Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የአዋጁን የተፈጻሚነት ወሰን እና ። የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር ስለ ውዝፍ ደመወዝ ውሣኔ የሕግ ትርጉም ስህተት ስላለበት ስህተቱ ታርሞ ውሣኔውን ውድቅ እንዲያደርግልን የሚሉ ናቸው አቤቱታው በሰበር ችሉት እንዲታይ ታዞ ተጠሪዋ መልስ እንድትሰጥ በታዘዘው መሠረት ሰኔ ቀን ዓም የተፃፈ መልስ አቅርባለች ዋና ዋና ክርክሮቹም መመሪያው በይግባኝ ባይ ላይ ግዴታ የሚጥለው መልቀቂያ የሌለው የጤና ባለመ ይቀጠር ነው። ከድርጅቱ ድርጅታዊ አቋም ወይም የሥራ እንቅስቃሴ ጋር ግንዕነት ያላቸው ምክንያቶች ምን ምን እንደሆኑ በአዋጁ አንቀጽ ሁሐ ተጠቅሰዋል እነሱም በሕጉ እንደተዘረዘረው በሥራ መቆም መቀዝቀዝና ምርታማነትን ለማሣደግ የአሠራር ዘዴዎችን ለመለወጥ ወይም በአዲስ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ሲባል የሠራተኞች ቅነሣ የሚያስከትል ሁኔታ ሲፈጠር ነው ወደ ጉዳዩ ስንመጣ አመልካች ከተጠሪ ጋር የነበራትን የሥራ ውል ማገድ ነፇጵ ወ የመወያያ ነጥቦች ዝርዝሩ ውሱን ነው።
ሠራተኛው በደረሰበት የአካል ጉዳት ምክንያት ስራ ለመስራት አለመቻሉ በሕክምና ተረጋግጦ ውሉ ሲቋረጥ የሚሉት ናቸው የስራ ስንብት ክፍያ መጠን በአንቀጽ ስር የተደነገገ ሲሆን እንደየስራተኛው የስራ ዘመን ርዝማኔ የሚለያይ ሆኖ በአጠቃላይ ግን ከሠራተኛው የአስራ ሁለት ወራት ደሞዝ መብለጥ የለበትም ከዚህ በተጨማሪ ውሉ የተቋረጠው ድርጅቱ በመክሰሩ ወይም በሌላ ምክንያት ለዘለቄታው በመዘጋቱ ከሆነ እና በሠራነኛው ቅነሳ ከሆነ አንቀጽ እንዲሁም በአንቀጽ ስር የተደነገጉትን ጥፋቶች አሰሪው በሠራተኛው ላይ በመፈጸሙ ምክንያት ውሉ የተቋረጠ ከሆነ አንቀጽ ሰራተኛው ሊያገኝ የሚገባው ተጨማሪ ክዋያና ካሳ ስሌት ተደንግጓል ከስራ ስንብት ክፍያ በተጨማሪ ውሉ በህጋዊ መንገድ የተቋረጠ ሰራተኛ ያልተጠቀመበት የአመት ፈቃድ በገንዘብ ተሰልቶ የሚሰጠው ሲሆን አንቀጽ የስራ ዓይነቱን የአገልግሎት ዘመኑን እና ሲከፈለው የነበረውን ደሞዝ የሚያሳይ ምስክር ወረቀት ከአሰሪው የማግኘት መብት አለው አንቀጽ ሰ ሕገወጥ የስራ ውል መቋረጥ የሚያስከትላቸው ውጤቶች የአሰሪና ሠራተኛ ሕግ ዋነኛ ግብ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን የስራ ግንኙነት በሕግ በመቆጣጠር እአና በዚህም ኢንዱስትሪያዊ ሰላምን በመፍጠር ምርታማነትን ማሣደግ አንደሆነ በዚህ ጽሑፍ መግቢያ ላይ ተመልክቷል የአዋጁ መግቢም አሠሪና ሠራተኛ የሥራ ግንኙነታቸውን መሠረታዊ በሆነ መብቶችና ግዴታዎች ላይ መስርተው የኢንዱስትሪ ሰላምን በመፍጠር ለአገራችን ሁለንተናዊ እድገትና ልማት በመተባበር በጋራ እንዲሰሩ ማድረግ ሕጉ ያስፈለገበት ምክንያት መሆኑን በመግለጽ ይጀምራል በመሆኑም ሕጉ በቅድሚያ የአሠሪና ሠራተኛው የስራ ግንኙነት መሠረታዊ በሆኑ መብቶችና ግዴታዎች ላይ እንዲመሠረት የሚፈልግ ሲሆን ይህ መብቶችንና ግዴታዎችን በማክበር የሚደረግ ግንኙነት ኢንዱስትሪያዊ ሠላም የሚያመጣ እንዲሆን የታሰበበት ነው በተጨማሪም የስራ ግንኙነቱ በቀጠለበት ወቅት የአንዱ መብት በሌላኛው ወገን መጣስ እንደሌለበት እና ግዴታዎቻቸውንም በአግባቡ መወጣታቸውን እንደሚቆጣጠረው ሁሉ ውሉ ሲቋረጥም በሕገወጥ መንገድ አንዳይሆን አስፈላጊውን ቁጥጥር ሕጉ ያካሔዳል አሠሪውም ሆነ ሠራተኛው ውሉን ሲያቋርጡ ህጋዊውን መንገድ መከተል የሚኖርባቸው ሲሆን በዚህ አዋጅ ወይም አግባብ ባለው ሌላ ሕግ የተወሰኑትን አስፈላጊ ሁፄታዎች ያላሟሉ እንደሆነ የስራ ውሉ መቋረጥ በሕገ ወጥነት ይፈረጃል አንቀጽ ይሁንና ሕጋዊ የሆኑ ሁኔታዎችን መዘርዘርና ከዝርዝሩ ውጭ ያሉትን ሁኔታዎች ሕገወጥ ነው ብሎ መፈረጁ ብቸውን የነገሩን ህጋዊነት ለመቆጣጠር በቂ አይሆንም ሕገወጥ ድርጊት የፈጸመው አካል የሚቀጣበት ድርጊቱ የተፈጸመበት ወገን ደግሞ የሚካስበት ስርዓት አብሮ የመዘርጋቱ አስፈላጊነት ግልጽ ነው በሠራተኛው አነሳሽነት የሚፈጸም የስራ ውል መቋረጥ ሕገወጥ ሊሆን የሚችለው ሠራተኛው ያለማስተንቀቂያ ማቋረጥ ከሚችልባቸው በአንቀጽ ስር ከተደነገጉት ውጪ ባሉ ሌሎች ምክንያቶች ሆኖ ነገር ግን ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ማስተንቀቂያ ለአሰሪው ሳይሰጥ ውሉን ያቋረጠ ከሆነ ነው በዚህ መልኩ የስራ ውሉን ያቋረጠ ሠራተኛ ለአሠሪው አሰሪው ለሱ ከሚከፍለው ቀሪ ክፍያ ውስጥ ከሠላሳ ቀናት ያልበለጠ ክፍያን በካሳ መልክ መክፈል ይኖርበታል አንቀጽ ይህ ሠራተኛው ውሉን በሕገወጥ መንገድ ሲያቋርጥ የሚያስከትልበት ውጤት እምብዛም ጠንካራ እነዳልሆነ አንረዳለን ውሉ በአሰሪው አነሳሽነት በሕገወጥ መንገድ ሲቋረጥ የሚኖረው ውጤት ግን በተለየ መልኩ ጠንከር ይላል የስራ ግንኙነት በዘፈቀደ እንዳይቋረጥ የሚደረግበት አንዱና ዋነኛ ምክንያት የሠራተኛውን የስራ ዋስትና ለማስከበር በማሰብ ነው በመሆኑም ይህን የስራ ዋስትና ለማረጋገጥ ይረዳል ከሚል አሳቤ በመነጨ አሰሪው በሕገወጥነት ውሉን ሲቋርጥ ። ሦርም ቃሉ በአሠሪና ሠራተኛ መካከል ያለ አለመግባባትን ይጠቁማል በአሠሪና ሠራተኛ ህጉ አዋጅ ቁጥር ላይ በተሰጠው ትርጉም የሥራ ክርክር ማለት ሕግን የኀብረት ሥምምነትን የሥራ ደንብን የሥራ ውልን ወይም ሲሠራበት የቆየ ልምድን መሠረት በማድረግ እንዲሁም በኀብረት ስምምነት ወቅት ወይም ከኀብረት ስምምነት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚመለከት በአሠሪና ሠራተኛ ወይም በሠራተኞች ማኅበር እና በአሠሪዎች መካከል የሚነሳ ክርክር ነው በዚህ ትርጉም ውስጥ ያለመግባባት ምከንያት የሚሆኑት ሕግ ሁ የኀብረት ስምምነት ሁ የሥራ ውል ወይም ሲሠራበት የቆየ ልምድ ሁ የሥራ ደንብ ወይም በኀብረት ድርድር ወቅት ወይም ከኀብረት ስምምነት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችንም የሚመለከት ሊሆኑ ይችላሉ ዝርዝሮቹን በውል ስናጤናቸው አንዱ ባንዱ ሊካተት የሚችል ነው ለምሳሌ የኀብረት ስምምነት የሚለው በሥራ ሁኔታዎች ላይ የሚደረግ በጽሁፍ የሰፈረ ስምምነት ነው የሥራ ሁኔታ ማለት ደግሞ ሰፊ አና ሁሉንም በሥራ ምክንያት የሚፈጠረውን ግንኙነት የሚመለከት ነው አንቀጽ በሌላ በኩል የሥራ ደንብ የሚለውም የሥራ ሁኔታን ይመለከታል ስለሆነም በጥቅሉ የሥራ ሁኔታዎችን በተመለከተ የሚፈጠር አለመግባባት ነው ቢባል ብዙውን ነገር የሚያካትት ይሆናል የሆነ ሆኖ ግልጽ ከመሆንበትርጉም ምክንያት ሊነሣ የሚችለውን ያልተፈለገ ውጤትንም ከማስቀረት አንፃር ሲታይ በዝርዝር መቀመጡ መልካም እንደሆነ ማሰብ ይቻላል ሮያሥራ ርረቻርዖሟታፖየገፖው መፇረደቻ የሥራ ክርክር ወይም አለመግባባት በሚከተሉት ሁኔታዎች ይገለጣል በራስ ኃይልርምጃ ፍላጐትን ለማስፈፀም በመሞከር ከርርሀዐከ ሀልዐ ዘከሯ ዘበበ አለመግባባትን ሊፈቱ ወደሚችሉ አካላት ጉዳዩን በመውሰድ ሲገለጥ ይችላል በራስ ኃይል አለመግባባትን ለመፍታት የሚሞከረው ደሥራ ማም ወይም ያሥራ መሯጋታፖ ርምጃ በመውሰድ ነው እነሂህን ቀደም ሲል በነበረው ክፍል ያየናቸው በመሆኑ በድጋሚ ማንሳቱ አስፈላጊ አይሆንም በሁለተኛው መንገድ አለመግባባትን ወደ ሦስተኛ አካል በመውሰድ ችግርን በመውሰድ ለመፍታት የሚሞከርበትን ሁኔታ ግን በመጠኑ ማንሳት ይገባል እንደሚታወቀው ማንኛውም ሰው ከሌላው ጋር ያለውን አለመግባባት በራሱ መፍታት ያልቻለ እንደሁ የመጀመሪያው ጥሩ አማራጭ ከተከራካሪው ጋር በመረጠው ሦስተኛ ወገን ገላጋይ ወይም አስታራቂ ዳኛ አማካኝነት ልዩነቱን መፍታት ነው በዚህ ዓይነት መንገድ በህግ ወይም በስምምነት ክልከላ ከሌለበት በቀር ማናቸውንም ጉዳይ የዕርቅ ወይም የድርድር መሰረት ሊያደርጉት ይችላሉ ይህ ማለት ነገሩ የወል ወይም የግል የሥራ ክርክር ቢሆንም ባይሆንም የማየት ስልጣን ይኖራቸዋል ማለት ነው ራሳቸው የመረጡት የግልግል ዳኛ ወይ አስታራቂ የሌለ እንደሁ ግን አንዱ ወገን ለሠራተኛ እና ማኀበራዊ ጉዳይ ሜኒስቴር አቤቱታ ሲያቀርብ ሚኒስቴሩ የተፈጠረውን አለመግባባት ሊፈታ የሚችል አስማሚ በብሔራዊ ደረጃ በክልል ወይም በወረዳ ደረጃ ጉዳዩን የሚያይ ሰው ይመድባል አንቀጽ ሀ አስማሚው የሚያያቸው ጉዳዮች ውሱን ናቸው በአንቀጽ ላይ የተገለፁት የወል የሥራ ክርክሮችን ብቻ የሚመለከት ነው አማራጭ የክርክር መፍቻ መድረኮች ከፍ ሲል እንደተገለፀው አማራጭ የክርክር መፍቻ መድረኮች የሥራ ክርክር ሲከሰት አለመግባባቱ በሦስተኛ ወገን የሚፈታው አንድም ራሳቸው በመረጡት ገላጋይ አሊያም ሚኒስቴሩ በሚመድበው አስማሚ አማካኝነት ነው እነፒህ አካላት የተቻላቸውን አድርገው ግራ ቀኙን የሚያስማማ ውሳኔ መስጠት ያልቻሉ እንደሁ ገላጋዩ ወይም አስታራቂ ዳኛው በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘው ወገን እንደ አግባቡ ነገሩን ለቦርድ ወይ ለፍርድ ቤት ያቀርበዋል ሁ አስማሚው በበኩሉ ሁለቱንም ወገኖች ጉዳዩ ከቀረበለት ጊዜ ጀምሮ ባሉት ቀናት ውስጥ ማስማማት ካልቻለ ይህንኑ በመግለጽ ሪፖርቱን ለሚኒስቴሩ ያቀርባል በዚህ ጊዜ ከተከራካሪ ወገኖች አንዱ ነገሩ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ እንዲታይለት ሊወስደው ይችላል ስለሆነም አማራጭ የሥራ ክርክር መፍቻ መድረኮች በዕርቅ በግልግል እና ሚኒስቴሩ በሚመድበው አስማሚ አማካኝነት የሚፈፀሙ ናቸው ማለት ነው መደበኛ የሆኑ የክርክር መፍቻ መድረኮች መደበኛ የሆኑት የክርክር መፍቻ መድረኮች ው ጊዜያዊ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ው ቋሚ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ እና ው ፍርድ ቤቶች ናቸው የጊዜያዊ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ሥልጣን በጊዜያዊ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ሥልጣን ሥር የሚወድቁት ጉዳዮች በአንቀጽ ሀ ላይ ስለደመወዝና ሌሎች ጥቅሞች አወሳሰን የተገለፁት ስለመሆናቸው ከአንቀጽ እና አንቀጽ መረዳት ይቻላል በአንቀጽ ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ ስናየው ጊዜያዊ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርዱ የሚያየው በአንቀጽ ላይ የተመለከቱትን የአየር መንገድየመብራት ኃይል እና አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን የውሃ አገልግሎት የሚሰጡ እና የከተማ ጽዳት የሚጠብቁ ድርጅቶችን የከተማ አገልግሎት ሆስፒታሎች ክሊኒኮች የመድኃኒት ማከፋፈያ ድርጅቶች እና የመድኃኒት መሸጫ ቤቶች የአሳት አደጋ አገልግሎቶች እአና የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሠራተኞች የሚነሳውን የደመወዝና የሌሎች ጥቅሞች አወሳሰን ብቻ እንጂ ከዚህ ውጪ ያሉትን ክፍሎች ጉዳይ የማየት ሥልጣን የሌለው ያስመስለዋል ወደ አንቀጽ ስንመለስ ግን የደመወዝና የሌሎች ጥቅሞች አወሳሰን በጥቅሉ የዚሁ ጊዜያዊ ቦርድ ሥልጣን እንደሆነ መገንዘብ ስለሚቻል በዚህ ረገድ የሚፈጠረውን ብዥታ ያጠፋል የቋሚ አሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ሥልጣን ቋሚ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የሚኖረው ሥልጣን በአንቀጽ ለ ሐ ላይ የተመለከቱት ናቸው ይህ ማለትም በአንቀጽ ለ ላይ እንደተገለፀው በአንቀጽ ሀ ላይ ከተገለፀው በቀር ሌሎቹን የወል የሥራ ክርክሮችን ሁሉ የማየት ሥልጣን አለው ከአንቀጽ ላይ መገንዘብ አንደሚቻለው በስሩ የተቀመጡት ዝርዝሮች በመንደርደሪያው ላይ ከተገለፀው አንፃር ሲታዩ የወል የሥራ ክርክሮች ናቸው ዝርዝሮቹ የተገለፁት ብቻም ሳይሆኑ ያልተገለፁ ነገር ግን የሁሉንም ሠራተኛ መብት ሊነኩ የሚችሉ መብቶችንም ሊያካትት የሚችል ነው ከዚህ በተረፈም ሜኒስቴሩ የመደበው አስማሚ ማስማማት ያለመቻሉን ሲገልፅና አንዱ ወገንም ይህንኑ ወደ ቦርዱ ሲወስደው ቋሚው ቦርድ ነገሩን ያየዋል በአንቀጽ ላይ የተገለፁትን የሥራ ማቆምን ወይም የሥራ መዝጋትን በተመለከተ የተከለከሉትን ድርጊቶችን በተመለከተም ጉዳዩ ሲቀርብለት የማየት ሥልጣን ይኖረዋል ያም ሆነ ይህ የሥልጣኑ መሠረታዊ ቁም ነገር ያለው የሚታየው ጉዳይ የወል ይዘት አለው የለውም የሚለው ላይ ነው በአንዳንድ አገሮች አንድ ጉዳይ የወል የሚሆነው በጉዳዩ ውስጥ መብታቸው የተነካው ሰዎች ቁጥር በርካታ ሲሆን ነው በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ አሠሪና ሠራተኛ ህግ አንቀጽ ሲታይ ጉዳዩ የወል የሚሆነው በነገሩ ውስጥ የገቡትን ሰዎች ቁጥር ከግምት ውስጥ የሚያስገባ አይመስልም አንቀጹ ገለዛውን የሚጀምረው ፈሀሠ ታቻ ዖፖሥመያሰያራሪፖና ፅታቻ ያወሳ ያሥራ ረረ ሦዳሎቻ በማለት ነው ዳና ታቻ ያወ ያሥራ ረቋሮቻ የሚለው በአንቀጹ ሥር ያሉት ሁሉ የወል የሥራ ክርክሮች መሆናቸውን የሚያሳይ ነው የተዘረዘሩትን ንዑስ አንቀጾች ስናያቸው ደግሞ በባህሪያቸው ጉዳዮቹ የብዙሃኑን ሠራተኛ መብት የግድ በርበሄ የሚነኩ ናቸው በዚህ የተነሳም ብዙሃኑ የሚካተተው ከጉዳዩ ባህሪ የተነሳ እንጂ ለችግሩ ምክንያት የሆነው አጋጣሚ በርከት ያሉ ሰዎችን ማሰባሰብ መቻሉ አይደለም ለምሳሌ የደመወዝና የሌሎች ጥቅሞችን አወሳሰን በተመለከተ ጠቅላላ ይዘቱ ምን መምሰል አለበት እንዴት ሊሠራ ይገባል የሚለው በተናጥል አንድን ሠራተኛ ብቻ የሚመለከት ሳይሆን ውጤቱ ብዙዛኑን የሚጠቅም ወይም የሚጐዳ ይሆናል ስለሆነም የጋራየወል ጉዳይ ይሆናል ሥርዓቱ ከተዘረጋ በኃላ ግን በተዘረጋው ሥርዓት መሠረት ላገኝ የሚገባኝ ፅድገት ቀርቶብኛል የሚል ቢኖር ችግሩ የዚሁ ሠራተኛ የግል ጉዳይ ብቻ አንጂ ሌሎችን በጋራ የሚመለከት አይሆንም ቁጥራቸው ምንም ያህል የበዛ ቢሆን ነገሩ የያንዳንዳቸው የየግል ጉዳይ እንጂ የወል አይሆንም ስለሆነም በኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ የወል የሥራ ክርክር ማለት የጉዳዩ ፍሬ ነገር የብዙፃኑን ሠራተኛ መብት የሚነካ ነው ወይስ አይደለም በሚለው ላይ የተመሠረተ ነው ለቅሬታው ምክንያት በሆነው አጋጣሚ ብዙዎች ቅር መሰኘታቸውና አቤት ማለታቸው የጉዳዩን ፍሬ ነገር ይዘት አይቀይረውም ስለሆነም በዚህ መንገድ የወል ሊባሉ የሚችሉ ጉዳዮች ሁሉ የቋሚ ቦርዱ ሥልጣን ይሆናሉ ማለት ነው አጠቃላይ በሆነ መንገድ የቦርዱ ሥልጣን የጋራ የሆኑ የሠራተኞቹን ጥቅም የሚመለከት ነው ስንል ይህን አቋም የሚፈትን ችግር የለም ማለት አይቻልም ለምሳሌ በአንቀጽ ሰ ላይ ያለውን ድንጋጌ ብንመለከት አሠሪው በሚወስዳቸው አርምጃዎች ምክንያት የሚቀርቡ ክሶች ከባህሪያቸው ስንነሳ የጋራ የሆነ የሠራተኞችን ጥቅም ይመለከታል ወይስ የግል ይሆናል። ፆዲሀፀ ያማሟመፅፉ ቦማዕ ቦጎሪ ረረ ማየኦ ቦፅፅሪሃ ፅሪሃሃኛ ዕዎድ ፍሪ ፅንፇድ ሃፖ አመልካች በሰራተኛ ማህበራችን አማካኝነት የተወሰደብን የቅነሳ እርምጃ ህገ ወጥ በመሆኑ የተቋረጠብን ክፍያ ተሰጥቶን ወደ ስራችን እንመለስ በማለት በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ያቀረቡትን ጥያቄ ቦርዱ በመቀበል የተደረገው ቅነሳ በአዋጅ ቁ አንቀጽ እና ድንጋጌዎችን የሚጥስ በመሆኑ አመልካቾች ወደ ስራ ሊመለሱ ይገባል በማለት የሰጠውን ውሳኔ ከስልጣኑ ውጭ የሰጠው ነው በሚል የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ስለሻረው የቀረበ አቤቱታ ው ሣ ኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የወል የስራ ክርክር ጉዳዮችን የሚመለከቱ ክርክሮችን እንዲዳኙ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል ህጉ የስራ ክርክር ጉዳዮችን የወል ወይም የግል ብሉ ለመለየት የተከራካሪ ሰራተኞችን ቁጥር እንደ መስፈርት መውሰድ እንዳለበት አያመላክትም ከአጠቃላይ የህጉ መንፈስ እና ድንጋጌዎች በመነሳት አንድ የስራ ክርክር ጉዳይ የወል ነው የሚባለው ጉዳዩ በጋራ የሆነ የሠራተኞች መብትና ጥቅም ላይ አሉታዊ ሆነ አዎንታዊ ውጤት የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ ብቻ ሲሆን አንድን የስራ ክርክር ጉዳይ የግል የሥራ ክርክር ጉዳይ የሚያደርገው ደግሞ ጉዳዩ ከግል አልፎ በጋራ መብት ላይ የሚያመጣው ለውጥ የሌለ እንደሆነ ነው የስራተኛ ቅነሳ ጉዳይ የጋራ በሆነ የሰራተኞች መብትና ጥቅም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያለው በመሆኑ የወል የስራ ክርክር ጉዳይ ነው ጉዳዩን የማየት ስልጣንም የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ነው የአሰሪና ሰራተኛ ፍቤት ቦርዱ የህግ ስህተት ፈጽሟል ብሎ ሲያምን ጉዳዩን ከመመሪያ ጋር ወደ ቦርዱ ከመመለስ አልፎ የቦርዱ ውሳኔ መሻር አይችልም የመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍሥሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አመልካችፁ የኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ መሰማ ሰዎች ወኪል ሰይድ ሀሚድ ቀረበ ተጠሪ የኬዜ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ የቀረበ የለም መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ በዚህ መዝገቡ የተያዘው ክርክር ከአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ የተጀመረ ነው ጉዳዩ አሠሪ የሆነው የአሁን ተጠሪ ሠራተኛ በሆኑት በአሁን አመልካቾች ላይ የወሰደውን የቅነሣ አርምጃ የሚመለከት ነው አመልካቾች በሠራተኛ ማኀበራቸው አማካኝነት የተወሰደብን የቅነሣ አርምጃ ሕገ ወጥ በመሆኑ የተቋረጠብን ክፍያ ተሰጥቶን ወደ ሥራችን እንመለስ ሲሉ በተጠሪው ላይ ክስ መስርተዋል ተጠሪም የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና የቅነሣውን ተገቢነት ይገልጻል የሚለውን መልስ አቅርቦ ተከራክሯል ክሱ የቀረበለት ቦርድ ደግሞ የተደረገው ቅነሣ አዋጅ ቁ አንቀጽ እና ን የሚጥስ በመሆኑ አመልካቾቹ በአንቀጽ መሠረት ወደ ሥራቸው ሊመለሱ ይገባል በማለት ወስኗል ከዚህ ውሣኔ ላይ በተጠሪ አማካኝነት በመቁ ይግባኝ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በበኩሉ ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ ቦርዱ ይህን የማየት ሥልጣን የለውም በማለት ከፍ ሲል የተጠቀሰውን የቦርዱን ውሣኔ ጥቅምት ዓም ሽሮታል በመቀጠል አመልካቾች ይኸ የፍቤቱ ውሣኔ የአዋጅ ቁ አንቀጽ ን እና ን የሚጥስ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ነውና ይሻርልን በማለት አቤቱታቸውን ለዚህ ችሎት አቅርበዋል ተጠሪም የቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት ሊያገኝ አይገባም የሚልበትን ምክንያት የሚዘረዝር መልስ አቅርቦ ተከራክራል ይህም ችሎት ክርክሩን ሊያስነሣ በቻለው አወዛጋቢ የህግ ነጥብ ላይ ብቻ በማተኮር መዝገቡን መርምራል በዋነኛነት ሊፈቱ የሚገባቸው የነገሩ ጭብጦችም ኛ የሠራተኛ ቅነሣን አስመልከቶ የቀረበውን የህን ክርክር የመዳኘት ሥል የማነው። የሚሉና ሌሎቹንም መሰል ጥያቄዎችን እንድናነሣ የሚያደርገን ነው ለእነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠታችን ደግሞ የሚቀርቡ የሥራ ክርክሮችን ከየትኛው እንደምንፈርጃቸው የሚያመለክተንና በዚህ ተጨባጭ ጉዳይ ለተያዘውም የመጀመሪያ ጭብጥ መፍቻ እንድናገኝለት የሚረዳን ነው ስለ የወል እና የግል የሥራ ክርክር አይነቶች የአዋጅ ቁ ለወልም ሆነ የግል የሥራ ክርክር የሰጠው ትርጓሜ የለም የሥራ ክርክር በዚህ አዋጅ የተተረጎመ ቢሆንም ትርጓሜው የወልና የግል የሥራ ክርክርን እንድንለይ የሚያስችለን አይደለም ስለሆነም በሁለቱ መካከል ያለውን ልዩነት በግርድፉ ለማስቀመጥ ሌላ መለኪያ አንድናበጅ የሚጠይቀን ነው እንደሚታወቀው ከአሠሪ ጋር የሚደረግ የሥራ ክርክር በሠራተኞች ማ ይም ቁጥራቸው ከአንድ በላይ በሆነ ሠራተኞች ወይም በአንድ ሠራተኛ ብቻ የሚካሄድ ነው የወል የ ል አገላለጽ የጋራ የሆነ ጉዳይ መኖሩን ለማመልከት ያህል የሚበቃ መሆኑም እርግጥ ነው ይሁን እንጂ የወሉን ከግል ለመለየት የተከራካሪዎቹን ሠራተኞች ቁጥር እንደመለያ መስፈርት መውሰድ እንደምንችል የሚጠቁመን የሕግ ድንጋጌ የለም ይህ ደግሞ ሕጉ ሁለቱን ክርክሮች ለመለየት የፈለገበትን ሌላ መንገድ እንድንፈትሽ ያደርገናል ለዚህም ሁለቱ የክርክር አይነቶች በምሣሌነት በተናጥል የተዘረዘሩበትን የአዋጅ ቁ አንቀጽ ን እና ን መሠረት ማድረጉ አሣማኝነት ያለው መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ ይጠቅመናል አዋጅ ቁ አንቀጽ ሀ ስለደመወዝና ሌሎች ጥቅምን አወሳሰን ለ አዲስ የሥራ ሁኔታዎችን ስለመመስረት ሐ የሕብረት ስምምነት ስለመዋዋል ስለማሻሻል ፀንቶ ስለሚቆይበት ጊዜና ስለሚፈርስበት መ አዋጁን የሕብረት ስምምነት ወይም የሥራ ደንብ ድንጋጌዎችን በሚመለከት የሚነሣ የትርጉም ክርክር ሠ ስለሠራተኛ አቀጣጠርና እድገት አሰጣጥ ሥርዓት ረ አጠቃላይ ሠራተኞችንና የድርጅቱን ሕልውና የሚነኩ ጉዳዮች ሰ ዕድገት ዝውውር እና ሥልጠናን በሚመለከት አሠሪው በሚወስዳቸው አርምጃዎች ምክንያት የሚቀርቡ ክሶች ሸሽ የሠራተኞች ቅነሣ እና የመሳሰሉት የሥራ ክርክሮች የወል የሥራ ክርክሮች መሆናቸውን ደንግጓል እንደዚሁም አብዛኛዎቹ የድንጋጌው ከፍሎች በውጤታቸው የሁሉንም ሠራተኞች መብትና ጥቅም የሚመለከቱ ጉዳዮችን ያቀፉ መሆናቸውን በግልጽ አመላክተውናል ለምሣሌነት በንዑስ አንቀጽ ሀ ለ ሐ ሠ ረ እና ሸ የተጠቀሱትን የሥራ ክርክር አይነቶች መመልከት ይቻላል እነዚህ የድንጋጌው አብዛኛው ንዑስ አንቀጾች ክርክሩ የወል ለመባል የጋራ የሆነን የሠራተኞቹን መብትና ጥቅም የሚመለከት ሊሆን እንደሚገባ በግልጽ ካሣዩን ደግሞ በቀሪዎቹ ንዑስ አንቀጾች ላይ የተጠቀሱትንና ሌሎችንም በድንጋጌው ያልተካተቱትን ተመሳሳይ የሥራ ክርክሮችን የወልነት ፀባይ ከሠራተኞቹ የጋራ መብትና ጥቅም ጋር ካለው ግንኙነት አኳያ ልንመዝነው የሚገባን ይሆናል ስለሆነም ጥያቄው የደመወዝም ሆነ የሥልጠና ርጉም ነክም ሆነ ወይም ሌላ የወል የሚሰኘው ጉዳዩ በጋራ በሆነ የሠራተኞች መብትና ጥቅም ላይ አ ሆነ አወንታዊ ውጤት የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ ብቻ ሊሆን ይገባዋል በሌላ በኩል ደግሞ የአዋጅ ቁ አንቀጽ ሀ ከሥራ ማስወጣትን ጨምሮ ሌሎች የዲሲፕሊን እርምጃዎችን የሚመለከቱ ክሶች ለ የሥራ ውል መቋረጥ ወይም መሰረዝን የሚመለከቱ ክሶች ሐ የሥራ ሰዓትን የተከፋይ ሂሳብን ፈቃድንና እረፍትን የሚመለከቱ ክሶች መ የቅጥር ማስረጃ ሠርተፊኬት መስጠትን የሚመለከቱ ክሶች ሠ የጉዳት ካሣን የሚመለከቱ ክሶች እና ረ በአዋጁ መሠረት የሚቀርብ ማንኛውም የወንጀልና ደንብ መተላፍ አንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች የግል የሥራ ክርክሮች መሆናቸው ተደንግጓል የዚህ ድንጋጌ ይዘት ከፍ ሲል እንደተጠቀሰው ድንጋጌ የጋራ የሆነን የሠራተኞች ጉዳይ እንደሚያጠቃልል የሚገልጽ አይደለም ስለሆነም ሥራ ክርክሩ በእነዚህ በተዘረዘሩትም ሆነ በተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ ተመስርቶ ሲቀርብ ከግል አልፎ በጋራ መብት ላይ የሚያመጣው ለውጥ ያለመኖሩ ጉዳይ ክርክሩን የወል ሳይሆን የግል የሥራ ክርክር እንዲሆን ያደርገዋል አንግዲህ አንድ የሥራ ክርክር በአንድ ወይም በብዙ ሠራተኞች መቅረቡ ጉዳዩ የወል ወይም የግል የሥራ ክርክር መሆኑን የሚያረጋግጥልን አይደለም ይልቁንም ክርክሩ የወል መሆኑን የሚያሳየን ውጤቱ በግል አልፎ የሠራተኞቹን የጋራ መብትና ጥቅም የሚነካ የመሆኑ ጉዳይ ሲሆን ክርክሩ የግል ነው የምንለው ደግሞ ውጤቱ በተከራካሪው ሠራተኛ ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሆኖ ስናገኘው ነው ወደ ጭብጣችን ስንመለስ አመልካቾች ተጠሪው የቅነሣ እርምጃ ለመወሰድ የሚያስችል ምክንያት የለውም ቅነሣውም በአዋጅ ቁ አንቀጽ የተመለከተውን ቅደም ተከተል ያከበረ አይደለም በሚል አይነት መሟገታቸውን ያሳየናል እንደሚታወቀው የሠራተኞች ቅነሣ መላውን የድርጅቱን ሠራተኞች ከግምት በማስገባት በሕግ አግባብ ሊከናወን የሚገባ ተግባር ነው ቅነሣው ህግን ተመስርቶ አለመደረጉን አሳያለሁ በሚል ሁኔታ የሚቀርብ አቤቱታም በውጤቱ ሁሉንም ሠራተኞች የሚመለከት መሆኑ የሚታመን ነው የአመልካቾች ክርክር ደግሞ በዚህ መልኩ የቀረበ መሆኑ ከፍ ሲል ተመልክቷል ስለሆነም ጉዳይ የወል እንጂ የግል የሥራ ክርክር የሚሰኝበት ምክንያት አይኖርም ክርክሩ የመዳኘቱ ሥልጣንም በአዋጅ ቁ አንቀጽ ሸ መሠረት የቦርድ እንጂ የፍቤት አይሆንም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በሰጠው ውሣኔ በግራ ቀኙ መካከል የነበረው የሥራ ውል የተቋረጠ መሆኑን ምክንያት በማድረግ የቅነሣውን ህጋዊነት የመመርመር ሥልጣን የፍቤት ነው ኗል ይሁን እንጂ ከፍ ሲል እንደተገለፀው አንድ የሥራ ክርክር በቦርድ ወይም የግል የሥራ ክርነ ኩኑ እንጂ የሥራ ውሉ የመቋረጥ ወይም ያለመቋረጡ ጉዳይ አይደለም ስለሆነም ፍቤቱ ለውሣኔው መሠረት ያደረገው ምክንያትም ከሕጉ ጋር የሚጣጣም አልሆነም በሁለተኛው ደረጃ የተያዘው ጭብጥም አግባብነት ከአለው የአዋጅ ቁ አንቀጽ ጋር ተገናዝቦ ተመርምራል በዚህ ድንጋጌ የቦርድ ውሣኔ የሕግ ስህተት ያለበትና የሕግ ስህተቱም የውሣኔውን ውጤት አዛብቶት የተገኘ እንደሆነ ይግባኝ የቀረበለት ፍቤት ጉዳዩን ከዝርዝርና ከአጠቃላይ መመሪያ ጋር ለመጨረሻ ውሣኔ ወደ ቦርድ እንደሚመልሰው ነገር ግን የቦርዱን ውሣኔ ለመሻርም ሆነ ለማሻሻል አንደማይችል ተደንግጓል በአርግጥ በዚህ ጉዳይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የቦርዱን ውሣኔ አራሱ መሻሩ የውሣኔ አሰጣጡ ከተጠቀሰው ሕግ ጋር አለመጣጣሙን ያሳያል ይሁን እንጂ ፍቤቱ የቦርዱን ውሣኔ የሕግ ስህተት ለማረም እንዲችል በዚሁ ሕግ ሰፊ ሥልጣን ተሰጥቶታል ውሣኔውን በይግባኝ ሊሽረውም ሆነ ሊያሻሽለው ባይችልም የሕግ ስህተቱ ታርሞ በጉዳዩ እንደገና ውሣኔ ይስጥበት ዘንድ ክርክሩን ወደ ቦርድ እንዲመልሰው ሕጉ በግልጽ ፈቅዶለታል ስለሆነም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የቦርዱን ውሣኔ እራሱ ለመሻር ሥልጣን የሌለው በመሆኑ የፍርድ አሰጣጡ ከተጠቀሰው ህግ አግባብ ሊቃና የሚገባው ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ ኛ ለዚህ ክርክር መነሻ የሆነው የሠራተኛ ቅነሣ የወል የሥራ ክርክር በመሆኑ ጉዳዩን የመዳኘት ሥልጣን የቦርድ እንጂ የፍርድ ቤት ሊሆን አይገባም በማለት ተወስኗል ኛ ይግባኙ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤትም ይህንኑ ተገንዝቦ ወደ ክርክሩ በመግባትና በቦርዱ የተሰጠው ፍርድ ከሕግ አኳያ ስህተት ያለበት መሆን አለመሆኑን በመመርመር ጉዳዩ ከመመሪያ ጋር ወደ ቦርድ ሊመለስ የሚገባው መሆን አለመሆኑ ረገድ ውሣኔ ሊሰጥበት ይገባል በማለትም ተወስኗል ኛ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ክርክሩን ማየት እንዲቀጥል ያስችለው ዘንድም ጉዳዩ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተመልሶለታል ሰበር መቁ ዝ። በሌላም በኩል የመንግሥት አስተዳደር ዩ በልዩ ሕግ ከሚተዳደሩ ሌሎች ሠራተኞች ውስጥ የተመደቡ መሆናቸው እና ከአሰሪያቸው ጋር ላላቸው ግንኙነት የአዋጅ ቁ ተፈፃሚ እንደማይሆን በአንቀጽ ሠ ላይ ተጠቅሷል አመልካች የሕዝብ አገልግሎት ሥራ የሚያካሂድ የመንግሥት ተቋም መሆኑን ከስያሜው እንኳ መገንዘብ ይቻላል በተጠሪ የቀረበውም ክርክር አመልካች ድርጅት ነው በሚል እና ይህንንም በማስረዳት ላይ የተመሠረተ አይደለም ክርክሩ ተጠሪ በመንግሥት ሠራተኝነት የታቀፈች አይደለችም እስከ ዓም ድረስም ሠራተኞቹ በመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር አዋጅ የታቀፉ አልነበሩም ተጠሪ ክስ ከመሠረተች በጊላ የወጣው የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር አዋጅ ቁ ም ወደ ኋላ ፄዶ ስለማይሰራ ግንኙነታችን በአዋጅ ቁ የሚሸፈን ነው የሚል ነው በዚህ ችሎት እምነት የአንድ ሙግት ይዘት ከአዋጅ ቁ አግባብ የሚዳኝ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ ለመድረስ በአዋጁ አንደተሰጠው ትርጓሜ አንድ ወገን ተከራካሪ አሰሪ ሌላው ወገን ተከራካሪ ደግሞ ሰራተኛ ሊሰኙ ይገባል ከአዋጁ አግባብ ቀጣሪው አሰሪ ተቀጣሪው ደግሞ ሠራተኛ ሊባሉና ሁለቱም በድንጋጌው የተቀመጠውን የትርጓሜ መስፈርት እንዲያሟሉ ያስፈልጋል ከፍ ሲል እንደተመለከተው አሰሪው አመልካች የሕዝብ አስተዳደር ሥራ የሚያካሂድ የመንግሥት መቤት በመሆኑ ድርጅት ሊባል የሚችል አይደለም አመልካቹ አሰሪ ድርጅት ባለመሆኑም ተጠሪዋ በአዋጁ አሰሪ ከተባለ አካል ጋር የሥራ ውል ግንኙነት ያላት ሠራተኛ ናት ልትባል የምትችል አይደለችም ይህ ደግሞ ሁለቱም በአዋጁ የተቀመጠውን ትርጓሜ አለማሟላታቸውን የሚያመላክት ነው በአርግጥ ተጠሪ በመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር አዋጅ ያልታቀፈች ሠራተኛ መሆንዋን በመግለጽ መከራከርዋን ተገንዝበናል ይህም አዋጁ ተፈፃሚ የማይሆነው በአዋጁ አንቀጽ ሠ መሠረት በልዩ ሕግ ለሚተዳደሩ የመንግሥት አስተዳደር ሠራተኞች እንጂ ለእኔ በልዩ አዋጁ ላልታቀፍኩት አይደለም በሚል ዓይነት መሟንገቷን ያመላክታል ይሁን እንጂ ተጠሪ እንደምትከራከረው በመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር አዋጁ የታቀፈች አይደለችም ሊባል የሚችል አይነት ቢሆን እንኳ አለመታቀፉ ብቻውን እርሷን በአዋጅ ቁ መሠረት ሠራተኛ አመልካቹን ደግሞ ድርጅት ሊያሰኛቸው የሚችል አይደለም ታቸው በተጠቀሰው አዋጅ የሚሸፈን ነው የሚል መደምደሚያ ላይ የሚያደርሰን አይሆንም አመልካች ድርጅት ተጠሪ ደግሞ የድርጅት ሠራተኛ መሆናቸው በአልተረጋገጠበት ሁኔታ የአዋጅ ቁ ን ለክርክራቸው ተገቢነት ሊኖረው የሚችልበት ሕጋዊ አግባብ አይኖርም እንዲሁም ተጠሪ አለኝ የምትለውን የመብት ጥያቄ ለግንኙነታቸው ተፈፃሚ ሊሆን ከሚገባው ሕግ አኳያ አቃንታ ልታቀርብ ከሚገባት በቀር የአዋጅ ቁ ድንጋጌዎችን ለመብቷ መጠየቂያ ልታደርግ አትችልም በዚህ ምክንያት የሥር ፍቤቶች የተቀጠሰውን አዋጅ ተመስርተው የሰጡትን ከፍ ሲል የተጠቀሰውን ፍርድ ይህ ችሎት አልተቀበለውም ውሣኔ የግምቢ ወረዳ ፍቤት የምዕራብ ወለጋ ከፍተኛ ፍቤት የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍሃቤት እና በመቁ ዐ የክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን በአዋጅ ቁ መሠረት አይተው የሰጡት ከፍ ሲል የተመለከተው ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽሯል የሰበር መቁ ዐ ቅምት ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ አሰግድ ጋሻው ወሮ ደስታ ገብሩ አመልካችፁ አቶ ተሾመ ጅፋር መልስ ሰጭ የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ኃቋሥራ ረረሮ ይሥራ ረረ ፇታሥዶቻ ፅዕልሳጣፇ ይሳሥሪና ሥራታኛ ፖዳይ ወጎኝ ዕርድ ፅዕሰማኃ ይላሰሐሪና ሥራፖኛ ዎጆ ቋ « አመልካች የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ይፈጸምልኝ በማለት ለአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ክስ ቢያቀርብም ቦርዱ ጉዳዩ በቦርዱ ውሣኔ ያገኘ በመሆነ በአፈጻጸም የሚጠየቅ ነው በማለት የሰጠውን ውሣኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ደመወዝ ጭማሪን አስመልክቶ የተሰጠ ውሣኔ የለም በማለት ሽሮ የደመወዝ ጭማሪውን ጉዳይ የማየት ሥልጣን የቦርዱ ነው ከሚል እምነት በመነሳት ጉዳዩን አይቶ እንዲወስን ለቦርዱ ሲመልስለት ቦርዱ በበኩሉ ጉዳዩን የማየት ስልጣን የለኝም በማለት ወሰነ ከቦርዱ ውሣኔ ይግባኝ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ቢቀርብም ፍሃቤቱ በጉዳዩ ፍርድ የሰጠሁበት በመሆኑ እንደገና ላየው የምችልበት ሥርዓት የለም በማለት ውድቅ ስላደረገው የቀረበ አቤቱታ ውሣኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የሰጡት ውሣኔ ፀንቷል የአሰሪ አጠቃላይ የደመወዝ ጭማሪ አወሳሰን ሥርዓት ሕገ ወጥ ነው በሚል የሚቀርብን ስክ የማየት ሥልጣን የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ነው የግል ጥቅምን መሠረት አድርጎ የሚቀርብን የደመወዝ ጭማሪ ክሱ የማየት ስልጣን የሥራ ክርክር ችሎት ነው ቅምት ቀን ዓም የመቁ ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ አሰግድ ጋሻው ወሮ ደስታ ገብሩ አመልካች አቶ ተሾመ ጅፋር ቀረበ ተጠሪ የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ግርማ ማርቆስ ቀረበ ፍርድ በዚህ መዝገብ የተያዘው የአመልካች እና የተጠሪ ክርክር የደመወዝ ጭማሪ ጥያቄን የሚመለከት ነው አመልካች ተጠሪው የተጠቀሰውን ክፍያ ይክፈለኝ ሲል ከአሰሪ እና ሠራተኛ ቦርድ ዘንድ ክስ ይመሰርታል ቦርዱም በሁለቱ መካከል በነበረ ክርክር አስቀድሞ የተሰጠ ፍርድ እንደነበር ጠቁሞ ይህም ጥያቄ አብሮ ፍርድ እንዳገኘ የሚቆጠር ነውና በአፈፃፀም እንጂ በክስ ሊጠየቅ የሚገባው አይደለም በማለት ይወስናል ከዚህ ውሣኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ደግሞ የደመወዝ ጭማሪን አስመልክቶ የተሰጠ ፍርድ ስለሌለ ጥያቄው በክስ እንጂ በአፈፃፀም ሊጠየቅ አይገባም በማለት የቦርዱን ውሣኔ ሳይቀበለው ቀርቷል እንደዚሁም ቦርዱ የደመወዝ ጭማሪውን ክርክር አይቶ ውሣኔ ይሰጥበት ዘንድ ጉዳዩን መልሶለታል ጉዳዩን ወደ ቦርድ የመለሰውም ይህን ክርክር የመዳኘት ስልጣን ያለው ቦርድ እንጂ ፍቤት አይደለም በሚል አምነት መሆኑን በውሣኔው አመላክቷል በመቀጠል ጥያቄው በቀጥታ ክስ አይነት ለአሰሪ እና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ ቀርቦለታል ቦርዱም ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ ጉዳዩን ለመዳኘት ስልጣን የለኝም ሲል መዝገቡን ዘግቶታል የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ደግሞ አስቀድሜ ፍርድ የሰጠሁበት ጉዳይ ስለሆነ ደግሜ ላየው የምችልበት ሥርዓት የለም በማለት በአሁን አመልካች የቀረበለትን ይግባኝ ውድቅ አድርጎታል ይህም ችሎት በግራ ቀኙ የቀረበለትን ክርክር መርምሯል ምላሽ ሊያገኝ የሚገባው የጉዳዩ ጭብጥም ቦርድ ይህን የደመወዝ « ርክር ለመዳኘት ሥልጣን አለው ። ምክንያት የለውም ሊባል የሚችል አይደለም ውሉ የተጣሰበት ወገን መፍትሄ ፍለጋ ወደሚመለከተው አካል ከሶ መቅረቡ ተገቢ ነው ውል ወይም ሕግ ተጥሶ የአንድ ወገን መብት የተጓደለ ከሆነ መብቱን ለማስጠበቅ ክስ ማቅረብ ትክክለኛ አሠራር ነው ጥቅም ተጓደለብኝ የሚል ሰራተኛ በሕጉ አንቀጽ መሠረት ቋሚ ነው የሚል የህግ ግምት ተጠቃሚ ስለሆነ ቋሚ መሆኑን ማስረዳት አያስፈልገውም ሠራተኛ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ እስካቀረበ ድረስ ጉዳዩን የሚያየው አካል ቋል እንደሆነ ግምት መውሰድ ይገባዋል ቋሚ እንዳልሆነ ማስረዳት የሌላኛው ወገን ኃላፊነት ነው ነገር ግን ይህ ጥቅም ቀረብኝ የሚል ሠራተኛ የሚያቀርበው ክስ የዛን ሠራተኛ ጉዳይ ብቻ የሚመለከት በመሆኑ በሕጉ አንቀጽ መሠረት እንደግል የሥራ ክርክር የሚቆጠር እንጂ የወል የሥራ ክርክር አይደለም ስለዚህ ከዚህ ጥያቄ የሚቀርበው ክስ የክስ ምክንያት የለውም ባይባልም ለቦርዱ ቀርቦ የሚስተናገድ ነጥብ ግን አይደለም የወል የሥራ ክርክር ከግል የሥራ ክርክር የሚለየው በምንድነው የሚለው የሕግ ነጥብ ላይ ይህ ፍቤት በመዝግብ ቁዐ በሐምሌ ቀን ዓም ውሣኔ የሰጠበት በመሆኑ አሁን በዝርዝር መድገሙ አስፈላጊ አይደለም ዋናው ነጥብ አንድ ሠራተኛ እሱን ብቻ የሚመለከትና የሌሎችን ሠራተኛ የሥራ ሁኔታ የማይመለከት ክስ ያቀረበ እንደሆነ ጉዳዩ የግሉ የሥራ ክርክር አንጂ የወል የሥራ ክርክር ሆኖ ሊታይ አይገባውም የወል የሥራ ክርክር ካልሆነ ደግሞ ለቦርዱ ቀርቦ ውሣኔ ሊሰጥበት የሚገባ አይሆንም በአዋጃ ቁ አንቀጽ መሠረት በአዲሱም አዋጅ ቁ አንቀጽ የግለ ሥራ ክርክር የማየት ሥልጣን ያለው መደበኛ ፍርድ ቤት ነው በመሆኑም በዚህም ረገድ ቦርድ የፄደበት አቅጣጫ ሕጉ ካስቀመጠው ሥርዓት ውጪ ነው በመሆኑም ለሌሎች ሠራተኞች የተሰጠ ጥቅማ ጥቅም ለኔ አልተጠበቀልኝም የሚለውን አጠቃላይ ክስ ቦርዱ የተመለከተው ከስልጣኑ ውጪ በመሆኑ ሊሻር የሚገባው ነው ለማጠቃለል ቋሚ ሰራተኛ እንደሆንኩ ይወሰንልኝ የሚለው ክስ የሌለው በመሆኑና የግል ጉዳይም በመሆኑ የጥቅማ ጥቅም ጥያቄውም ግል ክርክር በመሆኑ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ቀርበው መታየታቸው የጉዳዩ አመራር የህጉን ሥርዓት ያልተከተለ በመሆኑ የትክክለኛውን የሕግ ትርጉም ተከትሎ እንዲሄድ ማድረግ አስፈላጊ ነው ውሣኔ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ሚያዝያ ዓም በቁጥር ዐ የሰጠው ውሣኔና የፌከፍተኛ ፍቤት በመቁ ዐ ሰኔ ዓም የሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥቁ መሠረት በድምጽ ብልጫ ተሽሯል ውሣኔው የተሻረ መሆኑን እንዲያውቁት የፍርዱና የውሣኔው ቅጂ ይተላለፍላቸው ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ በየራሳቸው ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የሐሳብ ልዩነት አብዛኛው ድምጽ በተጠሪ የቀረበው አንድም የስራ ውሌ ያልተወሰነ ጊዜ የስራ ውል መሆኑነ ተረጋግጦ ይወሰንልኝ ሌላም የሚገባኝን ጥቅማ ጥቅም አንዳገኝ ውሳኔ ይሰጥልኝ የሚለው የክስ ነጥብ የውል የስራ ክርክር ሊሰኝ የሚችል ስለአልሆነ ጉዳዩን የመዳኘት ሥልጣን የአሰሪ እና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ አይደለም ሲል በሰጠው የውሣኔ ክፍል እኔም የምስማማበት ነው ይሁን እንጂ የሥራ ቅጥር ውሌ ላልተወሰነ ጊዜ እንደሆነ ይወሰንልኝ በሚል አይነት የቀረበው የተጠሪ አቤቱታ የክስ ምክንያት የለውምና በፍርድ ቤት ጭምር ሊስተናገድ የሚገባው አይደለም በሚል ዋነኛ ምክንያት ውድቅ በመደረጉ ባለመስማማት እንደሚከተለው በሐሳብ ተለይቻለሁ አንድ ከሣሽ ክስ በመሰረተበት ነገር ላይ ጥቅም ወይም መብት ያለው መሆኑን በማሳየት በሕግ አግባብ ዳኝነት ይሰጥለት ዘንድ መጠየቅ ይችላል ይህን ከላይ በአብዛኛው ድምፅ በተሰጠው ውሣኔ ውስጥ ከተጠቀሱት የፍብሥሥሕጉ ድንጋጌዎች ላይ ጭምር መረዳት ይቻላል ክሱ ጥቅም ወይም መብት የተጠየቀበት መሆኑን ለማሳየት የቻለ አስከሆነ ድረስ ደግሞ ጉዳዩ የክስ ምክንያት ያለው ነው ለመሰኘት ይበቃል በስራ ክርክር ጉዳይ በሚቀርቡ ክሶች እንዲጠየቅ የሚፈለገው ዳኝነትም ከዚህ አጠቃላይ መርህ በተለየ ሁኔታ እንዲታይ የሚያስገድድ ሕግ የለም ስለሆነም አንድ የሥራ ክርክርን የሚመለከት ክስ ደመወዝ የደመወዝ ጭማሪ የትርፍ ሰዓት ሥራ ክፍያ የሥራ ስንብት ክፍያ ወዘተ ሊከፈለኝ ይገባል በሚል አይነት የጥቅም ጥያቄን መሠረት አድርጐ ሊቀርብ ይችላል አለዚያም አድገት ይሰጠኝ ዝውውር ላገኝ ይገባል የተወሰደብኝ የዲሲፒሊን እርምጃ ተገቢ አይደለም ወዘተ የሚሉ የመብት ጥያቄዎችን ብቻ መሠረት አድርጎ ሊቀርብ ይችላል እነዚህ ከብዙ በጥቂቱ የተጠቀሱት የክፍያ ወይም የመብት ይረጋገጥልኝ ጥያቄዎች ለሥራ ክርክር ጉዳይ በተናጥልም ሆነ በጥምር የክስ ምክንያቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ከአዋጅ ቁ አንቀጽ ወዘተ መንፈስም መገንዘብ ይቻላል በተያዘው ጉዳይ ተጠሪ የሥራ ቅጥሩ የልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑ ተረጋግጦ እንዲወሰንለት በአቀረበው ክስ ጠይቋል በተጨማሪም ይገባኛል የሚላቸው ጥቅሞች መኖራቸውን እና አመልካቹ ጥቅሞቹን የከለከለውም ቅጥሩ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑን ስለአልተቀበለለት መሆኑን በክሱ አመላክቷል የክሱም አቀራረብ የሥራ ውሉ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል ነው ቢሰኝ ያጣቸው ጥቅሞች ያለ ሌላ ተጨማሪ ቅድመ ሁኔታ እንደሚከበሩለት ያስገነዝባል በሌላ በኩል ደግሞ አመልካቹ የተጠሪ የሥራ ውል የተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑን እና ጥቅሞቹ ያለተሰጡትም ቅጥሩ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል ባለመሆኑ ምክንያት መሆኑን ገልጾ ተከራክሯል ይህ የክርክራቸው ይዘት አመልካች እና ተጠሪ በመካከላቸው የነበረውን የሥራ ውል በየራሳቸው እንደሚጠ ቅማቸው የተረጎሙት መሆኑን ያረጋግጣል ይህም ግራ ቀኙ በተጠሪ የሥራ ውል ሁኔታ ላይ ማለትም የተጠሪ የሥራ ውል የተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል ነው። የሚል ክርክር ሊነሳ እንደሚችልም በአብዛኛው ድምፅ ጭምር መታመኑን ከውሣኔው መገንዘብ ይቻላል እንዲህ ከሆነ ደግሞ የሥራ ውሌ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑ ይረጋገጥልኝ በሚል አይነት የሚቀርብ ክስ የክስ ምክንያት የለውም የሚል መደምደሚያ ላይ ሊደርስ የሚገባ አይሆንም ምክንያቱም የክስ ምክንያት ያላቸውም የሚባሉ ክሶች በይዘታቸው ተከሣሹ ክሱ በተመሰረተበት ጉዳይ ላይ የውልም ሆነ የሕግ ኃላፊነት እንደአለበት የሚያመለከቱ አይደሉም እንዲህ ያሉ ክሶች ከመሰረቱም ክሱ ተከሣሹ ላይ ሊመሰረት የቻለበትን ሕጋዊ ምክንያት ለማሳየት የሚበቁም አይደሉም ጉዳዩ ተከሣሹን የማይመለከተው መሆኑነ ግልፅ ከመሆኑ የተነሳም ወደ ክርክሩ ፍሬ ነገር መግባቱ አስፈላጊ አይሆንም የሥራ ውሌ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑ ተረጋግጣ ውሣኔ ይሰጥልኝ የሚል ምክንያት ይዘው የሚመሰረቱ ክሶች ግን አሰሪ የሆነው ተከሣሽ ቅጥሩ የተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑን እስከአላስረዳ ድረስ የሥራ ውሉን ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል ያደረገው ዘንድ የሕግ ኃላፊነት እንዳለበት የሚያመላክቱ ናቸው በተጨማሪም በዚህ መዝገብ የተያዘውን ክርክር ጨምሮ በሌሎች በርካታ መሰል ሙግቶችም ውስጥ ተከታይ ጥቅሞችን ያለክርክር ለማስገኘት የሚበቃን የመብት ጥያቄ መሰረት አድርገው የሚመሰረቱ ናቸው ስለሆነም የክስ ምክንያት የላቸውም የሚባሉ አይሆኑም ከፍ ሲል አንደተመለከተው የዚህ መዝገብ ተከራካሪዎች ልዩነት የቅጥሩን የቆይታ ጊዜ ብቻ የሚመለከት ነው በጥቅሞቹ አከፋፈል ጉዳይ ላይ ስምምነት እንጂ ልዩነት አንደሌላቸው ግልፅ ነው የተጠሪ የሥራ ውል በሕግ አግባብ ተመዝኖ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑ ቢረጋገጥ ተጠሪው ጥቅሞቹን ሊያገኛቸው እንደሚችል በአመልካቹ ጭምር የታመነ መሆኑን ከክርክሩ መገንዘብ የሚቻል ነው ይህ ደግሞ የተጠሪ የሥራ ውል የተወሰነ ወይም ያልተወሰነ ጊዜ ውል መሆኑ በፍርድ ሳይረጋገጥ ተጠሪው ጥቅሞቹን ያገኛል ወይም አያገኝም የሚል መደምደሚያ ላይ ሊደርስ እንደማይችል የሚያረጋግጥ ነው አከራካሪ ሆኖ የተገኘው የሥራ ቅጥሩ ሁኔታ አስቀድሞ ሳይፈታ የጥቅም ጥያቄው ጉዳይ ምላሽ ሊያገኝ እንደማይችል እየታወቀም የክሱ ዋና ክፍል የሆነው የሥራ ውሌ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑ ተረጋገጦ ይወሰንልኝ የሚለው የተጠሪ አቤቱታ የክስ ምክንያት የለውም መባሉ ሕጋዊ አሳማኝነት የሌለው ነው በአኔ እምነት የሥራ ውሌ ያልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል መሆኑ ይወሰንልኝ በሚል አይነት የሚቀርቡ ክሶች ምንም እንኳን የወል የሥራ ክርክር ባለመሆናቸው ምክንያት በአሰሪ እና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ሊታዩ የማይችሉ ቢሆኑም የግል የሥራ ክርክር አይነቶች በመሆናቸው በፍርድ ቤት ሊዳኙ የሚገባቸው ናቸው ስለሆነም እነዚህ ጥያቄዎች የክስ ምክንያት የላቸውምና የትኛውም የዳኝነት አካል ዘንድ ሊቀርቡ አይችሉም በሚል በአብዛኛው ድምፅ በተሰጠው የውሣኔ ምክንያት ባለመስማማት ስሜ በሦስተኛ ተራ የተጠቀሰው ዳኛ በሐሳብ ተለይቻለሁ የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ መስፍን ዕቁበዮናስ አመልካች የሸቀጦች ጅምላ ንግድና አስመጪ ድርጅት መልስ ሰጪ አቶ ንጉሴ ዘለቀ ይጎነራ ፇቀፖ ዕሐማቋረም ፅሳሰሪ ለቱሳያጃራያኦታ ዖሟደረፇ ይጎራ ውሰ መቋረም ያዕማዕጠቃደዴዖ ይጎራ ውል ኃቋማያረዋ ዕፅ ደመወቻ ዕራ ልኋሦፅዕራያፖ ፍዖሥ ዕፅሟደረቨያምፖ ታኔሥ የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁ አንቀጽ በ መልስ ሰጪ የአመልካች ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ሆኖ በማሰራበት ወቅት በስሩ የሚገኘውን ገንዘብ ያዥ በተገቢው ሁኔታ ባለመቆጣጠሩ የአሰሪው ድርጅት ገንዘብ እንዲመዘበር ምክንያት በመሆኑ መሰጪ ከስራ የተሰናበተው በአዋጁ ቁ አንቀጽ በ መሠረት በአግባቡ ነው በሚል የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የሰጠውን ውሣኔ በመሻር የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት መሰጪ ውዝፍ ደመወዝ ተከፍሏቸው ወደ ስራ እንዲመለስ ውሣኔ በመስጠቱ የቀረበ አቤቱታ ውሣኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ውሣኔ በድምጽ ብልጫ ተሽራል ንዘብ አንድ ግዙፍነት ያለው ተንቀሣቃሽ ንብረት ነው በአሰሪ ገንዘብ ላይ የደረሰ ጉዳት በአሰሪ ንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት ነው የአዋጅ ቁ ድንጋጌዎች የስራ ውል በአሰሪው አነሳሽነት በተቋረጠበትና የስራ ውሉ የተቋረጠው ከሕግ ውጪ ነው የሚል ውሣኔ በሚሰጥበት ወቅት ሠራተኛው ያልሰራበትን ጊዜ ደመወዝ እንዲያገኝ የሚፈቅዱ አይደሉም የመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ አብድልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ መስፍን አቁበዮናስ አመልካችፁ የሸቀጦች ጅምላ ንግድና አስመጪ ድርጀት አልቀረበም ተጠሪ አቶ ንጉሜ ዘለቀ አልቀረበም ፍርድ ተጠሪ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአመልካች ላይ ክስ መስርቶ የሥራ ውሌን ከሕግ ውጭ ስላቋረጠው ውዝፍ ደመወዜን ከፍሎ ወደ ሥራ እንደመልሰኝ ይወሰንልኝ ሲል ጠይቋል ይህ ክስ የቀረበለት ፍቤት ግራ ቀኙ በጉዳዩ ያቀረቡለትን ክርክርና ማስረጃ ከመረመረ እና የአመልካችን ኦዲተር በምስክርነት ከሰማ በኋላ ተጠሪ ከሥራ የተሰናበተው በአመልካቹ ላይ ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት በማድረሱ ምክንያት ስለሆነ ስንብቱ በሕብረት ስምምነቱ እና በአዋጅ ቁ አንቀጽ በ የተደገፈ ነው ሲል ወስኗል ይህ ውሣኔ ይግባኝ በቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ተሽሮ ተጠሪ የሦስት ወር ደመወዝ ተከፍሎት ወደ ሥራው እንዲመለስ አንዲሁም ብር ወጭና ኪሣራ እንዲከፈለው ተወስኗል አመልካች ተጠሪው ወደ ሥራ ሊመለስም ሆነ ውዝፍ ደመወዝ ሊከፈለው አይገባም በማለት አቤቱታውን ለዚህ ችሎት አቅርቧል ተጠሪው ደግሞ በሰጠው መልስ ውዝፍ ደመወዙን የማላገኝበት የሕግ ምክንያት የለም በማለት ተከራክሯል ወደ ሥራ መመለስን አስመልከቶ ስለቀረበው አቤቱታ የሰጠው መልስ ግን አለመኖሩን ማመልከቻው ያስረዳል ይህም ችሎት ጉዳዩን መርምሯል በክርክሩ ሊፈቱ የሚገባቸው ጭብጦችም የተጠሪ የሥራ ውል መቋረጥ በሕግ የተደገፈ ነው። በተጠሪ ተፈጽመዋል ወደተባሉ ሌሉች ጥፋቶች ዘ « ኒጸም አለመፈጸማቸውንም ለማጣራት አልሞከረም ለፍርዱ መሠረት ያደረገው ገንዘብ ያዥው ገንዘብ ባጎደለበት ጊዜ ተጠሪው ሥራ ላይ ስላልነበረ ወደ ሥራ ሲመለስ አልተቆጣጠርክም ተብሎ መሰናበቱ ትክክል አይደለም የሚለውን ምክንያት ነው ይህ ደግሞ ፍቤቱ በአመልካች የተነሱትን የክርክር ነጥቦች በሙሉ ቃኝቶ ፍሬ ነገሩን በማጥራት ፍርድ አለመስጠቱን የሚያመላክት ነው እንዲሁም የሥር ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ፍሬ ነገር የደረሰበትን መደምደሚያ አሳማኝ ምክንያት ላይ ሳይመሰረት የለወጠው መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው ወደ ሕጉ ስንመለስ በአዋጅ ቁ አንቀጽ ስር ያለማስጠንቀቂያ የሥራ ውል ሊያቋርጡ የሚችሉ ምክንያቶች የተዘረዘሩ ሲሆን ለዚህ ጉዳይ አግባብነት የሚኖረው በአሰሪው ንብረት ወይም ከሥራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኛነት ጉዳት ማድረስ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ እንደሚያቋርጥ የሚደነግገው አንቀጽ በ መሆኑን ችሎቱ አምኖበታል ችሎቱ አዚህ እምነት ላይ የደረሰው ጉዳዩን ከፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ እና ጋር አገናዝቦ በማየትና ገንዘብ አንዱ ግዙፍነት ያለው ተንቀሳቃሽ ንብረት መሆኑን በመቀበል ነው በተጨማሪም አንድ ሠራተኛ በአሰሪው የተሰጠውን ኃላፊነት ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት አንድን ነገረ በማድረግም ይሁን ባለማድረግ ሳይወጣው ቢቀርና በዚህ ድርጊቱ ሌላው ሰው በአሰሪው ገንዘብ ላይ በቀጥታ ጉዳት እንደያደርስ ተባብሮ ቢገኝ እራሱ በአሰሪው ንብረት ላይ ጉዳት እንደደረሰ ሊቆጠር ይገባዋል የሚል ትርጓሜ ለተጠቀሰው የአዋጅ ቁ አንቀጽ በ በመስጠቱ ነው ከፍ ሲል እንደተመለከተው ተጠሪው ሥራ ላይ በነበረበት ወቅት ገንዘብ ያዥው ያደረሰውን የገንዘብ ጉድለት መቆጣጠር ሲገባው አልተቆጣጠረም ይህ ደግሞ ቢያንስ በከባድ ቸልተኛነት በአመልካች ንብረት ላይ ቀጥተኛ ባልሆነ ሁኔታ ጉዳት ማድረሱን ያረጋግጣል ስለሆነም የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት የሥራ ውሉን መቋረጥ ሕገ ወጥ በማድረግ ተጠሪ ወደ ሥራ እንደመለስ መወሰነ ከተጠቀሰው ድንጋጌ ጋር ያልተጣጣመ ሆኖ አግኝተነዋል ቀጥሎ ተጠሪ ከሥራ ከተሰናበተ ጊዜ ጀምሮ ያለው ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈለው ሕጉ ይፈቅዳል ወይስ አይፈቅድም የሚለውን ነጥብ እናያለን ከላይ እንደተጠቀሰው ፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ተጠሪ የሦስት ወር ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈለው ተወስኗል ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈል የታዘዘው ሥራ ያልተሠራው በሠራተኛው ጉድለት ባልሆነ ምክንያት ነው በማለትና የአዋጁን አንቀጽ መሠረት በማድረግ እንደሆነ ይታመናል ይህም ውሣኔ በአንቀጽ ላይ የሠፈረው ድንጋጌ አባባልና መንፈስ የሚመለከተው የሥራ ውሉ ተቋርጦ የቆየን ሠራተኛ ነው ወይስ ከዚህ የተለየ አኳኋን ያለውን ሠራተኛ ነው የሚለውን ጥያቄ ያስነሳል ይህንነ ለመረዳት ለዚህ አንቀጽ መሠረት የሆኑትን የ እና የን ድንጋጌዎች መመልከት ያስፈልጋል የአዋጁ አንቀጽ ደመወዝ ማለት አንድ ሠራተኛ በሥራ ውሉ መሠረት ለሚያከናውነው ሥራ የሚከፍለው መደበኛ ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል የአዋጁ አንቀጽ ም እንደዚሁ በአዋጁ ወይም አግባብ ባለው ሕግ በተለየ አኳኋቷን ካልተወሰነ ደመወዝ የሚከፈለው ለተሠራ ሥራ ብቻ መሆኑን በግልጽ ያስቀምጣል ከነዚህ ሁለት የተያያዙ የሕግ ድንጋጌዎች የደመወዝን ምንነት እና የአከፋፈል ሁኔታ መገንዘብ ይቻላል በአንድ በኩል አንድ ሠራተኛ ደመወዝ የሚከፈለው ከውል የመነጨ ግዴታውን መፈፀም ሲችል እንደሆነ እናያለን የሠራተኛ እና የአሠሪ ግንኙነት የሚመነጨው ሁለቱም ወገን ከሚገቡት ውል ነው። ይኸው ውል እንደማንኛውም ሌላ ውል ለሁለቱም ወገን መብት ያመነጫል ግዴታንም ይጥላል ከነዚህ ተያያዥ መብትና ግዴታዎች አንዱ ሠራተኛው በውል ለማከናወን ቃል የገባውን ሥራ የማከናወን በተሠራው ሥራ መጠን ደግሞ በውሉ በተጠቀሰው ጊዜና መጠን ደመወዝ የማግኘት መብትና ግዴታ ነው በዚህ መሠረት አሠሪው ከሠራተኛው ግልጋሎት ያገኛል ባገኘው ግልጋሎት መጠንም በውሉ የተጠቀሰውን ደመወዝ የመክፈል ግዴታ ይኖርበታል በመርህ ደረጃ እነዚህ መብትና ግዴታዎች ከውል የሚመነጩ አንዱ ያለሌላው ሊታሰቡ የማይችሉ የአንድ ሕጋዊ ግንኙነት ሁለት ገጽታዎች ናቸው ስለዚህ ሥራ ሳይሠራ ደመወዝ ሊከፈል አይችልም ደመወዝ ሳይከፈል ደግሞ ሥራ ሊከናወን አይችልም ይህ አጠቃላይ አባባል ከውል ሕግ መሠረተ ፃሳብ ጋር የሚጣጣም ነው ይህ አጠቃላይ መርህ እንደተጠበቀ ሆኖ ሕጉ ሠራተኛው ሥራ ባይሠራም ደመወዝ ሊከፈለው የሚችልበትን ሁኔታ በተለየ አስቀምጧል በዚህም መሠረት በአዋጁ አንቀጽ ከሁለት ሁኔታዎች አንዱ ተሟልቶ ከተገኘ ሠራተኛው ሥራ ባይሠራም አሠሪው ደመወዝ የመክፈ « ታ ተጥሉበታል እነዚህ ሁኔታዎች አንደኛ ሠራተኛው ዝንጁ ሆኖ እያለ አሠሪው ለሥራው አስፈላጊ የሆነውን መሣሪያና ጥሬ እቃ ሳያቀርብለት የቀረ እንደሆነ ወይም ሁለተኛ ሠራተኛው ሥራ ሳይሠራ የዋለው በራሱ ጉድለት ባልሆነ ምክንያት እንደሆነ የሚሉት ናቸው እነዚህ ሁለት የተለዩ ሁኔታዎች ከሥራ ውልም ሆነ ከአጠቃላይ የውል መሠረታዊ መርሆዎችና ድንጋጌዎች ጋር ተያይዘው መተርጎም ይኖርባቸዋል ከላይ እንደተገለፀው የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት የሚመነጨው ከሥራ ውሉ ነው የአሠሪ ደመወዝ የመክፈል ግዴታም የሚመነጨው እንዲሁ ከሥራ ውሉ ነው በሌላ በኩል የሥራ ውል ቢኖርም ደመወዝ የሚከፈለው ለተሠራ ሥራ ብቻ በመሆኑ ሠራተኛው ሥራ ሳይሠራ ደመወዝ እንዲከፈለው ሊጠይቅ አይችልም ሠራተኛው በርሱ በኩል ያለውን የመሥራት ግዴታ ሳይወጣ አሠሪው ደመወዝ የመክፈል ግዴታውን እንዲፈጽም ሊጠይቅ የሚችለው ከላይ ከተጠቀሱት ሁለት ምክንያቶቹ አንዱ መኖሩን በማስረዳት ነው ስለዚህ በአዋጁ አንቀጽ ያሉት ሁለት መስፈርቶች ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉት በአሠሪና በሠራተኛ መካከል ያለው የሥራ ውል ፀንቶ በሚቆይበትና ሠራተኛው በሥራ ገበታው በሚገኝበት ጊዜ ብቻ ነው የሥራ ውል በሌለበት ወይም የነበረ የሥራ ውል በተቋረጠበት ሁኔታ የአዋጁ አንቀጽ ተፈፃሚ ሊሆን አይችልም የሥራ ውል በሁለቱም ወገን ሊከበር እንደሚገባና ሊቋረጥ የሚችለውም በሕጉ በሰፈሩ ምክንያቶች ብቻ እንደሆነ ግልጽ ነው በሌላ በኩል አንድ አሠራ በአዋጁ አንቀጽ የተጠቀሱ ሁኔታዎች ተሟልተዋል ብሎ ሲያምን ያለማስጠንቀቂያ በአንቀጽ የተዘረዘሩት ሁኔታዎች ተሟልቷል ብሎ ሲያምን ደግሞ ሕጉን ተከትሎ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የሥራ ውሉን ማቋረጥ እንደሚችል ሕጉ ይደነግጋል በዚህም መሠረት የሥራ ውልን ለማቋረጥ አሠሪው ክስ መመስረት ሳያስፈልገው የተናጠል እርምጃ የመውሰድ ሕጋዊ መብት አለው አሠሪው በዚህ ረገድ የሰጠው ውሣኔ የሥራ ክርክርን መርምሮ የመወሰን ሥልጣን ባለው አካል ታይቶ እስካልተሻረ ድረስ በሁለቱም ወገን የነበረውን የሥራ ግንኙነት ቀሪ እንዲሆን ያደርጋል አሠሪው የሥራ ውሉን ያቋረጠው ሕግ በማይቀበለው ምክንያት የሆነ እንደሆነ ሠራተኛው ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን ወደአለው አካል ማቅረብ መብት አለው ጉዳዩ የቀረበለት አካል አሠሪው የወሰደው ውሣኔ ሕጉን መሠረት ያደረገ መሆን አለመሆኑን በመመርመር ውሣኔ መስጠት ይጠበቅበታል ቀድሞውኑ አሠሪው የሥራ ውሉን ያቋረጠው በሕጉ መሠረት አይደለም ወደሚል መደምደሚያ ከደረሰ ለሠራተኛው የሚሰጠው መፍትሔ ዐሃ ሕጉ የሥራ ውል አለአግባብ ባቋረጠ አሠሪ ተፈፃሚ አንዲሆን የፈቀደውን መፍትሔ ብቻ ነው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁ አንቀጽ የሥራውል አለአግባብ ወይም ሕገወጥ በሆነ ሁኔታ ሲቋረጥ ለሠራተኛው የሚሰጠው መብት በአማራጭ ወደ ሥራ መመለስ ወይም እነደነገሩ ሁኔታ የካሣ ክፍያ የማግኘት መብት ብቻ ነውር ሠራተኛ ወደ ሥራ እንዲመለስ ከማድረግ በተጨማሪ ሠራተኛው ሥራው ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ ያለው ደመወዝ እንዲከፈለው የሚያዝ የሕግ አንቀጽ የለም በመሆኑም አለአግባብ ከሥራ የተሰናበተ ሠራተኛ ወደ ሥራ እንዲመለስ ከማድረግ በተጨማሪ ሥራ ላይ ላልነበረበት ጊዜ ደመወዙ እንዲከፈለው ማድረግ ሕጉ አይፈቅድም ከላይ እንደተገለፀው በመሠረቱ መክፈልም ከተቻለ ደመወዝ የሚከፈለው የሥራ ውል ላለው ሠራተኛ ነውፎ የሥራ ውሉ የተቋረጠው ሕገወጥ በሆነ መንገድ ነው ቢባል እንኳ የሥራ ውሉ ውሣኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ እንዲቀጥል ከማድረግ አልፎ ውሣኔው ወደ ኋላ ተመልሶ አሠሪው የሰጠውን ውሣኔ እንዳልተሰጠ መቁጠርና የሥራ ውል እንዳልተቋረጠ በማሰብ ሠራተኛው ሳይሠራ የቀረው በርሱ ጥፋት ባልሆነ ምክንያት ነው ማለት የሚቻል አይደለም ሠራተኛው በአሠሪው ውሣኔ ከሥራ እንዲሰናበት ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ሠራተኛው በፍርድ ወደ ሥራ እንዲመለስ በተወሰነበት ጊዜ መካከል የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት አለ ሊባል አይችልም ለዚህ ጊዜ ደመወዝ እንዲከፈል ማዘዝም አይቻልም በአጠቃላይ ፍርድ ቤቱ አመልካች ውዝፍ ደመወዝ ይከፈል በማለት የሰጠው ውሣኔ አግባብነት በአላቸው የአዋጅ ቁ ድንጋጌዎች ትክክለኛ ትርጉም ላይ የተመሠረተ አይደለም በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ እያንዳንዱ ባለጉዳይ የሚያቀርበውን የሕግ ክርክር መርምሮ ውሣኔ የመስጠት ኃላፊነት አለበትፎ ተከሣሹ ወገን በሕግ ነጥብ ላይ መልስ ሰጥቶ ባይገኝ ደግሞ የሕግ ጉዳይ የቀረበለት ፍቤት በእራሱ አነሳሽነት በጉዳዩ ጭብጥ ይዞ ውሣኔ ይሰጥበት ዘንድ ይጠበቅበታል ውዝፍ ደመወዝ መከፈል አለበት ወይስ የለበትም የሚለው ነጥብ የሕግ ጥያቄ እንደመሆኑ መጠን ፍርድ ቤት ከተከሳሹ ወገን የቀረበለት ክርክር ያልነበረ ቢሆን እንኳ ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጥበት ያስፈልጋል ውሣኔ የተጠሪ የሥራ ውል መቋረጥ በአዋጅ ቁ አንቀፅ በ የተደገፈ ስለሆነ ወደ ሥራ ሊመለስ አይገባም በማለት ተወስኗል እንዲሁም ይህ ችሉት አግባብነት ያላቸውን የአዋጅ ቁ ድንጋጌዎች በመተርጎም ሕጉ አንድ የሥራ ውል በአሰሪው አነሳሽነት በተቋረጠበትም ሆነ የተቋረጠው ከሕግ ውጭ ነው በሚል ውሣኔ በሚሰጥበት ሁኔታ ሠራተኛው ያልሰራበትን ጊዜ ደመወዝ እንዲያገኝ የሚፈቅድ አይደለም የሚል መደምደሚያ ላይ በመድረሱ ተጠሪ ውዝፍ ደመወዝ ሊከፈለው አይገባም በማለት ተወስኗል የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት ተጠሪ የሦስት ወር ውዝፍ ደመወዝ ተከፍሎት ወደ ሥራ እንዲመለስ የሰጠው ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት በድምጽ ብልጫ ተሽራል ይኸው ይፃፍ የሐሳብ ልዩነት አኔ ስሜ በተራ ቁጥር ላይ የተመለከተው ዳኛ በዚህ ጉዳይ የአሁኑ ተጠሪ ለፈፀመው ተግባር የሥራ ውሉ እንዲቋረጥ በማለት በአብላጫው ድምፅ በተሰጠው መደምደሚያ የምስማማ ቢሆንም አብላጫው ድምፅ ተጠሪ ፈፀመ ለተባለው ተግባር ለውሣኔው ዋቢ አድርጐ የጠቀሰው አንቀጽ በ በተጠሪ ተፈፀመ ከተባለው ድርጊት ጋር ግንኙነት የሌለው በመሆኑ በዚህ የህግ ድንጋጌ ሊሸፈን ባልተገባው ነበር አላለሁ የተጠሪ የሥራ ውል በአሰሪው እንዲቋረጥ የተደረገው ተጠሪ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ በሚሠራበት ቅርንጫፍ በሥሩ የሚገኘውን ገንዘብ ያዥ በተገቢው ሁኔታ ባለመቆጣጠሩ የአሠሪው ድርጅት ገንዘብ እንዲመዘብር ምክንያት ሆኖአል በሜል ነው አብላጫው ድምፅ ይህ አይነቱ ድርጊት በአዋጁ አንቀጽ ። ዐህሀክ የሚፈፀሙ መሰል የገንዘብ ብክነቶችን የሚሸፍን አይደለም በማለት በመደምደሚያ ሃሣቡ ተስማምቼ በሕጉ አተረጓጉም ላይ በዛፃሣብ ተለይቻለሁ የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ ዓለሙ ወሮ ደስታ ገብሩ አቶ አሰግድ ጋሻው አመልካች ንብ ትራንስፖርት አማ መልስ ሰጪ አቶ ተገኑ መሸሻ ዖያነራዎሥቻ ፅሳፇሃታሦ መሰጋፖ ዖሟመሰጎ ውታፇ ፅራሦኛው ፅዕፅቋማሃፇፀው ደረመወሃ መታ ፅሰራ ጳኋሃፅዕራያፖው ፇናሦ ደመወጀ ፅዕጎፅማፇኝታ ዕፅ ዕራ አሐመናሂ ነዮረጅሦፖ ውዕምዎ ይጎራ መሪ ፅዕሰያ ራፖሯቻሪ ያፍፖጋጩጨረ ጋፇ ቋፖረ ሪዐ መልስ ሰጪ በአመልካች ድርጅት ውስጥ በቴክኒክ ዋና ክፍል ኃላፊ ሆኝ ስሰራ ከስራ ከመሰናበቴ በፊት ታግጄ በቆየሁበት ከታህሣሥ ቀን ዓም ጀምሮ እስከ ሰኔ ቀን ዓም ድረስ ያለው ደመወዜ እንዲከፈለኝ በማለት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ያቀረበውን ክስ ፍቤቱ ተቀብሎ መሰጪ የጠየቀው ገንዘብ እንዲከፈለው ውሣኔ በመስጠቱና ውሣኔውም በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመጽናቱ የቀረበ አቤቱታ ውሣኒኔ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የሰጠውና የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ያጸናው ውሣኔ ተሽራል በድርጅት ሥራ መሪና በድርጅቱ መካከል ያለ የስራ ክርክር የሚዳኘው በፍትሐብሔር ህጉ የስራ አገልግሎትን መስጠት ስለማመለከቱ ውሎች ከቁጥር አና ተከታታዮቹ በተደነገጉት ህጐች መሠረት ነው የስራ መሪ ደመወዝ ለተሰራ ስራ ብቻ የሚከፈል እንጂ ላልተሰራ ስራ የሚከፈል አይደለም የስራ መሪው አንድም የስራ አገልግሎት ባይሰጥም እንኳን ይኸው ሁኔታ አሰሪው ስራ ሳይሰጠው በመቅረቱ ወይም እንዳይሰራ በመከልከሉ የተነሳ አንደሆነ ደመወዙን ለማግኘት መብት የለው ውሉ ባልታገደበት ወይም ባልተቋረጠበት ጊዜ ሠራተኛው የስራ መሪው ስራ ላይ ሆኖ ነገር ግን አሰሪው ሥራ ሳይሰጠው ወይም እንዳይሰራ በከለከለው ጊዜ እንጂ ሠራተኛው ከስራና ከደመወዝ ታግዶ የስራ አገልግሎት ላልሰጠባቸው ጊዜያት አይደለም የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ ዓለሙ ወሮ ደስታ ገብሩ አቶ አሰግድ ጋሻው አመልካች ንብ ትራንስፖርት አማ መልስ ሰጪ አቶ ተገኑ መሸሻ ለዚህ የሠበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ነው በሥር ፍቤት የአሁን ተጠሪ ከሣሽ ሲሆን አመልካቹ ተከሣሽ ነበር የተሰጠው የሥራ ክስ በድርጅቱ ውስጥ የቴክኒክ ዋና ክፍል ሀላፊ ሆኝ ስሠራ ከታህሣሥ ዓም ጀምሮ ከሥራ ታግጄ ከቆየሁ በኋላ ሰኔ የተፃዓፈ የስንብት ደብዳቤ ተሠጥቶኛል ስለዚህ ከታገድኩበት ጊዜ አንስቶ እስከተሠናበትኩበት ጊዜ ድረስ ያለው የ ወር ከ ቀን የተጣራ ደመወዜ ሃያ ሦስት ሺህ አምስት መቶ ብር ወጪና ኪሣራ ተጨምሮ ይከፈለኝ የሚል ነው የሥር ተከሳሽ ማለትም ተጠሪው ቀርቦ የይርጋ መቃወሚያ አንስቶ በብይን ውድቅ የተደረገበት ቢሆንም ፍሬ ጉዳዩን በተመለከተ ከሣሽ ከሥራ የተሠናበተው ድርጅቱን የሚጐዳ ተግባር የፈፀመ መሆኑን በመግለጽ ሥራ ላልሠራበት ጊዜ ደመወዜ ሊከፈለው እንደማይገባ ይከፈለው ቢባል እንኳ ከ ወር ደመወዝ ሊበልጥ አንደማይችል በመግለጽ ተከራክራል ክሱ የቀረበለት ፍቤትም ከሣሽ የሥራ መሪ እንደመሆኑነ በፍህጉ ላይ የሥራ መሪን ከሥራ ስለማገድ የተደነገገ ድንጋጌ የለም በድርጅቱ የውስጥ ደንብ ስለመኖሩና በውስጥ ደንቡ መሠረት ስለማገዱ አላስረዳም በመልስ የዘረዘራቸውን ተግባራት ከሣሽ ፈጽመዋል ቢባል እንኳ ከሥራና ከደመወዝ ለማገድ በቂ ምክንያቶች አይደሉም በፍሕቁጥር ሠራተኛው አገልግሎት ባይሰጥም ይህ የሆነው በአሠሪው ምክንያት ከሆነ ደመወዝ የመክፈል ግዴታ አለበት የ ወር ደመወዝ ብቻ ሊከፈላቸው ይገባል የሚለው የተከሣሽ ክርክር በፍሕቁጥር የተመለከተው የ ወር ደመወዝ ክፍያ የሥራ ውሉ ለተቋረጠበት እንጂ የሥራ ውሉ ለታገደበት ጊዜ የሚመለከት አይደለም በማለት ክስ የቀረበበትን ገንዘብ ተከሣሽ ለከሣሽ እንዲከፍል ውሣኔ ሰጥቷል አመልካቹ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌከፍተኛ ፍቤት ቢያቀርብም በፍሥሥሕቁጥር መሠረት ይግባኙ ተሠርኮበታል አመልካቹ የሥር ፍቤቶች ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለበት ይታረምልኝ ሲል በ የተፃፈ የሰበር አቤቱታ አቅርቧል የአቤቱታው ፍሬ ቃል ተጠሪው በ እና በ ተጽፎ የተሰጣቸው ደብዳቤ የሥራ ስንብት ሣይሆን የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት መሆኑን የሥር ፍቤት በአግባቡ አልመረመረም አመልካች ተጠሪን ከሥራ ለማገድ ምክንያት ያደረገው በድርጅቱ ሥራና ገንዘብ ላይ በተለያዩ ጊዜያት ጉዳት ማድረሣቸውን የሚያመለክቱ ናቸው ፍቤቱ የፍሕቁጥር ስለ ሥራ ውል መቋረጥ እንጂ ስለ ሥራ ውል ማገድ የሚመለከት አይደለም ያለው ያለአግባብ ነው ተጠሪው በእገዳ ላይ ለቆዩበት ጊዜ ሥራ እንዳይሠሩ የከለከላቸው ድርጅቱ ነው ተብሎ ደመወዙ ይከፈለው መባሉ ስህተት ነው ምክንያቱም የፍሕቁጥር ሥራ ላልተሠራባቸው ቀኖች ሠራተኛው ደመወዝ ለማግኘት መብት የለውም የሚለውን የሚቃረን ነው የፍህግ ቁጥር ከ ወር የማይበልጥ ክፍያ እንዲከፈል የደነገገው የሥራ ውል ሲቋረጥ ብቻ ነው ተብሎ የተሰጠው ትርጉም ስህተት ነው በአጠቃላይ የሥር ፍቤቶች ውሣኔ መሠረታዊ የሕግ ሥህተት ያለበት ስለሆነ ውሣኔዎቹ ተሽረው ወጪና ኪሣራ ተከፍሎን እንሠናበት የሚል ነው የሰበር አቤቱታ ማመልከቻው ለተጠሪው ደርሶ ሚያዝያ ዓም በተፃፈ መልስ የአመልካች የሰበር አቤቱታ የሕግ ስህተት መፈፀሙን አይገልጽም የ ወር የጊዜ ገደብ የከሣሽን የጥቅም ጥያቄ በይርጋ አያግደውም ተጠሪው በጥፊት ተከስሼ አላውቅም ባልተቀጣሁበት ጉዳይ ጥፋት ነው ተብሎ ለሠበር አቤቱታ መቅረቡ የለአግባብ ነው ተጠሪ በ እና በ የተባፈው የሥራ የምስክር ወረቀት እንጂ የሥራ ስንብት ደብዳቤ አይደለም ያሉት የፍሬ ነገር ክርክር እንጂ የህግ ስህተት መሆኑን አያመለክትም አመልካች መቤት ከሥራና ከደመወዝ ያለበቂ ምክንያት አግደውና አሰናብተው ስለአጉላሉኝ በደሉ ታይቶ የተሰጠው ውሣኔ የሕግ ስህተት ሳይሆን የፍሬ ነገር ክርክር ነው በፍሕግ ቁጥር ሥራ ላልሠራባቸው ቀኖች ደመወዝ ሊከፈለው አይገባም ለተባለው ተጠቃሹ ህግ ሠራተኛው ሥራውን በራሱ ፍላጐት ሣይሠራ ሲቀር አንጂ አሠሪው ሥራ ሲከለክለው የሚጠቀስ አይደለም የፍሕግ ቁጥር ለኪሣራ እንጂ ውዝፍ ደመወዝን የሚመለከት አይደለም ከዚህ ጉዳይ ጋርም ግንኙነት የለውም ስለሆነም ጥያቄው ከበቂ ኪሣራ ጋር ተሠርዞ እንድሠናበት በማለት ሲከራከር አመልካቹ አቤቱታውን በማጠናከር የመልስ መልሱን አቅርቧል በግራ ቀኙ መካከል የቀረበው ክርክር ከፍ ብሎ በዝርዝር የተመለከተው ሲሆን በኛ በኩል ተጠሪው ከሥራ ታግዶ ለቆየበት ጊዜ ደመወዙ ይከፈለው መባሉ ተገቢ መሆን አለመሆኑን አግባብ ካላቸው ሕጐች ጋር በማገናዘብ መርምረናል ተጠሪው በአመልካቹ ድርጅት ውስጥ የሥራ ሆሮ ሲሠራ የነበረ በመሆኑ የአመልካችና የተጠሪው የሥራ ክርክር የሚዳኘው በፍትሐብሔር ሕጉ በአንቀጽ ሠራ አገልግሎትን መስጠት ስለሚመለከቱ ውሉች ከቁጥር እና ተከታታይዎቹ በተደነገጉት ሕጐች መሠረት ነው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የአሠሪን የሥራ ውል ስለማቋረጥ እንጂ አሠሪን ከሥራ ስለማገድ በፍብሔር ሕጉ የተቀመጠ ድንጋጌ የለም ካለ በጊላ በፍሕግ ቁጥር መሠረት አመልካቹ ተጠሪውን ከሥራና ከደመወዝ አግዶ ለቐፃመባቸው ወራቶች ደመወዙን ይክፈለው ሲል ወስኗል በመሠረቱ ከፍሕግ ቁጥር ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የሚቻለው ደመወዝ ለተሠራ ሥራ ብቻ የሚከፈል እንጂ ላልተሠራ ሥራ የሚከፈል አይደለም የፍብሔር ሕግ ቁጥር ይህንኑ የሕጉን መርህ በመከተል ሥራ ላልተሠራባቸው ጊዜያት ወይም ቀናት ሠራተኛው ደመወዝ ለማግኘት መብት የለውም በማለት ግልጽ ድንጋጌ አስፍሮ ይገኛል ይሁንና የፍሕግ ቁጥር ሠራተኛው አንድም የሥራ አገልግሎት ባይሠጥም እንኳን ይኸው ሁኔታ አሠሪው የሥራ ሣይሠጠው በመቅረቡ ወይም እንዳይሠራ በመከልከሉ የተነሣ የሆነ አንደሆነ ደመወዙን ለማግኘት መብት አለው ሲል ሠራተኛው የሥራ ውሉ ባልታገደበት ወይም ባልተቋረጠበት ጊዜ ሥራ ላይ ሆኖ ነገር ግን አሠሪው ሥራ ሣይሠጠው ወይም እንዳይሠራ በከለከለው ጊዜ የሚያገለግል እንጂ ሠራተኛው ከሥራና ከደመወዝ ታግዶ የሥራ አገልግሎት ላልሠጣባቸው ጊዜያት ደመወዝ እንዲከፈለው የሚፈቅድ ድንጋጌ አይደለም ስለሆነ የሥር ፍቤቶች ውሣኔ ብቻ ብለው በተመለከቱት የፍብፄር ድንጋጌዎች አተረጓጐም ረገድ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመባቸው በመሆኑ ሊሻሩ ይገባል ብለናል ሙሣኒ የፌከፍፍቤት በመቁጥር በ የሠጠው ውሣኔ እና የፌመደፍቤት በመቁ በ የሠጠው ውሣኔ በፍሥሥሕቁ መሠረት የተሻሩ ስለሆነ የውሣኔው ግልባጭ ለሥር ፍቤቶች ይድረሳቸው መዝገቡ ተዘግቷል ለመቤት ይመለስ ዴጄ ፖፖሥሠ ዕ ፇ ፀ ዔም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ አቶ መስፍን እቁበዮናስ አመልካች አርሲ እርሻ ልማት ድርጅት ቃሲም ፈጂስ ቀረበ ተጠሪ አቶ ሰለሞን አበቡ አልቀረበም ዖይነራ ረረ ዕፅ ማኔሯመታ ፅዓሳ ያሆነ ዕው ይነራ ዕፖ ፅ ዕራ ዕያ ኋና መመኃኃ ያነ ፍዖሥ ኋና ማዕጋፇዖ ዖዩፍህ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአሁን ተጠሪን አመልካች ከስራ ያባረረው ህጉን ተከትሎ ባለመሆኑ የተቋረጠበት ጥቅማ ጥቅም ተከፍሎት ወደ ስራ ሊመለስ ይገባል በማለት በአርሲ ዞን ከፍቤት የተሠጠውን ውሳኔ በማዕናቱ የቀረበ አቤቱታ ሙስልኔ የአርሲ ዞን ከፍቤት የሰጠውና የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያጸናዉ ዉሳኔ ተሽሯራል ኛ በስራ አመራር ላይ ያሉ አባላት የስራ ውላቸው ቢቋረጥ የሚያገኙት መፍትሔ በአሠሪ ሠራተኛ አዋጅ የሚሸፈኑ ሠራተኞች ከሚያገኙት መፍትሔ የተለየ ነው ኛ በአመራር ላይ ያለው ሠው ያለበቂ ምክንያት ያለማስጠንቀቂያ ቢባረር የሶስት ወር ደመወዝ ካሳ ይሠጠዋል እንጂ ወደ ስራ ሊመለስ አይችልም ፖፖ ዕ ፇ ሀ ዔዓም ያጨዴ ያሪ ምቻዴ ሉዶ መረይፊዕይ ሥደያዕ ዖ ፉፍዕሪ ወረፇሠ ዶ ጎመፍልሥሮሮ መጋመድ ሠሪ ፅሰፍፉ ፍሙ ፇ መፅሰፉኃ ጳቋያያናዕ መጳሷካጳቻ ጸረሷ ኋረፓ ለማታ ድርጅ ሃ ቃሷም ፈደቋፅ ፇረያ ሃሃጋሪ ሉዖዶ ዕቋምፇ ለዕ ለሰልፇረም ፍርድ ይህ ክርክር የተጀመረው በኦርሜያ አርሲ ዞን ከፍተኛ ፍቤት ነው ክሱን የመሠረተው ተጠሪው ሲሆን አቤቱታውም በአጭሩ አመልካች በ ዓም የወጣውን የማኔጅመንት መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ በመተላለፍ ከስራ ያሰናበተኝ በመሆኑ የቀረብኝ ጥቅማ ጥቅም ተከፍሉኝ ወደ ስራ እንድመለስ ይወሰንልኝ የማል ነው ክሱ የቀረበለት ፍቤትም ግራ ቀ ን በጉዳዩ ከአከራከረ በኋላ የተጠሪ የስራ ስንብት ደንቡን ተከትሉ ያልተፈፀመ ስለሆነ የተቋረጠበት ጥቅማ ጥቅም ተከፍሉት ወደ ስራ ሊመለስ ይገባል በማለት ወስኗል ይህ ውሣኔም ጉዳዩን በይግባኝ ባየው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍቤት ፀንቷል በመቀጠል አቤቱታ የቀረበለት ይህ ችሎትም የግራ ቀዕን ክርክር መርምሯል አንድ የማኔጅመንት አባል የሆነ ሰው ከሥራ ቢሰናበት ስንብቱ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም በማለት ወደ ስራ እንዲመለስ መወሰንን ሕጉ ይፈቅደዋል። የሚለው ሆኖ አግኝቶታል የተያዘውን ጭብጥ ለመፍታት በቅድሚያ ጉዳዩ በአዋጅ ቁ አንቀጽ ስር ከተመለከቱት የይርጋ ደንቦች ውስጥ ከየትኛው ንዑስ አንቀጽ አግባብ ሊታይ እንደሚገባው መለየት ያስፈልጋል ከመዝገቡ መረዳት እንደሜቻለው አመልካቹ ተጠሪዋ በእጅዋ ከገባው ውስጥ ብር አጉድላ ለግል ጥቅምዋ ማዋሏ ተረጋግጧል ቢልም ይህን ምክንያት ጠቅሶ የስሪ አለማቋረጡን አልካደም ክርክሩ ተጠሪ በዚህ ጉዳይ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በሕግ የስራ ውሏ ተቋርጧል ሊሰኝ ይገባዋል የሜል ነው ይሁን እንጂ ይህ ሁኔታ በሁለቱ መካከል ያለው የስራ ግንፅነት በሕግ መቋረጡን ስለማያመለክት ውሉ አልተቋረጠም ሲል የስር ፍርድ ቤት የደረሰበት መደምደሚያ ሊነቀፍ የሜገባው አልሆነም የስራ ውሉ ያልተቋረጠ በመሆኑም ተጠሪ ወደ ስራ ልመለስ ይገባል ስትል ያቀረበችው የክሷ ነጥብም ሆነ የውሉ አበል ክፍያ ይገባኛል ስትል ያነሣችው ጥያቄ የይርጋ ዘመን አቆጣጠር በአዋጅ ቁ አንቀጽ ስር ከተመለከተው አጠቃላይ የይርጋ ደንብ ድንጋጌ አኳያ እንጂ በተለይ ከተደነገጉት ንዑስ አንቀጽ እና አግባብ ሊታይ የሚገባው አይደለም በሌላ በኩል ተጠሪ ከስራ እና ከደመወዝ ከኀዳር ቀን ዒም ጀምሮ ታግዳ የቆየች መሆኑን አልካደችም ይሁን እንጂ እስከ ግንቦት ቀን ዒም ድረስ ሒሣብ እያስመረመርኩ ስለሆነ ስራ ላይ እንደነበርኩ ሊቆጠርልኝ ይገባል በሚል አይነት ተከራክራለች ተጠሪ በሒሣብ ማስመርመር ተግባር ላይ መቆየቷ ግን መደበኛ ስራዋን ስታከናውን ነበር የሚያሰኛት ባለመሆኑ በዚህ ረገድ ያቀረበችው ክርክር አሣማኝነት ያለው ሆኖ አላገዕ ነውም ስለሆነም ተጠሪ ከስራና ከደመወዝ የታገደችበት እለት ኀዳር ቀን ዒዔም መሆኑን ይህ ችሉት ተቀብሉታል እንግዲህ ከፍ ሲል እንደመለከተው ተጠሪ የስራ ውሏ መቃረጥ በአመልካቹ ባይገለጽላትም ከኀዳር ቀን ዓም ጀምሮ ከስራና ከደመወዝ መታገድዋ ግን ተረጋግጧል አንድ ሰራተኛ ከዘጠና ቀናት በላይ ከስራና ከደመወዝ ሊታገድ እንደማይችል ደግሞ ከአዋጅ ቁ አንቀጽ መንፈስ መገንዘብ ይቻላል ስለሆነም ተጠሪ ሕጉ ለእግድ የፈቀደው ጊዜ እንደአበቃ ይገባኛል የምትለው ነገር በአመልካቹ ካልተደረገላት መብቷን ክስ መስርታ ትጠይቅ ዘንድ ይገባል ክሷን የምትመሰርተውም በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት ጥያቄዋን ልታቀርብ ከምትችልበት ማለትም የእግዱ ጊዜ ከማደበቃበት ከየካቲት ቀን ዓም ጀምሮ በአንድ ዓመት ውስጥ ማለትም እስከ የካቲት ቀን ዓም ድረስ ብቻ እንዲሆን ያስፈልጋል አመልካች ግን ክሷን የመሠረተችው ጥቅምት ቀን ዓም በመሆኑ ክሱ የተጠቀሰውን የአንድ ዓመት የይርጋ ጊዜ አሳልፎ የቀረበ መሆኑ ተረጋግጧል ውሣኔ ኛ ተጠሪ በአመልካች ላይ የመሠረተችው ክስ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት በይርጋ ሊታገድ ይገባዋል ኛ የዓለም ገና ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ ጉዳዩ በይርጋ ይታገዳል ሲል የሰጠው ውሣኔ ፀንቶ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍቤት እና ደኦርሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት እንደቅደም ተከተላቸው በመቁ እና ተጠሪ ውዝፍ ደመወዝ ተከፍሏት ወደ ሥራ እንድትመለስ የሰጡት ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽሯል ያመ ታሀኃዕ ዐ ፇፇ ፍም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ ዓብዱልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ ወሮ ሆሳዕና ነጋሽ አመልካች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን መልስ ሰጭዎች እነ አቶ አንለይ ያየህ ሰዎች ኃቋ ሰራ ረረ ይፀረ ሄና ያራ ጂሽጭ ቀድሟዶ ያመታፖ ምሥራ ዕፅሪሟፇሪሃያፖ ያረይ ለፇማሟመጠረ ይፀር ይ መቋረም ደይፀር መያታፖ ዕሐመፖው ኃፊዕታ ዖያታዕጠው ሰሳኋማጋ ፅዕጎፅው ፅሰማጋ ያጎሰሐሪና ኃራፉሦኛ ሦዳፀ ለሐዎሯ ቋማረ ፇጽ ሪያፖ«ያ ዖሦዕወው ዖያፇ ሦረፇም ይጎሳዎጆ ፈዴሪ ያመጃ ያወጣው ዎሯ ዌጋፖጋ ድኗጋሥቻም ፈፃሜቀታፖ ኃውወ መሰጭዎች በጌዶነቀምት እና ጊምቢ ባከናወነው የትራንስሚሽን መስመር መዘርጋት ስራ ለተሳተፉት ሌሎች ሰራተኞች አመልካች መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው የሁለት ፅርከን ጭማሪ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ነሐሴ ቀን ዓም ለአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ባቀረቡት ክስ ክሱ በይርጋ ሊታገድ ይገባዋል በማለት አመልካች ያቀረበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ቦርድ ውድቅ በማድረግ በፍሬ ነገሩ ውሳኔ በመስጠቱና ውሳኔውም በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመጽናቱ የቀረበ አቤቱታ ውሳኔ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዩ ወሳኝ ቦርድ የሰጠውና የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ያጸናው ውሳኔ ተሽራል በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት የደመወዝ የትርፍ ሰዓትና የሌሎች ክፍያዎች ጥያቄ ሊጠየቅ ይገባው ነበር ከሚሰኝበት ጊዜ ጀምር የስራ ውሉ ተቋርጦ ቢሆን እንኳን ይህን ከግምት ሳያስገባ እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል የሰራተኛው ወይም የአሰሪው ጥያቄ በተተኪዎቻቸው ወይም በወራሾቻቸው በሚቀርብበት ጊዜ በአዋጅ ቁ አንቀጽ እና በተደረጉ የይርጋ ድን ይመራል የሰራተኛው ወይም የአሰሪው ተተኪዎች ወይም ወራሾች የሰራተ ይም የአሰሪውን ሳይሆን የራሳቸውን መብት መሰረት በማድረግ የሚያቀርቡት ጥያቄ በአዋጅ ቁ አንቀጽ እና በተደነገጉት ሳይሆን በአንቀጽ በተደነገገው የይርጋ ድንጋጌ ይመራል በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት የይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚቋረጠው ክሱ በአዋጅ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን በተሰጠው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ወይም በፍርድ ቤቶች በተቋቋሙ የስራ ክርክር ችሎቶች የቀረበ እንደሆነ ነው ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ባልተሰጠው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ወይም በስራ ክርክር ችሎት የቀረበ ክስ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት የይርጋ ጊዜን መቆጠር አያቋርጥም በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት የይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚቋረጠው አቤቱታው የቀረበው ለሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የቀረበ እንደሆን ብቻ ነው ለአሰሪ የቀረበ አቤቱታ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት የይርጋ ጊዜ መቆጠርን አያቋርጥም በአዋጅ ቁ አንቀጽ ከፍትሐብፄር ህግ ቁጥር ጋር ተገናዝቦ መታየት አለበት ሰራተኛ ወይም አሰሪ በአዋጅ ቁ አንቀጽ ለመጠቀም በድንጋጌው የተመለከቱት ሁኔታዎች መከሰታቸውን እና ክሱ በይርጋ የሚታገድበት ከመድረሱ በፊት ያልቀረበው በድንጋጌው ከተመለከቱት ሁኔዎች ቢያንስ በአንዱ መከሰት ምክንያት መሆኑን በማስረጃ ማረጋገጥ አለበት የመቁ ታህሣስ ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወሮ ስንዱ ዓለሙ ወሮ ሆሳዕና ነጋሽ አመልካች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን አልቀረበም ተጠሪዎች እነ አቶ አንለይ ያየህ ሰዎች ጠበቃ ብዙአለም መርሻ ቀረበ ፍርድ ይህ ክርክር አሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ዘንድ የተጀመረ ነው ተጠሪዎች ለቦርዱ ነሐሴ ቀን ዓም በተፃፈ ማመልከቻ ያቀረቡት ክስ ተከሣሽ አመልካች በጌዶ ነቀምት እና ጊምቢ በአከናወነው የትራስሚሽን መስመር መዘርጋት ሥራ ላይ በተለያየ የሥራ መደብ አገልግሎት ሰጥተናል ይሁን እንጂ አመልካች በዚህ ሥራ ላይ ለተሳተፉት ሠራተኞች በመሉ በመንግስት ትፅዛዝ መሠረት ከመጋቢት ቀን ዓም ጀምሮ የሁለት እርከን ጭማሪ ሲያደርግ እኛን ግን ከልክሎናልና ለእኛም ይህን ጭማሪ ከሞራል ካሣ እና ከወጭና ኪሣራችን ጋር ሊከፍለን ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል አመልካችም ለቀረበበት ክስ የተጠየቀው የአርከን ጭማሪ ክፍያ ለሌሎች ሠራተኞች ከተፈፀመበት ከመጋቢት ቀን ዓም ጀምሮ ክሱ እስከቀረበበት እስከ ነሐሴ ቀን ዓም ድረስ ያለው ጊዜ ከአስራ ሰባት ወር በላይ በመሆኑ ክሱ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት በይርጋ ሊታገድ ይገባዋል ሲል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወማያ አቅርቧል በአማራጭም መልሱን ሰጥቶ ተከራክሯል ክርክሩ የቀረበለት ቦርድም የከሣሽና የተከሣሽ የሥራ ግንኙነት ቀጣይነት ያለው በመሆኑ በክሱ የቀረበው ጥያቄ በይርጋ የሚታገድ አይደለም በማለት የአመልካችን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ውድቅ አድርጎታል ወደ ጉዳዩ ፍሬ ነገር በመግባትም ከከሣሾቹ ውስጥ ከፊሎቹ ብቻ የአንድ አርከን ጭማሪ እንዲሰጣቸው እና ይኸውም ከመጋቢት ቀን ዓም ጀምሮ ተስተካክሉ እንዲከፈላቸው ወስኗል ከዚህ ውሣኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ፍርዱ ጉድለት የለበትም በማለት የይግባኙን መዝገብ ዘግቶታል በመቀጠል አመልካች ከአስራ ሰባት ወራት በላ የቀረበው የተጠሪዎች ክስ በይርጋ አይታገድም በሚል በመወሰኑ ሕግ ተጥሷል እንዲሁም በዋናው ጉዳይ የተሰጠው ውሣኔ የተሳሳተ ፍሬ ነገርን መሰረት ያደረገ ስለሆነ ሊሻርልን ይገባል ሲል አቤቱታውን ለዚህ ችሎት አቅርቧል ተጠሪዎችም በጠበቃቸው አማካኝነት በአቀረቡት መልስ መጋቢት ቀን ዓም የእርከኑ ጭማሪ አንደሚሰጥ ውሣኔው ለሠራተኞቹ ይፋ የሆነበት ቀን እንጁ ክፍያው የተፈፀመበት ቀን አይደለም ይሁን እንጂ ሌሎቹ ሠራተኞች የካቲት ቀን ዓም የእርከኑ ጭማሪ ተጠቃሚዎች መሆናቸው ሲገለጽላቸው ይህ ለተጠሪዎቹ ሳይደረግ በመቅረቱ ተጠሪዎቹ ይህን እንደአወቁ የካቲት ቀን ዓም አቤቱታቸውን ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቅርበዋል ለዚህ አቤቱታ በዕሁፍ ምላሽ ያላገኙ ስለሆነም የይርጋው ጊዜ ተቋርጧል የሚልና በጥቅሉም ፍርዱ እንዲፀና የሚጠይቅ መልስ አቅርበዋል ችሎቱም በዚህ ጉዳይ ሊታይ የሚገባው ነጥብ በተጠሪዎች የቀረበው ክስ በይርጋ ሊታገድ ይገባዋል። የሚለው ሆኖ አግኝቶታል ሕግ የተለያዩ ጉዳዮች እንደየሁኔታው አግባብነት ላለው አካል ቀርበው የሚታዩበትን የተለያየ የጊዜ ገደብ አስቀምጦ ይገኛል በዚህም ምክንያት አንድን ጉዳይ ለአንድ አካል አቅርቦ አንዲታይ ለማድረግ ጉዳዩ በሕግ የተፈቀደለትን የጊዜ ገደብ ጠብቆ የቀረበ እንዲሆን ያስፈልጋል በሕግ የተወሰነለትን ጊዜ አሳልፎ የቀረበ ጉዳይ ወደ ፍሬ ነገሩ ተገብቶ የመታየትን አድል ሳያገኝ ከወዲሁ ውድቅ ሊደረግ ወይም በይርጋ ሊታገድ ይችላል ከላይ እንደተጠቀሰው በግራ ቀኙ የቀረበው ሙግት የሥራ ክርክርን የሚመለከት ነው ለክርክሩ አግባብነት ያለው ሕግም የአዋጅ ቁጥር ነው ይህ የአዋጅ ቁ በክፍል አስር ምዕራፍ አንድ ከአንቀጽ በሚገኙት ሕጎች ስር ስለ ይርጋ ደንብ ደንግጓል የአዋጅ ቁ ን የሻረው የአዋጅ ቁ ም በተመሳሳይ የሕጉ ክፍል በተመሳሳይ የሕጉ ምዕራፍ እና በይዘታቸው ጭምር አንድ አይነት በሆኑ አንቀጾች ስር የይርጋ ደንብን አስቀምጧል በእርግጥ ለዚህ ለያዝነው ጉዳይ ተፈፃሚነት ያለው የአዋጅ ቁ ነውና ለጭብጣችን ምላሽ ለመስጠት እንድንችል በዚህ ውሣኔያችን ውስጥ እንደአግባብነታቸው ይህ አዋጅ ያስቀመጣቸው የይርጋ ደንቦች በዋነኛነት የሚጠቀሱ ይሆናል ይሁን እንጂ እነዚህ ሁለት ሕጎች አንድ አይነት አንቀጾች የያዙ በመሆናቸው በዚህ ውሣኔ ውስጥ ለአዋጅ ቁ የይርጋ ደንብ ድንጋጌዎች የሚሰጠው ትርጓሜ በአዋጅ ቁ ለሚገኙትም ተፈፃሚነት ይኖረዋል የአዋጅ ቁ የመብት ጥያቄዎች ስለሚቀርቡበት የጊዜ ገደብ በአንቀጽ ላይ ደንግጓል ከመነሻው የተጠቀሰው አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ በዚህም ሆነ በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ከአልተወሰነ በስተቀር ጉዳዩን ማቅረብ ከሚቻልበት ቀን አንስቶ እስከ አንድ ዓመት ድረስ ከአልቀረበ የመብቱ ጥያቄ በይርጋ እንደሚታገድ አመልክቷል ይህ ድንጋጌ የጉዳዩ የይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ጉዳዩን ለማቅረብ ከሚቻልበት ጊዜ አንስቶ መሆኑን ይጠቅሳል እንዲሁም በሕግ የተለየ የጊዜ ገደብ ያልተደረለት ጉዳይ ሁሉ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ እንደሚገባው በመደንገግ አጠቃላይ የሆነ የጊዜ ወሰን አስቀምጧል በተጨማሪም ይኸው የአዋጅ ቁ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ እና ላይ ሕጉ የተለየ የይርጋ ጊዜ የወሰነላቸውን የአቤቱታ አይነቶች ለይቶ አመላክቷል የአዋጅ ቁ አንቀጽ የተለየ የይርጋ ጊዜ ከወሰነላቸው የመብት ጥያቄዎች ውስጥ የመጀመሪያው የሆነው አንቀጽ ሠራተኛው የሥራ ውሉ ከሕግ ውጭ ተቋርጦብኛል በማለት ወደ ሥራው ለመመለስ የሚያቀርበው ክስ ውሉ በተቋረጠ በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል በማለት ደንግጓል በሌላ በኩልም የሥራ ውልን መቋረጥ ምክንያት አድርጎ ሠራተኛ ሪው ላይ አሊያም አሰሪው በሠራተኛው ላይ የሚያነሳው የክፍያ ጥያቄ የሥራ ውሉ በተቋረጠ በስድየ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ እንደሚታገድ በዚሁ አንቀጽ ላይ ተደንግጓል በግልጽ እንደሚታየው የመጀመሪያው ድንጋጌ የሥራ ውሉን መቋረጥ ሕጋዊነት በመቃወም ወደ ሥራዬ ልመለስ ይገባል የሚል ሠራተኛ ይህን ጥያቄውን ለማቅረብ የሦስት ወር ጊዜ ብቻ እንዳለው ያስገነዝባል ሁለተኛው ድንጋጌ ደግሞ የሥራ ውልን መቋረጥ መነሻ አድርገው የሚቀርቡ ማናቸውም አይነት የክፈያ ጥያቄዎች በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ የተገደቡ መሆናቸውን ያመላክታል በተጨማሪም ከእነዚህ ሁለት ድንጋጌዎች አቤቱታ አቅራቢው የሥራ ውሉ ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ በመብቱ መጠቀም የሚችል መሆኑን መረዳት ይቻላል እንደሚታወቀው ወደ ሥራ ልመለስ ይገባል የሚል ክስ በሠራተኛው በእራሱ እንጂ በተተኪዎቹ ወይም በወራሾቹ ሊመሰረት የሚችል አይደለም ይሁን እንጂ ከሥራ ውል መቋረጥ በኋላ ሠራተኛውም ሆነ አሰሪው አንዱ ከሌላው ወገን ሊጠይቋቸው የሚችሏቸው የክፍያ አይነቶች በተተኪዎቻቸው ወይም በወራሾቻቸው ሊጠየቁ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል የሚታመን ነው እንዲህ በሚሆን ጊዜ ተተኪዎቹ ወይም ወራሾቹ መሰረት አድርገው የሚቀርቡት የአራሳቸውን ሳይሆን የአውራሻቸውን ሠራተኛ ወይም አሰሪ መብት ነውና በይርጋው ጊዜ አቆጣጠር ላይ የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም ስለሆነም የሠራተኛውን ወይም የአሰሪውን መብት ተክተው በወራሾቻቸው ወይም በተተኪዎቻቸው የሚቀርቡ የክፍያ ጥያቄዎች የሥራ ውሉ ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ በስድስት ወራት ውስጥ ካልቀረቡ በይርጋ ሊታገዱ ይገባል ሌላው የአዋጅ ቁ አንቀጽ የተለየ የይርጋ ጊዜ የወሰነለት የአቤቱታ አይነት በአንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ላይ ተመልክቷል ይኸውም ሠራተኛው የሚያቀርበው የደመወዝ የትርፍ ሰዓትና የሌሎች ክፍያዎች ጥያቄ መጠየቅ ከሚገባው ጊዜ ጀምሮ እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ መቅረብ እንደሚገባውና ይኸ ካልሆነ በይርጋ አንደሚታገድ ተደንግጓል ከድንጋጌው መረዳት እንደሚቻለው ይህን አንቀጽ ተመስርቶ የሚቀርብ የመብት ጥያቄ በአሰሪውና በሠራተኛው መካከል የተፈፀመው የሥራ ውል ፀንቶ በአለበት ሁኔታ ሠራተኛው ከአሰሪው የሚጠይቀውን ክፍያ የሚመለከት እንጂ የግድ የሥራ ውሉን መቋረጥ ተከትሎ የሚነሳ አይደለም በተጨማሪም የስድስት ወሩ የይርጋ ጊዜ እንደሁኔታው ክፍያው ሊጠየቅ ይገባ ነበር የሚሰኝበትን አለት ተመስርቶ መቀጠር የሚጀምር እንጂ ውስን የመነሻ ጊዜ የተቀመጠለት አይደለም ይኸ አንቀጽ ሠራተኛው አሰሪውን ደመወዝ የትርፍ ሰዓትና ሌሎችም ክፍያዎችን ሊጠይቅ የሚችልበትን ውስን ጊዜ ያስቀመጠ ቢሆንም የሥራ ውልን መቋረጥ ለይርጋው ጊዜ አቆጣጠር እንደመነሻ ባለመውሰዱ ከአንቀጽ እና ይለያል ይርጋውም ሠራተኛው የተጠቀሱትን ክፍያዎች ሊጠይቅ ይገባው ነበር ከሚሰኝበት ጊዜ ይነሳና ምናልባትም የሥራ ውሉ ተቋርጦ እንኳ ቢሆን ይኸን ከግምት ውስጥ ሳያስገባ እስከ ስድስት ወር ድረስ መቆጠሩ ይቀጥላል እንዲሁም እነዚህ ክፍያዎች በሠራ ይሆን በተተኪዎቹ ወይም በወራሾቹ ሊቀርብ የሚችልበት ሁኔታ ይኖራል እንዲህ በሚሆን ጊዜም ጥያቄው የሠራተኛውን መብት ተመስርቶ የሚቀርብ ነውና ልክ እንደቀድሞው ሁሉ በይርጋው ጊዜ አቆጣጠር ላይ የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም ስለሆነም ተተኪዎች ወይም ወራሾች የተጠቀሱትን ክፍያዎች ሠራተኛው ሊጠይቅ ይገባው ነበር ከሚባልበት ጊዜ አንስቶ እስከ ስድስት ወር ድረስ ካልጠየቁ በቀር ክሳቸው በይርጋ የሚታገድ ይሆናል እንግዲህ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት አንድ የሥራ ክርክር ጉዳይ የተለየ የይርጋ ጊዜ የተቀመጠላቸውን የመብት ጥያቄዎች የሚመለከት ከሆነ ከንዑስ አንቀጽ እስከ የተጠቀሱትን የሦስት ወይም የስድስት ወራት የጊዜ ገደብ አክብሮ የቀረበ ሊሆን ይገባዋል በእነዚህ ድንጋጌዎች ሥር የማይሸፈን ከሆነ ደግሞ በንዑስ አንቀጽ በተመለከተውና በአንፃሩም ሰፊ በሆነው የአንድ ዓመት የጊዜ ወሰን ውስጥ እንዲቀርብ ያስፈልጋል በሌላ በኩል ደግሞ ይህ የይርጋ ጊዜ የተወሰነበት የአዋጅ ቁ አንቀጽ ሠራተኛውና አሰሪው አንዱ ከሌላቸው የመብት ጥያቄዎችን የሚያቀርቡበትን ሁኔታ ብቻ በመጥቀስ የተደነገገ መሆኑን ከአንቀጾቹ መገንዘብ ይቻላል ይሁን እንጂ የሠራተኛው ወይም የአሰሪው ጥያቄ በተተኪዎቻቸው ወይም በወራሾቻቸው በሚቀርብበት ጊዜም የይርጋው አቆጣጠር ሊለወጥ እንደማይገባ ከላይ ተመልክቷል በአርግጥ የሠራተኛውም ሆነ የአሰሪው ተተኪዎች ወይም ወራሾች የሠራተኛውን ወይም የአሰሪውን ሳይሆን የአራሳቸውን መብት መሠረት አድርገው አንዳቸው ከሌላቸው ክፍያ ሊጠይቁ የሚችሉበት ሁኔታ ይኖራል እንዲህ በሚሆን ጊዜ ግን የይርጋው አቆጣጠር ከአዋጅ ቁ አንቀጽ ወይም አኳያ ሳይሆን አጠቃላይ የይርጋ ደንብ ድንጋጌ ከሆነው ከአንቀጽ አግባብ መታየት ይገባዋል ስለሆነም የተጠቀሱት ሰዎች በአራሳቸው መብት ላይ ተመስርተው የሚያቀርቡት ክስ በሌላ ሕግ ላይ በሌላ የይርጋ ደንብ ካልተሸፈነ በቀር በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት የመብታቸውን ጥያቄ ሊያቀርቡ ከሚችሉበት ጊዜ አንስቶ እስከ አንድ አመት ድረስ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል ከፍ ሲል እንደተመለከተው የአዋጅ ቁ አንቀጽ አንድ የሥራ ክርክር ጉዳይ ሊቀርብ የሚችልበትን የጊዜ ወሰን አስቀምጧል በሌላ በኩል ደግሞ አንድ ጉዳይ በሕግ የተወሰነለትን የጊዜ ወሰን ጠብቆ ባይቀርብም እንኳን ሊታይ የሚችልባቸው ሦስት ሁኔታዎች እንዳሉ ደንግጓል እነዚህም ሁኔታዎች ከአንቀጽ እስከ አንቀጽ ባሉት ድንጋጌዎች ላይ ተጠቅሰው የሚገኙ ሲሆን እነርሱም የይርጋ ጊዜ መቋረጥ የይርጋ መብትን መተው እአና ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ጊዜው ያለፈበትን ክስ መቀበል መሆናቸው በእነዚሁ ድንጋጌዎች ላይ ተመልክቶ ይገኛል ስለ ይርጋ ጊዜ መቋረጥ ከፍ ሲል እንደተመለከተው የመጀመሪያው ሁኔታ የይርጋ ጌዜ መቋረጥን ይመለከታል ይህ ሁኔታ የተደነገገበት የአዋጅ ቁ አንቀጽ የይርጋ ጊዜ የሥራ ክርክርን ለሚወሰን ባለስልጣን ክስ ቀርቦ የመጨረሻ ውሣኔ አስኪሰጥበት ቀን ድረስ የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅን በሥራ ላይ ለማዋልና ለማስፈጸም ኃላፊነት ለተሰጠው ባለስልጣን አቤቱታ ቀርቦ የመጨረሻ ውሣኔ በጽሁፍ እስኪሰጥበት ቀን ድረስ በይርጋው ጊዜ ተጠያቂ የሆነው ወገን የሌላውን መብት በጽሁፍ ሲያውቅለት ወይም በከፊል ሲፈጽምለት ሊቋረጥ አንደሚችል ደንግጓል በመሰረቱ አንድ ወገን ተከራካሪ በሌላው ላይ ክስ መስርቶ የመገኘቱ ጉዳይ ተጀምሮ የነበረን የይርጋ ጊዜ አቆጣጠር እንደሚያቋርጠው በፍብሕቁ ለ ላይ ተመልክቷል ለሥራ ክርክር ጉዳይ ተፈፃሚነት ያለው የአዋጅ ቁ ም ከዚህ የፍትሐብሔር ሕግ ጋር በተስማማ ሁኔታ ክስ አቅርቦ የመገኘት ነገር የይርጋን ጊዜ አቆጣጠር እንደሚያቋርጥ በአንቀጽ ላይ ጠቅሶታል የይርጋውን አቆጣጠር የሚያቋርጠው ክስ የተመሰረተውም የሥራ ክርክርን ከሚወስን ባለስልጣን ዘንድ ሊሆን እንደሚገባ በንዑስ አንቀጹ በግልጽ ተደንግጓል ይሁን እንጂ ይህ ድንጋጌ የሥራ ክርክርን እንዲወስን ኃላፊነት ለተሰጠው ባለስልጣን ሲል ማንን ለማለት ነው። ለሚለው ነጥብ ምላሽ ለማግኘት ድንጋጌውን መተርጎም ይገባናል በቅድሚያ ሁለተኛውን ጥያቄ እናያለን በመሰረቱ ከሕግ አግባብ ውሣኔ ሊባል የሚገባው ምን ዓይነት ውሣኔ እንደሆነ ከፍ ሲል ተገልዷል ውሣኔ ሊሰጡ የሚችሉት የሥራ ክርክርን ለመዳኘት ስልጣን ያላቸው አካላት ብቻ መሆናቸውንም በችሎት ከተሰጠው ትርጓሜ መገንዘብ ይቻላል ስለሆነም አዋጁን ለማስፈፀም ስልጣን በአለው አካል የሚሰጥ ውሣኔ የአስተዳደር ውሣኔ ሊባል ከሚችል በቀር በሕጉ አግባብ በዳኝነቱ አካል እንደተሰጠ ውሣኔ የሚቀጠር አይደለም ወደ መጀመሪያው ጥያቄ ስንመለስ ጉዳዩን የሠራተኛና የማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ወይም የክልሎች የሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ በሕጉ ከተሰጠው ስልጣን አኳያ መመርመሩ ተገቢነት ይኖረዋል ይህ ሚኒስቴር በርካታ ተግባሮችን እንዲያከናውን በአዋጅ ቁ ስልጣን የተሰጠው ሲሆን ጥቂቶቹ አንደሚከተለው ተጠቅሰዋል ከአዋጁ አንቀጽ ብንጀምር ይህ ሚኒስቴር በዚህ ድንጋጌ መሠረት የማሕበራትን ምዝገባ ሊከለክል ይችላል በአንቀጽ እና መሠረት የማሕበራትን የመመዝገቢያ የምስክር ወረቀት በመሰረዝ ለፍርድ ቤት ይግባኝ ሊቀርብበት የሚችል ውሣኔ ሊያሳልፍ ይችላል በአንቀጽ መሰረት ሠራተኛን ከሥራ ለማገድ የተሰጠ ምክንያት በቂ በመሆን አለመሆኑ ጉዳይ ላይ ውሣኔ ይሰጣል ከዚህ የሚኒስቴሩ ውሣኔ ላይ ይግባኝ ለፍርድ ቤት ሊቀርብ አንደሚችል ደግሞ በአዋጅ ቁ አንቀጽ ላይ ተመልክቷል በተጨማሪም ሚኒስቴሩ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት ፍርድ ቤት ዘንድ ተገቢ ብዛት ያላቸው የሥራ ክርክር ችሎቶች ይቋቋሙ ዘንድ ለተገቢው አካል ጥያቄ ለማቅረብ ይችላል በአሰሪውና በሠራተኛው መካከል የወል የሥራ ክርክር ሲነሳ በንቀጽ መሠረት ጉዳዩን በማስማማት ለመጨረስ አስማሚ ይመድባል እንደዚሁም በአንቀጽ መሠረት ስለ ሥራ ሁኔታ ቁጥጥር የሚያደርጉ የሥራ ሁኔታ ተቆጣጣሪዎችን ይመድባል እነዚህ ከሞላ ጎደል የተጠቀሱት በሕጉ የተፈቀዱት የሚኒስቴሩ ተግባራት ሚኒስቴሩ በአሰሪና ሠራተኛው ግንኙነት ላይ ከፍተኛ የሆነ የአፈፃፀም ኃላፊነት እንዳለበት ያረጋግጡልናል ሌላ ከሚኒስቴሩ የተስተካከለ የአስፈፃሚነት ኃላፊነት የተሰጠው አካል አለመኖሩንም ከአዋጁ መረዳት ይቻላል ይልቁንም ሚኒስቴሩ በአዋጁ አንቀጽ ላይ ሕጉን ለማስፈፀም ይችል ዘንድ በበርካታ ጉዳዮች ላይ መመሪያ የማውጣት ስልጣን አንደተሰጠው ተመልክቷል ይህም ሚኒስቴሩ የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ሕግን በሥራ ላይ ለማዋልና ለማስፈጸም በአዋጁ ስልጣን የተሰጠው ብቸኛ አካል መሆኑን ያስገነዝበናል ለዚህ አካል በስሩ እንዲመድባቸው ስልጣን ለተሰጠው ተቋማት ጭምር በአዋጁ እንዲያከናውናቸው ስልጣን በአገኘበት ተግባራት ረገድ አቤቱታ አቅርቦ መገኘትም በአንቀጽ መሠረት የይርጋውን ዘመን አቆጣጠር የሚያቋርጠው ይሆናል የመጨረሻው ለይርጋ ጊዜ መቋረጥ ምክንያት የሚሆነው በአንቀጽ ላይ እንደተመለከተው በይርጋው ጊዜ ማለፍ ተጠቃሚ የሆነው ወገን ያልሆነውን ወገን መብት በቃል ሳይሆን በጽሁፍ ሲያውቅለት አሊያም መብቱን በከፊል ፈጽሞለት ሲገኝ ነው ይሁን እንጂ ይህ ምክንያት የይርጋውን አቆጣጠር ከሦስት ጊዜ በላይ ሊያቋርጠው አንደማይችል በዚሁ ድንጋጌ ላይ የተመለከተ ነው በአርግጥ የአዋጅ ቁ አንቀጽ ሦስት አይነት የይርጋ ማቋረጫ ምክንያቶች ያስቀመጠ ቢሆንም የይርጋው መቋረጥ በይርጋ ዘመኑ አቆጣጠር ላይ ያለውን ውጤት ግን አላመለከተም በመሆኑም የይርጋ ጊዜ መቋረጥ ምን ውጤት እንደሚያስከትል ለማወቅ አግባብነት ያለውን የፍብሕቁ ን ከጉዳዩ ጋር አገናዝቦ መመልከት ያስፈልጋል ይህ አንቀጽ አንድ የይርጋ ዘመን ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ አንደገና አዲስ የይርጋ ዘመን ሊቀጠር አንደሚገባ ደንግጓል ይህም ይርጋው ከመቋረጡ በፊት ተቆጥረው የነበሩት ቀናት እንዳለ ቀሪ እንደሚሆኑና የይርጋው ጊዜ እንደገና እንደ አዲስ ተብሎ ሊቆጠር እንደሚገባ ያስገነዝበናል በመሆኑም በአዋጅ ቁ አንቀጽ በተመለከቱት ሁኔታዎች ሳቢያ አንድ የይርጋ ጊዜ መቋረጡ ቢረጋገጥ ቀጣዩ የይርጋ ዘመን ይኸን ከፍ ሲል የተጠቀሰውን በፍብሕቁ የተመለከተውን አቆጣጠር ይከተል ዘንድ ያስፈልጋል በመሰረቱ አንድ የሥራ ክርክር ክስ የቀረበበት ወገን ክሱ የይርጋ ጊዜው ያለፈበት ነው ሲል ቢቃወም በአርግጥ ክሱ ጊዜው ያለፈበት ነው። የሚለው ነጥብ የጉዳዩ ጭብጥ ሆኖ እንደሚያዝ ይታመናል ለዚህ ጭብጥ መመስረት ምክንያት የሆነው ክርክር የቀረበው በተከሣሹ በመሆኑም የይርጋውን ጊዜ ማለፍ ያስረዳ ዘንድ ይገባዋል በሌላ በኩል ደግሞ ክሱን ያቀረበው ወገን የይርጋው ጊዜ ተቋርጧል የሚል ክርክር የሚያነሳ ቢሆን ይህን ሙግቱን በቅድሚያ ያስረዳ ዘንድ ይጠበቅበታል በተጨማሪም የሥራ ክርክር ጉዳይ የቀረበለት ፍርድ ቤት ከሣሹ አስቀድሞ በአዋጅ ቁ መሠረት ጉዳዩን ለመዳኘት ስልጣን ለተሰጠው ፍርድ ቤት ወይም የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ማቅረቡን ከአረጋገጠ በአዋጁ አንቀጽ መሠረት የይርጋውን ዘመን መቋረጥ ሊቀበለው ይገባል ከተጠቀሰው የሕጉ መስፈርት ውጭ የሆኑ ምክንያቶችን ለውሣኔው መሠረት ሊያደርግ አይችልም ለምሳሌ ያህል ክሱ ሊቀርብ የሚገባው ለሥራ ክርክር ችሎቱ ነበር በሚልና በመሳሰለ ምክንያት የይርጋውን አቆጣጠር መቋረጥ አልቀበልም ሊል አይችልም በሌላ በኩል ደግሞ የአሰሪና ሠራተኛ አዋጅን ለማስፈፀም ስልጣን የተሰጠው ሚኒስቴሩ ብቻ መሆኑ ከላይ ተመልክቷል ስለሆነም ክርክሩ የቀረበለት ፍርድ ቤት ከሣሹ ለዚህ ሜኒስቴር በስሩ ለሚመድባቸው ተቋማት ጨምሮርሃበስልጣኑ ክልል አቤቱታ አቅርቦ እንደነበር ከአረጋገጠ የይርጋውን ዘመን በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት ሊያቋርጠው ይገባል ከዚህ ውጭ ለሆነ አካል አቤቱታ መቅረቡ መረጋገጡ ግን የይርጋውን ጊዜ አቆጣጠር የሚያቋርጠው አይሆንም ለምሳሌ ያህል አንድ ከሣሽ ሠራተኛ ለአሰሪው መቤት አቤቱታ አቅርቤ ውጤቱን ስጠባበቅ ነበር ሲል መከራከሩንና ይህንንም ማረጋገጡን ፍርድ ቤቱ ለይርጋው ዘመን አቆጣጠር ማቋረጫ አድርጎ ሊወስድለት አይችልም የይርጋ መብትን ስለመተው እንደሚታወቀው በአዋጅ ቁ ውስጥ የተመለከተው የይርጋ ሕግ በፍሬ ነገር ሕግ ሀከበከ ዉ ላይ እንጂ በሥነ ሥርዓት ሕግ ዞርርህ ጩዉለ ላይ የተቀመጠ የይርጋ ደንብ አይደለም በፍሬ ነገር ሕግ ህበክፀ ዉነ ላይ የሚገኝ የይርጋ ደንብ ደግሞ በተከሣሹ ወገን በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሊቀርብ የሚገባው ነው ተከሣሹ በመቃወሚያነት አንስቶ ከአልተከራከረበት በቀር ፍርድ ቤት በእራሱ አነሳሽነት ጉዳዩ የይርጋ ጊዜ ያለፈበት መሆን አለመሆኑን አጣርቶ እና ሕጉን ጠቅሶ ፍርድ ሊሰጥበት አይችልም ስለሆነም አንድ የሥራ ክርክር ክስ የተመሰረተበት ተከሣሽ የይርጋውን ክርክር በመቀወሚያነት ካላነሳው በአዋጅ ቁ አንቀጽ አግባብ በዚህ ረገድ የመከራከር መብቱን አንደተወው ይቀቆቀጠራል በውጤቱም በሕግ የተወሰነለትን ጊዜ አሳልፎ የቀረበው ክስ በይርጋ ምክንያት ውድቅ ሳይደረግ ወደ ጉዳዩ ፍሬ ነገር ተገብቶ የመዳኘት አድልን ያገኛል ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት አንድ የሥራ ክርክርን የሚመለከት ክስ የይርጋ ጊዜውን አሳልፎ ቢቀርብ እና ይህ የሆነው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ በውሣኔ ሰጭው አካል ቢረጋገጥ ምንም እንኳን ክሱ ጊዜው ያለፈበት ቢሆንም ሊታይ አንደሚገባ በአዋጅ ቁ አንቀጽ ላይ ተደንግጓል የተጠቀሰው ምክንያት በተወገደ በአስር ቀን ውስጥ ያልቀረበ ክስ ግን ተቀባይነት እንደማያገኝ በዚሁ ድንጋጌ ላይ ተመልክቷል በግልጽ እንደሚታየው ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ማለት ምን ማለት እንደሆነ ከፍ ሲል በተጠቀሰው ድንጋጌ አልተተረጎመም ስለዚህም ጉዳዩን ይህን ሐሳብ ከሚተረጉመው የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ ጋር አገናዝቦ መመልከት ያስፈልጋል በዚህ የፍብሕቁ እንደተደነገገው ከዓቅም በላይ የሆነ ሊመልሱት የማይቻል ኃይል ደርሷል የሚባለው አንድ ባለዕዳ ባላሰበው ነገር ድንገት ደራሽ ሆኖበት ግዴታውን እንዳይፈጽም ፍጹም መሰናክል በሆነ ዓይነት የሚያግደው ነገር ባጋጠመው ጊዜ ነው ጉዳዩ ከዚህ ትርጉም አኳያ ሲታይ አንድን የሥራ ክርክር ክስ ጊዜው ሊያልፍበት የቻለው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ነው በሚል ለመፈረጅ ክሱ ቀድሞ ሊታሰብ በማይችል እና ከሣሹም ፍጽም የሆነ መሰናክል የገጠመው በመሆኑ ምክንያት ብቻ በጊዜው ሳይመሰረት መቅረቱ ሲረጋገጥ ነው ይሁን እንጅ ይህ ትርጓሜ እነዚህ ምክንያቶች ምን አይነት ምክንያቶችን ይመለከታል። የሚለውን ጥያቄ ማስነሳቱ አይቀሬ ይሆናል የአዋጅ ቁ አንቀጽ ከአቅም በላይ ሊሰኙ የሚችሉ ምክንያቶችን ያላመላከተን በመሆኑም ለዚህ ጉዳይ እንደገና ወደ ፍትሐብሔር ሕጉ ድንጋጌዎች መመለስ ያስፈልገናል የፍትሐብሔር ሕጉ በቁጥር ላይ ከአቅም በላይ ሊሰኙ የሚችሉ ምክንያቶችን በመዘርዘር አስቀምጧል እነርሱም ሀ ባለዕዳው አላፊ የማይሆንበት ያልታሰቡና በሌላ ሰው ላይ የሚመጡ ድንገት ደራሽ ነገሮች ለ ውሉ አንዳይፈጸም በመንግሥት የሚደረግ ክልከላ ሐ እንደ መሬት መናወጽ መብረቅ ማዕበል ይህን የመሳሰለ ፍጥረታዊ መቅሠፍት መ የጠላት የውጭ አገር ጦርነትና የአገር ውስጥ ጦርነት ሠ የባለዕዳው መሞት ወይም ባልታሰበ ሁኔታ የሜደርስበት ከባድ አደጋ ወይም ጽኑ ሕመም መሆናቸው ተመልክቷል እንግዲህ ከሣሽ ክሱን በጊዜው ያልመሰረተበት ምክንያት ከፍ ሲል በተጠቀሰው ድንጋጌ በተመከቱት ምክንያቶች ስር የሚሸፈን ከሆነ ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ገጥሞታል የ ሆናል ዳኝነት ሰጭው አካልም ይህንን ከአረጋገጠ ጊዜው ያለፈበትን ክስ ተቀብሎ ወደ ፍሬ ጉዳዩ በ ፍርድ ይሰጥበት ዘንድ ይገደዳል ከላይ እንደተገለፀው የአዋጅ ቁ አንቀጽ ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ማለት ምን ማለት አንደሆነ አልተረጎመም እነዚህ ምክንያቶች ምን አይነት ሊሆኑ እንደሚገባም አላመለከተም ነገር ግን በይርጋ የታገደን ክስ ለመቀበል በቂ ምክንያት ተደርገው የሚወሰዱ ምክንያቶችን አመላክቷል እነዚህም የሚከተሉት ናቸው ሀ የሠራተኛ መታመም ለ የሠራተኛው በትዕዛዝ ከመደበኛ የመኖሪያ ሥፍራ ውጭ መዛወር ጠ የሠራተኛው ከብሔራዊ ጥሪ ላይ መገኘት እነዚህ በድንጋጌው የተመለከቱት ውስን ምክንያቶች በሠራተኛው የቀረበው ክስ በይርጋ የታገደ መሆኑ ቢታይም ተቀባይነት ያገኝለት ዘንድ የሚፈቅዱ ናቸው እንዲሁም እነዚህ እክሎች የገጠሙት ሠራተኛ ጉዳይ በዳኝነት አካል ሳይታይለት እንዳይቀር ልዩ የሆነ ጥበቃ የማድረግን ነገር አላማ ማድረጋቸውን ከድንጋጌው መረዳት የሜቻል ነው በእርግጥ እነዚህ ምክንያቶች በሠራተኛው ክስ ተጠቅሰው መገኘታቸው ብቻውን ጊዜው ያለፈበትን ጉዳይ ለመቀበል የሚበቃ አይሆንም ይህን ማድረግም ከድንጋጌው አላማ ጋር የተጣጣመ መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ አይረዳንም ስለሆነም ሠራተኛው ጊዜው ያልፈበትን ክስ ቢያቀርብ እና ጉዳዩ ከዚህ ድንጋጌ አግባብ እንዲታይለት ቢጠይቅ መታመሙን ወይም በትዕዛዝ ከመኖሪያ ሥፍራው መዛወሩን ወይም በብሔራዊ ጥሪ ላይ የነበረ መሆኑን የሚያሳይለትን ማስረጃ በማቅረብ በቅድሚያ ክርክሩን ያስረዳ ዘንድ ያስፈልጋል ጉዳይ የቀረበለት ፍርድ ቤትም የምክንያቱን ተገቢነት በግራ ቀኙ ከቀረበለትም ሆነ በእራሱ አነሳሽነት ከአስመጣው ማስረጃ አኳያ ሊመረምረው ይገባል ፍርድ ቤቱ ይህን ሲያደርግም እነዚህ ምክንያቶች ሠራተኛው ክሱን እንዳይመሰርት መስናክል የሆኑበትን መጠን ጭምር ከግምት እንዲያስገባ ያስፈልጋል በውጤቱም ፍርድ ቤቱ እነዚህ ምክንያቶች ከሣሹ ክሱን ሊመሰርት በማይችልበት ደረጃ ላይ አድርሰውት ነበር ሲል የሚያምንበት ሊሆን ይገባዋል ይህ ካልሆነ ግን ፍርድ ቤቱ በይርጋ የታገደውን ክስ ከወዲሁ ውድቅ ማድረግ ይኖርበታል አሁን በዚህ መዝገብ ወደተያዘው ክርክር እንመለሳለን በዚህ ውሣኔ መግቢያ ላይ እንደተመለከተው ተጠሪዎች ለቦርድ አቅርበውት የነበረው ክስ ለሌሎች ሠራተኞች የተደረገው የሁለት አርከን ጭማሪ ለእኛም ሊሰጠን ይገባል የሚል ሲሆን አመልካችም ክሱ በይርጋ ሊታገድ ይገባዋል በማለት ተቃውሞውን አቅርቦ የተከራከረበት ነው በመሠረቱ ይህ የተጠሪዎቹ ጥያቅ የክፍያ ጥያቄን የሚመለከት ነው እንዲሁም የክፍያ ጥያቄው በመካከላቸው ያለው የሥራ ውል ፀንቶ በአለበት ጊዜ የተነሳ እንጂ የሥራ ውል መቋረጥን ተከትሎ የቀረበ አይደለም በእነዚህ ምክንያቶች የይርጋው አቆጣጠር ጉዳይ በተለይ ከተደነ አዋጅ ቁ አንቀጽ አግባብ ሊታይ የሚገባው ነው በዚህ የአዋጅ ቁ አንቀጽ መሠረት የተጠቀሰው የክፍያ ጥያቄ ሊጠየቅ ከሚገባው ጊዜ ጀምሮ እስከ ስድስት ወር ድረስ ካልተጠየቀ በይርጋ ሊታገድ የሚገባው ነው ተጠሪዎች ይህ የሁለት እርከን ጭማሪ ለሌሎች ሠራተኞች ተደርጓል የሚሉት መጋቢት ቀን ዓም እንደነበር ከስር ውሣኔ ላይ መረዳት የሚቻል ነው ክሳቸውን ለቦርድ ያቀረቡት ደግሞ ነሐሴ ቀን ዓም መሆኑ በስር ውሣኔ የተመለከተ ነው በዚህ ችሎት እምነት አመልካች ለሌሎቹ ሠራተኞች ጭማሪውን አድርጓል መባሉ በስር ክርክር በተጠሪዎች ጭምር የታመነበት መጋቢት ቀን ዓም ክፍያው በተጠሪዎች ሊጠየቅ የሚገባበት ጊዜ እንደሆነ ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው ነው የተጠሪዎቹ ክስ የቀረበው ከዚህ ጊዜ በኋላ ከአንድ ዓመት በላይ ቆይቶ በመሆኑም ከፍ ሲል በተጠቀሰው ድንጋጌ መሠረት በስድስት ወሩ ይርጋ ሊታገድ የሚገባው መሆኑ የማያከራክር ነው በአርግጥ ተጠሪዎች የእርከን ጭማሪው ለሌሎቹ ሠራተኞች የተደረገው መጋቢት ቀን ዓም አይደለም ይኸ ቀን ጭማሪ መደረጉ ለሠራተኞች ይፋ የተደረገበት ቀን ነው ይሁን እንጂ የካቲት ቀን ዓም ለሌሎቹ ሠራተኞች ተጠቃሚ መሆናቸው ሲፃፍላቸው ለተጠሪዎች ግን ይኸ ባለመደረጉ የካቲት ቀን ዓም ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቤቱታ በማቅረባችን የይርጋው አቆጣጠር ተቋርጧል በማለት በስር ፍርድ ቤቶች ያላነሱትን ክርክር ለዚህ ችሎት አቅርበዋል በመሰረቱ ይኸ የተጠሪዎቹ ክርክር በዚህ ችሎት የቀረበ አዲስ የክርክር ነጥብ በመሆኑ ዳኝነት ሊሰጥበት የሚገባ አልነበረም ይኸ ቢታለፍ ደግሞ አሁንም ተጠሪዎቹ ሌሎቹ ሠራተኞች የእርከን ጭማሪው ተጠቃሚ መሆናቸው ሲፃፍላቸው ለእኛ ይህ ሳይደረግ ቀርቷል ከሚሉበት ከየካቲት ቀን ዓም ጀምሮ በስድስት ወራት ውስጥ ማለትም እስከ ነሐሴ ቀን ዓም ክሱን ሊመሰርቱ ሲገባ ይህን አድርገው ባለመገኘታቸው ይህም ክርክራቸው የይርጋውን ጊዜ ማለፍ የሚያረጋግጥባቸው ነው እንዲሁም ይህ ችሎት ለአዋጅ ቁ አንቀጽ ከሰጠው ትርጓሜ አግባብ የአመልካች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቤቱታ ማቅረብ አዋጁን እንዲያስፈጽም ስልጣን ለተሰጠው አካል አቤቱታ እንደማቅረብ ስለማይቆጠር ይኸ ተጠሪዎቹ ፈጽመነዋል ያሉት ድርጊትም የይርጋውን ጊዜ አቆጣጠር የሚያቋርጠው ሆኖ አልተገኘም ውሣኔ ኛ ተጠሪዎች በአመልካቹ ላይ የመሰረቱት ክስ በአዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት በይርጋ ሊታገድ ይገባል ኛ የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቦርድ እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደቅደም ተከተላቸው በመቁ እና በመቁ የአመልካችን የይርጋ ክርክር ውድቅ አድርገው የአንድ እርከን ጭማሪ ለተጠሪዎች እንዲከፍል የሰጡት ውሣኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽራል የሰበር መቁ ሕዳር ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ ዓለሙ ወሮ ሆሳዕና ነጋሽ አቶ አሰግድ ጋሻው አመልካች የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኔኬሽን ተጠሪ ወሪት ትዕግስት ወርቁ ያሥራ ውል ዕቋሟይዕታፖ ሓቋሳሦወፅሪሪ ሄ ያሟደረፇ ይጎራ ውል ሕና ፖወፅ ዖሟደረኘ ይዕራ ውጳ ዕቋ ዕራ ውሰ መቋረዎ ለና ውቓፍ ሪ ኗዖ ዕፖሥመጋለፖ ያጎዎጅ ቋፖረ ሪጽ ፇጵ ናሪ ተጠሪ ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአሁን ተጠሪ ወደ ስራ እንድትመለስ እና የአንድ አመት ደመወዝ እና የዓመት ፈቃድ እንዲሰጣት በማለት ስለወሰኑ የቀረበ አቤቱታ ሙሳ ነ የአመት ፈቃድን በተመለከተ ሳይጨምር በቀሪቹ ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጡት ውሳኔች ተሽረዋል ኛ በአንድ አሠሪ እና ሠራተኛ መካከል የተደረገ የስራ ውል ያልተወሰነ ጊዜ የተደረገ የስራ ውል ተደርጎ ሊቆጠር ይገባል እንዲሁም ማናቸውም የስራ ውል ጊዜ እንዲልተወሰነለት የስራ ውል ሊወሰድ ይገባል ኛ ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ሥራ የተደረገ አንድ የሥራ ውል ውሉ መስፈርቶችን በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ያሟላ ከሆነ ሊቆይ የሚችለው ጊዜው እስከሚያልቅ ወይም ስራው አስከሚያልቅ ድረስ ነው የሰበር መቁ ሕዳር ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍስሐ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ ዓለሙ ወሮ ሆሳዕና ነጋሽ አቶ አሰግድ ጋሻው አመልካች የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኔኬሽን ግርማ ማርቆስ ቀረበ ተጠሪ ወሪት ትዕግስት ወርቁ ቀረበች ፍርድ ለዚህ ጉዳይ መነሻ የሆነው የአሁን ተጠሪ እኤአ ከመጋቢት ዓም ጀምሮ እስከ መስከረም ዓም ድረስ በጠቅላላ አገልግሎት ውስጥ በሚገኝ የስራ መደብ በተላላኪነት ሳገለግል ቆይቼ አለአግባብ የስራ ውሌን ስላቋረጠው ጥቅሜን ከፍሎ ወደ ስራ ይመልሰኝ አሊያም የስራ ስንብት ከፍሉ ያሰናብተኝ ስትል በአሁን አመልካች ላይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጀ ፍቤት የመሰረተችው ክስ ነው ይህም ፍቤት ግራ ቀኙን በጉዳዩ አከራክሮ ተጠሪ ወደ ስራ እንድትመለስ የአንድ ዓመት ደመወዝ አና የዓመት ፈቃድ እንዲሰጣት ወስኗል ይግባኝ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ፍርዱ ጉድለት ያለበትም በማለት የይግባኙን መዝገብ ዘግቶታል ይህም ችሎት ግራ ቀኙ በጉዳዩ ያቀረቡለትን ክርክር መርምሯል በአመልካችና በመልስ ሰጭ መካከል የተደረገው የስራ ውል ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የተደረገ ነው። የሚለው ጭብጥ በጉዳዩ ምላሽ ማግኘት የሚገባው ነጥብ መሆኑን ተገንዝቧል ጭብጡን አሳማኝ በሆነ መልኩ ለመፍታት ይቻል ዘንድም በቅድሚያ የሥራ ውል ስለሚቆይበት ጊዜ የሚደነግጉትን የአዋጅ ቁ አንቀጽ እና ን በመመስረት ነጥቡን መመርመር ያስፈልጋል በመጀመሪያ አንቀጽ ን እንመልከት ይህ አንቀጽ በአንቀጽ ከተመለከቱት በቀር ማንኛውም የሥራ ውል ላልተወሰነ ጊዜ እንደተደረገ ይቆጠራል በማለት ደንግጓል ይህ ድንጋጌ የስራ ውል ቆይታን የሚመለከት አንድ መሰረት አስቀምጧል ይኸውም በአንድ አሰሪ እና ሰራተኛ መካከል የተደረገ የስራ ውል ያልተወሰነ ጊዜ የስራ ውል ተደርጎ ሊቆጠር እንደሚገባ አመልክቷል እንዲሁም ማናቸውም የስራ ውል ጊዜ አእንደአልተወሰነለት የስራ ውል ሊወሰድ ይገባው ዘንድ ሕጉ ግምት የወሰደበት መሆኑን ያረጋግጣል እንደ አንቀጽ አገላለጽ አንድ የስራ ውል ላልተወሰነ ጊዜ እንደተደረገ የሚያስቆጥረውን የሕግ ግምት ቀሪ አድርጎ ውሉን ለተወሰነ ጊዜ ወይም ስራ የተደረገ ነው የሚል ለመፈረጅ የስራ ውሉ ከአዋጅ አንቀጽ አኳያ የተደረገ መሆኑ እንዲረጋገጥ ያስፈልጋል ወደ ተከታዩ የአዋጅ ቁ አንቀጽ ስንመለስ ይህ አንቀጽ ለተወሰነ ስራ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የስራ ውል ሊደረግባቸው የሚችልባቸውን ሁኔታዎች በመዘርዘር አስቀምጧል ይህም በድንጋጌው የተወለከቱት መስፈርቶች የመማላታቸው ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ አንድን የስራ ውል ለተወሰነ ጊዜ ብቻ እንዲቆይ በማድረግ አሊያም የተወሰነ ስራ ለመስራትም ሆነ ለማሰራት ብቻ ሲባል ማድረግ በሕግ የተፈቀደ መሆኑን ያረጋግጣል እንደዚሁም ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የስራ ውል የሚደረገው በአንቀጹ በተመለከቱት ሁኔታዎች ብቻ መሆኑን በመጠቆም አንድን የስራ ውል ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ በሚል ማድረግ እንደ ልዩ ሁኔታ ሊቆጠር የሚገባው ተግባር መሆኑን ያመላክታል ይህ የሕጉ መንፈስም በዚህ ድንጋጌ በአንቀጽ ሊሸፈኑ የማይችሉ የስራ ውል አይነቶች ሁሉ በአሰሪውና በሰራተኛው መካከል ላልተወሰነ ጊዜ እንደተደረጉ ይቆጠራሉ በሚል በተደነገገው የአዋጁ አንቀጽ ይደግፋል እንግዲህ አንድ የሰራ ውል የተደረገው ለተወሰነ ጊዜ ወይም ስራ በመሆን አለመሆኑ ጉዳይ ላይ ሙግት ሲነሳ በቅድሚያ በአሰሪው እና በሰራተኛው መካከል በጽሑፍም ሆነ በቃል የተደረገውን የስራ ውል ይዘት ሰፊ ዝርዝር ከያዘው የአዋጁ አንቀጽ ጋር እያገናዘቡ መመርመር ያስፈልጋል ከዚያም አንድ አሳማኝነት ያለው መደምደሚያ ላይ ለመድረስ ሕጉ እንደዚህ ያሉ የስራ ውሎች እንዲደረጉ የፈቀደባቸውን የስራ ሁኔታዎች መለየት ተገቢነት ይኖረዋል እንዲሆም የስራ ውሉ ከተጠቀሰው ድንጋጌ አግባብ የተደረገ መሆኑን የማስረዳት ሸክሙ የአሰሪው ነው። የሚለው አከራካሪ ጭብጥ በአንድ ጉዳይ ሊመሰረት የሚችለው አንዱ ወገን ተከራካሪ የስራ ውሉ ያልተወሰነ ጊዜ የስራ ውል ነው ሲል ሌላው ደግሞ ውሉ ለተወሰነ ጊዜ ወይም ስራ የተደረገ ነው በማለት በሚሟገቱበት ሁኔታ ነው በአብዛኛ የመጀመሪያው አይነት ክርክር የሚቀርበው በሰራተኛው ሲሆን ሁለተኛው አይነት ክርክር ደግሞ በአሰሪው የሚቀርብ ነው ይህም የሙግታቸው አቀራረብ ለተጠቀሰው ጭብጥ መመስረት ምክንያት የሆነው ክርክር በአሰሪው በኩል መቅረቡን የሚያረጋግጥ ነው የጉዳዩ ጭብጥ እንዲሆን ያስቻለውን ክርክር ያቀረበው አሰሪው ከሆነ ደግሞ ይህን ክርክሩን በቅድሚያ ያስረዳ ዘንድ የግድ ይሆንበታል ይህም ከ በ ነከ በ ካ ቨዘበብከህ ከ ፀዐህፀ ቪ ከሚለው አገላለጽ ጋር የተስማማ ይሆናል እንደዚሁም ይህን ጉዳይ ስለ ማስረጃ ማቅረብ ግዴታ እና ስለአቀባበሉ ከተደነገገበት የፍትሐ ብሔር ሕጉ ክፍል ጋር ማገናዘብ ይቻላል በዚህ የፍትሐ ብሔር ሕግ ክፍል ስር የሚገኘው አንቀጽ ዐዐ አንድ ግዴታ እንዲፈፀምለት የሚጠይቅ ሰው የግዴታውን መኖር የሚያሳይለት ማስረጃ ማቅረብ አንደሚገባው ግዴታው ፈርሷል ወይም ተቀይራል ወይም ቀርቋል የሚል ወገን ደግሞ ይህ ተግባር መፈፀሙን የሚያሳይለትን ማስረጃ ማቅረብ እንዳለበት ደንግጓል በያዝነው አይነት የስራ ክርክር ጉዳይ የገባውን ግዴታ ሊፈጽምልኝ ይገባል የሚል ክርክር የሚቀርበው በአሰሪው ሳይሆን በሰራተኛው ነው ስለሆነም ከተጠቀሰው ድነጋጌ አግባብ ሰራተኛው የግዴታውን መኖር ለማስረዳት በመካከላቸው የስራ ውል ያለ መሆኑን ብቻ ማሳየቱ የሚበቃው ነው በሌላ በኩል ግን የስራ ውሉ በአዋጅ ቁ አንቀጽ የሚሸፈን ነው በሚል የሚከራከረው አሰሪ ይህን የስራ ውሉ በተጠቀሰው ድንጋጌ ስር የሚወድቅ መሆኑን ያረጋግጥልኛል የሚለውን ተግባር ያስረዳ ዘንድ ይጠበቅበታል እንግዲህ አንድ የስራ ውሉ በአንቀጽ የሚሸፈን ነው ሲል አሰሪው በተከራከረ ጊዜ ሁሉ ይህንን ክርክሩን የሚደግፍለት የጽሁፍም ሆነ የሰው ማስረጃ በቅድሚያ እንዲያቀርብ ያስፈልጋል በአሰሪው የቀረበው ማስረጃ ከተመዘነ በኋላ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ደግሞ ሰራተኛው ቅጥሩ በአሰሪው እንደተባለው ሳይሆን በሌላ በአንቀጽ ሊሸፈን በማይችል የተለየ ሁኔታ መፈፀሙን በማስረዳት በአሰሪው የቀረበውን ክርክርና ማስረጃ ያስተባብል ዘንድ ይገባዋል እንዲሁም አንድ ፍቤት የተከራካሪዎች የጽሁፍም ሆነ የቃል የስራ ውል ከአንቀጽ አግባብ መደረግ አለመደረጉን ሲፈትሽ አለነ የሚሉትን ማስረጃ ከፍ ሲል በተመለከተው ስርዓት ሊያስተናግድ ይገባዋል እርሱም ይጠቅመኛል የሚለውን ሌላ ተመሳሳይ አይነት ወይም አግባብነት ያለው የአካባቢ ማስረጃ ለውሳኔው መሰረት ሊያደርግ ይችላል በሌላም በኩል አንድ የስራ ውል ለተወሰነ ጊዜ ወይም ስራ የተደረገ መ መሆኑን የማጣራቱ ጉዳይ በአሰሪው እና በሰራተኛው መካከል የተደረገውን የስራ ውል የመተርጎምን ተ ሠምራል አከራካሪ ሆኖ የተገኘውን የስራ ውል ለመተርጎም ደግሞ ተዋዋዮቹ ውሉን ሲያደርጉ የነበራቸውን ፈቃድ መለየት ያስፈልጋል ስለሆነም ፍርድ ቤቱ በዚህ ረገድ የያዘውን ጭብጥ ሲፈታ የስራ ውሉ በተደረገበት ጊዜ አሰሪውና ሰራተኛው የነበራቸው የሐሳብ አንድነት ምን እንደነበር ሊያረጋግጥ ይገባል ፍቤቱ በአደረገው ማጣራት የስራ ውሉ የተደረገበት የተዋዋዮቹ ፈቃድ ውሉ በአዋጅ ቁ አንቀጽ በተመለከቱት ሁፄታዎች ላይ መፈጸሙን አረጋግጦልኛል የሚል ከሆነ ውሉ ለተወሰነ ጊዜ ወይም ስራ የተደረገ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ ይደርሳል የስራ ውሉ የተደረገበት የተዋዋዮቹ ፈቃድ በተጠቀሰው አንቀጽ ስር የሚወድቅ አይደለም ካለ ደግሞ ውሉን ላልተወሰነ ጊዜ እንደተደረገ የስራ ውል ይቆጥረዋል ወደያዘነው ጉዳይ ስንመለስ ክሱ የቀረበለት ፍቤት ተጠሪ ለተወሰነ ጊዜ ማለትም ለስድስት ወራት መቀጠራን የሚያሳይ የፅሁፍ የስራ ውል በማስረጃነት ቀርቦለታል ቅጥሩም ወቅታዊ ስራን ለማከናወን በሚል መፈፀሙን ውሉ በግልጽ ያመለክታል ከፍ ሲል እንደተጠቀሰው ውሉ ጊዜ የተወሰነለት መሆኑ ብቻውን የተወሰነ ጊዜ የስራ ውል የሚያሰኘው አይሆንም ስለሆነም ውሉ በአዋጅ አንቀጽ አግባብ የተደረገ መሆን አለመሆኑ ጭምር መታየት ይኖርበታል ሁለቱ ወገኖች የፈፀሙት ውል ተጠሪ የተቀጠረችው ወቅታዊ ስራን ለማከናወን መሆኑን የሚጠቅስ ሲሆን አመልካቹ ደግሞ ተጠሪ የተቀጠረችው በንድ ወቅት ተከስቶ የነበረን የስራ ብዛት ለማቃለል ነው ሲል ከስር ጀምሮ መከራከሩን መዝገቡ ያስረዳል ይህም የአመልካቹ ክርክር ምንም እንኳን ውሉ የቅጥሩ ምክንያት ወቅታዊ ስራን ለመስራት የተደረገ መሆኑን የሚያመላክት ቢሆንም ተጠሪ የተቀጠረችበት የጠቅላላ አገልገሎት ክፍል የተላላኪነት ስራ ወቅት ጠብቆ የሚሰራ ቋሚ የአሰሪው ስራ በሚል ሊፈረጅ እንደማይችል በአመልካቹ ጭምር የታመነበት መሆኑን ያረጋግጣል እንዲሁም የክርክሩ አቀራረብ ጉዳዩን ከንዑስ አንቀጽ ጋር ሳይሆን ከንዑስ ጋር አገናዝበን እንድናየው እና አመልካቹም በዚህ ረገድ ያቀረበውን ክርክር ማስረዳት አለማስረዳቱን እንድንለይ ይጠይቀናል ከጉዳዩ መረዳት እንደሚቻለው ተጠሪ የተቀጠረችው በቀጣይነት በሚከናወን የአሰሪው ቋሚ ስራ ላይ ነው ተጠሪም ብትሆን የምትከራከረው ስራው ወቅት ጠብቆ የሚሰራ ነው በሚል ሳይሆን ያለማቋረጥ የሚሰራ የስራ አይነት ነው በሜል ነው በቀጣይነት የሚሰራ የአሰሪ ቋሚ ስራ ላይ የስራ ብዛትን ለማቃለል በሚል የተወሰነ ጊዜ የስራ ውል ማድረግ በንዑስ ቁ የተፈቀደ ነው በእርግጥ የቀረበው የስራ ውል አመልካቹ እንደሚከራከረው ውሉ የተደረገው በአንድ ወቅት የተከሰተን የስራ ብዛት ለማቃለል መሆኑን በግልፅ የሚጠቅስ አይደለም ይህ ማለት ግን ውሉ የአመልካቹን ክርክር አያስረዳለትም በሚል ከወዲሁ እንድንደመድም የሚያስችለን አይደለም ይልቁንም በውሉ ላይ የተወለከተው የቅጥሩ ምክንያት ከዚህ ንዑስ አንቀፅ ጋር የሚጣጣም መሆን አለመሆኑን የማየቱን ጉዳይ አስፈላጊ የሚያደርገው ነው ተጠሪ የተቀጠረችበት የተላላኪነት ስራ የወቅት ስራ አይደለምና በዚህ ችሎት እምነት በውሉ ላይ ወቅታዊ ስራን ለማከናወን መቀጠሯ መገለፁ በጊዜው የነበረውን የሥራ ብዛት ለማቃለል ሲባል መቀጠራን ለማረጋገጥ ያህል የሚሜበቃ ነው ስለሆነም አመልካቹ ላቀረበው ክርክር ውሉ እንደ በቂ የፅሁፍ ማስረጃ ሊቆጠርለት የሚገባ ነው በሌላ በኩል ተጠሪ በቦታው ሌላ ቀጥሮ እኔን አለአግባብ አሰናበተኝ የሚል አጠቃላይ ይዘት ያለው ክርክር ከማቅረቧ ውጭ ስራ ለማቃለል ቀጠርኳት ማለቱ ሐሰት መሆኑን አስረዳለሁ በሚል አይነት አልተከራከረችም በዚህ አይነት ከልሟገች እና ሙግቷንም ካላስረዳች ደግሞ የአመልካቹን ክርክር አስተባብላለች የሚያስብላት አይደለም ተጠሪ እንደምትከራከረው በቦታው ሌላ መቀጠሩን በስር ፍቤት በቆጠረቻቸው ምስክሮች እንደአስረዳች ቢወስድላት እንኳ የተቀጠረችው የስራ ብዛት ለማቃለል አለመሆኑን በማስረዳት የአመልካቹን ክርክር አስተባብላለች የሚያሰኛት አይሆንም ምክንያቱም በእርሷ ቦታ ሌላ የመቀጠሩ ጉዳይ እርሷ የተቀጠረችው ስራ ለማቃለል ሲባል አይደለም የሚል አሳማኝነት ያለው መደምደሚያ ላይ ሊያደርስ የሚችል አይደለም በጥቅሉም በሁለቱ መካከል የተደረገው የስራ ውል በአዋጅ ቁ አንቀጽ የሚሸፈን የተወሰነ ጊዜ የስራ ውል መሆኑን ይህ ችሎት ተቀብሉሎታል በውሉ የተወሰነ ጊዜ ሲያልቅ ውሉ መቋረጡም በአዋጁ አንቀጽ የተደገፈ ነውና የስር ፍቤቶች የውሉን መቋረጥ ሕገወጥ አድርገው ወደስራ እንድትመለስ መወሰናቸው ከሕጉ ያልተጣጣመ ሆኖ አግኝተነዋል ውሣኔ ኛ በአመልካችና በተጠሪ መካከል የተደረገው የስራ ውል የተቋረጠበት ምክንያት ሕጋዊ እንጂ ሕገ ወጥ ባለመሆኑ አመልካች ወደ ስራ ልትመለስ አይገባም በማለት ተወስኗል ኛ ይህ ችሎት በመቁ ለጉዳዩ አግባብነት ላላቸው የአዋጅ ቁ ድንጋጌዎች ትርጓሜ በመስጠት ሕጉ ስራ ላልተሰራበት ጊዜ ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈል የሚፈቅድ አይደለም የሚል መደምደሚያ ላይ በመድረሱ ተጠሪ ያልሰራችበት ጊዜ ደመወዝ ሊከፈላት አይገባም በማለት ተወስኗል ኛ በመሆኑም ተጠሪ የአመት ፈቃድ እንዲሰጣት የተወሰነውን የስር ፍቤቶች ውሳኔ ሳይጨምር ቀሪዎቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ደግሞ በመቁ የተሰጡት የውሳኔ ክፍሎች በፍብሕሥሥ ቁ መሰረት ተሽረዋል የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍሰሀ ወርቅነህ ወሮ ስንዱ አለሙ ወሮ ሆሳዕና ነጋሽ አቶ አሰግድ ጋሻው አመልካች የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ተጠሪ አቶ ጌታሁን ኃይሉ ፅዕራ ረረ ዖፍዓመፖ ኋረፍፖ ረዖ ይሳምዎሯጅ ቋረ « አሉፇጽ ዳና ፖ የአሁን ተጠሪ በአመልካች ላይ ክስ መስርተው የ ቀናት የዓመት አረፍት በገንዘብ ተለውጦ እንዲሰጣቸው የጠየቁበመጀመሪያ ያየው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም የተላለፈ የዓመት እረፍት ፈቃድ ከሁለት አመት በላይ መራዘም ስለሌለበት የእረፍት ቀናት ተቀንሶ አዋጁ በሥራ ላይ ከዋለበት ጀምሮ ተጠሪ እስከተሰናበቱበት ድረስ የአንድ አመት ከአሥራ ሦስት ቀናት የዓመት እረፍት ክፍያ ብቻ ይከፈል በማለት ሊወሰን ጉዳዩን በይግባኝ ያየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ደግሞ የተጠሪ ገንዘብ የጠየቀው የአመት አረፍት ሳይቀነስ ሊከፈል ይገባል በማለት በመወሰኑ የቀረበ አቤቱታ ውሣኔ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠውና የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያሻሻለው ውሣኔ ተሻሽሏል ከሁለት አመት በላይ የተራዘሙ ፈቃዶች በገንዘብ የሚተኩ አይደሉም አንድ ሠራተኛ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ያልተጠቀመበት የዓመት ፈቃድ ክፍያ ሁሉ የጊዜ ገደብ ሳይኖረው በገንዘብ ተቀይሮ ሊከፈለው አይችልም የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞች መንበረፀሐይ ታደሰ ፍሰሀ ወርቅነህ ስንዱ አለሙ ሆሳዕና ነጋሽ አሰግድ ጋሻው አመልካች የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ነፈጅ ኃይሉ ተሰማ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ጌታሁን ኃይሉ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ አመልካች ለሰበር ችሎት አቤቱታ ያቀረበው የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመዝቁ ህዳር ቀን ዓም የዓመት ዕረፍት ክፍያን በተመለከተ በሰጠው ውሣኔ ቅር በመሰኘት ነው ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ነው የአሁኑ ተጠሪ በአመልካች ላይ ክስ የመሰረተው ከሌሎች ክፍያዎች ጋር የተጠራቀመ የ ቀናት የዓመት ዕረፍት በገንዘብ ተለውጦ እንዲከፈለው ነው አመልካች የዓመት ዕረፍት ክፍያን አስመልክቶ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ እና መሠረት የተላለፈው የዓመት ፈቃድ የሚቀጥለው ሁለት ዓመት በላይ ሊራዘም አይችልም ተጠሪ የጠየቀው ክፍያ በሕጉ ከተሰጠው በላይ ስለሆነ ሊከፈለው አይገባም በማለት መከራከሩን የፍቤቱ ውሣኔ ያሳያል ጉዳዩን በመጀመሪያ ያየው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የሰጠው ውሣኔ የአሰሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ሥ አዋጅ ቁጥር የሆነውን በግልጽ የሻረው በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ አዋጅ ቁጥር ተፈፃሚ ሊሆን አይችልም የሚለው የተከሣሽ ክርክር ተቀባይነት የለውም ስለሆነም በአዋጅ ቁ በአንቀጽ ሥር በአንቀጽ እና የተላለፈ የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ከሁለት ዓመት በላይ መራዘም እንደሌለበት የተደነገገ በመሆኑ በዚህ ድንጋጌ መሠረት የከሣሽ የእረፍት ቀናት ተቀንሶ አዋጁ በስራ ላይ ከዋለበት ከጥር ጀምሮ እስከተሰናበቱበት ጊዜ እስከ ጥር ዓም ያለው ጊዜ አንድ ዓመት ከአስራ ሶስት ቀናት የአመት ዕረፍት ክፍያ ብቻ በአንቀጽ መሠረት እንዲከፈል የሚል ነው የአሁን ተጠሪ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት አቅርቧል ፍቤቱም አዋጅ ቁጥር አንቀጽ የዓመት ዕረፍት ከሁለት ዓመት በላይ ሊተላለፍ አይችልም ሲል ሠራተኛው ከሁለት ዓመት በላይ ያጠራቀመው የዓመት ዕረፍት ካለ አይገባውም ማለቱ አይደለም በአዋጁ በቁጥር ላይ ያልወሰደው የዓመት ፈቃድ በጠቅላላ ታስቦ እንዲከፈለው ተደንግጓል በመ ዮሦጠሪ የጠየቀው የዓመት ዕረፍት ክፍያ ሳይቀነስ እንዲከፈለው በማለት የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ውሣኔውን በመሻሻል ወስኗል አመልካች የከፍተኛ ፍቤት መሠረታዊ የሆነ ሕግ ስህተት ፈጽሟል ሲል አቤቱታ ያቀረበው በዚህ ውሣኔ ነው ታህሣሥ ቀን ዓም ጽፎ ባቀረበው ማመልከቻ በውሣኔው መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ተሰርቷል ሲል የሚያቀርባቸው ክርክሮችም የተጠሪ የዓመት ዕረፍት በገንዘብ ተቀይሮ ይከፈለኝ ጥያቄ ከሥራ ከመሰናበታቸው ጥር ዓም በፊት የነበረና በተለይም አዋጅ በአንቀጽ ከሀሠ መሠረት ያልተላለፈ በመሆኑ ሊጠየቅ አይገባም በአዋጅ አንቀጽ መሠረት ሠራተኛው ጠይቆ ወይም አሠሪው የሥራ ሁኔታ አስገድዶት የተላለፈ ለመሆኑ የቀረበ ማስረጃ የሌለ ከመሆኑም በላይ በዚሁ አንቀጽ በግልጽ እንደተቀመጠው በሁለቱ ስምምነት የተላለፈ የዓመት ዕረፍት ቢኖር እንኳን ከሁለት አመት በላይ ሊራዘም እንደማይችል በግልጽ ሰፍሯል ተጠሪ በአዋጁ መሰረት የተላለፈ የዓመት ዕረፍት ያላቸው ለመሆኑ ያልገለጹ ከመሆኑም በላይ አንቀጽ ከሁለት አመት በላይ ሊተላለፍ እንደማይችል በግልጽ የደነገገውን ከፍተኛ ፍቤት ባለመቀበል በአዋጅ አንቀጽ በሙሉ በገንዘብ ተቀይሮ ይከፈላቸው በማለት የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት አለበት የሚሉ ናቸው አቤቱታው በሰበር ችሎት አንዲታይ ታዞ ተጠሪ መልስ አንዲሰጥ በታዘዘው መሠረት ሚያዚያ ቀን ዓም የተጻፈ መልስ አቅርቧል በመልሱም የከፍተኛ ፍቤት ውሣኔ የህግ ስህተት እንደሌለበት በመግለጽ እንዲፀና ጠይቋል አመልካቹም የመልስ መልስ አቅርቧል በዚህ ጉዳይ ተመርምሮ ሊወሰን የሚገባው ዋናው የክርክር ጭብጥ አንድ ሠራተኛ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ያልተጠቀመበትን የዓመት ዕረፍት ቀናት ሁሉ የጊዜ ገደብ ሳይኖረው በገንዘብ ተለውጦ እንዲከፈለው ይገባል ወይ።