Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
» በማለት በዐሳብ ወደ ኋላ አፈገፈጉ ዓለሚቱ ወደ ተላላኪው ጠጋ ብላ አባክህ እርዳኝ» አለች ድምጽዋን ዝቅ አድርጋ «ምን ነበር። አለ የሲጃራ ጪስ ደጅ ያደረ ማጭድ ያስመሰለውን ጥርሱን ከከንፈሩ እያላቀቀ «የከናፈሩ መላቀቅ ጆሮዎቹ ገደቧቸው እንጂ ዞረው ይጋጠሙ ነበር» አለችው ምን ችግር አለ እነዚያ የተቀመጡ ሰዎች ሲወጡ ያንቺ ተራ ስለሆነ ማነጋገር ትችያለሽ» አላት «ስማቸው ማን ነበር። አውነት ነው። ታዲያ ሁሉም መንገዶች ወደ ዓለም በቃኝ ያመራሉ የሚለውን በአብዮት ላይ መሳለቅ ምን አመጣው። መንግሥትኮ አባት ነው አባት ደግሞ ሩኅሩኅ ነው ታጋሽ ነው መሐሪም ነው ይሀ መንግሥት ሕዝብን ቆም ብሎ ማዳመጡ ከማንም ይልቅ ለራሱ ይበጀዋል የጥንቱ መሪዎች ሕዝብን የማዳመጥ ፍላጎት አረኛ ምን አለ። አለች የአኢሴማዋ ሊቀ መንበር ሦስቱም ድምጽ ሳያሰሙ ባንድ ጊዜ በአንድ አይነት ምልከታ ወደሷ አፈጠጡ አቶ ሁንዴ «እርሶ የሥርዓቱ ተጋፊ ነበሩ ከየትኛው ቡድን ጋር ነበር ያበሩት።» አሉ እናቱ ፊታቸውንም አካላቸውንም ወደሱ ዞር አድርገው የምን ነገር መቆስቆስ ነው።
የደሙን ኩሬ የበደል ካሳ ገፅ ያገሬ ልጅ አይበገሬ የወንዶቹ ወንድ እስቴው ጎንደሬ በማለት ይፎክራል አክሊሉ ክሚወደው የውትድርና አገልግሎት የተለየው ያሽከረክረው የነበረ ትሪኳርተር የሚባል መለስተኛ የሰውና የዕቃ ማጓጓዣ ወታደራዊ መኪና ከተቀበረ ፈንጂ ላይ ወጥቶ አደጋ ከደረሰበት በኋላ ነበር ሁለት ዓመት ያህል በሐኪም ቤትና በማገገሚያ ሲረዳ ቆይቶ በሕክምና ቦርድ ውሳኔ መሠረት ከሠራዊቱ ተሰናበተ ከስንብቱ በኋላ አስቴ መካነየሱስ ደብር ወላጆቹ ዘንድ አንድ ዓመት አዋዩን አሳርፎ ሥራ ፍለጋ ወደ አዲስ አበባ መጣ አክሊሉ ለጥቂት ወራት ዘመድ ቤት በእንግድነት ከቆየ በኋላ በአዲስ አበባ ኑሮ የስው ሸክም መሆን ስለከበደው ቤት ተከራይቶ ወጣ አክሊሉ የተከራያት ኖራ ሽው የተደረገባት የካርቶን ኮርኒስ የገባላት አንድ አልጋ የምታዘረጋ አንድ ጠረጴዛ ከ ወንበሮች ጋር የምታዳብል የወሮ ይፍቱ ሥራ ደመቀ ኩሽና ነች ወሮ ይፍቱ ሥራ የጋመረች ልጃገረድ አናት ናቸው እርሳቸውም ቢሆኑ የባለቤታቸውን ለሰባት ዓመት አስኪያስቆርቡ ተጠበቁ እንጂ እጃቸውን ገና ለአድሜ ጫና ያልሰጡ አዛውንት ናቸው ገላቸው የወንድ ጠረን መናፈቁን አላቋረጠም «ያገር ባል» በመባል ይታሙ የነበሩት ባለቤታቸው አቶ ተሰማ ይመር በርካታ ኮማሪ ቁባቶች ነበራቸው መጠጥና ሴት ሲያሳድዱ የበደል ካሳ ገፅ። አሉ ወንዶቹ አዳሜ ያልበላውን ቢያክም ወሮ ይፍቱ ሥራና ልጃቸው የአክሊሉን ቁጥብነት ጥርብርብነት በተለይም በጊዜ የበደል ካሳ ገፅ መስብስቡን ወደውሰታል ለቤተሰብ አባልነትም አየፈቀዱት ናቸው ወጣትነቱና ወንዳወንድ ቁመናው ከሁሉም በላይ ጎንደሬነቱ ድኽነቱን ይሸፍኑለት ይመስል አክሊሉ አንገቱን የደፋ ወጣት አይደለም አረማመዱ ሆድ ወደ ውስጥ ደረት ወደ ውጭ» የተባለ ወታደር ይመስላል የደኻ ኩሩ ነው ወሮ ይፍቱ ሥራ «ቡና ጠጣ» ብለው ሁለት ጊዜ ካላከበት በአንዴ ጥሪ ንክች አድርጎ አግሩን አያነሳም አርሳቸውም ይኽን ቁጥብነቱን በይፋ ባይናገሩለትም ወደውለታል ሸዋዬ ተሰማ ከአስራ አንደኛ ክፍል ትምህርቷን አቋርጣ ከእናቷ ጋር የምትኖር የጋመረች ልጃገረድ ነች አጎጠጎጤዋ አበባ አውጥቶ ከዘረዘረ ከረምረም ብሏል ሸዋዬ የተዋጣላት የቀበሌ ኪነት አቀንቃኝና አስተዋዋቂ ሆና ማገልገሏን እናቷ ባይወዱትም አይቃወሙም አንድ የግል ታይፕ ትቤት ለስድስት ወር የተከታተለችው ኮርስ ሥራ ሊያስገኝላት ስላልቻለ አንዳመቸ ቀንም ማታም ቀበሌ አካባቢ አንዳንዴም ከዚያ ራቅ በማለት ወጣ ገባ እያለች ኑሮን ተያይዛዋለች ወሮ ይፍቱ ሥራ «ገባሽ ወጣሽ የማለቱ ቁጥጥር ሰልችቷቸው እርግፍ አድርገው ከተውት አንድ ዓመት ሆኗቸዋል ሸዋዬ ከብሩህ ገጽታዋ ጋር ፍርጥም ያስ አካል ያላት ደሙግቡ ነች አካሄዷ ነጠቅ ነጠቅ ስለሆነ የዳሌዋና የጡቶቿ እንቅስቃሴ አረማመዷን ቄንጠኛ አድርገውታል «ከውሻ ክራንቻዋ መሾል በስተቀር የፊት ጥርሶቿ የወተት አረፋ ነው የሚመስሉት «ድኽነት ባይጫናት ፀጉሯን ብትሠራ ጥሩ የበደል ካሳ ገዕሩ ጥሩ ለብሳ ሹል ጫማ ብትጫማ ሽዋዬ እኮ ልዕልት ሣራን ታሳስታለች» ይሏታል አንድ ጎረቤታቸው የቀድሞ የክቡር ዘበኛ ባልደረባ በድንቡሽቡሽነቷ አንቺ የሥጋ ከብት የሚሏት ሰዎችም አሉ አንድ ቀን አክሊሉም ሸዋሼም በየበኩላቸው ሥራ ፍለጋ ሲዋትቱ ውለው ወደየቤታቸው ከመመለስ ላይ እንዳሉ በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ወቃቸው ከዝናሙ ለማምለጥ ቸፍቸፍ ሲሉ ከአጥር ውጭ ተገናኙ «ወይ የዛሬ ዝናብ» አለች ሸዋዬ «ደርሰናል በሩጫ አምልጠናል» አለ አክሊሉ እንዲሁ እያሉ ተንደርድረው ሳይገባበዙ የአክሊሉን ቤት ከፍተው ገቡ «ጥቁር እንግዳ አለ አክሊሉ «አብረን ከርመን የምን ጥቁር እንግዳ እያለች ሹራቧን አውልቃ ማራገፍ ቀጠለች በዝናብ የሾቀ ቀሚሷ ገላዋ ላይ ጥብቅ ብሎ መላ አካላዊ ቅርጽዋን አሳየባት ጉያዋን ጭምር ዝናሙ እያየለ የበረዶውና የቆርቆሮው ክዳን ጠብ ቱማታ ንግግርን ለመደማመጥ እስከ ማወክ ደረሰ አክሊሉ የእሷን ውብ ትክለ ሰውነት በእይታው እየቃኘ ፌዓይን ምን ይብላ። እሱ ክሆነ እዳው ገብስ ነው እኔ እንድታስወርድ ልትል እንደሆን ብዬ ድንግጥ አልኩ አለች አሰገደች አክሊሉ ቀበል አድርጎ ከተቀመጠበት ብድግ እንደማለት አያለ «አይደለም እመቤትዬ «ታጣፋው የላት ትከናነበው አማራት እንዲሉ ሆነና ሳይታሰብ ቋጠረችብኝ ታዲያ ሆዲ ባዶ በነበረበት ጊዜ ያልነበረ አዲስ ባሕሪ አመጣች ጤናዋ አየታወክ የጀመረውን አቋርጣ «ነገ ይዘፃት ና ትታያለች ለነገሩ የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ወራት እንደዚሁ ናቸው ያቅበጠብጣሉ» የበደል ካሳ ገፅ በማሰት አስገደች መልስ ሰጥታ እነ አክሊሱ አመስግነው በመውጣት ላይ እንዳሉ «አባ መላ አንድ ጊዜ በማለት ጠራችውና «ይህ ልጅ ሥራ ፈላጊ ከሆነ ለምን እዚህ ለጥበቃ አንቀጥረውም ሲያዩት ደህና ይመስላል» አለች «አኔማ በቂ ሰው አላችሁ ብዬ እንጂ ልጁ ንቁ ነው ደግሞም ገጠር አደግና ወታደር ቀመስ ስሰሆነ ታማኝ ፃይማኖተኛ ይመስላል» አለ አባ መላ «ግድ የሰህም በጥበቃ አንቀጥረውና ሥራ እንዲሰማመድ ማድረግ ይቻላል» በሚሰው የአስገደች አስተያየት ተስማምተው ተለያዩ «ወታደርነቱ ወጣትነቱ ባሳገርነቱ ሶታ ተክለ ስውነቱ ከሁሉም ከሁሉም ድኽነቱ ዋጋ አላቸው ለአሱም ለእኔም አስተማማኝ መሣሪያ ይሆናሉ ዛሬ የመጀመሪያው መጀመሪያ ሆኖአል» አለች አስገደች የአክሊሱን መቀጠር ጓደኞቹ «የሥራ ሎተሪ ወጣልህ ይሉታል አክሊሉ የሌሊት ታረኛ ሲሆን ቀን እቤቱ ገብቶ ያርፋል ይተኛል በምትተርፈው ጊዜ ከሸዋዬ ጋር ይዳሩበታል የባጡን የቆጡን ያወሩበታል ከቢሮ አካባቢ ብዙ እንዳይርቅ ከአሰገደች የተስጠውን ትእዛዝ በማክበር ወደ ቢሮም ብቅ ይላል ቢሮ አካባቢ ይላላካል አትክልት ይኮተኩታል ውፃ ያጠጣል ግቢ ያፀዳል። » ልክ ነሽ ሸዋዬ ሳይታወቅሽ ወደ ነገሩ እምብርት እየተጠጋሽ ነው» አለ አክሊሉ የበደል ካሳ ገፅ «በእናትህ አትቀልድ አክሊሉ» አለች ሸዋዬ የአክሊሉ ፍላጎት ያልገባት መሆኑን በገጽታዋና በአካል እንቅስቃሴ እየገለጸች «ሰውየውን በሊፍቱ ሰበብ እጠራዋለሁ ችግር የለም ግን አሱ ከመምጣቱ በፈት ከሆስፒታሉ ሠራተኞች ጋር የምንቋጥረው ትንሽ ቁም ነገር ይኖራል «አንተ ሰው። » አለች ሸዋዬ በፍንጠዛ «በነገራችን ላይ» አለ አክሊሉ ወደሸዋዬ ጠጋ ብሱ «ልብ አርጊ ይኸንን ሚስጢር እናትሽ አንኳ መስማት የለባቸውም» ኣለ አክሊሉ የበደል ካሳ ገፅ «አይ አክሊሉ ምን ብዬ ለምን ብዬ ነው የምነግራት። አስከዚያው እግዚያብሔር ያበርታሽ በልልኝ እህትህን» በማለት ተሰነባበቱ ሸዋዬና አክሊሉ ቀኑን ሙሉ በየበኩላቸው ሲያለዝቡ በዋሉት ሴራ ላይ ስለሚተባበሯቸው ሰዎች እንደገና አንስተው መነጋገር ጀመሩ «የሆስፒታሉን ሠራኞች እኔም አነጋግራለሁ ሲስተራ በጣም ተግባቢ ነች ሚስጢሩን ሳልነግራት የልጄ አባት በጣም እንደሚጨቁነኝ ከከተማው ሴቶች ግማሽ ያህሉ የአሉ ቅምጦች መሆናቸውን አንጀት በሚበሳ እሮሮ አስረዳታለሁ ከኔ የተረፈውን ሲስተር ካላት ልምድ ታሟላዋለች» በሚለው የሸዋዬ ዘዴ አክሊሉ ተስማማ ባለመኪናው በማግስቱ ጠዋት አራት ሰዓት ተሩብ ላይ አውቶሞቢሉን እያሽከረከረ የመጀመሪውን በር ያለፍተሻ ሰተት ብሎ ገባ በሆስፒታሉ ተመላላሽ መታከሚያ መግቢያ በር ላይ ቆሞ የጠበቀው አክሊሉ ማደግደግ ሲቀረው በጎንደርኛ እጅ አነሳስ የበደል ካሳ ገፅ ተቀበለው ሞቅ ባለ ሠላምታ ተጨባብጠው ወደ ኛ ፎቅ ወላድ ክፍል ለመፄድ የመጀመሪያውን ኬላ «በሽተኛ ለማውጣት ነው» ስላለ ያለችግር አለፉ ሸዋዬ የተኛችበትን ክፍል ገርበብ ያለ በር ገፋ አድርገው ዘው ሲሉ ሸዋዬ ከትራስ ላይ ራሷን ቀና አድርጋ እንደማቃሰት ባለ ስሜት ቅጭም ባለ ገጽታ ተቀበለቻቸው አክሊሉ እንግዳውን አስገብቶ ሹልክ ብሎ ወጣ «ምነው። ለብርቱ ጉዳይ ስለምፈልግህ ጥቁር አንበሣ ሆስፒታል አስተዳዳሪው ቢሮ እንድትመጣልኝ እባክህ ፈጠን በል» አለ ብር መክፈል የምችል ለው ነኝ የበደል ካሳ ገፅ «የአላካሚ ካርድ ያልያዚ ስሰው በዚህ ሰዓት አያስገቡም ኮ» «ተስፋዬ እንደምንም ብለህ ድረስልኝ በየትና እንዴት እንደምትገባ አላውቅም ብቻ ድረስልኝ» ካለ በኋላ ስልኩን ዘጋ «አስቲ ለማንኛውም ጊዜ ስጡኝ» አለ ዮሐንስ ገና ከወዲሁ የተረታ በሚመስል አንደበት አንድ ሺህ ብር ለማይሞላ ገንዘብ ይህን ያህል ከሚጨነቁ ለምን ወዲያ ከፍለው አይገላገሉም። » አለ የሂሣብ ሠራተኛው በሸሙጥ አንቱታ «የተጠየቅሁት ርዳታ ቢሆን ኖሮ ሁለትም ሦስትም ሺህ ነገር ግን ይህን በአጭበርባሪዎች ሴራ የተወሰነብኝን ዕዳ ብከፍል ራሴን ማለቂያና መቆሚያ ወደሌለው አዘቅት መጣሌ ነው» አለ ዮሐንስ የሆስፒታሉ ዕዳ ክፍያ የሚያመጣውን መዘዝ በሚያስገነዝብ አነጋገር በስልክ የተጠራው ተስፋዬ ከሩብ ሰዓት በኋላ ተንደርድሮ ሲገባ በቁም እስር ላይ የቆየው ዮሐንስ ቀና ብሎ ተመለከተው «አንድ ጊዜ አሱን ላነጋግረው» በማለት አስፈቅዶ ወደ ኮሪደሩ ገለል አሉ ድምጻቸውን ዝቅ አድርገው ለጥቂት ደቂቃዎች ከተነጋገሩ በኋላ የዮሐንስ ባለቤት አሰገደች ይህን ወሬ ከሌላ ሰው ከመስማቷ በፊት እየተፈጸመ ያለውን ተንኮል በቀጥታ ከተስፋዬ አንደበት ብትስማው እንደሚሻል ተስማመ «ለክፉም ለደጉም አሰገደች አንድ ሺህ ብር ይዛልህ ብትመጣ አይከፋም» አለ ተስፋዬ ዮሐንስም በዚሁ ተስማምቶ ተለያዩ የበደል ካሳ ገፅ ሰባት ሰዓት ተኩል ሲሆን አስተዳዳሪው መጡ ጸሐፊዋ የደረሰውን ሁሉ ባጭሩ አስረዳቻቸው ከተበደልኩ ባዩ አንደበት መስማት የፈለጉት አስተዳዳሪ ዮሐንስን አስጠሩ ዮሐንስ ነገሩን ከመነሻ እስከ መድረሻ ረጋ ብሎ አስረዳ አስተዳዳሪው ማመን እስኪያቅውቸው እየተገረሙ «ታዲያ አሁን ምን ቢደረግ ይሻላል ነው የምትለው አንተ። ኮ እኔ ነበርኩ እባክህ እነዚህን ሰዎች እንርዳቸው ብዬ መኪና ያስቆምኩህ ምነው ልሣኔን በዘጋው» አለች አሰገደች የበደል ካሳ ገዕ ሬቫሬ ግን እንዴትና ለምን ወደዚህ መጣህ» በማለት ፐያቴ ያስከተለች እንደሆነ ዮሐንስን መልስ ስለሚቸግረው ሥጋት ተወጠረ ነገሩን ለማረሳሳት ወይም መልሱን አማዘጋጀት የሚረዳውን ጊዜ ለመግዛት ብድግ ብሎ ወደ መጸዳጃ ቤት ሔደ እኔ ሌላ ምክንያት ብደረድር ውሎ አድሮ ሕቁ መውጣቱ ስለማይቀር መዋሸት የለብኝም እንዴት እንዳታለለችኝ እውነቱን መናገር ነው ያለብኝ» በማለት ወስኖ ወደ ሳሎን ተመለሰ ቀልዱ ሽሙጡና ተረቡ የነገው ውሎ ምክክር ራት ላይ እንደማባያ ተኮመኮመና ገበታ ከፍ እንዳለ ዮሐንስ ወደ መኝታ ቤት ገባ «ዛሬ ሥዕል ቤት ነው የማድረው» አለች አሰገደች «ይሁን» አለ ዮሐንስ ትንሽም ሳያቅማማ የበደል ካሳ ገፅ ምዕራፍ አሰገደች በሥዕል ቤት ሥዕል ቤት አሰገደች ፅለት በዕለት ከፈጣሪዋና ከአማላጆቿ ጋር የምትገናኝፄዲት የቪላው ኛው መኝታ ክፍል ነው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመላዕክት የጻድቃንና ስማዕታት ምስሎችና መንፈሳዊ ጥቅሶች ግድግዳውን ሞልተውታል በአንደኛው ግድግዳ ጥግ ከመጽሐፍ ቅዱስ እስከ መንፈሳዊ መጽሔት የያዘ መደርደሪያ አለ በሌላው ግድግዳ ጥግ መለስተኛ ጠረጴዛና አራት ወንበሮች ተሰይመዋል በስተምሥራቁ ግድግዳ ወለል ላይ አንድ ዳጎስ ያለ የጥጥ ፍራሽ አምሮ ተነጥፏል ይህ ቦታ አለገደች ጧትና ማታ ተንበርክካ የምትፀልይበት ስለሆነ አማላጆቿ ጭምር የሚስተናገዱበት መቅደስ ነው ብላ ታስባለች ሥዕል ቤት አስገደች አንዳንድ ጊዜ ነገር ሲገባት የምትቆዝምበት ከዚያም አለፍ ሲል የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ትልሟን የምትቀይስበት ክፍል ነው አስገደች ቀን በኅሊናዋ መዝግባ ከመደበኛ ሥራዋ ጋር ስትገረድፍ የዋለችውን የግልና የቤተለብ ጉዳዮች በጥንቃቄ የምታለዝበው በክክታ አቡክታ የምትጋግረው ሥዕል ቤት ውስጥ ሃው የአስገደች ሥዕል ቤት ከሚመስሏት ጠያቂ ጓደኛ ዘመድ አዝማድ ጋር ቆይታ ያደርጉበታል ሲያስኛቸውም ቡናና ሻይ ከልዩ መክስስ ጋር ይቋደሰበታል ሥዕል ቤት የአስገደች ሁለ ገብ ቢጢሌ አዳራሽ ናት የበደል ካሳ ገፅ ዛሬ አሰገደች ሥዕል ቤት የገባችው ራሱን የቻለ የቤት ሥራ አጀንዳ ይዛ ነው «ዛሬ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በአክሊሉ በሸዋዬ በሆስፒታሉ ባልደረቦች በአንድ ወንገን ዮሐንስ ተስፋዬና እኔ በሌላ ወገን የተወነው ትያትር የቱን የህል ተዋጥቶልናል። አለ ተስፋዬ ተስፋዬና ዮሐንስ የአስተዳዳሪውን ምክር አዘል አስተያየት በየራሣቸው እያፍተለተሉ እንደ ተኮራረፈ ስው ሳይነጋገሩ መኪናቸው ውስጥ ገብተው ከሆስፒታሉ ግቢ ወጡ ችታ ሸዋዬ ልጂን ታቅፋ በኮንትራት ታክሲ ከመኖሪያ ግቢዋ ደርሳ እግሯ መሬት ከመንካቱ በታከሲዋ የሞተር ድምጽ የተቀሰቀስ ጎረቤት በነቁስ ወጥቶ በእልልታ ተቀበላት የሠላሳ ብር ዱርዬ በግ ታርዶላት ደም ተራምዳ ወደ እናቷ ቤት ገባች ፈገግታዋና አረማመዲ ከአራስነት ይልቅ ክጦር ግንባር በድል አድራጊነት የተመለስ ጀግና ይመስል ነበር የሸዋዬ መፍነክነክ የጎረቤቶቿ አቀባበል ሲታከልበት ከዚህ ሁሉ ጀርባ የበደል ካሳ ገዕ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ያለብዙ ታዳሚ የተተወነው ትያትር ሥምረት ለሸዋዬ የጀግና አቀባበል ተደረገላት የሚያሰኝ ነበር አክሊሉ የሒሳብ ሠራተኛውን በማግባባት የደረስኙን ፎቶኮፒ ይዞ መጥቷል ሌላ ትልቅ ድል «የገንዘቡ ከፋይ ዮሐንስ ሁንዴ ተብሉሎ በደረሰኙ ላይ መጻፉን አክሊሱና ሸዋዬ ማመን ተስኗቸው አራስ ቤት እንደገና ፊደሉን እየቆጠሩ አነበቡት ልክ ነው ቀና ብሰው ተያዩና ፊታቸው በሙሉ ጥርስ እስኪሆን ድረስ ሳቁ በተለይ ሸዋዬ ሳቅ ከጣራ በላይ ነበር «አንበሲት ነሽ» አሰና አክሊሉ ከናፍሩን ሞጥሞጥ ሲያደርግ ሸዋዬ ዋ። እንዳልነክስሀ አክንባሎ ሰበራው እስኪደርስ ታገሥ» ብላ ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች «ትልቁን ማርክ የያዘው ዋናው የቤት ሥራ ተሠርቷል ኣሁን ውጤቱን መቶ በመቶ ለማድረግ በቀሪው የቤት ሥራ ላይ ማታ ለብቻችን ቆይታ እንይዝበታለን» አለ አክሊሱ «ልክ ነው ዳገቱን ጨርሰናል የቁልቁለቱ ጉዞ አያቅተንም» ብላው አክሊሉ አለባበሱን አሳምሮ ሌሳ ሰው መስሎ ኮፍያ አድርጎ ወደ «ድድ ማስጫ» ወጣ የበደል ካሳ ገፅ ምዕራፍ ያላቻ ጋብቻ መዘዝ በአባቱ ከራስ ጎበና ዳኤው በእናቱ ከአፄ ዮሐንስ ደጃዝማች በዝብዝ ካሣ የዘር ሐረጉ የሚመዘዘው ዮሐንስ አያት ቅደመ አያቶቹ አገራቸው ከእነርሱ የምትጠብቀውን ዜጋዊ ግዳጅ በሚያኮራ ድል ተወጥተው አልፈዋል ብሉ ያምናል ይኽን እምነቱን እንደ አብዛኞቹ የጨዋ ልጆች በየደረሰበት አንደ ውዳሴ ማርያም የመድገም ፍላጎት የለውም የመደብ ጀርባውን በተመለከተ ሌላም ሰው ቢሆን ሲያወራ መስማት አይፈልግም በዚህ ጉዳይ ላይ አባባ ጌቶችና ዮሐንስ ያላቸው አቋም ለየት ያለ ነው በታላላቅ ዓውዳመቶች «እንኳን አደረሰዎ» ለማለት የሚመጣ ወዳጅ ዘመድ ጠጁን እያንደቀደቀ ቁርጡን እያወራረደ በእግረመንገድ ስለ እሳቸውና አባቶቻቸው ባላባትነት ገዥነት ዐዳኝነት ጀግንነትና ለጋሥነት ይተረክለታል ይህ ሁልጊዜም የመስተንግዷቸው አንዱ አካል ነው ከዚህ ቀደም የሰማው ሰው ቢሆንም ደግሞ መስማቱ ጥቅም እንጂ ጉዳት የለውም ብለው ያምናሉ እሳቸው ገድሎቻቸውን ሲናገሩ ሁሉም ሰው ሕፃናት ጭምር ትንፍሽ ሳይሉ ማዳመጥ አለባቸው በአመቤት ጽዮን ሞገሳ በኩል ያለው የደም ጥራት የአጥንት ክብደት የሚነሳው ዋቢነቱ ለአባባ ጌቶች ታላቅ ሰውነት ተጠቃሽ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው ጌታ ሁንዴ ቤኛ ነወር ባይላችሁ አጥንቱ ከብዶት ነው ኮርቶ አይምሰላችሁ የበደል ካሳ ገዕ ስአባዱላ ሁንዴ መሶብ አሰፋለሁ በጋሻው እንጀራ ሲበላ አይቻለሁ በማለት ተቀባብለው ላሞገሷቸው ባልና ሚስት አዝማሪዎች አሩሲ ጠቅላይ ግዛት በጭላሎ አውራጃ ኮፈሌ ወረዳ ሽሬ ምወረዳ ከሚገኝ ርስታቸው ግማሽ ጋሻ መሬት መሸለማቸውን ዘወትር በኩራት ያነሱታል አንድ ጊዜ ደግሞ ከሸኖ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው ርስታቸው ላይ ባሠሩት የገጠር መኖሪያ ቤታቸው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ለመዘከር በተጣለ ሰፊ ግብር ላይ ደጉ የተባለ አሽከራቸው ቡከን ልጅ ከመውለድ ይሻላል ማስወረድ ደግሞም ከማስወረድ ይሻላል ሴት መውለድ ፀጉሯ የሐር ጎፍላ የመሰለ አንደሆን አባ ዱላ ሁንዴን ታመጣለች ዝሆን ይምጡ ባይ ይስብስቡ ባይ ሲሰበሰቡ እንፍጻቸው ባይ አሽከሩ ነብር ጌታው ግስላ ኩፍ ኩፍ ይላል አንደ ጉሽ ጠላ ያንተ አሽከር ያንተ ቡችላ የበደል ካሳ ገፅ በማለት አቅራርቶ ከጌቶችና አመቤት ጽዮን ሞገሳ ፊት ለፊት በርከክ ብሎ ፉከራውን ስላንደቀደቀው ጌቶች አንድ አጭር ምንሽር ከሃያ ጥይት ጋር ባለቤታቸው ደግሞ ኩታ ሸልመውታል ይኽንን የአባቱን ያለጋስነት ባሕሪ ዮሐንስ በአጅጉ ያደንቀዋል » ሪኝ ፖፍ ዮሐንስና አሰገደች በታላላቅ ዐመት በዐል ወላጆቻቸውን «አንኳን አደረሳችሁ» ማለት የማይታጎል ተግባራቸው ነው ካመቸ ባልና ሚስት በልጆቻቸው ታጅበው ካላመቸ ዮሐንስ ወደ ግቢ አለገደች ብቻዋን ወይም ከልጆች ጋር ወላጆቿ ቤት ይሔዳሉ ይህ ልማድ ከውጥረቱም በኋላ አልተቋረጠም የልጆቹ ምርጫ ከግቢ ይልቅ የአስገደች ወሳጆች ቤት መሆኑን በግልጽ ይናገራሉ የግቢው ሥነ ሥርዐት ያሸማቅቃቸዋል አያቶቻቸውን አጅ ነስተውና ጫማ ስመው አንዳንድ ጊዜ ገለል ይላሉ ሌላ ጊዜ ከሳሎኑ አንድ ጥግ አረፍ ብለው የሚቀርብላቸውን አየቀማመሱ ወግ ያዳምጣሉ የልጆቹ ሳሎን መቆየት በዚያ ያለውን ሥነ ሥርዓት ለመልመድ ዕድል ስሰሚሰጣቸው ዮሐንስ ይወድደዋል አስገደችም ብትሆን ልጆቿን ከአያቶቻቸው ጋር የሚያቀራርበውን አጋጣሚ ትፈልገዋለች በአንፃሩ በበዐልም ሆነ ባዘቦት ቀናት ልጆቹ አሰገደች ወላጆች ቤት ሲሔዱ «ከቪህ ተመስሰሱ» የለባቸውም አንደልባቸው ተናግረው አንዳሻቸው ወጥተው ገብተው የፈለጉትን በልተውና ጠጥተው ያልፈሰጉትን ትተው የበደል ካሳ ገዕ ይቦርቃሉ ከአቶ ደምሴ ጋር አንደ ጓደኛ ነው የሚያወሩት ይህ ደግሞ ከልጆቹ የበለጠ አሳቸውን ደስ ያሰኛቸዋል አንድ ጊዜ አቶ ደምሴ ለልጅ ልጆቻቸው አጣፍጠው የነገሯቸውን የወንድማቸውን የአዳኝ ጥዱ ተሰማን ታሪክ ደረጀ የበለጠ አጣፍጦ በመጻፍ ተደንቆበታል ደረጀ ታሪኩን የጻፈው ትቤቶች በክረምት ተዘግተው በመስከረም አንደ ተከፈቱ የኛ ክፍል መምህራቸው በእረፍታችሁ ጊዜ ስላነበባችሁት ምርጥ መጽሐፍ ወይም ስላያችሁትና ስለሰማችሁት ገጠመኝ ከ ባላነሱ ቃላት ድርስት ጻፉ ብለው ለሰጡአቸው የቤት ሥራ ነው ደደረጀ ድረፅታ ፋሺስት ኢጣሊያ በዓለም አቀፍ ሕግ በተከለከለ የጋዝ መርዝ ጭምር ተዋግታ የኢትዮጵያን ከተሞች በ ሚያዝያ ብትቆጣጠርም የኢትዮጵያ ባንዲራ በዱር በገደሉ መውለብለቧን አላቋረጠችም ስለ ሀገራቸው አንድነትና ሉዓላዊነት ደማቸውን ያፈሰሱ መራራ ሞትን የታገሱ ስማዕት አርበኞች ጣሊያንን ፋታ በማይሰጥ ጥቃት ሰቅዘው ስለ ያዙት አርበኛውን ሃበፈሪ ዱላሃ ሰማንበርከክ በመሞከር ላይ ነው አዳኝ ጥዱ ከአርበኞች አንዱ ነበሩፈ ዓይነ ጥሩ ተኳሽ ጥዱ በተለያዩ ዐውደ ግንባሮች ጣሊያንን ገጥመው ግዳይ ጥለዋል ምርኮም አስቆጥረዋል የአርበኝነት ሥሪታቸው በደጃች አበራ ካላ ውስጥ ነበር ደጃዝማች በአርበኝነቱ ሥራ የበደል ካሳ ገፅዕ ብዙም ሳይቆዩ ከጣሊያን መንግሥት ጋር ተደራድረው እጅ እንደሰጡ ወዲያውኑ በግፍ ተገደሉ የደጃች አበራ ጦር ሲፈታ አዳኝ ጥዱ ሃውዛ ስንቁሃ ዓይነት ቡድን መደበኛ ከልል የሌለው ጭፍራን መሥርተው በቀላሉ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ ዩባሊያንን ተግትገውታል አንድ ሁለት ጊዜ ፍቼ ከተማ ውስጥሠርገው በመግባት በሰነዘሩት ጥቃት በርካታ ሶልዳቶዎችንና ባንዶችን ገድለው አምልጠዋል አንድ ቀን አዳኝ ጥዱ ጠመንጃቸውን ደብቀው ከሁለት ጓደኞቻቸው ጋር አሳቻ የባላገር ልብስ ለብሰው የጠላትን ሁኔታ በመሰለል ላይ እንዳሉ በአፈሳ ተያዙ ቀደም ባለው ሰሞን በጠላትና በአርበኞች መካከል በተደረገ ውጊያ የተማረኩ አርበኞችና በአፈሳ የተያዙትን ተጠርጣሪዎች ከፍቼ ወደ አዲስ አበባ ለመላክ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑን የአካባቢው አርበኞች መረጃ ደረሳቸው ከዚያ በፊት ወደ አዲስ አበባ የተላክ ምርኮኛ ወይም ተጠርጣሪ በሠላም ወደ ቤቱ ተመልሶ አያውቅም ያንን የጠላት ዝግጅት ለማክሸፍ ከቀረቡ በርካታ አማራጭ አርምጃዎች የሚከተለው ተመረጠ ፍቼ ከተማ ውስጥ ካሉ የአርበኞች ደጋፊዎች ጋር መላላክ ተደርጎ ፃያ አምስት ብርቱ አርበኞች በቂ ጉርሻ ካላቸው ማለፊያ ጠመንጃዎች ጋር ፍቼ ከተማ እንዲገቡ ተደረገ መውጫ መግቢያውን ሁለት ቀን ካጠኑ በኋላ በሣልስቱ ጎኀ ከመቅደዱ በፊት አርበኞች በዘብጥያው ላይ ጥቃት ሰለነዘሩ በአፈሳና በምርኮ ከተያቡት እሥረኞች መካከል በተኩስ ልውውጥ ጊዜ አሥራ አንዱ ሞተው ከመቶ በላይ የሚሆኑት አመለጡ ከጠላት ወገን አምስት ጣሊያኖች የበደል ካሳ ገፅ የሐማሴን ባንዳዎች ተገደሉ ጥቃቱን ከሰነዘሩት አርበኞች መካከል ሦስት ሞቱ አዳኝ ጥዱ ግን ሳያመልጡ ቀሩና እዚያው በአሥረኛነት ቀጠሉ እሳቸው ከማምለጥ ወደ ኋላ የቀሩት ሌሎችን እንዲያመልጡ በማድረግ ላይ ስለነበሩ ነው በደረሰው ጥቃት ክፉኛ የተናደደው የአካባቢው አስተዳዳሪና የጦሩ የበላይ አዛዥ ኮሎኔል ሮቤርቶ ጋሊና ሳያመልጡ የቀሩ አርበኞችን እግር ተወርች አስሮ ሜዳ ላይ አሰጣቸው በእነሱ ላይ ሊወስድ የታሰበውን የመቀጣጫ እርምጃ ያይ ዘንድ ሕዝብ ታዝዞ ወጣ ሁሉም የተመደበለትን ቦታ ከያዘ በኋላ ሦስት የተማረኩ አርበኞች እጃቸው በካቴና እግራቸው በእግረ ሙቅ ታስሮ ከሕዝቡ ፊት ለፊት እንዲቆሙ ተደረገ በአፈሳ ከተያዙት መካከል አርበኞቹን ለመግደል ሦስት ሰዎች ተመርጠው ከሙሉ ጉርሻ ጋር ጠመንጃ ተሰጣቸው የተመረጡት ሰዎች ትዕዛዙን ለመፈጸም አመነቱ «በታዘዛችሁት መሠረት እነዚህን ሽፍቶች ከገደላችሁ በነፃ እለቅቃችኋለሁና አይዚችሁ» በማለት ኮሎኔል ጋሊና በቱርጁማን አግባባቸው በወገኖቻቸው ላይ ያን የመሰለ የግድያ ወንጀል መፈጸም የከበዳቸው ሦስቱ ሰዎች እርስ በርስ ተመካከሩና «አኛ መታሰሩ ይሻለናል ሰዎቹን መግደል አይሆንልንም» በማለት ለኮሎኔሉ ገለጡለት ጣሊያኑ በጣም ተናድዶ «እናንተ ፈሪዎች ናችሁ ጣሊያን ፈሪ አይወድም ዓለም ደግሞ የፈሪዎች አይደለችም ስለዚህ እናንተ ከነዚያ ከሚገደሉት ሰዎች ጋር መሞት ነው የበደል ካሳ ገፅ ያለባችሁ» አለና እጅና እግራቸው እንደ አርበኞቹ ታስሮ ለሞት አንዲዘጋጁ አስደረጋቸው ከዚያ በኋላ ኮሎኔሉ በአፈሳ ወደ ተያዙት በርካታ ሰላማዊ ተጠርጣሪ ሰዎች ቀረብ ብሎ «ማነው ወንድ ጥሩ ተኳሽ። » «እውነቱን ልንገርሽ አስካሁን አንድም የነገርሺኝ ነገር የለም የነገርሽኝ መስሎሽ ከሆነ ነገረሽኝ አንዳልነገርሽኝ መሆኑን ላረጋግጥልሽ የዮሐንስ አባባል አሰገደችን አዲስ ብግነት ለቀቀባት ብግነቱ ታፍኖ የቆየውን አንባ ፈነቀለው መንታ መንታው አየወረደ ፊቷን አቃጠለ ለጊዜው የምትናገረው የጠፋባት የበደል ካሳ ገዕ የበደል ካሳ ገፅ ይመስል ዝም አለችና ቀና ብላ ዮሐንስን በእንባዋ ጭጋግ ውስጥ አጨንቁራ ተመሰከተች ዮሐንስ ቀጣዩን ርምጃ በትግሥት አድፍጦ ይጠብቅ ገባ አሰገደች አንደ መርግ አክብዳ ለማሳየት የጀመረችው ብሶቷን ዮሐንስ ባዶውን ስላስቀረባት የንትርኩን አቅጣጫ መቀየር እንዳለባት በመረዳት «ትዳራችን አደጋ ላይ ነው ያለፈው ውርደቴ ሳያንሰኝ ለምን በላይ በላዩ ይጨመርበታል ጥቃቱ ከምሸከመው በላይ ሆኖብኛል በዚህ ጉዳይ ላይ ያለህን አቋም ማወቅ እፈልጋለሁ» በማለት የዮሐንስን መልስ ለመስማት አቆበቆበች «አሰገደች በከንቱ ባጀሽ የትናንቱን የእንቺንና የዓለሚቱን ድንገተኛ ግጭት ፍፁም ግንኙነት ከሌለው የአነ ሸዋዬ ከንቱ ሴራ ጋር ልታገናፒው እየሞከርሽ ይመስለኛል ፍላጎቴን ብሶቴን ንትርኬን ሙግቴን ለማስተጋባት ያገለግሉኛል ብለሸ ሁለት የማይገናኙ ጉዳዮችን አንድ ልታደርጊያቸው ትፈልጊያለሽ አይጠቅምሽም ደግሞም አያዋጣሽም የዮሐንስ አነጋገር እንደማስጠንቀቂያ የሚቆጠር ነበር «እሺ ቆይ። » አለ ዮሐንስ አሰገደች በራሷ ሙግት እየተረታች መሆኗን ከወዲሁ አንድትገነዘብ በሚያደርግ ፉከራ የባሏን የመሟገቻ ጭብወች ማስተባበል ተስኗት አሰገደች እንደገና ዝም አለች » ዓለሚቱ የእኔና የአንቺን መጋባት እንደማትቀበለው ያወቅሽው ዛሬ ወይም ትናንት አይመስለኝም ዓለሚቱ ጋብቻችንን የማትደግፍበት ለራሷ የራሷ የሆነ በቂ ምክንያት ሊኖራት ይችላል ግን ለእኔና ለአንቺ ጋብቻ የዓለሚቱ አቋም ወሳኝ ባለመሆኑ ተጋብተን ኖረናል አራት ልጆችም አፍርተናል «ከዚህ አውነት ፊት ለመቆም ብርታቱ ሊኖረን ይገባል ይህ ሳይሆን ቀርቶ ያለፉ ውጥንቅጥ ችግሮችን እያልመዘመዝን ቁስል ለቁስል የምንቧጠጥ ከሆነ ትዳራችን ይፈርሳል ጥቃቅን ችግሮችን እያገዘፍንና በስሜታዊነት እየተገፋፋን ትዳራችንን ባናፈርሰው ይሻለናል እኔና አንቺ ብሎ የጆመረውን ፃሣብ ሳይቋጭ ተወራጭቶ ከቤት ወጥቶ ሔደ ችችትጁት ዮሐንስ ከቤት ወጥቶ መኪናው ተጋብቶ ወዴት እንደሚሔድ ሳያውቀው ነዳ ሰሞኑን የተፈጠረው ችግር ቀደም ሲል ከነበረው ጋር ተጋግዞ ዮሐንስን የልጆቹ ጉዳይ ከመቸውም ይልቅ አሳሰበው የበደል ካሳ ገፅ የልጆቹ ከአናትና ካባቱ ማግኘት የሚገባቸውን አያታዊ ፍቅር ሙሉ ለሙሉ አለማግኘት ዮሐንስ ባይናገረውም ይከነክነዋል «በተለይ ወንዶቹ ልጆች ነፍስ አያወቁ መጥተዋል አንድ ቀን ይኽንን ጥያቄ ቢያነሱብኝ ምን እመልስላቸዋለሁ። በማለት ዝም አሰኘው «ወደፊት ከዚህ ጠንከር ያለ ጥያቄ ሊወረውሩ ይችላሉ የእኔና የአሰገደች ወላጆች መደባዊ ርቀት በልጆቼ ማንነት ላይ እውክታ አንዲፈጥር አልፈልግም» አለ ዮሐንስ በአጽንኦት የበደል ካሳ ገዕ ምዕራፍ አዲስ የጥቃት ግንባር እንደ ዮሐንስ ባይሆንምዓ አሰገደች ዛሬ ዛሬ እንዳቅሟ ዘመደ ብዙ ሆናለች ዮሐንስ በእሷ ላይ አደረሰ የተባለውን በደል ከሰሙበት ጊዜ ጀምሮ እየተጠራሩ ምክክር ይዘዋል «አኔ እስካሁንም ማመን ተስኖኛል በሌላ በኩል ደግሞ በፈጸመብኝ ክሕደት የግፍ አምላክ በእጁ ላይ ጥሎልኛል» በማለት አሰገደች በምታሰማው ሮሮ የተገፋፋው ወዳጅ ዘመድ ዮሐንስን ለመበቀል እያሸመቀ ነው በዚህና በሌላውም የተመቻቸ ሁኔታ የልብ ልብ የተሰማት አስገደች አዲስ የጥቃት ግንባር ለመክፈት የሚያስችላትን ቅድመ ዝግጅት በመንደፍ ላይ ነች «ለምን ዮሐንስ ብቻ። እሷ ላይ ጥብቅ በልባት ካስፈስገም ያው እንደልማደድህ » ብላ አሰገደች ተንከተከተች አስገደችና አክሊሉ ጠጠር ያስ ጉዳይ ሲገጥማቸው በቂ ጊዜ ወስዶ ሰመነጋገር ከከተማ ወደ ዳር ወጣ ይላሉ በደብ ረዘይት መንገድ ቃሊቲ ከመደረሱ በፊት ከዋናው መንገድ በስተቀኝ አንድ ኪሎ ሜትር ያህል ገባ ብሎ የሚገኘውዘመናዊ ፔንሲዮን የአንግዳ ማረፊያ የአሰገደች ምርጫ ነው በፔንሲዮኑ ጥንድ ሆነው በመኪና የሚመጡ ደንበኞች ሰዓት ይስተናገዱበታል ስአዳር ብር ስደርሶ መልስ ብር ያስከፍላል ሞራልና ሥነምግባር በጎደለው በፔንሲዮኑ አገልግሎት በተበሳጩ የቀበሌ አመራር አባላት ግብታዊ ርምጃ ሁሰት ጊዜ ተዘግቶ ነበር ባስቤቱ ባለው ሰፊ ማህበራዊ ግንኙነት እየመለሰ ከማስከፈቱም በላይ ቀበሌዎቹን እንዲገሰፁ አስደርጓል አሰገደች ወደዚህ ፔንሲዮን የምትመጣው በክሊኒኩ የሰርቪስ መኪና ነው ከአክሊሉ ጋር የሚገናኙት ቀደም ሲል በተያዘ ቀጠሮ መሠረት ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ዓውደ ምሕረት አካባቢ ነው አሰገደች ተሳላሚ መስላ ትገባለች መኪናውን ሳትቆልፍ ወጥታ በዕርዱ ባንደኛው ጥግ ቆም ብላ ሰውነቷን አማትባ ትሳለማለች ክፍት በተወችው መኪና ውስጥ የአክሊሉን መግባት እንዳረጋገጠች ክንብንቧን አስተካክላ ወደ መኪናዋ ታመራለች ክዚያ በኋላ ወደ ቃሊቲ ትረግጣለች የበደል ካሳ ገፅ የፔንሲዮኑ ጥበቃ ከወህኒ ቤት ጥበቃ ቢጠብቅ እንጂ አይላላም በ ሰዓት ፈረቃ የሚለዋወጡ ሰምንት በስውር የታተቁ ወጠምሻ ዘበኞች አሉት ልዩ የጭቅናና የበግ ጥብስ የፔንሲዮኑ ዕውቅ የምግብ ዓይነቶች ሲሆኑ ከመጠጥ ብላክ ሴቭል ሺቫስ ኮኛክና ጎርደን ጂን ያቀርባሉ ለስላሳና ቢራ ግቢው ውስጥ ገብተው አያውቁም ነው የሚባሰው ች በዮሐንስ ወላጆች ላይ ከውስጥና ከውጪ የተተከሉት ሰዎች ሰአኢሴማዋ ሊቀመንበር መረጃ ማቀበል ጀምረዋል አቶ ሁንዴ ቤኛ የወደቀው አድኃሪ ሥርዓት አቀንቃኝ አንዳልነበሩ ቢታወቅም ብር እንዳፈር ይዝቁበት የነበረውን የገጠር መሬት የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት ሰወረሰባቸው አብዮት የሚደማ ልብ እንደማይኖራቸው የአኢሴማዋ ሊቀመንበር ሌሎቹን የከነማና አኢወማ አመራር አባላት የማሳመን የሕቡዕ ዘመቻ ይካዛለች ሰዚህ አገልግሎቷ ያስፈልገኛል ያለችውን ብር ተችሯታል ፍች ብሩ ኤጀርሳ አቶ ሁንዴ ገና በሕፃንነቱ ካገር ቤት አምጥተው ያሳደጉት ወጣት ነው ጮሌና ተፌ ስለሆነ አቶ ሁንዴ በጣም ያቀርቡታል ብሩ አስከ ስምንተኛ ክፍል ተምሮ አቋርጧል ጌቶችን መክተልና መላላክ ከትምህርቱ ይልቅ ዋና ሥራው ስለሆነ በፈተና ቀን እንኳ ከትቤት የሚቀርበት ጊዜ የበደል ካሳ ገፅ አለ የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን የወደቀውም በዚህ ምክንያት ነው ይህ ደግሞ ብሩን አበሳጭቶታል በቀበሌ ለወጣቶች የሚሰጠውን የአብዮታዊ ንቃት ትምህርት አልፎ አልፎ መከታተሉና በኢህአፓም መመልመሉ የብሩን ልብ ወደ ውጭ እያሸፈተው ነው ይኽንን የብሩን ሁኔታ የተረዳችው የቀበሌው አኢሰማ ሊቀመንበር ወጣቱን በገንዘብም በአብዮታዊ ጓድነትም ቀርባዋለች መጨቆኑና የጉልበቱ መበዝበዝ እንደሚያስቆጫት በምትሰጠው አስተያየት ብሩ ልቡ ተነክቷል የአቶ ሁንዴንና የቤተሰቡን የዕለት ተዕለት አንቅስቃሴ የሚመለከቱ መረጃዎችን ልቅም እያደረገ ለአኢሴማዋ ሊቀመንበር የሚያቀብለው ብሩ የልብ ልብ ተሰምቶታል የብሩ ክትትል ያተኮረው በይበልጥ በአቶ ሁንዴ በደረጀና ባባቱ በአቶ ጉልቴ ላይ ነው አቶ ሁንዴ በእንግድነት ካስጠጓቸው ከአቶ ጉልቴ ጋር አፍ ላፍ ገጥመው የሚያወሩትን መስማት ባይችልም ሁለቱ የአደኃሪው ሥርዐት ሰዎች ከሰው ነጠል ብለው ቆይታ እንደሚይዙ አንዳንድ ጊዜም ደረጀ በቁጥጥር ሥር ከመዋሉ በፊት ያጅባቸው እንደነበር ብሩ የ ሰዓት ሪፖርት ያቀርብባቸው ነበር ብሩ የመሠረተ ትምህርት ኮሚቴ አባል በመሆን መመረጡ ወደ ቀበሌ ለመሔድ ደህና ሰበብ ሆኖለታል ብሩን በመሣሪያነት እስከ ወዲያኛው ለመጠቀም ያላትን ፍላጎት ለማሳካት በውነት በጣም ጎበዝ ወጣት ነህ በርታ ብቻ አንድ ነገር ላሳስብህ አእወዳለሁ ይኸውም አቶ ሁንዴ ወይም ሌላ የበደል ካሳ ገዕ የቤተሰቡ አባል የሆነ ሰው ከእኔ ጋር ስላለህ ግንኙነት አንዳችም ፍንጭ እንዳያገኙ ተጠንቀቅ እንደ ዱሮህ ሲጠሩህ አቤት ሲልኩህ ወዴት በማለት ትሁት ሁንላቸው ገባህ። » «በእኔ አለመገኘት ጥበቃው ላላ «ተወው እባክህ ያለውን ሰው አብቃቅቶ ይሠራል ካስፈለገም ይቀጠርለታል» አለች ኮምጨጭ ብላ የበደል ካሳ ገፅ አክሊሉ አሰገደች አፍሳ በምታሸክመው ብር ያላሰበው ሲሳይ ቢሆንለትም ከአሰገደች ጋር በፈጸመው ድርጊት በተለይ አሰገደች ባሏን በሐሰት ወንጅላ ለመጣል ለወጠነችው ሴራ መሣሪያ መሆኑ እየዘገነነው ነው «የምድሩን በዘዴም በገንዘብም ኃይል እንደተወጣነው ወሮ አሰገደች እንደሚሉት የሰማዩንም ንሰሐ በመግባት እናረግበዋለን» ይላል አክሊሉ ራሉ ለራሉ አክሊሉ ካደረበት ሥጋት የተነሳ ከሰው ጋር ያለው ግንኙነት ከምን ጊዜውም የተቆጠበ ሆኗል ትች ዮሐንስ በትዳሩ ላይ ማግጦ የደቀለ ስለሆነ ከንብረቱ ሙልጭ ወጥቶ አሰገደች በጋራ ያፈሩትን በሙሉ መጠቅለል አለባት በማለት የአሰገደች ዘመዶች በመሸረብ ላይ ያሉትን ሴራ ዮሐንስ ከለማበት ቀን ጀምሮ የአአምሮ ሠላም የለውም ለዚህ ሁሉ ሴራ መክሸፍ ዋናውና ዓይነተኛ መፍትዜሄ የሸዋዬ ሐሰተኛ ነት በአደባባይ መጋለጥ ስለሆነ ዮሐንስ በሕግ ብቻ ሳይሆን በገንዘብ ጭምር ፍትሕን ለመግዛት ቆርጦ ተነስቷል የበደል ካሳ ገፅ ምዕራፍ ዐ የዓለሚቱ መረጃ ዕደና ቄ በአሜሪካ አገር የአንጀሕ ካንሰር በሸታቸውን በሕክምና ሲረዱ ቆይተው የሞቱት የዶር ወሚካኤል ማዴቦ ኑዛዜ በአርባቸው ዕለት ይፈስሳል ተብሎ ሲጠበቅ ባለመፍሰሱ በቤተሰቡ መካከል ሁከት ተፈጥሯል በእናቷ በኩል ቤተሰባዊ ግንኙነት ያላት የዮሐንስ እህት ዓለሚቱ ከኑዛዜው አለመፍሰስ ጋር ተያይዞ የደረሳትን ግርድፍ ነገር ግን በጣም ጠቃሚ ወሬ በማለዘብ ላይ ነች ወሬው ያልተጣራ ነው ቢሆንም «ትንሽ እሳት በሌለበት ጭስ አይኖርም» እንደተባለው ስለሆነ ጭራውን ጨምድዳ ይዛለች። » የመጀመሪያ የዓለሚቱ ጥያቄ ነበር «ሳይኖር አይቀርም ወደ ውስጥ ገባ በይና አልጋ የሚያከራየውን ልጅ ጠይቂ» አላት ካዳሚው ባሬስታው ዓለሚቱ ሻንጣዋን ቡና ቤት ውስጥ ትታ ወደ ውስጥ እንደ ገባች አንድ ያላጠናቀቀችው የቤት ሥራ መኖሩ ትዝ አላት መሰብሰቢያ ሊሆን ይችላል ብላ ከጠረጠረችው ክፍል ግራና ቀኝ ያሉት መኝታ ክፍሎችን ቁጥሮች አውቃ «እዚህ ወይም አዚያ ክፍል ይሁንልኝ» ማለት ነበረባት የበደል ካሳ ገፅ መ ው መመ በዚህ መካከል አልጋ አከራዩ ልጅ «ምን ፈለግሽ አልጋ ነው። ሸዋዬኮ የማታለል ንግሥት ብትባል አይበዛባትም» በማለት አክሊሉ ውስጥ ውስጡን እየተብሰከሰከ «ወደ ሥራ መፄዴ ነው» ብሎ ከቤት ወጣ ችት ከውጭ ሸዋዬ ከቤት ደግሞ አሰገደች እንደ ብራና ወጥረው ዮሐንስን የተወለደበትን ቀን እያስረገሙት ናቸው የበደል ካሳ ገፅ ዙሪያው ገደል በሆነ ጠባብ መስክ ላይ «አዙረኝ አታዙረኝ» ሽክርክሪት ተጫውቶ እንደ ወደቀ ልጅ ነሁልሏል ማንንም የቅርብ ጓደኞቹን አንኳ ስለጉዳዩ ተናግሮ ማሳመን ተስኖታል የአሰገደችን መንታ ምላስ የፈሩ ኒአንዳንድ ወዳጆቹ ገና ክወዲሁ ጆሮአቸውን ከልክለውታል ከጊዜ ወደ ጊዜ የኃዘኔታው ሚዛን ወደ አሰገደች እየደፋ መምጣት ዮሐንስን ይበልጥ ገለልተኛና ቆዛሚ አደረገው የበደል ካሳ ገዕ ምዕራፍ ሌላው የመረጃ ዕደናና የአብዮት ፈተና ዓለሚቱ ማንንም ሳትይዝ ማንንም ሳታማክር ሁለተኛ ውን የመረጃ ዕደና ዕቅደ ነደፈች የፅደናውን ቅደም ተክተል ሒደትና ስልት ታሳቢ የመረጃ ምንጮች በመሣሪያነት ሊያገለግሉ የሚችሉ ግለሰቦችና ተቋማት የፅቅድ ማስፈፀሚያ ወጪ በሚገባ ታሽተውና ተሰልቀው ሰትግበራ ተመቻቹ ዓለሚቱ ለወጠነችው ዕቅድ መሳካት በአሥሩ የአዲስ አበባ አውራጃ የቤተሰብ ችሎቶችና ቤተ መዛግብት አካባቢ በማንዣበብ የቅድመትግበራ ቅኝት አደረገች የዓለሚቱ ትኩረት ዳኞችና የቤተ መዛግብት ሹሞች ላይ አነጣጠረ አንድ የተባረከ ቀን ዓለሚቱ ክቤት ማለድ ብላ በመውጣት የአራዳውን ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተሳልማ ወደ አውራጃው ፍርድ ቤት ችሎትና ጽሕፈት ቤቶች ግቢ ለመግባት መንታውን መንገድ በማቋረጥ ላይ እንዳለች የሟች ዶር ወሚካኤል ማዴቦ ባለቤት ወሮ ትግሥት ሙሉጌታ መኪናዋን አቁማ ስትቆላልፍ አሻግራ አየቻት ዓለሚቱ ወደ ኋላ መስስ ብላ የሴትዮዋን እንቅስቃሴ ጠበቀች «ቅዱስ ጊዮርጊስ። የበደል ካሳ ገሪ «ዘኪሮስ ከበደ ይባላሉ አዲስ ናቸው በጣም ጥሩ ሰው ናቸው» በማለት ሲያወራ የመዝገብ ቤቱ ሹም እያነጋገራቸው ከነበሩት ባለ ጉዳዮች ጋር ተያይዘው ወደ ችሎቱ ቤት ገቡ ብዙም ሳትቆይ ዓለሚሜቴቋ ነገ ጧት ለመመለስ ወስና ከግቢው ወጣች ችችትጁ ዓለሚቱ አደባባይ ስትወጣ የመጀመሪያ ጊዜዋ አይደለም ከአምስት ዓመት በፊት እናቷ ወሮ ታደለች ላኢሶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውንና እሷ የእናቷ ብቸኛ ወራሽ መሆኗን ያረጋገጠችው በአዲስ አበባ አውራጃ ፍቤት የቤተሰብ ችሎት ነበር ያን ጊዜ ዓለሚቱ አንዲህ እንደ ዛሬ ከተራ ሰው ጋር መጋፋት አልገጠማትም ጥላዋ ክለላዋ አባቷ ያጅቧት ነበር የሁንዴ ቤኛ እውቶሞቢል ችሉሎቱ በር ድረስ ተሸክርክሮ ሲቆም ዳኛው ራሉ እጅ ነስቶ የተቀበላቸው ጊዜ ነበር ዛሬ ያ ሁሉ የለም ጊዜው የአብዮት ነው አደባባዩ ክብርና ሞገሱ ተገፍፏል የቀድሞው ሥርዓት አገዛዝ መልክ በፈርሉ ተገልብጧል የመደብ ሹም ሽር ደርጉ ሥልጣኑን ያሟሸው መሳፍንቱን መኳንንቱንና ባለሥልጣናቱን ክብራቸውን ገፍፎ በሶሻሊዝም ዕወጃ ንብረታቸውን ዘርፎ ወደ የማጎሪያ ቤቱ በመወርወር ነው አፈላው ግድያውና ስደቱ በቀድሞው ሥርዓት ተጠቃሚዎች ላይ ብቻ አልቆመም በከፈለው የደም መስዋዕት አብዮቱን ያቀጣጠለው ተማሪውና ምሑሩ ደርግን ገና ከምሥረታው ስለተቃወመ የሥልጣን ጥያቄው ወደ እርስ በርስ የበደል ካሳ ገዕ ግድያ ተሸጋግሯል የተቃዋሚዎችን ነጭ ሽብር ለመደምሰስ ብሎም አብዮቱን ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ለማሸጋገር በሚል ምክንያት ደርግ ቀይ ሽብርን አውጂል የእርስ በርስ ፍጅቱ ከከተማ እስከ ገጠር ከአደባባይ እስክ ጦር ሠፈር ተዛምቷል «አኔ አላማረኝም ዓይን እገላለጡ ወንድ የወለዳችሁ መልሳችሁ ዋጡ» የተባለለት ቀይ ሽብር የአብዮቱንም ወገኖች አልማረ በሥልጣን ጥያቄ ድርድር የለም አስፈላጊ ሆኖ ካገኘችው አብዮት ልጂን መብላት ትችላለች በሚል ርምጃ የደርግ አባላት የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ካድሬዎች ጭምር ወደ ወህኒ እየተጣሉ ናቸው የተመቱም አሉ አቶ ሁንዴ የቀድሞውን ሥርዓት ተጋፊና አገር ወዳድ ዲሞክራት ናቸው በመባል ከእስራት ተርፈዋልሱፁ በመንጥር ዘመቻም ቤታቸው አልተፈተሸም የቀድሞው ሥርዓት ታላላቅ ሰዎች ሚስቶች በመብራት እየታሰሱ ለሚሊሺያ ስንቅ ዝግጅት የግዳጅ ተሳትፎ በአውቶብስ አንዳንዴም በከባድ የጭነት መኪና ኤንትሬ ወደ ታጠቅ ጦር ሠፈር ሲወስዱ አመቤት ጽዮን ሞገሳ ግን የቤት ሠራተኞቻቸውን እንዲልኩ ተፈቅዶላቸዋል አቶ ሁንዴና ቤተሰቡ በአብዮቱ የጎሪጥ ባለመታየታቸው ቢፅናኑም በአንዳንድ የአብዮቱ ጨካኝ ርምጃ ከማጉረምረም አልተቆጠቡም አንድ ቀን አቶ ሁንዴ «ሁሉም መንገዶች ወደ ዓለም በቃኝ ያመራሉ» በማለት በአብዮቱ ላይ ተሳልቀዋል የሚልና የበደል ካሳ ገፅ ሌላም ጥቆማ ለቀበሌ ይደርሳል ጥቆማውን ለማጣራት የቀበሌው ጥምር ኮሚቴ በደብዳቤ ጠርቷቸው ቀበሌ ይሄዳሉ አቶ ሁንዴ ለምን እንደተጠሩ ባያውቁም የጥሪውን ቀንና ሰዓት አክብረው ተገኘ «ምነው ደህና መጡ።