Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convertir en PDF
  • Liste de lecture
  • Abrégé
  • Livre audio
  • Chercher
  • Télécharger
  • myzon
  • S'identifier
  • registre
English  አማርኛ  Français  العربية
Livre du jour

የበደል ካሳ 1.pdf


  • word cloud

የበደል ካሳ 1.pdf
  • Extraction Summary

የምትለው እማዬ ነች እኔን ከጠየቀችህ አዚህ ቅርብ ደርሼ መጣሁሆ ብላ ነው የወጣችው በላት «እሺ እኔን ውሸታም እንዳታደርጊ ቶሎ ተመለሽ አለና የማለዳዋን ፀሐይ ለመሞቅ ወደ አጥሩ ጥግ ተመለለሰ ከአንድ ወር በፊት እንዲሁ እንደዛሬው ማልዳ ስትሔድ አናቷ ከቤተ ክርስቲያን ሲመሰሱ ድንገት መንገድ ላይ ተገጣጠሙና የት ልትሔጂ ነው። በሰንበት ምድር ገና በጧቱ ምን ያንቀዝቅዥሻል።» አሰገደች ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የአእምሮዋን ጓዳ በመፈተሸ ላይ እንዳለች «መፍራት ካለብኝ እግዚያብሔርን ብቻ ነው» አለ ዮሐንስ የአስገደችን ስጋት የተረዳ መሆኑን በሚገልጽ ፈገግታና አካላዊ እንቅስቃሴ «አፄኔማ ንግግሩን የጨረኸን መስሎኝ» አለች «ሳይጀመር።» አለች አሰገደች እንደማባባል ብላ እነ ደረጀ ነገሩ ስላልተዋጠላቸው ለንቦጫቸውን እንደጣሉ ከአናታቸው አጠገብ ገለል አሉ ለአሰገደች እንጂ ለሌላው አቢቹ አዲስ አይደለም ለእሷ ግን አዲስ አካባቢና አዲስ የሕይወት አጋጣሚ ነው የሆነላት አቢቹ የከተተው ዘመድ አዝማድ በዕድሜ በፆታና በማዕረግ ከፍና ዝቅ እንደ ማለሰቱ በግብር ጊዜ በቅደም ተከተል የበደል ካሳ ገፅ ሁለት ቀን ሙሉ ከደብረ ብርዛሃንና ከሸኖ ጭምር በመጡ አልቃሾች ከጥፍር ውስጥ እምባ በሚያስወጣ ሙሾ ድርደራ ተለቅሶ በሣልስቱ የቀብሩ ሥርዓት በደብረ ሊባኖስ ገዳም ጾተፈፀመ ፊታውራሪ የተቀበሩት ከ ዓመት በፊት ባለቤታቸው ወሮ አበራሽ ቱፋ ከዚህ ዓለም በተለዩ ጊዜ ባሠሩላቸው መቃብር ቤት ነው አቶ ሁንዴና ቤተሰቡ እስከ ሃሰባቱሃ በዚያው አስተዛዛኙን ሃለ ተበሉ ከርመው በሳምንቱ መጨረሻ ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ እንደ ተመለሱም ለቅሶ መቀመጣቸውን የሰማ ታላላቁ ሰው ሁሉ ግቢውን አጨናንቆት ከረመ አሰገደች በየአጋጣሚው አማቶቿን እጅ በመንሳትና እንዴት አደርሽ» ስትባል መሰንበቷን ወድዳዋለች የሁለት ንለጆች እናት እስከሆነችበት በእስከዛሬ ቆይታዋ ከአማቶቿ ጋር ይህን ያህል መቀራረብ ኖሯት አያውቅም አሰገደች ግቢ የምትሔደው በአብዛኛው በታላላቅ ዓውዳመቶች «እንኳን አደረሳችሁ» በማለት እጅ ለመንሳት ነው።

  • Cosine Similarity

ያው አሁን ባለቤት መጥቷል ግቢ» አለ ዮሐንስ በእጁ ወደ በረንዳው አእያመለከተ «እሺ» አለች አንገቷን ሰበር አድርጋ «በረንዳ ላይ ብንሆንስ ለሚለው የዮሐንስ ጥያቄ መልስ ከመስጠቷ በፊት አምረው ከተሠሩት የበረንዳ ወንበሮች አንዱ ላይ ዘፍ አለች የበደል ካሳ ገፅ «ለእኔ ቡና ለአለጉ የለንበት ቁርስ» አለ ዮሐንስ አሰገደች ያመጣችውን መጽሐፍ ከእጂ እየተቀበሰ «አኔም ቡና ይብቃኝ» የሚለውን የአለሰገደች መግደርደር የተረዳው ዮሐንስ አንዲያውም የጠበቃ ቁርስ ይሁንላት» አለ ድምፁን ከፍ አድርጎ «የጠበቃ ቁርስ ደግሞ ምን ፔሆን። » አለች አሰገደች የዛሬው ጭውውት ከመጽሐፍ ግምገማ በላይ መሆኑን በሚያንጸባርቅ መድምፀት ዮሐንስ የስልክ ጥሪ ለመመለስ «ይቅርታ መጣሁ» ብሎ ጻወደ ቤት ገባ ምንም አይደል በማለት አሰገደች አቀማመጧን አደላደለች የጓደኛዋ የራሔል አበራ ጓደኛ የሆነው ዮሐንስ አሷ በሌለቸበት በዚህ መልኩ ለምን እንዳነጋገራት ስታወጣና ስታወርድ ሠራተኛዋ እንደገና ቡና ይዛ ቀረበች ዮሐንስም መጣ ቡናውን እየተቋደሱ ላሉ «አባባ ጌቶች ጠርተውኛል» አለ ዮሐንስ የበደል ካሳ ገፅ በደህና ነው። መልካም ግብዣ» «መቸ ግብዣ ሆነ ቸፅዕዛዝ ነው የእኔ ፃሳብ አብረን ወጥተን ራሔልን ይዘን ራስ ሆቴል ምሳ እንድንበላ ነበር» አለ ዮሐንስ በቁጭት «ግድ የለም በበኩሌ ቁርሱ በዚህ ላይ ውይይቱ ከምጠብቀው በላይ ነው የረካሁት ከልብ አመሰግናለሁ በማለት አሰገደች ለመሔድ ብድግ አለች «ቀይ እንጂ እሸኝሻለሁ» «የዕለቱ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዬ ስለሆነች ቀስ እያልኩ በአግሬ እንዳዘግም ፍቀድልኝ እንደሱ ከሆነ እሺ» አለ ዮሐንስ ራሔል በሌለችበት ጓደኛዋን በመኪና ይዞ ሲሔድ ቢታይ የሚናፈሰውን አሚሜታ በማሰብ ዮሐንስና አሰገደች የተሰነባበቱት አንዱ በሌሳው ልብ ውስጥ ቦታ ተደላድለውና በስሜት ተናብበው ይመስላል አሰገደች እንደዚህ ደርዝ ያለው ጭውውት ከወንድ ጋር ያደረገችበት ጊዜ መኖሩን ለማስታወስ ሞክራ አልሆነላትም «ራሔል ምንኛ ታድላለች እንኳን ፈልጎና ለምኖ ተለምኖ ከማይገኝ ዮሐንስ ጋር አንሶላ መጋራቷ ከመልኩ ክትክለ ሰውነቱ የጠባዩ በዚህ ላይ ምሁራዊ ብስለቱ ከሁሉም በላይ ደግሞ ጌታ የጌታ ልጅ ቢጠሩት የማይሰማ አግር ጆሮ እስኪደርስ ቢኬድ የማይገኘውን ዮሐንስን ትታ ወደ ፓሪስ የበደል ካሳ ገፅ ለመሔድ መወሰኗ ስህተት ነው ትልቅ ስህተት። አሁንስ የተምታታብኝ ሯሰለኝ በማለት አሰገደች መቀመጫዋን ከበርጩጨማ ዓይኗን ከየካ ላይ አነሳች እንደገና ቆም ብላ ፊቷን አኮሳተፈረች «አልተሳሳትኩም እንዲያውም አንዳንድ የትልልቅ ሰው ልጆች በውርስ ያገኙትን ሀብትና ንብረት በማባከን የፅለት ጉርስ ያመት ልብስ አያረረባቸው መንጠው ወደ ደኻ ጎራ መቀላቀላቸውን እያየንና ኔየሰማን የባለርስት ደኻ የለም ብሎ መደምደም አይቻልም ስለዚህ የካም ሳያጣ ያጣ ዋልጌና ከንቱ ባለርስት ይዞታ የመሆን አሳዛኝ ዕድል ሊገጥመው እንደሚችል ማሰብ ይችላል አሰገደች ቀን የጎደለበትን የካን በምናቧ ለመፍጠር አሟጋች ጭብጦችን አፋጭታና ራሷን በራሷ ሞግታ በመርታቷ ደስ አላት «የካ የደኻ ይዞታ ቢሆን ኖሮ ደኑ ተመንጥሮ ግርማ ሞገሱ ተገፍፎ ገመናውን መሸፈን የተሳነው አሳዛኝና አስቀያሚ ተራራ ይሆን ነበር በደነዘ ምላጭ እንደ ተቦደለሰ ራስ እዚህም አዚያም ደኑ ሲመነጠር ሲጨፈጨፍ ተገጣጥቦ ውጡበቱና ልምላሜው ወደ ዓይን ቃር በተለወጠ ነበር የካም እኮ ማን ያውቃል አንድ ቀን ቀን ይጎድልበት ይሆናል» አለች በቅናትና በቁጭት «የዚህ እሰጥ ገባ ድምዳሜ ከትልቅነት ወደ ትንሽነት ከሀብታምነት ወደ ድኽነት ቁልቁል እንደካሮት ማደግ ካለ በግልባጩም ከትንሽሸነት ወደ ትልቅነት ከድኽነት ወደ ባለጸግነት ዘሸሙዴ የበደል ካሳ ገፅ ሽቅብ የማደግ የመመንደግ ተስፋ መኖሩ አያጠራጥርም ዋናው ነገር እንደምንም ታግሎ የድኽነትን ቀለበት መስበሩ ላይ ነው» በማለት የመጽናናት ተስፋ ፈንቅሎ ባወጣው ስሜት ተሞልታ አቋርጣ ወደ ነበረርዙ ንባቧ ተመሰሰች አሰገደች አንዱና ዋናው ጊዜ ማሳለፊዋ መጽሐፍ ማንበብና ስፖርት ነው ቅኔ የቆጠረችበትን የበዐታ ገዳምና በዘማሪነት ያገለገለችበትን ቅድስት ሥላሴ ካቴድል አሁንም አልፎ አልፎ ትጎበኛቸዋለች ሲኒማ ትያትር ፓርቲ ሽርሽር ያሰዚያም መኪና ውስጥ እየተዝናኑ ኬክ ለስላሳ ቡና በወተት መጠጣት ማጣጣም መደሰት ሰአሷ እንግዳ ነገሮች ናቸው አንዳንድ ጊዜ መልአክቱ ጠጠር ቢልባትም የአሰገደች የንባብ ምርጫ ከአማርኛ ይልቅ የእንግሊዘኛ መጻሕፍት ናቸው መጻሕፍቱን የምታገኘው ከቤተ መጻሕፍትና ከአንዳንድ የጓደኞቿ ክንፈር ወዳጆች ነው ባነበበቻቸው መጻሕፍት ላይ አልፎ አልፎ የሚከፍቱት ሒሳዊ ግምገማ ዮሐንስ ሁንዴንና ተስፋዬ አስራትን ይበልጥ እንድትቀርባቸው አድርዓታል በግምጋሜው ከእነ ዮሐንስ አንሶ ላለመገኘት አሰገደች አንዳንዶቹን መጻሕፍት ደጋግማ የምታነብበት ጊዜ አለ «የተዋሱትን መጽሐፍ አዘግይቶ በመመለስ አንደ እኔ አሚወቀስ ደንበኛ ይኖር ይሆን። አለ ዮሐንስ ሌላ ገና ያልተነካ ጉዳይ ወደፊት እንደሚኖር በሚያስተጋባ ድምጽ የበደል ካሳ ገፅ አሰገደች መልስ ሳትሰጥ ቀደም ሲል ነፍሷ ሹክ ያለቻትን የዮሐንስን «ሳይጀመር» ከሚለው ገነን ካለ ቃል ጋር ለማዛመድ ሞከረች ዮሐንስ የአሰገደችን መልስ እየጠበቀ መኪናውን አስተካክሎ አቆመ የመኪናዋን ተስተካክሎ መቆም በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ይጠባበቅ የነበረው ሳተና አስተናባሪ በሹፌሩ በኩል ጠጋ ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ ትዕዛዝ ለመቀበል አሰፈሰፈ አሰገደች ሰቅዞ በያዛት ድብልቅልቅ ስሜት ውስጥ ተዘፍቃለች «ምን ልበል። » አለች አሰገደች የአሰገደች ጥያቄ ከመብረድ በላይ መሆኑ የገባው ዮሐንስ «የልማድ ጉዳይ ነው ኮት እንደለበስኩ መቀመጥ አይሆንልኝም» አለና አስተናባሪውን ለመጥራት ደወል አንቃጨለ የበደል ካሳ ገፅ አዚያው አካባቢ ኖሮ አስተናባሪው ገርበብ ያለውን በር ከፍቶ ዘው አለና እጁን ወደኋላ አጣምሮ ቆመ ምን ይምጣ። » አለች ራሔል ፈገግ ብላ «ምናልባት» አሉ እናቷ ከተቀመጡበት አእአየተነሱ ራሔል መኝታ ቤቷን ዝግታ የተነገራትንና ያሳዩዋትን ሁሉ ስትለማመድ ከርማ በራሷ ተማምናለች ቤተ መንግሥት የበደል ካሳ ገፅ የምትቀርብበት ቀን አንድ ሳምንት ሲቀረው አባቷ ክከአልፍኝ አስከልካይ ጽቤት ጥሪ ደርሷቸው ሔዱ «ግርማዊ ጃንሆይ ሰሞኑን በአስቸኳይ ሥራ ስለተያዙ የዚያን ዕሰቱ ዐቃቤ ሰዓት ተሰርዛጻል የእርሶን ልጅ አመቤቴ ምሚኒስትሩ ተቀብለው እንዲያሰናብቱ ፕሮግራም ተይዞላቸዋል» የሚለውን የፕሮግራም ለውጥ ፊታውራሪ የተቀበሉት «ልዕልት አመቤቴስ ቢሆኑ ያሳደጓት አይደሉ ጥሩ ነውኬ በማሰት ነበር የራሔል ወላጆች ከቅዳሜ ምሳ አስከ እሁድ ራት የጣሉት ሙሉ ግብር የራሔልን ማንነት በውል ያረጋገጠ ፈንጠዝያ ነበር ከግብሩም በላይ በማግሥቱ ሰኞ ጠዋት ልዕልት ተናኘ ወርቅ ኃይለ ሥላሴ ዘንድ ቀርባ እጅ አንድትነሳ የተሰጣት ፅድል የራሔልንና የወላጆቿን ማንነት አስመሰከረ «አገርሸንና ወገንሸን አስታውሽ አንዳትረሽ ስትመለሽ የምንድርሽ እኛ ነን በማለት ልዕልት ሰባ አምስት ግራም የወርቅ ሐብል ሲያጠልቁላት ፊታውራሪ አበራና ወሮ ሰጋ ሴቱ ሲቃ እየተናነቃቸው «የአመቤታችንን ሕይወት ያለምልምልን በማለት ደስታቸውን መሬት እየሳሙ ገለፁ ራሔል በውጭ አገር ከፍተኛ ትምህርት ለመማር ካገኘ ቸው ዕድል ይልቅ በዚህ ሳቢያ በልዕልት ዘንድ ያገኘቸው ሞንስ ፋይዳ ይበልጥ ገነነ የበደል ካሳ ገዕ ራሔል የልዕልትን ቡራኬ ተቀብላ እቤት ከመድረሷ በፊት ዜናው ቀድሞ ደርሶ ኖሮ ወዳጅ ዘመድ በፅልልታ በዘፈንና በጭፈራ ተቀበላቸው ራታውራሪ አንኳን ደስ አላችሁ በማሰት ሰሚመጣው የደስታቸው ተካፋይ ግብር አንዲጣል ትዕዛዝ ሰጡ ፈንጠዝያው ራሔል ካገር አስከ ወጣችበት ቀን ዋዜማ ድረስ ቀጠሰ ራሔል ሰሌላ ግብዣ ጊዜ ሊተርፋት ስላልቻለ አነዮሐንስ አቅደውት የነበረው የራትና ዳንስ ምሽት ፕሮግራም ተድበስብሶ ቀረ ግብዣው ቢስረዝም ጓደኞቿ በመዋጮ የገዙላትን ስጦታዎች ቡድኑን በመወከል ዮሐንስ ዓለሚቱና አስገደች እቤቷ ድረስ በመውሰድ ለራሔል አበርክተውላታል በጓደኞቿ መካከል በአርሷ ምክንያት የተፈጠረውን አለመግባባትና መቀያየም በማስታወስ ሆድ ብሷት አሰቀስች ዮሐንስና ዓለሚቱ «ራሔል ምን ማለትሽ ነው። ራሔል የምታፈቅረውን ዮሐንስንና ሮጣ ያልጠገበችባትን አዲስ አበባን ትታ እንደ ፀሐይ ከሚሞቀው የወላጆቿ ጉያ ወጥታ በባዕድ አገር ፈታኙ የትምህርት ዓለም ውስጥ አገባች ከረምረም ብላለች ሙር ሙአየበደል ካሳ ገዕ እዚህ አዲስ አበባ በእሷ ካገር መልቀቅ በተፈጠረው ክፍት የፍቅር ቦታ ራሳቸውን ለመተካት አንዳንድ ጓደኞቿና ሌሎችም ጭምር ዮሐንስን ተጫርተው ነበር በስውርም በግልፅም በተደረገው ጨረታ የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ጨረታውን ታሸንፋለች ብለው ያልጠበቋት ልጅ መርታቷን ከጨረታው ተሸናፊዎች አንዷ አልማዝ ተስፋ እግዚእ ስለጨረታው ከርቀት ለምታ የታዘበች በመምሰል በእግረ መንገድም ነፃ የትምህርት ዕድል እንድታፈላልግላት በመጠየቅ ለራሔል ደብዳቤ ጽፋ አረዳቻት አልማዝ የራሔልን አድራሻ ያገኘችው በእስኮላርሽፕ ለበብ ከራሔል አህት ከሠናይት አበራ ነው ሁለቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድ መቤት ባልደረቦች ናቸው ራሔል ደብዳቤው እንደደረሳት ለጓደኞቼ መልሰ ልፃፍ ወይስ ነገሩን ንቄ ልተወው በሚል የሀሳብ ሙግት ውስጥ ከረመች በመጨረሻ ራሔል ደብዳቤ መፃፍ እንዳለባት ወሰነች የበደል ካሳ ገፅ ያሔጨሰ ደዳፍን የተወደዳችሁ ጓደኞቼ ዮሐንስ ሁንዴ ዓለሚቱ ሁንዴ ተስፋዬ አሥራት አሰገደች ደምሴ እንደምን አላችሁ እኔ ደህና ነኝ ወደ ፓሪስ እንደመጣሁ ስለ አጭሯ ቆይታዬ አንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ ከቤተሰብና አናንተን ከመሳሰለ ጓደኛ መለየት ስለፈጠረው ስሜት ደብዳቤ መጻፍ ጀምሬ ነበር እያንዳንዳችሁን ሳስታውስ ቁም ነገራችሁ ቀልዳችሁ በተለይ ዮሐንስ ፍቅርህ ይመጣብኝና ሆድ ይብሰኛል ድንገት የሚንዝቀዝቀው እንባዬ ወረቀቱን ላይ እየተንጠባጠበ ደብዳቤዬን ያበሳሸብኛል ይህም እንደገና ያናድደኛል በሌላ በኩል ማልቀሴን ሰው እንዳያይብኝ ራሴን ደብቃለሁ የናፍቆት ዘሸታ ነበር ይኽንን ደብዳቤ የጻፍኩት ግን ከበሽታዬ ተፈውሼ ነው ዘመድ አይጥፋ አሰገደች ደምሴ ሎተሪ እንደወጣልሽ ሰማሁ አንኳን ደስ አለሽ ዮሐንስም እንኳን ደስ አለህ ዓለሚቱንና ተስፋዬን ምን እንደምል ግራ ስለተጋባሁ እንዲሁ ብርታቱን ይስጣችሁ ዮሐንስ «ወንድ ልጅ ይለ ተቃራኒ ፆታ ጭን ሙቀት ውሎ ማደር የለበትም» በማለት እንደዋዛ ጣል ታደርግ የነበረውን ተልድ አስታውሳለሁ በፊት ከትምህርት ቤት በኋላም ከሥራ ቦታ በየጊዜው ታስኮበልለኝ እንደነበር ታስታውሳለህ አንተ ብቻ ሳትሆን እኔም ካንተ እቀበል በነበረው ሙቀት አረካ እንደነበር የበደል ካሳ ገዕ አልደበቅሁም ያም ሁሉ ሆኖ በስተመጨረሻ እንደማንጋባ ላውቀው ፊቴን ወደ ትምህርት አዞርኩ ከእኔ ጋር ከተለያየን በኋላ ያለ ጭን ሙቀት ትቆያለህ የሚል ግምት አልነበረኝም በእኔ ቦታ ስለምትተካዋ ወጣቴኔ አስብ ነበር ቅናት ቢጤም ጎነታትላኝ ነበር «ትውሰደዋ። » ከማለትም ተቆጥበዋል የዮሐንስ ወላጆች በልጃቼው የግል ሕይወት ውስጥ ጣልቃ የመግባት ፍላጎት ባይኖራቹውም አንዳንድ ጊዜ ጋብቻን እስታክከው በሚሰነዝሩት አስተያየት ያለብንን የሠርግ ጥሪ ዕዳ ዮሐንስን ስንድር እንከፍለዋለን» ይላሉ የዮሐንስ ጋብቻ በሀብትም ሆነ በማዕረግ ክወላጆቹ አቻ ከሆነ ቤተሰብ ጋር እንዲሆን የሁሉም የዮሐንስም ጭምር ፍላጎት ነው ችችችና ራሔል የጋብቻ ፕሮግራሟን ሰርዛ ፊቷን ወደ ትምህርት ዓለም የመለሰችው ዮሐንስ ቢያፈቅራትም ሊያገባት ዝግጁ እንዳልሆነ ከተረዳች በኋላ ነው ራሔል ከሔደች በኋላ የዮሐንስ ውሎ ከማን ጋር እንደሆነ ወለጆቹ መረጃ እንዳላቸው ዮሐንስ ደርሶበታል ዮሐንስ ክአሰገደች ጋር የመሠረተው ጊዜያዊ ጓደኝነት ጥያቄ ከማስነሳቱ በፊት እንዲቋረጥ መላ እየመታ ነው አንድ ቀን ዮሐንስ ፈራ ተባ እያለ «የዘለቄታ ዓላማሽ ምንድነው። ከአቅሟ በላይ መሸከም የማትችለውን ትልቅነት ባትጭንባት» «ተስፋዬ ላቋርጥህ አሰገደች የኢትዮጵያ ቸርችል የማትሆንበት ምክንያት የለም» አለ ዮሐንስ ከመቀመጫው በከፊል ብድግ ብሎ «አንቧጮ አድባር የሚሆንበት አገር ውስጥ አይደለንም «ተው ባክህ የጊዜ ጉዳይ ነው የማይለወጥ ነገር የለም» «አዚህ ላይ ወራጅ አለ ዮሐንስ ይኸንን የተጋነነ አመለካከት አሰገደች ራሷም እንኳ የምትቀበል አይመስለኝም» «ካልክስ ንትርካችን ሌላ የነገር ጉጥ ሳያወጣ ላለመስማማት ተስማምተን አዚህ ላይ ልናቆመው እንችላለን» አለ ዮሐንስ በታከተ ስሜት «ስለ አሰገደች ከዚህ በላይ መነጋገር ጊዜንና ውይይትን ዋጋ ማሳጣት ነው እንዳልከውም እዚህ ላይ ማቆሙ ይመረጣል» አስና ተስፋዬ የዮሐንስን መልስ ሳይጠብቅ ከሳሎን ወደ በረንዳ ወጣ ዮሐንስ የጓደኞቹን አፍ በመፍራት ግብዣውን ትቶ አስገደችን ኦሜጋ የእጅ ሰዓት ገዝቶ ሸለማት ሦ ደበሽ የበደል ካሳ ገፅ ምዕራፍ የዮሐንስ ስብእና ዮሐንስ ፈረንጆች «የብር ማንኪያ ባፉ ይዞ የተወሰደ» እንደሚሉት ዕድለኛ ልጅ ነው ቢጠሩት ወይ የማይል ቤተስብ አባል ነው የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ አበባው ዳግማዊ ምኒልክ ትቤት ጨርሶ ከዩንቨርስቲ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስና በሕዝብ አስተዳደር በማዕረግ የተመረቀ ነው ዮሐንስ ሲናገር ረጋ ሲሔድም ረጋ ስለሚል የቤተሰብ ስሙ ነው ሳቅና ጨዋታ ይወዳል። እንዲህም ሲል ትርጉሙን አነበበ «አጎናፈረ እንዳፈር እንደራስ ፀጉር አብዝቶ በላይ በላዩ አብዝቶ ስጠ አለልክ ቸረ ለገሠ አጎናፍር የሰው ስም ሀብታም ልጅ ቸር ዕድሉ አጎናፍር አንደዝማ የሆነ ያቶ አገሌ ቤት አጎናፍር ነው እንዲሉ» የሚለውን ተስፋዬ አንብቦ ሲጨርስ «ተስፉ ሙት አንደ ዛሬ ተሳክቶልህ አያውቅም» አሰ ዮሐንስ በአድናቆት «አንተ አምልጦዛል ከልጆችህ የአንደኛው ስም አጎናፍር ሊሆን ይችላል እናቱ የምትስማማ ከሆነ» አለ ተስፋዬ አሰገደችን በሹፈት መልክት ብሉ ዮሐንስ ከተመረቀ በኋላ ሥራ የጀመረው በኢትዮጵያ አየር መንገድ መሥሪያ ቤት ነው በአየር መንገድ የሦስት ዓመት ቆይታው ባገኘው ልምድና ከወላጆቹ በተሰገሰው ጎጆ መውጫ ጥሬ ገንዘብ ቤትና ቁሳቁስ ተደራጅጆቷል በኮሚሽን ኤጀንትነት የጀመረውን የግል ሥራ ወደ አስመጪና ላኪነት ኩባንያ ለማሳደግ ቅድመ ዝግጅቱን የበደል ካሳ ገዕ አጠናቋል ዮሐንስ ያለበቂ ጥናት የሚያከናውነው ሥራ የለውም ጥንቁቅ ነው ጥራት ባለው ሥራ ያምናል «ዮሐንስ በአጭር ጊዜ ቀጭን ጌታ ለሰመሆን ቆርጦ ተነስቷል» አሰ ተስፋዬ ሥላቅኛውን አንድ ቀን ስለሥራ ጎደኛ ሞች በብርጭቆ ዙሪያ ተኮልኩለው ሲጫወቱ «የአንድ ሥራ ቁምነገር ገንዘብ ማስገኘቱ ብቻ አይደለም» አለ ዮሐንስ አቋሙን ግልጽ ለማድረግ በኢኮኖሚክስ ጠበል እስቲ በል አጥምቀን» አለ ተስፋዬ አግቦውን «ትልቁ ቁምነገር ዛሬ የተገኘችው ሳንቲም ነገ ሌላ አዲስ ሣንቲም ወልዳ አንድታድር ከማድረጉ ላይ ነው ይህን ለማደረግ የሚያስችለው ፅውቀትና ተመክሮም ከአንዱ ወደሌላ መተላለፍ መቻል አለበት እያንዳንዱ ባለሙያ የዜግነት ግዴታውን በብቃትና በንቃት የመወጣት ኃላፊነት አለበት የአገርና የወገን ጥቅምና ፍላጎት መሣሪያ ያልሆነ ዕውቀት የጋን መብራት ነው» አስ ዮሐንስ «ዮሐንስ። ይኸውም በዚህ ሰው ትምህርት ላይ አገሪቱ ያፈሰሰችው ገንዘብ ዕውቀትና ጉልበት በከንቱ የተከሰረ መሆኑን በትምህርት ቤት ያሳለፈው ጊዜ በከንቱ የባከነ መሆኑን ክዶ መሟገት አይቻልም» «የተከበራችሁ ሊቃነ ሲቃውንት» አለ ተስፋዬ በሹፈት «ከቪህ በላይ እንድትጠቀጥቁኝ ዕድል አልሰጣችሁም ጉንጭ አልፋ ንትርካችሁን ተንግዲህ የምትቀጥሱ ከሆነ ስጋበዛችሁኝ መጠጥ አመስገኝ መስናበቴ ነው» «ከኖሩ ልጥቅ ከሔዱ ምንጥቅ» በሚለው የአስገደች መልስ እየተገረመ ተስፋዬ ብድግ ሲል ዮሐንስ እዚህ ላይ ይቁም» በማለት መልሶ አስቀመጠው ችችችት አስገደች ዘወትር ረቡፅና ቅዳሜ ሌሊቱን የምታሳልፈው ከዮሐንስ ጋር ነው በእነዚህ ዕስታት በጊዜ ታጥባ ታጥና ፀጉር ሠሪ የበደል ካሳ ገፅ ቤት ብላ ከቤት ትወጣለች የፀጉር ሥራው እንዳበቃ ለዮሐንስ ስልክ ትደውልስትና መጥቶ ይወስዳታል ይህ ፕሮግራም በተፈጥሮአዊ ግዴታ የወር አበባ ጊዜ ወይም ከአቅም በላይ የሆነ አስገዳጅ ምክንያት ካላጋጠመ በስተቀር አይተጓጎልም አዲስ ትያትር ወይም ፊልም ካለ በመኪና ውስጥ መቆያቸውን ከስክስው ወደዚያው ያመራሉ ከሌለ ራት በጊዜ በልተው ስናይት ክለብ ጭፈራ ይዘጋጃሉ ቪላ ዲዳናፖሊ ቪላ ቬርዴና ራስ ሆቴል የእነ ዮሐንስ ምርጫ ናቸው ዮሐንስ ወደ ናይት ክለብ ሲያስብ የጨዋ ልጅነቱን ጭምትነቱንና ርጋታውን ከቤት ትቶ ነው የሚወጣው የየምሽቱን የናይት ክለብ ቆይታ የተፈቀደ «የትንሽ ፅብደት» ጊዜ ይስዋል በለስላሰው ልስ የሚጀመረው መውረግረግ ሩምባ ሳምባ ታንጎ ቻቻ እያስ ወደ ቡጊ ቡጊ ርክ ኤንድ ሮል ይሸጋገራል ዳንስኛችን ያለውድ በግድ ተቃቅፈው እንዲሽከረከሩ የሚያስገድደውን ልስን የአካል ማፍታቻ የስሜት ማማሟቂያ ይሉታል አካል ለአካል መፋተጉ መተሻሽቱ የሽቶው እወዳ የመጠጡ ግፊት ሲታከልበት ይደራሉኹ ለብ ያስው ስሜት ወደ ግለት ይለወጣል ዳንሰኛው ይቁነጠነጣል እዚህ ደረጃ ሲደረስ ዳንሱ ይቋረጣል ከአዳራሽ ይወጣል ከአጭር ጊዜ ማረፊያ ክፍል ቆይታ በኋላ እንደገና ወደ አዳራሽ ይመጣል ይኽንን ነው ዮሐንስ «የትንሽ ዕብደት» ጊዜ የሚሰው ዮሐንስ ዘፈን ይወድዳል ዳንስም ነፍሱ ነው «ዳንስ ጠግቤና ረክቼ ከዳንስ መድረክ የተላቀቅሁበት ጊዜ የለም ድካም ሲጫነኝ ከዚያ በላይ ቆይቶ ስመደነስ አቅም ሲያንሰኝ የዳንሱን የበደል ካሳ ገፅ ወለል እሰናበታለሁ ዘፈንና ዳንስ በተጨመረ መጠን ይበልጡን ያለኘኛል እንደ ምግብና መጠጥ ጭማሪው ቁንጣን አያስይዝም የሚለውን የዮሐንስ አስተያየት አሰገደች ታደንቃለች አሰገደች ዮሐንስ የሚወድደውን ሁሉ መውደድን አየተለማመደች ነው ፄ እየደነሰ ዳንክ የሚራበው ዮሐንስ ከናይት ክለብ የሚወጣው ሙዚቀኞቹ መሣሪያዎቻቸውን መለባሰብ ሊጀምሩ ነው ከቪያ በኋላ ከጓደኛው ጋር ወደ ቤቱ ይመርሻል የተዛባባቸውን የሌሊትና ቀን ፍርቅርቅ ለማስተካከል ጧ ብለው ይተኛሉ እንደ ምንም ለቁርስ ይነሳሉ ብርቱ ጉዳይ ከሌላቸው ተመልሰው ይተኛሉ ፍቅራቸው ዮሐንስ ከጠበቀው በላይ አየጠና ሔዷል «አሰገደች ኮ የዳንስ ወለል ኮከብ የአልጋ ንግሥት ብትባል አይበዛባትም» የሚለውን የዮሐንስን አድናቆት ተስፋዬ አይቀበልም አለመቀበል ብቻ አይደለም ዮሐንስ በፈጠረህ ፊት አትስጣት አካሔድህ አላማረኝም ከወላጆችህ እንዳትቆራረጥ አስብበት» በማለት የመገሰጽ ያህል ይመክረዋል ዮሐንስ ግን በአሰገደች ሁለንተና መማረኩን መደበቅ እያቃተው ነው ወንድሟን ከአሰገደች ለማላቀቅ ዓለሚቱ የተቻላትን ሁሉ እየሞከረች ነው ሙከራው ያተኮረው ዮሐንስ ሌላ አማራጭ አንዲኖረው በማድረግ ነው ለውጥ የሕይወት ማጣፈጫ ቅመም ነው» ትለዋለች ዓለሚቱ ወንድሟ ከአንድ ሴት ጋር መሟዘዙ ተገቢ አለመሆኑን ለማስረዳት የበደል ካሳ ገፅ አባባሉን አየለዋወጠች እህቱ ለማስተላለፍ የምትሞክረውን መልእክት ዮሐንስ ገሸሽ ስለሚያደርግባት ዓለሚቱ አታኮርፍም አንድ ሌላ ቀን ዓለሚቱና ተስፋዬ የፆታ ጓደኝነትን በተመለከተ ሲጨዋወቱ «ወንድ ልጅ ባቡር ይመስል ዘላለም በአንድ ሐዲድ ላይ ሲሔድ መኖር የለበትም» በማለት ተስፋዬ የሰጠውን አስተያየት «አንተና እህቴኮ የፆታ ጓደኝነትን ወደ ሸቀጥነት ዝቅ አያደረጋችሁት መሆናችሁን የተረዳችሁት አይመስለኝም» በማለት ጠቅ አደረጋቸው «ዮሐንስ የጭቃ ጅራፉን አመጣ ለዛሬ በዚሁ ይብቃን ካስፈለገም ሌሳ ጊዜ እንመለስበታለን» በሚሰው የዓለሚቱ አስተያየት ተስማምተው የጭውውታቸውን ርዕስ ለወጡ ዮሐንስ አሰገደችን የያዛት ለመሸጋገሪያነት ነበር ከዚህ በኋላ ጎጆ በሚያስወጣት ድጎማ አግባብቶ ሊያገላት አቅዶ ነበር አሰገደች በበኩሏ ዮሐንስ ከአጂ እንዳይወጣ አቅሟ የቻለውን ያህል አጥብቃ ይዛዋለች አንዱ የሌላውን እሱ የአሷን እሷም የእሱን ድብቅ አጀንዳ አያውቁም የበደል ካሳ ገዕ ምዕራዊ ሹመት ያዳብር ግጫ ሹመት ያዳበር» ለማሳት የመጣው ወዳጅ ዘመድ የተስፋዬ አሥራትን ቤት ሞልቶ ግቢው ጭምር ለው በሰው እየሆነ ነው የማስተናገዱን ሥራ ወላጆቹ እህትና ወንድሞቹ ሌላ ሰው ጣልቃ ሳያስገቡ ቀጥ አድርገው ይዘውታል የደስ ደስ የመጣው መጠጥ ከላይ ከላዩ ቢጠጣለትም አንዱን ክፍል የመጠጥ መጋዘን አስመሰሎታል ሬድ ሌብል ብላክ ሌብል ሺቫስ ውስኪ ናፖሊዮን ሬሚ ማርቲን ኮኛክ ቢፍ ኢተርና ድራይ ጂን አንደዚሁም ሻምፓኝ በደርዘን በደርዘን አንዱ በሌላው ላይ ተከምሯል አንዳንድ የኤምባሲ ሰዎች ከውስኪ ጋር ምርጥ ምርጥ የወይን ጠጅ በደርዘን አምጥተዋል በተስፋዬ ረዳት ሚኒስትር ሆኖ መሾም የማስታወቂያ ሚኒስትሩን ያላመሰገነ ሠራተኛ አልነበረም ተስፋዬ አንቱ የተባለ ጋዜጠኛ ነው በየጋዜጦቹ በተለያየ ደረጃ ተመድቦ አገልግሏል በምሥጉን ባለሙያነቱ ተመርጦ ወደ አሜሪካ ተልኮ ከኮሎምቢያ ዮኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት የመጀመሪያ ድግሪውን አግኝቷል ተስፋዬ አባቱ የቅዱስ ራጉኤል ደብተራ እንደነበሩ እርሱም በዚያው ደብር በዲቁና ማገልገሉን የሚያውቁ ጓደኞቹ «ደብተራ» በሚል የቅፅል ስም ይጠሩታል ብልህ አዋቂ የቀለም ለው ለማስት ፈጂር ጐ። አለ ዮሐንስ ምንም ዓይነት ስሜት ሳያላይ «እ እ አኔ አላውቅም» ብላ እንደማፈር ባለ ስሜት አንገቱ ሥራ ልጥፍ አለች ዮሐንስ የሚለው ጠፍቶ ራቁት ጀርባዋን በቀኝ እጁ እያሻሸ በግራ አጁ እንዳቀፋት ትንሽ ቆየ ግን ደንግጣል «አሁን የሆነው ሆኗል ብቻ እነ ዓለሚቱ እነ አባባ ጌቶች መስማት የለባቸውም» አለ ራሱ ለራሉ የበደል ካሳ ገፅ ከመልበሻ ክፍል ወደ መኝታ ክፍል በመግባት ላይ እንዳሉ «ይኽን ነገር ከእኔና አንቺ ሌላ ማንም ሰው በምንም መልኩ ማወቅ የለበትም» ለሚለው የዮሐንስ ማስጠንቀቂያ አሰገደች «አሺ። » «ነገ ተነጎዲያ ጊዜ አለን» «መልካም» አለና ዮሐንስ ዝም አለ የበደል ካሳ ገፅ ፖሪራፉፍ ሟ ይሐኃዕና ዕሩይ ቀኑ ቅዳሜ ነው ዮሐቕስና ተስፋዬ ዓለሚቱ ቤት ምሳ አየተስተናገዱ ናቸው «የተሟላ ግብዣ ለጤናችን። » «አሷም ብትሆን ይፋዊ እውቅና ገና ያልተሰጣት ስለሆነች እንደዚህ ባለ ጠባብ ቤተሰባዊ ፕሮግራም ላይ ልትገኝ አይገባትም የጥቂት ጊዜ ደጅ ጥናት ይቀራታል ይህን ጥንቅሽ የመሰለ ልጅ ባንድ ሰሞን የናይት ክለብ ሆያ ሆዬ የግሏ አንድታደርግ አንፈቅድላትም ማንነቷ ይረጋገጥ «ዓለም የእኔ ባትሆፒ እንዴት በቆጨኝ» አለ ተስፋዬ በፊት ሙሉ ፈገግታ ገበታው ከፍ እንዳለ « ይህ በፆታ ያልተቀናጀ ቡድን በዚህ ምሳ ላይ እንዲገኝ የተደረገበትን ምክያንት እገልጽ ዘንድ ይፈቀድልኝ አለች ዓለሚቱ ለዘብ ባለ አነጋገር የበደል ካሳ ገፅገ ዮሐንስና ተስፋዬ አንደ መገረምም ግራ እንደ መጋባትም ባለ ስሜት ተያዩ ተጠቃቀሱና ፊታቸውን ወዳለሚቱ አዞሩ ሁለቱም ባንድ ድምጽ ባንድ ጊዜ «ተፈቅዶልሻል» አሉ ዮሐንስ ወዲያው ቀጠል አድርጎ «መቸም ያንቺ ነገር» ብሎ የጀመረውን ዓረፍተ ነገር ሳይጨርስ «ወደ ቁምነገሩ እንምጣ» አለች ዓለሚቱ ኮስተር ብላ «የእኔ ወንድም በወግ በማዕረግ ሳትሠረግ ራስህን ከዳርክ ቆየሕ ወላጆቻችን እኔም እንደ እህትነቴ ከአሰገደች ጋር ስላለህ ወይም ወደፊት ስለሚኖርህ ግንኙነት ማወቅ እንፈልጋለን «የእኔና የአለገደች ግንኙነት የእኔና የእሷ ጉዳይ መሰለኝ «ዮሐንስ። አለ ዮሐንስ በግራሞት የበደል ካሳ ገፅ። ዛሬ በወጣትነተ ስሜት ተገፋፍተህ ካልሆነች ሴት ላይ ብትወድቅ ነገ ይጸጽትፃል ያጋጠመህን ችግር ለመፈታት ጊዜ የሚጠይቅ ከሆነ ዋል አደር ብለን እንደገና እንመለስበት የበደል ካሳ ገፅ አይመስልዎትም ጌቶች አሉ በትህትና ወደ ባለቤታቸው አየተመለከቱ «ካልሽስ ዓለሚቱም ብትገባበት ደግ መለለኝ» አሉ ጌቶች የባለቤታቸውን ዐሳብ በመደገፍ «ካለሚቱ ጋር ተነጋግረን ጨርሰናል የቀረን ነገር የለም» በማለት እናትና አባቱ ከአለገደች ጋር የወጠነውን ጋብቻ እንደፈቅዱለት ከአባቱ ጫማ ሳይ ወደቀ እናትህ እንዳለችው ከማትሆን ሴት ዝርያዋ ካልታወቀ ሴት ጋር በጋብቻ ተቆራኝተህ የማታ ማታ ፍዳህን እንዳትቆጥር እንጂ እኛማ ምን ተዳችን እንደፈቃድህ ይሁንልህ አሉትና ዮሐንስ የአባቱን ጫማ ስሞ ከተነሳ በኋላ የእናቱን ጫማ ስሞ ቆመ ፍት አስገደች በጀመረችው ቆጥ አሠርነት ቀጠለች የከበሮ ድምድም የሜዜ እሽክም እሽክም በሌለበት በዚያው ለሞን ባልና ሚስት ሆኑ የሠርጋችን ሥነ ሥርዓት የጋብቻችንን ኛ ዓመት በምናስብበት ዕለት እናከብረዋለን» አለ ዮሐንስ «እንደፈቃድህ ይሁንልህ በሚለው የአባቱ ቃል የተሰማውን እፎይታ እያሰበ እኛ ስፈር አለገደች ተጠለፈች የሚል ወሬ መዛመቱን ለምቻለሁ ሠርግ እጠራለሁ ብሉ የሚጓጓ አይኖርም» አለች አሰገደች እሷም እንዳቅሟ ቆጥ አሠር ገሊ መግባቷን እንዲሸፍንላት የበደል ካሳ ገፅ ችችችጁት ዮሐንስ አላቻ ቢሆንም ጋብቻው የወላጆቹን ካንገት በላይ ይሁንታ በማግኘቱ እፎይ ብሎ ከርሟል ይሁንና ጋብቻውን ከማስፈቀድ ያላነሰ ሌላ የቤት ሥራ ከፊቱ እንደተደቀነ ነው «አሰገደች ከነ አባባ ጋር ተራርቃ የምትቆየው እስከ መቼ ነው። » አለና ተስፋዬ ሳያስበው በውስጡ በተፈጠረ ሽብር ንግግሩን አቆመ የዮሐንስ ያልተጠበቀ ጥያቄ ሦስቱንም አንገት አስደፋ «ተስፋዬ ይኽንን ጥያቄ ያነሳው ስሰአንተ በመቆጨት መሆኑ ግልጽ ነውቡ ወንድሜ ደግሞ በግልጽነት ስለምታምን የበደል ካሳ ገፅ ጥያቄውን በፀጋ አንደምትቀበለው እርግጠኛ ነኝ» አለች ዓለሚቱ እሷም ብትሆን ጋብቻውን ያልተቀበለችው መሆኗን ለማሳየት «ተስፋዬ» እለ ዮሐንስ አእምሮውን በምክንያት ሞረድ ሳል ሳል አድርጎ እንደጨረስ «ተስፋዬ። ሥሉስ የኮዞረላት አስገደች ገና ከጧቱ የባለቤቷን ፍቅር አመኔታና ከበሬታ አትርፋለች ለሁሉም ነገር «እሷ እንዳለች» መባሉን አስገደችን በውጭም በቤትም አዛዥ ናዛዥ እያደረጋት ነው ጋብቻቸው የእሷን ቤተሰቦች ፈቃድ እንጂ የዮሐንስ ዘላጆች ልባዊ ቡራኬ አሰማግኘቱ አሰገደችን እንዳሳሰባት ዮሐንስም ተገንዝቦታል በዐል ቀናት ግቢ ሔዳ እጅ መንሳቷ ሠልካም ጅምር ቢሆንም ፈጥኖ መጎልበት እንዳሰበት ዮሐንስ ያስባል የእሷና የእነሱ ግንኙነት መጠናከር ልጆቹ ከእሱ የበደል ካሳ ገፅ ቤተስብ ጋር ለሚኖራቸው የወደፊት ዘላቂ ግንኙነት ዋስት አንደሚሆን ዮሐንስ ያምናል አንዳንድ ጊዜ ዮሐንስ መሰስ ያደርግና «እንደ አነሱ ካ ወግ አጥባቂ ብዙም መጠበቅ የለበትም» ይሳላል የዮሐንስ ወላጆች ሰምኖ ሳይሆን ተለምኖ መገባ የነበረበት ልጃቸው እነሱ ወፍ ዘራሽ ጎርፍ አመጣሽ ፍና የሚሏትን በማግባቱ መጸጸታቸውን የደበቁበት ጊዜ የለም ዛሬም ወልዳ ከብዳ ባሰሟልነቷ ከእልፍኝ እስክ ጓዳ በዘለቀበት ጊዜ ያንኑ ይላሉ ጋብቻው ገና በሰጋነቱ እንዲቀጭ አመቤት ጽዮን ሞገሳ መጽሐፍ አስገልጠው የአሰገደች ኮከብ ከዮሐንስ ኮከብ ጋር ግጥ አይደሰም መባሉን የሰሙት በመረረ ሐዘን ነበር ሐዘኑን ይበልጥ ያከበደባቸው የጥንቆላውን ውጤት ሰባሰቤታቸውና ለልጆቻቸው ደፍሮ ለመናገር አለመቻላቸው ነበር አቶ ሁንዴ በምድር ላይ የሚጠሉት ነገር ቢኖር ጠንቋይ መሆኑን ባለቤታቸው ያውቃሉ አሰገደች የሁለት ልጆች እናት ከሆነች በኋላም እንኳ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ዮሐንስ። ካልጠፋ ሴት ምናለ የሚበቃትን ያህል ገንዘብና ንብረትም ረጥበህ ይህችን ዘር አጥፊ ወዲያ ብትገሳገል» በማለት ልጃቸውን ያስጨንቁታል ዮሐንስ ግን የእናቱን ምክር የማይቀበልበትን ምክንያት አንገቱን አያቅሰሰለሰ አንደበቱን አእያለሰለሰ ስለሚነግራቸው አይጫኑትትም በአንድ ወቅት በነገሩ ከመበሳጨታቸው የተነሳ እንጦጦ ማርያም ሔደው አልቅሰዋል አልያዘላቸውም እንጂ ጋብቻው እንዲፈርስ የበደል ካሳ ገፅ ተስሰውም ነበር ሌላ ጊዜ ደግሞ ከአብራካቸው የተከፈሉትን ሕፃናት ሲያዩ ረገብ ይላሉ «የሚገርመው ፍየልና ክፉ ሰው ሲረግሙት ይረባል አንደተባለው ነው የሆነላት ይህች መናጢ» አሉ አንድ ቀን አሰገደችና ልጆቿ እጅ ነስተው እንደ ወጡ ይህም ሁሉ ሆኖ አሰገደች ፈተናውን ተቋቁማ ትዳሯን ተጥ አድርጋ ይዛለች ፈራ ተባ ይል የነበረው አንደበቷ ርቱዕ ሆኗል ወዘናዋና ቅርዷም ኑሮዋን መስሎላታል የአሰገደች እንደ እንዝርት መሾር መኳኳልና መሽቀርቀር ደስ ያሰኛቸው አባቷ አቶ ደምሴ « መልካም ሚስት ለባሏ ዘውድ ናት የሚለውን ቅዱስ ተግባር የእኔ ልጅ ፈጽማዋለች» ይላሉ እናቷም ወሮ ዘምዘምም ከጉልት ኑሮ ተገላግለው ኪዎስካቸውን በከፈቱና በዘጉ ቁጥር «ብድርሽን በዘር ማንዘርሽ አግፒው ረዥም ዕድሜ ከሀብትና ከጤና ጋር ይስጥሽ በማለት አሰገደችን ይመርቃሉ ጁ ዮሐንስ ድሮም የሴት ጓደኞችን ይሰስት ነበር አሁን ደግሞ ሚስቱን ከሁሉም በላይ ይሰስታታል ከዚህም የተነሳ አሰገደች ተቀጥራ የሌላ ሰው ታዛዥ መሆኗ ሁልጊዜም ይቀፈዋል «አሰገደች የራሷን ድርጅት አቋቁማ ለመሥራት የዕውቀትም የልምድም ብቃት አካብታለች በዚህ ላይ የእኔ እገዛ ሲታከልበት አሰገደችን ባለድርጅት የማድረገ ፅቅድ ሥሙር የበደል ካሳ ገፅ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ» አለ ዮሐንስ አንድ ቀን አስገደችን ሙሉ በሙሉ የራሱ የማድረግ ስስቱን እያሰበ ዮሐንስ ይኽንን ዐሳብ ለሰአሰገደች ለመሸጥ አልተቸገረም አንድ ግሩም ምሽት ባልና ሚስት አልጋዎቻቸውን አጠጋግተው በድሪያ ቀልድ ላይ አንዳሉ ዮሐንስ አንገቱን ከትራሱ ላይ ቀና አድርጎ «አንድ ነገር አንቺ እስከመቼ ነው የሰው ተቀጣሪ የምትሆፒው።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Commentaires:


memezon

Options de téléchargement | Convertir en PDF | Livre du jour

© dirzon | Conditions d'utilisation | Intimité | Sur | Services | Contact