልደረሰ ልጅ አሳዳሪነት ወይም ሞግዚትነት ለመሾም ሲመርጥ ወይም የተሾመውን ከሥራው ሲሽር ከውሳኔው በፊት በተቻለ መጠን ከልጁ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች አካለመጠን የደረሱ ወንድሞቹና እህቶቹን ሀሳብ ሊያዳምጥ ይችላል አስፈላጊ መስሎ ሲታየው አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ያለውን ሀሳብ ሊያዳምጥ ይችላል ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ሲሰጥ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ጥቅም የማይጓደልበትን አሠራር ብቻ መከተል እንጂ የቀረቡለትን ሀሳቦች የመቀበል ግዴታ አይኖርበትም አንቀጽ ሥራው ያለ ክፍያ የሚከናወን ስለመሆኑ የአሳዳሪነትና የሞግዚትነት ሥራ የሚከናወነው ማናቸ ውም ዋጋ ሳይከፈልበት በነፃ ነው ሆኖም አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ ሥራውን ለማከናወን ረጅም ጊዜ የሚጠይቀው የሆነ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ አንድ የተወሰነ አበል ሊቆረጥለት ይችላል ይህም አበል አካለመጠን ካልደረሰው ልጅ የሀብት ገቢ ላይ ካልሆነ በስተቀር ከሌላ ሀብት ሊወሰድ አይችልም የአበሉም ልክ ከጠቅላላው የሀብት ገቢ ሲሶ ሊበልጥ አይችልም አንቀጽ የሥራው አካፄድ የግል ስለመሆኑ ጽ የአሳዳሪነቱ ወይም የሞግዚትነቱ ሥራ የግል ጠባይ የያዘ ስለሆነ ሥራውን የሚያከናውነው ራሱ እንጂ ለአሳዳሪው ወይም ለሞግዚቱ ወራሾች ሊተላለፍ አይችልም ወራሾቹ በኃላፊነት የሚጠየቁት አሳዳሪው ወይም ሞግዚቱ በፈፀመው የሥራ አካፄድ ጉድለት ብቻ ነው። አንቀጽ የመክፈያ ጊዜያቸው ያልደረሱ ገቢዎች የመክፈያ ጊዜያቸው ያልደረሱ ገቢዎችን አሳዳሪው ግዴታ ሊገባባቸው አይችልም አንቀጽ ስለወላጆች ሥልጣን አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ አባትና እናት በጋራ አሳዳሪዎቹ በሆኑ ጊዜ የአሳዳሪነት ተግባራቸውን በመመካከርና በመግባባት ይወጣሉ አባት እና አናት ያለመግባባታቸውን በግላቸው ወይም በሽምግልና ለመፍታት ያልቻሉ እንደሆነ ከሁለቱ አንደኛው በሚያቀርበው አቤቱታ መነሻነት ፍርድ ቤቱ አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት ውሳኔ ይሰጣል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ አባትና እናት በአሳዳሪነታቸው በሚሰጡት ውሳኔ ላይ አቤቱታ ሊቀርብበት አይችልም አንቀጽ የወላጆች መለያየት ወላጆች በመለያየታቸው ምክንያት የአሳዳሪነቱ ስልጣን የአንደኛው ወላጅ ብቻ የሆነ እንደሆነ ይኸው ወላጅ በሚሰጠው ውሳኔ ላይ የአሳዳሪነት ተግባር በማከናወን ላይ የሌለው ወገን ወደሳይ የሚቀጠሩ ወላጆቹ ወይም አካለመጠን ከደረሱ ወንድሞቹና እህቶቹ አንዳቸው አቤቱታ ለፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላሉ አንቀጽ አሳዳሪው አካለመጠን ደረሰው ወላጅ በማይሆንበት ጊዜ አሳዳሪው አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ወላጅ ያልሆነ እንደሆነ በልጁ አስተዳደግ ረገድ በሚሰጠው ውሳኔ ላይ ከወላጆቹ አንዳቸው ወይም ሌላ በጉዳዩ ያገባኛል የሚል ሰው ወይም ዐቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ሊያቀርብ ይችላል ንዑስ ክፍል አካለመጠን ያልደረሰን ልጅ ንብረት ስለማስተዳደር አንቀጽ መሠረቱ ሀብቱንና ንብረት ነክ ጥቅሞቹን በተመለከተ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ በሞግዚቱ ይወከላል ሀብቱንና ንብረት ነክ ጥቅሞቹን በማስከበርና በማስተዳደር ረገድ ሞግዚቱ ከፍተኛ ጥንቃቄ የማድረግ ግዴታ አለበት አንቀጽ የንብረት ቆጠራና የዋጋ ግምት ሞግዚቱ የሞግዚትነት ሥራውን ከጀመረ በኋላ ሞግዚቱ የሞግዚትነቱን ሥራ ከጀመረ በኋላ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ሦስት ምስክሮች ባሉበት አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ንብረት ይቆጥራል የዋጋውንም ግምት ያወጣል ሞግዚቱ አካለመጠን ካልደረሰው ልጅ የሚጠይቀው ዕዳ ሲኖር በንብረት ቆጠራው መዝገብ በወቅቱ ካላሰፈረው በስተቀር የዕዳው ክፍያ ቀሪ ይሆንበታል አንቀጽ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ የውርስ ሀብት አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ወራሽ በሚሆንበት ጊዜ ሞግዚቱ ስለልጁ ሆኖ ወርሱን ከመቀበሉ አስቀድሞ ሶስት ምስክሮች ባሉበት የውርስ ንብረቱን ቆጠራ ያከናውናል የዋጋውንም ግምት ያወጣል ሞግዚቱ ከውርሱ ሀብት ውስጥ ድርሻ ያለው እንደሆነ ይህንኑ በንብረት ቆጠራው መዝገብ ያላሰፈረው እንደሆነ ድርሻው ቀሪ ይሆንበታል የንብረት ቆጠራው ባለመከናወኑ ወይም በአግባቡ ባለመሠራቱ ለሚደርስ ጉዳት ሞግዚቱ በኃላፊነት ይጠ የቅበታል አንቀጽ የሞግዚቱ ንብረት አካለመጠን ካልደረሰው ልጅ ንብረት ጋር ስለሚቀላቀልበት ሁኔታ ሞግዚቱ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ንብረት ከግል ንብረቱ ጋር እንዳይቀላቀል አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሁሉ ማድረግ አለበት በተለይም አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ገንዘብ ሞግዚቱ በራሱ የባንክ ሂሣብ ማስቀመጥ ወይም እንዲቀ መጥ ማድረግ አይፈቀድለትም አንቀጽ የገንዘብ ሰነዶችና ች ውድ መጡበት ሁኔታ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ንብረት በማስተዳደር ረገድ ችግር የሚፈጥር ካልሆነ በስተቀር የገንዘብ ሰነዶችን ውድ ዕቃዎችን ጠቃሚ ጽሑፎችንና ሌሎች ተመሳሳይ ነገሮችን ሁሉ ሞግዚቱ ሊጠፉ ወይም ሊባክኑ በማይችሉበት አስተማማኝ ሥፍራ ማስቀመጥ አለበት አንቀጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ሞግዚቱ የልጁ ወላጅ ባልሆነ ጊዜ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ሀብት መልካም አስተዳደር በሚመለከት ለሞግዚቱ መመሪያ እንዲሰጥ የልጁ ወደላይ ከሚቆጠሩ ወላጆች ወይም አካለመጠን ከደረሱ ወንድሞቹ ወይም እህቶቹ አንዳቸው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ ፍርድ ቤቁም አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ሀብት አጠቃላይ ሁኔታ የሞግዚቱን ችሎታና የልጅየውን ጥቅም በማመዛዘን ስለሀብቱ አስተዳደር ጠቃሚ መስሎ የሚታየውን መመሪያ ይሰጠዋል አንቀጽ መጠን ላልደረሰው ልጅ በ ም በውርስ ስለሚተላለፍ ንብረት አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ በስጦታ ወይም በውርስ ንብረት የሚያስተላልፍ ሰው የንብረቱን አስተዳደር በሚመለከት ተገቢ ናቸው የሚላቸውን የአሠራር መመሪያዎች ሞግዚቱ እንዲክተል ሊያዝ ይችላል የአሠራር መመሪያዎቹን ተከትሎ ለመስራት የማይቻል ወይም አካለመጠን ባልደረሰው ልጅ ጥቅም ላይ ጉዳት የሚያደርስበት መስሎ የታየው እንደሆነ ሞግዚቱ መሪያዎቹ እንዲስተካከሉለት ፍርድ ቤትን ሊጠይቅ ይችላል አንቀጽ ስለንግድ ድ ሌሎች መሰል ድርጅቶ የንግድ የኢንዱስትሪ ወይም ሌሎች መሰል ድርጅቶች አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ሀብት አካል የሆኑ እንደሆነ ወደላይ ከሚቆጠሩ ወላጆቹ ወይም አካለመጠን ከደረሱ ወንድሞቹና እህቶቹ አንዳቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ የልጁ አባት ወይም እናት ያልሆነው ሞግዚት ንብረቱን እንዲያጣራ ወይም እንዳለ እንዲቀጥል እንዲያደርግ ፍርድ ቤት ሊያዘው ይችላል ፍርድ ቤቱ ይህንን ትእዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ ሞግዚትነቱ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ የሞግዚቱን ችሎታና አካለ መጠን ያልደረሰውን ልጅ ጥቅም ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት አንቀጽ አንዳንድ ንብረቶችን ስለመሸጥ ሞግዚቱ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ንብረት የሆኑ የሚንቀሳቀሱ ግዙፍ ንብረቶችን አክስዮኖችንና የገንዘብ ሰነዶችን ለመሸጥ ይችላል በልጁ አባት ወይም እናት ላይ ካልሆነ በስተቀር በጉዳዩ ያገባኛል የሚል ማንኛውም ሰው ጥያቄ ሲያቀርብለት ፍርድ ቤት ስለሺሽያጩ መመሪያ ለመስጠት ወይም ሽያጩ እንዳይካሄድ ለመከልከል ይችላል ለአምጪው ከፈል ስለሚሉ ሰነዶች አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ አባት ወይም እናት ያልሆነ ሞግዚት ለአምጪው እንዲከፈል የሚሉ ሰነዶች የልጁ ሀብት ከሆኑበት ጊዜ ጀምሮ በሶስት ወራት ውስጥ እንዲሸጡ ወይም በልጁ ስም በተመዘገቡ ሰነዶች እንዲለወጡ ማድረግ አለበት ሞግዚቱ ጥያቄ ሲያቀርብለት ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ከተመለከተው ግዴታ ነፃ እንዲሆን ሊያዝ ይችላል አንቀጽ ዕዳዎችና ገቢ ገንዘቦች ሞግዚቱ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ዕዳዎች ከልጁ ሀብት በመቀነስ ይከፍላል አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ መክፈል የሚገባውን ካፒታል እና ሌላ ገቢ ይቀበልለታል ስለመቀበሉ በማረጋገጥም ደረሰኝ ይሰጣል አንቀጽ ካፒታልን አትራፊ በሆነ ሥራ ላይ ስለማዋል የሞግዚቱ ግዴታ የገንዘቡ መጠን ከ ብር በላይ የሆነ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ካፒታል ሞግዚቱ አትራፊ በሆነ ሥራ ላይ ማዋል አለበት ፍርድ ቤት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተውን የገንዘብ መጠን ሊያሻሽለው ይችላል አንቀጽ የጊዜ ገደብ ካፒታሉ በሞግዚቱ እጅ በገባ በሶስት ወራት ውስጥ በአትራፊ ሥራ ላይ መዋል አለበት ፍርድ ቤቱ የጊዜውን መጠን ሊያሻሸለው ይችላል አንቀጽ ኃላፊነት በአትራፊ ሥራ ላይ ላላዋለው ገንዘብ ሞግዚቱ ሕጋዊ ወለዱን አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ መክፈል አለበት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ተጨማሪ የጉዳት ካሣ እንዲከፍል ሊፈረድበት ይችላል አንቀጽ ገቢዎች አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ገቢዎች ገቢዎቹ በቂ ሆነው የማይገኙ ሲሆንም ከሀብቱ ቀንሶ ለአስተዳደጉና ለትምህርቱ አገልግሎት እንዲውል ሞግዚቱ ለአሳ ዳሪው ይሰጠዋል ፍርድ ቤቱ በሌላ አኳኋን ካልወሰነ በስተቀር ለዚህ አገልግሎት የሚውለው ገንዘብ በየወሩ ለአሳዳሪው ይከፈላል የአከፋፈሉ ሁኔታ በአሳዳሪውና በሞግዚቱ ስምምነት ወይም በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔ መሠረት ሊሻሻል ይችላል የኪራይ ውሎ በፍርድ ቤት ፈቃድ የተደረጉ ካልሆነ በስተቀር ሞግዚቱ የሚያደርጋቸውን የኪራይ ውሎች ልጅየው አካለመጠን አደረሰ ከሶስት ዓመታት በኋላ እንዲፈጽማቸው አይገደድም አንቀጽ ስለውርስ ልጁ በውርስ የሚያገኘው ንብረት ሞግዚቱ ይቀበላል ሞግዚቱ የውርሱ ሀብት ዕዳውን ለመክፈል ፈጽሞ የማይችል ካልሆነ በስተቀር ውርሱን አልፈልግም ለማለት አይችልም አንቀጽ ስለ ስጦታ አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ የሚሰጠው ስጦታ ጠቃሚነት የለውም በማለት ካልሆነ በስተቀር ሞግዚት አል ቀበልም ለማለት አይችልም ጩ በተለምዶ ከሚሰጡ አነስተኛ ስጦታዎች ውጪ ሞግዚቱ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ንብረት በልጁ ስም በስጦታ ለመስጠት አይችልም አንቀጽ የዋስትና ግዴታ መግባት የማይቻል ስለመሆኑ ሞግዚቱ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ንብረት ለሌላ ሰው ዕዳ በዋስትና ሊያሲዝ አይችልም አንቀጽ ስለ ግልግል ክርክር የሚደረግበት ጥቅም ከ ሺህ ብር ያነሰ ካልሆነ ወይም አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ጥቅም በሚመለከት ፍርድ ቤት ካልፈቀደ በስተቀር ሞግዚቱ ጉዳዩን በግልግል ለመጨረስ አይችልም ንቀጽ ሞግ ካለመጠን ው ስለሚያደ ው ውሎች ሞግዚቱ ፍርድ ቤት ካልፈቀደለት በስተር አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ንብረት ለመግዛት በኪራይ ለመጠ ቀም ወይም ሌላ ማናቸውንም ውል ከእርሱ ጋር ለመፈፀም አይችልም እንዲሁም ሞግዚቱ በፍርድ ቤት ካልተፈቀደለት በስተቀር አካለመጠን ባልደረሰው ልጅ ላይ ማናቸውንም መብት ወይም ገንዘብ የሚጠይቅበትን መብት ለመቀበል አይችልም አንቀጽ ስለብድር ፍርድ ቤት ካልፈቀደ በስተቀር ሞግዚቱ አካለመጠን ባልደረሰው ልጅ ስም የብድር ውል ለመዋዋል አይችልም ንቀጽ አካለመ ካልደረሰው ል መመካ ስፈለጉ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ዕድሜ ከ ዓመት ያነሰ ካልሆነ በስተቀር ሞግዚቱ የልጁ ዕድሜ በሚፈቅድለት መጠንና እርሱን የሚመለከቱ ከፍተኛ ጉዳዮች በተነሱ ጊዜ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ማማከር አለበት አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ፈቃዱን መስጠቱ ሞግዚቱን ከተጠያቂነት አያድነውም ሞግዚቱ መጠን ልጅ እንዲሠ ስለሚሰጠው ፈቃድ መሠረቱ ና ። አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ዕድሜና የገንዘብ አቅም መሠረት በማድረግ የፅለት ጉዳዮችን የሚመለከቱ ውሎችን ብቻ እንዲያደርግ ሞግዚቱ ፈቃድ ሲሰጠው ይችላል ይኸው ፈቃድ በዝምታም ሲሰጥ ይችላል አንቀጽ የፅለት ጉዳዮች ድርጊቱ እንዲፈፀም የፍርድ ቤት ፈቃድ የሚያስፈልገው አንደሆነ በምንም መንገድ የፅለት ጉዳይ ሊባል አይችልም አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ከ ብር በላይ ግዴታ እንዲገባ የሚያስገድደው ሲሆን ድርጊቱ የዕለት ጉዳይ ነው ሊባል አይችልም አንቀጽ ላይ ስለ ውው አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ በሞግዚቱ ፈቃድ ለሚገባቸው ግዴታዎች ሞግዚቱ ለሶስተኛ ወገኖች ዋስ ነው አንቀጽ ኑዛዜ ሞግዚቱ አካለመጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ዓመት ሳይሞላው ትዛዜ ማድረግ አይችልም አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ዓመት ሳይሞላው የሚያደርገው ኑዛዜ ዓመት ከሞላው በኋላ ባይሰርዘውም ውጤት አይኖረውም ንቀጽ ማስተ ለ ሞግዚቱ አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ ጥቅም ሷል ከግሉ የሚያወጣቸው ወጪዎች እንዲተኩለት መብት አለው አንቀጽ አካለመጠ ሰው ልጅ ሀብት አስተዳደ ርት ማቅረብ ያለበት ስለመሆኑ ሞግዚቱ አካለመጠን ያልደረሰውን ልጅ ሀብት አስተዳደር ሁኔታና ሂዊሣቡን የሚያመለከት ሪፖርት አዘጋጅቶ መያዝ አለበት አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ወደላይ የሚቆጠሩ ወላጆች ወይም አካለመጠን የደረሱ ወንድሞቹና እህቶቹ በጋራ ወይም በተናጠል ጥያቄ ሲያቀርቡለት ሞግዚቱ የአስተዳደርና የሂሳብ ሪፖርቱን እንዲመለከቱት ያደ ርጋል አንቀጽ ተፈፃሚነት በዚህ ህግ ከአንቀጽ እስከ የተመለከቱት ድንጋጌዎች ለሞግዚትም ተፈፃሚነት ይኖራቸዋል ክፍል አካለመጠን ያልደረሰን ልጅ ለመጠበቅ የተመለከቱትን ደንቦች መጣስ ስለሚያስከትለው ውጤት ንዑስ ክፍል አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ ሥራዎች አንቀጽ መሠረቱ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ከሥልጣኑ በላይ የሚፈጽማቸው ሕጋዊ ድርጊቶች ሁሉ ፈራሽ ይሆናል አንቀጽ መ አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ የፈፀማቸው ሕጋዊ ድርጊቶች እንዲፈርሱ መጠየቅ የሚችሉት አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ወይም ወራሾቹ ወይም ወኪሎቹ ናቸው አንቀጽ ስለተዋዋዩ ቅን ልቦና በዚህ ሕግ አንቀጽ የተደነገገው ቢኖርም ሌላው ተዋዋይ ወገን ከልጁ ጋር የተዋዋለው ይህንን እንዲ ያደርግ ፈቃድ አለው ብሎ በቅን ልቦና በማመን የሆነ እንደሆነ ውሉ የፀና ይሆናል ሌላው ተዋዋይ በልጁ አላዋቁነት የተጠቀመ ከሆነ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተደነገገው ተፈፃሚነት አይኖረውም አንቀጽ ስለሚመለስ ገንዘብ አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ የተከፈለ ገንዘብ ሊመለስ የሚችለው ውሉ እንዲፈርስ ክስ በቀረበበት ቀን በልጽጐ በተገኘው መጠን ብቻ ይሆናል ከዚህ ሁኔታ ውጪ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ ለመመለስ አይገደድም አንቀጽ ከውል ውጭ ስለሚደርስ ኃላፊነትና ያለአግባብ ስለመበልጸግ መሠረቱ አካለ መጠን ያልደረሰው ልጅ ሕገወጥ በሆኑ ሥራዎች ያለአግባብ የበለፀገ ወይም በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በፍትሕብሔር ሕግ ውስጥ ከውል ውጪ ስለሚደርስ ኃላፊነትና ያለአግባብ ስለመበልጸግ በተደነገገው መሠረት ተጠያቂ ይሆናል አንቀጽ አካለመጠን ሳይደ ሻለ ለት አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ አካለመጠን ሳይደርስ ደርሻለሁ ብሎ ቢናገርም እንኳን ይህን በመናገሩ ብቻ አካለመጠን ባለመድረሱ ምክንያት የሚጠቀምበትን መብት አያ ጣም እንዲሁም አካለመጠን ደርሻለሁ ማለቱ ከውል ውጪ የሆነ ኃላፊነትን የሚያመጣ ጥፋት ሆኖ አይቆ ጠርበትም ንዑስ ክፍል የሞግዚቱ ሕጋዊ ድርጊቶች አንቀጽ በደንብ ስለተፈፀሙ ድርጊቶች ሞግዚቱ አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ የፈፀማቸው ሕጋዊ ድርጊቶች ሁሉ ልጁ አካለመጠን በደረሰ ጊዜ እንደ ፈፀማቸው ተቆጥረው በኃላፊነት ያስጠይቁታል ሞግዚቱ በኃላፊነት እጠየቅበታለሁ ሲል ግዴታ የገባበት ወይም በሕግ መሠረት ግዴታ የተጣለበት ካልሆነ በስ ተቀር አካለመጠን ላልደረሰው ልጅ ሲል ለፈፀማቸው ሕጋዊ ድርጊቶች ኃላፊ አይሆንም አንቀጽ የሕግ ድንጋጌዎችን ስለመተላለፍ የሕግ ድንጋጌዎች በመተላለፍ ሞግዚቱ ለሚፈፅማቸው ድርጊቶች ወኪል የሆነ ሰው ከተሰጠው ሥልጣን በላይ በሚሠራበት ጊዜ አግባብነት ያላቸው የውክልና ሕግ ድንጋጌዎች ተፈዓሚ ይሆናሉ አንቀጽ ስለ ሦስተ ፍርድ ቤት ለሞግዚቱ የተሰጠውን መመሪያ ሶስተኛ ወገኖች ካላወቁ ወይም ማወቅ የሚገባቸው ካልሆነ በስተቀር ሞግዚቱ መመሪያውን መተላለፉ በሶስተኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሊሆን አይችልም አካለመጠን ላልደረሰ ልጅ ንብረቱን የሰጠ የተናዘዘ ወይም የተወ ሰው ለሞግዚቱ መመሪያ በሰጠ ጊዜም የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ተፈዓሚ ይሆናል አንቀጽ ስለምትክ ሞግዚት በዚህ ንዑስ ክፍል የተመለከቱት ድንጋጌዎች በምትክ ሞግዚትም ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ ንዑስ ክፍል በኃላፊነት ሊያስ ስለ ሉ ድርጊቶ አንቀጽ ስለሞግዚት ሞግዚቱ በፈፀመው የንብረት አስተዳደር ጉድለት ምክንያት ወይም መመሪያ ባለማክበሩ ወይም የእርሱ ጥቅም አካለመጠን ካልደረሰው ልጅ ጥቅም ጋር የሚጋጭ ሆኖ እያለ ድርጊቱን በመፈፀሙ አካለመጠን ባልደረሰው ልጅ ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ሁሉ በኃላፊነት ይጠየቃል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ የተመለከተው ድንጋጌ በምትክ ሞግዚትም ላይ ተፈጻሚ ይሆናል ክፍል አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ ችሎታ ማጣት ስለመቅረቱ አንቀጽ ችሎታ ማጣት ስለሚቀርባቸው ምክንያቶች አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ ችሎታ የለውም መባሉ የሚቀረው ሀ አካለመጠን ሲደርስ ወይም ለ ከሞግዚት አስተዳደር ነፃ ይውጣ ሲባል ነው ንዑስ ክፍል ግዚት ዳደር ነፃ ስለመ ።